21 hours ago
በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወደ የመጨረሻ የውሳኔ መድረክ የሚያልፉ የማጣሪያ ምክረ ሀሳቦች
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የመጨረሻውን የውሳኔ መድረክ ለመጀመር መሠረት የሚጥሉ የማጣሪያ ምክረ ሀሳቦች ለተመካካሪዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በተለያዩ የውይይትና የማጣሪያ ሂደቶች ካለፈ በኋላ፣ በስልታዊ ቡድኖች የተጣሩና የተስማሙባቸውን ሀሳቦች ወደ ዋናው የውሳኔ መድረክ ተሸጋግረዋል።
በሂደቱ ወደ 500 የሚጠጉ ተመካካሪዎች በ250 የስልታዊ ቡድኖች ተደራጅተው፣ በስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎችና በንዑሳን አጀንዳዎች ላይ የተመረጡ ሀሳቦችን በዝርዝር በመመካከር ስምምነት የተደረሰባቸውን ጉዳዮች በፊርማ አረጋግጠዋል።
በአሁኑ ወቅት የቃለ ጉባኤ ያዦችና አመካካሪዎች እነዚህን በፊርማ የተረጋገጡ ሀሳቦች ለተመካካሪዎች በግልጽ ሁኔታ ቀርበዋል። ወደ የመጨረሻው የውሳኔ መድረክ የሚያልፉትን ጉዳዮችም አብራርተዋል።
ተመካካሪዎች በበኩላቸው የተመረጡት ሀሳቦች በትክክል በቃለ ጉባኤ መዝገብ መካተታቸውና ለውሳኔ መድረኩ መቅረባቸው ግልጽነትን እንዲሁም የሂደቱን ተዓማኒነት እንደሚያጠናክር አንስተዋል።
በውይይቱ ወቅት በዋና አጀንዳዎች ላይ ተጨማሪ ማሻሻያ፣ ማስተካከያ ወይም ያልተካተቱ ሀሳቦች ካሉ በዚህ ደረጃ እንዲቀርቡ ዕድል የሰጠ ሲሆን፤ ይህም ወደ የመጨረሻው የውሳኔ መድረክ የሚቀርቡ ሀሳቦች ሁሉን አቀፍ እንዲሆኑ እና ሰፊ ስምምነት እንዲያገኙ አግዟል።
ተመካካሪዎች፣ ከግላዊ አመለካከት ይልቅ ሀገራዊ ጥቅምን፣ ሀገራዊ መግባባትንና ህብረ ብሔራዊነትን ያስቀደመ ውይይት መካሄዱን ገልጸው፤ የመድረኩ ሂደት ከ"እኔ" ወደ "እኛ" የሚያሸጋግር የመግባባት ባህልን ያጠናከረ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም የቀረቡት ሀሳቦች በሙሉ በቃለ ጉባኤ መያዛቸው፣ መነበባቸው እና በአመካካሪዎች ማብራሪያ መሰጠቱ የሂደቱን ግልጽነትና አሳታፊነት ያጠናከረ እንደሆነ ተመላክቷል።
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የመጨረሻውን የውሳኔ መድረክ ለመጀመር መሠረት የሚጥሉ የማጣሪያ ምክረ ሀሳቦች ለተመካካሪዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በተለያዩ የውይይትና የማጣሪያ ሂደቶች ካለፈ በኋላ፣ በስልታዊ ቡድኖች የተጣሩና የተስማሙባቸውን ሀሳቦች ወደ ዋናው የውሳኔ መድረክ ተሸጋግረዋል።
በሂደቱ ወደ 500 የሚጠጉ ተመካካሪዎች በ250 የስልታዊ ቡድኖች ተደራጅተው፣ በስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎችና በንዑሳን አጀንዳዎች ላይ የተመረጡ ሀሳቦችን በዝርዝር በመመካከር ስምምነት የተደረሰባቸውን ጉዳዮች በፊርማ አረጋግጠዋል።
በአሁኑ ወቅት የቃለ ጉባኤ ያዦችና አመካካሪዎች እነዚህን በፊርማ የተረጋገጡ ሀሳቦች ለተመካካሪዎች በግልጽ ሁኔታ ቀርበዋል። ወደ የመጨረሻው የውሳኔ መድረክ የሚያልፉትን ጉዳዮችም አብራርተዋል።
ተመካካሪዎች በበኩላቸው የተመረጡት ሀሳቦች በትክክል በቃለ ጉባኤ መዝገብ መካተታቸውና ለውሳኔ መድረኩ መቅረባቸው ግልጽነትን እንዲሁም የሂደቱን ተዓማኒነት እንደሚያጠናክር አንስተዋል።
በውይይቱ ወቅት በዋና አጀንዳዎች ላይ ተጨማሪ ማሻሻያ፣ ማስተካከያ ወይም ያልተካተቱ ሀሳቦች ካሉ በዚህ ደረጃ እንዲቀርቡ ዕድል የሰጠ ሲሆን፤ ይህም ወደ የመጨረሻው የውሳኔ መድረክ የሚቀርቡ ሀሳቦች ሁሉን አቀፍ እንዲሆኑ እና ሰፊ ስምምነት እንዲያገኙ አግዟል።
ተመካካሪዎች፣ ከግላዊ አመለካከት ይልቅ ሀገራዊ ጥቅምን፣ ሀገራዊ መግባባትንና ህብረ ብሔራዊነትን ያስቀደመ ውይይት መካሄዱን ገልጸው፤ የመድረኩ ሂደት ከ"እኔ" ወደ "እኛ" የሚያሸጋግር የመግባባት ባህልን ያጠናከረ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም የቀረቡት ሀሳቦች በሙሉ በቃለ ጉባኤ መያዛቸው፣ መነበባቸው እና በአመካካሪዎች ማብራሪያ መሰጠቱ የሂደቱን ግልጽነትና አሳታፊነት ያጠናከረ እንደሆነ ተመላክቷል።
በዮናስ ጌትነት
1 day ago
ምክክር ለዘላቂ ሠላም
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከጥንታዊ ነጻ ሀገረ መንግሥታት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በበርካታ ባህሎች፣ ቋንቋዎችና እሴቶች የተዋቀረች ኅብረብሔራዊት ሀገር ናት፡፡
ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ መኖሪያ የሆነችው ሀገራችን ህልውናዋን አጽንታ ዘመናትን መሻገር የቻለችው በልጆቿ የተባበረ ክንድ ስለመሆኑ ታሪክ ህያው ምስክር ነው።
በእነዚያ ጊዜያት ውስጥ ሰላሟንና ልማቷን ሲፈታተኑ የዘለቁ ቅራኔዎችን በሰላማዊ ውይይት በመፍታት ነገዋን የተሻለ ለማድረግ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ትገኛለች፡፡
ዜጎቿ ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋግጥ የጋራ መግባባት ላይ የሚያደርስ መፍትሄ እንዲያበጁ በገለልተኛ የምክክር ኮሚሽን የሚመራ አሳታፊና አካታች ሀገራዊ መድረክ አበጅታለች፡፡
ይህ አሳታፊነት ምክከሩ በሀገሪቱ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከታዩ እጅግ ሰፊና ለውጥ አምጪ እንቅስቃሴዎች መካከል አንዱ መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡
ለብዙ ዓመታት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶች ዛሬም ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚቀሰቀሱ ግጭቶችና የሰላም እጦት በምክንያትነት ሲቀርቡ ይስተዋላል፡፡
ሀገር በቀል እውቀቶችንና ባህላዊ የውይይት እሴቶችን ማዕከል በማድረግ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር እነዚህን የቆዩ ቁርሾዎች በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል፡፡
የጋራ ሀገራዊ ራዕይ እውን የሚሆንበት ይህ መድረክ ከጊዜያዊ ፖለቲካዊ ጥቅም በላይ የሀገሪቱን የዘላቂ ሰላም ጉዞ የሚያሳልጥ ታሪካዊ እድል ነው፡፡
የሁሉም ኢትዮጵያውያን ድምፅ እኩል የሚሰማበት ይህ ሀገራዊ ምክክር የአሸናፊና ተሸናፊ ትርክትን በጋራ መግባባት ላይ በተመሠረተ ባህል የሚተካ ወሳኝ መድረክ ነው።
አንዲት ሀገር ለትናንት ቅራኔዎች ሕዝብን ባሳተፈ መንገድ እውነተኛ መፍትሄ ሳትሰጥ ሰላማዊ ነገን መገንባት አትችልም።
በዚህ መንፈስ በእኩልነት ላይ በተመሰረተ፣ ግልጽ፣ ነጻ እና አሳታፊ ሂደት እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፥ ሀገሪቱን ወደ ብልጽግና የሚያሸጋግር ድልድይ እንዲሁም ከውርስ ህመሟ የሚፈውስ ፍቱን መድሃኒት ነው፡፡
ግጭትና የሕዝቦች መለያየት የሀገርን ሀብት የሚያወድሙና ልማትን የሚያደናቅፉ በመሆናቸው፤ የሀገርን ጥቅም ባስቀደመ የጋራ መግባባት የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሁኔታን በመፍጠር ብሔራዊ ምክክሩ ለጠንካራ ኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት ይጥላል።
የዜጎችን የጋራ መግባባት ጽኑ መሰረት አድርጋ የምትገነባው ሰላማዊት ኢትዮጵያ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቴክኖሎጂና ሌሎች የመሠረተ ልማት ዘርፎች ያላትን አቅም ሙሉ በሙሉ በመጠቀም የዜጎቿን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ትችላለች፡፡
ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ማዕከል እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ እንደመሆኗ፤ አለመግባባትን በውይይት ለመፍታት የጀመረችው ጉዞ አፍሪካውያን ችግሮችን በራሳቸው ለመፍታት ለሚያደርጉት ጥረት መልካም አርአያ ነው።
የተዋሃደችና ደህንነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን በማረጋጋት የቀጣናውን የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድና የጋራ ደህንነት ማረጋገጥ ይቻላታል፡፡
ምክክሩ የአንድ ጊዜ ሁነት ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን ሀገራዊ ተቆርቋሪነት የሚጠይቅ የታሰበበት ረጅም ጉዞ ነው።
አለመግባባቶች የማህበረሰብ ተፈጥሯዊ አካል ቢሆኑም ጠንካራ ሀገር የሚገነባው ግን እነዚህን ልዩነቶች ባስተናገዱበት ጤናማ መንገድ እንደሆነ ይታመናል፡፡
ኢትዮጵያ ከግጭት ይልቅ ውይይትን በማስቀደም እያከናወነች የምትገኘው ሀገራዊ ምክክር አንድነት፣ የተቋማት ጥንካሬና ዘላቂ ሰላም የሚጸናበት አዲስ ምዕራፍ ነው፡፡
ከምንጊዜውም በላይ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በመጠቀም ለወደፊቱ ትውልድ ምቹ ሀገር ለመገንባት ጊዜው አሁን ነው።
በምሕረት ደምሴ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከጥንታዊ ነጻ ሀገረ መንግሥታት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በበርካታ ባህሎች፣ ቋንቋዎችና እሴቶች የተዋቀረች ኅብረብሔራዊት ሀገር ናት፡፡
ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ መኖሪያ የሆነችው ሀገራችን ህልውናዋን አጽንታ ዘመናትን መሻገር የቻለችው በልጆቿ የተባበረ ክንድ ስለመሆኑ ታሪክ ህያው ምስክር ነው።
በእነዚያ ጊዜያት ውስጥ ሰላሟንና ልማቷን ሲፈታተኑ የዘለቁ ቅራኔዎችን በሰላማዊ ውይይት በመፍታት ነገዋን የተሻለ ለማድረግ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ትገኛለች፡፡
ዜጎቿ ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋግጥ የጋራ መግባባት ላይ የሚያደርስ መፍትሄ እንዲያበጁ በገለልተኛ የምክክር ኮሚሽን የሚመራ አሳታፊና አካታች ሀገራዊ መድረክ አበጅታለች፡፡
ይህ አሳታፊነት ምክከሩ በሀገሪቱ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከታዩ እጅግ ሰፊና ለውጥ አምጪ እንቅስቃሴዎች መካከል አንዱ መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡
ለብዙ ዓመታት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶች ዛሬም ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚቀሰቀሱ ግጭቶችና የሰላም እጦት በምክንያትነት ሲቀርቡ ይስተዋላል፡፡
ሀገር በቀል እውቀቶችንና ባህላዊ የውይይት እሴቶችን ማዕከል በማድረግ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር እነዚህን የቆዩ ቁርሾዎች በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል፡፡
የጋራ ሀገራዊ ራዕይ እውን የሚሆንበት ይህ መድረክ ከጊዜያዊ ፖለቲካዊ ጥቅም በላይ የሀገሪቱን የዘላቂ ሰላም ጉዞ የሚያሳልጥ ታሪካዊ እድል ነው፡፡
የሁሉም ኢትዮጵያውያን ድምፅ እኩል የሚሰማበት ይህ ሀገራዊ ምክክር የአሸናፊና ተሸናፊ ትርክትን በጋራ መግባባት ላይ በተመሠረተ ባህል የሚተካ ወሳኝ መድረክ ነው።
አንዲት ሀገር ለትናንት ቅራኔዎች ሕዝብን ባሳተፈ መንገድ እውነተኛ መፍትሄ ሳትሰጥ ሰላማዊ ነገን መገንባት አትችልም።
በዚህ መንፈስ በእኩልነት ላይ በተመሰረተ፣ ግልጽ፣ ነጻ እና አሳታፊ ሂደት እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፥ ሀገሪቱን ወደ ብልጽግና የሚያሸጋግር ድልድይ እንዲሁም ከውርስ ህመሟ የሚፈውስ ፍቱን መድሃኒት ነው፡፡
ግጭትና የሕዝቦች መለያየት የሀገርን ሀብት የሚያወድሙና ልማትን የሚያደናቅፉ በመሆናቸው፤ የሀገርን ጥቅም ባስቀደመ የጋራ መግባባት የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሁኔታን በመፍጠር ብሔራዊ ምክክሩ ለጠንካራ ኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት ይጥላል።
የዜጎችን የጋራ መግባባት ጽኑ መሰረት አድርጋ የምትገነባው ሰላማዊት ኢትዮጵያ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቴክኖሎጂና ሌሎች የመሠረተ ልማት ዘርፎች ያላትን አቅም ሙሉ በሙሉ በመጠቀም የዜጎቿን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ትችላለች፡፡
ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ማዕከል እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ እንደመሆኗ፤ አለመግባባትን በውይይት ለመፍታት የጀመረችው ጉዞ አፍሪካውያን ችግሮችን በራሳቸው ለመፍታት ለሚያደርጉት ጥረት መልካም አርአያ ነው።
የተዋሃደችና ደህንነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን በማረጋጋት የቀጣናውን የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድና የጋራ ደህንነት ማረጋገጥ ይቻላታል፡፡
ምክክሩ የአንድ ጊዜ ሁነት ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን ሀገራዊ ተቆርቋሪነት የሚጠይቅ የታሰበበት ረጅም ጉዞ ነው።
አለመግባባቶች የማህበረሰብ ተፈጥሯዊ አካል ቢሆኑም ጠንካራ ሀገር የሚገነባው ግን እነዚህን ልዩነቶች ባስተናገዱበት ጤናማ መንገድ እንደሆነ ይታመናል፡፡
ኢትዮጵያ ከግጭት ይልቅ ውይይትን በማስቀደም እያከናወነች የምትገኘው ሀገራዊ ምክክር አንድነት፣ የተቋማት ጥንካሬና ዘላቂ ሰላም የሚጸናበት አዲስ ምዕራፍ ነው፡፡
ከምንጊዜውም በላይ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በመጠቀም ለወደፊቱ ትውልድ ምቹ ሀገር ለመገንባት ጊዜው አሁን ነው።
በምሕረት ደምሴ
1 day ago
አልማ ለ2019 በጀት ዓመት ከ4.3 ቢሊዮን ብር በላይ የልማት ሀብት ለማሰባሰብ አቀደ
#ethiopia | የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በመገምገም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን ያስተዋወቀ ሲሆን፣ የዕቅዱን ስኬት ለማረጋገጥ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍን በሙሉ ማጠናቀቅ እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መላኩ ፈንታ አሳስበዋል።
በዋና መሥሪያ ቤቱ ለሁለት ቀናት በተካሄደው የምክክር መድረክ፣ ከ11 ዞኖች የተውጣጡ የማኔጅመንት አባላትና የወረዳ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈው በቀጣዩ ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተወያይተዋል።
ስትራቴጂክና ኢኖቬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበረ መኩሪያ እንደገለጹት፣ በ2019 በጀት ዓመት ከአባላት 4.3 ቢሊዮን ብር፣ ከዳያስፖራ ከ34 ሚሊዮን ዶላር በላይ እና ከአጋር ተቋማት 55 ሚሊዮን ዶላር የልማት ሀብት ለማሰባሰብ ታቅዷል።
በተያዘው ዕቅድ 2,051 የመማሪያ ክፍሎች፣ 38 የጤና ተቋማት፣ 8 የቴክኒክ ኮሌጅ ወርክሾፖች እና 2 ሸዶች እንዲገነቡ ታቅዷል። ይህን ግዙፍ ዕቅድ ለማሳካት የህዝብ ተሳትፎን ማሳደግ፣ ከአጋር አካላትና ከዳያስፖራው ጋር የተጠናከረ ትብብር መፍጠር ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል።
አቶ መላኩ ፈንታ በማጠቃለያ ንግግራቸው፣ በ2019 በጀት ዓመት የዲጂታል ሽግግርን ማፋጠን፣ የአፈጻጸም ጥራትን ማሻሻል፣ የተቋሙን ብራንድ ማጠናከርና ዘላቂ የፋይናንስ አቅም መፍጠር ዋና ትኩረቶች እንደሚሆኑ ገልጸዋል።
በመድረኩ መጨረሻ በ2018 በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የዞንና የወረዳ አልማ ጽሕፈት ቤቶች፣ እንዲሁም ለተመራጭ ሠራተኞች የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በመገምገም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን ያስተዋወቀ ሲሆን፣ የዕቅዱን ስኬት ለማረጋገጥ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍን በሙሉ ማጠናቀቅ እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መላኩ ፈንታ አሳስበዋል።
በዋና መሥሪያ ቤቱ ለሁለት ቀናት በተካሄደው የምክክር መድረክ፣ ከ11 ዞኖች የተውጣጡ የማኔጅመንት አባላትና የወረዳ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈው በቀጣዩ ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተወያይተዋል።
ስትራቴጂክና ኢኖቬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበረ መኩሪያ እንደገለጹት፣ በ2019 በጀት ዓመት ከአባላት 4.3 ቢሊዮን ብር፣ ከዳያስፖራ ከ34 ሚሊዮን ዶላር በላይ እና ከአጋር ተቋማት 55 ሚሊዮን ዶላር የልማት ሀብት ለማሰባሰብ ታቅዷል።
በተያዘው ዕቅድ 2,051 የመማሪያ ክፍሎች፣ 38 የጤና ተቋማት፣ 8 የቴክኒክ ኮሌጅ ወርክሾፖች እና 2 ሸዶች እንዲገነቡ ታቅዷል። ይህን ግዙፍ ዕቅድ ለማሳካት የህዝብ ተሳትፎን ማሳደግ፣ ከአጋር አካላትና ከዳያስፖራው ጋር የተጠናከረ ትብብር መፍጠር ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል።
አቶ መላኩ ፈንታ በማጠቃለያ ንግግራቸው፣ በ2019 በጀት ዓመት የዲጂታል ሽግግርን ማፋጠን፣ የአፈጻጸም ጥራትን ማሻሻል፣ የተቋሙን ብራንድ ማጠናከርና ዘላቂ የፋይናንስ አቅም መፍጠር ዋና ትኩረቶች እንደሚሆኑ ገልጸዋል።
በመድረኩ መጨረሻ በ2018 በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የዞንና የወረዳ አልማ ጽሕፈት ቤቶች፣ እንዲሁም ለተመራጭ ሠራተኞች የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ጤና ልማትና ፀረ‐ወባ ማህበር በአማርኛ የተዘጋጀ የመጀመሪያውን የትምባሆ ቁጥጥር ዲጂታል ዳሽቦርድ ይፋ አደረገ!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ በትምባሆ ቁጥጥር ዙሪያ ያሉ የተበታተኑ መረጃዎችን በአንድ ማዕከል ለማደራጀትና ተደራሽነታቸውን ለማስፋት ያለመው «የትምባሆ ቁጥጥርዳታ ኢኒሺዬቲቭ» (TCDI Ethiopia) ዳሽቦርድ፣ የአማርኛ ገጾቹን በይዘት በማበልፀግ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመረቀ።
ይህ አገራዊ የዲጂታል ዳሽቦርድ ይፋ የተደረገው የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማህበር (HDAMA) ከኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት ልዩ የመክፈቻ መርሃ-ግብር ላይ ነው፡፡
የዳሽቦርዱ በይፋ መከፈት በኢትዮጵያ የትምባሆ ቁጥጥር ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችን እና ሕጋዊ ውሳኔዎችን ሙሉ በሙሉ በምርምርና በፅኑ መረጃ (Data-driven decision making) ላይ የተመሰረቱ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።
ቀደም ሲል በተለያዩ ተቋማት እና ተመራማሪዎች ዘንድ ተበታትነው ይገኙ የነበሩ መረጃዎች በአንድ ቋት መደራጀታቸው፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የሕብረተሰብ ጤና ባለሙያዎች ትክክለኛ አገራዊ ስታቲስቲክሶችን በመጠቀም ፈጣንና ውጤታማ እርምጃዎችን እንዲወስዱ እንደሚያስችላቸዉ ተገልጿል።
የቋንቋ ተደራሽነትና የባለድርሻ አካላት ምክክር የዳሽቦርዱ ገጾች በአማርኛ ቋንቋ ተበልፅገው መቅረባቸው የመረጃ ተደራሽነትን ከመጨመሩ ባለፈ፣ ለመገናኛ ብዙኃን፣ ለተመራማሪዎችና ለመላው ህብረተሰብ የግንዛቤ ማሳደጊያ ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ እንደሚያገለግል ታውቋል።
በማስጀመርያ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የየዘርፉ ባለድርሻ አካላት የዳሽቦርዱን መመረቅ ተከትሎ በስፋት ዉይይት የተካሄደባቸዉ ሲሆን በውይይቱም ዳሽቦርዱ የሚያቀርባቸውን ዳታዎች ለሕግና ፖሊሲ ማሻሻያ አግባብነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ ማዋል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ አስተያየቶችን ተለዋውጠዋል።
ይህንን ጠቃሚ ዳሽቦርድ ወደ አማርኛ በመተርጎም፣ በማበልፀግ እና ለዛሬው ማስተዋወቂያ መድረክ የቴክኒክና የመረጃ ማዕከል ድጋፍ ላደረጉት የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን፣ HDAMA፣ Development Gateway (DG) A Center for the Study of the Economies of Africa (CSEA) እንዲሁም ለሌሎች አጋር አካላት ምስጋና ቀርቧል።
#fastmereja :-በኢትዮጵያ በትምባሆ ቁጥጥር ዙሪያ ያሉ የተበታተኑ መረጃዎችን በአንድ ማዕከል ለማደራጀትና ተደራሽነታቸውን ለማስፋት ያለመው «የትምባሆ ቁጥጥርዳታ ኢኒሺዬቲቭ» (TCDI Ethiopia) ዳሽቦርድ፣ የአማርኛ ገጾቹን በይዘት በማበልፀግ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመረቀ።
ይህ አገራዊ የዲጂታል ዳሽቦርድ ይፋ የተደረገው የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማህበር (HDAMA) ከኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት ልዩ የመክፈቻ መርሃ-ግብር ላይ ነው፡፡
የዳሽቦርዱ በይፋ መከፈት በኢትዮጵያ የትምባሆ ቁጥጥር ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችን እና ሕጋዊ ውሳኔዎችን ሙሉ በሙሉ በምርምርና በፅኑ መረጃ (Data-driven decision making) ላይ የተመሰረቱ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።
ቀደም ሲል በተለያዩ ተቋማት እና ተመራማሪዎች ዘንድ ተበታትነው ይገኙ የነበሩ መረጃዎች በአንድ ቋት መደራጀታቸው፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የሕብረተሰብ ጤና ባለሙያዎች ትክክለኛ አገራዊ ስታቲስቲክሶችን በመጠቀም ፈጣንና ውጤታማ እርምጃዎችን እንዲወስዱ እንደሚያስችላቸዉ ተገልጿል።
የቋንቋ ተደራሽነትና የባለድርሻ አካላት ምክክር የዳሽቦርዱ ገጾች በአማርኛ ቋንቋ ተበልፅገው መቅረባቸው የመረጃ ተደራሽነትን ከመጨመሩ ባለፈ፣ ለመገናኛ ብዙኃን፣ ለተመራማሪዎችና ለመላው ህብረተሰብ የግንዛቤ ማሳደጊያ ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ እንደሚያገለግል ታውቋል።
በማስጀመርያ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የየዘርፉ ባለድርሻ አካላት የዳሽቦርዱን መመረቅ ተከትሎ በስፋት ዉይይት የተካሄደባቸዉ ሲሆን በውይይቱም ዳሽቦርዱ የሚያቀርባቸውን ዳታዎች ለሕግና ፖሊሲ ማሻሻያ አግባብነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ ማዋል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ አስተያየቶችን ተለዋውጠዋል።
ይህንን ጠቃሚ ዳሽቦርድ ወደ አማርኛ በመተርጎም፣ በማበልፀግ እና ለዛሬው ማስተዋወቂያ መድረክ የቴክኒክና የመረጃ ማዕከል ድጋፍ ላደረጉት የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን፣ HDAMA፣ Development Gateway (DG) A Center for the Study of the Economies of Africa (CSEA) እንዲሁም ለሌሎች አጋር አካላት ምስጋና ቀርቧል።
2 days ago
በአገራዊ ምክክር ጉባኤው አመካካሪዎችና ምሁራን ሐሳብ እንዲቀይሩ ለማድረግ ያልተገባ ተፅዕኖ እያሳደሩ መሆኑ ተነገረ
#ethiopia : - "የዘመሙ አካሄዶች ሲታዩ በጊዜውና በወቅቱ ዕርምት ይደረግባቸዋል"
የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን
- 250ው ስልታዊ ቡድን አዲስ አበባና ድሬዳዋ የፌዴራል አካል ሆነው እንዲቀጥሉ መግባባት ላይ መደረሱ ተገልጿል
የአገራዊ የምክክር ጉባዔ በአጀንዳ ጭብጦች ላይ ገለጻና ማብራሪያ እንዲሰጡ የተመደቡ አመካካሪዎች፣ምሁራንና ቃለ ጉባዔ ያዦች፣ ተመካካሪዎች የሚያነሱትን ሃሳብ ባለመቀበልና በተለይ የመጡበትን ተቋም መሠረት ያደረገ አቋም በመያዝ፣ ተመካካሪዎች ሐሳብ እንዲቀይሩና የምክክር ሒደቱ እንዲዘገይ ተፅዕኖ እያሳደሩ መሆኑን ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ ተመካካሪዎች ገለጹ
በተለይ መንግሥትን ወክለው የመጡ አመካካሪዎች እንደ የመንግሥት አደረጃጀትና አገር ግንባታ ያሉ አጀንዳዎችን በተመለከተ ከምክክሩ ሒደት ባፈነገጠ መልኩ የራሳቸውን ሐሳብ ማንፀባረቃቸውን ምንጮች ተናግረዋል።
የመንግሥት አደረጃደት አጀንዳን በተመለከተ እንዲያወያዩ በኮሚሽኑ የተመደቡ አመካካሪዎች በዚህ የተነሳ ለቀናቶች ውይይት እንዳይመሩና ማይክ ብቻ እንዲያቀብሉ በማድረግ፣ በእነርሱ ምትክ ደግሞ ከቡድን መሪዎች ተመርጠው ውይይት እንዲመሩ መደረጉን ገልጸዋል።
ከዚህ አልፎ የኮሚሽኑ አመካካሪዎች ውይይት እንዲመሩ የተደረገበት ሁኔታ መኖሩን ጨምረው ተናግረዋል።
በዚህ የአጀንዳ ሐሳብ በተለይ የተለያዩ የፓርቲዎችን ወክለው የተገኙ ተመካካሪዎች የአመካካሪዎች አካሄድ በተመለከተ ቅሬታ አቅርበው ሁኔታው ከላይ በተገለጸው መንገድ እንዲመራ መደረጉን ተመካካሪዎቹ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
#ethiopia : - "የዘመሙ አካሄዶች ሲታዩ በጊዜውና በወቅቱ ዕርምት ይደረግባቸዋል"
የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን
- 250ው ስልታዊ ቡድን አዲስ አበባና ድሬዳዋ የፌዴራል አካል ሆነው እንዲቀጥሉ መግባባት ላይ መደረሱ ተገልጿል
የአገራዊ የምክክር ጉባዔ በአጀንዳ ጭብጦች ላይ ገለጻና ማብራሪያ እንዲሰጡ የተመደቡ አመካካሪዎች፣ምሁራንና ቃለ ጉባዔ ያዦች፣ ተመካካሪዎች የሚያነሱትን ሃሳብ ባለመቀበልና በተለይ የመጡበትን ተቋም መሠረት ያደረገ አቋም በመያዝ፣ ተመካካሪዎች ሐሳብ እንዲቀይሩና የምክክር ሒደቱ እንዲዘገይ ተፅዕኖ እያሳደሩ መሆኑን ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ ተመካካሪዎች ገለጹ
በተለይ መንግሥትን ወክለው የመጡ አመካካሪዎች እንደ የመንግሥት አደረጃጀትና አገር ግንባታ ያሉ አጀንዳዎችን በተመለከተ ከምክክሩ ሒደት ባፈነገጠ መልኩ የራሳቸውን ሐሳብ ማንፀባረቃቸውን ምንጮች ተናግረዋል።
የመንግሥት አደረጃደት አጀንዳን በተመለከተ እንዲያወያዩ በኮሚሽኑ የተመደቡ አመካካሪዎች በዚህ የተነሳ ለቀናቶች ውይይት እንዳይመሩና ማይክ ብቻ እንዲያቀብሉ በማድረግ፣ በእነርሱ ምትክ ደግሞ ከቡድን መሪዎች ተመርጠው ውይይት እንዲመሩ መደረጉን ገልጸዋል።
ከዚህ አልፎ የኮሚሽኑ አመካካሪዎች ውይይት እንዲመሩ የተደረገበት ሁኔታ መኖሩን ጨምረው ተናግረዋል።
በዚህ የአጀንዳ ሐሳብ በተለይ የተለያዩ የፓርቲዎችን ወክለው የተገኙ ተመካካሪዎች የአመካካሪዎች አካሄድ በተመለከተ ቅሬታ አቅርበው ሁኔታው ከላይ በተገለጸው መንገድ እንዲመራ መደረጉን ተመካካሪዎቹ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ባለፉት 22 ቀናት በስልታዊ ቡድን ደረጃ ሲያካሂድ የቆየውን የምክክር ሂደት ቢያጠናቅቅም፣ ሂደቱ ግን በከባድ የገለልተኝነት ጥያቄዎች፣ በፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እና በተሳታፊዎች አድማ የታጀበ እንደነበር በዋዜማ ራድዮ ተጋልጧል። ለተጨማሪ ሦስት ቀናት በተራዘመው በዚህ የምክክር ምዕራፍ፣ የኮሚሽኑን ተአማኒነት እና የሂደቱን ነጻነት ፈተና ውስጥ የጣሉ በርካታ ክስተቶች ተስተውለዋል።
የምክክር ሂደቱን ነጻነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከከተቱት ዋነኛ ጉዳዮች አንዱ በአወያዮች እና ቃለ-ጉባኤ ያዦች ላይ የቀረበው "ለአንድ ወገን የማድላት" ከባድ ቅሬታ ነው። ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ይህንኑ ቅሬታ ማመናቸው የችግሩን ስፋት ያሳያል። ከዚህም ባሻገር፣ የምክክር መድረኩ የሃሳብ መንሸራሸሪያ ከመሆን ይልቅ፣ ተሳታፊዎች በብሔር፣ በሃይማኖት እና በፓርቲ ማንነት ተደራጅተው የቡድን ፍላጎታቸውን በኃይል የሚያንጸባርቁበት የትግል አውድማ እየመሰለ መምጣቱ ታዝቧል። ኮሚሽኑ ይህንን አደገኛ የቡድን (Factional) እንቅስቃሴ ለማስቆም እስካሁን የወሰደው እርምጃ አለመኖሩ ሂደቱ የተሳሳተ አቅጣጫ እንዳይዝ ስጋት ፈጥሯል።
በተለይም "የሀገር ግንባታ" እና "የአዲስ አበባ ከተማ ሕጋዊ ቁመና" በሚሉት አጀንዳዎች ላይ የተደረጉት ውይይቶች የምክክር መድረኩን ጫፍ ያረገገጡ ነበሩ። የኮሚሽኑ አባል ዶ/ር አምባዬ ኦጋቶ እንዳረጋገጡት፣ በብሔራዊ ቋንቋ እና በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ በተነሳው ከባድ የሃሳብ ልዩነት የተነሳ ተመካካሪዎች ለሁለት ጊዜያት ያህል "አድማ" እስከመምታት እና ሂደቱን እስከማቋረጥ ደርሰዋል። ይህ ሁኔታ በዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ያለውን ጥልቅ ስምጥ የሚያሳይ ነው።
የምክክር ኮሚሽኑን ነጻነት እጅግ አደጋ ላይ ከጣሉት ጉዳዮች መካከል የገዢው ብልጽግና ፓርቲ በሂደቱ ላይ እያደረገ ያለው ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት ይጠቀሳል። ፓርቲው በምክክሩ ላይ የሚሳተፉ አባላቱን ከዋናው መድረክ ውጭ በተለያዩ አዳራሾች (በለሚ ኩራ እና ሲቪል ሰርቪስ) በመሰብሰብ የጋራ አቋም እንዲይዙ አቅጣጫ መስጠቱ፣ ምክክሩን የፓርቲው አጀንዳ ማስፈጸሚያ እያደረገው ነው የሚል ጠንካራ ትችት አስነስቷል። በተለይም "አዲስ አበባ የኦሮሚያ አካል ትሁን" የሚል የተለየ ሀሳብ ያንጸባረቁ የኦሮሚያ ክልል አመራሮችን "አቋማችሁን አስተካክሉ" በማለት ፓርቲው ማስጠንቀቁ፣ መድረኩ የነጻ ሀሳብ መፍለቂያ መሆኑን ጥያቄ ውስጥ ከቶታል።
በሌላ በኩል የምክክር ሂደቱ ግልጽነት በጎደለው አሰራር መተብተቡ ተጋልጧል። የመጀመሪያዎቹን የጥቃቅን እና ንዑስ ቡድን ምክክሮች ያላለፉ አዳዲስ ግለሰቦች፣ በኮሚሽነሮች ግላዊ ፍቃድ ብቻ ወደ ስልታዊ ቡድኑ "በፓራሹት" እየገቡ መሆኑ ተሰምቷል። በተጨማሪም፣ በመጀመሪያ ካልተወያዩበት አጀንዳ በመነሳት፣ መታወቂያቸውን እያስቀየሩ ወደ ሌላ አጀንዳ የተዛወሩ ተሳታፊዎች መኖራቸው፣ የምክረ-ሀሳብ አሰባሰቡን እና የድምጽ አሰጣጡን ታማኝነት በእጅጉ ያጎድፈዋል።
ከሐምሌ 30 ቀን ጀምሮ ለሦስት ቀናት ይካሄዳል የተባለው የርዕሰ ጉዳይ ተመካካሪ ቡድኖች የውሳኔ አሰጣጥ ምዕራፍ፣ ከላይ በተዘረዘሩት የፖለቲካ ጫናዎች፣ የአሰራር ግድፈቶች እና የሃሳብ መከፋፈሎች ምክንያት ከተቀመጠለት ጊዜ በላይ ሊወስድ እንደሚችልና ከባድ ውዝግብ ሊገጥመው እንደሚችል ከወዲሁ ተገምቷል።
የምክክር ሂደቱን ነጻነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከከተቱት ዋነኛ ጉዳዮች አንዱ በአወያዮች እና ቃለ-ጉባኤ ያዦች ላይ የቀረበው "ለአንድ ወገን የማድላት" ከባድ ቅሬታ ነው። ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ይህንኑ ቅሬታ ማመናቸው የችግሩን ስፋት ያሳያል። ከዚህም ባሻገር፣ የምክክር መድረኩ የሃሳብ መንሸራሸሪያ ከመሆን ይልቅ፣ ተሳታፊዎች በብሔር፣ በሃይማኖት እና በፓርቲ ማንነት ተደራጅተው የቡድን ፍላጎታቸውን በኃይል የሚያንጸባርቁበት የትግል አውድማ እየመሰለ መምጣቱ ታዝቧል። ኮሚሽኑ ይህንን አደገኛ የቡድን (Factional) እንቅስቃሴ ለማስቆም እስካሁን የወሰደው እርምጃ አለመኖሩ ሂደቱ የተሳሳተ አቅጣጫ እንዳይዝ ስጋት ፈጥሯል።
በተለይም "የሀገር ግንባታ" እና "የአዲስ አበባ ከተማ ሕጋዊ ቁመና" በሚሉት አጀንዳዎች ላይ የተደረጉት ውይይቶች የምክክር መድረኩን ጫፍ ያረገገጡ ነበሩ። የኮሚሽኑ አባል ዶ/ር አምባዬ ኦጋቶ እንዳረጋገጡት፣ በብሔራዊ ቋንቋ እና በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ በተነሳው ከባድ የሃሳብ ልዩነት የተነሳ ተመካካሪዎች ለሁለት ጊዜያት ያህል "አድማ" እስከመምታት እና ሂደቱን እስከማቋረጥ ደርሰዋል። ይህ ሁኔታ በዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ያለውን ጥልቅ ስምጥ የሚያሳይ ነው።
የምክክር ኮሚሽኑን ነጻነት እጅግ አደጋ ላይ ከጣሉት ጉዳዮች መካከል የገዢው ብልጽግና ፓርቲ በሂደቱ ላይ እያደረገ ያለው ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት ይጠቀሳል። ፓርቲው በምክክሩ ላይ የሚሳተፉ አባላቱን ከዋናው መድረክ ውጭ በተለያዩ አዳራሾች (በለሚ ኩራ እና ሲቪል ሰርቪስ) በመሰብሰብ የጋራ አቋም እንዲይዙ አቅጣጫ መስጠቱ፣ ምክክሩን የፓርቲው አጀንዳ ማስፈጸሚያ እያደረገው ነው የሚል ጠንካራ ትችት አስነስቷል። በተለይም "አዲስ አበባ የኦሮሚያ አካል ትሁን" የሚል የተለየ ሀሳብ ያንጸባረቁ የኦሮሚያ ክልል አመራሮችን "አቋማችሁን አስተካክሉ" በማለት ፓርቲው ማስጠንቀቁ፣ መድረኩ የነጻ ሀሳብ መፍለቂያ መሆኑን ጥያቄ ውስጥ ከቶታል።
በሌላ በኩል የምክክር ሂደቱ ግልጽነት በጎደለው አሰራር መተብተቡ ተጋልጧል። የመጀመሪያዎቹን የጥቃቅን እና ንዑስ ቡድን ምክክሮች ያላለፉ አዳዲስ ግለሰቦች፣ በኮሚሽነሮች ግላዊ ፍቃድ ብቻ ወደ ስልታዊ ቡድኑ "በፓራሹት" እየገቡ መሆኑ ተሰምቷል። በተጨማሪም፣ በመጀመሪያ ካልተወያዩበት አጀንዳ በመነሳት፣ መታወቂያቸውን እያስቀየሩ ወደ ሌላ አጀንዳ የተዛወሩ ተሳታፊዎች መኖራቸው፣ የምክረ-ሀሳብ አሰባሰቡን እና የድምጽ አሰጣጡን ታማኝነት በእጅጉ ያጎድፈዋል።
ከሐምሌ 30 ቀን ጀምሮ ለሦስት ቀናት ይካሄዳል የተባለው የርዕሰ ጉዳይ ተመካካሪ ቡድኖች የውሳኔ አሰጣጥ ምዕራፍ፣ ከላይ በተዘረዘሩት የፖለቲካ ጫናዎች፣ የአሰራር ግድፈቶች እና የሃሳብ መከፋፈሎች ምክንያት ከተቀመጠለት ጊዜ በላይ ሊወስድ እንደሚችልና ከባድ ውዝግብ ሊገጥመው እንደሚችል ከወዲሁ ተገምቷል።
3 days ago
u12e8u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1200u1308u122bu12ca u121du12adu12adu122d u12aeu121au123du1295 u1218u130du1208u132b
#ethiopia #nationaldialogue #ebc ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መግለጫ
#ethiopia #nationaldialogue #ebc
3 days ago
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
*********************
ኢትዮጵያ በታሪኳ ትልቅ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ሀገራችንን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ ልዩነቶችን በሠለጠነ መንገድ ለመፍታት እና በዋና ዋና ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የዚህ ዘመን ትልቁ ታሪካዊ ክስተት ነው።
እንደ ሀገር የገጠሙንን ዘመናት የተሻገሩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ውጥንቅጦችን በዘላቂነት ለመፍታት ከግጭት ይልቅ ውይይትን፣ ከመግፋት ይልቅ አሳታፊነትን ማስቀደም ብቸኛው ዘላቂ መንገድ መሆኑ ግልጽ እውነታ ሆኗል።
የሀገራዊ ምክክሩ ዋነኛ ዓላማ በሕዝቦች መካከል ለዘመናት የዘለቁ እና መፍትሔ ያላገኙ መዋቅራዊ እና ፖለቲካዊ ልዩነቶችን ማጥበብ ነው። ሕዝቡ በነጻነት አስተያየቱን እንዲሰጥ በማድረግ የጋራ እሴቶችን መቅረጽ እንዲሁም ሀገራዊ አንድነትን እና ብዝኃነትን ያጣጣመ የጋራ የወደፊት ራዕይ በመቅረጽ የወል ትርክትን መገንባት ነው።
ይህንን የምክክር ሒደት ልዩ የሚያደርገው ከላይ ወደ ታች የሚወርድ ውሳኔ ሳይሆን፣ ከታች ወደ ላይ የኅብረተሰቡን ድምፅ የሚሰበስብ መሆኑ ነው። እውነተኛ ሀገር ግንባታ የሚጀምረውም የእያንዳንዱ ዜጋ ድምፅ እኩል ዋጋ አግኝቶ ሲደመጥ ብቻ ነው።
የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሃይማኖት አባቶች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማኅበራት በተወካዮቻቸው አማካኝነት የአጀንዳ ግብዓት ማቅረባቸው የሒደቱን ተቀባይነት እና ሕጋዊነት በማጎልበት አሳታፊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በየክልሎቹ እና በከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የተወካዮች መረጣ ሒደቶችን ባከናወነበት ወቅት ሒደቱ ግልጽነት ያለው እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲሄድ ማድረጉ ለምክክሩ ተዓማኒነት የራሱን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የትውልድ አደራ እና የጠንካራ ሀገር ግንባታ መሠረት ሲሆን፣ የዚህ ጉባኤ ስኬት የሚወሰነውም በኮሚሽኑ ጥረት ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዳችን በጎ ፈቃድ፣ አዳምጦ የመረዳት ባህል እና ለሀገራዊ አንድነት በምናሳየው ቁርጠኝነት ነው።
ውጤታማ ምክክር ያደረጉ ሀገራት ከቀውስ ወጥተው ወደ ብልጽግና እንደተሸጋገሩ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በዚሁ መንገድ በሰላም፣ በእኩልነት እና በብልጽግና ላይ የተመሠረተች ሀገር ሆና እንደምትቀጥል እምነታችን የጸና ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dialogue
*********************
ኢትዮጵያ በታሪኳ ትልቅ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ሀገራችንን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ ልዩነቶችን በሠለጠነ መንገድ ለመፍታት እና በዋና ዋና ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የዚህ ዘመን ትልቁ ታሪካዊ ክስተት ነው።
እንደ ሀገር የገጠሙንን ዘመናት የተሻገሩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ውጥንቅጦችን በዘላቂነት ለመፍታት ከግጭት ይልቅ ውይይትን፣ ከመግፋት ይልቅ አሳታፊነትን ማስቀደም ብቸኛው ዘላቂ መንገድ መሆኑ ግልጽ እውነታ ሆኗል።
የሀገራዊ ምክክሩ ዋነኛ ዓላማ በሕዝቦች መካከል ለዘመናት የዘለቁ እና መፍትሔ ያላገኙ መዋቅራዊ እና ፖለቲካዊ ልዩነቶችን ማጥበብ ነው። ሕዝቡ በነጻነት አስተያየቱን እንዲሰጥ በማድረግ የጋራ እሴቶችን መቅረጽ እንዲሁም ሀገራዊ አንድነትን እና ብዝኃነትን ያጣጣመ የጋራ የወደፊት ራዕይ በመቅረጽ የወል ትርክትን መገንባት ነው።
ይህንን የምክክር ሒደት ልዩ የሚያደርገው ከላይ ወደ ታች የሚወርድ ውሳኔ ሳይሆን፣ ከታች ወደ ላይ የኅብረተሰቡን ድምፅ የሚሰበስብ መሆኑ ነው። እውነተኛ ሀገር ግንባታ የሚጀምረውም የእያንዳንዱ ዜጋ ድምፅ እኩል ዋጋ አግኝቶ ሲደመጥ ብቻ ነው።
የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሃይማኖት አባቶች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማኅበራት በተወካዮቻቸው አማካኝነት የአጀንዳ ግብዓት ማቅረባቸው የሒደቱን ተቀባይነት እና ሕጋዊነት በማጎልበት አሳታፊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በየክልሎቹ እና በከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የተወካዮች መረጣ ሒደቶችን ባከናወነበት ወቅት ሒደቱ ግልጽነት ያለው እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲሄድ ማድረጉ ለምክክሩ ተዓማኒነት የራሱን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የትውልድ አደራ እና የጠንካራ ሀገር ግንባታ መሠረት ሲሆን፣ የዚህ ጉባኤ ስኬት የሚወሰነውም በኮሚሽኑ ጥረት ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዳችን በጎ ፈቃድ፣ አዳምጦ የመረዳት ባህል እና ለሀገራዊ አንድነት በምናሳየው ቁርጠኝነት ነው።
ውጤታማ ምክክር ያደረጉ ሀገራት ከቀውስ ወጥተው ወደ ብልጽግና እንደተሸጋገሩ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በዚሁ መንገድ በሰላም፣ በእኩልነት እና በብልጽግና ላይ የተመሠረተች ሀገር ሆና እንደምትቀጥል እምነታችን የጸና ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dialogue
Sponsored by
Surafel
3 days ago
ሰላም፥ እንደምን አደራችሁ?
ምክክር ለተሻለ ብሔራዊ መግባባት
ሀገራዊ ምክክር ከመጠፋፋት ወደ ሰለጠነ፣ ሰላማዊ እና አካታች ሀገራዊ አውድ ለመሸጋገር የወቅቱ ታሪካዊ እድል ነው።
ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችው የሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በጥልቀት ሲታይ ምክክር ከመረጃ ልውውጥ ያለፈ ሰዋዊነትን የሚያገናኝ ድልድይ ነው።
ዛሬ ኢትዮጵያ በብሔራዊ ደረጃ በሚደረግ የታሪክ አዲስ ምዕራፍ እና የታላቅ ምክክር ሂደት ላይ በምትገኝበት በዚህ ወቅት የምክክርን እውነተኛ ምንነትና ጥበብ መረዳት ለአንድትንና ለዘላቂ ሰላም መሰረት ነው።
ሰዎች ወደ ምክክር ሲመጡ ሃሳብን፣ ስብራትን፣ ፍርሃትንና ተስፋን ያለ ስጋት በጠረጴዛ ላይ ዘርግቶ የማየት ነጻነት ከመስጠት ባሻገር ለጥያቄዎቻቸው መልስ እንዲያገኙ መንገድ ያሳያል፡፡
የሀገራዊ ምክክር መድረክ ግብ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር ሳይሆን፤ የጋራ ተስፋዎችንንና ስጋቶችንን በግልጽነት የመጋራት ነጻነትን በመጎናጸፍ የጋራ መፍትሔ መፈለግ ነው።
ምክክሩ እርስ በእርስ ለመደማመጥ ክፍት በመሆን የሌላውን ህመም እና እይታ እንደራስ አድርጎ ለመገንዘብ በር ይከፈታል።
ምክክር የራስን ሃሳብ በሌላ ሰው ድምጽ እና እይታ ለመመልከት የሚያደርግ ሲሆን፤ በሀገራዊ ሂደትም የታሪክና የፖለቲካ ብዥታዎች መልክ የሚይዙት በጋራ በመመካር እና ሌላውን እይታ በማክበር ጨጭምር ነው፡፡
ምክክር ማለት በጨለማ ውስጥ መንገድ የሚጠቁም መብራት ሲሆን መፍትሔውም በጋራ ስምምነት ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡
መጠየቅ፣ መመካከርና ከሌሎች እይታ መማር የደካማነት ሳይሆን፤ የላቀ ብስለትና የጥበብ ምልክት ነው።
ኢትዮጵያ የብሔራዊ ምክክር በምታደርግበት በዚህ ወቅት ይህን የምክክር ጥበብ በመተግበር፣ በመደማመጥ፣ በግልጽነትና በቅንነት ወደተሻለ ሀገራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላም የመሸጋገር መንገድ ጀምራለች።
ምክክር ለተሻለ ብሔራዊ መግባባት
ሀገራዊ ምክክር ከመጠፋፋት ወደ ሰለጠነ፣ ሰላማዊ እና አካታች ሀገራዊ አውድ ለመሸጋገር የወቅቱ ታሪካዊ እድል ነው።
ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችው የሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በጥልቀት ሲታይ ምክክር ከመረጃ ልውውጥ ያለፈ ሰዋዊነትን የሚያገናኝ ድልድይ ነው።
ዛሬ ኢትዮጵያ በብሔራዊ ደረጃ በሚደረግ የታሪክ አዲስ ምዕራፍ እና የታላቅ ምክክር ሂደት ላይ በምትገኝበት በዚህ ወቅት የምክክርን እውነተኛ ምንነትና ጥበብ መረዳት ለአንድትንና ለዘላቂ ሰላም መሰረት ነው።
ሰዎች ወደ ምክክር ሲመጡ ሃሳብን፣ ስብራትን፣ ፍርሃትንና ተስፋን ያለ ስጋት በጠረጴዛ ላይ ዘርግቶ የማየት ነጻነት ከመስጠት ባሻገር ለጥያቄዎቻቸው መልስ እንዲያገኙ መንገድ ያሳያል፡፡
የሀገራዊ ምክክር መድረክ ግብ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር ሳይሆን፤ የጋራ ተስፋዎችንንና ስጋቶችንን በግልጽነት የመጋራት ነጻነትን በመጎናጸፍ የጋራ መፍትሔ መፈለግ ነው።
ምክክሩ እርስ በእርስ ለመደማመጥ ክፍት በመሆን የሌላውን ህመም እና እይታ እንደራስ አድርጎ ለመገንዘብ በር ይከፈታል።
ምክክር የራስን ሃሳብ በሌላ ሰው ድምጽ እና እይታ ለመመልከት የሚያደርግ ሲሆን፤ በሀገራዊ ሂደትም የታሪክና የፖለቲካ ብዥታዎች መልክ የሚይዙት በጋራ በመመካር እና ሌላውን እይታ በማክበር ጨጭምር ነው፡፡
ምክክር ማለት በጨለማ ውስጥ መንገድ የሚጠቁም መብራት ሲሆን መፍትሔውም በጋራ ስምምነት ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡
መጠየቅ፣ መመካከርና ከሌሎች እይታ መማር የደካማነት ሳይሆን፤ የላቀ ብስለትና የጥበብ ምልክት ነው።
ኢትዮጵያ የብሔራዊ ምክክር በምታደርግበት በዚህ ወቅት ይህን የምክክር ጥበብ በመተግበር፣ በመደማመጥ፣ በግልጽነትና በቅንነት ወደተሻለ ሀገራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላም የመሸጋገር መንገድ ጀምራለች።
4 days ago
የዘመናችን ሉዓላዊነት፡ ከድንበር ጥበቃ እስከ ኢኮኖሚያዊና ዲጂታል ልዕልና
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
5 days ago
6 days ago
በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ለትምህርት ጥራት እና ውጤታማነት መጠናከር ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል - የትምህርት ሚኒስቴር
**************************
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ ላይ ውይይት ማድረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች የቀረበው 7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII 2026/27 to 2030/31) ረቂቅ ዕቅድ፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ውጤታማነትን ማጠናከር ዋና ትኩረት እንደሚሆን አመላክቷል።
በረቂቅ ዕቅዱ መሠረት፣ የትምህርት ጥራትን እና ተገቢነትን ለማረጋገጥ ቀደም ሲል የተጀመሩ ሥራዎችን በአዳዲስ አሠራሮች ማጠናከር፣ የትምህርትን ውጤት በተጨባጭ መለካት እና በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ ቅድሚያ የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።
ፕሮግራሙ አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት በውጤታማነት መተግበር፣ ምዘናን በብቃት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ማድረግ፣ የተማሪዎችን የመማር ውጤት ማሻሻል እንዲሁም በቋንቋ፣ በሒሳብ እና በሳይንስ ትምህርቶች ያላቸውን ብቃት ማሳደግን እንደ ዋና ተግባራት አካቷል።
በተጨማሪም የዲጂታል ትምህርትን ማስፋፋት፣ የብሔራዊ ፈተናዎችን ማዘመን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና (TVET) እና በከፍተኛ ትምህርት መካከል ያለውን ቅንጅት ማጠናከር፣ የመምህራንን ሙያዊ ብቃት እና ማበረታቻ ማሻሻል፣ እንዲሁም የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጆችን እና ዩኒቨርሲቲዎችን ማጠናከር በዕቅዱ ውስጥ ተካትተዋል።
ረቂቅ ዕቅዱ የትምህርት ጥራት፣ ተገቢነትን ተደራሽነትን እና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት የተጎዱ የትምህርት ማኅበረሰቦችን መልሶ ማቋቋም፣ ትምህርትን ሳይቋረጥ እንዲዘልቅ የሚያስችል ሥርዓት መገንባት፣ እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች እና የሴት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ እና ውጤታማነት ማረጋገጥ ላይም ልዩ ትኩረት መስጠቱን ያመለክታል።
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ በምክክር መድረኩ ላይ ቀርቦ፣ በክልል እና በከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም በዘርፉ ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት የተደረገበት መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
#ethiopia #ebc #education #ministryofeducation #educationquality
**************************
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ ላይ ውይይት ማድረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች የቀረበው 7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII 2026/27 to 2030/31) ረቂቅ ዕቅድ፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ውጤታማነትን ማጠናከር ዋና ትኩረት እንደሚሆን አመላክቷል።
በረቂቅ ዕቅዱ መሠረት፣ የትምህርት ጥራትን እና ተገቢነትን ለማረጋገጥ ቀደም ሲል የተጀመሩ ሥራዎችን በአዳዲስ አሠራሮች ማጠናከር፣ የትምህርትን ውጤት በተጨባጭ መለካት እና በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ ቅድሚያ የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።
ፕሮግራሙ አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት በውጤታማነት መተግበር፣ ምዘናን በብቃት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ማድረግ፣ የተማሪዎችን የመማር ውጤት ማሻሻል እንዲሁም በቋንቋ፣ በሒሳብ እና በሳይንስ ትምህርቶች ያላቸውን ብቃት ማሳደግን እንደ ዋና ተግባራት አካቷል።
በተጨማሪም የዲጂታል ትምህርትን ማስፋፋት፣ የብሔራዊ ፈተናዎችን ማዘመን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና (TVET) እና በከፍተኛ ትምህርት መካከል ያለውን ቅንጅት ማጠናከር፣ የመምህራንን ሙያዊ ብቃት እና ማበረታቻ ማሻሻል፣ እንዲሁም የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጆችን እና ዩኒቨርሲቲዎችን ማጠናከር በዕቅዱ ውስጥ ተካትተዋል።
ረቂቅ ዕቅዱ የትምህርት ጥራት፣ ተገቢነትን ተደራሽነትን እና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት የተጎዱ የትምህርት ማኅበረሰቦችን መልሶ ማቋቋም፣ ትምህርትን ሳይቋረጥ እንዲዘልቅ የሚያስችል ሥርዓት መገንባት፣ እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች እና የሴት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ እና ውጤታማነት ማረጋገጥ ላይም ልዩ ትኩረት መስጠቱን ያመለክታል።
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ በምክክር መድረኩ ላይ ቀርቦ፣ በክልል እና በከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም በዘርፉ ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት የተደረገበት መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
#ethiopia #ebc #education #ministryofeducation #educationquality
6 days ago
u1270u1218u12abu12abu122a u12e8u12f3u12ebu1235u1353u122b u12a0u1263u120bu1275 u1235u1208 u1200u1308u122bu12ca u12e8u121du12adu12adu122d u1309u1263u12a4u12cd u121du1295 u12a0u1209?
#ebcdotstream #ethiopiannationaldialogue #ethiopiandiaspora #nationalconsensus #u1200u1308u122bu12cau121du12adu12adu122d ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ተመካካሪ የዳያስፓራ አባላት ስለ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ምን አሉ?
#ebcdotstream #ethiopiannationaldialogue #ethiopiandiaspora #nationalconsensus #ሀገራዊምክክር
7 days ago
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች፤ የሀገራዊ ምክክር ታሪካዊ ምዕራፍ
***************
የግጭትን መንገድ ትቶ ወደ ሰላማዊ ውይይት በመምጣት በአንድ መድረክ ላይ በእጃቸው መሳሪያ ሳይሆን ብዕርን በመያዝ ሀሳባቸውን ለማስፈር መላው ኢትዮጵያውያን ተገናኝተዋል።
የሀገር ግንባታ መሠረቱ የሚጠነክረው በግጭት ሳይሆን በመደማመጥ፣ እንዲሁም በጋራ በሚገነባ የሀሳብ ራዕይ መሆኑን በማስረፅ።
በዚህ እሳቤ መሠረት ነው የሀገራዊ ምክክር ሂደት "የሁሉም ሀሳብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል" በሚል መርህ የሁሉንም ድምፅ ለማዳመጥ በር የከፈተው።
ሀገራዊ ምክክር ዓላማው ልክ እንደ ውድድር አሸናፊና ተሸናፊ መለየት ሳይሆን በሕዝቦች ዘንድ የተወከሉ ተወካዮች ተጠናክረው የጋራ መፍትሔ በመፈለግ በሁሉም ውስጥ ኢትዮጵያን አሸናፊ ማድረግ ነው።
ለዚህም ዋና ማሳያ የሆነው ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች በስምንት ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ከመላው ኢትዮጵያ የተወከሉ በቡድን ተከፋፍለው እየተወያዩ ይገኛሉ።
ዓመታትን በትጥቅ ትግል ያሳለፉ ተመካካሪዎች ዛሬ መሣሪያን አስቀምጠው ብዕር በመያዝ ሐሳባቸውን በውይይት እያቀረቡ ይገኛሉ፤ ይህ የሚጠቁመው ምልክት የጦርነትን ኃይል ሳይሆን በመመካከር ችግሮች ሊፈቱ እንደሚችሉ የሚያሳይ ተስፋ ሰጪ ምልክት እና የሰላም መንገድ ለሁሉም ክፍት መሆኑን ያረጋግጣል።
ተመካካሪዎቹ ከ250 አባላት ወደ 50 አባላት፣ በመጨረሻም ወደ 10 አባላት በመከፋፈል ሁሉም ተመካካሪ ያመጣውን የማኅበረሰብ ጥያቄና ሐሳብ ያለ ግፊት፣ ያለ ፍርሃት እና ያለ ተፅዕኖ በነፃነት እንዲያቀርብ ዕድል ተፈጥሮለታል።
ልዩነታቸው ውበታቸው የሆነው የኢትዮጵያውያን ሐሳቦች ሲገናኙ፣ ልዩነቶች ሲከበሩ እና ሁሉም ድምፅ የመደመጥ ዕድል ሲያገኝ፣ የነገዋ ኢትዮጵያ በተስፋ እና በመተማመን የተመሠረተች ትሆናለች። ለዘመናት የቆዩ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የሰላም ባህልን ማጠናከር የዚህ ሂደት ትልቁ ስኬት ነው።
በዚህ መድረክ ላይ የሚጻፉት ቃላት በወረቀት ላይ ብቻ አይቀሩም፤ ወደ ታሪክ በመሻገር ከአዳራሹ አልፈው የቀጣዮቹን ትውልዶች ሊመሩ የሚችሉ እና ተስፋን፣ ይቅርታን፣ የጋራ ራዕይን የሚተክሉ ናቸው።
በዚህም ሀገር የምትገነባው በዜጎቿ የተረጋጋ ውይይት በመሆኑ ወደ ምክክር መምጣት የድክመት ምልክት ሳይሆን የብስለት፣ የኃላፊነት እና የጋራ የወደፊት ዕጣ ፈንታን በሰላማዊ መንገድ ለመወሰን የተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ነው።
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች የሚጽፉት የአንድ ቡድን ታሪክ አይደለም፤ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ የወደፊት ምዕራፍን ነው።
በልዩ እሸቱ
#nationaldialogue #peacebuilding #futureethiopia #inclusion #unityindiversity #reconciliation
***************
የግጭትን መንገድ ትቶ ወደ ሰላማዊ ውይይት በመምጣት በአንድ መድረክ ላይ በእጃቸው መሳሪያ ሳይሆን ብዕርን በመያዝ ሀሳባቸውን ለማስፈር መላው ኢትዮጵያውያን ተገናኝተዋል።
የሀገር ግንባታ መሠረቱ የሚጠነክረው በግጭት ሳይሆን በመደማመጥ፣ እንዲሁም በጋራ በሚገነባ የሀሳብ ራዕይ መሆኑን በማስረፅ።
በዚህ እሳቤ መሠረት ነው የሀገራዊ ምክክር ሂደት "የሁሉም ሀሳብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል" በሚል መርህ የሁሉንም ድምፅ ለማዳመጥ በር የከፈተው።
ሀገራዊ ምክክር ዓላማው ልክ እንደ ውድድር አሸናፊና ተሸናፊ መለየት ሳይሆን በሕዝቦች ዘንድ የተወከሉ ተወካዮች ተጠናክረው የጋራ መፍትሔ በመፈለግ በሁሉም ውስጥ ኢትዮጵያን አሸናፊ ማድረግ ነው።
ለዚህም ዋና ማሳያ የሆነው ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች በስምንት ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ከመላው ኢትዮጵያ የተወከሉ በቡድን ተከፋፍለው እየተወያዩ ይገኛሉ።
ዓመታትን በትጥቅ ትግል ያሳለፉ ተመካካሪዎች ዛሬ መሣሪያን አስቀምጠው ብዕር በመያዝ ሐሳባቸውን በውይይት እያቀረቡ ይገኛሉ፤ ይህ የሚጠቁመው ምልክት የጦርነትን ኃይል ሳይሆን በመመካከር ችግሮች ሊፈቱ እንደሚችሉ የሚያሳይ ተስፋ ሰጪ ምልክት እና የሰላም መንገድ ለሁሉም ክፍት መሆኑን ያረጋግጣል።
ተመካካሪዎቹ ከ250 አባላት ወደ 50 አባላት፣ በመጨረሻም ወደ 10 አባላት በመከፋፈል ሁሉም ተመካካሪ ያመጣውን የማኅበረሰብ ጥያቄና ሐሳብ ያለ ግፊት፣ ያለ ፍርሃት እና ያለ ተፅዕኖ በነፃነት እንዲያቀርብ ዕድል ተፈጥሮለታል።
ልዩነታቸው ውበታቸው የሆነው የኢትዮጵያውያን ሐሳቦች ሲገናኙ፣ ልዩነቶች ሲከበሩ እና ሁሉም ድምፅ የመደመጥ ዕድል ሲያገኝ፣ የነገዋ ኢትዮጵያ በተስፋ እና በመተማመን የተመሠረተች ትሆናለች። ለዘመናት የቆዩ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የሰላም ባህልን ማጠናከር የዚህ ሂደት ትልቁ ስኬት ነው።
በዚህ መድረክ ላይ የሚጻፉት ቃላት በወረቀት ላይ ብቻ አይቀሩም፤ ወደ ታሪክ በመሻገር ከአዳራሹ አልፈው የቀጣዮቹን ትውልዶች ሊመሩ የሚችሉ እና ተስፋን፣ ይቅርታን፣ የጋራ ራዕይን የሚተክሉ ናቸው።
በዚህም ሀገር የምትገነባው በዜጎቿ የተረጋጋ ውይይት በመሆኑ ወደ ምክክር መምጣት የድክመት ምልክት ሳይሆን የብስለት፣ የኃላፊነት እና የጋራ የወደፊት ዕጣ ፈንታን በሰላማዊ መንገድ ለመወሰን የተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ነው።
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች የሚጽፉት የአንድ ቡድን ታሪክ አይደለም፤ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ የወደፊት ምዕራፍን ነው።
በልዩ እሸቱ
#nationaldialogue #peacebuilding #futureethiopia #inclusion #unityindiversity #reconciliation
Sponsored by
Surafel
7 days ago
“በውይይት፣ በምክክር ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ አካሄድ ብንከተል ዘላቂ ሰላም ያረጋግጣል። ከዛ ውጭ ያለው መፍትሄ ለአማራም አይጠቅምም፣ ለትግራይም አይጠቅምም፣ ለኢትዮጵያም አይጠቅምም።” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ethiopia #ebc #pmabiyahmed #currentaffairs
#ethiopia #ebc #pmabiyahmed #currentaffairs
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢትዮጵያ ላለፉት ሶስት ዓመታት ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ የምክክር ሂደት አሁን ላይ ሀገሪቱን ክፉኛ ወደሚያወዛግቡ ፖለቲካዊ ጥያቄዎች መግባቱን ተከትሎ፣ ታዋቂው የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተንታኝ አቶ ክቡር ገና የሂደቱን መነሻ ሀሳብ አጥብቀው ተቹ። አቶ ክቡር ዛሬ ባወጡት ጽሁፍ፣ ጉባኤው መጀመር የነበረበት "ኢትዮጵያውያን በጋራ መገንባት የሚፈልጉት የወደፊት ዕጣ ፈንታ ምንድን ነው?" በሚለው ጥያቄ ሆኖ ሳለ፣ ሂደቱ ግን "ኢትዮጵያውያንን የሚከፋፍላቸው ምንድን ነው?" በሚል የተሳሳተ የመነሻ ጥያቄ መጀመሩን አስምረውበታል።
የምክክር ኮሚሽኑ በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱን ሰንደቅ ዓላማ፣ ምልክቶች፣ የወደፊቱን የህገ-መንግስት ቅርጽ፣ ፓርላማዊ ወይስ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ባለቤትነት፣ የፌደራሊዝም፣ የማንነት፣ የታሪክ እና የስልጣን ጉዳዮችን ወደ ጠረጴዛ አምጥቷል። እነዚህ ጥያቄዎች እጅግ አስፈላጊ ቢሆኑም፣ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ደረጃ የማይግባቡባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን አቶ ክቡር ያስረዳሉ።
የፖለቲካ ፍልስፍና እንደሚያሳየው፣ ሀገራት በህገ-መንግስት ወይም በሰንደቅ ዓላማ ብቻ በአንድነት ሊቆሙ አይችሉም። ይልቁንም ህዝቦች ልዩነቶቻቸው እንደተጠበቁ ሆነው የጋራ መጻኢ ጊዜን ለመምረጥ ሲወስኑ ብቻ ነው ሀገራት ሊቀጥሉ የሚችሉት። ይህ ምርጫ ደግሞ ከህገ-መንግስት ቀረጻ በፊት ሊመጣ የሚገባው እንጂ በኋላ የሚመጣ አለመሆኑን ተንታኙ ይሞግታሉ። የምክክር ሂደቱ ግን ይህንን ተፈጥሯዊ ቅደም ተከተል የገለበጠው ይመስላል።
የምክክር ሂደቱ ዋነኛ ሀገራዊ ቅራኔዎችን በመለየት እና ተወካዮችን በማሰባሰብ መግባባት ላይ መድረስ ይቻላል የሚል ፍልስፍናን የተከተለ ይመስላል። ነገር ግን ታሪክ እንደሚያሳየው፣ ሰዎች ከጥልቅ ቅራኔዎቻቸው በመነሳት አንድነትን ሲያገኙ አይታይም፤ ይልቁንም የየራሳቸውን አቋም በበለጠ ሁኔታ መከላከልን ነው የሚማሩት። በታሪክ አተረጓጎም ክርክር የሚጀምር ውይይት፣ በተሻለ የተብራራ የታሪክ ልዩነትን በማስገኘት ያበቃል። ተሳታፊዎች ይበልጥ ተማምነው ሳይሆን፣ እርስ በርስ በተሻለ ሁኔታ ተረድተው ብቻ ሊወጡ ይችላሉ። አቶ ክቡር እንደሚሉት፣ መደማመጥ ማለት ሀገር መገንባት ማለት አይደለም።
የምክክር ሂደቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የህዝብን ብሶት ከመሰብሰብ ይልቅ የህዝብን ምኞት ማሰባሰብ ነበረበት። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያ እንደ አንድ ሀገር ለምን መቀጠል እንዳለባት፣ ለየብቻ ሊገነባ የማይችል ነገር ግን በጋራ ሊገነባ የሚችል የወደፊት ጊዜ ምን እንደሆነ፣ እንዲሁም ለዚህ የጋራ ዕጣ ፈንታ ለመጠየቅ ሳይሆን ለመሰዋት ዝግጁ የሆነው ምን እንደሆነ ቢጠየቅ ኖሮ አቅጣጫው በተቀየረ ነበር። እነዚህ ጥያቄዎች ቢነሱ ኖሮ ውይይቱ ከባለቤትነት ይልቅ ወደ ዓላማ፣ ከመብት ይልቅ ወደ ኃላፊነት እንዲሁም ከትናንት ይልቅ ወደ ነገ በተሸጋገረ ነበር።
የሂደቱን ተአማኒነት አደጋ ላይ የሚጥለው ሌላው ትልቅ ፈተና፣ መሳተፍ የነበረባቸው ወሳኝ አካላት በጉባኤው ውስጥ አለመኖራቸው ነው። ታዋቂ የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች በእስር ላይ ይገኛሉ፣ አንዳንዶቹ በስደት ላይ ናቸው፣ ሌሎች ደግሞ በትጥቅ ትግል ውስጥ ተሳትፈዋል። ለኢትዮጵያ የተለየ ራዕይ ያላቸው በርካታ ተጽእኖ ፈጣሪ ምሁራን እና የፖለቲካ ተዋናዮች ሂደቱን እንደራሳቸው አድርገው አይመለከቱትም። ሰላም ብዙ ጊዜ የሚደራደረው አስቀድመው በሚግባቡ ሰዎች መካከል ሳይሆን፣ በመካከላቸው ጥልቅ ያለመተማመን ባለባቸው አካላት መካከል በመሆኑ፣ ወሳኝ ድምጽ ያላቸው አካላት ሁሉ በውጪ ከመቅረት ይልቅ በአዳራሹ ውስጥ መገኘታቸው እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ጽሁፉ ያትታል።
ታሪክ የሚያስታውሰው ስንት ውይይቶች እንደተካሄዱ፣ ስንት አጀንዳዎች እንደተሰበሰቡ ወይም ስንት ሪፖርቶች እንደወጡ አይደለም። አቶ ክቡር ገና በመደምደሚያቸው እንዳሰፈሩት፣ ታሪክ የሚዘክረው "ምክክሩ የኢትዮጵያን የጋራ ብሔራዊ ማንነት አጠናክሯል ወይስ በቀላሉ የኢትዮጵያን አለመግባባቶች በተሻለ ሁኔታ አደራጅቷል?" የሚለውን ብቻ ነው። ተሳታፊዎች ከጉባኤው ሲወጡ "አሁን በጋራ ምን ዓይነት የወደፊት ጊዜ መገንባት እንችላለን?" ብለው ከጠየቁ፣ ሀገርን የመገን ባት እጅግ ወሳኝ ስራ ተጀምሯል ማለት ነው። ይህ ደግሞ የምክክር ጉባኤው ሊጀምርበት ይገባ የነበረው ትክክለኛው የመጀመሪያ ጥያቄ መሆን ነበረበት።
የምክክር ኮሚሽኑ በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱን ሰንደቅ ዓላማ፣ ምልክቶች፣ የወደፊቱን የህገ-መንግስት ቅርጽ፣ ፓርላማዊ ወይስ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ባለቤትነት፣ የፌደራሊዝም፣ የማንነት፣ የታሪክ እና የስልጣን ጉዳዮችን ወደ ጠረጴዛ አምጥቷል። እነዚህ ጥያቄዎች እጅግ አስፈላጊ ቢሆኑም፣ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ደረጃ የማይግባቡባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን አቶ ክቡር ያስረዳሉ።
የፖለቲካ ፍልስፍና እንደሚያሳየው፣ ሀገራት በህገ-መንግስት ወይም በሰንደቅ ዓላማ ብቻ በአንድነት ሊቆሙ አይችሉም። ይልቁንም ህዝቦች ልዩነቶቻቸው እንደተጠበቁ ሆነው የጋራ መጻኢ ጊዜን ለመምረጥ ሲወስኑ ብቻ ነው ሀገራት ሊቀጥሉ የሚችሉት። ይህ ምርጫ ደግሞ ከህገ-መንግስት ቀረጻ በፊት ሊመጣ የሚገባው እንጂ በኋላ የሚመጣ አለመሆኑን ተንታኙ ይሞግታሉ። የምክክር ሂደቱ ግን ይህንን ተፈጥሯዊ ቅደም ተከተል የገለበጠው ይመስላል።
የምክክር ሂደቱ ዋነኛ ሀገራዊ ቅራኔዎችን በመለየት እና ተወካዮችን በማሰባሰብ መግባባት ላይ መድረስ ይቻላል የሚል ፍልስፍናን የተከተለ ይመስላል። ነገር ግን ታሪክ እንደሚያሳየው፣ ሰዎች ከጥልቅ ቅራኔዎቻቸው በመነሳት አንድነትን ሲያገኙ አይታይም፤ ይልቁንም የየራሳቸውን አቋም በበለጠ ሁኔታ መከላከልን ነው የሚማሩት። በታሪክ አተረጓጎም ክርክር የሚጀምር ውይይት፣ በተሻለ የተብራራ የታሪክ ልዩነትን በማስገኘት ያበቃል። ተሳታፊዎች ይበልጥ ተማምነው ሳይሆን፣ እርስ በርስ በተሻለ ሁኔታ ተረድተው ብቻ ሊወጡ ይችላሉ። አቶ ክቡር እንደሚሉት፣ መደማመጥ ማለት ሀገር መገንባት ማለት አይደለም።
የምክክር ሂደቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የህዝብን ብሶት ከመሰብሰብ ይልቅ የህዝብን ምኞት ማሰባሰብ ነበረበት። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያ እንደ አንድ ሀገር ለምን መቀጠል እንዳለባት፣ ለየብቻ ሊገነባ የማይችል ነገር ግን በጋራ ሊገነባ የሚችል የወደፊት ጊዜ ምን እንደሆነ፣ እንዲሁም ለዚህ የጋራ ዕጣ ፈንታ ለመጠየቅ ሳይሆን ለመሰዋት ዝግጁ የሆነው ምን እንደሆነ ቢጠየቅ ኖሮ አቅጣጫው በተቀየረ ነበር። እነዚህ ጥያቄዎች ቢነሱ ኖሮ ውይይቱ ከባለቤትነት ይልቅ ወደ ዓላማ፣ ከመብት ይልቅ ወደ ኃላፊነት እንዲሁም ከትናንት ይልቅ ወደ ነገ በተሸጋገረ ነበር።
የሂደቱን ተአማኒነት አደጋ ላይ የሚጥለው ሌላው ትልቅ ፈተና፣ መሳተፍ የነበረባቸው ወሳኝ አካላት በጉባኤው ውስጥ አለመኖራቸው ነው። ታዋቂ የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች በእስር ላይ ይገኛሉ፣ አንዳንዶቹ በስደት ላይ ናቸው፣ ሌሎች ደግሞ በትጥቅ ትግል ውስጥ ተሳትፈዋል። ለኢትዮጵያ የተለየ ራዕይ ያላቸው በርካታ ተጽእኖ ፈጣሪ ምሁራን እና የፖለቲካ ተዋናዮች ሂደቱን እንደራሳቸው አድርገው አይመለከቱትም። ሰላም ብዙ ጊዜ የሚደራደረው አስቀድመው በሚግባቡ ሰዎች መካከል ሳይሆን፣ በመካከላቸው ጥልቅ ያለመተማመን ባለባቸው አካላት መካከል በመሆኑ፣ ወሳኝ ድምጽ ያላቸው አካላት ሁሉ በውጪ ከመቅረት ይልቅ በአዳራሹ ውስጥ መገኘታቸው እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ጽሁፉ ያትታል።
ታሪክ የሚያስታውሰው ስንት ውይይቶች እንደተካሄዱ፣ ስንት አጀንዳዎች እንደተሰበሰቡ ወይም ስንት ሪፖርቶች እንደወጡ አይደለም። አቶ ክቡር ገና በመደምደሚያቸው እንዳሰፈሩት፣ ታሪክ የሚዘክረው "ምክክሩ የኢትዮጵያን የጋራ ብሔራዊ ማንነት አጠናክሯል ወይስ በቀላሉ የኢትዮጵያን አለመግባባቶች በተሻለ ሁኔታ አደራጅቷል?" የሚለውን ብቻ ነው። ተሳታፊዎች ከጉባኤው ሲወጡ "አሁን በጋራ ምን ዓይነት የወደፊት ጊዜ መገንባት እንችላለን?" ብለው ከጠየቁ፣ ሀገርን የመገን ባት እጅግ ወሳኝ ስራ ተጀምሯል ማለት ነው። ይህ ደግሞ የምክክር ጉባኤው ሊጀምርበት ይገባ የነበረው ትክክለኛው የመጀመሪያ ጥያቄ መሆን ነበረበት።
7 days ago
"ዘመናዊቷን ኢትዮጵያ ከአማራና ኦሮሞ ውህደት ውጭ ማየት አይቻልም"
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገሪቱን ለመቀየር ፖለቲካውንም ሆነ ኢኮኖሚውን ጎን ለጎን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበር ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩም የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአማራና ከኦሮሞ ሕዝቦች ጥብቅ ውህደትና ትስስር ውጭ ሊታይ አይችልም። የዓድዋ ድልም የዚሁ ታሪካዊ አንድነት ትልቁ ማሳያ ነው፤ አብሮ የመኖር ባህልም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ በሀገራችን ስልጣንን በኃይልና በሰው ግድያ ለመያዝ የመሞከር አጥፊ ባህል እንደነበር አውስተዋል። በዚህም የሰኔ 15ቱ ክስተት በለውጡ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሰዎች ያጣንበት የሕመም ጠባሳችን ነው ብለዋል።
ሆኖም ሕዝቡ ለውጡን በሙሉ ልብ የተቀበለ ሲሆን፣ በአንድነትና በትብብር አንዲት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደምንችል በምርጫው ወቅት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
***
“የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎች ለአጭር ጊዜ እፎይታ ተብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት መመለስ አይቻልም”
በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚነሡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ለአጭር ጊዜ እፎይታ ብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ መመለስ እንደማይቻል እና ጉዳዩ በሕግ አግባብ እና በሀገራዊ ምክክር ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የወልቃይትን ጉዳይ እንደ አብነት በማንሣት በትግራይም ሆነ በአማራ ክልል በኩል የሚነሡ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ዘላቂ መፍትሔው የሁለቱንም ሕዝቦች ጥቅም በማይጎዳ፣ በውይይት እና ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት ሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ካልሆነ መልሶ ለግጭት የሚዳርግ ቆይቶ የሚፈነዳ ቦምብ ይሆናል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በዚህም በፓርቲ ውስጥ የነበረውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራር ማስተካከል እና የክልሎችን ራስን የማስተዳደር መብት ማክበር ተችሏል ብለዋል ።
በተጨማሪም በመንግሥት ተቋማት አካታችነትን ማረጋገጥ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በካቢኔ እና በፖለቲካ ምኅዳር ማሳተፍ እንዲሁም አግላይ የነበሩ ትርክቶችን ማረቅም ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።
***
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል-
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሰኔ 15ቱን መጥፎ ክስተት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታሪክን ማዛባት ለነገው ትውልድ የሚተርፍ እዳ ነው ብለዋል።
ለውጥን ለማምጣት በጽናት ሲሰሩ የነበሩ የለውጥ አበጋዞችን ያጣንበት፣ በፖለቲካው መካከል የመተማመን መንፈስ እንዲሸረሸር ያደረገ እና የስልጣን ሽሚያ በሃይል የማስከበር መጥፎ ባህልን ያስቀጠለ አጋጣሚ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ እለቱና ስለተፈጠረው ክስተት ሲያብራሩ፤ እለቱ ቅዳሜ ነበረ፤ መረጃውን እንደሰማሁ ለህዝብ መግለጫ እንዲሰጥ ሚዲያዎች እንዲጠሩ አደረግኩ፤ ፋና እና ኢቢሲ በምሽቱ ፈጥነው አልደረሱም ነበር፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ግን እዚሁ 4 ኪሎ አቅራቢያ ስለነበር በፍጥነት ደረሰ ብለዋል።
መግለጫውን እኔ ቤት ሆኜ ለአሚኮ ሰጠሁ፤ በኋላ ግን 'ባህር ዳር ሆኖ መግለጫ ሰጠ' ተብሎ የሴራ ትንተና ተፈበረከበት በማለት አስታውሰዋል።
ይህ ክስተት ያስተማረን ትልቅ ሀቅም ታሪክን በትክክል አለማስቀመጥና ማዛባት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ እዳ ያተርፋል ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳይም ሟችም በአንድ ላይ 'ጀግና' የሚደረግበት የታሪክ ስብራት ሊቆም እንደሚገባም በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
***
"በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች በዘመናት መካከል አብረው ሲኖሩ በብዙ መልኩ የተጋመዱ፣ የተሳሰሩ፣ የተጋቡ፣ የተዋለዱ በጋራ የኖሩ ናቸው''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ethiopia #pmabiyahmed #currentaffairs #pmabiyahmed #amico #ethiopia #medemer #amharaandoromo #ethiopianunity
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገሪቱን ለመቀየር ፖለቲካውንም ሆነ ኢኮኖሚውን ጎን ለጎን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበር ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩም የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአማራና ከኦሮሞ ሕዝቦች ጥብቅ ውህደትና ትስስር ውጭ ሊታይ አይችልም። የዓድዋ ድልም የዚሁ ታሪካዊ አንድነት ትልቁ ማሳያ ነው፤ አብሮ የመኖር ባህልም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ በሀገራችን ስልጣንን በኃይልና በሰው ግድያ ለመያዝ የመሞከር አጥፊ ባህል እንደነበር አውስተዋል። በዚህም የሰኔ 15ቱ ክስተት በለውጡ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሰዎች ያጣንበት የሕመም ጠባሳችን ነው ብለዋል።
ሆኖም ሕዝቡ ለውጡን በሙሉ ልብ የተቀበለ ሲሆን፣ በአንድነትና በትብብር አንዲት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደምንችል በምርጫው ወቅት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
***
“የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎች ለአጭር ጊዜ እፎይታ ተብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት መመለስ አይቻልም”
በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚነሡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ለአጭር ጊዜ እፎይታ ብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ መመለስ እንደማይቻል እና ጉዳዩ በሕግ አግባብ እና በሀገራዊ ምክክር ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የወልቃይትን ጉዳይ እንደ አብነት በማንሣት በትግራይም ሆነ በአማራ ክልል በኩል የሚነሡ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ዘላቂ መፍትሔው የሁለቱንም ሕዝቦች ጥቅም በማይጎዳ፣ በውይይት እና ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት ሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ካልሆነ መልሶ ለግጭት የሚዳርግ ቆይቶ የሚፈነዳ ቦምብ ይሆናል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በዚህም በፓርቲ ውስጥ የነበረውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራር ማስተካከል እና የክልሎችን ራስን የማስተዳደር መብት ማክበር ተችሏል ብለዋል ።
በተጨማሪም በመንግሥት ተቋማት አካታችነትን ማረጋገጥ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በካቢኔ እና በፖለቲካ ምኅዳር ማሳተፍ እንዲሁም አግላይ የነበሩ ትርክቶችን ማረቅም ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።
***
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል-
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሰኔ 15ቱን መጥፎ ክስተት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታሪክን ማዛባት ለነገው ትውልድ የሚተርፍ እዳ ነው ብለዋል።
ለውጥን ለማምጣት በጽናት ሲሰሩ የነበሩ የለውጥ አበጋዞችን ያጣንበት፣ በፖለቲካው መካከል የመተማመን መንፈስ እንዲሸረሸር ያደረገ እና የስልጣን ሽሚያ በሃይል የማስከበር መጥፎ ባህልን ያስቀጠለ አጋጣሚ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ እለቱና ስለተፈጠረው ክስተት ሲያብራሩ፤ እለቱ ቅዳሜ ነበረ፤ መረጃውን እንደሰማሁ ለህዝብ መግለጫ እንዲሰጥ ሚዲያዎች እንዲጠሩ አደረግኩ፤ ፋና እና ኢቢሲ በምሽቱ ፈጥነው አልደረሱም ነበር፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ግን እዚሁ 4 ኪሎ አቅራቢያ ስለነበር በፍጥነት ደረሰ ብለዋል።
መግለጫውን እኔ ቤት ሆኜ ለአሚኮ ሰጠሁ፤ በኋላ ግን 'ባህር ዳር ሆኖ መግለጫ ሰጠ' ተብሎ የሴራ ትንተና ተፈበረከበት በማለት አስታውሰዋል።
ይህ ክስተት ያስተማረን ትልቅ ሀቅም ታሪክን በትክክል አለማስቀመጥና ማዛባት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ እዳ ያተርፋል ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳይም ሟችም በአንድ ላይ 'ጀግና' የሚደረግበት የታሪክ ስብራት ሊቆም እንደሚገባም በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
***
"በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች በዘመናት መካከል አብረው ሲኖሩ በብዙ መልኩ የተጋመዱ፣ የተሳሰሩ፣ የተጋቡ፣ የተዋለዱ በጋራ የኖሩ ናቸው''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ethiopia #pmabiyahmed #currentaffairs #pmabiyahmed #amico #ethiopia #medemer #amharaandoromo #ethiopianunity
8 days ago
በምክክር ሂደቱ የቀረቡ የአጀንዳ ምክረ ሀሳቦች በ75 በመቶ አባላት ተቀባይነት ካገኙ ከመግባባት እንደተደረሰ ጠቋሚ ነዉ የተባለለት የምክክር ምዕራፍ በመጪዉ ሰኞ ይጀመራል ተባለ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በባለፉት ሁለት ቀናት 250 ተመካካሪዎች በቡድን በመከፋፈል ዉይይት ሲያደርጉ መቆየታቸዉን ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ አሳዉቋል።
በዚህ የምክክር ምዕራፍ የተጀራጁ ምክረ ሀሳቦች 5መቶ አባላት ወዳሉት ቀርበዉ ፤ እነዚህ የ5 መቶ አባላት ተመካካሪዎች ቡድን ለውሳኔ መግባቢያ ሀሳብ ያደራጁታል ተብሏል።
እንደ ኮሚሽኑ መረጃ 5መቶ አባላት ያሏቸው ተመካካሪ ቡድኖች እያንዳንዳቸው በአንድ አጀንዳ ላይ የሚወያዩ ሲሆን፤በአጀንዳው ላይ ከመግባባት ደረሰ የሚባለው በዉይይቱ የመነጩ የመፍትሄ ሀሳቦች በ75 በመቶ አባላቱ ከመግባባት የተደረሰባቸው ወይም ተቀባይነት ያገኙ እንደሆነ ነው።
ሌላዉ የምክክሩ የውሳኔ አሰጣጥ አካል የሆነው አካሄድ ከክልል እና ከፌደራል አባላት ተመርጠዉ የሚዋቀረዉ የክልላዊ ጉባኤ ሲሆን፤በዛሬዉ ዕለት 330 ተወካዮች እንደተመረጡ ኮሚሽኑ በሰጠዉ መግለጫ ተናግሯል።
12 ክልሎች እና 2 ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የፌደራል ተቋማት ከእያንዳንዳቸው 22 ተወካዮች ተወጣጥተው የተዋቀረ ቡድን መሆኑን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ ገልፀዋል።
በዚህ ቡድን 70% ድምጽ ባለማግኘቱ ውድቅ በተደረገ የአጀንዳ የምክር ሀሳብ ላይ ቢያንስ ሶስት ክልሎች ቅሬታ ያቀረቡ እንደሆነ ያንን የሚፈቱበት አግባብ የሚኖር ነዉ ተብሏል። በቀደሙት የድምፅ አሰጣጥ ሂደቶች 70 በመቶ ድምጽ ማግኘት ሳይችል የቀረ የአጀንዳ ምክረ ሀሳብ በዚህ ቡድን በድጋሚ ታይቶ የሚጠበቀውን ዝቅተኛ የ70 በመቶ መስፈርት ካሟላ ወደ ሚቀጥለው ምዕራፍ የሚሸጋገር ይሆናል።
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በባለፉት ሁለት ቀናት 250 ተመካካሪዎች በቡድን በመከፋፈል ዉይይት ሲያደርጉ መቆየታቸዉን ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ አሳዉቋል።
በዚህ የምክክር ምዕራፍ የተጀራጁ ምክረ ሀሳቦች 5መቶ አባላት ወዳሉት ቀርበዉ ፤ እነዚህ የ5 መቶ አባላት ተመካካሪዎች ቡድን ለውሳኔ መግባቢያ ሀሳብ ያደራጁታል ተብሏል።
እንደ ኮሚሽኑ መረጃ 5መቶ አባላት ያሏቸው ተመካካሪ ቡድኖች እያንዳንዳቸው በአንድ አጀንዳ ላይ የሚወያዩ ሲሆን፤በአጀንዳው ላይ ከመግባባት ደረሰ የሚባለው በዉይይቱ የመነጩ የመፍትሄ ሀሳቦች በ75 በመቶ አባላቱ ከመግባባት የተደረሰባቸው ወይም ተቀባይነት ያገኙ እንደሆነ ነው።
ሌላዉ የምክክሩ የውሳኔ አሰጣጥ አካል የሆነው አካሄድ ከክልል እና ከፌደራል አባላት ተመርጠዉ የሚዋቀረዉ የክልላዊ ጉባኤ ሲሆን፤በዛሬዉ ዕለት 330 ተወካዮች እንደተመረጡ ኮሚሽኑ በሰጠዉ መግለጫ ተናግሯል።
12 ክልሎች እና 2 ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የፌደራል ተቋማት ከእያንዳንዳቸው 22 ተወካዮች ተወጣጥተው የተዋቀረ ቡድን መሆኑን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ ገልፀዋል።
በዚህ ቡድን 70% ድምጽ ባለማግኘቱ ውድቅ በተደረገ የአጀንዳ የምክር ሀሳብ ላይ ቢያንስ ሶስት ክልሎች ቅሬታ ያቀረቡ እንደሆነ ያንን የሚፈቱበት አግባብ የሚኖር ነዉ ተብሏል። በቀደሙት የድምፅ አሰጣጥ ሂደቶች 70 በመቶ ድምጽ ማግኘት ሳይችል የቀረ የአጀንዳ ምክረ ሀሳብ በዚህ ቡድን በድጋሚ ታይቶ የሚጠበቀውን ዝቅተኛ የ70 በመቶ መስፈርት ካሟላ ወደ ሚቀጥለው ምዕራፍ የሚሸጋገር ይሆናል።
Seledadotio
Seledadotio
8 days ago
ምክክሩ ወደ ጦርነት በወሰዱን አጀንዳዎች ላይ ተነጋግሮ ሰላምን ማምጣት የሚያስችል ነው - መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክክሩ ወደ ጦርነት በወሰዱን አጀንዳዎች ላይ ተነጋግሮ ሰላምን ማምጣት የሚያስችል በመሆኑ ሕዝቡ በትልቅ ተስፋ እየጠበቀው ነው አሉ የሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)፡፡
ዋና ኮሚሽነሩ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተከፈተው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አሁናዊ ሂደትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በሀገር ውስጥም በውጭም ያሉ ኢትዮጵያውያን ሰላም እንዲረጋገጥና መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው በምክክሩ ላይ ትልቅ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡
ምክክሩ ለዘመናት ወደ ጭቅጭቅና ወደ ጦርነት በወሰዱን አጀንዳዎች ላይ በመነጋገርና አቅጣጫ በማስቀመጥ ወደ ሰላም እንድንመጣ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
ተመካካሪዎች የተለያየ ጽንፍ የያዙና የሚጋጩ ሀሳቦችን ይዘው ቢመጡም ወደ መሃል ለመምጣት የሚያደርጉት ጥረት ለምክክሩ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል ነው ያሉት፡፡
ወደ መሃል መምጣት ሀገርን የማስቀደም ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ ከራሳቸው ጥያቄዎች ባሻገር በጋራ የሚጠቅሙ ጥያቄዎችን ማንሳት መጀመራቸውን አስረድተዋል፡፡
ይህም በቀጣይ በሚደረገው ዋናው ጉባኤ ላይ እየዳበረ ሀገርን ባስቀደመ መንፈስ ምክክሩ ይበልጥ እየተጠናከረ እንደሚሄድ ነው የገለጹት፡፡
በኃይለማርያም ተገኝ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክክሩ ወደ ጦርነት በወሰዱን አጀንዳዎች ላይ ተነጋግሮ ሰላምን ማምጣት የሚያስችል በመሆኑ ሕዝቡ በትልቅ ተስፋ እየጠበቀው ነው አሉ የሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)፡፡
ዋና ኮሚሽነሩ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተከፈተው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አሁናዊ ሂደትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በሀገር ውስጥም በውጭም ያሉ ኢትዮጵያውያን ሰላም እንዲረጋገጥና መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው በምክክሩ ላይ ትልቅ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡
ምክክሩ ለዘመናት ወደ ጭቅጭቅና ወደ ጦርነት በወሰዱን አጀንዳዎች ላይ በመነጋገርና አቅጣጫ በማስቀመጥ ወደ ሰላም እንድንመጣ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
ተመካካሪዎች የተለያየ ጽንፍ የያዙና የሚጋጩ ሀሳቦችን ይዘው ቢመጡም ወደ መሃል ለመምጣት የሚያደርጉት ጥረት ለምክክሩ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል ነው ያሉት፡፡
ወደ መሃል መምጣት ሀገርን የማስቀደም ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ ከራሳቸው ጥያቄዎች ባሻገር በጋራ የሚጠቅሙ ጥያቄዎችን ማንሳት መጀመራቸውን አስረድተዋል፡፡
ይህም በቀጣይ በሚደረገው ዋናው ጉባኤ ላይ እየዳበረ ሀገርን ባስቀደመ መንፈስ ምክክሩ ይበልጥ እየተጠናከረ እንደሚሄድ ነው የገለጹት፡፡
በኃይለማርያም ተገኝ
Sponsored by
Surafel
8 days ago
8 days ago
የመደመር አንቀጽ
"ሀገራዊ ምክክር፣ በአንድ በኩል አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር፣ ልሂቃን እና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋት እና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብት እና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል፡፡"
የመደመር መንግሥት
ገፅ 403
#ethiopia #ebc #medemer #dialogue #nationaldialogue
"ሀገራዊ ምክክር፣ በአንድ በኩል አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር፣ ልሂቃን እና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋት እና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብት እና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል፡፡"
የመደመር መንግሥት
ገፅ 403
#ethiopia #ebc #medemer #dialogue #nationaldialogue
8 days ago
ኢትዮጵያና አዘርባጃን፣ ከዲፕሎማሲ ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ጠንካራ ዲፕሎማሲዊ ግንኙት እየገነቡ መጥተዋል፡፡
በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙት እነዚህ ሁለት ሀገራት የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ የመከላከያ እና የቴክኖሎጂ ትብብሮችን ወደ ጠንካራና አዲስ ምዕራፍ ለማሳደግ እየሰሩ ናቸው።
ሀገራቱ የሶቪየት ኅብረት መፍረስን ተከትሎ አዘርባጃን ሪፐብሊክ ራሷን የቻለች ሀገር ከሆነች በኋላ ግንኙነታቸውን ቀስ በቀስ እያጠናከሩ መጥተዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ለበርካታ ዓመታት በዘለቀው ግንኙነታቸው የየሀገራቱ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጉብኝቶችን አድርገዋል፡፡
ሕዳር 2017 ዓ.ም አዘርባጃን ባስተናገደችው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ29) ለመሳተፍ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ወደ ባኩ ተጉዘው ነበር፡፡
በቆታቸውም የአዘርባጃንን የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ 3ኛው የኢትዮ-አዘርባጃን የፖለቲካ ምክክር መድረክ የተካሄደ ሲሆን÷ መድረኩ የሁለቱን ሀገራት የፖለቲካ ትስስር ወደ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን የሚያመላክት ነበር፡፡
በመቀጠልም የካቲት 2018 ዓ.ም ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባኩ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ከፍ አድርጓል።
በዚህ ሳምንት ደግሞ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ የፓርላማ አፈ ጉባዔ ሳሂባ ጋፋሮቫ ኢትዮጵያን እየጎበኙ የሚገኙ ሲሆን÷ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ከፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔዎች ጋር መክረዋል፡፡
ኢትዮጵያና አዘርባጃን በታሪክና በጂኦግራፊያዊ አቀማመጣቸው ቢለያዩም በርካታ የጋራ ባህሪያት አሏቸው።
ሁለቱም ጂኦፖለቲካዊ ፉክክር ባሉባቸው ቀጣናዎች ይገኛሉ፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ፤ አዘርባጃን ደግሞ በደቡብ ካውካሰስ ክልል፡፡ በየቀጣናቸው ሁለቱም ሀገራት ለሰላምና ደህንነት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡
በዓለም አቀፍ ፖለቲካም ሁለቱ ሀገራት ከምሥራቅና ከምዕራቡ ዓለማት ጋር ሚዛኑን የጠበቀ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን ይከተላሉ፡፡
ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን መሠረተ ልማትን፣ ዲጂታል ሽግግርን፣ ኢንዱስትሪን እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለልማትና ዕድገታቸው ትኩረት ሰጥተው እየሰሩባቸው ያሉ ዘርፎች ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዘርባጃንን በጎበኙበት ወቅት የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ የሀገራቱን ግንኙነት አስመልክተው ሲገልጹ፣ "አጋርነታችን በርካታ ጠቃሚ ጉዳዮችን ያካተተ ነው" ነበር ያሉት።
ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ በወታደራዊ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በሌሎች ዘርፎች ግንኙነታቸው እያደገ መምጣቱን መሪዎቹ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ ብልፅግና ፓርቲ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማሸነፉን አስመልክቶ በላኩት የደስታ መልዕክት፣ "በአዘርባጃን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት በአዎንታዊ አቅጣጫ እያደገ መሆኑ የሚያስደስት ነው" በማለት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በአዲስ መልክ እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት÷ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በአቪዬሽን፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በነጻ የንግድ ቀጣናዎች ረገድ የተከናወኑ የጋራ የኢኮኖሚዊ ትብብሮች፣ የሁለቱን ሀገራት አጋርነት እያደገ መምጣት ያመለከተ ነው ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት አንደኛቸው ከሌላኛው በበርካታ ዘርፎች ልምዶችን እየተለዋወጡ ሲሆን÷ ለአብነትም ኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአዘርባጃኑ አሳን ክድመት (ASAN Khidmet) የመንግሥት ዲጂታል አገልግሎት ልምድ የተወሰደ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ነው።
አዘርባጃን በበኩሏ በኢትዮጵያ በኩል ወደ አፍሪካ ገበያ ለመግባት ጥሩ መደላድል ታገኛለች። በዚህ መልኩ ሁለቱ ሀገራት የጋራ ጥቅምን በማስፋት በዓለም ኢኮኖሚና ጂኦፖለቲካ አወቃቀር ውስጥ ይበልጥ የሚጎለብት አጋርነት ሊገነቡ ይችላሉ።
ሁለቱ ሀገራት የሚጋሯቸው የልማት ርዕይ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታ፣ የዲጂታል ሽግግር፣ የኢኮኖሚ ብዝሃነት እና ቀጣናዊ ትብብሮች ግንኙነታቸውን ከፍ ወዳለ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚያሳድግ ነው።
በቴዎድሮስ ሳህለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ጠንካራ ዲፕሎማሲዊ ግንኙት እየገነቡ መጥተዋል፡፡
በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙት እነዚህ ሁለት ሀገራት የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ የመከላከያ እና የቴክኖሎጂ ትብብሮችን ወደ ጠንካራና አዲስ ምዕራፍ ለማሳደግ እየሰሩ ናቸው።
ሀገራቱ የሶቪየት ኅብረት መፍረስን ተከትሎ አዘርባጃን ሪፐብሊክ ራሷን የቻለች ሀገር ከሆነች በኋላ ግንኙነታቸውን ቀስ በቀስ እያጠናከሩ መጥተዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ለበርካታ ዓመታት በዘለቀው ግንኙነታቸው የየሀገራቱ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጉብኝቶችን አድርገዋል፡፡
ሕዳር 2017 ዓ.ም አዘርባጃን ባስተናገደችው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ29) ለመሳተፍ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ወደ ባኩ ተጉዘው ነበር፡፡
በቆታቸውም የአዘርባጃንን የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ 3ኛው የኢትዮ-አዘርባጃን የፖለቲካ ምክክር መድረክ የተካሄደ ሲሆን÷ መድረኩ የሁለቱን ሀገራት የፖለቲካ ትስስር ወደ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን የሚያመላክት ነበር፡፡
በመቀጠልም የካቲት 2018 ዓ.ም ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባኩ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ከፍ አድርጓል።
በዚህ ሳምንት ደግሞ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ የፓርላማ አፈ ጉባዔ ሳሂባ ጋፋሮቫ ኢትዮጵያን እየጎበኙ የሚገኙ ሲሆን÷ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ከፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔዎች ጋር መክረዋል፡፡
ኢትዮጵያና አዘርባጃን በታሪክና በጂኦግራፊያዊ አቀማመጣቸው ቢለያዩም በርካታ የጋራ ባህሪያት አሏቸው።
ሁለቱም ጂኦፖለቲካዊ ፉክክር ባሉባቸው ቀጣናዎች ይገኛሉ፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ፤ አዘርባጃን ደግሞ በደቡብ ካውካሰስ ክልል፡፡ በየቀጣናቸው ሁለቱም ሀገራት ለሰላምና ደህንነት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡
በዓለም አቀፍ ፖለቲካም ሁለቱ ሀገራት ከምሥራቅና ከምዕራቡ ዓለማት ጋር ሚዛኑን የጠበቀ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን ይከተላሉ፡፡
ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን መሠረተ ልማትን፣ ዲጂታል ሽግግርን፣ ኢንዱስትሪን እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለልማትና ዕድገታቸው ትኩረት ሰጥተው እየሰሩባቸው ያሉ ዘርፎች ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዘርባጃንን በጎበኙበት ወቅት የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ የሀገራቱን ግንኙነት አስመልክተው ሲገልጹ፣ "አጋርነታችን በርካታ ጠቃሚ ጉዳዮችን ያካተተ ነው" ነበር ያሉት።
ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ በወታደራዊ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በሌሎች ዘርፎች ግንኙነታቸው እያደገ መምጣቱን መሪዎቹ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ ብልፅግና ፓርቲ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማሸነፉን አስመልክቶ በላኩት የደስታ መልዕክት፣ "በአዘርባጃን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት በአዎንታዊ አቅጣጫ እያደገ መሆኑ የሚያስደስት ነው" በማለት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በአዲስ መልክ እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት÷ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በአቪዬሽን፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በነጻ የንግድ ቀጣናዎች ረገድ የተከናወኑ የጋራ የኢኮኖሚዊ ትብብሮች፣ የሁለቱን ሀገራት አጋርነት እያደገ መምጣት ያመለከተ ነው ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት አንደኛቸው ከሌላኛው በበርካታ ዘርፎች ልምዶችን እየተለዋወጡ ሲሆን÷ ለአብነትም ኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአዘርባጃኑ አሳን ክድመት (ASAN Khidmet) የመንግሥት ዲጂታል አገልግሎት ልምድ የተወሰደ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ነው።
አዘርባጃን በበኩሏ በኢትዮጵያ በኩል ወደ አፍሪካ ገበያ ለመግባት ጥሩ መደላድል ታገኛለች። በዚህ መልኩ ሁለቱ ሀገራት የጋራ ጥቅምን በማስፋት በዓለም ኢኮኖሚና ጂኦፖለቲካ አወቃቀር ውስጥ ይበልጥ የሚጎለብት አጋርነት ሊገነቡ ይችላሉ።
ሁለቱ ሀገራት የሚጋሯቸው የልማት ርዕይ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታ፣ የዲጂታል ሽግግር፣ የኢኮኖሚ ብዝሃነት እና ቀጣናዊ ትብብሮች ግንኙነታቸውን ከፍ ወዳለ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚያሳድግ ነው።
በቴዎድሮስ ሳህለ
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን የውሎ መድረክ ላይ፣ በሀገር ግንባታ አጀንዳዎች ዙሪያ የሚደረጉት ምክክሮች ወደ ላቀ ደረጃ ተሸጋግረዋል። በተለይም "ስልታዊ" ተባሉት ቡድኖች፣ ቀደም ሲል በንዑስ ቡድን ደረጃ የተዘጋጁ የምክረ ሀሳብ ቃለ-ጉባኤዎችን በማጠናቀር ሰፊ እና የሞቀ ክርክር አድርገዋል። በዚህ የውይይት መድረክ ላይ ከተነሱት በርካታ ማህበራዊ እና አስተዳደራዊ አጀንዳዎች መካከል፣ የኢትዮጵያ 13ኛ ወር የሆነችው የ"ጷጉሜን" ጉዳይ ዋነኛ መነጋገሪያ ሆኖ ውሏል።
በኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስም ሆነ የግል ዘርፍ የሥራ እና የደመወዝ ስሌት አሰራር መሰረት፣ ወርሃዊ ደመወዝ የሚከፈለው ለ12 ወራት (ለእያንዳንዱ 30 ቀናት) ብቻ ተብሎ ነው። በመሆኑም 5 ቀናት፣ እንዲሁም በዘመነ ዮሐንስ (በአራት ዓመት አንዴ) 6 ቀናት ያላት የጷጉሜን ወር፣ ሠራተኞች ምንም ዓይነት ክፍያ ሳይታሰብላቸው መደበኛ ስራቸውን በነጻ የሚያከናውኑባት ወር ሆና ለዘመናት ዘልቃለች።
ይህ ጉዳይ ለዓመታት የሠራተኞች የውስጥ ብሶት ሆኖ የቆየ ሲሆን፣ አሁን ግን በሀገራዊ የምክክር መድረኩ ላይ በይፋ ፈንድቷል። በውይይቱ ላይ የተገኙት ተመካካሪዎች ይህ አሰራር የዜጎችን ጉልበት ያለ አግባብ የሚበዘብዝ መሆኑን አጥብቀው በማንሳት፣ በሀገር ግንባታው ሂደት ውስጥ የዜጎች የሥራ መብት ሊከበር እንደሚገባ አሳስበዋል። ለዚህም ሁለት አማራጭ የመፍትሄ ሀሳቦችን አቅርበዋል። የመጀመሪያው አማራጭ ሠራተኛው በጷጉሜን ወር ለሚሰራቸው ቀናት የሚመጥን ተመጣጣኝ የደመወዝ ክፍያ እንዲከፈለው የሚጠይቅ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ መንግስት ተጨማሪ ክፍያ መክፈል የማይችል ከሆነ የጷጉሜን ቀናት ሀገር አቀፍ የሠራተኞች የእረፍት ቀናት ሆነው እንዲታወጁ የሚጠይቅ ነው።
የ15ኛው ቀን ውሎ ሌላው ትኩረት የሳበበት ክንውን፣ የስልታዊ ቡድኖቹ የምክረ ሀሳብ ማጥራት ሂደት ነበር። ከተለያዩ ንዑስ ቡድኖች የተሰበሰቡት ሀሳቦች ወደ ስልታዊ ቡድን ሲያድጉ፣ አባላቱ በጥንቅር ውስጥ አልተካተቱም ያሏቸውን ወሳኝ ህዝባዊ ሀሳቦች እንደገና በማንሳት እንዲካተቱ አድርገዋል። በሌላ በኩል ደግሞ በሀገር አቀፍ አጀንዳነት ሊካተቱ አይገባም በሚሏቸው ነጥቦች ላይ ጥብቅ ማጣሪያ እና የሞቀ ምክክር አካሂደዋል።
የጷጉሜን ወር የክፍያ ጥያቄ ወደ ሀገራዊ የምክክር መድረክ ከፍ ብሎ መነሳቱ፣ ጉባኤው ከትላልቅ የፖለቲካ፣ የጸጥታ እና የህገ-መንግስት ጉዳዮች ባሻገር፤ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ፣ አስተዳደራዊ በደሎች እና የሠራተኛ መብቶችን ጭምር በዝርዝር ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያሳይ መሆኑን የጉባኤው ታዛቢዎች ይገልጻሉ።
በኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስም ሆነ የግል ዘርፍ የሥራ እና የደመወዝ ስሌት አሰራር መሰረት፣ ወርሃዊ ደመወዝ የሚከፈለው ለ12 ወራት (ለእያንዳንዱ 30 ቀናት) ብቻ ተብሎ ነው። በመሆኑም 5 ቀናት፣ እንዲሁም በዘመነ ዮሐንስ (በአራት ዓመት አንዴ) 6 ቀናት ያላት የጷጉሜን ወር፣ ሠራተኞች ምንም ዓይነት ክፍያ ሳይታሰብላቸው መደበኛ ስራቸውን በነጻ የሚያከናውኑባት ወር ሆና ለዘመናት ዘልቃለች።
ይህ ጉዳይ ለዓመታት የሠራተኞች የውስጥ ብሶት ሆኖ የቆየ ሲሆን፣ አሁን ግን በሀገራዊ የምክክር መድረኩ ላይ በይፋ ፈንድቷል። በውይይቱ ላይ የተገኙት ተመካካሪዎች ይህ አሰራር የዜጎችን ጉልበት ያለ አግባብ የሚበዘብዝ መሆኑን አጥብቀው በማንሳት፣ በሀገር ግንባታው ሂደት ውስጥ የዜጎች የሥራ መብት ሊከበር እንደሚገባ አሳስበዋል። ለዚህም ሁለት አማራጭ የመፍትሄ ሀሳቦችን አቅርበዋል። የመጀመሪያው አማራጭ ሠራተኛው በጷጉሜን ወር ለሚሰራቸው ቀናት የሚመጥን ተመጣጣኝ የደመወዝ ክፍያ እንዲከፈለው የሚጠይቅ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ መንግስት ተጨማሪ ክፍያ መክፈል የማይችል ከሆነ የጷጉሜን ቀናት ሀገር አቀፍ የሠራተኞች የእረፍት ቀናት ሆነው እንዲታወጁ የሚጠይቅ ነው።
የ15ኛው ቀን ውሎ ሌላው ትኩረት የሳበበት ክንውን፣ የስልታዊ ቡድኖቹ የምክረ ሀሳብ ማጥራት ሂደት ነበር። ከተለያዩ ንዑስ ቡድኖች የተሰበሰቡት ሀሳቦች ወደ ስልታዊ ቡድን ሲያድጉ፣ አባላቱ በጥንቅር ውስጥ አልተካተቱም ያሏቸውን ወሳኝ ህዝባዊ ሀሳቦች እንደገና በማንሳት እንዲካተቱ አድርገዋል። በሌላ በኩል ደግሞ በሀገር አቀፍ አጀንዳነት ሊካተቱ አይገባም በሚሏቸው ነጥቦች ላይ ጥብቅ ማጣሪያ እና የሞቀ ምክክር አካሂደዋል።
የጷጉሜን ወር የክፍያ ጥያቄ ወደ ሀገራዊ የምክክር መድረክ ከፍ ብሎ መነሳቱ፣ ጉባኤው ከትላልቅ የፖለቲካ፣ የጸጥታ እና የህገ-መንግስት ጉዳዮች ባሻገር፤ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ፣ አስተዳደራዊ በደሎች እና የሠራተኛ መብቶችን ጭምር በዝርዝር ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያሳይ መሆኑን የጉባኤው ታዛቢዎች ይገልጻሉ።
9 days ago
በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው "ወርልድ ፐብሊክ ሰሚት አፍሪካ" ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሄደ!
#fastmereja I የአፍሪካ ሕዝቦችን ቁርኝትና አህጉራዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመውና በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው "ወርልድ ፐብሊክ ሰሚት አፍሪካ" (World Public Summit Africa) ጉባኤ በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ ተካሄደ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ECA) አዳራሽ በተካሄደው በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራንና ወጣቶች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ጉባኤው በስፖርት፣ በባህልና በትምህርት ዘርፎች ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ባተኮሩ አምስት የፓናል ውይይቶች የተከናወነ ሲሆን፤ አፍሪካ አዲስ በሚፈጠረው ዘብዙኃን ዓለም አቀፍ ሥርዓት (Multipolar World) ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅና በ"ኡቡንቱ" የፍልስፍና መርህ ላይ ያተኮረ ምክክር ተደርጎበታል።
በስብሰባው ማጠቃለያ ላይ የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063ን ለማሳካት የሚረዳ “የአፍሪካ ኮሙኒኬ” (African Communiqué) የጸደቀ ሲሆን፣ ሶስት ዋና ዋና አህጉራዊ ፕሮጀክቶችም ይፋ ሆነዋል።
ከእነዚህም መካከል አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክን የሚያስተሳስረው «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የቀረበው ሳይንሳዊ ጥናት ይገኝበታል። በተጨማሪም በሕዝብ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ 10 አፍሪካውያን ልዩ እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል።
ጉባኤው የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ የሚጠርግ ሲሆን የአዲስ አበባው ጉባኤ በመጪው መስከረም ወር በሞስኮ ለሚካሄደው ሁለተኛው የዓለም የህዝብ ለህዝብ ጉባኤ የአፍሪካን አቋም ያዘጋጀበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል።
የጉባኤው አካል የሆነውና ከ16 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ታዋቂ አርቲስቶች ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡበት «አንድነት» (Unity) የተሰኘ ዓለም አቀፍ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም መከፈቱ ታውቋል።
ይህ አህጉራዊ መድረክ መቀመጫውን በሩሲያ ሞስኮ ባደረገው "ወርልድ ፒፕልስ አሴምብሊ" (World Peoples Assembly) ከአገር በቀልና ዓለም አቀፍ አጋሮቹ ሰርቨ ግሎባል እና ግሎባል ብላክ ሴንተር ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው።
#fastmereja I የአፍሪካ ሕዝቦችን ቁርኝትና አህጉራዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመውና በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው "ወርልድ ፐብሊክ ሰሚት አፍሪካ" (World Public Summit Africa) ጉባኤ በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ ተካሄደ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ECA) አዳራሽ በተካሄደው በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራንና ወጣቶች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ጉባኤው በስፖርት፣ በባህልና በትምህርት ዘርፎች ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ባተኮሩ አምስት የፓናል ውይይቶች የተከናወነ ሲሆን፤ አፍሪካ አዲስ በሚፈጠረው ዘብዙኃን ዓለም አቀፍ ሥርዓት (Multipolar World) ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅና በ"ኡቡንቱ" የፍልስፍና መርህ ላይ ያተኮረ ምክክር ተደርጎበታል።
በስብሰባው ማጠቃለያ ላይ የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063ን ለማሳካት የሚረዳ “የአፍሪካ ኮሙኒኬ” (African Communiqué) የጸደቀ ሲሆን፣ ሶስት ዋና ዋና አህጉራዊ ፕሮጀክቶችም ይፋ ሆነዋል።
ከእነዚህም መካከል አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክን የሚያስተሳስረው «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የቀረበው ሳይንሳዊ ጥናት ይገኝበታል። በተጨማሪም በሕዝብ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ 10 አፍሪካውያን ልዩ እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል።
ጉባኤው የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ የሚጠርግ ሲሆን የአዲስ አበባው ጉባኤ በመጪው መስከረም ወር በሞስኮ ለሚካሄደው ሁለተኛው የዓለም የህዝብ ለህዝብ ጉባኤ የአፍሪካን አቋም ያዘጋጀበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል።
የጉባኤው አካል የሆነውና ከ16 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ታዋቂ አርቲስቶች ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡበት «አንድነት» (Unity) የተሰኘ ዓለም አቀፍ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም መከፈቱ ታውቋል።
ይህ አህጉራዊ መድረክ መቀመጫውን በሩሲያ ሞስኮ ባደረገው "ወርልድ ፒፕልስ አሴምብሊ" (World Peoples Assembly) ከአገር በቀልና ዓለም አቀፍ አጋሮቹ ሰርቨ ግሎባል እና ግሎባል ብላክ ሴንተር ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው።
9 days ago
የጠመንጃን ቋንቋ በውይይት እንተካለን | የደቡብ ምዕራቡ የሀገር ሽማግሌ እና የሶማሌው አርብቶ አደር ታሪካዊ የምክክር ምስክሮች
#ethiopia #nationaldialogue #traditionalreconciliation
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
#ethiopia #nationaldialogue #traditionalreconciliation
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት አምባሳደር ለገሰ ቱሉ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ ለተፈጠረው አውዳሚ ጦርነት መቋጫ የሆነው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ትግበራን በተመለከተ፣ የህወሓት እሳቸው "ጽንፈኛ" ያሉት አመራሮች እያራመዱት ያለው ፖለቲካዊ ትርክት የትግራይን ህዝብ ፍላጎት የረሳ እና የሰላም ሂደቱን አደጋ ላይ የጣለ መሆኑን የሚያብራራ ትችት አወጡ። አምባሳደሩ "TPLF’s rhetoric and Ethiopia’s reality on the ground: When politics forgets people" (የህወሓት ፖለቲካዊ ትርክቶች እና የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ፦ ፖለቲካ ህዝብን ሲረሳ" በሚል ርዕስ በኒው አፍሪካን መጽሔት ድረገጽ ላይ ዛሬ ባሳተሙት ጽሁፍ፣ ዘላቂ ሰላም ሊመጣ የሚችለው አካላት ከግል እና ከፓርቲ ፍላጎት ይልቅ የዜጎችን ደህንነት ሲያስቀድሙ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አምባሳደሩ በጽሁፋቸው እንዳስመዘገቡት ከጦርነቱ በኋላ እጅግ አሳሳቢ ከሆኑት ጉዳዮች አንዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ወደ ቀዬአቸው የመመለስ ስራ ነው። የፌደራል መንግስት ተፈናቃዮች ያለምንም የፖለቲካ ቅድመ ሁኔታ እና መጓተት ወደ ቤታቸው ሊመለሱ ይገባል የሚል ጽኑ አቋም ቢኖረውም፣ ህወሓቶች ግን የሰብዓዊ እርዳታን እና የተፈናቃዮችን ጉዳይ ካልተፈቱ የፖለቲካ አጀንዳዎቻቸው ጋር በማያያዝ የህዝቡን ስቃይ ለፖለቲካ መደራደሪያነት እያዋሉት መሆኑን ኮንነዋል። ቤተሰቦች በፖለቲካዊ ዲስኩር ብቻ ህይወታቸውን መልሰው ሊገነቡ አይችሉም ያሉት አምባሳደሩ፣ በአከራካሪ ግዛቶች ዙሪያም የፌደራል መንግስት ጉዳዩ በህገ-መንግስታዊ ስርአቱ እና በሰላም ስምምነቱ መሰረት እንዲፈታ ጥረት ቢያደርግም፣ አመራሮቹ እነዚህን ተቋማዊ አሰራሮች ውድቅ በማድረግ እና የጊዜያዊ አስተዳደሩን ስልጣን ጥያቄ ውስጥ በማስገባት እንቅፋት እየፈጠሩ ይገኛሉ ብለዋል።
የፕሪቶሪያው ስምምነት ህገ-መንግስታዊ እና ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን ለመገንባት ምርጫ እንዲካሄድ ቢደነግግም፣ ህወሓቶች የፓርቲው የውስጥ ፖለቲካዊ ልዩነቶች እስኪፈቱ በሚል ሰበብ ምርጫን ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም የፌደራል መንግስት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የብሄራዊ ምክክር ኮሚሽን ያቀረቡትን የሽምግልና እና የውይይት ጥሪዎች በተደጋጋሚ ውድቅ ማድረጋቸው የእርቅ እድሎችን እያጠበበው መምጣቱን አምባሳደር ለገሰ አስረድተዋል።
ተቋማትን እያፈረሱ እና የሽግግር ፍትህ ስርአቱን እየተቃወሙ በተመሳሳይ ጊዜ ፍትህ እንፈልጋለን ማለታቸውም ግልጽ የሆነ የተግባር ተቃርኖ መሆኑን አንስተዋል።
ዳግም ወታደራዊ ቅስቀሳ እና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስጋት
የሰላም ስምምነቱ ትጥቅ መፍታት፣ ከወታደራዊ መዋቅር መውጣት እና ወደ ሰላማዊ ህይወት መቀላቀልን (DDR) ቅድሚያ ቢሰጥም፣ አመራሮቹ ግን አሁንም ወታደራዊ ቅስቀሳ እያደረጉ፣ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን እየደበቁ እና ወጣቶችን በግዴታ እየመለመሉ መሆኑ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን አምባሳደሩ ገልጸዋል። ከዓመታት የጦርነት ስቃይ በኋላ ወጣቶች ወደ ትምህርት እና ስራ መመለስ ሲገባቸው ዳግም ለጦርነት መመልመላቸው ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው። ይህ ድርጊታቸው የአውሮፓ ህብረትን እና በሰላም አደናቃፊዎች ላይ የቪዛ ማዕቀብ የጣለችውን አሜሪካን ጨምሮ ዓለም አቀፍ አጋሮችን ጭምር በእጅጉ እንዳሳሰበ አምባሳደሩ አስታውሰዋል።
የትግራይ ህዝብ ከዚህ በላይ ጦርነት እና ስቃይ እንደማይገባው ያሳሰቡት አምባሳደር ለገሰ ቱሉ፣ የፕሪቶሪያው ስምምነት ወደ ዘላቂ ሰላም መሻገሪያ ጠንካራ መሰረት መሆኑን አውቆ ማክበር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ዳግም ወደ ጦርነት እና ወታደራዊ ፉክክር መግባት ትግራይን ብቻ ሳይሆን መላው ኢትዮጵያን አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን በማስጠንቀቅ፣ ፖለቲከኞች የጥቃት ፖለቲካን ትተው ለኢትዮጵያ ህዝብ ሲሉ የዲሞክራሲያዊ ውድድር ፖለቲካን ሊመርጡ እንደሚገባ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በአምባሳደሩ ጽሁፍ ዙሪያ፣ ይህ መረጃ እስከቀረበበት ጊዜ ድረስ ከሕወሐት ወገን የተሰጠ ምላሽ የለም።
አምባሳደሩ በጽሁፋቸው እንዳስመዘገቡት ከጦርነቱ በኋላ እጅግ አሳሳቢ ከሆኑት ጉዳዮች አንዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ወደ ቀዬአቸው የመመለስ ስራ ነው። የፌደራል መንግስት ተፈናቃዮች ያለምንም የፖለቲካ ቅድመ ሁኔታ እና መጓተት ወደ ቤታቸው ሊመለሱ ይገባል የሚል ጽኑ አቋም ቢኖረውም፣ ህወሓቶች ግን የሰብዓዊ እርዳታን እና የተፈናቃዮችን ጉዳይ ካልተፈቱ የፖለቲካ አጀንዳዎቻቸው ጋር በማያያዝ የህዝቡን ስቃይ ለፖለቲካ መደራደሪያነት እያዋሉት መሆኑን ኮንነዋል። ቤተሰቦች በፖለቲካዊ ዲስኩር ብቻ ህይወታቸውን መልሰው ሊገነቡ አይችሉም ያሉት አምባሳደሩ፣ በአከራካሪ ግዛቶች ዙሪያም የፌደራል መንግስት ጉዳዩ በህገ-መንግስታዊ ስርአቱ እና በሰላም ስምምነቱ መሰረት እንዲፈታ ጥረት ቢያደርግም፣ አመራሮቹ እነዚህን ተቋማዊ አሰራሮች ውድቅ በማድረግ እና የጊዜያዊ አስተዳደሩን ስልጣን ጥያቄ ውስጥ በማስገባት እንቅፋት እየፈጠሩ ይገኛሉ ብለዋል።
የፕሪቶሪያው ስምምነት ህገ-መንግስታዊ እና ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን ለመገንባት ምርጫ እንዲካሄድ ቢደነግግም፣ ህወሓቶች የፓርቲው የውስጥ ፖለቲካዊ ልዩነቶች እስኪፈቱ በሚል ሰበብ ምርጫን ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም የፌደራል መንግስት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የብሄራዊ ምክክር ኮሚሽን ያቀረቡትን የሽምግልና እና የውይይት ጥሪዎች በተደጋጋሚ ውድቅ ማድረጋቸው የእርቅ እድሎችን እያጠበበው መምጣቱን አምባሳደር ለገሰ አስረድተዋል።
ተቋማትን እያፈረሱ እና የሽግግር ፍትህ ስርአቱን እየተቃወሙ በተመሳሳይ ጊዜ ፍትህ እንፈልጋለን ማለታቸውም ግልጽ የሆነ የተግባር ተቃርኖ መሆኑን አንስተዋል።
ዳግም ወታደራዊ ቅስቀሳ እና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስጋት
የሰላም ስምምነቱ ትጥቅ መፍታት፣ ከወታደራዊ መዋቅር መውጣት እና ወደ ሰላማዊ ህይወት መቀላቀልን (DDR) ቅድሚያ ቢሰጥም፣ አመራሮቹ ግን አሁንም ወታደራዊ ቅስቀሳ እያደረጉ፣ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን እየደበቁ እና ወጣቶችን በግዴታ እየመለመሉ መሆኑ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን አምባሳደሩ ገልጸዋል። ከዓመታት የጦርነት ስቃይ በኋላ ወጣቶች ወደ ትምህርት እና ስራ መመለስ ሲገባቸው ዳግም ለጦርነት መመልመላቸው ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው። ይህ ድርጊታቸው የአውሮፓ ህብረትን እና በሰላም አደናቃፊዎች ላይ የቪዛ ማዕቀብ የጣለችውን አሜሪካን ጨምሮ ዓለም አቀፍ አጋሮችን ጭምር በእጅጉ እንዳሳሰበ አምባሳደሩ አስታውሰዋል።
የትግራይ ህዝብ ከዚህ በላይ ጦርነት እና ስቃይ እንደማይገባው ያሳሰቡት አምባሳደር ለገሰ ቱሉ፣ የፕሪቶሪያው ስምምነት ወደ ዘላቂ ሰላም መሻገሪያ ጠንካራ መሰረት መሆኑን አውቆ ማክበር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ዳግም ወደ ጦርነት እና ወታደራዊ ፉክክር መግባት ትግራይን ብቻ ሳይሆን መላው ኢትዮጵያን አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን በማስጠንቀቅ፣ ፖለቲከኞች የጥቃት ፖለቲካን ትተው ለኢትዮጵያ ህዝብ ሲሉ የዲሞክራሲያዊ ውድድር ፖለቲካን ሊመርጡ እንደሚገባ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በአምባሳደሩ ጽሁፍ ዙሪያ፣ ይህ መረጃ እስከቀረበበት ጊዜ ድረስ ከሕወሐት ወገን የተሰጠ ምላሽ የለም።
Sponsored by
Surafel
9 days ago
የመከረ ቤቱን አጠናከረ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀገራችን በአንድ ግዙፍ የታሪክ ምዕራፍ እጥፋት ላይ ትገኛለች፡፡ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የውስጥ ጉዳዮቿን የሀገር ልጆች ቁጭ ብለው ተመካክረው ሀገር ሊያጸኑ ተሰባስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክሩን አስፈላጊነት በተመለከተ ሲናገሩ፣ "ለልጆቿ ኩራት የሆነች፣ ተስፋ ያላት ምድር ለማድረግ አንድንችል ምክክሩ በእጅጉ ያስፈልጋል" ነው ያሉት፡፡
ኢትዮጵያ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩባት ባለ ብዝሃ ባህል፣ ብዝሃ ታሪክ፣ ብዝሃ ማህበረ ኢኮኖሚ ሀገር እንደመሆኗ በዘመናት ጉዞዋ የልማት፣ የአስተዳደራዊ እና ሌሎች አለመግባባቶች እንደሚኖሩ ይጠበቃል፡፡
የእነዚህን በህዝቦች መካል የሚስተዋሉ ልዩነቶች አለመግባባቶችና ጥያቄዎች በዘላቂነት በመፍታት ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ፣ የበለጸገችና የታፈረች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ምክክሩ እጅግ ያስፈልጋል።
ብሔራዊ ምክክሩ የታለመለትን ግብ እንዲመታ እና ሀገር እንድትጸና ለማድረግ የሁሉምን ህብረተሰብ ክፍሎች ያካተተ እና ያሳተፈ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክር ሂደቱ፣ "በፖለቲካ ልሂቃን መካከል የሚደረግ ብቻ ሳይሆን የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎ ያገናዘበ፣ በኢትዮጵያውያን የተመራ ሀገር በቀል መፍትሄዎችን ለማፍለቅ ታልሞ የሚከናወን ይሆናል" ባሉት መሰረት የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ምሁራን፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ሠራተኞች፣ አካል ጉዳተኞች፣ እንዲሁም ተፈናቃዮች እንዲሳተፉ ተደርጓል።
የተለያዩ የዘርፉ ምሁራን በምክክርና ውይይት ሂደት የአካታችነት እና አሳታፊነትን ፋይዳ ያሰምሩበታል፡፡ በስዊዝፒስ የድርድር ፕሮግራም ኃላፊ የሆኑት ዴቪድ ላንዝ የአንድን ሀገር መሰረታዊ ማንነትና የአስተዳደር ስርዓት ለመወያየት የሚያስችል ሁሉን አቀፍ አሰራር ከሌለ፣ ከዚያ በኋላ የሚደረጉ ማናቸውም ውሳኔዎች ወይም ተቋማዊ ማሻሻያዎች በአሸዋ ላይ እንደተገነባ ቤት ይሆናሉ ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ሀገር በቀል የሆኑ በዘመናት ተሞክረው እና ተፈትነው በውጤታማነት የዘለቁ የልዩነትና የግጭት መፍቻ ስርዓቶች ባለቤት እንደመሆኗ አሁን እየተካሄደ ያለው የምክክር ጉባኤ የእነዚህ እሴቶች አዲስ ምዕራፍ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ምክክሩ ሁሉም ሃሳቡን የሚገልፅበት፣ የሌሎች ጥያቄዎችና ቅሬታዎች የሚደምጥበት፣ በጋራ መፍትሄ የሚፈለግበትና የጋራ መግባባት ላይ የሚደረስበት በመሆኑ ውጤቱም ዘላቂና ሀገርን የሚያጸና ነው፡፡
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ዜማ ተግባብተው ታሪክ እንደሰሩ ሁሉ በሀገራዊ መግባባትና ሀገር መፅናት ጉዳይም ተመሳሳይ ድል የመቀዳጀት ጉዞ ላይ ናቸው።
ይህ ለአፍሪካውያን ብሎም ለዓለም ተምሳሌት ሊሆን የሚችል የኢትጵያውያን፣ በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያውያን የተዘጋጀ ታሪካዊ መድረክ የበለጸገች ህብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ፅኑ መሰረት ይጥላል።
የምክክር ሂደቱ በስኬት እስኪጠናቀቅ፣ ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚጠበቅባቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀገራችን በአንድ ግዙፍ የታሪክ ምዕራፍ እጥፋት ላይ ትገኛለች፡፡ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የውስጥ ጉዳዮቿን የሀገር ልጆች ቁጭ ብለው ተመካክረው ሀገር ሊያጸኑ ተሰባስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክሩን አስፈላጊነት በተመለከተ ሲናገሩ፣ "ለልጆቿ ኩራት የሆነች፣ ተስፋ ያላት ምድር ለማድረግ አንድንችል ምክክሩ በእጅጉ ያስፈልጋል" ነው ያሉት፡፡
ኢትዮጵያ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩባት ባለ ብዝሃ ባህል፣ ብዝሃ ታሪክ፣ ብዝሃ ማህበረ ኢኮኖሚ ሀገር እንደመሆኗ በዘመናት ጉዞዋ የልማት፣ የአስተዳደራዊ እና ሌሎች አለመግባባቶች እንደሚኖሩ ይጠበቃል፡፡
የእነዚህን በህዝቦች መካል የሚስተዋሉ ልዩነቶች አለመግባባቶችና ጥያቄዎች በዘላቂነት በመፍታት ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ፣ የበለጸገችና የታፈረች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ምክክሩ እጅግ ያስፈልጋል።
ብሔራዊ ምክክሩ የታለመለትን ግብ እንዲመታ እና ሀገር እንድትጸና ለማድረግ የሁሉምን ህብረተሰብ ክፍሎች ያካተተ እና ያሳተፈ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክር ሂደቱ፣ "በፖለቲካ ልሂቃን መካከል የሚደረግ ብቻ ሳይሆን የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎ ያገናዘበ፣ በኢትዮጵያውያን የተመራ ሀገር በቀል መፍትሄዎችን ለማፍለቅ ታልሞ የሚከናወን ይሆናል" ባሉት መሰረት የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ምሁራን፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ሠራተኞች፣ አካል ጉዳተኞች፣ እንዲሁም ተፈናቃዮች እንዲሳተፉ ተደርጓል።
የተለያዩ የዘርፉ ምሁራን በምክክርና ውይይት ሂደት የአካታችነት እና አሳታፊነትን ፋይዳ ያሰምሩበታል፡፡ በስዊዝፒስ የድርድር ፕሮግራም ኃላፊ የሆኑት ዴቪድ ላንዝ የአንድን ሀገር መሰረታዊ ማንነትና የአስተዳደር ስርዓት ለመወያየት የሚያስችል ሁሉን አቀፍ አሰራር ከሌለ፣ ከዚያ በኋላ የሚደረጉ ማናቸውም ውሳኔዎች ወይም ተቋማዊ ማሻሻያዎች በአሸዋ ላይ እንደተገነባ ቤት ይሆናሉ ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ሀገር በቀል የሆኑ በዘመናት ተሞክረው እና ተፈትነው በውጤታማነት የዘለቁ የልዩነትና የግጭት መፍቻ ስርዓቶች ባለቤት እንደመሆኗ አሁን እየተካሄደ ያለው የምክክር ጉባኤ የእነዚህ እሴቶች አዲስ ምዕራፍ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ምክክሩ ሁሉም ሃሳቡን የሚገልፅበት፣ የሌሎች ጥያቄዎችና ቅሬታዎች የሚደምጥበት፣ በጋራ መፍትሄ የሚፈለግበትና የጋራ መግባባት ላይ የሚደረስበት በመሆኑ ውጤቱም ዘላቂና ሀገርን የሚያጸና ነው፡፡
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ዜማ ተግባብተው ታሪክ እንደሰሩ ሁሉ በሀገራዊ መግባባትና ሀገር መፅናት ጉዳይም ተመሳሳይ ድል የመቀዳጀት ጉዞ ላይ ናቸው።
ይህ ለአፍሪካውያን ብሎም ለዓለም ተምሳሌት ሊሆን የሚችል የኢትጵያውያን፣ በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያውያን የተዘጋጀ ታሪካዊ መድረክ የበለጸገች ህብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ፅኑ መሰረት ይጥላል።
የምክክር ሂደቱ በስኬት እስኪጠናቀቅ፣ ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚጠበቅባቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
9 days ago
Comments