10 hours ago
አዲስ አበባ ፡ የኤምኤምኤ እና የቦክስ ስፖርት ውድድር ሊካሄድ ነው
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት የንክኪ ስፖርት ሁነቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነው የኢትዮ ፋይት ናይት የውድድር መድረክ ይፋ ሆኗል::
ዝግጅቱ የአዲስ አበባ ኪክ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ነሀሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (Aug 29/2026) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል::
በዚህ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ላይ በድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገራችንን ወክለው ደግሞ ቢኒያም ሽብሬ፣ ክብሮም ንጉሴ እና አገረሰላም አርባን ጨምሮ በርካታ ስፖርተኞች ወደ መድረኩ ይወርዳሉ::
በጠቅላላው ከ6 እስከ 8 የሚደርሱ ብርቱ ፍልሚያዎች የሚስተናገዱ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የተመረጡት በውድድር ታሪካቸው፣ በዓለም አቀፍ ልምዳቸው፣ በአካል ብቃት ጥንካሬያቸው እና ማራኪ ትዕይንት ማሳየት በሚችሉበት ብቃታቸው ላይ ተመስርቶ ነው::
አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ህግ መሰረት አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ፣ የክብደት ልኬትና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደቶችን ያጠናቀቁ ሲሆን ዝርዝር የክብደት መጠናቸውና ዜግነታቸው በቅርቡ ይፋ ይደረጋል::
ይህንን ታሪካዊ ፍልሚያ ለመታደም ከ8,000 እስከ 10,000 የሚደርሱ የስፖርት አፍቃሪዎች በአዳራሹ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አዘጋጆቹ የአፍሪካንና የሀገራችንን ስፖርታዊ አቅም ለዓለም የሚያስተዋውቅ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ፍጹም ሙያዊ ብቃት የተላበሰ ዝግጅት ለማቅረብ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል::
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ የንክኪ ስፖርቶችን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ አትሌቶች ሙያዊ መድረክ መፍጠር፣ ወጣቶችን ማነሳሳት፣ ስፖርታዊ ቱሪዝምን በአዲስ አበባና በኢትዮጵያ ማስፋፋት እንዲሁም ሀገራችንን የዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዕከል ማድረግ ነው::
ዝግጅቱ የሚስተናገድበት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር (AICC) ዘመናዊ የዲጂታል ምስልና የድምፅ መገልገያ መሳሪያዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለታዳሚው ምቹ መዝናኛን ለመፍጠር ተመራጭ አድርጎታል::
ገራሚ ኢቨንትስ የዝግጅቱን አጠቃላይ የፕሮዳክሽን ስራ በማስተናገድ ከባለቤቶቹ ጋር በጋራ የሚሰራ ሲሆን ለአትሌቶች ስልጠና፣ ለደህንነት፣ ለቦታ ዝግጅትና ለሎጂስቲክስ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሷል::
ይህንን ውድድር በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማዘጋጀት የታቀደ በመሆኑ፣ የዝግጅቱን ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በስፖንሰርሺፕ፣ በሚዲያ ሽፋን፣ በዲጂታል ግብይትና በቪአይፒ ተሳትፎ ላይ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል::
የመግቢያ ትኬት ዋጋንና የስርጭት ሽፋንን በተመለከተ ከሚዲያ አጋሮች ጋር ውይይት እየተደረገ ሲሆን የቴሌቪዥንና የዲጂታል ቀጥታ ስርጭት መረጃዎች በቅርቡ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል::
#mma #boxing #ethiofightnight #sportstourism #aicc #ethiopianathletes #geramievents #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት የንክኪ ስፖርት ሁነቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነው የኢትዮ ፋይት ናይት የውድድር መድረክ ይፋ ሆኗል::
ዝግጅቱ የአዲስ አበባ ኪክ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ነሀሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (Aug 29/2026) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል::
በዚህ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ላይ በድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገራችንን ወክለው ደግሞ ቢኒያም ሽብሬ፣ ክብሮም ንጉሴ እና አገረሰላም አርባን ጨምሮ በርካታ ስፖርተኞች ወደ መድረኩ ይወርዳሉ::
በጠቅላላው ከ6 እስከ 8 የሚደርሱ ብርቱ ፍልሚያዎች የሚስተናገዱ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የተመረጡት በውድድር ታሪካቸው፣ በዓለም አቀፍ ልምዳቸው፣ በአካል ብቃት ጥንካሬያቸው እና ማራኪ ትዕይንት ማሳየት በሚችሉበት ብቃታቸው ላይ ተመስርቶ ነው::
አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ህግ መሰረት አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ፣ የክብደት ልኬትና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደቶችን ያጠናቀቁ ሲሆን ዝርዝር የክብደት መጠናቸውና ዜግነታቸው በቅርቡ ይፋ ይደረጋል::
ይህንን ታሪካዊ ፍልሚያ ለመታደም ከ8,000 እስከ 10,000 የሚደርሱ የስፖርት አፍቃሪዎች በአዳራሹ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አዘጋጆቹ የአፍሪካንና የሀገራችንን ስፖርታዊ አቅም ለዓለም የሚያስተዋውቅ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ፍጹም ሙያዊ ብቃት የተላበሰ ዝግጅት ለማቅረብ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል::
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ የንክኪ ስፖርቶችን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ አትሌቶች ሙያዊ መድረክ መፍጠር፣ ወጣቶችን ማነሳሳት፣ ስፖርታዊ ቱሪዝምን በአዲስ አበባና በኢትዮጵያ ማስፋፋት እንዲሁም ሀገራችንን የዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዕከል ማድረግ ነው::
ዝግጅቱ የሚስተናገድበት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር (AICC) ዘመናዊ የዲጂታል ምስልና የድምፅ መገልገያ መሳሪያዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለታዳሚው ምቹ መዝናኛን ለመፍጠር ተመራጭ አድርጎታል::
ገራሚ ኢቨንትስ የዝግጅቱን አጠቃላይ የፕሮዳክሽን ስራ በማስተናገድ ከባለቤቶቹ ጋር በጋራ የሚሰራ ሲሆን ለአትሌቶች ስልጠና፣ ለደህንነት፣ ለቦታ ዝግጅትና ለሎጂስቲክስ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሷል::
ይህንን ውድድር በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማዘጋጀት የታቀደ በመሆኑ፣ የዝግጅቱን ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በስፖንሰርሺፕ፣ በሚዲያ ሽፋን፣ በዲጂታል ግብይትና በቪአይፒ ተሳትፎ ላይ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል::
የመግቢያ ትኬት ዋጋንና የስርጭት ሽፋንን በተመለከተ ከሚዲያ አጋሮች ጋር ውይይት እየተደረገ ሲሆን የቴሌቪዥንና የዲጂታል ቀጥታ ስርጭት መረጃዎች በቅርቡ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል::
#mma #boxing #ethiofightnight #sportstourism #aicc #ethiopianathletes #geramievents #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 days ago
በኒው ዌይ ኢትዮጵያ የተዘጋጀው የመጀመሪያው የአርሜንያ ጉዞ በስኬት ተጠናቀቀ ።
በኒው ዌይ ኢትዮጵያ አስጎብኚ ድርጅት የተዘጋጀው ለ5 ቀናት የቆየው የእናታችን የቅድስት አርሴማን ጨምሮ የበርካታ ገዳማት ጉብኝት እንዲሁም የከተማ ውስጥ ቱር ስኬታማ እንደነበር በተጓዦች ተመስክሮለታል።
በሁለተኛ እና ሶስተኛ ዙር ጉዞውን በሰኔ 17/2018 እና በሀምሌ 4/2018 እንደሚያደርግም ተገልፁዋል
በእነዚም ጉዞዎች ወደ አርሜንያ የደርሶ መልስ ትኬት፣ የአልጋ እና ቁርስ፣የቱር መኪና እና አስጎብኚ እንዲሁም የቪዛ እና ኢንሺራንስ ኒው ዌይ ኢትዮዽያ አስተካክሎ በእንክብካቤ ወስዶ እንደሚመልሳችሁ አሁንም ቃል ይገባል።
ለበለጠ መረጃ በዚህ በስልክ ይደውሉ :- +251978333435 ይደውሉ በተጨመሪም በውጪ ሀገር ለምትገኙ ውድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ለወዳጅ ዘመድዎ በWhatsApp ቁጥራችን በማስመዝገብ መጋበዝ ይችላሉ
ኒው ዌይ ኢትዮጲያ ከሚጎበኙ ቦታዎች መካከል :-
1.የእናታችን የቅድስት አርሴማ መቃብር የሚገኝበት ገዳም
2. በአለማችን የመጀመሪያ ጥንታዊው ገዳም የቅዱስ ጎርጎሪዎስ 13 ዓመት ክርስትናን በመስበኩ ከመሬት በታች የታሰረበት ገዳም
3. የመዳኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በስቅለቱ ጊዜ ጎኑን የተወጋበት ጦር የሚገኝበት ገዳምና ሌሎች ገዳማትን እንጎበኛለን። እንዲሁም የአርሜኒያ ከተሞችን እንጎበኛለን።
በተጨማሪም በTiktok . https://www.tiktok.com/@ne...
Instagram.https://www.instagram.com/...
Facebook.https://www.facebook.com/s...
ይመዝገቡ።
ኒው ዌይ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚታወቁ ዓለም አቀፍ ደረጃዎች የኮርፖሬት ቱሪዝምን ለማደራጀት እና የተሟላ አገልግሎትን ለመስጠት ዝግጅቱን ጨርሷል።
በኒው ዌይ ኢትዮጵያ አስጎብኚ ድርጅት የተዘጋጀው ለ5 ቀናት የቆየው የእናታችን የቅድስት አርሴማን ጨምሮ የበርካታ ገዳማት ጉብኝት እንዲሁም የከተማ ውስጥ ቱር ስኬታማ እንደነበር በተጓዦች ተመስክሮለታል።
በሁለተኛ እና ሶስተኛ ዙር ጉዞውን በሰኔ 17/2018 እና በሀምሌ 4/2018 እንደሚያደርግም ተገልፁዋል
በእነዚም ጉዞዎች ወደ አርሜንያ የደርሶ መልስ ትኬት፣ የአልጋ እና ቁርስ፣የቱር መኪና እና አስጎብኚ እንዲሁም የቪዛ እና ኢንሺራንስ ኒው ዌይ ኢትዮዽያ አስተካክሎ በእንክብካቤ ወስዶ እንደሚመልሳችሁ አሁንም ቃል ይገባል።
ለበለጠ መረጃ በዚህ በስልክ ይደውሉ :- +251978333435 ይደውሉ በተጨመሪም በውጪ ሀገር ለምትገኙ ውድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ለወዳጅ ዘመድዎ በWhatsApp ቁጥራችን በማስመዝገብ መጋበዝ ይችላሉ
ኒው ዌይ ኢትዮጲያ ከሚጎበኙ ቦታዎች መካከል :-
1.የእናታችን የቅድስት አርሴማ መቃብር የሚገኝበት ገዳም
2. በአለማችን የመጀመሪያ ጥንታዊው ገዳም የቅዱስ ጎርጎሪዎስ 13 ዓመት ክርስትናን በመስበኩ ከመሬት በታች የታሰረበት ገዳም
3. የመዳኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በስቅለቱ ጊዜ ጎኑን የተወጋበት ጦር የሚገኝበት ገዳምና ሌሎች ገዳማትን እንጎበኛለን። እንዲሁም የአርሜኒያ ከተሞችን እንጎበኛለን።
በተጨማሪም በTiktok . https://www.tiktok.com/@ne...
Instagram.https://www.instagram.com/...
Facebook.https://www.facebook.com/s...
ይመዝገቡ።
ኒው ዌይ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚታወቁ ዓለም አቀፍ ደረጃዎች የኮርፖሬት ቱሪዝምን ለማደራጀት እና የተሟላ አገልግሎትን ለመስጠት ዝግጅቱን ጨርሷል።
2 days ago
በአዲስ አበባ ስታዲየም :
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።
በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።
በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።
ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።
የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።
በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።
በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።
ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።
የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 days ago
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች
ኢትዮጵያ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀውን የተበታተነ የንግድ አስተዳደር ሥርዓት ለመቀየርና ለላኪዎች፣ አስመጪዎችና ባለሀብቶች ግልጽና ሊተነበይ የሚችል አሠራር ለመፍጠር የሚያስችላትን የመጀመሪያውን ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች።
በተጠናቀቀው ሳምንት በሚኒስትሮች ምክርቤት የጸደቀው ይህ ፖሊሲ፣ ለበርካታ አስርት ዓመታት የሀገሪቱን የንግድ ዘርፍ ተወዳዳሪነት ሲያዳክሙና ለብልሹ አሠራር በር ሲከፍቱ የቆዩትን እርስ በርሳቸው የሚጋጩ መመሪያዎችንና አሠራሮችን ሙሉ በሙሉ የሚተካ ነው።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ እንደገለጹት፣ አዲሱ ማዕቀፍ በተደጋጋሚ ለሚቀያየሩ መመሪያዎች እውቅና የማይሰጥ በመሆኑ በንግድ ቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ መረጋጋት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል።
ፖሊሲው የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከለመደው ያልተቀነባበሩ የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት ጥገኝነት በማውጣት፣ ወደ ማኑፋክቸሪንግ፣ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶች፣ አገልግሎቶችና ቱሪዝም ዘርፎች ላይ እንዲያተኩር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የንግድ ልማት አገልግሎትና ፖሊሲ ጥበቃ ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ ካሳሁን ማሞ፣ ምክር ቤቱ እንዲህ ዓይነት ሁሉን አቀፍ ፖሊሲ እንዲወጣ ለረጅም ጊዜ ሲወተውት እንደነበር አስታውሰዋል። ፖሊሲው የግል ባለሀብቱ በልበ ሙሉነት እንዲያቅድና ኢንቨስት እንዲያደርግ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
Via capital
ኢትዮጵያ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀውን የተበታተነ የንግድ አስተዳደር ሥርዓት ለመቀየርና ለላኪዎች፣ አስመጪዎችና ባለሀብቶች ግልጽና ሊተነበይ የሚችል አሠራር ለመፍጠር የሚያስችላትን የመጀመሪያውን ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች።
በተጠናቀቀው ሳምንት በሚኒስትሮች ምክርቤት የጸደቀው ይህ ፖሊሲ፣ ለበርካታ አስርት ዓመታት የሀገሪቱን የንግድ ዘርፍ ተወዳዳሪነት ሲያዳክሙና ለብልሹ አሠራር በር ሲከፍቱ የቆዩትን እርስ በርሳቸው የሚጋጩ መመሪያዎችንና አሠራሮችን ሙሉ በሙሉ የሚተካ ነው።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ እንደገለጹት፣ አዲሱ ማዕቀፍ በተደጋጋሚ ለሚቀያየሩ መመሪያዎች እውቅና የማይሰጥ በመሆኑ በንግድ ቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ መረጋጋት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል።
ፖሊሲው የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከለመደው ያልተቀነባበሩ የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት ጥገኝነት በማውጣት፣ ወደ ማኑፋክቸሪንግ፣ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶች፣ አገልግሎቶችና ቱሪዝም ዘርፎች ላይ እንዲያተኩር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የንግድ ልማት አገልግሎትና ፖሊሲ ጥበቃ ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ ካሳሁን ማሞ፣ ምክር ቤቱ እንዲህ ዓይነት ሁሉን አቀፍ ፖሊሲ እንዲወጣ ለረጅም ጊዜ ሲወተውት እንደነበር አስታውሰዋል። ፖሊሲው የግል ባለሀብቱ በልበ ሙሉነት እንዲያቅድና ኢንቨስት እንዲያደርግ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
Via capital
2 days ago
የንግድ ድንበሮችን በመሻገር የአፍሪካን ገበያ ይቆጣጠሩ!
የኢትዮጵያን የቢዝነስ መሪዎች፣ ሥራ አስኪያጆች እና ባለሀብቶች ከሩዋንዳ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ጋር የሚያገናኘው ታላቁ የኢትዮጵያ - ሩዋንዳ ቢዝነስ ፎረም 2026 ምዝገባ ጀምሯል። ይህ የ4 ቀናት የቢዝነስ ጉዞ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ለማሳደግ እና አዲስ የኢንቨስትመንት አድማስ ለመክፈት ታስቦ የተዘጋጀ ልዩ መድረክ ነው።
በፎረሙ ላይ በመሳተፍዎ ምን ያተርፋሉ?
• 🤝 አስቀድመው የተመቻቹ እና ያተኮሩ የB2B (የንግድ ለንግድ) ስብሰባዎች
• 🎯 ከታዋቂ ባለሀብቶች እና ዋና የንግድ ውሳኔ ሰጪዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት
• 📈 ወደ ሩዋንዳ ገበያ በምቾት ለመግባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ድጋፍ እና የተግባር የመስክ ምልከታ (Site Visits)
•በዛውም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ የሩዋንዳ ኤግዚቢሽን ላይ ይሳተፋሉ
ዋና ዋና የትኩረት ዘርፎች፦
ግብርና ማቀነባበሪያ (Agro-Processing) | ሪል ስቴት እና ኮንስትራክሽን | ቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ | አይሲቲ እና ኢኖቬሽን | ማኑፋክቸሪንግ (ማምረቻ ዘርፍ)
📅 ቀን፦ hamele 21-24፣ 2018 ዓ.ም (july 28–31, 2026)
📍 ቦታ፦ ኪጋሊ ፣ ሩዋንዳ (Kigali, Rwanda)
⏱️ ቆይታ፦ 4 ቀናት የንግድ ተልዕኮ
የመቀመጫዎች ብዛት በጣም ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ! 📞 ስልክ ቁጥር፦ +251 911874859/0913174052
📧 ኢሜይል፦ infoalohavistaevents.com
🌐 ድረ-ገጽ፦ www.alohavistaevents.com
በኢትዮጵያ የፌዴራል ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኤምባሲ (ኪጋሊ) እና በሩዋንዳ ልማት ቦርድ (RDB) ትብብር የተዘጋጀ።
የኢትዮጵያን የቢዝነስ መሪዎች፣ ሥራ አስኪያጆች እና ባለሀብቶች ከሩዋንዳ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ጋር የሚያገናኘው ታላቁ የኢትዮጵያ - ሩዋንዳ ቢዝነስ ፎረም 2026 ምዝገባ ጀምሯል። ይህ የ4 ቀናት የቢዝነስ ጉዞ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ለማሳደግ እና አዲስ የኢንቨስትመንት አድማስ ለመክፈት ታስቦ የተዘጋጀ ልዩ መድረክ ነው።
በፎረሙ ላይ በመሳተፍዎ ምን ያተርፋሉ?
• 🤝 አስቀድመው የተመቻቹ እና ያተኮሩ የB2B (የንግድ ለንግድ) ስብሰባዎች
• 🎯 ከታዋቂ ባለሀብቶች እና ዋና የንግድ ውሳኔ ሰጪዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት
• 📈 ወደ ሩዋንዳ ገበያ በምቾት ለመግባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ድጋፍ እና የተግባር የመስክ ምልከታ (Site Visits)
•በዛውም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ የሩዋንዳ ኤግዚቢሽን ላይ ይሳተፋሉ
ዋና ዋና የትኩረት ዘርፎች፦
ግብርና ማቀነባበሪያ (Agro-Processing) | ሪል ስቴት እና ኮንስትራክሽን | ቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ | አይሲቲ እና ኢኖቬሽን | ማኑፋክቸሪንግ (ማምረቻ ዘርፍ)
📅 ቀን፦ hamele 21-24፣ 2018 ዓ.ም (july 28–31, 2026)
📍 ቦታ፦ ኪጋሊ ፣ ሩዋንዳ (Kigali, Rwanda)
⏱️ ቆይታ፦ 4 ቀናት የንግድ ተልዕኮ
የመቀመጫዎች ብዛት በጣም ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ! 📞 ስልክ ቁጥር፦ +251 911874859/0913174052
📧 ኢሜይል፦ infoalohavistaevents.com
🌐 ድረ-ገጽ፦ www.alohavistaevents.com
በኢትዮጵያ የፌዴራል ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኤምባሲ (ኪጋሊ) እና በሩዋንዳ ልማት ቦርድ (RDB) ትብብር የተዘጋጀ።
2 days ago
የእንጦጦ-ቀጨኔ መድኃኔዓለም የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቋል።
22.25 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው ይህ ፕሮጀክት፣ የተጎዱ አካባቢዎችን ወደ ማራኪ እና የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉ ለምለም አረንጓዴ ሥፍራዎች የቀየረ ነው።
የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ምሰሶዎች፦
ሥነ-ምህዳርን መልሶ ማቋቋም እና የከተማ ግብርና፦
ፕሮጀክቱ በባሕር ዛፍ ምክንያት የተጎዳ 36 ሄክታር መሬትን ጨምሮ፣ በአጠቃላይ 438 ሄክታር የተጎዳ መሬትን አክሞ ዳግም አቋቁሟል። በተጨማሪም የከተማ ግብርና እና ብዝሃ-ሕይወትን ለማጠናከር አዲስ የ9.5 ሄክታር የፍራፍሬ ፓርክ እና 210 ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን አካቷል።
የውሃ ማጣሪያ እና መሠረተ-ልማት፦
በእንጦጦ-ቀጨኔ ኮሪደር ላይ 39 የወንዝ መገደቢያዎችን እና ሦስት የወንዝ ውሃ ማጣሪያ ሥርዓቶችን በመገንባት የአካባቢ ጥበቃና ዘላቂነት እንዲጠናከር ተደርጓል።
የአረንጓዴ ትራንስፖርት አማራጮች እና ቱሪዝም ፦
አረንጓዴ የትራንስፖርት አማራጮችንና መዝናኛን በማስፋፋት፣ ፕሮጀክቱ 19.4 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገዶችን፣ 7.7 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መስመሮችን እና 4 ኪሎ ሜትር የተራራ መውጫ (የእግር ጉዞ) መንገዶችን ያካተተ ሲሆን፣ ይህም ጤናማ፣ ምቹ እና ንቁ ማኅበረሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
#pmoethiopia #ethiopiadelivers
3 days ago
ተፈጸመ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 days ago
በኬንያ የአሜሪካ የኢቦላ ማቆያ ማዕከል ሊገነባ ነው መባሉ ህዝባዊ ተቃውሞ አስነሳ
#fastmereja በኬንያ ላይኪፒያ ግዛት ናኙኪ ከተማ የአሜሪካ መንግስት ሊገነባው ባቀደው የኢቦላ መከላከያ ማኳያ ማዕከል ላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ዛሬ ሰኞ ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ አደረጉ።
ነዋሪዎቹ የኢቦላ ቫይረስ ተጋላጭ የሆኑ አሜሪካውያንን ለማቆየት በኬንያ አየር ኃይል የጦር ሰፈር ውስጥ ሊገነባ የታቀደውን ባለ 50 አልጋ ማዕከል የተቃወሙት፣ አስቀድሞ ምንም ዓይነት የሕዝብ ውይይትና ምክክር ሳይደረግበት በምስጢር የተወሰነ ነው በሚል ነው።
ነዋሪዎችና ፖሊስ ወደ ግጭት ውስጥ የገቡ ሲሆን የጸጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ሰልፈኞችን ለመበተን መገደዳቸው ታውቋል። በተፈጠረው ግርግር ሳቢያ የናኙኪ ከተማ የንግድና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ የተስተጓጎለ ሲሆን፣ ማዕከሉ ሊገነባ ነው የሚለው ዜና የአካባቢውን የቱሪዝም ዘርፍ ክፉኛ መምታቱ ተገልጿል። በርካታ ዓለም አቀፍ ቱሪስቶች ወደ አካባቢው የሚያደርጉትን የሆቴልና የሆምስቴይ የቦታ ማስያዣ ጥያቄዎችን በጅምላ እየሰረዙ መሆኑን የዘርፉ ባለቤቶች በምሬት ተናግረዋል።
የአካባቢው የንግድ ምክር ቤትና የፖለቲካ መሪዎች መንግስትን በግልጽ እየተቹ ሲሆን፣ የአገሪቱ የጤና ሥርዓት መሰረታዊ ክትባቶችን እንኳን ማቅረብ ባልቻለበት ሁኔታ ዓለም አቀፍ አደጋ የሆነውን የኢቦላ ማቆያ ማዕከል መቀበል አደገኛ መሆኑን ገልጸዋል።
#fastmereja በኬንያ ላይኪፒያ ግዛት ናኙኪ ከተማ የአሜሪካ መንግስት ሊገነባው ባቀደው የኢቦላ መከላከያ ማኳያ ማዕከል ላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ዛሬ ሰኞ ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ አደረጉ።
ነዋሪዎቹ የኢቦላ ቫይረስ ተጋላጭ የሆኑ አሜሪካውያንን ለማቆየት በኬንያ አየር ኃይል የጦር ሰፈር ውስጥ ሊገነባ የታቀደውን ባለ 50 አልጋ ማዕከል የተቃወሙት፣ አስቀድሞ ምንም ዓይነት የሕዝብ ውይይትና ምክክር ሳይደረግበት በምስጢር የተወሰነ ነው በሚል ነው።
ነዋሪዎችና ፖሊስ ወደ ግጭት ውስጥ የገቡ ሲሆን የጸጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ሰልፈኞችን ለመበተን መገደዳቸው ታውቋል። በተፈጠረው ግርግር ሳቢያ የናኙኪ ከተማ የንግድና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ የተስተጓጎለ ሲሆን፣ ማዕከሉ ሊገነባ ነው የሚለው ዜና የአካባቢውን የቱሪዝም ዘርፍ ክፉኛ መምታቱ ተገልጿል። በርካታ ዓለም አቀፍ ቱሪስቶች ወደ አካባቢው የሚያደርጉትን የሆቴልና የሆምስቴይ የቦታ ማስያዣ ጥያቄዎችን በጅምላ እየሰረዙ መሆኑን የዘርፉ ባለቤቶች በምሬት ተናግረዋል።
የአካባቢው የንግድ ምክር ቤትና የፖለቲካ መሪዎች መንግስትን በግልጽ እየተቹ ሲሆን፣ የአገሪቱ የጤና ሥርዓት መሰረታዊ ክትባቶችን እንኳን ማቅረብ ባልቻለበት ሁኔታ ዓለም አቀፍ አደጋ የሆነውን የኢቦላ ማቆያ ማዕከል መቀበል አደገኛ መሆኑን ገልጸዋል።
Sponsored by
Surafel
4 days ago
ኪዱ አረፈ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
8 days ago
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
የቦረና ብሔራዊ ፓርክ
ይህ ተፈጥሯዊ ይዘቱ የተጠበቀ ስፍራ ለዱር እንስሳት ግዙፍ መጠለያ ከመሆኑም ባለፈ ለቱሪዝም ዘርፍ ሰፊ ዕድል የሚከፍት ነው።
ተፈጥሯዊ ሥነ-ምህዳርን ጠብቆ የያዘና ፣ የአጥቢ እንስሳት ዝርያዎች፣ ለተለያዩ የወፍ ዓይነቶች እንዲሁም የዕፅዋት ዓይነቶች እንደ ዋነኛ መኖሪያነት ያገለግላል።
8 days ago
ቀኝ አዝማች በኩረ ምዕመናን ትዛዙ ኮሬ የኢትዮጵያን ባህል፣ ቱሪዝምና በጎ አድራጎት በማስፋፋት የሚታወቁ ታዋቂ ኢንተርፕረነር፣ የባህል አምባሳደር እና ሀገር በቀል ሽማግሌ ናቸው። በተለይም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን እና ግዙፍ የባህል ምግብ ቤቶች አንዱ የሆነውን ዮድ አቢሲኒያ (Yod Abyssinia) ባህላዊ ምግብ ቤት በመመስረታቸው በሰፊው ይታወቃሉ።
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
8 days ago
መንግሥት ሁሉንም በፍትሃዊነት የጋራ ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሥራ እየሠራ ነው- ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ
******************
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት የለውጡ መንግሥት ከኢኮኖሚ እና ከፖለቲካ ተሳትፎ ርቀው የነበሩትን የማኅበረሰብ ከፍሎች ወደ ማዕከል በማምጣት እውነተኛ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እያደረገ ይገኛል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት ርቆ የነበረውን በማቅረብ የተገለሉ የሀገራችን ክፍሎችን በፍትሃዊነት የጋራ ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሥራ እየሠራ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም እንደ ሀገር እና እንደ ክልል በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በተቀመጡ ግልፅ የልማት አቅጣጫዎች መሰረት ሰፊ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በዚህም ህዝቡ በግብርና፣ በማዕድን፣ በኢንዱስትሪ እና በቱሪዝም ዘርፎች ያለውን ፀጋ አሟጥጦ በመጠቀም ከሴፍቲኔት ጥገኝነት በመላቀቅ በራሱ ላብ እና ጥረት ሕይወቱን እንዲቀይር ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን አስታውቀዋል፡፡
አዲሱ ትውልድም በዲጂታሉ ዓለም ተወዳዳሪ እንዲሆን በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በተለይም አዲሱ ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ከአዲስ አበባ በየብስ ጉዞ አስር ሰዓት ይወስድ የነበረውን ርቀት ወደ አንድ ሰዓት በማሳጠር የቦረናን ሕዝብ ከማዕከል ጋር በቅርበት እንዳገናኘው አቶ ሽመልስ ገልጸዋል፡፡
ይህ ግዙፍ መሰረተ ልማት የቦረናን ሕዝብ የእንስሳት ሀብት በቀላሉ ከገበያ ጋር በማስተሳሰር የኑሮ ለውጥ እንዲያመጣ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው፣ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #development #gadaairport #borana #unity #infrastructure
******************
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት የለውጡ መንግሥት ከኢኮኖሚ እና ከፖለቲካ ተሳትፎ ርቀው የነበሩትን የማኅበረሰብ ከፍሎች ወደ ማዕከል በማምጣት እውነተኛ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እያደረገ ይገኛል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት ርቆ የነበረውን በማቅረብ የተገለሉ የሀገራችን ክፍሎችን በፍትሃዊነት የጋራ ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሥራ እየሠራ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም እንደ ሀገር እና እንደ ክልል በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በተቀመጡ ግልፅ የልማት አቅጣጫዎች መሰረት ሰፊ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በዚህም ህዝቡ በግብርና፣ በማዕድን፣ በኢንዱስትሪ እና በቱሪዝም ዘርፎች ያለውን ፀጋ አሟጥጦ በመጠቀም ከሴፍቲኔት ጥገኝነት በመላቀቅ በራሱ ላብ እና ጥረት ሕይወቱን እንዲቀይር ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን አስታውቀዋል፡፡
አዲሱ ትውልድም በዲጂታሉ ዓለም ተወዳዳሪ እንዲሆን በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በተለይም አዲሱ ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ከአዲስ አበባ በየብስ ጉዞ አስር ሰዓት ይወስድ የነበረውን ርቀት ወደ አንድ ሰዓት በማሳጠር የቦረናን ሕዝብ ከማዕከል ጋር በቅርበት እንዳገናኘው አቶ ሽመልስ ገልጸዋል፡፡
ይህ ግዙፍ መሰረተ ልማት የቦረናን ሕዝብ የእንስሳት ሀብት በቀላሉ ከገበያ ጋር በማስተሳሰር የኑሮ ለውጥ እንዲያመጣ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው፣ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #development #gadaairport #borana #unity #infrastructure
9 days ago
በነገሌ ቦረና የተገነባው የገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ተመረቀ
ይህ አውሮፕላን ማረፊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻ ሲሆን፣ እንደ ቦይንግ 737 ማክስ ያሉ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም እንዳለው ተገልጿል።
በምረቃው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እንደተናገሩት፣ አውሮፕላን ማረፊያው የአካባቢውንና ድንበር ተሻጋሪ የንግድ ልውውጥን እንዲሁም ቱሪዝምን ለማሳደግ አልሞ በሳምንት ሦስት በረራዎችን ያስተናግዳል።
"የምንገነባው እያንዳንዱ አውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል፣ የክልሎችን ኢኮኖሚ ያነቃቃል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በፈረንጆቹ 2026 80ኛ ዓመቱን የያዘውና የአፍሪካ ኩራት የሆነው አየር መንገድ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ነው ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ይህ አውሮፕላን ማረፊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻ ሲሆን፣ እንደ ቦይንግ 737 ማክስ ያሉ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም እንዳለው ተገልጿል።
በምረቃው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እንደተናገሩት፣ አውሮፕላን ማረፊያው የአካባቢውንና ድንበር ተሻጋሪ የንግድ ልውውጥን እንዲሁም ቱሪዝምን ለማሳደግ አልሞ በሳምንት ሦስት በረራዎችን ያስተናግዳል።
"የምንገነባው እያንዳንዱ አውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል፣ የክልሎችን ኢኮኖሚ ያነቃቃል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በፈረንጆቹ 2026 80ኛ ዓመቱን የያዘውና የአፍሪካ ኩራት የሆነው አየር መንገድ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ነው ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
9 days ago
የነገሌ ቦረና አባ ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በይፋ ተመረቀ
#fastmereja I ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻ የሆነውን አዲሱን የነገሌ ቦረና አባ ገዳ አውሮፕላን ማረፊያን በዛሬው ዕለት በይፋ መርቀዋል። እንደ ቦይንግ 737 ማክስ ያሉ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን ማስተናገድ የሚችለው ይህ ማረፊያ፣ የአካባቢውን የንግድ፣ የቱሪዝምና ድንበር ተሻጋሪ ትስስርን ለማሳደግ ታቅዶ የተገነባ ሲሆን በሳምንት ሦስት ቀናት መደበኛ በረራዎችን እንደሚያስተናግድ ታውቋል።
የአውሮፕላን ማረፊያውን መመረቅ አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፣ የሚገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ከመፍጠሩም በላይ የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ አቅም እንደሚያነቃቃና ሕዝብን ይበልጥ እንደሚያቀራርብ ገልጸዋል። አያይዘውም 80ኛ ዓመቱን የያዘውና የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በእርግጥም "የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ" መሆኑን በተግባር እያሳየ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።
#fastmereja I ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻ የሆነውን አዲሱን የነገሌ ቦረና አባ ገዳ አውሮፕላን ማረፊያን በዛሬው ዕለት በይፋ መርቀዋል። እንደ ቦይንግ 737 ማክስ ያሉ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን ማስተናገድ የሚችለው ይህ ማረፊያ፣ የአካባቢውን የንግድ፣ የቱሪዝምና ድንበር ተሻጋሪ ትስስርን ለማሳደግ ታቅዶ የተገነባ ሲሆን በሳምንት ሦስት ቀናት መደበኛ በረራዎችን እንደሚያስተናግድ ታውቋል።
የአውሮፕላን ማረፊያውን መመረቅ አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፣ የሚገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ከመፍጠሩም በላይ የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ አቅም እንደሚያነቃቃና ሕዝብን ይበልጥ እንደሚያቀራርብ ገልጸዋል። አያይዘውም 80ኛ ዓመቱን የያዘውና የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በእርግጥም "የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ" መሆኑን በተግባር እያሳየ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።
9 days ago
ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች አዲስ ምዕራፍ ከፍተዋል
****************************
በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች እየተተገበሩ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች፣ የዜጎችን ክብርና ምቾት በማስቀደም በኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፍተዋል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች ጥራት ያላቸው የጤና ተቋማትን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችንና የምገባ ማዕከላትን ያካተቱ ሲሆን፤ የጤና ተቋማቱ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገዋል።
የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም ደግሞ በትምህርት ገበታ የመቆየት ምጣኔን በማሳደግ ረገድ ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በ2017 የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ 1.6 ሚሊዮን፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ከ8 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ሆነዋል። ይህም ለ36 ሺህ እናቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ ለምገባው የሚሆኑ ምርቶች ከአካባቢው አርሶ አደሮች የሚሸመቱ በመሆናቸው ኢኮኖሚያዊ ትስስሩን አጠናክሮታል።
በሌላ በኩል፣ በአቅመ ደካሞች የኑሮ ማሻሻያ ዘርፍ በመንግስትና በበጎ ፈቃደኞች ትብብር ከ45 ሺህ በላይ የመኖሪያ ቤቶች ተገንብተው ተላልፈዋል።
የዲጂታል ዘርፉን ለማሳደግ ታቅዶ እየተተገበረ ባለው የ«5 ሚሊዮን ኮደሮች» ሥልጠናም እስካሁን ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ባለፉት ዓመታት በቱሪዝም፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ በቀዳማዊ ልጅነት (Early Childhood) እንዲሁም በአረንጓዴ ኢኮኖሚ የተከናወኑ ተግባራት ዜጎችን ማዕከል ያደረገ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት በማስመዝገብ ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግረዋል።
በንፍታሌም እንግዳወርቅ
****************************
በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች እየተተገበሩ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች፣ የዜጎችን ክብርና ምቾት በማስቀደም በኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፍተዋል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች ጥራት ያላቸው የጤና ተቋማትን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችንና የምገባ ማዕከላትን ያካተቱ ሲሆን፤ የጤና ተቋማቱ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገዋል።
የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም ደግሞ በትምህርት ገበታ የመቆየት ምጣኔን በማሳደግ ረገድ ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በ2017 የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ 1.6 ሚሊዮን፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ከ8 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ሆነዋል። ይህም ለ36 ሺህ እናቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ ለምገባው የሚሆኑ ምርቶች ከአካባቢው አርሶ አደሮች የሚሸመቱ በመሆናቸው ኢኮኖሚያዊ ትስስሩን አጠናክሮታል።
በሌላ በኩል፣ በአቅመ ደካሞች የኑሮ ማሻሻያ ዘርፍ በመንግስትና በበጎ ፈቃደኞች ትብብር ከ45 ሺህ በላይ የመኖሪያ ቤቶች ተገንብተው ተላልፈዋል።
የዲጂታል ዘርፉን ለማሳደግ ታቅዶ እየተተገበረ ባለው የ«5 ሚሊዮን ኮደሮች» ሥልጠናም እስካሁን ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ባለፉት ዓመታት በቱሪዝም፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ በቀዳማዊ ልጅነት (Early Childhood) እንዲሁም በአረንጓዴ ኢኮኖሚ የተከናወኑ ተግባራት ዜጎችን ማዕከል ያደረገ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት በማስመዝገብ ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግረዋል።
በንፍታሌም እንግዳወርቅ
10 days ago
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዘመናት ባልቀየሩት ድንቅ ተፈጥሮና ጥንታዊ ማንነት ውስጥ የሚኖር ታላቅና ኩሩ ህዝብ አለ።
እነርሱ የሱሪ ህዝቦች ናቸው! እነርሱ የተፈጥሮ እውነተኛ ጠባቂዎች፣ የጀግንነት መፍለቂያዎችና የጥንታዊ ባህል ህያው ምስክሮች ናቸው።
ምድራቸው በለምለም ኮረብታዎች፣ ጥቅጥቅ ባሉ ደኖች፣ ሰፋፊ ሳር ምድሮችና ውድ ማዕድናት የተከበበች እውነተኛ ገነት ናት።
የሱሪ ህዝብ ማህበራዊ መሰረት በሶስት ታላላቅ ጎሳዎች ላይ የተገነባ ነው። እያንዳንዱ ጎሳ የራሱ የሆነ ታሪካዊ የአመራር መዋቅር ያለው ሲሆን፥ ዛሬም ድረስ በአባቶች ጥበብና ስርአት ይመራል።
ከነዚያ ውስጥም የቻይ ጎሳ የሚባሉት ናቸው። ቻይ በታሪካቸው ዶሎቴ ኤከዲ እና ሃላጋሜሪ የተባሉ ሶስት ታላላቅ መሪዎች ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ጎሳውን በቁርጠኝነትና በጥበብ እየመራ ያለው ግንባር ቀደሙ መሪያቸው ዶሎቴ ነው።
የቲርማጋ ጎሳ (Tirmaga): በአምስት ዝነኛ መሪዎች (ቦሎጊዳንጊ ፣ ኦሌዞጊ ፣ ኦሌሲርዋ ፣ ቤባላ እና ኦሊኛሜሪ) የሚታወቁ ሲሆን፥ በአሁኑ ሰዓት የህዝቡ ዋና አለኝታና መሪ ቦሎጊዳንጊ ነው።
የባሌ ጎሳ (Ba'ale): ልክ እንደ ቲርማጋ አምስት ታዋቂ መሪዎች (ዳላላ ፣ ሚሮሊንጎ ፣ ማሆሊ፣ ሲሪያሊ እና ዎሲ) ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ጊዜ ህዝባቸውን በጋራና በትብብር እየመሩ ያሉት ዳላላ እና ሚሮሊንጎ ናቸው።
በአሁኑ ሰዓት መላውን የሱሪ ህዝብ በአንድነት፣ በሰላምና በባህላዊ ስርአት እየመሩ ያሉ 4 ታላላቅ መሪዎች አሉ። እነርሱም፦ ዶሎቴ (ለቻይ) ፣ ቦሎጊዳንጊ (ለቲርማጋ) ፣ ዳላላ እና ሚሮሊንጎ (ለባሌ) ናቸው።
የእነርሱ ህይወት ከተፈጥሮ መሬታቸው ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው። የሚተዳደሩበት የምጣኔ ሀብት ዘይቤ ሶስት ዋና ምሰሶዎች አሉት።
በአብዛኛው ከብት አርቢ (Pastoralist) ማህበረሰብ ናቸው። ከብት ለእነርሱ ተራ እንስሳ አይደለም፤ የሀብት መለኪያ፣ የማህበራዊ ክብር መግለጫ፣ የጋብቻ ትስስር ማጠንጠኛና የህልውናቸው ትልቁ ምሰሶ ፣ ስያሜም (መጠሪያም ጭምር ነው።
ከከብት እርባታው ጎን ለጎን፣ ለም ምድራቸውን በጥረት የሚያርሱ ድንቅ ገበሬዎች አሏቸው። ስነ-ምህዳሩን በጠበቀ መልኩ ማሽላ፣ በቆሎ እና የተለያዩ ሰብሎችን በስፋት ያመርታሉ።
ከእርሻና ከከብት እርባታው ባሻገር፣ የሱሪ ምድር በወርቅ ማዕድን የበለፀገች ናት። የሱሪ ወጣቶችና ማህበረሰቡ በየወንዞቻቸውና በባህላዊ ማዕድን ቦታዎች (እንደ ባሻጊ ፣ ሞጋ ፣ናሜሪ ማዕድን ያሉ) በመሄድ ወርቅ በባህላዊ መንገድ የማውጣትና የማጠብ (Gold Panning) አስደናቂ የስራ ባህል አላቸው። ይህ ማዕድን ለቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የኑሮ መሠረት ይሆናል።
የሱሪ ምድር በዓለም ላይ ካሉ እጅግ ማራኪና ያልተነኩ (Unexplored) የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። በአለም አቀፍ ደረጃ ለቱሪዝም ተመራጭ ከሆኖ 7 መዳረሻዎች አንዱ ነው።
እምቅ የቱሪዝም ሀብቶቻቸው አሏቸው የሱሪ ህዝብ ከፍታና ዝቅታ ያላቸው አረንጓዴ ኮረብታዎች፣ ታላላቅ ወንዞችና የዱር እንስሳት መሸሸጊያ የሆኑ ጥቅጥቅ ያሉ ደኖች ሰላማዊ ድባብን ይፈጥራሉ።
ንጹህ አየርና አስደናቂ የተፈጥሮ እይታን ለሚፈልግ ተጓዥ ተመራጭ ስፍራ ነው።
የሱሪ ወጣቶች የወንድነት መገለጫ የሆነው የዶንጋ (Donga) የበትር ፍልሚያ አላቸው። ወጣቶቻቸው ጀግንነታቸውን፣ ጥንካሬያቸውንና ብቃታቸውን የሚያሳዩበት ታላቅ ባህላዊ የበትር ጨዋታ ነው። ይህ ጨዋታ ስነ-ስርአትንና የሱሪን ወንድነት መገለጫ የሚያሳይ በመሆኑ በየዓመቱ የበርካታ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ቀልብ ይስባል።
ሌላኛው የሴቶቻቸው የከንፈር ሸክላ (Lip plates) የውበትና የብስለት መገለጫ ሲሆን፥ በሰውነት ላይ የሚሳሉ ውብ የተፈጥሮ ቀለሞች (Body painting) እና ባህላዊ ንቅሳቶች የእነርሱን ጥልቅ የጥበብ ስሜት ያሳያሉ።
የሱሪ ህዝቦች የትናንት ታሪካቸውን ሳናጣ፣ የዛሬውን የአመራር ጥበባቸውን ጠብቀው፣ ከተፈጥሮና ከምድራቸው ወርቃማ ፀጋ ጋር በሰላም የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው። ምድራቸው የባህል ሙዚየም፣ የመልክዓ-ምድር ውበት ማሳያና የኢትዮጵያ ድንቅ ቀለም ናት። ይህንን እውነተኛና ያልተበረዘ ተፈጥሮአዊና ባህላዊ ሀብት ለማየት፣ ለመማርና ለመደመም ሁል ጊዜም በደስታ ይቀበሏችኋል!
ኢትዮጵያ በባህልና በተፈጥሮ የታደለች ውብ ሀገር ናት! የሱሪ ህዝቦች ደግሞ የዚህ ውበት ደማቅ ምስክሮች ናቸው!
(በሙባረክ አበበ)
ሚዛን ሚዲያና ኮሙኒኬሽን
እነርሱ የሱሪ ህዝቦች ናቸው! እነርሱ የተፈጥሮ እውነተኛ ጠባቂዎች፣ የጀግንነት መፍለቂያዎችና የጥንታዊ ባህል ህያው ምስክሮች ናቸው።
ምድራቸው በለምለም ኮረብታዎች፣ ጥቅጥቅ ባሉ ደኖች፣ ሰፋፊ ሳር ምድሮችና ውድ ማዕድናት የተከበበች እውነተኛ ገነት ናት።
የሱሪ ህዝብ ማህበራዊ መሰረት በሶስት ታላላቅ ጎሳዎች ላይ የተገነባ ነው። እያንዳንዱ ጎሳ የራሱ የሆነ ታሪካዊ የአመራር መዋቅር ያለው ሲሆን፥ ዛሬም ድረስ በአባቶች ጥበብና ስርአት ይመራል።
ከነዚያ ውስጥም የቻይ ጎሳ የሚባሉት ናቸው። ቻይ በታሪካቸው ዶሎቴ ኤከዲ እና ሃላጋሜሪ የተባሉ ሶስት ታላላቅ መሪዎች ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ጎሳውን በቁርጠኝነትና በጥበብ እየመራ ያለው ግንባር ቀደሙ መሪያቸው ዶሎቴ ነው።
የቲርማጋ ጎሳ (Tirmaga): በአምስት ዝነኛ መሪዎች (ቦሎጊዳንጊ ፣ ኦሌዞጊ ፣ ኦሌሲርዋ ፣ ቤባላ እና ኦሊኛሜሪ) የሚታወቁ ሲሆን፥ በአሁኑ ሰዓት የህዝቡ ዋና አለኝታና መሪ ቦሎጊዳንጊ ነው።
የባሌ ጎሳ (Ba'ale): ልክ እንደ ቲርማጋ አምስት ታዋቂ መሪዎች (ዳላላ ፣ ሚሮሊንጎ ፣ ማሆሊ፣ ሲሪያሊ እና ዎሲ) ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ጊዜ ህዝባቸውን በጋራና በትብብር እየመሩ ያሉት ዳላላ እና ሚሮሊንጎ ናቸው።
በአሁኑ ሰዓት መላውን የሱሪ ህዝብ በአንድነት፣ በሰላምና በባህላዊ ስርአት እየመሩ ያሉ 4 ታላላቅ መሪዎች አሉ። እነርሱም፦ ዶሎቴ (ለቻይ) ፣ ቦሎጊዳንጊ (ለቲርማጋ) ፣ ዳላላ እና ሚሮሊንጎ (ለባሌ) ናቸው።
የእነርሱ ህይወት ከተፈጥሮ መሬታቸው ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው። የሚተዳደሩበት የምጣኔ ሀብት ዘይቤ ሶስት ዋና ምሰሶዎች አሉት።
በአብዛኛው ከብት አርቢ (Pastoralist) ማህበረሰብ ናቸው። ከብት ለእነርሱ ተራ እንስሳ አይደለም፤ የሀብት መለኪያ፣ የማህበራዊ ክብር መግለጫ፣ የጋብቻ ትስስር ማጠንጠኛና የህልውናቸው ትልቁ ምሰሶ ፣ ስያሜም (መጠሪያም ጭምር ነው።
ከከብት እርባታው ጎን ለጎን፣ ለም ምድራቸውን በጥረት የሚያርሱ ድንቅ ገበሬዎች አሏቸው። ስነ-ምህዳሩን በጠበቀ መልኩ ማሽላ፣ በቆሎ እና የተለያዩ ሰብሎችን በስፋት ያመርታሉ።
ከእርሻና ከከብት እርባታው ባሻገር፣ የሱሪ ምድር በወርቅ ማዕድን የበለፀገች ናት። የሱሪ ወጣቶችና ማህበረሰቡ በየወንዞቻቸውና በባህላዊ ማዕድን ቦታዎች (እንደ ባሻጊ ፣ ሞጋ ፣ናሜሪ ማዕድን ያሉ) በመሄድ ወርቅ በባህላዊ መንገድ የማውጣትና የማጠብ (Gold Panning) አስደናቂ የስራ ባህል አላቸው። ይህ ማዕድን ለቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የኑሮ መሠረት ይሆናል።
የሱሪ ምድር በዓለም ላይ ካሉ እጅግ ማራኪና ያልተነኩ (Unexplored) የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። በአለም አቀፍ ደረጃ ለቱሪዝም ተመራጭ ከሆኖ 7 መዳረሻዎች አንዱ ነው።
እምቅ የቱሪዝም ሀብቶቻቸው አሏቸው የሱሪ ህዝብ ከፍታና ዝቅታ ያላቸው አረንጓዴ ኮረብታዎች፣ ታላላቅ ወንዞችና የዱር እንስሳት መሸሸጊያ የሆኑ ጥቅጥቅ ያሉ ደኖች ሰላማዊ ድባብን ይፈጥራሉ።
ንጹህ አየርና አስደናቂ የተፈጥሮ እይታን ለሚፈልግ ተጓዥ ተመራጭ ስፍራ ነው።
የሱሪ ወጣቶች የወንድነት መገለጫ የሆነው የዶንጋ (Donga) የበትር ፍልሚያ አላቸው። ወጣቶቻቸው ጀግንነታቸውን፣ ጥንካሬያቸውንና ብቃታቸውን የሚያሳዩበት ታላቅ ባህላዊ የበትር ጨዋታ ነው። ይህ ጨዋታ ስነ-ስርአትንና የሱሪን ወንድነት መገለጫ የሚያሳይ በመሆኑ በየዓመቱ የበርካታ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ቀልብ ይስባል።
ሌላኛው የሴቶቻቸው የከንፈር ሸክላ (Lip plates) የውበትና የብስለት መገለጫ ሲሆን፥ በሰውነት ላይ የሚሳሉ ውብ የተፈጥሮ ቀለሞች (Body painting) እና ባህላዊ ንቅሳቶች የእነርሱን ጥልቅ የጥበብ ስሜት ያሳያሉ።
የሱሪ ህዝቦች የትናንት ታሪካቸውን ሳናጣ፣ የዛሬውን የአመራር ጥበባቸውን ጠብቀው፣ ከተፈጥሮና ከምድራቸው ወርቃማ ፀጋ ጋር በሰላም የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው። ምድራቸው የባህል ሙዚየም፣ የመልክዓ-ምድር ውበት ማሳያና የኢትዮጵያ ድንቅ ቀለም ናት። ይህንን እውነተኛና ያልተበረዘ ተፈጥሮአዊና ባህላዊ ሀብት ለማየት፣ ለመማርና ለመደመም ሁል ጊዜም በደስታ ይቀበሏችኋል!
ኢትዮጵያ በባህልና በተፈጥሮ የታደለች ውብ ሀገር ናት! የሱሪ ህዝቦች ደግሞ የዚህ ውበት ደማቅ ምስክሮች ናቸው!
(በሙባረክ አበበ)
ሚዛን ሚዲያና ኮሙኒኬሽን
10 days ago
አዲስ አበባ : ኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ተመረቀ
ከ40 በላይ በሚሆኑ የህክምና ባለሙያዎችና አጋሮች ጥምረት የተከፈተው ዘመናዊው ኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዋና ከተማዋ በይፋ ተመርቋል።
ማዕከሉ አዲስ አበባን የህክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግና በከተማዋ ያለውን ከፍተኛ የህክምና አገልግሎት ፍላጎት ለማቃለል ያለመ መሆኑ በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ፍሬሁን አየለ እንደተናገሩት፣ ተቋሙ ከ35 በላይ ስፔሻሊስት እና ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞችን ጨምሮ ከተለያዩ የጤና ዘርፎች በተውጣጡ ባለሙያዎች የጋራ ራዕይ የተመሰረተ መሆኑን አስታውቀዋል።
የሆስፒታሉ ዋነኛ መርህ ሰብአዊ ክብርን የጠበቀና ርህራሄ የተሞላበት አገልግሎት መስጠት መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፣ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር ዘመናዊ የህክምና እውቀትና ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እንደሚሰሩ አስረድተዋል።
ዶክተር ፍሬሁን አያይዘውም ማህበረሰቡን ለማገልገል ለሚነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግስት ከባድ መያዣ የሌለበት የብድርና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያመቻች ጠይቀዋል።
በምረቃው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ የጤና ባለሙያዎች ከተናጠል አሰራር ወጥተው በህብረት እንዲህ ያለ ግዙፍ የህክምና ማዕከል መክፈታቸው ለሌሎች አርአያ የሚሆን ተግባር ነው በማለት አድንቀዋል።
ከተማ አስተዳደሩ ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ከሚያከናውናቸው የኮሪደር፣ የወንዝ ዳርቻ ልማትና የህዝብ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ጎን ለጎን፣ የግሉን የጤና ዘርፍ ለማገዝ የመሬት፣ የመሰረተ ልማት እና የካፒታል ሊዝ ፋይናንስ ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሆስፒታሉ ዜጎች ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚወስዱትን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በሀገር ውስጥ ለማስቀረትና የከተማዋን የሕክምና ቱሪዝም አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ እገዛ እንደሚኖረውም ጠቅሰዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ በበኩላቸው፣ ሆስፒታሉ ወደ ስራ መግባቱ ለጤናው ዘርፍ ትልቅ የምስራች መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲው ከበሽታ መከላከል ባለፈ በማከም፣ በማዳንና በተሃድሶ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ያስረዱት ኃላፊው፣ የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል መከፈት ለዘርፉ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል።
ባለሙያዎቹ የህክምና ስነ ምግባርን በጠበቀ መልኩ ህዝቡን በታማኝነት እንዲያገለግሉ አደራ ያሉት ኃላፊው፣ የጤና ቢሮው ተቋሙን እንደ መንግስት ሆስፒታል በመቁጠር አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አማረ አሰፋ ሆስፒታሉ ዓለም የደረሰበትን የሕክምና መሣሪያዎችና ምቹ የሕክምና ክፍሎችን በማሟላት ከአጎራባች ሀገራት የሚመጡ ታካሚዎችን ጭምር ለማስተናገድ ሙሉ ዝግጁ ሆኗል ብለዋል።
#nucleushospital #healthsector #addisababahealth #medicaltourism
ከ40 በላይ በሚሆኑ የህክምና ባለሙያዎችና አጋሮች ጥምረት የተከፈተው ዘመናዊው ኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዋና ከተማዋ በይፋ ተመርቋል።
ማዕከሉ አዲስ አበባን የህክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግና በከተማዋ ያለውን ከፍተኛ የህክምና አገልግሎት ፍላጎት ለማቃለል ያለመ መሆኑ በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ፍሬሁን አየለ እንደተናገሩት፣ ተቋሙ ከ35 በላይ ስፔሻሊስት እና ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞችን ጨምሮ ከተለያዩ የጤና ዘርፎች በተውጣጡ ባለሙያዎች የጋራ ራዕይ የተመሰረተ መሆኑን አስታውቀዋል።
የሆስፒታሉ ዋነኛ መርህ ሰብአዊ ክብርን የጠበቀና ርህራሄ የተሞላበት አገልግሎት መስጠት መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፣ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር ዘመናዊ የህክምና እውቀትና ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እንደሚሰሩ አስረድተዋል።
ዶክተር ፍሬሁን አያይዘውም ማህበረሰቡን ለማገልገል ለሚነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግስት ከባድ መያዣ የሌለበት የብድርና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያመቻች ጠይቀዋል።
በምረቃው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ የጤና ባለሙያዎች ከተናጠል አሰራር ወጥተው በህብረት እንዲህ ያለ ግዙፍ የህክምና ማዕከል መክፈታቸው ለሌሎች አርአያ የሚሆን ተግባር ነው በማለት አድንቀዋል።
ከተማ አስተዳደሩ ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ከሚያከናውናቸው የኮሪደር፣ የወንዝ ዳርቻ ልማትና የህዝብ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ጎን ለጎን፣ የግሉን የጤና ዘርፍ ለማገዝ የመሬት፣ የመሰረተ ልማት እና የካፒታል ሊዝ ፋይናንስ ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሆስፒታሉ ዜጎች ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚወስዱትን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በሀገር ውስጥ ለማስቀረትና የከተማዋን የሕክምና ቱሪዝም አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ እገዛ እንደሚኖረውም ጠቅሰዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ በበኩላቸው፣ ሆስፒታሉ ወደ ስራ መግባቱ ለጤናው ዘርፍ ትልቅ የምስራች መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲው ከበሽታ መከላከል ባለፈ በማከም፣ በማዳንና በተሃድሶ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ያስረዱት ኃላፊው፣ የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል መከፈት ለዘርፉ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል።
ባለሙያዎቹ የህክምና ስነ ምግባርን በጠበቀ መልኩ ህዝቡን በታማኝነት እንዲያገለግሉ አደራ ያሉት ኃላፊው፣ የጤና ቢሮው ተቋሙን እንደ መንግስት ሆስፒታል በመቁጠር አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አማረ አሰፋ ሆስፒታሉ ዓለም የደረሰበትን የሕክምና መሣሪያዎችና ምቹ የሕክምና ክፍሎችን በማሟላት ከአጎራባች ሀገራት የሚመጡ ታካሚዎችን ጭምር ለማስተናገድ ሙሉ ዝግጁ ሆኗል ብለዋል።
#nucleushospital #healthsector #addisababahealth #medicaltourism
11 days ago
አዲስ አበባ : ኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ተመረቀ
#ethiopia | ከ40 በላይ በሚሆኑ የህክምና ባለሙያዎችና አጋሮች ጥምረት የተከፈተው ዘመናዊው ኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዋና ከተማዋ በይፋ ተመርቋል።
ማዕከሉ አዲስ አበባን የህክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግና በከተማዋ ያለውን ከፍተኛ የህክምና አገልግሎት ፍላጎት ለማቃለል ያለመ መሆኑ በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ፍሬሁን አየለ እንደተናገሩት፣ ተቋሙ ከ35 በላይ ስፔሻሊስት እና ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞችን ጨምሮ ከተለያዩ የጤና ዘርፎች በተውጣጡ ባለሙያዎች የጋራ ራዕይ የተመሰረተ መሆኑን አስታውቀዋል።
የሆስፒታሉ ዋነኛ መርህ ሰብአዊ ክብርን የጠበቀና ርህራሄ የተሞላበት አገልግሎት መስጠት መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፣ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር ዘመናዊ የህክምና እውቀትና ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እንደሚሰሩ አስረድተዋል።
ዶክተር ፍሬሁን አያይዘውም ማህበረሰቡን ለማገልገል ለሚነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግስት ከባድ መያዣ የሌለበት የብድርና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያመቻች ጠይቀዋል።
በምረቃው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ የጤና ባለሙያዎች ከተናጠል አሰራር ወጥተው በህብረት እንዲህ ያለ ግዙፍ የህክምና ማዕከል መክፈታቸው ለሌሎች አርአያ የሚሆን ተግባር ነው በማለት አድንቀዋል።
ከተማ አስተዳደሩ ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ከሚያከናውናቸው የኮሪደር፣ የወንዝ ዳርቻ ልማትና የህዝብ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ጎን ለጎን፣ የግሉን የጤና ዘርፍ ለማገዝ የመሬት፣ የመሰረተ ልማት እና የካፒታል ሊዝ ፋይናንስ ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሆስፒታሉ ዜጎች ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚወስዱትን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በሀገር ውስጥ ለማስቀረትና የከተማዋን የሕክምና ቱሪዝም አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ እገዛ እንደሚኖረውም ጠቅሰዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ በበኩላቸው፣ ሆስፒታሉ ወደ ስራ መግባቱ ለጤናው ዘርፍ ትልቅ የምስራች መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲው ከበሽታ መከላከል ባለፈ በማከም፣ በማዳንና በተሃድሶ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ያስረዱት ኃላፊው፣ የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል መከፈት ለዘርፉ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል።
ባለሙያዎቹ የህክምና ስነ ምግባርን በጠበቀ መልኩ ህዝቡን በታማኝነት እንዲያገለግሉ አደራ ያሉት ኃላፊው፣ የጤና ቢሮው ተቋሙን እንደ መንግስት ሆስፒታል በመቁጠር አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አማረ አሰፋ ሆስፒታሉ ዓለም የደረሰበትን የሕክምና መሣሪያዎችና ምቹ የሕክምና ክፍሎችን በማሟላት ከአጎራባች ሀገራት የሚመጡ ታካሚዎችን ጭምር ለማስተናገድ ሙሉ ዝግጁ ሆኗል ብለዋል።
#ethiopia | ከ40 በላይ በሚሆኑ የህክምና ባለሙያዎችና አጋሮች ጥምረት የተከፈተው ዘመናዊው ኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዋና ከተማዋ በይፋ ተመርቋል።
ማዕከሉ አዲስ አበባን የህክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግና በከተማዋ ያለውን ከፍተኛ የህክምና አገልግሎት ፍላጎት ለማቃለል ያለመ መሆኑ በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ፍሬሁን አየለ እንደተናገሩት፣ ተቋሙ ከ35 በላይ ስፔሻሊስት እና ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞችን ጨምሮ ከተለያዩ የጤና ዘርፎች በተውጣጡ ባለሙያዎች የጋራ ራዕይ የተመሰረተ መሆኑን አስታውቀዋል።
የሆስፒታሉ ዋነኛ መርህ ሰብአዊ ክብርን የጠበቀና ርህራሄ የተሞላበት አገልግሎት መስጠት መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፣ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር ዘመናዊ የህክምና እውቀትና ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እንደሚሰሩ አስረድተዋል።
ዶክተር ፍሬሁን አያይዘውም ማህበረሰቡን ለማገልገል ለሚነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግስት ከባድ መያዣ የሌለበት የብድርና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያመቻች ጠይቀዋል።
በምረቃው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ የጤና ባለሙያዎች ከተናጠል አሰራር ወጥተው በህብረት እንዲህ ያለ ግዙፍ የህክምና ማዕከል መክፈታቸው ለሌሎች አርአያ የሚሆን ተግባር ነው በማለት አድንቀዋል።
ከተማ አስተዳደሩ ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ከሚያከናውናቸው የኮሪደር፣ የወንዝ ዳርቻ ልማትና የህዝብ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ጎን ለጎን፣ የግሉን የጤና ዘርፍ ለማገዝ የመሬት፣ የመሰረተ ልማት እና የካፒታል ሊዝ ፋይናንስ ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሆስፒታሉ ዜጎች ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚወስዱትን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በሀገር ውስጥ ለማስቀረትና የከተማዋን የሕክምና ቱሪዝም አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ እገዛ እንደሚኖረውም ጠቅሰዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ በበኩላቸው፣ ሆስፒታሉ ወደ ስራ መግባቱ ለጤናው ዘርፍ ትልቅ የምስራች መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲው ከበሽታ መከላከል ባለፈ በማከም፣ በማዳንና በተሃድሶ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ያስረዱት ኃላፊው፣ የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል መከፈት ለዘርፉ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል።
ባለሙያዎቹ የህክምና ስነ ምግባርን በጠበቀ መልኩ ህዝቡን በታማኝነት እንዲያገለግሉ አደራ ያሉት ኃላፊው፣ የጤና ቢሮው ተቋሙን እንደ መንግስት ሆስፒታል በመቁጠር አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አማረ አሰፋ ሆስፒታሉ ዓለም የደረሰበትን የሕክምና መሣሪያዎችና ምቹ የሕክምና ክፍሎችን በማሟላት ከአጎራባች ሀገራት የሚመጡ ታካሚዎችን ጭምር ለማስተናገድ ሙሉ ዝግጁ ሆኗል ብለዋል።
Sponsored by
Surafel
11 days ago
አዲስ አበባ : ኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ተመረቀ
#ethiopia | ከ40 በላይ በሚሆኑ የህክምና ባለሙያዎችና አጋሮች ጥምረት የተከፈተው ዘመናዊው ኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዋና ከተማዋ በይፋ ተመርቋል።
ማዕከሉ አዲስ አበባን የህክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግና በከተማዋ ያለውን ከፍተኛ የህክምና አገልግሎት ፍላጎት ለማቃለል ያለመ መሆኑ በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ፍሬሁን አየለ እንደተናገሩት፣ ተቋሙ ከ35 በላይ ስፔሻሊስት እና ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞችን ጨምሮ ከተለያዩ የጤና ዘርፎች በተውጣጡ ባለሙያዎች የጋራ ራዕይ የተመሰረተ መሆኑን አስታውቀዋል።
የሆስፒታሉ ዋነኛ መርህ ሰብአዊ ክብርን የጠበቀና ርህራሄ የተሞላበት አገልግሎት መስጠት መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፣ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር ዘመናዊ የህክምና እውቀትና ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እንደሚሰሩ አስረድተዋል።
ዶክተር ፍሬሁን አያይዘውም ማህበረሰቡን ለማገልገል ለሚነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግስት ከባድ መያዣ የሌለበት የብድርና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያመቻች ጠይቀዋል።
በምረቃው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ የጤና ባለሙያዎች ከተናጠል አሰራር ወጥተው በህብረት እንዲህ ያለ ግዙፍ የህክምና ማዕከል መክፈታቸው ለሌሎች አርአያ የሚሆን ተግባር ነው በማለት አድንቀዋል።
ከተማ አስተዳደሩ ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ከሚያከናውናቸው የኮሪደር፣ የወንዝ ዳርቻ ልማትና የህዝብ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ጎን ለጎን፣ የግሉን የጤና ዘርፍ ለማገዝ የመሬት፣ የመሰረተ ልማት እና የካፒታል ሊዝ ፋይናንስ ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሆስፒታሉ ዜጎች ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚወስዱትን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በሀገር ውስጥ ለማስቀረትና የከተማዋን የሕክምና ቱሪዝም አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ እገዛ እንደሚኖረውም ጠቅሰዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ በበኩላቸው፣ ሆስፒታሉ ወደ ስራ መግባቱ ለጤናው ዘርፍ ትልቅ የምስራች መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲው ከበሽታ መከላከል ባለፈ በማከም፣ በማዳንና በተሃድሶ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ያስረዱት ኃላፊው፣ የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል መከፈት ለዘርፉ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል።
ባለሙያዎቹ የህክምና ስነ ምግባርን በጠበቀ መልኩ ህዝቡን በታማኝነት እንዲያገለግሉ አደራ ያሉት ኃላፊው፣ የጤና ቢሮው ተቋሙን እንደ መንግስት ሆስፒታል በመቁጠር አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አማረ አሰፋ ሆስፒታሉ ዓለም የደረሰበትን የሕክምና መሣሪያዎችና ምቹ የሕክምና ክፍሎችን በማሟላት ከአጎራባች ሀገራት የሚመጡ ታካሚዎችን ጭምር ለማስተናገድ ሙሉ ዝግጁ ሆኗል ብለዋል።
#nucleushospital #healthsector #addisababahealth #medicaltourism #ethiopiahealthcare #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ከ40 በላይ በሚሆኑ የህክምና ባለሙያዎችና አጋሮች ጥምረት የተከፈተው ዘመናዊው ኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዋና ከተማዋ በይፋ ተመርቋል።
ማዕከሉ አዲስ አበባን የህክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግና በከተማዋ ያለውን ከፍተኛ የህክምና አገልግሎት ፍላጎት ለማቃለል ያለመ መሆኑ በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ፍሬሁን አየለ እንደተናገሩት፣ ተቋሙ ከ35 በላይ ስፔሻሊስት እና ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞችን ጨምሮ ከተለያዩ የጤና ዘርፎች በተውጣጡ ባለሙያዎች የጋራ ራዕይ የተመሰረተ መሆኑን አስታውቀዋል።
የሆስፒታሉ ዋነኛ መርህ ሰብአዊ ክብርን የጠበቀና ርህራሄ የተሞላበት አገልግሎት መስጠት መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፣ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር ዘመናዊ የህክምና እውቀትና ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እንደሚሰሩ አስረድተዋል።
ዶክተር ፍሬሁን አያይዘውም ማህበረሰቡን ለማገልገል ለሚነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግስት ከባድ መያዣ የሌለበት የብድርና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያመቻች ጠይቀዋል።
በምረቃው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ የጤና ባለሙያዎች ከተናጠል አሰራር ወጥተው በህብረት እንዲህ ያለ ግዙፍ የህክምና ማዕከል መክፈታቸው ለሌሎች አርአያ የሚሆን ተግባር ነው በማለት አድንቀዋል።
ከተማ አስተዳደሩ ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ከሚያከናውናቸው የኮሪደር፣ የወንዝ ዳርቻ ልማትና የህዝብ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ጎን ለጎን፣ የግሉን የጤና ዘርፍ ለማገዝ የመሬት፣ የመሰረተ ልማት እና የካፒታል ሊዝ ፋይናንስ ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሆስፒታሉ ዜጎች ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚወስዱትን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በሀገር ውስጥ ለማስቀረትና የከተማዋን የሕክምና ቱሪዝም አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ እገዛ እንደሚኖረውም ጠቅሰዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ በበኩላቸው፣ ሆስፒታሉ ወደ ስራ መግባቱ ለጤናው ዘርፍ ትልቅ የምስራች መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲው ከበሽታ መከላከል ባለፈ በማከም፣ በማዳንና በተሃድሶ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ያስረዱት ኃላፊው፣ የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል መከፈት ለዘርፉ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል።
ባለሙያዎቹ የህክምና ስነ ምግባርን በጠበቀ መልኩ ህዝቡን በታማኝነት እንዲያገለግሉ አደራ ያሉት ኃላፊው፣ የጤና ቢሮው ተቋሙን እንደ መንግስት ሆስፒታል በመቁጠር አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኒውክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አማረ አሰፋ ሆስፒታሉ ዓለም የደረሰበትን የሕክምና መሣሪያዎችና ምቹ የሕክምና ክፍሎችን በማሟላት ከአጎራባች ሀገራት የሚመጡ ታካሚዎችን ጭምር ለማስተናገድ ሙሉ ዝግጁ ሆኗል ብለዋል።
#nucleushospital #healthsector #addisababahealth #medicaltourism #ethiopiahealthcare #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
12 days ago
"በዐይኔ በብረቱ ...!"
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለም ማህበራዊ ጉዷንም፣ ገዷንም በድሯ ሸምና የሰው ልጅ የደረሰበትን ታላላቅ አብዮቶች ታስመለክተን ይዛለች ።
ይህ የዲጂታሉ ዘመን፣ አዲስ መስኮት ነው።
የዓለምን ታሪክ ሰፊ ንዋይ፣ ብዙ የሰው ኃይል እና ጊዜ በልቶ የመንገር ሩጫ በዚህ የመስኮት አቋራጭ በግለሰቦች ስልክና ካሜራ መዳፍ ላይ እየወደቀ ነው።
የማህበራዊ ትስስር ሜዳው ከትናንት ዛሬ፣ ከዛሬም ነገ ትተው ቢሄዱ ቆሞ አይጠብቅም። በዐይን ጥቅሻ ፈትለክ ነው። ለውጡ ፈጣን፣ ተለዋዋጭነቱ ነቅተው እንደ ቴኒስ ዳኛ ወዲህ ወዲያ አንገትዎን የሚነቀንቅ ሆኗል።
ወደ ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ የካሜራ ሌንሳቸውንና በሚሊየን የሚከተሏቸውን ዐይን ይዘው የሚመጡ የመስኮቱ ዘዋሪዎች ለኢትዮጵያ አዲስ ነጋሪት የሚጎስሙ ናቸው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ ተከታዮቻቸው በየሰከንዱ ለሚለቀቁ ይዘቶች ሲሉ ዐይንና ጆሯቸውን በእነዚህ የዘዋሪዎች ዳና ላይ አድርገዋል።
ምክንያቱም ዓለም የዲጂታል ዝመና አብዮቷ ላይ ወደ ፊት እንጂ የኋልዮች ዳራዋን ለመመልከት አፍታም የላትም፤ ተከታዮቻቸውም ጊዜ የለቸውም። አጭር፣ ፈጣን፣ አዲስ ይናፍቃሉ።
የአሜሪካው ታዋቂ የቀጥታ ስርጭት አቅራቢ አይሾው ስፒድ፣ እንዲሁም ከ19 ሚሊየን በላይ የቲክቶክ ተከታዮች ያሉት የዲጂታል ዜና አቅራቢው ዲላን ፔጅ ወደ አዲስ አበባ መምጣት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የዲጂታል ዲፕሎማሲና የቱሪዝም ስበት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የሚያሳይ ትልቅ የጂኦፖለቲካዊና የማኅበራዊ ሚዲያ ለውጥ ማሳያ ነው።
ቀድሞ በኢትዮጵያ ፍቅር የወደቀው ብሪታኒያዊው የቲክቶክ ዜና አቅራቢ ዲላን ፔጅ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታና ስለ ኢትዮጵያውያን የአንድነት መንፈስ በአዎንታ በመዘገብ መንፈሱ ከአካሉ ቀድሞ አዲስ አበባ ከደረሰ ከርሟል።
ይህ ፕሮጀክት በውጭ ዕዳ ሳይሆን በሕዝብ ቦንድና በላብ የተገነባ ነው በማለት አጉልቶ አሳይቷል።
ግድቡንም “በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት የሚቀይረው የአፍሪካ የብርሃን ተስፋ” በማለት ለዓለም ማስተዋወቁን አንረሳም።
ዲላን በርካታ ቀናትን የሚወስደውን ታላቁን ጉዞዬን፣ በቅኝ ግዛት ባልተገዛችው ሀገር ኢትዮጵያ ጀምሬያለሁ በማለት ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ይዞት የመጣው የካሜራ ሌንስ የኢትዮጵያን ጥንታዊነት ብቻ ሳይሆን አዲሱን የቴክኖሎጂ ምዕራፍም ጭምር የገለጠ ሆኗል።
በአዲስ አበባ ቆይታው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን በጎበኘበት ወቅት፥ ይህን በቴክኖሎጂ የተቃኘ ቦታ ሳየው ተደምሜያለሁ፤ አፍሪካ ተቀይራለች፣ አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም የሚያሳይ ቦታ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብሏል።
አዲስ አበባ በቅርቡ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና በጥምረት ከ470 ሚሊየን በላይ ተከታዮች ያሏቸው ከ200 በላይ የዲጂታል ፈጣሪዎች የተሳተፉበትን የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን ማስተናገዷ የይዘት ፈጣሪዎች የዲፕሎማሲ ዋና ከተማ አድርጓታል።
በጉባኤው ላይ በቀረቡ መረጃዎች መሠረት ስለ አፍሪካ የሚሰራጩ የተዛቡና አሉታዊ ትረካዎች በአህጉሪቱ ላይ በየዓመቱ እስከ 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር የሚደርስ የኢኮኖሚ ኪሳራ ያደርሳሉ።
ዲላን ፔጅ እና መሰል የይዘት ፈጣሪዎች ይህንን የተዛባ ምስል ለመስበር 'ሳይነገራችሁ በዓይናችሁ እዩት' በሚል መርህ እየመጡ ነው።
የዲላን ፔጅ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን እንደ አዶናይ ያሉ የሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው።
የተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉብኝት የዲጂታል ዲፕሎማሲና የሀገር ገፅታ ግንባታ ወሳኝ ተግባር ሲሆን፥ የወቅቱ የሀያላን ሀገራት ፉክክር ገር ኃይል መሆኑን ላጤነ ዲፕሎማሲው ይገለጥለታል።
ገር ዲፕሎማሲ ሰዎችን ሳያስገድዱ፣ ወደውና ፈቅደው አንተ የምትፈልገውን ነገር እንዲያደርጉ የማድረግ ብቃት መሆኑን የጽንሰ ሀሳቡ ፈጣሪ አሜሪካዊው ጆሴፍ ናይ ያስረዳሉ።
ለጆሴፍ ምስጋና ይግባውና ሀገራት ከጦር መሳሪያ እሽቅድምድሞሽ ወደ ለስላሳው አቀራረብ ፊታቸውን እንዲያዞሩ አድርጓል።
ከአሜሪካ ገር መንገዶች መካከል ሆሊውድ፣ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ብራንዶች (አፕል, ጎግል, ማይክሮሶፍት)፣ ምግቦች (ማክዶናልድ፣ ኮካ ኮላ) እና ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ይጠቀሳሉ።
ለደቡብ ኮሪያ "ሃሊዩ" ወይም የኮሪያ ማዕበል። ይህም የኬ-ፖፕ ሙዚቃ፣ የኮሪያ ፊልሞችና ድራማዎች እንዲሁም የውበት ምርቶች፤ ለብሪታንያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ፣ ቢቢሲ እና የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ገሩ መንገዳቸው ነው።
ሳዑዲ ዓረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እንደ ማንችስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ የእግር ኳስ ክለቦችን በመግዛት እንዲሁም የዓለም ዋንጫዎችን በማዘጋጀትና እንደ ሮናልዶ ታዋቂ ተጫዋቾችን ወደ ሀገራቸው በማምጣት የዓለምን ትኩረት በመሳብ የሀገራቸውን ገጽታ እያደሱ ይገኛሉ።
ኢትዮጵያም ምድረ ቀደምት፣ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምልክት የአድዋ ድል፣ የፓን-አፍሪካኒዝም ማዕከል መሆኗ፣ የቡና መገኛነቷ፣ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎቿን በማስተዋወቅ የራሷን የዲጂታል ለስላሳ ኃይል እየገነባች ትገኛለች።
በዚህም በቱሪዝም ዘርፍ ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ ይህንን ወርቃማ የዲጂታል ዲፕሎማሲ ዕድል በመጠቀም፣ የቱሪዝምና የኢኮኖሚ ምሰሶዎቿን ለማጠናከር በጥበብና በስልታዊ መሪነት ልትራመድበት ይጠበቃል።
ዲጂታሉ ዓለም በሮችን ከፍቷል፤ የኢትዮጵያን መልኮች በአዲሱ ነጋሪት ማስተጋባት የዛሬ ስራ ነው ።
በኃይለኢየሱስ መኮንን
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለም ማህበራዊ ጉዷንም፣ ገዷንም በድሯ ሸምና የሰው ልጅ የደረሰበትን ታላላቅ አብዮቶች ታስመለክተን ይዛለች ።
ይህ የዲጂታሉ ዘመን፣ አዲስ መስኮት ነው።
የዓለምን ታሪክ ሰፊ ንዋይ፣ ብዙ የሰው ኃይል እና ጊዜ በልቶ የመንገር ሩጫ በዚህ የመስኮት አቋራጭ በግለሰቦች ስልክና ካሜራ መዳፍ ላይ እየወደቀ ነው።
የማህበራዊ ትስስር ሜዳው ከትናንት ዛሬ፣ ከዛሬም ነገ ትተው ቢሄዱ ቆሞ አይጠብቅም። በዐይን ጥቅሻ ፈትለክ ነው። ለውጡ ፈጣን፣ ተለዋዋጭነቱ ነቅተው እንደ ቴኒስ ዳኛ ወዲህ ወዲያ አንገትዎን የሚነቀንቅ ሆኗል።
ወደ ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ የካሜራ ሌንሳቸውንና በሚሊየን የሚከተሏቸውን ዐይን ይዘው የሚመጡ የመስኮቱ ዘዋሪዎች ለኢትዮጵያ አዲስ ነጋሪት የሚጎስሙ ናቸው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ ተከታዮቻቸው በየሰከንዱ ለሚለቀቁ ይዘቶች ሲሉ ዐይንና ጆሯቸውን በእነዚህ የዘዋሪዎች ዳና ላይ አድርገዋል።
ምክንያቱም ዓለም የዲጂታል ዝመና አብዮቷ ላይ ወደ ፊት እንጂ የኋልዮች ዳራዋን ለመመልከት አፍታም የላትም፤ ተከታዮቻቸውም ጊዜ የለቸውም። አጭር፣ ፈጣን፣ አዲስ ይናፍቃሉ።
የአሜሪካው ታዋቂ የቀጥታ ስርጭት አቅራቢ አይሾው ስፒድ፣ እንዲሁም ከ19 ሚሊየን በላይ የቲክቶክ ተከታዮች ያሉት የዲጂታል ዜና አቅራቢው ዲላን ፔጅ ወደ አዲስ አበባ መምጣት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የዲጂታል ዲፕሎማሲና የቱሪዝም ስበት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የሚያሳይ ትልቅ የጂኦፖለቲካዊና የማኅበራዊ ሚዲያ ለውጥ ማሳያ ነው።
ቀድሞ በኢትዮጵያ ፍቅር የወደቀው ብሪታኒያዊው የቲክቶክ ዜና አቅራቢ ዲላን ፔጅ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታና ስለ ኢትዮጵያውያን የአንድነት መንፈስ በአዎንታ በመዘገብ መንፈሱ ከአካሉ ቀድሞ አዲስ አበባ ከደረሰ ከርሟል።
ይህ ፕሮጀክት በውጭ ዕዳ ሳይሆን በሕዝብ ቦንድና በላብ የተገነባ ነው በማለት አጉልቶ አሳይቷል።
ግድቡንም “በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት የሚቀይረው የአፍሪካ የብርሃን ተስፋ” በማለት ለዓለም ማስተዋወቁን አንረሳም።
ዲላን በርካታ ቀናትን የሚወስደውን ታላቁን ጉዞዬን፣ በቅኝ ግዛት ባልተገዛችው ሀገር ኢትዮጵያ ጀምሬያለሁ በማለት ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ይዞት የመጣው የካሜራ ሌንስ የኢትዮጵያን ጥንታዊነት ብቻ ሳይሆን አዲሱን የቴክኖሎጂ ምዕራፍም ጭምር የገለጠ ሆኗል።
በአዲስ አበባ ቆይታው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን በጎበኘበት ወቅት፥ ይህን በቴክኖሎጂ የተቃኘ ቦታ ሳየው ተደምሜያለሁ፤ አፍሪካ ተቀይራለች፣ አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም የሚያሳይ ቦታ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብሏል።
አዲስ አበባ በቅርቡ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና በጥምረት ከ470 ሚሊየን በላይ ተከታዮች ያሏቸው ከ200 በላይ የዲጂታል ፈጣሪዎች የተሳተፉበትን የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን ማስተናገዷ የይዘት ፈጣሪዎች የዲፕሎማሲ ዋና ከተማ አድርጓታል።
በጉባኤው ላይ በቀረቡ መረጃዎች መሠረት ስለ አፍሪካ የሚሰራጩ የተዛቡና አሉታዊ ትረካዎች በአህጉሪቱ ላይ በየዓመቱ እስከ 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር የሚደርስ የኢኮኖሚ ኪሳራ ያደርሳሉ።
ዲላን ፔጅ እና መሰል የይዘት ፈጣሪዎች ይህንን የተዛባ ምስል ለመስበር 'ሳይነገራችሁ በዓይናችሁ እዩት' በሚል መርህ እየመጡ ነው።
የዲላን ፔጅ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን እንደ አዶናይ ያሉ የሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው።
የተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉብኝት የዲጂታል ዲፕሎማሲና የሀገር ገፅታ ግንባታ ወሳኝ ተግባር ሲሆን፥ የወቅቱ የሀያላን ሀገራት ፉክክር ገር ኃይል መሆኑን ላጤነ ዲፕሎማሲው ይገለጥለታል።
ገር ዲፕሎማሲ ሰዎችን ሳያስገድዱ፣ ወደውና ፈቅደው አንተ የምትፈልገውን ነገር እንዲያደርጉ የማድረግ ብቃት መሆኑን የጽንሰ ሀሳቡ ፈጣሪ አሜሪካዊው ጆሴፍ ናይ ያስረዳሉ።
ለጆሴፍ ምስጋና ይግባውና ሀገራት ከጦር መሳሪያ እሽቅድምድሞሽ ወደ ለስላሳው አቀራረብ ፊታቸውን እንዲያዞሩ አድርጓል።
ከአሜሪካ ገር መንገዶች መካከል ሆሊውድ፣ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ብራንዶች (አፕል, ጎግል, ማይክሮሶፍት)፣ ምግቦች (ማክዶናልድ፣ ኮካ ኮላ) እና ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ይጠቀሳሉ።
ለደቡብ ኮሪያ "ሃሊዩ" ወይም የኮሪያ ማዕበል። ይህም የኬ-ፖፕ ሙዚቃ፣ የኮሪያ ፊልሞችና ድራማዎች እንዲሁም የውበት ምርቶች፤ ለብሪታንያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ፣ ቢቢሲ እና የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ገሩ መንገዳቸው ነው።
ሳዑዲ ዓረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እንደ ማንችስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ የእግር ኳስ ክለቦችን በመግዛት እንዲሁም የዓለም ዋንጫዎችን በማዘጋጀትና እንደ ሮናልዶ ታዋቂ ተጫዋቾችን ወደ ሀገራቸው በማምጣት የዓለምን ትኩረት በመሳብ የሀገራቸውን ገጽታ እያደሱ ይገኛሉ።
ኢትዮጵያም ምድረ ቀደምት፣ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምልክት የአድዋ ድል፣ የፓን-አፍሪካኒዝም ማዕከል መሆኗ፣ የቡና መገኛነቷ፣ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎቿን በማስተዋወቅ የራሷን የዲጂታል ለስላሳ ኃይል እየገነባች ትገኛለች።
በዚህም በቱሪዝም ዘርፍ ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ ይህንን ወርቃማ የዲጂታል ዲፕሎማሲ ዕድል በመጠቀም፣ የቱሪዝምና የኢኮኖሚ ምሰሶዎቿን ለማጠናከር በጥበብና በስልታዊ መሪነት ልትራመድበት ይጠበቃል።
ዲጂታሉ ዓለም በሮችን ከፍቷል፤ የኢትዮጵያን መልኮች በአዲሱ ነጋሪት ማስተጋባት የዛሬ ስራ ነው ።
በኃይለኢየሱስ መኮንን
12 days ago
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ቡኖ ማላ ዓለም አቀፍ ኤክስፖ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ በዲላ ኢንዱስትሪያል ፖርክ ተከፈተ።
የጌዴኦን የቡና እና ሥጋ ሀብት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ፣ የዲላን የኢንቨስትመንት የሥበት ማዕከልነት ከፍ ለማድረግና የቱሪዝም መዳረሻዎቹን ለዓለም በስፋት ለማሳየት ያለመው ይህ ግዙፍ መድረክ ዛሬ ከቀኑ 9:00 በዲላ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሲከፈት የፌደራል እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች የጌዴኦ ዞንና የዲላ ከተማ አመራሮች እና በርካታ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ኤክስፖው በነገው እለትም በበርካታ ባለድርሻ አካላት እየተጎበኘ በኪነ-ጥበባትና መዝናኛ ዝግጅቶች እየተዋዛ እስከ አመሻሽ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
የጌዴኦን የቡና እና ሥጋ ሀብት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ፣ የዲላን የኢንቨስትመንት የሥበት ማዕከልነት ከፍ ለማድረግና የቱሪዝም መዳረሻዎቹን ለዓለም በስፋት ለማሳየት ያለመው ይህ ግዙፍ መድረክ ዛሬ ከቀኑ 9:00 በዲላ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሲከፈት የፌደራል እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች የጌዴኦ ዞንና የዲላ ከተማ አመራሮች እና በርካታ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ኤክስፖው በነገው እለትም በበርካታ ባለድርሻ አካላት እየተጎበኘ በኪነ-ጥበባትና መዝናኛ ዝግጅቶች እየተዋዛ እስከ አመሻሽ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
13 days ago
ለሴት አስተናጋጆች የወጣው አለባበስን የሚመለከተው ደንብ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እየተደረገ እንዳልሆነ ተገለጸ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሴት አስተናጋጆች የተጋለጠ አለባበስ እንዳይለብሱ ለመከልከል ያወጣው ደንብ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እየተደረገ እንዳልሆነ የኢትዮጵያ መስተንግዶ ባለሙያዎች ማኅበር ለአሐዱ አስታውቋል።
ማኅበሩ ለአሐዱ እንዳስታወቀው፤ የከተማ አስተዳደሩ የደንብ ልብስ አለባበስና አፈጻጸም ደንብ ቁጥር 178/2016ትን ተግባራዊ ካደረገ በኋላ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለውጥ ቢታይም፣ በአንዳንድ ተቋማት አሁንም ሴት አስተናጋጆች ስራቸውን ሲሰሩ ሰውነታቸውን የሚያጋልጥ አጭር ቀሚስ እንዲለብሱ መገደዳቸው ቀጥሏል።
በተለይ በምሽት አገልግሎቶች አስተናጋጆች ደንበኛን ለመሳብ በጣም አጫጭር ቀሚሶችን እንዲለብሱ ይገደዳሉ ያሉት የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ያሬድ ደገፉ፤ ደንቡ ጸድቆ ስራ ላይ ከዋለ በኋላ የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለባለሙያዎች እና ለሆቴል ባለቤቶች ተከታታይ ሥልጠናዎች መስጠቱን አስታውሰው፤ አብዛኛዎቹ የሥራ ኃላፊዎች የደንቡን ድንጋጌዎች በመረዳታቸው መሻሻሎች ታይተዋል ብለዋል፡፡
ለችግሩ እንደ መፍትሔ ከቀረቡት አማራጮች መካከል ባህላዊ ሬስቶራንቶች ውስጥ ያሉ አስተናጋጆች ሙሉ የሀበሻ ልብስ እንዲለብሱ ማድረግ እንደሆነም ተነስቷል፡፡ ደንበኞች የቤት መምረጫ መስፈርታቸው የአገልግሎት ጥራት እንዲሆንም አቶ ያሬድ አሳስበዋል፡፡
በመስተንግዶ ዘርፍ ያሉ ባለሙያዎች መብታቸውን፣ ደመወዛቸውንና የአለባበስ ነፃነታቸውን ለማስከበር በማኅበር ተደራጅተው እንዲንቀሳቀሱም ጥሪ አቅርበዋል።
#አሐዱ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሴት አስተናጋጆች የተጋለጠ አለባበስ እንዳይለብሱ ለመከልከል ያወጣው ደንብ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እየተደረገ እንዳልሆነ የኢትዮጵያ መስተንግዶ ባለሙያዎች ማኅበር ለአሐዱ አስታውቋል።
ማኅበሩ ለአሐዱ እንዳስታወቀው፤ የከተማ አስተዳደሩ የደንብ ልብስ አለባበስና አፈጻጸም ደንብ ቁጥር 178/2016ትን ተግባራዊ ካደረገ በኋላ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለውጥ ቢታይም፣ በአንዳንድ ተቋማት አሁንም ሴት አስተናጋጆች ስራቸውን ሲሰሩ ሰውነታቸውን የሚያጋልጥ አጭር ቀሚስ እንዲለብሱ መገደዳቸው ቀጥሏል።
በተለይ በምሽት አገልግሎቶች አስተናጋጆች ደንበኛን ለመሳብ በጣም አጫጭር ቀሚሶችን እንዲለብሱ ይገደዳሉ ያሉት የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ያሬድ ደገፉ፤ ደንቡ ጸድቆ ስራ ላይ ከዋለ በኋላ የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለባለሙያዎች እና ለሆቴል ባለቤቶች ተከታታይ ሥልጠናዎች መስጠቱን አስታውሰው፤ አብዛኛዎቹ የሥራ ኃላፊዎች የደንቡን ድንጋጌዎች በመረዳታቸው መሻሻሎች ታይተዋል ብለዋል፡፡
ለችግሩ እንደ መፍትሔ ከቀረቡት አማራጮች መካከል ባህላዊ ሬስቶራንቶች ውስጥ ያሉ አስተናጋጆች ሙሉ የሀበሻ ልብስ እንዲለብሱ ማድረግ እንደሆነም ተነስቷል፡፡ ደንበኞች የቤት መምረጫ መስፈርታቸው የአገልግሎት ጥራት እንዲሆንም አቶ ያሬድ አሳስበዋል፡፡
በመስተንግዶ ዘርፍ ያሉ ባለሙያዎች መብታቸውን፣ ደመወዛቸውንና የአለባበስ ነፃነታቸውን ለማስከበር በማኅበር ተደራጅተው እንዲንቀሳቀሱም ጥሪ አቅርበዋል።
#አሐዱ
14 days ago
በሀረሪ ክልል ቅርሶችን በማልማትና በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ በትኩረት ተሰርቷል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሀረሪ ክልል ቅርሶችን በማልማትና በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የተለያዩ ሥራዎች ተሰርተዋል አለ የክልሉ ባህል፣ ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ።
በቢሮው የቅርስ ዳይሬክተር አሚር ረመዳን (ኢ/ር) እንዳሉት÷ በክልሉ ባለፉት ዓመታት ቅርሶችን በማልማትና በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም በማሳደግ ረገድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።
ከተከናወኑ ተግባራት መካከልም ዘመናትን ያስቆጠሩ ታሪካዊና ጥንታዊ ቅርሶችን ለጎብኚዎች ምቹና ማራኪ ለማድረግ የተከናወኑ ውጤታማ ሥራዎችን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በክልሉ የሚገኙ ቅርሶችን በመንከባከብና በማልማት ረገድ የተከናወኑ ሥራዎችም ሐረርን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ያደረጉና የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ፍሰትና ገቢ እንዲጨምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።
ሕዝብን በማሳተፍ ከመንግሥት ምንም አይነት በጀት ሳይመደብለት ከ22 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ማልማት መቻሉንም ገልጸዋል።
6 ሺህ 114 ካሬ ሜትር የሚሸፍነውን የጀጎል ግንብ ዙሪያ መልሶ የማልማትና የአረንጓዴ ስፍራ እውን ማድረግ መቻሉን ገልጸው÷ በዚህም ከ7 ሺህ በላይ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን ጠቁመዋል።
የአካባቢ ሀብትና እውቀት በመጠቀም የተከናወኑም የቅርሱን ይዘትና ታሪካዊነት ውብ እንዲሆን ማድረግ መቻሉ አመልክተዋል።
በጀጎል መልሶ ማልማት የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ከተማዋ ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን ከማሳደግ ባለፈ ለነዋሪዎች የተመቸች እንድትሆን ያስቻለ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በቀጣይም የጀጎል ዓለም አቀፍ ቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሀረሪ ክልል ቅርሶችን በማልማትና በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የተለያዩ ሥራዎች ተሰርተዋል አለ የክልሉ ባህል፣ ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ።
በቢሮው የቅርስ ዳይሬክተር አሚር ረመዳን (ኢ/ር) እንዳሉት÷ በክልሉ ባለፉት ዓመታት ቅርሶችን በማልማትና በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም በማሳደግ ረገድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።
ከተከናወኑ ተግባራት መካከልም ዘመናትን ያስቆጠሩ ታሪካዊና ጥንታዊ ቅርሶችን ለጎብኚዎች ምቹና ማራኪ ለማድረግ የተከናወኑ ውጤታማ ሥራዎችን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በክልሉ የሚገኙ ቅርሶችን በመንከባከብና በማልማት ረገድ የተከናወኑ ሥራዎችም ሐረርን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ያደረጉና የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ፍሰትና ገቢ እንዲጨምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።
ሕዝብን በማሳተፍ ከመንግሥት ምንም አይነት በጀት ሳይመደብለት ከ22 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ማልማት መቻሉንም ገልጸዋል።
6 ሺህ 114 ካሬ ሜትር የሚሸፍነውን የጀጎል ግንብ ዙሪያ መልሶ የማልማትና የአረንጓዴ ስፍራ እውን ማድረግ መቻሉን ገልጸው÷ በዚህም ከ7 ሺህ በላይ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን ጠቁመዋል።
የአካባቢ ሀብትና እውቀት በመጠቀም የተከናወኑም የቅርሱን ይዘትና ታሪካዊነት ውብ እንዲሆን ማድረግ መቻሉ አመልክተዋል።
በጀጎል መልሶ ማልማት የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ከተማዋ ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን ከማሳደግ ባለፈ ለነዋሪዎች የተመቸች እንድትሆን ያስቻለ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በቀጣይም የጀጎል ዓለም አቀፍ ቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
Sponsored by
Surafel
15 days ago
ኢትዮጵያ፡ የዓለም ቀጣዩ የቱሪዝም መናገሻ
**************************
የቀደሙ አባቶቻችን ክብር የትውልድ ኩራት ነው፡፡ የዛሬው ትጋት ደግሞ የነገው መተኪያ የሌለው ቅርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማዕዘን፣ የሰው ዘር በኩር መገኛና የታሪክ ማኅደር መሆኗን ዓለም አውቆት፣ እኛም ደግመን ደጋግመን ተርከነው የኖርነው እውነት ነው።
ሆኖም ግን "ያለፈው ታሪክ ለዛሬ ስንቅ እንጂ መኖሪያ አይሆንም" እንደሚባለው በትናንት ታሪክ ማማ ላይ ብቻ ተቀምጦ መኖር የጉዞ መዳረሻን አያሰፋም።
ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ የታሪኳን አቧራ አራግፋ፣ የተፈጥሮ ዝናዋን በሥራ ጥበብና በፈጠራ አድሳ የቱሪዝም ተስፋዋ እንደ አዲስ ፋክቶ የሚታይበት የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ትናንት በሙዚየሞችና በጥንታውያን ገዳማት ብቻ ዓይኑን ጥሎብን የነበረው ዓለም ዛሬ በጉልበትና በእውቀት በለሙት አዳዲስ መዳረሻዎቻችን ሳቢያ ቀልቡን ወደ እኛ መልሷል።
ይህ የቱሪዝም ሽግግር ለሀገራችን የኢኮኖሚ ሞተር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል። "ጉልበት ካለ ድንጋይም ይፈጫል፤ እውቀት ካለ ምድርም ይለማል" ነውና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመና ታሪክን ብቻ ከመተረክ ወጥቶ ወደ ተንቀሳቃሽ ልማት ተሸጋግሯል። በዚሁ እውነት መሠረት፣ የገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አዲስ አበባን ከኮንክሪት ጫካነትና ከትካዜ ድባብ አውጥተው ወደ አረንጓዴ፣ ሕያውና ሳቢ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
ይህ ስኬት ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሳይወሰን ወደ ክልሎች ተሻጋግሮ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር እሳቤ በማልማት ለዓለም ዕይታ ማብቃት ተችሏል። እነዚህ ልማቶች መሬት ላይ ያለውን እምቅ ሀብት ከዘመኑ የፈጠራ ጥበብ ጋር በማቀናጀት የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
ከዚህም ባሻገር አሁን ላይ በአዲስ ጉልበት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዋነኛ ማነቆ የነበረውን የመሰረተ ልማት ምቾት እጥረት በዘላቂነት የፈታ ታላቅ ሀገራዊ ሥራ ነው።
"መንገድ ካለ አገር አለ" እንዲሉ ጽዱና ሰፋፊ መንገዶች፣ ማራኪ የእግር ጉዞ ትራኮችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታን እንዲያገኙ የሚያስችሉ የለውጥ አውታሮች ሆነዋል። ውበትና ጥራት፣ ምቾትና ደህንነት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ እያደረጓት ነው። ለዚህም በቅርቡ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ በመገኘት መደነቃቸውን በተለያዩ መንገዶች ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የቱሪዝም ልማት ለእኛ ቁሳዊ ገቢ ብቻ ሳይሆን ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ያለው የስትራቴጂ ዘርፍ ነው። በአንድ በኩል፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በሰፊው በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ካላት የዲጂታል አቅምና ቴክኖሎጂ ጋር ተዳምሮ፣ ሀገራችንን የዓለም የሥራ፣ የጉባኤና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ይገኛል።
ሲጠቃላል የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ የመንግሥት የፖሊሲ ውጤት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ዜጋና የዘርፉ ባለሙያ የጋራ ጥረትና የቅንጅት ፍሬ ነው። "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲሉ ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ቅንጣት ታህል ጥርጥር የለንም። እናም እያንዳንዱ ዜጋ ሀገሩን በመወከል ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባትና ማሳወቅ ይጠበቅበታል።
የሀገራችንን አዲስ ትንሳኤ በጋራ እናብስር።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
**************************
የቀደሙ አባቶቻችን ክብር የትውልድ ኩራት ነው፡፡ የዛሬው ትጋት ደግሞ የነገው መተኪያ የሌለው ቅርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማዕዘን፣ የሰው ዘር በኩር መገኛና የታሪክ ማኅደር መሆኗን ዓለም አውቆት፣ እኛም ደግመን ደጋግመን ተርከነው የኖርነው እውነት ነው።
ሆኖም ግን "ያለፈው ታሪክ ለዛሬ ስንቅ እንጂ መኖሪያ አይሆንም" እንደሚባለው በትናንት ታሪክ ማማ ላይ ብቻ ተቀምጦ መኖር የጉዞ መዳረሻን አያሰፋም።
ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ የታሪኳን አቧራ አራግፋ፣ የተፈጥሮ ዝናዋን በሥራ ጥበብና በፈጠራ አድሳ የቱሪዝም ተስፋዋ እንደ አዲስ ፋክቶ የሚታይበት የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ትናንት በሙዚየሞችና በጥንታውያን ገዳማት ብቻ ዓይኑን ጥሎብን የነበረው ዓለም ዛሬ በጉልበትና በእውቀት በለሙት አዳዲስ መዳረሻዎቻችን ሳቢያ ቀልቡን ወደ እኛ መልሷል።
ይህ የቱሪዝም ሽግግር ለሀገራችን የኢኮኖሚ ሞተር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል። "ጉልበት ካለ ድንጋይም ይፈጫል፤ እውቀት ካለ ምድርም ይለማል" ነውና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመና ታሪክን ብቻ ከመተረክ ወጥቶ ወደ ተንቀሳቃሽ ልማት ተሸጋግሯል። በዚሁ እውነት መሠረት፣ የገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አዲስ አበባን ከኮንክሪት ጫካነትና ከትካዜ ድባብ አውጥተው ወደ አረንጓዴ፣ ሕያውና ሳቢ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
ይህ ስኬት ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሳይወሰን ወደ ክልሎች ተሻጋግሮ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር እሳቤ በማልማት ለዓለም ዕይታ ማብቃት ተችሏል። እነዚህ ልማቶች መሬት ላይ ያለውን እምቅ ሀብት ከዘመኑ የፈጠራ ጥበብ ጋር በማቀናጀት የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
ከዚህም ባሻገር አሁን ላይ በአዲስ ጉልበት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዋነኛ ማነቆ የነበረውን የመሰረተ ልማት ምቾት እጥረት በዘላቂነት የፈታ ታላቅ ሀገራዊ ሥራ ነው።
"መንገድ ካለ አገር አለ" እንዲሉ ጽዱና ሰፋፊ መንገዶች፣ ማራኪ የእግር ጉዞ ትራኮችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታን እንዲያገኙ የሚያስችሉ የለውጥ አውታሮች ሆነዋል። ውበትና ጥራት፣ ምቾትና ደህንነት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ እያደረጓት ነው። ለዚህም በቅርቡ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ በመገኘት መደነቃቸውን በተለያዩ መንገዶች ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የቱሪዝም ልማት ለእኛ ቁሳዊ ገቢ ብቻ ሳይሆን ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ያለው የስትራቴጂ ዘርፍ ነው። በአንድ በኩል፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በሰፊው በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ካላት የዲጂታል አቅምና ቴክኖሎጂ ጋር ተዳምሮ፣ ሀገራችንን የዓለም የሥራ፣ የጉባኤና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ይገኛል።
ሲጠቃላል የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ የመንግሥት የፖሊሲ ውጤት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ዜጋና የዘርፉ ባለሙያ የጋራ ጥረትና የቅንጅት ፍሬ ነው። "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲሉ ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ቅንጣት ታህል ጥርጥር የለንም። እናም እያንዳንዱ ዜጋ ሀገሩን በመወከል ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባትና ማሳወቅ ይጠበቅበታል።
የሀገራችንን አዲስ ትንሳኤ በጋራ እናብስር።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
15 days ago
የመደመር አንቀጽ
በእጃችን ላይ ያሉ የጎብኚ መዳረሻዎችን በሚገባ አገልግሎት ላይ ማዋልና ከዚህም ሊገኝ የሚችለውን ሀገራዊ ጥቅም ሁሉ መሰብሰብ ተገቢና በቀጣይ ለምንጓዘው አቅጣጫ ትልቅ ግብዓት የሚሆን ነው። ከዚህ አንጻርም ብዙዎችን በፍጥነት ወደ ሥራ አስገብተናል፤ ትሩፋቶችንም እያጣጣምን እንገኛለን።
በእነዚህ ጥረቶች ምክንያት ሀገራችንን የሚጎበኙ የውስጥም ይሁን የውጭ ጎብኚዎች ቁጥር በጥሩ ሁኔታ እያደገ ነው። ይሁንና ዘርፉ ከፍተኛ ዕድገት እንዲያስመዘግብ ገና ብዙ መሥራት ይጠበቅብናል።
ሀገራችን ከቱሪዝም ሊገኝ የሚችለውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መለኪያዎች (Strategies) ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን።"
የመደመር መንግስት
ገፅ 272-273
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #yemedemermengist #መደመር #ቱሪዝም #ኢትዮጵያ
በእጃችን ላይ ያሉ የጎብኚ መዳረሻዎችን በሚገባ አገልግሎት ላይ ማዋልና ከዚህም ሊገኝ የሚችለውን ሀገራዊ ጥቅም ሁሉ መሰብሰብ ተገቢና በቀጣይ ለምንጓዘው አቅጣጫ ትልቅ ግብዓት የሚሆን ነው። ከዚህ አንጻርም ብዙዎችን በፍጥነት ወደ ሥራ አስገብተናል፤ ትሩፋቶችንም እያጣጣምን እንገኛለን።
በእነዚህ ጥረቶች ምክንያት ሀገራችንን የሚጎበኙ የውስጥም ይሁን የውጭ ጎብኚዎች ቁጥር በጥሩ ሁኔታ እያደገ ነው። ይሁንና ዘርፉ ከፍተኛ ዕድገት እንዲያስመዘግብ ገና ብዙ መሥራት ይጠበቅብናል።
ሀገራችን ከቱሪዝም ሊገኝ የሚችለውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መለኪያዎች (Strategies) ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን።"
የመደመር መንግስት
ገፅ 272-273
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #yemedemermengist #መደመር #ቱሪዝም #ኢትዮጵያ
16 days ago
አሉታዊ ትርክቶችን የተሻገረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የአምስቱ ምሰሶዎች ስኬት
*************************
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መንግሥት በሚያከናውናቸው መጠነ ሰፊ የልማት ሥራዎች ላይ አልፎ አልፎ "ብልጭልጭ ጉዳዮች ላይ ብቻ ያተኮረ" የሚል ትችት ይሰማል።
ይሁን እንጂ መንግሥት ተግባራዊ እያደረገው ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ብዝኃ-ዘርፍን መሠረት ያደረገ እና ሁሉንም ቁልፍ የኢኮኖሚ ሞተሮች በእኩል ደረጃ በማልማት ላይ የተመሠረተ ስትራቴጂ ነው።
ይህ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አንዱን ዘርፍ ብቻ ነጥሎ የሚያለማ ሳይሆን ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም እና ዲጂታል ኢኮኖሚን በእኩል ደረጃ የሚያንቀሳቅስ መሆኑ በተግባር እየታየ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ማሻሻያ የሀገራችንን የኢኮኖሚ ሥርዓት ከፍጆታ ወደ ምርት፣ ከአስመጪነት ወደ ላኪነት እና ከመንግሥት-መር ወደ ግል ዘርፍ መሪነት የሚያሻግር ጠንካራ መሠረት እየጣለ ይገኛል።
በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው ታሪካዊው የስንዴ አብዮት ኢትዮጵያን ወደ ላኪነት እያሸጋገረ ሲሆን፣ በ2018 በጀት ዓመት ሀገራዊ የስንዴ ምርት አቅም 305 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ ይህንኑ ያረጋግጣል።
በሌላ በኩል፣ “ኢትዮጵያ ታምርት” በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ አማካኝነት የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 58 በመቶ የተኪ ምርት ድርሻ ላይ ደርሷል።
የዚህ ማሳያ የሚሆነው በ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄው ምርት አቁመው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ዳግም ወደ ምርት መግባታቸው ነው።
ቀደም ሲል ትኩረት ሳይሰጣቸው የቆዩት የኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶች አሁን እሴት ተጨምሮባቸው የኢኮኖሚው አዲስ የጀርባ አጥንት መሆን ችለዋል።
በማዕድን ዘርፉ በተወሰዱት የሕግ እና አሠራር ማሻሻያዎች የድንጋይ ከሰል የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻ በ2010 ከነበረበት 17 በመቶ በ2017 ወደ 75 በመቶ ማደግ ችሏል። ወርቅም የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ከቡና ልቆ የተገኘው በዚሁ ማሻሻያ ነው።
በቱሪዝም ዘርፍም የ“ገበታ” ፕሮጀክቶች አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመፍጠርና የቱሪስት ገበያውን በማስፋት ለውጥ እያመጡ ይገኛሉ።
በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 9 ወራት ብቻ 1.2 ሚሊዮን የውጭ ቱሪስቶችን በመሳብ ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ፖሊሲው ውጤማነት ማረጋገጫ ነው።
በቴክኖሎጂውና በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ረገድ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂ በስኬት ተጠናቅቆ ቦታውን ለ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ አስረክቧል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ እንቅስቃሴ የፋይናንስ ተደራሽነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ፣ እስከ መጋቢት 2018 ድረስ የተከፈቱ ዲጂታል አካውንቶችን ቁጥር 257.8 ሚሊዮን ማድረስ ተችሏል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትም እንደ “መላ” ያሉ የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን የሚረዱ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓቶችን በማልማት ኢትዮጵያን በአፍሪካ መሪ አድርጓታል።
ሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) በጤናው ዘርፍም እያመጣው ያለው እመርታ በአፍሪካ ሕብረት ጭምር ማረጋገጫ የተሰጠው እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕብረቱ ሹመት ያገኙበት ነው።
በአጠቃላይ በእነዚህ አምስቱ ምሰሶዎች የተገኙ ስኬቶች ሀገራችን ከዚህ ቀደም ይገጥማት የነበረውን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ለመቅረፍ ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
የሥራ አጥነት ችግርን ከመቅረፍ አኳያ፣ እነዚህ ንቅናቄዎች በ2018 በሦስተኛው መቶ ቀናት ውስጥ ብቻ ከ96 ሺህ በላይ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር ለዜጎች ተጠቃሚነት የላቀ ሚና ተጫውተዋል።
ባለፉት 8 ዓመታት ኢኮኖሚው በአማካይ በ7.5 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ በ2018 ደግሞ የ10.2 በመቶ ድርብ አሀዝ ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል።
ይህ ሁሉ ሀገራችን በትክክለኛው የለውጥ እና የዘላቂ ብልጽግና ጎዳና ላይ መሆኗን በተጨባጭ የሚያስረግጥ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #economy #homegrowneconomicreform #ebc
*************************
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መንግሥት በሚያከናውናቸው መጠነ ሰፊ የልማት ሥራዎች ላይ አልፎ አልፎ "ብልጭልጭ ጉዳዮች ላይ ብቻ ያተኮረ" የሚል ትችት ይሰማል።
ይሁን እንጂ መንግሥት ተግባራዊ እያደረገው ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ብዝኃ-ዘርፍን መሠረት ያደረገ እና ሁሉንም ቁልፍ የኢኮኖሚ ሞተሮች በእኩል ደረጃ በማልማት ላይ የተመሠረተ ስትራቴጂ ነው።
ይህ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አንዱን ዘርፍ ብቻ ነጥሎ የሚያለማ ሳይሆን ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም እና ዲጂታል ኢኮኖሚን በእኩል ደረጃ የሚያንቀሳቅስ መሆኑ በተግባር እየታየ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ማሻሻያ የሀገራችንን የኢኮኖሚ ሥርዓት ከፍጆታ ወደ ምርት፣ ከአስመጪነት ወደ ላኪነት እና ከመንግሥት-መር ወደ ግል ዘርፍ መሪነት የሚያሻግር ጠንካራ መሠረት እየጣለ ይገኛል።
በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው ታሪካዊው የስንዴ አብዮት ኢትዮጵያን ወደ ላኪነት እያሸጋገረ ሲሆን፣ በ2018 በጀት ዓመት ሀገራዊ የስንዴ ምርት አቅም 305 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ ይህንኑ ያረጋግጣል።
በሌላ በኩል፣ “ኢትዮጵያ ታምርት” በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ አማካኝነት የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 58 በመቶ የተኪ ምርት ድርሻ ላይ ደርሷል።
የዚህ ማሳያ የሚሆነው በ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄው ምርት አቁመው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ዳግም ወደ ምርት መግባታቸው ነው።
ቀደም ሲል ትኩረት ሳይሰጣቸው የቆዩት የኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶች አሁን እሴት ተጨምሮባቸው የኢኮኖሚው አዲስ የጀርባ አጥንት መሆን ችለዋል።
በማዕድን ዘርፉ በተወሰዱት የሕግ እና አሠራር ማሻሻያዎች የድንጋይ ከሰል የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻ በ2010 ከነበረበት 17 በመቶ በ2017 ወደ 75 በመቶ ማደግ ችሏል። ወርቅም የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ከቡና ልቆ የተገኘው በዚሁ ማሻሻያ ነው።
በቱሪዝም ዘርፍም የ“ገበታ” ፕሮጀክቶች አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመፍጠርና የቱሪስት ገበያውን በማስፋት ለውጥ እያመጡ ይገኛሉ።
በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 9 ወራት ብቻ 1.2 ሚሊዮን የውጭ ቱሪስቶችን በመሳብ ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ፖሊሲው ውጤማነት ማረጋገጫ ነው።
በቴክኖሎጂውና በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ረገድ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂ በስኬት ተጠናቅቆ ቦታውን ለ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ አስረክቧል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ እንቅስቃሴ የፋይናንስ ተደራሽነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ፣ እስከ መጋቢት 2018 ድረስ የተከፈቱ ዲጂታል አካውንቶችን ቁጥር 257.8 ሚሊዮን ማድረስ ተችሏል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትም እንደ “መላ” ያሉ የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን የሚረዱ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓቶችን በማልማት ኢትዮጵያን በአፍሪካ መሪ አድርጓታል።
ሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) በጤናው ዘርፍም እያመጣው ያለው እመርታ በአፍሪካ ሕብረት ጭምር ማረጋገጫ የተሰጠው እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕብረቱ ሹመት ያገኙበት ነው።
በአጠቃላይ በእነዚህ አምስቱ ምሰሶዎች የተገኙ ስኬቶች ሀገራችን ከዚህ ቀደም ይገጥማት የነበረውን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ለመቅረፍ ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
የሥራ አጥነት ችግርን ከመቅረፍ አኳያ፣ እነዚህ ንቅናቄዎች በ2018 በሦስተኛው መቶ ቀናት ውስጥ ብቻ ከ96 ሺህ በላይ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር ለዜጎች ተጠቃሚነት የላቀ ሚና ተጫውተዋል።
ባለፉት 8 ዓመታት ኢኮኖሚው በአማካይ በ7.5 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ በ2018 ደግሞ የ10.2 በመቶ ድርብ አሀዝ ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል።
ይህ ሁሉ ሀገራችን በትክክለኛው የለውጥ እና የዘላቂ ብልጽግና ጎዳና ላይ መሆኗን በተጨባጭ የሚያስረግጥ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #economy #homegrowneconomicreform #ebc
16 days ago
አዲስ አበባ እና ባኩ የእህትማማች ከተሞች ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | አዲስ አበባ እና ባኩ የእህትማማች ከተሞች ስምምነት ተፈራርመዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ከአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ጋር የተፈረመው ስምምነት፤ በከተማ ልማት፣ በአገልግሎት ዲጂታላይዜሽን፣ በቤት ልማት፣ በቱሪዝም (ስፖርት ቱሪዝምን) ጨምሮ በሁለቱ ህዝቦች መካከል የባህልና የታሪክ ልውውጥን የሚያጠናክር መሆኑን አመልክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | አዲስ አበባ እና ባኩ የእህትማማች ከተሞች ስምምነት ተፈራርመዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ከአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ጋር የተፈረመው ስምምነት፤ በከተማ ልማት፣ በአገልግሎት ዲጂታላይዜሽን፣ በቤት ልማት፣ በቱሪዝም (ስፖርት ቱሪዝምን) ጨምሮ በሁለቱ ህዝቦች መካከል የባህልና የታሪክ ልውውጥን የሚያጠናክር መሆኑን አመልክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
16 days ago
አዲስ አበባ እና ባኩ የእህትማማች ከተሞች ስምምነት ተፈራረሙ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አዲስ አበባ እና የአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ የእህትማማች ከተሞች ስምምነት ተፈራርመዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሉት፥ ስምምነቱ የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች የባህልና የታሪክ ልውውጥ የሚያጠናክር ነው፡፡
በተጨማሪም በከተማ ልማት፣ በአገልግሎት ዲጂታላይዜሽን፣ በቤት ልማት፣ የስፖርት ቱሪዝምን ጨምሮ በቱሪዝም ልማት የሁለቱን ከተሞች ትብብር ያጠናክራል ነው ያሉት፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አዲስ አበባ እና የአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ የእህትማማች ከተሞች ስምምነት ተፈራርመዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሉት፥ ስምምነቱ የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች የባህልና የታሪክ ልውውጥ የሚያጠናክር ነው፡፡
በተጨማሪም በከተማ ልማት፣ በአገልግሎት ዲጂታላይዜሽን፣ በቤት ልማት፣ የስፖርት ቱሪዝምን ጨምሮ በቱሪዝም ልማት የሁለቱን ከተሞች ትብብር ያጠናክራል ነው ያሉት፡፡
16 days ago
አዲስ አበባ እና ባኩ የእህትማማች ከተሞች ስምምነት ተፈራረሙ
************
አዲስ አበባ እና የአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ የእህትማማች ከተሞች (Sister Cities) ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ በከተማ ልማት፣ በአገልግሎት ዲጂታላይዜሽን፣ በቤት ልማት፣ (ስፖርት ቱሪዝምን ጨምሮ) በቱሪዝም እና በሁለቱ ህዝቦች መካከል የባህልና የታሪክ ልውውጥን የሚያጠናክር መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።
#ethiopia #azerbaijan #addisababa #baku #sistercities #ebc
************
አዲስ አበባ እና የአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ የእህትማማች ከተሞች (Sister Cities) ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ በከተማ ልማት፣ በአገልግሎት ዲጂታላይዜሽን፣ በቤት ልማት፣ (ስፖርት ቱሪዝምን ጨምሮ) በቱሪዝም እና በሁለቱ ህዝቦች መካከል የባህልና የታሪክ ልውውጥን የሚያጠናክር መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።
#ethiopia #azerbaijan #addisababa #baku #sistercities #ebc