5 days ago
ተንቀሳቃሽ ቤተ-መጽሐፍት፡ ስልክ ላይ የማቀርቀርን አዚም የሰበረው ባለታክሲ
********************
በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ የሚንቀሳቀሱ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ታክሲዎች አብዛኛውን ጊዜ በሙዚቃ ጩኸት፣ በትራፊክ ጫጫታና በጉዞ ድካም አዙሪት ውስጥ በመቆየት ይታወቃሉ።
ተሳፋሪውም ታክሲ ውስጥ እንደገባ አንገቱን ደፍቶ በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ መንሸራሸር የዘመናችን የተለመደ እውነታ ሆኗል። ወጣት ሰሎሞን አማረ ግን፣ የራሱን ሜትር ታክሲ ከዚህ አሰልቺ እና የተለመደ ምህዋር በማውጣት በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ወደ የሚሽከረከር "ተንቀሳቃሽ ቤተ-መጽሐፍት" ቀይሮታል።
በንግድና በጥድፊያ በሚታወቀው የመርካቶ ሰባተኛ ሰፈር ተወልዶ ያደገው ሰሎሞን፣ ከቅድስተ ማርያም ዩኒቨርሲቲ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ከዲጂታል ሚዲያው መስፋፋት ጋር ተያይዞ ህብረተሰቡ፣ በተለይም ወጣቱ፣ ከመጽሐፍት እየራቀ መምጣቱ በእጅጉ አሳስቦታል። በዚህም የተነሳ፣ ላለፉት ጥቂት ወራት ታክሲውን የዕውቀት ማዕከል በማድረግ ልዩ ልዩ የአማርኛና የእንግሊዝኛ መጻሕፍትን ለተሳፋሪዎቹ እንደ አዲስ አማራጭ ማቅረብ ጀምሯል።
ሁሉም ሰው ስልኩ ላይ ባቀረቀረበት በዚህ ዘመን፣ ሰሎሞን የታክሲው ውስጥ መደርደሪያዎች ላይ መጽሐፍትን በማስቀመጥ የሰዎችን ትኩረት ወደ ንባብ ለመመለስ የራሱን የትግል ስልት ነድፏል።
ሰለሞን ወደ ታክሲው ለሚገቡ መንገደኞች የሚያቀርበው ሞቅ ያለ ፈገግታና ሰላምታን ብቻ አይደለም፤ በስርዓት የተደረደሩ የዕውቀት ማህደሮችንም ጭምር እንጂ። የትራፊክ መጨናነቅን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም፣ ተሳፋሪዎች በጉዞ ወቅት መጽሐፍትን እንዲያነቡ ይጋብዛል።
የጀመሩት መጽሐፍ ልባቸውን ከሰረቀው ደግሞ፣ እዚያው ታክሲ ውስጥ ገዝተውት መንገዳቸውን ያለመሰልቸት በዕውቀት ታጅበው ያጠናቅቃሉ። ይህ አሰራር ከማህበራዊ ሚዲያ ጩኸት ለተወሰኑ ደቂቃዎችም ቢሆን አእምሮን የሚያሳርፉበት ልዩ የጉዞ ተሞክሮ ሆኗል።
የሰሎሞን አካሄድ የንባብ ባህልን ከማበረታታት ባለፈ፣ የገበያ ጥናትን (Marketing Management) ከተግባር ጋር ያዋሃደ አዲስ የስራ ፈጠራ ነው።
ጊዜን ወደ እሴት መቀየር፡ የታክሲ ተሳፋሪን የትራፊክ ውስጥ የባከነ ጊዜ ወደ ምርታማ የገበያ ሰዓት ቀይሮታል።
ድርብ ገቢ፡ ከትራንስፖርት አገልግሎቱ ባሻገር፣ መጽሐፍትን በመሸጥ የራሱን የገቢ ምንጭ አሳድጓል።
ማህበራዊ ካፒታል፡ "ተሳፋሪዎች የሚሰጡት አዎንታዊ ምላሽና አስደናቂ ስሜት ለስራዬ ትልቅ መነቃቃት ይፈጥርልኛል" የሚለው ሰሎሞን፣ በየቀኑ ከሚያገኛቸው አዳዲስ ሰዎች ጋር የሚያደርገው ገንቢ ውይይት ከገንዘብ በላይ የሆነ ትልቅ የህይወት ስንቅ እንደሆነለት ይናገራል።
የሰሎሞን አስገራሚው ጎን የዲጂታል ዓለሙን ሙሉ በሙሉ መሸሹ ሳይሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለራሱ ዓላማ ማዋሉ ነው። "Sol Books" በሚል ስያሜ በቲክቶክና በሌሎች ማኅበራዊ ገጾች መጻሕፍትን በማስተዋወቅ፣ ዲጂታል ትውልዱን በዲጂታል መድረክ እየቀሰቀሰ ይገኛል።
የዚህ አብዮተኛ ወጣት መልዕክት አጭር እና ግልጽ ነው፦ የተለመደውን አሰራር በመስበር ሌሎች የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችም ይህን መሰል በጎ ተግባር ቢያራምዱ፣ ታክሲዎቻችንን ከትራፊክ ጫና ማምለጫነት አልፈው የዕውቀት፣ የሰላምና የፈጠራ ማዕከል ማድረግ ይቻላል።
በሊያ ተስፋዬ
Ethiopian Broadcasting Corporation FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ #መጽሀፍ #ንባብ
********************
በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ የሚንቀሳቀሱ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ታክሲዎች አብዛኛውን ጊዜ በሙዚቃ ጩኸት፣ በትራፊክ ጫጫታና በጉዞ ድካም አዙሪት ውስጥ በመቆየት ይታወቃሉ።
ተሳፋሪውም ታክሲ ውስጥ እንደገባ አንገቱን ደፍቶ በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ መንሸራሸር የዘመናችን የተለመደ እውነታ ሆኗል። ወጣት ሰሎሞን አማረ ግን፣ የራሱን ሜትር ታክሲ ከዚህ አሰልቺ እና የተለመደ ምህዋር በማውጣት በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ወደ የሚሽከረከር "ተንቀሳቃሽ ቤተ-መጽሐፍት" ቀይሮታል።
በንግድና በጥድፊያ በሚታወቀው የመርካቶ ሰባተኛ ሰፈር ተወልዶ ያደገው ሰሎሞን፣ ከቅድስተ ማርያም ዩኒቨርሲቲ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ከዲጂታል ሚዲያው መስፋፋት ጋር ተያይዞ ህብረተሰቡ፣ በተለይም ወጣቱ፣ ከመጽሐፍት እየራቀ መምጣቱ በእጅጉ አሳስቦታል። በዚህም የተነሳ፣ ላለፉት ጥቂት ወራት ታክሲውን የዕውቀት ማዕከል በማድረግ ልዩ ልዩ የአማርኛና የእንግሊዝኛ መጻሕፍትን ለተሳፋሪዎቹ እንደ አዲስ አማራጭ ማቅረብ ጀምሯል።
ሁሉም ሰው ስልኩ ላይ ባቀረቀረበት በዚህ ዘመን፣ ሰሎሞን የታክሲው ውስጥ መደርደሪያዎች ላይ መጽሐፍትን በማስቀመጥ የሰዎችን ትኩረት ወደ ንባብ ለመመለስ የራሱን የትግል ስልት ነድፏል።
ሰለሞን ወደ ታክሲው ለሚገቡ መንገደኞች የሚያቀርበው ሞቅ ያለ ፈገግታና ሰላምታን ብቻ አይደለም፤ በስርዓት የተደረደሩ የዕውቀት ማህደሮችንም ጭምር እንጂ። የትራፊክ መጨናነቅን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም፣ ተሳፋሪዎች በጉዞ ወቅት መጽሐፍትን እንዲያነቡ ይጋብዛል።
የጀመሩት መጽሐፍ ልባቸውን ከሰረቀው ደግሞ፣ እዚያው ታክሲ ውስጥ ገዝተውት መንገዳቸውን ያለመሰልቸት በዕውቀት ታጅበው ያጠናቅቃሉ። ይህ አሰራር ከማህበራዊ ሚዲያ ጩኸት ለተወሰኑ ደቂቃዎችም ቢሆን አእምሮን የሚያሳርፉበት ልዩ የጉዞ ተሞክሮ ሆኗል።
የሰሎሞን አካሄድ የንባብ ባህልን ከማበረታታት ባለፈ፣ የገበያ ጥናትን (Marketing Management) ከተግባር ጋር ያዋሃደ አዲስ የስራ ፈጠራ ነው።
ጊዜን ወደ እሴት መቀየር፡ የታክሲ ተሳፋሪን የትራፊክ ውስጥ የባከነ ጊዜ ወደ ምርታማ የገበያ ሰዓት ቀይሮታል።
ድርብ ገቢ፡ ከትራንስፖርት አገልግሎቱ ባሻገር፣ መጽሐፍትን በመሸጥ የራሱን የገቢ ምንጭ አሳድጓል።
ማህበራዊ ካፒታል፡ "ተሳፋሪዎች የሚሰጡት አዎንታዊ ምላሽና አስደናቂ ስሜት ለስራዬ ትልቅ መነቃቃት ይፈጥርልኛል" የሚለው ሰሎሞን፣ በየቀኑ ከሚያገኛቸው አዳዲስ ሰዎች ጋር የሚያደርገው ገንቢ ውይይት ከገንዘብ በላይ የሆነ ትልቅ የህይወት ስንቅ እንደሆነለት ይናገራል።
የሰሎሞን አስገራሚው ጎን የዲጂታል ዓለሙን ሙሉ በሙሉ መሸሹ ሳይሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለራሱ ዓላማ ማዋሉ ነው። "Sol Books" በሚል ስያሜ በቲክቶክና በሌሎች ማኅበራዊ ገጾች መጻሕፍትን በማስተዋወቅ፣ ዲጂታል ትውልዱን በዲጂታል መድረክ እየቀሰቀሰ ይገኛል።
የዚህ አብዮተኛ ወጣት መልዕክት አጭር እና ግልጽ ነው፦ የተለመደውን አሰራር በመስበር ሌሎች የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችም ይህን መሰል በጎ ተግባር ቢያራምዱ፣ ታክሲዎቻችንን ከትራፊክ ጫና ማምለጫነት አልፈው የዕውቀት፣ የሰላምና የፈጠራ ማዕከል ማድረግ ይቻላል።
በሊያ ተስፋዬ
Ethiopian Broadcasting Corporation FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ #መጽሀፍ #ንባብ
9 days ago
በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ የክህሎትና የመዋቅር ችግሮችን ለመቅረፍ አዲስ የጋራ ስምምነት ተደረገ!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ መዋቅራዊና የክህሎት ችግሮችን ለመቅረፍ የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ በጋራ ለመስራት በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ።
በአዲሱ አስተዳደራዊ መዋቅር ስር የሚገኙትን ብሔራዊ ቴአትር፣ ሀገርፍቅር ቴአትር፣ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም (ባህል አዳራሽ)፣ ራስ ቴአትር እና የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትርን የሚያስተዳድረው ተቋሙ፤ ከግል ዘርፍ አጋሮች ጋር አብሮ ለመሥራት ባቀደው መሠረት ይፋዊ ስምምነቱን አድርጓል።
በስምምነቱ መሠረት የአስተዳደሩን የዘመናት የታሪክና የልምድ ክምችት ከአካዳሚው ዘመናዊና ፈጠራ የታከለበት የአሰልጠና ዘዴ ጋር በማዋሃድ በቴአትር፣ በሙዚቃ፣ በፊልምና ተዛማጅ የኪነ-ጥበብ ዘርፎች ሰፊ ስልጠናዎች በጋራ እንደሚሰጡ ተገልጿል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክና ወግ የሚያንፀባርቁ ጥበባዊ ሁነቶችንና ትላልቅ ፕሮዳክሽኖችን በጋራ በማዘጋጀት ለሕዝብ ለማቅረብ፣ እንዲሁም ከግጥም ምሽቶች እስከ ታላላቅ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫሎች ድረስ ያሉ መድረኮችን ለማስፋፋት መታቀዱም ነዉ የተገለፀዉ።
የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ ዋና መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሌንጮ ፍቅሩ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደገለጹት፤ አካዳሚው ከተመሠረተበት ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በርካታ ወጣትና ህጻናት
ተማሪዎችን አብቅቶ ያስመረቀ ሲሆን፣ በተለይም በልጆች አክቲንግ ዘርፍ አበራች አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ሌንጮ አክለው እንደገለጹት፣ አካዳሚው እስካሁን በነበረው ጉዞ የቦታ፣ የሎኬሽን እና የትወና ቁሳቁሶች (Props) እጥረት ዋና ዋና ማነቆዎች እንደነበሩበት አስታውሰዋል።
ሆኖም ከአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ጋር የተደረገው ይህ ይፋዊ ስምምነት እነዚህን የሎጅስቲክስና የቦታ ችግሮች በዘላቂነት በመቅረፍ፣ የሰለጠኑ አዳዲስ ከዋክብትን ወደ ታሪካዊ የቴአትር መድረኮች ለማውጣት ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ መዋቅራዊና የክህሎት ችግሮችን ለመቅረፍ የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ በጋራ ለመስራት በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ።
በአዲሱ አስተዳደራዊ መዋቅር ስር የሚገኙትን ብሔራዊ ቴአትር፣ ሀገርፍቅር ቴአትር፣ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም (ባህል አዳራሽ)፣ ራስ ቴአትር እና የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትርን የሚያስተዳድረው ተቋሙ፤ ከግል ዘርፍ አጋሮች ጋር አብሮ ለመሥራት ባቀደው መሠረት ይፋዊ ስምምነቱን አድርጓል።
በስምምነቱ መሠረት የአስተዳደሩን የዘመናት የታሪክና የልምድ ክምችት ከአካዳሚው ዘመናዊና ፈጠራ የታከለበት የአሰልጠና ዘዴ ጋር በማዋሃድ በቴአትር፣ በሙዚቃ፣ በፊልምና ተዛማጅ የኪነ-ጥበብ ዘርፎች ሰፊ ስልጠናዎች በጋራ እንደሚሰጡ ተገልጿል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክና ወግ የሚያንፀባርቁ ጥበባዊ ሁነቶችንና ትላልቅ ፕሮዳክሽኖችን በጋራ በማዘጋጀት ለሕዝብ ለማቅረብ፣ እንዲሁም ከግጥም ምሽቶች እስከ ታላላቅ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫሎች ድረስ ያሉ መድረኮችን ለማስፋፋት መታቀዱም ነዉ የተገለፀዉ።
የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ ዋና መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሌንጮ ፍቅሩ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደገለጹት፤ አካዳሚው ከተመሠረተበት ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በርካታ ወጣትና ህጻናት
ተማሪዎችን አብቅቶ ያስመረቀ ሲሆን፣ በተለይም በልጆች አክቲንግ ዘርፍ አበራች አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ሌንጮ አክለው እንደገለጹት፣ አካዳሚው እስካሁን በነበረው ጉዞ የቦታ፣ የሎኬሽን እና የትወና ቁሳቁሶች (Props) እጥረት ዋና ዋና ማነቆዎች እንደነበሩበት አስታውሰዋል።
ሆኖም ከአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ጋር የተደረገው ይህ ይፋዊ ስምምነት እነዚህን የሎጅስቲክስና የቦታ ችግሮች በዘላቂነት በመቅረፍ፣ የሰለጠኑ አዳዲስ ከዋክብትን ወደ ታሪካዊ የቴአትር መድረኮች ለማውጣት ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
9 days ago
የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነት አለም አቀፍ አልበም በይፋ ተመረቀ
#ethiopia | የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነት የባህላዊ ሙዚቃ አልበም ትናንት በጎንደር ከተማ በተካሄደ ደማቅ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት በይፋ ተመረቀ።
በሙዚቃዊ፣ በሰላም ኢትዮጵያ እና በጎንደር ከተማ አስተዳደር ባህልና ኪነጥበብ ቢሮ ትብብር የተዘጋጀው አልበም፣ የጎንደርን እና የአማራ ክልልን የባህል ሙዚቃ ለአለም አቀፍ አድማጮች ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የመንግስት ተወካዮች፣ አርቲስቶች፣ የባህል ባለሙያዎች፣ አጋር ተቋማት፣ የሚዲያ ተወካዮችና በርካታ የጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል። የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነትም የቀጥታ የሙዚቃና የውዝዋዜ ትርኢት በማቅረብ ታዳሚዎችን አስደስቷል።
በአልበሙ ውስጥ የቡድኑ ድምፃውያን ሕይወት እያሱ፣ እህተነሽ ፋንታ፣ ሰሎሞን ጥጋቤን ጨምሮ ሌሎች የቡድኑ አባላት ተሳትፈዋል።
የሙዚቃ ዳይሬክተርነቱንም ሙዚቀኛ ምሳሌ ለገሰ መርተዋል። አልበሙ በባህላዊ የኢትዮጵያ መሳሪያዎች የተቀናበረ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ተቀርጾ የድምፅ ማስተካከያውና ማስተሪንጉ በጣሊያን በሚገኘው ማክስሳውንድ ቫይብ ስቱዲዮ ተከናውኗል።
በዝግጅቱ ላይ የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነትን ከ50 ዓመታት በላይ የሚያስቆጥር ታሪክ የሚያሳይ የፎቶግራፍ አውደ ርዕይም ለእንግዶች ቀርቧል። አውደ ርዕዩ የቡድኑን እድገት፣ ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ትዕይንት ጥበባት ያበረከተውን አስተዋፅኦ እንዲሁም ያፈራቸውን ታዋቂ አርቲስቶች የሚያስታውሱ ታሪካዊ ፎቶግራፎችና ሰነዶችን አካቷል።
በዝግጅቱ ላይ የሙዚቃዊ ተወካይ ሲሳይ መንግስቴ፣ አልበሙ ከመደበኛ የሙዚቃ ስራ በላይ የኢትዮጵያን የባህል ሀብት ለማስጠበቅና ለአለም አቀፍ ተደራሽነት ለማብቃት የተደረገ ኢንቨስትመንት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ስራ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ በዓለም አቀፍ የሙዚቃ ገበያ ተወዳዳሪ ለማድረግ እና ለአዲስ ትውልድ ለማስተላለፍ ጠቃሚ እርምጃ መሆኑን ጠቁመዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #gondarfasilidesculture #የጎንደርፋሲለደስባህልኪነት #ethiopianmusic #ethiopianculture #gondar #traditionalmusic #ethiopia
#ethiopia | የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነት የባህላዊ ሙዚቃ አልበም ትናንት በጎንደር ከተማ በተካሄደ ደማቅ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት በይፋ ተመረቀ።
በሙዚቃዊ፣ በሰላም ኢትዮጵያ እና በጎንደር ከተማ አስተዳደር ባህልና ኪነጥበብ ቢሮ ትብብር የተዘጋጀው አልበም፣ የጎንደርን እና የአማራ ክልልን የባህል ሙዚቃ ለአለም አቀፍ አድማጮች ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የመንግስት ተወካዮች፣ አርቲስቶች፣ የባህል ባለሙያዎች፣ አጋር ተቋማት፣ የሚዲያ ተወካዮችና በርካታ የጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል። የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነትም የቀጥታ የሙዚቃና የውዝዋዜ ትርኢት በማቅረብ ታዳሚዎችን አስደስቷል።
በአልበሙ ውስጥ የቡድኑ ድምፃውያን ሕይወት እያሱ፣ እህተነሽ ፋንታ፣ ሰሎሞን ጥጋቤን ጨምሮ ሌሎች የቡድኑ አባላት ተሳትፈዋል።
የሙዚቃ ዳይሬክተርነቱንም ሙዚቀኛ ምሳሌ ለገሰ መርተዋል። አልበሙ በባህላዊ የኢትዮጵያ መሳሪያዎች የተቀናበረ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ተቀርጾ የድምፅ ማስተካከያውና ማስተሪንጉ በጣሊያን በሚገኘው ማክስሳውንድ ቫይብ ስቱዲዮ ተከናውኗል።
በዝግጅቱ ላይ የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነትን ከ50 ዓመታት በላይ የሚያስቆጥር ታሪክ የሚያሳይ የፎቶግራፍ አውደ ርዕይም ለእንግዶች ቀርቧል። አውደ ርዕዩ የቡድኑን እድገት፣ ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ትዕይንት ጥበባት ያበረከተውን አስተዋፅኦ እንዲሁም ያፈራቸውን ታዋቂ አርቲስቶች የሚያስታውሱ ታሪካዊ ፎቶግራፎችና ሰነዶችን አካቷል።
በዝግጅቱ ላይ የሙዚቃዊ ተወካይ ሲሳይ መንግስቴ፣ አልበሙ ከመደበኛ የሙዚቃ ስራ በላይ የኢትዮጵያን የባህል ሀብት ለማስጠበቅና ለአለም አቀፍ ተደራሽነት ለማብቃት የተደረገ ኢንቨስትመንት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ስራ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ በዓለም አቀፍ የሙዚቃ ገበያ ተወዳዳሪ ለማድረግ እና ለአዲስ ትውልድ ለማስተላለፍ ጠቃሚ እርምጃ መሆኑን ጠቁመዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #gondarfasilidesculture #የጎንደርፋሲለደስባህልኪነት #ethiopianmusic #ethiopianculture #gondar #traditionalmusic #ethiopia
10 days ago
ይድረስ ለአራቱ ድምፃውያን
– “ማንም የላት” ከተሰኘው የኅብረት ዜማ ጋር በተያያዘ
ከተመስገን ኡካሬ (የሐጌ ልጅ)
#ethiopia | "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ሙዚቃ ብቻ አይደለም፤ የህሊና ጥሪ፣ የማህበራዊ ኃላፊነት ማንቂያ እና የሰብአዊነት መልዕክት ነው። ይህ ስራ የአካል ጉዳተኞችንና የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያላቸውን ወገኖች በርኅራኄ ከመመልከት ይልቅ፣ እንደ ሙሉ መብት ባለቤቶች እንድናያቸው ያስጠይቃል።
ሙዚቃው የሚያነሳው ዋና ጥያቄ አካል ጉዳተኝነት ሳይሆን፣ እኛ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እጥረት ነው። ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ስራ፣ የህዝብ አገልግሎቶች እና ማህበራዊ ተሳትፎ ለሁሉም እኩል ተደራሽ ናቸው ወይ? የሚለውን ጥያቄ በጥልቅ ያቀርባል።
የኅብረት ዜማዎች ሁልጊዜም የዘመናቸውን ማህበራዊ ጉዳይ ያንጸባርቃሉ። "ማለባበስ ይቅር"፣ "ስደት"፣ "ሰላም ለሀገራችን" እና ሌሎችም እንደ ነበሩት ሁሉ፣ "ማንም የላት" ደግሞ የዚህ ዘመን የህሊና ጥሪ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ ስራ በስሜት ብቻ የተሞላ አይደለም፤ መፍትሄ የሚፈልግ ጥያቄ ያቀርባል። "ማንም የላት" የሚለውን አባባል "እኛም አለን" በሚል ተግባራዊ መልስ እንድንተካው ይጋብዘናል።
በዚህ ዜማ ላይ የተሳተፉት ድምፃዊ ማስተዋል እያዩ፣ ድምፃዊት ሀና ግርማ፣ ድምፃዊ አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) እና ድምፃዊት ሄዋን ገብረወልድ እያንዳንዳቸው መልዕክቱን በሚመጥን ስሜት አቅርበዋል።
ግጥሙን ናትናኤል ግርማቸው፣ ዜማውን አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ ቅንብሩን ደግሞ ታምሩ አማረ (ቶሚ) በሙያዊ ብቃት አስውበውታል። የግጥሙ፣ የዜማው፣ የድምፅ አቀራረቡና የቅንብሩ መዋሃድ ሙዚቃውን ከመዝናኛነት በላይ ወደ ማህበራዊ ንቅናቄ አሳድጎታል።
ይህ ዜማ የሚያስታውሰን አንድ እውነት አለ፤ ሰብአዊነት በቃላት ሳይሆን በተግባር ይለካል። አካል ጉዳተኞች ርኅራኄ አይፈልጉም፤ እኩል ዕድል፣ ተደራሽነትና ክብር ይፈልጋሉ።
ይድረስ ለአራቱ ድምፃውያን፤ ለህዝብ የሚያስብ፣ ህሊናን የሚያነቃ እና ማህበረሰብን ወደ በጎ ለውጥ የሚጋብዝ ስራ ስላቀረባችሁ ምስጋና ይገባችኋል። ይህ ዜማ በሙዚቃ ታሪክ ውስጥ እንደ ዜማ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ማህበራዊ ጥሪ የሚታወስ ስራ ይሆናል።
አቶ ሳሚ ተድላ ( የተድላ አምቡላንስ መሥራችና ባለቤት ) "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ፕሮውዲሰር ምስጋና ይገባቸዋል።
በተለይም ጥበብንና በጎ አድራጎትን አጣምሮ በመያዝ፣ አቅም የሌላቸውንና ረዳት ያጡ ወገኖችን ድምፅ ለማሰማት ያደረጉት ጥረትና ያወጡት ወጪ የሚወደስ ነው።
በተጨማሪም በተድላ አምቡላንስ በኩል የሚያደርጉት ድገስ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴ፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ ትልቅ አክብሮትና ምስጋና የሚያሰጣቸው ያደርጋቸዋል። እንደዚህ ያሉ በጎ አድራጊ ባለሃብቶችና ድርጅቶች ለሌላውም አርአያ የሚሆኑ ናቸው።
– “ማንም የላት” ከተሰኘው የኅብረት ዜማ ጋር በተያያዘ
ከተመስገን ኡካሬ (የሐጌ ልጅ)
#ethiopia | "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ሙዚቃ ብቻ አይደለም፤ የህሊና ጥሪ፣ የማህበራዊ ኃላፊነት ማንቂያ እና የሰብአዊነት መልዕክት ነው። ይህ ስራ የአካል ጉዳተኞችንና የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያላቸውን ወገኖች በርኅራኄ ከመመልከት ይልቅ፣ እንደ ሙሉ መብት ባለቤቶች እንድናያቸው ያስጠይቃል።
ሙዚቃው የሚያነሳው ዋና ጥያቄ አካል ጉዳተኝነት ሳይሆን፣ እኛ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እጥረት ነው። ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ስራ፣ የህዝብ አገልግሎቶች እና ማህበራዊ ተሳትፎ ለሁሉም እኩል ተደራሽ ናቸው ወይ? የሚለውን ጥያቄ በጥልቅ ያቀርባል።
የኅብረት ዜማዎች ሁልጊዜም የዘመናቸውን ማህበራዊ ጉዳይ ያንጸባርቃሉ። "ማለባበስ ይቅር"፣ "ስደት"፣ "ሰላም ለሀገራችን" እና ሌሎችም እንደ ነበሩት ሁሉ፣ "ማንም የላት" ደግሞ የዚህ ዘመን የህሊና ጥሪ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ ስራ በስሜት ብቻ የተሞላ አይደለም፤ መፍትሄ የሚፈልግ ጥያቄ ያቀርባል። "ማንም የላት" የሚለውን አባባል "እኛም አለን" በሚል ተግባራዊ መልስ እንድንተካው ይጋብዘናል።
በዚህ ዜማ ላይ የተሳተፉት ድምፃዊ ማስተዋል እያዩ፣ ድምፃዊት ሀና ግርማ፣ ድምፃዊ አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) እና ድምፃዊት ሄዋን ገብረወልድ እያንዳንዳቸው መልዕክቱን በሚመጥን ስሜት አቅርበዋል።
ግጥሙን ናትናኤል ግርማቸው፣ ዜማውን አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ ቅንብሩን ደግሞ ታምሩ አማረ (ቶሚ) በሙያዊ ብቃት አስውበውታል። የግጥሙ፣ የዜማው፣ የድምፅ አቀራረቡና የቅንብሩ መዋሃድ ሙዚቃውን ከመዝናኛነት በላይ ወደ ማህበራዊ ንቅናቄ አሳድጎታል።
ይህ ዜማ የሚያስታውሰን አንድ እውነት አለ፤ ሰብአዊነት በቃላት ሳይሆን በተግባር ይለካል። አካል ጉዳተኞች ርኅራኄ አይፈልጉም፤ እኩል ዕድል፣ ተደራሽነትና ክብር ይፈልጋሉ።
ይድረስ ለአራቱ ድምፃውያን፤ ለህዝብ የሚያስብ፣ ህሊናን የሚያነቃ እና ማህበረሰብን ወደ በጎ ለውጥ የሚጋብዝ ስራ ስላቀረባችሁ ምስጋና ይገባችኋል። ይህ ዜማ በሙዚቃ ታሪክ ውስጥ እንደ ዜማ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ማህበራዊ ጥሪ የሚታወስ ስራ ይሆናል።
አቶ ሳሚ ተድላ ( የተድላ አምቡላንስ መሥራችና ባለቤት ) "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ፕሮውዲሰር ምስጋና ይገባቸዋል።
በተለይም ጥበብንና በጎ አድራጎትን አጣምሮ በመያዝ፣ አቅም የሌላቸውንና ረዳት ያጡ ወገኖችን ድምፅ ለማሰማት ያደረጉት ጥረትና ያወጡት ወጪ የሚወደስ ነው።
በተጨማሪም በተድላ አምቡላንስ በኩል የሚያደርጉት ድገስ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴ፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ ትልቅ አክብሮትና ምስጋና የሚያሰጣቸው ያደርጋቸዋል። እንደዚህ ያሉ በጎ አድራጊ ባለሃብቶችና ድርጅቶች ለሌላውም አርአያ የሚሆኑ ናቸው።
15 days ago
ለአፍሪካውያን ታዳጊዎች የህልም ምሳሌ የሆኑት ጥቋቁር ወርቆች መድመቃቸውን ቀጥለዋል።
*ከጎዳና ህይወት እስከ አለም አቀፍ መድረክ
*አስከፊ ከሆነ የጎዳና ህይወት ተነስተው ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር እስከ መጣመር የደረሱት ጥቋቁር የአፍሪካ ወርቆች
#ethiopia | በምስራቅ አፍሪካ የጥበብ ዓለም ውስጥ የብዙዎችን ቀልብ የሳቡት የኡጋንዳው የዳንስ ቡድን ጌቶ ኪድስ የችሎታ እና የጽናት ተምሳሌት በመሆን ዓለምን እያስደነቁ ይገኛሉ።
ቡድኑ የተመሰረተው በኡጋንዳዋ ካምፓላ ከተማ በሚገኘው የካታዌ (Katwe) ሰፈር ነው።
በዳውዳ ካቫማ አማካኝነት የተደራጁት እነዚህ ታዳጊዎች መነሻቸው ከምንም ነበር ማለት ይቻላል።
እነዚህ ህጻናት በተስፋ መቁረጥ ውስጥ የነበሩ ከድህነት ጋር በጎዳና ህይወት ላይ የነበሩ ናቸው።
ይህ ብልሁ ዳውዳ ካቫማ የተባለው ወጣት ታዳጊዎችን በመሰብሰብ በሙዚቃ እና በዳንስ ተስፋ እንዲሰንቁ ብሎም ስማቸውን አለም እንዲያውቀው አድርጓል።
የዳውዳ ካቫማ አላማ የነበረው መዝናኛን ብቻ ሳይሆን ችሎታን በመጠቀም የጎዳና ላይ ህይወት በአማራጭ መንገድ ሊቀየር እንደሚችል ለዓለም ማሳየት ነበር።
ቡድኑ መጀመሪያ ላይ ትኩረት ያደረገው ጎዳና ላይ በመጨፈር የነበረ ሲሆን የነበራቸው ጉልበት እና ተፈጥሯዊ የዳንስ ችሎታ በየማህበራዊ ሚዲያው በወጡ አጫጭር ቪዲዮዎች የዓለምን ትኩረት በቶሎ እንዲስቡ አድርጓቸዋል።
ጌቶ ኪድስ ከኡጋንዳ አልፈው ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙት በተለያዩ የዓለም የሙዚቃ ቪዲዮዎች ላይ በመሳተፍ ነው።
በተለይም በፈረንጆቹ 2017 ላይ ከፈረንሳዊው አርቲስት ፍሬንች ሞንታና (French Montana) ጋር በሰሩት "Unforgettable" የሙዚቃ ቪዲዮ አማካኝነት ስማቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው ተሰማ።
ጌቶ ኪድስ በዓለም አቀፍ ደረጃ በታላላቅ የሙዚቃ ሽልማቶች ላይ ተጋባዥ ሆነዋል።
በዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ በመቅረብ የኡጋንዳን እና የአፍሪካን ስም በከፍተኛ ደረጃ እያስጠሩም ይገኛሉ።
በቅርቡ በተጠናቀቀው የ2026 የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር በመጣመር ባሳዩት ብቃት የስኬት ጉዟቸውን ከፍታ ላይ አድርሰውታል።
ዛሬ "ጌቶ ኪድስ" የዳንስ ቡድን ብቻ ሳይሆን የበርካታ አፍሪካውያን ታዳጊዎች የህልም ምሳሌ ሆነዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ugandaghettokids #dancingwithshakira #worldcupfinal
*ከጎዳና ህይወት እስከ አለም አቀፍ መድረክ
*አስከፊ ከሆነ የጎዳና ህይወት ተነስተው ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር እስከ መጣመር የደረሱት ጥቋቁር የአፍሪካ ወርቆች
#ethiopia | በምስራቅ አፍሪካ የጥበብ ዓለም ውስጥ የብዙዎችን ቀልብ የሳቡት የኡጋንዳው የዳንስ ቡድን ጌቶ ኪድስ የችሎታ እና የጽናት ተምሳሌት በመሆን ዓለምን እያስደነቁ ይገኛሉ።
ቡድኑ የተመሰረተው በኡጋንዳዋ ካምፓላ ከተማ በሚገኘው የካታዌ (Katwe) ሰፈር ነው።
በዳውዳ ካቫማ አማካኝነት የተደራጁት እነዚህ ታዳጊዎች መነሻቸው ከምንም ነበር ማለት ይቻላል።
እነዚህ ህጻናት በተስፋ መቁረጥ ውስጥ የነበሩ ከድህነት ጋር በጎዳና ህይወት ላይ የነበሩ ናቸው።
ይህ ብልሁ ዳውዳ ካቫማ የተባለው ወጣት ታዳጊዎችን በመሰብሰብ በሙዚቃ እና በዳንስ ተስፋ እንዲሰንቁ ብሎም ስማቸውን አለም እንዲያውቀው አድርጓል።
የዳውዳ ካቫማ አላማ የነበረው መዝናኛን ብቻ ሳይሆን ችሎታን በመጠቀም የጎዳና ላይ ህይወት በአማራጭ መንገድ ሊቀየር እንደሚችል ለዓለም ማሳየት ነበር።
ቡድኑ መጀመሪያ ላይ ትኩረት ያደረገው ጎዳና ላይ በመጨፈር የነበረ ሲሆን የነበራቸው ጉልበት እና ተፈጥሯዊ የዳንስ ችሎታ በየማህበራዊ ሚዲያው በወጡ አጫጭር ቪዲዮዎች የዓለምን ትኩረት በቶሎ እንዲስቡ አድርጓቸዋል።
ጌቶ ኪድስ ከኡጋንዳ አልፈው ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙት በተለያዩ የዓለም የሙዚቃ ቪዲዮዎች ላይ በመሳተፍ ነው።
በተለይም በፈረንጆቹ 2017 ላይ ከፈረንሳዊው አርቲስት ፍሬንች ሞንታና (French Montana) ጋር በሰሩት "Unforgettable" የሙዚቃ ቪዲዮ አማካኝነት ስማቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው ተሰማ።
ጌቶ ኪድስ በዓለም አቀፍ ደረጃ በታላላቅ የሙዚቃ ሽልማቶች ላይ ተጋባዥ ሆነዋል።
በዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ በመቅረብ የኡጋንዳን እና የአፍሪካን ስም በከፍተኛ ደረጃ እያስጠሩም ይገኛሉ።
በቅርቡ በተጠናቀቀው የ2026 የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር በመጣመር ባሳዩት ብቃት የስኬት ጉዟቸውን ከፍታ ላይ አድርሰውታል።
ዛሬ "ጌቶ ኪድስ" የዳንስ ቡድን ብቻ ሳይሆን የበርካታ አፍሪካውያን ታዳጊዎች የህልም ምሳሌ ሆነዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ugandaghettokids #dancingwithshakira #worldcupfinal
19 days ago
የአቤን አንጀት የምታርሰው ሙዚቃ
#ethiopia | ሁለገቡ የጥበብ ሰው አበበ ብርሃኔ ግጥምና ዜማቸው በሌሎች ከተሰሩ የሙዚቃ ስራዎች መካከል የሚወደው አንድ ሙዚቃ አለ።
አቤ እጅግ ከሚወዳቸው የሙዚቃ ስራዎች መካከል የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" የተሰኘው ሙዚቃ ሙዚቃ እንደሆነ በአንድ ወቅት ከጋዜጠኛ ሔኖክ ወ/ገብርኤል ጋር በሙዚቀኞች ብፌ ፕሮግራም ላይ በነበረው ቆይታ ተናግሮ ነበር።
ይህ ሙዚቃ ለአቤ ሁሉ ነገሩ ነው።
የጥበብ ሰው አበበ ብርሃኔ የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" ሲያዳምጥ ልክ በውስጡ የተደበቀ በቃላት ሊገለጽ የማይችል ጥልቅ ስሜት የሚቀሰቀስበት ይመስላል።
አበበ ብርሃኔ በሙዚቃ ዓለም ውስጥ ከ800 በላይ የግጥምና የዜማ ስራዎች የሰራ ታላቅ የጥበብ ሰው ነው።
በይልማ ገ/አብ እና በዜማ ደራሲው አበበ መለሰ የተሰራው ይህ ሰርካለም ሙዚቃ ስራ ግን ለአበበ ብርሀኔ ቀዳሚ የሙዚቃ ምርጫ ነው።
የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" ሲሰማ ምርጫው መሆኑን ከመመስከር ወደ ኋላ አይልም።
ለእርሱ ይህ ሙዚቃ ከአድማጭነት አልፎ የህይወት አጋሩ ሆኗል።
አበበ ለዚህ ሙዚቃ ያለው ክብር እንደ ተራ አድናቂ አይደለም።
ሙዚቃው ሲጀምር አበበ ወደ ትዝታው ጥግ ይጓዛል።
"ሰርካለም" ለእርሱ እንደ አንድ ታሪካዊ መጽሐፍ ገጾች ያለፉትን ጣፋጭና መራራ የህይወት ምዕራፎች ሁሉ እያገላበጠ የሚያስታውሰው ነው።
የሙዚቃው ዜማና የቴዎድሮስ ታደሰ ድምፅ በአበበ ልብ ውስጥ ልዩ የሆነ የመረጋጋት ስሜት ይፈጥራል የአንጀቱ መታረሻም ይኸው ነው።
"ሰርካለም" የጥበብ ጥግ ነው። በሙዚቃው ውስጥ የሚሰማው የፍቅር የናፍቆትና የህይወት ትርጉም ከአበበ የጥበብ እይታ ጋር ይዋሃዳል።
አበበ በግርምት ሲናገር እንዲህ ይላል
እንዴት እንዲህ አይነት ሙዚቃ ይሰራል የሚል።
የግጥሙ ጥልቀት የዜማው ጥራት እና ውበት ይደንቀኛልም ይላል።
"ሰርካለም" ለእርሱ የትላንት ናፍቆቱ የዛሬ ኩራቱ እና የነገ ተስፋው የሆነ ሙዚቃ ይመስላል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ኢትዮጵያሙዚቃሰርካለም #አበበብርሀኔቴዎድሮስታደሰ #ይልማገብረአብአበበመለሰ
#ethiopia | ሁለገቡ የጥበብ ሰው አበበ ብርሃኔ ግጥምና ዜማቸው በሌሎች ከተሰሩ የሙዚቃ ስራዎች መካከል የሚወደው አንድ ሙዚቃ አለ።
አቤ እጅግ ከሚወዳቸው የሙዚቃ ስራዎች መካከል የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" የተሰኘው ሙዚቃ ሙዚቃ እንደሆነ በአንድ ወቅት ከጋዜጠኛ ሔኖክ ወ/ገብርኤል ጋር በሙዚቀኞች ብፌ ፕሮግራም ላይ በነበረው ቆይታ ተናግሮ ነበር።
ይህ ሙዚቃ ለአቤ ሁሉ ነገሩ ነው።
የጥበብ ሰው አበበ ብርሃኔ የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" ሲያዳምጥ ልክ በውስጡ የተደበቀ በቃላት ሊገለጽ የማይችል ጥልቅ ስሜት የሚቀሰቀስበት ይመስላል።
አበበ ብርሃኔ በሙዚቃ ዓለም ውስጥ ከ800 በላይ የግጥምና የዜማ ስራዎች የሰራ ታላቅ የጥበብ ሰው ነው።
በይልማ ገ/አብ እና በዜማ ደራሲው አበበ መለሰ የተሰራው ይህ ሰርካለም ሙዚቃ ስራ ግን ለአበበ ብርሀኔ ቀዳሚ የሙዚቃ ምርጫ ነው።
የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" ሲሰማ ምርጫው መሆኑን ከመመስከር ወደ ኋላ አይልም።
ለእርሱ ይህ ሙዚቃ ከአድማጭነት አልፎ የህይወት አጋሩ ሆኗል።
አበበ ለዚህ ሙዚቃ ያለው ክብር እንደ ተራ አድናቂ አይደለም።
ሙዚቃው ሲጀምር አበበ ወደ ትዝታው ጥግ ይጓዛል።
"ሰርካለም" ለእርሱ እንደ አንድ ታሪካዊ መጽሐፍ ገጾች ያለፉትን ጣፋጭና መራራ የህይወት ምዕራፎች ሁሉ እያገላበጠ የሚያስታውሰው ነው።
የሙዚቃው ዜማና የቴዎድሮስ ታደሰ ድምፅ በአበበ ልብ ውስጥ ልዩ የሆነ የመረጋጋት ስሜት ይፈጥራል የአንጀቱ መታረሻም ይኸው ነው።
"ሰርካለም" የጥበብ ጥግ ነው። በሙዚቃው ውስጥ የሚሰማው የፍቅር የናፍቆትና የህይወት ትርጉም ከአበበ የጥበብ እይታ ጋር ይዋሃዳል።
አበበ በግርምት ሲናገር እንዲህ ይላል
እንዴት እንዲህ አይነት ሙዚቃ ይሰራል የሚል።
የግጥሙ ጥልቀት የዜማው ጥራት እና ውበት ይደንቀኛልም ይላል።
"ሰርካለም" ለእርሱ የትላንት ናፍቆቱ የዛሬ ኩራቱ እና የነገ ተስፋው የሆነ ሙዚቃ ይመስላል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ኢትዮጵያሙዚቃሰርካለም #አበበብርሀኔቴዎድሮስታደሰ #ይልማገብረአብአበበመለሰ
20 days ago
የአለም ዋንጫ ያለ እሷ አይታሰብም፦
የፊፋ ፕሬዝዳንት
*ፊፋ ሻኪራ የውድድሩ ቅመም ብሏታል።
#ethiopia | የዓለም ዋንጫዋ ድምቀት ሻኪራ እና የሙዚቃው ስሜት በአረንጓዴው ሜዳ ትላንት ምሽትም ደምቆ ታይቷል።
በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ከስፖርታዊ ብቃት ባሻገር በሙዚቃዊ ስሜት ሲታወስ የኖረው የዓለም ዋንጫ ዘንድሮም የኮሎምቢያዊቷን ኮከብ ሻኪራን ብቃት ተደምሟል።
ሻኪራ ከእግር ኳስ ዓለም ጋር ያላት ቁርኝት እጅግ የጠበቀ ነው።
በተለይም በ2010 የደቡብ አፍሪካ ዓለም ዋንጫ ላይ የዘፈነችው Waka Waka (This Time for Africa) ዘፈን እስካሁን ድረስ ከዓለም ዋንጫ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ምርጥ የሙዚቃ ስራዎች በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል።
የእሷ ሙዚቃ በዓለም ዙሪያ ያሉ የተለያዩ ባህሎችን የሚያቀናጅ በመሆኑ፣ የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን በማቀራረብ ረገድ ትልቅ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።
የፊፋው ፕሬዝዳንት እንደተናገሩት ሻኪራ መድረክ ላይ መገኘት ለጨዋታዎቹ ተጨማሪ ድምቀት በመስጠት የስታዲየሙን ድባብ ከፍ ታደርጋለች ብለዋል።
እሷ የአለም ዋንጫው ቅመም ናት ሲሉም አሞካሽተዋታል።
ሻኪራ የሙዚቃ ንግሥት ብቻ ሳትሆን የእግር ኳስ ዓለም የቅርብ ወዳጅ መሆኗን እንደገና ያረጋገጠችበት ሆኗልም ሲሉ አክለዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fifaworldcup2026 #colombiansinger #shakiradaidaiwakawaka
የፊፋ ፕሬዝዳንት
*ፊፋ ሻኪራ የውድድሩ ቅመም ብሏታል።
#ethiopia | የዓለም ዋንጫዋ ድምቀት ሻኪራ እና የሙዚቃው ስሜት በአረንጓዴው ሜዳ ትላንት ምሽትም ደምቆ ታይቷል።
በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ከስፖርታዊ ብቃት ባሻገር በሙዚቃዊ ስሜት ሲታወስ የኖረው የዓለም ዋንጫ ዘንድሮም የኮሎምቢያዊቷን ኮከብ ሻኪራን ብቃት ተደምሟል።
ሻኪራ ከእግር ኳስ ዓለም ጋር ያላት ቁርኝት እጅግ የጠበቀ ነው።
በተለይም በ2010 የደቡብ አፍሪካ ዓለም ዋንጫ ላይ የዘፈነችው Waka Waka (This Time for Africa) ዘፈን እስካሁን ድረስ ከዓለም ዋንጫ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ምርጥ የሙዚቃ ስራዎች በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል።
የእሷ ሙዚቃ በዓለም ዙሪያ ያሉ የተለያዩ ባህሎችን የሚያቀናጅ በመሆኑ፣ የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን በማቀራረብ ረገድ ትልቅ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።
የፊፋው ፕሬዝዳንት እንደተናገሩት ሻኪራ መድረክ ላይ መገኘት ለጨዋታዎቹ ተጨማሪ ድምቀት በመስጠት የስታዲየሙን ድባብ ከፍ ታደርጋለች ብለዋል።
እሷ የአለም ዋንጫው ቅመም ናት ሲሉም አሞካሽተዋታል።
ሻኪራ የሙዚቃ ንግሥት ብቻ ሳትሆን የእግር ኳስ ዓለም የቅርብ ወዳጅ መሆኗን እንደገና ያረጋገጠችበት ሆኗልም ሲሉ አክለዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fifaworldcup2026 #colombiansinger #shakiradaidaiwakawaka
Sponsored by
Surafel
25 days ago
ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አድናቂዎቹን አመስግኗል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፣ በሙዚቃው ዓለም የቆየባቸውን 25 ዓመታት አስመልክቶ ለደጋፊዎቹ የምስጋና መልእክት አስተላለፈ።
ድምጻዊው ዛሬ ባሰራጨው የጽሑፍ መልእክት የሙዚቃ ጉዞው የጀመረበትን 25ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ላለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የሚገኙ አድናቂዎቹ ላሳዩት የማይቀንስ ፍቅርና ድጋፍ በልዑል እግዚአብሔር ስም ምስጋናውን አቅርቧል።
ቴዲ አፍሮ በመልእክቱ እንዳስታወሰው፣ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከግማሽ በላይ በሙዚቃ ህይወቱ ውስጥ በነበሩት ውጣ ውረዶች፣ ስኬቶች እና ተግዳሮቶች ጊዜ ሁሉ አድናቂዎቹ ለእርሱ የነበራቸው ጽኑ ወዳጅነትና የማይጠፋ ፍቅር ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ገልጿል።
የሙዚቃው ዓለም እውቅና ያተረፈለትና በርካታ ተወዳጅ አልበሞችን ለአድማጭ ያደረሰው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ አድናቂዎቹ ላሳዩት ቀጣይነት ያለው ፍቅር ያለውን አክብሮት በመግለጽ ለወደፊቱም ሙዚቃዊ ስራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክቷል።
"ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ፍቅር ያሸንፋል!" በሚል መፈክር መልእክቱን የቋጨው ድምጻዊው፣ በአድናቂዎቹ ዘንድ ያለውን ትልቅ አክብሮት በምስጋና አረጋግጧል።
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ethiopiamusic #ድምጻዊቴዎድሮስካሳሁን
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፣ በሙዚቃው ዓለም የቆየባቸውን 25 ዓመታት አስመልክቶ ለደጋፊዎቹ የምስጋና መልእክት አስተላለፈ።
ድምጻዊው ዛሬ ባሰራጨው የጽሑፍ መልእክት የሙዚቃ ጉዞው የጀመረበትን 25ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ላለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የሚገኙ አድናቂዎቹ ላሳዩት የማይቀንስ ፍቅርና ድጋፍ በልዑል እግዚአብሔር ስም ምስጋናውን አቅርቧል።
ቴዲ አፍሮ በመልእክቱ እንዳስታወሰው፣ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከግማሽ በላይ በሙዚቃ ህይወቱ ውስጥ በነበሩት ውጣ ውረዶች፣ ስኬቶች እና ተግዳሮቶች ጊዜ ሁሉ አድናቂዎቹ ለእርሱ የነበራቸው ጽኑ ወዳጅነትና የማይጠፋ ፍቅር ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ገልጿል።
የሙዚቃው ዓለም እውቅና ያተረፈለትና በርካታ ተወዳጅ አልበሞችን ለአድማጭ ያደረሰው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ አድናቂዎቹ ላሳዩት ቀጣይነት ያለው ፍቅር ያለውን አክብሮት በመግለጽ ለወደፊቱም ሙዚቃዊ ስራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክቷል።
"ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ፍቅር ያሸንፋል!" በሚል መፈክር መልእክቱን የቋጨው ድምጻዊው፣ በአድናቂዎቹ ዘንድ ያለውን ትልቅ አክብሮት በምስጋና አረጋግጧል።
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ethiopiamusic #ድምጻዊቴዎድሮስካሳሁን
25 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፣ በሙዚቃው ዓለም የቆየባቸውን 25 ዓመታት አስመልክቶ ለደጋፊዎቹ የምስጋና መልእክት አስተላለፈ።
ድምጻዊው ዛሬ ባሰራጨው የጽሑፍ መልእክት የሙዚቃ ጉዞው የጀመረበትን 25ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ላለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የሚገኙ አድናቂዎቹ ላሳዩት የማይቀንስ ፍቅርና ድጋፍ በልዑል እግዚአብሔር ስም ምስጋናውን አቅርቧል። ቴዲ አፍሮ በመልእክቱ እንዳስታወሰው፣ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከግማሽ በላይ በሙዚቃ ህይወቱ ውስጥ በነበሩት ውጣ ውረዶች፣ ስኬቶች እና ተግዳሮቶች ጊዜ ሁሉ አድናቂዎቹ ለእርሱ የነበራቸው ጽኑ ወዳጅነትና የማይጠፋ ፍቅር ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ገልጿል።
የሙዚቃው ዓለም እውቅና ያተረፈለትና በርካታ ተወዳጅ አልበሞችን ለአድማጭ ያደረሰው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ አድናቂዎቹ ላሳዩት ቀጣይነት ያለው ፍቅር ያለውን አክብሮት በመግለጽ ለወደፊቱም ሙዚቃዊ ስራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክቷል።
"ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ፍቅር ያሸንፋል!" በሚል መፈክር መልእክቱን የቋጨው ድምጻዊው፣ በአድናቂዎቹ ዘንድ ያለውን ትልቅ አክብሮት በምስጋና አረጋግጧል።
ድምጻዊው ዛሬ ባሰራጨው የጽሑፍ መልእክት የሙዚቃ ጉዞው የጀመረበትን 25ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ላለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የሚገኙ አድናቂዎቹ ላሳዩት የማይቀንስ ፍቅርና ድጋፍ በልዑል እግዚአብሔር ስም ምስጋናውን አቅርቧል። ቴዲ አፍሮ በመልእክቱ እንዳስታወሰው፣ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከግማሽ በላይ በሙዚቃ ህይወቱ ውስጥ በነበሩት ውጣ ውረዶች፣ ስኬቶች እና ተግዳሮቶች ጊዜ ሁሉ አድናቂዎቹ ለእርሱ የነበራቸው ጽኑ ወዳጅነትና የማይጠፋ ፍቅር ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ገልጿል።
የሙዚቃው ዓለም እውቅና ያተረፈለትና በርካታ ተወዳጅ አልበሞችን ለአድማጭ ያደረሰው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ አድናቂዎቹ ላሳዩት ቀጣይነት ያለው ፍቅር ያለውን አክብሮት በመግለጽ ለወደፊቱም ሙዚቃዊ ስራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክቷል።
"ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ፍቅር ያሸንፋል!" በሚል መፈክር መልእክቱን የቋጨው ድምጻዊው፣ በአድናቂዎቹ ዘንድ ያለውን ትልቅ አክብሮት በምስጋና አረጋግጧል።
26 days ago
"5 ዓመት ደክሜበት ህዝብ የሚወደውን ቆንጆ ስራ ይዤ መጥቻለሁ" — ድምጻዊት ጄሪ አንተነህ
በ"ለኔ ባለው"፣ "ባዶ" እና "አላመደኝ" በተሰኙ ነጠላ ዜማዎቿ በአድማጮች ዘንድ ፍቅር ያተረፈችው ድምጻዊት ጄሪ አንተነህ፣ ለአምስት ዓመታት የለፋችበትን እና በብዙ ትጋት ያዘጋጀችውን "ወደ ንጋት" የተሰኘ ሙሉ አልበሟን ለአድማጮች አቅርባለች።
ድምጻዊቷ አልበሙን በራሷ የዩቲዩብ ቻናል ላይ ለህዝብ ይፋ ስታደርግ፣ "5 ዓመት ደክሜበት ህዝብ የሚወደውን ቆንጆ ስራ ይዤ መጥቻለሁ" በማለት ስራዋ በአድማጮች ዘንድ ተቀባይነት እንደሚያገኝ ያላትን እምነት ገልጻለች።
10 ትራኮች የያዘውን ይህን አልበም ለማጠናቀቅ ከካናዳ ወደ ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በመመላለስ ከፍተኛ ወጪና ጊዜ እንዳፈሰሰችበት ተናግራለች።
በአልበሙ ዝግጅትም በኢትዮጵያ የሙዚቃ ዘርፍ ታዋቂ ባለሙያዎች የሆኑት ብሩክ ተቀባ፣ ብሩክ አፍወርቅ እና ታምሩ አማረ የሰሩ ሲሆን፣ የማስተሪንግ ስራውን ደግሞ አበጋዙ ክብረወርቅ ሺዎታ እንዳከናወነ ተገልጿል።
"ወደ ንጋት" የተሰኘው አልበም ከረጅም ጊዜ ዝግጅት፣ ትጋት እና መስዋዕትነት በኋላ ለአድማጮች የደረሰ ሲሆን፣ በሙዚቃ ወዳዶች ዘንድ ምን ያህል ተቀባይነት እንደሚያገኝ በጉጉት እየተጠበቀ ነው።
ሊንኩን በመጫን ተመልከቷት
👇
https://youtube.com/jerry...
በ"ለኔ ባለው"፣ "ባዶ" እና "አላመደኝ" በተሰኙ ነጠላ ዜማዎቿ በአድማጮች ዘንድ ፍቅር ያተረፈችው ድምጻዊት ጄሪ አንተነህ፣ ለአምስት ዓመታት የለፋችበትን እና በብዙ ትጋት ያዘጋጀችውን "ወደ ንጋት" የተሰኘ ሙሉ አልበሟን ለአድማጮች አቅርባለች።
ድምጻዊቷ አልበሙን በራሷ የዩቲዩብ ቻናል ላይ ለህዝብ ይፋ ስታደርግ፣ "5 ዓመት ደክሜበት ህዝብ የሚወደውን ቆንጆ ስራ ይዤ መጥቻለሁ" በማለት ስራዋ በአድማጮች ዘንድ ተቀባይነት እንደሚያገኝ ያላትን እምነት ገልጻለች።
10 ትራኮች የያዘውን ይህን አልበም ለማጠናቀቅ ከካናዳ ወደ ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በመመላለስ ከፍተኛ ወጪና ጊዜ እንዳፈሰሰችበት ተናግራለች።
በአልበሙ ዝግጅትም በኢትዮጵያ የሙዚቃ ዘርፍ ታዋቂ ባለሙያዎች የሆኑት ብሩክ ተቀባ፣ ብሩክ አፍወርቅ እና ታምሩ አማረ የሰሩ ሲሆን፣ የማስተሪንግ ስራውን ደግሞ አበጋዙ ክብረወርቅ ሺዎታ እንዳከናወነ ተገልጿል።
"ወደ ንጋት" የተሰኘው አልበም ከረጅም ጊዜ ዝግጅት፣ ትጋት እና መስዋዕትነት በኋላ ለአድማጮች የደረሰ ሲሆን፣ በሙዚቃ ወዳዶች ዘንድ ምን ያህል ተቀባይነት እንደሚያገኝ በጉጉት እየተጠበቀ ነው።
ሊንኩን በመጫን ተመልከቷት
👇
https://youtube.com/jerry...
26 days ago
ዛሬ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ደማቅ ቀን ነው። አድማጮች በሙዚቃው የሚወዱት፣ ግጥምና ዜማውን በራሱ የሚቃኘው ተወዳጁ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የተወለደበት ቀን ነው።
የትውልድ እና እድገቱ አዲስ አበባ የሆነው ቴዲ፣ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትምህርቱን የተከታተለውም እዚሁ ከተማ ነው። ለሙዚቃ ባለው ከፍተኛ ፍቅር እና ባሳየው የፈጠራ ብቃት፣ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ስሙ በጉልህ እንዲሰፍር አድርጎታል።
"ፍቅር ያሸንፋል" በሚለው አባባሉ የሚታወቀውና በአድናቂዎቹ ዘንድ ትልቅ ስፍራ ያለው ቴዲ፣ ከውጫዊ ተጽዕኖዎች ይልቅ ትኩረቱን ሙዚቃው ላይ ብቻ በማድረግ ለሙዚቃው ኢንዱስትሪ ትልቅ አሻራ ጥሏል።
ዛሬ የተወለድክበት ቀን ነውና፣ ለቀጣይ የኪነ-ጥበብ ስራዎችህ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። እንኳን ተወለድክ!
የትውልድ እና እድገቱ አዲስ አበባ የሆነው ቴዲ፣ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትምህርቱን የተከታተለውም እዚሁ ከተማ ነው። ለሙዚቃ ባለው ከፍተኛ ፍቅር እና ባሳየው የፈጠራ ብቃት፣ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ስሙ በጉልህ እንዲሰፍር አድርጎታል።
"ፍቅር ያሸንፋል" በሚለው አባባሉ የሚታወቀውና በአድናቂዎቹ ዘንድ ትልቅ ስፍራ ያለው ቴዲ፣ ከውጫዊ ተጽዕኖዎች ይልቅ ትኩረቱን ሙዚቃው ላይ ብቻ በማድረግ ለሙዚቃው ኢንዱስትሪ ትልቅ አሻራ ጥሏል።
ዛሬ የተወለድክበት ቀን ነውና፣ ለቀጣይ የኪነ-ጥበብ ስራዎችህ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። እንኳን ተወለድክ!
27 days ago
ድምፃዊ አህመድ ተሾመ አዲሱን "ጊዜ አይሄድም" አልበም ለታዋቂ የጥበብ ሰዎች አስቀድሞ አስደመጠ
#ethiopia | ድምፃዊና የዜማ ደራሲ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) በመጪው አርብ ሐምሌ 10 ቀን በናሆም ሪከርድስ አማካኝነት ለአድማጮች የሚያቀርበውን "ጊዜ አይሄድም" የተሰኘ 3ኛ የሙዚቃ አልበሙን ከመለቀቁ በፊት ለታዋቂ የሀገራችን የጥበብ ሰዎች ያስደመጠበት የአልበም ቅምሻ ዝግጅት በደብል ትሪ (ባይ ሂልተን) ሆቴል ተካሂዷል።
በዝግጅቱ ላይ ባለቅኔ፣ ገጣሚና ፀሐፊ ተውኔት አያልነህ ሙላት፣ አርቲስት አበበ ባልቻ፣ ፀሐፊ ተውኔት ሀይሉ ፀጋዬ፣ አርቲስት ታምሩ ብርሃኑ፣ የሙዚቃ ባለሙያዎች ጆርጋ መስፍን፣ ብሌን ዮሴፍ፣ ብሩክ አሰፋ እንዲሁም ድምፃዊ አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ)፣ አርቲስት ዕድልወርቅ ጣሰው፣ ቲክቶከር ሀያት ናስር (ዩቲ ናስ) እና ሌሎች በርካታ የጥበብ ባለሙያዎች ተገኝተው አልበሙን ቀድመው አዳምጠዋል።
አህመድ ተሾመ፣ "አልበሜን ለመላው የሙዚቃ አፍቃሪ ከማስደመጤ በፊት መርቁኝ፤ ሀሳብና አስተያየታችሁን ንገሩኝ" በማለት ከተጋባዦቹ ጋር ሰፊ ውይይት አድርጓል።
አልበሙን ቀድመው ያዳመጡት የጥበብ ሰዎችም በሙዚቃዎቹ እጅግ እንደተደሰቱ በመግለጽ ለድምፃዊው መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
"ጊዜ አይሄድም" የተሰኘው 3ኛው የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) አልበም በመጪው አርብ በይፋ ለአድማጮች የሚቀርብ ሲሆን፣ በብዙ የሙዚቃና የጥበብ አፍቃሪዎች በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል።
#ethiopia | ድምፃዊና የዜማ ደራሲ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) በመጪው አርብ ሐምሌ 10 ቀን በናሆም ሪከርድስ አማካኝነት ለአድማጮች የሚያቀርበውን "ጊዜ አይሄድም" የተሰኘ 3ኛ የሙዚቃ አልበሙን ከመለቀቁ በፊት ለታዋቂ የሀገራችን የጥበብ ሰዎች ያስደመጠበት የአልበም ቅምሻ ዝግጅት በደብል ትሪ (ባይ ሂልተን) ሆቴል ተካሂዷል።
በዝግጅቱ ላይ ባለቅኔ፣ ገጣሚና ፀሐፊ ተውኔት አያልነህ ሙላት፣ አርቲስት አበበ ባልቻ፣ ፀሐፊ ተውኔት ሀይሉ ፀጋዬ፣ አርቲስት ታምሩ ብርሃኑ፣ የሙዚቃ ባለሙያዎች ጆርጋ መስፍን፣ ብሌን ዮሴፍ፣ ብሩክ አሰፋ እንዲሁም ድምፃዊ አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ)፣ አርቲስት ዕድልወርቅ ጣሰው፣ ቲክቶከር ሀያት ናስር (ዩቲ ናስ) እና ሌሎች በርካታ የጥበብ ባለሙያዎች ተገኝተው አልበሙን ቀድመው አዳምጠዋል።
አህመድ ተሾመ፣ "አልበሜን ለመላው የሙዚቃ አፍቃሪ ከማስደመጤ በፊት መርቁኝ፤ ሀሳብና አስተያየታችሁን ንገሩኝ" በማለት ከተጋባዦቹ ጋር ሰፊ ውይይት አድርጓል።
አልበሙን ቀድመው ያዳመጡት የጥበብ ሰዎችም በሙዚቃዎቹ እጅግ እንደተደሰቱ በመግለጽ ለድምፃዊው መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
"ጊዜ አይሄድም" የተሰኘው 3ኛው የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) አልበም በመጪው አርብ በይፋ ለአድማጮች የሚቀርብ ሲሆን፣ በብዙ የሙዚቃና የጥበብ አፍቃሪዎች በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል።
27 days ago
"ገላ ገላ" አስቱካን እካችሁ
የሰው ልጅ ነፍስ የምትተነፍስበት ጥልቅ ውቅያኖስ "ሙዚቃ"
"ሙዚቃ" እና "ፍቅር" ደግሞ ተነጣጥለው የማይታዩ፣ አንዱ ለአንዱ የተፈጠሩ፣ የሰማይ እና የምድር ያህል የተሳሰሩ የነፍስ ቋንቋዎች ናቸው።
ከትላንት እስከ ዛሬ... ከካሴት ክር እስከ ዲጂታል ዘመን፣ ቴክኖሎጂው ቢለዋወጥም፣ ትውልድ ቢተካካም እነዚህን ሁለት መለኮታዊ ጸጋዎች በአንድ ልብ አዋህዳ፣ ስሜትን በዜማ ሸምና ያቀረበችልን የዘመናቶች ፈርጥ—እሷ አስቴር አወቀ ናት!
የትውልድን ልብ ያንኳኳች፣ ማዕበል እና ጸጥታን በድምጿ ያስማማች የኢትዮጵያ የሙዚቃ ጸጋ! አስቴር የ"ሶል" (Soul)
የፍቅር ንግሥት በድምጿ ጅረት ውስጥ የሰውን ልጅ ጥልቅ የልብ ጓዳ የምትፈትሽ፣ ስንከፋ አባባይ፣ ስንደሰት አጀብ ባይ የሆነች የዘመን ሀብት ናት።
ትዝታን ብቻ አይቀሰቅሱም፤ ገና ሳንኖረው የናፈቀንን፣ በቃላት የማይገለጸውን ያንን ጥልቅ ናፍቆት (መናፍቅነት) በውስጣችን ይፈጥራሉ። "ፍቅር" የሚለውን ቃል ስታዜመው፣ የፍቅርን ፊደል ያልቆጠረው እንኳ በፍቅር ይነድፋል፤ ገና ያላየነውን የፍቅር ብስራት በሙዚቃዋ እንድንኖረው፣ ያላጣጣመነውን ስሜት በምናባችን እንድንስለው ታደርገናለች። ድምጿ ሲሰማ የሌለብን ትዝታ ይጭንብናል፣ የሌለ ስንብት ያስለቅሰናል፣ ገና ያልመጣ ተስፋ ያስፈነድቀናል።
ትላንት አባቶቻችን እና እናቶቻችን ያደመጧትን፣ ዛሬ እኛ በፍቅር እንሰማታለን፤ ነገም ልጆቻችን ይወርሷታል። ጊዜ የማይሽራት፣ ዘመን የማያልፍባት ተወዳጅ አርቲስት!
እስኪ አንድ ሁለቲቱን እንምልክት
"ለመድክ ወይ" የተሰኘውን ይህን ልብ ሰባሪ እና ስሜት አንጀት ሰርስሮ የሚገባ የሙዚቃ ስራ ስናዳምጥ፣ የሰውን ልጅ የፍቅር ስነ-ልቦና፣ የልብ ስብራትን (Heartbreak) እና የመለየትን መራር እውነት በሚያስገርም ጥልቀት ስትፈትሸው እናገኛለን።
ይህ ዘፈን ተራ የሙዚቃ ዜማ አይደለም፤ ይልቁንም አንዲት በፍቅር የተከዳች፣ ማመን ያቃታት እና በትዝታ እስር ቤት ውስጥ የቀረች ነፍስ የምታሰማው የውስጥ ጩኸት ነው።
የዚህን ድንቅ ዘፈን ጥልቅ መልእክት በበሰለ የኪነ-ጥበብ መነጽር ስንተነትነው የሚከተሉትን ህያው እውነታዎች እናገኛለን
1. "ለመድክ ወይ?" ይህ ጥያቄ ተራ መጠይቅ አይደለም። የድንጋጤ እና የመገረም ጩኸት
ያለኔ መኖርን ቻልከው? እኔ ገና የትላንቱን አብሮነታችንን መርሳት አቅቶኝ በትዝታ እሳት እየነደድኩ፣ አንተ ግን እንዴት ያለምንም ህመም የክህደት እና የመገረም ስሜት ነው አንድ ሰው የነፍሱን ግማሽ አድርጎ ያሰበው አካል አዲስ ህይወት በአንድ ጀንበር የሚፈጠረውን የአእምሮ ንዝረት ያሳያል
አስቴር ይህንን ሚዛን የሳተ ፍቅር በጉልህ ታሳያለች።
በፍቅር መለያየት ውስጥ እጅግ አሳማሚው ነገር የህመሙ አለመመጣጠን ነው።
ለአንዱ (ለአፍቃሪዋ) ፍቅር የህይወት መሰረት፣ እስትንፋስ እና አለም ሲሆን፤ ለሌላኛው (ለተፈቃሪው) ግን ፍቅር ጊዜያዊ ማረፊያ፣ በቀላሉ ሊተካ እና ሊረሳ የሚችል ተራ ክስተት ሆኖ እናገኘዋለን። "እኔ እንዲህ ሆኜ፣ አንተ እንዴት ሆንክ?" የሚለው የዘፈኑ የጀርባ አጥንት ይህንን የስሜት መራራቅ ያጋልጣል።ያ የለመደችው ድምፅ፣ ያ የለመደችው መዓዛ በድንገት ሲቋረጥ ነፍስ ባዶ ትቀራለች። አስቴር በዚህ ዘፈኗ፣ መለየቱን አምና ለመቀበል የሚደረገውን የውስጥ ትግል እና የትዝታን አረመኔነት በቃላቷ ትስላለች። "ልመዳ" እንዴት ከባድ እንደሆነና ያንን ማቋረጥ ደግሞ ሞት መሆኑን ልክ አንዲት ሴት ብቻዋን ክፍሏ ውስጥ ሆና የምታነባውን፣ የምታቃስተውን እና ከራሷ ጋር የምታደርገውን ሙግት በዜማ ልክ ሰፍታ ታለብሰናለች።
የናፍቆትን እሳት እና የልብን መታለል ያለምንም ማለዘቢያ ፊት ለፊት
ለመድክ ወይ" የፍቅርን የጨለመ ገፅ ሚያዳምጣት ሁሉ የተወሳሰበ የሰው ልጅ ስሜት ወስዳ
የቆሰለ ልብ ያለው ሁሉ፣ በዚህ ዘፈን ውስጥ የራሱን እንባ ያገኛል!
"ገላ ገላ" በረቂቅ ቃላት የተሳለበት የፍቅር ጸሎት ።
ይህ ዘፈን ተራ የቃላት ድርደራ ሳይሆን፣ አንዲት የሰው ልጅ ነፍስ በፍቅር ስትገዛ፣ ስትማረክ እና ራሷን አሳልፋ ስትሰጥ የሚኖራትን ጥልቅ ስነ-ልቦናዊ እና ስጋዊ ውህደት የሚያሳይ ህያው ማሳያ ነው።
ገላ—የነፍስ ማረፊያ፣ የስሜት መግለጫ እና የፍቅር ቤተ-መቅደስ ነው።
አስቴር "ገላ" ስትል፣ መነካካትን ብቻ ሳይሆን፣ ሁለት ነፍሶች አንድ የሚሆኑበትን፣ መለያየት የሌለበትን ያንን የመጨረሻውን የፍቅር ልዕልና (Intimacy) እየጠራች ነው። ለእሷ ህይወት የሚዘራ፣ ግን ደግሞ ናፍቆትን የሚያባብስ ጣፋጭ እስር ቤት ነው።
አንድ የምታውቀው ፍጹም እውነት ቢኖር የራሷን የልብ ትርታ ነው።
የሷ "ሆድ" (ውስጧ/ነፍሷ) ለእሱ መገዛቱን አምና መቀበሏ፣ በፍቅር ውስጥ ያለውን ያለምንም ቅድመ-ሁኔታ ራስን አሳልፎ የመስጠት ጀግንነት ያሳያል።ፍቅር ከስሜት አልፎ ወደ "መኖር እና አለመኖር" ትርጉም ይሸጋገራል። ፍቅር የልብ ምት ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ሳንባ ገብቶ የሚያኖራት ኦክስጅኗ ሆኗል።
የነፍስ ኑዛዜ ነው ገና ያላፈቀረውን "እንዲህ ያለ ጥልቅ ፍቅር ባገኘሁ" ብሎ እንዲመኝ ሲያደርግ፤ ያፈቀረውን ደግሞ የልቡን ቋንቋ አግኝቶለታል።የሰውን ልጅ ድብቅ እና ጥልቅ የልብ ጓዳ ገብታ፣ ትበረብራልች
በሥራ መክበርን" በተግባር በማሳየቷ እንጂ! 40የልማሳ ዓመታት ሙሉ በመድረክ ላይ መቆየት፣ 28 አልበሞችን ማበርከት... ይህ ቁጥር ብቻ አይደለም፤ የትጋት፣ ለጥበብ የመገዛት እና የተሰጥኦ ጥግ ነው። አስቴር ጥበብን ከትጋት ጋር አጣምራ፣ የሰራችው ስራ ሁሉ ወርቅ ሆኖላት፣ በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ለዘላለም የነገሰች የጥበብ ጀግና ናት። "ሙዚቃ" ፍቅር ነው፤ "ፍቅርም" ሙዚቃ ነው። ሁለቱም ደግሞ በአንድነት ሲጣመሩ "አስቴር አወቀ" የሚል ትርጉም ይሰጡናል።
ክብር በሥራዋ ለከበረችው...
ክብር ጥበብን አክብራ ላስከበረችን...
ክብር ትውልድን በዜማ እና በፍቅር ላዋሃደችው...ክብርም በስራሽ ሁሉ እድንወድሽ ላደረጉት በስራዎችሽ አሻራቸውን ላኖሩ ከቴዎድሮስ መኩሪያ ላስቱካ
የሰው ልጅ ነፍስ የምትተነፍስበት ጥልቅ ውቅያኖስ "ሙዚቃ"
"ሙዚቃ" እና "ፍቅር" ደግሞ ተነጣጥለው የማይታዩ፣ አንዱ ለአንዱ የተፈጠሩ፣ የሰማይ እና የምድር ያህል የተሳሰሩ የነፍስ ቋንቋዎች ናቸው።
ከትላንት እስከ ዛሬ... ከካሴት ክር እስከ ዲጂታል ዘመን፣ ቴክኖሎጂው ቢለዋወጥም፣ ትውልድ ቢተካካም እነዚህን ሁለት መለኮታዊ ጸጋዎች በአንድ ልብ አዋህዳ፣ ስሜትን በዜማ ሸምና ያቀረበችልን የዘመናቶች ፈርጥ—እሷ አስቴር አወቀ ናት!
የትውልድን ልብ ያንኳኳች፣ ማዕበል እና ጸጥታን በድምጿ ያስማማች የኢትዮጵያ የሙዚቃ ጸጋ! አስቴር የ"ሶል" (Soul)
የፍቅር ንግሥት በድምጿ ጅረት ውስጥ የሰውን ልጅ ጥልቅ የልብ ጓዳ የምትፈትሽ፣ ስንከፋ አባባይ፣ ስንደሰት አጀብ ባይ የሆነች የዘመን ሀብት ናት።
ትዝታን ብቻ አይቀሰቅሱም፤ ገና ሳንኖረው የናፈቀንን፣ በቃላት የማይገለጸውን ያንን ጥልቅ ናፍቆት (መናፍቅነት) በውስጣችን ይፈጥራሉ። "ፍቅር" የሚለውን ቃል ስታዜመው፣ የፍቅርን ፊደል ያልቆጠረው እንኳ በፍቅር ይነድፋል፤ ገና ያላየነውን የፍቅር ብስራት በሙዚቃዋ እንድንኖረው፣ ያላጣጣመነውን ስሜት በምናባችን እንድንስለው ታደርገናለች። ድምጿ ሲሰማ የሌለብን ትዝታ ይጭንብናል፣ የሌለ ስንብት ያስለቅሰናል፣ ገና ያልመጣ ተስፋ ያስፈነድቀናል።
ትላንት አባቶቻችን እና እናቶቻችን ያደመጧትን፣ ዛሬ እኛ በፍቅር እንሰማታለን፤ ነገም ልጆቻችን ይወርሷታል። ጊዜ የማይሽራት፣ ዘመን የማያልፍባት ተወዳጅ አርቲስት!
እስኪ አንድ ሁለቲቱን እንምልክት
"ለመድክ ወይ" የተሰኘውን ይህን ልብ ሰባሪ እና ስሜት አንጀት ሰርስሮ የሚገባ የሙዚቃ ስራ ስናዳምጥ፣ የሰውን ልጅ የፍቅር ስነ-ልቦና፣ የልብ ስብራትን (Heartbreak) እና የመለየትን መራር እውነት በሚያስገርም ጥልቀት ስትፈትሸው እናገኛለን።
ይህ ዘፈን ተራ የሙዚቃ ዜማ አይደለም፤ ይልቁንም አንዲት በፍቅር የተከዳች፣ ማመን ያቃታት እና በትዝታ እስር ቤት ውስጥ የቀረች ነፍስ የምታሰማው የውስጥ ጩኸት ነው።
የዚህን ድንቅ ዘፈን ጥልቅ መልእክት በበሰለ የኪነ-ጥበብ መነጽር ስንተነትነው የሚከተሉትን ህያው እውነታዎች እናገኛለን
1. "ለመድክ ወይ?" ይህ ጥያቄ ተራ መጠይቅ አይደለም። የድንጋጤ እና የመገረም ጩኸት
ያለኔ መኖርን ቻልከው? እኔ ገና የትላንቱን አብሮነታችንን መርሳት አቅቶኝ በትዝታ እሳት እየነደድኩ፣ አንተ ግን እንዴት ያለምንም ህመም የክህደት እና የመገረም ስሜት ነው አንድ ሰው የነፍሱን ግማሽ አድርጎ ያሰበው አካል አዲስ ህይወት በአንድ ጀንበር የሚፈጠረውን የአእምሮ ንዝረት ያሳያል
አስቴር ይህንን ሚዛን የሳተ ፍቅር በጉልህ ታሳያለች።
በፍቅር መለያየት ውስጥ እጅግ አሳማሚው ነገር የህመሙ አለመመጣጠን ነው።
ለአንዱ (ለአፍቃሪዋ) ፍቅር የህይወት መሰረት፣ እስትንፋስ እና አለም ሲሆን፤ ለሌላኛው (ለተፈቃሪው) ግን ፍቅር ጊዜያዊ ማረፊያ፣ በቀላሉ ሊተካ እና ሊረሳ የሚችል ተራ ክስተት ሆኖ እናገኘዋለን። "እኔ እንዲህ ሆኜ፣ አንተ እንዴት ሆንክ?" የሚለው የዘፈኑ የጀርባ አጥንት ይህንን የስሜት መራራቅ ያጋልጣል።ያ የለመደችው ድምፅ፣ ያ የለመደችው መዓዛ በድንገት ሲቋረጥ ነፍስ ባዶ ትቀራለች። አስቴር በዚህ ዘፈኗ፣ መለየቱን አምና ለመቀበል የሚደረገውን የውስጥ ትግል እና የትዝታን አረመኔነት በቃላቷ ትስላለች። "ልመዳ" እንዴት ከባድ እንደሆነና ያንን ማቋረጥ ደግሞ ሞት መሆኑን ልክ አንዲት ሴት ብቻዋን ክፍሏ ውስጥ ሆና የምታነባውን፣ የምታቃስተውን እና ከራሷ ጋር የምታደርገውን ሙግት በዜማ ልክ ሰፍታ ታለብሰናለች።
የናፍቆትን እሳት እና የልብን መታለል ያለምንም ማለዘቢያ ፊት ለፊት
ለመድክ ወይ" የፍቅርን የጨለመ ገፅ ሚያዳምጣት ሁሉ የተወሳሰበ የሰው ልጅ ስሜት ወስዳ
የቆሰለ ልብ ያለው ሁሉ፣ በዚህ ዘፈን ውስጥ የራሱን እንባ ያገኛል!
"ገላ ገላ" በረቂቅ ቃላት የተሳለበት የፍቅር ጸሎት ።
ይህ ዘፈን ተራ የቃላት ድርደራ ሳይሆን፣ አንዲት የሰው ልጅ ነፍስ በፍቅር ስትገዛ፣ ስትማረክ እና ራሷን አሳልፋ ስትሰጥ የሚኖራትን ጥልቅ ስነ-ልቦናዊ እና ስጋዊ ውህደት የሚያሳይ ህያው ማሳያ ነው።
ገላ—የነፍስ ማረፊያ፣ የስሜት መግለጫ እና የፍቅር ቤተ-መቅደስ ነው።
አስቴር "ገላ" ስትል፣ መነካካትን ብቻ ሳይሆን፣ ሁለት ነፍሶች አንድ የሚሆኑበትን፣ መለያየት የሌለበትን ያንን የመጨረሻውን የፍቅር ልዕልና (Intimacy) እየጠራች ነው። ለእሷ ህይወት የሚዘራ፣ ግን ደግሞ ናፍቆትን የሚያባብስ ጣፋጭ እስር ቤት ነው።
አንድ የምታውቀው ፍጹም እውነት ቢኖር የራሷን የልብ ትርታ ነው።
የሷ "ሆድ" (ውስጧ/ነፍሷ) ለእሱ መገዛቱን አምና መቀበሏ፣ በፍቅር ውስጥ ያለውን ያለምንም ቅድመ-ሁኔታ ራስን አሳልፎ የመስጠት ጀግንነት ያሳያል።ፍቅር ከስሜት አልፎ ወደ "መኖር እና አለመኖር" ትርጉም ይሸጋገራል። ፍቅር የልብ ምት ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ሳንባ ገብቶ የሚያኖራት ኦክስጅኗ ሆኗል።
የነፍስ ኑዛዜ ነው ገና ያላፈቀረውን "እንዲህ ያለ ጥልቅ ፍቅር ባገኘሁ" ብሎ እንዲመኝ ሲያደርግ፤ ያፈቀረውን ደግሞ የልቡን ቋንቋ አግኝቶለታል።የሰውን ልጅ ድብቅ እና ጥልቅ የልብ ጓዳ ገብታ፣ ትበረብራልች
በሥራ መክበርን" በተግባር በማሳየቷ እንጂ! 40የልማሳ ዓመታት ሙሉ በመድረክ ላይ መቆየት፣ 28 አልበሞችን ማበርከት... ይህ ቁጥር ብቻ አይደለም፤ የትጋት፣ ለጥበብ የመገዛት እና የተሰጥኦ ጥግ ነው። አስቴር ጥበብን ከትጋት ጋር አጣምራ፣ የሰራችው ስራ ሁሉ ወርቅ ሆኖላት፣ በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ለዘላለም የነገሰች የጥበብ ጀግና ናት። "ሙዚቃ" ፍቅር ነው፤ "ፍቅርም" ሙዚቃ ነው። ሁለቱም ደግሞ በአንድነት ሲጣመሩ "አስቴር አወቀ" የሚል ትርጉም ይሰጡናል።
ክብር በሥራዋ ለከበረችው...
ክብር ጥበብን አክብራ ላስከበረችን...
ክብር ትውልድን በዜማ እና በፍቅር ላዋሃደችው...ክብርም በስራሽ ሁሉ እድንወድሽ ላደረጉት በስራዎችሽ አሻራቸውን ላኖሩ ከቴዎድሮስ መኩሪያ ላስቱካ
Sponsored by
Surafel
27 days ago
(ዘ-ሐበሻ መዝናኛ ዜና) ሰባት ጊዜ የግራሚ ሽልማት አሸናፊዋ የ67 ዓመቷ ማዶና ኮንፌሽንስ 2 በተሰኘው አዲሱ አልበሟ አዳዲስ ሪከርዶችን የሰበረች ሲሆን፣ አልበሙ በቢልቦርድ 200 ገበታ ላይ አንደኛ ደረጃን በመያዝ አስረኛው አልበሟ ሆኖ ተመዝግቧል።
እንደወጡት ሪፖርቶች ከፍተኛ አድናቆት የተቸረው ይህ አልበም በአሜሪካ ውስጥ በተለቀቀ በመጀመሪያው ሳምንት ብቻ ከ134,000 በላይ ቅጂዎች የተሸጠ ሲሆን፣ ይህ ስኬቷም በቢልቦርድ 200 እና በዩናይትድ ኪንግደም አልበም ገበታዎች ላይ 10 አልበሞቻቸው አንደኛ ደረጃን በመያዝ ታሪክ ከሰሩት 'ዘ ቢትልስ' ጋር እኩል አድርጓታል።
እ.ኤ.አ በ2005 ለወጣው "Confessions on a Dance Floor" አልበም ቀጣይ ክፍል የሆነው ይህ ስራ፣ ከደጋፊዎቿ እና ከሙዚቃ ተቺዎች ከፍተኛ አድናቆትን ያተረፈ ሲሆን፣ ለግራሚ ሽልማትም ትልቅ ግምት ተሰጥቶታል። ማዶና ይህንን አልበም ለማስተዋወቅ በዌስት ሆሊውድ፣ ፓሪስ እና ለንደን ካደረገቻቸው ድንገተኛ መድረኮች በተጨማሪ፣ ጁላይ 11 በብሩክሊን በሚገኘው 'ኖክዳውን ሴንተር' ድንገተኛ ዝግጅት አቅርባለች።
ስሜት የሚነካው ይህ አልበም ሀዘንን፣ መፈወስን እና ጥንካሬን ይዳስሳል። በተለይም በቅርቡ ላጣችው ወንድሟ ክሪስቶፈር "Fragile" በተሰኘው ዘፈን የመታሰቢያ ክብር ስትሰጥ፣ ከመጀመሪያ ልጇ ሎላ ሊዮን ጋር በጋራ በሰራችው "The Test" በተሰኘው ዘፈን ደግሞ ይቅርታን ትጠይቃለች። "Danceteria" በሚለው ስራዋም በሙዚቃው ዓለም ገና በጀመረችበት አስቸጋሪ ጊዜ አብረዋት የነበሩ ጓደኞቿን ታወድሳለች።
ባለፈው ወር መጨረሻ በቢቢሲ የግራሃም ኖርተን ሾው ላይ በቀረበችበት ወቅት፣ አልበሙን በስቱዲዮ ውስጥ ስትሰራ ስለነበራት ቆይታ ተናግራለች። "በሆነ መንፈስ የተዋጥኩ ያህል ነበር፤ ሀሳቦች የሚመጡት ብዙ ሳልጨነቅ ነው" ያለችው ማዶና፣ እንደ "One Step Away" ያሉት ዘፈኖች ከነፍሷ የመነጩ መሆናቸውን አብራርታለች።
አልበሙ ከመለቀቁ በፊት ኒውዮርክ ታይምስ ስኩዌር ላይ ድንገተኛ ኮንሰርት ያቀረበችው ድምፃዊቷ፣ በትሪቤካ ፌስቲቫል ላይም አጭር ፊልም ለእይታ አብቅታለች። ለዚህ አጭር ፊልም መነሻ ሀሳብ የሰጣት የረጅም ጊዜ ስራ አስኪያጇ ጋይ ኦሴሪ መሆኑን የገለጸችው ማዶና፣ ከዳይሬክተሮች ጋር በመሆን ለስድስት ወራት እንደሰራችበት ተናግራለች።
በመጨረሻም በዚህ የዕድሜ እና የስራ ደረጃ ላይ ሆና ለአድናቂዎቿ የሰጠችው ምክር፦ "አደጋዎችን ለመጋፈጥ አትፍሩ፣ ለማወቅ ጉጉ ሁኑ፣ አስተውሉ፣ እንዲሁም ስልኮቻችሁን አስቀምጣችሁ ከሰዎች ጋር ተገናኙ!" የሚል ነበር።
እንደወጡት ሪፖርቶች ከፍተኛ አድናቆት የተቸረው ይህ አልበም በአሜሪካ ውስጥ በተለቀቀ በመጀመሪያው ሳምንት ብቻ ከ134,000 በላይ ቅጂዎች የተሸጠ ሲሆን፣ ይህ ስኬቷም በቢልቦርድ 200 እና በዩናይትድ ኪንግደም አልበም ገበታዎች ላይ 10 አልበሞቻቸው አንደኛ ደረጃን በመያዝ ታሪክ ከሰሩት 'ዘ ቢትልስ' ጋር እኩል አድርጓታል።
እ.ኤ.አ በ2005 ለወጣው "Confessions on a Dance Floor" አልበም ቀጣይ ክፍል የሆነው ይህ ስራ፣ ከደጋፊዎቿ እና ከሙዚቃ ተቺዎች ከፍተኛ አድናቆትን ያተረፈ ሲሆን፣ ለግራሚ ሽልማትም ትልቅ ግምት ተሰጥቶታል። ማዶና ይህንን አልበም ለማስተዋወቅ በዌስት ሆሊውድ፣ ፓሪስ እና ለንደን ካደረገቻቸው ድንገተኛ መድረኮች በተጨማሪ፣ ጁላይ 11 በብሩክሊን በሚገኘው 'ኖክዳውን ሴንተር' ድንገተኛ ዝግጅት አቅርባለች።
ስሜት የሚነካው ይህ አልበም ሀዘንን፣ መፈወስን እና ጥንካሬን ይዳስሳል። በተለይም በቅርቡ ላጣችው ወንድሟ ክሪስቶፈር "Fragile" በተሰኘው ዘፈን የመታሰቢያ ክብር ስትሰጥ፣ ከመጀመሪያ ልጇ ሎላ ሊዮን ጋር በጋራ በሰራችው "The Test" በተሰኘው ዘፈን ደግሞ ይቅርታን ትጠይቃለች። "Danceteria" በሚለው ስራዋም በሙዚቃው ዓለም ገና በጀመረችበት አስቸጋሪ ጊዜ አብረዋት የነበሩ ጓደኞቿን ታወድሳለች።
ባለፈው ወር መጨረሻ በቢቢሲ የግራሃም ኖርተን ሾው ላይ በቀረበችበት ወቅት፣ አልበሙን በስቱዲዮ ውስጥ ስትሰራ ስለነበራት ቆይታ ተናግራለች። "በሆነ መንፈስ የተዋጥኩ ያህል ነበር፤ ሀሳቦች የሚመጡት ብዙ ሳልጨነቅ ነው" ያለችው ማዶና፣ እንደ "One Step Away" ያሉት ዘፈኖች ከነፍሷ የመነጩ መሆናቸውን አብራርታለች።
አልበሙ ከመለቀቁ በፊት ኒውዮርክ ታይምስ ስኩዌር ላይ ድንገተኛ ኮንሰርት ያቀረበችው ድምፃዊቷ፣ በትሪቤካ ፌስቲቫል ላይም አጭር ፊልም ለእይታ አብቅታለች። ለዚህ አጭር ፊልም መነሻ ሀሳብ የሰጣት የረጅም ጊዜ ስራ አስኪያጇ ጋይ ኦሴሪ መሆኑን የገለጸችው ማዶና፣ ከዳይሬክተሮች ጋር በመሆን ለስድስት ወራት እንደሰራችበት ተናግራለች።
በመጨረሻም በዚህ የዕድሜ እና የስራ ደረጃ ላይ ሆና ለአድናቂዎቿ የሰጠችው ምክር፦ "አደጋዎችን ለመጋፈጥ አትፍሩ፣ ለማወቅ ጉጉ ሁኑ፣ አስተውሉ፣ እንዲሁም ስልኮቻችሁን አስቀምጣችሁ ከሰዎች ጋር ተገናኙ!" የሚል ነበር።
29 days ago
ዛሬ እና ነገ ታላቅ የፎቶ ኤግዚቢሽንና የሙዚቃ ድግስ ይካሄዳል!
#ethiopia | ዛሬ ሐምሌ 4 እና ነገ ሐምሌ 5 ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ፣ ከፍላሚንጎ ሬስቶራንት ገባ ብሎ በሚገኘው የሕፃናት እና ወጣቶች የቴያትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስ ታላቅ የፎቶ ኤግዚቢሽን እና የሙዚቃ ድግስ ተዘጋጅቷል።
በዝግጅቱ ላይ የተለያዩ የፎቶ ሥራዎች ለዕይታ የሚቀርቡ ሲሆን፣ በሙዚቃ ዝግጅቶችም ታዳሚዎች አስደሳች ቆይታ እንዲያደርጉ ተዘጋጅቷል።
መግቢያ በነፃ ነው!
ይህን ልዩ የጥበብ እና የመዝናኛ መርሃ ግብር እንዳያመልጣችሁ፣ በቦታው በመገኘት ተሳተፉ።
#ethiopia | ዛሬ ሐምሌ 4 እና ነገ ሐምሌ 5 ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ፣ ከፍላሚንጎ ሬስቶራንት ገባ ብሎ በሚገኘው የሕፃናት እና ወጣቶች የቴያትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስ ታላቅ የፎቶ ኤግዚቢሽን እና የሙዚቃ ድግስ ተዘጋጅቷል።
በዝግጅቱ ላይ የተለያዩ የፎቶ ሥራዎች ለዕይታ የሚቀርቡ ሲሆን፣ በሙዚቃ ዝግጅቶችም ታዳሚዎች አስደሳች ቆይታ እንዲያደርጉ ተዘጋጅቷል።
መግቢያ በነፃ ነው!
ይህን ልዩ የጥበብ እና የመዝናኛ መርሃ ግብር እንዳያመልጣችሁ፣ በቦታው በመገኘት ተሳተፉ።
1 month ago
ድምጻዊ ሣሞን ዜማስ «የዘመን ምልክት» የተሰኘ አዲስ አልበሙን ይፋ አደረገ
በኢትዮጵያ የዘመናዊ ሙዚቃ ዓለም ውስጥ ከዝና ይልቅ ለጥበብ ጥራት ቅድሚያ በመስጠት የሚታወቀው ድምጻዊ ሣሞን ዜማስ፣ በሙዚቃ አፍቃሪያን ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን «የዘመን ምልክት» የተሰኘ አዲስ የሙዚቃ አልበሙን በይፋ ለሕዝብ አስተዋወቀ።
ይህ አልበም ድምጻዊው ለሙዚቃ ያለው ጥልቅ ተሰጥኦ እና ለጥራት የማይደራደር አቋም ማሳያ ተደርጎ የተወሰደ ሲሆን፣ በውስጡ 13 በብቃት እና በጥንቃቄ የተሰሩ የሙዚቃ ስራዎችን የያዘ ነው።
የአሁኑን ትውልድ ስሜት፣ ፍቅር፣ ስብራት፣ ተስፋ እና ራስን ፍለጋ በአንድ ላይ አቀናጅቶ የያዘው ይህ የጥበብ መዝገብ፣ ከሙዚቃ ቅንብር እስከ ግጥም ድረስ የትውልዱን የውስጥ ውጊያና ስኬት የሚያንጸባርቁ የጥበብ ፍሬዎችን አካቷል።
የአልበሙን መውጣት ለየት የሚያደርገው፣ ድምጻዊው ለደጋፊዎቹ ያዘጋጃቸው ሁለት ዋና ዋና የሙዚቃ ክሊፖች በአንድ ጊዜ ይፋ መደረጋቸው ነው። በተለይም የአልበሙ መጠሪያ የሆነው «የዘመን ምልክት» እና ተወዳጅነት ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቀው «ንገርዋት» የተሰኙት የሙዚቃ ስራዎች በምስል እና በድምፅ ታጅበው የሙዚቃ ወዳጆችን እይታ ተጋብዘዋል።
ይህንን የትውልድ አሻራ የሚያሳርፍ የሙዚቃ ስራ ለሁሉም አድማጮች ተደራሽ እንዲሆን የተደረገ ሲሆን፣ ሙሉውን የአልበም ይዘት እና አዳዲስ ክሊፖቹን በድምጻዊ ሣሞን ዜማስ ይፋዊ የዩቲዩብ ቻናል መከታተል ይቻላል።
በተጨማሪም በመላው ዓለም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና የሙዚቃ አፍቃሪያን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚታወቁ የሙዚቃ ማዳመጫ ፕላትፎርሞች አማካይነት በማንኛውም ሰዓት እና ቦታ አልበሙን ማዳመጥ ይችላሉ ተብሏል።
ሣሞን ዜማስ «የዘመን ምልክት» የጥበብ ስራ ብቻ ሳይሆን፣ ለትውልዱ የማይደበዝዝ አሻራ ለማሳረፍ የያዘው ታላቅ የጥበብ አዋጅ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ አድማጮች ይህንን የጥበብ ጉዞ አብረው እንዲጋሩ እና በየሙዚቃ መድረኮቹ በመታደም የልባቸው አካል እንዲያደርጉት ጥሪ ቀርቧል።
በኢትዮጵያ የዘመናዊ ሙዚቃ ዓለም ውስጥ ከዝና ይልቅ ለጥበብ ጥራት ቅድሚያ በመስጠት የሚታወቀው ድምጻዊ ሣሞን ዜማስ፣ በሙዚቃ አፍቃሪያን ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን «የዘመን ምልክት» የተሰኘ አዲስ የሙዚቃ አልበሙን በይፋ ለሕዝብ አስተዋወቀ።
ይህ አልበም ድምጻዊው ለሙዚቃ ያለው ጥልቅ ተሰጥኦ እና ለጥራት የማይደራደር አቋም ማሳያ ተደርጎ የተወሰደ ሲሆን፣ በውስጡ 13 በብቃት እና በጥንቃቄ የተሰሩ የሙዚቃ ስራዎችን የያዘ ነው።
የአሁኑን ትውልድ ስሜት፣ ፍቅር፣ ስብራት፣ ተስፋ እና ራስን ፍለጋ በአንድ ላይ አቀናጅቶ የያዘው ይህ የጥበብ መዝገብ፣ ከሙዚቃ ቅንብር እስከ ግጥም ድረስ የትውልዱን የውስጥ ውጊያና ስኬት የሚያንጸባርቁ የጥበብ ፍሬዎችን አካቷል።
የአልበሙን መውጣት ለየት የሚያደርገው፣ ድምጻዊው ለደጋፊዎቹ ያዘጋጃቸው ሁለት ዋና ዋና የሙዚቃ ክሊፖች በአንድ ጊዜ ይፋ መደረጋቸው ነው። በተለይም የአልበሙ መጠሪያ የሆነው «የዘመን ምልክት» እና ተወዳጅነት ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቀው «ንገርዋት» የተሰኙት የሙዚቃ ስራዎች በምስል እና በድምፅ ታጅበው የሙዚቃ ወዳጆችን እይታ ተጋብዘዋል።
ይህንን የትውልድ አሻራ የሚያሳርፍ የሙዚቃ ስራ ለሁሉም አድማጮች ተደራሽ እንዲሆን የተደረገ ሲሆን፣ ሙሉውን የአልበም ይዘት እና አዳዲስ ክሊፖቹን በድምጻዊ ሣሞን ዜማስ ይፋዊ የዩቲዩብ ቻናል መከታተል ይቻላል።
በተጨማሪም በመላው ዓለም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና የሙዚቃ አፍቃሪያን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚታወቁ የሙዚቃ ማዳመጫ ፕላትፎርሞች አማካይነት በማንኛውም ሰዓት እና ቦታ አልበሙን ማዳመጥ ይችላሉ ተብሏል።
ሣሞን ዜማስ «የዘመን ምልክት» የጥበብ ስራ ብቻ ሳይሆን፣ ለትውልዱ የማይደበዝዝ አሻራ ለማሳረፍ የያዘው ታላቅ የጥበብ አዋጅ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ አድማጮች ይህንን የጥበብ ጉዞ አብረው እንዲጋሩ እና በየሙዚቃ መድረኮቹ በመታደም የልባቸው አካል እንዲያደርጉት ጥሪ ቀርቧል።
1 month ago
"ጊዜ አይሄድም" እየመጣ ነው!
ሰላም የምወዳችሁና የማከብራችሁ የጥበብ ቤተሰቦቼና ውድ አድናቂዎቼ!
#ethiopia | ሐምሌ 10 በናሆም ሪከርድስ የማይረሳ ቀጠሮ አለን። በአዲሱ "ጊዜ አይሄድም" ቅጽ 3 አልበሜ ውስጥ ዘፈኖችን ብቻ ሳይሆን የሕይወቴን ተሞክሮ፣ ስሜትና ታሪክ በሙዚቃ ቋንቋ አቅርቤላችኋለሁ።
ይህ ሥራ ወደ እናንተ እንዲደርስ ከመጀመሪያው ጀምሮ ከጎኔ በመቆም ላልተቆጠበ ድጋፍ የናሆም ሪከርድስ ባለቤት አቶ ኤሊያስ ፍቅሩን ከልብ አመሰግናለሁ።
እንዲሁም ድምፃዊና ፕሮዲውሰር ደመላሽ ንጉሴ በዚህ አልበም ላይ በፕሮዲውሰርነት ላደረግኸው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
በግጥም ችሎታችሁ ለአልበሙ ልዩ ውበት ያከላችሁ፤ እልፍአግድ እምሻው፣ ናትናኤል ግርማቸው፣ ከድር አሊ፣ ምልዕቲ ኪሮስ፣ አቡዲ እና ወንድወሰን ይሁብ ሁላችሁንም ብዕራችሁ አይነጥፍ፤ ከልብ አመሰግናለሁ።
በሙዚቃ ቅንብር ደግሞ ለዘፈኖቼ ነፍስ የዘራችሁ፤ ታምሩ አማረ፣ ሚካኤል ሀይሉ (ሚኪ ጃኖ)፣ አንተነህ ተፈራ (አቡዝ)፣ አዲስ ፍቃዱ፣ ፋኑ ጊዳቦ እና ኤርሚያስ በዳዳ ሁላችሁንም በጣም አመሰግናለሁ።
እንዲሁም ሁሉንም ሙዚቃዎቼ በማስተር ሥራ የአለባበሰው ሰለሞን ሀ/ማርያም ላደረግኸው ድንቅ ሙያዊ አስተዋፅኦ ልዩ ምስጋናዬ ይድረስህ።
በአጠቃላይ በዚህ አልበም ጉዞ ላይ በሙያችሁ፣ በሀሳባችሁ እና በማበረታቻችሁ ከጎኔ ለቆማችሁ ወዳጆቼና ባለሙያዎች በሙሉ ከልብ አመሰግናለሁ።
ሐምሌ 10 በናሆም ሪከርድስ እንገናኝ! ከእናንተ ጋር ይህን ልዩ የሙዚቃ ጉዞ ለመጋራት በታላቅ ጉጉት እጠብቃለሁ።
ከፍቅር ጋር፣
አህመድ ተሾመ ( ዲንቢ )
ሰላም የምወዳችሁና የማከብራችሁ የጥበብ ቤተሰቦቼና ውድ አድናቂዎቼ!
#ethiopia | ሐምሌ 10 በናሆም ሪከርድስ የማይረሳ ቀጠሮ አለን። በአዲሱ "ጊዜ አይሄድም" ቅጽ 3 አልበሜ ውስጥ ዘፈኖችን ብቻ ሳይሆን የሕይወቴን ተሞክሮ፣ ስሜትና ታሪክ በሙዚቃ ቋንቋ አቅርቤላችኋለሁ።
ይህ ሥራ ወደ እናንተ እንዲደርስ ከመጀመሪያው ጀምሮ ከጎኔ በመቆም ላልተቆጠበ ድጋፍ የናሆም ሪከርድስ ባለቤት አቶ ኤሊያስ ፍቅሩን ከልብ አመሰግናለሁ።
እንዲሁም ድምፃዊና ፕሮዲውሰር ደመላሽ ንጉሴ በዚህ አልበም ላይ በፕሮዲውሰርነት ላደረግኸው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
በግጥም ችሎታችሁ ለአልበሙ ልዩ ውበት ያከላችሁ፤ እልፍአግድ እምሻው፣ ናትናኤል ግርማቸው፣ ከድር አሊ፣ ምልዕቲ ኪሮስ፣ አቡዲ እና ወንድወሰን ይሁብ ሁላችሁንም ብዕራችሁ አይነጥፍ፤ ከልብ አመሰግናለሁ።
በሙዚቃ ቅንብር ደግሞ ለዘፈኖቼ ነፍስ የዘራችሁ፤ ታምሩ አማረ፣ ሚካኤል ሀይሉ (ሚኪ ጃኖ)፣ አንተነህ ተፈራ (አቡዝ)፣ አዲስ ፍቃዱ፣ ፋኑ ጊዳቦ እና ኤርሚያስ በዳዳ ሁላችሁንም በጣም አመሰግናለሁ።
እንዲሁም ሁሉንም ሙዚቃዎቼ በማስተር ሥራ የአለባበሰው ሰለሞን ሀ/ማርያም ላደረግኸው ድንቅ ሙያዊ አስተዋፅኦ ልዩ ምስጋናዬ ይድረስህ።
በአጠቃላይ በዚህ አልበም ጉዞ ላይ በሙያችሁ፣ በሀሳባችሁ እና በማበረታቻችሁ ከጎኔ ለቆማችሁ ወዳጆቼና ባለሙያዎች በሙሉ ከልብ አመሰግናለሁ።
ሐምሌ 10 በናሆም ሪከርድስ እንገናኝ! ከእናንተ ጋር ይህን ልዩ የሙዚቃ ጉዞ ለመጋራት በታላቅ ጉጉት እጠብቃለሁ።
ከፍቅር ጋር፣
አህመድ ተሾመ ( ዲንቢ )
1 month ago
ደህና ሁኚ
#ethiopia | ታዋቂዋና አንጋፋዋ ድምፃዊት አርቲስት ራሔል ዮሐንስ በ80 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷን ተከትሎ፣ ሥርዓተ ቀብሯ ዛሬ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ በታላቅ ሐዘን ተፈጽሟል። በሕይወት ዘመኗ በሙዚቃው ዓለም ጉልህ አሻራ ያሳረፈችውና በመጨረሻ ዓመታትዋ ራሷን ለመንፈሳዊ አገልግሎት የሰጠችው ይህች ድንቅ አርቲስት፣ በትዳር ሕይወቷ የ6 ልጆች እናት፣ የ14 የልጅ ልጆች እንዲሁም የ5 የልጅ ልጅ ልጆች ባለጸጋ መሆን የቻለች ሲሆን፣ ያበረከተችው በጎነትና የጥበብ ሥራዎቿ ሁልጊዜም ሲታወሱ ይኖራሉ።
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ደብረ ምህረት ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴደራል ዛሬ ቀን ሥርዓተ ቀብሯ ተፈጽሟል።
***
የሕይወት ታሪክ እና የጥበብ ጉዞ
በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ በተለይም በዘመን አይሽሬ (Oldies) እና ባህላዊ ሥራዎቿ የብዙዎችን ልብ የማረከችው አንጋፋዋ ድምፃዊትና የዜማ ደራሲ **አርቲስት ራሔል ዮሐንስ** በተደረገላት የሕክምና እርዳታ ስትረዳ ቆይታ በ80 ዓመቷ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷ ተሰምቷል።
የሕይወት ታሪክ እና የጥበብ ጉዞ
መጋቢት 20 ቀን 1938 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ በገዥኖችን አካባቢ ከአባቷ ከአቶ ዮሐንስ መኮንን እና ከእናቷ ከወ/ሮ ወይንእሸት ጎንፋ ተወለደች።
በአንድ እህትና በሁለት ወንድሞች መካከል በፍቅር አድጋ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በአስፋው ወሰን ትምህርት ቤት፣ ሁለተኛ ደረጃዋን ደግሞ በቀድሞው የኪነ-ጥበብ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠናቃለች።
ወደ ሥራው ዓለም በመግባት በአዲስ አበባ በሚገኙት በጊዮን ሆቴል እና ሒልተን ሆቴል ውስጥ ለብዙ ዓመታት ያገለገለች ሲሆን፣ በፈርስት ኬተሪንግ ኤጀንሲም ለጥቂት ዓመታት ሠርታለች።
ከ1973 ዓ/ም ጀምሮ በሙዚቃው ዓለም ውስጥ በይፋ በመሳተፍ ከ13 በላይ አልበሞችንና በርካታ ነጠላ ዜማዎችን ለሕዝብ አበርክታለች።
በተለይም "አራዳ"፣ "ምኒልክ" እና "ይዳኘኝ ሰው" የተሰኙት ሥራዎቿ በብዙዎች ዘንድ የማይረሱ ድንቅ አሻራዎቿ ናቸው። በኪነ-ጥበብ ጉዞዋም ከበርካታ የኢትዮጵያ አንጋፋ ድምፃውያን ጋር በጋራ ለመሥራት ችላለች።
አርቲስት ራሔል ዮሐንስ ለሀገሯ ያላትን ፍቅር በሥራዎቿ የገለጸች ሲሆን፣ በተለይም ለኢትዮጵያ አየር ኃይል፣ ለባሕር ኃይል እና ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ያቀረበቻቸው ሥራዎቿ ተጠቃሽ ናቸው።
በማኅበራዊ ሕይወቷም ሰውን የምትወድ፣ የምታከብር እና ችግረኞችን በመርዳት የምትታወቅ የብዙዎች "ሩኅሩኅ እናት" ነበረች።
የሕይወት ምዕራፍ ለውጥ እና መንፈሳዊ ሕይወት
በሕይወቷ የመጨረሻዎቹ ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ከዓለማዊ ሙዚቃ በመራቅ፣ ሕይወቷን ለሃይማኖቷና ለመንፈሳዊ አገልግሎት ሰጥታ ነበር።
በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነቷ ጸንታ፣ ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል እስከ ዕለተ ሞቷ ድረስ በጠንካራ መንፈሳዊ ሕይወትና በምስጋና (በመዝሙር) ከፈጣሪዋ ጋር ኖራለች።
አርቲስት ራሔል የ2 ወንድና የ4 ሴት (በድምሩ የ6 ልጆች) እናት፣ የ14 የልጅ ልጆች አያት እንዲሁም የ5 የልጅ ልጅ ልጆች ቅድመ-አያት የመሆንን ትልቅ የቤተሰብ ጸጋ ተጎናጽፋ ነበር።
ሥርዓተ ቀብሯ ዛሬ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በደብረ ምሕረት ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴደራል በ8:00 ሰዓት ላይ ተፈጽሟል።
ቤተሰቦቿ በሕመም ወቅት ለስታመሟት፣ በአካልም ሆነ በስልክ ላጠያቋት እንዲሁም በሥርዓተ ቀብሩ ላይ በድምቀት ለተገኘው ለመከላከያ ሠራዊት ማርች ባንድ በፈጣሪ ስም ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ለቤተሰቦቿ፣ ለአድናቂዎቿና ለመላው የጥበብ አፍቃሪያን መጽናናትን እንመኛለን።
#ethiopia #rahelyohannes #rip #artist #የረገፈች_ጥበብ
#ethiopia | ታዋቂዋና አንጋፋዋ ድምፃዊት አርቲስት ራሔል ዮሐንስ በ80 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷን ተከትሎ፣ ሥርዓተ ቀብሯ ዛሬ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ በታላቅ ሐዘን ተፈጽሟል። በሕይወት ዘመኗ በሙዚቃው ዓለም ጉልህ አሻራ ያሳረፈችውና በመጨረሻ ዓመታትዋ ራሷን ለመንፈሳዊ አገልግሎት የሰጠችው ይህች ድንቅ አርቲስት፣ በትዳር ሕይወቷ የ6 ልጆች እናት፣ የ14 የልጅ ልጆች እንዲሁም የ5 የልጅ ልጅ ልጆች ባለጸጋ መሆን የቻለች ሲሆን፣ ያበረከተችው በጎነትና የጥበብ ሥራዎቿ ሁልጊዜም ሲታወሱ ይኖራሉ።
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ደብረ ምህረት ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴደራል ዛሬ ቀን ሥርዓተ ቀብሯ ተፈጽሟል።
***
የሕይወት ታሪክ እና የጥበብ ጉዞ
በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ በተለይም በዘመን አይሽሬ (Oldies) እና ባህላዊ ሥራዎቿ የብዙዎችን ልብ የማረከችው አንጋፋዋ ድምፃዊትና የዜማ ደራሲ **አርቲስት ራሔል ዮሐንስ** በተደረገላት የሕክምና እርዳታ ስትረዳ ቆይታ በ80 ዓመቷ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷ ተሰምቷል።
የሕይወት ታሪክ እና የጥበብ ጉዞ
መጋቢት 20 ቀን 1938 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ በገዥኖችን አካባቢ ከአባቷ ከአቶ ዮሐንስ መኮንን እና ከእናቷ ከወ/ሮ ወይንእሸት ጎንፋ ተወለደች።
በአንድ እህትና በሁለት ወንድሞች መካከል በፍቅር አድጋ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በአስፋው ወሰን ትምህርት ቤት፣ ሁለተኛ ደረጃዋን ደግሞ በቀድሞው የኪነ-ጥበብ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠናቃለች።
ወደ ሥራው ዓለም በመግባት በአዲስ አበባ በሚገኙት በጊዮን ሆቴል እና ሒልተን ሆቴል ውስጥ ለብዙ ዓመታት ያገለገለች ሲሆን፣ በፈርስት ኬተሪንግ ኤጀንሲም ለጥቂት ዓመታት ሠርታለች።
ከ1973 ዓ/ም ጀምሮ በሙዚቃው ዓለም ውስጥ በይፋ በመሳተፍ ከ13 በላይ አልበሞችንና በርካታ ነጠላ ዜማዎችን ለሕዝብ አበርክታለች።
በተለይም "አራዳ"፣ "ምኒልክ" እና "ይዳኘኝ ሰው" የተሰኙት ሥራዎቿ በብዙዎች ዘንድ የማይረሱ ድንቅ አሻራዎቿ ናቸው። በኪነ-ጥበብ ጉዞዋም ከበርካታ የኢትዮጵያ አንጋፋ ድምፃውያን ጋር በጋራ ለመሥራት ችላለች።
አርቲስት ራሔል ዮሐንስ ለሀገሯ ያላትን ፍቅር በሥራዎቿ የገለጸች ሲሆን፣ በተለይም ለኢትዮጵያ አየር ኃይል፣ ለባሕር ኃይል እና ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ያቀረበቻቸው ሥራዎቿ ተጠቃሽ ናቸው።
በማኅበራዊ ሕይወቷም ሰውን የምትወድ፣ የምታከብር እና ችግረኞችን በመርዳት የምትታወቅ የብዙዎች "ሩኅሩኅ እናት" ነበረች።
የሕይወት ምዕራፍ ለውጥ እና መንፈሳዊ ሕይወት
በሕይወቷ የመጨረሻዎቹ ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ከዓለማዊ ሙዚቃ በመራቅ፣ ሕይወቷን ለሃይማኖቷና ለመንፈሳዊ አገልግሎት ሰጥታ ነበር።
በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነቷ ጸንታ፣ ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል እስከ ዕለተ ሞቷ ድረስ በጠንካራ መንፈሳዊ ሕይወትና በምስጋና (በመዝሙር) ከፈጣሪዋ ጋር ኖራለች።
አርቲስት ራሔል የ2 ወንድና የ4 ሴት (በድምሩ የ6 ልጆች) እናት፣ የ14 የልጅ ልጆች አያት እንዲሁም የ5 የልጅ ልጅ ልጆች ቅድመ-አያት የመሆንን ትልቅ የቤተሰብ ጸጋ ተጎናጽፋ ነበር።
ሥርዓተ ቀብሯ ዛሬ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በደብረ ምሕረት ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴደራል በ8:00 ሰዓት ላይ ተፈጽሟል።
ቤተሰቦቿ በሕመም ወቅት ለስታመሟት፣ በአካልም ሆነ በስልክ ላጠያቋት እንዲሁም በሥርዓተ ቀብሩ ላይ በድምቀት ለተገኘው ለመከላከያ ሠራዊት ማርች ባንድ በፈጣሪ ስም ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ለቤተሰቦቿ፣ ለአድናቂዎቿና ለመላው የጥበብ አፍቃሪያን መጽናናትን እንመኛለን።
#ethiopia #rahelyohannes #rip #artist #የረገፈች_ጥበብ
1 month ago
የአንጋፋዋ ድምፃዊት አርቲስት ራሔል ዮሐንስ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ”
ሀገራችን ካፈራቻቸው እጅግ ድንቅና አንጋፋ ድምፃውያን መካከል አንዷ የሆነችው አርቲስት ራሔል ዮሐንስ በ80 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷን ተከትሎ፣ ሥርዓተ ቀብሯ ዛሬ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ደብረ ምህረት ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴደራል ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ተፈጽሟል።
ሁላችንም አንድ ቀን በምናገኘውና በማይቀረው የሞት መንገድ ቀድማን የተጓዘችው የዚህች ታላቅ ድምፃዊት ሕይወት ማለፍ መላውን የኪነጥበብ ማህበረሰብና የሀገራችንን ሕዝብ በታላቅ ሐዘን ውስጥ ጥሏል።
በሕይወት ዘመኗ በሙዚቃው ዓለም የራሷን ጉልህ አሻራ ማሳረፍ የቻለችው ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ፣ በሕይወቷ የመጨረሻ ዓመታት ላይ ሙሉ በሙሉ ከዓለማዊ ሙዚቃ በመራቅ ራሷን ለመንፈሳዊ አገልግሎትና ለምስጋና መዝሙሮች አውላ እንደነበር ይታወሳል።
በትዳርና በቤተሰብ ሕይወቷም የሁለት ወንድና የአራት ሴት ልጆች እናት ለመሆን የበቃች ሲሆን፣ የ14 የልጅ ልጆች እንዲሁም የ5 የልጅ ልጅ ልጆችን የመሳም ታላቅ የእድሜና የሕይወት ጸጋን አግኝታለች።
ይህች ድንቅ የጥበብ ሰው ዛሬ ምድራዊ ጉዞዋን አጠናቃ ወደ ዘላለማዊ እረፍቷ ብትሸኝም፣ ያበረከተቻቸው ስራዎችና ያሳየችው በጎነት ሁልጊዜም ሲታወሱ ይኖራሉ።
እኛም ለታላቋ ድምፃዊት ቤተሰቦች፣ ለአድናቂዎቿና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፈጣሪ ጽናቱንና መጽናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን።
Nahom Records
ሀገራችን ካፈራቻቸው እጅግ ድንቅና አንጋፋ ድምፃውያን መካከል አንዷ የሆነችው አርቲስት ራሔል ዮሐንስ በ80 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷን ተከትሎ፣ ሥርዓተ ቀብሯ ዛሬ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ደብረ ምህረት ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴደራል ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ተፈጽሟል።
ሁላችንም አንድ ቀን በምናገኘውና በማይቀረው የሞት መንገድ ቀድማን የተጓዘችው የዚህች ታላቅ ድምፃዊት ሕይወት ማለፍ መላውን የኪነጥበብ ማህበረሰብና የሀገራችንን ሕዝብ በታላቅ ሐዘን ውስጥ ጥሏል።
በሕይወት ዘመኗ በሙዚቃው ዓለም የራሷን ጉልህ አሻራ ማሳረፍ የቻለችው ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ፣ በሕይወቷ የመጨረሻ ዓመታት ላይ ሙሉ በሙሉ ከዓለማዊ ሙዚቃ በመራቅ ራሷን ለመንፈሳዊ አገልግሎትና ለምስጋና መዝሙሮች አውላ እንደነበር ይታወሳል።
በትዳርና በቤተሰብ ሕይወቷም የሁለት ወንድና የአራት ሴት ልጆች እናት ለመሆን የበቃች ሲሆን፣ የ14 የልጅ ልጆች እንዲሁም የ5 የልጅ ልጅ ልጆችን የመሳም ታላቅ የእድሜና የሕይወት ጸጋን አግኝታለች።
ይህች ድንቅ የጥበብ ሰው ዛሬ ምድራዊ ጉዞዋን አጠናቃ ወደ ዘላለማዊ እረፍቷ ብትሸኝም፣ ያበረከተቻቸው ስራዎችና ያሳየችው በጎነት ሁልጊዜም ሲታወሱ ይኖራሉ።
እኛም ለታላቋ ድምፃዊት ቤተሰቦች፣ ለአድናቂዎቿና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፈጣሪ ጽናቱንና መጽናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን።
Nahom Records
1 month ago
ተወዳጇ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች
በበርካታ የባህል ሙዚቃ ዜማዎቿ ከፍተኛ አድናቆትን ያገኘችው ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
ድምፃዊቷ ያጋጠማትን የጤና እክል ተከትሎ በሕክምና ስትረዳ ቆይታለች።
ራሔል ዮሐንስ በግሏ እናከተለያዩ ድምፃውያን ጋር በመሆን በርካታ ተወዳጅነት ያገኙ ሙዚቃዎችን ሠርታለች።
በሙዚቃዎቿ ከድምፃዊነቷ ባለፈ፣ በአንዳንዶቹ ላይ በግጥም እና በዜማ ድርሰትም አስተዋፅኦ ታደርግ ነበር።
ራሔል ዮሐንስ ከሠራቻቸው ሙዚቃዎቿ መካከል እንደ "ኢትዮጵያ"፣ "አራዳ"፣ "እንደ ኢየሩሳሌም"፣ "ትዝታ"፣ "አንቺ ባለድሪ"እና "አየር ኃይላችን" የመሳሰሉት ተወዳጅነት አግኝተውላታል።
Seledadotio
Seledadotio
በበርካታ የባህል ሙዚቃ ዜማዎቿ ከፍተኛ አድናቆትን ያገኘችው ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
ድምፃዊቷ ያጋጠማትን የጤና እክል ተከትሎ በሕክምና ስትረዳ ቆይታለች።
ራሔል ዮሐንስ በግሏ እናከተለያዩ ድምፃውያን ጋር በመሆን በርካታ ተወዳጅነት ያገኙ ሙዚቃዎችን ሠርታለች።
በሙዚቃዎቿ ከድምፃዊነቷ ባለፈ፣ በአንዳንዶቹ ላይ በግጥም እና በዜማ ድርሰትም አስተዋፅኦ ታደርግ ነበር።
ራሔል ዮሐንስ ከሠራቻቸው ሙዚቃዎቿ መካከል እንደ "ኢትዮጵያ"፣ "አራዳ"፣ "እንደ ኢየሩሳሌም"፣ "ትዝታ"፣ "አንቺ ባለድሪ"እና "አየር ኃይላችን" የመሳሰሉት ተወዳጅነት አግኝተውላታል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
የሜላት ቀለመወርቅ “መላ መላ” ሙዚቃ ምን አዲስ ነገር ይዞ መጣ?
ጋዜጠኛ መሉቀን አሰን እንደገለጸው፣ ድምፃዊት ሜላት ቀለመወርቅ በብስራት ሱራፌል ዜማና በምልዕቲ ኪሮስ ግጥም የቀረበው “መላ መላ” ከተለመዱ የሙዚቃ ስራዎች የሚለየው በሶስት ዋና ጉዳዮች ነው።
1. የሙሉ ባንድ አቀራረብ
በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ስም ያተረፉ ሙዚቀኞችን በአንድ መድረክ ማሰባሰብ ስራውን ልዩ አድርጎታል።
የሙዚቀኞቹ የመድረክ አለባበስ፣ ሙያዊ ሥነ-ምግባር እና በሙዚቃው ውስጥ በደስታ መሳተፋቸው የድሮውን የኢትዮጵያ የሙዚቃ ዘመን አስታውሷል።
2. የሜላት ቀለመወርቅ ብቃት
በስቱዲዮ ሳይሆን በቀጥታ ከመድረክ መዘፈኗ የድምፅ አቅሟን በግልጽ አሳይታለች።
ከባንዱ ጋር ያሳየችው መግባባት፣ የመድረክ አያያዝና አለባበሷ ስራውን የበለጠ ማራኪ አድርጎታል።
3. የምስልና ድምፅ ጥራት
የድምፅ ቀረፃው ጥራት ንጹህና ሙያዊ መሆኑ ተደንቋል።
የቪዲዮው ቀረፃ በተለያዩ የካሜራ አንግሎችና በጥሩ ኤዲቲንግ የተደገፈ በመሆኑ የእይታ ልምዱን ከፍ አድርጎታል።
መደምደሚያ “መላ መላ” የሙዚቃ ስራ ከመዝናኛነት በላይ ሙያዊ ጥራት፣ የመድረክ ክብር፣ የባንድ ባህል እና የቀጥታ አቀራረብን ያጣመረ ስራ እንደሆነ ተገልጿል። ለአዲሱ ትውልድ ድምፃውያን፣ ሙዚቀኞችና የፕሮዳክሽን ባለሙያዎች ጥራት ያለው ስራ ለመፍጠር አበረታች ምሳሌ መሆኑ ተጠቅሷል።
1 month ago
🇨🇦 በቫንኩቨር፣ ካናዳ ልዩ የመዝናኛ ዝግጅት
Live in Vancouver, Canada!
📅 Date: July 25
📍 Venue: Taj Park
📍 Address: 8580 – 132 Street, Vancouver, BC
✨ Join 3 Arada Entertainment for an unforgettable evening filled with great entertainment, music, and an amazing atmosphere.
Don't miss this special event—bring your family and friends for a memorable night!
For tickets and more information:
+1 (780) 876‑7343
See you on July 25 at Taj Park! 🇨🇦
Arada Entertainment Presents
🎉 3 አራዳ ኢንተርቴይንመንት ያቀርባል!
🇨🇦 በቫንኩቨር፣ ካናዳ ልዩ የመዝናኛ ዝግጅት
📅 ቀን: ጁላይ 25
📍 ቦታ: ታጅ ፓርክ (Taj Park)
📍 አድራሻ: 8580 – 132 Street, Vancouver, BC
✨ በ3 አራዳ ኢንተርቴይንመንት የተዘጋጀውን ይህን ልዩ የመዝናኛ ምሽት አያምልጥዎ!
በሙዚቃ፣ በመዝናኛ እና በደስታ የተሞላ ድንቅ ምሽት ይጠብቅዎታል። ከቤተሰብዎና ከወዳጆችዎ ጋር በመገኘት የማይረሳ ጊዜ ያሳልፉ።
ለተጨማሪ መረጃና ትኬት:
+1 (780) 876‑7343)
በጁላይ 25 በታጅ ፓርክ እንገናኝ! 🇨🇦🎤
1 month ago
የሜላት ቀለመወርቅ “መላ መላ” ሙዚቃ ምን አዲስ ነገር ይዞ መጣ?
#ethiopia | ጋዜጠኛ መሉቀን አሰን እንደገለጸው፣ ድምፃዊት ሜላት ቀለመወርቅ በብስራት ሱራፌል ዜማና በምልዕቲ ኪሮስ ግጥም የቀረበው “መላ መላ” ከተለመዱ የሙዚቃ ስራዎች የሚለየው በሶስት ዋና ጉዳዮች ነው።
1. የሙሉ ባንድ አቀራረብ
በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ስም ያተረፉ ሙዚቀኞችን በአንድ መድረክ ማሰባሰብ ስራውን ልዩ አድርጎታል።
የሙዚቀኞቹ የመድረክ አለባበስ፣ ሙያዊ ሥነ-ምግባር እና በሙዚቃው ውስጥ በደስታ መሳተፋቸው የድሮውን የኢትዮጵያ የሙዚቃ ዘመን አስታውሷል።
2. የሜላት ቀለመወርቅ ብቃት
በስቱዲዮ ሳይሆን በቀጥታ ከመድረክ መዘፈኗ የድምፅ አቅሟን በግልጽ አሳይታለች።
ከባንዱ ጋር ያሳየችው መግባባት፣ የመድረክ አያያዝና አለባበሷ ስራውን የበለጠ ማራኪ አድርጎታል።
3. የምስልና ድምፅ ጥራት
የድምፅ ቀረፃው ጥራት ንጹህና ሙያዊ መሆኑ ተደንቋል።
የቪዲዮው ቀረፃ በተለያዩ የካሜራ አንግሎችና በጥሩ ኤዲቲንግ የተደገፈ በመሆኑ የእይታ ልምዱን ከፍ አድርጎታል።
መደምደሚያ “መላ መላ” የሙዚቃ ስራ ከመዝናኛነት በላይ ሙያዊ ጥራት፣ የመድረክ ክብር፣ የባንድ ባህል እና የቀጥታ አቀራረብን ያጣመረ ስራ እንደሆነ ተገልጿል። ለአዲሱ ትውልድ ድምፃውያን፣ ሙዚቀኞችና የፕሮዳክሽን ባለሙያዎች ጥራት ያለው ስራ ለመፍጠር አበረታች ምሳሌ መሆኑ ተጠቅሷል።
1 month ago
የአዲስ አበባ ሯጮች በአፍሪካ እምብርት ላይ በሚካሄድ ማራቶን ላይ እንዲሳተፉ ግብዣ ቀረበ
#ethiopia | በኢትዮዽያ ሩጫ ከስፖርት በላይ ነው ፤ ሩጫ የሀገር ኩራት፣ የጋራ በዓል፣ የጤና ፣ የህብረተሰብ ትስስር እና የነፍስ ደስታ ነው።
በአፍሪካ ዕምብርቷ ኡጋንዳም ተመሳሳይነት ያለውን ስሜት ለመጋራት፣ ታላቁ ሩጫ በኢትዮዽያ ከተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን ጋር በመተባበር ለሩጫ ወዳጆች ጥሪን አቅርቧል።
ኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ የምስራቅ አፍሪካን ተራራማ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ እያንዳንዱን የሩጫ ውድድር ወደ ታላቅ በዓል የመቀየር ተመሳሳይ ባህል አላቸው። ከአዲስ አበባ ለሚሄዱ ሯጮች በካሴሴ የሚስተዋለው የባህል ድባብ፣ ሙዚቃ እና የህዝብ አቀባበል እንደ ቤት እንዲሰማ የሚያደርግ የቅርብነት ስሜት አለው።
በሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ፣ በእንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ ላይ የሚሳተፉ እና ሌሎችም የሩጫ አፍቃሪያን፣ ያንኑ የሩጫ መንፈስ በመያዝ ከሀገር ውጪ በመጓዝ ውድድሩን እንዲቀላቀሉ እንጋብዛለን።
ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. በኡጋንዳ፣ ካሴሴ ከተማ የሚካሄደው ተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን፣ ከአዲስ አበባ የባህር ዛፍ ጠረን ካለው ቀዝቃዛ አየር ወደ ሳቫናው ግርማ ሞገስ እና ወደ ሩዌንዞሪ ተራሮች ግርጌ የሚያደርጉት ልዩ የሩጫ ጉዞ ነው። በኢትዮጵያ የክረምቱ ዝናብና ቅዝቃዜ ሲጠነከር፣ በዩጋንዳ ካሴሴ ደግሞ ሞቅ ያለ ፀሐይና የኢኩዌተር መስመር ላይ የሚደረግ ውድድር ይጠብቅዎታል።
የተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን የዓለም አትሌቲክስ ሌብል (World Athletics Label Road Race) ደረጃ ያለዉ ዉድድር ነዉ። ይህም በአትሌቶች ጥራት እና በአደረጃጀት በዓለም ላይ ካሉ ምርጥ 200 ውድድሮች አንዱ ያደርገዋል። በውድድሩ ከማራቶን በተጨማሪ በ5 ኪ.ሜ.፣ 10 ኪ.ሜ.፣ እና 21 ኪ.ሜ . (ግማሽ ማራቶን) መሳተፍ ይችላሉ።
የሩጫው መስመር በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ በሆነው የንግስት ኤልሳቤጥ ብሔራዊ ፓርክ ይጀምራል። በከበሮና በሙዚቃ በምትደምቀው የካሴሴ ከተማ መንገዶች አድርጎ፣ በበረዶ በተሸፈኑት የሩዌንዞሪ ተራሮች ግርጌ በሚገኘው አስደናቂው የኪሌምቤ ሸለቆ ይዘልቃል። ማጠናቀቂያው ላይ ሲደርሱ፣ ከኋላዎ የተዘረጋው ግዙፍ የተራራ ሰንሰለት ለእርስዎ የሚሰጠው ስሜት ምን ያህል ድንቅ እንደሆነ በራስዎ ይመሰክራሉ።
እንዴት መመዝገብ ይቻላል?
ይህንን ታላቅ የሩጫ በዓል ለመቀላቀል እና በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ፣ አሁኑኑ ከዚህ በታች በተቀመጠው ድረ-ገጽ አማካኝነት በመግባት መመዝገብ ይችላሉ።
www.rwenzorimarathon.com/r...
#ethiopia | በኢትዮዽያ ሩጫ ከስፖርት በላይ ነው ፤ ሩጫ የሀገር ኩራት፣ የጋራ በዓል፣ የጤና ፣ የህብረተሰብ ትስስር እና የነፍስ ደስታ ነው።
በአፍሪካ ዕምብርቷ ኡጋንዳም ተመሳሳይነት ያለውን ስሜት ለመጋራት፣ ታላቁ ሩጫ በኢትዮዽያ ከተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን ጋር በመተባበር ለሩጫ ወዳጆች ጥሪን አቅርቧል።
ኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ የምስራቅ አፍሪካን ተራራማ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ እያንዳንዱን የሩጫ ውድድር ወደ ታላቅ በዓል የመቀየር ተመሳሳይ ባህል አላቸው። ከአዲስ አበባ ለሚሄዱ ሯጮች በካሴሴ የሚስተዋለው የባህል ድባብ፣ ሙዚቃ እና የህዝብ አቀባበል እንደ ቤት እንዲሰማ የሚያደርግ የቅርብነት ስሜት አለው።
በሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ፣ በእንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ ላይ የሚሳተፉ እና ሌሎችም የሩጫ አፍቃሪያን፣ ያንኑ የሩጫ መንፈስ በመያዝ ከሀገር ውጪ በመጓዝ ውድድሩን እንዲቀላቀሉ እንጋብዛለን።
ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. በኡጋንዳ፣ ካሴሴ ከተማ የሚካሄደው ተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን፣ ከአዲስ አበባ የባህር ዛፍ ጠረን ካለው ቀዝቃዛ አየር ወደ ሳቫናው ግርማ ሞገስ እና ወደ ሩዌንዞሪ ተራሮች ግርጌ የሚያደርጉት ልዩ የሩጫ ጉዞ ነው። በኢትዮጵያ የክረምቱ ዝናብና ቅዝቃዜ ሲጠነከር፣ በዩጋንዳ ካሴሴ ደግሞ ሞቅ ያለ ፀሐይና የኢኩዌተር መስመር ላይ የሚደረግ ውድድር ይጠብቅዎታል።
የተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን የዓለም አትሌቲክስ ሌብል (World Athletics Label Road Race) ደረጃ ያለዉ ዉድድር ነዉ። ይህም በአትሌቶች ጥራት እና በአደረጃጀት በዓለም ላይ ካሉ ምርጥ 200 ውድድሮች አንዱ ያደርገዋል። በውድድሩ ከማራቶን በተጨማሪ በ5 ኪ.ሜ.፣ 10 ኪ.ሜ.፣ እና 21 ኪ.ሜ . (ግማሽ ማራቶን) መሳተፍ ይችላሉ።
የሩጫው መስመር በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ በሆነው የንግስት ኤልሳቤጥ ብሔራዊ ፓርክ ይጀምራል። በከበሮና በሙዚቃ በምትደምቀው የካሴሴ ከተማ መንገዶች አድርጎ፣ በበረዶ በተሸፈኑት የሩዌንዞሪ ተራሮች ግርጌ በሚገኘው አስደናቂው የኪሌምቤ ሸለቆ ይዘልቃል። ማጠናቀቂያው ላይ ሲደርሱ፣ ከኋላዎ የተዘረጋው ግዙፍ የተራራ ሰንሰለት ለእርስዎ የሚሰጠው ስሜት ምን ያህል ድንቅ እንደሆነ በራስዎ ይመሰክራሉ።
እንዴት መመዝገብ ይቻላል?
ይህንን ታላቅ የሩጫ በዓል ለመቀላቀል እና በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ፣ አሁኑኑ ከዚህ በታች በተቀመጠው ድረ-ገጽ አማካኝነት በመግባት መመዝገብ ይችላሉ።
www.rwenzorimarathon.com/r...
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ለድምፃዊ ኤልያስ ገዛኸኝ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ እና የገንዘብ ሽልማት አበረከተ
በ22ኛው ዙር የፋና ላምሮት የድምፅ ውድድር 3ኛ ደረጃን ይዞ ላጠናቀቀው ወጣት ድምፃዊ ኤልያስ ገዛኸኝ በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ደማቅ አቀባበል ተደርጓል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የካፋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ እንደተናገሩት፣ ኤልያስ ለህዝብ በኪነ ጥበብ ዘርፍ የባህል እሴት ግንባታ ያበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ገልፀዋል ።
የአካባቢው ማኅበረሰብ በተፈጥሮው የታመመን የመጠየቅ፣ በደስታ አብሮ የመደሰት፣ በሞትና በችግር ጊዜ ደግሞ የመረዳዳትና የማዘን ትልቅ ባህላዊ እሴትና ፍቅር ያለው መሆኑንም ነው አቶ እንዳሻው።
አቶ እንዳሻው ወደፊት በሙዚቃው ዓለም ያሉ የጥበብ በሮች በራስ አቅም እና ጥበብ እንዲከፈቱ ተጨማሪ የብርታት ድምጽ ለመሆን የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸው የእንኳን ደስ አለህ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በዚህም በዞን መንግስት ስም የ300,000 ብር የገንዘብ ሽልማት ተሰጥቶታል።
የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶክተር ተክለዓብ ቡሎ በበኩላቸው በማንኛውም የህይወት ጉዞ ውስጥ ከባድ ፈተናዎች እና ተስፋ የሚያስቆርጡ ተራራዎች ሊገጥሙ እንደሚችሉ ጠቁመው፣ በእንደዚህ አይነት ወቅቶች "አለሁልህ፣ አይዞህ" የሚል አጋዥ ድምጽ ማግኘት ፈተናዎችን ወደ ሜዳ በመቀየር ህልምን ለማሳካት ትልቅ አቅም እንደሚሆን አስገንዝበዋል።
የኤልያስ ስኬት በራስ ጥረት ትልቅ ደረጃ መድረስ እንደሚቻል ለወጣቶች ያሳየ መሆኑን ገልጸው አካባቢውን ለማስተዋወቅ ላበረከተው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበው ይበልጥ ጠንክሮ እንዲሰራ አሳስበዋል።
ድምፃዊው ለከተማዋ የገነባውን መልካም ስም በማድነቅ የ500 ካ.ሜ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ስጦታ አበርክተውለታል።
በዚሁ መርሃ ግብር ወጣቶችን ለማብቃት ላደረጉት አስተዋጽኦ መምህር ወሰናቸው አጥናፌ ከዞን መንግስት የ200,000 ብር እንዲሁም ከከተማ አሰተዳደር መንግስት የአንድ መቶ ሀምሳ ሺ ብር የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በ22ኛው ዙር የፋና ላምሮት የድምፅ ውድድር 3ኛ ደረጃን ይዞ ላጠናቀቀው ወጣት ድምፃዊ ኤልያስ ገዛኸኝ በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ደማቅ አቀባበል ተደርጓል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የካፋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ እንደተናገሩት፣ ኤልያስ ለህዝብ በኪነ ጥበብ ዘርፍ የባህል እሴት ግንባታ ያበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ገልፀዋል ።
የአካባቢው ማኅበረሰብ በተፈጥሮው የታመመን የመጠየቅ፣ በደስታ አብሮ የመደሰት፣ በሞትና በችግር ጊዜ ደግሞ የመረዳዳትና የማዘን ትልቅ ባህላዊ እሴትና ፍቅር ያለው መሆኑንም ነው አቶ እንዳሻው።
አቶ እንዳሻው ወደፊት በሙዚቃው ዓለም ያሉ የጥበብ በሮች በራስ አቅም እና ጥበብ እንዲከፈቱ ተጨማሪ የብርታት ድምጽ ለመሆን የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸው የእንኳን ደስ አለህ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በዚህም በዞን መንግስት ስም የ300,000 ብር የገንዘብ ሽልማት ተሰጥቶታል።
የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶክተር ተክለዓብ ቡሎ በበኩላቸው በማንኛውም የህይወት ጉዞ ውስጥ ከባድ ፈተናዎች እና ተስፋ የሚያስቆርጡ ተራራዎች ሊገጥሙ እንደሚችሉ ጠቁመው፣ በእንደዚህ አይነት ወቅቶች "አለሁልህ፣ አይዞህ" የሚል አጋዥ ድምጽ ማግኘት ፈተናዎችን ወደ ሜዳ በመቀየር ህልምን ለማሳካት ትልቅ አቅም እንደሚሆን አስገንዝበዋል።
የኤልያስ ስኬት በራስ ጥረት ትልቅ ደረጃ መድረስ እንደሚቻል ለወጣቶች ያሳየ መሆኑን ገልጸው አካባቢውን ለማስተዋወቅ ላበረከተው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበው ይበልጥ ጠንክሮ እንዲሰራ አሳስበዋል።
ድምፃዊው ለከተማዋ የገነባውን መልካም ስም በማድነቅ የ500 ካ.ሜ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ስጦታ አበርክተውለታል።
በዚሁ መርሃ ግብር ወጣቶችን ለማብቃት ላደረጉት አስተዋጽኦ መምህር ወሰናቸው አጥናፌ ከዞን መንግስት የ200,000 ብር እንዲሁም ከከተማ አሰተዳደር መንግስት የአንድ መቶ ሀምሳ ሺ ብር የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
1 month ago
ያልተዘመረለት ጀግና!
* በኢትዮጵያ 30 ትምህርት ቤት አስገንብቷል
***
የአቶ አዲስ ገሠሠ አጭር የሕይወት ታሪክ
#ethiopia | አቶ አዲስ ገሰሰ ከአባታቸው ከግራዝማች ገሰሰ መንገሻ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ አስናቀች መልሴ ጥር 8 ቀን 1945 ዓ.ም. በቀድሞው ኢሊባቦር ጠቅላይ ግዛት ጎሬ ከተማ ተወለዱ፡፡
እስከ 9ነኛ ክፍል በጎሬ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ት/ቤት ከተማሩ በኋላ፤ የ10ኛ ክፍል ትምህርታቸውን አዲስ አበባ በዳግማዊ ምንሊክ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተምረው፤ ወደ ጅማ በመሄድ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሚያዝያ 27 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በህይወታቸው ትልቅ ቦታ የሚሰጡትና “ ስብዕናዬን በዲሲፕሊን ገንብቶታል” የሚሉትን የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በ1961 ዓ.ም. በመቀላቀል ከወታደራዊ ስልጠና ጋር በበረራ ቴክኒሻንነት ተመርቀዋል፡፡
በሙያቸው አንድ ዓመት ካገለገሉ በኋላ፤ በ1964 ዓ.ም. ነፃ የትምህርት እድል በማግኘታቸው ወደ አሜሪካ ሀገር ሺካጎ ከተማ በማቅናት በራንቱል ኤርፎርስ ቤዝ፤ እና በቴክሳስ ላክላንድ ኤርፎርስ ቤዝ ትምህርታቸውን አጠናቀው ተመርቀዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በወጣትነት ዘመናቸው ያን ጊዜ ሉፕ ኮሌጅ በሚባለው ሃሮልድ ዋሺንግተን ዩኒቨርሲቲ የሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ በመቀጠልም በኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይ ዩኒቨርሲቲ በማኔጅመንት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ወንድሞቻቸውን ሙሉጌታ ገሰሰን፤ ዘለቀ ገሰሰንና ጓደኞቻቸውን እነ መላኩ ረታን ወደ ሺካጎ ካመጡ በኋላ ዳሎል ባንድን መስርተዋል፡፡ አቶ አዲስ ገሰሰ በሚማሩበት ኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር ታሪክ ወር /Black History Month/ በሚል መጠሪያ በየዓመቱ የካቲት ወር ላይ በተለያየ መዘክር በሚከበር በዓል ላይ፤ ዳሎል ባንድ ሙዚቃ እንዲያቀርብ በማስቻል የሙዚቃ ማኔጅመንት የህይወት ጉዟቸውን ሀ ብለው ጀመሩ፡፡
በመቀጠልም ዳሎል ባንድን ይዘው በዋሺንግተን፤ በሎስ አንጀለስ እና በመላው አሜሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ለኢትዮጵያውያን-በኢትዮጵያ ባንድ የሙዚቃ ኮንሰርት በማቅረብ ፈር ቀዳጅ እና ውጤታማ ስራ ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ሙዚቃን ማኔጅ በማድረግ ጉዟቸው የእውቁን የሬጌ ሙዚቃ ንጉስ የቦብ ማርሌን ቤተሰብ ሃብትና ንብረቱን በማስተዳደር ብቻ ሳይሆን፤ የቦብን ልጆች በስነ ምግባር ኮትኮቶ ለማሳደግ ከአሜሪካ ኒውዮርክ -ጃማይካ ኪንግስተን እየተመላለሱ በትጋትና በታማኝነት ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡
በዚያን ጊዜም ዘመን አይሽሬውን የቦብ ማርሌይ “ሌጀንድ አልበም" እንዲሰራ ባቀረቡት ንድፈ-ሃሳብ መሰረት ከአይላንድ ሪከርዲንግ ጋር በመፈራረም ውጤማ ስራ ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በቦብ ማርሌይ ቤተሰቦች የተዘጋጁትንና ከምድር ዳር እስከ ምድር ዳር ድረስ የተደረጉትን ዓለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ ኮንሰርቶች ሃሳብ ከመጠንሰስ ጀምሮ ለሃያ ሁለት ዓመታት ያክል ስራውን በሃላፊነት መርተዋል፡፡ አስተዳድረዋል፡፡
በዚሁ የአስተዳደር ዘመናቸው በዘረጉት መንገድ እስካሁን ድረስ በየዓመቱ የሚደረገውን ዓለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ ፌስቲቫል በማይናወጥ መሰረት ላይ አፅንተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ዚጊ ማርሌይን ከጃማይካ… የነዘለቀን ገሰሰን ዳሎል ባንድ ደግሞ ከሺካጎ ወደኒዮርክ በማምጣት ካጣመሩ በኋላ ፤ ከሲግማ ስቱዲዮ እና ከቨርጂኒያ ሪከርድስ ጋር ውል በመፈራረም በአሜሪካ ምድር ቁጥር አንድ ተደማጭ የነበረውን ኮንሺየስ ፓርቲ አልበም እንዲለቀቅ አድርገዋል፡፡
በአልበሙ ከተካተቱት ስራዎች መካከል ቱሞሮ ፒውፕል የተሰኘው ሙዚቃ በዓለም ላይ እጅግ ከመወደዱ የተነሳ ብዙዎች እንደ ብሔራዊ መዝሙር ያዜሙት ነበር፡፡
በአቶ አዲስ ገሰሰ ማናጀርነት በተመራው በዚሁ የሙዚቃ አልበም ዚጊ ማርሌይ የአሜሪካንን ትልቁን ግራሚ አዋርድ ሽልማት ሲያገኝ፤ የኢትዮጵያው ዳሎል ባንድ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ባንድ የግራሚ ሽልማት እንዲወስድ በማስቻል ታሪክ የማይረሳውን ስራ ሰርተዋል፡፡
ለሀገራቸው ኢትዮጵያ የተለየ ፍቅር የነበራቸው አቶ አዲስ ገሰሰ ከወንድማቸው ከአርቲስት ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን የቦብ ማርሊ 60ኛ ዓመት የልደት በዓሉን ለመዘከር የሚዘጋጀውን “አፍሪካ ዩናይት” ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ዝግጅት ኢትዮጵያን መዳረሻ በማድረግና አንድ አመት የፈጀ የዘመቻ /ካምፔይን/ በመስራት ፤ በ1997 ዓ.ም. መስቀል አደባባይ የተካሄደውን የሙዚቃ ፌስቲቫል ስኬታማ እንዲሆን አስችለዋል፡፡ በዚሁ ፌስቲቫል ላይ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ጨምሮ ሪታ ማርሌይና አምስቱ የቦብ ልጆች ተገኝተዋል፡፡
ይኸው ፌስቲቫል በፈጠረው መልካም አጋጣሚም ሀገራችንን በዓለም ዙሪያ ለማስተዋወቅ፤ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግና ኢንቨስመንት ለመሳብ በማለም ከ50 በላይ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን ጋብዘው የራሳቸውን የዜግነት ድርሻ ተወጥተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንት የሕይወት ጉዟቸው ያካበቱትን እውቀትና ልምድ ተጠቅመው ተሰጥዎ ያላቸውን ልጆች በመቃኘት ሀገራቸውን በሙዚቃው ኢንደስትሪ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ትልቅ ህልም ነበራቸው፡፡ ለዚህም ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮን/ከመጀመሪያው አልበሙ ጀምሮ ማኔጅመንቱን በመያዝ ፤ እንዲሁም እጅጋየው ሽባባው /ጂጂን/ ከአጋራቸው ፓልም ሪከርዲንግ ጋር በመሆን ተወዳጅ የሆነ አልበሟን እንድተሰራ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ነው፡፡
ይሄም ብቻ ሳይሆን ጃኖ ባንድን በመመስረት ለልጆቹ ውጤታማነት አቶ አዲስ ገሰሰ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ፡፡ አቶ አዲስ “ጃናናይት” የተባለ ተሰጥዎ ያላቸውን ሴቶች የያዘ ባንድ መስርተው ስኬታማ ለማድረግ ያደረጉት ጥረትም የሚወሳ ነው፡፡
በሙዚቃ ኢንዱስትሪው- እጅግ ገዝፈው፤ በተለያየ የአድናቆት ቃል የሚጠሩት አቶ አዲስ ገሰሰ ከሀገራችን ውጪ እንደ ዚጊ ማርሌ፤ ስቴፈን ማርሌ፤ ሎረን ሂል፣ ፊል ኮሊንስ፣ ኧርዝ ዊንድ ኤንድ ፋየር እና ሌሎችንም በርካታ የሙዚቃ ከዋክብትን በማግኘትና በማስተዳደር በዓለም አቀፍ ደረጃ የብዙ ታላላቅ የሙዚቃ ሰዎች ስራን መስመር አሲዘዋል።
አቶ አዲስ ገሰሰ መደበኛ መኖሪያቸውን ወደ ኢትዮጵያ ካዞሩ በኋላ በሆቴሊንግ ዘርፍ በመሰማራት ላየንስ ዴን ሆቴልን፤ በማእድን ዘርፍም ዩኒቨርሳል ማይኒንግን፤ በግብርና መስክ አድሶጌት ኩባንያን በማቋቋም ለሀገራቸው እድገት ቀን ከሌት ያለእረፍት ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንትና በኢንቨስትመንት ስራቸው ብቻ ሳይሆን በበጎ አድራጎታቸውም አርአያነት ያለው ተግባር ፈፅመዋል፡፡ በግል ከደገፏቸው ግለሰቦች በተጨማሪ በሀገራችን በተለያዩ ወቅቶች በተፈጠሩ ሰብአዊ ችግሮች ቀድመው በመድረስ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ነው፡፡
በዋናነትም ከወንድማቸው ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን በተለያዩ ገጠራማ አካባቢዎች 30 ትምህርት ቤቶችን አሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ስለእነኚሁ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ስላሰሯቸው 30 ትምህርት ቤቶች ሲናገሩ “ተስፋ ሳልቆርጥ በፅናት የታገልኩበት በጎ ተግባር በመሆኑ ያስደስተኛል” ይሉ ነበር፡፡
ቤተ-ክርስቲያን በጠራቻቸው ጊዜ ሁሉ እየተገኙም በመላው ኢትዮጵያ አዳዲስ ቤተክርስቲያኖችን በማሰራት ፤ የተጎዱ ገዳማትንና ቤተክርስቲያኖችን በማደስ ፤ የተዘጉ ቤተክርስቲያኖችን በማስከፈት፤ የቤተክርስቲያኖችን ንዋየ ቅዱሳን በማሟላትና የካህናት ደሞዝን በመክፈል እስከ ህይወት ፍፃሜያቸው ድረስ ድምፃቸውን አጥፍተው አገልግለዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በማህበራዊ ህይወታቸው ቀልድ አዋቂ፤ ተጫዋች እና በቀላሉ ከሰዎች ጋር ተግባብተው የመኖር ፀጋ የነበራቸው ሲሆን ከሁሉም ግን ሰው አካባሪ እና ስነ-ምግባር ያለው ቀረቤታቸው ተወዳጅና በሰው ልብ አይረሴ አድርጓቸዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ከወ/ሮ ሶስና ሽፈራው ጋር በነበራቸው የፀና ትዳር አንድ ወንድና አንዲት ሴት ልጅ አፍርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ፤ በአሜሪካ ሀገር ኒውጄርሲ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡
የቀብር ሥነ ስርዓቱ ዛሬ፣ ሰኔ 20 ቀን 2018ዓ.ም በ6:00 ሰዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።
አቶ አዲስ ገሰሰን ከአጠገቡ ሳትለዩ ላስታመማችሁትና ለጠየቃችሁት ወዳጅ ዘመዶች ልዑል እግዚአብሔር ብድራችሁን ይከፈላችሁ፡፡
የአቶ አዲስ ገሰሰን ነፍስ ልዑል እግዚአብሔር በአፀደ ገነት ከደጋጎቹ አብርሃም ይስሐቅ እና ያቆብ ጎን ያሳርፍልን፡፡
ለቤተሰቡ፤ ለወዳጆቹ፤ ለዘመዶቹ፤ ለሙያ አጋሮቹ፤ ለአድናቂዎቹ ሁሉ መፅናናቱን ይስጣቸው፡፡
* በኢትዮጵያ 30 ትምህርት ቤት አስገንብቷል
***
የአቶ አዲስ ገሠሠ አጭር የሕይወት ታሪክ
#ethiopia | አቶ አዲስ ገሰሰ ከአባታቸው ከግራዝማች ገሰሰ መንገሻ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ አስናቀች መልሴ ጥር 8 ቀን 1945 ዓ.ም. በቀድሞው ኢሊባቦር ጠቅላይ ግዛት ጎሬ ከተማ ተወለዱ፡፡
እስከ 9ነኛ ክፍል በጎሬ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ት/ቤት ከተማሩ በኋላ፤ የ10ኛ ክፍል ትምህርታቸውን አዲስ አበባ በዳግማዊ ምንሊክ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተምረው፤ ወደ ጅማ በመሄድ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሚያዝያ 27 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በህይወታቸው ትልቅ ቦታ የሚሰጡትና “ ስብዕናዬን በዲሲፕሊን ገንብቶታል” የሚሉትን የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በ1961 ዓ.ም. በመቀላቀል ከወታደራዊ ስልጠና ጋር በበረራ ቴክኒሻንነት ተመርቀዋል፡፡
በሙያቸው አንድ ዓመት ካገለገሉ በኋላ፤ በ1964 ዓ.ም. ነፃ የትምህርት እድል በማግኘታቸው ወደ አሜሪካ ሀገር ሺካጎ ከተማ በማቅናት በራንቱል ኤርፎርስ ቤዝ፤ እና በቴክሳስ ላክላንድ ኤርፎርስ ቤዝ ትምህርታቸውን አጠናቀው ተመርቀዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በወጣትነት ዘመናቸው ያን ጊዜ ሉፕ ኮሌጅ በሚባለው ሃሮልድ ዋሺንግተን ዩኒቨርሲቲ የሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ በመቀጠልም በኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይ ዩኒቨርሲቲ በማኔጅመንት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ወንድሞቻቸውን ሙሉጌታ ገሰሰን፤ ዘለቀ ገሰሰንና ጓደኞቻቸውን እነ መላኩ ረታን ወደ ሺካጎ ካመጡ በኋላ ዳሎል ባንድን መስርተዋል፡፡ አቶ አዲስ ገሰሰ በሚማሩበት ኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር ታሪክ ወር /Black History Month/ በሚል መጠሪያ በየዓመቱ የካቲት ወር ላይ በተለያየ መዘክር በሚከበር በዓል ላይ፤ ዳሎል ባንድ ሙዚቃ እንዲያቀርብ በማስቻል የሙዚቃ ማኔጅመንት የህይወት ጉዟቸውን ሀ ብለው ጀመሩ፡፡
በመቀጠልም ዳሎል ባንድን ይዘው በዋሺንግተን፤ በሎስ አንጀለስ እና በመላው አሜሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ለኢትዮጵያውያን-በኢትዮጵያ ባንድ የሙዚቃ ኮንሰርት በማቅረብ ፈር ቀዳጅ እና ውጤታማ ስራ ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ሙዚቃን ማኔጅ በማድረግ ጉዟቸው የእውቁን የሬጌ ሙዚቃ ንጉስ የቦብ ማርሌን ቤተሰብ ሃብትና ንብረቱን በማስተዳደር ብቻ ሳይሆን፤ የቦብን ልጆች በስነ ምግባር ኮትኮቶ ለማሳደግ ከአሜሪካ ኒውዮርክ -ጃማይካ ኪንግስተን እየተመላለሱ በትጋትና በታማኝነት ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡
በዚያን ጊዜም ዘመን አይሽሬውን የቦብ ማርሌይ “ሌጀንድ አልበም" እንዲሰራ ባቀረቡት ንድፈ-ሃሳብ መሰረት ከአይላንድ ሪከርዲንግ ጋር በመፈራረም ውጤማ ስራ ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በቦብ ማርሌይ ቤተሰቦች የተዘጋጁትንና ከምድር ዳር እስከ ምድር ዳር ድረስ የተደረጉትን ዓለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ ኮንሰርቶች ሃሳብ ከመጠንሰስ ጀምሮ ለሃያ ሁለት ዓመታት ያክል ስራውን በሃላፊነት መርተዋል፡፡ አስተዳድረዋል፡፡
በዚሁ የአስተዳደር ዘመናቸው በዘረጉት መንገድ እስካሁን ድረስ በየዓመቱ የሚደረገውን ዓለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ ፌስቲቫል በማይናወጥ መሰረት ላይ አፅንተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ዚጊ ማርሌይን ከጃማይካ… የነዘለቀን ገሰሰን ዳሎል ባንድ ደግሞ ከሺካጎ ወደኒዮርክ በማምጣት ካጣመሩ በኋላ ፤ ከሲግማ ስቱዲዮ እና ከቨርጂኒያ ሪከርድስ ጋር ውል በመፈራረም በአሜሪካ ምድር ቁጥር አንድ ተደማጭ የነበረውን ኮንሺየስ ፓርቲ አልበም እንዲለቀቅ አድርገዋል፡፡
በአልበሙ ከተካተቱት ስራዎች መካከል ቱሞሮ ፒውፕል የተሰኘው ሙዚቃ በዓለም ላይ እጅግ ከመወደዱ የተነሳ ብዙዎች እንደ ብሔራዊ መዝሙር ያዜሙት ነበር፡፡
በአቶ አዲስ ገሰሰ ማናጀርነት በተመራው በዚሁ የሙዚቃ አልበም ዚጊ ማርሌይ የአሜሪካንን ትልቁን ግራሚ አዋርድ ሽልማት ሲያገኝ፤ የኢትዮጵያው ዳሎል ባንድ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ባንድ የግራሚ ሽልማት እንዲወስድ በማስቻል ታሪክ የማይረሳውን ስራ ሰርተዋል፡፡
ለሀገራቸው ኢትዮጵያ የተለየ ፍቅር የነበራቸው አቶ አዲስ ገሰሰ ከወንድማቸው ከአርቲስት ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን የቦብ ማርሊ 60ኛ ዓመት የልደት በዓሉን ለመዘከር የሚዘጋጀውን “አፍሪካ ዩናይት” ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ዝግጅት ኢትዮጵያን መዳረሻ በማድረግና አንድ አመት የፈጀ የዘመቻ /ካምፔይን/ በመስራት ፤ በ1997 ዓ.ም. መስቀል አደባባይ የተካሄደውን የሙዚቃ ፌስቲቫል ስኬታማ እንዲሆን አስችለዋል፡፡ በዚሁ ፌስቲቫል ላይ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ጨምሮ ሪታ ማርሌይና አምስቱ የቦብ ልጆች ተገኝተዋል፡፡
ይኸው ፌስቲቫል በፈጠረው መልካም አጋጣሚም ሀገራችንን በዓለም ዙሪያ ለማስተዋወቅ፤ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግና ኢንቨስመንት ለመሳብ በማለም ከ50 በላይ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን ጋብዘው የራሳቸውን የዜግነት ድርሻ ተወጥተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንት የሕይወት ጉዟቸው ያካበቱትን እውቀትና ልምድ ተጠቅመው ተሰጥዎ ያላቸውን ልጆች በመቃኘት ሀገራቸውን በሙዚቃው ኢንደስትሪ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ትልቅ ህልም ነበራቸው፡፡ ለዚህም ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮን/ከመጀመሪያው አልበሙ ጀምሮ ማኔጅመንቱን በመያዝ ፤ እንዲሁም እጅጋየው ሽባባው /ጂጂን/ ከአጋራቸው ፓልም ሪከርዲንግ ጋር በመሆን ተወዳጅ የሆነ አልበሟን እንድተሰራ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ነው፡፡
ይሄም ብቻ ሳይሆን ጃኖ ባንድን በመመስረት ለልጆቹ ውጤታማነት አቶ አዲስ ገሰሰ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ፡፡ አቶ አዲስ “ጃናናይት” የተባለ ተሰጥዎ ያላቸውን ሴቶች የያዘ ባንድ መስርተው ስኬታማ ለማድረግ ያደረጉት ጥረትም የሚወሳ ነው፡፡
በሙዚቃ ኢንዱስትሪው- እጅግ ገዝፈው፤ በተለያየ የአድናቆት ቃል የሚጠሩት አቶ አዲስ ገሰሰ ከሀገራችን ውጪ እንደ ዚጊ ማርሌ፤ ስቴፈን ማርሌ፤ ሎረን ሂል፣ ፊል ኮሊንስ፣ ኧርዝ ዊንድ ኤንድ ፋየር እና ሌሎችንም በርካታ የሙዚቃ ከዋክብትን በማግኘትና በማስተዳደር በዓለም አቀፍ ደረጃ የብዙ ታላላቅ የሙዚቃ ሰዎች ስራን መስመር አሲዘዋል።
አቶ አዲስ ገሰሰ መደበኛ መኖሪያቸውን ወደ ኢትዮጵያ ካዞሩ በኋላ በሆቴሊንግ ዘርፍ በመሰማራት ላየንስ ዴን ሆቴልን፤ በማእድን ዘርፍም ዩኒቨርሳል ማይኒንግን፤ በግብርና መስክ አድሶጌት ኩባንያን በማቋቋም ለሀገራቸው እድገት ቀን ከሌት ያለእረፍት ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንትና በኢንቨስትመንት ስራቸው ብቻ ሳይሆን በበጎ አድራጎታቸውም አርአያነት ያለው ተግባር ፈፅመዋል፡፡ በግል ከደገፏቸው ግለሰቦች በተጨማሪ በሀገራችን በተለያዩ ወቅቶች በተፈጠሩ ሰብአዊ ችግሮች ቀድመው በመድረስ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ነው፡፡
በዋናነትም ከወንድማቸው ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን በተለያዩ ገጠራማ አካባቢዎች 30 ትምህርት ቤቶችን አሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ስለእነኚሁ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ስላሰሯቸው 30 ትምህርት ቤቶች ሲናገሩ “ተስፋ ሳልቆርጥ በፅናት የታገልኩበት በጎ ተግባር በመሆኑ ያስደስተኛል” ይሉ ነበር፡፡
ቤተ-ክርስቲያን በጠራቻቸው ጊዜ ሁሉ እየተገኙም በመላው ኢትዮጵያ አዳዲስ ቤተክርስቲያኖችን በማሰራት ፤ የተጎዱ ገዳማትንና ቤተክርስቲያኖችን በማደስ ፤ የተዘጉ ቤተክርስቲያኖችን በማስከፈት፤ የቤተክርስቲያኖችን ንዋየ ቅዱሳን በማሟላትና የካህናት ደሞዝን በመክፈል እስከ ህይወት ፍፃሜያቸው ድረስ ድምፃቸውን አጥፍተው አገልግለዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በማህበራዊ ህይወታቸው ቀልድ አዋቂ፤ ተጫዋች እና በቀላሉ ከሰዎች ጋር ተግባብተው የመኖር ፀጋ የነበራቸው ሲሆን ከሁሉም ግን ሰው አካባሪ እና ስነ-ምግባር ያለው ቀረቤታቸው ተወዳጅና በሰው ልብ አይረሴ አድርጓቸዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ከወ/ሮ ሶስና ሽፈራው ጋር በነበራቸው የፀና ትዳር አንድ ወንድና አንዲት ሴት ልጅ አፍርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ፤ በአሜሪካ ሀገር ኒውጄርሲ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡
የቀብር ሥነ ስርዓቱ ዛሬ፣ ሰኔ 20 ቀን 2018ዓ.ም በ6:00 ሰዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።
አቶ አዲስ ገሰሰን ከአጠገቡ ሳትለዩ ላስታመማችሁትና ለጠየቃችሁት ወዳጅ ዘመዶች ልዑል እግዚአብሔር ብድራችሁን ይከፈላችሁ፡፡
የአቶ አዲስ ገሰሰን ነፍስ ልዑል እግዚአብሔር በአፀደ ገነት ከደጋጎቹ አብርሃም ይስሐቅ እና ያቆብ ጎን ያሳርፍልን፡፡
ለቤተሰቡ፤ ለወዳጆቹ፤ ለዘመዶቹ፤ ለሙያ አጋሮቹ፤ ለአድናቂዎቹ ሁሉ መፅናናቱን ይስጣቸው፡፡
2 months ago
በባሕር ዳር ለተወዳጁ ሰማኸኝ በለው መንገድ ተሰየመለት!!
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ለጎጃም ግሽ አባይ የኪነት ቡድን አባል ለነበረው በኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ላተረፈው ለአርቲስት ሰማህኝ በለው መንገድ በስሙ ሰይሟል::
ይህ የታወቀው ዛሬ የባሕር ዳር ህዝብ ለአርቲስቱ መታሰቢያ ባዘጋጀበት ቀን ሲሆን ከባሕር ዳር ልማት ባንክ እሰከ አዲሱ ስቴዲየም ያለው መንገድ "ሰማኸን በለው መንገድ" ተብሎ እዲጠራ መወሰኑን የከተማዋ ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው አሳውቀዋል::
አርቲስት ሰማኸኝ በለው በባሕርዳር ተወልዶ ያደገ ሲሆን እጅግ የተዋጣለት የባህል ዘፈችን ማበርክት የቻለና ህይወቱን በሙሉ በሙዚቃ ስራ ላይ ያሳለፈ ተወዳጅ አርቲስት ነበረ::
በባሕር ዳር ለአርቲስቱ መታሰቢያ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችና ውሳኔዎች የሚቀጥሉ መሆናቸውንም መረጃዎች ያሳያሉ::
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ለጎጃም ግሽ አባይ የኪነት ቡድን አባል ለነበረው በኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ላተረፈው ለአርቲስት ሰማህኝ በለው መንገድ በስሙ ሰይሟል::
ይህ የታወቀው ዛሬ የባሕር ዳር ህዝብ ለአርቲስቱ መታሰቢያ ባዘጋጀበት ቀን ሲሆን ከባሕር ዳር ልማት ባንክ እሰከ አዲሱ ስቴዲየም ያለው መንገድ "ሰማኸን በለው መንገድ" ተብሎ እዲጠራ መወሰኑን የከተማዋ ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው አሳውቀዋል::
አርቲስት ሰማኸኝ በለው በባሕርዳር ተወልዶ ያደገ ሲሆን እጅግ የተዋጣለት የባህል ዘፈችን ማበርክት የቻለና ህይወቱን በሙሉ በሙዚቃ ስራ ላይ ያሳለፈ ተወዳጅ አርቲስት ነበረ::
በባሕር ዳር ለአርቲስቱ መታሰቢያ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችና ውሳኔዎች የሚቀጥሉ መሆናቸውንም መረጃዎች ያሳያሉ::
2 months ago
የሀዘን መግለጫ
#ethiopia | ዓለም አቀፍ እውቅናን የነበረቻው እውቁ የሙዚቃ ማናጀር አቶ አዲሱ ገሰሰ ባደረባቸው ህመም በአሜሪካ ሀገር በህክምና ሲረዱ ቆይተው በ73 ዓመታቸው ሰኔ 09 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
በሙዚቃ ኢንዱስትሪው "የነፍስ አባት" (Godfather) በመባል የሚታወቁት አቶ አዲሱ ገሰሰ የህይወት ፔንዱለም ወደ ሙዚቃ ማናጀርነት ከማዞሯ በፊት በዲሲፕሊን አንፆኛል በሚሉት ዝነኛው የኢትዮጵያ አየር ኃይል በግራንድ ቴክኒሳንነት ለአንድ አመት እንዳገለገሉ የትምህርት እድል በማግኘታቸው ወደ አሜሪካ ሺካጎ በማቅናት ራንቱል ኤርፎርስ ቤዝ እና ቴክሳስ ላክላንድ ኤርፎርስ ቤዝ ትምህርታቸውን ተከታትለው ተመርቀዋል፡፡
በመቀጠልም ሃሮልድ ዋሺንግተን ዩኒቨርሲቲ በዛን ስያሜው ሉፕ ኮሌጅ በሚባለው ሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ ኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ በማኔጅመንት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ ይማሩበት በነበረው ኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር ታሪክ ወር /Black History Month/ ተብሎ በየዓመቱ የካቲት ወር ላይ በተለያየ መዘክር ወንሞቻቸው ዘለቀ ገሰሰ፤ ሙሉጌታ ገሰሰ፤ እና ጓደኞቻቸውን እነ መላኩ ረታ በዳሎል ባንድ ሙዚቃ እንዲያቀርቡ በማስቻል የማናጅመንቱን ስራ በመስራት የሙዚቃ ህይወት ጉዟቸውን ሀ ብለው ጀመሩ፡፡
በዋሺንግተን፤ በሎስ አንጀለስ በአሜሪካ መድር በኢትዮጵያን ለኢትዪጵያን የመጀመሪያውን የሙዚቃ መድረክ በዳሎል ባንድ ውጤታማ ስራ መስራት ችለዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ የማርሌን ቤተሰብ ከነሃብት ንብረቱ በሚያስተዳድሩበት ጊዜ ዘመን አይሽሬውን ኤክሶደስ ሌጀንድ አልበም ከአይስ ላንድ ሪከርዲንግ ጋር እነዲሰራ ማድረግ የቻሉ ሲሆን አቶ አዲሱ ገሰሰ በማርሌ ቤተሰቦች በሚዘጋጀው አለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ መድረክ ከምድር ዳር እስከ ምድር ዳር ድረስ ለተደረጉት የሙዚቃ መድረኮች የሙዚቃ ጉዞ ሃሳቡን ከመጠንሰስ ጀምሮ ከሁለት አስር ዐመታት በላይ ስራውን በማኔጅመንትነት በመምራት እና በማስተዳደር የዘረጉት መንገድ እስካሁን ድረስ በየዓመቱ የሚደረግን ዓለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ ፌስቲቫል የማይናወፅ የማእዘን ድንጋይ ተክለዋል፡፡
በየሀገሩ እና ሙዚቃ በተደረገበት መድረክ ሁሉ አቶ አዲስ ፕሮግራሙን የሚያስጀምሩት አባታችን ሆይ በሚለው ቡራኬና ፀሎት በመሆኑ ፌስቲቫሉን የተለየ ድባብ መፍጠራቸውም የሚዘነጋ አይደለም፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ ዚጊን ከጃማይካ የነዘለቀን ዳሎል ባንድ ከሺካጎ ወደኒዮርክ በማምጣት ካጣመሩ በኋላ ከሲግማ ስቱዲዮ ጋር፤ እና ከቨርጂኒያ ሪከርድስ ጋር ውል በማድረግ በአሜሪካ ምድር ቁጥር አንድ አልበም የሆነውን ኮንሺየስ ፓርቲ ማኔጅ በማድረግ ዚጊ ማርሌ የሜሪካንን ትልቁን ግራሚ አዋርድ ሽልማት ሲያገኝ፤ የኢትዮጵያ ዳሎል ባንድ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ባንድ የግራሚ ሽልማቱን እንዲወስዱ በማስቻል ታሪክ የማይረሳው ስራ ሰርተው አልፈዋል፡፡
ለሀገራቸው ኢትዮጵያ የተለየ ፍቅር የነበራቸው አቶ አዲሱ ገሰሰ ከወንድማቸው አርቲስት ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን የቦብ ማርሊ 60 ዓመት የልደት በዓሉን ምክንያት በማድረግ የሚዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ዝግጅት ኢትዮጵያን መዳረሻ በማድረግ አንድ አመት የፈጀ የዘመቻ /ካምፔይን/ በመስራት በ1997 ዓ.ም. መስቀል አደባባይ የተካሄደውን የሙዚቃ ፌስቲቫል ስኬታማ እንዲሆን በማስቻል መልካም አጋጣሚ በመፍጠር፤ ሀገራችንን በዓለም ዙሪያ ለማስተዋወቅ፤ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ፤ እና ኢንቨስመንት ለመሳብ በማለም ዓለም አቀፍ የሆኑ ከ50 በላይ ሚዲያዎችን በመጋብዝ ድርሻቸውን ተወጥተዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንት የሕይወት ጉዟቸው ያካበቱትን እውቀትና ልምድ በመላ ተጠቅመው ተሰጥዎ ያላቸውን ልጆች በመቃኘት ሀገራቸውን በሙዚቃው ኢንደስትሪ ዓለም አቀፍ ተወዳዳዳሪ ለማድረግ ትልቅ ህልም ነበራቸው፡፡ በዚህም እጅጋየው ሽባባውን /ጂጂ/ ከአጋራቸው ፓልም ሪከርዲንግ ጋር በመሆን ተወዳጅ የሆነ አልበሟን እንድተሰራ ያደረጉ ሲሆን፤ ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ በሚሰራው ሙዚቃም ማኔጅምቱን በመያዝ ያበረከቱት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ነው፡፡
ይሄም ብቻ ሳይሆን ጃኖ ባንድን በመመስረት እና ለፍሬ እንዲበቁ የአቶ አዲስ ገሰሰ ድጋፍ የአንበሳውን ድርሻ የሚይዝ ተግባር ነበር፡፡ አቶ አዲስ ጃናናይት የተባለ ተሰጥዎ ያላቸውን ሴቶች የያዘም ባንድ መስርተው ለመጓዝ ያደረጉትንም ጥረት የሚወሳ ነው፡፡ በሙዚቃ ኢንዱስትሪው "የነፍስ አባት" (Godfather) በመባል የሚታወቁ አቶ አዲሱ ገሰሰ ከሀገራችን ውጪ እንደ ዚጊ ማርሌ፤ ስቴፈን ማርሌ፤ ሎሪን ሂል፣ ፊል ኮሊንስ፣ አርዝ ዊንድ ኤንድ ፋየር (Earth, Wind, & Fire) እና ሌሎችንም በርካታ የሙዚቃ ከዋክብትን በማግኘትና በማስተዳደር በዓለም አቀፍ ደረጃ የብዙዎችን የሙዚቃ ስራ መስመር አሲዘዋል።
አቶ አዲሱ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንት ስራቸው ብቻ ሳይሆን በበጎ ስራ ተግባራቸው የተወደደ አርአያነት ያለው ተግባር ፈፅመዋል፡፡ ከነዚህም መሃከል በግል ከደገፏቸው ግለሰቦች በተጨማሪ በሀገራችን በተለያያ ጊዜ የተፈጠሩ ሰብአዊ ችግሮችን ለመድረስ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ሲሆን በዋናነት ከወንድማቸው ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን በተለያዩ ገጠረማ አካባቢዎች 30 ትምህርት ቤቶችን በማሰራት ያደረጉት በጎ ተግባር በታሪክ የሚወሳ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ መደበኛ መኖሪያቸውን ወደ ኢትዮጵያ ካዞሩ በኋላ በሆቴሊንግ ዘርፍ በመሰማራት ላየንስ ዴን ሆቴልን፤ በማእድን ዘርፍ ዩኒቨርሳል ማይኒንግን፤ በግብርና መስክ አድሶጌት ኩባንያን በማቋቋም የራሳቸውን ጡብ ለማስቀመጥ ቀን ከሌት ያለእረፍት ጥረዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በማህበራዊ ህይወታቸው ቀልድ አዋቂ፤ ተጫዋች እና በቀላሉ ከሰዎች ጋር ተግባብተው የመኖር ፀጋ የነበራቸው ሲሆን ከሁሉም ግን ሰው አካባሪ እና ስነ ምግባር ያለው ቀረቤታቸው ተወዳጅ እና በሰው ልብ አይረሴ አድርጓቸዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ ከወ/ሮ ሶስና ሽፈራው ጋር በነበረው የፀና ትዳር አንድ ወንድ እና አንድ ሴት ለማፍራት ችለዋል፡፡
የአቶ አዲሱ ገሰሰ የአስክሪን ሽኝትና ስርዓተ ቀብር አፈጻጸም ስንነስርዓት በቅርቡ እናሳውቃለን ፡፡
#ethiopia | ዓለም አቀፍ እውቅናን የነበረቻው እውቁ የሙዚቃ ማናጀር አቶ አዲሱ ገሰሰ ባደረባቸው ህመም በአሜሪካ ሀገር በህክምና ሲረዱ ቆይተው በ73 ዓመታቸው ሰኔ 09 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
በሙዚቃ ኢንዱስትሪው "የነፍስ አባት" (Godfather) በመባል የሚታወቁት አቶ አዲሱ ገሰሰ የህይወት ፔንዱለም ወደ ሙዚቃ ማናጀርነት ከማዞሯ በፊት በዲሲፕሊን አንፆኛል በሚሉት ዝነኛው የኢትዮጵያ አየር ኃይል በግራንድ ቴክኒሳንነት ለአንድ አመት እንዳገለገሉ የትምህርት እድል በማግኘታቸው ወደ አሜሪካ ሺካጎ በማቅናት ራንቱል ኤርፎርስ ቤዝ እና ቴክሳስ ላክላንድ ኤርፎርስ ቤዝ ትምህርታቸውን ተከታትለው ተመርቀዋል፡፡
በመቀጠልም ሃሮልድ ዋሺንግተን ዩኒቨርሲቲ በዛን ስያሜው ሉፕ ኮሌጅ በሚባለው ሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ ኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ በማኔጅመንት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ ይማሩበት በነበረው ኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር ታሪክ ወር /Black History Month/ ተብሎ በየዓመቱ የካቲት ወር ላይ በተለያየ መዘክር ወንሞቻቸው ዘለቀ ገሰሰ፤ ሙሉጌታ ገሰሰ፤ እና ጓደኞቻቸውን እነ መላኩ ረታ በዳሎል ባንድ ሙዚቃ እንዲያቀርቡ በማስቻል የማናጅመንቱን ስራ በመስራት የሙዚቃ ህይወት ጉዟቸውን ሀ ብለው ጀመሩ፡፡
በዋሺንግተን፤ በሎስ አንጀለስ በአሜሪካ መድር በኢትዮጵያን ለኢትዪጵያን የመጀመሪያውን የሙዚቃ መድረክ በዳሎል ባንድ ውጤታማ ስራ መስራት ችለዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ የማርሌን ቤተሰብ ከነሃብት ንብረቱ በሚያስተዳድሩበት ጊዜ ዘመን አይሽሬውን ኤክሶደስ ሌጀንድ አልበም ከአይስ ላንድ ሪከርዲንግ ጋር እነዲሰራ ማድረግ የቻሉ ሲሆን አቶ አዲሱ ገሰሰ በማርሌ ቤተሰቦች በሚዘጋጀው አለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ መድረክ ከምድር ዳር እስከ ምድር ዳር ድረስ ለተደረጉት የሙዚቃ መድረኮች የሙዚቃ ጉዞ ሃሳቡን ከመጠንሰስ ጀምሮ ከሁለት አስር ዐመታት በላይ ስራውን በማኔጅመንትነት በመምራት እና በማስተዳደር የዘረጉት መንገድ እስካሁን ድረስ በየዓመቱ የሚደረግን ዓለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ ፌስቲቫል የማይናወፅ የማእዘን ድንጋይ ተክለዋል፡፡
በየሀገሩ እና ሙዚቃ በተደረገበት መድረክ ሁሉ አቶ አዲስ ፕሮግራሙን የሚያስጀምሩት አባታችን ሆይ በሚለው ቡራኬና ፀሎት በመሆኑ ፌስቲቫሉን የተለየ ድባብ መፍጠራቸውም የሚዘነጋ አይደለም፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ ዚጊን ከጃማይካ የነዘለቀን ዳሎል ባንድ ከሺካጎ ወደኒዮርክ በማምጣት ካጣመሩ በኋላ ከሲግማ ስቱዲዮ ጋር፤ እና ከቨርጂኒያ ሪከርድስ ጋር ውል በማድረግ በአሜሪካ ምድር ቁጥር አንድ አልበም የሆነውን ኮንሺየስ ፓርቲ ማኔጅ በማድረግ ዚጊ ማርሌ የሜሪካንን ትልቁን ግራሚ አዋርድ ሽልማት ሲያገኝ፤ የኢትዮጵያ ዳሎል ባንድ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ባንድ የግራሚ ሽልማቱን እንዲወስዱ በማስቻል ታሪክ የማይረሳው ስራ ሰርተው አልፈዋል፡፡
ለሀገራቸው ኢትዮጵያ የተለየ ፍቅር የነበራቸው አቶ አዲሱ ገሰሰ ከወንድማቸው አርቲስት ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን የቦብ ማርሊ 60 ዓመት የልደት በዓሉን ምክንያት በማድረግ የሚዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ዝግጅት ኢትዮጵያን መዳረሻ በማድረግ አንድ አመት የፈጀ የዘመቻ /ካምፔይን/ በመስራት በ1997 ዓ.ም. መስቀል አደባባይ የተካሄደውን የሙዚቃ ፌስቲቫል ስኬታማ እንዲሆን በማስቻል መልካም አጋጣሚ በመፍጠር፤ ሀገራችንን በዓለም ዙሪያ ለማስተዋወቅ፤ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ፤ እና ኢንቨስመንት ለመሳብ በማለም ዓለም አቀፍ የሆኑ ከ50 በላይ ሚዲያዎችን በመጋብዝ ድርሻቸውን ተወጥተዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንት የሕይወት ጉዟቸው ያካበቱትን እውቀትና ልምድ በመላ ተጠቅመው ተሰጥዎ ያላቸውን ልጆች በመቃኘት ሀገራቸውን በሙዚቃው ኢንደስትሪ ዓለም አቀፍ ተወዳዳዳሪ ለማድረግ ትልቅ ህልም ነበራቸው፡፡ በዚህም እጅጋየው ሽባባውን /ጂጂ/ ከአጋራቸው ፓልም ሪከርዲንግ ጋር በመሆን ተወዳጅ የሆነ አልበሟን እንድተሰራ ያደረጉ ሲሆን፤ ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ በሚሰራው ሙዚቃም ማኔጅምቱን በመያዝ ያበረከቱት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ነው፡፡
ይሄም ብቻ ሳይሆን ጃኖ ባንድን በመመስረት እና ለፍሬ እንዲበቁ የአቶ አዲስ ገሰሰ ድጋፍ የአንበሳውን ድርሻ የሚይዝ ተግባር ነበር፡፡ አቶ አዲስ ጃናናይት የተባለ ተሰጥዎ ያላቸውን ሴቶች የያዘም ባንድ መስርተው ለመጓዝ ያደረጉትንም ጥረት የሚወሳ ነው፡፡ በሙዚቃ ኢንዱስትሪው "የነፍስ አባት" (Godfather) በመባል የሚታወቁ አቶ አዲሱ ገሰሰ ከሀገራችን ውጪ እንደ ዚጊ ማርሌ፤ ስቴፈን ማርሌ፤ ሎሪን ሂል፣ ፊል ኮሊንስ፣ አርዝ ዊንድ ኤንድ ፋየር (Earth, Wind, & Fire) እና ሌሎችንም በርካታ የሙዚቃ ከዋክብትን በማግኘትና በማስተዳደር በዓለም አቀፍ ደረጃ የብዙዎችን የሙዚቃ ስራ መስመር አሲዘዋል።
አቶ አዲሱ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንት ስራቸው ብቻ ሳይሆን በበጎ ስራ ተግባራቸው የተወደደ አርአያነት ያለው ተግባር ፈፅመዋል፡፡ ከነዚህም መሃከል በግል ከደገፏቸው ግለሰቦች በተጨማሪ በሀገራችን በተለያያ ጊዜ የተፈጠሩ ሰብአዊ ችግሮችን ለመድረስ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ሲሆን በዋናነት ከወንድማቸው ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን በተለያዩ ገጠረማ አካባቢዎች 30 ትምህርት ቤቶችን በማሰራት ያደረጉት በጎ ተግባር በታሪክ የሚወሳ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ መደበኛ መኖሪያቸውን ወደ ኢትዮጵያ ካዞሩ በኋላ በሆቴሊንግ ዘርፍ በመሰማራት ላየንስ ዴን ሆቴልን፤ በማእድን ዘርፍ ዩኒቨርሳል ማይኒንግን፤ በግብርና መስክ አድሶጌት ኩባንያን በማቋቋም የራሳቸውን ጡብ ለማስቀመጥ ቀን ከሌት ያለእረፍት ጥረዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በማህበራዊ ህይወታቸው ቀልድ አዋቂ፤ ተጫዋች እና በቀላሉ ከሰዎች ጋር ተግባብተው የመኖር ፀጋ የነበራቸው ሲሆን ከሁሉም ግን ሰው አካባሪ እና ስነ ምግባር ያለው ቀረቤታቸው ተወዳጅ እና በሰው ልብ አይረሴ አድርጓቸዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ ከወ/ሮ ሶስና ሽፈራው ጋር በነበረው የፀና ትዳር አንድ ወንድ እና አንድ ሴት ለማፍራት ችለዋል፡፡
የአቶ አዲሱ ገሰሰ የአስክሪን ሽኝትና ስርዓተ ቀብር አፈጻጸም ስንነስርዓት በቅርቡ እናሳውቃለን ፡፡
Sponsored by
Surafel
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) የጃኖ ባንድ መስራች፣ የዳሎል ባንድ አባል የነበሩት ሙዚቀኛ ዘለቀ ገሰሰ ወንድም እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ስማቸው የገነነ ታዋቂው የሙዚቃ ፕሮዲውሰር እና ማኔጀር አቶ አዲስ ገሰሰ፣ በኒው ጀርሲ፣ አሜሪካ ባደሩበት በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የቅርብ ወዳጆቻቸው አሳዝነው አስታውቀዋል። የሞታቸው ምክንያት ገና በውል ያልታወቀ ሲሆን፣ አስከሬናቸው ወደ ውዲቷ ሀገራቸው ኢትዮጵያ እንደሚሸኝም መረጃዎች ያመለክታሉ።
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃው ኢንደስትሪ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፉ፣ የብዙዎችን ህይወት የቀየሩ እና የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ አድርገው ያቆሙ ታላቅ ሰው ነበሩ። እኚህ የሙዚቃ ማኔጅመንት ባለሙያ፣ ዓለም አቀፍ ዝና ያተረፉትን የሬጌው ንጉስ የቦብ ማርሊ ቤተሰቦችን ጨምሮ የበርካታ ታዋቂ ሙዚቀኞች የጀርባ አጥንት በመሆን አገልግለዋል። የእሳቸው የህይወት ጉዞ ከኢትዮጵያ ጀምሮ፣ በቺካጎ፣ ጃማይካ፣ ኒው ዮርክ እና በመጨረሻም ኒው ጀርሲን ያዳረሰ ረዥም እና አስደናቂ መንገድ ነበር።
አቶ አዲስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተመረቁ በኋላ፣ ከ30 ዓመታት በፊት ወደ አሜሪካ አቅንተው ማኔጅመንት አጠኑ። ከዚያም ወንድሞቻቸው ሲከተሏቸው፣ ህይወታቸውን ሙሉ ለሙሉ ለወንድሞቻቸው የሙዚቃ ስኬት አዋሉ። ወንድሞቻቸውና ጓደኞቻቸው የመሰረቱት "ዳሎል" የተሰኘው ባንድ፣ ከኢትዮጵያዊ ሙዚቃ ወደ ሬጌ በማዘንበል፣ በአቶ አዲስ አመራር ስር በቺካጎ ስሙን ማግነን ጀመረ።
በ1982 የቦብ ማርሊ ባለቤት ሪታ ማርሊ ባቀረበችላቸው ጥሪ መሰረት፣ ዳሎል ባንድ በጃማይካ ኪንግስተን በተካሄደው የመጀመሪያው የቦብ ማርሊ መታሰቢያ ላይ ለመጫወት በቅቷል። አቶ አዲስ ሪታ ማርሊ በባለቤቷ ሞት እያዘነች በነበረችበት ወቅት የሰጧት ድጋፍ፣ ጠንካራ ወዳጅነትን ፈጠረ። ይህ ግንኙነት ዳሎል ባንድ ከ1988 እስከ 1991 ድረስ የዚጊ ማርሊ ይፋዊ ባንድ እንዲሆን አስችሎታል። ዳሎል ባንድ በ "Conscious Party" አልበም ፕላቲነም፣ እና በ "One Bright Day" አልበም ጎልድ ደረጃ በመድረስ፣ ይህን ታሪካዊ ስኬት ያገኘ የመጀመሪያው የኢትዮጵያውያን ባንድ ለመሆን በቅቷል።
አቶ አዲስ ከሪታ ማርሊ ጋር በመሆን የቦብ ማርሊን 'Legend' አልበም ዓለም አቀፍ ጉብኝት አደራጅተዋል። ከሁሉም በላይ ግን፣ አቶ አዲስ በ2005 በአዲስ አበባ የተካሄደውንና ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ህዝብ የታደመበትን ታሪካዊውን "Africa Unite" ኮንሰርት በዋናነት የጠነሰሱት እሳቸው ነበሩ። ይህ ኮንሰርት የቦብ ማርሊን 60ኛ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ፣ የቦብ ማርሊ ቤተሰብ፣ አንጀሊክ ኪጆን ጨምሮ በርካታ ከዋክብትን በአዲስ አበባ ያሰባሰበና ስለ ኢትዮጵያ አዎንታዊ ገጽታ ለዓለም ያሳየ ታላቅ ኩነት ነበር።
አቶ አዲስ የዓለም አቀፍ ከዋክብትን ከማስተዳደር ባሻገር፣ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ወደ ዓለም መድረክ ለማሸጋገር ትልቅ ህልም ነበራቸው። ለዚህም ነው "አዲስ ማኔጅመንት" የተሰኘውን ድርጅታቸውን መስርተው በርካታ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶችን የደገፉት።
ታዋቂውን ድምጻዊ ቴዲ አፍሮን በማግኘትና ለረጅም ጊዜ ማኔጀሩ በመሆን አገልግለዋል። እንዲሁም፣ ታዋቂዋን ድምጻዊት ጂጂን በአጋጣሚ ቤታቸው ውስጥ ካገኟት በኋላ፣ ችሎታዋን አይተው፣ ኒው ዮርክ እንድትመጣ በመምከር፣ ከታዋቂው የአይላንድ ሪከርድስ መስራች ክሪስ ብላክዌል ጋር አስተዋውቀዋት፣ ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ውል እንድትፈራረም አድርገዋል።
አቶ አዲስ ዓለም አቀፍ ኔትዎርክ ያላቸውና ስኬታማ ቢሆኑም፣ እንደቅርብ ወዳጆቻቸው ምስክርነት እጅግ ትሁት ነበሩ። ኒው ጀርሲ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው፣ ሹራብና አጭር ሱሪ ለብሰው ከሶስት ዓመት ልጃቸው ሀና ጋር ጊዜ ማሳለፍን የሚወዱ አባት ነበሩ። ከሙዚቃ ስራቸው በተጨማሪ በቺካጎ የሬጌ ክለብ፣ በኢትዮጵያ የእርሻ ስራ እና በ "One Love Africa Foundation" አማካኝነት በኢትዮጵያ ገጠራማ ክፍሎች ትምህርት ቤቶችን የመገንባት ሰፊ ራዕይ ነበራቸው።
አቶ አዲስ ገሰሰ ኢትዮጵያን በዓለም አደባባይ በክብር ያስጠሩ፣ የሙዚቃውን ኢንደስትሪ ያሳደጉ እና ለብዙዎች መነሻ የሆኑ ታላቅ ሰው ናቸው። በድንገተኛ ህልፈታቸው የሙዚቃው ዓለም፣ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጆቻቸው፣ እንዲሁም አድናቂዎቻቸው ጥልቅ ሀዘን ላይ ይገኛሉ።
ነፍስ ይማር! አቶ አዲስ ገሰሰ፣ ስራዎ እና አሻራዎ ለዘለዓለም ሲታወስ ይኖራል።
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃው ኢንደስትሪ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፉ፣ የብዙዎችን ህይወት የቀየሩ እና የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ አድርገው ያቆሙ ታላቅ ሰው ነበሩ። እኚህ የሙዚቃ ማኔጅመንት ባለሙያ፣ ዓለም አቀፍ ዝና ያተረፉትን የሬጌው ንጉስ የቦብ ማርሊ ቤተሰቦችን ጨምሮ የበርካታ ታዋቂ ሙዚቀኞች የጀርባ አጥንት በመሆን አገልግለዋል። የእሳቸው የህይወት ጉዞ ከኢትዮጵያ ጀምሮ፣ በቺካጎ፣ ጃማይካ፣ ኒው ዮርክ እና በመጨረሻም ኒው ጀርሲን ያዳረሰ ረዥም እና አስደናቂ መንገድ ነበር።
አቶ አዲስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተመረቁ በኋላ፣ ከ30 ዓመታት በፊት ወደ አሜሪካ አቅንተው ማኔጅመንት አጠኑ። ከዚያም ወንድሞቻቸው ሲከተሏቸው፣ ህይወታቸውን ሙሉ ለሙሉ ለወንድሞቻቸው የሙዚቃ ስኬት አዋሉ። ወንድሞቻቸውና ጓደኞቻቸው የመሰረቱት "ዳሎል" የተሰኘው ባንድ፣ ከኢትዮጵያዊ ሙዚቃ ወደ ሬጌ በማዘንበል፣ በአቶ አዲስ አመራር ስር በቺካጎ ስሙን ማግነን ጀመረ።
በ1982 የቦብ ማርሊ ባለቤት ሪታ ማርሊ ባቀረበችላቸው ጥሪ መሰረት፣ ዳሎል ባንድ በጃማይካ ኪንግስተን በተካሄደው የመጀመሪያው የቦብ ማርሊ መታሰቢያ ላይ ለመጫወት በቅቷል። አቶ አዲስ ሪታ ማርሊ በባለቤቷ ሞት እያዘነች በነበረችበት ወቅት የሰጧት ድጋፍ፣ ጠንካራ ወዳጅነትን ፈጠረ። ይህ ግንኙነት ዳሎል ባንድ ከ1988 እስከ 1991 ድረስ የዚጊ ማርሊ ይፋዊ ባንድ እንዲሆን አስችሎታል። ዳሎል ባንድ በ "Conscious Party" አልበም ፕላቲነም፣ እና በ "One Bright Day" አልበም ጎልድ ደረጃ በመድረስ፣ ይህን ታሪካዊ ስኬት ያገኘ የመጀመሪያው የኢትዮጵያውያን ባንድ ለመሆን በቅቷል።
አቶ አዲስ ከሪታ ማርሊ ጋር በመሆን የቦብ ማርሊን 'Legend' አልበም ዓለም አቀፍ ጉብኝት አደራጅተዋል። ከሁሉም በላይ ግን፣ አቶ አዲስ በ2005 በአዲስ አበባ የተካሄደውንና ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ህዝብ የታደመበትን ታሪካዊውን "Africa Unite" ኮንሰርት በዋናነት የጠነሰሱት እሳቸው ነበሩ። ይህ ኮንሰርት የቦብ ማርሊን 60ኛ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ፣ የቦብ ማርሊ ቤተሰብ፣ አንጀሊክ ኪጆን ጨምሮ በርካታ ከዋክብትን በአዲስ አበባ ያሰባሰበና ስለ ኢትዮጵያ አዎንታዊ ገጽታ ለዓለም ያሳየ ታላቅ ኩነት ነበር።
አቶ አዲስ የዓለም አቀፍ ከዋክብትን ከማስተዳደር ባሻገር፣ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ወደ ዓለም መድረክ ለማሸጋገር ትልቅ ህልም ነበራቸው። ለዚህም ነው "አዲስ ማኔጅመንት" የተሰኘውን ድርጅታቸውን መስርተው በርካታ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶችን የደገፉት።
ታዋቂውን ድምጻዊ ቴዲ አፍሮን በማግኘትና ለረጅም ጊዜ ማኔጀሩ በመሆን አገልግለዋል። እንዲሁም፣ ታዋቂዋን ድምጻዊት ጂጂን በአጋጣሚ ቤታቸው ውስጥ ካገኟት በኋላ፣ ችሎታዋን አይተው፣ ኒው ዮርክ እንድትመጣ በመምከር፣ ከታዋቂው የአይላንድ ሪከርድስ መስራች ክሪስ ብላክዌል ጋር አስተዋውቀዋት፣ ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ውል እንድትፈራረም አድርገዋል።
አቶ አዲስ ዓለም አቀፍ ኔትዎርክ ያላቸውና ስኬታማ ቢሆኑም፣ እንደቅርብ ወዳጆቻቸው ምስክርነት እጅግ ትሁት ነበሩ። ኒው ጀርሲ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው፣ ሹራብና አጭር ሱሪ ለብሰው ከሶስት ዓመት ልጃቸው ሀና ጋር ጊዜ ማሳለፍን የሚወዱ አባት ነበሩ። ከሙዚቃ ስራቸው በተጨማሪ በቺካጎ የሬጌ ክለብ፣ በኢትዮጵያ የእርሻ ስራ እና በ "One Love Africa Foundation" አማካኝነት በኢትዮጵያ ገጠራማ ክፍሎች ትምህርት ቤቶችን የመገንባት ሰፊ ራዕይ ነበራቸው።
አቶ አዲስ ገሰሰ ኢትዮጵያን በዓለም አደባባይ በክብር ያስጠሩ፣ የሙዚቃውን ኢንደስትሪ ያሳደጉ እና ለብዙዎች መነሻ የሆኑ ታላቅ ሰው ናቸው። በድንገተኛ ህልፈታቸው የሙዚቃው ዓለም፣ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጆቻቸው፣ እንዲሁም አድናቂዎቻቸው ጥልቅ ሀዘን ላይ ይገኛሉ።
ነፍስ ይማር! አቶ አዲስ ገሰሰ፣ ስራዎ እና አሻራዎ ለዘለዓለም ሲታወስ ይኖራል።
2 months ago
የሀዘን መግለጫ
የጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር፤ የጥበብ ሰው፣ የህዝብ ድምፅ እና የለውጥ አጋራችን የነበረው ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ስንሰማ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀዘን ተሰምቶናል።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው በሙዚቃ ስራዎቹ የሀገራችንን ባህልና እሴቶች በመጠበቅ ረገድ የማይረሳ አሻራ ጥሏል። ከጥበብ ስራው ጎን ለጎን ደግሞ፣ እንደ ማህበረሰብ የሚገጥሙንን የጤና ችግሮች በመቅረፍ ረገድ የነበረው አበርክቶ የሚዘነጋ አይደለም።
በተለይም ከጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር ጋር በመተባበር፤ ድምጻዊት ቤተለሄም ዳኛቸው እና ትዕግስት መኮንን ጋር በመሆን በነጻ ያበረከቱት “እኛ ለእኛ” የተሰኘ ሙዚቃ፣ ወባን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ የነበረው አስተዋጽኦ የላቀ ነበር።
በተጨማሪም፣ "ደቦት እንስራ" በሚለው እና በማህበረሰቡ ዘንድ "እያበል እያ እያ" በሚል በሚታወቀው ተወዳጅ ስራው እንዲሁም በሌሎች የቅስቀሳ ስራዎች፣ ማህበሩ የሚያከናውናቸውን የገቢ ማሰባሰቢያና የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻዎች በቅንነትና በታማኝነት በመምራት፣ ለብዙዎች ህይወት መትረፍ እና ለበሽታው ስርጭት መቀነስ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል።
እንደ ማኅበር፣ ለሰጠን የላቀ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና ለነበረን የትብብር ዘመን ምስጋናችንን እያቀረብን፣ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለመላው የጥበብ ቤተሰብ እንገልጻለን።
ለአርቲስቱ ነፍስ ዘላለማዊ እረፍትን፣ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ መጽናናትን እንመኛለን።
ጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር
የጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር፤ የጥበብ ሰው፣ የህዝብ ድምፅ እና የለውጥ አጋራችን የነበረው ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ስንሰማ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀዘን ተሰምቶናል።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው በሙዚቃ ስራዎቹ የሀገራችንን ባህልና እሴቶች በመጠበቅ ረገድ የማይረሳ አሻራ ጥሏል። ከጥበብ ስራው ጎን ለጎን ደግሞ፣ እንደ ማህበረሰብ የሚገጥሙንን የጤና ችግሮች በመቅረፍ ረገድ የነበረው አበርክቶ የሚዘነጋ አይደለም።
በተለይም ከጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር ጋር በመተባበር፤ ድምጻዊት ቤተለሄም ዳኛቸው እና ትዕግስት መኮንን ጋር በመሆን በነጻ ያበረከቱት “እኛ ለእኛ” የተሰኘ ሙዚቃ፣ ወባን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ የነበረው አስተዋጽኦ የላቀ ነበር።
በተጨማሪም፣ "ደቦት እንስራ" በሚለው እና በማህበረሰቡ ዘንድ "እያበል እያ እያ" በሚል በሚታወቀው ተወዳጅ ስራው እንዲሁም በሌሎች የቅስቀሳ ስራዎች፣ ማህበሩ የሚያከናውናቸውን የገቢ ማሰባሰቢያና የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻዎች በቅንነትና በታማኝነት በመምራት፣ ለብዙዎች ህይወት መትረፍ እና ለበሽታው ስርጭት መቀነስ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል።
እንደ ማኅበር፣ ለሰጠን የላቀ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና ለነበረን የትብብር ዘመን ምስጋናችንን እያቀረብን፣ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለመላው የጥበብ ቤተሰብ እንገልጻለን።
ለአርቲስቱ ነፍስ ዘላለማዊ እረፍትን፣ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ መጽናናትን እንመኛለን።
ጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር
Comments