6 hours ago
ፔንታጎን በጦር ኃይሉ እውቅና ከተሰጣቸው ሃይማኖቶች ዝርዝር ውስጥ ከ180 በላዩን ቀነሰ
#ethiopia | ፔንታጎን በጦር ኃይሉ እውቅና ከተሰጣቸው ሃይማኖቶች ዝርዝር ውስጥ 180 እምነቶችን መቀነሱን ፎክስ ኒውስ ከውስጥ ማስታወሻ ተመለከትኩት ባለው ዘገባ ላይ ጠቅሷል።
ይህ እርምጃ የተወሰደው የመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴት በወታደራዊ ተቋማት ውስጥ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች የጦር ሠራዊቱን አርበኝነት እና ዲሲፕሊን እየሸረሸሩ ነው የሚል አቋም በመያዛቸው ነው ተብሏል።
ቀደም ሲል ከ200 በላይ ለሚሆኑ ሃይማኖቶች እወቅቅና አግኝተው በሰራዊቱ አባላት ዘንድ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ነበር ሲባል፣ አሁን ይህ ቁጥር ወደ 31 ብቻ ዝቅ ብሏል።
ውሳኔው ወታደራዊ ተቋሙን ከፖለቲካዊ እና ሃይማኖታዊ አክራሪነት ለመከላከል አስፈላጊ እንደሆነ ቢገለጽም፥ በሌላ በኩል በሠራዊቱ ውስጥ የሚያገለግሉ አባላትን የሃይማኖት ነፃነት የሚገድብ እና ኢ-ሕገ-መንግሥታዊ ነው በሚል ቅሬታ ቀርቦበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #fox News #tikvahethmagazine
#ethiopia | ፔንታጎን በጦር ኃይሉ እውቅና ከተሰጣቸው ሃይማኖቶች ዝርዝር ውስጥ 180 እምነቶችን መቀነሱን ፎክስ ኒውስ ከውስጥ ማስታወሻ ተመለከትኩት ባለው ዘገባ ላይ ጠቅሷል።
ይህ እርምጃ የተወሰደው የመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴት በወታደራዊ ተቋማት ውስጥ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች የጦር ሠራዊቱን አርበኝነት እና ዲሲፕሊን እየሸረሸሩ ነው የሚል አቋም በመያዛቸው ነው ተብሏል።
ቀደም ሲል ከ200 በላይ ለሚሆኑ ሃይማኖቶች እወቅቅና አግኝተው በሰራዊቱ አባላት ዘንድ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ነበር ሲባል፣ አሁን ይህ ቁጥር ወደ 31 ብቻ ዝቅ ብሏል።
ውሳኔው ወታደራዊ ተቋሙን ከፖለቲካዊ እና ሃይማኖታዊ አክራሪነት ለመከላከል አስፈላጊ እንደሆነ ቢገለጽም፥ በሌላ በኩል በሠራዊቱ ውስጥ የሚያገለግሉ አባላትን የሃይማኖት ነፃነት የሚገድብ እና ኢ-ሕገ-መንግሥታዊ ነው በሚል ቅሬታ ቀርቦበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #fox News #tikvahethmagazine
29 days ago
የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ያለመው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ…
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2014 ዓ.ም “ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ” ከመጀመሩ በፊት እንደ ሀገር ኢንዱስትሪዎች በዓይነትም ሆነ በቁጥር አነስተኛ ነበሩ አሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 25 "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ የተከፈተው 4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በድምቀት ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል።
ተኪ ምርቶችን በዓይነት፣ በጥራትና በብዛት ማምረት የውጭ ምንዛሪ ወጪን ከማስቀረት ባለፈ የዘርፉን አቅም መገንባት የዘመኑ አርበኝነት ተደርጎ ይወሰዳልና ሁነቱ በዘንድሮው የአርበኞች በዓል ላይ ማረፉ ታሪካዊ ግጥምጥሞሽ ሆኗል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት÷ ከኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በፊት እንደ ሀገር የነበሩት ኢንዱስትሪዎች አነስተኛ ነበሩ።
የነበሩት ኢንዱስትሪዎችም በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት በምርት ሂደት መስተጓጎላቸው እና በሰሜኑ ጦርነት የጥቃት ኢላማ መሆናቸው ትልቅ ጫና እንደነበር አንስተዋል።
ከዚያ መንገድ ለመውጣት እና አዲስ መንገድ ለመከተል የ“ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ” መጀመሩን ያስታወሱት ሚኒስትሩ÷ የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተግዳሮቶች ለመፍታት የሚያግዝ ሰነድ ቀርቦ ውይይት በመደረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ድጋፍ ማግኘቱን አመልክተዋል።
በዚህም በንቅናቄው "በኢትዮጵያ ዲዛይን ተደርገው፣ በኢትዮጵያ ተመርተው እና ተገጣጥመው ለሥራ የቀረቡ ማሽኖችን ወደምናይበት ምዕራፍ ተሸጋግረናል" ብለዋል።
ሚኒስትሩ ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ👇
https://www.youtube.com/wa...
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2014 ዓ.ም “ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ” ከመጀመሩ በፊት እንደ ሀገር ኢንዱስትሪዎች በዓይነትም ሆነ በቁጥር አነስተኛ ነበሩ አሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 25 "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ የተከፈተው 4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በድምቀት ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል።
ተኪ ምርቶችን በዓይነት፣ በጥራትና በብዛት ማምረት የውጭ ምንዛሪ ወጪን ከማስቀረት ባለፈ የዘርፉን አቅም መገንባት የዘመኑ አርበኝነት ተደርጎ ይወሰዳልና ሁነቱ በዘንድሮው የአርበኞች በዓል ላይ ማረፉ ታሪካዊ ግጥምጥሞሽ ሆኗል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት÷ ከኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በፊት እንደ ሀገር የነበሩት ኢንዱስትሪዎች አነስተኛ ነበሩ።
የነበሩት ኢንዱስትሪዎችም በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት በምርት ሂደት መስተጓጎላቸው እና በሰሜኑ ጦርነት የጥቃት ኢላማ መሆናቸው ትልቅ ጫና እንደነበር አንስተዋል።
ከዚያ መንገድ ለመውጣት እና አዲስ መንገድ ለመከተል የ“ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ” መጀመሩን ያስታወሱት ሚኒስትሩ÷ የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተግዳሮቶች ለመፍታት የሚያግዝ ሰነድ ቀርቦ ውይይት በመደረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ድጋፍ ማግኘቱን አመልክተዋል።
በዚህም በንቅናቄው "በኢትዮጵያ ዲዛይን ተደርገው፣ በኢትዮጵያ ተመርተው እና ተገጣጥመው ለሥራ የቀረቡ ማሽኖችን ወደምናይበት ምዕራፍ ተሸጋግረናል" ብለዋል።
ሚኒስትሩ ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ👇
https://www.youtube.com/wa...
1 month ago
ሚያዝያ 27! ለአምስት ዓመታት በጨለማ የተዋጠው የኢትዮጵያ ሰማይ በነፃነት ጎህ የፈካበት፣ የግፍ ወረራ ቀንበር የተሰበረበት ታላቅ ዕለት ነው።
ነገር ግን የአባቶቻችን ገድል ለእኛ የታሪክ ማስታወሻ ብቻ ነው? ወይስ ዛሬን የምንመራበት ኮምፓስ?
በዚህ ቪዲዮ የአባቶቻችንን የዱር በገደል ተጋድሎ ከዛሬው የልማትና የቴክኖሎጂ አርበኝነት ጋር እናነፃፅራለን።
#ethiopianpatriotsday #arbenyoch #victoryday #grandethiopianrenaissancedam #gerd
1 month ago
አርበኝነት ለሀገር ያለ ዋጋ የሚከፈል ከራስ ወዳድነት የነጻ መሥዋዕትነት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርበኝነት ማለት ለሀገር ያለ ዋጋ የሚከፈል ከራስ ወዳድነት የነጻ መሥዋዕትነት ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለ85ኛው የአርበኞች በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እንዳሉት÷ ሚያዚያ 27 ቀን ኢትዮጵያውያን ጀግኖች አርበኞች የፋሽስትን ወረራ የቀለበሱበትና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ሙሉ በሙሉ ያስከበሩበት በዓል ነው።
አርበኝነት ማለት ለሀገር ያለ ዋጋ የሚከፈል ከራስ ወዳድነት የነጻ መሥዋዕትነት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ዓላማውም ሀገርንና ሕዝብን ብቻ ማዕከል ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
እናትና አባት አርበኞች ከፋሺስት ጋር የተዋጉት ለሀገር እና ለወገን ብለው ነው፤ በግል ጥቅም ለማግኘትማ ከአርበኝነት ይልቅ ባንዳነት አቋራጭ ነበር፤ ግን አላደረጉትም ሲሉም አብራርተዋል።
የአርበኝነት ትግሉ ከሦስት ጠላቶች ጋር የተደረገ ነበር በማለት ገልጸው÷ ከራስ ፍላጎት፣ ከባንዳና ከወራሪ ፋሺስት ጋር መሆኑን አስረድተዋል።
አርበኝነት የራስን ጥቅም ለሀገር ጥቅም ሲባል መተው ነው፤ የግል ክብርን፣ የግል ሥልጣንን እና የግል ጥቅምን መሠዋት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)÷ ይሄንን ለመቀበል ከጠላት በፊት ራስን ማሸነፍ ይጠይቃል ብለዋል።
ባንዳዎች ራሳቸውን ማሸነፍ ያቃታቸው ናቸው፤ የግል ጥቅምንና ክብርን ማሸነፍ ሲያቅታቸው የሀገራቸውን ክብርና ጥቅም ይሸጣሉ ሲሉም አመልክተዋል።
ባንዳነት ማለት ሀገርን ለራስ ጥቅም በመሸጥ የሚከናነቡት የውርደት ካባ ነው፤ አርበኞች ከባንዳዎች ጋር ታግለዋል፤ ባንዳዎች በአንድ በኩል ሀገራችሁን ሽጣችሁ እንደኛ በግል ተጠቀሙ ይሏቸዋል፤ በሌላ በኩል መንገድ እየመሩ ወራሪውን ያመጡባቸዋል። ያም አልሆን ሲላቸው ሕዝቡን በሐሰተኛ ወሬ ልቡን ይሰልቡባቸዋል ነው ያሉት።
ዛሬም ሦስቱም ጠላቶች አሉ፤ መልክና ስም ብቻ ቀይረዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ በሌላም በኩል ዛሬም በየመስኩ የተሠማሩ ኢትዮጵያውያን አርበኞች አሉ ብለዋል።
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርበኝነት ማለት ለሀገር ያለ ዋጋ የሚከፈል ከራስ ወዳድነት የነጻ መሥዋዕትነት ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለ85ኛው የአርበኞች በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እንዳሉት÷ ሚያዚያ 27 ቀን ኢትዮጵያውያን ጀግኖች አርበኞች የፋሽስትን ወረራ የቀለበሱበትና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ሙሉ በሙሉ ያስከበሩበት በዓል ነው።
አርበኝነት ማለት ለሀገር ያለ ዋጋ የሚከፈል ከራስ ወዳድነት የነጻ መሥዋዕትነት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ዓላማውም ሀገርንና ሕዝብን ብቻ ማዕከል ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
እናትና አባት አርበኞች ከፋሺስት ጋር የተዋጉት ለሀገር እና ለወገን ብለው ነው፤ በግል ጥቅም ለማግኘትማ ከአርበኝነት ይልቅ ባንዳነት አቋራጭ ነበር፤ ግን አላደረጉትም ሲሉም አብራርተዋል።
የአርበኝነት ትግሉ ከሦስት ጠላቶች ጋር የተደረገ ነበር በማለት ገልጸው÷ ከራስ ፍላጎት፣ ከባንዳና ከወራሪ ፋሺስት ጋር መሆኑን አስረድተዋል።
አርበኝነት የራስን ጥቅም ለሀገር ጥቅም ሲባል መተው ነው፤ የግል ክብርን፣ የግል ሥልጣንን እና የግል ጥቅምን መሠዋት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)÷ ይሄንን ለመቀበል ከጠላት በፊት ራስን ማሸነፍ ይጠይቃል ብለዋል።
ባንዳዎች ራሳቸውን ማሸነፍ ያቃታቸው ናቸው፤ የግል ጥቅምንና ክብርን ማሸነፍ ሲያቅታቸው የሀገራቸውን ክብርና ጥቅም ይሸጣሉ ሲሉም አመልክተዋል።
ባንዳነት ማለት ሀገርን ለራስ ጥቅም በመሸጥ የሚከናነቡት የውርደት ካባ ነው፤ አርበኞች ከባንዳዎች ጋር ታግለዋል፤ ባንዳዎች በአንድ በኩል ሀገራችሁን ሽጣችሁ እንደኛ በግል ተጠቀሙ ይሏቸዋል፤ በሌላ በኩል መንገድ እየመሩ ወራሪውን ያመጡባቸዋል። ያም አልሆን ሲላቸው ሕዝቡን በሐሰተኛ ወሬ ልቡን ይሰልቡባቸዋል ነው ያሉት።
ዛሬም ሦስቱም ጠላቶች አሉ፤ መልክና ስም ብቻ ቀይረዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ በሌላም በኩል ዛሬም በየመስኩ የተሠማሩ ኢትዮጵያውያን አርበኞች አሉ ብለዋል።
1 month ago
u12a8u12d0u122du1260u129du1290u1275 u1260u120bu12ed u121du1295 u12a0u1208? | u12a8u122bu1235 u12c8u12f3u12f5u1290u1275 u12e8u1290u133bu12cd u12e8u12a0u1263u1276u127bu127du1295 u1273u120bu1245 u1218u1235u12cbu12d5u1275u1290u1275 #ethiopia #patriotism #freedom #sacrifice #nationalidentity #miyazya27 #africanhistory #sovereignty #u12a2u1275u12eeu1335u12eb #u12a0u122du1260u129du1290u1275 ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ከዐርበኝነት በላይ ምን አለ? | ከራስ ወዳድነት የነጻው የአባቶቻችን ታላቅ መስዋዕትነት #ethiopia #patriotism #freedom #sacrifice #nationalidentity #miyazya27 #africanhistory #sovereignty #ኢትዮጵያ #አርበኝነት
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ትውልዱ ፈተናዎችን ለመሻገር የጸና አንድነት ሊኖረው ይገባል - ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ትውልዱ ፈተናዎችን በጽናት ለመሻገር እንደ አባቶቹ የጸና አንድነትና የሀገር ፍቅር ስሜት ሊኖረው ይገባል አሉ የባሕር ኃይል አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ።
85ኛው የአርበኞች በዓል በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው የድል ሐውልት አደባባይ ተከብሯል።
የባሕር ኃይል አዛዡ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ኢትዮጵያ በዘመናዊ ወታደራዊ ጥበብ፣ በላቀ ሥነ ልቦና የታነጸና ጥቃትን በብቃት መመከት የሚችል ሠራዊት ገንብታለች።
ጀግንነት የኢትዮጵያውያን መታወቂያና የነፃነታቸው ዋስትና መሆኑን አንስተው÷ ሀገሪቱ በረጅም ዘመን ታሪኳ በልጆቿ መስዋዕትነት የነፃነትና የታላቅነት የድል ባለቤት መሆኗን አስረድተዋል።
የድል በዓሉ የአምስት ዓመታት የአርበኝነት ትግል ጊዜ አልፎ ዳግም የነፃነት ብርሃን የበራበት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በደማቅ ቀለም የተጻፈ ነው ብለዋል።
አርበኞች ወራሪ ኃይሉን መስዋዕትነት ከፍለው በትብብር ድል እንዳደረጉ ዛሬም ለሀገር ሕልውናና ሉዓላዊነት መከበር በአንድነትና በመተባበር ሁሉም ዜጋ ሊረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያ በግፍ ያጣችውን የባሕር በር ለማስመለስ መንግሥት የሚያደርገውን ዘርፈ ብዙ ጥረት ለመደገፍ ጠንካራ የባሕር ኃይል እየተገነባ መሆኑንም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ትውልዱ ፈተናዎችን በጽናት ለመሻገር እንደ አባቶቹ የጸና አንድነትና የሀገር ፍቅር ስሜት ሊኖረው ይገባል አሉ የባሕር ኃይል አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ።
85ኛው የአርበኞች በዓል በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው የድል ሐውልት አደባባይ ተከብሯል።
የባሕር ኃይል አዛዡ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ኢትዮጵያ በዘመናዊ ወታደራዊ ጥበብ፣ በላቀ ሥነ ልቦና የታነጸና ጥቃትን በብቃት መመከት የሚችል ሠራዊት ገንብታለች።
ጀግንነት የኢትዮጵያውያን መታወቂያና የነፃነታቸው ዋስትና መሆኑን አንስተው÷ ሀገሪቱ በረጅም ዘመን ታሪኳ በልጆቿ መስዋዕትነት የነፃነትና የታላቅነት የድል ባለቤት መሆኗን አስረድተዋል።
የድል በዓሉ የአምስት ዓመታት የአርበኝነት ትግል ጊዜ አልፎ ዳግም የነፃነት ብርሃን የበራበት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በደማቅ ቀለም የተጻፈ ነው ብለዋል።
አርበኞች ወራሪ ኃይሉን መስዋዕትነት ከፍለው በትብብር ድል እንዳደረጉ ዛሬም ለሀገር ሕልውናና ሉዓላዊነት መከበር በአንድነትና በመተባበር ሁሉም ዜጋ ሊረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያ በግፍ ያጣችውን የባሕር በር ለማስመለስ መንግሥት የሚያደርገውን ዘርፈ ብዙ ጥረት ለመደገፍ ጠንካራ የባሕር ኃይል እየተገነባ መሆኑንም ተናግረዋል።
1 month ago
የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲሳካ ብሔራዊ አርበኞችን ይፈልጋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲሳካ ብሔራዊ አርበኞችን ይፈልጋል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ለ85ኛው የአርበኞች በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ነው።
በመልዕክታቸውም የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲሳካ ብሔራዊ አርበኞችን ይፈልጋል፤ የራስ ፍላጎትን፣ ባንዳነትን እና ወራሪን እምቢ የሚል አርበኝነት ብለዋል።
የኢንዱስትሪ አርበኞች፣ የግብርና አርበኞች፣ የጸጥታ አርበኞች፣ የፖለቲካ አርበኞች፣ የንግድ አርበኞች፣ የዲፕሎማሲ አርበኞች፣ የመንግሥት አገልጋይ አርበኞች፣ የሕክምና አርበኞች እንዲሁም የትምህርት አርበኞች እንደሚያስፈልጉም አብራርተዋል።
ይሄንን በዓል የምናከብረው የየራሳችንን የአርበኝነት ደረጃ በመገምገም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ለኢትዮጵያ ምን ያህል አርበኞች ነን? ሲሉም ጠይቀዋል፡፡
ዛሬም የግል ፍላጎት የሚያሸንፋቸው ደካሞች አሉ፤ ሀገርን አፍርሰው የግል ቤት መሥራት የሚመኙ በማለት ጠቅሰው÷ ትልቁን መርከብ አፍርሰው ትንንሽ ታንኳዎችን ለመሸጥ የሚመኙ እንዲሁም ለቅንጥብጣቢ ነገር ውርደትን ለመሸከም የማይሳቀቁ ሲሉም አብራርተዋል።
ዛሬም ወራሪዎች አሉ፤ በአካል ሀገርን ለመውረር ካሰፈሰፉት በተጨማሪ ድህነት፣ ኋላቀርነትና ሌብነት የሚባሉ እንደ ሰርዶ ሀገርን ወርረው ሽባ የሚያደርጉ ጠላቶች አሉ ብለዋል።
ሀገርን ለባዳ ከሚሸጡት ባንዳዎች እኩል የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የሚሸጡ እንዲሁም አገልግሎትንና የሕዝብን ሀብት የሚሸቅጡ ባንዳዎች መኖራቸውንም አመልክተዋል።
ብሔራዊ አርበኝነት ማለት እነዚህን ሦስት ጠላቶች ታግሎ ማሸነፍ ማለት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ዛሬ የምናየውን የኢትዮጵያ ለውጥና ዕድገት ማስመዝገብ የተቻለው ብሔራዊ አርበኞች በየአካባቢው በመኖራቸው ነው ብለዋል።
ብሔራዊ አርበኞች ሦስቱን ጠላቶች እያሸነፉ ቢሆንም ገና ሙሉ በሙሉ ድልን አልተቀዳጁም በማለት ገልጸው÷ ድሉ እንደ ሚያዚያ 27 የሚታወጀው ኢትዮጵያ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት እንዲሁም በዓለም ደረጃ ከሚገኙ ኃያል ሀገራት አንዷ ስትሆን ነው ሲሉም አስገንዝበዋል።
ይሄንን ድል እውን ለማድረግ ኢትዮጵያን የሚወዱ የኢትዮጵያ አርበኞች ሁሉ እንዲነሡ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲሳካ ብሔራዊ አርበኞችን ይፈልጋል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ለ85ኛው የአርበኞች በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ነው።
በመልዕክታቸውም የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲሳካ ብሔራዊ አርበኞችን ይፈልጋል፤ የራስ ፍላጎትን፣ ባንዳነትን እና ወራሪን እምቢ የሚል አርበኝነት ብለዋል።
የኢንዱስትሪ አርበኞች፣ የግብርና አርበኞች፣ የጸጥታ አርበኞች፣ የፖለቲካ አርበኞች፣ የንግድ አርበኞች፣ የዲፕሎማሲ አርበኞች፣ የመንግሥት አገልጋይ አርበኞች፣ የሕክምና አርበኞች እንዲሁም የትምህርት አርበኞች እንደሚያስፈልጉም አብራርተዋል።
ይሄንን በዓል የምናከብረው የየራሳችንን የአርበኝነት ደረጃ በመገምገም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ለኢትዮጵያ ምን ያህል አርበኞች ነን? ሲሉም ጠይቀዋል፡፡
ዛሬም የግል ፍላጎት የሚያሸንፋቸው ደካሞች አሉ፤ ሀገርን አፍርሰው የግል ቤት መሥራት የሚመኙ በማለት ጠቅሰው÷ ትልቁን መርከብ አፍርሰው ትንንሽ ታንኳዎችን ለመሸጥ የሚመኙ እንዲሁም ለቅንጥብጣቢ ነገር ውርደትን ለመሸከም የማይሳቀቁ ሲሉም አብራርተዋል።
ዛሬም ወራሪዎች አሉ፤ በአካል ሀገርን ለመውረር ካሰፈሰፉት በተጨማሪ ድህነት፣ ኋላቀርነትና ሌብነት የሚባሉ እንደ ሰርዶ ሀገርን ወርረው ሽባ የሚያደርጉ ጠላቶች አሉ ብለዋል።
ሀገርን ለባዳ ከሚሸጡት ባንዳዎች እኩል የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የሚሸጡ እንዲሁም አገልግሎትንና የሕዝብን ሀብት የሚሸቅጡ ባንዳዎች መኖራቸውንም አመልክተዋል።
ብሔራዊ አርበኝነት ማለት እነዚህን ሦስት ጠላቶች ታግሎ ማሸነፍ ማለት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ዛሬ የምናየውን የኢትዮጵያ ለውጥና ዕድገት ማስመዝገብ የተቻለው ብሔራዊ አርበኞች በየአካባቢው በመኖራቸው ነው ብለዋል።
ብሔራዊ አርበኞች ሦስቱን ጠላቶች እያሸነፉ ቢሆንም ገና ሙሉ በሙሉ ድልን አልተቀዳጁም በማለት ገልጸው÷ ድሉ እንደ ሚያዚያ 27 የሚታወጀው ኢትዮጵያ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት እንዲሁም በዓለም ደረጃ ከሚገኙ ኃያል ሀገራት አንዷ ስትሆን ነው ሲሉም አስገንዝበዋል።
ይሄንን ድል እውን ለማድረግ ኢትዮጵያን የሚወዱ የኢትዮጵያ አርበኞች ሁሉ እንዲነሡ ጥሪ አቅርበዋል።
1 month ago
ሚያዝያ 27 የታሪክ ማኅደር ተገልጦ የሚነበብበት የትላንት ትዝታ ብቻ አይደለም - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
***********************
ሚያዝያ 27 ለእኛ የታሪክ ማኅደር ተገልጦ የሚነበብበት የትላንት ትዝታ ብቻ አይደለም፤ የአርበኞች አባቶቻችንን እና እናቶቻችንን የድል መንፈስ እንደ ብዕር በመጠቀም አዲስ የታሪክ ምዕራፍ መጻፍ የጀመርንበት የትንሣኤ ጉዟችን መነሻ መሠረት ነው! ሚያዝያ 27 የነፃነት ማስታወሻ ብቻ ሳይሆን፣ ወጣቱ ትውልድ ሀገሩን በክብር ለመረከብ ላቡን የሚያፈስበትና ያለውን የሚሰጥበት የቁርጠኝነት ቀን ነው!
ከ85 ዓመታት በፊት አባቶቻችን በደምና በአጥንታቸው ሀገርን ጠብቀው የማቆየት ታሪካዊ ግዴታቸውን በድል ተወጥተዋል። ዛሬ የታሪኩ ምዕራፍ ተቀይሮ ተረኝነቱ የእኛ ሆኗል፤ እነርሱ በነፃነት ያቆዩልንን ሀገር እኛ በዕውቀታችን፣ በላባችንና በሥራችን የመገንባት የዘመኑ አርበኝነት አደራ አለብን።
አባቶች በጠመንጃ ሀገር ጠበቁ፤ እኛ በቴክኖሎጂ ሀገር እንገነባለን። አባቶች ዳር ድንበር አስከበሩ፤ እኛ ድህነትን አሸንፈን ብልጽግናን እናረጋግጣለን። አባቶች ለነፃነት ወደቁ፤ እኛ ለታላቅነት እንቆማለን። ይህ የትውልድ ቅብብል ነው ። ያለ አባቶች ጥበቃ ዛሬ የምንገነባት ሀገር ባልኖረች ነበር፤ ያለ እኛ ግንባታም አባቶች የጠበቋት ሀገር ትርጉም ያለው ሕይወት ለዜጎቿ መስጠት አትችልም። በመሆኑም ትናንት በጀግንነት የተረከብናትን ሀገር፣ ዛሬ በሥልጣኔ አንጸን ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ የሞራል ዕዳ፣ የሀገር አደራ አለብን።
ለዚህም ነው ኢትዮጵያዊያን ከስንዴ ልመና ለመላቀቅ ወገባችንን አጥብቀን፣ ማረሻችንን ጨብጠን የተነሳነው፣ ለዚህ ነው አለም እኪደመም ተደምረን 48 ቢሊዮን ችግኝ የተከለነወ፣ ለዚህ ነው ከመቀነታችን ፈትተን፣ ከጉርሳችን ቀንሰን ህዳሴያችንን እውን ያደረግነው፣ ለዚህ ነው የዘመናት የጉስቁልና ምልክት የነበሩ ያረጁ ከተሞቻችንን ለመለወጥ እያመመን የበረታነው፣ ለዚህ ነው የከረሙ ስብራቶቻችንን ለመጠገን እንመካከር ያለነው፣ ለዚህ ነው ዙሪያው ተቸንክሮብን እስከመቼ እንኖራለን ያልነው! ለዚህ ነው የታዳሽ ሀይል መሠረት ለመጣል እየተጋን ያለነው ፣ ለዚህ ነው የአፍሪካ ትልቁን የአቬሽን ማዕከል እየገነባን ያለነው አደራ ስላለብን፣ ሀገርን በላብ የማሻገር አደራ!
በመሆኑም በዚህ ታሪካዊ ቀን፣ እያንዳንዱ ዜጋ በተሰማራበት የሥራ መስክ ሁሉ ለሀገሩ ጡብ የሚደረድር የራሱ ዘመን አርበኛ መሆን ይጠበቅበታል። ዛሬ እኛ የምናከናውናቸው የልማት ሥራዎች፣ የምናሳየው ጽኑ አንድነትና ዳር የምናደርሳቸው ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሀገርን ጠብቀው ላቆዩን አባቶች የምንሰጠው ትልቁ የክብር መግለጫና የታሪክ ምላሻችን ነው።"
ክብር ሀገርን ጠብቀው ላቆዩን አባቶች!
በትጋት ሀገርን ለሚገነቡ ልጆች!
ኢትዮጵያ በላባችን ታላቅ ትሆናለች!
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ድል #
***********************
ሚያዝያ 27 ለእኛ የታሪክ ማኅደር ተገልጦ የሚነበብበት የትላንት ትዝታ ብቻ አይደለም፤ የአርበኞች አባቶቻችንን እና እናቶቻችንን የድል መንፈስ እንደ ብዕር በመጠቀም አዲስ የታሪክ ምዕራፍ መጻፍ የጀመርንበት የትንሣኤ ጉዟችን መነሻ መሠረት ነው! ሚያዝያ 27 የነፃነት ማስታወሻ ብቻ ሳይሆን፣ ወጣቱ ትውልድ ሀገሩን በክብር ለመረከብ ላቡን የሚያፈስበትና ያለውን የሚሰጥበት የቁርጠኝነት ቀን ነው!
ከ85 ዓመታት በፊት አባቶቻችን በደምና በአጥንታቸው ሀገርን ጠብቀው የማቆየት ታሪካዊ ግዴታቸውን በድል ተወጥተዋል። ዛሬ የታሪኩ ምዕራፍ ተቀይሮ ተረኝነቱ የእኛ ሆኗል፤ እነርሱ በነፃነት ያቆዩልንን ሀገር እኛ በዕውቀታችን፣ በላባችንና በሥራችን የመገንባት የዘመኑ አርበኝነት አደራ አለብን።
አባቶች በጠመንጃ ሀገር ጠበቁ፤ እኛ በቴክኖሎጂ ሀገር እንገነባለን። አባቶች ዳር ድንበር አስከበሩ፤ እኛ ድህነትን አሸንፈን ብልጽግናን እናረጋግጣለን። አባቶች ለነፃነት ወደቁ፤ እኛ ለታላቅነት እንቆማለን። ይህ የትውልድ ቅብብል ነው ። ያለ አባቶች ጥበቃ ዛሬ የምንገነባት ሀገር ባልኖረች ነበር፤ ያለ እኛ ግንባታም አባቶች የጠበቋት ሀገር ትርጉም ያለው ሕይወት ለዜጎቿ መስጠት አትችልም። በመሆኑም ትናንት በጀግንነት የተረከብናትን ሀገር፣ ዛሬ በሥልጣኔ አንጸን ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ የሞራል ዕዳ፣ የሀገር አደራ አለብን።
ለዚህም ነው ኢትዮጵያዊያን ከስንዴ ልመና ለመላቀቅ ወገባችንን አጥብቀን፣ ማረሻችንን ጨብጠን የተነሳነው፣ ለዚህ ነው አለም እኪደመም ተደምረን 48 ቢሊዮን ችግኝ የተከለነወ፣ ለዚህ ነው ከመቀነታችን ፈትተን፣ ከጉርሳችን ቀንሰን ህዳሴያችንን እውን ያደረግነው፣ ለዚህ ነው የዘመናት የጉስቁልና ምልክት የነበሩ ያረጁ ከተሞቻችንን ለመለወጥ እያመመን የበረታነው፣ ለዚህ ነው የከረሙ ስብራቶቻችንን ለመጠገን እንመካከር ያለነው፣ ለዚህ ነው ዙሪያው ተቸንክሮብን እስከመቼ እንኖራለን ያልነው! ለዚህ ነው የታዳሽ ሀይል መሠረት ለመጣል እየተጋን ያለነው ፣ ለዚህ ነው የአፍሪካ ትልቁን የአቬሽን ማዕከል እየገነባን ያለነው አደራ ስላለብን፣ ሀገርን በላብ የማሻገር አደራ!
በመሆኑም በዚህ ታሪካዊ ቀን፣ እያንዳንዱ ዜጋ በተሰማራበት የሥራ መስክ ሁሉ ለሀገሩ ጡብ የሚደረድር የራሱ ዘመን አርበኛ መሆን ይጠበቅበታል። ዛሬ እኛ የምናከናውናቸው የልማት ሥራዎች፣ የምናሳየው ጽኑ አንድነትና ዳር የምናደርሳቸው ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሀገርን ጠብቀው ላቆዩን አባቶች የምንሰጠው ትልቁ የክብር መግለጫና የታሪክ ምላሻችን ነው።"
ክብር ሀገርን ጠብቀው ላቆዩን አባቶች!
በትጋት ሀገርን ለሚገነቡ ልጆች!
ኢትዮጵያ በላባችን ታላቅ ትሆናለች!
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ድል #
1 month ago
እንኳን ለ85ኛው የጀግኖች አርበኞች የድል በዓል አደረሳችሁ! - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
****************
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለ85ኛው የጀግኖች አርበኞች የድል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የከንቲባዋ የእንኳን አደረሳችሁ ሙሉ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፦
የአርበኞች ቀንን በደማቅ ሁኔታ ክቡር የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ታየ አፅቀስላሴ ፥የባህር ሃይል ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ ፥ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን እና ጀግኖች አርበኞች በተገኙበት ልዩ ሆኖ በኮሪደር ልማት በተዋበው የአራት ኪሎ ፕላዛ ላይ አክብረናል።
አባቶቻችን እና እናቶቻችን ሕይወታቸውን ሳይሳሱ ራሳቸውን አሳልፈው በመስጠት፣ ዛሬ በነጻ ሕዝቦች ፊት በኩራት የምትጠራዋን ሉዓላዊት ሀገራችንን ኢትዮጵያን አቆይተውልናል።
ይህንን ዘመን ተሻጋሪ እውነት እና ምትክ የማይገኝለት የታሪክ መስዋዕትነት ትውልድ ፈጽሞ አይዘነጋውም።
የዛሬው ዘመን ትውልድ የአባቶቹን መታወሻ እና የታሪክ ቅርስ ከመዘከርና ከመጠበቅ ባሻገር ሌላ አዲስ የአርበኝነት እውድ ሊፈጥር ይገባዋል።
የትላንቱ አርበኝነት ሀገርን ከባዕድ ወራሪ ማዳን እንደነበር ኹሉ፣ የዛሬው አርበኝነት ደግሞ ሀገርን ከድህነት፣ ከኋላቀርነት እና ከተመጽዋችነት ማላቀቅ ነው።
ጀግኖች አባቶቻችን ወራሪውንም ሆነ የውስጥ ባንዳውን ታግለው አሸንፈው ሀገር እንዳቆዩልን ኹሉ፣ እኛም ዛሬ የልማት እና የሰላም ጉዟችንን ለማደናቀፍ የሚሞክሩትን የዘመኑን ባንዳዎች በአንድነት፣ በንቃት እና በሥራ ማሸነፍ ግድ ይለናል።
በድጋሚ እንኳን ለ85ኛው የአርበኞች ቀን አደረሳችሁ።
****************
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለ85ኛው የጀግኖች አርበኞች የድል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የከንቲባዋ የእንኳን አደረሳችሁ ሙሉ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፦
የአርበኞች ቀንን በደማቅ ሁኔታ ክቡር የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ታየ አፅቀስላሴ ፥የባህር ሃይል ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ ፥ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን እና ጀግኖች አርበኞች በተገኙበት ልዩ ሆኖ በኮሪደር ልማት በተዋበው የአራት ኪሎ ፕላዛ ላይ አክብረናል።
አባቶቻችን እና እናቶቻችን ሕይወታቸውን ሳይሳሱ ራሳቸውን አሳልፈው በመስጠት፣ ዛሬ በነጻ ሕዝቦች ፊት በኩራት የምትጠራዋን ሉዓላዊት ሀገራችንን ኢትዮጵያን አቆይተውልናል።
ይህንን ዘመን ተሻጋሪ እውነት እና ምትክ የማይገኝለት የታሪክ መስዋዕትነት ትውልድ ፈጽሞ አይዘነጋውም።
የዛሬው ዘመን ትውልድ የአባቶቹን መታወሻ እና የታሪክ ቅርስ ከመዘከርና ከመጠበቅ ባሻገር ሌላ አዲስ የአርበኝነት እውድ ሊፈጥር ይገባዋል።
የትላንቱ አርበኝነት ሀገርን ከባዕድ ወራሪ ማዳን እንደነበር ኹሉ፣ የዛሬው አርበኝነት ደግሞ ሀገርን ከድህነት፣ ከኋላቀርነት እና ከተመጽዋችነት ማላቀቅ ነው።
ጀግኖች አባቶቻችን ወራሪውንም ሆነ የውስጥ ባንዳውን ታግለው አሸንፈው ሀገር እንዳቆዩልን ኹሉ፣ እኛም ዛሬ የልማት እና የሰላም ጉዟችንን ለማደናቀፍ የሚሞክሩትን የዘመኑን ባንዳዎች በአንድነት፣ በንቃት እና በሥራ ማሸነፍ ግድ ይለናል።
በድጋሚ እንኳን ለ85ኛው የአርበኞች ቀን አደረሳችሁ።
1 month ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለአርበኞች በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ85ኛው የአርበኞች በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-
እንኳን ለ85ኛው የጀግኖች አርበኞች በዓል አደረሳችሁ
ሚያዝያ 27 ቀን ኢትዮጵያውያን ጀግኖች አርበኞች የፋሽስትን ወረራ የቀለበሱበትና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ሙሉ በሙሉ ያስከበሩበት በዓል ነው።
አርበኝነት ማለት ለሀገር ያለ ዋጋ የሚከፈል ከራስ ወዳድነት የነጻ መሥዋዕትነት ነው። ዓላማውም ሀገርንና ሕዝብን ብቻ ማዕከል ያደረገ ነው። ለግል ወይም ለቡድን በተለየ የሚገኝ ነገር የለውም። ለሀገር ከሚገኘው ነጻነት፣ ሉዓላዊነት እና ክብር ከሚደርስ የዜጋ ድርሻ በቀር።
እናትና አባት አርበኞች ከፋሺስት ጋር የተዋጉት ለሀገር እና ለወገን ብለው ነው። በግል ጥቅም ለማግኘትማ ከአርበኝነት ይልቅ ባንዳነት አቋራጭ ነበር። ግን አላደረጉትም።
የአርበኝነት ትግሉ ከሦስት ጠላቶች ጋር የተደረገ ነበር። ከራስ ፍላጎት፣ ከባንዳና ከወራሪ ፋሺስት ጋር። አርበኝነት የራስን ጥቅም ለሀገር ጥቅም ሲባል መተው ነው። አርበኝነት የግል ክብርን፣ የግል ሥልጣንን እና የግል ጥቅምን መሠዋት ነው። ይሄንን ለመቀበል ከጠላት በፊት ራስን ማሸነፍ ይጠይቃል።
ባንዳዎች ማለት ራሳቸውን ማሸነፍ ያቃታቸው ናቸው። የግል ጥቅምንና ክብርን ማሸነፍ ሲያቅታቸው የሀገራቸውን ክብርና ጥቅም ይሸጣሉ። ባንዳነት ማለት ሀገርን ለራስ ጥቅም በመሸጥ የሚከናነቡት የውርደት ካባ ነው። አርበኞች ከባንዳዎች ጋር ታግለዋል። ባንዳዎች በአንድ በኩል ሀገራችሁን ሽጣችሁ እንደኛ በግል ተጠቀሙ ይሏቸዋል። በሌላ በኩል መንገድ እየመሩ ወራሪውን ያመጡባቸዋል። ያም አልሆን ሲላቸው ሕዝቡን በሐሰተኛ ወሬ ልቡን ይሰልቡባቸዋል።
ዛሬም ሦስቱም ጠላቶች አሉ። መልክና ስም ብቻ ቀይረዋል። በሌላም በኩል ዛሬም በየመስኩ የተሠማሩ ኢትዮጵያውያን አርበኞች አሉ።
የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲሳካ ብሔራዊ አርበኞችን ይፈልጋል። የራስ ፍላጎትን፣ ባንዳነትን እና ወራሪን እምቢ የሚል አርበኝነት።
የኢንዱስትሪ አርበኞች፣ የግብርና አርበኞች፣ የጸጥታ አርበኞች፣ የፖለቲካ አርበኞች፣ የንግድ አርበኞች፣ የዲፕሎማሲ አርበኞች፣ የመንግሥት አገልጋይ አርበኞች፣ የሕክምና አርበኞች፣ የትምህርት አርበኞች፣ ወዘተ. ያስፈልጉናል።
ይሄንን በዓል የምናከብረው የየራሳችንን የአርበኝነት ደረጃ በመገምገም ነው። ለኢትዮጵያ ምን ያህል አርበኞች ነን?
ዛሬም የግል ፍላጎት የሚያሸንፋቸው ደካሞች አሉ። ሀገርን አፍርሰው የግል ቤት መሥራት የሚመኙ። ትልቁን መርከብ አፍርሰው ትንንሽ ታንኳዎችን ለመሸጥ የሚመኙ። ለቅንጥብጣቢ ነገር ውርደትን ለመሸከም የማይሰቀቁ።
ዛሬም ወራሪዎች አሉ። በአካል ሀገርን ለመውረር ካሰፈሰፉት በተጨማሪ ድህነት፣ ኋላቀርነትና ሌብነት የሚባሉ እንደ ሰርዶ ሀገርን ወርረው ሽባ የሚያደርጉ ጠላቶች አሉ። ሀገርን ለባዳ ከሚሸጡት ባንዳዎች እኩል፣ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የሚሸጡ ባንዳዎች አሉ። አገልግሎትንና የሕዝብን ሀብት የሚሸቅጡ ባንዳዎች አሉ።
ብሔራዊ አርበኝነት ማለት እነዚህን ሦስት ጠላቶች ታግሎ ማሸነፍ ማለት ነው። ዛሬ የምናየውን የኢትዮጵያ ለውጥና ዕድገት ማስመዝገብ የተቻለው ብሔራዊ አርበኞች በየአካባቢው በመኖራቸው ነው። ብሔራዊ አርበኞች ሦስቱን ጠላቶች እያሸነፉ ቢሆንም ገና ሙሉ በሙሉ ድልን አልተቀዳጁም።
ድሉ እንደ ሚያዝያ 27 የሚታወጀው ኢትዮጵያ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌትስትሆን ነው። ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ከሚገኙ ኃያል ሀገሮች አንዷ ስትሆን ነው።
ይሄንን ድል እውን ለማድረግ ኢትዮጵያን የሚወዱ የኢትዮጵያ አርበኞች ሁሉ እንዲነሡ በዚህ አጋጣሚ ጥሪ አቀርባለሁ።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ሚያዝያ 27፣ 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ85ኛው የአርበኞች በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-
እንኳን ለ85ኛው የጀግኖች አርበኞች በዓል አደረሳችሁ
ሚያዝያ 27 ቀን ኢትዮጵያውያን ጀግኖች አርበኞች የፋሽስትን ወረራ የቀለበሱበትና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ሙሉ በሙሉ ያስከበሩበት በዓል ነው።
አርበኝነት ማለት ለሀገር ያለ ዋጋ የሚከፈል ከራስ ወዳድነት የነጻ መሥዋዕትነት ነው። ዓላማውም ሀገርንና ሕዝብን ብቻ ማዕከል ያደረገ ነው። ለግል ወይም ለቡድን በተለየ የሚገኝ ነገር የለውም። ለሀገር ከሚገኘው ነጻነት፣ ሉዓላዊነት እና ክብር ከሚደርስ የዜጋ ድርሻ በቀር።
እናትና አባት አርበኞች ከፋሺስት ጋር የተዋጉት ለሀገር እና ለወገን ብለው ነው። በግል ጥቅም ለማግኘትማ ከአርበኝነት ይልቅ ባንዳነት አቋራጭ ነበር። ግን አላደረጉትም።
የአርበኝነት ትግሉ ከሦስት ጠላቶች ጋር የተደረገ ነበር። ከራስ ፍላጎት፣ ከባንዳና ከወራሪ ፋሺስት ጋር። አርበኝነት የራስን ጥቅም ለሀገር ጥቅም ሲባል መተው ነው። አርበኝነት የግል ክብርን፣ የግል ሥልጣንን እና የግል ጥቅምን መሠዋት ነው። ይሄንን ለመቀበል ከጠላት በፊት ራስን ማሸነፍ ይጠይቃል።
ባንዳዎች ማለት ራሳቸውን ማሸነፍ ያቃታቸው ናቸው። የግል ጥቅምንና ክብርን ማሸነፍ ሲያቅታቸው የሀገራቸውን ክብርና ጥቅም ይሸጣሉ። ባንዳነት ማለት ሀገርን ለራስ ጥቅም በመሸጥ የሚከናነቡት የውርደት ካባ ነው። አርበኞች ከባንዳዎች ጋር ታግለዋል። ባንዳዎች በአንድ በኩል ሀገራችሁን ሽጣችሁ እንደኛ በግል ተጠቀሙ ይሏቸዋል። በሌላ በኩል መንገድ እየመሩ ወራሪውን ያመጡባቸዋል። ያም አልሆን ሲላቸው ሕዝቡን በሐሰተኛ ወሬ ልቡን ይሰልቡባቸዋል።
ዛሬም ሦስቱም ጠላቶች አሉ። መልክና ስም ብቻ ቀይረዋል። በሌላም በኩል ዛሬም በየመስኩ የተሠማሩ ኢትዮጵያውያን አርበኞች አሉ።
የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲሳካ ብሔራዊ አርበኞችን ይፈልጋል። የራስ ፍላጎትን፣ ባንዳነትን እና ወራሪን እምቢ የሚል አርበኝነት።
የኢንዱስትሪ አርበኞች፣ የግብርና አርበኞች፣ የጸጥታ አርበኞች፣ የፖለቲካ አርበኞች፣ የንግድ አርበኞች፣ የዲፕሎማሲ አርበኞች፣ የመንግሥት አገልጋይ አርበኞች፣ የሕክምና አርበኞች፣ የትምህርት አርበኞች፣ ወዘተ. ያስፈልጉናል።
ይሄንን በዓል የምናከብረው የየራሳችንን የአርበኝነት ደረጃ በመገምገም ነው። ለኢትዮጵያ ምን ያህል አርበኞች ነን?
ዛሬም የግል ፍላጎት የሚያሸንፋቸው ደካሞች አሉ። ሀገርን አፍርሰው የግል ቤት መሥራት የሚመኙ። ትልቁን መርከብ አፍርሰው ትንንሽ ታንኳዎችን ለመሸጥ የሚመኙ። ለቅንጥብጣቢ ነገር ውርደትን ለመሸከም የማይሰቀቁ።
ዛሬም ወራሪዎች አሉ። በአካል ሀገርን ለመውረር ካሰፈሰፉት በተጨማሪ ድህነት፣ ኋላቀርነትና ሌብነት የሚባሉ እንደ ሰርዶ ሀገርን ወርረው ሽባ የሚያደርጉ ጠላቶች አሉ። ሀገርን ለባዳ ከሚሸጡት ባንዳዎች እኩል፣ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የሚሸጡ ባንዳዎች አሉ። አገልግሎትንና የሕዝብን ሀብት የሚሸቅጡ ባንዳዎች አሉ።
ብሔራዊ አርበኝነት ማለት እነዚህን ሦስት ጠላቶች ታግሎ ማሸነፍ ማለት ነው። ዛሬ የምናየውን የኢትዮጵያ ለውጥና ዕድገት ማስመዝገብ የተቻለው ብሔራዊ አርበኞች በየአካባቢው በመኖራቸው ነው። ብሔራዊ አርበኞች ሦስቱን ጠላቶች እያሸነፉ ቢሆንም ገና ሙሉ በሙሉ ድልን አልተቀዳጁም።
ድሉ እንደ ሚያዝያ 27 የሚታወጀው ኢትዮጵያ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌትስትሆን ነው። ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ከሚገኙ ኃያል ሀገሮች አንዷ ስትሆን ነው።
ይሄንን ድል እውን ለማድረግ ኢትዮጵያን የሚወዱ የኢትዮጵያ አርበኞች ሁሉ እንዲነሡ በዚህ አጋጣሚ ጥሪ አቀርባለሁ።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ሚያዝያ 27፣ 2018 ዓ.ም
1 month ago
አርበኝነት በእውቀት ጎዳና መመራት ነው - ፕሬዚዳንት ታዬ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ አርበኝነት በእውቀት ጎዳና መመራት ነው አሉ።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት 85ኛው የአርበኞች ቀን በአዲስ አበባ አራት ኪሎ የአርበኞች መታሰቢያ ሐውልት እየተከበረ ነው።
በበዓሉ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞ ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፣ ጀግኖች አርበኞች፣ የአርበኛ ቤተሰቦች እና የመዲናዋ ነዋሪዎች በስፍራው ተገኝተዋል።
ፕሬዚዳንት ታዬ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሰላም፣ ነፃነት እና በራስ መተማመን ማንም የማይነጥቀን ኖረን የያዝነው የራሳችን ሐብት ነው ብለዋል።
ጀግንነት የሰከነና ለሀገር የሚታበኑበት ጸጋ መሆኑን ገልጸው፤ በላባቸው፣ በደማችው፣ በሙያቸውና በእውቀታቸው ሀገርን የሚያገለግሉ የዘመኑ አርበኞች እንደሆኑ አስገንዝበዋል።
በጥፋት መስመር ላይ የተሰማሩ ወደልማት መስመር እንዲመለሱም ጥሪ አቅርበዋል።
ሀሰትን፣ ውስልትንና ቅጥፈት የማይፀየፍ ትውልድ ከአርበኝነህ እንደሚርቅ አስረድተው፤ አርበኝነት በእውቀት ጎዳና መመራት ነው ሲሉ ገልጸዋል።
አርበኝነት የዕድሜ ልክ መታመን ውጤት መሆኑንም አፅንዖት በመስጠት አንስተዋል።
በአሸናፊ ሽብሩ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ አርበኝነት በእውቀት ጎዳና መመራት ነው አሉ።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት 85ኛው የአርበኞች ቀን በአዲስ አበባ አራት ኪሎ የአርበኞች መታሰቢያ ሐውልት እየተከበረ ነው።
በበዓሉ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞ ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፣ ጀግኖች አርበኞች፣ የአርበኛ ቤተሰቦች እና የመዲናዋ ነዋሪዎች በስፍራው ተገኝተዋል።
ፕሬዚዳንት ታዬ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሰላም፣ ነፃነት እና በራስ መተማመን ማንም የማይነጥቀን ኖረን የያዝነው የራሳችን ሐብት ነው ብለዋል።
ጀግንነት የሰከነና ለሀገር የሚታበኑበት ጸጋ መሆኑን ገልጸው፤ በላባቸው፣ በደማችው፣ በሙያቸውና በእውቀታቸው ሀገርን የሚያገለግሉ የዘመኑ አርበኞች እንደሆኑ አስገንዝበዋል።
በጥፋት መስመር ላይ የተሰማሩ ወደልማት መስመር እንዲመለሱም ጥሪ አቅርበዋል።
ሀሰትን፣ ውስልትንና ቅጥፈት የማይፀየፍ ትውልድ ከአርበኝነህ እንደሚርቅ አስረድተው፤ አርበኝነት በእውቀት ጎዳና መመራት ነው ሲሉ ገልጸዋል።
አርበኝነት የዕድሜ ልክ መታመን ውጤት መሆኑንም አፅንዖት በመስጠት አንስተዋል።
በአሸናፊ ሽብሩ
1 month ago
የላብ አድዋ፡- አዲሱ አርበኝነት
****************
የኢትዮጵያ ታሪክ በጽናትና በጀግንነት የወርቅ ቀለም የተጻፈ መጽሐፍ ነው። አባቶቻችንና እናቶቻችን ሀገርን በክብር አቆይተውልናል።ትናንት አርበኝነት ማለት በጫካና በዱር ለነፃነት መውደቅ፣ በደምና በአጥንት ድንበር ማስከበር ነበር። ዛሬ ግን የታሪክ የሩጫ ቅብብል በትውልዱ እጅ ገብቷል፤ የዛሬው አርበኝነት ግንባሩ ተቀይሯል፣ ጠላቱም መልክ ለውጧል። ዛሬ አርበኝነት ማለት ለሀገር ብልጽግና መቆም፣ ድህነትንና ድንቁርናን ድል ማድረግ ነው።
ታሪክን መዘከር የትናንትን ድል ለማውራት ብቻ ሳይሆን ለነገው ጉዞ ስንቅ ለመሰብሰብ ነው። የአድዋ ድል መታሰቢያና የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ዝም ብለው የድንጋይና የሲሚንቶ ክምር ህንፃዎች አይደሉም። እነርሱ የኢትዮጵያዊነት ጽናትና የጥበብ ጥማት ህያው መገለጫዎች ናቸው።
"ከታሪክ ያልተማረ፣ ለታሪክ አይበቃም" እንደሚባለው እነዚህ መዘክሮች ወጣቱ ትውልድ የትናንቱን ነፃነት እንዲዳስሰው፣ ዛሬን ደግሞ በኩራት እንዲተነፍሰው የሚያስችሉ የንቃተ-ህሊና ማዕከላት ናቸው።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ አይደለም። እውነተኛ ሉዓላዊነት የሚለካው በምግብ ራስን በመቻል፣ በኢንዱስትሪ ብቃትና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ልዕልና ነው።
ትናንት በጠብመንጃ ድንበር ይከበር ነበር፤ ዛሬ ግን የሉዓላዊነት ድንበራችን የስንዴ ማሳዎቻችን፣ የፋብሪካዎቻችን ጭስና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ኮዲንግ ብቃታችን ነው። ከእርዳታ ጠባቂነትና ከተመፅዋችነት ሰንሰለት ተላቆ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገር፣ የዘመናችን ሌላው "የአድዋ ድል" ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው የኢኮኖሚ ነፃነት አዋጅ ነው።
ታላቁ የህዳሴ ግድብ የአዲሱ አርበኝነታችን ትልቅ ማኅተም ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችንና የዲፕሎማሲ አዙሪቶችን ተቋቁመን፣ ከራስ ጉርስ ቀንሰን የዓባይን ውሃ መገደብ መቻላችን "እምቢኝ ለጭቆና" የሚለው የጥንት መንፈሳችን በዘመናዊ ምህንድስና መገለጡን ያሳያል። ከዚህም በተጓዳኝ፣ ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋን በዲፕሎማሲና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማሳካት የምታደርገው ጥረት፣ የህልውናችንና የኢኮኖሚ ነፃነታችን ዋስትና ነው።
የብሪክስ አባልነትና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ቀና ብላ እንድትቆም እያደረጓት ነው። ከተሞቻችንን ለኑሮ ምቹ ማድረግና ቱሪዝምን ማስፋፋት የሀገር ፍቅር ተግባራዊ መግለጫዎች ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ሁሉ ልማቶችና ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ዘላቂ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና አንድነት ሲሰፍን ብቻ ነው። የአባቶቻችን አንድነት በጠላት ፊት የነበረውን አሸናፊነት፣ እኛ ዛሬ በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይትና በሀገራዊ ምክክር ልንደግመው ይገባል። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በሀገራዊ ስምምነት ካልተሳሰርን፣ ድህነት የሚባለውን የጋራ ጠላታችንን ማሸነፍ አንችልም።
አርበኝነትን ከአውድማ ወደ ፋብሪካ፣ ከዱር ወደ ላቦራቶሪ፣ ከጠመንጃ ወደ ኮዲንግ (Coding) የምናሸጋግርበት ጊዜ አሁን ነው። አባቶቻችን በደማቸው የጻፉትን ነፃነት፣ እኛ በላባችንና በእውቀታችን ቀለም እናድምቀው።
ኢትዮጵያዊነት ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ጥበብ ነውና የትናንቱ የድል መንፈስ ዛሬም በሥራችን ውስጥ ይንገሥ!
****************
የኢትዮጵያ ታሪክ በጽናትና በጀግንነት የወርቅ ቀለም የተጻፈ መጽሐፍ ነው። አባቶቻችንና እናቶቻችን ሀገርን በክብር አቆይተውልናል።ትናንት አርበኝነት ማለት በጫካና በዱር ለነፃነት መውደቅ፣ በደምና በአጥንት ድንበር ማስከበር ነበር። ዛሬ ግን የታሪክ የሩጫ ቅብብል በትውልዱ እጅ ገብቷል፤ የዛሬው አርበኝነት ግንባሩ ተቀይሯል፣ ጠላቱም መልክ ለውጧል። ዛሬ አርበኝነት ማለት ለሀገር ብልጽግና መቆም፣ ድህነትንና ድንቁርናን ድል ማድረግ ነው።
ታሪክን መዘከር የትናንትን ድል ለማውራት ብቻ ሳይሆን ለነገው ጉዞ ስንቅ ለመሰብሰብ ነው። የአድዋ ድል መታሰቢያና የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ዝም ብለው የድንጋይና የሲሚንቶ ክምር ህንፃዎች አይደሉም። እነርሱ የኢትዮጵያዊነት ጽናትና የጥበብ ጥማት ህያው መገለጫዎች ናቸው።
"ከታሪክ ያልተማረ፣ ለታሪክ አይበቃም" እንደሚባለው እነዚህ መዘክሮች ወጣቱ ትውልድ የትናንቱን ነፃነት እንዲዳስሰው፣ ዛሬን ደግሞ በኩራት እንዲተነፍሰው የሚያስችሉ የንቃተ-ህሊና ማዕከላት ናቸው።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ አይደለም። እውነተኛ ሉዓላዊነት የሚለካው በምግብ ራስን በመቻል፣ በኢንዱስትሪ ብቃትና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ልዕልና ነው።
ትናንት በጠብመንጃ ድንበር ይከበር ነበር፤ ዛሬ ግን የሉዓላዊነት ድንበራችን የስንዴ ማሳዎቻችን፣ የፋብሪካዎቻችን ጭስና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ኮዲንግ ብቃታችን ነው። ከእርዳታ ጠባቂነትና ከተመፅዋችነት ሰንሰለት ተላቆ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገር፣ የዘመናችን ሌላው "የአድዋ ድል" ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው የኢኮኖሚ ነፃነት አዋጅ ነው።
ታላቁ የህዳሴ ግድብ የአዲሱ አርበኝነታችን ትልቅ ማኅተም ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችንና የዲፕሎማሲ አዙሪቶችን ተቋቁመን፣ ከራስ ጉርስ ቀንሰን የዓባይን ውሃ መገደብ መቻላችን "እምቢኝ ለጭቆና" የሚለው የጥንት መንፈሳችን በዘመናዊ ምህንድስና መገለጡን ያሳያል። ከዚህም በተጓዳኝ፣ ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋን በዲፕሎማሲና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማሳካት የምታደርገው ጥረት፣ የህልውናችንና የኢኮኖሚ ነፃነታችን ዋስትና ነው።
የብሪክስ አባልነትና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ቀና ብላ እንድትቆም እያደረጓት ነው። ከተሞቻችንን ለኑሮ ምቹ ማድረግና ቱሪዝምን ማስፋፋት የሀገር ፍቅር ተግባራዊ መግለጫዎች ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ሁሉ ልማቶችና ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ዘላቂ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና አንድነት ሲሰፍን ብቻ ነው። የአባቶቻችን አንድነት በጠላት ፊት የነበረውን አሸናፊነት፣ እኛ ዛሬ በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይትና በሀገራዊ ምክክር ልንደግመው ይገባል። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በሀገራዊ ስምምነት ካልተሳሰርን፣ ድህነት የሚባለውን የጋራ ጠላታችንን ማሸነፍ አንችልም።
አርበኝነትን ከአውድማ ወደ ፋብሪካ፣ ከዱር ወደ ላቦራቶሪ፣ ከጠመንጃ ወደ ኮዲንግ (Coding) የምናሸጋግርበት ጊዜ አሁን ነው። አባቶቻችን በደማቸው የጻፉትን ነፃነት፣ እኛ በላባችንና በእውቀታችን ቀለም እናድምቀው።
ኢትዮጵያዊነት ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ጥበብ ነውና የትናንቱ የድል መንፈስ ዛሬም በሥራችን ውስጥ ይንገሥ!
1 month ago
ከደምና አጥንት... ወደ ላብና እውቀት፦ የዘመኑ አርበኝነት ጥሪ
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያውያን አባቶቻችንና እናቶቻችን "የማይነቃነቅ ድንጋይ፣ የማይታጠፍ ብረት" ሆነው ሀገርን አቆይተውልናል። ትላንት አርበኝነት ማለት በጫካና በዱር ለነፃነት መውደቅ ነበር፤ ዛሬ ግን አርበኝነት ማለት ለሀገር ብልጽግና መቆም ነዉ። የአባቶቻችንን ገድል በታሪክ መጻሕፍት ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመናዊ መታሰቢያዎችና በልማት ስራዎቻችን ውስጥ ህያው ማድረግ የዚህ ትውልድ የቤት ስራ ነው።
የአድዋ ድል መታሰቢያና የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ዝም ብለው ህንፃዎች አይደሉም፤ እነርሱ የኢትዮጵያዊነት ጽናት መገለጫ ናቸው። "የቆመበትን መሠረት የማያውቅ፣ የሚሄድበትን መንገድ አያውቅም።"እንደሚባለዉ እነዚህ መዘክሮች ወጣቱ ትውልድ የትናንቱን ነፃነት እንዲዳስሰው፣ ዛሬን ደግሞ በኩራት እንዲተነፍሰው ያደርጉታል።
ዛሬ ጦርነቱ የተለየ መልክ ይዟል። ጠላቶቻችን ድህነት፣ ኋላቀርነትና የተመፅዋችነት ሰንሰለት ናቸው። ትላንት በጠብመንጃ ድንበር ይከበር ነበር፤ ዛሬ ግን ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው በስንዴ ልማት፣ በኢንዱስትሪ ሉዓላዊነትና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃት ነው። ዛሬ በቴክኖሎጂና በሳይንስ እውቀት ካልታጠቅን የነገዋን ኢትዮጵያ ማስጠበቅ አንችልም። ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገራችን፣ የዘመናችን ሌላው አድዋ ነው።
ታላቁ የህዳሴ ግድብም የዚሁ አዲስ አርበኝነት ማኅተም ነው። የውጭ ጫናን ተቋቁሞ፣ ከራስ ጉርስ ቀንሶ የዓባይን ውሃ መግደብ መቻል "እምቢኝ ለጭቆና" የሚለው የጥንት መንፈሳችን በዘመናዊ ምህንድስና መገለጡ ነው። ከዚህም ባለፈ ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋን በዲፕሎማሲና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማሳካት የምታደርገው ጥረት፣ የህልውናችንና የኢኮኖሚ ነፃነታችን ዋስትና ነው።
የብሪክስ (BRICS) አባልነትና የኮሪደር ልማት ስራዎች ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ቀና ብላ እንድትቆም እያደረጓት ነው። ከተሞቻችንን ለኑሮ ምቹ ማድረግና ቱሪዝምን ማስፋፋት ሀገርን የመውደድ ተግባራዊ መግለጫዎች ናቸው። ይሁንና ይህ ሁሉ ውጤት ትርጉም የሚኖረው በውስጣችን ሰላምና አንድነት ሲሰፍን ብቻ ነው። የአባቶቻችን አንድነት በጠላት ፊት የነበረውን ጥንካሬ፣ እኛ ዛሬ በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይትና በሀገራዊ ምክክር ልንደግመው ይገባል። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በሀገራዊ ስምምነት ካልተሳሰርን ድህነትን ማሸነፍ አንችልም።
አርበኝነትን ከአውድማ ወደ ፋብሪካ፣ ከዱር ወደ ላቦራቶሪ፣ ከጠመንጃ ወደ ኮዲንግ (Coding) የምናሸጋግርበት ሊሆን ይገባል። አባቶቻችን በደማቸው የጻፉትን ነፃነት፣ እኛ በላባችንና በእውቀታችን ቀለም እናድምቀው።
ኢትዮጵያዊነት ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ጥበብ ነውና፣ የትናንቱ የድል መንፈስ ዛሬም በሥራችን ውስጥ ይንገሥ!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopia #adwa #addisababa #ዓድዋ
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያውያን አባቶቻችንና እናቶቻችን "የማይነቃነቅ ድንጋይ፣ የማይታጠፍ ብረት" ሆነው ሀገርን አቆይተውልናል። ትላንት አርበኝነት ማለት በጫካና በዱር ለነፃነት መውደቅ ነበር፤ ዛሬ ግን አርበኝነት ማለት ለሀገር ብልጽግና መቆም ነዉ። የአባቶቻችንን ገድል በታሪክ መጻሕፍት ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመናዊ መታሰቢያዎችና በልማት ስራዎቻችን ውስጥ ህያው ማድረግ የዚህ ትውልድ የቤት ስራ ነው።
የአድዋ ድል መታሰቢያና የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ዝም ብለው ህንፃዎች አይደሉም፤ እነርሱ የኢትዮጵያዊነት ጽናት መገለጫ ናቸው። "የቆመበትን መሠረት የማያውቅ፣ የሚሄድበትን መንገድ አያውቅም።"እንደሚባለዉ እነዚህ መዘክሮች ወጣቱ ትውልድ የትናንቱን ነፃነት እንዲዳስሰው፣ ዛሬን ደግሞ በኩራት እንዲተነፍሰው ያደርጉታል።
ዛሬ ጦርነቱ የተለየ መልክ ይዟል። ጠላቶቻችን ድህነት፣ ኋላቀርነትና የተመፅዋችነት ሰንሰለት ናቸው። ትላንት በጠብመንጃ ድንበር ይከበር ነበር፤ ዛሬ ግን ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው በስንዴ ልማት፣ በኢንዱስትሪ ሉዓላዊነትና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃት ነው። ዛሬ በቴክኖሎጂና በሳይንስ እውቀት ካልታጠቅን የነገዋን ኢትዮጵያ ማስጠበቅ አንችልም። ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገራችን፣ የዘመናችን ሌላው አድዋ ነው።
ታላቁ የህዳሴ ግድብም የዚሁ አዲስ አርበኝነት ማኅተም ነው። የውጭ ጫናን ተቋቁሞ፣ ከራስ ጉርስ ቀንሶ የዓባይን ውሃ መግደብ መቻል "እምቢኝ ለጭቆና" የሚለው የጥንት መንፈሳችን በዘመናዊ ምህንድስና መገለጡ ነው። ከዚህም ባለፈ ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋን በዲፕሎማሲና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማሳካት የምታደርገው ጥረት፣ የህልውናችንና የኢኮኖሚ ነፃነታችን ዋስትና ነው።
የብሪክስ (BRICS) አባልነትና የኮሪደር ልማት ስራዎች ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ቀና ብላ እንድትቆም እያደረጓት ነው። ከተሞቻችንን ለኑሮ ምቹ ማድረግና ቱሪዝምን ማስፋፋት ሀገርን የመውደድ ተግባራዊ መግለጫዎች ናቸው። ይሁንና ይህ ሁሉ ውጤት ትርጉም የሚኖረው በውስጣችን ሰላምና አንድነት ሲሰፍን ብቻ ነው። የአባቶቻችን አንድነት በጠላት ፊት የነበረውን ጥንካሬ፣ እኛ ዛሬ በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይትና በሀገራዊ ምክክር ልንደግመው ይገባል። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በሀገራዊ ስምምነት ካልተሳሰርን ድህነትን ማሸነፍ አንችልም።
አርበኝነትን ከአውድማ ወደ ፋብሪካ፣ ከዱር ወደ ላቦራቶሪ፣ ከጠመንጃ ወደ ኮዲንግ (Coding) የምናሸጋግርበት ሊሆን ይገባል። አባቶቻችን በደማቸው የጻፉትን ነፃነት፣ እኛ በላባችንና በእውቀታችን ቀለም እናድምቀው።
ኢትዮጵያዊነት ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ጥበብ ነውና፣ የትናንቱ የድል መንፈስ ዛሬም በሥራችን ውስጥ ይንገሥ!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopia #adwa #addisababa #ዓድዋ
Sponsored by
Surafel
3 months ago
“በኢ-ፍትሐዊነት የተዘጋብንን የባህር በር በማስከፈት የራሳችንን ታላቅ ታሪክ ሰርቶ ለማለፍ በቁጭት እንነሳ”
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
#ethiopia | በኢ-ፍትሐዊነት የተዘጋብንን የባሕር በር በማስከፈት የቀድሞ አርበኞቻችንን ታሪክ ከመዘከር ባለፈ ይህ ትውልድ የራሱን ታላቅ ታሪክ ሠርቶ ለማለፍ በቁጭት ሊነሳ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባዋ ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል መሪ ቃል በመላው ኢትዮጵያ በድምቀት እየተከበረ በሚገኝበት ወቅት ሲሆን፤ ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦችና የአፍሪካውያን የነፃነት ፋና መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በውስጣዊ ጉዳዮች ልዩነት ቢኖራቸውም፣ በሀገር ሉዓላዊነትና በብሔራዊ ክብር ላይ ግን በጋራ መቆም እንዳለባቸው ዓድዋ ትልቅ ቁምነገር ያስተማረበት መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍንም በበኩላቸው፤ በደምና በአጥንታቸው ሀገርን ላቆዩ ጀግኖች ተገቢውን ክብር መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #ዓድዋ #የባሕር_በር #ጀግንነት #አዳነች_አቤቤ #ዳንኤል_ጆቴ #አርበኝነት
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
#ethiopia | በኢ-ፍትሐዊነት የተዘጋብንን የባሕር በር በማስከፈት የቀድሞ አርበኞቻችንን ታሪክ ከመዘከር ባለፈ ይህ ትውልድ የራሱን ታላቅ ታሪክ ሠርቶ ለማለፍ በቁጭት ሊነሳ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባዋ ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል መሪ ቃል በመላው ኢትዮጵያ በድምቀት እየተከበረ በሚገኝበት ወቅት ሲሆን፤ ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦችና የአፍሪካውያን የነፃነት ፋና መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በውስጣዊ ጉዳዮች ልዩነት ቢኖራቸውም፣ በሀገር ሉዓላዊነትና በብሔራዊ ክብር ላይ ግን በጋራ መቆም እንዳለባቸው ዓድዋ ትልቅ ቁምነገር ያስተማረበት መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍንም በበኩላቸው፤ በደምና በአጥንታቸው ሀገርን ላቆዩ ጀግኖች ተገቢውን ክብር መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #ዓድዋ #የባሕር_በር #ጀግንነት #አዳነች_አቤቤ #ዳንኤል_ጆቴ #አርበኝነት
3 months ago
እንኳን ደስ አላችሁ ~ እንኳን ደስ አለን !
#ethiopia | “የኮምትኬስ ካርኩ ( ሚዛን- አማን ) ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ተብሎ እንዲሰየም በሙሉ ድምፅ በምክር ቤት ፀደቀ ፦
የሚዛን -አማን ከተማ አሥተዳደር ምክር ቤት የሚዛን አማን ከተማ ዓለም- አማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቀኝ አዝማች ኮምትኬስ ካርኩ ሥም እንዲሠየም አፀደቀ።
የሚዛን- አማን አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 18ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 34ኛ መደበኛ ጉባኤ በተለያዩ አጀንዳዎች ሲመክር ቆይቷል።
ጉባኤው የቀኛዝማች ከምትኬስ ጋርኩ እና የልጃቸው ግራዝማች ጃዊ ኮምትኬስ የሠሯቸው የልማት ስራዎች ከተማዋ ዛሬ ላይ ለመድረስ መሠረት የጣሉ መሆናቸው ተገልጿል።
ለሕዝብ ሥለ አበረከቷቸው የአርበኝነት እና የልማት ሥራ በሚዛን- ቴፒ ዩንቨርስቲ ተቋም ጥናትና ምርምር ተደርጎ በሚለከታቸው አካላት እየተተቸ መሆኑ ተጠቁሟል።
በተለይ የቤንች ምድር በትራንስፓርት ያለመኖር ከማዕከላዊ መንግስት የራቁ መሆናቸው መነሻ በማድረግ ቦታቸውን በመፍቀድ የአውሮፕላን ማረፊያ እንዲሠሩ ያደረጉ ናቸው።
አዲስ እየተገነባ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የሚዛን አማን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሥማቸው እንዲሠየም ቀርቦ ምክር ቤቱ መክሮበታል።
በዚህ መሠረት አዲሱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያው “የሚዛን- አማን ኮምትኬስ ካርኩ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ” ተብሎ እንጢጠራና እንዲሠየም በሚዛን- አማን ከተማ ምክር ቤቱ አባላት በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።
ጌታመሳይ ሙሉጌታ ~ (Getamesay Mulugeta)
#ethiopia | “የኮምትኬስ ካርኩ ( ሚዛን- አማን ) ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ተብሎ እንዲሰየም በሙሉ ድምፅ በምክር ቤት ፀደቀ ፦
የሚዛን -አማን ከተማ አሥተዳደር ምክር ቤት የሚዛን አማን ከተማ ዓለም- አማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቀኝ አዝማች ኮምትኬስ ካርኩ ሥም እንዲሠየም አፀደቀ።
የሚዛን- አማን አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 18ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 34ኛ መደበኛ ጉባኤ በተለያዩ አጀንዳዎች ሲመክር ቆይቷል።
ጉባኤው የቀኛዝማች ከምትኬስ ጋርኩ እና የልጃቸው ግራዝማች ጃዊ ኮምትኬስ የሠሯቸው የልማት ስራዎች ከተማዋ ዛሬ ላይ ለመድረስ መሠረት የጣሉ መሆናቸው ተገልጿል።
ለሕዝብ ሥለ አበረከቷቸው የአርበኝነት እና የልማት ሥራ በሚዛን- ቴፒ ዩንቨርስቲ ተቋም ጥናትና ምርምር ተደርጎ በሚለከታቸው አካላት እየተተቸ መሆኑ ተጠቁሟል።
በተለይ የቤንች ምድር በትራንስፓርት ያለመኖር ከማዕከላዊ መንግስት የራቁ መሆናቸው መነሻ በማድረግ ቦታቸውን በመፍቀድ የአውሮፕላን ማረፊያ እንዲሠሩ ያደረጉ ናቸው።
አዲስ እየተገነባ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የሚዛን አማን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሥማቸው እንዲሠየም ቀርቦ ምክር ቤቱ መክሮበታል።
በዚህ መሠረት አዲሱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያው “የሚዛን- አማን ኮምትኬስ ካርኩ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ” ተብሎ እንጢጠራና እንዲሠየም በሚዛን- አማን ከተማ ምክር ቤቱ አባላት በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።
ጌታመሳይ ሙሉጌታ ~ (Getamesay Mulugeta)
4 months ago
የነፃነት ሻማው እሳት፡ ሸዋረገድ ገድሌ እና የየካቲት 12 ቁጭት
የካቲት 12፤ የታሪክ ጥቁር ጠባሳ ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነት ጽናት ዳግም የተወለደበት የደም ጥምቀት ቀን ነው። የፋሺስት ጣሊያን ግፈኛ መሪ ግራዚያኒ በአብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ቦምብ ቆስሎ፣ ለበቀል ባዘዘው የጅምላ ጭፍጨፋ አዲስ አበባ በደም ስትታጠብ፣ ያ ያፈሰሰው ደም ግን አልደረቀም።
ይልቁንም እንደ ሸዋረገድ ገድሌ ያሉ ቆራጥ እናቶችን ልብ በማንደድ ለነፃነት የሚፋጅ እሳት ሆኖ ተቀጣጠለ።
ፈላስፎች ስለ ነፃነት ሲተነትኑ "ነፃነት የሚገኘው በሞት ጥላ ስር ቆሞ ለሕይወት ዋጋ ሲሰጥ ነው" ይላሉ። ሸዋረገድ ገድሌ ለዚህ የፍልስፍና እውነት ሕያው ምስክር ነበሩ። የታሪክ ምሁራን ዘመን ተሻጋሪ ጀግንነታቸውን ሲዘክሩ፣ ፖለቲካል ሳይንቲስቶች ደግሞ በሴቶች የማይበገር የዲፕሎማሲ እና የስለላ ጥበብ ላይ ያተኩራሉ። ሸዋረገድ ገድሌ ግን ከቃላት በላይ የሆነች፣ ለሀገሯ ፍቅር ራሷን መሥዋዕት ያደረገች "የሴት ጀግና " ነበረች።
የቁጭቱ ጅማሬ እና የአደባባዩ እምቢተኝነት
ወይዘሮ ሸዋረገድ ገድሌ በ1878 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ተወልደው፣ በአባታቸው በፊታውራሪ ገድሌ እቅፍ ውስጥ የሀገር ፍቅርን እየተጋቱ አደጉ። በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ጣሊያን ዳግም ሀገራችንን ሲወር፣ ሸዋረገድ የ52 ዓመት ጎልማሳ ነበሩ። በወቅቱ ጣሊያን አዲስ አበባን ሲቆጣጠር፣ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ወርዶ የጣሊያን ባንዲራ ሲሰቀል ሲያዩ ልባቸው በሀዘን ተሰበረ።
ያኔ ነበር የየካቲት 12 የጭፍጨፋ ድባብ በከተማዋ ላይ ሲያንዣብብ፣ ሸዋረገድ በአደባባይ ወጥተው ማልቀስ የጀመሩት። ጣሊያኖች "ለምን ታለቅሻለሽ?" ብለው ሲጠይቋቸው የሰጡት ምላሽ ለታሪክ ምሁራን ትልቅ ትምህርት ነው፦
"አዎ አልቅሻለሁ፤ የሀገሬን መወረርና መዋረድ ያወቅሁት የኛ ሰንደቅ ዓላማ ወርዶ የናንተ ሲውለበለብ በመታየቱ ነው። ሰው ለእናት ሀገሩ ቢያለቅስ ነውሩ የት ላይ ነው?"
ይህ ንግግር የፖለቲካ ሳይንስ ምሁራን እንደሚሉት "የሕዝባዊ እምቢተኝነት" (Civil Disobedience) ቀዳሚ ማሳያ ነበር። በዚህ ድርጊታቸው የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በልመና ወደ እስር ተቀየረላቸው። ነገር ግን እስር ቤቱ ለእሳቸው የትግል አውድማ እንጂ የመሸነፊያ ስፍራ አልነበረም።
ልብ አንጠልጣይ ተጋድሎ እና የግል መስዋዕትነት
የሸዋረገድ ገድሌ ታሪክ በጣም ልብን የሚነካው በሁለት ምክንያቶች ነው፡- ንብረታቸውን ለሀገር መስጠታቸው እና በልጆቻቸው ላይ የደረሰው መከራ።
አባታቸው ፊታውራሪ ገድሌ ካወረሷቸው ሰፊ መሬትና ሀብት መካከል አብዛኛውን በመሸጥ ለአርበኞች ጥይት፣ ልብስና መድኃኒት ይገዙ ነበር። የሴትነት አጥሩን ሰብረው፣ የቤት እመቤትነቱን ትተው፣ በንግድ ስራ ያገኙትን ትርፍ ሁሉ ለቀይ መስቀልና ለነፃነት ትግሉ አዋሉ።
በጣም አስለቃሹ የታሪካቸው ምዕራፍ የሚጀምረው በሚስጥራዊ መረጃ ልውውጥ ወቅት ነው። መረጃዎችን በቅርጫት ውስጥ ደብቀው ለአርበኞች ሲልኩ፣ መልእክተኛው ተይዞ መረጃው እንዳይወጣ ደብዳቤውን አላምጦ ዋጠው።
ሸዋረገድ ይህን ሲሰሙ መልእክተኛው መረጃውን በእርግጥም መዋጡን ለማረጋገጥ ኮሶ በጥብጠው አጠጡት። ይህ የሚያሳየው ለሀገር ነፃነት ሲባል የሚደረግን ጥንቃቄና የላቀ የቁርጠኝነት ደረጃ ነው።
የሸዋረገድን ልብ የሰበረው ግን የታሰሩ እለት የማደጎ ልጃቸው በዓይናቸው ፊት በፋሺስቶች መገደሉ ነበር። እናት ሆና ልጇ ሲታረድ እያየች፣ ለሀገሯ ምስጢር ግን አልበገረችም። ጣሊያኖች በኤሌክትሪክ ገመድ እየገረፉ ሰውነቷን ሲያቆስሉ፣ እሷ ግን "ለሀገሬ የሰራሁት ሲያንስ እንጂ አይበዛብኝም" በሚል ጽናት መከራውን ተቀበለች።
ከአሲናራ ደሴት እስከ አዲስ ዓለም ምሽግ
ፋሺስቶች ሸዋረገድን አዲስ አበባ ውስጥ ማሰር ስላልቻሉ፣ ወደ ሜድትራኒያን ባሕር አሲናራ ወደተባለችው የጣሊያን ደሴት በግዞት ሰደዷቸው። እዚያም ሆነው ግን አልተኙም። ከጅቡቲ በመጣላቸው "ሞአ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ" የሚል ምልክት ያለበት ወረቀት ላይ፣ ከንጉሡ የተላከ መልዕክት በማስመሰል ለአርበኞች የሞራል ማበረታቻ ደብዳቤዎችን በምስጢር ይልኩ ነበር።
ከግዞት ተመልሰው እንደገቡም በቀጥታ ወደ ጦር ግንባር ነበር ያመሩት። የታሪክ ጸሐፊዎች እንደሚዘግቡት፣ በህዳር 5 ቀን 1933 ዓ.ም. የአዲስ ዓለም የጣሊያን ምሽግ ሲሰበር፣ ዋናውን የመረጃ አውታር የዘረጉትና ዕቅዱን የነደፉት እሳቸው ነበሩ።
ለአራት ሰዓታት ያህል መቂ አካባቢ በነበረው ውጊያ ላይ ራሳቸው ጥይት እየተኮሱ ተዋግተዋል። በመጨረሻም በገረሱ ዱኪ ጦር አቅራቢያ በተደረገ ድንገተኛ ውጊያ ተማረኩ። ወደ እስር ቤት ተወስደው የፊጥኝ ታስረው እያለ እንኳን፣ "የሀገሬ ነፃነት ካልመጣ ሞቴን እመርጣለሁ" በማለት የረሀብ አድማ አድርገዋል።
የታሪክ ምሁራንና የትውልድ ዕዳ
የፖለቲካ ሳይንስ ጸሐፊዎች ሸዋረገድን "የውስጥ አርበኝነትና የደጀን ግንባታ ምሰሶ" ይሏታል። ፈላስፎች ደግሞ "የአንድ ሀገር ነፃነት የሚረጋገጠው በወንዶች ክንድ ብቻ ሳይሆን፣ በሴቶች ጽናትና መስዋዕትነት ነው" ለሚለው አስተሳሰብ ሸዋረገድን እንደ ትልቅ ምሳሌ ያነሳሉ።
ሸዋረገድ ገድሌ በጥቅምት 22 ቀን 1942 ዓ.ም. ሲያርፉ፣ ሕዝቡ በለቅሶ እንዲህ ብሎ ነበር፡-
"እናንት ወጥ ቤቶች በርበሬ ቀንጥሱ፣
እናንት ሥጋ ቤቶች ሥጋውን ምረጡ፣
ሸዋረገድ ገድሌ ለገና ሲመጡ...
ቤተሰቧ ሰፊ ገና እና ጥቅምት፣
ሸዋረገድ ገድሌ እንደምን ትሙት?"
በእርግጥም ሸዋረገድ አልሞተችም። የካቲት 12 ቀን በፈሰሰው ደም ውስጥ፣ በአሲናራ ደሴት ግዞት ውስጥ፣ በአዲስ ዓለም ምሽግ ሰበራ ውስጥ እና በዛሬዋ ኢትዮጵያ ውስጥ ስሟ ህያው ነው።
ትምህርቱ፡- ጀግንነት ጾታ የለውም፤ ሀገር ወዳድነት ደግሞ ዋጋ ያስከፍላል። የሸዋረገድ ገድሌ ታሪክ ለዘመኑ ትውልድ የሚያስተምረው፣ ለሀገር የሚከፈል መስዋዕትነት ከመቃብር በላይ የሚያስከብር ስም እንደሚሰጥ ነው።
ክብርና ዘላለማዊ እረፍት ለጀግናዋ ሸዋረገድ ገድሌ!
የካቲት 12፤ የታሪክ ጥቁር ጠባሳ ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነት ጽናት ዳግም የተወለደበት የደም ጥምቀት ቀን ነው። የፋሺስት ጣሊያን ግፈኛ መሪ ግራዚያኒ በአብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ቦምብ ቆስሎ፣ ለበቀል ባዘዘው የጅምላ ጭፍጨፋ አዲስ አበባ በደም ስትታጠብ፣ ያ ያፈሰሰው ደም ግን አልደረቀም።
ይልቁንም እንደ ሸዋረገድ ገድሌ ያሉ ቆራጥ እናቶችን ልብ በማንደድ ለነፃነት የሚፋጅ እሳት ሆኖ ተቀጣጠለ።
ፈላስፎች ስለ ነፃነት ሲተነትኑ "ነፃነት የሚገኘው በሞት ጥላ ስር ቆሞ ለሕይወት ዋጋ ሲሰጥ ነው" ይላሉ። ሸዋረገድ ገድሌ ለዚህ የፍልስፍና እውነት ሕያው ምስክር ነበሩ። የታሪክ ምሁራን ዘመን ተሻጋሪ ጀግንነታቸውን ሲዘክሩ፣ ፖለቲካል ሳይንቲስቶች ደግሞ በሴቶች የማይበገር የዲፕሎማሲ እና የስለላ ጥበብ ላይ ያተኩራሉ። ሸዋረገድ ገድሌ ግን ከቃላት በላይ የሆነች፣ ለሀገሯ ፍቅር ራሷን መሥዋዕት ያደረገች "የሴት ጀግና " ነበረች።
የቁጭቱ ጅማሬ እና የአደባባዩ እምቢተኝነት
ወይዘሮ ሸዋረገድ ገድሌ በ1878 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ተወልደው፣ በአባታቸው በፊታውራሪ ገድሌ እቅፍ ውስጥ የሀገር ፍቅርን እየተጋቱ አደጉ። በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ጣሊያን ዳግም ሀገራችንን ሲወር፣ ሸዋረገድ የ52 ዓመት ጎልማሳ ነበሩ። በወቅቱ ጣሊያን አዲስ አበባን ሲቆጣጠር፣ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ወርዶ የጣሊያን ባንዲራ ሲሰቀል ሲያዩ ልባቸው በሀዘን ተሰበረ።
ያኔ ነበር የየካቲት 12 የጭፍጨፋ ድባብ በከተማዋ ላይ ሲያንዣብብ፣ ሸዋረገድ በአደባባይ ወጥተው ማልቀስ የጀመሩት። ጣሊያኖች "ለምን ታለቅሻለሽ?" ብለው ሲጠይቋቸው የሰጡት ምላሽ ለታሪክ ምሁራን ትልቅ ትምህርት ነው፦
"አዎ አልቅሻለሁ፤ የሀገሬን መወረርና መዋረድ ያወቅሁት የኛ ሰንደቅ ዓላማ ወርዶ የናንተ ሲውለበለብ በመታየቱ ነው። ሰው ለእናት ሀገሩ ቢያለቅስ ነውሩ የት ላይ ነው?"
ይህ ንግግር የፖለቲካ ሳይንስ ምሁራን እንደሚሉት "የሕዝባዊ እምቢተኝነት" (Civil Disobedience) ቀዳሚ ማሳያ ነበር። በዚህ ድርጊታቸው የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በልመና ወደ እስር ተቀየረላቸው። ነገር ግን እስር ቤቱ ለእሳቸው የትግል አውድማ እንጂ የመሸነፊያ ስፍራ አልነበረም።
ልብ አንጠልጣይ ተጋድሎ እና የግል መስዋዕትነት
የሸዋረገድ ገድሌ ታሪክ በጣም ልብን የሚነካው በሁለት ምክንያቶች ነው፡- ንብረታቸውን ለሀገር መስጠታቸው እና በልጆቻቸው ላይ የደረሰው መከራ።
አባታቸው ፊታውራሪ ገድሌ ካወረሷቸው ሰፊ መሬትና ሀብት መካከል አብዛኛውን በመሸጥ ለአርበኞች ጥይት፣ ልብስና መድኃኒት ይገዙ ነበር። የሴትነት አጥሩን ሰብረው፣ የቤት እመቤትነቱን ትተው፣ በንግድ ስራ ያገኙትን ትርፍ ሁሉ ለቀይ መስቀልና ለነፃነት ትግሉ አዋሉ።
በጣም አስለቃሹ የታሪካቸው ምዕራፍ የሚጀምረው በሚስጥራዊ መረጃ ልውውጥ ወቅት ነው። መረጃዎችን በቅርጫት ውስጥ ደብቀው ለአርበኞች ሲልኩ፣ መልእክተኛው ተይዞ መረጃው እንዳይወጣ ደብዳቤውን አላምጦ ዋጠው።
ሸዋረገድ ይህን ሲሰሙ መልእክተኛው መረጃውን በእርግጥም መዋጡን ለማረጋገጥ ኮሶ በጥብጠው አጠጡት። ይህ የሚያሳየው ለሀገር ነፃነት ሲባል የሚደረግን ጥንቃቄና የላቀ የቁርጠኝነት ደረጃ ነው።
የሸዋረገድን ልብ የሰበረው ግን የታሰሩ እለት የማደጎ ልጃቸው በዓይናቸው ፊት በፋሺስቶች መገደሉ ነበር። እናት ሆና ልጇ ሲታረድ እያየች፣ ለሀገሯ ምስጢር ግን አልበገረችም። ጣሊያኖች በኤሌክትሪክ ገመድ እየገረፉ ሰውነቷን ሲያቆስሉ፣ እሷ ግን "ለሀገሬ የሰራሁት ሲያንስ እንጂ አይበዛብኝም" በሚል ጽናት መከራውን ተቀበለች።
ከአሲናራ ደሴት እስከ አዲስ ዓለም ምሽግ
ፋሺስቶች ሸዋረገድን አዲስ አበባ ውስጥ ማሰር ስላልቻሉ፣ ወደ ሜድትራኒያን ባሕር አሲናራ ወደተባለችው የጣሊያን ደሴት በግዞት ሰደዷቸው። እዚያም ሆነው ግን አልተኙም። ከጅቡቲ በመጣላቸው "ሞአ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ" የሚል ምልክት ያለበት ወረቀት ላይ፣ ከንጉሡ የተላከ መልዕክት በማስመሰል ለአርበኞች የሞራል ማበረታቻ ደብዳቤዎችን በምስጢር ይልኩ ነበር።
ከግዞት ተመልሰው እንደገቡም በቀጥታ ወደ ጦር ግንባር ነበር ያመሩት። የታሪክ ጸሐፊዎች እንደሚዘግቡት፣ በህዳር 5 ቀን 1933 ዓ.ም. የአዲስ ዓለም የጣሊያን ምሽግ ሲሰበር፣ ዋናውን የመረጃ አውታር የዘረጉትና ዕቅዱን የነደፉት እሳቸው ነበሩ።
ለአራት ሰዓታት ያህል መቂ አካባቢ በነበረው ውጊያ ላይ ራሳቸው ጥይት እየተኮሱ ተዋግተዋል። በመጨረሻም በገረሱ ዱኪ ጦር አቅራቢያ በተደረገ ድንገተኛ ውጊያ ተማረኩ። ወደ እስር ቤት ተወስደው የፊጥኝ ታስረው እያለ እንኳን፣ "የሀገሬ ነፃነት ካልመጣ ሞቴን እመርጣለሁ" በማለት የረሀብ አድማ አድርገዋል።
የታሪክ ምሁራንና የትውልድ ዕዳ
የፖለቲካ ሳይንስ ጸሐፊዎች ሸዋረገድን "የውስጥ አርበኝነትና የደጀን ግንባታ ምሰሶ" ይሏታል። ፈላስፎች ደግሞ "የአንድ ሀገር ነፃነት የሚረጋገጠው በወንዶች ክንድ ብቻ ሳይሆን፣ በሴቶች ጽናትና መስዋዕትነት ነው" ለሚለው አስተሳሰብ ሸዋረገድን እንደ ትልቅ ምሳሌ ያነሳሉ።
ሸዋረገድ ገድሌ በጥቅምት 22 ቀን 1942 ዓ.ም. ሲያርፉ፣ ሕዝቡ በለቅሶ እንዲህ ብሎ ነበር፡-
"እናንት ወጥ ቤቶች በርበሬ ቀንጥሱ፣
እናንት ሥጋ ቤቶች ሥጋውን ምረጡ፣
ሸዋረገድ ገድሌ ለገና ሲመጡ...
ቤተሰቧ ሰፊ ገና እና ጥቅምት፣
ሸዋረገድ ገድሌ እንደምን ትሙት?"
በእርግጥም ሸዋረገድ አልሞተችም። የካቲት 12 ቀን በፈሰሰው ደም ውስጥ፣ በአሲናራ ደሴት ግዞት ውስጥ፣ በአዲስ ዓለም ምሽግ ሰበራ ውስጥ እና በዛሬዋ ኢትዮጵያ ውስጥ ስሟ ህያው ነው።
ትምህርቱ፡- ጀግንነት ጾታ የለውም፤ ሀገር ወዳድነት ደግሞ ዋጋ ያስከፍላል። የሸዋረገድ ገድሌ ታሪክ ለዘመኑ ትውልድ የሚያስተምረው፣ ለሀገር የሚከፈል መስዋዕትነት ከመቃብር በላይ የሚያስከብር ስም እንደሚሰጥ ነው።
ክብርና ዘላለማዊ እረፍት ለጀግናዋ ሸዋረገድ ገድሌ!
4 months ago
🇪🇹 "የአሁኑ ትውልድ የልማት አርበኝነትን ሊላበስ ይገባል!" — ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን 🇪🇹
#ethiopia | ዛሬ፣ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም.፤ በፋሺስት ጣሊያን ግፍ ያለቁ ሰማዕታትን የምንዘክርበት 89ኛው መታሰቢያ ቀን በአዲስ አበባ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የሰማዕታት ሐውልት በድምቀት ተከብሯል።
በበዓሉ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ጥንታዊት ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ለወጣቱ ትውልድ ጥሪ አቅርበዋል፦
ቁልፍ መልዕክቶች፦
✊ የታሪክ አደራ፦
ቀደምት አርበኞች በከፈሉት ውድ መስዋዕትነት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አስከብረው ለትውልድ አስረክበዋል።
🏗️ የልማት አርበኝነት፦
የአሁኑ ትውልድ ደግሞ ወቅቱ የሚጠይቀውን "የልማት አርበኝነት" በመላበስ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ተግቶ መሥራት ይኖርበታል።
🤝 አንድነትና ሰላም፦
የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ ሕብረትና አንድነትን መጠበቅ አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አሳስበዋል።
የሰማዕታት ቀን መከበሩ የጀግኖቻችንን ታማኝነትና መስዋዕትነት ትውልዱ እንዲዘክረውና የሀገር ፍቅር ትምህርት እንዲቀስምበት ትልቅ ሚና አለው።
ክብር ለሀገራቸው ሲሉ ደምና አጥንታቸውን ለገበሩ ሰማዕታት! 🕯️🇪🇹
#የካቲት12 #የሰማዕታትቀን #ኢትዮጵያ #አርበኞች #ልጅዳንኤልጆቴ #ethiopia #martyrsday #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | ዛሬ፣ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም.፤ በፋሺስት ጣሊያን ግፍ ያለቁ ሰማዕታትን የምንዘክርበት 89ኛው መታሰቢያ ቀን በአዲስ አበባ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የሰማዕታት ሐውልት በድምቀት ተከብሯል።
በበዓሉ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ጥንታዊት ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ለወጣቱ ትውልድ ጥሪ አቅርበዋል፦
ቁልፍ መልዕክቶች፦
✊ የታሪክ አደራ፦
ቀደምት አርበኞች በከፈሉት ውድ መስዋዕትነት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አስከብረው ለትውልድ አስረክበዋል።
🏗️ የልማት አርበኝነት፦
የአሁኑ ትውልድ ደግሞ ወቅቱ የሚጠይቀውን "የልማት አርበኝነት" በመላበስ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ተግቶ መሥራት ይኖርበታል።
🤝 አንድነትና ሰላም፦
የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ ሕብረትና አንድነትን መጠበቅ አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አሳስበዋል።
የሰማዕታት ቀን መከበሩ የጀግኖቻችንን ታማኝነትና መስዋዕትነት ትውልዱ እንዲዘክረውና የሀገር ፍቅር ትምህርት እንዲቀስምበት ትልቅ ሚና አለው።
ክብር ለሀገራቸው ሲሉ ደምና አጥንታቸውን ለገበሩ ሰማዕታት! 🕯️🇪🇹
#የካቲት12 #የሰማዕታትቀን #ኢትዮጵያ #አርበኞች #ልጅዳንኤልጆቴ #ethiopia #martyrsday #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
ፈረሰኛውና ፈረሶቹ በጥቅሻ የሚግባቡበት ምድር‼️
🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎
#ethiopia | ምድሩ ለፈረሶች ተመርጦ የተፈጠረ ይመስላል፤ ሕዝቡም ፈረስን ከሰማይ በአደራ የተቀበለ ደገኛ ሕዝብ ። የአገው ታሪክ በፈረስ ኮቴ በለምለም ምድር የተጻፈ በትውልድ የሚነበብ ሕያው ብራና ነው። 🐎🐎🐎
የአገው ታሪክ እንደ አምፖል ከጣራ በታች ሳይሆን እንደፀሐይ ከሰማይ በታች የሚያበራ ብርሃናማ የተጋድሎ ታሪክ ነው። አክሱም ሲነሳ ፈረሰኛው አገውና ፈረሶቹ በዚያ ይነሳሉ ።
ላሊበላም ሲዘከር ከነ ዛጉዌ ሥርወ መንግስታቸው ንጉስም ቅዱስም፤ ካህንም አናጺም፤ መሪም ዘካሪም ኾነው
ፈረስ ጋላቢዎቹ አገዎች፣ ከተጋላቢዎቹ ፈረሶቻቸው ጋር በወርቅ ቀለም ተጽፈው በዚያ አሉ።
የፓን አፍሪካኒዝም የልደት ምስክር ወረቀት አድዋ ሲነሳም ፈረሰኞቹ አገዎችና ፈረሶች፤ በአይበገሬነት ታሪካቸው በደማቁ ድላቸው በዚያ አሉ። በአድዋ ተራራ ከተቀበሩ እልፍ አርበኞች አጽም ጋር የፈረሶች አጽምም በዚያ አለ። ፈረሰኛውና ፈረሶቹ በየታሪኩ ምዕራፍ ለሀገር ግንባታ ጡብ ደርድረዋል፤ የስማቸውንም ሐውልት አቁመዋል ። 🐎🐎🐎
የፈረስን ውለታ አገው ያውቀዋል፤ እንኳን ለባለውለታው ፈረስ፤ ነፍስ ላለው ፍጥረት ሁሉ የሚራራው የአገው ሕዝብ፤ ፈረስን እንደ ልጁ መርጦ ይመግበዋል። በሥርዓትና በማዕረግ ያሳድገዋል፣ በትጋትና በሥልጣኔ ይገራዋል፣ በግርማና በሞገስ በተዋቡ አልባሳትና ጌጦች ይሸልመዋል። ፈረሱን በልኩ እንዲሠራ በሚገባውም እንዲያርፍ ያደርገዋል። 🐎🐎🐎
ፈረሱም ለአባቱ ለአገው ሕዝብ እንደሚታዘዘው ለሌላው የሚገራና የሚታዘዝ አይመስልም ። በእርሻው በኩል በግራም በቀኝም ተጠምዶ ትከሻው እስኪላጥ አርሶ፣ ወቅቶ፣ አዝመራ ተሸክሞ ወደ ጎተራ አስገብቶ አገልግሏል ። 🐎🐎🐎
አገው ልጁን ቢድር ሙሽሮቹን እንደሊሞዚን ተሸክሞ ጫጉላ አውጥቷል ። ቢታመም እንደ አምፑላንስ ኾኖ ሐኪም ደጅ አድርሷል ። ሞት መከራ ቢመጣ ከአልቃሽና አስለቃሽ ጋር ደክሞ፣ አልቅሶ በክብር ይሸኛል ። ዘመድ ቢናፍቁ ፈጣን ትራንስፖርት ኾኖ ወንዝ አሻግሮ ዘመድ በማገናኘት ናፍቆትን አስወጥቷል ። 🐎🐎🐎
አይሞሎ አይሞሎ ሞሎ ዎ!
ሲዋጋ ውሎ ሲዋጋ አመሸ፣
ጋሻውን በዘንግ እያንኮላሸ፡፡
ቦራ ብሎ ጠራው ጀግና ፈረሱን፣
እንኳን አግዜር ሰጠው የተመኘውን፡፡
የጀግናው ባለሟል እኔነኝ ፈረስ፣
ከተፋፋመው ጦር አብሬ ምደርስ፡፡
ጀግናው ፈረሰኛ መጣ ገሰገሰ፤
የጠላቱን ምሽግ እየደረመሰ። የተባለለት ...🐎🐎🐎
ጠላት ቢመጣ ጦር ሜዳ አድርሶ፣ ጠላትን እየረገጠ፣ በጌታው ፋንታ በጦሩም፣ በጎራዴውም፣ በጥይቱም እየቆሰለና እየሞተ ተዋግቷል ። ክብረ በዓላቱን ትርዒት እንደሰለጠነ ወታደር በሥርዓት ተሰልፈው ሰላምታ እየሰጡ ያደምቁታል። 🐎🐎🐎
ለዚህም በአገው ምድር ፈረስ፤ አርበኝነት፣ ነጻነት፣ ድል አድራጊነት፣ የሀገር ፍቅር እና አንድነት የሚንጸባረቅበት የድል ምልክት ኾኖ ይዘከራል ። ፈረሰኛው በንፁህ ባርኔጣ፣ በሎፊሳ፣ በነጭ ኮት እና ሱሪ (ግርቭ ታምባ) በገምባሌ እና አለንጋውን ከሰነደቁ ፤ ጋሻውን ከዘንጉ ጋር ይዞ ከመድመቁ በላይ፤ ፈረሱ በኮርቻ፣ በልቫቭ፣ በልጓም፣ በአምፓጉሲ እና በወደሊ ቀይ አበባ ይደምቃል፡፡ 🐎🐎🐎
የፈረሱ ሰላምታ አሰጣጥ፣ የድንግል ዓሳ ትርዒት፣ የስግሪያ፣ የጉግስ ፣ እና ሽርጥ ትርዒት ሲካሄድ ማየት ልብን ቀጥ የሚያደርግ ደስታ ይሰጣል። ፈረሰኛውና ፈረሱ በጥቅሻ የሚግባቡበት፣ የፈረስ ማዕበል በቀይ ጌጥ ተውቦ የሚፈስበት ትርዒት በአገው ምድር ሰማይ ሥር ይታያል። 🐎🐎🐎
ለሕጻናት ፈረሰኞች የሚታዘዝ ፈረስ በዚያ አለ፤ ለዐይነ ሥውሩ የሚታዘዝ መንገድ መሪ ብቻ ሳይሆን ከዐይናማዎቹ ጋር ተወዳድሮ አሸናፊ ፈረስ በዚያ አለ። ሴት ፈረሰኞች የሳይንስን የዙረት ስሌት ሽረው እየተሽከረከሩ የሚጋልቡት ፈረስ፣ በምልክት ተረድቶ የሚሽከረከር ፈረስ በአገው ምድር ይታያል ። 🐎🐎🐎
በአገው ምድር ሰባቱ ወንድማማቾች «አንክሺ፣ ባንጂ፣ ዚጋሚ፣ አዚኒ፣ ኳኩሪ፣ ቻሪና ሚቲክሊ» እንደአንድ ልብ መካሪ እንድ ቃል ተናጋሪ ናቸው። ፈረስ 🐎 ልዩ ምልክታቸው ስልጣኔ መለያቸው ነው።
ፀሐዩ አይሰማም እንጅ ከተሰማህ ለፀሐዩ አዊት ድጋግ (የአገው ጥላ) አለ። ለሆድህ አትጨነቅ አብዚ፣ ጉዝጉዝ፣ በመልክ በመልኩ ከጠላው ከጠጁና ከብርዙ ጋር በበቃኝ ይቀርባል ። በአገው ምድር የምታየውን ዐይተህ ታደንቀዋለህ፣ እያሰብኸው ትደመማለህ እንጅ ለመጻፍ እንዴት ይቻላል ?
በዚያ ምድር የተገኘህ፣ ፈረሰኛውና ፈረሶቹ በጥቅሻ ሲግባቡ ያየህ፣ ከፈረሱ ጋር ተጫወት።
አይሞሎ አይሞሎ ሞሎ ዎ! 🐎🐎
የፈንዞ ጌታ፣ የጥሪኝ ጌታ የሻሾ ጌታ፤ 🐎🐎
ጀምር ጨዋታ በል ጋሻ ምታ ግጠም እስክስታ ።
👉62 ሺህ ፈረሰኞችና ፈረሶች ያሉት፣ 🐎🐎🐎
👉86 ዓመታትን በሦስት ዐለቃ እየተመራ ዛሬ ላይ የደረሰ፣
👉ባህልን፣ ታሪክን፣ ባለውለታን የሚዘክር፣
👉 የድል አድራጊነት ምልክትና አንድነትን የሚያጠናክር፣
‼️ የአገው ፈረሰኞች 🐎 ማኅበር ‼️👌
እንኳን አደረሳችሁ ‼️
እንኮዋን 86ንቲ አጋው ፌሬስቴኑ ባልስ ታምፅኾስ‼️
🐎🐎🐎 የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን 🐎🐎🐎
🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎
#ethiopia | ምድሩ ለፈረሶች ተመርጦ የተፈጠረ ይመስላል፤ ሕዝቡም ፈረስን ከሰማይ በአደራ የተቀበለ ደገኛ ሕዝብ ። የአገው ታሪክ በፈረስ ኮቴ በለምለም ምድር የተጻፈ በትውልድ የሚነበብ ሕያው ብራና ነው። 🐎🐎🐎
የአገው ታሪክ እንደ አምፖል ከጣራ በታች ሳይሆን እንደፀሐይ ከሰማይ በታች የሚያበራ ብርሃናማ የተጋድሎ ታሪክ ነው። አክሱም ሲነሳ ፈረሰኛው አገውና ፈረሶቹ በዚያ ይነሳሉ ።
ላሊበላም ሲዘከር ከነ ዛጉዌ ሥርወ መንግስታቸው ንጉስም ቅዱስም፤ ካህንም አናጺም፤ መሪም ዘካሪም ኾነው
ፈረስ ጋላቢዎቹ አገዎች፣ ከተጋላቢዎቹ ፈረሶቻቸው ጋር በወርቅ ቀለም ተጽፈው በዚያ አሉ።
የፓን አፍሪካኒዝም የልደት ምስክር ወረቀት አድዋ ሲነሳም ፈረሰኞቹ አገዎችና ፈረሶች፤ በአይበገሬነት ታሪካቸው በደማቁ ድላቸው በዚያ አሉ። በአድዋ ተራራ ከተቀበሩ እልፍ አርበኞች አጽም ጋር የፈረሶች አጽምም በዚያ አለ። ፈረሰኛውና ፈረሶቹ በየታሪኩ ምዕራፍ ለሀገር ግንባታ ጡብ ደርድረዋል፤ የስማቸውንም ሐውልት አቁመዋል ። 🐎🐎🐎
የፈረስን ውለታ አገው ያውቀዋል፤ እንኳን ለባለውለታው ፈረስ፤ ነፍስ ላለው ፍጥረት ሁሉ የሚራራው የአገው ሕዝብ፤ ፈረስን እንደ ልጁ መርጦ ይመግበዋል። በሥርዓትና በማዕረግ ያሳድገዋል፣ በትጋትና በሥልጣኔ ይገራዋል፣ በግርማና በሞገስ በተዋቡ አልባሳትና ጌጦች ይሸልመዋል። ፈረሱን በልኩ እንዲሠራ በሚገባውም እንዲያርፍ ያደርገዋል። 🐎🐎🐎
ፈረሱም ለአባቱ ለአገው ሕዝብ እንደሚታዘዘው ለሌላው የሚገራና የሚታዘዝ አይመስልም ። በእርሻው በኩል በግራም በቀኝም ተጠምዶ ትከሻው እስኪላጥ አርሶ፣ ወቅቶ፣ አዝመራ ተሸክሞ ወደ ጎተራ አስገብቶ አገልግሏል ። 🐎🐎🐎
አገው ልጁን ቢድር ሙሽሮቹን እንደሊሞዚን ተሸክሞ ጫጉላ አውጥቷል ። ቢታመም እንደ አምፑላንስ ኾኖ ሐኪም ደጅ አድርሷል ። ሞት መከራ ቢመጣ ከአልቃሽና አስለቃሽ ጋር ደክሞ፣ አልቅሶ በክብር ይሸኛል ። ዘመድ ቢናፍቁ ፈጣን ትራንስፖርት ኾኖ ወንዝ አሻግሮ ዘመድ በማገናኘት ናፍቆትን አስወጥቷል ። 🐎🐎🐎
አይሞሎ አይሞሎ ሞሎ ዎ!
ሲዋጋ ውሎ ሲዋጋ አመሸ፣
ጋሻውን በዘንግ እያንኮላሸ፡፡
ቦራ ብሎ ጠራው ጀግና ፈረሱን፣
እንኳን አግዜር ሰጠው የተመኘውን፡፡
የጀግናው ባለሟል እኔነኝ ፈረስ፣
ከተፋፋመው ጦር አብሬ ምደርስ፡፡
ጀግናው ፈረሰኛ መጣ ገሰገሰ፤
የጠላቱን ምሽግ እየደረመሰ። የተባለለት ...🐎🐎🐎
ጠላት ቢመጣ ጦር ሜዳ አድርሶ፣ ጠላትን እየረገጠ፣ በጌታው ፋንታ በጦሩም፣ በጎራዴውም፣ በጥይቱም እየቆሰለና እየሞተ ተዋግቷል ። ክብረ በዓላቱን ትርዒት እንደሰለጠነ ወታደር በሥርዓት ተሰልፈው ሰላምታ እየሰጡ ያደምቁታል። 🐎🐎🐎
ለዚህም በአገው ምድር ፈረስ፤ አርበኝነት፣ ነጻነት፣ ድል አድራጊነት፣ የሀገር ፍቅር እና አንድነት የሚንጸባረቅበት የድል ምልክት ኾኖ ይዘከራል ። ፈረሰኛው በንፁህ ባርኔጣ፣ በሎፊሳ፣ በነጭ ኮት እና ሱሪ (ግርቭ ታምባ) በገምባሌ እና አለንጋውን ከሰነደቁ ፤ ጋሻውን ከዘንጉ ጋር ይዞ ከመድመቁ በላይ፤ ፈረሱ በኮርቻ፣ በልቫቭ፣ በልጓም፣ በአምፓጉሲ እና በወደሊ ቀይ አበባ ይደምቃል፡፡ 🐎🐎🐎
የፈረሱ ሰላምታ አሰጣጥ፣ የድንግል ዓሳ ትርዒት፣ የስግሪያ፣ የጉግስ ፣ እና ሽርጥ ትርዒት ሲካሄድ ማየት ልብን ቀጥ የሚያደርግ ደስታ ይሰጣል። ፈረሰኛውና ፈረሱ በጥቅሻ የሚግባቡበት፣ የፈረስ ማዕበል በቀይ ጌጥ ተውቦ የሚፈስበት ትርዒት በአገው ምድር ሰማይ ሥር ይታያል። 🐎🐎🐎
ለሕጻናት ፈረሰኞች የሚታዘዝ ፈረስ በዚያ አለ፤ ለዐይነ ሥውሩ የሚታዘዝ መንገድ መሪ ብቻ ሳይሆን ከዐይናማዎቹ ጋር ተወዳድሮ አሸናፊ ፈረስ በዚያ አለ። ሴት ፈረሰኞች የሳይንስን የዙረት ስሌት ሽረው እየተሽከረከሩ የሚጋልቡት ፈረስ፣ በምልክት ተረድቶ የሚሽከረከር ፈረስ በአገው ምድር ይታያል ። 🐎🐎🐎
በአገው ምድር ሰባቱ ወንድማማቾች «አንክሺ፣ ባንጂ፣ ዚጋሚ፣ አዚኒ፣ ኳኩሪ፣ ቻሪና ሚቲክሊ» እንደአንድ ልብ መካሪ እንድ ቃል ተናጋሪ ናቸው። ፈረስ 🐎 ልዩ ምልክታቸው ስልጣኔ መለያቸው ነው።
ፀሐዩ አይሰማም እንጅ ከተሰማህ ለፀሐዩ አዊት ድጋግ (የአገው ጥላ) አለ። ለሆድህ አትጨነቅ አብዚ፣ ጉዝጉዝ፣ በመልክ በመልኩ ከጠላው ከጠጁና ከብርዙ ጋር በበቃኝ ይቀርባል ። በአገው ምድር የምታየውን ዐይተህ ታደንቀዋለህ፣ እያሰብኸው ትደመማለህ እንጅ ለመጻፍ እንዴት ይቻላል ?
በዚያ ምድር የተገኘህ፣ ፈረሰኛውና ፈረሶቹ በጥቅሻ ሲግባቡ ያየህ፣ ከፈረሱ ጋር ተጫወት።
አይሞሎ አይሞሎ ሞሎ ዎ! 🐎🐎
የፈንዞ ጌታ፣ የጥሪኝ ጌታ የሻሾ ጌታ፤ 🐎🐎
ጀምር ጨዋታ በል ጋሻ ምታ ግጠም እስክስታ ።
👉62 ሺህ ፈረሰኞችና ፈረሶች ያሉት፣ 🐎🐎🐎
👉86 ዓመታትን በሦስት ዐለቃ እየተመራ ዛሬ ላይ የደረሰ፣
👉ባህልን፣ ታሪክን፣ ባለውለታን የሚዘክር፣
👉 የድል አድራጊነት ምልክትና አንድነትን የሚያጠናክር፣
‼️ የአገው ፈረሰኞች 🐎 ማኅበር ‼️👌
እንኳን አደረሳችሁ ‼️
እንኮዋን 86ንቲ አጋው ፌሬስቴኑ ባልስ ታምፅኾስ‼️
🐎🐎🐎 የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን 🐎🐎🐎
5 months ago
🏇 የአገው ፈረስ ባህል በዩኔስኮ ሊመዘገብ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደረሰ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ቀዳሚ የጀግንነትና የጽናት መገለጫ የሆነው የአገው ፈረስ ባህል፣ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) የማይዳሰስ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ የሚደረገው ጥረት ፍሬ እያፈራ ይገኛል። ይህንን ታሪካዊ ሂደት የሚያፋጥን የምክክር መድረክ በባህር ዳር ከተማ ተካሂዷል።
🇪🇹 የጀግንነት እና የጽናት ተምሳሌት
በመድረኩ ላይ የተገኙት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንደገለጹት፣ የአገው ፈረስ ባህል የጥንታዊ አባቶቻችንን የአንድነት፣ የጽናትና የ"አልሸነፍ ባይነት" እሴቶችን ለትውልድ የሚያስተላልፍ ድንቅ ሐብት ነው።
🔍 ቁልፍ ነጥቦች፦
የመመዝገብ ሂደት፦ ባህሉን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ የሚደረገው ጥረት አሁን ላይ በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል።
የአባላት ብዛት፦ ታሪካዊው የአገው ፈረሰኞች ማህበር በአሁኑ ወቅት ከ 62 ሺህ በላይ አባላትን በማቀፍ በሀገር ፍቅር ስሜት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ታሪካዊ ፋይዳ፦ ማህበሩ አባቶቻችን ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የከፈሉትን መስዋዕትነት እየዘከረ፣ ለአዲሱ ትውልድ አርበኝነትን እያስተማረ ይገኛል።
📅 የዘንድሮው ክብረ በዓል
86ኛው የአገው ፈረሰኞች ክብረ በዓል የፊታችን ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር መቀመጫ በሆነችው እንጅባራ ከተማ በታላቅ ድምቀት ይከበራል። ይህ በዓል ባህሉን በዓለም አደባባይ ለማስተዋወቅና የቱሪስት መስህብነቱን ለማጠናከር ትልቅ አጋጣሚ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #agewhorseculture #unesco #awiagew #heritage #ethiopianculture #enjibara #horsefestival #culturalpride
#ethiopia | የኢትዮጵያ ቀዳሚ የጀግንነትና የጽናት መገለጫ የሆነው የአገው ፈረስ ባህል፣ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) የማይዳሰስ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ የሚደረገው ጥረት ፍሬ እያፈራ ይገኛል። ይህንን ታሪካዊ ሂደት የሚያፋጥን የምክክር መድረክ በባህር ዳር ከተማ ተካሂዷል።
🇪🇹 የጀግንነት እና የጽናት ተምሳሌት
በመድረኩ ላይ የተገኙት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንደገለጹት፣ የአገው ፈረስ ባህል የጥንታዊ አባቶቻችንን የአንድነት፣ የጽናትና የ"አልሸነፍ ባይነት" እሴቶችን ለትውልድ የሚያስተላልፍ ድንቅ ሐብት ነው።
🔍 ቁልፍ ነጥቦች፦
የመመዝገብ ሂደት፦ ባህሉን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ የሚደረገው ጥረት አሁን ላይ በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል።
የአባላት ብዛት፦ ታሪካዊው የአገው ፈረሰኞች ማህበር በአሁኑ ወቅት ከ 62 ሺህ በላይ አባላትን በማቀፍ በሀገር ፍቅር ስሜት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ታሪካዊ ፋይዳ፦ ማህበሩ አባቶቻችን ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የከፈሉትን መስዋዕትነት እየዘከረ፣ ለአዲሱ ትውልድ አርበኝነትን እያስተማረ ይገኛል።
📅 የዘንድሮው ክብረ በዓል
86ኛው የአገው ፈረሰኞች ክብረ በዓል የፊታችን ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር መቀመጫ በሆነችው እንጅባራ ከተማ በታላቅ ድምቀት ይከበራል። ይህ በዓል ባህሉን በዓለም አደባባይ ለማስተዋወቅና የቱሪስት መስህብነቱን ለማጠናከር ትልቅ አጋጣሚ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #agewhorseculture #unesco #awiagew #heritage #ethiopianculture #enjibara #horsefestival #culturalpride
5 months ago
እስራኤል ሶማሊላንድን እንደ ሀገር እውቅና መስጠቷን ተከትሎ በሀርጌሳ ዛሬ ሰፊ የደስታ ሰላማዊ ሰልፎች ተካሂደዋል
በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ የተሰበሰበ ሲሆን፣ የሶማሊላንድን ሰንደቅ ዓላማ በማውለብለብ እንዲሁም አንድነትን እና ብሔራዊ ኩራትን የሚገልጹ መፈክሮችን በማሰማት ዋና ዋና መንገዶችን አጨናንቀዋል።
ወጣቶችና ሴቶች በብዛት የተሳተፉባቸው የአርበኝነት መዝሙሮች፣ ባህላዊ ትርኢቶች እና የህዝብ ሰልፎችም ተካሂደዋል።
በተለያዩ መድረኮች ላይ ንግግር ያደረጉ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የእስራኤል እውቅና የታሪክ ምዕራፍ መሆኑንና ሶማሊላንድ ዓለም አቀፍ እውቅና ለማግኘት ለምታደርገው የረጅም ጊዜ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ትልቅ መነቃቃት መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ እርምጃ እንደ ደህንነት፣ ንግድ፣ ቴክኖሎጂ እና ልማት ባሉ ዘርፎች ለአዲስ የትብብር ዕድሎች መንገድ ሊከፍት እንደሚችልም ጠቁመዋል።
ለሚዲያ አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች፣ ይህ እውቅና ሶማሊላንድ ለሰላም፣ ለመረጋጋት እና ለራስን በራስ ማስተዳደር ላሳየችው የበርካታ አስርት ዓመታት ቁርጠኝነት የተገኘ ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።
ሌሎች ሀገራትም የእስራኤልን ፈለግ በመከተል ለሶማሊላንድ ይፋዊ እውቅና ይሰጣሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።
በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ የተሰበሰበ ሲሆን፣ የሶማሊላንድን ሰንደቅ ዓላማ በማውለብለብ እንዲሁም አንድነትን እና ብሔራዊ ኩራትን የሚገልጹ መፈክሮችን በማሰማት ዋና ዋና መንገዶችን አጨናንቀዋል።
ወጣቶችና ሴቶች በብዛት የተሳተፉባቸው የአርበኝነት መዝሙሮች፣ ባህላዊ ትርኢቶች እና የህዝብ ሰልፎችም ተካሂደዋል።
በተለያዩ መድረኮች ላይ ንግግር ያደረጉ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የእስራኤል እውቅና የታሪክ ምዕራፍ መሆኑንና ሶማሊላንድ ዓለም አቀፍ እውቅና ለማግኘት ለምታደርገው የረጅም ጊዜ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ትልቅ መነቃቃት መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ እርምጃ እንደ ደህንነት፣ ንግድ፣ ቴክኖሎጂ እና ልማት ባሉ ዘርፎች ለአዲስ የትብብር ዕድሎች መንገድ ሊከፍት እንደሚችልም ጠቁመዋል።
ለሚዲያ አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች፣ ይህ እውቅና ሶማሊላንድ ለሰላም፣ ለመረጋጋት እና ለራስን በራስ ማስተዳደር ላሳየችው የበርካታ አስርት ዓመታት ቁርጠኝነት የተገኘ ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።
ሌሎች ሀገራትም የእስራኤልን ፈለግ በመከተል ለሶማሊላንድ ይፋዊ እውቅና ይሰጣሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።
6 months ago
ሊከተሉት የሚገባ ሰው!
ሠዓሊና ቀራፂ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን
(ሂላሪያ ተስፋዬ እና ዕዝራ እጅጉ ተወዳጅ ሚድያ)
#ፕሮፌሰር በቀለመኮንን ለተወዳጅ ሚድያ የቅርብ ወዳጅና ቤተሰብ ነው። የምንሠራውን የስነዳ ፕሮጀክት በሙሉ ልብና መንፈስ የሚደግፍ ቀና ምሁር ነው። ታናሾቹን ለማገዝ በቀዳሚነት የሚሰለፍ ኩራት ያልፈጠረበት ታላቅ ወንድም እንደማለት ነው። ከ4 ዓመት አስቀድም "መዝገበ አእምሮ" ቅጽ አንድ ሲዘጋጅ ከጀርባ እና ከጎን ሆኖ ሲረዳን ነበር። የኃይሉ ልመንህን ታሪክ ፕሮፌሰር በቀለ አስታውሶ ታሪኩን ባይነግረን ኖሮ ኃይሉ ልመንህን አናገኘውም። ፕሮፌሰር በቀለ ሌሎችም ስሙን ከአክብሮት ጋር የሚያነሱት የሥነጥበብ ሰው ነው።
#ተወዳጅ ሚድያ እስከዛሬ የ432 ባለሙያዎችን ታሪክ በመፅሐፍ፣ በዲጂታል ሚድያ እና በድምፅ ሲሰንድ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንንም እንዲካተት አድርጓል። እስከዛሬ በሚዲያ እና ኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሠሩትን በምንችለው አቅም ታሪካቸው ዘመን እንዲሻገር ያደረግን ሲሆን የስነዳ ተግባሩም ተጠናክሮ ቀጥሏል። በቀጣይ እያዘጋጀነው ባለነው ዕትም ከ20 ዘርፎች የተውጣጡ ታላላቆችን በማሰባሰብ ላይ እንገኛለን ። ከእነዚህ ታላላቆች ውስጥ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን አንዱ ነው። የሕይወት ታሪኩንም ብዙ ካልታዩ የልጅነት ምስሎቹ ጋር አንድ ላይ በማድረግ ታሪኩን አጋርቶናል። ዕዝራ እጅጉ እና ሂላሪያ ተስፋዬም ታሪኩን እንደሚከተለው ሰንደውታል።በነገራችን ላይ በዚህ የሕይወት ታሪክ መጣጥፍ ውስጥ ተባባሪ ፕሮፌሰር ቴዎድርስ ገብሬ "በቀለን በብሔራዊ ትእምርት ፍለጋ ውስጥ" ብሎ የጻፈው ረዘም ያለ ምሁራዊ ትንተና አቅርበናል። የፕሮፌሰር በቀለ መምህር ወርቁ ጎሹ የሰጡትንም ምስክርነት አካተናል። መልካም ንባብ።
#የሰባተኛ ክፍል ተማሪ እያለ የስዕል ዝንባሌውን እንዲከተል እንዲሁም የስዕል ትምህርትን እንዲማር ያመለከቱትን መምህሩን በአንደበቱ ቃላት ይስላቸዋል። እኚህ መምህሩን፥ “ሊከተሉት የሚገባ ሰው” ሲል ይገልጻቸዋል። ምንአልባት ከበርካታ ዓመታት በኋላ እርሱ ራሱም እንዲያ ያለ ‘ሊከተሉት የሚገባ’ የጥበብ ሰው ሊሆን እንደሚችል አልገመተ ይሆናል።
#ፍላጎቱ ከእኩዮቹ የተለየ፣ ‘ተርታ’ ለሆነ ነገር መሻት የሌለው፣ በለጋ እድሜው ሳይቀር ነገሮችን እንደሆኑ ማየትና መሥራትን የማይመርጥ፣ አዲስ ነገር መፍጠርን አልያም የነበረውን በአዲስ መልክ መቃኘት ይቀናው የነበረ ተማሪ ነው። ስሙን ሳይቀር በስዕል ይጽፍ እንደነበር ይናገራል። በስጋው ላይ ያሠለጠናት ነፍሱ፥ ሰዓሊ የመሆን ግቡን ለማሳካት ይችል ዘንድ ‘የሰው ልጅ መሠረታዊ ነገሮችን’ አሻግሮ እንዲያይ ጉልበት ሰጥታዋለች። ይህ ጉልበትና ጽናት ነው፣ አሁን በሥነ ጥበብ ዘርፍ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ሙሉ ፕሮፌሰር የወለደው፥ ሠዓሊና ቀራፂ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን።
#ትውልድና እድገቱ ደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማ ነው። ጥር 6 1956 ዓ.ም። ትምህርትን አሃዱ ያለው በቆሎ ትምህርት አቡጊዳ ብሎ ፊደል ቆጥሮ፣ ዳዊት ደግሞ ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን አፄ ልብነ-ድንግል ወናግሰገድ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ እንዲሁም ኹለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በዚያው ደብረዘይት ልዕልት ተናኘወርቅ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል። የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተናውን የወሰደው ደግሞ በአዲስ አበባ ምኒልክ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው።
ከልጅነት እድሜው ጀምሮ የተገዛው ለስዕል ጥበብ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላ ለጥበብ ነበር። አዲስ ነገርን አልያም የነበረው በተሻለ መንገድ ሆኖ ማየትን ይመርጣል። በጥበብ ለሚሠራ ነገር ሁሉ ልዩ ፍቅር አለው። አሁን በአዋቂነትና በርቱዕ አንደበቱ ውበት እንደሚገዛው፥ ሰው የማይሠራውን መሥራት አልያም የተሠራውን ነገር ባልተሠራበት መንገድ መሥራት እንደሚወድድ ይናገራል። ይህን ቃሉን በልጅነት እድሜው ሲገልጥ ደግሞ፣ ስሙን ሳይቀር በስዕል ይጽፍ ነበር።
#የተካነበት፣ የሠለጠነበትና የታወቀበት የስዕል እና የቅርጻ ቅርጽ ጥበብ ይሁን እንጂ፥ ለጽሑፍ ጥበብ እና ውበትም ስሱ ነው። በልጅነትና ወጣትነት እድሜው በደብረዘይት ኪነት ውስጥ ቴአትር፣ ግጥም እንዲሁም መፈክር ጭምር በመጻፍ ይታወቃል። እንደውም ለተማሪዎች፣ ለሰፈሩ ወጣቶች የጻፋቸው የፍቅር ብሎም ልዩ ልዩ ደብዳቤዎችና ግጥሞች ጋር በተያያዘ በተለያየ አጋጣሚ የሚያነሳቸው ገጠመኞቹ ጥቂት አይደሉም። የእጅ ጽሑፉን ብቻ ሳይሆን የሚጽፋቸው ጽሑፎችና ግጥሞች ይዘት ጭምር ነበር ብዙዎችን የሚስበው።
#በኋላ 12ኛ ክፍል ፈተናን ከመውሰዱ አስቀድሞ፥ የስዕል ትምህርትን ለመማርና መምህሩ የዘራበትን ዘር ለማፍራት ዝንባሌውን ተከትሎ በዘመኑ አዲስ አበባ የሥነ ጥበብ ትምህርት ቤት (አሁን አለ ሥነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት) አቀና። ትምህርት ቤቱን ለመቀላቀል ደጅ ጥናትና ምልልስ እንዲሁም ተማጽኖ አስፈልጎታል። በኋላም ተሳክቶለት ተማሪ ለመሆን በሚጠበቀው ፈተና አንድ ሺህ ከሚጠጉ ተወዳዳሪዎች መካከል ከ14 አላፊ ተማሪዎች አንዱ መሆን ቻለ።በ1971።
#በአንድ ወቅት በአራዳ ኤፍኤም አዲስ አራዳ የራድዮ ፕሮግራም ላይ ባደረገው ቆይታ፣ የዚያን የአምስት ዓመት የትምህርት ዘመን ሲያነሳ፥ በትምህርት ቤቱ የነበረው የ5 ዓመት ቆይታ ቀላል እንዳልነበር ያስታውሳል። ሌሊት ማረፊያ የሚያጣባቸው ቀናት ብዙ ናቸው። ምንም እንኳ ለአምስት ዓመታት እያንዳንዱ ቀን የአንድ ዓመት ያህል ከባድ የነበር ቢሆንም፥ እርሱ ግን ‘ቀኑን ጎበዝ መሆን ነበር የሚፈልገው’። እናም ቀኑን ጎብዞ ከባዱን ጊዜ በብልሃትና በጽናት ተወጣው። ትምህርቱን አጠናቅቆም በማዕረግ ተመረቀና እዚያው የተማረበት ትምህርት ቤት መምህር ሆኖ ተቀጠረ።
በተማረበት ትምህርት ቤት በወጣት መምህርነት ለአራት ዓመታት አገልግሏል። ከዚያ በኋላ፥ ወደ ሩሲያ ለከፍተኛ ትምህርት ተላከና ሞስኮ ከተመ። ‘ግራጫ’ ይለዋል፣ የሩስያን ፀሐይ አልባ ቀዝቃዛና ደመናማ የጨላለመ የዘመኑን ድባብ። በዙሪያው ውበትን ማሰስ የለመደ ዐይኑ በሞስኮ ያንን ሊያገኝ አልቻለም። እንዲያም ሆኖ የደከመለት ትምህርቱን ለመፈጸም ጽናትን በመምረጥ፥ ከስድስት ዓመት የሞስኮ ቆይታ በኋላ የከፍተኛ የሥነጥበብ ትምህርቱን በሚገባ አጠናቅቆ ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ተመለሰ።
ከሩስያ መልስ አስቀድሞ በመምህርነት ያገለግልበት በነበረው ሥነ -ጥበብ ትምህርት ቤት የማስተማር እድል አገኘ። በዚያም በመጀመሪያ በሥነ ጥበብ ታሪክ ከዚያም በንድፍ ጥናት መምህር ሆኖ ቆይቷል። በመምህርነት ብቻም አይደለ፥ በጊዜው ‘አርት ስኩል’ ይባል የነበረውን ይህን ትምህርት ቤት፣ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋምነት ለማሳደግ ከ1990ዎቹ ጀምሮ ለዓመታት በዘለቀውና በተደረገው እልህ አስጨራሽ ትግል ውስጥ ከፊት ሆነው ሲያስተባብሩ ከነበሩት መካከል ሆኗል። በመጨረሻም ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ በተሰጠ የጥናት ውሳኔ ሥነ ጥበብ ትምህርት ቤቱ ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተዛውሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሲሆን ትልቁን ድርሻ ከተወጡት ጥቂት ግለሰቦች መካከል ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን ተጠቃሽ ነው።
ትምህርት ቤቱ የዩኒቨርሲቲው አንድ አካል ክፍል ከሆነ በኋላ የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሠርቷል። በዚያም ወቅት የትምህርት ቤቱን ነባር ስርዓት የከፍተኛ ትምህርት ስርአት ቅርፅ ለማስያዝ በብርቱ ለፍቷል፣ አሳክቷልም። በ2009 ዓ.ም ገደማ የሥነጥበባት ኮሌጅ ሲመሠረት በድጋሚ የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር ሆኖ ከማገልገሉ ባሻገር፥ ትምህርት ቤቱ መጠሪያው ወደ አለ የሥነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የተቀየረው የኮሌጁ ዲን ሆኖ ባገለገለበት ዘመን ነበር። ከዚያም ባሻገር አዲስና ተጨማሪ የፊልም ትምህርት ክፍል እንዲቋቋም ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ትምህርት ክፍሉ እውን እንዲሆን አስችሏል። ከዚህም ባሻገር በማስተማርና በማማከር በርካታ ተማሪዎችን ያፈራ ብርቱ ባለሙያ ነው።
#ፕሮፌሰር በቀለ በብሉይ ወይም ክላሲክ አካዳሚ ትምህርቱን ጠንቅቆ የተማረ ይሁን እንጂ በዘመነኛ የሥነ ጥበብ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ከሚጠቀሱ ባለሙያዎች አንዱ ነው። አዳዲስ ሙከራዎችና አሰሳዎችን በድፍረት ግን በኃላፊነት በማከናወን ሁሌም ፈር ቀዳጅና አዲስ መንገድ የሚያሳይ ከልቡ የፈጠራ ሰው ስለመሆኑም ብዙዎች ይመሰክራሉ፥ ከዚያም በላይ ሥራዎቹ ምስክሮቹ ናቸው።
#ፕሮፌሰር በቀለ የመጀመሪያ የሥዕል ኤግዚቢሽኑን ያቀረበው ከሀገር ውጭ ፊንላንድ፥ ‘ኮ’ፕዮ’ የሚባል ዩኒቨርሲቲ (Kuopio - በአሁኑ ምሥራቅ ፊንላንድ ዩኒቨርሲቲ) ነበር። ይህም በሞስኮ የሥነጥበባት የመጨረሻ ዓመት ተማሪ እያለ ሲሆን፣ ለዕይታ ያቀረባቸው ሥራዎቹም የተለያዩ አስቀድሞ በትምህርት ቤት ቆይታው ያዘጋጃቸው ናቸው።
ከዚያ በኋላ ለቁጥር በርካታ፣ ለዓይነት ብዙ፣ ለዐይን ውብና አስደማሚ የሆኑ ሥራዎችን ያለማቋረጠ ለበርካታ ዓመታት ሲያቀርብ ቆይቷል። ከስዕል ኤግዚቢሽን እስከ አደባባይ ሐውልቶችና ዓለም አቀፍ መድረኮች፥ በቀለ መኮንን የሚለው ስም እንግዳ ሆኖ አያውቅም።
#በ1996 ዓ.ም ያቀረበው ‘እንቆቅልሽ’ የተሰኘ የ‘ኢንስታሌሽን ጥበብ’ ትርዒቱ ዘይቤያዊ (Methaphorical) ትርጉም የያዘና አሁንም ድረስ አነጋጋሪ ሆኖ የቆየ ሥራ አንዱ ተጠቃሽ ነው። በ2000 ዓ.ም ‘እድልና ምርጫ’ የሚል ‘ክሪቲካል’ ትርዒቱን አቅርቦ ተመልካቹን አስደምሟል። በ2010 ዓ.ም ‘ባሩድና ብርጉድ’ ሲል የሰየመው አነጋጋሪና አወያይ ኤግዚቢሽኑ፥ ተመልካቹ ስለ ሥነጥበብ ያለውን አመለካከት ደጋግሞ እንዲፈትሽ ያስገደደ ነበር።
በ2016 ዓ.ም በኢትዮጵያውያን የሕይወት ዘይቤ ላይ ትልቅ ጥያቄ አንስቶ ያወያየውንና እስከ አሁንም የሚያወያየውን “ግሉተን ፍሪ-ደም” ወይም ‘ጤፍና ነፃነት’ የተሰኘውን ልዩ ትርዒት አቅርቦ የሥነ ጥበብ ተመልካቾችን ማስደነቁና ማነጋገሩን ቀጠለበት።
ከ25 ዓመታት በላይ እነዚህን የፈጠራ ሥራዎቹን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በተለያዩ መድረኮች ሲያሳይ ቆይቷል። በአፍሪካ፣ በአውሮፓ እና በአሜሪካ፣ በተለያዩ ሙዚየሞች ሥራዎቹን አቅርቧል፣ ሐሳብና ዕይታውን አስደምጧል። ሀገሩን አልፎም አኅጉሩን አፍሪካን በዓለም መድረክ በዘርፉ በኩራት እንዲቆሙም ምክንያት ሆኗል።
#በቅርብ ማለትም ባለፈው 2017 ዓ.ም፥ በኢጣሊያ ቱሪን ከተማ ሮያል ፓላስ ሙዚየም ተጋብዞ ‘ዘ ስሞኪንግ ቴብል’ ወይም ‘የሚጤሰው ጠረጴዛ’ የተሰኘ ፀረ ቅኝ ግዛት ይዘት ያለው ዘመነኛ የሥነ ጥበብ ሥራ በመፍጠር ለዕይታ አቅርቧል። ይህም ከፍተኛ እድናቆትን ያስገኘለት ብሎም ሐሳቡን ያስደመጠበት አውድ መሆን ችሏል።
#መሥራት እንጂ ይህን ሠራሁ ብሎ መናገርን የማያዘወትረው ፕሮፌሰር በቀለ፣ እንዲህ ካሉ አውደ ርዕዮች ባሻገር በቀራጺነቱ የተጠበበባቸው ሥራዎችም እጅግ በርካታ ናቸው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሠራቸውን በማማከር የተሳተፈባቸውን ብቻ ለመጥቀስ፥ በሙሉ ነሃስ የተሠራው የቀዳማይ ኃይለሥላሴ ኪነ ሀውልትን ጨምሮ፥ አብርኆት የሕዝብ ቤተመጻሕፍት ደጃፍ የሚገኘው ኪነ ሀውልት (ከነሐስ ቀልጦ የተሠራው ሕፃን)፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ያሠራው ሕንጻ ጋር የሚገኘው የባንኩን ዓላማና ርዕይ የሚያሳየው ግዙፍ ኪነ ሀውልት (ሀብት ካለ በሰማይ መንገድ አለ) እጅግ ጥቂቶቹ ናቸው።
ታድያ ለእነዚህና ለበርካታ ሥራዎቹ ሽልማቶችና እውቅናዎች ተበርክተዉለታል። ከእነዚያም መካከል በ1990 ዓ.ም የቺካጎ አርቲስቶች ዓለም አቀፍ ሽልማትን ያሸነፈ ብቸኛው አፍሪካዊ የስነ ጥበብ ባለሙያ መሆን ችሏል። እ.ኤ.አ. በ2006 በአሜሪካ ኒው-ዮርክ ውስጥ የIIE ፕሮግራም የሆነውን የ’Scholar Rescue Fund’ ሲቀበል የመጀመሪያው የሥነ ጥበብ ሰው ነበር። በዚያው ዓመት በባልቲሞር ሜሪላንድ ውስጥ በተጋባዥ ሠዓሊነት በበሜሪላንድ የአርት ኮሌጅ (MICA-Maryland institute college of Art) ለስምንት ወራት ቆይታ አድርጓል።
#ፕሮፌሰር በቀለ የኢትዮጵያ ሚሌኒየም ዓርማ ነዳፊ ሲሆን በመላ ሀገሪቱ በርካታ ኪነ ሀውልቶችን ነድፏል፣ አቅዷል፣ አማክሯል፣ መርቷል፣ ሠርቷል። በርካታ የመጻሕፍት ሽፋኖችንና የውስጥ ምስሎችን አዘጋጅቷል። በሀገር እና በዓለም አቀፍ የሥነጥበብ እና የሥነ ሕንፃ የውድድር መድረኮች ላይ በከፍተኛ ዳኝነት አገልግሏል። ከስነጥበቡ ማኅበረሰብ ውስጥ ደግሞ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ መደበኛ አባል ነው።
#ከዚህም በላይ ከእለት እለት የማስተማር ተግባሩ ጎን ለጎን በቅርቡ በተባበሩት መንግሥታት ፕሮጀክት ስር ነባሩ የአፍሪካ አዳራሽና የሥነ ጥበብ ሥራዎቹ እድሳት ውስጥ ባለሞያ፣ አማካሪና ተቆጣጣሪ በመሆን የተሳካ ሙያዊ ተልዕኮ ፈፅሟል። በአሁኑ ወቅትም በአለ ሥነጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት የቅድመ እና ድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ፕሮፌሰር ሲሆን፣ የዘመናዊ ሥነጥበብ ሙዚየም ገብረ ክርስቶስ ማዕከልንም በመምራት ላይ ይገኛል።
#ኅዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም የአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ የአክብሮትና የምስጋና ፕሮግራም አድርገዉለታል። ተማሪዎቹ ያንን ያደረጉት ፕሮፌሰር በቀለ በጀርመን ሀገር ፍራንክፈርት ከተማ ከሚገኝው የሥነጥበብ ዩንቨርሲቲ ጋር ከዓመታት በፊት የተጀመረውን የኹለትዮሽ ግንኙነት ዳር በማድረስ ላደረገው ታላቅ ተግባር እና የትምህርት ቤቱን ዳግም ትንሳኤ ለማሳካት ድልድይ በመሆኑ በማመስገን ነው።
አሁን ታድያ ይህና ያልተነገረ እጅግ በርካታ፣ ውብና አስደናቂ፣ ገና ያልተተነተነና ዐይን የሚሻ ሥራን የሠራ ሰው ነው፥ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የመጀመርያው ሙሉ ፕሮፌሰር ማዕረግ የተሰጠው።
#ምንአሉ ?
ይህንን ዜና በደስታ በማኅበራዊ ገጾቻቸው ካጋሪት መካከል ጋዜጠኛ #ቴዎድሮስተክለአረጋይ እንዲህ አለ፥
“አንዳንድ ጊዜ ማዕረግም፣ ሹመትም፣ ሽልማትም በተለያዩ ምክንያትና አጋጣሚዎች ያልተገባ ሰው እጅ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ። ይህ ይበልጡን በሀገራችን፣ በዓለምም ላይ ታይቷል። ለፕሮፌሰር በቀለ መኮንን ዓይነቱ ደግሞ እንዲህ ግጥም ያለ ፣ በልኩ የተሰፋ ይሆናል። የበቄ ፕሮፌሰርነት በሥነ ጥበብ ዘርፍ የተሰጠ የመጀመሪያው ቢሆንም የሰውየው የበቀለ ብቻ አይደለም። የመጭው ትውልድ ሁሉ ነው። የሥነ ጥበብነት ብቻ ሳይሆን የመቻል ፕሮፌሰርነት ነው። ከእንግዲህ ለአንድ ጥበበኛ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መሰጠት እንደሚችል ማሳያው፣ ማመላከቻው፣ ዳገቱ፣ ምልክቱ ነው፥ በቀለ መኮንን። ያሉትና የመጭዎቹ የሥነጥበብ ልሂቃን ተስፋና ብርታት ነው። እንደሚቻል ማሳያውም፣ ማረጋገጫውም ሆኗል። ይህ ለሥነጥበቡ ብቻም ሳይሆን ለሙዚቃውም ፣ ለትያትሩም ነው።”
የሙያ አጋሩንናበአለ የሥነ ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት ዲን #ሠዓሊአገኘሁአዳነ በበኩሉ፥ “የቤት ሰው፣ መምህር፣ ባልደረባ፣ የሞያ አባት… ከፍ ሲል፣ ሲከብር፣ ድካሙ ፍሬ ሲያፈራ ወዘተ. ልብ ይሞላል። በቀለ መኮንን ንጉሡ ባለግዙፍ ሰብዕና፣ ከሰው ፊት የሚያቀረቡት፣ የሚያኮራ፣ ጥንቅቅ ያለ ሙያተኛ፣ በጥረቱ ከጉልበተኞች ቅሚያና ንጥቂያ፣ ከሰሜነኛው ንፍቀ ክበብ (global north) በር ጠባቂነት በጥበብ ሾልኮ በርካታ ዓለማቀፍ መድረኮችን የተጋራ፣ ረብ ያለው ተግባር እየፈጸመ ያለ ሰው የሚሠራበት ተቋም አዲስ አበባ ዮኒቨርስቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቶታል። የአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የመጀመርያው ሙሉ ፕሮፌሰርሽፕ ማዕረግ መሆኑ ነው።” ሲል አያይዞ የእንኳን ደስ አለህ መልዕክቱን እስተላልፏል። #ደራሲእንዳለጌታከበደ (ፒኤችዲ) “አሁን የሆንከውን ለመሆን፣ አንተው ራስህ የጻፍከውን ግጥም ኖሮ መገኘትን ይጠይቃል።” ሲል መግቢያ አኑሮ ባጋራውና ራሱ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን በጻፈው ‘ቼ በለው’ በተሰኘው ግጥም እናብቃ፥
ቼ በለው!
ሕይወት ጎዳናው ገጹ ሲለወጥ
በጭነት ታክቶ ጀርባው ሲመለጥ
የእንቅፋት አጽሙ ቋጥኙ ሲገጥ
ሸክም ዘንቦበት ትቢያው ሲላቆጥ
ሲሆን ድጥ በድጥ
ሾህ ጭቃ ቅይጥ
ልብህ አይደንግጥ።
በምኞት ቅዥት በስጋት ርዶ
አይፍረስ ግንቡ ወኔህ ተንዶ
ከቆመው ቆመህ ከንፈር ከመምጠጥ
በተስፋ ፈረስ በልጓም ሸምጥጥ።
አያረጅ የለም አይለዋወጥ
ነገን ተማምነህ በመጓዝ ቁረጥ…
ከሩቅ አልመህ ቅርብ አትርመጥመጥ
ሰግተህ ከምትቆም ስትጋልብ ፍረጥ።
#መምህሩጋሽወርቁ ስለ ፕሮፌሰር በቀለ
መምህር ወርቁ ጎሹ የፕሮፌሰር በቀለ መኮንን አስተማሪ ሲሆኑ የ85 ዓመት ሰውም ናቸው። በቀለ ከወጣትነቱ አንስቶ ህልሙን ለማሳካት ታላቅ ጥረት የሚያደርግ ተማሪዬ ነው ሲሉ በኩራት ምስክርነት ይሰጣሉ። መምህር ወርቁ ጎሹ ቀራጺ በቀለ ከሰዎች ጋር የመግባባት ክህሎትን የታደለ የሚወደውን ሙያ እየሠራ ያለ ብቃት ያለው የሥነ ጥበብ ባለሙያ ነው ሲሉ ይገልጹታል።
ጋሽ ወርቁ 30 ዓመታት አስተምረዋል። በቀለን ሲገልጹት የሚደነቅና የሚከበር ይሉታል። በራሳቸው ጥረት ካደጉት ተርታ ይመድቡታል።
ጋሽ ወርቁ ወደ ኃላ መለስ ብለው የፕሮፌሰር በቀለን የትምህርት አቀባበል ሲያጤኑ የቀን የሌት ጥረት የሚያደርግና የልፋቱን ያገኘ በሚል ያስረዳሉ። ተሰጥዖም የሚታይ ነው ይላሉ።
ዛሬ ፕሮፌሰር መሆኑ ለአገር ትልቅ ኩራት መሆኑንም ነግረውናል።
" የበቀለ ፕሮፌሰር መሆን ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለአገር ኩራት ነው። እኔ እንደ አስተማሪው ይህን የምሥራች ስሰማ ደስታዬ ያይላል።እንኳን ደስ ያለህ ልለውም እወዳለሁ። "ሲሉ ለተወዳጅ ሚድያ ምስክርነት ሰጥተዋል።
በቀለ መኮንን፤
በብሔራዊ ትእምርት ፍለጋ ውስጥ
#በተባባሪፕሮፌሰርቴዎድሮስገብሬ
I
ከብረት እስከ ጨርቅ በደረሱ ትይዩ ተቃራኒዎች መካከል ሲያመላልሰን የከረመው በቀለ መኮንን፣ ጥቁር ጤፍ ፈጭቶ--ጥቁር ጤፍ አቡክቶ “በጋገራቸው” ኪነቶች አማካይነት ሊፈትነን “ጤፍና ነጻነት” የሚል ርእስ በሰጠው አዲስ ትርኢት ተገልጧል፡፡ “ጤፍ” እና “ነጻነት”? ጤፍ ገቢር ነው፡፡ ነጻነት ደግሞ ኀልዮ፡፡ ጤፍ ይሰፈራል፤ ይፈጫል፤ ይቦካል፤ ይጋገራል፡፡ ነጻነት ግን በኅሊና ይነደፋል፡፡ ጤፍ እና ነጻነት በነገረ ፍጥረታቸው አይገናኙም፡፡ 'እናስ በምን ተጠየቅ ተዛምደው በአንድ ርእስ ውስጥ በ“እና” ተዳሩ?' የሚል ጠያቂ ከመጣ ምላሹን የሚያገኘው ከትርኢቱ ዐውድ ይሆናል፡፡
በቀለ በትርኢት መግለጫዎቹ በገሀድ እንደሚጠቁመን በአዳዲስ ሥራዎቹ ውስጥ ረቂቁ “ነጻነት” በግዙፉ ጋሻ ውስጥ አድሮ ተጨባጭ ሆኗል፡፡ በእርግጥ ጋሻ የሚመስሉ “እብጠቶች” በበቀለ ዕይታዊ መድበለ ቃላት ውስጥ የሰርክ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በቀደሙት ትርኢቶች ውስጥ ጋሻዎች አንድም ቅርጽ ከቅርጽ ተጋጭተው ለሚፈጥሩት “ግብታዊ” ፍቺ ሲባል ይመላለሳሉ፤ አንድም ደግሞ የማረሻን የገነነ ወንዴነት ማስከኛ ሆነው በሚዛን ጠባቂነት (as a feminine energy) ይመጣሉ፡፡ በ“ጤፍና ነጻነት” ነጻነት በጋሻ ውስጥ በማደሩ፣ ጋሻ ከቀደመ ግብሩ የተለየ አዲስና ቋሚ ሚናና ግብር ይዟል ማለት እንችላለን፡፡ አዲስ ግብር ለመያዙ ምስክሩ ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በትርኢቱ ውስጥ የሚገጥሙን ጋሻዎች በሙሉ በጤፍ ዱቄት የተገነቡ (የተለሰኑ) ናቸው፡፡ የጋሻዎቹ በጤፍ ዱቄት መገንባት አንድም፣ በትእምርቶቹ መካከል የባሕርይ መጋራት እንዲፈጠር፤ አንድም በኪነቱ ውስጥ ጥንድ ምናብ--ድርብ አስተማስሎ (double representation) እንዲከሰት ዕድል ሰጥቷል፡፡ የጉዳዮች በአንድ ወደተሸረቡ መንታ ትእምርትነት ማደግ ተመልካች ሐሳቡን የሚያሰላበትን፣ ትችቱን የሚያፍታታበትን ምቹ የመፈከሪያ ዐውድ እንዲያገኝ አስችሎታል፡፡
ጋሻ የነጻነት እና የአርበኝነት ማኅደር ነው፡፡ (ይህ ዓይነቱ የጋሻ ፍቺ በተገኘበት ባህል ውስጥ ጭምር ይታወቃል፡፡) ቆየት አድርጌ በስፋት እንደማሳየው ጤፍ በፈንታው የ“ኢትዮጵያ” እና “የኢትዮጵያዊነት” ብሔራዊ ትእምርት ነው፡፡ በዚህ ዐውድ የብሔራዊ ትእምርት ፋይዳ አንድም፣ በነጻነት፣ በአገር እና በብሔራዊ ምንትነት መካከል ያለውን ረቂት ተራክቦና ውስብስብ ተጻምሮ ተጨባጭ ማድረግ ነው፡፡ አንድም ደግሞ ተራክቦውን--ተጻምሮውን ጠብቆ ለማኖር ዜጎች በአርበኝነት መንፈስ የሚከፍሉትን የላብና የደም መስዋዕትነት ማመልከት ነው ማለት እንችላለን፡፡ (በ“Gluten-free-dom II” እንጀራ የጠመጠመ ጋሻ በአናታቸው የደፉ፣ በትኩስ የአመድ ደለል ላይ/ውስጥ የቆሙ ሰባት እናቶች እንዲህ ላለው አንድምታ አስረጂዎች ይሆኑናል፡፡)
II
ብሔራዊ ትእምርቶች የብሔራዊ ምንትነት ግላጼዎች (identity expressions) ናቸው፡፡ የምንትነቱ ሥሪት (identity construction) በተረኮቹና በትእምርቶቹ ጥራትና ጥንካሬ ላይ ይወሰናል፡፡ ግላጼዎቹ እና ሥሪቱ የሚተጋገዙ ብቻ ሳይሆን የሚተካኩ ጉዳዮች ጭምር ናቸው፡፡ ያንዱ መድከም ሌላውን ያጎድላል፡፡ ያንዱ መዛል ሌላውን ያፈርሳል፡፡ የብሔራዊ ትእምርት ቀረጻ ብሔራዊ-ጥበባዊ ተልእኮ ነው፡፡ የአንድ ሕዝብ ብሔራዊ ምንትነት በአንጻራዊነት ለዘመናት ጸንቶ ይዘልቅ ዘንድ ተረኮች (ቃላዊ፣ ዕይታዊ፣ ትውናዊ፣ ወዘተ. ተረኮች) እና ትእምርቶች በጥንቃቄ መመረጥና መቀናበር፣ በየጊዜው እየተመረመሩ መታረምና መከለስ ይኖርባቸዋል፡፡ ብሔራዊ ምንትነት በዐቢይነት የውክልና ጉዳይ ነው፡፡ በአንድ አገር ውስጥ እያሉ እንደሌሉ የተቆጠሩ ወገኖች፣ ቸል የተባሉ ሰብአዊ ዕሤቶች፤ አቅም ባገኙ፣ የኃይል ሚዛን በለወጡ ጊዜ በነባር ተረኮች እና ትእምርቶች የተሸመነውን ብሔራዊ ምንትነት እስከ መሻር፣ አፍርሶ እንደ አዲስ እስከመሥራት የሚያደርስ ጥያቄ ያነሳሉ፡፡ ይህ ሲከሰት የአገር ግንባታ ሂደት ይስተጓጎላል፤ ማኅበራዊ ውጥረት ይነግሣል፡፡ (የዛሬዋ ኢትዮጵያ ለዚህ ዓይነቱ እውነታ አብነታችን ናት፡፡) በመሆኑም ብሔራዊ ትእምርት ቢያንስ ቢያንስ ረጅም የታሪክ ዘመንን፣ ሰፊ መልክአ ምድርን እና ገሀድ የወጡ የማኅበረሰብ ክፍሎችን እና ዕሤቶችን ሊያካልል ይገባል፡፡ ብሔራዊ ትእምርት ከውክልናው ፈርጀ ብዙነት ባሻገር በኪነት ከፍታው እና በኀልዮ ጥራቱም ተለይቶ መታወቅ አለበት፡፡ ጥቅል በሆነ አነጋገር፣ ብሔራዊ ትእምርት ጥልቅ በሆነ ጊዜ ውስጥ፣ ጽኑእ በሆነ መሠረት ላይ የሚታነጽ በነባርና በአዳዲስ ዕሤቶች ትብብር የሚሸመን ዐውራ ምስል ነው፡፡
እንደ ኢትዮጵያ ላለ ኅብረ ባህላዊ አገር ብሔራዊ ትእምርት በትግግዝ የሚፈጸም ብሔራዊ--ኪናዊ ተልእኮ ነው፡፡ ብሔራዊ ትእምርት እርስ በርስ ሊናበቡና ሊከታተሉ በሚችሉ በግለሰብ፣ በቡድን፣ በትውልድ በሚፈጠሩ ገባር ምናቦች ትግግዝ በዘመናት ሂደት ምልዓት ላይ የሚደርስ ዐውራ ትእምርት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ኪናዊ ትግግዝ--የምናብ ተናባቢነትና የምስል ተከታታይነት--በተጨባጭ ለማሳየት “ጤፍና ነጻነት”ን በሁለት መንገዶች ማንጸር እንችላለን፡፡ ቀዳሚው መንገድ ይህንን ትርኢት ከበቀለ መኮንን ነባር ትርኢቶች ጋራ እያመሳከሩ መፈከር ሲሆን፤ ተከታዩ ደግሞ በየትኛውም የኪነት ዘርፍ ካሉ ዘመነኞቹ ጋራ--ለምሳሌ ከአዳም ረታ ጋራ--እያናበቡ ማስተሳሰር ነው፡፡ የበቀለ መኮንንን ዕይታዊ ጥበብ ከአዳም ረታ ቃላዊ ኪነት አናብቦ በብሔራዊ ትእምርትነት ለማስላት በቂ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለዛሬው ትርኢት የነፍስ ያህል የሆነውን ዐውራ መባያ[1]--ጤፍን በበቀለ የአከያየን ልማድ ውስጥ ከገነነው፣ ከማረሻ ጋራ አስተሳስሮ ለማሰብም እንዲሁ፡፡ ከምክንያቶቹ ውስጥ መሠረታዊዎቹ፡- አንደኛ፣ የዐውድ ተዛማጅነት፤ ሁለተኛ፣ የኀልዮ (የጭብጥ) ተከታታይነት፤ ሦስተኛ፣ የቅኝት ወይንም (የርእዮተ ዓለም) ተወራራሽነት፤ አራተኛ፣ የጊዜ ጥልቀት (የነገረ ፍጥረት ብሉይነት)፤ አምስተኛ፣ ሥነ ልሳናዊ ተዛማችነት ናቸው፡፡
“ማረሻ” የግብርና ማምረቻ መሣሪያ፣ “ጤፍ” ደግሞ የግብርና ምርት በመሆናቸው በተፈጥሮ የቅደም-ተከተል ዝምድና አላቸው፡፡ (ተፈጥሯዊው ቅደም ተከተል በጉዳዮቹ መካከል አለ ያልነውን የጭብጥ ተከታታይነት እና የትእምርት ተጋጋዥነት ተጨባጭ ያደርግልናል፡፡) የማምረቻ መሣሪያው (ማረሻ)፣ የአምራቹ (ገበሬ) እና የምርቱ (ጤፍ) ተፈጥሯዊ የተራክቦ ዐውድ ገጠር ነው፡፡ ጤፍ እና ማረሻ ከ85 ከመቶ በላይ ኢትዮጵያዊ ይኖርበታል የሚባለውን፤ ዳሩ ግን በአገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ተገቢ ሥፍራ የተነፈገውን ወገን በቀጥታ ይመለከታሉ፡፡ ከያኒው ለተገፉ፣ ሥፍራ ለተነፈጉ ብሔራዊ ጉዳዮች ማድላቱ የትእምርቶቹን ምርጫ ተገቢነት ከማረጋገጡ ባሻገር ቅኝቱን ርእዮተ ዓለማዊ ያደርገዋል፤ (“history from below” እንደሚባለው)፡፡ ገጠርን አትኩሮ፣ ነባር የግብርና መሣሪያንና ጥንታዊ ምርትን (ማረሻንና ጤፍን) ከዚያው ዐውድ መልምሎ በምናብ ማጥለቁ፣ በምስል ማበልጸጉ እና በኀልዮ ማራቀቁ ብዙኃኑን የሚወክል፣ ዘመናትን የሚዋጅ ጽኑእ ብሔራዊ ትእምርት ለመቅረጽ ዕድል የሚሰጥ ይመስለኛል፡፡
የጤፍ ነገረ ኪን እና ፖለቲካም (the poetics and politics of teff) በቅኝት ከዚህ የሚለይ አይመስለኝም፡፡ ጤፍ በመጠን በአነስተኛነቱ “ዝነኛ” ነው፡፡ ለምሳሌ፣ አንድ የስንዴ ቅንጣት በአማካይ ከአንድ መቶ ሃምሳ የጤፍ ቅንጣቶች ጋራ እኩል እንደሆነ ይገመታል፡፡ ይህ ደግሞ “ከትውልድ ሥፍራው” አልፎ በዓለም ካሉ የእኽል ዝርያዎች በሙሉ በመጠን ትንሹ ያደርገዋል፡፡ በደስታ ተክለ ወልድ መዝገበ ቃላት ይህ የእኽል ዘር በተከታዩ መንገድ ተበይኖ እንመለከታለን፤ “ጤፍ፤ የታናሽ እኽል ስም፤ የሣር ዐይነት ሙርዬ የሚመስል፡፡ (ተረት)፤ ሳይቸግር ጤፍ ብድር” (19962፡ 675)፡፡[2] በዓለም ምግብ ድርጅት ገጽ ላይ ሰፍሮ እንደምናነበው፣ ጤፍ ከኢትዮጵያ ውጪ ባሉ አገራት፣ ለምሳሌ በደቡብ አፍሪካ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ከከብቶች ቀለብነት ባለፈ የአፈር መሸርሸርንና የውሃ ብክነትን ለመቀነስ ታስቦ የሚለማ “ተራ ሣር” ነበር፡፡[3] ተወዳጅ ነው በሚባልባት እናት አገሩም ቢሆን በመጠን ማነሱን ታክከው የሚቀርቡ ንጽጽሮች አጓጉልነት አላጣቸውም፡፡ ለአብነት፣ “ከመጤፍ አልቆጠረኝም” እና “ሰው ጤፉ” የሚሉ አገላለጾች በደረጃ ማነስን በገሀድ ያውጃሉ፡፡
ጤፍ በጄኔቲካዊ አወቃቀሩ እጅግ የተወሳሰበ፣ በጾታ ቅንብሩ የተደባለቀ (ፈናፍንት)፣ በምግብ ይዘቱ የበለጸገ የእኽል ዓይነት እንደሆነ የአዝርእት ባለሙያዎች ያስረዳሉ (ሰይፉ 1997)[4]፡፡ ሰይፉ ከተማ በመስኩ ላይ የተካሄዱ ምርምሮችን በከለሱበት ጽሑፋቸው እንደሚያስረዱን፣ የጤፍን የትውልድ ቦታ በእርግጠኝነት መናገር ቢከብድም፣ ጄኔቲካዊ ብዝኃነቱን በማጤን ኢትዮጵያ እናት ምድሩ ልትሆን እንደምትችል መገመት አስቸጋሪ አይሆንም፤ “[T]he genetic diversity for teff exists nowhere in the world except in Ethiopia, indicates that tef originated and was domesticated in Ethiopia” (12)፡፡ ጤፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ ጥንታዊ ከሚባሉ ጥቂት የእኽል ዘሮች መካከል አንዱ ነው፡፡ በዚህ የእኽል ዘር ላይ ከተካሄዱ ምርምሮች መካከል ብዙዎቹ፣ Nicolai Vavilovን (1951)[5] መሠረት በማድረግ፣ ቅድመ ክርስቶስ ከ4000–1000 በኢትዮጵያ ውስጥ እንደበቀለና ተስፋፍቶ እንደለመደ ይገምታሉ፡፡ እንደ ጤፉ ሁሉ፣ “ኢትዮጵያዊው” ማረሻ፣ ከዕድሜው ጥንትነት ባለፈ ልደትና ዕድገቱም እዚሁ መሆኑን የሚያመላክቱ ምርምሮች አሉ፤ ለምሳሌ፣ Hubert Cochet ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች በማረሻ ለ2000 ዓመታት እንዳረሱ ይጠቁማል (2011፡ 31)፡፡[6]
በኢትዮጵያ ውስጥ ከሦስት ሺህ በላይ ዘመናትን ያስቆጠረው፣ ከአገሪቱ ሕዝብ መካከል 70 ከመቶው በእንጀራ መልክ ይመገበዋል ተብሎ የሚገመተው ጤፍ (ታደሠ 2017፡ 50) በሦስቱ ዐበይት የሥነ ልሳን ቡድኖች ተቀራራቢ ስያሜም አለው፡፡ በአማርኛ “ጤፍ”፣ በኦሮምኛ “tafi” በትግሪኛ “ጣፍ”፡፡ በቀለም ስርጭትም ረገድ ወተት ከመሰለ ነጭ (ማኛ) አንስቶ እስከ ጥቁር ድረስ የሚዘልቁ አራትና አምስት ቀለማትን ያቅፋል (አዳም በሁሉም ቀለሞች የሚጫወት ሲሆን የበቀለ ምርጫ ጥቁሩ ነው)፡፡ እንዲህ ያለው የባሕርይ ውስብስብነት፣ የጾታ መንታነት፣ ኅብረ ቀለማዊነት ጤፍን--በአዳም ረታ ጥበበ ቃላት እና በበቀለ ዕይታዊ ጥበብ--ውስጥ ለብሔራዊ ትእምርትነት የተመቸ መባያ አድርጎታል፡፡ “ማረሻ” በበኩሉ ኢትዮጵያውያን የወል ምንትነታቸውን ከሚቀርጹባቸው ብሉይ ዕሤቶች መካከል አንደኛው ነው፡፡ የወልነቱን በዐበይቱ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ውስጥ ባለው የስያሜ ተወራራሽነት መረዳቱ አያሰቸግርም (የአማርኛው “ማረሻ”-- በግእዝ “ማሕረስ”፣ በኦሮምኛ “maarashaa”፣ በትግርኛ “ማሕረሻ” የሚሉ አቻዎች አሉት)፡፡ ብሉይ ነው ስል አንድም፣ የዘፍጥረቱን ጥንታዊነት፤ አንድም፣ የጊዜ ጥልቀቱን ታክኮ የሚመሠረተውን ባህል ጽኑእነት ማመልከቴ ነው፡፡ በተፈጥሮው ቀጥ ያለው፣ የተሳለውና የሾለው ማረሻ፣ በበቀለ ትርኢቶች ውስጥ በከያኒው ፈቃድ፣ ፍላጎትና እጅ መዋቅሩ ተናግቶ፣ “ተፈጥሮው” ተዛብቶ ልክ እንደ ጤፍ ወደ ፈናፍንትነት ተቀይሯል፡፡ የበቀለ ማረሻዎች መዋቅር መናጋት የአድሏዊው የተባዕትነት ሥርዓት ፈርሶ በአዲስ ተምኔታዊ ሥርዓት የመተካቱ አምሳያ ነው፡፡ ከዚህ ሥርዓት ውስጥ ነው እንግዲህ ከያኒው አዳዲስና ነባር ዕሤቶች ተዳርተው የሚሰናኙበትን ብሔራዊ ትእምርት ለመፍጠር የሚታገለው፡፡[7]
ጤፍ እና ማረሻ ኢትዮጵያውያን ጥልቅ ከሆነ ጊዜ፣ የጋራ ታሪካቸውን፣ ርእዮታቸውንና ንጽረታቸውን የሚጠልቁባቸው፤ ሩቅ ከሚባል ትናንት የወል ልቡናቸውንና ምንትነታቸውን የሚያደሩባቸው “ቁሳዊ” ዕሤቶች ናቸው፡፡ ቤኔዲክት አንደርሰን፣ “It is the magic of nationalism to turn chance into destiny” (1983፡ 12)[8] እንዳለው ዕጣ ፈንታቸው ጭምር ተጠላልፎ የተሰናኘባቸው የወል ዕሤቶች፡፡ ማን ከዕጣው ማምለጥ ይቻለዋል? እንደሚታወቀው እንዲህ ያለ ዕሤት በጥልቅ ጊዜ እና በጽኑእ መሠረት ላይ የሚቆም አገር ለማነጽ ምቹ ዕድል ይፈጥራል፡፡ በእርግጥ አንድ ማኅበር በጽናት ይቆም ዘንድ ዕጣውን ከቋጠረበት ሩቅ ትናንት በተጨማሪ፣ በገነነ “የሕዝብ ማኅበራዊ ልቡና” ነገውን የሚዋጅበት የጋራ ስኬት እንደሚያስፈልገው አሌ አይባልም፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ስኬት ጤፍ እንግዳ አይመስለኝም፡፡ ትናንት፣ ጤፍን ለሰው ልጅ ምግብነት በማዋል ረገድ ኢትዮጵያ ከዓለም ብቸኛ አገር ነበረች፡፡ ዛሬ፣ በተለይ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ በሚኖሩ፣ እንጀራን መለያቸው ባደረጉ በ“ነባሬ ባዕድ”[9] (diaspora) ኢትዮጵያውያን በሚተዳደሩ ምግብ ቤቶች አማካይነት ዝናን ያተረፈው ይህ የእኽል ዘር የኢትዮጵያን ድንበር ተሻግሯል፡፡ በጣዕሙ፣ በምግብ ይዘቱና ለጤና ባለው ጠቀሜታ ከተመጋቢው እኩል በሥነ ምግብ ተመራማሪዎች ዘንድ ተወዳጅ የሆነው ጤፍ በትልልቆቹ የዓለም የመገናኛ ብዙኋን ሳይቀር (ለምሳሌ፣ በBBC, VoA, The Washington Post, The Guardian, The New York Times, ወዘተ.) “the next ‘super grain’ of the World” የሚል መወድስ ወርዶለታል፡፡ ይህንን ዝና ተከትሎ ሊመጣ የሚችለው ማኅበራዊ ከፍታ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ--(as a national branding) ብሔራዊ ክብርና ኩራትን የመፍጠር አቅም አለው፡፡ የጤፍ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው አንድም በመከባበር ላይ የተመሠረተ አንድነትን ለመፍጠር የሚያግዝ፤ አንድም በጎሣ፣ በሃይማኖት እና በቋንቋ ምክንያቶች የተፈረቀቀውን ብሔራዊ ልቡና (the national psyche) ለማከም የሚያስችል ዕድል እመስጠቱ ላይ ነው፡፡[10]
III
ትኩረታችንን ወደ ዛሬው ትርኢት እንመልስ፡፡ “ጤፍና ነጻነት”፡፡ ጤፍ የ“ኢትዮጵያ” እና “የኢትዮጵያዊነት” ብሔራዊ ትእምርት፤ ጋሻ በበኩሉ የነጻነት እና የአርበኝነት ማኅደር መሆኑን በመግቢያዬ አመልክቻለሁ፡፡ እንዲህ ያለው የጋሻ ትርጉም ህልው በሆነበት ባህል ውስጥ ጭምር ታውቆ የሚሠራበት ነው፡፡ በትርኢቱ ውስጥ ከቀረቡት ሥራዎች ብዙዎቹ ከጤፍ እና ከጋሻ ተራክቦ የተገኙ ናቸው፡፡ ይህ ማለት ግን ሁለቱ ጉዳዮች በሁሉም ትዕይንቶች ውስጥ እኩል ሥፍራ አላቸው ማለት አይደለም፤ በፍጹም፡፡ ጤፍ በሚናው ይልቃል፡፡ የጭብጥ ክትትል ከመፍጠር፣ የመተርጎሚያ ዐውድ ከመተለም ባለፍ ዝርው ህልውናም አለው፡፡ ጤፍ በቤት ውስጥ ቁስነት ተከስቷል፤ የግድግዳ ምርጊት ሆኖ ተገልጧል፤ ወዘተ፡፡ ጤፍ ታሪክ ነው፤ ምጣኔ ሀብት ነው፤ ፖለቲካ ነው፤ ርእዮተ ዓለም ነው፡፡ በጤፍ የሰው አካል ተገንብቷል፤ የሰው ገጽ ተነድፏል፡፡ ገጻተ ሰብኡ ከጤፍ መልኩንም ይዘቱንም ወርሰዋልና ወደ ጤፍነት ተለወጡ ማለትም እንችላለን፡፡ ከተጨባጭ ሁነቶችና ህልውናዎች ባለፈ ጤፍ ለልእለ አካላዊ ክስተቶች ማድሪያነት ውሎም እንመለከታለን፡፡ ለምሳሌ፣ “ጓዳና ግርግዳ” የሚል ርእስ በተሰጠው፣ በቀጫጭን ዘንጎችና በጥቁር ጤፍ ትግግዝ በተቀናበረ ግድግዳ ላይ (በጤፍ ቡኮ የተመረገ፣ ጋሻ ያዘለ ግድግዳ) ከያኒው ይሁነኝ ብሎ በተዋቸው ሽንትር ሽንቁሮች ውስጥ አሳልፈን የምናየው “የቤተ ክርስቲያን” ጨርቅ ልእለ ፍጥረት ህላዌ ከልደትና ሞት ጋራ የታተመበት ነው፡፡ በመሆኑም ጤፍ በትርኢቱ ውስጥ የነገረ ሰብእን ዕጣ የምናሰላበትን ስብርባሪ አፍታ ጭምር ይሰጠናል ማለት ነው፡፡
በትርኢቱ ውስጥ በጤፍ ከተገነቡ ምስሎች መካከል ገጸ ሰብእ[11] የተነደፈው በሁለት ተከታታይ ትዕይንቶች ውስጥ ብቻ ነው፤ በ“Gluten-free-dom I” እና በ“Gluten-free-dom II”፡፡ እነዚህ ትዕይንቶች “ተከታታይ” ብለን ብቻ የምናልፋቸው አይመስሉኝም፡፡ ይልቁንም እጅግ በተወሳሰበ ትእምርታዊነትና በተራቀቀ ዘይቤ የተከየኑ፣ ለፈርጀ ብዙ ንጽጽርና ትርጓሜ የተመቹ ወደረኛ ቅርጾች ናቸው፡፡ ኋለኛውን መነሻ እናድርግ፡፡ ጀርባ ለጀርባ እንጂ ፊት ለፊት የማይተያዩ፣ ትከሻ ለትከሻ ገጥመው ክብ የሰሩ የሰባት ነፍሰ ጡሮች ትዕይንት ነው፡፡ በዚህ ትዕይንት ውስጥ ሴቶቹ ክብነቱን ጠብቆ በጠባቡ በሚዞራቸው ቡላ ቀለም ያለው የአመድ ደለል ላይ ቆመዋል፡፡ ደለሉን ተከትሎ በክቡ የሰፈነው ነጭ አመድ ከሸማ የተሠራ ምንጣፍ፣ በዙሪያው የተኮለኮለው የከሰል ሰልፈኛ ደግሞ ጥቁር ጥለት ይመስላሉ፡፡ በሆዳቸው ፍሬ የያዙ ሰባት ሴቶች የተደራረቡ እጆቻቸውን ሐፍረታቸው ላይ ጣል እንዳደረጉ፣ እንጀራ የለበሰ ጋሻ አናታቸው ላይ እንደደፉ፣ በአክብሮት ይሁን በፍርሐት አልያም በሐፍረት አቀርቅረዋል፡፡
ሁለተኛው ትዕይንት የአንድ ሰው “ገድል” ነው፡፡ ይህንን ገድል እኔ “ገልና ገልቱ” ብዬ እጠራዋለሁ፡፡ (“ገል” የጋን ስባሪ፤ “ገልቱ” ያልሠለጠነ፣ በድንቁርና የተደፈነ፡፡) ዙሪያውን በተሰባበሩ ሸክላዎች የተከበበ፣ ከምድር ከፍ ብሎ የታነጸ፣ ባለ ስድስት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ጡብ ገዝፎ ይታያል፡፡ ሙቀት ፍለጋ እጆቹን ወደ ፊት የዘረጋው ሰው እጡቡ አናት ላይ ባፍጢሙ እደፋው የአባቶቹ ጋሻ ላይ “ተመቻችቶ” ተቀምጦ “የደቀቁ የሸክላ ገሎችን በተመስጦ ይሞቃል”፡፡ ሁለቱ ትይዕንቶች የመከታተል ብቻ ሳይሆን እርስ በእርስ የመተረጓጎም ባሕርይም አላቸው፡፡ ይህንን ለማጤን እላይ በገለጻዎቹ ውስጥ የሰፈሩትን ወደረኛ ድርጊቶችና ሁነቶች ማነጻጸሩ ብቻ በቂ ይመስለኛል፡፡
ሴቶቹ በገዛ ፈቃዳቸው ፋታ ለማይሰጥ፣ ድካም ለበረታበት፣ ህመም ላለበት ኃላፊነት ራሳቸውን የሞሸሩ ይመስላሉ፡፡ አንድም የቁጥራቸው ሰባትነት የኃላፊነቱን ክብደት ያጸናል፡፡ ሰባት ቁጥር በትውፊት፣ በሃይማኖት፣ በኪነት፣ ወዘተ. ውስጥ ምልዐትን፣ ፍጹምነትን ለማመልከት ተመላልሶ የሚመጣ ነባር መባያ ነው፡፡ ፍጹምነቱና ሙሉነቱ የበረከትም የቅጣትም ሊሆን ቢችልም፡፡ አንድም ሴቶቹ የቆሙበት የአመድ ደለልም ሆነ አካላቸው ተገጣጥሞ የፈጠረው የቅርጽ ክብነት እላይ በቁጥር ጸና ያልነውን በድካምና በህመም የተሞላ ኃላፊነት ፍጹም ያደርገዋል፡፡ በክብነት ውስጥ መውጫ ቀዳዳ ይጠፋል፤ መነሻና መድረሻ ይታጣል፡፡ ለእረፍት የሚሆን ጥጋት አይሰጥም፡፡ በቀለ በምስሉ መግለጫ ላይ በገሀድ እንደሚጠቁመን ሰባቱ ሴቶች በዝርው ሰባቱን ቀናት ይወክላሉ፡፡ በዚህም ሰንበት ተገድፏል፤ የለመድነው የጊዜ መስፈሪያ ተሽሯል፡፡ ቀናቱ በሴቶቹ ድርጊት ተቃኝተው “ጊዜ” ከሰው ጋራ የሚለያይበት መስመር ደብዝዟል፡፡ መነሻ፣ ማጋመሻ፣ መዳረሻ የሚባሉ አንድም፣ የድርጊትና የሁነትና መሥፈሪያዎች፤ አንድም የጊዜ ዋቢዎች ሳስተዋል፡፡
እላይ በእንጥልጥል ወደተውነው ጉዳይ እንመለስ፤ “ገሎችን መሞቅ” ምን ማለት ነው? ከከያኒው ምስክርነት ባሻገር የወጣቱ የእጅ አዘረጋግ ሁኔታ በሙቀቱና በአካሉ መካከል በፈጠረው ሚዛን ሙቀትና ምቾት መኖራቸውን እንረዳለን፡፡ ግን እሳቱ ወዴት ነው? የሙቀቱ ምንጭስ ምንድ ነው? ለእነዚህ ጥያቄዎች በአንድምታ የምንገልጠው እውነታ ካልሆነ በቀር፤ በቀጥታ የምናገኘው መልስ ያለ አይመስለኝም፡፡ በባለ ስድስቱ ማዕዘን ጡብ ዙሪያ በሰፊው የፈሰሱት የገል ስብርባሪዎች በኢትዮጵያውን የቆየ ታሪክ ውስጥ ቋሚ ሥፍራ ያላቸው፣ በሸክላ የተሠሩ አገረ ሰብአዊ ዕደ ጥበባት ናቸው፤ በየዓይነቱ --የጀበና፣ የምጣድ፣ የድስት፣ የጋን፣ የጣባ፣ የዕጣን ማጨሻ፣ ወዘተ. ስብርባሪዎች፡፡ ስብርባሪዎቹን በቅርበት ላጤነ ሰው ዕደ ጥበባቱ በእርጅና ምክንያት ከሰርክ ግብራቸው የተገለሉ አይመስሉም፡፡ ይልቁንም ከነወዛቸው ከነጉልበታቸው ያሉ፣ ከግብራቸው በግድ ተነቅለው የደቀቁ ነው የሚመስሉት፡፡ በሌላ ቋንቋ ሙቀቱ የሚመነጨው ከገሎቹ ትኩስነት ነው፡፡ ትኩስነት፤ አንድም፣ ከእሳት ምድጃ የሰበሰቡትን ሙቀት ይዞ ማቆየት ነው፡፡ ገልቱው ዕደ ጥበባቱን ከተሰየሙበት ምድጃ ላይ ነቅሎ --ቡናና ወጡን ደፍቶ፣ ዳቦና እንጀራውን ገልብጦ--ጀበናውን፣ ድስቱን፣ ገበር ምጣዱን፣ ምጣዱን አንክቶ፣ እንካቹን ሜዳ ላይ ዘርቶ ትኩስነታቸውን እየሞቀ ነው፡፡ አንድም በዘይቤ ተራ እንናገርና ትኩስነት አፍላነት ነው፡፡ የአገልግሎት ዘመን አለመጋመስ፡፡ ከብርታትና ጥንካሬ ጋራ መሆን፡፡ ጠላውን ደፍቶ፣ እርጎውን ገልብጦ፣ ወዘተ. ያደቀቃቸው የሸክላ ውጤቶች፡፡
በዚሁ ተጠየቅ ከተጓዝን የሴቶቹን አቋቋም በመመርመር በሰባት ቁጥር እና በክብ ቅርጽ ትግግዝ ጸና ያልነውን ህመም በተጨባጭ መመልከት እንችላለን፡፡ የሴቶቹ ፋታ የለሽነት ድርጊቶቹንና ሁነቶቹን በሙሉ ወደማያቋርጥ ሂደትነት ለውጧቸዋል፡፡ ይህንን ለማጤን--በተለመደው አገላለጽ--እንጀራ የጠመጠመ ጋሻ ከሰፈነበት የራስ ጸጉራቸው፣ በአመድ ደለል እስከተደበቀው የእግር ጥፍራቸው ድረስ መመልከቱ በቂ ነው፡፡ አመዱ እና እንጀራው ትይዩ ናቸው፤ አንዱ ምርት ሌላው ግርድ፡፡ ከአናት እንጀራው በተመረተ ቁጥር ከስር አዲስ አመድ ይወድቃል፡፡ አዲስ አመድ --ትኩሣቱን ያልጨረሰ አመድ፤ ረመጥ፡፡ ይህ ማለት ሴቶቹ ረመጥ ላይ ቆመዋል እንደማለት ነው፡፡
ቀደም አድርጌ ለማሳየት እንደሞከርኩት ሴቶቹ እንዲህ ያለውን በድካምና በህመም የተሞላ ኃላፊነት በፈቃዳቸው መርጠው ተቀብለዋል፡፡ በማሕፀኗ ሽል የያዘችን እናት በረመጥ እስከመድበን የሚያደርስ መስዋዕትነት ምን የሚሉት ኃላፊነት፣ እንዴት ያለ ዓላማና ተልእኮ ነው? የራስን ሰብእና የሚያደቅቅ፣ ህልውናን የሚያመነምን፣ ሕይወትን የሚያሰልል ተግባር ውስጥ በፈቃድ መሳተፍ ራስን ለከፋ ጉዳት ማጨት ይመስላል፡፡ የፈቃድ ጉዳት (self-destruction)፣ ከፍ ሲልም የፈቃድ ሞት ከዳግም ልደት ጋር የሚዛመዱበት እንዲህ ያለው አቀራረብ ሚታዊ አመሳሰል ነው፡፡ ይህን ዓይነቱን አመሳሰል በሚቶሎጂ ውስጥ በብሉየ መዋዕልና[12] ደንብ ከተቀረጹ ምስሎች (archetypal imageries) ጋራ አቆራኝተን መመልከት እንችላለን፡፡ በሆዳቸው ፍሬ የያዙ ሴቶች ትከሻ ለትከሻ ገጥመው ክብ መሥራታቸው፣ በሠሩት ክበብ ውስጥ ረመጥ ላይ መቆማቸው፣ በአመድ ደለል መያዛቸው፣ እንጀራ “ማብቀላቸው” በአንድ ግዜ ኦሮቡረስን (በክብነት) እና ፊኒክስን (በረመጥነት-አመድነት) አቃልጠን እንድናስብ ያደርገናል፡፡ ራሷን አቃጥላ ከትቢያዋ ላይ ነፍስ የምትዘራው ፊኒክስ (Phoenix) እና በክብ ቅርጽ ከጅራቱ አንስቶ ሙሉ አካሉን በልቶ በአዲስ ህልውና የሚከሰተው አሮቡሮስ (Ouroborus) “ሁለንተናዊ” ሊባሉ የሚችሉ የህመምና ድኅነት፣ የሞትና ልደት ትእምርቶች ናቸው፡፡ ባዶ እግራቸውን ረመጥ ላይ የቆሙ ሰባት እናቶች በቸልታ የተጎዳውን ነባር ምንትነት፤ በሆዷቸው የያዟቸው ሰባት ፍሬዎች ደግሞ እንደ አዲስ ይወለድ ዘንድ የሚጠበቀውን ርእይና ርእዮት ይወክላሉ፡፡ ከዚህ ትዕይንት ዓላማዎች መካከል አንዱና ምናልባትም ቀዳሚው ለዘመናት ለኖረው፣ ዳሩ ግን ቸል ለተባለው የእናቶች ህመምና ድካም--የላቀ ብሔራዊ ተግባር--ዕውቅና መስጠት ነው፡፡ ይህ ዕውቅና ልዕለ ሰብአዊ እና ልዕለ ታሪካዊ እንጂ ተርታና ሰርካዊ አይደለም፡፡ በሌላ ቋንቋ፣ ከያኒው ከፍ ባለ የአከያየን ስልትና ርእዮት እናቶችን ጥልቅ ጊዜ ውስጥ በመትከል ወደ ሚታዊ ተጋዳሊነት ቀይሯቸዋል፡፡ በምላሹም ከዚያው ጥልቀት ውስጥ በጽናት የሚቆም ብሔራዊ ትእምርት እና ብሔራዊ ምንትነት ለማስገር ሞክሯል፡፡
አንድም እናቶች ካለመኖር ህጽን መኖርን አስገኝተዋልና ለዚያም ኪናዊ ውዳሴ እንደ ማውረድ ሊቆጠር ይችላል፡፡ በአንዳንዶች ግምት “ጤፍ” የሚለው መጠሪያ “ጠፋ” ከሚለው ቃል የተገኘ ነው፤ ጠፋ፣ መኖር አቆመ፣ ህልውናው አበቃ እንደማለት፡፡ በሌላ ቋንቋ የዚህ የእህል ዘር የመጠን አነስተኛነት ከመኖር ይልቅ ላለመኖር ይቀርባል እንደማለትም ነው፡፡ የ“ጤፍ” የፍቺ ነቅኡ “ጠፋ” የሚለው ግስ ከሆነ፣ አንድም፣ ጤፍ የምንለው፣ በጣት የምንቆነጥረው ደቃቅ ነገር በተጨባጭ አለመኖርን ያስተማስላል (the representation of absence, the visibility of invisibilty) እንደማለት ነው፡፡ አንድም ዐውራውን የብሔራዊ ሚቶች መሻት--የመነሻዎች ሁሉ መነሻ የመሆንን፣ ከምንምነት ነቅእ የመፍለቅን መሻት--ይጠልፍልናል፡፡ ጤፍ አለመኖርን ከወከለ ከጤፍ የምንጠልቀው “ኢትዮጵያዊነት” ከእመ አበ አልቦ እንደተገኘ (creation ex nihilo, that is, creation from nothing) ይቆጠራል፡፡ በዘይቤ ተራ እንነጋገርና የኢትዮጵያ ገበሬ “አለመኖርን” ይዘራል፡፡ እናቶች ደግሞ ከአለመኖር ማሕጸን “እንጀራን” የመሰለ ግዙፍ ኑባሬ ያዋልዳሉ እንደማለት ነው፡፡ ከጤፍ አብራክ እንጀራ የመክፈሉን ጉዳይ፣ እናቶቹ በሆዳቸው ከያዙት ጽንስ መወለድ ጋራ አቆራኝቶ ማየት ይቻላል፤ ያ ጽንስ አንድም በነባርና በአዳዲስ እሴቶች ትብብር ይሸመናል ያልነው “ኢትዮጵያዊነት” (pan-Ethiopianism) ነው፡፡ የእንጀራው አናት ወጥቶ በጋሻ ቅርጽ መስፈኑ ደግሞ የልደቱ መፈጸም ማረጋገጫ ትእምርት ነው፡፡ ጋሻ የአርበኝነትና የነጻነት ትእምርት፤ ጤፍ ደግሞ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት ማደርያ ነው ካልን፣ በጋሻ መልክ የተከሰተው እንጀራ የዚህ ማረጋገጫ ሰንደቁ (the symbol of national imaginary) ይሆናል፡፡ አንድም በጋሻ ቅርጽ አናታቸውን የከበበው እንጀራ በሰማዕትነት እንዳገኙት የብርሃን አክሊል (halo or nimbus) ሊቆጠር ይችላል፡፡ እንዲህ ያለው ሐቲት ለኪነቱ በ“በብሉየ መዋዕልና” ደንብ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን አጥልቆ የሚተክልበትን ረቂቅ ዐውድ ይሰጠዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን አንጀራን መመገብ የጀመሩበትን ጊዜ የሚያመለክት እርግጠኛ መረጃ የለም፡፡ ነገር ግን የእንጀራን መነሻ የሚጠቁሙ፣ ዘመኑን እስከ ቅድመ ክርስቶስ እስከ 100 ዓ.ዓ.
የሚያደርሱ የቃል ተረኮች እንዳሉ ስትዋርትና አስናቀ ይናገራሉ (1962: 127)[13]፡፡ በእነዚህ ተረኮች ወስጥ እንጀራ ኢትዮጵያውያን በተቸገሩ ወቅት ከልእለ ፍጥረት ህላዌ የተሰጠ በረከት ተደርጎ ነው የሚቀርበው፡፡ (በበቀለ ኪነት ውስጥ ያንን ሚና ወደ ሚታዊ ህልውናነት የተሸጋገሩት እናቶች ወስደውታል):: ቀደም አድርገን የጠቀስነው የታደሠ ጥናት እንደሚያመላክተን (2017፣ 50) ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ 70 ከመቶ ያህሉ ጤፍን በእንጀራ መልክ ተመጋቢ ነው፡፡ ይህ ቁጥር የጤፍ እንጀራን ለብሔራዊ ምግብነት የሚያበቃው ይመስለኛል፡፡
ጋኖቹን[14] አንክቶ፣ ባፍጢሙ እደፋው ጋሻ ላይ ተቀምጦ ስብርባሪ ገሎች እየሞቀ በምቾት የሚመሰጠው ገልቱ በፈንታው ፍቺው የዚህ ተቃራኒ ነው የሚመስለው፡፡ በእኔ አረዳድ ትዕይንቱ የዘመናችን ክፉ አባዜ--አገር ለዘመናት ጸንታ የኖረችባቸውን የዕሤት ሥርዓቶች፣ የጋራ ታሪኮች፣ የወል ልቡናዎች የመቀናቀን አባዜ--በስላቅ የተነደፈበት ነው፡፡ ስላቁ የቤቱን ማገር እየመዘዘ በሚያነድድ፣ መሠረቱን እየቆረቆረ ቤቱን ራሱ ላይ በሚንድ ገልቱ ላይ ቢያርፍም፣ አገራዊ አደጋው የምር እና ቅርብ መሆኑን ትላልቅ ጋኖችን በማውደም አሳይቷል፡፡ አገር ጸናባቸው ያልናቸው ረቂቅ ዕሤቶች ወጣቱን በከበቡት ስብርባሪ ገሎች ገዝፈው ይታያሉ፡፡ “ጋን” ከአገረ ሰብእ ጥበብነቱ ባሻገር አገር አጽንተው ያቆዩትን ረቂቅ ዕሤቶች ለመወከል የሚያበቃ ሥነ ልሳናዊ እና ሥነ ፍቻዊ ባሕርይ አለው፡፡ በተለይም ቃሉ “ጋኖች” ተብሎ በብዙ ቁጥር ሲጠራ የፍቺው ስፋት ከማጀት እስከ አደባባይ ይዘልቃል፤ “ጋኖች፤ ትልልቆች ሰዎች ዋኖች ጨዎች ጎምቱዎች አባቶች ዐዛውንቶች፡፡ (ተረት)፤ ጋኖች ዐለቁና ምንቸቶች ጋን ኾኑ” (ደስታ ተክለ ወልድ፣ 280)፡፡ አንድም፣ ከማጀት እስከ ቤተ መንግሥት የተዘረጋ ፍቺ አለው፤ ከጠላ መጥመቂያ፣ ከጠጅ መጣያ ቁስነት እስከ ንጉሥ መጠሪያት የሚደርስ ፍቺ፤ የጃን ሆይ አቻ ሆኖ፣ “ጋን ሆይ ፤-ገናና ሆይ፤--ጃን ሆይ፡፡” (280) እያስባለ፡፡
እስካሁን ለማሳየት እንደሞከርኩት Gluten-free-dom “I” እና “II” በተወሳሰቡ ትእምርቶች እና በተራቀቁ እይታዊ ሜታፈሮች የተከየኑ ድንቅ ምስሎች ናቸው፡፡ በምስሎቹ መካከል የሚካሄደው ንጽጽር ከዚህም አልፎ ልሄድ ይችላል፡፡ እኛ ይህን በይደር ዘግተን ለመጣጥፉ እንደ ማሳረጊያ ወደሚያገለግሉ አንድ ሁለት ነጥቦች እንለፍ፡፡
IV
በትርኢቱ ውስጥ ከቀረቡት ሥራዎች ብዙዎቹ --ከፀሐይ እና ጎጆ (ከባህል እና ተፈጥሮ ) መስተጋብር ከተቀሰቀሱ የሰርክ ደፋ ቀናዎች (“አሁንና ቅድም” I፣ II፣ III)፣ የዘወትር ስሜቶች (“አዙረኝ አዛዙረኝ”) አንስቶ፤ ረቂቆቹ የወል ዕሤቶች፣ የጋራ ልቡናዎች እስከተከተቡባቸው ምስሎች (“ጓዳና ግድግዳ”፣ Gluten-free-dom “I” እና “II”) ድረስ ከጤፍ እና ከጋሻ ትእምርታዊ ተራክቦ የተገኙ ናቸው፡፡ እርግጥ ነው እንዲህ ካለው የትርኢት ጠቅላይ ፈለግ የሚሸሹ ጥቂት ሥራዎች አይጠፉም፡፡ ለዚህ ደግሞ፣ “የገደል ማሚቶ”፣ “ቆሜ ተቀምጬ” እና “አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” አብነት ይሆናሉ፡፡ “የገደል ማሚቶ” ለኀልዮ እምብዛም ያልተጨነቀ፣ ምናልባትም የሄደ ድምጽ ተመልሶ የሚመጣበት የቅርጾች ጨዋታ ነው፡፡ በ“አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” ውስጥ የጤፍና የጋሻን የተናጠልም ይሁን የወል ህልውና በገሀድ ፈልገን ስለማናገኝ ሥራው ከትርኢቱ አጠቃላይ መንፈስ ያፈነገጠ ይመስላል፡፡ ይሔ ግምት ግን ኪነቱን ከቀሪዎቹ ሥራዎች ጋራ አናብበን መተርጎም ስንጀምር በቀላሉ የሚፈርስ ነው፡፡ እንዲህ፣ እንደ “ጤፍና ነጻነት” ባለ አንድ ወጥ ርእስ በተሰጠው ከፍ ያለ ትርኢት ውስጥ ሥፍራ ያገኙ፣ በተቀራራቢ የጊዜ ክበብ ውስጥ የተከየኑ ሥራዎች በአመዛኙ ተነጥሎ ከሚከናወን ዝግ ምልከታ ይልቅ ለአጎራባች (co-textual) እና ለዐውዳዊ (contextual) ምርምር ይጋብዛሉ፡፡ ይህንን አጠቃላይ የነገረ ፍካሬ መርህ ከግምት ካስገባን፣ ከያኒው በምስሉ መግለጫ ላይ ባቀረበው ፍቺ ብቻ ረግተን የምንቆም አይመስለኝም፡፡ ይልቁንም በአንድምታ ተጨማሪ ትርጉም ለማከል እንጋበዛለን፡፡ በእኔ እምነት በትርኢቱ ውስጥ በአካል ጭምር የተጎራበቱት Gluten-free-dom “I” እና “አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” ከጤፍ እና ጋሻ መጉደል ባሻገር በገሎቻቸው ተሳስበው በመንፈስ ይሰምራሉ፤ በጭብጥ ይከታተላሉ፡፡ በትርጓሜም እንደሚከተለው ይተጋገዛሉ፡፡
በጥንታዊው የሒሳብ ማሰላሰያ፣ በአባከስ አምሳያ የተበጀው በአራት ማዕዘን የብረት ፍሬም የታጠረ ምስል፣ ብረቱ ላይ ሻጥ ሻጥ ተደርገው አግድም የተዘረጉ ወልጋዳ የእንጨት ዘንጎች፣ በዘንጎቹ ላይ የሚንሸራሸሩ በቅርጽ
ሠዓሊና ቀራፂ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን
(ሂላሪያ ተስፋዬ እና ዕዝራ እጅጉ ተወዳጅ ሚድያ)
#ፕሮፌሰር በቀለመኮንን ለተወዳጅ ሚድያ የቅርብ ወዳጅና ቤተሰብ ነው። የምንሠራውን የስነዳ ፕሮጀክት በሙሉ ልብና መንፈስ የሚደግፍ ቀና ምሁር ነው። ታናሾቹን ለማገዝ በቀዳሚነት የሚሰለፍ ኩራት ያልፈጠረበት ታላቅ ወንድም እንደማለት ነው። ከ4 ዓመት አስቀድም "መዝገበ አእምሮ" ቅጽ አንድ ሲዘጋጅ ከጀርባ እና ከጎን ሆኖ ሲረዳን ነበር። የኃይሉ ልመንህን ታሪክ ፕሮፌሰር በቀለ አስታውሶ ታሪኩን ባይነግረን ኖሮ ኃይሉ ልመንህን አናገኘውም። ፕሮፌሰር በቀለ ሌሎችም ስሙን ከአክብሮት ጋር የሚያነሱት የሥነጥበብ ሰው ነው።
#ተወዳጅ ሚድያ እስከዛሬ የ432 ባለሙያዎችን ታሪክ በመፅሐፍ፣ በዲጂታል ሚድያ እና በድምፅ ሲሰንድ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንንም እንዲካተት አድርጓል። እስከዛሬ በሚዲያ እና ኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሠሩትን በምንችለው አቅም ታሪካቸው ዘመን እንዲሻገር ያደረግን ሲሆን የስነዳ ተግባሩም ተጠናክሮ ቀጥሏል። በቀጣይ እያዘጋጀነው ባለነው ዕትም ከ20 ዘርፎች የተውጣጡ ታላላቆችን በማሰባሰብ ላይ እንገኛለን ። ከእነዚህ ታላላቆች ውስጥ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን አንዱ ነው። የሕይወት ታሪኩንም ብዙ ካልታዩ የልጅነት ምስሎቹ ጋር አንድ ላይ በማድረግ ታሪኩን አጋርቶናል። ዕዝራ እጅጉ እና ሂላሪያ ተስፋዬም ታሪኩን እንደሚከተለው ሰንደውታል።በነገራችን ላይ በዚህ የሕይወት ታሪክ መጣጥፍ ውስጥ ተባባሪ ፕሮፌሰር ቴዎድርስ ገብሬ "በቀለን በብሔራዊ ትእምርት ፍለጋ ውስጥ" ብሎ የጻፈው ረዘም ያለ ምሁራዊ ትንተና አቅርበናል። የፕሮፌሰር በቀለ መምህር ወርቁ ጎሹ የሰጡትንም ምስክርነት አካተናል። መልካም ንባብ።
#የሰባተኛ ክፍል ተማሪ እያለ የስዕል ዝንባሌውን እንዲከተል እንዲሁም የስዕል ትምህርትን እንዲማር ያመለከቱትን መምህሩን በአንደበቱ ቃላት ይስላቸዋል። እኚህ መምህሩን፥ “ሊከተሉት የሚገባ ሰው” ሲል ይገልጻቸዋል። ምንአልባት ከበርካታ ዓመታት በኋላ እርሱ ራሱም እንዲያ ያለ ‘ሊከተሉት የሚገባ’ የጥበብ ሰው ሊሆን እንደሚችል አልገመተ ይሆናል።
#ፍላጎቱ ከእኩዮቹ የተለየ፣ ‘ተርታ’ ለሆነ ነገር መሻት የሌለው፣ በለጋ እድሜው ሳይቀር ነገሮችን እንደሆኑ ማየትና መሥራትን የማይመርጥ፣ አዲስ ነገር መፍጠርን አልያም የነበረውን በአዲስ መልክ መቃኘት ይቀናው የነበረ ተማሪ ነው። ስሙን ሳይቀር በስዕል ይጽፍ እንደነበር ይናገራል። በስጋው ላይ ያሠለጠናት ነፍሱ፥ ሰዓሊ የመሆን ግቡን ለማሳካት ይችል ዘንድ ‘የሰው ልጅ መሠረታዊ ነገሮችን’ አሻግሮ እንዲያይ ጉልበት ሰጥታዋለች። ይህ ጉልበትና ጽናት ነው፣ አሁን በሥነ ጥበብ ዘርፍ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ሙሉ ፕሮፌሰር የወለደው፥ ሠዓሊና ቀራፂ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን።
#ትውልድና እድገቱ ደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማ ነው። ጥር 6 1956 ዓ.ም። ትምህርትን አሃዱ ያለው በቆሎ ትምህርት አቡጊዳ ብሎ ፊደል ቆጥሮ፣ ዳዊት ደግሞ ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን አፄ ልብነ-ድንግል ወናግሰገድ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ እንዲሁም ኹለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በዚያው ደብረዘይት ልዕልት ተናኘወርቅ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል። የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተናውን የወሰደው ደግሞ በአዲስ አበባ ምኒልክ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው።
ከልጅነት እድሜው ጀምሮ የተገዛው ለስዕል ጥበብ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላ ለጥበብ ነበር። አዲስ ነገርን አልያም የነበረው በተሻለ መንገድ ሆኖ ማየትን ይመርጣል። በጥበብ ለሚሠራ ነገር ሁሉ ልዩ ፍቅር አለው። አሁን በአዋቂነትና በርቱዕ አንደበቱ ውበት እንደሚገዛው፥ ሰው የማይሠራውን መሥራት አልያም የተሠራውን ነገር ባልተሠራበት መንገድ መሥራት እንደሚወድድ ይናገራል። ይህን ቃሉን በልጅነት እድሜው ሲገልጥ ደግሞ፣ ስሙን ሳይቀር በስዕል ይጽፍ ነበር።
#የተካነበት፣ የሠለጠነበትና የታወቀበት የስዕል እና የቅርጻ ቅርጽ ጥበብ ይሁን እንጂ፥ ለጽሑፍ ጥበብ እና ውበትም ስሱ ነው። በልጅነትና ወጣትነት እድሜው በደብረዘይት ኪነት ውስጥ ቴአትር፣ ግጥም እንዲሁም መፈክር ጭምር በመጻፍ ይታወቃል። እንደውም ለተማሪዎች፣ ለሰፈሩ ወጣቶች የጻፋቸው የፍቅር ብሎም ልዩ ልዩ ደብዳቤዎችና ግጥሞች ጋር በተያያዘ በተለያየ አጋጣሚ የሚያነሳቸው ገጠመኞቹ ጥቂት አይደሉም። የእጅ ጽሑፉን ብቻ ሳይሆን የሚጽፋቸው ጽሑፎችና ግጥሞች ይዘት ጭምር ነበር ብዙዎችን የሚስበው።
#በኋላ 12ኛ ክፍል ፈተናን ከመውሰዱ አስቀድሞ፥ የስዕል ትምህርትን ለመማርና መምህሩ የዘራበትን ዘር ለማፍራት ዝንባሌውን ተከትሎ በዘመኑ አዲስ አበባ የሥነ ጥበብ ትምህርት ቤት (አሁን አለ ሥነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት) አቀና። ትምህርት ቤቱን ለመቀላቀል ደጅ ጥናትና ምልልስ እንዲሁም ተማጽኖ አስፈልጎታል። በኋላም ተሳክቶለት ተማሪ ለመሆን በሚጠበቀው ፈተና አንድ ሺህ ከሚጠጉ ተወዳዳሪዎች መካከል ከ14 አላፊ ተማሪዎች አንዱ መሆን ቻለ።በ1971።
#በአንድ ወቅት በአራዳ ኤፍኤም አዲስ አራዳ የራድዮ ፕሮግራም ላይ ባደረገው ቆይታ፣ የዚያን የአምስት ዓመት የትምህርት ዘመን ሲያነሳ፥ በትምህርት ቤቱ የነበረው የ5 ዓመት ቆይታ ቀላል እንዳልነበር ያስታውሳል። ሌሊት ማረፊያ የሚያጣባቸው ቀናት ብዙ ናቸው። ምንም እንኳ ለአምስት ዓመታት እያንዳንዱ ቀን የአንድ ዓመት ያህል ከባድ የነበር ቢሆንም፥ እርሱ ግን ‘ቀኑን ጎበዝ መሆን ነበር የሚፈልገው’። እናም ቀኑን ጎብዞ ከባዱን ጊዜ በብልሃትና በጽናት ተወጣው። ትምህርቱን አጠናቅቆም በማዕረግ ተመረቀና እዚያው የተማረበት ትምህርት ቤት መምህር ሆኖ ተቀጠረ።
በተማረበት ትምህርት ቤት በወጣት መምህርነት ለአራት ዓመታት አገልግሏል። ከዚያ በኋላ፥ ወደ ሩሲያ ለከፍተኛ ትምህርት ተላከና ሞስኮ ከተመ። ‘ግራጫ’ ይለዋል፣ የሩስያን ፀሐይ አልባ ቀዝቃዛና ደመናማ የጨላለመ የዘመኑን ድባብ። በዙሪያው ውበትን ማሰስ የለመደ ዐይኑ በሞስኮ ያንን ሊያገኝ አልቻለም። እንዲያም ሆኖ የደከመለት ትምህርቱን ለመፈጸም ጽናትን በመምረጥ፥ ከስድስት ዓመት የሞስኮ ቆይታ በኋላ የከፍተኛ የሥነጥበብ ትምህርቱን በሚገባ አጠናቅቆ ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ተመለሰ።
ከሩስያ መልስ አስቀድሞ በመምህርነት ያገለግልበት በነበረው ሥነ -ጥበብ ትምህርት ቤት የማስተማር እድል አገኘ። በዚያም በመጀመሪያ በሥነ ጥበብ ታሪክ ከዚያም በንድፍ ጥናት መምህር ሆኖ ቆይቷል። በመምህርነት ብቻም አይደለ፥ በጊዜው ‘አርት ስኩል’ ይባል የነበረውን ይህን ትምህርት ቤት፣ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋምነት ለማሳደግ ከ1990ዎቹ ጀምሮ ለዓመታት በዘለቀውና በተደረገው እልህ አስጨራሽ ትግል ውስጥ ከፊት ሆነው ሲያስተባብሩ ከነበሩት መካከል ሆኗል። በመጨረሻም ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ በተሰጠ የጥናት ውሳኔ ሥነ ጥበብ ትምህርት ቤቱ ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተዛውሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሲሆን ትልቁን ድርሻ ከተወጡት ጥቂት ግለሰቦች መካከል ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን ተጠቃሽ ነው።
ትምህርት ቤቱ የዩኒቨርሲቲው አንድ አካል ክፍል ከሆነ በኋላ የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሠርቷል። በዚያም ወቅት የትምህርት ቤቱን ነባር ስርዓት የከፍተኛ ትምህርት ስርአት ቅርፅ ለማስያዝ በብርቱ ለፍቷል፣ አሳክቷልም። በ2009 ዓ.ም ገደማ የሥነጥበባት ኮሌጅ ሲመሠረት በድጋሚ የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር ሆኖ ከማገልገሉ ባሻገር፥ ትምህርት ቤቱ መጠሪያው ወደ አለ የሥነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የተቀየረው የኮሌጁ ዲን ሆኖ ባገለገለበት ዘመን ነበር። ከዚያም ባሻገር አዲስና ተጨማሪ የፊልም ትምህርት ክፍል እንዲቋቋም ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ትምህርት ክፍሉ እውን እንዲሆን አስችሏል። ከዚህም ባሻገር በማስተማርና በማማከር በርካታ ተማሪዎችን ያፈራ ብርቱ ባለሙያ ነው።
#ፕሮፌሰር በቀለ በብሉይ ወይም ክላሲክ አካዳሚ ትምህርቱን ጠንቅቆ የተማረ ይሁን እንጂ በዘመነኛ የሥነ ጥበብ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ከሚጠቀሱ ባለሙያዎች አንዱ ነው። አዳዲስ ሙከራዎችና አሰሳዎችን በድፍረት ግን በኃላፊነት በማከናወን ሁሌም ፈር ቀዳጅና አዲስ መንገድ የሚያሳይ ከልቡ የፈጠራ ሰው ስለመሆኑም ብዙዎች ይመሰክራሉ፥ ከዚያም በላይ ሥራዎቹ ምስክሮቹ ናቸው።
#ፕሮፌሰር በቀለ የመጀመሪያ የሥዕል ኤግዚቢሽኑን ያቀረበው ከሀገር ውጭ ፊንላንድ፥ ‘ኮ’ፕዮ’ የሚባል ዩኒቨርሲቲ (Kuopio - በአሁኑ ምሥራቅ ፊንላንድ ዩኒቨርሲቲ) ነበር። ይህም በሞስኮ የሥነጥበባት የመጨረሻ ዓመት ተማሪ እያለ ሲሆን፣ ለዕይታ ያቀረባቸው ሥራዎቹም የተለያዩ አስቀድሞ በትምህርት ቤት ቆይታው ያዘጋጃቸው ናቸው።
ከዚያ በኋላ ለቁጥር በርካታ፣ ለዓይነት ብዙ፣ ለዐይን ውብና አስደማሚ የሆኑ ሥራዎችን ያለማቋረጠ ለበርካታ ዓመታት ሲያቀርብ ቆይቷል። ከስዕል ኤግዚቢሽን እስከ አደባባይ ሐውልቶችና ዓለም አቀፍ መድረኮች፥ በቀለ መኮንን የሚለው ስም እንግዳ ሆኖ አያውቅም።
#በ1996 ዓ.ም ያቀረበው ‘እንቆቅልሽ’ የተሰኘ የ‘ኢንስታሌሽን ጥበብ’ ትርዒቱ ዘይቤያዊ (Methaphorical) ትርጉም የያዘና አሁንም ድረስ አነጋጋሪ ሆኖ የቆየ ሥራ አንዱ ተጠቃሽ ነው። በ2000 ዓ.ም ‘እድልና ምርጫ’ የሚል ‘ክሪቲካል’ ትርዒቱን አቅርቦ ተመልካቹን አስደምሟል። በ2010 ዓ.ም ‘ባሩድና ብርጉድ’ ሲል የሰየመው አነጋጋሪና አወያይ ኤግዚቢሽኑ፥ ተመልካቹ ስለ ሥነጥበብ ያለውን አመለካከት ደጋግሞ እንዲፈትሽ ያስገደደ ነበር።
በ2016 ዓ.ም በኢትዮጵያውያን የሕይወት ዘይቤ ላይ ትልቅ ጥያቄ አንስቶ ያወያየውንና እስከ አሁንም የሚያወያየውን “ግሉተን ፍሪ-ደም” ወይም ‘ጤፍና ነፃነት’ የተሰኘውን ልዩ ትርዒት አቅርቦ የሥነ ጥበብ ተመልካቾችን ማስደነቁና ማነጋገሩን ቀጠለበት።
ከ25 ዓመታት በላይ እነዚህን የፈጠራ ሥራዎቹን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በተለያዩ መድረኮች ሲያሳይ ቆይቷል። በአፍሪካ፣ በአውሮፓ እና በአሜሪካ፣ በተለያዩ ሙዚየሞች ሥራዎቹን አቅርቧል፣ ሐሳብና ዕይታውን አስደምጧል። ሀገሩን አልፎም አኅጉሩን አፍሪካን በዓለም መድረክ በዘርፉ በኩራት እንዲቆሙም ምክንያት ሆኗል።
#በቅርብ ማለትም ባለፈው 2017 ዓ.ም፥ በኢጣሊያ ቱሪን ከተማ ሮያል ፓላስ ሙዚየም ተጋብዞ ‘ዘ ስሞኪንግ ቴብል’ ወይም ‘የሚጤሰው ጠረጴዛ’ የተሰኘ ፀረ ቅኝ ግዛት ይዘት ያለው ዘመነኛ የሥነ ጥበብ ሥራ በመፍጠር ለዕይታ አቅርቧል። ይህም ከፍተኛ እድናቆትን ያስገኘለት ብሎም ሐሳቡን ያስደመጠበት አውድ መሆን ችሏል።
#መሥራት እንጂ ይህን ሠራሁ ብሎ መናገርን የማያዘወትረው ፕሮፌሰር በቀለ፣ እንዲህ ካሉ አውደ ርዕዮች ባሻገር በቀራጺነቱ የተጠበበባቸው ሥራዎችም እጅግ በርካታ ናቸው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሠራቸውን በማማከር የተሳተፈባቸውን ብቻ ለመጥቀስ፥ በሙሉ ነሃስ የተሠራው የቀዳማይ ኃይለሥላሴ ኪነ ሀውልትን ጨምሮ፥ አብርኆት የሕዝብ ቤተመጻሕፍት ደጃፍ የሚገኘው ኪነ ሀውልት (ከነሐስ ቀልጦ የተሠራው ሕፃን)፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ያሠራው ሕንጻ ጋር የሚገኘው የባንኩን ዓላማና ርዕይ የሚያሳየው ግዙፍ ኪነ ሀውልት (ሀብት ካለ በሰማይ መንገድ አለ) እጅግ ጥቂቶቹ ናቸው።
ታድያ ለእነዚህና ለበርካታ ሥራዎቹ ሽልማቶችና እውቅናዎች ተበርክተዉለታል። ከእነዚያም መካከል በ1990 ዓ.ም የቺካጎ አርቲስቶች ዓለም አቀፍ ሽልማትን ያሸነፈ ብቸኛው አፍሪካዊ የስነ ጥበብ ባለሙያ መሆን ችሏል። እ.ኤ.አ. በ2006 በአሜሪካ ኒው-ዮርክ ውስጥ የIIE ፕሮግራም የሆነውን የ’Scholar Rescue Fund’ ሲቀበል የመጀመሪያው የሥነ ጥበብ ሰው ነበር። በዚያው ዓመት በባልቲሞር ሜሪላንድ ውስጥ በተጋባዥ ሠዓሊነት በበሜሪላንድ የአርት ኮሌጅ (MICA-Maryland institute college of Art) ለስምንት ወራት ቆይታ አድርጓል።
#ፕሮፌሰር በቀለ የኢትዮጵያ ሚሌኒየም ዓርማ ነዳፊ ሲሆን በመላ ሀገሪቱ በርካታ ኪነ ሀውልቶችን ነድፏል፣ አቅዷል፣ አማክሯል፣ መርቷል፣ ሠርቷል። በርካታ የመጻሕፍት ሽፋኖችንና የውስጥ ምስሎችን አዘጋጅቷል። በሀገር እና በዓለም አቀፍ የሥነጥበብ እና የሥነ ሕንፃ የውድድር መድረኮች ላይ በከፍተኛ ዳኝነት አገልግሏል። ከስነጥበቡ ማኅበረሰብ ውስጥ ደግሞ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ መደበኛ አባል ነው።
#ከዚህም በላይ ከእለት እለት የማስተማር ተግባሩ ጎን ለጎን በቅርቡ በተባበሩት መንግሥታት ፕሮጀክት ስር ነባሩ የአፍሪካ አዳራሽና የሥነ ጥበብ ሥራዎቹ እድሳት ውስጥ ባለሞያ፣ አማካሪና ተቆጣጣሪ በመሆን የተሳካ ሙያዊ ተልዕኮ ፈፅሟል። በአሁኑ ወቅትም በአለ ሥነጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት የቅድመ እና ድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ፕሮፌሰር ሲሆን፣ የዘመናዊ ሥነጥበብ ሙዚየም ገብረ ክርስቶስ ማዕከልንም በመምራት ላይ ይገኛል።
#ኅዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም የአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ የአክብሮትና የምስጋና ፕሮግራም አድርገዉለታል። ተማሪዎቹ ያንን ያደረጉት ፕሮፌሰር በቀለ በጀርመን ሀገር ፍራንክፈርት ከተማ ከሚገኝው የሥነጥበብ ዩንቨርሲቲ ጋር ከዓመታት በፊት የተጀመረውን የኹለትዮሽ ግንኙነት ዳር በማድረስ ላደረገው ታላቅ ተግባር እና የትምህርት ቤቱን ዳግም ትንሳኤ ለማሳካት ድልድይ በመሆኑ በማመስገን ነው።
አሁን ታድያ ይህና ያልተነገረ እጅግ በርካታ፣ ውብና አስደናቂ፣ ገና ያልተተነተነና ዐይን የሚሻ ሥራን የሠራ ሰው ነው፥ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የመጀመርያው ሙሉ ፕሮፌሰር ማዕረግ የተሰጠው።
#ምንአሉ ?
ይህንን ዜና በደስታ በማኅበራዊ ገጾቻቸው ካጋሪት መካከል ጋዜጠኛ #ቴዎድሮስተክለአረጋይ እንዲህ አለ፥
“አንዳንድ ጊዜ ማዕረግም፣ ሹመትም፣ ሽልማትም በተለያዩ ምክንያትና አጋጣሚዎች ያልተገባ ሰው እጅ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ። ይህ ይበልጡን በሀገራችን፣ በዓለምም ላይ ታይቷል። ለፕሮፌሰር በቀለ መኮንን ዓይነቱ ደግሞ እንዲህ ግጥም ያለ ፣ በልኩ የተሰፋ ይሆናል። የበቄ ፕሮፌሰርነት በሥነ ጥበብ ዘርፍ የተሰጠ የመጀመሪያው ቢሆንም የሰውየው የበቀለ ብቻ አይደለም። የመጭው ትውልድ ሁሉ ነው። የሥነ ጥበብነት ብቻ ሳይሆን የመቻል ፕሮፌሰርነት ነው። ከእንግዲህ ለአንድ ጥበበኛ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መሰጠት እንደሚችል ማሳያው፣ ማመላከቻው፣ ዳገቱ፣ ምልክቱ ነው፥ በቀለ መኮንን። ያሉትና የመጭዎቹ የሥነጥበብ ልሂቃን ተስፋና ብርታት ነው። እንደሚቻል ማሳያውም፣ ማረጋገጫውም ሆኗል። ይህ ለሥነጥበቡ ብቻም ሳይሆን ለሙዚቃውም ፣ ለትያትሩም ነው።”
የሙያ አጋሩንናበአለ የሥነ ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት ዲን #ሠዓሊአገኘሁአዳነ በበኩሉ፥ “የቤት ሰው፣ መምህር፣ ባልደረባ፣ የሞያ አባት… ከፍ ሲል፣ ሲከብር፣ ድካሙ ፍሬ ሲያፈራ ወዘተ. ልብ ይሞላል። በቀለ መኮንን ንጉሡ ባለግዙፍ ሰብዕና፣ ከሰው ፊት የሚያቀረቡት፣ የሚያኮራ፣ ጥንቅቅ ያለ ሙያተኛ፣ በጥረቱ ከጉልበተኞች ቅሚያና ንጥቂያ፣ ከሰሜነኛው ንፍቀ ክበብ (global north) በር ጠባቂነት በጥበብ ሾልኮ በርካታ ዓለማቀፍ መድረኮችን የተጋራ፣ ረብ ያለው ተግባር እየፈጸመ ያለ ሰው የሚሠራበት ተቋም አዲስ አበባ ዮኒቨርስቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቶታል። የአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የመጀመርያው ሙሉ ፕሮፌሰርሽፕ ማዕረግ መሆኑ ነው።” ሲል አያይዞ የእንኳን ደስ አለህ መልዕክቱን እስተላልፏል። #ደራሲእንዳለጌታከበደ (ፒኤችዲ) “አሁን የሆንከውን ለመሆን፣ አንተው ራስህ የጻፍከውን ግጥም ኖሮ መገኘትን ይጠይቃል።” ሲል መግቢያ አኑሮ ባጋራውና ራሱ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን በጻፈው ‘ቼ በለው’ በተሰኘው ግጥም እናብቃ፥
ቼ በለው!
ሕይወት ጎዳናው ገጹ ሲለወጥ
በጭነት ታክቶ ጀርባው ሲመለጥ
የእንቅፋት አጽሙ ቋጥኙ ሲገጥ
ሸክም ዘንቦበት ትቢያው ሲላቆጥ
ሲሆን ድጥ በድጥ
ሾህ ጭቃ ቅይጥ
ልብህ አይደንግጥ።
በምኞት ቅዥት በስጋት ርዶ
አይፍረስ ግንቡ ወኔህ ተንዶ
ከቆመው ቆመህ ከንፈር ከመምጠጥ
በተስፋ ፈረስ በልጓም ሸምጥጥ።
አያረጅ የለም አይለዋወጥ
ነገን ተማምነህ በመጓዝ ቁረጥ…
ከሩቅ አልመህ ቅርብ አትርመጥመጥ
ሰግተህ ከምትቆም ስትጋልብ ፍረጥ።
#መምህሩጋሽወርቁ ስለ ፕሮፌሰር በቀለ
መምህር ወርቁ ጎሹ የፕሮፌሰር በቀለ መኮንን አስተማሪ ሲሆኑ የ85 ዓመት ሰውም ናቸው። በቀለ ከወጣትነቱ አንስቶ ህልሙን ለማሳካት ታላቅ ጥረት የሚያደርግ ተማሪዬ ነው ሲሉ በኩራት ምስክርነት ይሰጣሉ። መምህር ወርቁ ጎሹ ቀራጺ በቀለ ከሰዎች ጋር የመግባባት ክህሎትን የታደለ የሚወደውን ሙያ እየሠራ ያለ ብቃት ያለው የሥነ ጥበብ ባለሙያ ነው ሲሉ ይገልጹታል።
ጋሽ ወርቁ 30 ዓመታት አስተምረዋል። በቀለን ሲገልጹት የሚደነቅና የሚከበር ይሉታል። በራሳቸው ጥረት ካደጉት ተርታ ይመድቡታል።
ጋሽ ወርቁ ወደ ኃላ መለስ ብለው የፕሮፌሰር በቀለን የትምህርት አቀባበል ሲያጤኑ የቀን የሌት ጥረት የሚያደርግና የልፋቱን ያገኘ በሚል ያስረዳሉ። ተሰጥዖም የሚታይ ነው ይላሉ።
ዛሬ ፕሮፌሰር መሆኑ ለአገር ትልቅ ኩራት መሆኑንም ነግረውናል።
" የበቀለ ፕሮፌሰር መሆን ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለአገር ኩራት ነው። እኔ እንደ አስተማሪው ይህን የምሥራች ስሰማ ደስታዬ ያይላል።እንኳን ደስ ያለህ ልለውም እወዳለሁ። "ሲሉ ለተወዳጅ ሚድያ ምስክርነት ሰጥተዋል።
በቀለ መኮንን፤
በብሔራዊ ትእምርት ፍለጋ ውስጥ
#በተባባሪፕሮፌሰርቴዎድሮስገብሬ
I
ከብረት እስከ ጨርቅ በደረሱ ትይዩ ተቃራኒዎች መካከል ሲያመላልሰን የከረመው በቀለ መኮንን፣ ጥቁር ጤፍ ፈጭቶ--ጥቁር ጤፍ አቡክቶ “በጋገራቸው” ኪነቶች አማካይነት ሊፈትነን “ጤፍና ነጻነት” የሚል ርእስ በሰጠው አዲስ ትርኢት ተገልጧል፡፡ “ጤፍ” እና “ነጻነት”? ጤፍ ገቢር ነው፡፡ ነጻነት ደግሞ ኀልዮ፡፡ ጤፍ ይሰፈራል፤ ይፈጫል፤ ይቦካል፤ ይጋገራል፡፡ ነጻነት ግን በኅሊና ይነደፋል፡፡ ጤፍ እና ነጻነት በነገረ ፍጥረታቸው አይገናኙም፡፡ 'እናስ በምን ተጠየቅ ተዛምደው በአንድ ርእስ ውስጥ በ“እና” ተዳሩ?' የሚል ጠያቂ ከመጣ ምላሹን የሚያገኘው ከትርኢቱ ዐውድ ይሆናል፡፡
በቀለ በትርኢት መግለጫዎቹ በገሀድ እንደሚጠቁመን በአዳዲስ ሥራዎቹ ውስጥ ረቂቁ “ነጻነት” በግዙፉ ጋሻ ውስጥ አድሮ ተጨባጭ ሆኗል፡፡ በእርግጥ ጋሻ የሚመስሉ “እብጠቶች” በበቀለ ዕይታዊ መድበለ ቃላት ውስጥ የሰርክ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በቀደሙት ትርኢቶች ውስጥ ጋሻዎች አንድም ቅርጽ ከቅርጽ ተጋጭተው ለሚፈጥሩት “ግብታዊ” ፍቺ ሲባል ይመላለሳሉ፤ አንድም ደግሞ የማረሻን የገነነ ወንዴነት ማስከኛ ሆነው በሚዛን ጠባቂነት (as a feminine energy) ይመጣሉ፡፡ በ“ጤፍና ነጻነት” ነጻነት በጋሻ ውስጥ በማደሩ፣ ጋሻ ከቀደመ ግብሩ የተለየ አዲስና ቋሚ ሚናና ግብር ይዟል ማለት እንችላለን፡፡ አዲስ ግብር ለመያዙ ምስክሩ ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በትርኢቱ ውስጥ የሚገጥሙን ጋሻዎች በሙሉ በጤፍ ዱቄት የተገነቡ (የተለሰኑ) ናቸው፡፡ የጋሻዎቹ በጤፍ ዱቄት መገንባት አንድም፣ በትእምርቶቹ መካከል የባሕርይ መጋራት እንዲፈጠር፤ አንድም በኪነቱ ውስጥ ጥንድ ምናብ--ድርብ አስተማስሎ (double representation) እንዲከሰት ዕድል ሰጥቷል፡፡ የጉዳዮች በአንድ ወደተሸረቡ መንታ ትእምርትነት ማደግ ተመልካች ሐሳቡን የሚያሰላበትን፣ ትችቱን የሚያፍታታበትን ምቹ የመፈከሪያ ዐውድ እንዲያገኝ አስችሎታል፡፡
ጋሻ የነጻነት እና የአርበኝነት ማኅደር ነው፡፡ (ይህ ዓይነቱ የጋሻ ፍቺ በተገኘበት ባህል ውስጥ ጭምር ይታወቃል፡፡) ቆየት አድርጌ በስፋት እንደማሳየው ጤፍ በፈንታው የ“ኢትዮጵያ” እና “የኢትዮጵያዊነት” ብሔራዊ ትእምርት ነው፡፡ በዚህ ዐውድ የብሔራዊ ትእምርት ፋይዳ አንድም፣ በነጻነት፣ በአገር እና በብሔራዊ ምንትነት መካከል ያለውን ረቂት ተራክቦና ውስብስብ ተጻምሮ ተጨባጭ ማድረግ ነው፡፡ አንድም ደግሞ ተራክቦውን--ተጻምሮውን ጠብቆ ለማኖር ዜጎች በአርበኝነት መንፈስ የሚከፍሉትን የላብና የደም መስዋዕትነት ማመልከት ነው ማለት እንችላለን፡፡ (በ“Gluten-free-dom II” እንጀራ የጠመጠመ ጋሻ በአናታቸው የደፉ፣ በትኩስ የአመድ ደለል ላይ/ውስጥ የቆሙ ሰባት እናቶች እንዲህ ላለው አንድምታ አስረጂዎች ይሆኑናል፡፡)
II
ብሔራዊ ትእምርቶች የብሔራዊ ምንትነት ግላጼዎች (identity expressions) ናቸው፡፡ የምንትነቱ ሥሪት (identity construction) በተረኮቹና በትእምርቶቹ ጥራትና ጥንካሬ ላይ ይወሰናል፡፡ ግላጼዎቹ እና ሥሪቱ የሚተጋገዙ ብቻ ሳይሆን የሚተካኩ ጉዳዮች ጭምር ናቸው፡፡ ያንዱ መድከም ሌላውን ያጎድላል፡፡ ያንዱ መዛል ሌላውን ያፈርሳል፡፡ የብሔራዊ ትእምርት ቀረጻ ብሔራዊ-ጥበባዊ ተልእኮ ነው፡፡ የአንድ ሕዝብ ብሔራዊ ምንትነት በአንጻራዊነት ለዘመናት ጸንቶ ይዘልቅ ዘንድ ተረኮች (ቃላዊ፣ ዕይታዊ፣ ትውናዊ፣ ወዘተ. ተረኮች) እና ትእምርቶች በጥንቃቄ መመረጥና መቀናበር፣ በየጊዜው እየተመረመሩ መታረምና መከለስ ይኖርባቸዋል፡፡ ብሔራዊ ምንትነት በዐቢይነት የውክልና ጉዳይ ነው፡፡ በአንድ አገር ውስጥ እያሉ እንደሌሉ የተቆጠሩ ወገኖች፣ ቸል የተባሉ ሰብአዊ ዕሤቶች፤ አቅም ባገኙ፣ የኃይል ሚዛን በለወጡ ጊዜ በነባር ተረኮች እና ትእምርቶች የተሸመነውን ብሔራዊ ምንትነት እስከ መሻር፣ አፍርሶ እንደ አዲስ እስከመሥራት የሚያደርስ ጥያቄ ያነሳሉ፡፡ ይህ ሲከሰት የአገር ግንባታ ሂደት ይስተጓጎላል፤ ማኅበራዊ ውጥረት ይነግሣል፡፡ (የዛሬዋ ኢትዮጵያ ለዚህ ዓይነቱ እውነታ አብነታችን ናት፡፡) በመሆኑም ብሔራዊ ትእምርት ቢያንስ ቢያንስ ረጅም የታሪክ ዘመንን፣ ሰፊ መልክአ ምድርን እና ገሀድ የወጡ የማኅበረሰብ ክፍሎችን እና ዕሤቶችን ሊያካልል ይገባል፡፡ ብሔራዊ ትእምርት ከውክልናው ፈርጀ ብዙነት ባሻገር በኪነት ከፍታው እና በኀልዮ ጥራቱም ተለይቶ መታወቅ አለበት፡፡ ጥቅል በሆነ አነጋገር፣ ብሔራዊ ትእምርት ጥልቅ በሆነ ጊዜ ውስጥ፣ ጽኑእ በሆነ መሠረት ላይ የሚታነጽ በነባርና በአዳዲስ ዕሤቶች ትብብር የሚሸመን ዐውራ ምስል ነው፡፡
እንደ ኢትዮጵያ ላለ ኅብረ ባህላዊ አገር ብሔራዊ ትእምርት በትግግዝ የሚፈጸም ብሔራዊ--ኪናዊ ተልእኮ ነው፡፡ ብሔራዊ ትእምርት እርስ በርስ ሊናበቡና ሊከታተሉ በሚችሉ በግለሰብ፣ በቡድን፣ በትውልድ በሚፈጠሩ ገባር ምናቦች ትግግዝ በዘመናት ሂደት ምልዓት ላይ የሚደርስ ዐውራ ትእምርት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ኪናዊ ትግግዝ--የምናብ ተናባቢነትና የምስል ተከታታይነት--በተጨባጭ ለማሳየት “ጤፍና ነጻነት”ን በሁለት መንገዶች ማንጸር እንችላለን፡፡ ቀዳሚው መንገድ ይህንን ትርኢት ከበቀለ መኮንን ነባር ትርኢቶች ጋራ እያመሳከሩ መፈከር ሲሆን፤ ተከታዩ ደግሞ በየትኛውም የኪነት ዘርፍ ካሉ ዘመነኞቹ ጋራ--ለምሳሌ ከአዳም ረታ ጋራ--እያናበቡ ማስተሳሰር ነው፡፡ የበቀለ መኮንንን ዕይታዊ ጥበብ ከአዳም ረታ ቃላዊ ኪነት አናብቦ በብሔራዊ ትእምርትነት ለማስላት በቂ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለዛሬው ትርኢት የነፍስ ያህል የሆነውን ዐውራ መባያ[1]--ጤፍን በበቀለ የአከያየን ልማድ ውስጥ ከገነነው፣ ከማረሻ ጋራ አስተሳስሮ ለማሰብም እንዲሁ፡፡ ከምክንያቶቹ ውስጥ መሠረታዊዎቹ፡- አንደኛ፣ የዐውድ ተዛማጅነት፤ ሁለተኛ፣ የኀልዮ (የጭብጥ) ተከታታይነት፤ ሦስተኛ፣ የቅኝት ወይንም (የርእዮተ ዓለም) ተወራራሽነት፤ አራተኛ፣ የጊዜ ጥልቀት (የነገረ ፍጥረት ብሉይነት)፤ አምስተኛ፣ ሥነ ልሳናዊ ተዛማችነት ናቸው፡፡
“ማረሻ” የግብርና ማምረቻ መሣሪያ፣ “ጤፍ” ደግሞ የግብርና ምርት በመሆናቸው በተፈጥሮ የቅደም-ተከተል ዝምድና አላቸው፡፡ (ተፈጥሯዊው ቅደም ተከተል በጉዳዮቹ መካከል አለ ያልነውን የጭብጥ ተከታታይነት እና የትእምርት ተጋጋዥነት ተጨባጭ ያደርግልናል፡፡) የማምረቻ መሣሪያው (ማረሻ)፣ የአምራቹ (ገበሬ) እና የምርቱ (ጤፍ) ተፈጥሯዊ የተራክቦ ዐውድ ገጠር ነው፡፡ ጤፍ እና ማረሻ ከ85 ከመቶ በላይ ኢትዮጵያዊ ይኖርበታል የሚባለውን፤ ዳሩ ግን በአገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ተገቢ ሥፍራ የተነፈገውን ወገን በቀጥታ ይመለከታሉ፡፡ ከያኒው ለተገፉ፣ ሥፍራ ለተነፈጉ ብሔራዊ ጉዳዮች ማድላቱ የትእምርቶቹን ምርጫ ተገቢነት ከማረጋገጡ ባሻገር ቅኝቱን ርእዮተ ዓለማዊ ያደርገዋል፤ (“history from below” እንደሚባለው)፡፡ ገጠርን አትኩሮ፣ ነባር የግብርና መሣሪያንና ጥንታዊ ምርትን (ማረሻንና ጤፍን) ከዚያው ዐውድ መልምሎ በምናብ ማጥለቁ፣ በምስል ማበልጸጉ እና በኀልዮ ማራቀቁ ብዙኃኑን የሚወክል፣ ዘመናትን የሚዋጅ ጽኑእ ብሔራዊ ትእምርት ለመቅረጽ ዕድል የሚሰጥ ይመስለኛል፡፡
የጤፍ ነገረ ኪን እና ፖለቲካም (the poetics and politics of teff) በቅኝት ከዚህ የሚለይ አይመስለኝም፡፡ ጤፍ በመጠን በአነስተኛነቱ “ዝነኛ” ነው፡፡ ለምሳሌ፣ አንድ የስንዴ ቅንጣት በአማካይ ከአንድ መቶ ሃምሳ የጤፍ ቅንጣቶች ጋራ እኩል እንደሆነ ይገመታል፡፡ ይህ ደግሞ “ከትውልድ ሥፍራው” አልፎ በዓለም ካሉ የእኽል ዝርያዎች በሙሉ በመጠን ትንሹ ያደርገዋል፡፡ በደስታ ተክለ ወልድ መዝገበ ቃላት ይህ የእኽል ዘር በተከታዩ መንገድ ተበይኖ እንመለከታለን፤ “ጤፍ፤ የታናሽ እኽል ስም፤ የሣር ዐይነት ሙርዬ የሚመስል፡፡ (ተረት)፤ ሳይቸግር ጤፍ ብድር” (19962፡ 675)፡፡[2] በዓለም ምግብ ድርጅት ገጽ ላይ ሰፍሮ እንደምናነበው፣ ጤፍ ከኢትዮጵያ ውጪ ባሉ አገራት፣ ለምሳሌ በደቡብ አፍሪካ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ከከብቶች ቀለብነት ባለፈ የአፈር መሸርሸርንና የውሃ ብክነትን ለመቀነስ ታስቦ የሚለማ “ተራ ሣር” ነበር፡፡[3] ተወዳጅ ነው በሚባልባት እናት አገሩም ቢሆን በመጠን ማነሱን ታክከው የሚቀርቡ ንጽጽሮች አጓጉልነት አላጣቸውም፡፡ ለአብነት፣ “ከመጤፍ አልቆጠረኝም” እና “ሰው ጤፉ” የሚሉ አገላለጾች በደረጃ ማነስን በገሀድ ያውጃሉ፡፡
ጤፍ በጄኔቲካዊ አወቃቀሩ እጅግ የተወሳሰበ፣ በጾታ ቅንብሩ የተደባለቀ (ፈናፍንት)፣ በምግብ ይዘቱ የበለጸገ የእኽል ዓይነት እንደሆነ የአዝርእት ባለሙያዎች ያስረዳሉ (ሰይፉ 1997)[4]፡፡ ሰይፉ ከተማ በመስኩ ላይ የተካሄዱ ምርምሮችን በከለሱበት ጽሑፋቸው እንደሚያስረዱን፣ የጤፍን የትውልድ ቦታ በእርግጠኝነት መናገር ቢከብድም፣ ጄኔቲካዊ ብዝኃነቱን በማጤን ኢትዮጵያ እናት ምድሩ ልትሆን እንደምትችል መገመት አስቸጋሪ አይሆንም፤ “[T]he genetic diversity for teff exists nowhere in the world except in Ethiopia, indicates that tef originated and was domesticated in Ethiopia” (12)፡፡ ጤፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ ጥንታዊ ከሚባሉ ጥቂት የእኽል ዘሮች መካከል አንዱ ነው፡፡ በዚህ የእኽል ዘር ላይ ከተካሄዱ ምርምሮች መካከል ብዙዎቹ፣ Nicolai Vavilovን (1951)[5] መሠረት በማድረግ፣ ቅድመ ክርስቶስ ከ4000–1000 በኢትዮጵያ ውስጥ እንደበቀለና ተስፋፍቶ እንደለመደ ይገምታሉ፡፡ እንደ ጤፉ ሁሉ፣ “ኢትዮጵያዊው” ማረሻ፣ ከዕድሜው ጥንትነት ባለፈ ልደትና ዕድገቱም እዚሁ መሆኑን የሚያመላክቱ ምርምሮች አሉ፤ ለምሳሌ፣ Hubert Cochet ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች በማረሻ ለ2000 ዓመታት እንዳረሱ ይጠቁማል (2011፡ 31)፡፡[6]
በኢትዮጵያ ውስጥ ከሦስት ሺህ በላይ ዘመናትን ያስቆጠረው፣ ከአገሪቱ ሕዝብ መካከል 70 ከመቶው በእንጀራ መልክ ይመገበዋል ተብሎ የሚገመተው ጤፍ (ታደሠ 2017፡ 50) በሦስቱ ዐበይት የሥነ ልሳን ቡድኖች ተቀራራቢ ስያሜም አለው፡፡ በአማርኛ “ጤፍ”፣ በኦሮምኛ “tafi” በትግሪኛ “ጣፍ”፡፡ በቀለም ስርጭትም ረገድ ወተት ከመሰለ ነጭ (ማኛ) አንስቶ እስከ ጥቁር ድረስ የሚዘልቁ አራትና አምስት ቀለማትን ያቅፋል (አዳም በሁሉም ቀለሞች የሚጫወት ሲሆን የበቀለ ምርጫ ጥቁሩ ነው)፡፡ እንዲህ ያለው የባሕርይ ውስብስብነት፣ የጾታ መንታነት፣ ኅብረ ቀለማዊነት ጤፍን--በአዳም ረታ ጥበበ ቃላት እና በበቀለ ዕይታዊ ጥበብ--ውስጥ ለብሔራዊ ትእምርትነት የተመቸ መባያ አድርጎታል፡፡ “ማረሻ” በበኩሉ ኢትዮጵያውያን የወል ምንትነታቸውን ከሚቀርጹባቸው ብሉይ ዕሤቶች መካከል አንደኛው ነው፡፡ የወልነቱን በዐበይቱ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ውስጥ ባለው የስያሜ ተወራራሽነት መረዳቱ አያሰቸግርም (የአማርኛው “ማረሻ”-- በግእዝ “ማሕረስ”፣ በኦሮምኛ “maarashaa”፣ በትግርኛ “ማሕረሻ” የሚሉ አቻዎች አሉት)፡፡ ብሉይ ነው ስል አንድም፣ የዘፍጥረቱን ጥንታዊነት፤ አንድም፣ የጊዜ ጥልቀቱን ታክኮ የሚመሠረተውን ባህል ጽኑእነት ማመልከቴ ነው፡፡ በተፈጥሮው ቀጥ ያለው፣ የተሳለውና የሾለው ማረሻ፣ በበቀለ ትርኢቶች ውስጥ በከያኒው ፈቃድ፣ ፍላጎትና እጅ መዋቅሩ ተናግቶ፣ “ተፈጥሮው” ተዛብቶ ልክ እንደ ጤፍ ወደ ፈናፍንትነት ተቀይሯል፡፡ የበቀለ ማረሻዎች መዋቅር መናጋት የአድሏዊው የተባዕትነት ሥርዓት ፈርሶ በአዲስ ተምኔታዊ ሥርዓት የመተካቱ አምሳያ ነው፡፡ ከዚህ ሥርዓት ውስጥ ነው እንግዲህ ከያኒው አዳዲስና ነባር ዕሤቶች ተዳርተው የሚሰናኙበትን ብሔራዊ ትእምርት ለመፍጠር የሚታገለው፡፡[7]
ጤፍ እና ማረሻ ኢትዮጵያውያን ጥልቅ ከሆነ ጊዜ፣ የጋራ ታሪካቸውን፣ ርእዮታቸውንና ንጽረታቸውን የሚጠልቁባቸው፤ ሩቅ ከሚባል ትናንት የወል ልቡናቸውንና ምንትነታቸውን የሚያደሩባቸው “ቁሳዊ” ዕሤቶች ናቸው፡፡ ቤኔዲክት አንደርሰን፣ “It is the magic of nationalism to turn chance into destiny” (1983፡ 12)[8] እንዳለው ዕጣ ፈንታቸው ጭምር ተጠላልፎ የተሰናኘባቸው የወል ዕሤቶች፡፡ ማን ከዕጣው ማምለጥ ይቻለዋል? እንደሚታወቀው እንዲህ ያለ ዕሤት በጥልቅ ጊዜ እና በጽኑእ መሠረት ላይ የሚቆም አገር ለማነጽ ምቹ ዕድል ይፈጥራል፡፡ በእርግጥ አንድ ማኅበር በጽናት ይቆም ዘንድ ዕጣውን ከቋጠረበት ሩቅ ትናንት በተጨማሪ፣ በገነነ “የሕዝብ ማኅበራዊ ልቡና” ነገውን የሚዋጅበት የጋራ ስኬት እንደሚያስፈልገው አሌ አይባልም፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ስኬት ጤፍ እንግዳ አይመስለኝም፡፡ ትናንት፣ ጤፍን ለሰው ልጅ ምግብነት በማዋል ረገድ ኢትዮጵያ ከዓለም ብቸኛ አገር ነበረች፡፡ ዛሬ፣ በተለይ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ በሚኖሩ፣ እንጀራን መለያቸው ባደረጉ በ“ነባሬ ባዕድ”[9] (diaspora) ኢትዮጵያውያን በሚተዳደሩ ምግብ ቤቶች አማካይነት ዝናን ያተረፈው ይህ የእኽል ዘር የኢትዮጵያን ድንበር ተሻግሯል፡፡ በጣዕሙ፣ በምግብ ይዘቱና ለጤና ባለው ጠቀሜታ ከተመጋቢው እኩል በሥነ ምግብ ተመራማሪዎች ዘንድ ተወዳጅ የሆነው ጤፍ በትልልቆቹ የዓለም የመገናኛ ብዙኋን ሳይቀር (ለምሳሌ፣ በBBC, VoA, The Washington Post, The Guardian, The New York Times, ወዘተ.) “the next ‘super grain’ of the World” የሚል መወድስ ወርዶለታል፡፡ ይህንን ዝና ተከትሎ ሊመጣ የሚችለው ማኅበራዊ ከፍታ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ--(as a national branding) ብሔራዊ ክብርና ኩራትን የመፍጠር አቅም አለው፡፡ የጤፍ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው አንድም በመከባበር ላይ የተመሠረተ አንድነትን ለመፍጠር የሚያግዝ፤ አንድም በጎሣ፣ በሃይማኖት እና በቋንቋ ምክንያቶች የተፈረቀቀውን ብሔራዊ ልቡና (the national psyche) ለማከም የሚያስችል ዕድል እመስጠቱ ላይ ነው፡፡[10]
III
ትኩረታችንን ወደ ዛሬው ትርኢት እንመልስ፡፡ “ጤፍና ነጻነት”፡፡ ጤፍ የ“ኢትዮጵያ” እና “የኢትዮጵያዊነት” ብሔራዊ ትእምርት፤ ጋሻ በበኩሉ የነጻነት እና የአርበኝነት ማኅደር መሆኑን በመግቢያዬ አመልክቻለሁ፡፡ እንዲህ ያለው የጋሻ ትርጉም ህልው በሆነበት ባህል ውስጥ ጭምር ታውቆ የሚሠራበት ነው፡፡ በትርኢቱ ውስጥ ከቀረቡት ሥራዎች ብዙዎቹ ከጤፍ እና ከጋሻ ተራክቦ የተገኙ ናቸው፡፡ ይህ ማለት ግን ሁለቱ ጉዳዮች በሁሉም ትዕይንቶች ውስጥ እኩል ሥፍራ አላቸው ማለት አይደለም፤ በፍጹም፡፡ ጤፍ በሚናው ይልቃል፡፡ የጭብጥ ክትትል ከመፍጠር፣ የመተርጎሚያ ዐውድ ከመተለም ባለፍ ዝርው ህልውናም አለው፡፡ ጤፍ በቤት ውስጥ ቁስነት ተከስቷል፤ የግድግዳ ምርጊት ሆኖ ተገልጧል፤ ወዘተ፡፡ ጤፍ ታሪክ ነው፤ ምጣኔ ሀብት ነው፤ ፖለቲካ ነው፤ ርእዮተ ዓለም ነው፡፡ በጤፍ የሰው አካል ተገንብቷል፤ የሰው ገጽ ተነድፏል፡፡ ገጻተ ሰብኡ ከጤፍ መልኩንም ይዘቱንም ወርሰዋልና ወደ ጤፍነት ተለወጡ ማለትም እንችላለን፡፡ ከተጨባጭ ሁነቶችና ህልውናዎች ባለፈ ጤፍ ለልእለ አካላዊ ክስተቶች ማድሪያነት ውሎም እንመለከታለን፡፡ ለምሳሌ፣ “ጓዳና ግርግዳ” የሚል ርእስ በተሰጠው፣ በቀጫጭን ዘንጎችና በጥቁር ጤፍ ትግግዝ በተቀናበረ ግድግዳ ላይ (በጤፍ ቡኮ የተመረገ፣ ጋሻ ያዘለ ግድግዳ) ከያኒው ይሁነኝ ብሎ በተዋቸው ሽንትር ሽንቁሮች ውስጥ አሳልፈን የምናየው “የቤተ ክርስቲያን” ጨርቅ ልእለ ፍጥረት ህላዌ ከልደትና ሞት ጋራ የታተመበት ነው፡፡ በመሆኑም ጤፍ በትርኢቱ ውስጥ የነገረ ሰብእን ዕጣ የምናሰላበትን ስብርባሪ አፍታ ጭምር ይሰጠናል ማለት ነው፡፡
በትርኢቱ ውስጥ በጤፍ ከተገነቡ ምስሎች መካከል ገጸ ሰብእ[11] የተነደፈው በሁለት ተከታታይ ትዕይንቶች ውስጥ ብቻ ነው፤ በ“Gluten-free-dom I” እና በ“Gluten-free-dom II”፡፡ እነዚህ ትዕይንቶች “ተከታታይ” ብለን ብቻ የምናልፋቸው አይመስሉኝም፡፡ ይልቁንም እጅግ በተወሳሰበ ትእምርታዊነትና በተራቀቀ ዘይቤ የተከየኑ፣ ለፈርጀ ብዙ ንጽጽርና ትርጓሜ የተመቹ ወደረኛ ቅርጾች ናቸው፡፡ ኋለኛውን መነሻ እናድርግ፡፡ ጀርባ ለጀርባ እንጂ ፊት ለፊት የማይተያዩ፣ ትከሻ ለትከሻ ገጥመው ክብ የሰሩ የሰባት ነፍሰ ጡሮች ትዕይንት ነው፡፡ በዚህ ትዕይንት ውስጥ ሴቶቹ ክብነቱን ጠብቆ በጠባቡ በሚዞራቸው ቡላ ቀለም ያለው የአመድ ደለል ላይ ቆመዋል፡፡ ደለሉን ተከትሎ በክቡ የሰፈነው ነጭ አመድ ከሸማ የተሠራ ምንጣፍ፣ በዙሪያው የተኮለኮለው የከሰል ሰልፈኛ ደግሞ ጥቁር ጥለት ይመስላሉ፡፡ በሆዳቸው ፍሬ የያዙ ሰባት ሴቶች የተደራረቡ እጆቻቸውን ሐፍረታቸው ላይ ጣል እንዳደረጉ፣ እንጀራ የለበሰ ጋሻ አናታቸው ላይ እንደደፉ፣ በአክብሮት ይሁን በፍርሐት አልያም በሐፍረት አቀርቅረዋል፡፡
ሁለተኛው ትዕይንት የአንድ ሰው “ገድል” ነው፡፡ ይህንን ገድል እኔ “ገልና ገልቱ” ብዬ እጠራዋለሁ፡፡ (“ገል” የጋን ስባሪ፤ “ገልቱ” ያልሠለጠነ፣ በድንቁርና የተደፈነ፡፡) ዙሪያውን በተሰባበሩ ሸክላዎች የተከበበ፣ ከምድር ከፍ ብሎ የታነጸ፣ ባለ ስድስት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ጡብ ገዝፎ ይታያል፡፡ ሙቀት ፍለጋ እጆቹን ወደ ፊት የዘረጋው ሰው እጡቡ አናት ላይ ባፍጢሙ እደፋው የአባቶቹ ጋሻ ላይ “ተመቻችቶ” ተቀምጦ “የደቀቁ የሸክላ ገሎችን በተመስጦ ይሞቃል”፡፡ ሁለቱ ትይዕንቶች የመከታተል ብቻ ሳይሆን እርስ በእርስ የመተረጓጎም ባሕርይም አላቸው፡፡ ይህንን ለማጤን እላይ በገለጻዎቹ ውስጥ የሰፈሩትን ወደረኛ ድርጊቶችና ሁነቶች ማነጻጸሩ ብቻ በቂ ይመስለኛል፡፡
ሴቶቹ በገዛ ፈቃዳቸው ፋታ ለማይሰጥ፣ ድካም ለበረታበት፣ ህመም ላለበት ኃላፊነት ራሳቸውን የሞሸሩ ይመስላሉ፡፡ አንድም የቁጥራቸው ሰባትነት የኃላፊነቱን ክብደት ያጸናል፡፡ ሰባት ቁጥር በትውፊት፣ በሃይማኖት፣ በኪነት፣ ወዘተ. ውስጥ ምልዐትን፣ ፍጹምነትን ለማመልከት ተመላልሶ የሚመጣ ነባር መባያ ነው፡፡ ፍጹምነቱና ሙሉነቱ የበረከትም የቅጣትም ሊሆን ቢችልም፡፡ አንድም ሴቶቹ የቆሙበት የአመድ ደለልም ሆነ አካላቸው ተገጣጥሞ የፈጠረው የቅርጽ ክብነት እላይ በቁጥር ጸና ያልነውን በድካምና በህመም የተሞላ ኃላፊነት ፍጹም ያደርገዋል፡፡ በክብነት ውስጥ መውጫ ቀዳዳ ይጠፋል፤ መነሻና መድረሻ ይታጣል፡፡ ለእረፍት የሚሆን ጥጋት አይሰጥም፡፡ በቀለ በምስሉ መግለጫ ላይ በገሀድ እንደሚጠቁመን ሰባቱ ሴቶች በዝርው ሰባቱን ቀናት ይወክላሉ፡፡ በዚህም ሰንበት ተገድፏል፤ የለመድነው የጊዜ መስፈሪያ ተሽሯል፡፡ ቀናቱ በሴቶቹ ድርጊት ተቃኝተው “ጊዜ” ከሰው ጋራ የሚለያይበት መስመር ደብዝዟል፡፡ መነሻ፣ ማጋመሻ፣ መዳረሻ የሚባሉ አንድም፣ የድርጊትና የሁነትና መሥፈሪያዎች፤ አንድም የጊዜ ዋቢዎች ሳስተዋል፡፡
እላይ በእንጥልጥል ወደተውነው ጉዳይ እንመለስ፤ “ገሎችን መሞቅ” ምን ማለት ነው? ከከያኒው ምስክርነት ባሻገር የወጣቱ የእጅ አዘረጋግ ሁኔታ በሙቀቱና በአካሉ መካከል በፈጠረው ሚዛን ሙቀትና ምቾት መኖራቸውን እንረዳለን፡፡ ግን እሳቱ ወዴት ነው? የሙቀቱ ምንጭስ ምንድ ነው? ለእነዚህ ጥያቄዎች በአንድምታ የምንገልጠው እውነታ ካልሆነ በቀር፤ በቀጥታ የምናገኘው መልስ ያለ አይመስለኝም፡፡ በባለ ስድስቱ ማዕዘን ጡብ ዙሪያ በሰፊው የፈሰሱት የገል ስብርባሪዎች በኢትዮጵያውን የቆየ ታሪክ ውስጥ ቋሚ ሥፍራ ያላቸው፣ በሸክላ የተሠሩ አገረ ሰብአዊ ዕደ ጥበባት ናቸው፤ በየዓይነቱ --የጀበና፣ የምጣድ፣ የድስት፣ የጋን፣ የጣባ፣ የዕጣን ማጨሻ፣ ወዘተ. ስብርባሪዎች፡፡ ስብርባሪዎቹን በቅርበት ላጤነ ሰው ዕደ ጥበባቱ በእርጅና ምክንያት ከሰርክ ግብራቸው የተገለሉ አይመስሉም፡፡ ይልቁንም ከነወዛቸው ከነጉልበታቸው ያሉ፣ ከግብራቸው በግድ ተነቅለው የደቀቁ ነው የሚመስሉት፡፡ በሌላ ቋንቋ ሙቀቱ የሚመነጨው ከገሎቹ ትኩስነት ነው፡፡ ትኩስነት፤ አንድም፣ ከእሳት ምድጃ የሰበሰቡትን ሙቀት ይዞ ማቆየት ነው፡፡ ገልቱው ዕደ ጥበባቱን ከተሰየሙበት ምድጃ ላይ ነቅሎ --ቡናና ወጡን ደፍቶ፣ ዳቦና እንጀራውን ገልብጦ--ጀበናውን፣ ድስቱን፣ ገበር ምጣዱን፣ ምጣዱን አንክቶ፣ እንካቹን ሜዳ ላይ ዘርቶ ትኩስነታቸውን እየሞቀ ነው፡፡ አንድም በዘይቤ ተራ እንናገርና ትኩስነት አፍላነት ነው፡፡ የአገልግሎት ዘመን አለመጋመስ፡፡ ከብርታትና ጥንካሬ ጋራ መሆን፡፡ ጠላውን ደፍቶ፣ እርጎውን ገልብጦ፣ ወዘተ. ያደቀቃቸው የሸክላ ውጤቶች፡፡
በዚሁ ተጠየቅ ከተጓዝን የሴቶቹን አቋቋም በመመርመር በሰባት ቁጥር እና በክብ ቅርጽ ትግግዝ ጸና ያልነውን ህመም በተጨባጭ መመልከት እንችላለን፡፡ የሴቶቹ ፋታ የለሽነት ድርጊቶቹንና ሁነቶቹን በሙሉ ወደማያቋርጥ ሂደትነት ለውጧቸዋል፡፡ ይህንን ለማጤን--በተለመደው አገላለጽ--እንጀራ የጠመጠመ ጋሻ ከሰፈነበት የራስ ጸጉራቸው፣ በአመድ ደለል እስከተደበቀው የእግር ጥፍራቸው ድረስ መመልከቱ በቂ ነው፡፡ አመዱ እና እንጀራው ትይዩ ናቸው፤ አንዱ ምርት ሌላው ግርድ፡፡ ከአናት እንጀራው በተመረተ ቁጥር ከስር አዲስ አመድ ይወድቃል፡፡ አዲስ አመድ --ትኩሣቱን ያልጨረሰ አመድ፤ ረመጥ፡፡ ይህ ማለት ሴቶቹ ረመጥ ላይ ቆመዋል እንደማለት ነው፡፡
ቀደም አድርጌ ለማሳየት እንደሞከርኩት ሴቶቹ እንዲህ ያለውን በድካምና በህመም የተሞላ ኃላፊነት በፈቃዳቸው መርጠው ተቀብለዋል፡፡ በማሕፀኗ ሽል የያዘችን እናት በረመጥ እስከመድበን የሚያደርስ መስዋዕትነት ምን የሚሉት ኃላፊነት፣ እንዴት ያለ ዓላማና ተልእኮ ነው? የራስን ሰብእና የሚያደቅቅ፣ ህልውናን የሚያመነምን፣ ሕይወትን የሚያሰልል ተግባር ውስጥ በፈቃድ መሳተፍ ራስን ለከፋ ጉዳት ማጨት ይመስላል፡፡ የፈቃድ ጉዳት (self-destruction)፣ ከፍ ሲልም የፈቃድ ሞት ከዳግም ልደት ጋር የሚዛመዱበት እንዲህ ያለው አቀራረብ ሚታዊ አመሳሰል ነው፡፡ ይህን ዓይነቱን አመሳሰል በሚቶሎጂ ውስጥ በብሉየ መዋዕልና[12] ደንብ ከተቀረጹ ምስሎች (archetypal imageries) ጋራ አቆራኝተን መመልከት እንችላለን፡፡ በሆዳቸው ፍሬ የያዙ ሴቶች ትከሻ ለትከሻ ገጥመው ክብ መሥራታቸው፣ በሠሩት ክበብ ውስጥ ረመጥ ላይ መቆማቸው፣ በአመድ ደለል መያዛቸው፣ እንጀራ “ማብቀላቸው” በአንድ ግዜ ኦሮቡረስን (በክብነት) እና ፊኒክስን (በረመጥነት-አመድነት) አቃልጠን እንድናስብ ያደርገናል፡፡ ራሷን አቃጥላ ከትቢያዋ ላይ ነፍስ የምትዘራው ፊኒክስ (Phoenix) እና በክብ ቅርጽ ከጅራቱ አንስቶ ሙሉ አካሉን በልቶ በአዲስ ህልውና የሚከሰተው አሮቡሮስ (Ouroborus) “ሁለንተናዊ” ሊባሉ የሚችሉ የህመምና ድኅነት፣ የሞትና ልደት ትእምርቶች ናቸው፡፡ ባዶ እግራቸውን ረመጥ ላይ የቆሙ ሰባት እናቶች በቸልታ የተጎዳውን ነባር ምንትነት፤ በሆዷቸው የያዟቸው ሰባት ፍሬዎች ደግሞ እንደ አዲስ ይወለድ ዘንድ የሚጠበቀውን ርእይና ርእዮት ይወክላሉ፡፡ ከዚህ ትዕይንት ዓላማዎች መካከል አንዱና ምናልባትም ቀዳሚው ለዘመናት ለኖረው፣ ዳሩ ግን ቸል ለተባለው የእናቶች ህመምና ድካም--የላቀ ብሔራዊ ተግባር--ዕውቅና መስጠት ነው፡፡ ይህ ዕውቅና ልዕለ ሰብአዊ እና ልዕለ ታሪካዊ እንጂ ተርታና ሰርካዊ አይደለም፡፡ በሌላ ቋንቋ፣ ከያኒው ከፍ ባለ የአከያየን ስልትና ርእዮት እናቶችን ጥልቅ ጊዜ ውስጥ በመትከል ወደ ሚታዊ ተጋዳሊነት ቀይሯቸዋል፡፡ በምላሹም ከዚያው ጥልቀት ውስጥ በጽናት የሚቆም ብሔራዊ ትእምርት እና ብሔራዊ ምንትነት ለማስገር ሞክሯል፡፡
አንድም እናቶች ካለመኖር ህጽን መኖርን አስገኝተዋልና ለዚያም ኪናዊ ውዳሴ እንደ ማውረድ ሊቆጠር ይችላል፡፡ በአንዳንዶች ግምት “ጤፍ” የሚለው መጠሪያ “ጠፋ” ከሚለው ቃል የተገኘ ነው፤ ጠፋ፣ መኖር አቆመ፣ ህልውናው አበቃ እንደማለት፡፡ በሌላ ቋንቋ የዚህ የእህል ዘር የመጠን አነስተኛነት ከመኖር ይልቅ ላለመኖር ይቀርባል እንደማለትም ነው፡፡ የ“ጤፍ” የፍቺ ነቅኡ “ጠፋ” የሚለው ግስ ከሆነ፣ አንድም፣ ጤፍ የምንለው፣ በጣት የምንቆነጥረው ደቃቅ ነገር በተጨባጭ አለመኖርን ያስተማስላል (the representation of absence, the visibility of invisibilty) እንደማለት ነው፡፡ አንድም ዐውራውን የብሔራዊ ሚቶች መሻት--የመነሻዎች ሁሉ መነሻ የመሆንን፣ ከምንምነት ነቅእ የመፍለቅን መሻት--ይጠልፍልናል፡፡ ጤፍ አለመኖርን ከወከለ ከጤፍ የምንጠልቀው “ኢትዮጵያዊነት” ከእመ አበ አልቦ እንደተገኘ (creation ex nihilo, that is, creation from nothing) ይቆጠራል፡፡ በዘይቤ ተራ እንነጋገርና የኢትዮጵያ ገበሬ “አለመኖርን” ይዘራል፡፡ እናቶች ደግሞ ከአለመኖር ማሕጸን “እንጀራን” የመሰለ ግዙፍ ኑባሬ ያዋልዳሉ እንደማለት ነው፡፡ ከጤፍ አብራክ እንጀራ የመክፈሉን ጉዳይ፣ እናቶቹ በሆዳቸው ከያዙት ጽንስ መወለድ ጋራ አቆራኝቶ ማየት ይቻላል፤ ያ ጽንስ አንድም በነባርና በአዳዲስ እሴቶች ትብብር ይሸመናል ያልነው “ኢትዮጵያዊነት” (pan-Ethiopianism) ነው፡፡ የእንጀራው አናት ወጥቶ በጋሻ ቅርጽ መስፈኑ ደግሞ የልደቱ መፈጸም ማረጋገጫ ትእምርት ነው፡፡ ጋሻ የአርበኝነትና የነጻነት ትእምርት፤ ጤፍ ደግሞ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት ማደርያ ነው ካልን፣ በጋሻ መልክ የተከሰተው እንጀራ የዚህ ማረጋገጫ ሰንደቁ (the symbol of national imaginary) ይሆናል፡፡ አንድም በጋሻ ቅርጽ አናታቸውን የከበበው እንጀራ በሰማዕትነት እንዳገኙት የብርሃን አክሊል (halo or nimbus) ሊቆጠር ይችላል፡፡ እንዲህ ያለው ሐቲት ለኪነቱ በ“በብሉየ መዋዕልና” ደንብ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን አጥልቆ የሚተክልበትን ረቂቅ ዐውድ ይሰጠዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን አንጀራን መመገብ የጀመሩበትን ጊዜ የሚያመለክት እርግጠኛ መረጃ የለም፡፡ ነገር ግን የእንጀራን መነሻ የሚጠቁሙ፣ ዘመኑን እስከ ቅድመ ክርስቶስ እስከ 100 ዓ.ዓ.
የሚያደርሱ የቃል ተረኮች እንዳሉ ስትዋርትና አስናቀ ይናገራሉ (1962: 127)[13]፡፡ በእነዚህ ተረኮች ወስጥ እንጀራ ኢትዮጵያውያን በተቸገሩ ወቅት ከልእለ ፍጥረት ህላዌ የተሰጠ በረከት ተደርጎ ነው የሚቀርበው፡፡ (በበቀለ ኪነት ውስጥ ያንን ሚና ወደ ሚታዊ ህልውናነት የተሸጋገሩት እናቶች ወስደውታል):: ቀደም አድርገን የጠቀስነው የታደሠ ጥናት እንደሚያመላክተን (2017፣ 50) ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ 70 ከመቶ ያህሉ ጤፍን በእንጀራ መልክ ተመጋቢ ነው፡፡ ይህ ቁጥር የጤፍ እንጀራን ለብሔራዊ ምግብነት የሚያበቃው ይመስለኛል፡፡
ጋኖቹን[14] አንክቶ፣ ባፍጢሙ እደፋው ጋሻ ላይ ተቀምጦ ስብርባሪ ገሎች እየሞቀ በምቾት የሚመሰጠው ገልቱ በፈንታው ፍቺው የዚህ ተቃራኒ ነው የሚመስለው፡፡ በእኔ አረዳድ ትዕይንቱ የዘመናችን ክፉ አባዜ--አገር ለዘመናት ጸንታ የኖረችባቸውን የዕሤት ሥርዓቶች፣ የጋራ ታሪኮች፣ የወል ልቡናዎች የመቀናቀን አባዜ--በስላቅ የተነደፈበት ነው፡፡ ስላቁ የቤቱን ማገር እየመዘዘ በሚያነድድ፣ መሠረቱን እየቆረቆረ ቤቱን ራሱ ላይ በሚንድ ገልቱ ላይ ቢያርፍም፣ አገራዊ አደጋው የምር እና ቅርብ መሆኑን ትላልቅ ጋኖችን በማውደም አሳይቷል፡፡ አገር ጸናባቸው ያልናቸው ረቂቅ ዕሤቶች ወጣቱን በከበቡት ስብርባሪ ገሎች ገዝፈው ይታያሉ፡፡ “ጋን” ከአገረ ሰብእ ጥበብነቱ ባሻገር አገር አጽንተው ያቆዩትን ረቂቅ ዕሤቶች ለመወከል የሚያበቃ ሥነ ልሳናዊ እና ሥነ ፍቻዊ ባሕርይ አለው፡፡ በተለይም ቃሉ “ጋኖች” ተብሎ በብዙ ቁጥር ሲጠራ የፍቺው ስፋት ከማጀት እስከ አደባባይ ይዘልቃል፤ “ጋኖች፤ ትልልቆች ሰዎች ዋኖች ጨዎች ጎምቱዎች አባቶች ዐዛውንቶች፡፡ (ተረት)፤ ጋኖች ዐለቁና ምንቸቶች ጋን ኾኑ” (ደስታ ተክለ ወልድ፣ 280)፡፡ አንድም፣ ከማጀት እስከ ቤተ መንግሥት የተዘረጋ ፍቺ አለው፤ ከጠላ መጥመቂያ፣ ከጠጅ መጣያ ቁስነት እስከ ንጉሥ መጠሪያት የሚደርስ ፍቺ፤ የጃን ሆይ አቻ ሆኖ፣ “ጋን ሆይ ፤-ገናና ሆይ፤--ጃን ሆይ፡፡” (280) እያስባለ፡፡
እስካሁን ለማሳየት እንደሞከርኩት Gluten-free-dom “I” እና “II” በተወሳሰቡ ትእምርቶች እና በተራቀቁ እይታዊ ሜታፈሮች የተከየኑ ድንቅ ምስሎች ናቸው፡፡ በምስሎቹ መካከል የሚካሄደው ንጽጽር ከዚህም አልፎ ልሄድ ይችላል፡፡ እኛ ይህን በይደር ዘግተን ለመጣጥፉ እንደ ማሳረጊያ ወደሚያገለግሉ አንድ ሁለት ነጥቦች እንለፍ፡፡
IV
በትርኢቱ ውስጥ ከቀረቡት ሥራዎች ብዙዎቹ --ከፀሐይ እና ጎጆ (ከባህል እና ተፈጥሮ ) መስተጋብር ከተቀሰቀሱ የሰርክ ደፋ ቀናዎች (“አሁንና ቅድም” I፣ II፣ III)፣ የዘወትር ስሜቶች (“አዙረኝ አዛዙረኝ”) አንስቶ፤ ረቂቆቹ የወል ዕሤቶች፣ የጋራ ልቡናዎች እስከተከተቡባቸው ምስሎች (“ጓዳና ግድግዳ”፣ Gluten-free-dom “I” እና “II”) ድረስ ከጤፍ እና ከጋሻ ትእምርታዊ ተራክቦ የተገኙ ናቸው፡፡ እርግጥ ነው እንዲህ ካለው የትርኢት ጠቅላይ ፈለግ የሚሸሹ ጥቂት ሥራዎች አይጠፉም፡፡ ለዚህ ደግሞ፣ “የገደል ማሚቶ”፣ “ቆሜ ተቀምጬ” እና “አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” አብነት ይሆናሉ፡፡ “የገደል ማሚቶ” ለኀልዮ እምብዛም ያልተጨነቀ፣ ምናልባትም የሄደ ድምጽ ተመልሶ የሚመጣበት የቅርጾች ጨዋታ ነው፡፡ በ“አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” ውስጥ የጤፍና የጋሻን የተናጠልም ይሁን የወል ህልውና በገሀድ ፈልገን ስለማናገኝ ሥራው ከትርኢቱ አጠቃላይ መንፈስ ያፈነገጠ ይመስላል፡፡ ይሔ ግምት ግን ኪነቱን ከቀሪዎቹ ሥራዎች ጋራ አናብበን መተርጎም ስንጀምር በቀላሉ የሚፈርስ ነው፡፡ እንዲህ፣ እንደ “ጤፍና ነጻነት” ባለ አንድ ወጥ ርእስ በተሰጠው ከፍ ያለ ትርኢት ውስጥ ሥፍራ ያገኙ፣ በተቀራራቢ የጊዜ ክበብ ውስጥ የተከየኑ ሥራዎች በአመዛኙ ተነጥሎ ከሚከናወን ዝግ ምልከታ ይልቅ ለአጎራባች (co-textual) እና ለዐውዳዊ (contextual) ምርምር ይጋብዛሉ፡፡ ይህንን አጠቃላይ የነገረ ፍካሬ መርህ ከግምት ካስገባን፣ ከያኒው በምስሉ መግለጫ ላይ ባቀረበው ፍቺ ብቻ ረግተን የምንቆም አይመስለኝም፡፡ ይልቁንም በአንድምታ ተጨማሪ ትርጉም ለማከል እንጋበዛለን፡፡ በእኔ እምነት በትርኢቱ ውስጥ በአካል ጭምር የተጎራበቱት Gluten-free-dom “I” እና “አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” ከጤፍ እና ጋሻ መጉደል ባሻገር በገሎቻቸው ተሳስበው በመንፈስ ይሰምራሉ፤ በጭብጥ ይከታተላሉ፡፡ በትርጓሜም እንደሚከተለው ይተጋገዛሉ፡፡
በጥንታዊው የሒሳብ ማሰላሰያ፣ በአባከስ አምሳያ የተበጀው በአራት ማዕዘን የብረት ፍሬም የታጠረ ምስል፣ ብረቱ ላይ ሻጥ ሻጥ ተደርገው አግድም የተዘረጉ ወልጋዳ የእንጨት ዘንጎች፣ በዘንጎቹ ላይ የሚንሸራሸሩ በቅርጽ
9 months ago
ሚስ ከምባታ 2018
ወ/ሪት ሜሮን ታዲዎስ ሆና ተመርጣለች
#ethiopia | የ2018 የሚስ ከምባታ አጓጓጊ ውድድር በስተመጨራሻ ሚስ 2018 ወ/ሪት ሜሮን ታዲዎስ ሆና አሸናፊ ሆናለች።
ተመራጯ ሚስ በቀጣይ የከምባታ ዞን አምባሳደር በመሆን የከምባታን ባህል ፣ የቱሪዝም ስፍራ ፣ እሴት እና ገፅታ ለኢትዮጵያና ለተቀሪው ዓለም የማስተዋወቅ ትልቅ ኃላፊነት ይጠብቃታል።
የዞኑ ባህል ታሪክና የተፈጥሮ ፀጋዎችን ለተቀረው ዓለም ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ቪዚት ከምባታ አስጎብኚ ድርጅት አስታወቀ ።
ድርጅቱ ከከምባታ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር የ2018 ዓ/ም 3ኛውን የመሳላ አዋርድ ውድድር በዱራሜ ከተማ አካሂዷል ።
ወይዘሪት ሜሮን ታደሰ የ3ኛው የሚስ መሳላ አዋርድ አሸናፊ ሆናለች ።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የከምባታ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሀላፊና የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ሀይሉ ሀደሮ እንደተናገሩት ቪዚት ከምባታ ድርጅት የዞኑን የሪዝሙን አቅም ለማሳደግ ለማሳደግና የዞኑን ፀጋዎች በማስተዋወቅ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ነው ብለዋል ።
የዞኑን የቱሪዝም አቅም ለማስተዋወቅ የኘስጎብኚ ቁጥር እንዲጨምር ይበረታታል ያሉት አቶ ሀይሉ ድርጅቱ የመሳላ አዋርድ የመሳላ ታላቁ ሩጫና ሌሎች ሁነቶችን በማዘጋጀት የሚሠራቸው ሥራር ለዞኑ ተጨማሪ የቱሪስት አቅም የሚሆኑ ናቸው ሲሉም አክለዋል ።
በመርሃግብሩ ላይ የቪዚት የከምባታ ድርጅት መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሳምሶን ቶማስ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር ድርጅቱ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ የዞኑን ህዝብ ባህል ታሪክ ቅርስና የተፈጥሮ መስህቦችን በማስተዋወቅ ረገድ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል ብለዋል ።
ድርጅቱ እየሠራ ባለው ሥራ አካባቢያቸውን የሚወዱ ስለአካባቢያቸው ለማወቅ የሚጓጉና ታታሪ ወጣቶች እየተፈጠሩ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሳምሶን ይህ ድርጅት እዚህ እንዲደርስ የድርሻቸውን እየተወጡ ያሉ አጋሮችን አመስግነዋል ።
ለከምባታ ብሔር ባህል ዕድገት ታሪካዊ የድርሻቸውን የተወጡና አሻራቸውን ያኖሩ የብሔሩ አባላት በያሉበት ማስታወስና ዕውቅና መስጠት ከድርጅቱ ዓላማዎች አንዱ መሆኑን የጠቆሙት ሥራአስኪያጁ ድርጅቱ ከዚህ በበለጠ በሥራው እንዲያድግ ሁሉም አካላት ከድርጅቱ ጎን ከመሆኑም ጠይቀዋል ።
ሶስተኛው የመሳላ አዋርድ ለመምረጥ በተደረገው ውድድር ወይዘሪት ሜሮን ታደሰ ማሸነፏን የገለፁት አቶ ሳምሶን የውድድሩ አሸናፊ ሚስ ሜሮንም ለሚቀጥለው አንድ ዓመት በአገር ውስጥና ለመላው ዓለም የከምባታን ባህል ታሪክና የተፈጥሮ ፀጋዎችን የማስተዋወቅ ሀላፊነት ተቀብላለች ብለዋል ።
የ2018 ዓ/ም 3ኛው የመሳላ አዋርድ አሽናፊዋ ሚስ ሜሮን ታደሰ በሰጠችው አስተያየት ድርጅቱ ለሰጣት ዕድል በማመስገን ባገኘችው ዕድል የብሔሩን ታሪክ ባህልና የተፈጥሮ መስህቦችን በማስተዋወቅ ሀላፊነቷን እንደሚትወጣ ተናግራለች።
በ3ኛው የመሳላ አዋርድ በተለያዩ ዘርፎች አሸናፊዎች የተሸለሙ ሲሆን በዚህም መሠረት :-
የ2018 የ777 ዳግም ደረጃ መንገድ ህብረተሠቡን በማስተባበርና በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ በዞኑ ህዝብ ላይ ለፈጠሩት ህዝባዊ አንድነት የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ
የ2018 ምርጥ መስህብ አጆራ መንትያ ፏፏቴ
የ2018 አርኤል በጎ አድራጎት ማህበር
የ2018 ተጽዕኖ ፈጣሪ ማህበራዊ ሚዲያ ሄኖክ ታደሰ
የ2018 የህይወት ዘመን አገልግሎት ዶክተር ፍቅሩ ገለሶ
የ2018 አለምአቀፍ አስጎብኚ ሴና ቱር
የ2018 በጤና ዘርፍ ዶክተር ዳኛቸው ዮሐንስ
የ2018 ለከምባታ ልማት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ዶክተር ግዛቸው ከበደ
የ2018 ማህበራዊ ሚዳዲያን ለበጎ ዓላማ ይድነቃቸው ያሬድ እና ቢኒያም ዓለሙ
የ2018 ምርጥ ዶክመንተሪ ረታ ዓለሙ
የ2018 የከምባታ የባህል ሙዚቃ ዘርፍ አሸናፊ አርቲስት ዙሪያሽወርቅ አበራ
የ2018 በወንዶች የሙዚቃ ዘርፍ ድምጻዊ ከተማ ገብረመድህን
የ2018 ባህላዊ ምግብ አዘገጃጀት ትሁት አየለ
የ2018 በዶክተር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል ልዩ ተሸላሚ ለመጣው ለውጥ የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ደረበ ዮሐንስ
የ2018 ልዩ ተሸላሚ ታላቅ መሪ ዘርፍ መቶ አለቃ ጴጥሮስ ገብሬ
የ2018 ልየ ተሸላሚ በደቡብ አፍሪካ የከምባታ ልማት ማህበር
የ2018 ሞዴል አርሶ አደር በአካባቢው ላመጣው የሥራ ባህል ለውጥ ልዩ ተሸላሚ ወጣት አብነት ዴላሞ
የ2018 በዞኑ ልማት ላይ ላበረከቱት አበርክቶ ልዩ ተሸላሚ የተከበሩ ወይዘሮ ማርታ ልውጂ
የ2018 የሥራ ፈጠራና የልማት ተሳትፎ አርበኝነት ልዩ ተሸላሚ አቶ አበበ አበሞ ሆነዋል ።
በመርሃ ግብሩ ላይ የከምባታ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሀላፊና የዋና አስተዳዳሪውን ተወካይ አቶ ሀይሉ ሀደሮና የከምባታ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳዊት ሀንዲኖን ጨምሮ ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎችና ዓለም አገራት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ወ/ሪት ሜሮን ታዲዎስ ሆና ተመርጣለች
#ethiopia | የ2018 የሚስ ከምባታ አጓጓጊ ውድድር በስተመጨራሻ ሚስ 2018 ወ/ሪት ሜሮን ታዲዎስ ሆና አሸናፊ ሆናለች።
ተመራጯ ሚስ በቀጣይ የከምባታ ዞን አምባሳደር በመሆን የከምባታን ባህል ፣ የቱሪዝም ስፍራ ፣ እሴት እና ገፅታ ለኢትዮጵያና ለተቀሪው ዓለም የማስተዋወቅ ትልቅ ኃላፊነት ይጠብቃታል።
የዞኑ ባህል ታሪክና የተፈጥሮ ፀጋዎችን ለተቀረው ዓለም ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ቪዚት ከምባታ አስጎብኚ ድርጅት አስታወቀ ።
ድርጅቱ ከከምባታ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር የ2018 ዓ/ም 3ኛውን የመሳላ አዋርድ ውድድር በዱራሜ ከተማ አካሂዷል ።
ወይዘሪት ሜሮን ታደሰ የ3ኛው የሚስ መሳላ አዋርድ አሸናፊ ሆናለች ።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የከምባታ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሀላፊና የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ሀይሉ ሀደሮ እንደተናገሩት ቪዚት ከምባታ ድርጅት የዞኑን የሪዝሙን አቅም ለማሳደግ ለማሳደግና የዞኑን ፀጋዎች በማስተዋወቅ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ነው ብለዋል ።
የዞኑን የቱሪዝም አቅም ለማስተዋወቅ የኘስጎብኚ ቁጥር እንዲጨምር ይበረታታል ያሉት አቶ ሀይሉ ድርጅቱ የመሳላ አዋርድ የመሳላ ታላቁ ሩጫና ሌሎች ሁነቶችን በማዘጋጀት የሚሠራቸው ሥራር ለዞኑ ተጨማሪ የቱሪስት አቅም የሚሆኑ ናቸው ሲሉም አክለዋል ።
በመርሃግብሩ ላይ የቪዚት የከምባታ ድርጅት መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሳምሶን ቶማስ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር ድርጅቱ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ የዞኑን ህዝብ ባህል ታሪክ ቅርስና የተፈጥሮ መስህቦችን በማስተዋወቅ ረገድ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል ብለዋል ።
ድርጅቱ እየሠራ ባለው ሥራ አካባቢያቸውን የሚወዱ ስለአካባቢያቸው ለማወቅ የሚጓጉና ታታሪ ወጣቶች እየተፈጠሩ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሳምሶን ይህ ድርጅት እዚህ እንዲደርስ የድርሻቸውን እየተወጡ ያሉ አጋሮችን አመስግነዋል ።
ለከምባታ ብሔር ባህል ዕድገት ታሪካዊ የድርሻቸውን የተወጡና አሻራቸውን ያኖሩ የብሔሩ አባላት በያሉበት ማስታወስና ዕውቅና መስጠት ከድርጅቱ ዓላማዎች አንዱ መሆኑን የጠቆሙት ሥራአስኪያጁ ድርጅቱ ከዚህ በበለጠ በሥራው እንዲያድግ ሁሉም አካላት ከድርጅቱ ጎን ከመሆኑም ጠይቀዋል ።
ሶስተኛው የመሳላ አዋርድ ለመምረጥ በተደረገው ውድድር ወይዘሪት ሜሮን ታደሰ ማሸነፏን የገለፁት አቶ ሳምሶን የውድድሩ አሸናፊ ሚስ ሜሮንም ለሚቀጥለው አንድ ዓመት በአገር ውስጥና ለመላው ዓለም የከምባታን ባህል ታሪክና የተፈጥሮ ፀጋዎችን የማስተዋወቅ ሀላፊነት ተቀብላለች ብለዋል ።
የ2018 ዓ/ም 3ኛው የመሳላ አዋርድ አሽናፊዋ ሚስ ሜሮን ታደሰ በሰጠችው አስተያየት ድርጅቱ ለሰጣት ዕድል በማመስገን ባገኘችው ዕድል የብሔሩን ታሪክ ባህልና የተፈጥሮ መስህቦችን በማስተዋወቅ ሀላፊነቷን እንደሚትወጣ ተናግራለች።
በ3ኛው የመሳላ አዋርድ በተለያዩ ዘርፎች አሸናፊዎች የተሸለሙ ሲሆን በዚህም መሠረት :-
የ2018 የ777 ዳግም ደረጃ መንገድ ህብረተሠቡን በማስተባበርና በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ በዞኑ ህዝብ ላይ ለፈጠሩት ህዝባዊ አንድነት የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ
የ2018 ምርጥ መስህብ አጆራ መንትያ ፏፏቴ
የ2018 አርኤል በጎ አድራጎት ማህበር
የ2018 ተጽዕኖ ፈጣሪ ማህበራዊ ሚዲያ ሄኖክ ታደሰ
የ2018 የህይወት ዘመን አገልግሎት ዶክተር ፍቅሩ ገለሶ
የ2018 አለምአቀፍ አስጎብኚ ሴና ቱር
የ2018 በጤና ዘርፍ ዶክተር ዳኛቸው ዮሐንስ
የ2018 ለከምባታ ልማት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ዶክተር ግዛቸው ከበደ
የ2018 ማህበራዊ ሚዳዲያን ለበጎ ዓላማ ይድነቃቸው ያሬድ እና ቢኒያም ዓለሙ
የ2018 ምርጥ ዶክመንተሪ ረታ ዓለሙ
የ2018 የከምባታ የባህል ሙዚቃ ዘርፍ አሸናፊ አርቲስት ዙሪያሽወርቅ አበራ
የ2018 በወንዶች የሙዚቃ ዘርፍ ድምጻዊ ከተማ ገብረመድህን
የ2018 ባህላዊ ምግብ አዘገጃጀት ትሁት አየለ
የ2018 በዶክተር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል ልዩ ተሸላሚ ለመጣው ለውጥ የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ደረበ ዮሐንስ
የ2018 ልዩ ተሸላሚ ታላቅ መሪ ዘርፍ መቶ አለቃ ጴጥሮስ ገብሬ
የ2018 ልየ ተሸላሚ በደቡብ አፍሪካ የከምባታ ልማት ማህበር
የ2018 ሞዴል አርሶ አደር በአካባቢው ላመጣው የሥራ ባህል ለውጥ ልዩ ተሸላሚ ወጣት አብነት ዴላሞ
የ2018 በዞኑ ልማት ላይ ላበረከቱት አበርክቶ ልዩ ተሸላሚ የተከበሩ ወይዘሮ ማርታ ልውጂ
የ2018 የሥራ ፈጠራና የልማት ተሳትፎ አርበኝነት ልዩ ተሸላሚ አቶ አበበ አበሞ ሆነዋል ።
በመርሃ ግብሩ ላይ የከምባታ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሀላፊና የዋና አስተዳዳሪውን ተወካይ አቶ ሀይሉ ሀደሮና የከምባታ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳዊት ሀንዲኖን ጨምሮ ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎችና ዓለም አገራት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
Sponsored by
Surafel
9 months ago
ግድብ እውን ሆኗል‼️
ይድረስ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያዊያን ሁሉ!
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በሰላም መጠናቀቁን ስናበስር በታላቅ ደስታ ነው።
ለዘመናት የቆየው የትውልድ ህልም፣ የኢትዮጵያ ህዝብ የቁርጥ ቀን ውሳኔና አንድነት ውጤት የሆነው ይህ ታላቅ ፕሮጀክት፣ አሁን በታሪክ ማህደር ውስጥ ስሙን አስፍሯል።
ይህ ግድብ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ምልክት ብቻ አይደለም። የብዙሃን ኢትዮጵያውያንን ላብ፣ ደም እና ህይወት ዋጋ የተቀመጠበት፣ በጋራ መቆም እና መቻል የሚለውን መርህ ያስመሰከረ የድል አድራጊነት ማሳያ ነው።
በቅርቡ ከሀገራችን ወዳጆች ጋር በመሆን በደማቅ ስነ-ስርዓት የሚመረቅ ሲሆን፣ የግድቡ ግንባታ ማሽነሪዎች ደግሞ ወደ አዲስ የአባይ ፕሮጀክት እየተጓዙ መሆኑን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ይህ የህዳሴው ዘመን የአርበኝነት ታሪክ፣ ለመጪው ትውልድ ትልቅ ትምህርት እና የኩራት ምንጭ ሆኖ የሚያገለግል ታሪካዊ ክስተት ነው።
Seledadotio
Seledadotio
ይድረስ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያዊያን ሁሉ!
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በሰላም መጠናቀቁን ስናበስር በታላቅ ደስታ ነው።
ለዘመናት የቆየው የትውልድ ህልም፣ የኢትዮጵያ ህዝብ የቁርጥ ቀን ውሳኔና አንድነት ውጤት የሆነው ይህ ታላቅ ፕሮጀክት፣ አሁን በታሪክ ማህደር ውስጥ ስሙን አስፍሯል።
ይህ ግድብ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ምልክት ብቻ አይደለም። የብዙሃን ኢትዮጵያውያንን ላብ፣ ደም እና ህይወት ዋጋ የተቀመጠበት፣ በጋራ መቆም እና መቻል የሚለውን መርህ ያስመሰከረ የድል አድራጊነት ማሳያ ነው።
በቅርቡ ከሀገራችን ወዳጆች ጋር በመሆን በደማቅ ስነ-ስርዓት የሚመረቅ ሲሆን፣ የግድቡ ግንባታ ማሽነሪዎች ደግሞ ወደ አዲስ የአባይ ፕሮጀክት እየተጓዙ መሆኑን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ይህ የህዳሴው ዘመን የአርበኝነት ታሪክ፣ ለመጪው ትውልድ ትልቅ ትምህርት እና የኩራት ምንጭ ሆኖ የሚያገለግል ታሪካዊ ክስተት ነው።
Seledadotio
Seledadotio
10 months ago
የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ታሪክ በኢንሳይክሎፔዲያ መልክ ሊዘጋጅ ነው
#ethiopia | የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ጋር በመተባበር የጀግኖች አርበኞችን ታሪክ በሳይንሳዊ መንገድ ለማጥናትና በኢንሳይክሎፔዲያ መልክ ለማዘጋጀት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ነሐሴ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ የተዋደቁ አርበኞች ታሪክ በትክክለኛና በተሟላ መንገድ ተደራጅቶ እንዲሰነድና ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ያለመ ነው።
የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ ስምምነቱ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖችን ታሪክ በጥናትና ምርምር በሳይንሳዊ ዘዴ በመምራት ፣ በማዘጋጀት እና በማሳተም ለትውልድ ማስተላለፍ ጠንካራ አገራዊ አንድነት ለመፍጠርና ቀጣዩ ትውልድ ለአገሩ በአርበኝነት እንዲቆም በእጅጉ ያግዛል ሲሉ የጥናቱን ጠቀሜታ አብራርተዋል፡፡
በፊርማው ሥነሥርዓት ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው ጥናቱ ጥራቱን ጠብቆ አንዲካሄድ ለማድረግ ዩኒቨርስቲው ተገቢውን ባለሙያ፣ ሃብትና አመራር እንደሚመድብ አስረድተዋል፡፡(AAU)
#ethiopia | የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ጋር በመተባበር የጀግኖች አርበኞችን ታሪክ በሳይንሳዊ መንገድ ለማጥናትና በኢንሳይክሎፔዲያ መልክ ለማዘጋጀት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ነሐሴ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ የተዋደቁ አርበኞች ታሪክ በትክክለኛና በተሟላ መንገድ ተደራጅቶ እንዲሰነድና ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ያለመ ነው።
የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ ስምምነቱ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖችን ታሪክ በጥናትና ምርምር በሳይንሳዊ ዘዴ በመምራት ፣ በማዘጋጀት እና በማሳተም ለትውልድ ማስተላለፍ ጠንካራ አገራዊ አንድነት ለመፍጠርና ቀጣዩ ትውልድ ለአገሩ በአርበኝነት እንዲቆም በእጅጉ ያግዛል ሲሉ የጥናቱን ጠቀሜታ አብራርተዋል፡፡
በፊርማው ሥነሥርዓት ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው ጥናቱ ጥራቱን ጠብቆ አንዲካሄድ ለማድረግ ዩኒቨርስቲው ተገቢውን ባለሙያ፣ ሃብትና አመራር እንደሚመድብ አስረድተዋል፡፡(AAU)
11 months ago
መኮንን ሃብተ ማርያም(መ/አ)
ሕይወትን በአንድ እጅ ~ [ ግለ ታሪክ ]
#ethiopia | በአየለ እሸቱ የተጻፈው በኢትዮጵያ አየር ኃይል ተጋድሎ ውስጥ የመ/አ መኮንን ሃብተማርያም ግለ ታሪክ ሐምሌ 12 ቀን 2017 ዓ.ም ቦሌ ብራስ በሚገኘው ዮድ አቢሲኒያ የባህል ማዕከል ከቀኑ 7:00 ሰዓት ይመረቃል።
***
ስለባለታሪኩ
መኮንን ምንም አይነት ፈተና ሳይሰብረውና ከዓላማው ሳያሰናከለው በአየር ኃይል በኋላም በሲቪል አቪየሽንና በኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በውጪም በትራንስፖርት ካናዳ ዐቢይ ግልጋሎትን ፈፅሟል። ለብዙ ሰው በሁለት እጅ እንኳ አስቸጋሪ የሆነውን ህይወት መኮንን ውጣ ውረዱን ቁብ ሳይለው በአንድ እጁ ብቻ ዘለቀበት፡፡ ባለቤቱ አጠገቡ ባልነበረችበት ወቅት ለአምስት ልጆቹ ምግብ አብስሎና ተንከባከቦ ትምህርት ቤት አመላልሶ ያለምንም ረዳት አሳደጋቸው።
ይህ የመ/አ መኮንን መጽሐፍ የእውነትን፣ የፅናትን፣ የአርበኝነትና ለመከራ ያልተንበረከከ ህይወትን አሸናፊነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው :: መኮንን በአንድ እጁ ብቻ የመራውን ህይወት በአግራሞት ዕለት በዕለት ስመለከተው ኖሬያለሁ። የፅናትና የስኬት ተምሳሌት በመሆኑ ለትውልድ አርዓያ ይሆን ዘንድ ታሪኩን በመጽሐፍ መልኩ እንዲያቀርብም ጎትጉቼዋለሁ። መኮንን ሁልጊዜም አድማጭነው:: ስለዚህም ይህንን ስጦታ ለትውልድ በማበርከቱ እጅግ ሊመሰገን ይገባል፡፡
ተስፋዬ አብዲ (አምባሳደር)
በአየር ኃይል፣ በመከላከያ ሚኒስቴርና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገለገሉ ዲፕሎማት
***
በህይወቴ ብዙ የማደንቃቸው ሰዎች አሉ፡፡ ግን መኮንን በዚህ ሁኔታ ኑሮውን አስተካክሎ ዛሬ የደረሰበትን ደረጃ ሳስብ ያስገርመኛልም፣ አደንቀዋለሁም። ማንም ሰው ይህንን ያደርጋል ብዬ በሃሳቤ ኖሮ አያውቅም። ያሳለፈውን ፈታኝ ጊዜ ሳየው ሊደረግ የማይቻል መስሎ ነበር የሚታየኝ። ያኔ አደጋ በደረሰበት ጊዜ ይህ ሰው አበቃለት፣ ህይወቱ ተበላሸ፣ እንግዲህ እንዴት ሊኖር ነው? ብዬ እንዳላዘንኩኝ ዛሬ ከብዙ ትግል በኋላ እዚህ መድረሱ እጅግ ያስደንቀኛል። ማንንም ሰው በዚህ ደረጃ አስቤም፣ አይቼም አላውቅም። መኮንን ትሁት፣ በሁሉም አንፃር የተሟላ ስብዕና ያለው ሰው ነው:: ያደረገው ትግልና የደረሰበት ደረጃ በቃላት ከሚነገረው በላይ ነው :: ታሪኩን በመጽሐፍም ብቻ ሳይሆን ፊልምም ሆኖ የሚታይ አስደናቂ ታሪክ እንደሆነ ይሰማኛል።
ውብሸት ተፈራ (ኮሎኔል)
አየር ኃይልና ሲቪል አቪየሽን ያገለገሉ
***
መኮንን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወጥነት ያለውና ዓለም አቀፋዊነቱን የጠበቀ የክንውን መመሪያና የፖሊሲ ማኑዋል እንዲኖረው ለማድረግና ያንንም ወደ መሬት ለማውረድ ከፍተኛ ተግባር ከማከናወኑም በላይ በሴፍቲ ጉዳይ አየር መንገዱን በቅርበት ዕለት በዕለት በመከታተል በተጨባጭ የታዩ ተግባሮችን አከናወኗል፡፡ አየር መንገዱ እያደገና እየሰፋ ሲሄድ ይበልጥ ጠንካራና ውጤታማ ሊሆን የቻለውም በዚያን ጊዜ የነበሩ፣በሳል ባለሙያዎች ለአየር መንገዱ አድጎት አስተማማኝ መሰረት በመጣላቸው ነው። ያ ቢሮ ጠንካራና ራሱን ችሎ በትኩረት የሚሠራ ከፍል እንዲሆን ማድረግ የተቻለው መኮንን ከመጣ በኋላ ነበር። እኔ ሁልጊዜም አብሬው ብሆንም፣ በሌሎች መደበኛ ተግባሮቼ የተነሳ አብዛኛውን ተግባር ያከናውን የነበረው እሱ ነበር፡፡ አዳዲስ ሃሳቦችን በማፍለቅና ወደፊት ተመልካች እቅዶችን በመዘርጋት የሴፍቲ ክፍሉ የሚጠበቅበትን ተግባር በአግባቡ እንዲወጣና ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ለማድረግ የነበረው ትጋት ሁልጊዜም ያስደንቀኝ ነበር። መኮንን ሰው መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ በጥልቀት እንድገነዘብ ያስቻለኝ፣ ተግባርን በትጋት የማከናወንን አስፈላጊነት የተማርኩበት ሰው ነው::
አስረስ አርኢያ (ካፒቴን)
ለበርካታ ዓመታት አየር መንገድን በካፒቴንነት ያገለገሉ
ሕይወትን በአንድ እጅ ~ [ ግለ ታሪክ ]
#ethiopia | በአየለ እሸቱ የተጻፈው በኢትዮጵያ አየር ኃይል ተጋድሎ ውስጥ የመ/አ መኮንን ሃብተማርያም ግለ ታሪክ ሐምሌ 12 ቀን 2017 ዓ.ም ቦሌ ብራስ በሚገኘው ዮድ አቢሲኒያ የባህል ማዕከል ከቀኑ 7:00 ሰዓት ይመረቃል።
***
ስለባለታሪኩ
መኮንን ምንም አይነት ፈተና ሳይሰብረውና ከዓላማው ሳያሰናከለው በአየር ኃይል በኋላም በሲቪል አቪየሽንና በኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በውጪም በትራንስፖርት ካናዳ ዐቢይ ግልጋሎትን ፈፅሟል። ለብዙ ሰው በሁለት እጅ እንኳ አስቸጋሪ የሆነውን ህይወት መኮንን ውጣ ውረዱን ቁብ ሳይለው በአንድ እጁ ብቻ ዘለቀበት፡፡ ባለቤቱ አጠገቡ ባልነበረችበት ወቅት ለአምስት ልጆቹ ምግብ አብስሎና ተንከባከቦ ትምህርት ቤት አመላልሶ ያለምንም ረዳት አሳደጋቸው።
ይህ የመ/አ መኮንን መጽሐፍ የእውነትን፣ የፅናትን፣ የአርበኝነትና ለመከራ ያልተንበረከከ ህይወትን አሸናፊነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው :: መኮንን በአንድ እጁ ብቻ የመራውን ህይወት በአግራሞት ዕለት በዕለት ስመለከተው ኖሬያለሁ። የፅናትና የስኬት ተምሳሌት በመሆኑ ለትውልድ አርዓያ ይሆን ዘንድ ታሪኩን በመጽሐፍ መልኩ እንዲያቀርብም ጎትጉቼዋለሁ። መኮንን ሁልጊዜም አድማጭነው:: ስለዚህም ይህንን ስጦታ ለትውልድ በማበርከቱ እጅግ ሊመሰገን ይገባል፡፡
ተስፋዬ አብዲ (አምባሳደር)
በአየር ኃይል፣ በመከላከያ ሚኒስቴርና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገለገሉ ዲፕሎማት
***
በህይወቴ ብዙ የማደንቃቸው ሰዎች አሉ፡፡ ግን መኮንን በዚህ ሁኔታ ኑሮውን አስተካክሎ ዛሬ የደረሰበትን ደረጃ ሳስብ ያስገርመኛልም፣ አደንቀዋለሁም። ማንም ሰው ይህንን ያደርጋል ብዬ በሃሳቤ ኖሮ አያውቅም። ያሳለፈውን ፈታኝ ጊዜ ሳየው ሊደረግ የማይቻል መስሎ ነበር የሚታየኝ። ያኔ አደጋ በደረሰበት ጊዜ ይህ ሰው አበቃለት፣ ህይወቱ ተበላሸ፣ እንግዲህ እንዴት ሊኖር ነው? ብዬ እንዳላዘንኩኝ ዛሬ ከብዙ ትግል በኋላ እዚህ መድረሱ እጅግ ያስደንቀኛል። ማንንም ሰው በዚህ ደረጃ አስቤም፣ አይቼም አላውቅም። መኮንን ትሁት፣ በሁሉም አንፃር የተሟላ ስብዕና ያለው ሰው ነው:: ያደረገው ትግልና የደረሰበት ደረጃ በቃላት ከሚነገረው በላይ ነው :: ታሪኩን በመጽሐፍም ብቻ ሳይሆን ፊልምም ሆኖ የሚታይ አስደናቂ ታሪክ እንደሆነ ይሰማኛል።
ውብሸት ተፈራ (ኮሎኔል)
አየር ኃይልና ሲቪል አቪየሽን ያገለገሉ
***
መኮንን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወጥነት ያለውና ዓለም አቀፋዊነቱን የጠበቀ የክንውን መመሪያና የፖሊሲ ማኑዋል እንዲኖረው ለማድረግና ያንንም ወደ መሬት ለማውረድ ከፍተኛ ተግባር ከማከናወኑም በላይ በሴፍቲ ጉዳይ አየር መንገዱን በቅርበት ዕለት በዕለት በመከታተል በተጨባጭ የታዩ ተግባሮችን አከናወኗል፡፡ አየር መንገዱ እያደገና እየሰፋ ሲሄድ ይበልጥ ጠንካራና ውጤታማ ሊሆን የቻለውም በዚያን ጊዜ የነበሩ፣በሳል ባለሙያዎች ለአየር መንገዱ አድጎት አስተማማኝ መሰረት በመጣላቸው ነው። ያ ቢሮ ጠንካራና ራሱን ችሎ በትኩረት የሚሠራ ከፍል እንዲሆን ማድረግ የተቻለው መኮንን ከመጣ በኋላ ነበር። እኔ ሁልጊዜም አብሬው ብሆንም፣ በሌሎች መደበኛ ተግባሮቼ የተነሳ አብዛኛውን ተግባር ያከናውን የነበረው እሱ ነበር፡፡ አዳዲስ ሃሳቦችን በማፍለቅና ወደፊት ተመልካች እቅዶችን በመዘርጋት የሴፍቲ ክፍሉ የሚጠበቅበትን ተግባር በአግባቡ እንዲወጣና ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ለማድረግ የነበረው ትጋት ሁልጊዜም ያስደንቀኝ ነበር። መኮንን ሰው መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ በጥልቀት እንድገነዘብ ያስቻለኝ፣ ተግባርን በትጋት የማከናወንን አስፈላጊነት የተማርኩበት ሰው ነው::
አስረስ አርኢያ (ካፒቴን)
ለበርካታ ዓመታት አየር መንገድን በካፒቴንነት ያገለገሉ
11 months ago
የኬንያ ፕሬዚዳንት በቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ ነው
#ethiopia | የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ናይሮቢ በሚገኘው ቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ እንደሆነ አሳወቁ።
ሩቶ ለቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ራሳቸው ወጪያቸውን እንደሚሸፍኑ ገልጸው የማንም ፈቃድ እንደማያስፈልጋቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
"ቤተክርስቲያን ለመገንባት የማንም ይሁንታ አያስፈልገኝም። ሰይጣንን ሊያበሳጨው ይችላል እናም የፈለገውን ማድረግ ይችላል" ሲሉ ሩቶ አርብ ዕለት ተናግረዋል።
የፕሬዚዳንቱ ንግግር በሳቸው አመራር የቤተ ክርስቲያንን እና የመንግሥት በጽኑ መጣመር ቀድሞውኑ የሚተቹት ኬንያውያንን አበሳጭቷል።
ቢቢሲ የኬንያ መንግሥትን አስተያየት እንዲሰጠው ጠይቋል።
ሩቶ ስቴት ሃውስ በተሰኘው ቤተ መንግሥታቸው በሰጡት አስተያየት "ሰይጣን" ብለው የጠሩት አካል ማን እንደሆነ ግልጽ ባይሆንም የቤተ ክርስቲያኑን ፕሮጀክት ከመቀጠል የሚያግዳቸው ምንም ነገር እንደሌለ ገልጸዋል።
"ይህንን ቤተ ክርስቲያን መገንባት የጀመርኩት ወደ ቤተ መንግሥት ስገባ አይደለም። እዚሁ በቆርቆሮ የተሰራ ቤተ ክርስቲያን አገኘሁ። ይህ ለቤተ መንግሥቱ የሚመጥን ይመስላችኋል?" ሲሉ አርብ ዕለት ከፖለቲከኞች ጋር በነበራቸው ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።
አርብ ዕለት ከኬንያ ታዋቂ ከሆኑት ጋዜጦች አንዱ የሆነው ዴይሊ ኔሽን 8 ሺህ ሰዎችን የሚይዝ ትልቅ ህንጻ የሚያሳይ ዲዛይን አትሟል።
ጋዜጣው፤ ይህ ፕሮጀክት መንግሥትና ሃይማኖት የተነጣጠለ ነው የሚለውን የኬንያ ሕገ መንግሥት የሚያከብር ነው ወይ? የሚል ጥያቄን አቅርቧል።
በርካታ ኬንያውያን በዋጋ ግሽበት እና በኑሮ ውድነት እየተፈተኑ ባለበት በዚህ ወቅት 9 ሚሊዮን ዶላር
እንደሚያስወጣ የተገመተው ይህ ቤተ ክርስቲያን ትችቶችን እያስተናገደ ነው።
ሩቶ የቤተክርስቲያኑን ወጪ ከኪሳቸው እከፍላለሁ ቢሉም በሕዝብ ንብረት ላይ ይህን ያህል ትልቅ መዋቅር የመገንባት አቅም አላቸው ወይ የሚል ጥያቄ አጭሯል።
የኬንያ ኢ-አማኒያን ማህበር የቤተ ክርስቲያኑን ግንባታ አስደንጋጭ እና ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ገልጾ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
"ይህ ድርጊት ጸረ ዲሞክራሲያዊ፤ እንዲሁም ፕሬዚዳንት ሩቶ ክርስቲያናዊ አርበኝነትን የማነሳሳት ተግባር አድርገን ነው የምንመለከተው። ኬንያ የክርስቲያኖች አገር ብቻ እንዳልሆነች ልናሳስባቸው እንፈልጋለን" ሲሉ የማህበሩ ኃላፊ ሐሪሰን ሙሚያ አጽንኦት ሰጥተዋል፥
ዊልያም ሩቶ የመጀመሪያው የኢቫንጀሊካል ክርስትና ተከታይ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ በአንዳንዶችም ዘንድ "የእየሱስ ምክትል" የሚል ቅጽል ስም አትርፈዋል።
ሩቶ በሥልጣን ላይ በቆዩባቸው ዓመታት ከመጽሃፍ ቅዱስ ጥቅሶች በመምዘዝ በአደባባይ ሲያለቅሱ ታይተዋል። ይህም ባህርያቸው የሳቸውን እምነት የማይከተሉ ኬንያውያንን ያገለለ ሆኖ ታይቷል።
ሩቶ ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት ከረን በሚገኘው መኖሪያቸው ውስጥ ቤተ ክርስቲያን አቁመው የተለያዩ ዕምነት ያላቸውን የሃይማኖት መሪዎችን ለማስተናገድ ይጠቀሙበት ነበር።
በኬንያ 85 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ የክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆን፣ 11 በመቶ ገደማ ሙስሊሞች እንዲሁም ሂንዱይዝም እና ባህላዊ እምነት ተከታዮች አሉ። #yeneta_tube
#ethiopia | የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ናይሮቢ በሚገኘው ቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ እንደሆነ አሳወቁ።
ሩቶ ለቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ራሳቸው ወጪያቸውን እንደሚሸፍኑ ገልጸው የማንም ፈቃድ እንደማያስፈልጋቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
"ቤተክርስቲያን ለመገንባት የማንም ይሁንታ አያስፈልገኝም። ሰይጣንን ሊያበሳጨው ይችላል እናም የፈለገውን ማድረግ ይችላል" ሲሉ ሩቶ አርብ ዕለት ተናግረዋል።
የፕሬዚዳንቱ ንግግር በሳቸው አመራር የቤተ ክርስቲያንን እና የመንግሥት በጽኑ መጣመር ቀድሞውኑ የሚተቹት ኬንያውያንን አበሳጭቷል።
ቢቢሲ የኬንያ መንግሥትን አስተያየት እንዲሰጠው ጠይቋል።
ሩቶ ስቴት ሃውስ በተሰኘው ቤተ መንግሥታቸው በሰጡት አስተያየት "ሰይጣን" ብለው የጠሩት አካል ማን እንደሆነ ግልጽ ባይሆንም የቤተ ክርስቲያኑን ፕሮጀክት ከመቀጠል የሚያግዳቸው ምንም ነገር እንደሌለ ገልጸዋል።
"ይህንን ቤተ ክርስቲያን መገንባት የጀመርኩት ወደ ቤተ መንግሥት ስገባ አይደለም። እዚሁ በቆርቆሮ የተሰራ ቤተ ክርስቲያን አገኘሁ። ይህ ለቤተ መንግሥቱ የሚመጥን ይመስላችኋል?" ሲሉ አርብ ዕለት ከፖለቲከኞች ጋር በነበራቸው ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።
አርብ ዕለት ከኬንያ ታዋቂ ከሆኑት ጋዜጦች አንዱ የሆነው ዴይሊ ኔሽን 8 ሺህ ሰዎችን የሚይዝ ትልቅ ህንጻ የሚያሳይ ዲዛይን አትሟል።
ጋዜጣው፤ ይህ ፕሮጀክት መንግሥትና ሃይማኖት የተነጣጠለ ነው የሚለውን የኬንያ ሕገ መንግሥት የሚያከብር ነው ወይ? የሚል ጥያቄን አቅርቧል።
በርካታ ኬንያውያን በዋጋ ግሽበት እና በኑሮ ውድነት እየተፈተኑ ባለበት በዚህ ወቅት 9 ሚሊዮን ዶላር
እንደሚያስወጣ የተገመተው ይህ ቤተ ክርስቲያን ትችቶችን እያስተናገደ ነው።
ሩቶ የቤተክርስቲያኑን ወጪ ከኪሳቸው እከፍላለሁ ቢሉም በሕዝብ ንብረት ላይ ይህን ያህል ትልቅ መዋቅር የመገንባት አቅም አላቸው ወይ የሚል ጥያቄ አጭሯል።
የኬንያ ኢ-አማኒያን ማህበር የቤተ ክርስቲያኑን ግንባታ አስደንጋጭ እና ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ገልጾ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
"ይህ ድርጊት ጸረ ዲሞክራሲያዊ፤ እንዲሁም ፕሬዚዳንት ሩቶ ክርስቲያናዊ አርበኝነትን የማነሳሳት ተግባር አድርገን ነው የምንመለከተው። ኬንያ የክርስቲያኖች አገር ብቻ እንዳልሆነች ልናሳስባቸው እንፈልጋለን" ሲሉ የማህበሩ ኃላፊ ሐሪሰን ሙሚያ አጽንኦት ሰጥተዋል፥
ዊልያም ሩቶ የመጀመሪያው የኢቫንጀሊካል ክርስትና ተከታይ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ በአንዳንዶችም ዘንድ "የእየሱስ ምክትል" የሚል ቅጽል ስም አትርፈዋል።
ሩቶ በሥልጣን ላይ በቆዩባቸው ዓመታት ከመጽሃፍ ቅዱስ ጥቅሶች በመምዘዝ በአደባባይ ሲያለቅሱ ታይተዋል። ይህም ባህርያቸው የሳቸውን እምነት የማይከተሉ ኬንያውያንን ያገለለ ሆኖ ታይቷል።
ሩቶ ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት ከረን በሚገኘው መኖሪያቸው ውስጥ ቤተ ክርስቲያን አቁመው የተለያዩ ዕምነት ያላቸውን የሃይማኖት መሪዎችን ለማስተናገድ ይጠቀሙበት ነበር።
በኬንያ 85 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ የክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆን፣ 11 በመቶ ገደማ ሙስሊሞች እንዲሁም ሂንዱይዝም እና ባህላዊ እምነት ተከታዮች አሉ። #yeneta_tube
11 months ago
የኬንያ ፕሬዚዳንት በቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ ነው
የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ናይሮቢ በሚገኘው ቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ እንደሆነ አሳወቁ።
ሩቶ ለቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ራሳቸው ወጪያቸውን እንደሚሸፍኑ ገልጸው የማንም ፈቃድ እንደማያስፈልጋቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
"ቤተክርስቲያን ለመገንባት የማንም ይሁንታ አያስፈልገኝም። ሰይጣንን ሊያበሳጨው ይችላል እናም የፈለገውን ማድረግ ይችላል" ሲሉ ሩቶ አርብ ዕለት ተናግረዋል።
የፕሬዚዳንቱ ንግግር በሳቸው አመራር የቤተ ክርስቲያንን እና የመንግሥት በጽኑ መጣመር ቀድሞውኑ የሚተቹት ኬንያውያንን አበሳጭቷል።
ቢቢሲ የኬንያ መንግሥትን አስተያየት እንዲሰጠው ጠይቋል።
ሩቶ ስቴት ሃውስ በተሰኘው ቤተ መንግሥታቸው በሰጡት አስተያየት "ሰይጣን" ብለው የጠሩት አካል ማን እንደሆነ ግልጽ ባይሆንም የቤተ ክርስቲያኑን ፕሮጀክት ከመቀጠል የሚያግዳቸው ምንም ነገር እንደሌለ ገልጸዋል።
"ይህንን ቤተ ክርስቲያን መገንባት የጀመርኩት ወደ ቤተ መንግሥት ስገባ አይደለም። እዚሁ በቆርቆሮ የተሰራ ቤተ ክርስቲያን አገኘሁ። ይህ ለቤተ መንግሥቱ የሚመጥን ይመስላችኋል?" ሲሉ አርብ ዕለት ከፖለቲከኞች ጋር በነበራቸው ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።
አርብ ዕለት ከኬንያ ታዋቂ ከሆኑት ጋዜጦች አንዱ የሆነው ዴይሊ ኔሽን 8 ሺህ ሰዎችን የሚይዝ ትልቅ ህንጻ የሚያሳይ ዲዛይን አትሟል።
ጋዜጣው፤ ይህ ፕሮጀክት መንግሥትና ሃይማኖት የተነጣጠለ ነው የሚለውን የኬንያ ሕገ መንግሥት የሚያከብር ነው ወይ? የሚል ጥያቄን አቅርቧል።
በርካታ ኬንያውያን በዋጋ ግሽበት እና በኑሮ ውድነት እየተፈተኑ ባለበት በዚህ ወቅት 9 ሚሊዮን ዶላር
እንደሚያስወጣ የተገመተው ይህ ቤተ ክርስቲያን ትችቶችን እያስተናገደ ነው።
ሩቶ የቤተክርስቲያኑን ወጪ ከኪሳቸው እከፍላለሁ ቢሉም በሕዝብ ንብረት ላይ ይህን ያህል ትልቅ መዋቅር የመገንባት አቅም አላቸው ወይ የሚል ጥያቄ አጭሯል።
የኬንያ ኢ-አማኒያን ማህበር የቤተ ክርስቲያኑን ግንባታ አስደንጋጭ እና ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ገልጾ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
"ይህ ድርጊት ጸረ ዲሞክራሲያዊ፤ እንዲሁም ፕሬዚዳንት ሩቶ ክርስቲያናዊ አርበኝነትን የማነሳሳት ተግባር አድርገን ነው የምንመለከተው። ኬንያ የክርስቲያኖች አገር ብቻ እንዳልሆነች ልናሳስባቸው እንፈልጋለን" ሲሉ የማህበሩ ኃላፊ ሐሪሰን ሙሚያ አጽንኦት ሰጥተዋል፥
ዊልያም ሩቶ የመጀመሪያው የኢቫንጀሊካል ክርስትና ተከታይ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ በአንዳንዶችም ዘንድ "የእየሱስ ምክትል" የሚል ቅጽል ስም አትርፈዋል።
ሩቶ በሥልጣን ላይ በቆዩባቸው ዓመታት ከመጽሃፍ ቅዱስ ጥቅሶች በመምዘዝ በአደባባይ ሲያለቅሱ ታይተዋል። ይህም ባህርያቸው የሳቸውን እምነት የማይከተሉ ኬንያውያንን ያገለለ ሆኖ ታይቷል።
ሩቶ ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት ከረን በሚገኘው መኖሪያቸው ውስጥ ቤተ ክርስቲያን አቁመው የተለያዩ ዕምነት ያላቸውን የሃይማኖት መሪዎችን ለማስተናገድ ይጠቀሙበት ነበር።
በኬንያ 85 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ የክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆን፣ 11 በመቶ ገደማ ሙስሊሞች እንዲሁም ሂንዱይዝም እና ባህላዊ እምነት ተከታዮች አሉ።
የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ናይሮቢ በሚገኘው ቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ እንደሆነ አሳወቁ።
ሩቶ ለቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ራሳቸው ወጪያቸውን እንደሚሸፍኑ ገልጸው የማንም ፈቃድ እንደማያስፈልጋቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
"ቤተክርስቲያን ለመገንባት የማንም ይሁንታ አያስፈልገኝም። ሰይጣንን ሊያበሳጨው ይችላል እናም የፈለገውን ማድረግ ይችላል" ሲሉ ሩቶ አርብ ዕለት ተናግረዋል።
የፕሬዚዳንቱ ንግግር በሳቸው አመራር የቤተ ክርስቲያንን እና የመንግሥት በጽኑ መጣመር ቀድሞውኑ የሚተቹት ኬንያውያንን አበሳጭቷል።
ቢቢሲ የኬንያ መንግሥትን አስተያየት እንዲሰጠው ጠይቋል።
ሩቶ ስቴት ሃውስ በተሰኘው ቤተ መንግሥታቸው በሰጡት አስተያየት "ሰይጣን" ብለው የጠሩት አካል ማን እንደሆነ ግልጽ ባይሆንም የቤተ ክርስቲያኑን ፕሮጀክት ከመቀጠል የሚያግዳቸው ምንም ነገር እንደሌለ ገልጸዋል።
"ይህንን ቤተ ክርስቲያን መገንባት የጀመርኩት ወደ ቤተ መንግሥት ስገባ አይደለም። እዚሁ በቆርቆሮ የተሰራ ቤተ ክርስቲያን አገኘሁ። ይህ ለቤተ መንግሥቱ የሚመጥን ይመስላችኋል?" ሲሉ አርብ ዕለት ከፖለቲከኞች ጋር በነበራቸው ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።
አርብ ዕለት ከኬንያ ታዋቂ ከሆኑት ጋዜጦች አንዱ የሆነው ዴይሊ ኔሽን 8 ሺህ ሰዎችን የሚይዝ ትልቅ ህንጻ የሚያሳይ ዲዛይን አትሟል።
ጋዜጣው፤ ይህ ፕሮጀክት መንግሥትና ሃይማኖት የተነጣጠለ ነው የሚለውን የኬንያ ሕገ መንግሥት የሚያከብር ነው ወይ? የሚል ጥያቄን አቅርቧል።
በርካታ ኬንያውያን በዋጋ ግሽበት እና በኑሮ ውድነት እየተፈተኑ ባለበት በዚህ ወቅት 9 ሚሊዮን ዶላር
እንደሚያስወጣ የተገመተው ይህ ቤተ ክርስቲያን ትችቶችን እያስተናገደ ነው።
ሩቶ የቤተክርስቲያኑን ወጪ ከኪሳቸው እከፍላለሁ ቢሉም በሕዝብ ንብረት ላይ ይህን ያህል ትልቅ መዋቅር የመገንባት አቅም አላቸው ወይ የሚል ጥያቄ አጭሯል።
የኬንያ ኢ-አማኒያን ማህበር የቤተ ክርስቲያኑን ግንባታ አስደንጋጭ እና ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ገልጾ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
"ይህ ድርጊት ጸረ ዲሞክራሲያዊ፤ እንዲሁም ፕሬዚዳንት ሩቶ ክርስቲያናዊ አርበኝነትን የማነሳሳት ተግባር አድርገን ነው የምንመለከተው። ኬንያ የክርስቲያኖች አገር ብቻ እንዳልሆነች ልናሳስባቸው እንፈልጋለን" ሲሉ የማህበሩ ኃላፊ ሐሪሰን ሙሚያ አጽንኦት ሰጥተዋል፥
ዊልያም ሩቶ የመጀመሪያው የኢቫንጀሊካል ክርስትና ተከታይ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ በአንዳንዶችም ዘንድ "የእየሱስ ምክትል" የሚል ቅጽል ስም አትርፈዋል።
ሩቶ በሥልጣን ላይ በቆዩባቸው ዓመታት ከመጽሃፍ ቅዱስ ጥቅሶች በመምዘዝ በአደባባይ ሲያለቅሱ ታይተዋል። ይህም ባህርያቸው የሳቸውን እምነት የማይከተሉ ኬንያውያንን ያገለለ ሆኖ ታይቷል።
ሩቶ ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት ከረን በሚገኘው መኖሪያቸው ውስጥ ቤተ ክርስቲያን አቁመው የተለያዩ ዕምነት ያላቸውን የሃይማኖት መሪዎችን ለማስተናገድ ይጠቀሙበት ነበር።
በኬንያ 85 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ የክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆን፣ 11 በመቶ ገደማ ሙስሊሞች እንዲሁም ሂንዱይዝም እና ባህላዊ እምነት ተከታዮች አሉ።
Sponsored by
Surafel
Comments