Logo
Getu Temesgen
“በኢ-ፍትሐዊነት የተዘጋብንን የባህር በር በማስከፈት የራሳችንን ታላቅ ታሪክ ሰርቶ ለማለፍ በቁጭት እንነሳ”
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
#ethiopia | በኢ-ፍትሐዊነት የተዘጋብንን የባሕር በር በማስከፈት የቀድሞ አርበኞቻችንን ታሪክ ከመዘከር ባለፈ ይህ ትውልድ የራሱን ታላቅ ታሪክ ሠርቶ ለማለፍ በቁጭት ሊነሳ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባዋ ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል መሪ ቃል በመላው ኢትዮጵያ በድምቀት እየተከበረ በሚገኝበት ወቅት ሲሆን፤ ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦችና የአፍሪካውያን የነፃነት ፋና መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያውያን በውስጣዊ ጉዳዮች ልዩነት ቢኖራቸውም፣ በሀገር ሉዓላዊነትና በብሔራዊ ክብር ላይ ግን በጋራ መቆም እንዳለባቸው ዓድዋ ትልቅ ቁምነገር ያስተማረበት መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።

የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍንም በበኩላቸው፤ በደምና በአጥንታቸው ሀገርን ላቆዩ ጀግኖች ተገቢውን ክብር መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #ዓድዋ #የባሕር_በር #ጀግንነት #አዳነች_አቤቤ #ዳንኤል_ጆቴ #አርበኝነት

3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.