2 hours ago
ትራምፕ በቢሯቸው ውስጥ በተካሄደ አንድ መርሃ ግብር ላይ እንቅልፍ ወሰዳቸው።
ይህ የሆነው የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሩቢዮ፣ ትራምፕ “አይተኙም” በማለት እስካሁን እንቅልፍ የወሰደው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት አይተው እንደማያውቁ ከተናገሩ በኋላ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
ይህ የሆነው የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሩቢዮ፣ ትራምፕ “አይተኙም” በማለት እስካሁን እንቅልፍ የወሰደው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት አይተው እንደማያውቁ ከተናገሩ በኋላ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
2 hours ago
የእጥፋት ዘመን፡ የኢትዮጵያ መጪው አምስት ዓመታት
***************
( የዕለቱ መልዕክት)
በታሪካዊ እጥፋቶችና ስር በሰደዱ መዋቅራዊ ማነቆዎች ውስጥ ስትመላለስ የኖረችው ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ከትናንት የዳተኝነት ቀንበር ተላቃ ወደ ላቀ ምዕራፍ ለመሻገር የሚያስችላትን ታሪካዊ መሠረት ጥላለች። የሀገራችን የልማትና የለውጥ ጉዞ በመጀመሪያው ምዕራፍ ላይ የጥርጣሬና የፈተና ድንጋዮች ቢወረወሩበትም ዛሬ ግን ኢትዮጵያ በፈጣን እና መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር ሂደት ውስጥ ትገኛለች።
ለብዙ አስርት ዓመታት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ የቆየውን ባህላዊ የግብርና መር ሞዴል ወደ ላቀ የኢንዱስትሪ፣ የቴክኖሎጂ እና የአገልግሎት ዘርፍ ለማሸጋገር የተነደፉት ግዙፍና ሁለንተናዊ የልማት ፕሮጀክቶች መሬት በመያዝ ላይ ናቸው።
ይህ ስልታዊ እርምጃ ተራ የድንጋይና የኮንክሪት ክምችት ሳይሆን የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ስር የሰደደውን የንግድ ሚዛን መዛባት ለመቅረፍ እና የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማስፈን የታለመ የሉዓላዊነት ማህተም ነው።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ በሕዝብ ብዛት በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለች ብትሆንም የኢኮኖሚ ዕድገቷን የገደቡ ሦስት ዋና ዋና መዋቅራዊ እጥረቶች ነበሩባት። የመጀመሪያው ወደ ውጭ ከምትልካቸው ጥሬ የግብርና ምርቶች የምታገኘው ገቢና ለውጭ መሠረታዊ ቁሳቁሶች የምታወጣው ወጪ አለመመጣጠን የወለደው የንግድ ሚዛን መዛባት እና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ነው።
ሁለተኛው ብሔራዊ የምግብ ዋስትናን ሁልጊዜም ለአደጋ የሚያጋልጠውና በየዓመቱ ከዓለም አቀፍ ገበያ በሚመጣ ማዳበሪያ ላይ የተንጠለጠለው የግብርና ዘርፍ የውጭ ጥገኝነት ነው።
ሦስተኛውና ታሪካዊው ተግዳሮት ደግሞ የባህር በር ማጣት ያስከተለው የሎጂስቲክስ ጫና እና ከአንድ የጅቡቲ ወደብ ኮሪደር ጋር ብቻ መተሳሰር የፈጠረው የብሔራዊ ደህንነት ስጋት ነው። እነዚህን ስር የሰደዱ ችግሮች ለመቅረፍ ባለፉት ዓመታት በተለይም በግብርናው ዘርፍ የበጋ ስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከውጪ አስመጪነት ወደ ላኪነት የተደረገው ሽግግር፣ “የማይሞቅ ፍም አይነድም፣ የማይሆን ነገር አይሆንም” የሚሉትን የጥርጣሬ ድምፆች በተግባር ያፈረሰ ተምሳሌታዊ ስኬት ሆኗል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ከሰጡ በኋላ እንዳመለከቱት መጪው አምስት ዓመት የኢትዮጵያ በርካታ የታሪክ እጥፋት የሚታይበት ዘመን ነው።
"የትናንትናዋን ኢትዮጵያ በሚቀጥለው አምስት ዓመት አናያትም። የተቀየረች፣ የተለወጠች፣ ቢያንስ የማትለምን፣ ራሷን ችላ የምትቆም፣ በቀጠናው መልህቅ የሆነች አገር ለማየት ብዙ ልፋት ይፈልጋል" ማለታቸው የዚህን ሽግግር ጥልቀትና የሚጠይቀውን ብሔራዊ ቁርጠኝነት ያሳያል።
በመሆኑም መጪው አምስት ዓመት የምክንያትና የውጤት ትስስር የሚታይበት፣ ባለፉት ዓመታት የተጀመሩት ስልታዊና ትላልቅ ስራዎች ፍሬ የሚያፈሩበት ወርቃማ ምዕራፍ ይሆናል።
በዚህም መሠረት በኃይልና ታዳሽ ኢነርጂ ዘርፍ እንደ የኮይሻ ሃይድሮ-ኤሌክትሪክ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ ኢትዮጵያን የቀጠናዉ የኃይል ማማ ከማድረግ ባለፈ ለኢንዱስትሪ መስፋፋት አስተማማኝና ርካሽ ግብዓት ይፈጥራል።
በፔትሮ-ኬሚካልና ማምረቻ ዘርፍ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝና የሀገር ውስጥ የማዳበሪያ ፋብሪካ ስራ መጀመር የግብርናውን ዘርፍ ከውጭ ጥገኝነት በማላቀቅ የውጭ ምንዛሬን በከፍተኛ ሁኔታ ይታደጋል። በአቪዬሽንና ግሎባል ትራንስፖርት ዘርፍ አዲሱ የቢሾፍቱ ሜጋ አየር ማረፊያ ግንባታ ኢትዮጵያን የአፍሪካ ቁልፍ የሎጂስቲክስና የትራንዚት ማእከልነቷን ያጠናክራል።
በከተማ ውበትና የቦታ ልማት ኢኮኖሚ ረገድ ደግሞ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማትና የገበታ ለትዉልድ ፕሮጀክቶች ከተሞችን የቱሪስት መዳረሻና የኢኮኖሚ መፈልፈያ ማዕከል በማድረግ ረገድ ያላቸው ፋይዳ የጎላ ነው።
ይህንን ታላቅ አህጉራዊ ተስፋ እውን ለማድረግና ኢትዮጵያን በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ድምፅዋ ጎልቶ የሚሰማ ግዙፍ የአፍሪካ ኃያል ሀገር ለማድረግ የሚቻለው ቀጣናዊና ሀገራዊ የቤት ስራዎችን በብልሃት መወጣት ሲቻል ነው።
በመሆኑም መዋቅራዊ ሽግግሩን በስኬት ለማጠናቀቅ የሀገር ውስጥ ሰላምና ጸጥታን በአስተማማኝ ሁኔታ ማስቀጠል፣ የማክሮኢኮኖሚ መረጋጋትን መፍጠር፣ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር እና የፋይናንስ አቅርቦቶችን የበለጠ ማሻሻል ድርድር የማይገባባቸው ቅድመ ሁኔታዎች ናቸው።
ኢትዮጵያ ያላትን ስትራቴጂካዊና ጂኦ-ፖለቲካዊ አቀማመጥ እና የተፈጥሮ ፀጋ በአግባቡ ከተጠቀመች መጪው አምስት ዓመት የልመና ታሪኳ የሚያበቃበት ራሷን ችላ የምትቆምበት እና የበለፀገች ሀገር የመሆን ጉዞዋ በተጨባጭ የሚረጋገጥበት ዘመን እንደሚሆን አያጠራጥርም።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #dot #ebc
***************
( የዕለቱ መልዕክት)
በታሪካዊ እጥፋቶችና ስር በሰደዱ መዋቅራዊ ማነቆዎች ውስጥ ስትመላለስ የኖረችው ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ከትናንት የዳተኝነት ቀንበር ተላቃ ወደ ላቀ ምዕራፍ ለመሻገር የሚያስችላትን ታሪካዊ መሠረት ጥላለች። የሀገራችን የልማትና የለውጥ ጉዞ በመጀመሪያው ምዕራፍ ላይ የጥርጣሬና የፈተና ድንጋዮች ቢወረወሩበትም ዛሬ ግን ኢትዮጵያ በፈጣን እና መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር ሂደት ውስጥ ትገኛለች።
ለብዙ አስርት ዓመታት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ የቆየውን ባህላዊ የግብርና መር ሞዴል ወደ ላቀ የኢንዱስትሪ፣ የቴክኖሎጂ እና የአገልግሎት ዘርፍ ለማሸጋገር የተነደፉት ግዙፍና ሁለንተናዊ የልማት ፕሮጀክቶች መሬት በመያዝ ላይ ናቸው።
ይህ ስልታዊ እርምጃ ተራ የድንጋይና የኮንክሪት ክምችት ሳይሆን የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ስር የሰደደውን የንግድ ሚዛን መዛባት ለመቅረፍ እና የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማስፈን የታለመ የሉዓላዊነት ማህተም ነው።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ በሕዝብ ብዛት በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለች ብትሆንም የኢኮኖሚ ዕድገቷን የገደቡ ሦስት ዋና ዋና መዋቅራዊ እጥረቶች ነበሩባት። የመጀመሪያው ወደ ውጭ ከምትልካቸው ጥሬ የግብርና ምርቶች የምታገኘው ገቢና ለውጭ መሠረታዊ ቁሳቁሶች የምታወጣው ወጪ አለመመጣጠን የወለደው የንግድ ሚዛን መዛባት እና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ነው።
ሁለተኛው ብሔራዊ የምግብ ዋስትናን ሁልጊዜም ለአደጋ የሚያጋልጠውና በየዓመቱ ከዓለም አቀፍ ገበያ በሚመጣ ማዳበሪያ ላይ የተንጠለጠለው የግብርና ዘርፍ የውጭ ጥገኝነት ነው።
ሦስተኛውና ታሪካዊው ተግዳሮት ደግሞ የባህር በር ማጣት ያስከተለው የሎጂስቲክስ ጫና እና ከአንድ የጅቡቲ ወደብ ኮሪደር ጋር ብቻ መተሳሰር የፈጠረው የብሔራዊ ደህንነት ስጋት ነው። እነዚህን ስር የሰደዱ ችግሮች ለመቅረፍ ባለፉት ዓመታት በተለይም በግብርናው ዘርፍ የበጋ ስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከውጪ አስመጪነት ወደ ላኪነት የተደረገው ሽግግር፣ “የማይሞቅ ፍም አይነድም፣ የማይሆን ነገር አይሆንም” የሚሉትን የጥርጣሬ ድምፆች በተግባር ያፈረሰ ተምሳሌታዊ ስኬት ሆኗል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ከሰጡ በኋላ እንዳመለከቱት መጪው አምስት ዓመት የኢትዮጵያ በርካታ የታሪክ እጥፋት የሚታይበት ዘመን ነው።
"የትናንትናዋን ኢትዮጵያ በሚቀጥለው አምስት ዓመት አናያትም። የተቀየረች፣ የተለወጠች፣ ቢያንስ የማትለምን፣ ራሷን ችላ የምትቆም፣ በቀጠናው መልህቅ የሆነች አገር ለማየት ብዙ ልፋት ይፈልጋል" ማለታቸው የዚህን ሽግግር ጥልቀትና የሚጠይቀውን ብሔራዊ ቁርጠኝነት ያሳያል።
በመሆኑም መጪው አምስት ዓመት የምክንያትና የውጤት ትስስር የሚታይበት፣ ባለፉት ዓመታት የተጀመሩት ስልታዊና ትላልቅ ስራዎች ፍሬ የሚያፈሩበት ወርቃማ ምዕራፍ ይሆናል።
በዚህም መሠረት በኃይልና ታዳሽ ኢነርጂ ዘርፍ እንደ የኮይሻ ሃይድሮ-ኤሌክትሪክ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ ኢትዮጵያን የቀጠናዉ የኃይል ማማ ከማድረግ ባለፈ ለኢንዱስትሪ መስፋፋት አስተማማኝና ርካሽ ግብዓት ይፈጥራል።
በፔትሮ-ኬሚካልና ማምረቻ ዘርፍ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝና የሀገር ውስጥ የማዳበሪያ ፋብሪካ ስራ መጀመር የግብርናውን ዘርፍ ከውጭ ጥገኝነት በማላቀቅ የውጭ ምንዛሬን በከፍተኛ ሁኔታ ይታደጋል። በአቪዬሽንና ግሎባል ትራንስፖርት ዘርፍ አዲሱ የቢሾፍቱ ሜጋ አየር ማረፊያ ግንባታ ኢትዮጵያን የአፍሪካ ቁልፍ የሎጂስቲክስና የትራንዚት ማእከልነቷን ያጠናክራል።
በከተማ ውበትና የቦታ ልማት ኢኮኖሚ ረገድ ደግሞ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማትና የገበታ ለትዉልድ ፕሮጀክቶች ከተሞችን የቱሪስት መዳረሻና የኢኮኖሚ መፈልፈያ ማዕከል በማድረግ ረገድ ያላቸው ፋይዳ የጎላ ነው።
ይህንን ታላቅ አህጉራዊ ተስፋ እውን ለማድረግና ኢትዮጵያን በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ድምፅዋ ጎልቶ የሚሰማ ግዙፍ የአፍሪካ ኃያል ሀገር ለማድረግ የሚቻለው ቀጣናዊና ሀገራዊ የቤት ስራዎችን በብልሃት መወጣት ሲቻል ነው።
በመሆኑም መዋቅራዊ ሽግግሩን በስኬት ለማጠናቀቅ የሀገር ውስጥ ሰላምና ጸጥታን በአስተማማኝ ሁኔታ ማስቀጠል፣ የማክሮኢኮኖሚ መረጋጋትን መፍጠር፣ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር እና የፋይናንስ አቅርቦቶችን የበለጠ ማሻሻል ድርድር የማይገባባቸው ቅድመ ሁኔታዎች ናቸው።
ኢትዮጵያ ያላትን ስትራቴጂካዊና ጂኦ-ፖለቲካዊ አቀማመጥ እና የተፈጥሮ ፀጋ በአግባቡ ከተጠቀመች መጪው አምስት ዓመት የልመና ታሪኳ የሚያበቃበት ራሷን ችላ የምትቆምበት እና የበለፀገች ሀገር የመሆን ጉዞዋ በተጨባጭ የሚረጋገጥበት ዘመን እንደሚሆን አያጠራጥርም።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #dot #ebc
2 hours ago
ኤርትራ የንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት ገጠማት።
የውሃ ማጓጓዣ ታንከሮች ስራ ማቆማቸው ለዋሃ እጥረት መከሰት ምክንያት ሆኗል።
የአሜሪካ እና የኢራን ጦርነት ባስከተለው የሀይል እጥረት ኤርትራ ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩ ተገልጿል።
በዚሁ የሀይል እጥረት ሳቢያ ነዳጅ የሚጠቀሙ የውሃ ታንከሮች ስራ አቁመዋል ተብሏል።
የመጠጥ፣ የንፅህና እና ሌሎች አገልግሎት የሚውል በቂ የውሃ አቅርቦት አለመኖሩ ተመልክቷል። የውሃ እጥረት በከተማ እና በገጠር ዋነኛ ችግር ሆኗል ተብሏል። #awate
Seledadotio
Seledadotio
የውሃ ማጓጓዣ ታንከሮች ስራ ማቆማቸው ለዋሃ እጥረት መከሰት ምክንያት ሆኗል።
የአሜሪካ እና የኢራን ጦርነት ባስከተለው የሀይል እጥረት ኤርትራ ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩ ተገልጿል።
በዚሁ የሀይል እጥረት ሳቢያ ነዳጅ የሚጠቀሙ የውሃ ታንከሮች ስራ አቁመዋል ተብሏል።
የመጠጥ፣ የንፅህና እና ሌሎች አገልግሎት የሚውል በቂ የውሃ አቅርቦት አለመኖሩ ተመልክቷል። የውሃ እጥረት በከተማ እና በገጠር ዋነኛ ችግር ሆኗል ተብሏል። #awate
Seledadotio
Seledadotio
11 hours ago
በሰሀራ በረሃ 49 ስደተኞች ህይወታቸው አልፎ ተገኙ።
ስደተኞቹ በህገወጥ መንገድ ሰፊውን በረሃ እያቋረጡ በነበረበት ወቅት እነሱን የያዘው ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው ህይወታቸው ያለፈው ተብሏል።
ከአደጋው የተረፉ ሁለት ስደተኞች 50 ኪሎሜትር ተጉዘው ለባለስልጣናት ከተናገሩ በኋላ የህይወት አድን ቡድን መሰማራታቸው ተገልጿል።
ስደተኞቹ የማሊ ዜግነት ሲኖራቸው በኒጀር እና አልጀሪያ አዋሳኝ አሳማካ ክልል ነው አደጋው የደረሰባቸው።
ይህ አሳዛኝ ክስተት በሰሀራ በረሃ እየደረሰ ያለውን አስከፊ የስደተኞች ሰቆቃ እንደሚያሳይ ተመልክቷል። #legit
Seledadotio
Seledadotio
ስደተኞቹ በህገወጥ መንገድ ሰፊውን በረሃ እያቋረጡ በነበረበት ወቅት እነሱን የያዘው ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው ህይወታቸው ያለፈው ተብሏል።
ከአደጋው የተረፉ ሁለት ስደተኞች 50 ኪሎሜትር ተጉዘው ለባለስልጣናት ከተናገሩ በኋላ የህይወት አድን ቡድን መሰማራታቸው ተገልጿል።
ስደተኞቹ የማሊ ዜግነት ሲኖራቸው በኒጀር እና አልጀሪያ አዋሳኝ አሳማካ ክልል ነው አደጋው የደረሰባቸው።
ይህ አሳዛኝ ክስተት በሰሀራ በረሃ እየደረሰ ያለውን አስከፊ የስደተኞች ሰቆቃ እንደሚያሳይ ተመልክቷል። #legit
Seledadotio
Seledadotio
12 hours ago
"ጥልቅ ኅዘን ተሰምቶኛል" ጠቅላይ ሚኒስትሩ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአርሲው የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞችና ቤተ እምነት ጥቃት፣ "ጥልቅ ኅዘን" እንደተሰማቸው በጽ/ቤታቸው በኩል ባወጡት መገለጫ አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ምርጫ እና ልማት ላይ ባደረገው መግለጫው፣ የአርሲውን ሃይማኖታዊ ጥቃት ከታጣቂዎች እና ከውጭ ኃይሎች ጋር አያይዞታል። የጥቃቱ ፈጻሚ ኦነግ-ሸኔ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ አማጺያን እና ለኢትዮጵያ ጥላቻ አላቸው ከተባሉ የውጭ ኃይሎች ጋር በቅንጅት የተፈጸመ ነውም ብሏል።
በአርሲው ጥቃት የተወነጀሉት የውስጥና የውጭ ኃይሎች፣ 'ጽምዶ' የተሸኘ ቅንጅት እንደፈጠረበትም መንግሥት ገልጿል። በዚሁ ቅንጅት ባለፈው ሰኞ'ለት የተካሄደውን 7ኛ ዙር ጠቅላላ ምርጫ ለማኮላሸት መከራ የተደረገ ቢሆንም፣ የደህነንት ኃይሉ አምክኖታል ተብሏል።
የመግለጫውን ሙሉ ይዘት ከላይ ይመልከቱ
Seledadotio
Seledadotio
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአርሲው የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞችና ቤተ እምነት ጥቃት፣ "ጥልቅ ኅዘን" እንደተሰማቸው በጽ/ቤታቸው በኩል ባወጡት መገለጫ አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ምርጫ እና ልማት ላይ ባደረገው መግለጫው፣ የአርሲውን ሃይማኖታዊ ጥቃት ከታጣቂዎች እና ከውጭ ኃይሎች ጋር አያይዞታል። የጥቃቱ ፈጻሚ ኦነግ-ሸኔ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ አማጺያን እና ለኢትዮጵያ ጥላቻ አላቸው ከተባሉ የውጭ ኃይሎች ጋር በቅንጅት የተፈጸመ ነውም ብሏል።
በአርሲው ጥቃት የተወነጀሉት የውስጥና የውጭ ኃይሎች፣ 'ጽምዶ' የተሸኘ ቅንጅት እንደፈጠረበትም መንግሥት ገልጿል። በዚሁ ቅንጅት ባለፈው ሰኞ'ለት የተካሄደውን 7ኛ ዙር ጠቅላላ ምርጫ ለማኮላሸት መከራ የተደረገ ቢሆንም፣ የደህነንት ኃይሉ አምክኖታል ተብሏል።
የመግለጫውን ሙሉ ይዘት ከላይ ይመልከቱ
Seledadotio
Seledadotio
13 hours ago
የባንኩ መግለጫ‼️
በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ደንበኞች የባንክ ሒሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማጣመርን በተመለከተ ከንግድ ባንክ የተሰጠ መግለጫ‼️
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት በዋና ዋና ከተሞች በሚገኙ የባንካችን ቅርንጫፎች የተከፈቱ የባንክ ሒሳቦች ባለቤቶች የሆኑ እና እስከ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ሳያጣምሩ የቀሩ ደንበኞች በቀጣይ እስኪያጣምሩ ሒሳባቸው በጊዜያዊነት እንዳይንቀሳቀስ መደረጉ ይታወቃል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መኖሪያቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ ያደረጉ ደንበኞች የባንክ ሒሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማጣመር ሳያስፈልጋቸው በጊዜያዊነት በልዩ ሁኔታ መስተናገድ የሚችሉበትን አሠራር ዘርግቷል።
በዚህ መሠረት ከዚህ በፊት ሒሳብ በሚከፍቱበት ወቅት የመኖሪያ አድራሻቸው ከኢትዮጵያ ውጭ እንደሆነ በባንካችን የመረጃ ቋት የተመዘገበ ማስረጃ ያቀረቡ ደንበኞች ሒሳብ ያልታገደ መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታውቋል።
በተለያየ ምክንያት ውጭ ሀገር እንደሚኖሩ በባንኩ የመረጃ ቋት ላይ ያላስመዘገቡ እና የባንክ ሒሳባቸው የታገደባቸው ደንበኞች ከዚህ በታች በተገለፀው አግባብ መስተናገድ የሚችሉ መሆኑን ገልጿል፦
1. ከኢትዮጵያ ውጭ መኖራቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ለምሳሌ - የትምህርት ማስረጃ፣ የሕክምና ማስረጃ፣ የውጭ ሀገር መንጃ ፈቃድ፣ ከውጭ ሀገር የተሰጠ ውክልና፣ የመኖሪያ ፈቃድ (የሎው ካርድ)፣ የሥራ ፈቃድ ወይም ሀገር ውስጥ እያሉ የተሰጠ ውክልና ሆኖ ነገር ግን ውክልናው ላይ ውጭ ሀገር መኖራቸውን የሚገልጽ ሐሳብ ካለ በሕጋዊ መኪሎቻቸው አማካኝነት በማቅረብ እግዱን ማስለቀቅ ይችላሉ፤
2. ዲፕሎማቶች የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ መታወቂያቸውን በማሳየት ወይም ሒሳቡ የተከፈተው በዲፕሎማት መታወቂያ ከሆነ እግዱ ተነስቶላቸው ሒሳባቸውን ማንቀሳቀስ ይችላሉ፤
3. ደንበኛው በውጭ ሀገር እንደሚኖር የሚያረጋግጥ የኢሜይል መልእክት በኢምባሲ/ቆንስላ በኩል ከመጣ እግዱ በጊዜያዊነት ተነስቶላቸው መሰተናገድ ይችላሉ፤
4. በተጨማሪም ደንበኞች በውጭ ሀገር መኖራቸውን ሊያስረዱ የሚችሉ ማስረጃዎችን በቀጥታ የባንክ ሒሳቡ በተከፈተበት ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ የኢ-ሜል አድራሻ ወይም በዲያስፖራ ባንኪንግ ክፍል የኢ-ሜል አድራሻ DiasporaBankingcbe.com.et በመላክ እግዱን በጊዜያዊነት ማስነሳት ይችላሉ ብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ደንበኞች የባንክ ሒሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማጣመርን በተመለከተ ከንግድ ባንክ የተሰጠ መግለጫ‼️
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት በዋና ዋና ከተሞች በሚገኙ የባንካችን ቅርንጫፎች የተከፈቱ የባንክ ሒሳቦች ባለቤቶች የሆኑ እና እስከ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ሳያጣምሩ የቀሩ ደንበኞች በቀጣይ እስኪያጣምሩ ሒሳባቸው በጊዜያዊነት እንዳይንቀሳቀስ መደረጉ ይታወቃል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መኖሪያቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ ያደረጉ ደንበኞች የባንክ ሒሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማጣመር ሳያስፈልጋቸው በጊዜያዊነት በልዩ ሁኔታ መስተናገድ የሚችሉበትን አሠራር ዘርግቷል።
በዚህ መሠረት ከዚህ በፊት ሒሳብ በሚከፍቱበት ወቅት የመኖሪያ አድራሻቸው ከኢትዮጵያ ውጭ እንደሆነ በባንካችን የመረጃ ቋት የተመዘገበ ማስረጃ ያቀረቡ ደንበኞች ሒሳብ ያልታገደ መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታውቋል።
በተለያየ ምክንያት ውጭ ሀገር እንደሚኖሩ በባንኩ የመረጃ ቋት ላይ ያላስመዘገቡ እና የባንክ ሒሳባቸው የታገደባቸው ደንበኞች ከዚህ በታች በተገለፀው አግባብ መስተናገድ የሚችሉ መሆኑን ገልጿል፦
1. ከኢትዮጵያ ውጭ መኖራቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ለምሳሌ - የትምህርት ማስረጃ፣ የሕክምና ማስረጃ፣ የውጭ ሀገር መንጃ ፈቃድ፣ ከውጭ ሀገር የተሰጠ ውክልና፣ የመኖሪያ ፈቃድ (የሎው ካርድ)፣ የሥራ ፈቃድ ወይም ሀገር ውስጥ እያሉ የተሰጠ ውክልና ሆኖ ነገር ግን ውክልናው ላይ ውጭ ሀገር መኖራቸውን የሚገልጽ ሐሳብ ካለ በሕጋዊ መኪሎቻቸው አማካኝነት በማቅረብ እግዱን ማስለቀቅ ይችላሉ፤
2. ዲፕሎማቶች የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ መታወቂያቸውን በማሳየት ወይም ሒሳቡ የተከፈተው በዲፕሎማት መታወቂያ ከሆነ እግዱ ተነስቶላቸው ሒሳባቸውን ማንቀሳቀስ ይችላሉ፤
3. ደንበኛው በውጭ ሀገር እንደሚኖር የሚያረጋግጥ የኢሜይል መልእክት በኢምባሲ/ቆንስላ በኩል ከመጣ እግዱ በጊዜያዊነት ተነስቶላቸው መሰተናገድ ይችላሉ፤
4. በተጨማሪም ደንበኞች በውጭ ሀገር መኖራቸውን ሊያስረዱ የሚችሉ ማስረጃዎችን በቀጥታ የባንክ ሒሳቡ በተከፈተበት ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ የኢ-ሜል አድራሻ ወይም በዲያስፖራ ባንኪንግ ክፍል የኢ-ሜል አድራሻ DiasporaBankingcbe.com.et በመላክ እግዱን በጊዜያዊነት ማስነሳት ይችላሉ ብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
13 hours ago
u12e8u121du123du1275 2 u1230u12d3u1275 u12a0u121bu122du129b u12dcu1293 u2026 u130du1295u1266u127528/2018 u12d3.u121d #ebcdotstream #ebc #ethiopia ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የምሽት 2 ሰዓት አማርኛ ዜና … ግንቦት28/2018 ዓ.ም #ebcdotstream #ebc #ethiopia
14 hours ago
ኦብነግ ከፋኖ ጋር መነጋገሩን ይፋ አደረገ
ከአንድ ወር በፊት በአስመራ ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር የተገናኙት የኦብነግ አንጃ መሪ የሆኑት አብዱራህማን መህዲ ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ንግግር እያደረጉ መሆናቸውን አሳውቀዋል፡፡ አፍሪካን ኢንተለጀንስ ትናንት ባወጣው ዘገባ፣ ከሰላማዊ ትግል ራሱን ያገለለው የኦብነግ አንጃ ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ እና አማጺ ኃይሎች ጋር ጥምረት እንዲፈጥሩ ከግብጽ እና ኤርትራ መንግስታት ጫና እየተደረገባቸው መሆኑን ዘግቧል፡፡
የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች በጋራ እየተሰባሰቡ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው፤ ከሚሰባሰቡት ኃይሎች መካከል ኦብነግ አንዱ ነው ብሏል፡፡ እንደ ፋኖ፣ ህውሃት እና ኦነግ ሸኔ ካሉ ሀይሎች ጋር ጥምረት መፍጠራቸውን በአፍሪካ ኢንተለጀንስ የተጠየቁት የቡድኑ መሪ አብዱራህማን መህዲ፤ ‹‹ጥምረት የመፍጠር ደረጃ ላይ ባንደርስም፤ ከፋኖም ሆነ ሌሎች ሀይሎች ጋር ተነጋግረናል፤ ለመስራትም ዝግጁ ነን፤ ነገር ግን ውይጥቱ የመጨረሻ ደረጃ ላይ አልደረሰም›› በማለት መልሰዋል፡፡
አፍሪካን ኢንተለጀንስ እንደዘገባው፣ የኦብነግ አንጃ ከሌሎች ሀይሎች ጋር ትብብር እንዲፈጥር፣ በሱዳን፣ ኤርትራ እና ግብጽ መንግስታት ጫና እየተደረገበት ሲሆን፤ በቅርቡም በአስመራ እና በፖርት ሱዳን ስብሰባዎችን ማደረረጋቸውን ጠቅሷል፡፡via:- andafta
Seledadotio
Seledadotio
ከአንድ ወር በፊት በአስመራ ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር የተገናኙት የኦብነግ አንጃ መሪ የሆኑት አብዱራህማን መህዲ ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ንግግር እያደረጉ መሆናቸውን አሳውቀዋል፡፡ አፍሪካን ኢንተለጀንስ ትናንት ባወጣው ዘገባ፣ ከሰላማዊ ትግል ራሱን ያገለለው የኦብነግ አንጃ ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ እና አማጺ ኃይሎች ጋር ጥምረት እንዲፈጥሩ ከግብጽ እና ኤርትራ መንግስታት ጫና እየተደረገባቸው መሆኑን ዘግቧል፡፡
የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች በጋራ እየተሰባሰቡ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው፤ ከሚሰባሰቡት ኃይሎች መካከል ኦብነግ አንዱ ነው ብሏል፡፡ እንደ ፋኖ፣ ህውሃት እና ኦነግ ሸኔ ካሉ ሀይሎች ጋር ጥምረት መፍጠራቸውን በአፍሪካ ኢንተለጀንስ የተጠየቁት የቡድኑ መሪ አብዱራህማን መህዲ፤ ‹‹ጥምረት የመፍጠር ደረጃ ላይ ባንደርስም፤ ከፋኖም ሆነ ሌሎች ሀይሎች ጋር ተነጋግረናል፤ ለመስራትም ዝግጁ ነን፤ ነገር ግን ውይጥቱ የመጨረሻ ደረጃ ላይ አልደረሰም›› በማለት መልሰዋል፡፡
አፍሪካን ኢንተለጀንስ እንደዘገባው፣ የኦብነግ አንጃ ከሌሎች ሀይሎች ጋር ትብብር እንዲፈጥር፣ በሱዳን፣ ኤርትራ እና ግብጽ መንግስታት ጫና እየተደረገበት ሲሆን፤ በቅርቡም በአስመራ እና በፖርት ሱዳን ስብሰባዎችን ማደረረጋቸውን ጠቅሷል፡፡via:- andafta
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
17 hours ago
በነገው እለት የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅4:30 – 9:00
👉መስቀል ፋላዎር፣ ወንግላዊት፣ ወሎ ሰፈር ጀርባ፣ ጎርጎርዮስ፣ ጎተራ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30
👉ሰበታ ከተማ ፣ አለርት ሆስፒታል፣ ቻይና ቱቦ አካባቢ፣ ኢንዱስቲሪ መንደር እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 12፡00 – 7፡00
👉መቀለ ከተማ 03፣ አይደር ሪፌራል ሆስፒታል፣ አድሽምን፣ አዲሃ አክረም እና ደኤሮ አካባቢ፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 12፡00
👉መቀለ ከተማ 05፣ ኮንዶሚኒየም ሰፈር፣ ግብርና ብሮና ማይዱባ እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
👉አዳማ ፖስታ ቤት፣ አዳማ ሆስፒታል፣ ፍራንኮ፣ ፒኮክ፣ 105 አካባቢ፣ አኪሊስያ ሆስፕታል እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 6፡30
👉በወልድያ መቻሬ፣ አዳጎ፣ አሸዋ ሜዳ፣ አመያመጫ፣ ሁርጌሳ፣ ኡድመን፣ ልብሶ፣ ጊረና፣ መሀለምብ እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 12፡00 - 11፡00
👉የአዳሚ ቱሉ ገንዳ አርባ 132 ኪ.ቮ አግሮ ኢንዱትሪ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት በታወር ቁጥር 11 እና በታወር ቁጥር 12 መካከል በሚገኙ ኩርማ 33 ኪ.ቮ ኢንዱስትሪ ፓርክ 33 ኪ.ቮ እና ቡልቡላ 15 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ መስመሮች ይቋረጣሉ፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ የተከበራችሁ ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
ነገ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅4:30 – 9:00
👉መስቀል ፋላዎር፣ ወንግላዊት፣ ወሎ ሰፈር ጀርባ፣ ጎርጎርዮስ፣ ጎተራ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30
👉ሰበታ ከተማ ፣ አለርት ሆስፒታል፣ ቻይና ቱቦ አካባቢ፣ ኢንዱስቲሪ መንደር እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 12፡00 – 7፡00
👉መቀለ ከተማ 03፣ አይደር ሪፌራል ሆስፒታል፣ አድሽምን፣ አዲሃ አክረም እና ደኤሮ አካባቢ፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 12፡00
👉መቀለ ከተማ 05፣ ኮንዶሚኒየም ሰፈር፣ ግብርና ብሮና ማይዱባ እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
👉አዳማ ፖስታ ቤት፣ አዳማ ሆስፒታል፣ ፍራንኮ፣ ፒኮክ፣ 105 አካባቢ፣ አኪሊስያ ሆስፕታል እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 6፡30
👉በወልድያ መቻሬ፣ አዳጎ፣ አሸዋ ሜዳ፣ አመያመጫ፣ ሁርጌሳ፣ ኡድመን፣ ልብሶ፣ ጊረና፣ መሀለምብ እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 12፡00 - 11፡00
👉የአዳሚ ቱሉ ገንዳ አርባ 132 ኪ.ቮ አግሮ ኢንዱትሪ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት በታወር ቁጥር 11 እና በታወር ቁጥር 12 መካከል በሚገኙ ኩርማ 33 ኪ.ቮ ኢንዱስትሪ ፓርክ 33 ኪ.ቮ እና ቡልቡላ 15 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ መስመሮች ይቋረጣሉ፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ የተከበራችሁ ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
18 hours ago
የኢቦላ ስጋት እና የሀገራት ጥንቃቄ
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን (UAE) ጨምሮ በርካታ ሀገራት የኢቦላ ቫይረስ ወደ ሀገራቸው እንዳይገባ ጠንካራ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምረዋል።
በዚህም መሰረት ሦስት ሀገራት ዜጎች ከዛሬ ጀምሮ ለጊዜው ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል።
እነዚህ ሀገራትም፦
* ዲ.አር. ኮንጎ (DRC)
* ደቡብ ሱዳን እና
* ኡጋንዳ ናቸው።
Via GN
በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የአፍሪካ መገናኛ ማዕከል እንደመሆናችን መጠን፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የሚመለከታቸው የጤና ተቋማት ይህንን ወቅታዊ ሁኔታ በአስቸኳይ አይተው፣ የህዝባችንን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አፋጣኝ ውሳኔና የጥንቃቄ እርምጃ ቢወስዱበት መልካም ነው እንላለን።
ጤና ለሀገራችን! 🇪🇹
Seledadotio
Seledadotio
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን (UAE) ጨምሮ በርካታ ሀገራት የኢቦላ ቫይረስ ወደ ሀገራቸው እንዳይገባ ጠንካራ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምረዋል።
በዚህም መሰረት ሦስት ሀገራት ዜጎች ከዛሬ ጀምሮ ለጊዜው ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል።
እነዚህ ሀገራትም፦
* ዲ.አር. ኮንጎ (DRC)
* ደቡብ ሱዳን እና
* ኡጋንዳ ናቸው።
Via GN
በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የአፍሪካ መገናኛ ማዕከል እንደመሆናችን መጠን፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የሚመለከታቸው የጤና ተቋማት ይህንን ወቅታዊ ሁኔታ በአስቸኳይ አይተው፣ የህዝባችንን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አፋጣኝ ውሳኔና የጥንቃቄ እርምጃ ቢወስዱበት መልካም ነው እንላለን።
ጤና ለሀገራችን! 🇪🇹
Seledadotio
Seledadotio
18 hours ago
የአዲስ አበባ ከተማ የቀድሞ ከንቲባ አምባሳደር ዓሊ አብዶ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በ27ኛ ከንቲባነት ከ1990 እስከ 1995 ዓ.ል. የመሩት አምባሳደር ዓሊ አብዶ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰማ።
አምባሳደር ዓሊ አብዶ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው፣ ዛሬ ሌሊት ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል። በአርሲ ድሬ ከተማ ከአባታቸው ከአቶ ዓሊ ሱለይማን እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አፀደ ወልደማሪያም የተወለዱት አምባሳደር ዓሊ፣ ከትዳር አጋራቸው ጋር በጋራ ያፈሯቸው ሁለት ሴት እና አንድ ወንድ ልጆች አሏቸው።
አምባሳደር ዓሊ አብዶ በቆዩባቸው የሥራ ዘመናት ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን በቅንነት፣ በታማኝነትና በታታሪነት ሲያገለግሉ የነበሩ መሪ እንደነበሩ ተገልጿል።
የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው በዛሬው ዕለት ከጁምዓ ሶላት በኋላ፣ በዳለቲ አካባቢ በሚገኘው የሙስሊሞች መቃብር ስፍራ፤ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ይፈጸማል።
የኔቲዩብ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን እየተመኘ፤ አላህ (ሱ.ወ) ጀነተል ፊርዶስ ይወፍቃቸው ዘንድ ዱዓ ያደርጋል።
Seledadotio
Seledadotio
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በ27ኛ ከንቲባነት ከ1990 እስከ 1995 ዓ.ል. የመሩት አምባሳደር ዓሊ አብዶ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰማ።
አምባሳደር ዓሊ አብዶ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው፣ ዛሬ ሌሊት ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል። በአርሲ ድሬ ከተማ ከአባታቸው ከአቶ ዓሊ ሱለይማን እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አፀደ ወልደማሪያም የተወለዱት አምባሳደር ዓሊ፣ ከትዳር አጋራቸው ጋር በጋራ ያፈሯቸው ሁለት ሴት እና አንድ ወንድ ልጆች አሏቸው።
አምባሳደር ዓሊ አብዶ በቆዩባቸው የሥራ ዘመናት ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን በቅንነት፣ በታማኝነትና በታታሪነት ሲያገለግሉ የነበሩ መሪ እንደነበሩ ተገልጿል።
የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው በዛሬው ዕለት ከጁምዓ ሶላት በኋላ፣ በዳለቲ አካባቢ በሚገኘው የሙስሊሞች መቃብር ስፍራ፤ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ይፈጸማል።
የኔቲዩብ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን እየተመኘ፤ አላህ (ሱ.ወ) ጀነተል ፊርዶስ ይወፍቃቸው ዘንድ ዱዓ ያደርጋል።
Seledadotio
Seledadotio
19 hours ago
🔴 ቻይና ግዙፍ የዳታ ማዕከላትን በባህር ወለል ስር ማሰማራት ጀመረች፤ ባህሩ እንደ ተፈጥሯዊ ማቀዝቀዣ ያገለግላል!
የቴክኖሎጂው ልዕለ-ኃያል ቻይና የዓለማችንን የዲጂታል መሠረተ-ልማት አወቃቀር ሙሉ በሙሉ ሊቀይር የሚችል እጅግ አስደናቂ የፈጠራ ስራ በተግባር ማከናወን መጀመሯ ይፋ ሆኗል። ሀገሪቱ እጅግ ግዙፍ የሆኑ የዳታ ማዕከላትን (Data Centers) በቀጥታ በውቅያኖስ ወለል ላይ የማስቀመጥ እና ለንግድ አገልግሎት የማዋል ስራን በተሳካ ሁኔታ ጀምራለች።
ይህ ታይቶ የማይታወቅ አዲስ አሰራር የዳታ ማዕከላቱ ሰርቨሮች መረጃዎችን በከፍተኛ ፍጥነት በሚያሰሉበት ጊዜ የሚፈጥሩትን እጅግ ኃይለኛ ሙቀት ለማስወገድ ቀዝቃዛውን የባህር ውሃ እንደ ተፈጥሯዊ ማቀዝቀዣ የሚጠቀም ነው። ይህም በየብስ ላይ እንደሚደረገው ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ማቀዝቀዣ ማሽኖችን (Chillers) የመጠቀም አስፈላጊነትን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል።
ይህ የቴክኖሎጂ ስኬት ባህላዊ የዳታ ማዕከላት የሚጠይቁትን የኤሌክትሪክ ፍጆታ በ22.8 በመቶ የሚቀንስ ሲሆን፣ ለባህላዊ ማቀዝቀዣ የሚባክነውን በሚሊዮን የሚቆጠር ሊትር ንጹህ የውሃ ፍጆታን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል። በተጨማሪም በየብስ ላይ ሊያዝ የሚችለውን ውድ የቦታ ስፋት በ90 በመቶ መታደግ ያስቻለ ሲሆን፣ ማዕከላቱ በቀጥታ በባህር ላይ ከተተከሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ጋር የተገናኙ በመሆኑ ሙሉ በሙሉ በአረንጓዴ እና ታዳሽ ኃይል የሚሰሩ ናቸው።
Seledadotio
Seledadotio
የቴክኖሎጂው ልዕለ-ኃያል ቻይና የዓለማችንን የዲጂታል መሠረተ-ልማት አወቃቀር ሙሉ በሙሉ ሊቀይር የሚችል እጅግ አስደናቂ የፈጠራ ስራ በተግባር ማከናወን መጀመሯ ይፋ ሆኗል። ሀገሪቱ እጅግ ግዙፍ የሆኑ የዳታ ማዕከላትን (Data Centers) በቀጥታ በውቅያኖስ ወለል ላይ የማስቀመጥ እና ለንግድ አገልግሎት የማዋል ስራን በተሳካ ሁኔታ ጀምራለች።
ይህ ታይቶ የማይታወቅ አዲስ አሰራር የዳታ ማዕከላቱ ሰርቨሮች መረጃዎችን በከፍተኛ ፍጥነት በሚያሰሉበት ጊዜ የሚፈጥሩትን እጅግ ኃይለኛ ሙቀት ለማስወገድ ቀዝቃዛውን የባህር ውሃ እንደ ተፈጥሯዊ ማቀዝቀዣ የሚጠቀም ነው። ይህም በየብስ ላይ እንደሚደረገው ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ማቀዝቀዣ ማሽኖችን (Chillers) የመጠቀም አስፈላጊነትን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል።
ይህ የቴክኖሎጂ ስኬት ባህላዊ የዳታ ማዕከላት የሚጠይቁትን የኤሌክትሪክ ፍጆታ በ22.8 በመቶ የሚቀንስ ሲሆን፣ ለባህላዊ ማቀዝቀዣ የሚባክነውን በሚሊዮን የሚቆጠር ሊትር ንጹህ የውሃ ፍጆታን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል። በተጨማሪም በየብስ ላይ ሊያዝ የሚችለውን ውድ የቦታ ስፋት በ90 በመቶ መታደግ ያስቻለ ሲሆን፣ ማዕከላቱ በቀጥታ በባህር ላይ ከተተከሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ጋር የተገናኙ በመሆኑ ሙሉ በሙሉ በአረንጓዴ እና ታዳሽ ኃይል የሚሰሩ ናቸው።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 day ago
የዓለም የፕሬስ ነፃነት ታይቶ
በማይታወቅ ሁኔታ አሽቆልቁሏል
የድንበር የለሽ ጋዜጠኞች ድርጅት (RSF) ባወጣው የ25ኛ ዓመት ዓለም አቀፍ መግለጫ መሠረት፣ በዓለም ዙሪያ የሚዲያ ነፃነት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ማሽቆልቆሉንና ጋዜጠኝነትን ወደ ወንጀል የመቀየር ሂደት መባባሱን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት አምባገነን መንግሥታት የሚዲያ ነፃነትን ለማፈን የብሔራዊ ደኅንነት ሕግጋትን እንደ መሣሪያ እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ድርጅቱ የገለጸ ሲሆን፣ ኖርዌይ ለ10ኛ ተከታታይ ዓመት 1ኛ ደረጃን በመያዝ የዓለም የፕሬስ ነጻነትን በማስፈን ግንባር ቀደምነቷን አስመስክራለች። በአንጻሩ አሜሪካ በሚዲያ ላይ በሚሰነዘሩ የፖለቲካ ጥቃቶች ምክንያት በ7 ደረጃዎች በማሽቆልቆል 64ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በዚሁ ዓለም አቀፍ የደረጃ ሰንጠረዥ መሠረት ኢትዮጵያ ከ180 የዓለም ሀገራት መካከል 148ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፤ ለዚህም በሀገሪቱ አራት ጋዜጠኞች ከፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ ጋር በተያያዘ ክስ ለሦስት ዓመታት ታስረው መቆየታቸው በሕጋዊ መመዘኛ ዝቅተኛ ውጤት እንድታገኝ ማድረጉ ተገልጿል። ከአፍሪካ ቀንድ ሀገራት መካከል የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኘው ሱዳን 161ኛ ደረጃን ስትይዝ፣ ኤርትራ ደግሞ 180ኛ በመሆን ከዓለም የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።
Seledadotio
Seledadotio
በማይታወቅ ሁኔታ አሽቆልቁሏል
የድንበር የለሽ ጋዜጠኞች ድርጅት (RSF) ባወጣው የ25ኛ ዓመት ዓለም አቀፍ መግለጫ መሠረት፣ በዓለም ዙሪያ የሚዲያ ነፃነት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ማሽቆልቆሉንና ጋዜጠኝነትን ወደ ወንጀል የመቀየር ሂደት መባባሱን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት አምባገነን መንግሥታት የሚዲያ ነፃነትን ለማፈን የብሔራዊ ደኅንነት ሕግጋትን እንደ መሣሪያ እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ድርጅቱ የገለጸ ሲሆን፣ ኖርዌይ ለ10ኛ ተከታታይ ዓመት 1ኛ ደረጃን በመያዝ የዓለም የፕሬስ ነጻነትን በማስፈን ግንባር ቀደምነቷን አስመስክራለች። በአንጻሩ አሜሪካ በሚዲያ ላይ በሚሰነዘሩ የፖለቲካ ጥቃቶች ምክንያት በ7 ደረጃዎች በማሽቆልቆል 64ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በዚሁ ዓለም አቀፍ የደረጃ ሰንጠረዥ መሠረት ኢትዮጵያ ከ180 የዓለም ሀገራት መካከል 148ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፤ ለዚህም በሀገሪቱ አራት ጋዜጠኞች ከፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ ጋር በተያያዘ ክስ ለሦስት ዓመታት ታስረው መቆየታቸው በሕጋዊ መመዘኛ ዝቅተኛ ውጤት እንድታገኝ ማድረጉ ተገልጿል። ከአፍሪካ ቀንድ ሀገራት መካከል የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኘው ሱዳን 161ኛ ደረጃን ስትይዝ፣ ኤርትራ ደግሞ 180ኛ በመሆን ከዓለም የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
🚨 የአያቶላ አሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ከ4 ወራት በኋላ በሰኔ ወር ሊፈጸም ነው!
በመካከለኛው ምስራቅ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና እጅግ ግዙፍ የተባለለት የሽኝት ፕሮግራም ይፋ ሆኗል። ባለፈው የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም (የካቲት 28, 2026) በቴህራን በሚገኘው መኖሪያና ቢሯቸው ላይ በተሰነዘረ የጋራ የአሜሪካ እና የእስራኤል የአየር ጥቃት ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተገደሉት የ86 ዓመቱ የኢራን የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ፣ ከናፈቁት የመጨረሻ ምኞታቸው ጋር በተያያዘ በማሽሃድ በሚገኘው ታዋቂው የኢማም ረዛ መቅደስ አጠገብ ሊቀበሩ መሆኑ ተረጋግጧል።
የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ጦር (IRGC) እንዳስታወቀው ታላቁ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በሰኔ 14 ቀን (June 21) አካባቢ የሚጀምር ሲሆን ለሦስት ቀናት የሚቆይና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢራናውያን የሚሳተፉበት አገር አቀፍ የሽኝት ሰልፍ በቴህራን፣ በቆም እና በማሽሃድ ከተሞች ላይ ይካሄዳል ተብሏል።
የሀገሪቱ ባለስልጣናት እንደገለጹት በዚህ ታሪካዊ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ከ20 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ሊታደም ይችላል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ይህም በሰው ልጅ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ህዝባዊ ስብስብ ያደርገዋል። ይህ አስገራሚ የህዝብ ቁጥር እ.ኤ.አ በ1989 የተከናወነውን እና 10 ሚሊዮን ህዝብ የተገኘበትን የቀድሞውን መሪ የአያቶላ ሩሆላ ኾሜኒን የቀብር ሥነ-ሥርዓት በእጅጉ የሚበልጥ እንደሚሆን ተነግሯል።
Seledadotio
Seledadotio
በመካከለኛው ምስራቅ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና እጅግ ግዙፍ የተባለለት የሽኝት ፕሮግራም ይፋ ሆኗል። ባለፈው የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም (የካቲት 28, 2026) በቴህራን በሚገኘው መኖሪያና ቢሯቸው ላይ በተሰነዘረ የጋራ የአሜሪካ እና የእስራኤል የአየር ጥቃት ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተገደሉት የ86 ዓመቱ የኢራን የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ፣ ከናፈቁት የመጨረሻ ምኞታቸው ጋር በተያያዘ በማሽሃድ በሚገኘው ታዋቂው የኢማም ረዛ መቅደስ አጠገብ ሊቀበሩ መሆኑ ተረጋግጧል።
የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ጦር (IRGC) እንዳስታወቀው ታላቁ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በሰኔ 14 ቀን (June 21) አካባቢ የሚጀምር ሲሆን ለሦስት ቀናት የሚቆይና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢራናውያን የሚሳተፉበት አገር አቀፍ የሽኝት ሰልፍ በቴህራን፣ በቆም እና በማሽሃድ ከተሞች ላይ ይካሄዳል ተብሏል።
የሀገሪቱ ባለስልጣናት እንደገለጹት በዚህ ታሪካዊ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ከ20 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ሊታደም ይችላል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ይህም በሰው ልጅ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ህዝባዊ ስብስብ ያደርገዋል። ይህ አስገራሚ የህዝብ ቁጥር እ.ኤ.አ በ1989 የተከናወነውን እና 10 ሚሊዮን ህዝብ የተገኘበትን የቀድሞውን መሪ የአያቶላ ሩሆላ ኾሜኒን የቀብር ሥነ-ሥርዓት በእጅጉ የሚበልጥ እንደሚሆን ተነግሯል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
እዳ ባለመከፈሉ ኢትዮጵያ ልትከሰስ❓‼️
#የኢትዮጵያ #ዩሮቦንድ አበዳሪዎች ያልተከፈለ ዕዳን በተመለከተ መንግሥትን ለመክሰስ የሕግ ሂደት መጀመራቸው ተዘገበ‼️
የኢትዮጵያ የዩሮቦንድ አበዳሪዎች ቡድን፣ መንግሥት ያልከፈለውን የ1 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ በተመለከተ ክስ ለመመሥረት የሚያስችላቸውን የሕግ ሂደት በይፋ መጀመራቸው ተዘገበ።
ብሉምበርግ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ምንጮች ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፤ የኢትዮጵያ ‘አድ ሆክ’ የቦንድ ባለቤቶች ኮሚቴ (Ethiopia Ad Hoc Bondholder Committee) አባላት፣ በእንግሊዝ ፍርድ ቤቶች ክስ ለመመሥረት ማቀዳቸውን የሚገልጽ የቅድመ-ክስ ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ባለፈው ሳምንት ለኢትዮጵያ መንግሥት ልከዋል።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉት የመረጃው ምንጮች እንዳሉት፣ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰው ለማሳወቅ 14 ቀናት አሉት ያሉ ሲሆን፣ ሆኖም የጊዜ ገደቡ መቼ እንደሚጀምር በዝርዝር አላብራሩም።
Seledadotio
Seledadotio
#የኢትዮጵያ #ዩሮቦንድ አበዳሪዎች ያልተከፈለ ዕዳን በተመለከተ መንግሥትን ለመክሰስ የሕግ ሂደት መጀመራቸው ተዘገበ‼️
የኢትዮጵያ የዩሮቦንድ አበዳሪዎች ቡድን፣ መንግሥት ያልከፈለውን የ1 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ በተመለከተ ክስ ለመመሥረት የሚያስችላቸውን የሕግ ሂደት በይፋ መጀመራቸው ተዘገበ።
ብሉምበርግ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ምንጮች ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፤ የኢትዮጵያ ‘አድ ሆክ’ የቦንድ ባለቤቶች ኮሚቴ (Ethiopia Ad Hoc Bondholder Committee) አባላት፣ በእንግሊዝ ፍርድ ቤቶች ክስ ለመመሥረት ማቀዳቸውን የሚገልጽ የቅድመ-ክስ ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ባለፈው ሳምንት ለኢትዮጵያ መንግሥት ልከዋል።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉት የመረጃው ምንጮች እንዳሉት፣ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰው ለማሳወቅ 14 ቀናት አሉት ያሉ ሲሆን፣ ሆኖም የጊዜ ገደቡ መቼ እንደሚጀምር በዝርዝር አላብራሩም።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 day ago
ችሎት ውስጥ የተፈፀመ አሰቃቂ ግድያ‼
ዛሬ ረፋድ ላይ በሆለታ ወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት፣ የዕለቱን የችሎት ውሳኔ በማንበብ ላይ የነበሩ ዳኛ እና አንዲት ተከራካሪ ህይወታቸው ማለፉን አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ - ኢትዮጵያ አስታውቋል።
እንደ ምንጩ መረጃ፣ የቤተሰብ ክርክር ጉዳይን በመመልከት ላይ የነበሩት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ የፍርድ ውሳኔውን እያነበቡ ባሉበት ወቅት፣ ተከሳሹ በድንገት ባወጣው ሽጉጥ ዳኛዋን በጥይት በመምታት ህይወታቸውን ቀጥፏል።
በዚሁ አጋጣሚ በችሎቱ ላይ በጉዳዩ ላይ ይከራከሩ የነበሩት (ተከራካሪዋ) በተመሳሳይ ሁኔታ በተከሳሹ በተተኮሰ ጥይት ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል።
የሕግ ባለሙያዎችና ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን በጽኑ ያኮነኑ ሲሆን፤ ዳኞችና የሕግ ባለሙያዎች በሥራ ገበታቸው ላይ አስተማማኝ የደህንነት ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ በርካቶች በመጻፍ ላይ ይገኛሉ።
“አንድ ግለሰብ ታጥቆ ወደ ፍርድ ቤት አዳራሽ መግባት መቻሉ፣ የፍርድ ቤቶችን የጸጥታና የፍተሻ አሰራር ምን ያህል ደካማ እንደሆነ በአሳዛኝ ሁኔታ አሳይቷል” በማለት አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ የድርጊቱን አሳሳቢነት ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
ዛሬ ረፋድ ላይ በሆለታ ወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት፣ የዕለቱን የችሎት ውሳኔ በማንበብ ላይ የነበሩ ዳኛ እና አንዲት ተከራካሪ ህይወታቸው ማለፉን አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ - ኢትዮጵያ አስታውቋል።
እንደ ምንጩ መረጃ፣ የቤተሰብ ክርክር ጉዳይን በመመልከት ላይ የነበሩት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ የፍርድ ውሳኔውን እያነበቡ ባሉበት ወቅት፣ ተከሳሹ በድንገት ባወጣው ሽጉጥ ዳኛዋን በጥይት በመምታት ህይወታቸውን ቀጥፏል።
በዚሁ አጋጣሚ በችሎቱ ላይ በጉዳዩ ላይ ይከራከሩ የነበሩት (ተከራካሪዋ) በተመሳሳይ ሁኔታ በተከሳሹ በተተኮሰ ጥይት ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል።
የሕግ ባለሙያዎችና ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን በጽኑ ያኮነኑ ሲሆን፤ ዳኞችና የሕግ ባለሙያዎች በሥራ ገበታቸው ላይ አስተማማኝ የደህንነት ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ በርካቶች በመጻፍ ላይ ይገኛሉ።
“አንድ ግለሰብ ታጥቆ ወደ ፍርድ ቤት አዳራሽ መግባት መቻሉ፣ የፍርድ ቤቶችን የጸጥታና የፍተሻ አሰራር ምን ያህል ደካማ እንደሆነ በአሳዛኝ ሁኔታ አሳይቷል” በማለት አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ የድርጊቱን አሳሳቢነት ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
ወደኋላ አስር አመት‼️
ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀረበ፡፡
ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡
ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡
ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ እና ሆን ብሎ ድርጊቱን መፈፀሙን ከቀጠለ ድርጊቱ እንደ ወንጀል ጥፋት ተቀጥሮ በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑም ተብራርቷል፡፡
በተጠቀሰው ድርጊት የድርጅት ስራ አስኪያጅ በግል በወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው በወንጀሉ ተግባር ተባባሪ ከሆነ ወይንም ደረሰኝ ያለመስጠትን መከላከል የሚያስችል የቁጥጥር ሥርዓት ያልዘረጋ ከሆነ እንዲሆንም ተደንግጓል፡፡
በሌላ በኩል አንድ ግብር ከፋይ ግብር ከከፈለ በኋላ በ10 አመት ጊዜ ውስጥ በማንኛው ጊዜ እንደገና ሂሳቡ ተመርምሮ ወይም በኦዲት ተጨማሪ ግብር ሊጠየቅ ይችላል ይላል የረቂቅ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
ይህም በ10 ዓመት የተገደበው በኢትዮጵያ የንግድ ህግና የሂሳብ አያያዝ ህጎች መሰረት የሂሳብ ሰነዶች ተጠብቀው መቆየት ያለባቸው ለ10 ዓመታት ብቻ በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡
ሌላው የታክስ አስተዳደር አዋጁ ማሻሻያ የያዘው አዲስ ነገር በታክስ ባለስልጣኑ እና በታክስ ከፋዩ መካከል የሚፈጠርን አለመግባባት መፍቻ ዘዴን ይመለከታል፡፡
ከዚህ ቀደም በነበረው ህግ ግብር ከፋዮች የተጣለባቸውን ግብር ተገቢ አይደለም ብለው ባመኑ ጊዜ መፍትሄ ፍለጋ በታክስ አስተዳደሩ ስር ለተቋቋመ የቅሬታ ሰሚ ፣ ለግብር ይግባኝ ኮሚሽን እና የህግ ትርጉምን በተመለከተ በየደረጃው ባሉ ፍርድ ቤቶች እንዲመለከቱት የሚያስችል ስርዓት ነበር፡፡
ይህን ለማድረግ ግን ግብር ከፋዮች ቅድሚያ የተወሰነባቸውን ግብር ከ50 እስከ 75 በመቶ መክፈልም ይጠበቅባቸው ነበር፡፡
ያም ሆኖ መፍትሄ ለማግኘት ረዥም ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል በማብራሪያው ተጠቅሷል፡፡
በተሻሻለውና በረቂቅ ደረጃ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበው የታክስ አስተዳደር አዋጅ የተጠቀሰው አሰራር እንዳለ ሆኖ በአጭር ጊዜ አለመግባባቶችን ለመፍታት ያግዛል የተባለ የገለልተኛ አስማሚን አሰራር ስራ ላይ ያውላል ተብለዋል፡፡
ይህም አዲስ “የመስማማት ሥርዓት” በሚል አዋጁ እንዲዘረጋ በሚፈቅደው ገለልተኛ አስማሚ ግብር ከፋዩን እና ግብር ሰብሳቢውን በሚስጥራዊነት መርህዎች ጭምር የሚያስማማበት ሥርዓት ነው ተብሏል፡፡
#ሸገር ኤፍኤም
Seledadotio
Seledadotio
ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀረበ፡፡
ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡
ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡
ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ እና ሆን ብሎ ድርጊቱን መፈፀሙን ከቀጠለ ድርጊቱ እንደ ወንጀል ጥፋት ተቀጥሮ በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑም ተብራርቷል፡፡
በተጠቀሰው ድርጊት የድርጅት ስራ አስኪያጅ በግል በወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው በወንጀሉ ተግባር ተባባሪ ከሆነ ወይንም ደረሰኝ ያለመስጠትን መከላከል የሚያስችል የቁጥጥር ሥርዓት ያልዘረጋ ከሆነ እንዲሆንም ተደንግጓል፡፡
በሌላ በኩል አንድ ግብር ከፋይ ግብር ከከፈለ በኋላ በ10 አመት ጊዜ ውስጥ በማንኛው ጊዜ እንደገና ሂሳቡ ተመርምሮ ወይም በኦዲት ተጨማሪ ግብር ሊጠየቅ ይችላል ይላል የረቂቅ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
ይህም በ10 ዓመት የተገደበው በኢትዮጵያ የንግድ ህግና የሂሳብ አያያዝ ህጎች መሰረት የሂሳብ ሰነዶች ተጠብቀው መቆየት ያለባቸው ለ10 ዓመታት ብቻ በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡
ሌላው የታክስ አስተዳደር አዋጁ ማሻሻያ የያዘው አዲስ ነገር በታክስ ባለስልጣኑ እና በታክስ ከፋዩ መካከል የሚፈጠርን አለመግባባት መፍቻ ዘዴን ይመለከታል፡፡
ከዚህ ቀደም በነበረው ህግ ግብር ከፋዮች የተጣለባቸውን ግብር ተገቢ አይደለም ብለው ባመኑ ጊዜ መፍትሄ ፍለጋ በታክስ አስተዳደሩ ስር ለተቋቋመ የቅሬታ ሰሚ ፣ ለግብር ይግባኝ ኮሚሽን እና የህግ ትርጉምን በተመለከተ በየደረጃው ባሉ ፍርድ ቤቶች እንዲመለከቱት የሚያስችል ስርዓት ነበር፡፡
ይህን ለማድረግ ግን ግብር ከፋዮች ቅድሚያ የተወሰነባቸውን ግብር ከ50 እስከ 75 በመቶ መክፈልም ይጠበቅባቸው ነበር፡፡
ያም ሆኖ መፍትሄ ለማግኘት ረዥም ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል በማብራሪያው ተጠቅሷል፡፡
በተሻሻለውና በረቂቅ ደረጃ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበው የታክስ አስተዳደር አዋጅ የተጠቀሰው አሰራር እንዳለ ሆኖ በአጭር ጊዜ አለመግባባቶችን ለመፍታት ያግዛል የተባለ የገለልተኛ አስማሚን አሰራር ስራ ላይ ያውላል ተብለዋል፡፡
ይህም አዲስ “የመስማማት ሥርዓት” በሚል አዋጁ እንዲዘረጋ በሚፈቅደው ገለልተኛ አስማሚ ግብር ከፋዩን እና ግብር ሰብሳቢውን በሚስጥራዊነት መርህዎች ጭምር የሚያስማማበት ሥርዓት ነው ተብሏል፡፡
#ሸገር ኤፍኤም
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
ዲያስፓራ አዳባባይ መገናኛ አካባቢ በደረሰዉ የተሽከርካሪ አደጋ ምክንያት አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገድ እንዲጠቀሙ ፖሊስ አሳሰበ!
ዲያስፓራ አዳባባይ መገናኛ አካባቢ በደረሰዉ የተሽከርካሪ አደጋ ምክንያት አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገድ እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳሰበ፡፡በአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የየካ ክፍለ ከተማ የትራፊክ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ጋሻ ሁነኝ ሙሉጌታ ለኤኤምኤን ዲጂታል እንደተናገሩት አደጋዉ 10፡30 አካባቢ በዲያስፓራ አዳባባይ በታክሲ ተርሚናሉ አካባቢ የደረሰ ሲሆን በአደጋዉ ሁለት ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዉ በህክምና ላይ ይገኛሉ፡፡
በታክሲ ተርሚናሉ ዉስጥ በተለምዶ ቅጥቅጥ የሚባለዉ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ወደ ኋላ ሲያሽከረክር ወድቆ ተንጠልጥሎ እንደሚገኝ ጨምረዉ ገልጸዋል፡፡ተሽከርካሪዉ በአሁኑ ወቅት ከላይኛዉ ትሚናል ወደ ታችኛዉ ተርሚናል ተንጠልጥሎ ይገኛል፡፡የእሳትና አደጋ መከላከል አሽከርካሪዎች በቦታዉ ደርሰዉ ተሽከርካሪዉን ለማንሳት ጥረት እያደረጉ መሆኑን የገለጹት ሃላፊዉ ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት ክትትል እየተደረገ ይገኛል፡፡
ከቀበና መጥተዉ ወደ ኮተቤ የሚሄዱ ተሽከርካሪዎች በሚናሮል ጀርባ በኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ባለዉ አማራጭ መንገድ እንዲጠቀሙ አሳስበዋል፡፡የትራፊክ ፖሊሶች በአካባቢዉ የትራፊክ እንቅስቃሴዉን በማሳላጥ ላይ እንደሚገኙም የየካ ክፍለ ከተማ የትራፊክ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ጋሻ ሁነኝ ሙሉጌታ ለኤኤምኤን ዲጂታልተናግረዋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
ዲያስፓራ አዳባባይ መገናኛ አካባቢ በደረሰዉ የተሽከርካሪ አደጋ ምክንያት አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገድ እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳሰበ፡፡በአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የየካ ክፍለ ከተማ የትራፊክ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ጋሻ ሁነኝ ሙሉጌታ ለኤኤምኤን ዲጂታል እንደተናገሩት አደጋዉ 10፡30 አካባቢ በዲያስፓራ አዳባባይ በታክሲ ተርሚናሉ አካባቢ የደረሰ ሲሆን በአደጋዉ ሁለት ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዉ በህክምና ላይ ይገኛሉ፡፡
በታክሲ ተርሚናሉ ዉስጥ በተለምዶ ቅጥቅጥ የሚባለዉ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ወደ ኋላ ሲያሽከረክር ወድቆ ተንጠልጥሎ እንደሚገኝ ጨምረዉ ገልጸዋል፡፡ተሽከርካሪዉ በአሁኑ ወቅት ከላይኛዉ ትሚናል ወደ ታችኛዉ ተርሚናል ተንጠልጥሎ ይገኛል፡፡የእሳትና አደጋ መከላከል አሽከርካሪዎች በቦታዉ ደርሰዉ ተሽከርካሪዉን ለማንሳት ጥረት እያደረጉ መሆኑን የገለጹት ሃላፊዉ ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት ክትትል እየተደረገ ይገኛል፡፡
ከቀበና መጥተዉ ወደ ኮተቤ የሚሄዱ ተሽከርካሪዎች በሚናሮል ጀርባ በኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ባለዉ አማራጭ መንገድ እንዲጠቀሙ አሳስበዋል፡፡የትራፊክ ፖሊሶች በአካባቢዉ የትራፊክ እንቅስቃሴዉን በማሳላጥ ላይ እንደሚገኙም የየካ ክፍለ ከተማ የትራፊክ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ጋሻ ሁነኝ ሙሉጌታ ለኤኤምኤን ዲጂታልተናግረዋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
u12e8u121du123du1275 2 u1230u12d3u1275 u12a0u121bu122du129b u12dcu1293 u2026 u130du1295u1266u1275 27/2018 u12d3.u121d #ebcdotstream #etv #ethiopia #etv57 ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የምሽት 2 ሰዓት አማርኛ ዜና … ግንቦት 27/2018 ዓ.ም #ebcdotstream #etv #ethiopia #etv57
2 days ago
u12a2u1272u126a 57 u2026 u130du1295u1266u1275 27/2018 u12d3.u121d #ebcdotstream #etv #ethiopia #etv57 ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ኢቲቪ 57 … ግንቦት 27/2018 ዓ.ም #ebcdotstream #etv #ethiopia #etv57
2 days ago
የቻይናው ኩባንያ የአዲስአበባ አውቶቡሶችን ወደ ተፈጥሮ ጋዝ ተሽከርካሪዎች የመቀየር ሥራ ጀመረ
ኢትዮጵያ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችን ከናፍጣ ወደ ተፈጥሮ ጋዝ ለመቀየር የሚያስችል መጠነ ሰፊ ፕሮግራም የጀመረች ሲሆን፥ በቻይናው ኩባንያ የመጀመሪያው ማሻሻያ የተደረገለት አውቶቡስ በአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ፍተሻውን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን ቻይና ዴይሊ ዘግቧል።
በቻይናው ጂሲኤል አፍሪካ ኢንዱስትሪያል ግሩፕ የሚመራው ይህ መርሃ ግብር፥ ኢትዮጵያ ከውጭ በሚገባ ነዳጅ ላይ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ እና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆነ የሕዝብ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የምታደርገው ሰፊ ጥረት አካል ነው ተብሏል።
ቻይና ዴይሊ እንደዘገበው፤ ፕሮጀክቱ፤ በአዲስ አበባ አገልግሎት የሚሰጡ ከ2,000 በላይ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችን በስምንት ወራት ውስጥ ለመቀየር ያለመ ነው።
በተጨማሪም የመንግሥት ንብረት የሆኑ የመርሴዲስ ቤንዝ አውቶቡሶችን ለመቀየር ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
Seledadotio
Seledadotio
ኢትዮጵያ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችን ከናፍጣ ወደ ተፈጥሮ ጋዝ ለመቀየር የሚያስችል መጠነ ሰፊ ፕሮግራም የጀመረች ሲሆን፥ በቻይናው ኩባንያ የመጀመሪያው ማሻሻያ የተደረገለት አውቶቡስ በአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ፍተሻውን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን ቻይና ዴይሊ ዘግቧል።
በቻይናው ጂሲኤል አፍሪካ ኢንዱስትሪያል ግሩፕ የሚመራው ይህ መርሃ ግብር፥ ኢትዮጵያ ከውጭ በሚገባ ነዳጅ ላይ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ እና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆነ የሕዝብ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የምታደርገው ሰፊ ጥረት አካል ነው ተብሏል።
ቻይና ዴይሊ እንደዘገበው፤ ፕሮጀክቱ፤ በአዲስ አበባ አገልግሎት የሚሰጡ ከ2,000 በላይ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችን በስምንት ወራት ውስጥ ለመቀየር ያለመ ነው።
በተጨማሪም የመንግሥት ንብረት የሆኑ የመርሴዲስ ቤንዝ አውቶቡሶችን ለመቀየር ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ነዳጅ በሁለት ዶላር ቀነሰ።
የነዳጅ ዋጋ በአለማቀፍ ደረጃ መጠነኛ ቅናሽ አሳየ።
የዋጋ ቅናሽ የተስተዋለው እስራኤል እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነት ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው።
አንድ ብሬንት ነዳጅ በርሚል 67 ሳንቲም ወይም 0.69 % ቅናሽ አሳይቷል ተብሏል።
በ97.14 ዶላር ሲሸጥ የነበረው አንድ በርሚል ነዳጅ ወደ 95.40 ዝቅ ማለቱ ተመላክቷል።
Seledadotio
Seledadotio
የነዳጅ ዋጋ በአለማቀፍ ደረጃ መጠነኛ ቅናሽ አሳየ።
የዋጋ ቅናሽ የተስተዋለው እስራኤል እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነት ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው።
አንድ ብሬንት ነዳጅ በርሚል 67 ሳንቲም ወይም 0.69 % ቅናሽ አሳይቷል ተብሏል።
በ97.14 ዶላር ሲሸጥ የነበረው አንድ በርሚል ነዳጅ ወደ 95.40 ዝቅ ማለቱ ተመላክቷል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
2 days ago
"የአርሲው ጥቃት በሸኔ ታጣቂዎች የተፈጸመ ነው"፦ አቶ ሀይሉ አዱኛ
"የአርሲው ጥቃት ምርጫውን ለማደናቀፍ በሸኔ ታጣቂዎች የተፈጸመ ነው" የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ።
በጥቃቱ ከዚህም በላይ ጉዳት እንዳይደርስ ህዝቡና የኦሮሚያ ክልል የፀጥታ ሀይል መስዋዕትነት ከፍሏል ብለዋል። አሸባሪው ሸኔ ይህንን ጥቃት ያደረሰው ከታሪካዊ ጠላቶች ተልዕኮ ተቀብሎ የሀይማኖት ግጭት ለማስነሳት የነበረ ቢሆንም በህዝቡ አስተዋይነት ከሽፏል ብለዋል።
መከላከያ ሰራዊት፣የፌዴራል ፖሊስ የኦሮሚያ ክልል የፀጥታ ሀይል የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ እና አካባቢውን ለማረጋጋት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
"የአርሲው ጥቃት ምርጫውን ለማደናቀፍ በሸኔ ታጣቂዎች የተፈጸመ ነው" የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ።
በጥቃቱ ከዚህም በላይ ጉዳት እንዳይደርስ ህዝቡና የኦሮሚያ ክልል የፀጥታ ሀይል መስዋዕትነት ከፍሏል ብለዋል። አሸባሪው ሸኔ ይህንን ጥቃት ያደረሰው ከታሪካዊ ጠላቶች ተልዕኮ ተቀብሎ የሀይማኖት ግጭት ለማስነሳት የነበረ ቢሆንም በህዝቡ አስተዋይነት ከሽፏል ብለዋል።
መከላከያ ሰራዊት፣የፌዴራል ፖሊስ የኦሮሚያ ክልል የፀጥታ ሀይል የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ እና አካባቢውን ለማረጋጋት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
ኤርትራ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆና ተመረጠች
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በ85ኛው መደበኛ ስብሰባው ላይ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ ቁልፍ አጀንዳዎችን የተወያየ ሲሆን፣ በስብሰባውም ለድርጅቱ 81ኛ ጠቅላላ ጉባኤ መሪ የሚሆኑትን አካላት መርጧል።
በዚህም መሰረት የምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ኤርትራ የከፍተኛ አባል ሀገራትን ድምጽ በማግኘት ከጠቅላላ ጉባኤው ምክትል ፕሬዝዳንቶች አንዷ ሆና
ኤርትራ ከተመረጡ ሌሎች 16 አገራት ጋር በመሆን የጸጥታው ምክር ቤት አምስት ቋሚ አባላትን (ቻይና፣ ፈረንሳይ፣ ሩሲያ፣ ብሪታንያ እና አሜሪካ) በመቀላቀል የጠቅላላ ጉባኤውን ቢሮ በጋራ ትመራለች።
በተጨማሪም ከእሷ ጋር እንደ አፍጋኒስታን፣ ፊንላንድ፣ ግብፅ፣ ሊባኖስ፣ ፓራጓይ እና ዚምባብዌ ያሉ ሀገራትም በምክትል ፕሬዝዳንትነት መመረጣቸውን ለመረዳት ተችሏል።
በተመሳሳይ ዕለት በምስጢር በተካሄደው የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት፣ የወቅቱ የባንግላዲሽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካሊሉር ራህማን የ81ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል
ሚስተር ራህማን 99 ድምጽ በማግኘት የተመረጡ ሲሆን፣ ተፎካካሪያቸውን የቆጵሮሱን አንድሪያስ ካኩሪስን በ91 ድምጽ አሸንፈዋል። በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ሥራቸውን በይፋ የሚረከቡት ተመራጩ ፕሬዝዳንት ካሊሉር ራህማን ከአሸናፊነታቸው በኋላ ባደረጉት ንግግር፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአሁኑ ወቅት ከባድ የፋይናንስ ቀውስ እና ዓለም አቀፍ የእምነት ማጣት ጉድለት እየገጠመው መሆኑን ጠቅሰው፣ አባል ሀገራቱ ድርጅቱ መለወጥና የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በተግባር ማሳየት እንዳለባቸውና በየብስ የሚደረገውን እያንዳንዱን አስተዋጽኦ ውጤታማ በማድረግ የጠፋውን እምነት መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል
Seledadotio
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በ85ኛው መደበኛ ስብሰባው ላይ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ ቁልፍ አጀንዳዎችን የተወያየ ሲሆን፣ በስብሰባውም ለድርጅቱ 81ኛ ጠቅላላ ጉባኤ መሪ የሚሆኑትን አካላት መርጧል።
በዚህም መሰረት የምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ኤርትራ የከፍተኛ አባል ሀገራትን ድምጽ በማግኘት ከጠቅላላ ጉባኤው ምክትል ፕሬዝዳንቶች አንዷ ሆና
ኤርትራ ከተመረጡ ሌሎች 16 አገራት ጋር በመሆን የጸጥታው ምክር ቤት አምስት ቋሚ አባላትን (ቻይና፣ ፈረንሳይ፣ ሩሲያ፣ ብሪታንያ እና አሜሪካ) በመቀላቀል የጠቅላላ ጉባኤውን ቢሮ በጋራ ትመራለች።
በተጨማሪም ከእሷ ጋር እንደ አፍጋኒስታን፣ ፊንላንድ፣ ግብፅ፣ ሊባኖስ፣ ፓራጓይ እና ዚምባብዌ ያሉ ሀገራትም በምክትል ፕሬዝዳንትነት መመረጣቸውን ለመረዳት ተችሏል።
በተመሳሳይ ዕለት በምስጢር በተካሄደው የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት፣ የወቅቱ የባንግላዲሽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካሊሉር ራህማን የ81ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል
ሚስተር ራህማን 99 ድምጽ በማግኘት የተመረጡ ሲሆን፣ ተፎካካሪያቸውን የቆጵሮሱን አንድሪያስ ካኩሪስን በ91 ድምጽ አሸንፈዋል። በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ሥራቸውን በይፋ የሚረከቡት ተመራጩ ፕሬዝዳንት ካሊሉር ራህማን ከአሸናፊነታቸው በኋላ ባደረጉት ንግግር፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአሁኑ ወቅት ከባድ የፋይናንስ ቀውስ እና ዓለም አቀፍ የእምነት ማጣት ጉድለት እየገጠመው መሆኑን ጠቅሰው፣ አባል ሀገራቱ ድርጅቱ መለወጥና የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በተግባር ማሳየት እንዳለባቸውና በየብስ የሚደረገውን እያንዳንዱን አስተዋጽኦ ውጤታማ በማድረግ የጠፋውን እምነት መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 days ago
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ስርጭት
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል።
እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል።
የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።
በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴሊሺየስ በላይ ይሆናል።
Seledadotio
Seledadotio
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል።
እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል።
የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።
በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴሊሺየስ በላይ ይሆናል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
ሕወሃት አዲስ አውዳሚ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አስቸኳይ ጥሪ አቀረበ።
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
ኢትዮጵያና አይ ኤም ኤፍ (አይኤምኤፍ) የ468 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደረሱ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመው የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ በባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።
ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት ሳምንታት በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሙሉ በሙሉ ሲጸድቅ፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል።
ይህም ሀገሪቱ በ4 ዓመታት ውስጥ ከምታገኘው የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ውስጥ እስካሁን የተለቀቀላትን የገንዘብ መጠን ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ ስምምነቱ ሊደረስ የተቻለው ከአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የድርጅቱ ልዑክ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባደረገው የሁለት ሳምንታት ጉብኝትና ተከታታይ የሥራ ውይይቶች ማጠናቀቂያ ላይ ነው።
በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት መግለጫ ላይ እንደተመለከተው ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከቀጠናዊ ቀውሶች ጋር ተያይዞ የመጣውን ትልቅ ውጫዊ ጫና በመቋቋም ረገድ ከፍተኛ ጥንካሬ አሳይቷል።
ይሁን እንጂ፣ ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ አሁንም እያደገ በመምጣቱ በኢኮኖሚው የወደፊት ጉዞ ላይ የሚታዩት ስጋቶች መጨመራቸውን አይ ኤም ኤፍ አስጠንቅቋል።
የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መረጋጋት በዘላቂነት ለማስቀጠልም ድርጅቱ ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቁልፍ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን የጠቆመ ሲሆን፣ ይህም የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን አጠናክሮ መቀጠልን፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ግልጽነትና አሠራር ይበልጥ ማሻሻልን እንዲሁም የአገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን በማጠናከር የወጪ አያያዝን በጥንቃቄ መምራት አስፈላጊ መሆኑን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመው የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ በባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።
ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት ሳምንታት በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሙሉ በሙሉ ሲጸድቅ፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል።
ይህም ሀገሪቱ በ4 ዓመታት ውስጥ ከምታገኘው የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ውስጥ እስካሁን የተለቀቀላትን የገንዘብ መጠን ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ ስምምነቱ ሊደረስ የተቻለው ከአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የድርጅቱ ልዑክ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባደረገው የሁለት ሳምንታት ጉብኝትና ተከታታይ የሥራ ውይይቶች ማጠናቀቂያ ላይ ነው።
በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት መግለጫ ላይ እንደተመለከተው ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከቀጠናዊ ቀውሶች ጋር ተያይዞ የመጣውን ትልቅ ውጫዊ ጫና በመቋቋም ረገድ ከፍተኛ ጥንካሬ አሳይቷል።
ይሁን እንጂ፣ ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ አሁንም እያደገ በመምጣቱ በኢኮኖሚው የወደፊት ጉዞ ላይ የሚታዩት ስጋቶች መጨመራቸውን አይ ኤም ኤፍ አስጠንቅቋል።
የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መረጋጋት በዘላቂነት ለማስቀጠልም ድርጅቱ ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቁልፍ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን የጠቆመ ሲሆን፣ ይህም የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን አጠናክሮ መቀጠልን፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ግልጽነትና አሠራር ይበልጥ ማሻሻልን እንዲሁም የአገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን በማጠናከር የወጪ አያያዝን በጥንቃቄ መምራት አስፈላጊ መሆኑን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
Comments