13 hours ago
✴️ የ47ኛው ዙር አድማስ ዲጂታል ሎተሪ አሸናፊዎች ታወቁ!
ዕድለኞች እንኳን ደስ አላችሁ 🎉🎉
💁♂️ 48ኛው ዙር ቀጥሏል፤ በቴሌብር ወይም ወደ 605 A ብለው በመላክ በ10 ብር ዕድልዎን ይሞክሩ!
🍀 ዕድል ከእርስዎ ጋር ትሁን!
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት እና ኢትዮ ቴሌኮም በአጋርነት
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ዕድለኞች እንኳን ደስ አላችሁ 🎉🎉
💁♂️ 48ኛው ዙር ቀጥሏል፤ በቴሌብር ወይም ወደ 605 A ብለው በመላክ በ10 ብር ዕድልዎን ይሞክሩ!
🍀 ዕድል ከእርስዎ ጋር ትሁን!
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት እና ኢትዮ ቴሌኮም በአጋርነት
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
14 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አሜሪካ ከሶማሊላንድ ጋር ያላትን ግንኙነት በይፋዊ የዲፕሎማሲ እውቅና ላይ ሳይሆን በተግባራዊ የኢኮኖሚና የደህንነት አጋርነት ላይ መሠረት በማድረግ እያሳደገች መምጣቷን አንድ አዲስ የጥናት ሰነድ አጋለጠ። ተመራማሪ ሳሚያ መሐመድ ባቀረቡት በዚህ ትንተና አሜሪካ የሶማሊያን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት በይፋዊ መግለጫዎቿ ብታስከብርም፤ በተግባር ግን የሶማሊላንድን አስተማማኝ የደህንነትና የኢኮኖሚ አጋርነት በመገንዘብ ግንኙነቷን ደረጃ በደረጃ እያሻሻለች ይገኛል።
ይህ የፖሊሲ ለውጥ ድንገተኛ ወይም አብዮታዊ ሳይሆን የሶማሊላንድን መረጋጋት፣ የአስተዳደር አቅምና ስትራቴጂካዊ መልክዓ ምድር ግምት ውስጥ ያስገባ ቀስ በቀስ የሚደረግ የፖሊሲ ማስተካከያ መሆኑ ተጠቅሷል። በተለይም የበርበራ ወደብ በአካባቢው ካሉ መጨናነቅ የሚታይባቸው ወደቦች እንደ አማራጭ ሆኖ ማገልገል መቻሉ እና ለንግድና ትራንስፖርት ያለው ከፍተኛ ጠቀሜታ በአሜሪካ መንግሥት በኩል አዎንታዊ እይታን አትርፎለታል። ሆኖም ይህ አካሄድ በሞቃዲሾ ከሚገኘው የሶማሊያ ፌዴራላዊ መንግሥት ጋር ውጥረት ላለመፍጠር ሲባል፣ ሙሉ የዲፕሎማሲ እውቅና ከመስጠት ይልቅ በጥንቃቄ የተመጠነ የመካከለኛ መንገድ ስትራቴጂን የሚከተል ነው።
ጥናቱ እንደሚያብራራው በዘመናዊው የዓለም አቀፍ ግንኙነት አገራት አጋሮቻቸውን የሚመዝኑት በይፋዊ የዲፕሎማሲ ማዕረጋቸው ብቻ ሳይሆን፣ በተግባራዊ ብቃታቸው፣ አስተማማኝነታቸውና አገልግሎት ሰጪነታቸው ነው። በዚህ ረገድ ሶማሊላንድ መረጋጋትን በማስፈን፣ የጸረ-ሽብር ግቦችን በመደገፍ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን በማቀላጠፍ ያሳየችው አንጻራዊ ስኬት፣ ለአሜሪካ ተመራጭ እና ጠቃሚ ተግባራዊ አጋር እንድትሆን አስችሏታል። ይህ ማለት የፖለቲካው ሉዓላዊነት ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ተመልሷል ማለት ሳይሆን፣ መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚጣጣም የፖሊሲ አተገባበር እየታየ መሆኑን ያሳያል።
በሌላ በኩል ጥናቱ ለሶማሊላንድ የማስጠንቀቂያ መልእክትም አስተላልፏል። ምቹ መልክዓ ምድር ወይም ስትራቴጂካዊ ቦታ መኖር ብቻውን ቀጣይነት ላለው ዓለም አቀፍ ትብብር ዋስትና እንደማይሆን እና ይህም ጠንካራ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የደህንነት ተቋማዊ አቅምን በማጎልበት መታገዝ እንዳለበት አሳስቧል። በተጨማሪም ይህ የአሜሪካ አዲስ አካሄድ በአካባቢው ሀገራት በተለይም በጅቡቲ ላይ ጫና ሊፈጥር እንደሚችል ተጠቁሟል። የአሜሪካ አማራጭ የመሠረተ ልማት ማዕከሎችን መፈለግ የጅቡቲን ጠቀሜታ ባያሳጣም፣ ቀጠናዊ ፉክክሩን በማጠናከር ሀገራቱ ተወዳዳሪነታቸውን እንዲያሳድጉ ያስገድዳቸዋል ተብሏል።
አሜሪካ የሶማሊላንድን ጉዳይ ከዳር እንደቆመ የፖለቲካ ጥያቄ ከማየት ይልቅ፣ በቀጠናው የደህንነትና የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ሊያበረክት የሚችል ወሳኝ ተዋናይ አድርጋ እየቆጠረችው መምጣቷን የጥናት ሰነዱ ያትታል። ይህ ሂደት በቅርብ ጊዜ ውስጥ የሕግ እና የዲፕሎማሲ እውቅናን ላያመጣ ቢችልም፣ በአፍሪካ ቀንድ ጂኦ-ፖለቲካ ውስጥ ሶማሊላንድ ያላት ሥፍራ እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ታሪካዊ ማሳያ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የፖሊሲ ለውጥ ድንገተኛ ወይም አብዮታዊ ሳይሆን የሶማሊላንድን መረጋጋት፣ የአስተዳደር አቅምና ስትራቴጂካዊ መልክዓ ምድር ግምት ውስጥ ያስገባ ቀስ በቀስ የሚደረግ የፖሊሲ ማስተካከያ መሆኑ ተጠቅሷል። በተለይም የበርበራ ወደብ በአካባቢው ካሉ መጨናነቅ የሚታይባቸው ወደቦች እንደ አማራጭ ሆኖ ማገልገል መቻሉ እና ለንግድና ትራንስፖርት ያለው ከፍተኛ ጠቀሜታ በአሜሪካ መንግሥት በኩል አዎንታዊ እይታን አትርፎለታል። ሆኖም ይህ አካሄድ በሞቃዲሾ ከሚገኘው የሶማሊያ ፌዴራላዊ መንግሥት ጋር ውጥረት ላለመፍጠር ሲባል፣ ሙሉ የዲፕሎማሲ እውቅና ከመስጠት ይልቅ በጥንቃቄ የተመጠነ የመካከለኛ መንገድ ስትራቴጂን የሚከተል ነው።
ጥናቱ እንደሚያብራራው በዘመናዊው የዓለም አቀፍ ግንኙነት አገራት አጋሮቻቸውን የሚመዝኑት በይፋዊ የዲፕሎማሲ ማዕረጋቸው ብቻ ሳይሆን፣ በተግባራዊ ብቃታቸው፣ አስተማማኝነታቸውና አገልግሎት ሰጪነታቸው ነው። በዚህ ረገድ ሶማሊላንድ መረጋጋትን በማስፈን፣ የጸረ-ሽብር ግቦችን በመደገፍ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን በማቀላጠፍ ያሳየችው አንጻራዊ ስኬት፣ ለአሜሪካ ተመራጭ እና ጠቃሚ ተግባራዊ አጋር እንድትሆን አስችሏታል። ይህ ማለት የፖለቲካው ሉዓላዊነት ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ተመልሷል ማለት ሳይሆን፣ መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚጣጣም የፖሊሲ አተገባበር እየታየ መሆኑን ያሳያል።
በሌላ በኩል ጥናቱ ለሶማሊላንድ የማስጠንቀቂያ መልእክትም አስተላልፏል። ምቹ መልክዓ ምድር ወይም ስትራቴጂካዊ ቦታ መኖር ብቻውን ቀጣይነት ላለው ዓለም አቀፍ ትብብር ዋስትና እንደማይሆን እና ይህም ጠንካራ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የደህንነት ተቋማዊ አቅምን በማጎልበት መታገዝ እንዳለበት አሳስቧል። በተጨማሪም ይህ የአሜሪካ አዲስ አካሄድ በአካባቢው ሀገራት በተለይም በጅቡቲ ላይ ጫና ሊፈጥር እንደሚችል ተጠቁሟል። የአሜሪካ አማራጭ የመሠረተ ልማት ማዕከሎችን መፈለግ የጅቡቲን ጠቀሜታ ባያሳጣም፣ ቀጠናዊ ፉክክሩን በማጠናከር ሀገራቱ ተወዳዳሪነታቸውን እንዲያሳድጉ ያስገድዳቸዋል ተብሏል።
አሜሪካ የሶማሊላንድን ጉዳይ ከዳር እንደቆመ የፖለቲካ ጥያቄ ከማየት ይልቅ፣ በቀጠናው የደህንነትና የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ሊያበረክት የሚችል ወሳኝ ተዋናይ አድርጋ እየቆጠረችው መምጣቷን የጥናት ሰነዱ ያትታል። ይህ ሂደት በቅርብ ጊዜ ውስጥ የሕግ እና የዲፕሎማሲ እውቅናን ላያመጣ ቢችልም፣ በአፍሪካ ቀንድ ጂኦ-ፖለቲካ ውስጥ ሶማሊላንድ ያላት ሥፍራ እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ታሪካዊ ማሳያ መሆኑ ተገልጿል።
2 days ago
ሁለተኛው የኢትዮጵያ እና ፊንላንድ የፖለቲካ ምክክር በአዲስ አበባ ተካሄደ
*********************
ሁለተኛው የኢትዮጵያ እና ፊንላንድ የፖለቲካ ምክክር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን በምክክሩ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ በትምህርት እና በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ሰፊ ግምገማ ተደርጓል።
ምክክሩን በጋራ የመሩት አምባሳደር መለስ ዓለም እና የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን የሁለቱን ሀገራት የቆየ ግንኙነት እና አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በዚሁ ወቅት ማብራሪያ የሰጡት አምባሳደር መለስ ዓለም በኢትዮጵያ ስላለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ስለ 7ኛው አጠቃላይ ምርጫ፣ ስለ ብሔራዊ ምክክር ሂደት እና ስለ ፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ለፊንላንድ ልዑካን ገልጸዋል።
አምባሳደሩ የፊንላንድ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂ እና በግብርና ማቀነባበሪያ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጥሪ በማቅረብ ንግድን ለማሳደግ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ምክር ቤቶች በቅርበት እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን በበኩላቸው፣ በአዲስ አበባ እየታየ ያለውን ፈጣን የልማት ለውጥ አድንቀዋል።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ለሀገራቸው ቁልፍ አጋር መሆኗን ገልጸው፣ ፊንላንድ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ተናግረዋል።
በተለይም በዲጂታላይዜሽን፣ በከፍተኛ ትምህርት፣ በሜትሮሎጂ እና በአስተማሪዎች ሥልጠና ዙሪያ የሚደረገው ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀው፣ መሰል መደበኛ ውይይቶችን አጠናክሮ ለመቀጠል መስማማታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #finland #ethiopiafinlandconsultation #addisababa
*********************
ሁለተኛው የኢትዮጵያ እና ፊንላንድ የፖለቲካ ምክክር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን በምክክሩ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ በትምህርት እና በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ሰፊ ግምገማ ተደርጓል።
ምክክሩን በጋራ የመሩት አምባሳደር መለስ ዓለም እና የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን የሁለቱን ሀገራት የቆየ ግንኙነት እና አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በዚሁ ወቅት ማብራሪያ የሰጡት አምባሳደር መለስ ዓለም በኢትዮጵያ ስላለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ስለ 7ኛው አጠቃላይ ምርጫ፣ ስለ ብሔራዊ ምክክር ሂደት እና ስለ ፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ለፊንላንድ ልዑካን ገልጸዋል።
አምባሳደሩ የፊንላንድ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂ እና በግብርና ማቀነባበሪያ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጥሪ በማቅረብ ንግድን ለማሳደግ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ምክር ቤቶች በቅርበት እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን በበኩላቸው፣ በአዲስ አበባ እየታየ ያለውን ፈጣን የልማት ለውጥ አድንቀዋል።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ለሀገራቸው ቁልፍ አጋር መሆኗን ገልጸው፣ ፊንላንድ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ተናግረዋል።
በተለይም በዲጂታላይዜሽን፣ በከፍተኛ ትምህርት፣ በሜትሮሎጂ እና በአስተማሪዎች ሥልጠና ዙሪያ የሚደረገው ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀው፣ መሰል መደበኛ ውይይቶችን አጠናክሮ ለመቀጠል መስማማታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #finland #ethiopiafinlandconsultation #addisababa
5 days ago
ለወጣቶች እና የሚዲያ ተቋማት በስደት አስተዳደር ዙሪያ የሚዲያ ንቅናቄን ለማጠናከር የስትራቴጂክ አጋርነት ውይይት ተካሄደ።
ውይይቱ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ አተኩረው በሚሰሩት ሲግማ ኢስት አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል Sweet Life for All Charity Organization የተሰናዳ መሆኑ ተጠቁሟል ።
ተቋማቱ "ይመለከተኛል" ሲሉ ከዚህ ቀደም አብረው መስራታቸውን በመጥቀስ በመድረኩ እኤአ 2025–2026 ዓ.ም የ“Digital Voices, Real Impact” ዘመቻ የተገኙ ውጤቶች፣ የስደት ጉዳይ ላይ የሚዲያ ሚና፣ የወጣቶች አቅም ግንባታ፣ የሰው ዝውውር እና የህገ-ወጥ ስደት መከላከል እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ ያለው የተቀናጀ ክልላዊ ምላሽ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስትር ተወክለው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ደረጀ ተግይበሉ "እንደዚህ ያሉ መድረኮችን ለማገዝ መረጃዎችን በማቅረብ ፣ ግንዛቤን ከመፍጠር አንፃር እንዲህ ያለው ምክክር እና ስትራቴጂክ አጋርነት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።"
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ዬሀንስ ብርሀኑ መከላከል ፣ከለላ እና ጥበቃ ቅንጅታዊ አሰራር ፣ የህግ ተጠያቂነት፣ በጋራ መስራት ላይ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በዘርፉ የረጅም አመት የስራ ልምድ ያላቸው የውዲንዳድ ሀላፊ እና የምስራቅ አፍሪካ ስትራቴጂክ ተወካይ የሆኑት አቶ ኤፍሬም ሽፈራው ሀገራዊ ምላሹ እንዳለ ሆኖ ቀጠናዊ ጉዳይ ላይም አብሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል ።
የ Sweet Life for All Charity Organization መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አንተነህ ተስፋዬ በንግግራቸው፣ “ዲጂታል ሚዲያ የማህበረሰብ ንቅናቄ መፍጠሪያ እና የወጣቶች ድምፅ ማጉሊያ ኃይለኛ መሳሪያ ነው በማለት በተለይ በፍልሰት እና በህገወጥ ሰው ዝውውር ጉዳዮች ላይ የተቀናጀ የሚዲያ ተሳትፎ ወሳኝ ነው” ብለዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ SIGMA EAST AFRICA CHARITABLE ORGANIZATION FOUNDER AND
CEO የሲግማ ኢስት አፍሪካ መስራች እና ስራ አስኪያጅ በፍልሰት ዙሪያ ሀገራዊና ቀጠናዊ ምላሾች ላይ አብሮ መስራቱ በከፍተኛ ትኩረት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመላከቱ ተገቢ መሆኑን አንስተዋል ።
በውይይቱ ውስጥ የስደት አስተዳደር፣ የተመላሽ ዜጎች ድጋፍ፣ የወጣቶች ስራ ፈጠራ፣ የሚዲያ ተሳትፎ እና የህገወጥ የሰው ዝውውር ግንዛቤ ማስፋፊያ ላይ በባለሙያዎች የተመራ ውይይት ተካሂዷል።
ሲግማ ኢስት አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል የተሰኙት ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የምስረታ እድሜያቸው አጭር ቢሆኑም በእቅድ እና በተግባራዊ አፈፃፀማቸው ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ መሆናቸውም ተገልጿል ።
በዛሬው ውይይት ሀገራችን ኢትዮጵያ በሰዎች ዝውውር እያደረገችው ስላለ እንቅስቃሴ እና ስለመጣ ለውጥ የተነሳ ሲሆን ተቋማቱ ከአጋር አካላት ጋር የሰሩትን በቀጣይም በተለያዩ ሀገራት በተለይም በአረቡ አለም በችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎቻችን ድምፅ ለመሆን ንቅናቄም ለመጀመር ከስምምነት ተደርሷል።
ዝግጅቱ በአዲስ አበባ ማግኖሊያ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን ከመንግስት ተቋማት የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ፣
ሴቶችና ማኀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናስ ቢሮ ፣ ከሚዲያ ተቋማት፣ ከሲቪል ማህበራት፣ ከወጣቶች አደረጃጀት እና ከአለም አቀፍ አጋሮች የተውጣጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
ይህንንም አላማ ከግብ ለማድረስ አምስት ተቋማት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል ።
በስተመጨረሻም ሁለቱ ተቋማት ላስመዘገቡት ውጤት በሥራ እንቅስቃሴያቸው ደጋፊ ለነበሩ ተቋማትና ግለሰቦች የምስጋና እና የእውቅና ሰርተፍኬት አበርክተዋል።
ውይይቱ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ አተኩረው በሚሰሩት ሲግማ ኢስት አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል Sweet Life for All Charity Organization የተሰናዳ መሆኑ ተጠቁሟል ።
ተቋማቱ "ይመለከተኛል" ሲሉ ከዚህ ቀደም አብረው መስራታቸውን በመጥቀስ በመድረኩ እኤአ 2025–2026 ዓ.ም የ“Digital Voices, Real Impact” ዘመቻ የተገኙ ውጤቶች፣ የስደት ጉዳይ ላይ የሚዲያ ሚና፣ የወጣቶች አቅም ግንባታ፣ የሰው ዝውውር እና የህገ-ወጥ ስደት መከላከል እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ ያለው የተቀናጀ ክልላዊ ምላሽ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስትር ተወክለው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ደረጀ ተግይበሉ "እንደዚህ ያሉ መድረኮችን ለማገዝ መረጃዎችን በማቅረብ ፣ ግንዛቤን ከመፍጠር አንፃር እንዲህ ያለው ምክክር እና ስትራቴጂክ አጋርነት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።"
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ዬሀንስ ብርሀኑ መከላከል ፣ከለላ እና ጥበቃ ቅንጅታዊ አሰራር ፣ የህግ ተጠያቂነት፣ በጋራ መስራት ላይ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በዘርፉ የረጅም አመት የስራ ልምድ ያላቸው የውዲንዳድ ሀላፊ እና የምስራቅ አፍሪካ ስትራቴጂክ ተወካይ የሆኑት አቶ ኤፍሬም ሽፈራው ሀገራዊ ምላሹ እንዳለ ሆኖ ቀጠናዊ ጉዳይ ላይም አብሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል ።
የ Sweet Life for All Charity Organization መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አንተነህ ተስፋዬ በንግግራቸው፣ “ዲጂታል ሚዲያ የማህበረሰብ ንቅናቄ መፍጠሪያ እና የወጣቶች ድምፅ ማጉሊያ ኃይለኛ መሳሪያ ነው በማለት በተለይ በፍልሰት እና በህገወጥ ሰው ዝውውር ጉዳዮች ላይ የተቀናጀ የሚዲያ ተሳትፎ ወሳኝ ነው” ብለዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ SIGMA EAST AFRICA CHARITABLE ORGANIZATION FOUNDER AND
CEO የሲግማ ኢስት አፍሪካ መስራች እና ስራ አስኪያጅ በፍልሰት ዙሪያ ሀገራዊና ቀጠናዊ ምላሾች ላይ አብሮ መስራቱ በከፍተኛ ትኩረት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመላከቱ ተገቢ መሆኑን አንስተዋል ።
በውይይቱ ውስጥ የስደት አስተዳደር፣ የተመላሽ ዜጎች ድጋፍ፣ የወጣቶች ስራ ፈጠራ፣ የሚዲያ ተሳትፎ እና የህገወጥ የሰው ዝውውር ግንዛቤ ማስፋፊያ ላይ በባለሙያዎች የተመራ ውይይት ተካሂዷል።
ሲግማ ኢስት አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል የተሰኙት ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የምስረታ እድሜያቸው አጭር ቢሆኑም በእቅድ እና በተግባራዊ አፈፃፀማቸው ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ መሆናቸውም ተገልጿል ።
በዛሬው ውይይት ሀገራችን ኢትዮጵያ በሰዎች ዝውውር እያደረገችው ስላለ እንቅስቃሴ እና ስለመጣ ለውጥ የተነሳ ሲሆን ተቋማቱ ከአጋር አካላት ጋር የሰሩትን በቀጣይም በተለያዩ ሀገራት በተለይም በአረቡ አለም በችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎቻችን ድምፅ ለመሆን ንቅናቄም ለመጀመር ከስምምነት ተደርሷል።
ዝግጅቱ በአዲስ አበባ ማግኖሊያ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን ከመንግስት ተቋማት የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ፣
ሴቶችና ማኀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናስ ቢሮ ፣ ከሚዲያ ተቋማት፣ ከሲቪል ማህበራት፣ ከወጣቶች አደረጃጀት እና ከአለም አቀፍ አጋሮች የተውጣጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
ይህንንም አላማ ከግብ ለማድረስ አምስት ተቋማት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል ።
በስተመጨረሻም ሁለቱ ተቋማት ላስመዘገቡት ውጤት በሥራ እንቅስቃሴያቸው ደጋፊ ለነበሩ ተቋማትና ግለሰቦች የምስጋና እና የእውቅና ሰርተፍኬት አበርክተዋል።
9 days ago
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና የሲንቄ ባንክ ስትራቴጂካዊ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እያከናወናቸው ያሉትን የቤት ልማትና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ይበልጥ ለማጠናከር እንዲሁም የፋይናንስ አቅሙን ለማሳደግ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከሲንቄ ባንክ ጋር ተፈራርሟል።
ኮርፖሬሽኑ በሀገሪቱ የኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት ላይ እያበረከተ ያለውን በጎ አስተዋጽኦ ለማስፋት እና ዘመናዊ የቤት ልማት ስራዎችን ተደራሽ ለማድረግ ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ያለውን አጋርነት እያጠናከረ ይገኛል።
በዚሁ መሰረት ዛሬ የተደረሰው ስምምነት ኮርፖሬሽኑ ለሚያከናውናቸው ሰፊ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች የሚውል የፋይናንስ አቅርቦት ማመቻቸትን የሚያካትት ሲሆን፥ ሁለቱ ተቋማት በሌሎች ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል።
በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ላይ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል፣ የሲንቄ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ንዋይ መገርሣ እና የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በወቅቱም የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት፤ ይህ ስምምነት ኮርፖሬሽኑ የጀመራቸውን ግዙፍ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች በላቀ የፋይናንስ አቅም ለመደገፍ እና የተቋሙን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
#የፌደራልቤቶችኮርፖሬሽን #ሲንቄባንክ #የቤትልማት #ኢንቨስትመንት #ፋይናንስ #ባንክ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እያከናወናቸው ያሉትን የቤት ልማትና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ይበልጥ ለማጠናከር እንዲሁም የፋይናንስ አቅሙን ለማሳደግ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከሲንቄ ባንክ ጋር ተፈራርሟል።
ኮርፖሬሽኑ በሀገሪቱ የኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት ላይ እያበረከተ ያለውን በጎ አስተዋጽኦ ለማስፋት እና ዘመናዊ የቤት ልማት ስራዎችን ተደራሽ ለማድረግ ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ያለውን አጋርነት እያጠናከረ ይገኛል።
በዚሁ መሰረት ዛሬ የተደረሰው ስምምነት ኮርፖሬሽኑ ለሚያከናውናቸው ሰፊ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች የሚውል የፋይናንስ አቅርቦት ማመቻቸትን የሚያካትት ሲሆን፥ ሁለቱ ተቋማት በሌሎች ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል።
በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ላይ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል፣ የሲንቄ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ንዋይ መገርሣ እና የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በወቅቱም የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት፤ ይህ ስምምነት ኮርፖሬሽኑ የጀመራቸውን ግዙፍ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች በላቀ የፋይናንስ አቅም ለመደገፍ እና የተቋሙን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
#የፌደራልቤቶችኮርፖሬሽን #ሲንቄባንክ #የቤትልማት #ኢንቨስትመንት #ፋይናንስ #ባንክ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
10 days ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍ መድረክ ጠንካራ የፉክክር አቅም መገንባት የቻለ ታላቅ ተቋም መሆኑን በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ አስታወቁ።
አየር መንገዱ ሰሞኑን የ80ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በተለያዩ ደማቅ ዝግጅቶች ማክበሩ ይታወሳል።
አምባሳደሩ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት አየር መንገዱ የሚሰጠው የበረራ አገልግሎት ጥራትና ሰፊ ተደራሽነት ተከታታይ ተቋማዊ ዕድገት እንዲያስመዘግብ ረድቶታል።
ተቋሙ ባስመዘገበው የረጅም ዘመናት ዓለም አቀፍ ዝና አማካኝነት ከአሜሪካ የአቪዬሽን ዘርፍ ኩባንያዎች ጋር ጠንካራ ስትራቴጂካዊ ትብብር መፍጠሩን የጠቀሱት አምባሳደሩ ለዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሆኑት ቦይንግና ጂኢ ኤሮስፔስ ኩባንያዎች ጋር ያለውን የጠበቀ አጋርነት በምሳሌነት አንስተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካን አህጉር ከቀሪው ዓለም ጋር የሚያገናኝ እጅግ ግዙፍ የአቪዬሽን መሠረተ ልማት በማስፋፋት ላይ የምትገኝ ሀገር መሆኗን የገለጹት አምባሳደር ማሲንጋ አየር መንገዱ አዳዲስ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን በማስገባት የበረራ መዳረሻዎችን በማስፋት እንዲሁም በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያዎችን በመገንባት ረገድ የሚደነቅ ሥራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
ይህ የዳበረ አቅም ተቋሙ ቀጣናዊ ተዋናይ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ መድረክም ተወዳዳሪ እንዲሆን አድርጎታል።
በተለይም በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት በአሜሪካ እና በኢትዮጵያ አየር መንገድ መካከል የነበረው ትብብር ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበረው ሲሆን አየር መንገዱ ክትባቶችንና ሕይወት አድን የሕክምና ቁሳቁሶችን በማጓጓዝ ረገድ የላቀ ሚና ተጫውቷል።
የአየር መንገዱ የወደፊት ስትራቴጂካዊ ዕቅዶችና የአቅም ግንባታ ሥራዎች ለቀጣይ ስኬቱ ወሳኝ መሆናቸውን የገለጹት አምባሳደሩ አሜሪካና የሀገሪቱ የአቪዬሽን ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ያላቸውን አጋርነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ የልማት ትብብር ይበልጥ እንደሚያሳድገው ገልጸዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #አቪዬሽን #ኢትዮጵያ #አሜሪካ #ዲፕሎማሲ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍ መድረክ ጠንካራ የፉክክር አቅም መገንባት የቻለ ታላቅ ተቋም መሆኑን በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ አስታወቁ።
አየር መንገዱ ሰሞኑን የ80ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በተለያዩ ደማቅ ዝግጅቶች ማክበሩ ይታወሳል።
አምባሳደሩ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት አየር መንገዱ የሚሰጠው የበረራ አገልግሎት ጥራትና ሰፊ ተደራሽነት ተከታታይ ተቋማዊ ዕድገት እንዲያስመዘግብ ረድቶታል።
ተቋሙ ባስመዘገበው የረጅም ዘመናት ዓለም አቀፍ ዝና አማካኝነት ከአሜሪካ የአቪዬሽን ዘርፍ ኩባንያዎች ጋር ጠንካራ ስትራቴጂካዊ ትብብር መፍጠሩን የጠቀሱት አምባሳደሩ ለዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሆኑት ቦይንግና ጂኢ ኤሮስፔስ ኩባንያዎች ጋር ያለውን የጠበቀ አጋርነት በምሳሌነት አንስተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካን አህጉር ከቀሪው ዓለም ጋር የሚያገናኝ እጅግ ግዙፍ የአቪዬሽን መሠረተ ልማት በማስፋፋት ላይ የምትገኝ ሀገር መሆኗን የገለጹት አምባሳደር ማሲንጋ አየር መንገዱ አዳዲስ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን በማስገባት የበረራ መዳረሻዎችን በማስፋት እንዲሁም በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያዎችን በመገንባት ረገድ የሚደነቅ ሥራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
ይህ የዳበረ አቅም ተቋሙ ቀጣናዊ ተዋናይ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ መድረክም ተወዳዳሪ እንዲሆን አድርጎታል።
በተለይም በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት በአሜሪካ እና በኢትዮጵያ አየር መንገድ መካከል የነበረው ትብብር ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበረው ሲሆን አየር መንገዱ ክትባቶችንና ሕይወት አድን የሕክምና ቁሳቁሶችን በማጓጓዝ ረገድ የላቀ ሚና ተጫውቷል።
የአየር መንገዱ የወደፊት ስትራቴጂካዊ ዕቅዶችና የአቅም ግንባታ ሥራዎች ለቀጣይ ስኬቱ ወሳኝ መሆናቸውን የገለጹት አምባሳደሩ አሜሪካና የሀገሪቱ የአቪዬሽን ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ያላቸውን አጋርነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ የልማት ትብብር ይበልጥ እንደሚያሳድገው ገልጸዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #አቪዬሽን #ኢትዮጵያ #አሜሪካ #ዲፕሎማሲ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
10 days ago
የቻይና የእርዳታ እህል ኩባ ገብቷል
#ethiopia | ቻይና ለከባድ የምግብና የኃይል ቀውስ ውስጥ ለምትገኘው ኩባ ቃል ከገባችው 60 ሺህ ቶን የአደጋ ጊዜ የምግብ ድጋፍ ውስጥ የመጀመሪያውን 15 ሺህ ቶን ሩዝ በሃቫና ወደብ በኩል አስረከበች።
ይህ በቤጂንግ የተላከው ግዙፍ ጭነት በኩባ በቅርብ ታሪክ የተደረገ ትልቁ የምግብ ድጋፍ ሲሆን፥ በአሜሪካ ማዕቀብና ከቬንዙዌላ የሚመጣው ነዳጅ በመቋረጡ ምክንያት በደሴቲቱ ላይ የተከሰተውን ታይቶ የማይታወቅ የሸቀጦችና የኃይል እጥረት ለመቅረፍ ያለመ ነው።
የኩባው ፕሬዝዳንት ሚጌል ዲያዝ-ካኔል ዕርዳታው በሁሉም ግዛቶች ለሚገኙ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ ለሆስፒታሎችና ለትምህርት ቤቶች እንደሚሰራጭ የገለጹ ሲሆን፥ በኩባ የቻይና አምባሳደር ሁዋ ሺን በበኩላቸው እርምጃው በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ አጋርነት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።
#china #cuba #havana #foodaid #geopolitics #globalnews #chinacubarelations
#ethiopia | ቻይና ለከባድ የምግብና የኃይል ቀውስ ውስጥ ለምትገኘው ኩባ ቃል ከገባችው 60 ሺህ ቶን የአደጋ ጊዜ የምግብ ድጋፍ ውስጥ የመጀመሪያውን 15 ሺህ ቶን ሩዝ በሃቫና ወደብ በኩል አስረከበች።
ይህ በቤጂንግ የተላከው ግዙፍ ጭነት በኩባ በቅርብ ታሪክ የተደረገ ትልቁ የምግብ ድጋፍ ሲሆን፥ በአሜሪካ ማዕቀብና ከቬንዙዌላ የሚመጣው ነዳጅ በመቋረጡ ምክንያት በደሴቲቱ ላይ የተከሰተውን ታይቶ የማይታወቅ የሸቀጦችና የኃይል እጥረት ለመቅረፍ ያለመ ነው።
የኩባው ፕሬዝዳንት ሚጌል ዲያዝ-ካኔል ዕርዳታው በሁሉም ግዛቶች ለሚገኙ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ ለሆስፒታሎችና ለትምህርት ቤቶች እንደሚሰራጭ የገለጹ ሲሆን፥ በኩባ የቻይና አምባሳደር ሁዋ ሺን በበኩላቸው እርምጃው በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ አጋርነት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።
#china #cuba #havana #foodaid #geopolitics #globalnews #chinacubarelations
10 days ago
ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ላይ አራተኛው ኩባንያ ሆኖ ተመዘገበ።
#ethiopia | ተቋሙ በዚህ ገበያ ላይ መመዝገቡን ይፋ ያደረገው ከኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ጋር በመተባበር በሰጠው የጋራ መግለጫ ነው።
እስካሁን በሀገሪቱ የመጀመሪያውና ብቸኛው የተደራጀ የካፒታል ማርኬት የሆነው እና በመንግሥትና በግል አጋርነት የተመሠረተው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ላይ በይፋ ተመዝግበው ተሳታፊ የሆኑት ሦስት የፋይናንስ ተቋማት ብቻ ነበሩ።
መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ተቋም በሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መድረክ ላይ ከመመዝገቡ አስቀድሞ 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖቹን ለሽያጭ ገበያ አውጥቶ ነበር።
ኩባንያው ባለፈው ሚያዝያ ወር ባወጣው መግለጫ ለአራት ወራት ያህል ክፍት ሆኖ በቆየው በዚህ የሽያጭ ሂደት ለሽያጭ ካቀረበው የ10 በመቶ የኩባንያው ድርሻ ውስጥ 10.7 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ብቻ የተሸጡ ሲሆን፤ቀሪዎቹ 89.3 ሚሊዮን አክሲዮኖች ግን ሳይሸጡ ቀርተዋል።
በተመሳሳይ ተቋሙ ከአክሲዮን ሽያጩ 30 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ የነበረ ቢሆንም ማሳካት የቻለው ግን 3.2 ቢሊዮን ብር ብቻ እንደሆነ መግለጹ አይዘነጋም።
በዚህ የሽያጭ ሂደት ላይ ከ47 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን አክሲዮን መግዛታቸውን ተቋሙ አስታውቋል።
አክሲዮን ከገዙ ዜጎች ውስጥ 45,336 የሚሆኑት “የባለቤትነት ማረጋገጫ” እና “አክሲዮኖችን ወደ ዲጂታል የመቀየር ሂደታቸውን ሙሉ በሙሉ ማጠናቀቃቸው በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ተገልጿል።
የባለቤትነት ማረጋገጫ ሂደታቸውን ያጠናቀቁ ዜጎች አክሲዮኖች በገንዘብ ሲሰላ 3.04 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው መሆናቸውንም ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል።
አክሲዮን ከገዙ ባለሀብቶች ውስጥ 3.7 በመቶ የሚሆኑት የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ባለማቅረባቸው እና ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው በመሆኑ፤ ለአክሲዮን ግዢ የከፈሉት ገንዘብ ተመላሽ እንደሚደረግላቸው የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ተናግረዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | ተቋሙ በዚህ ገበያ ላይ መመዝገቡን ይፋ ያደረገው ከኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ጋር በመተባበር በሰጠው የጋራ መግለጫ ነው።
እስካሁን በሀገሪቱ የመጀመሪያውና ብቸኛው የተደራጀ የካፒታል ማርኬት የሆነው እና በመንግሥትና በግል አጋርነት የተመሠረተው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ላይ በይፋ ተመዝግበው ተሳታፊ የሆኑት ሦስት የፋይናንስ ተቋማት ብቻ ነበሩ።
መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ተቋም በሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መድረክ ላይ ከመመዝገቡ አስቀድሞ 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖቹን ለሽያጭ ገበያ አውጥቶ ነበር።
ኩባንያው ባለፈው ሚያዝያ ወር ባወጣው መግለጫ ለአራት ወራት ያህል ክፍት ሆኖ በቆየው በዚህ የሽያጭ ሂደት ለሽያጭ ካቀረበው የ10 በመቶ የኩባንያው ድርሻ ውስጥ 10.7 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ብቻ የተሸጡ ሲሆን፤ቀሪዎቹ 89.3 ሚሊዮን አክሲዮኖች ግን ሳይሸጡ ቀርተዋል።
በተመሳሳይ ተቋሙ ከአክሲዮን ሽያጩ 30 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ የነበረ ቢሆንም ማሳካት የቻለው ግን 3.2 ቢሊዮን ብር ብቻ እንደሆነ መግለጹ አይዘነጋም።
በዚህ የሽያጭ ሂደት ላይ ከ47 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን አክሲዮን መግዛታቸውን ተቋሙ አስታውቋል።
አክሲዮን ከገዙ ዜጎች ውስጥ 45,336 የሚሆኑት “የባለቤትነት ማረጋገጫ” እና “አክሲዮኖችን ወደ ዲጂታል የመቀየር ሂደታቸውን ሙሉ በሙሉ ማጠናቀቃቸው በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ተገልጿል።
የባለቤትነት ማረጋገጫ ሂደታቸውን ያጠናቀቁ ዜጎች አክሲዮኖች በገንዘብ ሲሰላ 3.04 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው መሆናቸውንም ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል።
አክሲዮን ከገዙ ባለሀብቶች ውስጥ 3.7 በመቶ የሚሆኑት የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ባለማቅረባቸው እና ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው በመሆኑ፤ ለአክሲዮን ግዢ የከፈሉት ገንዘብ ተመላሽ እንደሚደረግላቸው የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ተናግረዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
Sponsored by
Surafel
10 days ago
በባሕር ዳር ከተማ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው
***********************
የብልፅግና ፓርቲ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል የምረጡኝ ቅስቀሳ ማጠቃለያ መርሐ ግብር በባሕርዳር ከተማ እያካሄደ ይገኛል፡፡
የፓርቲው አባላት እና ደጋፊዎች በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም በመገኘት ለብልፅግና ፓርቲ ያላቸውን ድጋፍና አጋርነት እየገለጹ ይገኛሉ።
በዚህ የሕዝብ ድጋፍና የምርጫ ቅስቀሳ ማጠቃለያ መርሐ ግብር ላይ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ አባል አቶ አረጋ ከበደን ጨምሮ ሌሎች የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።
#ethiopianbroadcastingcorporation
***********************
የብልፅግና ፓርቲ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል የምረጡኝ ቅስቀሳ ማጠቃለያ መርሐ ግብር በባሕርዳር ከተማ እያካሄደ ይገኛል፡፡
የፓርቲው አባላት እና ደጋፊዎች በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም በመገኘት ለብልፅግና ፓርቲ ያላቸውን ድጋፍና አጋርነት እየገለጹ ይገኛሉ።
በዚህ የሕዝብ ድጋፍና የምርጫ ቅስቀሳ ማጠቃለያ መርሐ ግብር ላይ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ አባል አቶ አረጋ ከበደን ጨምሮ ሌሎች የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።
#ethiopianbroadcastingcorporation
11 days ago
ፓይለቱ በበራራ ላይ እያለ የልብ ህመም አጋጠመው
ባለፈው አርብ ከቴነሪፍ ወደ በርሚንግሃም 220 ተጓዦችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረው የጄት2 (Jet2 LS1266) በረራ፣ ዋናው አብራሪ በድንገት በደረሰባቸው የልብ ህመም ምክንያት በፖርቶ፣ ፖርቱጋል አስቸኳይ ማረፊያ ለማድረግ ተገዷል ሲል ሜትሮ ዘግቧል።
በበረራው ወቅት የረዳት አብራሪው አይሮፕላኑን ለመቆጣጠር ከፍታ በፍጥነት በቀነሰበት ወቅት ተጓዦች ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ወድቀው ነበር።
የበረራ አስተናጋጆች እያለቀሱ በህክምና የሰለጠነ ሰው ይፈልጉ እንደነበር ተገልጿል።
አይሮፕላኑ በፖርቶ አውሮፕላን ማረፊያ በሰላም ያረፈ ሲሆን፣ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ለአብራሪው አስቸኳይ ህክምና አድርገውላቸዋል።
ተሳፋሪዎች ግን ያለምንም ማረፊያ ለአውሮፕላን ሰራተኞቹ ያላቸውን አጋርነት እየገለጹ፣ ለአስራ ሶስት ሰዓታት በአውሮፕላን ማረፊያው ለመቆየት መገደዳቸውን ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ባለፈው አርብ ከቴነሪፍ ወደ በርሚንግሃም 220 ተጓዦችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረው የጄት2 (Jet2 LS1266) በረራ፣ ዋናው አብራሪ በድንገት በደረሰባቸው የልብ ህመም ምክንያት በፖርቶ፣ ፖርቱጋል አስቸኳይ ማረፊያ ለማድረግ ተገዷል ሲል ሜትሮ ዘግቧል።
በበረራው ወቅት የረዳት አብራሪው አይሮፕላኑን ለመቆጣጠር ከፍታ በፍጥነት በቀነሰበት ወቅት ተጓዦች ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ወድቀው ነበር።
የበረራ አስተናጋጆች እያለቀሱ በህክምና የሰለጠነ ሰው ይፈልጉ እንደነበር ተገልጿል።
አይሮፕላኑ በፖርቶ አውሮፕላን ማረፊያ በሰላም ያረፈ ሲሆን፣ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ለአብራሪው አስቸኳይ ህክምና አድርገውላቸዋል።
ተሳፋሪዎች ግን ያለምንም ማረፊያ ለአውሮፕላን ሰራተኞቹ ያላቸውን አጋርነት እየገለጹ፣ ለአስራ ሶስት ሰዓታት በአውሮፕላን ማረፊያው ለመቆየት መገደዳቸውን ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በኢራን ጉዳይ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ጥልቅ እና ወሳኝ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ እንዳሰፈሩት፣ የሁለቱ መሪዎች ውይይት የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን መልሶ ለመክፈት በተደረሰው የመግባቢያ ሰነድ እና በኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ዙሪያ ወደፊት በሚደረገው የመጨረሻው የድርድር ሂደት ላይ ያተኮረ ነበር።
ኔታንያሁ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለእስራኤል ደህንነት ላሳዩት የማይናወጥ ቁርጠኝነት ጥልቅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተለይም "ኦፕሬሽን ሮሪንግ ላይየን" እና "ኤፒክ ፊዩሪ" በተባሉት ወታደራዊ ዘመቻዎች የአሜሪካ እና የእስራኤል ጦር የኢራንን ስጋት ለመመከት ትከሻ ለትከሻ ተሰልፈው መዋጋታቸውን በኩራት አስታውሰዋል።
በውይይታቸው ወቅት ሁለቱ መሪዎች ከኢራን ጋር የሚደረግ ማንኛውም የመጨረሻ ስምምነት የኒውክሌር አደጋን ሙሉ በሙሉ ማስወገድ እንዳለበት በጽኑ ተስማምተዋል። ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የኢራንን የኒውክሌር ማበልጸጊያ ጣቢያዎችን ሙሉ በሙሉ ማፍረስ እና የበለጸገውን የኒውክሌር ማዕድን ከኢራን ግዛት ጠራርጎ ማስወጣት የግድ እንደሚል አስምረውበታል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በበኩላቸው፣ እስራኤል ሊባኖስን ጨምሮ በየትኛውም ግንባር ከሚቃጣባት ጥቃት እና ስጋት ራስዋን የመከላከል ሙሉ መብት እንዳላት ዳግም አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ መግለጫቸውን ሲያጠቃልሉ፣ በእነርሱ እና በሀገሮቻቸው መካከል ያለው አጋርነት በጦር ሜዳ የተረጋገጠ እና ከምንጊዜውም በላይ የጠነከረ መሆኑን ገልጸው፣ የሁለቱም መሪዎች ፖሊሲ አሁንም እንዳልተቀየረ እና ኢራን የኒውክሌር መሳሪያ ፈጽሞ እንደማይኖራት በማሳሰብ የጋራ አቋማቸውን አስተጋብተዋል።
ኔታንያሁ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለእስራኤል ደህንነት ላሳዩት የማይናወጥ ቁርጠኝነት ጥልቅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተለይም "ኦፕሬሽን ሮሪንግ ላይየን" እና "ኤፒክ ፊዩሪ" በተባሉት ወታደራዊ ዘመቻዎች የአሜሪካ እና የእስራኤል ጦር የኢራንን ስጋት ለመመከት ትከሻ ለትከሻ ተሰልፈው መዋጋታቸውን በኩራት አስታውሰዋል።
በውይይታቸው ወቅት ሁለቱ መሪዎች ከኢራን ጋር የሚደረግ ማንኛውም የመጨረሻ ስምምነት የኒውክሌር አደጋን ሙሉ በሙሉ ማስወገድ እንዳለበት በጽኑ ተስማምተዋል። ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የኢራንን የኒውክሌር ማበልጸጊያ ጣቢያዎችን ሙሉ በሙሉ ማፍረስ እና የበለጸገውን የኒውክሌር ማዕድን ከኢራን ግዛት ጠራርጎ ማስወጣት የግድ እንደሚል አስምረውበታል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በበኩላቸው፣ እስራኤል ሊባኖስን ጨምሮ በየትኛውም ግንባር ከሚቃጣባት ጥቃት እና ስጋት ራስዋን የመከላከል ሙሉ መብት እንዳላት ዳግም አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ መግለጫቸውን ሲያጠቃልሉ፣ በእነርሱ እና በሀገሮቻቸው መካከል ያለው አጋርነት በጦር ሜዳ የተረጋገጠ እና ከምንጊዜውም በላይ የጠነከረ መሆኑን ገልጸው፣ የሁለቱም መሪዎች ፖሊሲ አሁንም እንዳልተቀየረ እና ኢራን የኒውክሌር መሳሪያ ፈጽሞ እንደማይኖራት በማሳሰብ የጋራ አቋማቸውን አስተጋብተዋል።
12 days ago
የFB Addis ሆቴል 20ኛ አመቱን አክብሯል። በእለቱ The Golden Age የተሰኘ ዘመናዊ ላውንጅ አስመርቋል። የሆቴሉ ባለቤት አቶ ኤፍሬም በለጠ ከአስተናጋጅነት በመነሳት ለከፍተኛ ባለሀብትነት የበቁ ኢንተርፕርነር ናቸው።
በታዋቂው «ኤፍሬም ውስኪ» ወይም በሚላቪት ግሮሰሪ ስማቸው የሚታወቁት የሥራ ፈጣሪው አቶ ኤፍሬም በለጠ ንብረት የሆነው ባለ 3 ኮከብ ደረጃው «ኤፍቢ አዲስ ሆቴል» (FB Addis Hotel) 20ኛ አመቱን ሲያከብር በእለቱ በ9ኛ ፎቅ ላይ የሰራውን the golden age ላውንጅን በድምቀት አስመርቋል።ላውንጁ አዲስ አበባን ከፒያሳ 70 ደረጃ ግርጌ ሆኖ 360 ዲግሪ ውበቷን ለመመልከትና ለመዝናናት እድል የሚሰጥ ነው።
ሆቴሉ ወደዚህ ከፍተኛ ደረጃ ከመሸጋገሩ በፊት፣ መሥራቹ አቶ ኤፍሬም በለጠ ከሰው ቤት ተቀጥረው በብርጭቆ ማጠብ ስራ የጀመሩበትን እና ራሳቸውን ችለው የንግድ ፈቃድ ያወጡበትን 20ኛ ዓመት ክብረ-በዓል ጭምር ታሳቢ ባደረገ መልኩ የተከናወነ ልዩ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ነው።
ባለ 12 ወለል ሕንጻ የሆነው ኤፍቢ አዲስ ሆቴል ዘመናዊና ሁለንተናዊ አገልግሎቶችን ያካተተ ሲሆን፣ ለዜጎችም ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ችሏል። 24 ደረጃቸውን የጠበቁ የመኝታ ክፍሎች አሉት።
ስፖርት ቤት፣ ስቲም ሳውና፣ ሬስቶራንት፣ ባር፣ እንዲሁም በሆቴሉ 9ኛ ፎቅ ላይ ማራኪ ከተማ አቀፍ እይታ (View) ያለው አዲስ የተገነባ ዘመናዊ ላውንጅ (Lounge) ያካትታል።
ከታሪካዊው የደጃችሁ ቤት አካባቢ ጀምሮ መሠረት የጣለበትን የነበረውን የስኪ ቤትና የስኪ ሥራዎች አገልግሎትም በጥራት ማቅረቡን ይቀጥላል። ሆቴሉ በአሁኑ ወቅት ለ62 ቋሚ ሠራተኞች የሥራ ዕድል መፍጠር ችሏል።
የሆቴሉ ማናጀርና ባለቤት አቶ ኤፍሬም በለጠ እንደገለጹት፣ የዛሬ 20 ዓመት ከሰው ቤት ወጥተው በኪራይ ቤት የጀመሩት ንግድ፤ በአራት የቀበሌ ሱቆች ግዢ አልፎ፣ ከ11 ዓመታት በፊት አካባቢው በልማት ሲፈርስ አሁን ወደሚገኝበት ቦታ ተዛውሯል።
በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ «ኤፍሬም ውስኪ» በሚል ትልቅ ስም ሊገነቡ የቻሉበትን ሚስጥር ሲያስረዱ፣ አስቀድመው ይሠሩበት ከነበረው ቤት የተማሩትንና ያደጉበትን ለንጹህ ነገር የመገዛትና ያለመደራደር እሴት እንደሆነ ገልጸዋል።
ሆቴሉ ዘመናዊ አሠራርና ሲስተም ያለው ቢሆንም፣ አቶ ኤፍሬም ግን አሁንም ያንን የቆየውን፣ ታዋቂው ደራሲ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር የጻፈበትን የደጃችሁ ቤት (ውቤ በረሃ) ፍቅር፣ ክብር፣ አንድነትና ማኅበራዊ ትስስር እንዳስቀጠሉበት ይናገራሉ።
በምረቃው ዕለትም የታደሙት ታላላቅ እንግዶች አብረዋቸው የ32 እና የ20 ዓመታት የሕይወት ታሪክ ያላቸው የቅርብ ወዳጆቻቸውና እንደ ቤተሰብ የሚቆጠሩ ደንበኞቻቸው ናቸው።
በመጨረሻም፣ ሆቴሉ ለደረሰበት የዕድገት ደረጃ ዓለም አቀፉ የመጠጥ አምራች ኩባንያ ዲያጆ ላደረገላቸው ዘላቂ የስፖንሰርሺፕና የድጋፍ አጋርነት አቶ ኤፍሬም ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
በታዋቂው «ኤፍሬም ውስኪ» ወይም በሚላቪት ግሮሰሪ ስማቸው የሚታወቁት የሥራ ፈጣሪው አቶ ኤፍሬም በለጠ ንብረት የሆነው ባለ 3 ኮከብ ደረጃው «ኤፍቢ አዲስ ሆቴል» (FB Addis Hotel) 20ኛ አመቱን ሲያከብር በእለቱ በ9ኛ ፎቅ ላይ የሰራውን the golden age ላውንጅን በድምቀት አስመርቋል።ላውንጁ አዲስ አበባን ከፒያሳ 70 ደረጃ ግርጌ ሆኖ 360 ዲግሪ ውበቷን ለመመልከትና ለመዝናናት እድል የሚሰጥ ነው።
ሆቴሉ ወደዚህ ከፍተኛ ደረጃ ከመሸጋገሩ በፊት፣ መሥራቹ አቶ ኤፍሬም በለጠ ከሰው ቤት ተቀጥረው በብርጭቆ ማጠብ ስራ የጀመሩበትን እና ራሳቸውን ችለው የንግድ ፈቃድ ያወጡበትን 20ኛ ዓመት ክብረ-በዓል ጭምር ታሳቢ ባደረገ መልኩ የተከናወነ ልዩ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ነው።
ባለ 12 ወለል ሕንጻ የሆነው ኤፍቢ አዲስ ሆቴል ዘመናዊና ሁለንተናዊ አገልግሎቶችን ያካተተ ሲሆን፣ ለዜጎችም ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ችሏል። 24 ደረጃቸውን የጠበቁ የመኝታ ክፍሎች አሉት።
ስፖርት ቤት፣ ስቲም ሳውና፣ ሬስቶራንት፣ ባር፣ እንዲሁም በሆቴሉ 9ኛ ፎቅ ላይ ማራኪ ከተማ አቀፍ እይታ (View) ያለው አዲስ የተገነባ ዘመናዊ ላውንጅ (Lounge) ያካትታል።
ከታሪካዊው የደጃችሁ ቤት አካባቢ ጀምሮ መሠረት የጣለበትን የነበረውን የስኪ ቤትና የስኪ ሥራዎች አገልግሎትም በጥራት ማቅረቡን ይቀጥላል። ሆቴሉ በአሁኑ ወቅት ለ62 ቋሚ ሠራተኞች የሥራ ዕድል መፍጠር ችሏል።
የሆቴሉ ማናጀርና ባለቤት አቶ ኤፍሬም በለጠ እንደገለጹት፣ የዛሬ 20 ዓመት ከሰው ቤት ወጥተው በኪራይ ቤት የጀመሩት ንግድ፤ በአራት የቀበሌ ሱቆች ግዢ አልፎ፣ ከ11 ዓመታት በፊት አካባቢው በልማት ሲፈርስ አሁን ወደሚገኝበት ቦታ ተዛውሯል።
በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ «ኤፍሬም ውስኪ» በሚል ትልቅ ስም ሊገነቡ የቻሉበትን ሚስጥር ሲያስረዱ፣ አስቀድመው ይሠሩበት ከነበረው ቤት የተማሩትንና ያደጉበትን ለንጹህ ነገር የመገዛትና ያለመደራደር እሴት እንደሆነ ገልጸዋል።
ሆቴሉ ዘመናዊ አሠራርና ሲስተም ያለው ቢሆንም፣ አቶ ኤፍሬም ግን አሁንም ያንን የቆየውን፣ ታዋቂው ደራሲ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር የጻፈበትን የደጃችሁ ቤት (ውቤ በረሃ) ፍቅር፣ ክብር፣ አንድነትና ማኅበራዊ ትስስር እንዳስቀጠሉበት ይናገራሉ።
በምረቃው ዕለትም የታደሙት ታላላቅ እንግዶች አብረዋቸው የ32 እና የ20 ዓመታት የሕይወት ታሪክ ያላቸው የቅርብ ወዳጆቻቸውና እንደ ቤተሰብ የሚቆጠሩ ደንበኞቻቸው ናቸው።
በመጨረሻም፣ ሆቴሉ ለደረሰበት የዕድገት ደረጃ ዓለም አቀፉ የመጠጥ አምራች ኩባንያ ዲያጆ ላደረገላቸው ዘላቂ የስፖንሰርሺፕና የድጋፍ አጋርነት አቶ ኤፍሬም ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
Sponsored by
Surafel
14 days ago
በሰሜን ሸዋ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ለብልፅግና ፓርቲ የድጋፍና የቅስቀሳ ሰልፎች ተካሄዱ
****************
በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች "በላቀ የወጣቶች ተሳትፎ፤ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!" በሚል መሪ ሀሳብ በርካታ ወጣቶች የተሳተፉባቸው የብልፅግና ፓርቲ የድጋፍና የጎዳና ላይ የምረጡኝ ቅስቀሳ ሰልፎች ተካሂደዋል።
እነዚህ የድጋፍ ሰልፎች በዞኑ ስር በሚገኙ በጣርማበር፣ አሳግርት እና አንጾኪያ ገምዛ ወረዳዎች የተከናወኑ ሲሆን የየአካባቢው ወጣቶች በነቂስ በመውጣት ለፓርቲው ያላቸውን አጋርነት በተግባር አሳይተዋል።
ሰልፈኞቹ ባስተላለፉት መልዕክት መጪው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሀዊ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ወጣቶች ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው መህለጻቸውን የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።
በተጨማሪም ወጣቶች ያለምንም ችግር ድምጻቸውን በመስጠትና በምርጫው ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ኢትዮጵያን የማሻገርና የማጽናት ታሪካዊ አደራቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
#ethiopianelection2026 #ethiopianbroadcastingcorporation
****************
በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች "በላቀ የወጣቶች ተሳትፎ፤ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!" በሚል መሪ ሀሳብ በርካታ ወጣቶች የተሳተፉባቸው የብልፅግና ፓርቲ የድጋፍና የጎዳና ላይ የምረጡኝ ቅስቀሳ ሰልፎች ተካሂደዋል።
እነዚህ የድጋፍ ሰልፎች በዞኑ ስር በሚገኙ በጣርማበር፣ አሳግርት እና አንጾኪያ ገምዛ ወረዳዎች የተከናወኑ ሲሆን የየአካባቢው ወጣቶች በነቂስ በመውጣት ለፓርቲው ያላቸውን አጋርነት በተግባር አሳይተዋል።
ሰልፈኞቹ ባስተላለፉት መልዕክት መጪው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሀዊ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ወጣቶች ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው መህለጻቸውን የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።
በተጨማሪም ወጣቶች ያለምንም ችግር ድምጻቸውን በመስጠትና በምርጫው ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ኢትዮጵያን የማሻገርና የማጽናት ታሪካዊ አደራቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
#ethiopianelection2026 #ethiopianbroadcastingcorporation
14 days ago
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ ተጀመረ
#ethiopia | በከባድ የልብ ሕመም ለሚሰቃዩ ሕፃናት ተስፋና ፈውስን ይዞ የመጣውና ለሦስት ቀናት የሚቆየው የነፃ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዛሬ በይፋ መካሄድ ጀምሯል።
ለዚህ ታላቅ ሰብአዊ ተልዕኮ ወደ ስፍራው ለገሰገሰው ዓለም አቀፍ የሕክምና ቡድን ዛሬ ጠዋት ደማቅ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት የተደረገለት ሲሆን፣ ቡድኑም የሕይወት አድን ሥራውን ወዲያውኑ አግልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ይህ አገር አቀፍ ጠቀሜታ ያለው ተነሳሽነት ሊሳካ የቻለው በHeart to Heart Children’s Aid፣ በኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል፣ በፓድሬ ፒዮ ኢጣሊያ፣ በኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር እና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ መካከል በተደረገ ጠንካራ ትብብር ሲሆን፣ ይህም በኢትዮጵያ ለሚገኙ የልብ ህመም ተጋላጭ ለሆኑ ሕፃናት ልዩ የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የታሰበ መሆኑ ተገልጿል።
በዛሬው ዕለት ሥራቸውን በይፋ የጀመሩት ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ዓለም አቀፍ የልብ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስቶችና የሕክምና ባለሙያዎች፣ የላቀ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምናና ልዩ የልብ ሕክምና አገልግሎቶችን ለሕጻናቱ ሙሉ በሙሉ መሆኑን ጎንደር ዩኒቨርስቲ ገልጿል።
በዚህ ወሳኝ የሕክምና ዘመቻ ወደ 20 የሚጠጉ ሕፃናት ቀጥተኛ የጤና ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ዘመቻ በአሁኑ ወቅት ሕጻናቱን ያለ ምንም ክፍያ ከማከም ባለፈ፣ ወደፊት አገሪቱ በዘርፉ ራሷን እንድትችል በዓለም አቀፍ ባለሙያዎችና በአገር ውስጥ የጤና ባለሙያዎች መካከል የእውቀትና የባለሙያ ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ይሰጣል ተብላል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን ዛሬ ለህክምና ቡድኑ ባደረጉት የአቀባበል መርሐ ግብር ላይ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የተቀበሉ ሲሆን፣ ለሁሉም አጋር ድርጅቶች ስላሳዩት ሰብአዊነትና ፈጣን ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ይህ ተነሳሽነት የዓለም አቀፍ አጋርነት፣ የርኅራኄ እና የሕክምና አንድነት ትልቅ ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ ወደፊት በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የሕፃናት ልብ ሕክምና አገልግሎትን በዘላቂነት ለመገንባትና ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ብለዋል።
በተጨማሪም ዘመቻው የሕፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ ለቤተሰቦቻቸው ተስፋን የሚመልስና የሕፃናትን ጤናና የወደፊት ሕይወት ለመጠበቅ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | በከባድ የልብ ሕመም ለሚሰቃዩ ሕፃናት ተስፋና ፈውስን ይዞ የመጣውና ለሦስት ቀናት የሚቆየው የነፃ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዛሬ በይፋ መካሄድ ጀምሯል።
ለዚህ ታላቅ ሰብአዊ ተልዕኮ ወደ ስፍራው ለገሰገሰው ዓለም አቀፍ የሕክምና ቡድን ዛሬ ጠዋት ደማቅ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት የተደረገለት ሲሆን፣ ቡድኑም የሕይወት አድን ሥራውን ወዲያውኑ አግልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ይህ አገር አቀፍ ጠቀሜታ ያለው ተነሳሽነት ሊሳካ የቻለው በHeart to Heart Children’s Aid፣ በኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል፣ በፓድሬ ፒዮ ኢጣሊያ፣ በኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር እና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ መካከል በተደረገ ጠንካራ ትብብር ሲሆን፣ ይህም በኢትዮጵያ ለሚገኙ የልብ ህመም ተጋላጭ ለሆኑ ሕፃናት ልዩ የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የታሰበ መሆኑ ተገልጿል።
በዛሬው ዕለት ሥራቸውን በይፋ የጀመሩት ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ዓለም አቀፍ የልብ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስቶችና የሕክምና ባለሙያዎች፣ የላቀ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምናና ልዩ የልብ ሕክምና አገልግሎቶችን ለሕጻናቱ ሙሉ በሙሉ መሆኑን ጎንደር ዩኒቨርስቲ ገልጿል።
በዚህ ወሳኝ የሕክምና ዘመቻ ወደ 20 የሚጠጉ ሕፃናት ቀጥተኛ የጤና ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ዘመቻ በአሁኑ ወቅት ሕጻናቱን ያለ ምንም ክፍያ ከማከም ባለፈ፣ ወደፊት አገሪቱ በዘርፉ ራሷን እንድትችል በዓለም አቀፍ ባለሙያዎችና በአገር ውስጥ የጤና ባለሙያዎች መካከል የእውቀትና የባለሙያ ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ይሰጣል ተብላል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን ዛሬ ለህክምና ቡድኑ ባደረጉት የአቀባበል መርሐ ግብር ላይ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የተቀበሉ ሲሆን፣ ለሁሉም አጋር ድርጅቶች ስላሳዩት ሰብአዊነትና ፈጣን ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ይህ ተነሳሽነት የዓለም አቀፍ አጋርነት፣ የርኅራኄ እና የሕክምና አንድነት ትልቅ ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ ወደፊት በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የሕፃናት ልብ ሕክምና አገልግሎትን በዘላቂነት ለመገንባትና ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ብለዋል።
በተጨማሪም ዘመቻው የሕፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ ለቤተሰቦቻቸው ተስፋን የሚመልስና የሕፃናትን ጤናና የወደፊት ሕይወት ለመጠበቅ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
15 days ago
በጎንደር ነፃ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ ተጀመረ
#fastmereja በከባድ የልብ ሕመም ለሚሰቃዩ ሕፃናት ተስፋና ፈውስን ይዞ የመጣውና ለሦስት ቀናት የሚቆየው የነፃ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዛሬ በይፋ መካሄድ ጀምሯል። ለዚህ ታላቅ ሰብአዊ ተልዕኮ ወደ ስፍራው ለገሰገሰው ዓለም አቀፍ የሕክምና ቡድን ዛሬ ጠዋት ደማቅ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት የተደረገለት ሲሆን፣ ቡድኑም ወዲያውኑ ሥራውን በይፋ አስጀምሯል። ይህ ሕይወት አታራፊ ተነሳሽነት ሊሳካ የቻለው በHeart to Heart Children’s Aid፣ በኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል፣ በፓድሬ ፒዮ ኢጣሊያ፣ በኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር እና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ መካከል በተደረገ ጠንካራ ትብብር ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ተጋላጭ ሕፃናት ልዩ የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተፈጠረውን የጋራ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው።
በዛሬው ዕለት ሥራቸውን በይፋ የጀመሩት ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ዓለም አቀፍ የልብ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስቶችና የሕክምና ባለሙያዎች፣ የላቀ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምናና ልዩ የልብ ሕክምና አገልግሎቶችን ለሕጻናቱ ሙሉ በሙሉ በነፃ መስጠት ጀምረዋል። በዚህ ወሳኝ የሕክምና ጣልቃ ገብነት ወደ 20 የሚጠጉ ሕፃናት ቀጥተኛ ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ዘመቻ በአሁኑ ወቅት ሕጻናቱን በነፃ ከማከም ባለፈ፣ ወደፊት አገሪቱ በዘርፉ ራሷን እንድትችል በዓለም አቀፍ ባለሙያዎችና በአገር ውስጥ የጤና ባለሙያዎች መካከል የእውቀትና የባለሙያ ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ዛሬውኑ ትልቅ ዕድልና መሠረት እየጣለ ይገኛል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን ዛሬ በነበረው የአቀባበል መርሐ-ግብር ላይ ዓለም አቀፉን የሕክምና ቡድን ከፍተኛ አክብሮት ባለው ስሜት እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የተቀበሉ ሲሆን፥ ለሁሉም አጋር ድርጅቶች ስላሳዩት ሰብአዊነትና ፈጣን ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ይህ ተነሳሽነት የዓለም አቀፍ አጋርነት፣ የርኅራኄ እና የሕክምና አንድነት ትልቅ ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ ወደፊት በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የሕፃናት ልብ ሕክምና አገልግሎትን በዘላቂነት ለመገንባትና ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ብለዋል። በተጨማሪም ዘመቻው የሕፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ ለቤተሰቦቻቸው ተስፋን የሚመልስና የሕፃናትን ጤናና የወደፊት ሕይወት ለመጠበቅ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል::
#fastmereja በከባድ የልብ ሕመም ለሚሰቃዩ ሕፃናት ተስፋና ፈውስን ይዞ የመጣውና ለሦስት ቀናት የሚቆየው የነፃ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዛሬ በይፋ መካሄድ ጀምሯል። ለዚህ ታላቅ ሰብአዊ ተልዕኮ ወደ ስፍራው ለገሰገሰው ዓለም አቀፍ የሕክምና ቡድን ዛሬ ጠዋት ደማቅ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት የተደረገለት ሲሆን፣ ቡድኑም ወዲያውኑ ሥራውን በይፋ አስጀምሯል። ይህ ሕይወት አታራፊ ተነሳሽነት ሊሳካ የቻለው በHeart to Heart Children’s Aid፣ በኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል፣ በፓድሬ ፒዮ ኢጣሊያ፣ በኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር እና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ መካከል በተደረገ ጠንካራ ትብብር ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ተጋላጭ ሕፃናት ልዩ የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተፈጠረውን የጋራ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው።
በዛሬው ዕለት ሥራቸውን በይፋ የጀመሩት ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ዓለም አቀፍ የልብ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስቶችና የሕክምና ባለሙያዎች፣ የላቀ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምናና ልዩ የልብ ሕክምና አገልግሎቶችን ለሕጻናቱ ሙሉ በሙሉ በነፃ መስጠት ጀምረዋል። በዚህ ወሳኝ የሕክምና ጣልቃ ገብነት ወደ 20 የሚጠጉ ሕፃናት ቀጥተኛ ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ዘመቻ በአሁኑ ወቅት ሕጻናቱን በነፃ ከማከም ባለፈ፣ ወደፊት አገሪቱ በዘርፉ ራሷን እንድትችል በዓለም አቀፍ ባለሙያዎችና በአገር ውስጥ የጤና ባለሙያዎች መካከል የእውቀትና የባለሙያ ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ዛሬውኑ ትልቅ ዕድልና መሠረት እየጣለ ይገኛል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን ዛሬ በነበረው የአቀባበል መርሐ-ግብር ላይ ዓለም አቀፉን የሕክምና ቡድን ከፍተኛ አክብሮት ባለው ስሜት እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የተቀበሉ ሲሆን፥ ለሁሉም አጋር ድርጅቶች ስላሳዩት ሰብአዊነትና ፈጣን ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ይህ ተነሳሽነት የዓለም አቀፍ አጋርነት፣ የርኅራኄ እና የሕክምና አንድነት ትልቅ ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ ወደፊት በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የሕፃናት ልብ ሕክምና አገልግሎትን በዘላቂነት ለመገንባትና ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ብለዋል። በተጨማሪም ዘመቻው የሕፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ ለቤተሰቦቻቸው ተስፋን የሚመልስና የሕፃናትን ጤናና የወደፊት ሕይወት ለመጠበቅ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል::
15 days ago
ብልጽግና ፓርቲ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሄደ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብልጽግና ፓርቲ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብር አካሂዷል።
የፓርቲው የምርጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብር “በጸና እና በተደራጀ የሴቶች ድምጽ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር እናሻግራለን” በሚል መሪ ሃሳብ ነው የተካሄደው፡፡
የምረጡኝ ቅስቀሳው በደብረ ማርቆስ፣ ላሊበላ፣ ዱርቤቴ፣ ሸዋሮቢት፣ ደንበጫ፣ ደብረታቦር፣ ወረኢሉ፣ አዴት፣ ደብረሲና፣ ወረታ፣ አጣዬ፣ ግንደወይን እና ሌሎች ከተሞች መከናወኑ ተመልክቷል፡፡
በምርጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብሩ ላይ በየአካባቢዎቹ የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ አባላት እና ደጋፊዎች እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡
በዚህ ወቅትም ብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ የሚሠራ ሀገራዊ ፓርቲ መሆኑን የሚያንጸባርቁ መልዕክቶች ተላልፈዋል፡፡
ተሳታፊዎቹ ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ጽኑ አጋርነት በመግለጽ ÷ ፓርቲው የጀመራቸውን የልማት፣ የሰላምና የብልጽግና ሥራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ሕጋዊ እና የጸና ሀገረ መንግሥት ለመመስረት ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸውም በመርሐ ግብሩ ላይ ተጠቁሟል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብልጽግና ፓርቲ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብር አካሂዷል።
የፓርቲው የምርጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብር “በጸና እና በተደራጀ የሴቶች ድምጽ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር እናሻግራለን” በሚል መሪ ሃሳብ ነው የተካሄደው፡፡
የምረጡኝ ቅስቀሳው በደብረ ማርቆስ፣ ላሊበላ፣ ዱርቤቴ፣ ሸዋሮቢት፣ ደንበጫ፣ ደብረታቦር፣ ወረኢሉ፣ አዴት፣ ደብረሲና፣ ወረታ፣ አጣዬ፣ ግንደወይን እና ሌሎች ከተሞች መከናወኑ ተመልክቷል፡፡
በምርጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብሩ ላይ በየአካባቢዎቹ የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ አባላት እና ደጋፊዎች እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡
በዚህ ወቅትም ብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ የሚሠራ ሀገራዊ ፓርቲ መሆኑን የሚያንጸባርቁ መልዕክቶች ተላልፈዋል፡፡
ተሳታፊዎቹ ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ጽኑ አጋርነት በመግለጽ ÷ ፓርቲው የጀመራቸውን የልማት፣ የሰላምና የብልጽግና ሥራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ሕጋዊ እና የጸና ሀገረ መንግሥት ለመመስረት ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸውም በመርሐ ግብሩ ላይ ተጠቁሟል፡፡
16 days ago
ድምፃዊ ሳሚ ዳን ለፕሪሚየር ሊግ አሸናፊው አርሰናል አዲስ የደስታ መግለጫ ሙዚቃ ሊለቅ ነዉ
ድምፃዊ ሳሚ ዳን ለፕሪሚየር ሊግ ዋንጫው ባለቤት አርሰናል አዲስ የደስታ መግለጫ ሙዚቃ ሊለቅ መሆኑን አስታወቀ።
ድምፃዊ ሳሚ ዳን መድፈኞቹ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የኢንግሊሽ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማንሳታቸውን ተከትሎ፣ ዛሬ ምሽት 12:00 ሰዓት ላይ አዲስ ልዩ የደስታ መግለጫ ሙዚቃ ለአድማጮች እንደሚያደርስ ይፋ አድርጓል።
ታዋቂው ድምፃዊ ለአርሰናል ክለብ ያለውን ጥልቅ ፍቅርና አጋርነት በገለጸበት ማስታወቂያው፥ My አርሴ እማ አንድ ሙዚቃማ ይገባታል!!! 12 ሰዓት 🙌”በማለት የስሜቱን መጋፈል የገለጸ ሲሆን፣ ሙዚቃው ክለቡና ደጋፊዎቹ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ያሳለፉትን ውጣ ውረድና አሁን የተቀዳጁትን ታላቅ ድል የሚያጣጥም እንደሚሆን ይጠበቃል።
የአርሰናልን የዋንጫ ድል ተከትሎ በርካታ ታዋቂ ሰዎችና ከያንያን ደስታቸውን እየገለጹ በሚገኙበት በዚህ ወቅት፣ በሳሚ ዳን የሚለቀቀው አዲስ ዜማ በማህበራዊ ሚዲያ እና በስፖርት አፍቃሪው ዘንድ ከፍተኛ ጉጉትን ፈጥሯል።Via ጉርሻ page
seledadotio
seledadotio
ድምፃዊ ሳሚ ዳን ለፕሪሚየር ሊግ ዋንጫው ባለቤት አርሰናል አዲስ የደስታ መግለጫ ሙዚቃ ሊለቅ መሆኑን አስታወቀ።
ድምፃዊ ሳሚ ዳን መድፈኞቹ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የኢንግሊሽ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማንሳታቸውን ተከትሎ፣ ዛሬ ምሽት 12:00 ሰዓት ላይ አዲስ ልዩ የደስታ መግለጫ ሙዚቃ ለአድማጮች እንደሚያደርስ ይፋ አድርጓል።
ታዋቂው ድምፃዊ ለአርሰናል ክለብ ያለውን ጥልቅ ፍቅርና አጋርነት በገለጸበት ማስታወቂያው፥ My አርሴ እማ አንድ ሙዚቃማ ይገባታል!!! 12 ሰዓት 🙌”በማለት የስሜቱን መጋፈል የገለጸ ሲሆን፣ ሙዚቃው ክለቡና ደጋፊዎቹ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ያሳለፉትን ውጣ ውረድና አሁን የተቀዳጁትን ታላቅ ድል የሚያጣጥም እንደሚሆን ይጠበቃል።
የአርሰናልን የዋንጫ ድል ተከትሎ በርካታ ታዋቂ ሰዎችና ከያንያን ደስታቸውን እየገለጹ በሚገኙበት በዚህ ወቅት፣ በሳሚ ዳን የሚለቀቀው አዲስ ዜማ በማህበራዊ ሚዲያ እና በስፖርት አፍቃሪው ዘንድ ከፍተኛ ጉጉትን ፈጥሯል።Via ጉርሻ page
seledadotio
seledadotio
16 days ago
ኢትዮጵያ እና ኳታር የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ አጋርነት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገለጹ
*****************
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ከኳታር ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ መሐመድ ቢን አብዱልራህማን ቢን ጃሲም አል ታኒ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
በውይይቱ ወቅት በኢትዮጵያ እና በኳታር መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።
ሁለቱ ወገኖች መደበኛ የፖለቲካ ምክክሮችን በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትብብርን በማጠናከር እና የግል ዘርፍ ኢንቨስትመንትን በማሳደግ ረገድ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ አጋርነት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም በአፍሪካ ቀንድ፣ በባህረ ሰላጤው ቀጣና እና ከዚያም ባሻገር ቀጣናዊ ሰላምና ደህንነትን ለማስፈን የሚደረጉ የጋራ ጥረቶችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
#ethiopia #qatar #bilateral #partnership #ebc
*****************
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ከኳታር ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ መሐመድ ቢን አብዱልራህማን ቢን ጃሲም አል ታኒ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
በውይይቱ ወቅት በኢትዮጵያ እና በኳታር መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።
ሁለቱ ወገኖች መደበኛ የፖለቲካ ምክክሮችን በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትብብርን በማጠናከር እና የግል ዘርፍ ኢንቨስትመንትን በማሳደግ ረገድ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ አጋርነት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም በአፍሪካ ቀንድ፣ በባህረ ሰላጤው ቀጣና እና ከዚያም ባሻገር ቀጣናዊ ሰላምና ደህንነትን ለማስፈን የሚደረጉ የጋራ ጥረቶችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
#ethiopia #qatar #bilateral #partnership #ebc
Sponsored by
Surafel
17 days ago
በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን የተዘጋጀው ይፋዊ የዲጂታል ገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ሊካሄድ ነው።
👉ተቋማቱ የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ
በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን በጋራ የተዘጋጀው ይፋዊ የገቢ ማሰባሰቢያ የመክፈቻ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማትም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ልዩ መርሃ-ግብር ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ግልጽነት ባለው እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፉ ዲጂታል የለጋሽነት መፍትሄዎች አማካኝነት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰብአዊ እና ማህበረሰባዊ እገዛዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ ያለመ ስትራቴጂካዊ የገቢ ማሰባሰብ አጋርነት መጀመሩን አብስረዋል።
በዕለቱም አይራብ ዶኔሽን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ለጋሾች በቴሌብር ሱፐር አፕ እና በአይራብ ዶኔሽን ድረ-ገጽ አማካኝነት በቀላሉና በአስተማማኝ ሁኔታ መዋጮ ማድረግ የሚችሉበትን ምቹ ዲጂታል አሰራር በጉልህ የሚያሳይ ይሆናል።
የአይራብ ቴክ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (AYRAB TECH SOLUTION PLC) መስራች አቶ ቢኒያም ፈቃዱ እና የጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር መሌቻ ሎጄ ህዝቡ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ በዚህ ሰብአዊ ስራ ላይ ከጎናቸው እንዲሆንና አጋርነቱን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጃታኒ አሊ ፋውንዴሽን በአርቆ አሳቢው ሻለቃ ጃታኒ አሊ ማስታወሻነት የተመሰረተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲችል፣ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ እንዲገነባ እና ዘላቂ ልማት እንዲፈጠር በትምህርት፣ በውሃ፣ በጤና እና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በትጋት እየሰራ ነው።
ዛሬ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚና በተለያዩ ሀገር የሃላፊነት ቦታዎች የሚያገለግሉ ብዙ ግለሰቦች ሻለቃ ጃታኒ አሊ በተቋቋመው ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ ይህም የፋውንዴሽኑ ትውልድ የሚቀይር ራዕይ ህያው ማስረጃ ነው።
የእርስዎ ድጋፍ አንድ ልጅ እንዲማር፣ አንድ ቤተሰብ ተስፋ እንዲያገኝ እና አንድ ማህበረሰብ በራሱ እግር እንዲቆም ያግዛል።
ዛሬ ይቀላቀሉ ፣ ይደግፉ ፣ዘላቂ ለውጥ ይፍጠሩ። ሲሉ ጥሪያቸውንም አስተላልፈዋል።
እንዲሁም: በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ በሚገኘው አይራብ(AYRAB) አፕ ላይ እና በአይራብ ዶኔሽን ( https://donate.ayrabtech.c... ) ሊንክ በመግባት በቀላሉ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮዽያ ወዳጆች በቀላሉ የፈለጉትን እና የቻሉትን ያህል መለገስ የሚችሉ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ትልቅ ሰብአዊ እቅድ በይፋ ለመጀመር በሚሰናዳው በዚሁ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎች፣ የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ ስብዕናዎች እና ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል።
👉ተቋማቱ የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ
በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን በጋራ የተዘጋጀው ይፋዊ የገቢ ማሰባሰቢያ የመክፈቻ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማትም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ልዩ መርሃ-ግብር ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ግልጽነት ባለው እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፉ ዲጂታል የለጋሽነት መፍትሄዎች አማካኝነት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰብአዊ እና ማህበረሰባዊ እገዛዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ ያለመ ስትራቴጂካዊ የገቢ ማሰባሰብ አጋርነት መጀመሩን አብስረዋል።
በዕለቱም አይራብ ዶኔሽን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ለጋሾች በቴሌብር ሱፐር አፕ እና በአይራብ ዶኔሽን ድረ-ገጽ አማካኝነት በቀላሉና በአስተማማኝ ሁኔታ መዋጮ ማድረግ የሚችሉበትን ምቹ ዲጂታል አሰራር በጉልህ የሚያሳይ ይሆናል።
የአይራብ ቴክ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (AYRAB TECH SOLUTION PLC) መስራች አቶ ቢኒያም ፈቃዱ እና የጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር መሌቻ ሎጄ ህዝቡ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ በዚህ ሰብአዊ ስራ ላይ ከጎናቸው እንዲሆንና አጋርነቱን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጃታኒ አሊ ፋውንዴሽን በአርቆ አሳቢው ሻለቃ ጃታኒ አሊ ማስታወሻነት የተመሰረተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲችል፣ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ እንዲገነባ እና ዘላቂ ልማት እንዲፈጠር በትምህርት፣ በውሃ፣ በጤና እና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በትጋት እየሰራ ነው።
ዛሬ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚና በተለያዩ ሀገር የሃላፊነት ቦታዎች የሚያገለግሉ ብዙ ግለሰቦች ሻለቃ ጃታኒ አሊ በተቋቋመው ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ ይህም የፋውንዴሽኑ ትውልድ የሚቀይር ራዕይ ህያው ማስረጃ ነው።
የእርስዎ ድጋፍ አንድ ልጅ እንዲማር፣ አንድ ቤተሰብ ተስፋ እንዲያገኝ እና አንድ ማህበረሰብ በራሱ እግር እንዲቆም ያግዛል።
ዛሬ ይቀላቀሉ ፣ ይደግፉ ፣ዘላቂ ለውጥ ይፍጠሩ። ሲሉ ጥሪያቸውንም አስተላልፈዋል።
እንዲሁም: በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ በሚገኘው አይራብ(AYRAB) አፕ ላይ እና በአይራብ ዶኔሽን ( https://donate.ayrabtech.c... ) ሊንክ በመግባት በቀላሉ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮዽያ ወዳጆች በቀላሉ የፈለጉትን እና የቻሉትን ያህል መለገስ የሚችሉ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ትልቅ ሰብአዊ እቅድ በይፋ ለመጀመር በሚሰናዳው በዚሁ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎች፣ የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ ስብዕናዎች እና ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል።
17 days ago
በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን የተዘጋጀው ይፋዊ የዲጂታል ገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ሊካሄድ ነው
📌ተቋማቱ የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን በጋራ የተዘጋጀው ይፋዊ የገቢ ማሰባሰቢያ የመክፈቻ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማትም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ልዩ መርሃ-ግብር ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ግልጽነት ባለው እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፉ ዲጂታል የለጋሽነት መፍትሄዎች አማካኝነት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰብአዊ እና ማህበረሰባዊ እገዛዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ ያለመ ስትራቴጂካዊ የገቢ ማሰባሰብ አጋርነት መጀመሩን አብስረዋል።
በዕለቱም አይራብ ዶኔሽን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ለጋሾች በቴሌብር ሱፐር አፕ እና በአይራብ ዶኔሽን ድረ-ገጽ አማካኝነት በቀላሉና በአስተማማኝ ሁኔታ መዋጮ ማድረግ የሚችሉበትን ምቹ ዲጂታል አሰራር በጉልህ የሚያሳይ ይሆናል።
የአይራብ ቴክ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (AYRAB TECH SOLUTION PLC) መስራች አቶ ቢኒያም ፈቃዱ እና የጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር መሌቻ ሎጄ ህዝቡ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ በዚህ ሰብአዊ ስራ ላይ ከጎናቸው እንዲሆንና አጋርነቱን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጃታኒ አሊ ፋውንዴሽን በአርቆ አሳቢው ሻለቃ ጃታኒ አሊ ማስታወሻነት የተመሰረተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲችል፣ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ እንዲገነባ እና ዘላቂ ልማት እንዲፈጠር በትምህርት፣ በውሃ፣ በጤና እና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በትጋት እየሰራ ነው።
ዛሬ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚና በተለያዩ ሀገር የሃላፊነት ቦታዎች የሚያገለግሉ ብዙ ግለሰቦች ሻለቃ ጃታኒ አሊ በተቋቋመው ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ ይህም የፋውንዴሽኑ ትውልድ የሚቀይር ራዕይ ህያው ማስረጃ ነው።
የእርስዎ ድጋፍ አንድ ልጅ እንዲማር፣ አንድ ቤተሰብ ተስፋ እንዲያገኝ እና አንድ ማህበረሰብ በራሱ እግር እንዲቆም ያግዛል።
ዛሬ ይቀላቀሉ ፣ ይደግፉ ፣ዘላቂ ለውጥ ይፍጠሩ። ሲሉ ጥሪያቸውንም አስተላልፈዋል።
እንዲሁም: በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ በሚገኘው አይራብ(AYRAB) አፕ ላይ እና በአይራብ ዶኔሽን ( https://donate.ayrabtech.c... ) ሊንክ በመግባት በቀላሉ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮዽያ ወዳጆች በቀላሉ የፈለጉትን እና የቻሉትን ያህል መለገስ የሚችሉ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ትልቅ ሰብአዊ እቅድ በይፋ ለመጀመር በሚሰናዳው በዚሁ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎች፣ የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ ስብዕናዎች እና ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia #ayrabdonation #jatanialifoundation #digitalfundraising #techforgood #humanitarianaid #telebirr #addisababa #socialimpact #ethiopiannews
📌ተቋማቱ የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን በጋራ የተዘጋጀው ይፋዊ የገቢ ማሰባሰቢያ የመክፈቻ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማትም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ልዩ መርሃ-ግብር ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ግልጽነት ባለው እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፉ ዲጂታል የለጋሽነት መፍትሄዎች አማካኝነት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰብአዊ እና ማህበረሰባዊ እገዛዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ ያለመ ስትራቴጂካዊ የገቢ ማሰባሰብ አጋርነት መጀመሩን አብስረዋል።
በዕለቱም አይራብ ዶኔሽን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ለጋሾች በቴሌብር ሱፐር አፕ እና በአይራብ ዶኔሽን ድረ-ገጽ አማካኝነት በቀላሉና በአስተማማኝ ሁኔታ መዋጮ ማድረግ የሚችሉበትን ምቹ ዲጂታል አሰራር በጉልህ የሚያሳይ ይሆናል።
የአይራብ ቴክ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (AYRAB TECH SOLUTION PLC) መስራች አቶ ቢኒያም ፈቃዱ እና የጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር መሌቻ ሎጄ ህዝቡ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ በዚህ ሰብአዊ ስራ ላይ ከጎናቸው እንዲሆንና አጋርነቱን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጃታኒ አሊ ፋውንዴሽን በአርቆ አሳቢው ሻለቃ ጃታኒ አሊ ማስታወሻነት የተመሰረተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲችል፣ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ እንዲገነባ እና ዘላቂ ልማት እንዲፈጠር በትምህርት፣ በውሃ፣ በጤና እና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በትጋት እየሰራ ነው።
ዛሬ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚና በተለያዩ ሀገር የሃላፊነት ቦታዎች የሚያገለግሉ ብዙ ግለሰቦች ሻለቃ ጃታኒ አሊ በተቋቋመው ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ ይህም የፋውንዴሽኑ ትውልድ የሚቀይር ራዕይ ህያው ማስረጃ ነው።
የእርስዎ ድጋፍ አንድ ልጅ እንዲማር፣ አንድ ቤተሰብ ተስፋ እንዲያገኝ እና አንድ ማህበረሰብ በራሱ እግር እንዲቆም ያግዛል።
ዛሬ ይቀላቀሉ ፣ ይደግፉ ፣ዘላቂ ለውጥ ይፍጠሩ። ሲሉ ጥሪያቸውንም አስተላልፈዋል።
እንዲሁም: በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ በሚገኘው አይራብ(AYRAB) አፕ ላይ እና በአይራብ ዶኔሽን ( https://donate.ayrabtech.c... ) ሊንክ በመግባት በቀላሉ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮዽያ ወዳጆች በቀላሉ የፈለጉትን እና የቻሉትን ያህል መለገስ የሚችሉ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ትልቅ ሰብአዊ እቅድ በይፋ ለመጀመር በሚሰናዳው በዚሁ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎች፣ የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ ስብዕናዎች እና ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia #ayrabdonation #jatanialifoundation #digitalfundraising #techforgood #humanitarianaid #telebirr #addisababa #socialimpact #ethiopiannews
17 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በካሊፎርኒያ ግዛት በሳን ዲዬጎ ከተማ በሚገኘው ታላቁ መስጂድ ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ጥቃት ተከትሎ፣ የሳን ዲዬጎ የካቶሊክ ዲዮሴስ ከሙስሊሙ ማህበረሰብ ጋር በኅብረት እና በጸሎት አብሮ እንደሚቆም በይፋ አስታውቋል። የዲዮሴሱ ቢሾፍ ማይክል ፋም በዛሬው ዕለት ባወጡት መግለጫ፣ ድርጊቱን ምክንያት አልባ እና ዘግናኝ የጥቃት ድርጊት ሲሉ የኮነኑት ሲሆን፤ ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ለመላው የሙስሊም ማህበረሰብ ያላቸውን ጥልቅ መረዳት፣ አጋርነት እና ልባዊ ጸሎት አቅርበዋል።
ቢሾፍ ፋም በመግለጫቸው ላይ እንዳሰፈሩት፣ ጥቃቱ የተፈጸመበት የሳን ዲዬጎ እስላማዊ ማዕከል በተለይም ስደተኞችን በመደገፍ እና ፍትህን በማስፈን ረገድ ለረጅም ጊዜ አብሮአቸው የሠራ የቆየ የቅርብ አጋራቸው ነው። የአምልኮ ሥፍራዎች ሁልጊዜም የሰላም፣ የደህንነት እና የጸሎት መጠለያዎች መሆን እንዳለባቸው የጠቆሙት ቢሾፉ፣ በአንድ የእምነት ማህበረሰብ ላይ የሚሰነዘር ጥቃት በሰው ልጅ የተቀደሰ ክብር ላይ የተሰነዘረ ጥቃት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
በአሁኑ ወቅት የወጡ ዘ-ሐበሻ ያሰባሰባቸው ወቅታዊ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ በዚህ አሰቃቂ ጥቃት የጥበቃ ሰራተኛውን ጨምሮ የሦስት ንፁሃን ዜጎች ሕይወት አልፏል። የሳን ዲዬጎ ፖሊስ አዛዥ ስኮት ዋህል እንደገለጹት፣ ሕይወቱን የሰጠው ጥበቃ ሰራተኛ በወቅቱ ባሳየው እጅግ አስደናቂ የጀግንነት ተጋድሎ የብዙዎችን ሕይወት ማዳን ችሏል። ጥቃቱን ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩት የ17 እና የ18 ዓመት ሁለት ታዳጊዎች ከመስጂዱ አቅራቢያ በቆመ መኪና ውስጥ ራሳቸውን አጥፍተው ሞተው ተገኝተዋል።
ከተባባሪዎቹ መካከል አንዱ የ17 ዓመቱ ኬን ክላርክ መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ጥቃቱ ከመፈጸሙ ከሰዓታት በፊት እናቱ ልጇ፣ መኪናዋ እና ሦስት ገዳይ መሣሪያዎች አብረው መጥፋታቸውን ለፖሊስ አመልክታ ነበር። በአሁኑ ሰዓት የሕግ አስከባሪ አካላት ጥቃቱን የጥላቻ ወንጀል በማድረግ ምርመራቸውን በስፋት ቀጥለዋል። ለጥቃቱ ጥቅም ላይ ከዋሉት መሣሪያዎች በአንዱ ላይ የጥላቻ ንግግሮች ተፅፈው የተገኙ ሲሆን፣ ከተጠርጣሪዎቹ በአንዱ ቤት ውስጥ ደግሞ ስለ ዘር የበላይነት እና ኩራት የሚናገር የራስ ማጥፊያ ማስታወሻ መገኘቱን የደህንነት ባለሥልጣናት ለሲኤንኤን አረጋግጠዋል።
ቢሾፍ ፋም በመግለጫቸው ላይ እንዳሰፈሩት፣ ጥቃቱ የተፈጸመበት የሳን ዲዬጎ እስላማዊ ማዕከል በተለይም ስደተኞችን በመደገፍ እና ፍትህን በማስፈን ረገድ ለረጅም ጊዜ አብሮአቸው የሠራ የቆየ የቅርብ አጋራቸው ነው። የአምልኮ ሥፍራዎች ሁልጊዜም የሰላም፣ የደህንነት እና የጸሎት መጠለያዎች መሆን እንዳለባቸው የጠቆሙት ቢሾፉ፣ በአንድ የእምነት ማህበረሰብ ላይ የሚሰነዘር ጥቃት በሰው ልጅ የተቀደሰ ክብር ላይ የተሰነዘረ ጥቃት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
በአሁኑ ወቅት የወጡ ዘ-ሐበሻ ያሰባሰባቸው ወቅታዊ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ በዚህ አሰቃቂ ጥቃት የጥበቃ ሰራተኛውን ጨምሮ የሦስት ንፁሃን ዜጎች ሕይወት አልፏል። የሳን ዲዬጎ ፖሊስ አዛዥ ስኮት ዋህል እንደገለጹት፣ ሕይወቱን የሰጠው ጥበቃ ሰራተኛ በወቅቱ ባሳየው እጅግ አስደናቂ የጀግንነት ተጋድሎ የብዙዎችን ሕይወት ማዳን ችሏል። ጥቃቱን ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩት የ17 እና የ18 ዓመት ሁለት ታዳጊዎች ከመስጂዱ አቅራቢያ በቆመ መኪና ውስጥ ራሳቸውን አጥፍተው ሞተው ተገኝተዋል።
ከተባባሪዎቹ መካከል አንዱ የ17 ዓመቱ ኬን ክላርክ መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ጥቃቱ ከመፈጸሙ ከሰዓታት በፊት እናቱ ልጇ፣ መኪናዋ እና ሦስት ገዳይ መሣሪያዎች አብረው መጥፋታቸውን ለፖሊስ አመልክታ ነበር። በአሁኑ ሰዓት የሕግ አስከባሪ አካላት ጥቃቱን የጥላቻ ወንጀል በማድረግ ምርመራቸውን በስፋት ቀጥለዋል። ለጥቃቱ ጥቅም ላይ ከዋሉት መሣሪያዎች በአንዱ ላይ የጥላቻ ንግግሮች ተፅፈው የተገኙ ሲሆን፣ ከተጠርጣሪዎቹ በአንዱ ቤት ውስጥ ደግሞ ስለ ዘር የበላይነት እና ኩራት የሚናገር የራስ ማጥፊያ ማስታወሻ መገኘቱን የደህንነት ባለሥልጣናት ለሲኤንኤን አረጋግጠዋል።
17 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ ሳን ዲዬጎ እስላማዊ ማዕከል (መስጂድ) ላይ በተሰነዘረው የጥላቻ ጥቃት ሕይወቱን ያጣው ጀግና የጥበቃ ሰራተኛ አሚን አብዱላህ መሆኑ በይፋ ተረጋገጠ። ዘ-ሐበሻ እንደተመለከተው የሳን ዲዬጎ እስላማዊ ማዕከል እና የአሜሪካ-እስላማዊ ግንኙነት ምክር ቤት በጋራ በመሆን ለሟቹ ቤተሰቦች ያዘጋጁት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዘመቻ በአጭር ጊዜ ውስጥ 1.4 ሚሊዮን ዶላር ሊጠጋ ችሏል።
ለገንዘብ ማሰባሰቢያው በተከፈተው ገጽ ላይ ስለ አሚን አብዱላህ የጀግንነት ሚና ሲገለጽ፦ "እሱ ተራ ጥበቃ ብቻ አልነበረም። ወደዚያ በር ለሚገባ ለማንኛውም ሰው የማህበረሰቡ የመጀመሪያው የደግነት ፊት፣ ነገር ግን ጥቃት በበረታበት በዚያ አስጨናቂ ቅጽበት ደግሞ የሁሉም የመጨረሻው መከላከያ ግንብ ነበር" የሚል ልብ የሚነካ ቃል ሰፍሯል።
የአሚን የቅርብ ጓደኛ ሳም ሃሚደህ ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃል፣ ሟቹ የስምንት ልጆች አባት መሆኑን ጠቅሶ፦ "በተገናኛችሁ ቁጥር ሁልጊዜም ፊትህ ላይ ፈገግታን የሚስል፣ 'ሁሉ ነገር መልካም ይሆናል' የሚል ልዩ አዎንታዊ ኃይል ያለው፣ በፈጣሪው ላይ ጠንካራ እምነት የነበረውና ደግ ሰው ነበር" ሲል በከባድ ሀዘን አስታውሶታል።
ይህ የአጋርነት ገንዘብ እየተሰበሰበ የሚገኘው ሙስሊም ማህበረሰቦችን መሰረት አድርጎ በሚንቀሳቀሰው "ሎንች ጉድ" በተሰኘው ታዋቂ የበጎ አድራጎት ድረ-ገጽ ላይ ነው። የዝግጅቱ አስተባባሪዎች እንደገለጹት፣ ከተገደሉት ሦስት ሰዎች መካከል የሌሎቹን ሁለት ንፁሃን ዜጎች ስም ይፋ ለማድረግ ከቤተሰቦቻቸው በኩል ፈቃድ እየተጠባበቁ መሆኑን አስታውቀዋል።
ለገንዘብ ማሰባሰቢያው በተከፈተው ገጽ ላይ ስለ አሚን አብዱላህ የጀግንነት ሚና ሲገለጽ፦ "እሱ ተራ ጥበቃ ብቻ አልነበረም። ወደዚያ በር ለሚገባ ለማንኛውም ሰው የማህበረሰቡ የመጀመሪያው የደግነት ፊት፣ ነገር ግን ጥቃት በበረታበት በዚያ አስጨናቂ ቅጽበት ደግሞ የሁሉም የመጨረሻው መከላከያ ግንብ ነበር" የሚል ልብ የሚነካ ቃል ሰፍሯል።
የአሚን የቅርብ ጓደኛ ሳም ሃሚደህ ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃል፣ ሟቹ የስምንት ልጆች አባት መሆኑን ጠቅሶ፦ "በተገናኛችሁ ቁጥር ሁልጊዜም ፊትህ ላይ ፈገግታን የሚስል፣ 'ሁሉ ነገር መልካም ይሆናል' የሚል ልዩ አዎንታዊ ኃይል ያለው፣ በፈጣሪው ላይ ጠንካራ እምነት የነበረውና ደግ ሰው ነበር" ሲል በከባድ ሀዘን አስታውሶታል።
ይህ የአጋርነት ገንዘብ እየተሰበሰበ የሚገኘው ሙስሊም ማህበረሰቦችን መሰረት አድርጎ በሚንቀሳቀሰው "ሎንች ጉድ" በተሰኘው ታዋቂ የበጎ አድራጎት ድረ-ገጽ ላይ ነው። የዝግጅቱ አስተባባሪዎች እንደገለጹት፣ ከተገደሉት ሦስት ሰዎች መካከል የሌሎቹን ሁለት ንፁሃን ዜጎች ስም ይፋ ለማድረግ ከቤተሰቦቻቸው በኩል ፈቃድ እየተጠባበቁ መሆኑን አስታውቀዋል።
18 days ago
የስመኝ ግዛውን መፅሐፍ ይግዙ!!!!!
*48 ሰዓት ሳይሞላ 1000 የመፅሀፍ ኮፒ በቅድመ ሽያጭ ተሸጠ
#ethiopia | ቅዳሜ ግንቦት 8 2018 ምሽት ላይ የተጀመረው "የእናቴ ሮሚዬ" የቅድመ ግዢ ቻሌንጅ ተጠናክሯል። 1000 መፅሀፎች በመሸጣቸው ደራሲዋ ስመኝ ግዛው የከበረ ምስጋናዋን አቅርባለች።
ከደራሲዋ ጎን ቆሞ ቻሌንጁን ያስጀመራት ተወዳጅ ሚድያም የማስተዋወቁን እና መፅሀፉን ግዟት በሚል የጀመረውን ቅስቀሳ አጠናክሮ ይቀጥላል ።
ተወዳጅ ሚድያ ስመኝን ለሚያውቁ ሁሉ መረጃውን በቴሌግራም ፣ በሜሴንጀር እና በሌሎችም መንገዶች እያደረሰ ሲሆን መፅሀፍ የገዙ ሰዎችን ከእነ ስማቸው እና አጭር ታሪካቸው ማውጣታችን ይከተላል። ድር ቢያብር አንበሳ ያስር እንዲሉ ነገ እርስዎም መፅሀፍ ቢያሳትሙ አጠገብዎ ሰው ያስፈልጋልና ነገ ሳይሉ ዛሬ በቻሌንጁ ይሳተፉ።
የቅድመ-መጽሐፍ ግዢ (Pre-Order) እና የአጋርነት ጥሪ!
ላለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት በጋዜጠኝነት እና በድንቅ የፈጠራ ሥራዎቿ የምናውቃት ደራሲ ስመኝ ግዛው፣ «የእናቴ ሮሚዮ» የተሰኘውን አዲስ የአጫጭር ልቦለዶች መድብል ለንባብ ልታበቃ ጥቂት ቀናት ቀርተዋታል።
በመሆኑም፣ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን፣ የደራሲዋ ሥራዎች አድናቂዎች፣ ተቋማትና ወዳጆች መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ ፓኬጆች በመግዛት አጋርነታችሁን እንድታሳዩ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
የቅድመ-ግዢ ፓኬጆች እና የዋጋ ዝርዝር፦
• 5 መጽሐፍ፦ 2,500 ብር
• 10 መጽሐፍት፦ 5,000 ብር
• 20 መጽሐፍት፦ 10,000 ብር
• 30 መጽሐፍት፦ 15,000 ብር
• 40 መጽሐፍት፦ 20,000 ብር
• 50 መጽሐፍት፦ 25,000 ብር
💳 የክፍያ እና የምዝገባ መመሪያ፦
1. ክፍያውን በሚከተለው የባንክ አካውንት ያስገቡ፦
o የባንክ አካውንት ቁጥር ፦ ኢት. ንግድ ባንክ 1000345019158
o ቴሌ ብር፦ ____0966925299
o የአካውንት ስም፦ ስመኝ ግዛው
2. ክፍያውን ከፈጸሙ በኋላ፣ የማረጋገጫ ደረሰኙን (Screenshot) በቴሌግራም አድራሻችን ይላኩ፦
የቴሌግራም ሊንክ/ዩዘርኔም፦ https://t.me/SimegnGizaw
• አስፈላጊ ማሳሰቢያ፦ መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ በመግዛት ለምታሳዩት ድጋፍና ውድ አጋርነት ልዩ እውቅና ለመስጠት ስለምንፈልግ፤ ከክፍያ ደረሰኙ ጋር ስለራስዎ የሚገልጽ አጭር መግለጫ (Bio) እና ፎቶግራፍዎን አያይዘው እንዲልኩልን በአክብሮት እንመክራለን።
ስለ ቅን አጋርነታችሁ አስቀድመን እናመሰግናለን!
*48 ሰዓት ሳይሞላ 1000 የመፅሀፍ ኮፒ በቅድመ ሽያጭ ተሸጠ
#ethiopia | ቅዳሜ ግንቦት 8 2018 ምሽት ላይ የተጀመረው "የእናቴ ሮሚዬ" የቅድመ ግዢ ቻሌንጅ ተጠናክሯል። 1000 መፅሀፎች በመሸጣቸው ደራሲዋ ስመኝ ግዛው የከበረ ምስጋናዋን አቅርባለች።
ከደራሲዋ ጎን ቆሞ ቻሌንጁን ያስጀመራት ተወዳጅ ሚድያም የማስተዋወቁን እና መፅሀፉን ግዟት በሚል የጀመረውን ቅስቀሳ አጠናክሮ ይቀጥላል ።
ተወዳጅ ሚድያ ስመኝን ለሚያውቁ ሁሉ መረጃውን በቴሌግራም ፣ በሜሴንጀር እና በሌሎችም መንገዶች እያደረሰ ሲሆን መፅሀፍ የገዙ ሰዎችን ከእነ ስማቸው እና አጭር ታሪካቸው ማውጣታችን ይከተላል። ድር ቢያብር አንበሳ ያስር እንዲሉ ነገ እርስዎም መፅሀፍ ቢያሳትሙ አጠገብዎ ሰው ያስፈልጋልና ነገ ሳይሉ ዛሬ በቻሌንጁ ይሳተፉ።
የቅድመ-መጽሐፍ ግዢ (Pre-Order) እና የአጋርነት ጥሪ!
ላለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት በጋዜጠኝነት እና በድንቅ የፈጠራ ሥራዎቿ የምናውቃት ደራሲ ስመኝ ግዛው፣ «የእናቴ ሮሚዮ» የተሰኘውን አዲስ የአጫጭር ልቦለዶች መድብል ለንባብ ልታበቃ ጥቂት ቀናት ቀርተዋታል።
በመሆኑም፣ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን፣ የደራሲዋ ሥራዎች አድናቂዎች፣ ተቋማትና ወዳጆች መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ ፓኬጆች በመግዛት አጋርነታችሁን እንድታሳዩ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
የቅድመ-ግዢ ፓኬጆች እና የዋጋ ዝርዝር፦
• 5 መጽሐፍ፦ 2,500 ብር
• 10 መጽሐፍት፦ 5,000 ብር
• 20 መጽሐፍት፦ 10,000 ብር
• 30 መጽሐፍት፦ 15,000 ብር
• 40 መጽሐፍት፦ 20,000 ብር
• 50 መጽሐፍት፦ 25,000 ብር
💳 የክፍያ እና የምዝገባ መመሪያ፦
1. ክፍያውን በሚከተለው የባንክ አካውንት ያስገቡ፦
o የባንክ አካውንት ቁጥር ፦ ኢት. ንግድ ባንክ 1000345019158
o ቴሌ ብር፦ ____0966925299
o የአካውንት ስም፦ ስመኝ ግዛው
2. ክፍያውን ከፈጸሙ በኋላ፣ የማረጋገጫ ደረሰኙን (Screenshot) በቴሌግራም አድራሻችን ይላኩ፦
የቴሌግራም ሊንክ/ዩዘርኔም፦ https://t.me/SimegnGizaw
• አስፈላጊ ማሳሰቢያ፦ መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ በመግዛት ለምታሳዩት ድጋፍና ውድ አጋርነት ልዩ እውቅና ለመስጠት ስለምንፈልግ፤ ከክፍያ ደረሰኙ ጋር ስለራስዎ የሚገልጽ አጭር መግለጫ (Bio) እና ፎቶግራፍዎን አያይዘው እንዲልኩልን በአክብሮት እንመክራለን።
ስለ ቅን አጋርነታችሁ አስቀድመን እናመሰግናለን!
18 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያን የቴሌኮም ዘርፍ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተወዳዳሪ ለማድረግ፣ ሀገሪቱ ተጨማሪ 5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ኢንቨስትመንት እና የሶስተኛ ቴሌኮም ኦፕሬተር ወደ ገበያው መግባት በእጅጉ እንደሚያስፈልጋት ተጠቆመ። የቀድሞው የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና የአሁኑ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ዋና ኃላፊ ዶክተር አንዱዓለም አድማሴ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የዘርፉን መዋቅራዊና መሰረተ ልማታዊ ክፍተቶች በግልጽ አብራርተዋል። ሀገሪቱ ለያዘችው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ራዕይ መሳካት፣ የቴሌኮም ማማዎችን ቁጥር አሁን ካለበት በሶስት እጥፍ ማሳደግ የግድ እንደሚልም አሳስበዋል።
በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ያለው የቴሌኮም መሰረተ ልማት ከሕዝብ ቁጥሩ አኳያ ሲመዘን እጅግ ዝቅተኛ መሆኑን ኃላፊው በቁጥራዊ መረጃ ሞግተዋል። ለምሳሌ ያህል፣ አንጋፋው ኢትዮ ቴሌኮም ወደ 10 ሺሕ የሚጠጉ ማማዎች ያሉት ሲሆን፣ ሳፋሪኮም በበኩሉ 3,500 ማማዎች አሉት። ከሳፋሪኮም ማማዎች ውስጥ 40 በመቶ የሚሆኑት ከኢትዮ ቴሌኮም የተከራያቸው ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹን ደግሞ ራሱ የገነባቸው ናቸው። በአጠቃላይ የሁለቱም ኦፕሬተሮች የቴሌኮም ማማዎች ድምር ከ15 ሺሕ በታች ነው። በጎረቤት ሀገራት ካለው የማማ እና የሕዝብ ቁጥር ንጽጽር አንጻር ሲታይ ይህ ቁጥር እጅግ አነስተኛ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ አሁን ካላት የሕዝብ ብዛት አኳያ ተጨማሪ 30 ሺሕ አዳዲስ ማማዎች ያስፈልጓታል። ይህንን ግዙፍ ክፍተት ለመሙላት ደግሞ የመንግሥትና የግል ዘርፍ አጋርነት (PPP) ወሳኝ ሚና እንዳለው ዶክተር አንዱዓለም አስረድተዋል።
ከዚህም ባሻገር፣ በቴሌኮም ዘርፉ ላይ መሠረታዊ የፖሊሲ እና የአሠራር ለውጥ ሊደረግ እንደሚገባ ባለሙያው ክሪቲካል የሆነ ሐሳብ ሰንዝረዋል። እስካሁን ባለው አሠራር የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የመሰረተ ልማት ግንባታውንም ሆነ የቴሌኮም አገልግሎት አቅርቦቱን አጣምረው እየሠሩ ይገኛሉ። ይህ አሠራር ኦፕሬተሮችን ከዋናው ተልዕኳቸው እንዲዘናጉ እንደሚያደርጋቸው ኃላፊው ያምናሉ። በመሆኑም፣ የመሰረተ ልማት አውታሮችን (ማማዎችን) ብቻ የሚገነቡ ገለልተኛ ኩባንያዎች ፈቃድ አግኝተው ወደ ገበያው ሊገቡ ይገባል። ይህ አሠራር ቢተገበር፣ ኢትዮ ቴሌኮምን ጨምሮ ኦፕሬተሮቹ ማማዎቻቸውን ለእነዚህ ገለልተኛ ኩባንያዎች በመሸጥ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የካፒታል ገንዘብ ማሰባሰብ ይችላሉ። አዳዲሶቹም ሆነ ነባሮቹ ኦፕሬተሮች ማማ ከመገንባት ውጣ ውረድ ተላቀው፣ ከመሰረተ ልማት አቅራቢዎች ማማዎቹን እየተከራዩ ጥራት ያለው የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ ያስችላቸዋል ሲሉ ተንትነዋል።
ወደ ሀገሪቱ የገባው ሁለተኛው ኦፕሬተር ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ ለቴሌኮም ፈቃድ ከከፈለው 850 ሚሊዮን ዶላር እና ለኤም-ፔሳ (M-Pesa) ፈቃድ ካወጣው 50 ሚሊዮን ዶላር በተጨማሪ፣ እስካሁን በሥራ ማስኬጃ እንቅስቃሴዎች ላይ ብቻ ወደ 2 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ መዋዕለ ንዋይ አፍስሷል። ኩባንያው ባለፉት ሶስት የሥራ ዓመታት ውስጥ 12 ቢሊዮን ብር ግብር ለመንግሥት ገቢ አድርጓል። የዘርፉን ዕድገት ይበልጥ ለማፋጠንና ጤናማ ፉክክር ለመፍጠር የሶስተኛ ኦፕሬተር መግባት ቁልፍ መሆኑ ቢታመንም፣ በሁሉም ኦፕሬተሮች መካከል ፍትሐዊ የውድድር ሜዳ መኖሩን ማረጋገጥ ቀዳሚ ተግባር መሆን አለበት። ለዚህም ሲባል፣ የኢትዮጵያ የኢንተርኔት መለያ ጎራ (ዶሜይን - .et) በአንድ ኦፕሬተር ሥር ከመሆን ይልቅ፣ ሙሉ በሙሉ ገለልተኛ በሆነ ተቆጣጣሪ አካል ሥር ሊተዳደር እንደሚገባ ዶክተር አንዱዓለም በአጽንዖት አሳስበዋል።
በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ያለው የቴሌኮም መሰረተ ልማት ከሕዝብ ቁጥሩ አኳያ ሲመዘን እጅግ ዝቅተኛ መሆኑን ኃላፊው በቁጥራዊ መረጃ ሞግተዋል። ለምሳሌ ያህል፣ አንጋፋው ኢትዮ ቴሌኮም ወደ 10 ሺሕ የሚጠጉ ማማዎች ያሉት ሲሆን፣ ሳፋሪኮም በበኩሉ 3,500 ማማዎች አሉት። ከሳፋሪኮም ማማዎች ውስጥ 40 በመቶ የሚሆኑት ከኢትዮ ቴሌኮም የተከራያቸው ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹን ደግሞ ራሱ የገነባቸው ናቸው። በአጠቃላይ የሁለቱም ኦፕሬተሮች የቴሌኮም ማማዎች ድምር ከ15 ሺሕ በታች ነው። በጎረቤት ሀገራት ካለው የማማ እና የሕዝብ ቁጥር ንጽጽር አንጻር ሲታይ ይህ ቁጥር እጅግ አነስተኛ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ አሁን ካላት የሕዝብ ብዛት አኳያ ተጨማሪ 30 ሺሕ አዳዲስ ማማዎች ያስፈልጓታል። ይህንን ግዙፍ ክፍተት ለመሙላት ደግሞ የመንግሥትና የግል ዘርፍ አጋርነት (PPP) ወሳኝ ሚና እንዳለው ዶክተር አንዱዓለም አስረድተዋል።
ከዚህም ባሻገር፣ በቴሌኮም ዘርፉ ላይ መሠረታዊ የፖሊሲ እና የአሠራር ለውጥ ሊደረግ እንደሚገባ ባለሙያው ክሪቲካል የሆነ ሐሳብ ሰንዝረዋል። እስካሁን ባለው አሠራር የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የመሰረተ ልማት ግንባታውንም ሆነ የቴሌኮም አገልግሎት አቅርቦቱን አጣምረው እየሠሩ ይገኛሉ። ይህ አሠራር ኦፕሬተሮችን ከዋናው ተልዕኳቸው እንዲዘናጉ እንደሚያደርጋቸው ኃላፊው ያምናሉ። በመሆኑም፣ የመሰረተ ልማት አውታሮችን (ማማዎችን) ብቻ የሚገነቡ ገለልተኛ ኩባንያዎች ፈቃድ አግኝተው ወደ ገበያው ሊገቡ ይገባል። ይህ አሠራር ቢተገበር፣ ኢትዮ ቴሌኮምን ጨምሮ ኦፕሬተሮቹ ማማዎቻቸውን ለእነዚህ ገለልተኛ ኩባንያዎች በመሸጥ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የካፒታል ገንዘብ ማሰባሰብ ይችላሉ። አዳዲሶቹም ሆነ ነባሮቹ ኦፕሬተሮች ማማ ከመገንባት ውጣ ውረድ ተላቀው፣ ከመሰረተ ልማት አቅራቢዎች ማማዎቹን እየተከራዩ ጥራት ያለው የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ ያስችላቸዋል ሲሉ ተንትነዋል።
ወደ ሀገሪቱ የገባው ሁለተኛው ኦፕሬተር ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ ለቴሌኮም ፈቃድ ከከፈለው 850 ሚሊዮን ዶላር እና ለኤም-ፔሳ (M-Pesa) ፈቃድ ካወጣው 50 ሚሊዮን ዶላር በተጨማሪ፣ እስካሁን በሥራ ማስኬጃ እንቅስቃሴዎች ላይ ብቻ ወደ 2 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ መዋዕለ ንዋይ አፍስሷል። ኩባንያው ባለፉት ሶስት የሥራ ዓመታት ውስጥ 12 ቢሊዮን ብር ግብር ለመንግሥት ገቢ አድርጓል። የዘርፉን ዕድገት ይበልጥ ለማፋጠንና ጤናማ ፉክክር ለመፍጠር የሶስተኛ ኦፕሬተር መግባት ቁልፍ መሆኑ ቢታመንም፣ በሁሉም ኦፕሬተሮች መካከል ፍትሐዊ የውድድር ሜዳ መኖሩን ማረጋገጥ ቀዳሚ ተግባር መሆን አለበት። ለዚህም ሲባል፣ የኢትዮጵያ የኢንተርኔት መለያ ጎራ (ዶሜይን - .et) በአንድ ኦፕሬተር ሥር ከመሆን ይልቅ፣ ሙሉ በሙሉ ገለልተኛ በሆነ ተቆጣጣሪ አካል ሥር ሊተዳደር እንደሚገባ ዶክተር አንዱዓለም በአጽንዖት አሳስበዋል።
18 days ago
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 "ሿሿ" ሲሰሩ የነበሩ ሌቦች ተያዙ።
ዛሬ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:30 ገደማ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ቃጥላ ማርያም አካባቢ "ሿሿ" በመስራት የተሰማሩ የሌቦች ቡድን በህዝብ ትብብር በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል።
ህብረተሰቡ ካለው የተለመደ የደህንነት ስጋት አንጻር ያሳየው ይሄው አጋርነትና የጋራ ትብብር ሌቦቹ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል።
seledadotio
seledadotio
ዛሬ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:30 ገደማ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ቃጥላ ማርያም አካባቢ "ሿሿ" በመስራት የተሰማሩ የሌቦች ቡድን በህዝብ ትብብር በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል።
ህብረተሰቡ ካለው የተለመደ የደህንነት ስጋት አንጻር ያሳየው ይሄው አጋርነትና የጋራ ትብብር ሌቦቹ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
20 days ago
ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቻይናን ሊጎበኙ ነው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪው ሳምንት በቻይና ይፋዊ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ክሬምሊን አስታውቋል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቀናት በፊት በቻይና ይፋዊ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፥ በቤጂንግ ቆይታቸው ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በሁለትዮሽና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ሺ ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጉብኝት በኋላ በቀናት ልዩነት የሩሲያ አቻቸውን ቭላድሚር ፑቲን ይቀበላሉ፡፡
ፕሬዚዳንት ፑቲን ከመጪው ማክሰኞ ጀምሮ በሚያደርጉት የሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት በንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ዙሪያ ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር እንደሚመክሩ ተገልጿል፡፡
ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የጠበቀ አጋርነትና ስትራቴጂያዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመ መሆኑን የፕሬዚዳንቱን ጽ/ቤት ጠቅሶ የሩሲያ የዜና ወኪል ታስ ዘግቧል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቻይና ቆይታቸው ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከል የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት አንዱ እንደነበር ይታወሳል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪው ሳምንት በቻይና ይፋዊ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ክሬምሊን አስታውቋል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቀናት በፊት በቻይና ይፋዊ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፥ በቤጂንግ ቆይታቸው ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በሁለትዮሽና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ሺ ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጉብኝት በኋላ በቀናት ልዩነት የሩሲያ አቻቸውን ቭላድሚር ፑቲን ይቀበላሉ፡፡
ፕሬዚዳንት ፑቲን ከመጪው ማክሰኞ ጀምሮ በሚያደርጉት የሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት በንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ዙሪያ ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር እንደሚመክሩ ተገልጿል፡፡
ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የጠበቀ አጋርነትና ስትራቴጂያዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመ መሆኑን የፕሬዚዳንቱን ጽ/ቤት ጠቅሶ የሩሲያ የዜና ወኪል ታስ ዘግቧል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቻይና ቆይታቸው ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከል የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት አንዱ እንደነበር ይታወሳል፡፡
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ የሆኑት የባህር ኃይል አድሚራል ብራድ ኩፐር፣ አሜሪካ በየካቲት ወር መገባደጃ ላይ የጀመረችው "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊዩሪ" የተሰኘው ወታደራዊ ዘመቻ የኢራንን ወታደራዊ አቅም እና በቀጠናው ያላትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት ሙሉ በሙሉ ማዳከሙን አስታወቁ። አዛዡ ይህንን የተናገሩት በዋሽንግተን ዲሲ ለሴኔቱ የጦር ኃይሎች ኮሚቴ ስለ 2027 የበጀት ዓመት ጥያቄ እና በቀጠናው ስላለው ወታደራዊ አሰላለፍ ምስክርነት በሰጡበት ወቅት ነው።
አዛዡ በምስክርነታቸው እንዳብራሩት፣ የአሜሪካ ኃይሎች ከ40 ቀናት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወታደራዊ ግባቸውን በማሳካት የኢራንን የመከላከል አቅም ክፉኛ መትተዋል። በተለይም ባለፈው ዓመት ሚያዝያ እና ጥቅምት ወራት በእስራኤል ላይ ታይቶ የማያውቅ የጅምላ ሚሳኤል ጥቃት የፈጸመችው ኢራን፣ አሁን ላይ ይህን መሰል ጥቃት የመፈጸም አቅሟ በአሜሪካ ኃይሎች ተወግዷል። አድሚራል ኩፐር አክለውም፣ የኢራን የድሮን፣ የሚሳኤል እና የባህር ኃይል መከላከያ ኢንዱስትሪ በ90 በመቶ መውደሙን እና ቀሪ አቅሟ 10 በመቶ ብቻ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኢራን የባህር ኃይል ይህንን ከባድ ውድመት ተቋቁሞ አቅሙን መልሶ ለመገንባት ከ5 እስከ 10 ዓመታት ሊወስድበት እንደሚችልም ወታደራዊ ግምገማቸውን አቅርበዋል።
ይህ ወታደራዊ እርምጃ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን መቼም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዳይኖራት ያስቀመጡትን ብሔራዊ ግብ ለማሳካት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ከዚህም ባሻገር ኢራን በቀጠናው ለሚገኙ አሸባሪ ቡድኖች ስታደርግ የነበረው ቀጥተኛ ያልሆነ ድጋፍ ክፉኛ ተመቷል። ለዓመታት በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እና የጦር መሣሪያ ሲቀርብላቸው የነበሩት እንደ ሐማስ፣ ሕዝቦላህ እና ሁቲ ያሉ የተኪ ተዋጊ (Proxy) ቡድኖች፣ በዘመቻው ምክንያት ከኢራን የሚያገኙት ማንኛውም ዓይነት ትጥቅም ሆነ ሃብት መቋረጡን አዛዡ አብራርተዋል። ይህ ድል በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን፣ ለወራት የተደረገ ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ እና የዓመታት ልምድ ውጤት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
"ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊዩሪ" የአሜሪካን ወታደራዊ የበላይነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ ካሉ አጋር አገራት ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገሩ ተገልጿል። አድሚራል ኩፐር እንደገለጹት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ባህሬን፣ ኩዌት፣ ኳታር እና ሳዑዲ አረቢያ ከአሜሪካ ጋር ጎን ለጎን በመቆም ራሳቸውንም ሆነ አሜሪካውያንን በመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። በተጨማሪም ይህ ግዙፍ ወታደራዊ ስኬት ያለ ዮርዳኖስ እና እስራኤል የጠበቀ አጋርነት ሊሳካ እንደማይችል በመግለጽ፣ ዘመቻው በቀጠናው ያለውን የጸጥታ ትብብር ምን ያህል እንዳጠናከረው መስክረዋል።
አዛዡ በምስክርነታቸው እንዳብራሩት፣ የአሜሪካ ኃይሎች ከ40 ቀናት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወታደራዊ ግባቸውን በማሳካት የኢራንን የመከላከል አቅም ክፉኛ መትተዋል። በተለይም ባለፈው ዓመት ሚያዝያ እና ጥቅምት ወራት በእስራኤል ላይ ታይቶ የማያውቅ የጅምላ ሚሳኤል ጥቃት የፈጸመችው ኢራን፣ አሁን ላይ ይህን መሰል ጥቃት የመፈጸም አቅሟ በአሜሪካ ኃይሎች ተወግዷል። አድሚራል ኩፐር አክለውም፣ የኢራን የድሮን፣ የሚሳኤል እና የባህር ኃይል መከላከያ ኢንዱስትሪ በ90 በመቶ መውደሙን እና ቀሪ አቅሟ 10 በመቶ ብቻ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኢራን የባህር ኃይል ይህንን ከባድ ውድመት ተቋቁሞ አቅሙን መልሶ ለመገንባት ከ5 እስከ 10 ዓመታት ሊወስድበት እንደሚችልም ወታደራዊ ግምገማቸውን አቅርበዋል።
ይህ ወታደራዊ እርምጃ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን መቼም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዳይኖራት ያስቀመጡትን ብሔራዊ ግብ ለማሳካት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ከዚህም ባሻገር ኢራን በቀጠናው ለሚገኙ አሸባሪ ቡድኖች ስታደርግ የነበረው ቀጥተኛ ያልሆነ ድጋፍ ክፉኛ ተመቷል። ለዓመታት በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እና የጦር መሣሪያ ሲቀርብላቸው የነበሩት እንደ ሐማስ፣ ሕዝቦላህ እና ሁቲ ያሉ የተኪ ተዋጊ (Proxy) ቡድኖች፣ በዘመቻው ምክንያት ከኢራን የሚያገኙት ማንኛውም ዓይነት ትጥቅም ሆነ ሃብት መቋረጡን አዛዡ አብራርተዋል። ይህ ድል በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን፣ ለወራት የተደረገ ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ እና የዓመታት ልምድ ውጤት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
"ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊዩሪ" የአሜሪካን ወታደራዊ የበላይነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ ካሉ አጋር አገራት ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገሩ ተገልጿል። አድሚራል ኩፐር እንደገለጹት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ባህሬን፣ ኩዌት፣ ኳታር እና ሳዑዲ አረቢያ ከአሜሪካ ጋር ጎን ለጎን በመቆም ራሳቸውንም ሆነ አሜሪካውያንን በመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። በተጨማሪም ይህ ግዙፍ ወታደራዊ ስኬት ያለ ዮርዳኖስ እና እስራኤል የጠበቀ አጋርነት ሊሳካ እንደማይችል በመግለጽ፣ ዘመቻው በቀጠናው ያለውን የጸጥታ ትብብር ምን ያህል እንዳጠናከረው መስክረዋል።
21 days ago
የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ ፍጹም ተገቢና ህጋዊ ነው - የፈረንሳይ አምባሳደር
ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት ፍጹም ህጋዊ መሆኑን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲ ላሜክ ገለጹ።
አምባሳደሩ ይህ ጥያቄ በዓለም ላይ በብዛት ህዝብ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለምትሰለፈው ኢትዮጵያ ተገቢና ምክንያታዊ መሆኑንም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል።
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከአንድ ዓመት ተኩል ገደማ በፊት በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝት ወቅት የገለጹትን አቋም ያስታወሱት አምባሳደሩ፤ ጉዳዩ አሁንም ቢሆን መሰረታዊና ህጋዊ ጥያቄ ሆኖ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የህዝብ ቁጥር እና የአገሪቱ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ እንደ ዋነኛ ምክንያት ጠቅሰዋል።
በርካታ ታዛቢዎች እንደሚስማሙት፣ የቀይ ባሕር ጉዳይ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅርስ፣ ከጥንታዊ ስልጣኔዋ፣ ከሀገረ መንግስት ምስረታዋ ፣ ከብሄራዊ ደህንነትና ከረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ግቦች ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው ነው።
ኢትዮጵያም ይህንን መልክዓ-ምድራዊ፣ ታሪካዊና ኢኮኖሚያዊ አውድ መሰረት በማድረግ፣ በጋራ ተጠቃሚነትና በአጋርነት መርህ ላይ የተመሰረተ የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለጋራ ልማት የሚረዱ ውይይቶችን ስታካሂድ ቆይታለች።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነትን በተመለከተ ያላትን ሉዓላዊ መብት ለማረጋገጥ፣ በትውልዶች መካከል የተሸጋገረውን ይህን ጥያቄ በዲፕሎማሲያዊና በህጋዊ መንገዶች መፍትሄ እንዲያገኙ እየሰራች ትገኛለች።
አምባሳደር አሌክሲ ፈረንሳይ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ለመፍታት የሚደረጉ ገንቢ ጥረቶችን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ጠቁመው፤ በዚህ ረገድ ፈረንሳይ የምታበረክተው ማንኛውም እገዛ ካለ ድጋፍ ለመስጠት ፍላጎቱ አለን ብለዋል።
EBC
ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት ፍጹም ህጋዊ መሆኑን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲ ላሜክ ገለጹ።
አምባሳደሩ ይህ ጥያቄ በዓለም ላይ በብዛት ህዝብ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለምትሰለፈው ኢትዮጵያ ተገቢና ምክንያታዊ መሆኑንም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል።
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከአንድ ዓመት ተኩል ገደማ በፊት በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝት ወቅት የገለጹትን አቋም ያስታወሱት አምባሳደሩ፤ ጉዳዩ አሁንም ቢሆን መሰረታዊና ህጋዊ ጥያቄ ሆኖ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የህዝብ ቁጥር እና የአገሪቱ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ እንደ ዋነኛ ምክንያት ጠቅሰዋል።
በርካታ ታዛቢዎች እንደሚስማሙት፣ የቀይ ባሕር ጉዳይ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅርስ፣ ከጥንታዊ ስልጣኔዋ፣ ከሀገረ መንግስት ምስረታዋ ፣ ከብሄራዊ ደህንነትና ከረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ግቦች ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው ነው።
ኢትዮጵያም ይህንን መልክዓ-ምድራዊ፣ ታሪካዊና ኢኮኖሚያዊ አውድ መሰረት በማድረግ፣ በጋራ ተጠቃሚነትና በአጋርነት መርህ ላይ የተመሰረተ የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለጋራ ልማት የሚረዱ ውይይቶችን ስታካሂድ ቆይታለች።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነትን በተመለከተ ያላትን ሉዓላዊ መብት ለማረጋገጥ፣ በትውልዶች መካከል የተሸጋገረውን ይህን ጥያቄ በዲፕሎማሲያዊና በህጋዊ መንገዶች መፍትሄ እንዲያገኙ እየሰራች ትገኛለች።
አምባሳደር አሌክሲ ፈረንሳይ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ለመፍታት የሚደረጉ ገንቢ ጥረቶችን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ጠቁመው፤ በዚህ ረገድ ፈረንሳይ የምታበረክተው ማንኛውም እገዛ ካለ ድጋፍ ለመስጠት ፍላጎቱ አለን ብለዋል።
EBC
21 days ago
‹‹የአዲስአበባ አመታዊ በጀት 350 ቢሊዮን ብር ቢሆንም፤ ለወንዝ ዳር ፕሮጄክት ብቻ 1.3 ትሪሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል.››
#ethiopia | ከሰሞኑ በተዘጋጀ አንድ የውይይት መድረክ ላይ የአዲስአበባን የኮሪደር እና የወንዝ ዳር ፕሮጄክቶችን በተመለከተ አነጋጋሪ ጉዳይ ተሰምቷል፡፡ ናሽናል ሚዲያ አክሲዮን ማህበር "አዲሲቷ አዲስ" በሚል መሪ ቃል የአዲስ አበባ ከተማን የማደስ እና የልማት ስራዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ትላንት በዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየም አካሂዶ ነበር፡፡
በዚህ መድረክ ላይ የተሳተፉ አካላት በልማቱ ሂደት ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎችን ሰንዝረዋል። አንድ ተሳታፊ ከተማዋን ለማደስ የተሰራው የፋይናንስ ሞዴል እና ምንጩ ምን እንደሆነ ጥያቄ አቅርበዋል። ለዚህ ጥያቄ የኢዜማ ፓርቲ አመራር እና የአዲስአበባ ከተማ ውበት እና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ አነጋጋሪ ምላሽን ሰጥተዋል፡፡
አቶ ግርማ፣ ‹‹የአዲስ አበባ በጀት 350 ቢሊዮን ብር ሆኖ፤ በኮሪደር ልማቱ ግን በወንዝ ዳር ብቻ 1.3 ትሪሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል›› ሲሉ አነጋጋሪ ምላሽን ሰጥተዋል። የኮሪደር ልማት የፋይናንስ ፕላን ምን ይመስል እንደነበር ሲያስረዱም፣ ‹‹ኮሪደሩ ከመንግስት ካዝና እንደሚሰራ ተደርጎ›› መወሰዱ ልክ አይደለም ይላሉ። ‹‹የፋይናንስ ፕላኑ የወጣው በአብዛኛው በግሉ ሴክተር እንዲሰራ ተደርጎ ነው። የመንግስት ትልቁ ሚና በተለይ መሰረተ ልማቶቹ የሚቀናጁበትን ሁኔታ ነበር›› ሲሉ ገልጸዋል።
‹‹ለምሳሌ በመንግስትና በግል አጋርነት በወንዝ ዳር ብቻ በሰራናቸው ስራዎች ከ1.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጓል›› ነው ያሉት አቶ ግርማ። ለልማት ግንባታ ገንዘቡ ከየት መጣ? የሚለውን ጥያቄ በተመለከተ "የህብረተሰቡ በተለይ የባለሃብቱ ተሳትፎ በጣም ትልቅ ድርሻ ነበረው" ብለዋል ሲል አንድ አፍታ ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ethiopia | ከሰሞኑ በተዘጋጀ አንድ የውይይት መድረክ ላይ የአዲስአበባን የኮሪደር እና የወንዝ ዳር ፕሮጄክቶችን በተመለከተ አነጋጋሪ ጉዳይ ተሰምቷል፡፡ ናሽናል ሚዲያ አክሲዮን ማህበር "አዲሲቷ አዲስ" በሚል መሪ ቃል የአዲስ አበባ ከተማን የማደስ እና የልማት ስራዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ትላንት በዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየም አካሂዶ ነበር፡፡
በዚህ መድረክ ላይ የተሳተፉ አካላት በልማቱ ሂደት ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎችን ሰንዝረዋል። አንድ ተሳታፊ ከተማዋን ለማደስ የተሰራው የፋይናንስ ሞዴል እና ምንጩ ምን እንደሆነ ጥያቄ አቅርበዋል። ለዚህ ጥያቄ የኢዜማ ፓርቲ አመራር እና የአዲስአበባ ከተማ ውበት እና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ አነጋጋሪ ምላሽን ሰጥተዋል፡፡
አቶ ግርማ፣ ‹‹የአዲስ አበባ በጀት 350 ቢሊዮን ብር ሆኖ፤ በኮሪደር ልማቱ ግን በወንዝ ዳር ብቻ 1.3 ትሪሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል›› ሲሉ አነጋጋሪ ምላሽን ሰጥተዋል። የኮሪደር ልማት የፋይናንስ ፕላን ምን ይመስል እንደነበር ሲያስረዱም፣ ‹‹ኮሪደሩ ከመንግስት ካዝና እንደሚሰራ ተደርጎ›› መወሰዱ ልክ አይደለም ይላሉ። ‹‹የፋይናንስ ፕላኑ የወጣው በአብዛኛው በግሉ ሴክተር እንዲሰራ ተደርጎ ነው። የመንግስት ትልቁ ሚና በተለይ መሰረተ ልማቶቹ የሚቀናጁበትን ሁኔታ ነበር›› ሲሉ ገልጸዋል።
‹‹ለምሳሌ በመንግስትና በግል አጋርነት በወንዝ ዳር ብቻ በሰራናቸው ስራዎች ከ1.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጓል›› ነው ያሉት አቶ ግርማ። ለልማት ግንባታ ገንዘቡ ከየት መጣ? የሚለውን ጥያቄ በተመለከተ "የህብረተሰቡ በተለይ የባለሃብቱ ተሳትፎ በጣም ትልቅ ድርሻ ነበረው" ብለዋል ሲል አንድ አፍታ ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
21 days ago
የአሜሪካ የቻይና መኪናዎች እገዳ በአፍሪካ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል ተጠቆመ
በአሜሪካ ምክር ቤት በሁለቱም የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ የቀረበውና በቻይና የተሰሩ መኪናዎች እንዲሁም የመኪና መለዋወጫዎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚከለክለው አዲስ የህግ ረቂቅ፣ በአፍሪካ እያደገ ባለው የመኪና መገጣጠም ዘርፍ ላይ ከፍተኛ አንድምታ ሊኖረው እንደሚችል ተገለጸ።
የአሜሪካ የደህንነትና የኢኮኖሚ ስጋቶችን መሰረት ያደረገው ይህ እገዳ፣ የቻይና የመኪና አምራቾች ፊታቸውን በስፋት ወደ አፍሪካ ገበያ እንዲያዞሩና ምርቶቻቸውን ወደ አህጉሪቱ እንዲያፈሱ የሚያስገድድ እንደሆነ ተመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት አፍሪካ ከዓለም አቀፍ የመኪና ምርት ውስጥ የምታበረክተው ድርሻ ከሁለት በመቶ በታች ቢሆንም፣ እንደ ቢ.ዋይ.ዲ (BYD) እና ቼሪ (Chery) ያሉ የቻይና ኩባንያዎች በአህጉሪቱ ያላቸውን የተሽከርካሪ ሽያጭና የመገጣጠም አጋርነት በከፍተኛ ሁኔታ እያሰፉ ይገኛሉ።
ይህ የቻይና ኩባንያዎች ወደ አፍሪካ በስፋት መተምመም፣ እንደ ደቡብ አፍሪካ እና ሞሮኮ ያሉ ግዙፍ አምራቾችን ብቻ ሳይሆን እንደ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ኬንያ ያሉ የአገር ውስጥ መኪና መገጣጠም ኢንዱስትሪን ለማሳደግ የሚጥሩ ሀገራትን ፈተና ላይ ሊጥል እንደሚችል ተገምቷል።
በአሜሪካ ገበያ የተገደቡት ምርቶች ወደ አፍሪካ በብዛት መፍሰሳቸው ለአገር ውስጥ አነስተኛ መገጣጠሚያዎች የገበያ ፉክክርን የሚያከብድ ሲሆን፣ ይህም በአገር ውስጥ የሚመረቱ መኪናዎችን ተወዳዳሪነት ሊቀንስ እንደሚችል ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ።
seledadotio
seledadotio
በአሜሪካ ምክር ቤት በሁለቱም የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ የቀረበውና በቻይና የተሰሩ መኪናዎች እንዲሁም የመኪና መለዋወጫዎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚከለክለው አዲስ የህግ ረቂቅ፣ በአፍሪካ እያደገ ባለው የመኪና መገጣጠም ዘርፍ ላይ ከፍተኛ አንድምታ ሊኖረው እንደሚችል ተገለጸ።
የአሜሪካ የደህንነትና የኢኮኖሚ ስጋቶችን መሰረት ያደረገው ይህ እገዳ፣ የቻይና የመኪና አምራቾች ፊታቸውን በስፋት ወደ አፍሪካ ገበያ እንዲያዞሩና ምርቶቻቸውን ወደ አህጉሪቱ እንዲያፈሱ የሚያስገድድ እንደሆነ ተመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት አፍሪካ ከዓለም አቀፍ የመኪና ምርት ውስጥ የምታበረክተው ድርሻ ከሁለት በመቶ በታች ቢሆንም፣ እንደ ቢ.ዋይ.ዲ (BYD) እና ቼሪ (Chery) ያሉ የቻይና ኩባንያዎች በአህጉሪቱ ያላቸውን የተሽከርካሪ ሽያጭና የመገጣጠም አጋርነት በከፍተኛ ሁኔታ እያሰፉ ይገኛሉ።
ይህ የቻይና ኩባንያዎች ወደ አፍሪካ በስፋት መተምመም፣ እንደ ደቡብ አፍሪካ እና ሞሮኮ ያሉ ግዙፍ አምራቾችን ብቻ ሳይሆን እንደ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ኬንያ ያሉ የአገር ውስጥ መኪና መገጣጠም ኢንዱስትሪን ለማሳደግ የሚጥሩ ሀገራትን ፈተና ላይ ሊጥል እንደሚችል ተገምቷል።
በአሜሪካ ገበያ የተገደቡት ምርቶች ወደ አፍሪካ በብዛት መፍሰሳቸው ለአገር ውስጥ አነስተኛ መገጣጠሚያዎች የገበያ ፉክክርን የሚያከብድ ሲሆን፣ ይህም በአገር ውስጥ የሚመረቱ መኪናዎችን ተወዳዳሪነት ሊቀንስ እንደሚችል ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ።
seledadotio
seledadotio