2 days ago
የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሪ ተወልደ ገብረማሪያም የኤር ኢንዲያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ
የሕንድ ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ የቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፋሚ ተወልደ ወልደማሪያምን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከአስር ዓመት በላይ የመሩት እና አየር መንገዱን ከአፍሪካ ግዙፉ እንዲሁም ቀዳሚው በማድረግ አሁን ከደረሰበት ደረጃ ላይ በማድረስ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ተወልደ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያካሄደውን የባለ ብዙ ሚሊዮን ዶላር ማስፋፋት እና ባለ ብዙ አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ያስቻሉ መሆናቸው ይነገራል።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬት ላይ ብቻ ሳይሆን ፈተናዎች በገጠሙት ጊዜ ተቋሙ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ በስኬት እንዲያልፍ አድርገዋል።
በተለይም በአየር መንገዱ ታሪክ ውስጥ ከባድ በነበሩት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት በርካታ አየር መንገዶች ለኪሳራ እና ከሥራ ውጪ ለመሆን ሲገደዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሥራው ላይ ለውጥ በማድረግ ትርፋማ ለመሆን አስችለውታል።
በተጨማሪም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር ተከስክሶ ሁሉም መንገደኞች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ከሞቱበት የቦይን 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ወቅት የአየር መንገዱን ጥንካሬ ዝና ጠብቀው ከቀውሱ ለመውጣት መቻላቸው ከሚጠቀሱላችው ስኬቶቻቸው መካከል ናቸው።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም አሁን የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ቦታ የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ አየር መንገድ ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት አውሮፕላኑ ተከስክሶ 260 መንገደኞች ከሞቱ በኋላ በከባድ ፈተና ውስጥ ይገኛል።
አየር መንገዱ በተጨማሪም ከፍተኛ የገንዘብ እና የሥራውን የማካሄድ ፈተና የገጠመው ሲሆን፣ ከደረሰበት አደጋ ተያይዞ በአቪየሽን ተቆጣጣሪ አካላት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግበት ነው።
አቶ ተወልደ የመሪነት ኃላፊነቱን የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ በሚያጓጉዛቸው መንገደኞች ብዛት በሕንድ ውስጥ ካሉ አየር መንገዶች ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ ነው።
ታታ ግሩፕ 75 በመቶ የባለቤትንት ድርሻውን እንዲሁም የሴንጋፖር አየር መንገድ 25 ባለቤትነት ያለው ወደ 200 የሚጠጉ አውሮፕላኖች እና ከ31 ሺህ በላይ ሠራተኞች የሚሰስተደድረው አየር መንገዱ ወደ 90 ዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ የበረራ መስመሮች አሉት።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት አቶ ተወልደ ገብረማሪያም የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት በጥር 2003 ዓ.ም. ነበረ።
አቶ ተወልደ በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ዘላቂነት ባለው ትራንስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የአማካሪዎች ቡድን አባል ሆነው ሠርተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አባል በሆነበት የስታር አሊያንስ ዋና የቦርድ አባል፣ የዓለም አቀፉ የትራንስፖርት ማኅበር (አይኤቲኤ) የቦርድ አባል በተጨማሪም የአፍሪካ የአየር መንገዶች ማኅበር (ኤኤፍአርኤኤ) የዋና ኮሚቴ አባል በመሆን አገልግለዋል።
አቶ ተወልደ የአፍሪካ የጉዞ ማኅበር (ኤቲኤ) የቦርድ አባል እና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት (ኢቲኦ) የዳይሬክተሮች ቦርድ አባልም ነበሩ።
አቶ ተወልደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ባገለገሉባቸው በርካታ ዓመታት የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
ከሽልማቶቹ መካከል የዓመቱ የአፍሪካ ምርጥ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ምርጥ የአፍሪካ የቢዝነስ መሪ፣ የቀጣናዊ የአየር መንገድ አመራር ሽልማት እንዲሁም ምርጥ ፆታን ያማከለ ሥራ አስፈፃሚ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢኮኖሚክስ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከዩናይትድ ኪንግደም ኦፕን ዩኒቨርስቲ በንግድ አስተዳደር ያገኙ ሲሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬትም ተበርክቶላቸዋል።
አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም ከአስር ዓመት በላይ በስኬት የመሩትን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የለቀቁት በጤና ሁኔታን በምክንያት ጠቅሰው በ2014 ዓ.ም. ነበር።
BBC
የሕንድ ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ የቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፋሚ ተወልደ ወልደማሪያምን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከአስር ዓመት በላይ የመሩት እና አየር መንገዱን ከአፍሪካ ግዙፉ እንዲሁም ቀዳሚው በማድረግ አሁን ከደረሰበት ደረጃ ላይ በማድረስ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ተወልደ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያካሄደውን የባለ ብዙ ሚሊዮን ዶላር ማስፋፋት እና ባለ ብዙ አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ያስቻሉ መሆናቸው ይነገራል።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬት ላይ ብቻ ሳይሆን ፈተናዎች በገጠሙት ጊዜ ተቋሙ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ በስኬት እንዲያልፍ አድርገዋል።
በተለይም በአየር መንገዱ ታሪክ ውስጥ ከባድ በነበሩት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት በርካታ አየር መንገዶች ለኪሳራ እና ከሥራ ውጪ ለመሆን ሲገደዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሥራው ላይ ለውጥ በማድረግ ትርፋማ ለመሆን አስችለውታል።
በተጨማሪም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር ተከስክሶ ሁሉም መንገደኞች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ከሞቱበት የቦይን 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ወቅት የአየር መንገዱን ጥንካሬ ዝና ጠብቀው ከቀውሱ ለመውጣት መቻላቸው ከሚጠቀሱላችው ስኬቶቻቸው መካከል ናቸው።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም አሁን የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ቦታ የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ አየር መንገድ ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት አውሮፕላኑ ተከስክሶ 260 መንገደኞች ከሞቱ በኋላ በከባድ ፈተና ውስጥ ይገኛል።
አየር መንገዱ በተጨማሪም ከፍተኛ የገንዘብ እና የሥራውን የማካሄድ ፈተና የገጠመው ሲሆን፣ ከደረሰበት አደጋ ተያይዞ በአቪየሽን ተቆጣጣሪ አካላት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግበት ነው።
አቶ ተወልደ የመሪነት ኃላፊነቱን የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ በሚያጓጉዛቸው መንገደኞች ብዛት በሕንድ ውስጥ ካሉ አየር መንገዶች ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ ነው።
ታታ ግሩፕ 75 በመቶ የባለቤትንት ድርሻውን እንዲሁም የሴንጋፖር አየር መንገድ 25 ባለቤትነት ያለው ወደ 200 የሚጠጉ አውሮፕላኖች እና ከ31 ሺህ በላይ ሠራተኞች የሚሰስተደድረው አየር መንገዱ ወደ 90 ዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ የበረራ መስመሮች አሉት።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት አቶ ተወልደ ገብረማሪያም የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት በጥር 2003 ዓ.ም. ነበረ።
አቶ ተወልደ በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ዘላቂነት ባለው ትራንስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የአማካሪዎች ቡድን አባል ሆነው ሠርተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አባል በሆነበት የስታር አሊያንስ ዋና የቦርድ አባል፣ የዓለም አቀፉ የትራንስፖርት ማኅበር (አይኤቲኤ) የቦርድ አባል በተጨማሪም የአፍሪካ የአየር መንገዶች ማኅበር (ኤኤፍአርኤኤ) የዋና ኮሚቴ አባል በመሆን አገልግለዋል።
አቶ ተወልደ የአፍሪካ የጉዞ ማኅበር (ኤቲኤ) የቦርድ አባል እና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት (ኢቲኦ) የዳይሬክተሮች ቦርድ አባልም ነበሩ።
አቶ ተወልደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ባገለገሉባቸው በርካታ ዓመታት የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
ከሽልማቶቹ መካከል የዓመቱ የአፍሪካ ምርጥ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ምርጥ የአፍሪካ የቢዝነስ መሪ፣ የቀጣናዊ የአየር መንገድ አመራር ሽልማት እንዲሁም ምርጥ ፆታን ያማከለ ሥራ አስፈፃሚ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢኮኖሚክስ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከዩናይትድ ኪንግደም ኦፕን ዩኒቨርስቲ በንግድ አስተዳደር ያገኙ ሲሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬትም ተበርክቶላቸዋል።
አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም ከአስር ዓመት በላይ በስኬት የመሩትን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የለቀቁት በጤና ሁኔታን በምክንያት ጠቅሰው በ2014 ዓ.ም. ነበር።
BBC
4 days ago
"ሁለተኛው የስልጣን ዘመኔ ልክ እንደ ኢየሱስ መመለስ ነው!"
– የፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ንግግር በኬንያ አነጋጋሪ ሆነ
አዲስ አበባ – የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ሁለተኛ የስልጣን ዘመንን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሁለተኛ መምጣት ጋር በማያያዝ የተናገሩት ንግግር በኬንያ የፖለቲካ እና የሃይማኖት ውይይቶችን አቀጣጥሏል።
ፕሬዚዳንቱ በናይሮቢ ጊኮምባ በተካሄደ የቤተ ክርስቲያን መርሃ ግብር ላይ ለደጋፊዎቻቸው የፖለቲካ መፈክር የሆነውን "Tutam" በመጥቀስ፣ "ኢየሱስ ለሁለተኛ ጊዜ ይመጣል፤ ስለዚህ 'Tutam' ስትሉ ለዚያም ዝግጁ ሁኑ" በማለት ንግግር አድርገዋል።
እንዲሁም "ምድራዊ Tutam አለ፣ ሰማያዊ Tutam አለ" በማለት የፖለቲካ መፈክሩን ከክርስቲያናዊ ትምህርት ጋር ለማገናኘት ሞክረዋል።
ይህ ንግግር በማኅበራዊ ሚዲያ ፈጣን ምላሽ አስከትሏል። አንዳንዶች ፕሬዚዳንቱ የመንፈሳዊ መልእክት ለማስተላለፍ እንደሞከሩ ሲገልጹ፣ ሌሎች ግን የሃይማኖት ምሳሌዎችን ለፖለቲካ ዘመቻ መጠቀም ተገቢ አይደለም ሲሉ ተችተዋል።
"Tutam" የሚለው ቃል በሩቶ ደጋፊዎች መካከል "ሁለተኛ ዘመን እናሸንፋለን" የሚል የፖለቲካ መፈክር ሲሆን፣ ተቃዋሚዎቹ ደግሞ "Wantam" (አንድ ዘመን ብቻ) በሚል መፈክር ለ2027 ምርጫ ዘመቻቸውን እያጠናከሩ ነው። ይህም በኬንያ ፖለቲካ ውስጥ በጣም አነጋጋሪ የሆኑ መፈክሮች ሆነዋል።
የ2027 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እየተቃረበ በመምጣቱ፣ ሩቶ ሁለተኛ ዘመን ለማሸነፍ በግልጽ እየዘመቱ ሲሆን፣ ተቃዋሚዎቻቸውም "Wantam" በሚል መፈክር የስልጣን ለውጥ እየጠየቁ ነው። የፖለቲካ ውድድሩ ቀድሞውኑ ወደ ከፍተኛ ሙቀት ገብቷል።
የሩቶ የቅርብ ጊዜ ንግግር ደግሞ በኬንያ ውስጥ የፖለቲካና የሃይማኖት ግንኙነት እንደገና የውይይት ርዕስ እንዲሆን አድርጎታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
– የፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ንግግር በኬንያ አነጋጋሪ ሆነ
አዲስ አበባ – የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ሁለተኛ የስልጣን ዘመንን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሁለተኛ መምጣት ጋር በማያያዝ የተናገሩት ንግግር በኬንያ የፖለቲካ እና የሃይማኖት ውይይቶችን አቀጣጥሏል።
ፕሬዚዳንቱ በናይሮቢ ጊኮምባ በተካሄደ የቤተ ክርስቲያን መርሃ ግብር ላይ ለደጋፊዎቻቸው የፖለቲካ መፈክር የሆነውን "Tutam" በመጥቀስ፣ "ኢየሱስ ለሁለተኛ ጊዜ ይመጣል፤ ስለዚህ 'Tutam' ስትሉ ለዚያም ዝግጁ ሁኑ" በማለት ንግግር አድርገዋል።
እንዲሁም "ምድራዊ Tutam አለ፣ ሰማያዊ Tutam አለ" በማለት የፖለቲካ መፈክሩን ከክርስቲያናዊ ትምህርት ጋር ለማገናኘት ሞክረዋል።
ይህ ንግግር በማኅበራዊ ሚዲያ ፈጣን ምላሽ አስከትሏል። አንዳንዶች ፕሬዚዳንቱ የመንፈሳዊ መልእክት ለማስተላለፍ እንደሞከሩ ሲገልጹ፣ ሌሎች ግን የሃይማኖት ምሳሌዎችን ለፖለቲካ ዘመቻ መጠቀም ተገቢ አይደለም ሲሉ ተችተዋል።
"Tutam" የሚለው ቃል በሩቶ ደጋፊዎች መካከል "ሁለተኛ ዘመን እናሸንፋለን" የሚል የፖለቲካ መፈክር ሲሆን፣ ተቃዋሚዎቹ ደግሞ "Wantam" (አንድ ዘመን ብቻ) በሚል መፈክር ለ2027 ምርጫ ዘመቻቸውን እያጠናከሩ ነው። ይህም በኬንያ ፖለቲካ ውስጥ በጣም አነጋጋሪ የሆኑ መፈክሮች ሆነዋል።
የ2027 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እየተቃረበ በመምጣቱ፣ ሩቶ ሁለተኛ ዘመን ለማሸነፍ በግልጽ እየዘመቱ ሲሆን፣ ተቃዋሚዎቻቸውም "Wantam" በሚል መፈክር የስልጣን ለውጥ እየጠየቁ ነው። የፖለቲካ ውድድሩ ቀድሞውኑ ወደ ከፍተኛ ሙቀት ገብቷል።
የሩቶ የቅርብ ጊዜ ንግግር ደግሞ በኬንያ ውስጥ የፖለቲካና የሃይማኖት ግንኙነት እንደገና የውይይት ርዕስ እንዲሆን አድርጎታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኦገስት 1 ቀን 2026 ጀምሮ ከሰሃራ በታች ባሉ 25 የአፍሪካ ሀገራት በሚገኙ ዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች የሚሰጠውን መደበኛ የቪዛ ማስተናገጃ አገልግሎት ማቋረጡን አስታውቋል። የትራምፕ አስተዳደር ይህንን ውሳኔ በቅርብ ታሪክ ውስጥ ከተደረጉት የአሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ የቪዛ አገልግሎቶች ትልቁ የማሻሻያ መርሃ ግብር ሲል ገልጾታል።
በአዲሱ አሰራር መሰረት የቪዛ አመልካቾች ከዚህ በኋላ በአቅራቢያቸው በሚገኝ የአሜሪካ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ጽህፈት ቤት ቀጠሮ መያዝም ሆነ የቪዛ ሂደታቸውን ማጠናቀቅ አይችሉም። ከዚህ ይልቅ በአህጉሪቱ ወደተመደቡ 20 ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት እንዲያቀኑ ይደረጋል።
የቪዛ አገልግሎታቸው የተቋረጠባቸው 25ቱ ሚሲዮኖች አቡጃ (ናይጄሪያ)፣ አንታናናሪቮ (ማዳጋስካር)፣ አስመራ (ኤርትራ)፣ ባማኮ (ማሊ)፣ ባንጁል (ጋምቢያ)፣ ብራዛቪል (የኮንጎ ሪፐብሊክ)፣ ቡጁምቡራ (ብሩንዲ)፣ ኮናክሪ (ጊኒ)፣ ኮቶኑ (ቤኒን)፣ ደርባን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ፍሪታውን (ሴራሊዮን)፣ ጋቦሮኔ (ቦትስዋና)፣ ሃራሬ (ዚምባብዌ)፣ ጁባ (ደቡብ ሱዳን)፣ ሊብረቪል (ጋቦን)፣ ሊሎንግዌ (ማላዊ)፣ ሉሳካ (ዛምቢያ)፣ ማፑቶ (ሞዛምቢክ)፣ ማሴሩ (ሌሴቶ)፣ ምባባኔ (ኤስዋቲኒ)፣ ንጃሜና (ቻድ)፣ ኒያሜይ (ኒጀር)፣ ኑዋክሾት (ሞሪታኒያ)፣ ዋጋዱጉ (ቡርኪና ፋሶ) እና ዊንድሆክ (ናሚቢያ) ናቸው። በደቡብ አፍሪካ ደርባን የሚገኘው የቪዛ ማዕከል ቢዘጋም፣ በኬፕታውን የሚሰጠው ተመሳሳይ አገልግሎት ግን ሳይቋረጥ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
20ዎቹ አዳዲስ ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት በአቢጃን፣ አክራ፣ አዲስ አበባ፣ ኬፕታውን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ዳካር፣ ዳሬሰላም፣ ጅቡቲ፣ ጆሃንስበርግ፣ ካምፓላ፣ ኪጋሊ፣ ኪንሻሳ፣ ሌጎስ፣ ሎሜ፣ ሉዋንዳ፣ ማላቦ፣ ሞንሮቪያ፣ ናይሮቢ፣ ፖርት ሉዊስ፣ ፕራያ እና ያውንዴ የሚገኙ ይሆናሉ። እያንዳንዱ ማዕከል በርካታ ጎረቤት ሀገራትን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ ለምሳሌ ከማሊ የሚመጡ አመልካቾች በዳካር (ሴኔጋል)፣ እንዲሁም ከቤኒን እና ኒጀር የሚመጡት ደግሞ በሎሜ (ቶጎ) የቪዛ ሂደታቸውን እንዲያከናውኑ ይመራሉ።
ሚኒስቴሩ ውሳኔውን የትራምፕ አስተዳደር ብሔራዊ ደህንነትን ለማጠናከር፣ የማጣራት ሂደቶችን ወጥ ለማድረግ፣ የመንግስት ወጪን ለመቀነስ እና የአሰራር ቅልጥፍናን ለማሻሻል ከሚያደርገው ጥረት አንዱ አካል መሆኑን አብራርቷል። ተመሳሳይ የውህደት ስራዎች በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እና በአውሮፓ ክፍሎች ቀደም ሲል መከናወናቸውን የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ብሔራዊ ደህንነትን በማጠናከር እና የመንግስትን ብክነት በመቀነስ አሜሪካን እና አሜሪካውያንን እያስቀደሙ ነው ብሏል።
ይህ ማሻሻያ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የቪዛ ማመልከቻዎችን የሚያስተናግዱ የአሜሪካ ሚሲዮኖችን ቁጥር ከ50 ገደማ ወደ 20 ዝቅ ያደርገዋል። ይህ በአመልካቾች ላይ ጉልህ የሆነ ተግባራዊ ተጽእኖ የሚያሳድር ሲሆን፣ የአገር ውስጥ የቪዛ አገልግሎት በተቋረጠባቸው ሀገራት የሚገኙ ዜጎች በአካል ለሚደረግ ቃለ ምልልስ እና የጣት አሻራ (ባዮሜትሪክ) ምዝገባ አለም አቀፍ ድንበሮችን አቋርጠው ለመጓዝ ስለሚገደዱ ለተጨማሪ የትራንስፖርት እና የማረፊያ ወጪዎች ይዳረጋሉ።
በአዲሱ አሰራር መሰረት የቪዛ አመልካቾች ከዚህ በኋላ በአቅራቢያቸው በሚገኝ የአሜሪካ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ጽህፈት ቤት ቀጠሮ መያዝም ሆነ የቪዛ ሂደታቸውን ማጠናቀቅ አይችሉም። ከዚህ ይልቅ በአህጉሪቱ ወደተመደቡ 20 ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት እንዲያቀኑ ይደረጋል።
የቪዛ አገልግሎታቸው የተቋረጠባቸው 25ቱ ሚሲዮኖች አቡጃ (ናይጄሪያ)፣ አንታናናሪቮ (ማዳጋስካር)፣ አስመራ (ኤርትራ)፣ ባማኮ (ማሊ)፣ ባንጁል (ጋምቢያ)፣ ብራዛቪል (የኮንጎ ሪፐብሊክ)፣ ቡጁምቡራ (ብሩንዲ)፣ ኮናክሪ (ጊኒ)፣ ኮቶኑ (ቤኒን)፣ ደርባን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ፍሪታውን (ሴራሊዮን)፣ ጋቦሮኔ (ቦትስዋና)፣ ሃራሬ (ዚምባብዌ)፣ ጁባ (ደቡብ ሱዳን)፣ ሊብረቪል (ጋቦን)፣ ሊሎንግዌ (ማላዊ)፣ ሉሳካ (ዛምቢያ)፣ ማፑቶ (ሞዛምቢክ)፣ ማሴሩ (ሌሴቶ)፣ ምባባኔ (ኤስዋቲኒ)፣ ንጃሜና (ቻድ)፣ ኒያሜይ (ኒጀር)፣ ኑዋክሾት (ሞሪታኒያ)፣ ዋጋዱጉ (ቡርኪና ፋሶ) እና ዊንድሆክ (ናሚቢያ) ናቸው። በደቡብ አፍሪካ ደርባን የሚገኘው የቪዛ ማዕከል ቢዘጋም፣ በኬፕታውን የሚሰጠው ተመሳሳይ አገልግሎት ግን ሳይቋረጥ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
20ዎቹ አዳዲስ ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት በአቢጃን፣ አክራ፣ አዲስ አበባ፣ ኬፕታውን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ዳካር፣ ዳሬሰላም፣ ጅቡቲ፣ ጆሃንስበርግ፣ ካምፓላ፣ ኪጋሊ፣ ኪንሻሳ፣ ሌጎስ፣ ሎሜ፣ ሉዋንዳ፣ ማላቦ፣ ሞንሮቪያ፣ ናይሮቢ፣ ፖርት ሉዊስ፣ ፕራያ እና ያውንዴ የሚገኙ ይሆናሉ። እያንዳንዱ ማዕከል በርካታ ጎረቤት ሀገራትን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ ለምሳሌ ከማሊ የሚመጡ አመልካቾች በዳካር (ሴኔጋል)፣ እንዲሁም ከቤኒን እና ኒጀር የሚመጡት ደግሞ በሎሜ (ቶጎ) የቪዛ ሂደታቸውን እንዲያከናውኑ ይመራሉ።
ሚኒስቴሩ ውሳኔውን የትራምፕ አስተዳደር ብሔራዊ ደህንነትን ለማጠናከር፣ የማጣራት ሂደቶችን ወጥ ለማድረግ፣ የመንግስት ወጪን ለመቀነስ እና የአሰራር ቅልጥፍናን ለማሻሻል ከሚያደርገው ጥረት አንዱ አካል መሆኑን አብራርቷል። ተመሳሳይ የውህደት ስራዎች በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እና በአውሮፓ ክፍሎች ቀደም ሲል መከናወናቸውን የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ብሔራዊ ደህንነትን በማጠናከር እና የመንግስትን ብክነት በመቀነስ አሜሪካን እና አሜሪካውያንን እያስቀደሙ ነው ብሏል።
ይህ ማሻሻያ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የቪዛ ማመልከቻዎችን የሚያስተናግዱ የአሜሪካ ሚሲዮኖችን ቁጥር ከ50 ገደማ ወደ 20 ዝቅ ያደርገዋል። ይህ በአመልካቾች ላይ ጉልህ የሆነ ተግባራዊ ተጽእኖ የሚያሳድር ሲሆን፣ የአገር ውስጥ የቪዛ አገልግሎት በተቋረጠባቸው ሀገራት የሚገኙ ዜጎች በአካል ለሚደረግ ቃለ ምልልስ እና የጣት አሻራ (ባዮሜትሪክ) ምዝገባ አለም አቀፍ ድንበሮችን አቋርጠው ለመጓዝ ስለሚገደዱ ለተጨማሪ የትራንስፖርት እና የማረፊያ ወጪዎች ይዳረጋሉ።
6 days ago
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደርጉ ዘንድ ግብዣ እና የጸሎት ጥሪ ቀረበ
#ethiopia | ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዝደንት ባሳለፍነው ሰኔ ወር በቅድስት መንበር ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ ጋር ባደረጉት የካርዲናሎች ጉባኤ ለቅዱስነታቸው የግብዣ ጥሪ አቅርበዋል።
ብፁዕነታቸው በየአመቱ በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች ለሚደረገው የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሐዋርያዊ ጉዞ የአፍሪካ ቀንድ ዋና ማዕከል ወደሆነችው ኢትዮጵያ ጉብኝት እንዲያደርጉ ጥሪ እንደቀረበላቸው በመግለጽ ምዕመናን ለዚህ ምኞት መሳካት እንዲጸልዩ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ የዘመናት የታሪክ ባለቤት የሆነች፣ የአማኞች ሀገር፣ የአፍሪካ ማዕከል እና በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ2027 ለሚዘጋጀው 32ኛው የአየር ንብረት ጉባኤ (COP32) በአዘጋጅነት የተመረጠች ሀገር በመሆኗ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ በቀጣይ ዓመት ለሚኖራቸው ሐዋርያዊ ጉብኝት ኢትዮጵያን ማካተት እንዲቻል ጥሪ አቅርበዋል።
ከሐምሌ 11-19 ቀን 2018 ዓ.ም. በኬንያ ናይሮቢ በተካሔደው 21ኛው የምስራቅ አፍሪካ የጳጳሳት ጉባኤም ይህ ጥሪ ለርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ሌዎ 14ኛ መቅረቡ ተገልጿል።
ይህም ታላቅ እና የዘመናት የኢትዮጵያ ካቶሊካውያን ምኞት ምላሽ ይገኝ ዘንድ መላው ካቶሊካውያን እና በጎ ፍቃድ ያላቸው ሰዎች ሁሉ በጸሎት እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል #ethiopia #getutemesgen #getunews #catholic #popeleo
#ethiopia | ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዝደንት ባሳለፍነው ሰኔ ወር በቅድስት መንበር ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ ጋር ባደረጉት የካርዲናሎች ጉባኤ ለቅዱስነታቸው የግብዣ ጥሪ አቅርበዋል።
ብፁዕነታቸው በየአመቱ በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች ለሚደረገው የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሐዋርያዊ ጉዞ የአፍሪካ ቀንድ ዋና ማዕከል ወደሆነችው ኢትዮጵያ ጉብኝት እንዲያደርጉ ጥሪ እንደቀረበላቸው በመግለጽ ምዕመናን ለዚህ ምኞት መሳካት እንዲጸልዩ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ የዘመናት የታሪክ ባለቤት የሆነች፣ የአማኞች ሀገር፣ የአፍሪካ ማዕከል እና በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ2027 ለሚዘጋጀው 32ኛው የአየር ንብረት ጉባኤ (COP32) በአዘጋጅነት የተመረጠች ሀገር በመሆኗ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ በቀጣይ ዓመት ለሚኖራቸው ሐዋርያዊ ጉብኝት ኢትዮጵያን ማካተት እንዲቻል ጥሪ አቅርበዋል።
ከሐምሌ 11-19 ቀን 2018 ዓ.ም. በኬንያ ናይሮቢ በተካሔደው 21ኛው የምስራቅ አፍሪካ የጳጳሳት ጉባኤም ይህ ጥሪ ለርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ሌዎ 14ኛ መቅረቡ ተገልጿል።
ይህም ታላቅ እና የዘመናት የኢትዮጵያ ካቶሊካውያን ምኞት ምላሽ ይገኝ ዘንድ መላው ካቶሊካውያን እና በጎ ፍቃድ ያላቸው ሰዎች ሁሉ በጸሎት እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል #ethiopia #getutemesgen #getunews #catholic #popeleo
Sponsored by
Surafel
8 days ago
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖልና ከማላዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር በአደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪነት ወንጀል የተጠረጠረውን አድነው ባሻው ውዳሞን በማላዊ በቁጥጥር ሥር በማዋል ወደ ኢትዮጵያ አምጥቷል።
ተጠርጣሪው ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን በተለይም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሀድያ እና ከንባታ ዞኖች በርካታ ወጣቶችን ሕይወታቸውን እንደሚያሻሽል በመሐላና በአጉል ተስፋ በማታለል ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያዘዋውር መቆየቱ በሰውና በሰነድ ማስረጃ ተረጋግጧል።
ተጓዦችን ከ600 ሺህ እስከ 800 ሺህ ብር ያስከፍል የነበረ ሲሆን፣ በቅድመ ክፍያ በኢትዮጵያ እስከ 100 ሺህ ብር እና ከዚያ በላይ በባንክ ይቀበል እንደነበር የምርመራ መዝገቡ ያመላክታል።
ተጓዦቹን በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ ካሻገረ በኋላ በጋንቦ ጫካ ውስጥ በድብቅ በማስቀመጥ በየ24 ሰዓቱ ትንሽ ሩዝ ከቁራጭ ዳቦ ጋር ብቻ በመስጠት ለከፍተኛ ረሃብና የውሃ ጥም የዳረጋቸው ሲሆን፣ በሞተርና በእግር ሴሎ በረሃን እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል።
ናይሮቢ ካደረሳቸው በኋላም በአንድ ክፍል ውስጥ በማጎር ከቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ ገንዘብ እንዲያስልኩ በማስገደድ፣ ገንዘብ ማስላክ ያልቻሉትን በዱላ በመደብደብና በኤሌክትሪክ ንዝረት በማሰቃየት ተጨማሪ ገንዘብ በኢትዮጵያ ባሉ ግብረ አበሮቹ በኩል እንዲከፈለው አድርጓል።
በተጨማሪም ተጓዦቹን ከናይሮቢ ወደ ሞምባሳና ታንዛኒያ በዕቃ መጫኛ ኮንቴነሮች፣ በተሳቢና በሸራ በተሸፈኑ መኪኖች ውስጥ አጉሮ በመጫን ታንዛኒያ በሚገኝ ጫካ ውስጥ ጥሏቸው የተሰወረ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ወጣቶች ደቡብ አፍሪካ ሳይደርሱ በተለያዩ ሀገራት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው እስከ ሦስት ዓመት እስራት ከተቀጡ በኋላ እስከ 170 ሺህ ብር ከፍለው ወደ ሀገር መመለሳቸው ተገልጿል።
ፌደራል ፖሊስ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪውን በማላዊ ፖሊስ አስይዞ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ተረክቦ ወደ ሀገር ያመጣው ሲሆን፣ ህብረተሰቡ በEFPApp፣ በ991 እና በSPS ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።
ተጠርጣሪው ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን በተለይም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሀድያ እና ከንባታ ዞኖች በርካታ ወጣቶችን ሕይወታቸውን እንደሚያሻሽል በመሐላና በአጉል ተስፋ በማታለል ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያዘዋውር መቆየቱ በሰውና በሰነድ ማስረጃ ተረጋግጧል።
ተጓዦችን ከ600 ሺህ እስከ 800 ሺህ ብር ያስከፍል የነበረ ሲሆን፣ በቅድመ ክፍያ በኢትዮጵያ እስከ 100 ሺህ ብር እና ከዚያ በላይ በባንክ ይቀበል እንደነበር የምርመራ መዝገቡ ያመላክታል።
ተጓዦቹን በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ ካሻገረ በኋላ በጋንቦ ጫካ ውስጥ በድብቅ በማስቀመጥ በየ24 ሰዓቱ ትንሽ ሩዝ ከቁራጭ ዳቦ ጋር ብቻ በመስጠት ለከፍተኛ ረሃብና የውሃ ጥም የዳረጋቸው ሲሆን፣ በሞተርና በእግር ሴሎ በረሃን እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል።
ናይሮቢ ካደረሳቸው በኋላም በአንድ ክፍል ውስጥ በማጎር ከቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ ገንዘብ እንዲያስልኩ በማስገደድ፣ ገንዘብ ማስላክ ያልቻሉትን በዱላ በመደብደብና በኤሌክትሪክ ንዝረት በማሰቃየት ተጨማሪ ገንዘብ በኢትዮጵያ ባሉ ግብረ አበሮቹ በኩል እንዲከፈለው አድርጓል።
በተጨማሪም ተጓዦቹን ከናይሮቢ ወደ ሞምባሳና ታንዛኒያ በዕቃ መጫኛ ኮንቴነሮች፣ በተሳቢና በሸራ በተሸፈኑ መኪኖች ውስጥ አጉሮ በመጫን ታንዛኒያ በሚገኝ ጫካ ውስጥ ጥሏቸው የተሰወረ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ወጣቶች ደቡብ አፍሪካ ሳይደርሱ በተለያዩ ሀገራት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው እስከ ሦስት ዓመት እስራት ከተቀጡ በኋላ እስከ 170 ሺህ ብር ከፍለው ወደ ሀገር መመለሳቸው ተገልጿል።
ፌደራል ፖሊስ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪውን በማላዊ ፖሊስ አስይዞ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ተረክቦ ወደ ሀገር ያመጣው ሲሆን፣ ህብረተሰቡ በEFPApp፣ በ991 እና በSPS ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።
12 days ago
የኩሪፍቱ ባለቤት በኬንያ በምሥራቅ አፍሪካ ትልቁን የውሃ ፓርክ ሊገነቡ ነው
#ethiopia | የቦስተን ፓርትነርስ መስራችና የኩሪፍቱ ሪዞርትስ እና ስፓ ባለቤት የሆኑት ኢትዮጵያዊው ባለሀብት ታዲዮስ በለጠ፣ በኬንያ የቱሪዝም ዘርፍ ትልቅ ኢንቨስትመንት ለማከናወን መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
ባለሀብቱ በኬንያዋ የወደብ ከተማ ሞምባሳ ከአገሪቱ ባለሀብቶች ጋር በመተባበር ግዙፍ የውሃ መዝናኛ ፓርክ (Water Park) ለመገንባት ማቀዳቸውን ይፋ አድርገዋል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ትልቁ የውሃ ፓርክ እንደሚሆን የኬንያ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ይህ የኢንቨስትመንት ዕቅድ ይፋ የሆነው፣ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ያዘጋጀውን የኢትዮጵያ የቱሪዝም መስህቦች ማስተዋወቂያ መድረክ ተከትሎ ነው።
በመድረኩ ላይ ለኬንያ ባለሀብቶች፣ ለአስጎብኝ ድርጅቶች፣ ለጋዜጠኞችና ለሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ስለ ኢትዮጵያ የቱሪዝም አቅምና የኢንቨስትመንት እድሎች ማብራሪያ ተሰጥቷል። በቀጣይም የኬንያ አስጎብኝ ድርጅቶችንና የሚዲያ ተወካዮችን ወደ ኢትዮጵያ በመጋበዝ የሀገሪቱን የቱሪዝም ሀብቶች በቀጥታ እንዲጎበኙ የማድረግ ዕቅድ መኖሩም ተገልጿል።
የታዲዮስ በለጠ ይህ አዲስ ኢንቨስትመንት በኢትዮጵያና በኬንያ መካከል የቱሪዝም ትብብርን ለማጠናከር እና የምሥራቅ አፍሪካን የመዝናኛ ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ከሚደረጉ ጥረቶች መካከል አንዱ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዋዜማ
#ethiopia | የቦስተን ፓርትነርስ መስራችና የኩሪፍቱ ሪዞርትስ እና ስፓ ባለቤት የሆኑት ኢትዮጵያዊው ባለሀብት ታዲዮስ በለጠ፣ በኬንያ የቱሪዝም ዘርፍ ትልቅ ኢንቨስትመንት ለማከናወን መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
ባለሀብቱ በኬንያዋ የወደብ ከተማ ሞምባሳ ከአገሪቱ ባለሀብቶች ጋር በመተባበር ግዙፍ የውሃ መዝናኛ ፓርክ (Water Park) ለመገንባት ማቀዳቸውን ይፋ አድርገዋል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ትልቁ የውሃ ፓርክ እንደሚሆን የኬንያ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ይህ የኢንቨስትመንት ዕቅድ ይፋ የሆነው፣ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ያዘጋጀውን የኢትዮጵያ የቱሪዝም መስህቦች ማስተዋወቂያ መድረክ ተከትሎ ነው።
በመድረኩ ላይ ለኬንያ ባለሀብቶች፣ ለአስጎብኝ ድርጅቶች፣ ለጋዜጠኞችና ለሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ስለ ኢትዮጵያ የቱሪዝም አቅምና የኢንቨስትመንት እድሎች ማብራሪያ ተሰጥቷል። በቀጣይም የኬንያ አስጎብኝ ድርጅቶችንና የሚዲያ ተወካዮችን ወደ ኢትዮጵያ በመጋበዝ የሀገሪቱን የቱሪዝም ሀብቶች በቀጥታ እንዲጎበኙ የማድረግ ዕቅድ መኖሩም ተገልጿል።
የታዲዮስ በለጠ ይህ አዲስ ኢንቨስትመንት በኢትዮጵያና በኬንያ መካከል የቱሪዝም ትብብርን ለማጠናከር እና የምሥራቅ አፍሪካን የመዝናኛ ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ከሚደረጉ ጥረቶች መካከል አንዱ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዋዜማ
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዛሬ ማክሰኞ በናይሮቢ በተካሄደው 3ኛው የልዩ መልዕክተኞች እና ተወካዮች መድረክ ላይ፣ የዓለም አቀፉ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና የኬንያ መንግሥት በሱዳን እየተካሄደ ያለው የእርስ በእርስ ጦርነት ሀገሪቱን ወደ ሙሉ መበታተን እንዳያመራት ክልላዊና ዓለም አቀፋዊ አስታራቂዎች ስልታዊና የተቀናጀ አካሄድ እንዲከተሉ በጥብቅ አሳስበዋል። የኢጋድ ዋና ጸሐፊ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ የሱዳን ቀውስ አሁን ላይ የደረሰበት ደረጃ በአንድ ሀገር ወይም በአንድ ድርጅት ብቻ ሊፈታ የማይችል እጅግ ውስብስብ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ዶክተር ወርቅነህ “ሱዳን የትኩረት እጥረት የለባትም፤ የሚያስፈልጋት ስልታዊ አንድነት ነው፤ ተነሳሽነትም አልጠፋም፤ የሚያስፈልጋት ግን ሥርዓት ያለው መደጋገፍ ነው” በማለት በተለያዩ አካላት የሚደረጉ ያልተቀናጁ የሰላም ጥረቶች ይልቁኑ የፖለቲካ መፍትሔ የመምጣት ዕድሉን እያጨለሙት መሆኑን አስጠንቅቀዋል።
ይህንን አሳሳቢ የዲፕሎማሲ እና የወታደራዊ መደናቀፍ ሁኔታ ስንመለከተው የኢጋድ እና የኬንያ ስጋት መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው። እ.ኤ.አ. ከኤፕሪል 2023 ጀምሮ በሱዳን መደበኛ ጦር (SAF) እና በፈጣን ድጋፍ ኃይሎች (RSF) መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት ቢያንስ 59 ሺህ ሰዎችን ለሞት የዳረገ፣ ከ14 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ያፈናቀለ እና 33.7 ሚሊዮን ሰዎችን ለከባድ የረሃብና ሰብዓዊ ቀውስ የዳረገ የዓለማችን ትልቁ ሰብዓዊ አደጋ ሆኗል።
የኬንያው ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ በበኩላቸው እንዳስጠነቀቁት፣ ጦርነቱ በዋለ ቁጥር የተፋላሚ ወገኖች አቋም ይበልጥ እየጠነከረ፣ ትይዩ የሆኑ የሥልጣን ማዕከላት እየተፈጠሩ እና ሀገሪቱ ወደ መፈራረስ እየተቃረበች ነው።
ዶክተር ወርቅነህ “ሱዳን የትኩረት እጥረት የለባትም፤ የሚያስፈልጋት ስልታዊ አንድነት ነው፤ ተነሳሽነትም አልጠፋም፤ የሚያስፈልጋት ግን ሥርዓት ያለው መደጋገፍ ነው” በማለት በተለያዩ አካላት የሚደረጉ ያልተቀናጁ የሰላም ጥረቶች ይልቁኑ የፖለቲካ መፍትሔ የመምጣት ዕድሉን እያጨለሙት መሆኑን አስጠንቅቀዋል።
ይህንን አሳሳቢ የዲፕሎማሲ እና የወታደራዊ መደናቀፍ ሁኔታ ስንመለከተው የኢጋድ እና የኬንያ ስጋት መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው። እ.ኤ.አ. ከኤፕሪል 2023 ጀምሮ በሱዳን መደበኛ ጦር (SAF) እና በፈጣን ድጋፍ ኃይሎች (RSF) መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት ቢያንስ 59 ሺህ ሰዎችን ለሞት የዳረገ፣ ከ14 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ያፈናቀለ እና 33.7 ሚሊዮን ሰዎችን ለከባድ የረሃብና ሰብዓዊ ቀውስ የዳረገ የዓለማችን ትልቁ ሰብዓዊ አደጋ ሆኗል።
የኬንያው ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ በበኩላቸው እንዳስጠነቀቁት፣ ጦርነቱ በዋለ ቁጥር የተፋላሚ ወገኖች አቋም ይበልጥ እየጠነከረ፣ ትይዩ የሆኑ የሥልጣን ማዕከላት እየተፈጠሩ እና ሀገሪቱ ወደ መፈራረስ እየተቃረበች ነው።
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአውሮፓው ግዙፍ የአቪዬሽን ተቋም 'ኤርባስ' በቅርቡ ባወጣው የትንታኔ ሪፖርት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከለንደን እና ዱባይ ከመሳሰሉ ከተሞች ጋር በሚያገናኙ መስመሮች ላይ የመካከለኛው ምስራቅ እና የቀጣናውን ተቀናቃኝ አየር መንገዶች በመብለጥ የገበያ ድርሻውን በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደገ መምጣቱን አስታውቋል።
በሪፖርቱ መሰረት አየር መንገዱ ከዚምባብዌ ሐራሬ ወደ ለንደን ጋትዊክ የጀመረው ቀጥታ በረራ እጅግ ስኬታማ በመሆኑ፣ የኤምሬትስ አየር መንገድን በመብለጥ ቀዳሚው ተመራጭ መሆን ችሏል። በተመሳሳይ ከካሜሩን ዱዋላ ወደ ዱባይ በሚደረገው በረራ የሩዋንዳ አየር መንገድን በገበያ ድርሻ በልጧል። በሐራሬ እና ዱባይ መስመር ላይ ደግሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ክላስ ተጓዦችን መሳብ የቻለ ሲሆን፣ ኤምሬትስ በበኩሉ የቅንጦት ተጓዦችን ገበያ መቆጣጠሩን ሪፖርቱ አሳይቷል።
ኤርባስ በአፍሪካ የአየር ትራንስፖርት ላይ ሰፊ ያልተነኩ የገበያ ክፍተቶች መኖራቸውንም ጠቁሟል። ከእነዚህም ውስጥ ናይጄሪያውያን ለትምህርት እና ለንግድ በብዛት የሚጓዙባቸው የሌጎስ-ካናዳ እና የሌጎስ-ጓንግዡ መስመሮች በዋናነት ይጠቀሳሉ። በሌላ በኩል በምስራቅ እና ምዕራብ አፍሪካ መካከል ያለውን ውስን የአየር ትራንስፖርት ትስስር በዋናነት የተቆጣጠሩት መዳረሻቸውን አዲስ አበባ እና ናይሮቢ ያደረጉ በረራዎች ብቻ መሆናቸውን ሪፖርቱ አጋልጧል።
በጭነት (ካርጎ) ዘርፍ ከብራስልስ ወደ ጆሃንስበርግ የሚደረገው በረራ ለአየር መንገዱ ሌላኛው ትልቅ የገበያ ዕድል መሆኑ ተጠቅሷል። በተለይም የደቡብ አፍሪካ የግብርና እና የስጋ ምርቶችን ወደ አውሮፓ ገበያ ለማቅረብ አየር መንገዱ ሰፊ ዕድል አለው ተብሏል።
በሪፖርቱ መሰረት አየር መንገዱ ከዚምባብዌ ሐራሬ ወደ ለንደን ጋትዊክ የጀመረው ቀጥታ በረራ እጅግ ስኬታማ በመሆኑ፣ የኤምሬትስ አየር መንገድን በመብለጥ ቀዳሚው ተመራጭ መሆን ችሏል። በተመሳሳይ ከካሜሩን ዱዋላ ወደ ዱባይ በሚደረገው በረራ የሩዋንዳ አየር መንገድን በገበያ ድርሻ በልጧል። በሐራሬ እና ዱባይ መስመር ላይ ደግሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ክላስ ተጓዦችን መሳብ የቻለ ሲሆን፣ ኤምሬትስ በበኩሉ የቅንጦት ተጓዦችን ገበያ መቆጣጠሩን ሪፖርቱ አሳይቷል።
ኤርባስ በአፍሪካ የአየር ትራንስፖርት ላይ ሰፊ ያልተነኩ የገበያ ክፍተቶች መኖራቸውንም ጠቁሟል። ከእነዚህም ውስጥ ናይጄሪያውያን ለትምህርት እና ለንግድ በብዛት የሚጓዙባቸው የሌጎስ-ካናዳ እና የሌጎስ-ጓንግዡ መስመሮች በዋናነት ይጠቀሳሉ። በሌላ በኩል በምስራቅ እና ምዕራብ አፍሪካ መካከል ያለውን ውስን የአየር ትራንስፖርት ትስስር በዋናነት የተቆጣጠሩት መዳረሻቸውን አዲስ አበባ እና ናይሮቢ ያደረጉ በረራዎች ብቻ መሆናቸውን ሪፖርቱ አጋልጧል።
በጭነት (ካርጎ) ዘርፍ ከብራስልስ ወደ ጆሃንስበርግ የሚደረገው በረራ ለአየር መንገዱ ሌላኛው ትልቅ የገበያ ዕድል መሆኑ ተጠቅሷል። በተለይም የደቡብ አፍሪካ የግብርና እና የስጋ ምርቶችን ወደ አውሮፓ ገበያ ለማቅረብ አየር መንገዱ ሰፊ ዕድል አለው ተብሏል።
2 months ago
የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ መድፈኞቹ ኬንያን እነዲጎበኙ ይፉዊ ጥያቄ አቀረቡ
#ethiopia | የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊው አርሰናል እግር ኳስ ክለብ በምሥራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ኬንያ ይፋዊ ጉብኝት እንዲያደርግ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ራሳቸው የለንድኑ መድፈኞች ደጋፊ የሆኑት ፕሬዚዳንት ሩቶ ይህንን ግብዣ ያቀረቡት፣ ክለቡ ከ20 ዓመታት በላይ የዘለቀውን የዋንጫ ድርቅ አብቅቶ የዘንድሮውን የፕሪሚየር ሊግ ዘውድ በመቀዳጀቱ በናይሮቢ ጎዳናዎች ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች ደስታቸውን በደመቀ ሁኔታ መግለጻቸውን ተከትሎ ነው።
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ባለፈው ግንቦት ወር ማጠናቀቂያ ላይ ያሳካው ይህ የሊግ ዋንጫ ድል በኬንያ መዲና ናይሮቢ ታይቶ የማይታወቅ እጅግ ከፍተኛ የደጋፊዎች አከባበር እንዲቀጣጠል ማድረጉ ይታወሳል።
በፈረንሳይ እየተካሄደ በሚገኘው የቡድን-7 (G7) የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለሮይተርስ የዜና ወኪል ቃለ-መጠይቅ የሰጡት ፕሬዚዳንት ሩቶ፣ "አርሰናል በመጨረሻ የነበረውን ክፍተት ዘግቶ ዋንጫውን ማንሳት ችሏል፤ ይህም ትልቅ ክስተት ነበር። በናይሮቢ የታየው የደስታ አገላለጽ እኔንም ጭምር አስገርሞኛል" ብለዋል። አክለውም "በመሆኑም በሚቀጥለው ዓመት አርሰናል ወደ ኬንያ መጥቶ መጎብኘት የሚችልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየጣርኩ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
አርሰናል ከዋና ተፎካካሪው ማንቸስተር ሲቲ ጋር ሲያደርግ የነበረውን የሻምፒዮንነት ፍልሚያ በበላይነት ማጠናቀቁን ተከትሎ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የኬንያ ደጋፊዎች የክለቡን ቀይ እና ነጭ መለያ በመልበስና ሰንደቅ ዓላማዎችን በመያዝ ወደ ጎዳና ወጥተው ደስታቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።
ፕሬዚዳንት ሩቶ በመጨረሻም “ክለቡ በኬንያ ውስጥ እጅግ በርካታና ድንቅ ደጋፊዎች አሉት፤ በመሆኑም አርሰናል ወደ ኬንያ ቢመጣ ትልቅ ታሪካዊ ምዕራፍ ይሆናል ብዬ ስለምማምን ይፋዊ የግብዣ ጥሪ ልኬላቸዋለሁ” ብለዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊው አርሰናል እግር ኳስ ክለብ በምሥራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ኬንያ ይፋዊ ጉብኝት እንዲያደርግ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ራሳቸው የለንድኑ መድፈኞች ደጋፊ የሆኑት ፕሬዚዳንት ሩቶ ይህንን ግብዣ ያቀረቡት፣ ክለቡ ከ20 ዓመታት በላይ የዘለቀውን የዋንጫ ድርቅ አብቅቶ የዘንድሮውን የፕሪሚየር ሊግ ዘውድ በመቀዳጀቱ በናይሮቢ ጎዳናዎች ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች ደስታቸውን በደመቀ ሁኔታ መግለጻቸውን ተከትሎ ነው።
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ባለፈው ግንቦት ወር ማጠናቀቂያ ላይ ያሳካው ይህ የሊግ ዋንጫ ድል በኬንያ መዲና ናይሮቢ ታይቶ የማይታወቅ እጅግ ከፍተኛ የደጋፊዎች አከባበር እንዲቀጣጠል ማድረጉ ይታወሳል።
በፈረንሳይ እየተካሄደ በሚገኘው የቡድን-7 (G7) የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለሮይተርስ የዜና ወኪል ቃለ-መጠይቅ የሰጡት ፕሬዚዳንት ሩቶ፣ "አርሰናል በመጨረሻ የነበረውን ክፍተት ዘግቶ ዋንጫውን ማንሳት ችሏል፤ ይህም ትልቅ ክስተት ነበር። በናይሮቢ የታየው የደስታ አገላለጽ እኔንም ጭምር አስገርሞኛል" ብለዋል። አክለውም "በመሆኑም በሚቀጥለው ዓመት አርሰናል ወደ ኬንያ መጥቶ መጎብኘት የሚችልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየጣርኩ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
አርሰናል ከዋና ተፎካካሪው ማንቸስተር ሲቲ ጋር ሲያደርግ የነበረውን የሻምፒዮንነት ፍልሚያ በበላይነት ማጠናቀቁን ተከትሎ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የኬንያ ደጋፊዎች የክለቡን ቀይ እና ነጭ መለያ በመልበስና ሰንደቅ ዓላማዎችን በመያዝ ወደ ጎዳና ወጥተው ደስታቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።
ፕሬዚዳንት ሩቶ በመጨረሻም “ክለቡ በኬንያ ውስጥ እጅግ በርካታና ድንቅ ደጋፊዎች አሉት፤ በመሆኑም አርሰናል ወደ ኬንያ ቢመጣ ትልቅ ታሪካዊ ምዕራፍ ይሆናል ብዬ ስለምማምን ይፋዊ የግብዣ ጥሪ ልኬላቸዋለሁ” ብለዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ከትናንት ጀምሮ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ "የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ከፋ ኖ ተወካዮች ጋር ድርድር ለማድረግ በኬንያ ናይሮቢ ተቀምጠዋል" በሚል በስፋት ሲሰራጭ የነበረው መረጃ ሙሉ በሙሉ ሐሰተኛ መሆኑን ዘ-ሐበሻ ማረጋገጥ ችሏል። ምንጮቻችን እንዳረጋገጡት፣ የክልሉ አመራሮች ወደ ናይሮቢ ያቀኑት ለማንኛውም ዓይነት የፖለቲካ ድርድር ሳይሆን፣ ከውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ሃይጅን (WASH - Water, Sanitation, and Hygiene) ፕሮጀክት ጋር በተያያዘ ልማታዊ ስራ ነው።
ወደ ኬንያ የተጓዘው የልዑካን ቡድን የክልሉን ከፍተኛ አመራሮች ያካተተ ነው። ከድምጽ መረጃዎች ማረጋገጥ እንደተቻለው በልዑካን ቡድኑ ውስጥ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፣ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር አብዱ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሰላምና ደህንነት ክላስተር አስተባባሪ የሆኑት ዶክተር አማኑኤል ይገኙበታል። በተጨማሪም የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ በቀለ፣ የትምህርት ቢሮ ኃላፊው አቶ ጥላሁን፣ እንዲሁም ስማቸው ያልተገለጸ የውሃ ሀብት ቢሮ ኃላፊ የዚህ ጉዞ አካል ናቸው።
ይህ የWASH (የውሃና ንጽህና) ፕሮጀክት ጉዞ ለምን አስፈለገ? የክልሉ አመራሮች ይህንን ፕሮጀክት አንግበው ወደ ኬንያ ማቅናታቸው ከፖለቲካው ጀርባ ያለውን የክልሉን የጤና እና የመሰረተ ልማት ቀውስ ለመፍታት ያለመ ነው። ለዚህም በቅርቡ በአማራ ክልል የትራኮማ በሽታ ስርጭት እና የውሃ አቅርቦት ትስስርን አስመልክቶ ይፋ የተደረገው አዲስ ዓለም አቀፍ ጥናት በቂ ማሳያ ነው።
በአማራ ክልል ዕድሜያቸው ከ1 እስከ 9 ዓመት በሆኑ ህጻናት ላይ የተካሄደው ይህ ጥናት እንዳመለከተው፣ በክልሉ የትራኮማ በሽታ (TF) አማካይ ስርጭት 25.1 በመቶ ደርሷል። ትራኮማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለዓይነ ስውርነት ከሚዳርጉ ተላላፊ በሽታዎች ቀዳሚው ሲሆን፣ ይህን በሽታ ለመከላከል ደግሞ የውሃ አቅርቦት እና የፊት ንጽህና (WASH) ወሳኝ ሚና አላቸው። ጥናቱ እንዳረጋገጠው፣ ከ30 ደቂቃ ባነሰ የእግር ጉዞ ርቀት ውስጥ የንጹህ መጠጥ ውሃ ማግኘት በሚችሉ ማህበረሰቦች ውስጥ፣ የትራኮማ በሽታ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ ዝቅተኛ ሆኖ ተገኝቷል።
በመሆኑም፣ በሽታውን ከክልሉ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት መሰረተ-ልማትን ማሳደግ እጅግ ወሳኝ ነው። የውሃ ሀብት ቢሮ፣ የትምህርት ቢሮ (በትምህርት ቤቶች የውሃ እና ንጽህና አቅርቦትን ከማሳደግ አኳያ)፣ እንዲሁም የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በኬንያ ናይሮቢ እያደረጉት ያለው ቆይታም፣ ይህንኑ የህዝብ ጤና እና የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር የሚፈታውን የWASH ፕሮጀክት ለማጠናከር፣ የገንዘብ ድጋፍ ለማፈላለግ እና ልምድ ለመለዋወጥ ያለመ መሆኑ ተረጋግጧል።
ማህበረሰቡ እና የሚዲያ ተከታታዮች በማህበራዊ ሚዲያ ለሚለቀቁ እና የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ለሚፈበረኩ የሐሰት ወሬዎች ጆሮ ከመስጠት ይልቅ፣ ከእውነተኛ ምንጮች የተረጋገጡ መረጃዎችን ብቻ ሊከታተሉ እንደሚገባ ማሳሰቢያ ተላልፏል። ማረጋገጥ እንደቻልነው የአመራሮቹ የኬንያ ጉዞ ከፋኖ ድርድር ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌለው፣ እና ከላይ በተጠቀሰው የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ንጽህና (WASH) ፕሮጀክት ዙሪያ ላይ ብቻ ያተኮረ ነው።
ወደ ኬንያ የተጓዘው የልዑካን ቡድን የክልሉን ከፍተኛ አመራሮች ያካተተ ነው። ከድምጽ መረጃዎች ማረጋገጥ እንደተቻለው በልዑካን ቡድኑ ውስጥ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፣ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር አብዱ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሰላምና ደህንነት ክላስተር አስተባባሪ የሆኑት ዶክተር አማኑኤል ይገኙበታል። በተጨማሪም የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ በቀለ፣ የትምህርት ቢሮ ኃላፊው አቶ ጥላሁን፣ እንዲሁም ስማቸው ያልተገለጸ የውሃ ሀብት ቢሮ ኃላፊ የዚህ ጉዞ አካል ናቸው።
ይህ የWASH (የውሃና ንጽህና) ፕሮጀክት ጉዞ ለምን አስፈለገ? የክልሉ አመራሮች ይህንን ፕሮጀክት አንግበው ወደ ኬንያ ማቅናታቸው ከፖለቲካው ጀርባ ያለውን የክልሉን የጤና እና የመሰረተ ልማት ቀውስ ለመፍታት ያለመ ነው። ለዚህም በቅርቡ በአማራ ክልል የትራኮማ በሽታ ስርጭት እና የውሃ አቅርቦት ትስስርን አስመልክቶ ይፋ የተደረገው አዲስ ዓለም አቀፍ ጥናት በቂ ማሳያ ነው።
በአማራ ክልል ዕድሜያቸው ከ1 እስከ 9 ዓመት በሆኑ ህጻናት ላይ የተካሄደው ይህ ጥናት እንዳመለከተው፣ በክልሉ የትራኮማ በሽታ (TF) አማካይ ስርጭት 25.1 በመቶ ደርሷል። ትራኮማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለዓይነ ስውርነት ከሚዳርጉ ተላላፊ በሽታዎች ቀዳሚው ሲሆን፣ ይህን በሽታ ለመከላከል ደግሞ የውሃ አቅርቦት እና የፊት ንጽህና (WASH) ወሳኝ ሚና አላቸው። ጥናቱ እንዳረጋገጠው፣ ከ30 ደቂቃ ባነሰ የእግር ጉዞ ርቀት ውስጥ የንጹህ መጠጥ ውሃ ማግኘት በሚችሉ ማህበረሰቦች ውስጥ፣ የትራኮማ በሽታ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ ዝቅተኛ ሆኖ ተገኝቷል።
በመሆኑም፣ በሽታውን ከክልሉ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት መሰረተ-ልማትን ማሳደግ እጅግ ወሳኝ ነው። የውሃ ሀብት ቢሮ፣ የትምህርት ቢሮ (በትምህርት ቤቶች የውሃ እና ንጽህና አቅርቦትን ከማሳደግ አኳያ)፣ እንዲሁም የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በኬንያ ናይሮቢ እያደረጉት ያለው ቆይታም፣ ይህንኑ የህዝብ ጤና እና የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር የሚፈታውን የWASH ፕሮጀክት ለማጠናከር፣ የገንዘብ ድጋፍ ለማፈላለግ እና ልምድ ለመለዋወጥ ያለመ መሆኑ ተረጋግጧል።
ማህበረሰቡ እና የሚዲያ ተከታታዮች በማህበራዊ ሚዲያ ለሚለቀቁ እና የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ለሚፈበረኩ የሐሰት ወሬዎች ጆሮ ከመስጠት ይልቅ፣ ከእውነተኛ ምንጮች የተረጋገጡ መረጃዎችን ብቻ ሊከታተሉ እንደሚገባ ማሳሰቢያ ተላልፏል። ማረጋገጥ እንደቻልነው የአመራሮቹ የኬንያ ጉዞ ከፋኖ ድርድር ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌለው፣ እና ከላይ በተጠቀሰው የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ንጽህና (WASH) ፕሮጀክት ዙሪያ ላይ ብቻ ያተኮረ ነው።
2 months ago
ሦስት ኢትዮጵያውያን የ2026ቱ የአፍሪካ ምርጥ 100 ሥራ ፈጣሪዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ
#ethiopia | በጃክ ማ ፋውንዴሽን እና በአሊባባ ፊላንትሮፒ አዘጋጅነት በሚካሄደው 'የአፍሪካ ቢዝነስ ጀግኖች' (ABH) የ2026 ውድድር ላይ ሦስት ኢትዮጵያውያን የቢዝነስ ሰዎች ከአፍሪካ ምርጥ 100 ሥራ ፈጣሪዎች መካከል መመረጣቸው ተገለጸ። ለዚህ ውድድር ከ54ቱም የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ከ24,000 በላይ አመልካቾች ተሳትፈዋል።
ዘንድሮ ዕውቅና የተሰጣቸው ኢትዮጵያውያን የኢግል-ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርሱፍቃድ ጌታቸው አማረ፣ የቻፓ ተባባሪ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ናኤል ኃይለማርያም፣ እንዲሁም የቱር ባዮቴክ (Thur Biotech) ተባባሪ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳምሶን ፈንታዬ ናቸው።
ኤቢኤች (ABH) እንዳስታወቀው፣ እነዚህ ምርጥ 100 ሥራ ፈጣሪዎች ከ27 የአፍሪካ ሀገራት የተመረጡ ሲሆን፤ በግብርና፣ በፋይናንስ አገልግሎት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በጤና አጠባበቅ እና በኃይል ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ናቸው። የዘንድሮውን ስብጥር በመምራት ግብርና 21 በመቶውን ሲይዝ፣ የፋይናንስ አገልግሎት ደግሞ በ12 በመቶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
አቶ ብርሱፍቃድ የሚመሩት ኢግል-ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶችን፣ የክፍያ፣ የብድር እና የሐዋላ ሥርዓቶችን የሚያለማ የፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ ኩባንያ ሲሆን፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ዳሸን ባንክ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ማስተርካርድ እና ቪዛ ጋር አብሮ ይሰራል።
በሌላ በኩል፣ አቶ ናኤል የሚመሩት ቻፓ በኢትዮጵያ ቀዳሚ ከሆኑት የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች አንዱ ሲሆን፣ የንግድ ተቋማት ኤሌክትሮኒክ ክፍያዎችን በቀላሉ እንዲቀበሉ እና አፍሪካውያን የንግድ ተቋማትን ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓቶች ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል መሠረተ ልማት ያቀርባል።
ሦስተኛው ተወዳዳሪ አቶ ሳምሶን የሚመሩት ቱር ባዮቴክ ደግሞ፣ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ ተፈጥሯዊ ማዳበሪያዎችን በማምረት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚሰራ የባዮቴክኖሎጂ ኩባንያ ነው።
እነዚህ ምርጥ 100 ኩባንያዎች በ2025 እ.ኤ.አ. በጋራ 170 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማመንጨታቸውን፣ ከ6,200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን እና 10 ሚሊዮን ለሚጠጉ ደንበኞች በመላው አፍሪካ አገልግሎት መስጠታቸውን ድርጅቱ አስታውቋል። ይህ አኃዝ አፍሪካውያን ሥራ ፈጣሪዎች እያበረከቱት ያለውን የጎላ ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ያሳያል።
የተመረጡት ሥራ ፈጣሪዎች ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያልፉ ሲሆን፣ ዳኞች ቁጥራቸውን በማጣራት ወደ 20 ግማሽ ፍጻሜ ተወዳዳሪዎች ዝቅ ያደርጉታል። የተመረጡት ተወዳዳሪዎች በመጪው ነሐሴ ወር በናይሮቢ፣ ኬንያ የቢዝነስ ሥራቸውን በማቅረብ፣ በመጨረሻዎቹ 10 ምርጥ ሥራ ፈጣሪዎች ውስጥ ለመካተት እና የ1.5 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ፈንድ ተቋዳሽ ለመሆን ይወዳደራሉ።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በጃክ ማ ፋውንዴሽን እና በአሊባባ ፊላንትሮፒ አዘጋጅነት በሚካሄደው 'የአፍሪካ ቢዝነስ ጀግኖች' (ABH) የ2026 ውድድር ላይ ሦስት ኢትዮጵያውያን የቢዝነስ ሰዎች ከአፍሪካ ምርጥ 100 ሥራ ፈጣሪዎች መካከል መመረጣቸው ተገለጸ። ለዚህ ውድድር ከ54ቱም የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ከ24,000 በላይ አመልካቾች ተሳትፈዋል።
ዘንድሮ ዕውቅና የተሰጣቸው ኢትዮጵያውያን የኢግል-ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርሱፍቃድ ጌታቸው አማረ፣ የቻፓ ተባባሪ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ናኤል ኃይለማርያም፣ እንዲሁም የቱር ባዮቴክ (Thur Biotech) ተባባሪ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳምሶን ፈንታዬ ናቸው።
ኤቢኤች (ABH) እንዳስታወቀው፣ እነዚህ ምርጥ 100 ሥራ ፈጣሪዎች ከ27 የአፍሪካ ሀገራት የተመረጡ ሲሆን፤ በግብርና፣ በፋይናንስ አገልግሎት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በጤና አጠባበቅ እና በኃይል ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ናቸው። የዘንድሮውን ስብጥር በመምራት ግብርና 21 በመቶውን ሲይዝ፣ የፋይናንስ አገልግሎት ደግሞ በ12 በመቶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
አቶ ብርሱፍቃድ የሚመሩት ኢግል-ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶችን፣ የክፍያ፣ የብድር እና የሐዋላ ሥርዓቶችን የሚያለማ የፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ ኩባንያ ሲሆን፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ዳሸን ባንክ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ማስተርካርድ እና ቪዛ ጋር አብሮ ይሰራል።
በሌላ በኩል፣ አቶ ናኤል የሚመሩት ቻፓ በኢትዮጵያ ቀዳሚ ከሆኑት የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች አንዱ ሲሆን፣ የንግድ ተቋማት ኤሌክትሮኒክ ክፍያዎችን በቀላሉ እንዲቀበሉ እና አፍሪካውያን የንግድ ተቋማትን ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓቶች ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል መሠረተ ልማት ያቀርባል።
ሦስተኛው ተወዳዳሪ አቶ ሳምሶን የሚመሩት ቱር ባዮቴክ ደግሞ፣ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ ተፈጥሯዊ ማዳበሪያዎችን በማምረት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚሰራ የባዮቴክኖሎጂ ኩባንያ ነው።
እነዚህ ምርጥ 100 ኩባንያዎች በ2025 እ.ኤ.አ. በጋራ 170 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማመንጨታቸውን፣ ከ6,200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን እና 10 ሚሊዮን ለሚጠጉ ደንበኞች በመላው አፍሪካ አገልግሎት መስጠታቸውን ድርጅቱ አስታውቋል። ይህ አኃዝ አፍሪካውያን ሥራ ፈጣሪዎች እያበረከቱት ያለውን የጎላ ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ያሳያል።
የተመረጡት ሥራ ፈጣሪዎች ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያልፉ ሲሆን፣ ዳኞች ቁጥራቸውን በማጣራት ወደ 20 ግማሽ ፍጻሜ ተወዳዳሪዎች ዝቅ ያደርጉታል። የተመረጡት ተወዳዳሪዎች በመጪው ነሐሴ ወር በናይሮቢ፣ ኬንያ የቢዝነስ ሥራቸውን በማቅረብ፣ በመጨረሻዎቹ 10 ምርጥ ሥራ ፈጣሪዎች ውስጥ ለመካተት እና የ1.5 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ፈንድ ተቋዳሽ ለመሆን ይወዳደራሉ።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 months ago
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕና አለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) የ80 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት ተፈራረሙ።
በስምምነቱ መሰረት ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ለሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ 80 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የረዥም ጊዜ ብድር ያቀርባል ።
በተገኘው ገንዘብ ደግሞ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሸራተን አዲስ ሌግዠሪ ኮሌክሽን ሆቴልን በዘመናዊ መልኩ ያድሳል፣በሸራተን ደረጃ አዲስ ሆቴል ይገነባል።
የብድር ስምምነቱን የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አህመድና የአለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) የአፍሪካ ቀጠና ምክትል ፕሬዚዳንት ኢትዮዺስ ተፈራ በኬንያ ናይሮቢ ተፈራርመዋል።
ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ተቋም ጋር ከፍተኛ ፋይዳ ያለውን አጋርነት በማድረጋችን ለተቋሙ ያለንን አድናቆት መግለጽ እንወዳለን ያሉት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አሕመድ፤ ይህ አጋርነት የሀገሪቱን የሆስፒታሊቲ ዘርፍ ለማዘመን እንዲሁም በኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለው የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።
የአለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን የአፍሪካ ቀጠና ምክትል ፕሬዚዳንት ኢትዮዺስ ተፈራ በበኩላቸው ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የአገልግሎት ዘርፉን የበለጠ እንዲያዘምንና ተጨማሪ የስራ እድል እንደፈጥር ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል።
ከአለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በሚገኘው ገንዘብ ሸራተን አዲስ ኤሌግዠሪ ኮሌክሽን ሆቴል ዘመኑን በሚመጥን መልኩ የሚታደስ ሲሆን በሸራተን የንግድ ምልክት የሚጠራ ተጨማሪ አዲስ ሆቴልም ይገነባል።
የአለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) የብድር አቅርቦት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አካል የሆነውን የሸራተን አዲስን ገጽታ በእጅጉ እንደሚለውጠው ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማዘጋጀት መመረጧን ተከትሎ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በሚሊኒየም አዳራሽ ቅጥር ግቢ ዘመናዊ ሆቴል (Moxy by Marriott) ፣ በመሀመድያ የመኖሪያ መንደር (Four Points by Sheraton) ሆቴሎች ግንባታን አስጀምሯል።
በቅርቡ የሚድሮክ ቤተሰብን የተቀላቀለው ዋቢሸበሌ ሆቴል (autograph collection by Marriot) ደረጃ ለጉባኤው ዝግጁ ለማድረግ ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ የእድሳት ስራው ተጀምሯል።
አፍሪካ ህብረት አጠገብ እየተገነባ ያለው ዌስት ኢን አዲስ (Westin Addis) ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በባህርዳር ከተማ (Four Points by Sheraton) እና (Protea by Marriott) ፣በጂማ እና ሃዋሳም በተመሳሳይ (Four Points by Sheraton) ሆቴሎችን እየገነባ ይገኛል።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የላንጋኖ ሳቫና ሪዞርትን በግዥ የተረከበው ሲሆን በማርዮት ብራንዶች ደረጃ አለም አቀፍ ሪዞርት በመገንባት ወደ ስራ ይገባል።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና፣ በማእድን፣ በንግድና በሆስፒታሊቲ ዘርፍ በመሰማራት ከ80 ሺህ በላይ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ተቋም ነው።
በስምምነቱ መሰረት ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ለሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ 80 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የረዥም ጊዜ ብድር ያቀርባል ።
በተገኘው ገንዘብ ደግሞ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሸራተን አዲስ ሌግዠሪ ኮሌክሽን ሆቴልን በዘመናዊ መልኩ ያድሳል፣በሸራተን ደረጃ አዲስ ሆቴል ይገነባል።
የብድር ስምምነቱን የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አህመድና የአለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) የአፍሪካ ቀጠና ምክትል ፕሬዚዳንት ኢትዮዺስ ተፈራ በኬንያ ናይሮቢ ተፈራርመዋል።
ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ተቋም ጋር ከፍተኛ ፋይዳ ያለውን አጋርነት በማድረጋችን ለተቋሙ ያለንን አድናቆት መግለጽ እንወዳለን ያሉት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አሕመድ፤ ይህ አጋርነት የሀገሪቱን የሆስፒታሊቲ ዘርፍ ለማዘመን እንዲሁም በኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለው የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።
የአለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን የአፍሪካ ቀጠና ምክትል ፕሬዚዳንት ኢትዮዺስ ተፈራ በበኩላቸው ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የአገልግሎት ዘርፉን የበለጠ እንዲያዘምንና ተጨማሪ የስራ እድል እንደፈጥር ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል።
ከአለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በሚገኘው ገንዘብ ሸራተን አዲስ ኤሌግዠሪ ኮሌክሽን ሆቴል ዘመኑን በሚመጥን መልኩ የሚታደስ ሲሆን በሸራተን የንግድ ምልክት የሚጠራ ተጨማሪ አዲስ ሆቴልም ይገነባል።
የአለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) የብድር አቅርቦት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አካል የሆነውን የሸራተን አዲስን ገጽታ በእጅጉ እንደሚለውጠው ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማዘጋጀት መመረጧን ተከትሎ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በሚሊኒየም አዳራሽ ቅጥር ግቢ ዘመናዊ ሆቴል (Moxy by Marriott) ፣ በመሀመድያ የመኖሪያ መንደር (Four Points by Sheraton) ሆቴሎች ግንባታን አስጀምሯል።
በቅርቡ የሚድሮክ ቤተሰብን የተቀላቀለው ዋቢሸበሌ ሆቴል (autograph collection by Marriot) ደረጃ ለጉባኤው ዝግጁ ለማድረግ ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ የእድሳት ስራው ተጀምሯል።
አፍሪካ ህብረት አጠገብ እየተገነባ ያለው ዌስት ኢን አዲስ (Westin Addis) ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በባህርዳር ከተማ (Four Points by Sheraton) እና (Protea by Marriott) ፣በጂማ እና ሃዋሳም በተመሳሳይ (Four Points by Sheraton) ሆቴሎችን እየገነባ ይገኛል።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የላንጋኖ ሳቫና ሪዞርትን በግዥ የተረከበው ሲሆን በማርዮት ብራንዶች ደረጃ አለም አቀፍ ሪዞርት በመገንባት ወደ ስራ ይገባል።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና፣ በማእድን፣ በንግድና በሆስፒታሊቲ ዘርፍ በመሰማራት ከ80 ሺህ በላይ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ተቋም ነው።
2 months ago
ሚድሮክ የ80 ሚሊዮን ዶላር ታሪካዊ ስምምነት ተፈራረመ
#fastmereja I ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) በኬንያ ናይሮቢ ከተማ የ80 ሚሊዮን አሜሪካን ዶላር የረጅም ጊዜ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የሚድሮክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አሕመድ እና የIFC የአፍሪካ ቀጠና ምክትል ፕሬዚዳንት ኢትዮጲስ ተፈራ የፈረሙት ሲሆን፣ የተገኘው የገንዘብ ድጋፍ በዋናነት ታዋቂውን ሸራተን አዲስ ሌግዠሪ ኮሌክሽን ሆቴልን በዘመናዊ መልኩ ለማደስ እና በሸራተን ደረጃ አዲስ ተጨማሪ ሆቴል ለመገንባት ይውላል።
ይህ ከፍተኛ የፋይናንስ አጋርነት የሀገሪቱን የሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም ዘርፍ ከማዘመን ባለፈ፣ ከ9,400 በላይ ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በተለይም ለወጣቶችና ለሴቶች እንደሚፈጥር ተገልጿል። አቶ ጀማል አሕመድ አጋርነቱ ቀጣይነት ላለው የሀገር ውስጥ ሥራ ዕድል ፈጠራ ያለውን ሚና ሲያጎሉ፣ የIFC ምክትል ፕሬዚዳንት በበኩላቸው ስምምነቱ የሚድሮክን የአገልግሎት ጥራት ለማሳደግ ታስቦ የተደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) ለማስተናገድ መመረጧን ተከትሎ ሚድሮክ ግዙፍ የሆቴል ማስፋፊያና የእድሳት ስራዎችን በከፍተኛ ፍጥነት እያከናወነ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል በሚሊኒየም አዳራሽ ቅጥር ግቢ የ"Moxy by Marriott"፣ በመሀመድያ የመኖሪያ መንደር የ"Four Points by Sheraton" እና በአፍሪካ ህብረት አጠገብ የ"Westin Addis" ሆቴሎች ግንባታ በስፋት እየተካሄደ ይገኛል።
በተጨማሪም በቅርቡ ግሩፑን የተቀላቀለው ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ወደ "Autograph Collection by Marriott" ደረጃ የማደስ ስራው የተጀመረ ሲሆን፣ በባህርዳር፣ ጅማ፣ ሃዋሳ እና በላንጋኖ ሳቫና ሪዞርት ተመሳሳይ ዓለም አቀፍ የሆቴል ፕሮጀክቶች በመገንባት ላይ ናቸው። በአሁኑ ወቅት ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በማኑፋክቸሪንግ፣ ግብርና፣ ማዕድን፣ ንግድና ሆስፒታሊቲ ዘርፎች ላይ በመሰማራት ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ይታወቃል።
#fastmereja I ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) በኬንያ ናይሮቢ ከተማ የ80 ሚሊዮን አሜሪካን ዶላር የረጅም ጊዜ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የሚድሮክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አሕመድ እና የIFC የአፍሪካ ቀጠና ምክትል ፕሬዚዳንት ኢትዮጲስ ተፈራ የፈረሙት ሲሆን፣ የተገኘው የገንዘብ ድጋፍ በዋናነት ታዋቂውን ሸራተን አዲስ ሌግዠሪ ኮሌክሽን ሆቴልን በዘመናዊ መልኩ ለማደስ እና በሸራተን ደረጃ አዲስ ተጨማሪ ሆቴል ለመገንባት ይውላል።
ይህ ከፍተኛ የፋይናንስ አጋርነት የሀገሪቱን የሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም ዘርፍ ከማዘመን ባለፈ፣ ከ9,400 በላይ ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በተለይም ለወጣቶችና ለሴቶች እንደሚፈጥር ተገልጿል። አቶ ጀማል አሕመድ አጋርነቱ ቀጣይነት ላለው የሀገር ውስጥ ሥራ ዕድል ፈጠራ ያለውን ሚና ሲያጎሉ፣ የIFC ምክትል ፕሬዚዳንት በበኩላቸው ስምምነቱ የሚድሮክን የአገልግሎት ጥራት ለማሳደግ ታስቦ የተደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) ለማስተናገድ መመረጧን ተከትሎ ሚድሮክ ግዙፍ የሆቴል ማስፋፊያና የእድሳት ስራዎችን በከፍተኛ ፍጥነት እያከናወነ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል በሚሊኒየም አዳራሽ ቅጥር ግቢ የ"Moxy by Marriott"፣ በመሀመድያ የመኖሪያ መንደር የ"Four Points by Sheraton" እና በአፍሪካ ህብረት አጠገብ የ"Westin Addis" ሆቴሎች ግንባታ በስፋት እየተካሄደ ይገኛል።
በተጨማሪም በቅርቡ ግሩፑን የተቀላቀለው ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ወደ "Autograph Collection by Marriott" ደረጃ የማደስ ስራው የተጀመረ ሲሆን፣ በባህርዳር፣ ጅማ፣ ሃዋሳ እና በላንጋኖ ሳቫና ሪዞርት ተመሳሳይ ዓለም አቀፍ የሆቴል ፕሮጀክቶች በመገንባት ላይ ናቸው። በአሁኑ ወቅት ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በማኑፋክቸሪንግ፣ ግብርና፣ ማዕድን፣ ንግድና ሆስፒታሊቲ ዘርፎች ላይ በመሰማራት ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ይታወቃል።
2 months ago
በተግባር የተገለጠው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል - አዲስ አበባን የማዘመን ጉዞ ስኬት
**********************
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የዛሬ አምስት ዓመት አዲስ አበባ በአፍሪካ ውስጥ እጅግ ውብ ከሚባሉ ከተሞች አንዷ ትሆናለች" ሲሉ ተናግረው ነበር።
ያኔ ንግግራቸውን ከሰሙት መካከል የመዲናዋን የዛሬ ገጽታ በዐይነ ኅሊናቸው የሣሉት ጥቂቶች ነበሩ።
በወቅቱ ንግግሩ ከተራ የፖለቲካ ተስፋ በላይ ትርጉም አይኖረውም ብለው የተጠራጠሩ ቢኖሩም፣ ዛሬ ግን አዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ ማራኪ፣ ጽዱ እና ዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከል በመሆን ራዕዩን በተግባር አሳይታለች።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመዲናዋ ተበታትነው የሚገኙትን እምቅ አቅሞች ወይም "ያልተያያዙ ትላልቅ ዶቶችን" በማገናኘት ከተማዋን በአዲስ መልክ የመገንባት ዕቅድ እንዳላቸው አስረድተውም ነበር።
ይህ አርቆ አሳቢ የከተማ ልማት ፍልስፍና ታሪካዊ ክስተቶችን የሚያስታውስ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳስታወሱት፣ ንጉሥ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን መገንባት በጀመሩበት ወቅት "ድንጋይ መቆርቆር የስንፍና ምልክት ነው" በማለት ያሾፉባቸው ነበሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈጣሪዎች እና አልሚዎች ሁልጊዜም በዘመናቸው ካሉ "አውርቶ አደር" ተቺዎች ጋር መጋፈጣቸው አይቀርም የሚል እሳቤ አላቸው።
ዛሬ በኮሪደር ልማቱ እየታየ ያለውም ይኸው እውነታ ነው፤ "እኛ የምንሠራው ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ እና ለቀጣዩ ትውልድ ነው፤ ነገ የሚፈርስ ዳስ አንሠራም" በሚለው መርሐቸው ለትውልድ የሚሻገር ዘላቂ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
"የመደመር መንግሥት" መጽሐፍ ላይ እንደተብራራው፣ ከተሜነት የብልጽግና መዳረሻ እና የኢኮኖሚ ሞተር ነው።
ከተማን ማዘመን ረጃጅም ሕንፃዎችን ከመገንባት ባለፈ ሰፊ የእግረኛ እና የሳይክል መንገዶችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን እና ምቹ መሠረተ ልማቶችን ማካተትን ይጠይቃል።
አዲስ አበባ ላይ በተግባር ሥራ ላይ ውሎ አዲስ አበባን ምርጥ የአፍሪካ ከተማ ያደረገው ይኸው ሰዎችን ማዕከል ያደረገው ፍልስፍና ነው።
ከዚህ ቀደም የተገነቡት አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ ወዳጅነት አደባባይ እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ የዚህ ዘመናዊ አስተሳሰብ ማሳያዎች ናቸው።
በዚህም የኮሪደር ልማቱ በግንባታው ሂደት ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ የካርቦን ልቀትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ጤና እና ደኅንነት የሚጠብቅ ንፁህ አካባቢን መፍጠር ችሏል።
እነዚህ ስልታዊ ለውጦች አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለበርካታ ሽልማቶች አብቅተዋታል።
በ2015 ዓ.ም በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ስማርት ሲቲዎች ኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ 36 የአፍሪካ ከተሞችን በመብለጥ ‘የዓመቱ ምርጥ ስማርት ሲቲ' ሽልማትን አሸንፋለች።
እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ አዳራሽ (Historic Africa Hall) እድሳት ፕሮጀክት የሞደርኒዝም ጥበቃ ሽልማትን (World Monuments Fund/Knoll Modernism Prize) ተቀዳጅቷል።
ይህ ሽልማት ከተመሠረተበት እ.ኤ.አ. 2008 ጀምሮ በአፍሪካ አህጉር ሲሰጥ አዲስ አበባ የመጀመሪያዋ ነች።
እነዚህ ስኬቶች ከተማዋ እ.አ.አ በ2027 የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) እንድታስተናግድ ትልቅ መተማመኛ ፈጥረዋል።
በአዲስ አበባ የተመዘገበው ይህ ስኬታማ የከተማ ማዘመን ልምድ በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ወደሚሆኑ የሀገራችን ከተሞችም እንዲስፋፋ ተደርጓል።
ይህ አዲስ የከተማ ማሻሻያ ፍልስፍና በቱሪዝም ዘርፉ ላይም ታይቶ የማይታወቅ መነቃቃት ፈጥሯል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) መረጃ መሰረትም ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2025 የዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን ፍሰት በ15 በመቶ በማሳደግ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተርታ ተሰልፋለች።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህን ግዙፍ ልማት ሲያከናውን ያጋጠሙትን ማኅበራዊ እና ሕጋዊ ተግዳሮቶች ሰብአዊነትን በተላበሰ መንገድ ለመፍታት ያደረገው ጥረት የልማቱን ፍትሐዊነት ያረጋግጣል።
ከተማዋን ለሕፃናት፣ ለወጣቶች እና ለአካል ጉዳተኞች ጭምር ምቹ በማድረግ የቦታ ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም የተነገረው ራዕይ ዛሬ እውን ሆኖ፣ አዲስ አበባ በምድረ አፍሪካ ውብ፣ ተመራጭ እና የሁሉንም ነዋሪዎቿን ፍላጎት ያማከለች መዲና መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #addisababa #corridordevelopment #smartcity
**********************
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የዛሬ አምስት ዓመት አዲስ አበባ በአፍሪካ ውስጥ እጅግ ውብ ከሚባሉ ከተሞች አንዷ ትሆናለች" ሲሉ ተናግረው ነበር።
ያኔ ንግግራቸውን ከሰሙት መካከል የመዲናዋን የዛሬ ገጽታ በዐይነ ኅሊናቸው የሣሉት ጥቂቶች ነበሩ።
በወቅቱ ንግግሩ ከተራ የፖለቲካ ተስፋ በላይ ትርጉም አይኖረውም ብለው የተጠራጠሩ ቢኖሩም፣ ዛሬ ግን አዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ ማራኪ፣ ጽዱ እና ዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከል በመሆን ራዕዩን በተግባር አሳይታለች።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመዲናዋ ተበታትነው የሚገኙትን እምቅ አቅሞች ወይም "ያልተያያዙ ትላልቅ ዶቶችን" በማገናኘት ከተማዋን በአዲስ መልክ የመገንባት ዕቅድ እንዳላቸው አስረድተውም ነበር።
ይህ አርቆ አሳቢ የከተማ ልማት ፍልስፍና ታሪካዊ ክስተቶችን የሚያስታውስ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳስታወሱት፣ ንጉሥ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን መገንባት በጀመሩበት ወቅት "ድንጋይ መቆርቆር የስንፍና ምልክት ነው" በማለት ያሾፉባቸው ነበሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈጣሪዎች እና አልሚዎች ሁልጊዜም በዘመናቸው ካሉ "አውርቶ አደር" ተቺዎች ጋር መጋፈጣቸው አይቀርም የሚል እሳቤ አላቸው።
ዛሬ በኮሪደር ልማቱ እየታየ ያለውም ይኸው እውነታ ነው፤ "እኛ የምንሠራው ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ እና ለቀጣዩ ትውልድ ነው፤ ነገ የሚፈርስ ዳስ አንሠራም" በሚለው መርሐቸው ለትውልድ የሚሻገር ዘላቂ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
"የመደመር መንግሥት" መጽሐፍ ላይ እንደተብራራው፣ ከተሜነት የብልጽግና መዳረሻ እና የኢኮኖሚ ሞተር ነው።
ከተማን ማዘመን ረጃጅም ሕንፃዎችን ከመገንባት ባለፈ ሰፊ የእግረኛ እና የሳይክል መንገዶችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን እና ምቹ መሠረተ ልማቶችን ማካተትን ይጠይቃል።
አዲስ አበባ ላይ በተግባር ሥራ ላይ ውሎ አዲስ አበባን ምርጥ የአፍሪካ ከተማ ያደረገው ይኸው ሰዎችን ማዕከል ያደረገው ፍልስፍና ነው።
ከዚህ ቀደም የተገነቡት አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ ወዳጅነት አደባባይ እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ የዚህ ዘመናዊ አስተሳሰብ ማሳያዎች ናቸው።
በዚህም የኮሪደር ልማቱ በግንባታው ሂደት ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ የካርቦን ልቀትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ጤና እና ደኅንነት የሚጠብቅ ንፁህ አካባቢን መፍጠር ችሏል።
እነዚህ ስልታዊ ለውጦች አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለበርካታ ሽልማቶች አብቅተዋታል።
በ2015 ዓ.ም በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ስማርት ሲቲዎች ኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ 36 የአፍሪካ ከተሞችን በመብለጥ ‘የዓመቱ ምርጥ ስማርት ሲቲ' ሽልማትን አሸንፋለች።
እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ አዳራሽ (Historic Africa Hall) እድሳት ፕሮጀክት የሞደርኒዝም ጥበቃ ሽልማትን (World Monuments Fund/Knoll Modernism Prize) ተቀዳጅቷል።
ይህ ሽልማት ከተመሠረተበት እ.ኤ.አ. 2008 ጀምሮ በአፍሪካ አህጉር ሲሰጥ አዲስ አበባ የመጀመሪያዋ ነች።
እነዚህ ስኬቶች ከተማዋ እ.አ.አ በ2027 የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) እንድታስተናግድ ትልቅ መተማመኛ ፈጥረዋል።
በአዲስ አበባ የተመዘገበው ይህ ስኬታማ የከተማ ማዘመን ልምድ በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ወደሚሆኑ የሀገራችን ከተሞችም እንዲስፋፋ ተደርጓል።
ይህ አዲስ የከተማ ማሻሻያ ፍልስፍና በቱሪዝም ዘርፉ ላይም ታይቶ የማይታወቅ መነቃቃት ፈጥሯል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) መረጃ መሰረትም ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2025 የዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን ፍሰት በ15 በመቶ በማሳደግ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተርታ ተሰልፋለች።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህን ግዙፍ ልማት ሲያከናውን ያጋጠሙትን ማኅበራዊ እና ሕጋዊ ተግዳሮቶች ሰብአዊነትን በተላበሰ መንገድ ለመፍታት ያደረገው ጥረት የልማቱን ፍትሐዊነት ያረጋግጣል።
ከተማዋን ለሕፃናት፣ ለወጣቶች እና ለአካል ጉዳተኞች ጭምር ምቹ በማድረግ የቦታ ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም የተነገረው ራዕይ ዛሬ እውን ሆኖ፣ አዲስ አበባ በምድረ አፍሪካ ውብ፣ ተመራጭ እና የሁሉንም ነዋሪዎቿን ፍላጎት ያማከለች መዲና መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #addisababa #corridordevelopment #smartcity
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የአሜሪካ መንግሥት ከአፍሪካ ቪዛ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን መካከል ኢትዮጵያን አልቀነሳትም
#ethiopia | የአሜሪካ መንግሥት በአፍሪካ አህጉሉአንዳ የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል እየተዘጋጀ ነው።
በዚህ መሠረት በአፍሪካ ውስጥ የቪዛ አገልግሎት የሚሰጡ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች ቁጥር ከ50 ወደ 20 ብቻ ለመቀነስ ወስኗል። ይህ ለውጥ በቅርብ ጊዜያት ይጀመራል ተብሏል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ያጸደቁት ይህ አዲስ እቅድ፣ በአፍሪካ 20 ዋና የክልል ማዕከላት (Regional Hubs) በመሾም፣ ሌሎች ቦታዎችን የቪዛ ሙሉ አገልግሎት እንዳይሰጡ ለመዝጋት ያቀደ ነው።
እነዚህ የ20 ዋና ማዕከላት የትኞቹ ናቸው ፦
° አዲስ አበባ (ኢትዮጵያ) 🇪🇹
° አክራ (ጋና) 🇬🇭
° ዳካር (ሴኔጋል) 🇸🇳
° ጅቡቲ (ጅቡቲ) 🇩🇯
° ካምፓላ (ኡጋንዳ) 🇺🇬
° ኪጋሊ (ሩዋንዳ) 🇷🇼
° ኪንሻሳ (ኮንጎ) 🇨🇩
° ላጎስ (ናይጄሪያ) 🇳🇬
° ናይሮቢ (ኬንያ) 🇰🇪
° አቢጃን (አይቮሪ ኮስት) 🇨🇮
° ዳሬሰላም (ታንዛኒያ) 🇹🇿
° ሎሜ (ቶጎ) 🇹🇬
° ሉዋአንዳ (አንጎላ) 🇦🇴
° ማላቦ (ኢኳቶሪያል ጊኒ) 🇬🇶
° ሞንሮቪያ (ላይቤሪያ) 🇱🇷
° ፖርት ሉዊስ (ሞሪሸስ) 🇲🇺
° ፕራያ (ኬፕ ቨርዴ) 🇻🇪
° ያውንዴ (ካሜሩን) 🇨🇲
° ኬፕ ታውን (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
° ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
ከእንግዲህ ወዲያ በእነዚህ 20 ማዕከላት ያልተካተቱ ሀገራት ዜጎች የቪዛ ቃለ መጠይቅ፣ የጣት አሻራ እና ሌሎች ሂደቶችን ለማጠናቀቅ በራሳቸው ወጪ ወደ ቅርብ ማዕከል መጓዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል ያለው ቲክቫህ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የአሜሪካ መንግሥት በአፍሪካ አህጉሉአንዳ የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል እየተዘጋጀ ነው።
በዚህ መሠረት በአፍሪካ ውስጥ የቪዛ አገልግሎት የሚሰጡ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች ቁጥር ከ50 ወደ 20 ብቻ ለመቀነስ ወስኗል። ይህ ለውጥ በቅርብ ጊዜያት ይጀመራል ተብሏል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ያጸደቁት ይህ አዲስ እቅድ፣ በአፍሪካ 20 ዋና የክልል ማዕከላት (Regional Hubs) በመሾም፣ ሌሎች ቦታዎችን የቪዛ ሙሉ አገልግሎት እንዳይሰጡ ለመዝጋት ያቀደ ነው።
እነዚህ የ20 ዋና ማዕከላት የትኞቹ ናቸው ፦
° አዲስ አበባ (ኢትዮጵያ) 🇪🇹
° አክራ (ጋና) 🇬🇭
° ዳካር (ሴኔጋል) 🇸🇳
° ጅቡቲ (ጅቡቲ) 🇩🇯
° ካምፓላ (ኡጋንዳ) 🇺🇬
° ኪጋሊ (ሩዋንዳ) 🇷🇼
° ኪንሻሳ (ኮንጎ) 🇨🇩
° ላጎስ (ናይጄሪያ) 🇳🇬
° ናይሮቢ (ኬንያ) 🇰🇪
° አቢጃን (አይቮሪ ኮስት) 🇨🇮
° ዳሬሰላም (ታንዛኒያ) 🇹🇿
° ሎሜ (ቶጎ) 🇹🇬
° ሉዋአንዳ (አንጎላ) 🇦🇴
° ማላቦ (ኢኳቶሪያል ጊኒ) 🇬🇶
° ሞንሮቪያ (ላይቤሪያ) 🇱🇷
° ፖርት ሉዊስ (ሞሪሸስ) 🇲🇺
° ፕራያ (ኬፕ ቨርዴ) 🇻🇪
° ያውንዴ (ካሜሩን) 🇨🇲
° ኬፕ ታውን (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
° ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
ከእንግዲህ ወዲያ በእነዚህ 20 ማዕከላት ያልተካተቱ ሀገራት ዜጎች የቪዛ ቃለ መጠይቅ፣ የጣት አሻራ እና ሌሎች ሂደቶችን ለማጠናቀቅ በራሳቸው ወጪ ወደ ቅርብ ማዕከል መጓዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል ያለው ቲክቫህ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 months ago
አፍሪካውያን ስለ ራሳቸው ያላቸውን አመለካከት ሲቀይሩ፣ ቀሪው ዓለምም ስለ አፍሪካ ያለውን ዕይታ ይቀይራል።
#ethiopia | አፍሪካውያን በራሳቸው ጥረትና አቅም እየገነቧት ያለችውን አህጉር ለዓለም ለማስተዋወቅና ስኬቶቻቸውን ወደ አደባባይ ለማውጣት ያለመ #notwaiting (አልጠብቅም) ዘመቻ ተጀመረ።
ይህ አህጉር አቀፍ ዘመቻ ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም (May 25, 2026) በአፍሪካ ቀን በይፋ መጀመሩ ተገልጿል።
በአዲስ አበባ፣ ጆሃንስበርግ፣ ናይሮቢ፣ ሌጎስ እና አክራ ከተሞች በጋራ ይፋ የተደረገው ይህ ዘመቻ፤ «ኦፖርቹኒቲ አፍሪካ» (Opportunity Africa) በተሰኘ ተቋም የሚመራ ነው።
በአህጉሪቱና በዲያስፖራው የሚገኙ አፍሪካውያን በአፍሪካ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ እያመጡት ያለውን በጎ ተጽዕኖ፣ አዳዲስ ዕይታዎችና የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተገልጿል።
የዘመቻው ዋነኛ መርህ አፍሪካውያን ስለ ራሳቸው ያላቸውን አመለካከት ሲቀይሩ፣ ቀሪው ዓለምም ስለ አፍሪካ ያለውን ዕይታ ይቀይራል በሚል እምነት ላይ የተመሠረተ ነው።
በአሁኑ ወቅት በርካታ አፍሪካውያን ሥራ ፈጣሪዎችና የፈጠራ ባለሙያዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ተቋማትን እየገነቡና ማኅበረሰባቸውን እየለወጡ ቢሆንም፣ እነዚህ የስኬት ታሪኮች አሁንም ድረስ በችግር፣ በረሃብና በውስንነቶች ላይ ብቻ በሚያተኩሩ አሉታዊ ትረካዎች (narratives) እየተሸፈኑ መሆኑ ተጠቅሷል።
የዚህ እንቅስቃሴ ዓላማ አፍሪካን በተመለከተ የሚነገሩ ትረካዎችን ሚዛን ለመጠበቅና ፍሬያማ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን፣ ግንባታዎችንና እድገቶችን በጋራ ድምፅ ከፍ አድርጎ ለማሳየት ነው።
ይህ እንቅስቃሴ የጥቂት ስኬታማ ሰዎች ታሪክ ሳይሆን፣ መላው አህጉሪቱ እያሳየችው ያለውን የእድገት ጉዞና አጠቃላይ እንቅስቃሴ የሚያሳይ መሆኑ ተመልክቷል።
አዘጋጆቹ መላው የአፍሪካ ሕዝብና ትውልደ አፍሪካውያን በፈጠራ ሥራዎቻቸው፣ ስኬቶቻቸውና አዳዲስ ሐሳቦቻቸው ላይ ያተኮሩ ታሪኮችን በ#notwaiting የሃሽታግ ምልክት በመጠቀም በማኅበራዊ ሚዲያዎች እንዲያጋሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በተጨማሪም ፍላጎት ያላቸው ወገኖች www.notwaiting.africa በተሰኘው ድረ-ገጽ ላይ በመግባት የዘመቻውን ማኒፌስቶ መፈረም እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህ ዘመቻ ዛሬ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ በየወሩ በ25ኛው ቀን እየታደሰ የሚቀጥልና አፍሪካውያን በአንድነት በመሆን የኢንተርኔት ዓለምን በስኬት፣ በፈጠራና በዕድሎች ታሪክ የሚያጥለቀልቁበት ተከታታይ መድረክ እንደሚሆን ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | አፍሪካውያን በራሳቸው ጥረትና አቅም እየገነቧት ያለችውን አህጉር ለዓለም ለማስተዋወቅና ስኬቶቻቸውን ወደ አደባባይ ለማውጣት ያለመ #notwaiting (አልጠብቅም) ዘመቻ ተጀመረ።
ይህ አህጉር አቀፍ ዘመቻ ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም (May 25, 2026) በአፍሪካ ቀን በይፋ መጀመሩ ተገልጿል።
በአዲስ አበባ፣ ጆሃንስበርግ፣ ናይሮቢ፣ ሌጎስ እና አክራ ከተሞች በጋራ ይፋ የተደረገው ይህ ዘመቻ፤ «ኦፖርቹኒቲ አፍሪካ» (Opportunity Africa) በተሰኘ ተቋም የሚመራ ነው።
በአህጉሪቱና በዲያስፖራው የሚገኙ አፍሪካውያን በአፍሪካ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ እያመጡት ያለውን በጎ ተጽዕኖ፣ አዳዲስ ዕይታዎችና የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተገልጿል።
የዘመቻው ዋነኛ መርህ አፍሪካውያን ስለ ራሳቸው ያላቸውን አመለካከት ሲቀይሩ፣ ቀሪው ዓለምም ስለ አፍሪካ ያለውን ዕይታ ይቀይራል በሚል እምነት ላይ የተመሠረተ ነው።
በአሁኑ ወቅት በርካታ አፍሪካውያን ሥራ ፈጣሪዎችና የፈጠራ ባለሙያዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ተቋማትን እየገነቡና ማኅበረሰባቸውን እየለወጡ ቢሆንም፣ እነዚህ የስኬት ታሪኮች አሁንም ድረስ በችግር፣ በረሃብና በውስንነቶች ላይ ብቻ በሚያተኩሩ አሉታዊ ትረካዎች (narratives) እየተሸፈኑ መሆኑ ተጠቅሷል።
የዚህ እንቅስቃሴ ዓላማ አፍሪካን በተመለከተ የሚነገሩ ትረካዎችን ሚዛን ለመጠበቅና ፍሬያማ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን፣ ግንባታዎችንና እድገቶችን በጋራ ድምፅ ከፍ አድርጎ ለማሳየት ነው።
ይህ እንቅስቃሴ የጥቂት ስኬታማ ሰዎች ታሪክ ሳይሆን፣ መላው አህጉሪቱ እያሳየችው ያለውን የእድገት ጉዞና አጠቃላይ እንቅስቃሴ የሚያሳይ መሆኑ ተመልክቷል።
አዘጋጆቹ መላው የአፍሪካ ሕዝብና ትውልደ አፍሪካውያን በፈጠራ ሥራዎቻቸው፣ ስኬቶቻቸውና አዳዲስ ሐሳቦቻቸው ላይ ያተኮሩ ታሪኮችን በ#notwaiting የሃሽታግ ምልክት በመጠቀም በማኅበራዊ ሚዲያዎች እንዲያጋሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በተጨማሪም ፍላጎት ያላቸው ወገኖች www.notwaiting.africa በተሰኘው ድረ-ገጽ ላይ በመግባት የዘመቻውን ማኒፌስቶ መፈረም እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህ ዘመቻ ዛሬ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ በየወሩ በ25ኛው ቀን እየታደሰ የሚቀጥልና አፍሪካውያን በአንድነት በመሆን የኢንተርኔት ዓለምን በስኬት፣ በፈጠራና በዕድሎች ታሪክ የሚያጥለቀልቁበት ተከታታይ መድረክ እንደሚሆን ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) እግር ኳስ የድሃ እና የሀብታም ልዩነትን የሚያጠፋ ልዩ ስፖርት ነው። ከሪዮ ዴጄኔሮ እና ናይሮቢ መንደሮች እስከ ሞናኮ እና ቤቨርሊ ሂልስ የቅንጦት መንደሮች ድረስ ልጆች እግር ኳስን ሲጫወቱ ማየት የተለመደ ነው። ይህ ስፖርት ከዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የተነሱ በርካታ ተጫዋቾችን የሀገር ጀግና እና የዓለም ምልክት ለማድረግ ችሏል።
የምንጊዜም ምርጥ 10 የዓለም ዋንጫ ጀግኖችን በተመለከተ ለበርካታ አስርት ዓመታት አከራካሪ ሆኖ ቆይቷል። ውይይቱ እግር ኳስ እስካለ ድረስ የሚቀጥል ቢሆንም፣ ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በፊት የተመረጡትን የምንጊዜም ምርጥ 10 የዓለም ዋንጫ ጀግኖች ዝርዝር እንደሚከተለው አቅርበነዋል፦
10. ዚነዲን ዚዳን (ፈረንሳይ)
ከምንጊዜም ምርጥ እና አነጋጋሪ ተጫዋቾች አንዱ የሆነው ዚዳን፣ በ1998ቱ የዓለም ዋንጫ ሀገሩ ፈረንሳይ ዋንጫውን ስታነሳ በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል። በ2006ቱ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ በጣሊያኑ ተጫዋች ማትራዚ ላይ በፈጸመው ታሪካዊ የጭንቅላት ምት (Headbutt) በቀይ ካርድ ከሜዳ ቢወጣም፣ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ሆኖ ተመርጧል። ለፈረንሳይ በ108 ጨዋታዎች 31 ግቦችን ሲያስቆጥር፣ በአሰልጣኝነትም ከሪያል ማድሪድ ጋር ሦስት የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎችን አግኝቷል።
9. ጂሚ ግሪቭስ (እንግሊዝ)
እንደ ቦቢ ሙር ያሉ ታላላቅ ተጫዋቾች ቢኖሩም፣ በእንግሊዝ ደጋፊዎች ዘንድ እንደ ጂሚ ግሪቭስ የተወደደ አልነበረም። በ1962ቱ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ላይ ወደ ሜዳ የገባን ውሻ በመያዝ ታዋቂነትን ያተረፈ ሲሆን፣ በ1966ቱ የእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ስብስብ ውስጥም ቁልፍ ተጫዋች ነበር። በእንግሊዝ ብሔራዊ ማሊያ 6 ጊዜ ሃት-ትሪክ የሰራ ሲሆን፣ ክብረወሰኑም እስካሁን አልተሰበረም።
8. ፌረንች ፑሽካሽ (ሀንጋሪ)
የሀንጋሪ ወርቃማ ትውልድ ቡድን አምበል የነበረው ፑሽካሽ፣ ለሀንጋሪ ባደረጋቸው 85 ጨዋታዎች 84 ግቦችን አስቆጥሯል። ሀንጋሪ በእሱ መሪነት በ1950ዎቹ እጅግ አስፈሪ ቡድን የነበረች ሲሆን፣ በ10 ዓመት ውስጥ የተሸነፈችው የ1954ቱን የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ ብቻ ነበር። በአጠቃላይ በሙያው ባደረጋቸው 705 ጨዋታዎች 702 ግቦችን አስቆጥሯል።
7. ሎታር ማቲዎስ (ጀርመን)
ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን 150 ጨዋታዎችን በማድረግ ክብረወሰን የያዘው ማቲዎስ፣ በአምስት የዓለም ዋንጫዎች ላይ የተሳተፈ ሲሆን፣ በ1990 ምዕራብ ጀርመን ዋንጫውን እንድታነሳ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ብዙ ጨዋታዎችን (25) በማድረግም ክብረወሰን ይዟል። ታላቁ ማራዶና "በህይወቴ ከገጠሙኝ ተጫዋቾች ሁሉ እጅግ ከባዱ እሱ ነበር" ሲል መስክሮለታል።
6. ሚሮስላቭ ክሎዘ (ጀርመን)
በስፖርታዊ ጨዋነቱ (Fair play) ወደር የማይገኝለት ክሎዘ፣ በዓለም ዋንጫ ታሪክ 16 ግቦችን በማስቆጠር የምንጊዜም ከፍተኛው የግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰን ባለቤት ነው። በአራት የዓለም ዋንጫዎች ላይ ግብ ያስቆጠረ ሲሆን፣ በ2014 የዓለም ዋንጫን ከጀርመን ጋር አንስቷል። ለሀገሩ በ137 ጨዋታዎች 71 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል።
5. ሮናልዶ ናዛሪዮ (ብራዚል)
"ዘ ፌኖሜኖን" በመባል የሚታወቀው ሮናልዶ፣ ገና በ17 ዓመቱ በ1994 የዓለም ዋንጫን አሸንፏል። በ1998ቱ የዓለም ዋንጫ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ሲባል፣ በ2002ቱ ፍጻሜ ደግሞ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ብራዚልን ለድል አብቅቷል። በዓለም ዋንጫ ታሪክ 15 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፤ ፍጥነቱ፣ ኳስ የመቆጣጠር ችሎታው እና አጨራረሱ ወደር አይገኝለትም።
4. ፍራንዝ ቤከንባወር (ጀርመን)
በእግር ኳስ ታሪክ እንደ ተጫዋችም ሆነ እንደ አሰልጣኝ የዓለም ዋንጫን ካነሱ ሦስት ሰዎች አንዱ ነው። በ1974 የዓለም ዋንጫውን የጀርመን አምበል ሆኖ ሲያነሳ፣ በ1990 ደግሞ በዋና አሰልጣኝነት አሸንፏል። ተከላካይ ቢሆንም ለሀገሩ 14 ግቦችን በ103 ጨዋታዎች አስቆጥሯል።
3. ዮሃን ክራይፍ (ኔዘርላንድስ)
ባሎን ዶርን ሦስት ጊዜ ያሸነፈው ክራይፍ፣ የ"ቶታል ፉትቦል" ፍልስፍና አባት ነው። እግር ኳስን ከጉልበት ስፖርትነት ወደ ጥበብ እና ውበት የቀየረ ታላቅ ፈጣሪ ነበር። በ1974 ኔዘርላንድስን እስከ ፍጻሜ ያደረሰ ሲሆን፣ እርሱ ግብ ባስቆጠረባቸው ጨዋታዎች ሀገሩ ተሸንፋ አታውቅም (በ48 ጨዋታዎች 33 ግቦች)።
2. ዲዬጎ ማራዶና (አርጀንቲና)
በእግር ኳስ ታሪክ አቻ ከሌላቸው ተጫዋቾች አንዱ ነው። በ1986 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በእንግሊዝ ላይ ያስቆጠራት "የክፍለ ዘመኑ ምርጥ ጎል" እና በውዝግብ የምትታወቀው "የፈጣሪ እጅ" ግቡ አይረሱም። በዛው ዓመት አርጀንቲናን ለዓለም ዋንጫ ድል አብቅቷል።
1. ፔሌ (ብራዚል)
ከብራዚሉ ፔሌ የበለጠ የተሳካ የእግር ኳስ አዶ የለም። የዓለም ዋንጫን ሦስት ጊዜ (1958፣ 1962 እና 1970) ያነሳ ብቸኛው ተጫዋች ነው። ለብራዚል በ92 ጨዋታዎች 77 ግቦችን አስቆጥሯል። ታዋቂነቱ ከማየሉ የተነሳ በ1969 በናይጄሪያ የእርስ በእርስ ጦርነት ወቅት እርሱ የሚጫወትበትን ጨዋታ ለማየት ሲባል ጦርነቱ ለጊዜው እንዲቆም ተደርጎ ነበር። ፔሌ እግር ኳስን ወደ ላቀ የጥበብ ደረጃ ያደረሰ የምንጊዜም ምርጥ ተጫዋች ነው።
የምንጊዜም ምርጥ 10 የዓለም ዋንጫ ጀግኖችን በተመለከተ ለበርካታ አስርት ዓመታት አከራካሪ ሆኖ ቆይቷል። ውይይቱ እግር ኳስ እስካለ ድረስ የሚቀጥል ቢሆንም፣ ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በፊት የተመረጡትን የምንጊዜም ምርጥ 10 የዓለም ዋንጫ ጀግኖች ዝርዝር እንደሚከተለው አቅርበነዋል፦
10. ዚነዲን ዚዳን (ፈረንሳይ)
ከምንጊዜም ምርጥ እና አነጋጋሪ ተጫዋቾች አንዱ የሆነው ዚዳን፣ በ1998ቱ የዓለም ዋንጫ ሀገሩ ፈረንሳይ ዋንጫውን ስታነሳ በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል። በ2006ቱ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ በጣሊያኑ ተጫዋች ማትራዚ ላይ በፈጸመው ታሪካዊ የጭንቅላት ምት (Headbutt) በቀይ ካርድ ከሜዳ ቢወጣም፣ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ሆኖ ተመርጧል። ለፈረንሳይ በ108 ጨዋታዎች 31 ግቦችን ሲያስቆጥር፣ በአሰልጣኝነትም ከሪያል ማድሪድ ጋር ሦስት የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎችን አግኝቷል።
9. ጂሚ ግሪቭስ (እንግሊዝ)
እንደ ቦቢ ሙር ያሉ ታላላቅ ተጫዋቾች ቢኖሩም፣ በእንግሊዝ ደጋፊዎች ዘንድ እንደ ጂሚ ግሪቭስ የተወደደ አልነበረም። በ1962ቱ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ላይ ወደ ሜዳ የገባን ውሻ በመያዝ ታዋቂነትን ያተረፈ ሲሆን፣ በ1966ቱ የእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ስብስብ ውስጥም ቁልፍ ተጫዋች ነበር። በእንግሊዝ ብሔራዊ ማሊያ 6 ጊዜ ሃት-ትሪክ የሰራ ሲሆን፣ ክብረወሰኑም እስካሁን አልተሰበረም።
8. ፌረንች ፑሽካሽ (ሀንጋሪ)
የሀንጋሪ ወርቃማ ትውልድ ቡድን አምበል የነበረው ፑሽካሽ፣ ለሀንጋሪ ባደረጋቸው 85 ጨዋታዎች 84 ግቦችን አስቆጥሯል። ሀንጋሪ በእሱ መሪነት በ1950ዎቹ እጅግ አስፈሪ ቡድን የነበረች ሲሆን፣ በ10 ዓመት ውስጥ የተሸነፈችው የ1954ቱን የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ ብቻ ነበር። በአጠቃላይ በሙያው ባደረጋቸው 705 ጨዋታዎች 702 ግቦችን አስቆጥሯል።
7. ሎታር ማቲዎስ (ጀርመን)
ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን 150 ጨዋታዎችን በማድረግ ክብረወሰን የያዘው ማቲዎስ፣ በአምስት የዓለም ዋንጫዎች ላይ የተሳተፈ ሲሆን፣ በ1990 ምዕራብ ጀርመን ዋንጫውን እንድታነሳ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ብዙ ጨዋታዎችን (25) በማድረግም ክብረወሰን ይዟል። ታላቁ ማራዶና "በህይወቴ ከገጠሙኝ ተጫዋቾች ሁሉ እጅግ ከባዱ እሱ ነበር" ሲል መስክሮለታል።
6. ሚሮስላቭ ክሎዘ (ጀርመን)
በስፖርታዊ ጨዋነቱ (Fair play) ወደር የማይገኝለት ክሎዘ፣ በዓለም ዋንጫ ታሪክ 16 ግቦችን በማስቆጠር የምንጊዜም ከፍተኛው የግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰን ባለቤት ነው። በአራት የዓለም ዋንጫዎች ላይ ግብ ያስቆጠረ ሲሆን፣ በ2014 የዓለም ዋንጫን ከጀርመን ጋር አንስቷል። ለሀገሩ በ137 ጨዋታዎች 71 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል።
5. ሮናልዶ ናዛሪዮ (ብራዚል)
"ዘ ፌኖሜኖን" በመባል የሚታወቀው ሮናልዶ፣ ገና በ17 ዓመቱ በ1994 የዓለም ዋንጫን አሸንፏል። በ1998ቱ የዓለም ዋንጫ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ሲባል፣ በ2002ቱ ፍጻሜ ደግሞ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ብራዚልን ለድል አብቅቷል። በዓለም ዋንጫ ታሪክ 15 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፤ ፍጥነቱ፣ ኳስ የመቆጣጠር ችሎታው እና አጨራረሱ ወደር አይገኝለትም።
4. ፍራንዝ ቤከንባወር (ጀርመን)
በእግር ኳስ ታሪክ እንደ ተጫዋችም ሆነ እንደ አሰልጣኝ የዓለም ዋንጫን ካነሱ ሦስት ሰዎች አንዱ ነው። በ1974 የዓለም ዋንጫውን የጀርመን አምበል ሆኖ ሲያነሳ፣ በ1990 ደግሞ በዋና አሰልጣኝነት አሸንፏል። ተከላካይ ቢሆንም ለሀገሩ 14 ግቦችን በ103 ጨዋታዎች አስቆጥሯል።
3. ዮሃን ክራይፍ (ኔዘርላንድስ)
ባሎን ዶርን ሦስት ጊዜ ያሸነፈው ክራይፍ፣ የ"ቶታል ፉትቦል" ፍልስፍና አባት ነው። እግር ኳስን ከጉልበት ስፖርትነት ወደ ጥበብ እና ውበት የቀየረ ታላቅ ፈጣሪ ነበር። በ1974 ኔዘርላንድስን እስከ ፍጻሜ ያደረሰ ሲሆን፣ እርሱ ግብ ባስቆጠረባቸው ጨዋታዎች ሀገሩ ተሸንፋ አታውቅም (በ48 ጨዋታዎች 33 ግቦች)።
2. ዲዬጎ ማራዶና (አርጀንቲና)
በእግር ኳስ ታሪክ አቻ ከሌላቸው ተጫዋቾች አንዱ ነው። በ1986 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በእንግሊዝ ላይ ያስቆጠራት "የክፍለ ዘመኑ ምርጥ ጎል" እና በውዝግብ የምትታወቀው "የፈጣሪ እጅ" ግቡ አይረሱም። በዛው ዓመት አርጀንቲናን ለዓለም ዋንጫ ድል አብቅቷል።
1. ፔሌ (ብራዚል)
ከብራዚሉ ፔሌ የበለጠ የተሳካ የእግር ኳስ አዶ የለም። የዓለም ዋንጫን ሦስት ጊዜ (1958፣ 1962 እና 1970) ያነሳ ብቸኛው ተጫዋች ነው። ለብራዚል በ92 ጨዋታዎች 77 ግቦችን አስቆጥሯል። ታዋቂነቱ ከማየሉ የተነሳ በ1969 በናይጄሪያ የእርስ በእርስ ጦርነት ወቅት እርሱ የሚጫወትበትን ጨዋታ ለማየት ሲባል ጦርነቱ ለጊዜው እንዲቆም ተደርጎ ነበር። ፔሌ እግር ኳስን ወደ ላቀ የጥበብ ደረጃ ያደረሰ የምንጊዜም ምርጥ ተጫዋች ነው።
3 months ago
በኬንያ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ጭማሪ መደረጉን የተቃወሙ አሽከርካሪዎች ሥራ አቆሙ
ኬንያውያን አሽከርካሪዎች እና የመኪና ባለንብረቶች ባለፈው ሳምንት የተደረገውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በመቃወም ሥራ በማቆማቸው በሺህዎች የሚቆጠሩ መንገደኞች እና ንግዶች ተስተጓጉለዋል።
በኬንያ ናይሮቢ ዋና ዋና መንገዶች እንቅስቃሴ አልባ ሆነው ያረፈዱ ሲሆን፣ የተወሰኑ መንገደኞች በእግራቸው ከቦታ ወደ ቦታ ለመንቀሳቀስ ተገድደዋል።
በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎችም የትራንስፖርት አገልግሎት በመቋረጡ ሥራ መስተጓጎሉ ተሰምቷል።
በዋና ከተማዋ ናይሮቢ የንግድ ሱቆች የተዘጉ ሲሆን፣ ተማሪዎችም ወደ ትምህርት ቤት እንዳይሄዱ ተደርገዋል።
የመንግሥትን የዋጋ ጭማሪ የተቃወሙ ሰዎች መንገዶችን በድንጋይ በመዝጋት ጎማዎችን አቃጥለዋል።
አሽከርካሪዎች እና የመኪና ባለቤቶች ተቃውሟቸውን የገለጹት ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የነዳጅ ዋጋ ላይ የ20 በመቶ ጭማሪ በመደረጉ ነው።
ኬንያ ነዳጅ የምታስገባው ከባሕረ ሰላጤው አገራት በመሆኑ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጦርነት ከከፈቱ በኋላ አቅርቦቱ ተስተጓጉሏል።
ምንም እንኳን በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ቢደረስም የዓለም አንድ አምስተኛ የሆነው ነዳጅ የሚተላለፍበት ሆርሙዝ አሁንም እንደተዘጋ ይገኛል።
ባለፈው ሳምንት የተገለጸውን የዋጋ ጭማሪ እንዲቀለበስ እና የነዳጅ ዋጋ በ35 በመቶ እንዲቀንስ ጥሪ አቅርቧል።
የኢነርጂ እና የነዳጅ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ናፍጣ እና ቤንዚን በአንድ ሊትር ወደ 242 ሽልንግ (1.8 ዶላር እና 1.65 ዶላር) ከፍ አድርጓል።
የገንዘብ ሚኒስትሩ ጆን ምባዲ ሰኞ ዕለት ለኤንቲቪ እንደተናገሩት የነዳጅ ዋጋ መጨመር "አሳዛኝ" መሆኑን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚውን እየጎዳ መሆኑን ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ተቃውሞውን "ፈጽሞ አላስፈላጊ" ሲሉ ጠርተው መንግሥት "ከስሜት ይልቅ በመረጃ ላይ የተመሠረቱ ውሳኔዎችን" ብቻ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
"ለምን አንድን ዓለም አቀፍ ችግር በአገር ውስጥ መንገዶች ለመፍታት እንሞክራለን?" ሲሉም ጠይቀዋል።
የነዳጅ ዋጋ በመጨመሩ የምግብ እና ለሌሎች መሠረታዊ ሸቀጦች እና አገልግሎቶች ዋጋ እንዲጨምር ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን፣ የሕዝብ አገልግሎት ተሽከርካሪዎች የመጓጓዣ ዋጋን አስቀድመው ጨምረዋል።
ባለፈው ወር መንግሥት እስከ ሐምሌ ወር ድረስ በነዳጅ ላይ ያለውን የተጨማሪ እሴት ታክስ ከ16 በመቶ ወደ 8 በመቶ የቀነሰ ቢሆንም ተጨማሪ እርምጃዎችን እንዲወስድ ተጠይቋል።
BBC
ኬንያውያን አሽከርካሪዎች እና የመኪና ባለንብረቶች ባለፈው ሳምንት የተደረገውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በመቃወም ሥራ በማቆማቸው በሺህዎች የሚቆጠሩ መንገደኞች እና ንግዶች ተስተጓጉለዋል።
በኬንያ ናይሮቢ ዋና ዋና መንገዶች እንቅስቃሴ አልባ ሆነው ያረፈዱ ሲሆን፣ የተወሰኑ መንገደኞች በእግራቸው ከቦታ ወደ ቦታ ለመንቀሳቀስ ተገድደዋል።
በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎችም የትራንስፖርት አገልግሎት በመቋረጡ ሥራ መስተጓጎሉ ተሰምቷል።
በዋና ከተማዋ ናይሮቢ የንግድ ሱቆች የተዘጉ ሲሆን፣ ተማሪዎችም ወደ ትምህርት ቤት እንዳይሄዱ ተደርገዋል።
የመንግሥትን የዋጋ ጭማሪ የተቃወሙ ሰዎች መንገዶችን በድንጋይ በመዝጋት ጎማዎችን አቃጥለዋል።
አሽከርካሪዎች እና የመኪና ባለቤቶች ተቃውሟቸውን የገለጹት ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የነዳጅ ዋጋ ላይ የ20 በመቶ ጭማሪ በመደረጉ ነው።
ኬንያ ነዳጅ የምታስገባው ከባሕረ ሰላጤው አገራት በመሆኑ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጦርነት ከከፈቱ በኋላ አቅርቦቱ ተስተጓጉሏል።
ምንም እንኳን በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ቢደረስም የዓለም አንድ አምስተኛ የሆነው ነዳጅ የሚተላለፍበት ሆርሙዝ አሁንም እንደተዘጋ ይገኛል።
ባለፈው ሳምንት የተገለጸውን የዋጋ ጭማሪ እንዲቀለበስ እና የነዳጅ ዋጋ በ35 በመቶ እንዲቀንስ ጥሪ አቅርቧል።
የኢነርጂ እና የነዳጅ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ናፍጣ እና ቤንዚን በአንድ ሊትር ወደ 242 ሽልንግ (1.8 ዶላር እና 1.65 ዶላር) ከፍ አድርጓል።
የገንዘብ ሚኒስትሩ ጆን ምባዲ ሰኞ ዕለት ለኤንቲቪ እንደተናገሩት የነዳጅ ዋጋ መጨመር "አሳዛኝ" መሆኑን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚውን እየጎዳ መሆኑን ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ተቃውሞውን "ፈጽሞ አላስፈላጊ" ሲሉ ጠርተው መንግሥት "ከስሜት ይልቅ በመረጃ ላይ የተመሠረቱ ውሳኔዎችን" ብቻ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
"ለምን አንድን ዓለም አቀፍ ችግር በአገር ውስጥ መንገዶች ለመፍታት እንሞክራለን?" ሲሉም ጠይቀዋል።
የነዳጅ ዋጋ በመጨመሩ የምግብ እና ለሌሎች መሠረታዊ ሸቀጦች እና አገልግሎቶች ዋጋ እንዲጨምር ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን፣ የሕዝብ አገልግሎት ተሽከርካሪዎች የመጓጓዣ ዋጋን አስቀድመው ጨምረዋል።
ባለፈው ወር መንግሥት እስከ ሐምሌ ወር ድረስ በነዳጅ ላይ ያለውን የተጨማሪ እሴት ታክስ ከ16 በመቶ ወደ 8 በመቶ የቀነሰ ቢሆንም ተጨማሪ እርምጃዎችን እንዲወስድ ተጠይቋል።
BBC
3 months ago
በኬንያ የነዳጅ ዋጋ መናር ከፍተኛ ሕዝባዊ ተቃውሞ አስነሳ
#ethiopia | በባለፈው ሳምንት በኬንያ የተደረገውንና ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የ20 በመቶ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በመቃወም አሽከርካሪዎች በመላው አገሪቱ የሚገኙ የትራንስፖርት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ ያደናቀፈ የሥራ ማቆም አድማ ማድረጋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
በዚህ የተቃውሞ እርምጃ ምክንያት በዋና ከተማዋ ናይሮቢና በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ መንገዶች ዝግ ሆነው የዋሉ ሲሆን፣ የንግድ ተቋማት ተዘግተውና ተማሪዎችም ከቤታቸው ሳይወጡ እንዲቀሩ ተደርጓል።
ለዚህ የዋጋ ጭማሪ ዋነኛው መንስኤ በአሜሪካና በኢራን መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት ሳቢያ የዓለም አንድ አምስተኛ የነዳጅ ምርት የሚጓጓዝበት የሆርሙዝ ወሽመጥ አሁንም ተዘግቶ በመቆየቱና የባሕረ ሰላጤው የነዳጅ አቅርቦት በመስተጓጎሉ ነው።
የኬንያ የትራንስፖርት ዘርፍ ጥምረት መንግሥት ዜጎቹን ከከፍተኛ የኑሮ ውድነት መከላከል አልቻለም ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ የነዳጅ ዋጋ በአስቸኳይ በ35 በመቶ እንዲቀነስ ጠይቋል።
በአንጻሩ የኬንያው የገንዘብ ሚኒስትር ጆን ምባዲ የተፈጠረው የዋጋ ጭማሪ አሳዛኝ መሆኑን ቢያምኑም፣ የተነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ግን ፈጽሞ አላስፈላጊ ሲሉ አጣጥለውታል።
ሚኒስትሩ መንግሥት ውሳኔዎችን የሚያሳልፈው ተጨባጭ መረጃዎችን መሠረት በማድረግ መሆኑን ገልጸው፣ የዓለም አቀፍ ችግርን በአገር ውስጥ መንገዶች ለመፍታት መሞከር ተገቢ አለመሆኑን መጠየቃቸውን ቢቢሲ ጨምሮ አስታውቋል።
#kenya #fuelprice #protest #africa #economy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በባለፈው ሳምንት በኬንያ የተደረገውንና ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የ20 በመቶ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በመቃወም አሽከርካሪዎች በመላው አገሪቱ የሚገኙ የትራንስፖርት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ ያደናቀፈ የሥራ ማቆም አድማ ማድረጋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
በዚህ የተቃውሞ እርምጃ ምክንያት በዋና ከተማዋ ናይሮቢና በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ መንገዶች ዝግ ሆነው የዋሉ ሲሆን፣ የንግድ ተቋማት ተዘግተውና ተማሪዎችም ከቤታቸው ሳይወጡ እንዲቀሩ ተደርጓል።
ለዚህ የዋጋ ጭማሪ ዋነኛው መንስኤ በአሜሪካና በኢራን መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት ሳቢያ የዓለም አንድ አምስተኛ የነዳጅ ምርት የሚጓጓዝበት የሆርሙዝ ወሽመጥ አሁንም ተዘግቶ በመቆየቱና የባሕረ ሰላጤው የነዳጅ አቅርቦት በመስተጓጎሉ ነው።
የኬንያ የትራንስፖርት ዘርፍ ጥምረት መንግሥት ዜጎቹን ከከፍተኛ የኑሮ ውድነት መከላከል አልቻለም ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ የነዳጅ ዋጋ በአስቸኳይ በ35 በመቶ እንዲቀነስ ጠይቋል።
በአንጻሩ የኬንያው የገንዘብ ሚኒስትር ጆን ምባዲ የተፈጠረው የዋጋ ጭማሪ አሳዛኝ መሆኑን ቢያምኑም፣ የተነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ግን ፈጽሞ አላስፈላጊ ሲሉ አጣጥለውታል።
ሚኒስትሩ መንግሥት ውሳኔዎችን የሚያሳልፈው ተጨባጭ መረጃዎችን መሠረት በማድረግ መሆኑን ገልጸው፣ የዓለም አቀፍ ችግርን በአገር ውስጥ መንገዶች ለመፍታት መሞከር ተገቢ አለመሆኑን መጠየቃቸውን ቢቢሲ ጨምሮ አስታውቋል።
#kenya #fuelprice #protest #africa #economy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
3 months ago
በቦይንግ 737 ማክስ አደጋ ህይወቷ ለጠፋው ሳምያ ስቱሞ ቤተሰቦች የ49.5 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ተፈረደ!
በቺካጎ የሚገኝ የፍርድ ቤት ዳኝነት፣ እ.ኤ.አ በ2019 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ህይወቷ ለጠፋው አሜሪካዊቷ ሳምያ ስቱሞ ቤተሰቦች የ49.5 ሚሊዮን ዶላር የካሳ ክፍያ እንዲፈጸም ወሰነ።ይህ የፍርድ ቤት ውሳኔ በዓለም ዙሪያ የ346 ሰዎችን ህይወት በቀጠፉት በሁለቱ የቦይንግ 737 ማክስ አሰቃቂ አደጋዎች ምክንያት በቦይንግ ኩባንያ ላይ የተሰጠ ሁለተኛው ትልቅ የዳኝነት ውሳኔ ነው።
የ24 ዓመቷ ሳምያ ስቱሞ በአውሮፕላን ደህንነት ላይ የምትሰራ ወጣት የነበረች ሲሆን፣ እ.ኤ.አ መጋቢት 10 ቀን 2019 የአውሮፕላን በረራ ቁጥር ET 302 ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ ናይሮቢ በመጓዝ ላይ ሳለ ቢሾፍቱ አቅራቢያ በደረሰው አደጋ ህይወታቸው ካለፈው 157 ሰዎች መካከል አንዷ ነበረች። ይህ አደጋ ከመድረሱ ከአምስት ወራት በፊት በኢንዶኔዢያ የሊዮን ኤር አውሮፕላን በተመሳሳይ ችግር ተከስክሶ የነበረ ሲሆን፣ የቺካጎ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቦይንግ ኩባንያ በአውሮፕላኑ የቴክኖሎጂ አሰራር ላይ ለነበረበት ከፍተኛ የቸልተኝነት ጉድለት ተጠያቂ መሆኑን በድጋሚ ያረጋገጠ ሆኗል።
seledadotio
seledadotio
በቺካጎ የሚገኝ የፍርድ ቤት ዳኝነት፣ እ.ኤ.አ በ2019 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ህይወቷ ለጠፋው አሜሪካዊቷ ሳምያ ስቱሞ ቤተሰቦች የ49.5 ሚሊዮን ዶላር የካሳ ክፍያ እንዲፈጸም ወሰነ።ይህ የፍርድ ቤት ውሳኔ በዓለም ዙሪያ የ346 ሰዎችን ህይወት በቀጠፉት በሁለቱ የቦይንግ 737 ማክስ አሰቃቂ አደጋዎች ምክንያት በቦይንግ ኩባንያ ላይ የተሰጠ ሁለተኛው ትልቅ የዳኝነት ውሳኔ ነው።
የ24 ዓመቷ ሳምያ ስቱሞ በአውሮፕላን ደህንነት ላይ የምትሰራ ወጣት የነበረች ሲሆን፣ እ.ኤ.አ መጋቢት 10 ቀን 2019 የአውሮፕላን በረራ ቁጥር ET 302 ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ ናይሮቢ በመጓዝ ላይ ሳለ ቢሾፍቱ አቅራቢያ በደረሰው አደጋ ህይወታቸው ካለፈው 157 ሰዎች መካከል አንዷ ነበረች። ይህ አደጋ ከመድረሱ ከአምስት ወራት በፊት በኢንዶኔዢያ የሊዮን ኤር አውሮፕላን በተመሳሳይ ችግር ተከስክሶ የነበረ ሲሆን፣ የቺካጎ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቦይንግ ኩባንያ በአውሮፕላኑ የቴክኖሎጂ አሰራር ላይ ለነበረበት ከፍተኛ የቸልተኝነት ጉድለት ተጠያቂ መሆኑን በድጋሚ ያረጋገጠ ሆኗል።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ፦ ከታሪካዊ ወዳጅነት ወደ ስትራቴጂያዊ አጋርነት
*********************
የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የዘመናት ታሪክ ያለው ብቻ ሳይሆን፣ በጋራ ጥቅም እና በእርስ በርስ መከባበር ላይ የቆመ ብርቱ ወዳጅነት ነው።
ይህ ግንኙነት ዛሬ ላይ ከታሪክ ባለፈ ለቀጣናዊ ሰላም እና ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ ምሰሶ ሆኗል።
ከመቶ ዓመታት በፊት የተገነባው እና አዲስ አበባን ከጅቡቲ ያቆራኘው የባቡር መስመር የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ጥንካሬ ማሳያ ነው። ይህ ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ከዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ጋር በማስተሳሰር ግንኙነቱ በሉዓላዊ እኩልነት ላይ የተመሠረተ መሆኑን በተግባር ያሳየ ነበር።
ፈረንሳይ የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ አግባብነት እና ሕጋዊነት በግልጽ ከሚደግፉ ሀገራት ቀዳሚዋ ናት።
የፕሬዚዳንት ማክሮን አቋም፦ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ እና በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት የፈረንሳይን ሙሉ ድጋፍ ያገኛል።
የባሕር ኃይል ግንባታ፦ የኢትዮጵያን የባሕር ኃይል መልሶ ለማደራጀት እና አባላቱን ለማሰልጠን የሚደረገው የመከላከያ ትብብር ሀገራቱ ለባሕር ደኅንነት ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
የሁለቱ ሀገራት የኢኮኖሚ ትብብር ከተለምዷዊው ‘የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ' ግንኙነት ወጥቶ ወደ ኢንቨስትመንት እና የጋራ ምርታማነት ተሸጋግሯል።
አረንጓዴ ኢነርጂ፦ በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባኤ ላይ እንደተገለጸው፣ ፈረንሳይ በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ እና ታዳሽ ኃይል ላይ በትኩረት እየሠራች ትገኛለች።
የገንዘብ ድጋፍ፦ የፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ (AFD) ለኤሌክትሪክ ኃይል መረብ ማዘመኛ የ80 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ፈቅዷል።
ቅርሶችን መጠበቅ፦ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመጠገን የተደረሰው ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ጥልቅ የባሕል ትሥሥር ያሳያል።
የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ ግንኙነት ታሪካዊ መከባበርን መሠረት አድርጎ፣ ዛሬ ላይ አስተማማኝ ወደሆነ ስትራቴጂያዊ እና ኢኮኖሚያዊ አጋርነት ተሸጋግሯል!
በለሚ ታደሰ
የዚህን መረጃ ሙሉ ሐሳብ አስተያየት መስጫው ውስጥ ካለው ሊንክ ያገኛሉ
#ethiopia #france #diplomacy #history #lalibela #ethiofrance
*********************
የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የዘመናት ታሪክ ያለው ብቻ ሳይሆን፣ በጋራ ጥቅም እና በእርስ በርስ መከባበር ላይ የቆመ ብርቱ ወዳጅነት ነው።
ይህ ግንኙነት ዛሬ ላይ ከታሪክ ባለፈ ለቀጣናዊ ሰላም እና ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ ምሰሶ ሆኗል።
ከመቶ ዓመታት በፊት የተገነባው እና አዲስ አበባን ከጅቡቲ ያቆራኘው የባቡር መስመር የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ጥንካሬ ማሳያ ነው። ይህ ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ከዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ጋር በማስተሳሰር ግንኙነቱ በሉዓላዊ እኩልነት ላይ የተመሠረተ መሆኑን በተግባር ያሳየ ነበር።
ፈረንሳይ የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ አግባብነት እና ሕጋዊነት በግልጽ ከሚደግፉ ሀገራት ቀዳሚዋ ናት።
የፕሬዚዳንት ማክሮን አቋም፦ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ እና በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት የፈረንሳይን ሙሉ ድጋፍ ያገኛል።
የባሕር ኃይል ግንባታ፦ የኢትዮጵያን የባሕር ኃይል መልሶ ለማደራጀት እና አባላቱን ለማሰልጠን የሚደረገው የመከላከያ ትብብር ሀገራቱ ለባሕር ደኅንነት ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
የሁለቱ ሀገራት የኢኮኖሚ ትብብር ከተለምዷዊው ‘የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ' ግንኙነት ወጥቶ ወደ ኢንቨስትመንት እና የጋራ ምርታማነት ተሸጋግሯል።
አረንጓዴ ኢነርጂ፦ በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባኤ ላይ እንደተገለጸው፣ ፈረንሳይ በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ እና ታዳሽ ኃይል ላይ በትኩረት እየሠራች ትገኛለች።
የገንዘብ ድጋፍ፦ የፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ (AFD) ለኤሌክትሪክ ኃይል መረብ ማዘመኛ የ80 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ፈቅዷል።
ቅርሶችን መጠበቅ፦ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመጠገን የተደረሰው ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ጥልቅ የባሕል ትሥሥር ያሳያል።
የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ ግንኙነት ታሪካዊ መከባበርን መሠረት አድርጎ፣ ዛሬ ላይ አስተማማኝ ወደሆነ ስትራቴጂያዊ እና ኢኮኖሚያዊ አጋርነት ተሸጋግሯል!
በለሚ ታደሰ
የዚህን መረጃ ሙሉ ሐሳብ አስተያየት መስጫው ውስጥ ካለው ሊንክ ያገኛሉ
#ethiopia #france #diplomacy #history #lalibela #ethiofrance
3 months ago
የአይ.ኤም.ኤፍ እና የኢትዮጵያ መንግሥት 5ኛውን የኢኮኖሚ ግምገማ ጀመሩ፤ የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ተፅዕኖ የውይይቱ ትኩረት ሆኗል
#ethiopia | በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ ) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በአምስተኛው የተራዘመ ብድር አቅርቦት ፕሮግራም ክለሳ ላይ ውይይት እያደረገ ይገኛል።
የዚህ ውይይት ዋነኛ ትኩረት በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ለመቋቋም የሚያስችሉ የፖሊሲ እርምጃዎችን መቀየስ ነው።
ወይዘሮ ጆርጂየቫ ናይሮቢ ለሚካሄደው የ"Africa Forward" ጉባኤ ሲጓዙ አዲስ አበባ ላይ በነበራቸው ቆይታ፤ ኢትዮጵያ የምትከተለው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አበረታች መሆኑን ገልጸው፣ ሆኖም የውጭ ተፅዕኖዎች የሀገሪቱን ጥንካሬ እየፈተኑ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ቢኖርም፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ባሳየችው ጠንካራ እድገት፣ የወጪ ንግድ አፈጻጸም እና ከመንግስት ገቢ አሰባሰብ አንጻር ለገጠማት ድንገተኛ ጫና ዝግጁ ሆና መገኘቷን ዋና ዳይሬክተሯ ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነት በተለይም የሆርሙዝ የባህር በር መዘጋት በኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ስጋት የደቀነ ሲሆን፣ ሀገሪቱ ነዳጅን ሙሉ በሙሉ ከውጭ የምታስገባ በመሆኗ ለዋጋ ንረት ተጋላጭ እንድትሆን አድርጓታል።
ከዚህ በተጨማሪ የማዳበሪያ ዋጋ መጨመር በግብርናው ዘርፍ ላይ ጫና እየፈጠረ ሲሆን፣ ከወርቅ ውጭ ካለው የወጪ ንግድ 19 በመቶው እና ከሃዋላ ገቢ 35 በመቶው ከመካከለኛው ምስራቅና ከባህረ ሰላጤው ሀገራት የሚገኝ በመሆኑ አካባቢው በከፍተኛ ክትትል ስር እንዲውል አድርጓል።
ዋና ዳይሬክተሯ በዚህ አምስተኛ ክለሳ ወቅት ሀብትን በጥንቃቄ ጥቅም ላይ ማዋል ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን አሳስበው፣ የዋጋ ንረቱን ለመቆጣጠር መንግስት ጥብቅ የፊስካልና የገንዘብ ፖሊሲን መከተል እንዳለበት መክረዋል።
በተለይም እንደ ነዳጅ ድጎማ ወይም አጠቃላይ የቀረጥ ቅነሳ ያሉ ኢላማቸውን ያልጠበቁ እርምጃዎች በከፍተኛ ዋጋ ምክንያት የሚመጣውን ስቃይ ከማራዘም ውጭ ፋይዳ እንደሌላቸው በመጥቀስ፤ መንግስት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት እና በሀገሪቱ የፋይናንስ ዘላቂነት መካከል ጥንቃቄ የተሞላበት ሚዛን መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።
በአይኤምኤፍ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው አጋርነት ተጠናክሮ መቀጠሉ የተገለጸ ሲሆን፣ ፕሮግራሙ ከተጀመረ አንስቶ ድርጅቱ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ መልቀቁና ባለፈው ጥር ወር አራተኛው ክለሳ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ይታወሳል።
ኢትዮጵያ በጋራ ማዕቀፍ ስር እያከናወነች ያለው የዕዳ ሽግሽግ ሂደት ከሌሎች ሀገራት በበለጠ ፍጥነት እየተጓዘ መሆኑን ያደነቁት ጆርጂየቫ፣ ይህም ለዓለም አቀፍ ባለሀብቶች ትልቅ የቁርጠኝነት ምልክት መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን በቴክኒክ ባለሙያዎች ደረጃ የቀጠለው አምስተኛው ክለሳ ዋና ዓላማው የሀገር በቀል ማሻሻያው በክልላዊ አለመረጋጋት ሳይደናቀፍ ይልቁንም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማስቻል ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #ቅዳሜገበያ #etbusinessview #ethiopia
#ethiopia | በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ ) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በአምስተኛው የተራዘመ ብድር አቅርቦት ፕሮግራም ክለሳ ላይ ውይይት እያደረገ ይገኛል።
የዚህ ውይይት ዋነኛ ትኩረት በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ለመቋቋም የሚያስችሉ የፖሊሲ እርምጃዎችን መቀየስ ነው።
ወይዘሮ ጆርጂየቫ ናይሮቢ ለሚካሄደው የ"Africa Forward" ጉባኤ ሲጓዙ አዲስ አበባ ላይ በነበራቸው ቆይታ፤ ኢትዮጵያ የምትከተለው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አበረታች መሆኑን ገልጸው፣ ሆኖም የውጭ ተፅዕኖዎች የሀገሪቱን ጥንካሬ እየፈተኑ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ቢኖርም፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ባሳየችው ጠንካራ እድገት፣ የወጪ ንግድ አፈጻጸም እና ከመንግስት ገቢ አሰባሰብ አንጻር ለገጠማት ድንገተኛ ጫና ዝግጁ ሆና መገኘቷን ዋና ዳይሬክተሯ ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነት በተለይም የሆርሙዝ የባህር በር መዘጋት በኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ስጋት የደቀነ ሲሆን፣ ሀገሪቱ ነዳጅን ሙሉ በሙሉ ከውጭ የምታስገባ በመሆኗ ለዋጋ ንረት ተጋላጭ እንድትሆን አድርጓታል።
ከዚህ በተጨማሪ የማዳበሪያ ዋጋ መጨመር በግብርናው ዘርፍ ላይ ጫና እየፈጠረ ሲሆን፣ ከወርቅ ውጭ ካለው የወጪ ንግድ 19 በመቶው እና ከሃዋላ ገቢ 35 በመቶው ከመካከለኛው ምስራቅና ከባህረ ሰላጤው ሀገራት የሚገኝ በመሆኑ አካባቢው በከፍተኛ ክትትል ስር እንዲውል አድርጓል።
ዋና ዳይሬክተሯ በዚህ አምስተኛ ክለሳ ወቅት ሀብትን በጥንቃቄ ጥቅም ላይ ማዋል ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን አሳስበው፣ የዋጋ ንረቱን ለመቆጣጠር መንግስት ጥብቅ የፊስካልና የገንዘብ ፖሊሲን መከተል እንዳለበት መክረዋል።
በተለይም እንደ ነዳጅ ድጎማ ወይም አጠቃላይ የቀረጥ ቅነሳ ያሉ ኢላማቸውን ያልጠበቁ እርምጃዎች በከፍተኛ ዋጋ ምክንያት የሚመጣውን ስቃይ ከማራዘም ውጭ ፋይዳ እንደሌላቸው በመጥቀስ፤ መንግስት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት እና በሀገሪቱ የፋይናንስ ዘላቂነት መካከል ጥንቃቄ የተሞላበት ሚዛን መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።
በአይኤምኤፍ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው አጋርነት ተጠናክሮ መቀጠሉ የተገለጸ ሲሆን፣ ፕሮግራሙ ከተጀመረ አንስቶ ድርጅቱ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ መልቀቁና ባለፈው ጥር ወር አራተኛው ክለሳ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ይታወሳል።
ኢትዮጵያ በጋራ ማዕቀፍ ስር እያከናወነች ያለው የዕዳ ሽግሽግ ሂደት ከሌሎች ሀገራት በበለጠ ፍጥነት እየተጓዘ መሆኑን ያደነቁት ጆርጂየቫ፣ ይህም ለዓለም አቀፍ ባለሀብቶች ትልቅ የቁርጠኝነት ምልክት መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን በቴክኒክ ባለሙያዎች ደረጃ የቀጠለው አምስተኛው ክለሳ ዋና ዓላማው የሀገር በቀል ማሻሻያው በክልላዊ አለመረጋጋት ሳይደናቀፍ ይልቁንም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማስቻል ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #ቅዳሜገበያ #etbusinessview #ethiopia
3 months ago
ፈረንሳይ ለአፍሪካ የ27 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኢንቨስትመንት ዕቅድ ይፋ አደረገች
****************************
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ናይሮቢ በተካሄደ የ"Africa Forward" ጉባኤ ላይ፣ ከአፍሪካ አህጉር ጋር ያለውን ግንኙነት በአዲስ መልክ ለመቅረጽ ያለመ የ23 ቢሊዮን ዩሮ (27 ቢሊዮን ዶላር) የኢንቨስትመንት ዕቅድ ይፋ አድርገዋል።
ይህ እርምጃ ፈረንሳይ ከቀድሞ ቅኝ ግዛቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት እየቀነሰ በመጣበት ወቅት፣ ከእንግሊዝኛ ተናጋሪ አገራት ጋር ያለውን የንግድ ትስስር ለማጠናከር የወሰደችው እርምጃ ተደርጎ ተወስዷል።
ፕሬዝዳንት ማክሮን በመግለጫቸው አፍሪካ እና ፈረንሳይ የጋራ ዓላማ ያላቸው "የእኩልነት አጋሮች" መሆናቸውን ገልጸው፣ ከጠቅላላው የገንዘብ ጥቅል ውስጥ 14 ቢሊዮን ዩሮ የሚሆነው ከፈረንሳይ ኩባንያዎች የሚመነጭ ሲሆን፣ ቀሪው 9 ቢሊዮን ዩሮ ደግሞ ከአፍሪካ ኩባንያዎች የሚጠበቅ መሆኑን አስታውቀዋል።
ይህ ኢንቨስትመንት በዋናነት በኢነርጂ ሽግግር፣ በግብርና፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ በባህር ላይ ፕሮጀክቶች እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ላይ የሚውል ይሆናል።
ይህ ግዙፍ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በአፍሪካ እና በፈረንሳይ 250,000 አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን እንደሚፈጥር ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
"እኛ እዚህ የተገኘነው በአፍሪካ አህጉር ላይ ኢንቨስት ለማድረግ ብቻ አይደለም፤ ታላላቅ አፍሪካውያን የንግድ መሪዎችም ወደ ፈረንሳይ መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ እንፈልጋለን" ሲሉ ግንኙነቱ የሁለትዮሽ ተጠቃሚነትን ያማከለ መሆኑን ገልጸዋል።
በጉባኤው ላይ አፍሪካዊው ባለጸጋ አልኮ ዳንጎቴን ጨምሮ የቶታል ኢነርጂ እና የኦሬንጅ ኩባንያዎች ከፍተኛ ሥራ አስፈፃሚዎች ተገኝተዋል። በመድረኩም የፈረንሳዩ የጭነት መርከብ ድርጅት (CMA CGM) የሞምባሳ ወደብን ለማዘመን የ700 ሚሊዮን ዩሮ ኢንቨስትመንት ለማድረግ ቃል ገብቷል።
ይህ ጉባኤ አውሮፓ ከቻይና እና ከአሜሪካ ጋር እየበረታ የመጣውን የጂኦፖለቲካዊ ፉክክር ተከትሎ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የኢኮኖሚ አጋርነት ለማጠናከር እያደረገች ያለችውን ጥረት እንደሚያንፀባርቅ አልጀዚራ ዘግቧል።
#africaforward #nairobisummit #investment #economy
****************************
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ናይሮቢ በተካሄደ የ"Africa Forward" ጉባኤ ላይ፣ ከአፍሪካ አህጉር ጋር ያለውን ግንኙነት በአዲስ መልክ ለመቅረጽ ያለመ የ23 ቢሊዮን ዩሮ (27 ቢሊዮን ዶላር) የኢንቨስትመንት ዕቅድ ይፋ አድርገዋል።
ይህ እርምጃ ፈረንሳይ ከቀድሞ ቅኝ ግዛቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት እየቀነሰ በመጣበት ወቅት፣ ከእንግሊዝኛ ተናጋሪ አገራት ጋር ያለውን የንግድ ትስስር ለማጠናከር የወሰደችው እርምጃ ተደርጎ ተወስዷል።
ፕሬዝዳንት ማክሮን በመግለጫቸው አፍሪካ እና ፈረንሳይ የጋራ ዓላማ ያላቸው "የእኩልነት አጋሮች" መሆናቸውን ገልጸው፣ ከጠቅላላው የገንዘብ ጥቅል ውስጥ 14 ቢሊዮን ዩሮ የሚሆነው ከፈረንሳይ ኩባንያዎች የሚመነጭ ሲሆን፣ ቀሪው 9 ቢሊዮን ዩሮ ደግሞ ከአፍሪካ ኩባንያዎች የሚጠበቅ መሆኑን አስታውቀዋል።
ይህ ኢንቨስትመንት በዋናነት በኢነርጂ ሽግግር፣ በግብርና፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ በባህር ላይ ፕሮጀክቶች እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ላይ የሚውል ይሆናል።
ይህ ግዙፍ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በአፍሪካ እና በፈረንሳይ 250,000 አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን እንደሚፈጥር ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
"እኛ እዚህ የተገኘነው በአፍሪካ አህጉር ላይ ኢንቨስት ለማድረግ ብቻ አይደለም፤ ታላላቅ አፍሪካውያን የንግድ መሪዎችም ወደ ፈረንሳይ መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ እንፈልጋለን" ሲሉ ግንኙነቱ የሁለትዮሽ ተጠቃሚነትን ያማከለ መሆኑን ገልጸዋል።
በጉባኤው ላይ አፍሪካዊው ባለጸጋ አልኮ ዳንጎቴን ጨምሮ የቶታል ኢነርጂ እና የኦሬንጅ ኩባንያዎች ከፍተኛ ሥራ አስፈፃሚዎች ተገኝተዋል። በመድረኩም የፈረንሳዩ የጭነት መርከብ ድርጅት (CMA CGM) የሞምባሳ ወደብን ለማዘመን የ700 ሚሊዮን ዩሮ ኢንቨስትመንት ለማድረግ ቃል ገብቷል።
ይህ ጉባኤ አውሮፓ ከቻይና እና ከአሜሪካ ጋር እየበረታ የመጣውን የጂኦፖለቲካዊ ፉክክር ተከትሎ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የኢኮኖሚ አጋርነት ለማጠናከር እያደረገች ያለችውን ጥረት እንደሚያንፀባርቅ አልጀዚራ ዘግቧል።
#africaforward #nairobisummit #investment #economy
3 months ago
ለወይዘሮ የሺእመቤት ንጉሴ
አስቸኳይ የህይወት አድን የህክምና እርዳታ ጥሪ
#ethiopia | በፅናት የካንሰር ህመምን እየተጋፈጠች ለምትገኘውና የሁለት ልጆች እናት ለሆነችው ወይዘሮ የሺእመቤት ንጉሴ አስቸኳይ የድጋፍ ጥሪ ቀርቧል።
ወይዘሮ የሺእመቤት እ.ኤ.አ በ2023 ማርች ወር ላይ የማህፀን ዕጢ እንዳለባት ታውቆ በቀዶ ጥገና ህክምና ክትትል ስታደርግ የቆየች ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን ህመሙ በከፍተኛ ሁኔታ አገርሽቶባታል።
በማርች 2026 በናይሮቢ አጋ ካን ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል በተደረገላት የላቀ የፒኢቲ ሲቲ ምርመራ ካንሰሩ ወደ ሳምባዋ፣ ጉበቷ እና ሆድ ዕቃዋ መሰራጨቱ ተረጋግጧል።
የህክምና ባለሙያዎች ህይወቷን ለመታደግ እጅግ ዘመናዊ እና ተስፋ ሰጭ የሆኑ የመድኃኒት ህክምናዎችን እንድትጀምር የወሰኑ ቢሆንም እነዚህ መድኃኒቶች በየሶስት ሳምንቱ የሚወሰዱና እጅግ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ በመሆናቸው ከቤተሰቧ አቅም በላይ ሆኗል።
በመሆኑም ደግ ኢትዮጵያውያን ለዚች እናት የህይወት ተስፋ እንድትሆኑና በገንዘብም ሆነ መረጃውን በማጋራት ከጎኗ እንድትቆሙ ጥሪ ተላልፏል።
ለመርዳት የምትፈልጉ ወገኖች በሚከተሉት የባንክ ሂሳቦችና የገቢ ማሰባሰቢያ መንገዶች ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000131098816 የሺእመቤት ንጉሴ
የአቢሲኒያ ባንክ
97406863 የሺእመቤት ንጉሴ
የጎፈንድሚ ሊንክ
https://gofund.me/6cd26162...
#ጤና #እርዳታ #ደግነት #ኢትዮጵያ #ካንሰር #ህክምና #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
አስቸኳይ የህይወት አድን የህክምና እርዳታ ጥሪ
#ethiopia | በፅናት የካንሰር ህመምን እየተጋፈጠች ለምትገኘውና የሁለት ልጆች እናት ለሆነችው ወይዘሮ የሺእመቤት ንጉሴ አስቸኳይ የድጋፍ ጥሪ ቀርቧል።
ወይዘሮ የሺእመቤት እ.ኤ.አ በ2023 ማርች ወር ላይ የማህፀን ዕጢ እንዳለባት ታውቆ በቀዶ ጥገና ህክምና ክትትል ስታደርግ የቆየች ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን ህመሙ በከፍተኛ ሁኔታ አገርሽቶባታል።
በማርች 2026 በናይሮቢ አጋ ካን ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል በተደረገላት የላቀ የፒኢቲ ሲቲ ምርመራ ካንሰሩ ወደ ሳምባዋ፣ ጉበቷ እና ሆድ ዕቃዋ መሰራጨቱ ተረጋግጧል።
የህክምና ባለሙያዎች ህይወቷን ለመታደግ እጅግ ዘመናዊ እና ተስፋ ሰጭ የሆኑ የመድኃኒት ህክምናዎችን እንድትጀምር የወሰኑ ቢሆንም እነዚህ መድኃኒቶች በየሶስት ሳምንቱ የሚወሰዱና እጅግ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ በመሆናቸው ከቤተሰቧ አቅም በላይ ሆኗል።
በመሆኑም ደግ ኢትዮጵያውያን ለዚች እናት የህይወት ተስፋ እንድትሆኑና በገንዘብም ሆነ መረጃውን በማጋራት ከጎኗ እንድትቆሙ ጥሪ ተላልፏል።
ለመርዳት የምትፈልጉ ወገኖች በሚከተሉት የባንክ ሂሳቦችና የገቢ ማሰባሰቢያ መንገዶች ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000131098816 የሺእመቤት ንጉሴ
የአቢሲኒያ ባንክ
97406863 የሺእመቤት ንጉሴ
የጎፈንድሚ ሊንክ
https://gofund.me/6cd26162...
#ጤና #እርዳታ #ደግነት #ኢትዮጵያ #ካንሰር #ህክምና #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
ብሩክ ጫላ በናይሮቢው የአፍሪካ-ፈረንሳይ የፈጠራ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያን እየወከለ ነው
#fastmereja I "ብሩክ ኒውስ" (Brook News) ብሩክ ጫላ በናይሮቢ እየተካሄደ በሚገኘው የ #africaforward Summit ላይ የኢትዮጵያን የዲጂታል ዜና ዘርፍ በመወከል በመሳተፍ ላይ ይገኛል።
በቲክቶክ እና በፌስቡክ ገጾቹ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተከታዮችን ማፍራት የቻለው ብሩክ፣ በተለይም አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎችን፣ ሰበር ዜናዎችንና በወቅታዊ የፖለቲካና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ በሚሰጣቸው መረጃዎች ይታወቃል። ብሩክ ከሚዲያ ስራው በተጓዳኝ በሙያው መሃንዲስና የዩኒቨርሲቲ መምህር ሲሆን፣ በዘንድሮው ጉባኤ ላይ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች በፈጠራ፣ በወጣቶች ተሳትፎና በአፍሪካ-ፈረንሳይ የትብብር ማዕቀፎች ዙሪያ ያላቸውን ሚና በተመለከተ ሰፋ ያሉ ውይይቶችን እያደረገ ይገኛል።
ይህ በናይሮቢ ኬንያ እየተካሄደ ያለው ጉባኤ፣ በአፍሪካና በፈረንሳይ መካከል ያለውን የፈጠራና የኢኮኖሚ እድገት ትስስር ለማጠናከር ያለመ ሲሆን፣ እንደ ብሩክ ያሉ ተፅዕኖ ፈጣሪ የዲጂታል ድምጾች መገኘት መረጃው ለብዙሃኑ ተደራሽ እንዲሆን ትልቅ ፋይዳ እንዳለው በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኤምባሲ አስታውቋል።
#fastmereja I "ብሩክ ኒውስ" (Brook News) ብሩክ ጫላ በናይሮቢ እየተካሄደ በሚገኘው የ #africaforward Summit ላይ የኢትዮጵያን የዲጂታል ዜና ዘርፍ በመወከል በመሳተፍ ላይ ይገኛል።
በቲክቶክ እና በፌስቡክ ገጾቹ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተከታዮችን ማፍራት የቻለው ብሩክ፣ በተለይም አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎችን፣ ሰበር ዜናዎችንና በወቅታዊ የፖለቲካና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ በሚሰጣቸው መረጃዎች ይታወቃል። ብሩክ ከሚዲያ ስራው በተጓዳኝ በሙያው መሃንዲስና የዩኒቨርሲቲ መምህር ሲሆን፣ በዘንድሮው ጉባኤ ላይ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች በፈጠራ፣ በወጣቶች ተሳትፎና በአፍሪካ-ፈረንሳይ የትብብር ማዕቀፎች ዙሪያ ያላቸውን ሚና በተመለከተ ሰፋ ያሉ ውይይቶችን እያደረገ ይገኛል።
ይህ በናይሮቢ ኬንያ እየተካሄደ ያለው ጉባኤ፣ በአፍሪካና በፈረንሳይ መካከል ያለውን የፈጠራና የኢኮኖሚ እድገት ትስስር ለማጠናከር ያለመ ሲሆን፣ እንደ ብሩክ ያሉ ተፅዕኖ ፈጣሪ የዲጂታል ድምጾች መገኘት መረጃው ለብዙሃኑ ተደራሽ እንዲሆን ትልቅ ፋይዳ እንዳለው በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኤምባሲ አስታውቋል።
3 months ago
የአፍሪካ ፎርዋርድ 2026 ጉባኤ፦ ከአሮጌው የእርዳታ ዘይቤ ወደ አዲስ የኢኮኖሚና የቴክኖሎጂ ትብብር
*****************
በፈረንሳይ እና በአፍሪካ አህጉር መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ያለመው "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ በኬንያ መዲና ናይሮቢ በደመቀ ሁኔታ መጀመሩን ገልጸናል።
"አፍሪካ ፎርዋርድ፡ የአፍሪካ-ፈረንሳይ አጋርነት ለፈጠራ እና ለዕድገት" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ ለበርካታ ዓመታት ሲተገበር ከቆየውና "ፍራንኮ-አፍሪካ" ተብሎ ከሚጠራው የተለመደ ግንኙነት ወጥቶ ሁሉንም የአፍሪካ ሀገራት ያካተተ አዲስ ስትራቴጂ ለመቅረጽ ያለመ ታሪካዊ መድረክ ነው።
ጉባኤው ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ባልሆኑ እንደ ኬንያ ባሉ ሀገራት መካሄዱ፣ ፈረንሳይ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ትብብር ይበልጥ ለማስፋትና ከአዳዲስ የኢኮኖሚ ማዕከላት ጋር ለመተሳሰር የጀመረችውን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው ተብሏል።
የጉባኤው ዋነኛ ግብም በአፍሪካ እና በፈረንሳይ መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና በጋራ ክብር ላይ የተመሰረተ እኩል አጋርነትን መፍጠር እንደሆነ ታውቋል።
የዘንድሮው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባኤ በሰባት ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየመከረ ይገኛል።
አፍሪካን የጥሬ ዕቃ ላኪ ከመሆን አውጥቶ ወደ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ማዕከልነት ለማሸጋገር የሚያስችለው የኢነርጂ ሽግግር፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ለአፍሪካ የሚሰጡትን ድጋፍ እንዲያሻሽሉ የሚጠይቀው የፋይናንስ ሥርዓት ለውጥ እና የባሕር ላይ ኢኮኖሚ ልማት በውይይቱ ከተነሱት ዐበይት ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ።
በዘላቂ ግብርና እና የምግብ ዋስትና፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እንዲሁም ጠንካራ የጤና ሥርዓት በመገንባት ረገድ አህጉሪቱ የራሷን ክትባትና መድኃኒት ማምረት የምትችልበትን ሁኔታ በዝርዝር እየተመለከተ ይገኛል።
ሰላምና ደኅንነትን እንደ ልማት መሠረት በመውሰድ አህጉራዊ የሰላም ማስከበር ጥረቶችን መደገፍም ሌላው የውይይቱ አንኳር ሆኖ ቀርቧል።
በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የጉባኤው አስተናጋጅ የሆኑት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።
እንደ ሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ያሉ መሪዎችም በተለያዩ የውይይት መድረኮች ላይ የመሪነት ሚናቸውን እየተወጡ ነው።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ እንዲሁም የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የዓለም ንግድ ድርጅት መሪዎች መገኘት ለውይይቱ ዓለም አቀፋዊ ክብደት ሰጥቶታል።
ከፖለቲካ መሪዎቹ ባሻገር እንደ አሊኮ ዳንጎቴ እና ስትራይቭ ማሲዪዋ ያሉ የአፍሪካ ባለሀብቶች ከፈረንሳይ ኩባንያዎች ጋር በቀጥታ ኢንቨስትመንት ዙሪያ እየመከሩ ነው።
ይህም ጉባኤው ከተለመደው የፖለቲካ ንግግር ባለፈ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ትብብር መሸጋገሩን የሚያረጋግጥ እንደሆነ ነው መረጃዎች የሚያሳዩት።
በለሚ ታደሰ
#africa #france #africaforward2026 #economiccooperation #partnership #ebc
*****************
በፈረንሳይ እና በአፍሪካ አህጉር መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ያለመው "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ በኬንያ መዲና ናይሮቢ በደመቀ ሁኔታ መጀመሩን ገልጸናል።
"አፍሪካ ፎርዋርድ፡ የአፍሪካ-ፈረንሳይ አጋርነት ለፈጠራ እና ለዕድገት" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ ለበርካታ ዓመታት ሲተገበር ከቆየውና "ፍራንኮ-አፍሪካ" ተብሎ ከሚጠራው የተለመደ ግንኙነት ወጥቶ ሁሉንም የአፍሪካ ሀገራት ያካተተ አዲስ ስትራቴጂ ለመቅረጽ ያለመ ታሪካዊ መድረክ ነው።
ጉባኤው ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ባልሆኑ እንደ ኬንያ ባሉ ሀገራት መካሄዱ፣ ፈረንሳይ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ትብብር ይበልጥ ለማስፋትና ከአዳዲስ የኢኮኖሚ ማዕከላት ጋር ለመተሳሰር የጀመረችውን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው ተብሏል።
የጉባኤው ዋነኛ ግብም በአፍሪካ እና በፈረንሳይ መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና በጋራ ክብር ላይ የተመሰረተ እኩል አጋርነትን መፍጠር እንደሆነ ታውቋል።
የዘንድሮው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባኤ በሰባት ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየመከረ ይገኛል።
አፍሪካን የጥሬ ዕቃ ላኪ ከመሆን አውጥቶ ወደ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ማዕከልነት ለማሸጋገር የሚያስችለው የኢነርጂ ሽግግር፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ለአፍሪካ የሚሰጡትን ድጋፍ እንዲያሻሽሉ የሚጠይቀው የፋይናንስ ሥርዓት ለውጥ እና የባሕር ላይ ኢኮኖሚ ልማት በውይይቱ ከተነሱት ዐበይት ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ።
በዘላቂ ግብርና እና የምግብ ዋስትና፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እንዲሁም ጠንካራ የጤና ሥርዓት በመገንባት ረገድ አህጉሪቱ የራሷን ክትባትና መድኃኒት ማምረት የምትችልበትን ሁኔታ በዝርዝር እየተመለከተ ይገኛል።
ሰላምና ደኅንነትን እንደ ልማት መሠረት በመውሰድ አህጉራዊ የሰላም ማስከበር ጥረቶችን መደገፍም ሌላው የውይይቱ አንኳር ሆኖ ቀርቧል።
በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የጉባኤው አስተናጋጅ የሆኑት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።
እንደ ሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ያሉ መሪዎችም በተለያዩ የውይይት መድረኮች ላይ የመሪነት ሚናቸውን እየተወጡ ነው።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ እንዲሁም የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የዓለም ንግድ ድርጅት መሪዎች መገኘት ለውይይቱ ዓለም አቀፋዊ ክብደት ሰጥቶታል።
ከፖለቲካ መሪዎቹ ባሻገር እንደ አሊኮ ዳንጎቴ እና ስትራይቭ ማሲዪዋ ያሉ የአፍሪካ ባለሀብቶች ከፈረንሳይ ኩባንያዎች ጋር በቀጥታ ኢንቨስትመንት ዙሪያ እየመከሩ ነው።
ይህም ጉባኤው ከተለመደው የፖለቲካ ንግግር ባለፈ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ትብብር መሸጋገሩን የሚያረጋግጥ እንደሆነ ነው መረጃዎች የሚያሳዩት።
በለሚ ታደሰ
#africa #france #africaforward2026 #economiccooperation #partnership #ebc
Sponsored by
Surafel
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን የጀመሩት ከግብፅ ነበር፡፡ ቅዳሜ እለት ካይሮ የገቡት ፕሬዝደንቱ ምሽቱን ወደአሌክሳንድሪያ አቅንተው ለሊቱን በዚያው አሳልፈዋል፡፡
እሁድ ጠዋት ከመኝታቸው የተነሱት ሰማያዊ ቲሸርትና ቱታ ለብሰው ሲሆን ከዚያም በአሌክሳንድሪያ አውራ ጎዳናዎች ላይ በመሮጥ ስፖርት ሰርተዋል፡፡ መንገድ ሳይዘጋና እግረኞች ማለፍ ሳይከለከሉ ይህንን ሩጫ ማድረጋቸው በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት መነጋገሪያ ሆኖ ነበር፡፡ ፕሬዝደንት ማክሮን ቀጣይ መዳረሻቸውን ኬንያ አድርገው ትላንት ናይሮቢ ገብተዋል፡፡
ዛሬ ጠዋትም የተለመደውን የስፖርት ልብሳቸውን አድርገው ከመኝታቸው በመነሳት በናይሮቢ አውራጎዳናዎች ላይ ሮጠዋል፡፡ የዛሬውን ለየት የሚያደርገው ፕሬዝደንቱ የሮጡት ከአንጋፋው የማራቶን ኮከብ ኤሉድ ኪፕቾጌ ጋት በመሆን ነበር፡፡ ይህም ሩጫቸው በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት ሲጋራ ውሏል፡፡ ፕሬዝደንት ማክሮን የፊታችን ሮብ ወደአዲስ አበባ እንደሚያቀኑ የሚጠበቅ ሲሆን በርካቶች ሩጫውን በአዲስ አበባ ይደግሙት ይሆን? የሚል ጥያቄ እያነሱ ናቸው፡፡
እሁድ ጠዋት ከመኝታቸው የተነሱት ሰማያዊ ቲሸርትና ቱታ ለብሰው ሲሆን ከዚያም በአሌክሳንድሪያ አውራ ጎዳናዎች ላይ በመሮጥ ስፖርት ሰርተዋል፡፡ መንገድ ሳይዘጋና እግረኞች ማለፍ ሳይከለከሉ ይህንን ሩጫ ማድረጋቸው በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት መነጋገሪያ ሆኖ ነበር፡፡ ፕሬዝደንት ማክሮን ቀጣይ መዳረሻቸውን ኬንያ አድርገው ትላንት ናይሮቢ ገብተዋል፡፡
ዛሬ ጠዋትም የተለመደውን የስፖርት ልብሳቸውን አድርገው ከመኝታቸው በመነሳት በናይሮቢ አውራጎዳናዎች ላይ ሮጠዋል፡፡ የዛሬውን ለየት የሚያደርገው ፕሬዝደንቱ የሮጡት ከአንጋፋው የማራቶን ኮከብ ኤሉድ ኪፕቾጌ ጋት በመሆን ነበር፡፡ ይህም ሩጫቸው በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት ሲጋራ ውሏል፡፡ ፕሬዝደንት ማክሮን የፊታችን ሮብ ወደአዲስ አበባ እንደሚያቀኑ የሚጠበቅ ሲሆን በርካቶች ሩጫውን በአዲስ አበባ ይደግሙት ይሆን? የሚል ጥያቄ እያነሱ ናቸው፡፡
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ኢትዮጵያና ኬንያን የሚያገናኘው መንገድ ተዘግቶ ዋለ፡፡ ኢትዮጵያንና ኬንያን የሚያገናኘው ከሶሎሎ እስከ ሞያሌ የተዘረጋው አውራጎዳና ዛሬ ዝግ ሆኖ ውሏል፡፡ ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ተቃዋሚዎች መንገዱን በድንጋይና በተቃጠለ ጎማ መሙላታቸው ነው፡፡ የኬንያ ጋዜጦች እንደዘገቡት በሶሎሎ ውስጥ ዛሬ ከጠዋት አንስቶ ተቃዋሚዎች አደባባይ የወጡ ሲሆን በአካባቢው የሚኖሩ ሁለት ሽማግሌዎች መታገታቸውን ሲቃወሙ ውለዋል፡፡
እንደዘገባዎቹ አንደኛው የአካባቢው ሽማግሌ ትላንት ምሽት ፊታቸውን በጭንብል በሸፈኑ ማንነታቸው ባልታወቁ ግለሰቦች የታገቱት ከመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ነበር፡፡ ሌላኛውን ደግሞ ወደናይሮቢ በመጓዝ ላይ እያሉ መኪናቸውን አስቁመው በሀይል ካስወረዷቸው በኋላ በሌላ መኪና ይዘዋቸው ሄደዋል፡፡ ተቃዋሚዎቹ በአካባቢያቸው ላይ ተደጋጋሚ እገታና የሰዎች መሰወር እየተፈፀመ የፀጥታ አካላት ይህንን ለማስቆም አለመቻላቸውን የገለፁ ሲሆን ለደህንነታቸው ስጋት እንዳደረባቸው ሲናገሩም ተደምጠዋል፡፡
በዚህ ተቃውሞ የተነሳ በኢትዮጵያና ኬንያ መካከል የሚደረገው የየብስ ግንኙነት ሊቋረጥ ችሏል፡፡ ይህ አውራ ጎዳና ሁለቱን አገራት በንግድ የሚያስተሳስራቸው በመሆኑ በርካታ የጭነት መኪናዎች በሁለቱም በኩል ረጅም ሰልፍ ቆመው ለመዋል ተገደዋል፡፡
እንደዘገባዎቹ አንደኛው የአካባቢው ሽማግሌ ትላንት ምሽት ፊታቸውን በጭንብል በሸፈኑ ማንነታቸው ባልታወቁ ግለሰቦች የታገቱት ከመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ነበር፡፡ ሌላኛውን ደግሞ ወደናይሮቢ በመጓዝ ላይ እያሉ መኪናቸውን አስቁመው በሀይል ካስወረዷቸው በኋላ በሌላ መኪና ይዘዋቸው ሄደዋል፡፡ ተቃዋሚዎቹ በአካባቢያቸው ላይ ተደጋጋሚ እገታና የሰዎች መሰወር እየተፈፀመ የፀጥታ አካላት ይህንን ለማስቆም አለመቻላቸውን የገለፁ ሲሆን ለደህንነታቸው ስጋት እንዳደረባቸው ሲናገሩም ተደምጠዋል፡፡
በዚህ ተቃውሞ የተነሳ በኢትዮጵያና ኬንያ መካከል የሚደረገው የየብስ ግንኙነት ሊቋረጥ ችሏል፡፡ ይህ አውራ ጎዳና ሁለቱን አገራት በንግድ የሚያስተሳስራቸው በመሆኑ በርካታ የጭነት መኪናዎች በሁለቱም በኩል ረጅም ሰልፍ ቆመው ለመዋል ተገደዋል፡፡
3 months ago
የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ማክሮን ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው
#ethiopia | የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ በኬንያ ናይሮቢ የሚካሄደውን የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ካጠናቀቁ በኋላ፣ በመጪው ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለአጭር የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ታውቋል።
ይህ ጉብኝት ከመደበኛው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባለፈ፣ የፈረንሳይን የንግድ ጡንቻ በኢትዮጵያ ገበያ ውስጥ ለማፈርጠም የታለመ እንደሆነ ተመልክቷል። ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት ዝም ብለው ሳይሆን፣ የፈረንሳይን ግዙፍ ኩባንያዎች መሪዎች በክብር አስከትለው ነው።
የካፒታል ዘገባ እንደሚያመለክተው፣ የፕሬዝዳንቱ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው። በተለይም በልዑካን ቡድኑ ውስጥ የተካተቱት ተቋማት የጉብኝቱን ክብደት ያሳያሉ፦
ካርፉር (Carrefour): በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቀው የችርቻሮ ንግድ ተቋም፣ ከኢትዮጵያው ሚድሮክ (MIDROC) ጋር በፈጠረው የፍራንቻይዝ ስምምነት አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት እንቅስቃሴ እየጀመረ ይገኛል።
ሜሪዲያም (Meridiam): በትላልቅ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንቶች ላይ የሚንቀሳቀሰው ድርጅት አመራሮችም የጉዞው አካል ናቸው።
ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የገበያ ክፍትነት፣ እንደ ፈረንሳይ ያሉ የአውሮፓ ሀገራት ቀልባቸውን ወደ አዲስ አበባ እንዲያዞሩ አድርጓቸዋል። ማክሮን በጉብኝታቸው ወቅት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ከሚያደርጉት ውይይት ባሻገር፣ የፈረንሳይ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸውን ድርሻ ለማሳደግ የሚያስችሉ መንገዶች ላይ እንደሚመክሩ ይጠበቃል።
ይህ ጉብኝት የፈረንሳይ "የንግድ ዲፕሎማሲ" በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ተጽዕኖ ለማሳረፍ የሚያደርገው ጥረት አካል ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የፈረንሳይ ውበት እና የኢትዮጵያ የንግድ ዕድሎች በአዲስ አበባ በሚያደርጉት ቆይታ ምን አይነት ውጤት ይዘው እንደሚመጡ በጉጉት የሚጠበቅ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia #france #emmanuelmacron #investment #addisababa #carrefour #businessdiplomacy #africaforward
#ethiopia | የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ በኬንያ ናይሮቢ የሚካሄደውን የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ካጠናቀቁ በኋላ፣ በመጪው ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለአጭር የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ታውቋል።
ይህ ጉብኝት ከመደበኛው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባለፈ፣ የፈረንሳይን የንግድ ጡንቻ በኢትዮጵያ ገበያ ውስጥ ለማፈርጠም የታለመ እንደሆነ ተመልክቷል። ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት ዝም ብለው ሳይሆን፣ የፈረንሳይን ግዙፍ ኩባንያዎች መሪዎች በክብር አስከትለው ነው።
የካፒታል ዘገባ እንደሚያመለክተው፣ የፕሬዝዳንቱ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው። በተለይም በልዑካን ቡድኑ ውስጥ የተካተቱት ተቋማት የጉብኝቱን ክብደት ያሳያሉ፦
ካርፉር (Carrefour): በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቀው የችርቻሮ ንግድ ተቋም፣ ከኢትዮጵያው ሚድሮክ (MIDROC) ጋር በፈጠረው የፍራንቻይዝ ስምምነት አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት እንቅስቃሴ እየጀመረ ይገኛል።
ሜሪዲያም (Meridiam): በትላልቅ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንቶች ላይ የሚንቀሳቀሰው ድርጅት አመራሮችም የጉዞው አካል ናቸው።
ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የገበያ ክፍትነት፣ እንደ ፈረንሳይ ያሉ የአውሮፓ ሀገራት ቀልባቸውን ወደ አዲስ አበባ እንዲያዞሩ አድርጓቸዋል። ማክሮን በጉብኝታቸው ወቅት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ከሚያደርጉት ውይይት ባሻገር፣ የፈረንሳይ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸውን ድርሻ ለማሳደግ የሚያስችሉ መንገዶች ላይ እንደሚመክሩ ይጠበቃል።
ይህ ጉብኝት የፈረንሳይ "የንግድ ዲፕሎማሲ" በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ተጽዕኖ ለማሳረፍ የሚያደርገው ጥረት አካል ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የፈረንሳይ ውበት እና የኢትዮጵያ የንግድ ዕድሎች በአዲስ አበባ በሚያደርጉት ቆይታ ምን አይነት ውጤት ይዘው እንደሚመጡ በጉጉት የሚጠበቅ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia #france #emmanuelmacron #investment #addisababa #carrefour #businessdiplomacy #africaforward
3 months ago
ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ሊመጡ ነው
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ መሆኑ ተዘግቧል
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ናይሮቢ የሚካሄደውን "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ ካጠናቀቁ በኋላ፣ በመጪው ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለአጭር የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ታውቋል።
ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት በጥንቃቄ የተመረጡ የፈረንሳይ ግዙፍ ኩባንያዎች መሪዎችን በማስከተል ሲሆን፣ ጉብኝቱም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው ይላል የካፒታል ዘገባ።
በፕሬዝዳንቱ የታጀበው ልዑክ እንደ ካርፉር ያሉ ታዋቂ የችርቻሮ ንግድ ተቋማትን እና ሜሪዲያም የተሰኘውን የኢንቨስትመንት ድርጅት አመራሮችን ያካተተ ሲሆን፣ በተለይም ካርፉር ከኢትዮጵያው ሚድሮክ ጋር በፈጠረው የፍራንቻይዝ ስምምነት አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት ማቀዱ የጉብኝቱ አንዱ ዋነኛ ትኩረት መሆኑ ተጠቁሟል።
seledadotio
seledadotio
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ መሆኑ ተዘግቧል
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ናይሮቢ የሚካሄደውን "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ ካጠናቀቁ በኋላ፣ በመጪው ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለአጭር የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ታውቋል።
ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት በጥንቃቄ የተመረጡ የፈረንሳይ ግዙፍ ኩባንያዎች መሪዎችን በማስከተል ሲሆን፣ ጉብኝቱም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው ይላል የካፒታል ዘገባ።
በፕሬዝዳንቱ የታጀበው ልዑክ እንደ ካርፉር ያሉ ታዋቂ የችርቻሮ ንግድ ተቋማትን እና ሜሪዲያም የተሰኘውን የኢንቨስትመንት ድርጅት አመራሮችን ያካተተ ሲሆን፣ በተለይም ካርፉር ከኢትዮጵያው ሚድሮክ ጋር በፈጠረው የፍራንቻይዝ ስምምነት አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት ማቀዱ የጉብኝቱ አንዱ ዋነኛ ትኩረት መሆኑ ተጠቁሟል።
seledadotio
seledadotio
Comments