ኢትዮጵያ እና ኳታር የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ አጋርነት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገለጹ
*****************
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ከኳታር ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ መሐመድ ቢን አብዱልራህማን ቢን ጃሲም አል ታኒ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
በውይይቱ ወቅት በኢትዮጵያ እና በኳታር መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።
ሁለቱ ወገኖች መደበኛ የፖለቲካ ምክክሮችን በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትብብርን በማጠናከር እና የግል ዘርፍ ኢንቨስትመንትን በማሳደግ ረገድ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ አጋርነት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም በአፍሪካ ቀንድ፣ በባህረ ሰላጤው ቀጣና እና ከዚያም ባሻገር ቀጣናዊ ሰላምና ደህንነትን ለማስፈን የሚደረጉ የጋራ ጥረቶችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
#ethiopia #qatar #bilateral #partnership #ebc
*****************
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ከኳታር ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ መሐመድ ቢን አብዱልራህማን ቢን ጃሲም አል ታኒ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
በውይይቱ ወቅት በኢትዮጵያ እና በኳታር መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።
ሁለቱ ወገኖች መደበኛ የፖለቲካ ምክክሮችን በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትብብርን በማጠናከር እና የግል ዘርፍ ኢንቨስትመንትን በማሳደግ ረገድ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ አጋርነት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም በአፍሪካ ቀንድ፣ በባህረ ሰላጤው ቀጣና እና ከዚያም ባሻገር ቀጣናዊ ሰላምና ደህንነትን ለማስፈን የሚደረጉ የጋራ ጥረቶችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
#ethiopia #qatar #bilateral #partnership #ebc
16 days ago