Logo
FastMereja
"5 ዓመት ደክሜበት ህዝብ የሚወደውን ቆንጆ ስራ ይዤ መጥቻለሁ" — ድምጻዊት ጄሪ አንተነህ

‎በ"ለኔ ባለው"፣ "ባዶ" እና "አላመደኝ" በተሰኙ ነጠላ ዜማዎቿ በአድማጮች ዘንድ ፍቅር ያተረፈችው ድምጻዊት ጄሪ አንተነህ፣ ለአምስት ዓመታት የለፋችበትን እና በብዙ ትጋት ያዘጋጀችውን "ወደ ንጋት" የተሰኘ ሙሉ አልበሟን ለአድማጮች አቅርባለች።

‎ድምጻዊቷ አልበሙን በራሷ የዩቲዩብ ቻናል ላይ ለህዝብ ይፋ ስታደርግ፣ "5 ዓመት ደክሜበት ህዝብ የሚወደውን ቆንጆ ስራ ይዤ መጥቻለሁ" በማለት ስራዋ በአድማጮች ዘንድ ተቀባይነት እንደሚያገኝ ያላትን እምነት ገልጻለች።

‎10 ትራኮች የያዘውን ይህን አልበም ለማጠናቀቅ ከካናዳ ወደ ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በመመላለስ ከፍተኛ ወጪና ጊዜ እንዳፈሰሰችበት ተናግራለች።

‎በአልበሙ ዝግጅትም በኢትዮጵያ የሙዚቃ ዘርፍ ታዋቂ ባለሙያዎች የሆኑት ብሩክ ተቀባ፣ ብሩክ አፍወርቅ እና ታምሩ አማረ የሰሩ ሲሆን፣ የማስተሪንግ ስራውን ደግሞ አበጋዙ ክብረወርቅ ሺዎታ እንዳከናወነ ተገልጿል።

‎"ወደ ንጋት" የተሰኘው አልበም ከረጅም ጊዜ ዝግጅት፣ ትጋት እና መስዋዕትነት በኋላ ለአድማጮች የደረሰ ሲሆን፣ በሙዚቃ ወዳዶች ዘንድ ምን ያህል ተቀባይነት እንደሚያገኝ በጉጉት እየተጠበቀ ነው።

ሊንኩን በመጫን ተመልከቷት
👇
https://youtube.com/jerry...



27 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.