8 hours ago
ቶልሷ፦ ተወዳጁ የወላይታ ጥሬ ስጋ እና ማህበራዊ እሴት!
#ethiopia | ጥሬ ስጋ በወላይታ ህዝብ ዘንድ የምግብ አይነት ብቻ ሳይሆን፤ ከማህበራዊ እሴት፣ ከበዓላትና ከከፍተኛ የእንግዳ አቀባበል ስነ-ስርዓት ጋር የተሳሰረ የጠበቀ ባህል ነው።
በወላይታ ባህል የታወቁ የጥሬ ስጋ አዘጋጃጀት አይነቶች፦
ቶልሷ (ቁርጥ ሥጋ)፦ የወላይታ አዲስ ዓመት (ግፋታ) ሲከበር በተለየ ሁኔታ ከተቀለበ ሰንጋ በሬ ተመርጦ የሚዘጋጅ፣ ከዋና ዋና የጮማ እና የቀይ ስጋ ክፍሎች የሚቀርብ ልዩ ቁርጥ ነው።
ሱልሷ፦ ምንም ጮማ ሳይቀላቀል ቀይ ስጋ ብቻ ተመርጦ በደቃቁ ከተከተፈ በኋላ ከነጠረ ቅቤ ጋር ተሰርቶ "ሞቂያ" በተሰኘ ባህላዊ ማንኪያ የሚበላ ነው። ይህ ምግብ በተለይም ለአባወራ እና ለክብር እንግዳ የሚቀርብ እጅግ ተወዳጅ ባህላዊ ምግብ ነው።
አሿ ጢጣ (ጥብስ)፦ ገና በእሳት ላይ ሲጠበስ ምራቅ የሚያስውጥ፣ ልዩ ጣዕም ያለውና በጥብስነቱ በእጅጉ የሚወደድ ነው።
የአቀራረብ ስነ-ስርዓት
ጥሬ ስጋ ብቻውን አይበላም!
በቅመማቅመም እና በቅቤ ከተለወሰው "ሳዎ ባምባሪያ" (ዳታ በርበሬ) ጋር ይጣቀሳል።
ከእንሴት ውጤት ቆጮ (ጎዴታ ኡንጫ) እና ከበቆሎ ቅጣ (ባዳላ ኦይታ) ጋር በመሶብ ዙሪያ አምሮ ይቀርባል።
ዳታው የሚቀርበው "ሻትያ" በተሰኘ ባህላዊ የሸክላ እቃ ላይ ተደርጎ ነው።
"እማታ ፓያ ኤሆ" (መልካም እንግዳ ያምጣልን!)
የወላይታ ሰው እንግዳ አሳቦ ስጋ መብላት ስለሚወድ ሁልጊዜ መልካም እንግዳ እንዲመጣ ይመኛል። ድንገት እግር ጥሎት ወደ ወላይታ የመጣ እንግዳ ጥሬ ስጋ በዳታ አጣቅሶ ሳይበላ አይመለስም—በላ ማለት ደግሞ ቤተኛ ሆኖ የመቅረት ዕድሉ ሰፊ ነው!
በሴፉ ሳሙኤል
#wolaita #ethiopianfood #culture #tolsuwa #sulsuwa #ethiopia #giphata #traditionalfood
#ethiopia | ጥሬ ስጋ በወላይታ ህዝብ ዘንድ የምግብ አይነት ብቻ ሳይሆን፤ ከማህበራዊ እሴት፣ ከበዓላትና ከከፍተኛ የእንግዳ አቀባበል ስነ-ስርዓት ጋር የተሳሰረ የጠበቀ ባህል ነው።
በወላይታ ባህል የታወቁ የጥሬ ስጋ አዘጋጃጀት አይነቶች፦
ቶልሷ (ቁርጥ ሥጋ)፦ የወላይታ አዲስ ዓመት (ግፋታ) ሲከበር በተለየ ሁኔታ ከተቀለበ ሰንጋ በሬ ተመርጦ የሚዘጋጅ፣ ከዋና ዋና የጮማ እና የቀይ ስጋ ክፍሎች የሚቀርብ ልዩ ቁርጥ ነው።
ሱልሷ፦ ምንም ጮማ ሳይቀላቀል ቀይ ስጋ ብቻ ተመርጦ በደቃቁ ከተከተፈ በኋላ ከነጠረ ቅቤ ጋር ተሰርቶ "ሞቂያ" በተሰኘ ባህላዊ ማንኪያ የሚበላ ነው። ይህ ምግብ በተለይም ለአባወራ እና ለክብር እንግዳ የሚቀርብ እጅግ ተወዳጅ ባህላዊ ምግብ ነው።
አሿ ጢጣ (ጥብስ)፦ ገና በእሳት ላይ ሲጠበስ ምራቅ የሚያስውጥ፣ ልዩ ጣዕም ያለውና በጥብስነቱ በእጅጉ የሚወደድ ነው።
የአቀራረብ ስነ-ስርዓት
ጥሬ ስጋ ብቻውን አይበላም!
በቅመማቅመም እና በቅቤ ከተለወሰው "ሳዎ ባምባሪያ" (ዳታ በርበሬ) ጋር ይጣቀሳል።
ከእንሴት ውጤት ቆጮ (ጎዴታ ኡንጫ) እና ከበቆሎ ቅጣ (ባዳላ ኦይታ) ጋር በመሶብ ዙሪያ አምሮ ይቀርባል።
ዳታው የሚቀርበው "ሻትያ" በተሰኘ ባህላዊ የሸክላ እቃ ላይ ተደርጎ ነው።
"እማታ ፓያ ኤሆ" (መልካም እንግዳ ያምጣልን!)
የወላይታ ሰው እንግዳ አሳቦ ስጋ መብላት ስለሚወድ ሁልጊዜ መልካም እንግዳ እንዲመጣ ይመኛል። ድንገት እግር ጥሎት ወደ ወላይታ የመጣ እንግዳ ጥሬ ስጋ በዳታ አጣቅሶ ሳይበላ አይመለስም—በላ ማለት ደግሞ ቤተኛ ሆኖ የመቅረት ዕድሉ ሰፊ ነው!
በሴፉ ሳሙኤል
#wolaita #ethiopianfood #culture #tolsuwa #sulsuwa #ethiopia #giphata #traditionalfood
6 days ago
ተራዝሟል!!
የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሀሴ 30 /2018 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት እየወሰደ ባለው እርምጃ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መወስኑን ተከትሎ የውል እድሳት ምዝገባም ከ ሐምሌ 1 / 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ የውል እድሳት ምዝገባ ግዜ እስከ እስከ ሀምሌ 30 /2018 ዓ.ም የነበረው እስከ ነሀሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
የውል እድሳት ግዜው በህብረተሰቡ ጥያቄ መስረት የተራዘመ ሲሆን ነዋሪው ያለምንም መጨናነቅ እንዲዋዋል ታሳቢ ያደረገ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።
ህብረተሰቡ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት ፤ በየወረዳው በተዘጋጁ የውል ቦታዎች እና በሁሉም ክፍለ ከተማ አዲስ መሶብ አስፈላጊውን መረጃ ይዞ በመገኘት አገልግሎቱን ማግኘት የሚቻል መሆኑን ቢሮው በድጋሚ ያሳውቃል፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሀሴ 30 /2018 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት እየወሰደ ባለው እርምጃ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መወስኑን ተከትሎ የውል እድሳት ምዝገባም ከ ሐምሌ 1 / 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ የውል እድሳት ምዝገባ ግዜ እስከ እስከ ሀምሌ 30 /2018 ዓ.ም የነበረው እስከ ነሀሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
የውል እድሳት ግዜው በህብረተሰቡ ጥያቄ መስረት የተራዘመ ሲሆን ነዋሪው ያለምንም መጨናነቅ እንዲዋዋል ታሳቢ ያደረገ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።
ህብረተሰቡ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት ፤ በየወረዳው በተዘጋጁ የውል ቦታዎች እና በሁሉም ክፍለ ከተማ አዲስ መሶብ አስፈላጊውን መረጃ ይዞ በመገኘት አገልግሎቱን ማግኘት የሚቻል መሆኑን ቢሮው በድጋሚ ያሳውቃል፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
7 days ago
ተራዝሟል‼️
በመዲናዋ የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት ጊዜ ተራዘመ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ተራዝሟል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲካሄድ አስታውቆት የነበረውን የቤት ኪራይ ውል እድሳት ነው እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ያራዘመው፡፡
የከተማ አስተዳደሩ የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ሕገ ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሆን መወሰኑ ይታወቃል፡፡
ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ ተከራይ የውል እድሳት ምዝገባ ጊዜ እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረው እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን ቢሮው አስታውቋል።
የውል እድሳት ጊዜው በሕብረተሰቡ ጥያቄ መሰረት የተራዘመ ሲሆን ÷ ይህም ነዋሪው ያለምንም መጨናነቅ እንዲዋዋል ያስችላል፡፡
ነዋሪው በሁሉም ክ/ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ፤ በየወረዳው በተዘጋጁ የውል ቦታዎች እና በሁሉም ክ/ከተማ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስፈላጊውን መረጃ በመያዝ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችል መገለጹን የቢሮው መረጃ አመልክቷል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
በመዲናዋ የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት ጊዜ ተራዘመ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ተራዝሟል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲካሄድ አስታውቆት የነበረውን የቤት ኪራይ ውል እድሳት ነው እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ያራዘመው፡፡
የከተማ አስተዳደሩ የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ሕገ ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሆን መወሰኑ ይታወቃል፡፡
ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ ተከራይ የውል እድሳት ምዝገባ ጊዜ እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረው እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን ቢሮው አስታውቋል።
የውል እድሳት ጊዜው በሕብረተሰቡ ጥያቄ መሰረት የተራዘመ ሲሆን ÷ ይህም ነዋሪው ያለምንም መጨናነቅ እንዲዋዋል ያስችላል፡፡
ነዋሪው በሁሉም ክ/ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ፤ በየወረዳው በተዘጋጁ የውል ቦታዎች እና በሁሉም ክ/ከተማ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስፈላጊውን መረጃ በመያዝ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችል መገለጹን የቢሮው መረጃ አመልክቷል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
9 days ago
ኢትዮጵያና አዘርባጃን፣ ከዲፕሎማሲ ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ጠንካራ ዲፕሎማሲዊ ግንኙት እየገነቡ መጥተዋል፡፡
በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙት እነዚህ ሁለት ሀገራት የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ የመከላከያ እና የቴክኖሎጂ ትብብሮችን ወደ ጠንካራና አዲስ ምዕራፍ ለማሳደግ እየሰሩ ናቸው።
ሀገራቱ የሶቪየት ኅብረት መፍረስን ተከትሎ አዘርባጃን ሪፐብሊክ ራሷን የቻለች ሀገር ከሆነች በኋላ ግንኙነታቸውን ቀስ በቀስ እያጠናከሩ መጥተዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ለበርካታ ዓመታት በዘለቀው ግንኙነታቸው የየሀገራቱ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጉብኝቶችን አድርገዋል፡፡
ሕዳር 2017 ዓ.ም አዘርባጃን ባስተናገደችው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ29) ለመሳተፍ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ወደ ባኩ ተጉዘው ነበር፡፡
በቆታቸውም የአዘርባጃንን የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ 3ኛው የኢትዮ-አዘርባጃን የፖለቲካ ምክክር መድረክ የተካሄደ ሲሆን÷ መድረኩ የሁለቱን ሀገራት የፖለቲካ ትስስር ወደ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን የሚያመላክት ነበር፡፡
በመቀጠልም የካቲት 2018 ዓ.ም ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባኩ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ከፍ አድርጓል።
በዚህ ሳምንት ደግሞ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ የፓርላማ አፈ ጉባዔ ሳሂባ ጋፋሮቫ ኢትዮጵያን እየጎበኙ የሚገኙ ሲሆን÷ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ከፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔዎች ጋር መክረዋል፡፡
ኢትዮጵያና አዘርባጃን በታሪክና በጂኦግራፊያዊ አቀማመጣቸው ቢለያዩም በርካታ የጋራ ባህሪያት አሏቸው።
ሁለቱም ጂኦፖለቲካዊ ፉክክር ባሉባቸው ቀጣናዎች ይገኛሉ፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ፤ አዘርባጃን ደግሞ በደቡብ ካውካሰስ ክልል፡፡ በየቀጣናቸው ሁለቱም ሀገራት ለሰላምና ደህንነት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡
በዓለም አቀፍ ፖለቲካም ሁለቱ ሀገራት ከምሥራቅና ከምዕራቡ ዓለማት ጋር ሚዛኑን የጠበቀ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን ይከተላሉ፡፡
ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን መሠረተ ልማትን፣ ዲጂታል ሽግግርን፣ ኢንዱስትሪን እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለልማትና ዕድገታቸው ትኩረት ሰጥተው እየሰሩባቸው ያሉ ዘርፎች ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዘርባጃንን በጎበኙበት ወቅት የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ የሀገራቱን ግንኙነት አስመልክተው ሲገልጹ፣ "አጋርነታችን በርካታ ጠቃሚ ጉዳዮችን ያካተተ ነው" ነበር ያሉት።
ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ በወታደራዊ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በሌሎች ዘርፎች ግንኙነታቸው እያደገ መምጣቱን መሪዎቹ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ ብልፅግና ፓርቲ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማሸነፉን አስመልክቶ በላኩት የደስታ መልዕክት፣ "በአዘርባጃን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት በአዎንታዊ አቅጣጫ እያደገ መሆኑ የሚያስደስት ነው" በማለት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በአዲስ መልክ እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት÷ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በአቪዬሽን፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በነጻ የንግድ ቀጣናዎች ረገድ የተከናወኑ የጋራ የኢኮኖሚዊ ትብብሮች፣ የሁለቱን ሀገራት አጋርነት እያደገ መምጣት ያመለከተ ነው ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት አንደኛቸው ከሌላኛው በበርካታ ዘርፎች ልምዶችን እየተለዋወጡ ሲሆን÷ ለአብነትም ኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአዘርባጃኑ አሳን ክድመት (ASAN Khidmet) የመንግሥት ዲጂታል አገልግሎት ልምድ የተወሰደ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ነው።
አዘርባጃን በበኩሏ በኢትዮጵያ በኩል ወደ አፍሪካ ገበያ ለመግባት ጥሩ መደላድል ታገኛለች። በዚህ መልኩ ሁለቱ ሀገራት የጋራ ጥቅምን በማስፋት በዓለም ኢኮኖሚና ጂኦፖለቲካ አወቃቀር ውስጥ ይበልጥ የሚጎለብት አጋርነት ሊገነቡ ይችላሉ።
ሁለቱ ሀገራት የሚጋሯቸው የልማት ርዕይ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታ፣ የዲጂታል ሽግግር፣ የኢኮኖሚ ብዝሃነት እና ቀጣናዊ ትብብሮች ግንኙነታቸውን ከፍ ወዳለ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚያሳድግ ነው።
በቴዎድሮስ ሳህለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ጠንካራ ዲፕሎማሲዊ ግንኙት እየገነቡ መጥተዋል፡፡
በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙት እነዚህ ሁለት ሀገራት የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ የመከላከያ እና የቴክኖሎጂ ትብብሮችን ወደ ጠንካራና አዲስ ምዕራፍ ለማሳደግ እየሰሩ ናቸው።
ሀገራቱ የሶቪየት ኅብረት መፍረስን ተከትሎ አዘርባጃን ሪፐብሊክ ራሷን የቻለች ሀገር ከሆነች በኋላ ግንኙነታቸውን ቀስ በቀስ እያጠናከሩ መጥተዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ለበርካታ ዓመታት በዘለቀው ግንኙነታቸው የየሀገራቱ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጉብኝቶችን አድርገዋል፡፡
ሕዳር 2017 ዓ.ም አዘርባጃን ባስተናገደችው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ29) ለመሳተፍ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ወደ ባኩ ተጉዘው ነበር፡፡
በቆታቸውም የአዘርባጃንን የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ 3ኛው የኢትዮ-አዘርባጃን የፖለቲካ ምክክር መድረክ የተካሄደ ሲሆን÷ መድረኩ የሁለቱን ሀገራት የፖለቲካ ትስስር ወደ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን የሚያመላክት ነበር፡፡
በመቀጠልም የካቲት 2018 ዓ.ም ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባኩ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ከፍ አድርጓል።
በዚህ ሳምንት ደግሞ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ የፓርላማ አፈ ጉባዔ ሳሂባ ጋፋሮቫ ኢትዮጵያን እየጎበኙ የሚገኙ ሲሆን÷ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ከፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔዎች ጋር መክረዋል፡፡
ኢትዮጵያና አዘርባጃን በታሪክና በጂኦግራፊያዊ አቀማመጣቸው ቢለያዩም በርካታ የጋራ ባህሪያት አሏቸው።
ሁለቱም ጂኦፖለቲካዊ ፉክክር ባሉባቸው ቀጣናዎች ይገኛሉ፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ፤ አዘርባጃን ደግሞ በደቡብ ካውካሰስ ክልል፡፡ በየቀጣናቸው ሁለቱም ሀገራት ለሰላምና ደህንነት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡
በዓለም አቀፍ ፖለቲካም ሁለቱ ሀገራት ከምሥራቅና ከምዕራቡ ዓለማት ጋር ሚዛኑን የጠበቀ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን ይከተላሉ፡፡
ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን መሠረተ ልማትን፣ ዲጂታል ሽግግርን፣ ኢንዱስትሪን እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለልማትና ዕድገታቸው ትኩረት ሰጥተው እየሰሩባቸው ያሉ ዘርፎች ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዘርባጃንን በጎበኙበት ወቅት የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ የሀገራቱን ግንኙነት አስመልክተው ሲገልጹ፣ "አጋርነታችን በርካታ ጠቃሚ ጉዳዮችን ያካተተ ነው" ነበር ያሉት።
ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ በወታደራዊ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በሌሎች ዘርፎች ግንኙነታቸው እያደገ መምጣቱን መሪዎቹ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ ብልፅግና ፓርቲ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማሸነፉን አስመልክቶ በላኩት የደስታ መልዕክት፣ "በአዘርባጃን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት በአዎንታዊ አቅጣጫ እያደገ መሆኑ የሚያስደስት ነው" በማለት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በአዲስ መልክ እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት÷ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በአቪዬሽን፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በነጻ የንግድ ቀጣናዎች ረገድ የተከናወኑ የጋራ የኢኮኖሚዊ ትብብሮች፣ የሁለቱን ሀገራት አጋርነት እያደገ መምጣት ያመለከተ ነው ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት አንደኛቸው ከሌላኛው በበርካታ ዘርፎች ልምዶችን እየተለዋወጡ ሲሆን÷ ለአብነትም ኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአዘርባጃኑ አሳን ክድመት (ASAN Khidmet) የመንግሥት ዲጂታል አገልግሎት ልምድ የተወሰደ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ነው።
አዘርባጃን በበኩሏ በኢትዮጵያ በኩል ወደ አፍሪካ ገበያ ለመግባት ጥሩ መደላድል ታገኛለች። በዚህ መልኩ ሁለቱ ሀገራት የጋራ ጥቅምን በማስፋት በዓለም ኢኮኖሚና ጂኦፖለቲካ አወቃቀር ውስጥ ይበልጥ የሚጎለብት አጋርነት ሊገነቡ ይችላሉ።
ሁለቱ ሀገራት የሚጋሯቸው የልማት ርዕይ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታ፣ የዲጂታል ሽግግር፣ የኢኮኖሚ ብዝሃነት እና ቀጣናዊ ትብብሮች ግንኙነታቸውን ከፍ ወዳለ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚያሳድግ ነው።
በቴዎድሮስ ሳህለ
Sponsored by
Surafel
9 days ago
የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ በፍጥነትና በጥራት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
******************
የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ በቴክኖሎጂ፣ በፍጥነት፣ በፈጠራና በጥራት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ ሀገር በቀል ሆኖ በሰባት አምዶች ተደራጅቶ የተቀረጸው የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር አፈጻጸም ሪፖርት ለሪፎርም ምክር ቤቱ ቀርቦ በዝርዝር መገምገሙን አስታውቀዋል።
ሪፖርቱ ዘመኑን የዋጀና በተዋረድ የተናበበ አደረጃጀት፣ ብቃት ያለው የሰው ኃይል ስምሪት፣ ብዝሃነት፣ ዲጂታላይዜሽን፣ የለውጥ አመራር እና የአገልግሎት ማሻሻያን የያዘ መሆኑን ገልጸዋል።
አፈጻጸሙም ፍጥነትን፣ ፈጠራን፣ ፈጻሚዎቹን ባለቤት ማድረግንና ዘላቂ ሥርዓት ግንባታን መሠረት በማድረግ በጥብቅ ዲስፕሊንና በእውቀት ውጤታማ እና ተስፋ በሚሰጥ ሁኔታ እየተፈጸመ መሆኑን አይተናል ብለዋል።
በሪፖርቱ መሠረት ሰው ተኮር በሆነ ሁኔታ የመሶብ አገልግሎትን በማስፋፋት ሂደት በየከተሞቹ ጉልህ የሚባል መሻሻል መታየቱን ጠቁመው፣ በአገልግሎት ማሻሻያ ረገድ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻልና በዜጎች በኩል የነበረውን እሮሮ መፍታት መጀመሩ በተግባር የታየ መሆኑን አመልክተዋል።
የተጀመረው የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ በቴክኖሎጂ፣ በፍጥነት፣ በፈጠራ፣ በጥራትና በታማኝነት ማስፋፋቱ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም ገልጸዋል።
ለዚህም ሥራ የጠራ መረጃ ማደራጀት፣ ቴክኖሎጂን ማበልጸግ እና የሰራተኞችን ብቃት ማጠናከር የቀጣይ ትኩረት እንዲሆን በሪፎርም ምክር ቤቱ አቅጣጫ መቀመጡንም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገልጸዋል።
******************
የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ በቴክኖሎጂ፣ በፍጥነት፣ በፈጠራና በጥራት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ ሀገር በቀል ሆኖ በሰባት አምዶች ተደራጅቶ የተቀረጸው የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር አፈጻጸም ሪፖርት ለሪፎርም ምክር ቤቱ ቀርቦ በዝርዝር መገምገሙን አስታውቀዋል።
ሪፖርቱ ዘመኑን የዋጀና በተዋረድ የተናበበ አደረጃጀት፣ ብቃት ያለው የሰው ኃይል ስምሪት፣ ብዝሃነት፣ ዲጂታላይዜሽን፣ የለውጥ አመራር እና የአገልግሎት ማሻሻያን የያዘ መሆኑን ገልጸዋል።
አፈጻጸሙም ፍጥነትን፣ ፈጠራን፣ ፈጻሚዎቹን ባለቤት ማድረግንና ዘላቂ ሥርዓት ግንባታን መሠረት በማድረግ በጥብቅ ዲስፕሊንና በእውቀት ውጤታማ እና ተስፋ በሚሰጥ ሁኔታ እየተፈጸመ መሆኑን አይተናል ብለዋል።
በሪፖርቱ መሠረት ሰው ተኮር በሆነ ሁኔታ የመሶብ አገልግሎትን በማስፋፋት ሂደት በየከተሞቹ ጉልህ የሚባል መሻሻል መታየቱን ጠቁመው፣ በአገልግሎት ማሻሻያ ረገድ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻልና በዜጎች በኩል የነበረውን እሮሮ መፍታት መጀመሩ በተግባር የታየ መሆኑን አመልክተዋል።
የተጀመረው የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ በቴክኖሎጂ፣ በፍጥነት፣ በፈጠራ፣ በጥራትና በታማኝነት ማስፋፋቱ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም ገልጸዋል።
ለዚህም ሥራ የጠራ መረጃ ማደራጀት፣ ቴክኖሎጂን ማበልጸግ እና የሰራተኞችን ብቃት ማጠናከር የቀጣይ ትኩረት እንዲሆን በሪፎርም ምክር ቤቱ አቅጣጫ መቀመጡንም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገልጸዋል።
10 days ago
የአበል አፈፃፀም መመሪያ‼️
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጭ እና በቅዳሜ ቀናት ለሚሰሩ ሠራተኞች የትራንስፖርት አበል አፈጻጸም መመሪያ አውጥቷል።
በመመሪያው መሠረት በቅዳሜ ቀን ለሚሰሩ ሠራተኞች በቀን 200 ብር (በወር 800 ብር) እንዲሁም በምሽት ለሚሰሩ የትራንስፖርት መመለሻ በቀን 100 ብር (በወር 2,200 ብር) ተመድቧል። በዚህም መሠረት አንድ ሠራተኛ በወር እስከ 3,000 ብር የትራንስፖርት አበል ማግኘት ይችላል።
የትራንስፖርት አበል የሚከፈለው ከመደበኛ ሰዓት በኋላ አገልግሎት ለሚሰጡ ሠራተኞች፤ በቅዳሜ ቀናት በተፈቀደ የሥራ መርሐ-ግብር መሠረት ለሚሰሩ ሠራተኞች ብቻ ነው።
- በረዥም ጊዜ ሥልጠና ወይም ትምህርት ላይ ለሚገኝ ሠራተኛ፤
- በተፈቀደው የሥራ መርሐ-ግብር መሠረት በሥራ ላይ ላልተገኘ ሠራተኛ፤
- ተቋሙ የጋራ ወይም በተናጥል ትራንስፖርት አገልግሎት ላቀረበለት ሠራተኛ እና በተመሳሳይ ዓላማ ከሌላ ምንጭ የመጓጓዣ ድጋፍ የሚያገኝ ሠራተኛ የዚህ ትራንስፖርት አበል ተጠቃሚ አይሆንም
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጭ እና በቅዳሜ ቀናት ለሚሰሩ ሠራተኞች የትራንስፖርት አበል አፈጻጸም መመሪያ አውጥቷል።
በመመሪያው መሠረት በቅዳሜ ቀን ለሚሰሩ ሠራተኞች በቀን 200 ብር (በወር 800 ብር) እንዲሁም በምሽት ለሚሰሩ የትራንስፖርት መመለሻ በቀን 100 ብር (በወር 2,200 ብር) ተመድቧል። በዚህም መሠረት አንድ ሠራተኛ በወር እስከ 3,000 ብር የትራንስፖርት አበል ማግኘት ይችላል።
የትራንስፖርት አበል የሚከፈለው ከመደበኛ ሰዓት በኋላ አገልግሎት ለሚሰጡ ሠራተኞች፤ በቅዳሜ ቀናት በተፈቀደ የሥራ መርሐ-ግብር መሠረት ለሚሰሩ ሠራተኞች ብቻ ነው።
- በረዥም ጊዜ ሥልጠና ወይም ትምህርት ላይ ለሚገኝ ሠራተኛ፤
- በተፈቀደው የሥራ መርሐ-ግብር መሠረት በሥራ ላይ ላልተገኘ ሠራተኛ፤
- ተቋሙ የጋራ ወይም በተናጥል ትራንስፖርት አገልግሎት ላቀረበለት ሠራተኛ እና በተመሳሳይ ዓላማ ከሌላ ምንጭ የመጓጓዣ ድጋፍ የሚያገኝ ሠራተኛ የዚህ ትራንስፖርት አበል ተጠቃሚ አይሆንም
Seledadotio
Seledadotio
13 days ago
በካናዳ የሚኖሩ የዳያስፖራ አባላት በኢትዮጵያ ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው ገለፁ
**********************
በካናዳ ካልጋሪና ብሩክስ ከተሞች የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት በሀገራቸው ባሉ ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ተሳትፏቸውን ለማሳደግና ተጠቃሚ ለመሆን ያላቸውን ፍላጎት ገልፀዋል።
በካናዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባዘጋጀው የዳያስፖራ መድረክ ላይ፣ መንግሥት ለውጭ ነዋሪዎች ያመቻቻቸው አዳዲስ የኢንቨስትመንት ዕድሎች፣ የህግ ማዕቀፎች እና የአገልግሎት ማሻሻያዎች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የዳያስፖራ አባላት፣ መንግሥት የዜጎችን ተሳትፎ ለማጠናከር እያደረጋቸው ያሉትን የፖሊሲ ማሻሻያዎች አድንቀዋል።
በተለይም በአሁኑ ወቅት የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በመላ ኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ሀገሪቱን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ እያሸጋገሯት መሆኑን ጠቅሰው፤ በተጨማሪም የ«መሶብ» የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ መጀመር መንግሥት አሰራርን ለማዘመንና ለማቀላጠፍ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አውስተዋል።
በካናዳ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ቴዎድሮስ ግርማ በበኩላቸው፣ ዳያስፖራው በሀገሩ ሁለንተናዊ ልማት ላይ የድርሻውን እንዲወጣ መንግሥት የፈጠራቸውን ምቹ መደላድሎች በዝርዝር አብራርተዋል።
መንግሥት የዳያስፖራውን ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ዘመናዊ፣ ግልጽና ቀልጣፋ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን መግለፃቸውን በካናዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመልክቷል።
አምባሳደሩ አክለውም፣ የዳያስፖራ አባላት በመካከላቸው ያሉ ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው፣ እውቀትና ገንዘባቸውን አቀናጅተው በትላልቅ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ በጋራ እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።
**********************
በካናዳ ካልጋሪና ብሩክስ ከተሞች የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት በሀገራቸው ባሉ ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ተሳትፏቸውን ለማሳደግና ተጠቃሚ ለመሆን ያላቸውን ፍላጎት ገልፀዋል።
በካናዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባዘጋጀው የዳያስፖራ መድረክ ላይ፣ መንግሥት ለውጭ ነዋሪዎች ያመቻቻቸው አዳዲስ የኢንቨስትመንት ዕድሎች፣ የህግ ማዕቀፎች እና የአገልግሎት ማሻሻያዎች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የዳያስፖራ አባላት፣ መንግሥት የዜጎችን ተሳትፎ ለማጠናከር እያደረጋቸው ያሉትን የፖሊሲ ማሻሻያዎች አድንቀዋል።
በተለይም በአሁኑ ወቅት የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በመላ ኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ሀገሪቱን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ እያሸጋገሯት መሆኑን ጠቅሰው፤ በተጨማሪም የ«መሶብ» የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ መጀመር መንግሥት አሰራርን ለማዘመንና ለማቀላጠፍ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አውስተዋል።
በካናዳ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ቴዎድሮስ ግርማ በበኩላቸው፣ ዳያስፖራው በሀገሩ ሁለንተናዊ ልማት ላይ የድርሻውን እንዲወጣ መንግሥት የፈጠራቸውን ምቹ መደላድሎች በዝርዝር አብራርተዋል።
መንግሥት የዳያስፖራውን ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ዘመናዊ፣ ግልጽና ቀልጣፋ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን መግለፃቸውን በካናዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመልክቷል።
አምባሳደሩ አክለውም፣ የዳያስፖራ አባላት በመካከላቸው ያሉ ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው፣ እውቀትና ገንዘባቸውን አቀናጅተው በትላልቅ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ በጋራ እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።
14 days ago
የአገልግሎት በደልን ያከሰመው ቴክኖሎጂ
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ለዘመናት የኢትዮጵያ መንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ የዜጎችን ትዕግሥት የሚፈትን፣ ጉልበት እና ጊዜን የሚበላ የ"ዶሴ ዘመን" እስረኛ ሆኖ ቆይቷል።
ዜጎች ወረቀት ታቅፈው ረጅም ሰልፍ ተሰልፈው ከአንዱ ቢሮ ወደ ሌላው ሲንከራተቱ፣ "ፋይል ጠፍቷል" በሚል ሰበብ ለሙስና፣ ለእጅ መንሻ እንዲሁም ለተለያየ እንግልት ሲዳረጉ መቆየታቸው የአደባባይ ምስጢር ብቻ ሳይሆን የሀገር ሕመም ነበር።
ይህ ማነቆ ግለሰባዊ እንግልት ብቻ ሳይሆን በመንግሥት እና በሕዝብ መካከል ያለውን መተማመን የሚሸረሽር፣ መልካም አስተዳደርን የሚያቀጭጭ የፖለቲካ እና የማህበራዊ ቀውስ ምንጭ ሆኖ ቆይቷል።
አሁን ግን ይህን አድካሚ የወረቀት ቢሮክራሲ ታሪክ የሚያደርግ፣ የመንግሥትን የአገልግሎት አሰጣጥ ባህል ከመሰረቱ የሚቀይር "መሶብ" የተሰኘ ሀገር በቀል የዲጂታል ሥርዓት የብርሃን ጮራ ፈንጥቋል።
«መሶብ» የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ ተቋማትን አገልግሎቶች በአንድ ማዕድ በማሰባሰብ ዜጎች ሁሉንም ጉዳዮቻቸውን በአንድ መስኮት በቀላሉ እንዲያጠናቅቁ የሚያስችል ሥርዓት ነው።
ይህ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ሥርዓት ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂን ከማቀናጀት የላቀ ጥልቅ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ትርጉም አለው።
አንድ ጉዳይ መቼ እንደገባ እና በማን እጅ እንዳለ በግልጽ የሚያሳይ በመሆኑ፣ ለሙስና የሚደረጉ ድብቅ ድርድሮችን ከመሰረቱ ያመክናል።
አገልግሎት ፈላጊው ከሚስተናገድበት አካል ጋር የሚኖረውን ኢ-መደበኛ የጥቅም መስተጋብር በመቁረጥ መልካም አስተዳደርን በተግባር ያረጋግጣል።
ይህ ደግሞ የተንዛዙ አሠራሮች የሚፈጥሩትን የዜጎች ቅሬታ በማስወገድ፣ በመንግሥት ሥርዓት ላይ ያላቸውን አመኔታ እና እርካታ በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል፤ ፖለቲካዊ መረጋጋትንም ያጠናክራል።
በኢኮኖሚው ዘርፍም ቢሆን የመሶብ ትሩፋት እጅግ የጎላ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር እውን የሚሆነው በመሰል ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ነው። ዜጎች ወረቀት በማሳደድ የሚያጠፉት ወርቃማ ጊዜ ወደ ማምረቻነት ሲቀየር ሀገራዊ ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ ያድጋል። ሥራ ፈጣሪዎች እና ነጋዴዎች ፈጣን አገልግሎት ሲያገኙ፣ የንግድ እንቅስቃሴው ይፋጠናል፤ የሀብት ብክነትም ይቆማል።
ማኅበራዊ ፍትሕን ከማስፈን አኳያም፣ ሁሉም ዜጋ በቴክኖሎጂ ታግዞ ያለ አድልዎ እኩል፣ ቀልጣፋ እና ግልጽ አገልግሎት ማግኘቱ ዴሞክራሲያዊ እኩልነትን እና ማኅበራዊ መስተጋብርን ያጠናክራል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጅማሬውን ያደረገው ይህ የተቀናጀ የአገልግሎት ሥርዓት፣ በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ክልሎች ከ100 በላይ ማዕከላትን በመክፈት ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
ከዚህም አልፎ ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎቶች እና ዜጎች ባሉበት ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበት የተቀናጀ የዲጂታል ሞባይል መተግበሪያ ወደ ሥራ መግባቱ ተደራሽነትን ይበልጥ አስፍቶታል።
ይህ አበረታች ጅማሬ በተጠና ስትራቴጂ እየተመራ ሲሆን፣ ከ2019 እስከ 2021 ዓ.ም በሚተገበረው አዲስ ስትራቴጂክ ዕቅድ መሠረት በመጪዎቹ ሦስት ዓመታት በሁሉም ወረዳዎች ተደራሽ ለማድረግ፣ ተቋማዊ አሠራሩን ለማዘመንና ጥራቱን ለማሳደግ ትልቅ ራዕይ ተሰንቋል።
በአጠቃላይ «መሶብ» የዶሴ ዘመንን ሸኝቶ የዲጂታል ዘመንን ያበሰረ፣ መንግሥት ለሰው ተኮር አገልግሎት የሰጠው ትኩረት ማረጋገጫ ነው። ይህ ሥርዓት የሀገራችንን ፖለቲካዊ ጤናማነት፣ ማህበራዊ ፍትሕ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የሚያፋጥን ሞተር ነው።
በመሆኑም ይህ ታሪካዊ የአገልግሎት አሰጣጥ እጥፋት ወደ ኋላ እንዳይቀለበስ፣ የጀመርነው የዲጂታል ብርሃን እንዳይደበዝዝ እንዲሁም ለሥርዓቱ ቀጣይነት ጠንካራ የሳይበር ደኅንነት ጥበቃ ማድረግ ይገባል።
እያንዳንዱ ዜጋ፣ ማኅበረሰብ እና ባለድርሻ አካል ይህን ሥርዓት በባለቤትነት ሊጠብቀው፣ ከአሠራር ግድፈቶች ሊታደገው፣ ባህል አድርጎ ሊወስደው እና ይበልጥ ሊያጎለብተው ግድ ይላል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ለዘመናት የኢትዮጵያ መንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ የዜጎችን ትዕግሥት የሚፈትን፣ ጉልበት እና ጊዜን የሚበላ የ"ዶሴ ዘመን" እስረኛ ሆኖ ቆይቷል።
ዜጎች ወረቀት ታቅፈው ረጅም ሰልፍ ተሰልፈው ከአንዱ ቢሮ ወደ ሌላው ሲንከራተቱ፣ "ፋይል ጠፍቷል" በሚል ሰበብ ለሙስና፣ ለእጅ መንሻ እንዲሁም ለተለያየ እንግልት ሲዳረጉ መቆየታቸው የአደባባይ ምስጢር ብቻ ሳይሆን የሀገር ሕመም ነበር።
ይህ ማነቆ ግለሰባዊ እንግልት ብቻ ሳይሆን በመንግሥት እና በሕዝብ መካከል ያለውን መተማመን የሚሸረሽር፣ መልካም አስተዳደርን የሚያቀጭጭ የፖለቲካ እና የማህበራዊ ቀውስ ምንጭ ሆኖ ቆይቷል።
አሁን ግን ይህን አድካሚ የወረቀት ቢሮክራሲ ታሪክ የሚያደርግ፣ የመንግሥትን የአገልግሎት አሰጣጥ ባህል ከመሰረቱ የሚቀይር "መሶብ" የተሰኘ ሀገር በቀል የዲጂታል ሥርዓት የብርሃን ጮራ ፈንጥቋል።
«መሶብ» የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ ተቋማትን አገልግሎቶች በአንድ ማዕድ በማሰባሰብ ዜጎች ሁሉንም ጉዳዮቻቸውን በአንድ መስኮት በቀላሉ እንዲያጠናቅቁ የሚያስችል ሥርዓት ነው።
ይህ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ሥርዓት ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂን ከማቀናጀት የላቀ ጥልቅ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ትርጉም አለው።
አንድ ጉዳይ መቼ እንደገባ እና በማን እጅ እንዳለ በግልጽ የሚያሳይ በመሆኑ፣ ለሙስና የሚደረጉ ድብቅ ድርድሮችን ከመሰረቱ ያመክናል።
አገልግሎት ፈላጊው ከሚስተናገድበት አካል ጋር የሚኖረውን ኢ-መደበኛ የጥቅም መስተጋብር በመቁረጥ መልካም አስተዳደርን በተግባር ያረጋግጣል።
ይህ ደግሞ የተንዛዙ አሠራሮች የሚፈጥሩትን የዜጎች ቅሬታ በማስወገድ፣ በመንግሥት ሥርዓት ላይ ያላቸውን አመኔታ እና እርካታ በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል፤ ፖለቲካዊ መረጋጋትንም ያጠናክራል።
በኢኮኖሚው ዘርፍም ቢሆን የመሶብ ትሩፋት እጅግ የጎላ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር እውን የሚሆነው በመሰል ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ነው። ዜጎች ወረቀት በማሳደድ የሚያጠፉት ወርቃማ ጊዜ ወደ ማምረቻነት ሲቀየር ሀገራዊ ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ ያድጋል። ሥራ ፈጣሪዎች እና ነጋዴዎች ፈጣን አገልግሎት ሲያገኙ፣ የንግድ እንቅስቃሴው ይፋጠናል፤ የሀብት ብክነትም ይቆማል።
ማኅበራዊ ፍትሕን ከማስፈን አኳያም፣ ሁሉም ዜጋ በቴክኖሎጂ ታግዞ ያለ አድልዎ እኩል፣ ቀልጣፋ እና ግልጽ አገልግሎት ማግኘቱ ዴሞክራሲያዊ እኩልነትን እና ማኅበራዊ መስተጋብርን ያጠናክራል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጅማሬውን ያደረገው ይህ የተቀናጀ የአገልግሎት ሥርዓት፣ በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ክልሎች ከ100 በላይ ማዕከላትን በመክፈት ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
ከዚህም አልፎ ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎቶች እና ዜጎች ባሉበት ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበት የተቀናጀ የዲጂታል ሞባይል መተግበሪያ ወደ ሥራ መግባቱ ተደራሽነትን ይበልጥ አስፍቶታል።
ይህ አበረታች ጅማሬ በተጠና ስትራቴጂ እየተመራ ሲሆን፣ ከ2019 እስከ 2021 ዓ.ም በሚተገበረው አዲስ ስትራቴጂክ ዕቅድ መሠረት በመጪዎቹ ሦስት ዓመታት በሁሉም ወረዳዎች ተደራሽ ለማድረግ፣ ተቋማዊ አሠራሩን ለማዘመንና ጥራቱን ለማሳደግ ትልቅ ራዕይ ተሰንቋል።
በአጠቃላይ «መሶብ» የዶሴ ዘመንን ሸኝቶ የዲጂታል ዘመንን ያበሰረ፣ መንግሥት ለሰው ተኮር አገልግሎት የሰጠው ትኩረት ማረጋገጫ ነው። ይህ ሥርዓት የሀገራችንን ፖለቲካዊ ጤናማነት፣ ማህበራዊ ፍትሕ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የሚያፋጥን ሞተር ነው።
በመሆኑም ይህ ታሪካዊ የአገልግሎት አሰጣጥ እጥፋት ወደ ኋላ እንዳይቀለበስ፣ የጀመርነው የዲጂታል ብርሃን እንዳይደበዝዝ እንዲሁም ለሥርዓቱ ቀጣይነት ጠንካራ የሳይበር ደኅንነት ጥበቃ ማድረግ ይገባል።
እያንዳንዱ ዜጋ፣ ማኅበረሰብ እና ባለድርሻ አካል ይህን ሥርዓት በባለቤትነት ሊጠብቀው፣ ከአሠራር ግድፈቶች ሊታደገው፣ ባህል አድርጎ ሊወስደው እና ይበልጥ ሊያጎለብተው ግድ ይላል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
19 days ago
መሶብ የጊዜና የሀብት ብክነትን አስቀርቶልናል - የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
******************
የመንግሥት አገልግሎት እና የአስተዳደር ሪፎርም ውጤታማ እንዲሆን በከተሞች የተጀመረው የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ነባራዊ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ አይነተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል።
ይህ ዘመናዊ አሠራር በተለይም ከዚህ ቀደም በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የነበረውን ጥርጣሬ በመቀነስ ዜጎች ያጋጥማቸው የነበረውን የጊዜ እና የሀብት ብክነት በከፍተኛ ደረጃ ማስቀረት ችሏል።
የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች እንደገለጹት፤ ማዕከሉ የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ማስተሳሰሩ ከዚህ ቀደም ከአንድ ቢሮ ወደ ሌላ ቢሮ ለመንከራተት ይዳርግ የነበረውን ከፍተኛ እንግልት አስቀርቶላቸዋል።
የማዕከሉ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ የታገዙ መሆናቸው፣ ማኅበረሰቡ ቴክኖሎጂን በአግባቡና በብቃት እንዲጠቀም አዲስ መነቃቃትን የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል።
የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተክለአብ ቡሎ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ መንግሥት ነባራዊ የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ስትራቴጂካዊ ማዕቀፎችን ቀርጾ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አመላክተዋል።
የቦንጋ መሶብ አንድ ማዕከልም የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን በማዘመን፣ ለዜጎች ምቹና ቀልጣፋ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እየተካሄደ የሚገኘውን አገራዊ ጥረት የሚያግዝ ተጨማሪ ትልቅ አቅም መሆኑን ከንቲባው አብራርተዋል።
አሁን ላይ በሙሉ አቅሙ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ይህ የቦንጋ መሶብ አንድ ማዕከል፤ 3 የፌዴራል ተቋማትን ጨምሮ 8 የተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን በአንድ ጥላ ሥር ያካተተ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 44 ልዩ ልዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን ለአካባቢው ነዋሪዎች በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ ተደራሽ እያደረገ ይገኛል።
በሰለሞን ባረና
******************
የመንግሥት አገልግሎት እና የአስተዳደር ሪፎርም ውጤታማ እንዲሆን በከተሞች የተጀመረው የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ነባራዊ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ አይነተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል።
ይህ ዘመናዊ አሠራር በተለይም ከዚህ ቀደም በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የነበረውን ጥርጣሬ በመቀነስ ዜጎች ያጋጥማቸው የነበረውን የጊዜ እና የሀብት ብክነት በከፍተኛ ደረጃ ማስቀረት ችሏል።
የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች እንደገለጹት፤ ማዕከሉ የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ማስተሳሰሩ ከዚህ ቀደም ከአንድ ቢሮ ወደ ሌላ ቢሮ ለመንከራተት ይዳርግ የነበረውን ከፍተኛ እንግልት አስቀርቶላቸዋል።
የማዕከሉ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ የታገዙ መሆናቸው፣ ማኅበረሰቡ ቴክኖሎጂን በአግባቡና በብቃት እንዲጠቀም አዲስ መነቃቃትን የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል።
የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተክለአብ ቡሎ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ መንግሥት ነባራዊ የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ስትራቴጂካዊ ማዕቀፎችን ቀርጾ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አመላክተዋል።
የቦንጋ መሶብ አንድ ማዕከልም የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን በማዘመን፣ ለዜጎች ምቹና ቀልጣፋ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እየተካሄደ የሚገኘውን አገራዊ ጥረት የሚያግዝ ተጨማሪ ትልቅ አቅም መሆኑን ከንቲባው አብራርተዋል።
አሁን ላይ በሙሉ አቅሙ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ይህ የቦንጋ መሶብ አንድ ማዕከል፤ 3 የፌዴራል ተቋማትን ጨምሮ 8 የተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን በአንድ ጥላ ሥር ያካተተ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 44 ልዩ ልዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን ለአካባቢው ነዋሪዎች በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ ተደራሽ እያደረገ ይገኛል።
በሰለሞን ባረና
Sponsored by
Surafel
29 days ago
" ህጋዊው የውል ማሻሻያ ለ2 ዓመታት ይቆያል " - ቢሮው
በአዲስ አበባ የ2019 በጀት ዓመት የቤት ኪራይ ዓመታዊ የጭማሪ ጣሪያ 11.5 በመቶ ሆኖ እንዲጸድቅ መደረጉ ይታወሳል።
ከዚህ ተመን በላይ መጨመር በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን ህጋዊው የውል ማሻሻያም ለ2 ዓመታት ይቆያል ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
ከህጋዊ አሰራር ውጪ የሚደረጉ "የመንደር ውሎች" የተከለከሉ ሲሆን ውል በማያድሱና ህግ በሚተላለፉ አካላት ላይ ቅጣት ይጣላል።
የውል እድሳት ጊዜያቸው አልፎ አከራይም ተከራይም አብረው ኖረው እድሳት ሳይፈጽሙ እስከ 2 ወር ከቆዩ የ1 ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይጣልባቸዋል።
ውል ሳያድሱ 3 ወር እና ከዚያ በላይ የቆዩ የ2 ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይከፍላሉ።
አዲስ ተከራይ አስገብተው ውል ያላደሱ እና ያላስመዘገቡ የ1 ወር የቤት ኪራይ ይቀጣሉ።
በጥቆማ ወይም በክትትል ውል ያላደሱ ወይም ያላስመዘገቡ መሆናቸው ከተረጋገጠ ደግሞ ከ1 እስከ 3 ወር የሚደርስ የኪራይ መጠን ቅጣት እንደሚጣልባቸው ቢሮው አሳውቋል።
የቤት ኪራይ የውል እድሳት በክፍለ ከተማ፣ በወረዳ ጽህፈት ቤቶች ወይም በ"መሶብ" ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች ማከናወን ይቻላል ተብሏል።
tikvahethiopia
በአዲስ አበባ የ2019 በጀት ዓመት የቤት ኪራይ ዓመታዊ የጭማሪ ጣሪያ 11.5 በመቶ ሆኖ እንዲጸድቅ መደረጉ ይታወሳል።
ከዚህ ተመን በላይ መጨመር በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን ህጋዊው የውል ማሻሻያም ለ2 ዓመታት ይቆያል ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
ከህጋዊ አሰራር ውጪ የሚደረጉ "የመንደር ውሎች" የተከለከሉ ሲሆን ውል በማያድሱና ህግ በሚተላለፉ አካላት ላይ ቅጣት ይጣላል።
የውል እድሳት ጊዜያቸው አልፎ አከራይም ተከራይም አብረው ኖረው እድሳት ሳይፈጽሙ እስከ 2 ወር ከቆዩ የ1 ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይጣልባቸዋል።
ውል ሳያድሱ 3 ወር እና ከዚያ በላይ የቆዩ የ2 ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይከፍላሉ።
አዲስ ተከራይ አስገብተው ውል ያላደሱ እና ያላስመዘገቡ የ1 ወር የቤት ኪራይ ይቀጣሉ።
በጥቆማ ወይም በክትትል ውል ያላደሱ ወይም ያላስመዘገቡ መሆናቸው ከተረጋገጠ ደግሞ ከ1 እስከ 3 ወር የሚደርስ የኪራይ መጠን ቅጣት እንደሚጣልባቸው ቢሮው አሳውቋል።
የቤት ኪራይ የውል እድሳት በክፍለ ከተማ፣ በወረዳ ጽህፈት ቤቶች ወይም በ"መሶብ" ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች ማከናወን ይቻላል ተብሏል።
tikvahethiopia
1 month ago
አዲሱ የቤት ኪራይ ውል ህገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪን የሚገታ ነው
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በነዋሪዎች ላይ ያለውን የኑሮ ጫና ለማቃለል እና በቤት ኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥ አሰራሮችን ለመፍታት አዲስ የቤት ኪራይ ውል እድሳት እና የጭማሪ ጣሪያ ተግባራዊ አድርጓል፡፡
ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው ፍትሀዊ የቤት ኪራይ አመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5 በመቶ ሆኖ የጸደቀ ሲሆን ከተቀመጠው የጭማሪ ጣሪያ በላይ ዋጋ መጨመር በጥብቅ የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ እንዳስታወቁት፤ የውል እድሳቱ አከራይንም ሆነ ተከራይን ተጠቃሚ የሚያደርግ እና ህገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪን የሚገታ ነው፡፡
ቢሮው ለውል እድሳቱ ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን እና የአተገባበር ሂደቱን በመከታተል አዋጁን ተፈጻሚ ለማድረግ በጥብቅ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል፡፡
ከህጋዊ አሰራር ውጪ የሚደረጉ "የመንደር ውሎች" ፈጽሞ የተከለከሉ መሆናቸውን እና ከተቀመጠው ህጋዊ ተመን ውጪ የሚያስከፍሉ አከራዮች በህግ ተጠያቂ እንደሚሆኑም ኃላፊዋ አሳስበዋል፡፡
ህጉን በሚተላለፉ እና ውላቸውን በማያድሱ አካላት ላይ ቅጣት እንደሚጣል የገለጹት የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ፤ የውል እድሳት ጊዜያቸው አልፎ አከራይም ተከራይም አብረው ኖረው እድሳት ሳይፈጽሙ እስከ ሁለት ወር ከቆዩ የአንድ ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይጣልባቸዋል ብለዋል፡፡
ውል ሳያድሱ ሶስት ወር እና ከዚያ በላይ የቆዩ ደግሞ የሁለት ወር የቤት ኪራይ ቅጣት የሚከፍሉ ሲሆን አዲስ ተከራይ አስገብተው ውል ያላደሱ እና ያላስመዘገቡ የአንድ ወር የቤት ኪራይ ይቀጣሉም ነው ያሉት፡፡
በጥቆማ ወይም በክትትል ውል ያላደሱ ወይም ያላስመዘገቡ መሆናቸው ከተረጋገጠ ደግሞ ከአንድ እስከ ሶስት ወር የሚደርስ የኪራይ መጠን ቅጣት እንደሚጣልባቸው ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተክሌ በዛብህ በበኩላቸው፣ ከሁለት ዓመት በፊት በወጣው የመኖሪያ ቤት ኪራይ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ከተቆጣጣሪው አካል እውቅና ውጪ የሚደረጉ ውሎች ተቀባይነት እንደሌላቸው ገልጸዋል፡፡
የውል ጊዜ ሲያልቅ አከራዩ ውሉን ማደስ እና ማሳወቅ ግዴታ እንዳለበት በመግለጽ አዲሱ ውል ለሁለት አመታት የሚቆይ ይሆናል ብለዋል፡፡
አዋጁ ተከራዮች መኖሪያ ሲቀይሩ የሚደርስባቸውን የልጆች ትምህርት ቤት እና የሥራ ቦታ መናጋት በማስቀረት ማህበራዊ አብሮነትን እንደሚያጠናክርም ገልጸዋል፡፡
የሚመለከታቸው አካላት በክፍለ ከተማ እና በወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤቶች እንዲሁም በመሶብ ዲጂታል የአንድ ማእከል አገልግሎት መስጫዎች ህጋዊ የውል እድሳት ማከናወን እንደሚችሉም ተጠቁሟል፡፡
AMN
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በነዋሪዎች ላይ ያለውን የኑሮ ጫና ለማቃለል እና በቤት ኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥ አሰራሮችን ለመፍታት አዲስ የቤት ኪራይ ውል እድሳት እና የጭማሪ ጣሪያ ተግባራዊ አድርጓል፡፡
ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው ፍትሀዊ የቤት ኪራይ አመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5 በመቶ ሆኖ የጸደቀ ሲሆን ከተቀመጠው የጭማሪ ጣሪያ በላይ ዋጋ መጨመር በጥብቅ የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ እንዳስታወቁት፤ የውል እድሳቱ አከራይንም ሆነ ተከራይን ተጠቃሚ የሚያደርግ እና ህገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪን የሚገታ ነው፡፡
ቢሮው ለውል እድሳቱ ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን እና የአተገባበር ሂደቱን በመከታተል አዋጁን ተፈጻሚ ለማድረግ በጥብቅ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል፡፡
ከህጋዊ አሰራር ውጪ የሚደረጉ "የመንደር ውሎች" ፈጽሞ የተከለከሉ መሆናቸውን እና ከተቀመጠው ህጋዊ ተመን ውጪ የሚያስከፍሉ አከራዮች በህግ ተጠያቂ እንደሚሆኑም ኃላፊዋ አሳስበዋል፡፡
ህጉን በሚተላለፉ እና ውላቸውን በማያድሱ አካላት ላይ ቅጣት እንደሚጣል የገለጹት የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ፤ የውል እድሳት ጊዜያቸው አልፎ አከራይም ተከራይም አብረው ኖረው እድሳት ሳይፈጽሙ እስከ ሁለት ወር ከቆዩ የአንድ ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይጣልባቸዋል ብለዋል፡፡
ውል ሳያድሱ ሶስት ወር እና ከዚያ በላይ የቆዩ ደግሞ የሁለት ወር የቤት ኪራይ ቅጣት የሚከፍሉ ሲሆን አዲስ ተከራይ አስገብተው ውል ያላደሱ እና ያላስመዘገቡ የአንድ ወር የቤት ኪራይ ይቀጣሉም ነው ያሉት፡፡
በጥቆማ ወይም በክትትል ውል ያላደሱ ወይም ያላስመዘገቡ መሆናቸው ከተረጋገጠ ደግሞ ከአንድ እስከ ሶስት ወር የሚደርስ የኪራይ መጠን ቅጣት እንደሚጣልባቸው ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተክሌ በዛብህ በበኩላቸው፣ ከሁለት ዓመት በፊት በወጣው የመኖሪያ ቤት ኪራይ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ከተቆጣጣሪው አካል እውቅና ውጪ የሚደረጉ ውሎች ተቀባይነት እንደሌላቸው ገልጸዋል፡፡
የውል ጊዜ ሲያልቅ አከራዩ ውሉን ማደስ እና ማሳወቅ ግዴታ እንዳለበት በመግለጽ አዲሱ ውል ለሁለት አመታት የሚቆይ ይሆናል ብለዋል፡፡
አዋጁ ተከራዮች መኖሪያ ሲቀይሩ የሚደርስባቸውን የልጆች ትምህርት ቤት እና የሥራ ቦታ መናጋት በማስቀረት ማህበራዊ አብሮነትን እንደሚያጠናክርም ገልጸዋል፡፡
የሚመለከታቸው አካላት በክፍለ ከተማ እና በወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤቶች እንዲሁም በመሶብ ዲጂታል የአንድ ማእከል አገልግሎት መስጫዎች ህጋዊ የውል እድሳት ማከናወን እንደሚችሉም ተጠቁሟል፡፡
AMN
1 month ago
ተግባራዊ ቅቡልነት፦ በቃላት ሳይሆን በውጤት የሚለካው አዲሱ የሀገር ግንባታ
*****************************
(የዕለቱ መልዕክት)
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ለዘመናት በማይፈጸሙ የተስፋ ቃላት እና በብሔር ማንነት አጀንዳ ሲታመስ ቆይቷል። አሁን ግን ሀገራችን ከዚህ የቃላት እና የተስፋ ፖለቲካ ወጥታ የመንግሥት ቅቡልነት በሚያወራው ሳይሆን በተግባር በሚሠራው ሥራ እና በሚያመጣው ተጨባጭ ውጤት ወደሚሆንበት አዲስ አሠራር እየተሸጋገረች ነው።
ይህ አሠራር በሚመጡ ተጨባጭ ለውጦች ለመለካት የሚሻ አዲስ የሀገር ግንባታ ማዕቀፍ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ኢትዮጵያ ታከናውናለች" በሚለው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በአጽንዖት እንደገለጹት፣ የሀገራችን አዲሱ የታሪክ ምዕራፍ በተስፋ ቃላት ላይ ሳይሆን በተግባራዊ ክንውን እና በጥራት ላይ የተመሠረተ ነው።
ይህ "ኢትዮጵያ ታከናውናለች" የሚለው መርሕ ከተራ መፈክር በላይ በመሆን፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ያላትን የማስፈጸም አቅም እና የሥልጣኔ ልክ የምታሳይበት ዋነኛ መሣሪያ ሆኗል።
በአሁኑ ወቅት በሀገራችን እየታዩ ያሉ ስኬቶች መንግሥት ውጤት የማምጣት አቅሙን በተግባር ያረጋገጠባቸው ማሳያዎች ናቸው።
ከታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታን ከማጠናቀቅ እና ኃይል ማመንጨት ጀምሮ፣ በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው የስንዴ ኤክስፖርት እና የመስኖ ልማት ስኬት፣ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች፣ እንዲሁም የአዲስ አበባ እና የክልል ከተሞችን ገጽታ የቀየሩት የኮሪደር ልማት ሥራዎች የዚሁ ተግባራዊ ሕጋዊነት ውጤቶች ናቸው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እና የኢትዮጵያ ታምርት የኢንዱስትሪ ንቅናቄም ሀገራችን ትላልቅ ዕቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም እንዳላት በተጨባጭ እያሳዩ ነው።
ዋናው ማዕቀፍ ግን የእነዚህ ፕሮጀክቶች መፈጸም ብቻ ሳይሆን፣ ጥቅሞቻቸው በሁሉም ክልሎች፣ ማንነቶች እና የፖለቲካ አመለካከቶች ውስጥ እኩል ሊሰርጹ መቻላቸው ላይ ነው። መንገዶች፣ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እና ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ልማታዊ ውጤቶች ብቻ ሳይሆኑ፣ የፌዴራል ሥርዓቱን ልዩነቶች አቀናጅተው የጋራ ብሔራዊ ልምድን የሚፈጥሩ ሥልታዊ ድልድዮች ናቸው።
ይህ አካሄድ ቀደም ሲል ከነበረው እና ሥልጣኑን በረጅም ጊዜ ተስፋዎች ላይ ብቻ ይመሠርት ከነበረው "ልማታዊ መንግሥት" አስተሳሰብ በእጅጉ የላቀ ነው።
የአሁኑ የመፈጸም ሞዴል ሊለኩ በሚችሉ ውጤቶች፣ በትግበራ ፍጥነት እና በተቋማዊ ብቃት ላይ የተመሠረተ ነው። የሲንጋፖር፣ የቪየትናም እና የማሌዢያ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት፣ ዘላቂ ማኅበራዊ ውል የሚገነባው እና ቢሮክራሲው የሚቀናጀው በተግባር በሚታይ የድህነት ቅነሳ እና የዜጎች የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻል ላይ ነው።
መንግሥት ለኢኮኖሚ ችግሮች የሚሰጠው መፍትሔ በርዕዮተ ዓለም የታጠረ ሳይሆን፣ በተግባር በሚታይ ውጤት ላይ የተመሠረተ ገቢር ነበብ የኢኮኖሚ ፍልስፍና ነው።
ከለውጡ በፊት ኢኮኖሚው በከፍተኛ ዕዳ ተሸብቦ እና በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ተፈትኖ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ይህን የውድቀት ታሪክ መቀየር ተችሏል።
"ለረጅም ጊዜ ኢትዮጵያ በችግሮቿ እንጂ በእምቅ አቅሟ ስትገለጽ አልኖረችም፤ ዛሬ ግን የተለየ ታሪክ ብቅ እያለ ነው" ሲሉ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገራችንን አዲስ ምዕራፍ ያበሰሩት።
ይህ “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” የሚለው መንፈስ በቴክኖሎጂ እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽኑ መስክም በጉልህ እየታየ ይገኛል። በ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ አማካኝነት የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ማቅረብ፣ የ“መሶብ” የአንድ ማዕከል የአገልግሎት መተግበሪያን መዘርጋት እና የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ሥልጠና ንቅናቄን መተግበር ኢትዮጵያን ወደ ዘመናዊ እና ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት እያሸጋገሯት ነው።
እነዚህ የዲጂታል መሠረቶች የቢሮክራሲውን ቅልጥፍና ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ከመንግሥት ጋር ያላቸውን ግንኙነት ፍጹም ዘመናዊ እና ግልጽ ያደርጉታል።
ይህ የተግባር ስኬት እና የማስፈጸም አቅም በሀገር ውስጥ ብቻ የተገደበ ሳይሆን በቀጣናዊ ዲፕሎማሲ እና በጂኦ-ፖለቲካ አቋማችን ላይም ትልቅ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር አካባቢ ያላትን የባሕር በር የማግኘት ሕጋዊ መብት ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት፣ በአፍሪካ ቀንድ ያላት የሰላም እና የፀጥታ ሚና እንዲሁም የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ አጋርነቶቿን የማጠናከር ሥራ የዲፕሎማሲያዊ ቁመቷን በእጅጉ እያሳደገው ይገኛል።
የሀገር ውስጥ የልማት አቅም ሲጎለብት የውጭ ዲፕሎማሲያዊ ተሰሚነትም አብሮ እንደሚገነባ ይህ አካሄድ ሕያው ማሳያ ነው።
"ኢትዮጵያ ታከናውናለች" የሚለው ይፋዊ እውነት በተግባር እየተረጋገጠ በሄደ ቁጥር፣ ልማት ለብሔራዊ ትሥሥር እንደ ትሥሥር ገመድ ማገልገሉን ይቀጥላል። ይሄ የአፈጻጸም ሥልጣኔ ከተራ ፍልስፍና በላይ በመሆን አዲሲቷን ኢትዮጵያ በጠንካራ ዐለት ላይ የሚገነባ ተግባራዊ መሠረት ሆኖ ሊጸና ይገባል።
ኢትዮጵያ ታከናውናለች፤ በሕዝቦቿ ጥረት፣ በጠንካራ ሀገራዊ ተቋማት ግንባታ እና በዲጂታል ዘመን በሚፈጠሩ አዳዲስ ዕድሎች በመታገዝ የተሻለ እና ብሩህ ነገን ትቀርጻለች።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #ebcdotstream #nationalinterest
*****************************
(የዕለቱ መልዕክት)
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ለዘመናት በማይፈጸሙ የተስፋ ቃላት እና በብሔር ማንነት አጀንዳ ሲታመስ ቆይቷል። አሁን ግን ሀገራችን ከዚህ የቃላት እና የተስፋ ፖለቲካ ወጥታ የመንግሥት ቅቡልነት በሚያወራው ሳይሆን በተግባር በሚሠራው ሥራ እና በሚያመጣው ተጨባጭ ውጤት ወደሚሆንበት አዲስ አሠራር እየተሸጋገረች ነው።
ይህ አሠራር በሚመጡ ተጨባጭ ለውጦች ለመለካት የሚሻ አዲስ የሀገር ግንባታ ማዕቀፍ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ኢትዮጵያ ታከናውናለች" በሚለው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በአጽንዖት እንደገለጹት፣ የሀገራችን አዲሱ የታሪክ ምዕራፍ በተስፋ ቃላት ላይ ሳይሆን በተግባራዊ ክንውን እና በጥራት ላይ የተመሠረተ ነው።
ይህ "ኢትዮጵያ ታከናውናለች" የሚለው መርሕ ከተራ መፈክር በላይ በመሆን፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ያላትን የማስፈጸም አቅም እና የሥልጣኔ ልክ የምታሳይበት ዋነኛ መሣሪያ ሆኗል።
በአሁኑ ወቅት በሀገራችን እየታዩ ያሉ ስኬቶች መንግሥት ውጤት የማምጣት አቅሙን በተግባር ያረጋገጠባቸው ማሳያዎች ናቸው።
ከታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታን ከማጠናቀቅ እና ኃይል ማመንጨት ጀምሮ፣ በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው የስንዴ ኤክስፖርት እና የመስኖ ልማት ስኬት፣ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች፣ እንዲሁም የአዲስ አበባ እና የክልል ከተሞችን ገጽታ የቀየሩት የኮሪደር ልማት ሥራዎች የዚሁ ተግባራዊ ሕጋዊነት ውጤቶች ናቸው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እና የኢትዮጵያ ታምርት የኢንዱስትሪ ንቅናቄም ሀገራችን ትላልቅ ዕቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም እንዳላት በተጨባጭ እያሳዩ ነው።
ዋናው ማዕቀፍ ግን የእነዚህ ፕሮጀክቶች መፈጸም ብቻ ሳይሆን፣ ጥቅሞቻቸው በሁሉም ክልሎች፣ ማንነቶች እና የፖለቲካ አመለካከቶች ውስጥ እኩል ሊሰርጹ መቻላቸው ላይ ነው። መንገዶች፣ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እና ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ልማታዊ ውጤቶች ብቻ ሳይሆኑ፣ የፌዴራል ሥርዓቱን ልዩነቶች አቀናጅተው የጋራ ብሔራዊ ልምድን የሚፈጥሩ ሥልታዊ ድልድዮች ናቸው።
ይህ አካሄድ ቀደም ሲል ከነበረው እና ሥልጣኑን በረጅም ጊዜ ተስፋዎች ላይ ብቻ ይመሠርት ከነበረው "ልማታዊ መንግሥት" አስተሳሰብ በእጅጉ የላቀ ነው።
የአሁኑ የመፈጸም ሞዴል ሊለኩ በሚችሉ ውጤቶች፣ በትግበራ ፍጥነት እና በተቋማዊ ብቃት ላይ የተመሠረተ ነው። የሲንጋፖር፣ የቪየትናም እና የማሌዢያ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት፣ ዘላቂ ማኅበራዊ ውል የሚገነባው እና ቢሮክራሲው የሚቀናጀው በተግባር በሚታይ የድህነት ቅነሳ እና የዜጎች የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻል ላይ ነው።
መንግሥት ለኢኮኖሚ ችግሮች የሚሰጠው መፍትሔ በርዕዮተ ዓለም የታጠረ ሳይሆን፣ በተግባር በሚታይ ውጤት ላይ የተመሠረተ ገቢር ነበብ የኢኮኖሚ ፍልስፍና ነው።
ከለውጡ በፊት ኢኮኖሚው በከፍተኛ ዕዳ ተሸብቦ እና በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ተፈትኖ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ይህን የውድቀት ታሪክ መቀየር ተችሏል።
"ለረጅም ጊዜ ኢትዮጵያ በችግሮቿ እንጂ በእምቅ አቅሟ ስትገለጽ አልኖረችም፤ ዛሬ ግን የተለየ ታሪክ ብቅ እያለ ነው" ሲሉ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገራችንን አዲስ ምዕራፍ ያበሰሩት።
ይህ “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” የሚለው መንፈስ በቴክኖሎጂ እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽኑ መስክም በጉልህ እየታየ ይገኛል። በ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ አማካኝነት የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ማቅረብ፣ የ“መሶብ” የአንድ ማዕከል የአገልግሎት መተግበሪያን መዘርጋት እና የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ሥልጠና ንቅናቄን መተግበር ኢትዮጵያን ወደ ዘመናዊ እና ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት እያሸጋገሯት ነው።
እነዚህ የዲጂታል መሠረቶች የቢሮክራሲውን ቅልጥፍና ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ከመንግሥት ጋር ያላቸውን ግንኙነት ፍጹም ዘመናዊ እና ግልጽ ያደርጉታል።
ይህ የተግባር ስኬት እና የማስፈጸም አቅም በሀገር ውስጥ ብቻ የተገደበ ሳይሆን በቀጣናዊ ዲፕሎማሲ እና በጂኦ-ፖለቲካ አቋማችን ላይም ትልቅ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር አካባቢ ያላትን የባሕር በር የማግኘት ሕጋዊ መብት ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት፣ በአፍሪካ ቀንድ ያላት የሰላም እና የፀጥታ ሚና እንዲሁም የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ አጋርነቶቿን የማጠናከር ሥራ የዲፕሎማሲያዊ ቁመቷን በእጅጉ እያሳደገው ይገኛል።
የሀገር ውስጥ የልማት አቅም ሲጎለብት የውጭ ዲፕሎማሲያዊ ተሰሚነትም አብሮ እንደሚገነባ ይህ አካሄድ ሕያው ማሳያ ነው።
"ኢትዮጵያ ታከናውናለች" የሚለው ይፋዊ እውነት በተግባር እየተረጋገጠ በሄደ ቁጥር፣ ልማት ለብሔራዊ ትሥሥር እንደ ትሥሥር ገመድ ማገልገሉን ይቀጥላል። ይሄ የአፈጻጸም ሥልጣኔ ከተራ ፍልስፍና በላይ በመሆን አዲሲቷን ኢትዮጵያ በጠንካራ ዐለት ላይ የሚገነባ ተግባራዊ መሠረት ሆኖ ሊጸና ይገባል።
ኢትዮጵያ ታከናውናለች፤ በሕዝቦቿ ጥረት፣ በጠንካራ ሀገራዊ ተቋማት ግንባታ እና በዲጂታል ዘመን በሚፈጠሩ አዳዲስ ዕድሎች በመታገዝ የተሻለ እና ብሩህ ነገን ትቀርጻለች።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #ebcdotstream #nationalinterest
1 month ago
የቢሮክራሲውን ማነቆዎች የሚገታው የኢትዮጵያ ዲጂታላይዜሽን
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ባልተቀላጠፈበት እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በሌለበት ስለ ተገልጋይ እርካታ ማውራት ከንቱ ድካም ነው።
በሀገራችን ለረጅም ዘመናት የቆየው እና የዜጎችን እንግልት ሲያበዛ የኖረው “ዛሬ ሂድ፤ ነገ ና” የሚለው አሰልቺ ቢሮክራሲ፣ የሕዝብን ሮሮ ከመጨመሩ ባለፈ የሙስና አዙሪት መፈልፈያ ሆኖ መቆየቱ የአደባባይ ምስጢር ነው።
ይህንን ሥር የሰደደ ማነቆ ለመፍታት ቴክኖሎጂን እንደ ዋና መፍትሔ መውሰድ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ሆኗል።
ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ እና ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም የመንግሥትን ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት በመጠቀም፣ ቴክኖሎጂውን ለሕዝብ ተጠቃሚነት እና ለኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት እያዋለችው ትገኛለች።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በዘርፉ የተመዘገቡት ስኬቶች የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙን ከማሳካት ባለፈ፣ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት የሚያቀልሉ፣ ጊዜን እና ገንዘብን የሚቆጥቡ ትልልቅ ተስፋዎችን አብስረዋል።
ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተቀረጸው እና በይፋ ሥራ የጀመረው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተንቀሳቃሽ አውቶቡስ ስምሪት አንዱ ነው።
ይህ በአፍሪካ ፈር ቀዳጅ የሆነ አሠራር የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማግኘት በየቢሮው እና በየደረጃው በሚገጥሙ የቢሮክራሲ ሰንሰለቶች የመጉላላት እና በፀሐይም በዝናብም የመንከራተትን ዘመን በዘላቂነት የሚቀይር አዲስ ምዕራፍ ነው።
በልዩ ሁኔታ በተዘጋጁ ንጹሕ ኢነርጂ በሚጠቀሙ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ የተመሠረተው ይህ አገልግሎት፤ የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN)፣ የንግድ ፈቃድ፣ የመንጃ ፈቃድ፣ የተሽከርካሪ ታርጋ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ዕድሳት፣ የልደት ምዝገባ እንዲሁም የመንገድ ፈንድ እና የኤሌክትሪክ ቅድመ-ክፍያ አገልግሎቶችን ጨምሮ ስምንት ዋና ዋና የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣራ ሥር ይዞ ወደ ማኅበረሰቡ ደጃፍ መጥቷል።
የዚህ የዲጂታላይዜሽን ስኬት ትልቁ ፋይዳ የአገልግሎት አሰጣጥን ከማቀላጠፍ ባለፈ ሙስናንና የአሠራር ብልሹነትን በተጨባጭ መግታቱ ላይ ነው።
ተንቀሳቃሽ አውቶቡሶቹ ከዋና ዋና የፌዴራል ተቋማት የመረጃ ማዕከላት ጋር በቀጥታ የተገናኙ መሆናቸው፣ በውስጣቸውም ዲጂታል የሰዎች ወረፋ ማስተናገጃ፣ የክትትል ካሜራዎች እና የተለዋዋጭ ዲጂታል ክፍያ አማራጮች መካተታቸው አሠራሩን ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት ያደርገዋል።
ይህ ዓይነቱ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አዲስ ስምሪት በመንግሥት አገልግሎት ላይ የሚታየውን አሰልቺ ቢሮክራሲ በመቀነስ፣ ሕገ ወጥ ደላሎችን እና ብልሹ አሠራሮችን ከአምራቹ ማኅበረሰብ ትከሻ ላይ ያወርዳል። የአገልግሎት አሰጣጥ ሲፋጠን የሚቆጠበው ጊዜ እና ጉልበት ደግሞ በቀጥታ ወደ ምርታማነትና ወደ ሀገር ሀብት ይቀየራል።
ይሁን እንጂ ይህ የተጀመረው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ ውጤታማና ዘላቂ እንዲሆን የዜጎች እና የሚመለከታቸው አካላት ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው።
የቆየውን ተቋማዊ እና ግለሰባዊ ልምምድ ቀይሮ በፈገግታና በታማኝነት ማገልገል ቀላል ባይሆንም፣ ቴክኖሎጂው ግን ይህንን የሥራ ባህል ለውጥ እያፋጠነው ይገኛል። በመሆኑም ዜጎች እነዚህን ዘመናዊና ምቹ አገልግሎቶች በባለቤትነት ስሜት በመጠቀም፣ የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት በመሆን ጊዜያቸውንና ገንዘባቸውን ሊቆጥቡ ይገባል።
በሌላ በኩል፣ የአመራር አካላት እና የሚመለከታቸው ተቋማት ይህ አመርቂ ጅምር ይበልጥ እንዲስፋፋ፣ መሠረተ ልማቱ እንዲጠናከር እና ኢትዮጵያውያን ባሉበት ስፍራ ሆነው በሞባይላቸው ሙሉ አገልግሎት የሚያገኙበት ደረጃ ላይ እስኪደርስ በትጋት ሊሠሩ ይገባል።
ቴክኖሎጂ የሀገር ብልጽግና ምሰሶ ከመሆኑም በላይ የዜጎችን ክብር የሚመልስ መሣሪያ በመሆኑ፣ የአገልግሎት ማነቆዎችን የመስበር ይህ አመርቂ ጅምር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #mesob #digitalization
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ባልተቀላጠፈበት እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በሌለበት ስለ ተገልጋይ እርካታ ማውራት ከንቱ ድካም ነው።
በሀገራችን ለረጅም ዘመናት የቆየው እና የዜጎችን እንግልት ሲያበዛ የኖረው “ዛሬ ሂድ፤ ነገ ና” የሚለው አሰልቺ ቢሮክራሲ፣ የሕዝብን ሮሮ ከመጨመሩ ባለፈ የሙስና አዙሪት መፈልፈያ ሆኖ መቆየቱ የአደባባይ ምስጢር ነው።
ይህንን ሥር የሰደደ ማነቆ ለመፍታት ቴክኖሎጂን እንደ ዋና መፍትሔ መውሰድ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ሆኗል።
ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ እና ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም የመንግሥትን ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት በመጠቀም፣ ቴክኖሎጂውን ለሕዝብ ተጠቃሚነት እና ለኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት እያዋለችው ትገኛለች።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በዘርፉ የተመዘገቡት ስኬቶች የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙን ከማሳካት ባለፈ፣ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት የሚያቀልሉ፣ ጊዜን እና ገንዘብን የሚቆጥቡ ትልልቅ ተስፋዎችን አብስረዋል።
ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተቀረጸው እና በይፋ ሥራ የጀመረው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተንቀሳቃሽ አውቶቡስ ስምሪት አንዱ ነው።
ይህ በአፍሪካ ፈር ቀዳጅ የሆነ አሠራር የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማግኘት በየቢሮው እና በየደረጃው በሚገጥሙ የቢሮክራሲ ሰንሰለቶች የመጉላላት እና በፀሐይም በዝናብም የመንከራተትን ዘመን በዘላቂነት የሚቀይር አዲስ ምዕራፍ ነው።
በልዩ ሁኔታ በተዘጋጁ ንጹሕ ኢነርጂ በሚጠቀሙ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ የተመሠረተው ይህ አገልግሎት፤ የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN)፣ የንግድ ፈቃድ፣ የመንጃ ፈቃድ፣ የተሽከርካሪ ታርጋ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ዕድሳት፣ የልደት ምዝገባ እንዲሁም የመንገድ ፈንድ እና የኤሌክትሪክ ቅድመ-ክፍያ አገልግሎቶችን ጨምሮ ስምንት ዋና ዋና የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣራ ሥር ይዞ ወደ ማኅበረሰቡ ደጃፍ መጥቷል።
የዚህ የዲጂታላይዜሽን ስኬት ትልቁ ፋይዳ የአገልግሎት አሰጣጥን ከማቀላጠፍ ባለፈ ሙስናንና የአሠራር ብልሹነትን በተጨባጭ መግታቱ ላይ ነው።
ተንቀሳቃሽ አውቶቡሶቹ ከዋና ዋና የፌዴራል ተቋማት የመረጃ ማዕከላት ጋር በቀጥታ የተገናኙ መሆናቸው፣ በውስጣቸውም ዲጂታል የሰዎች ወረፋ ማስተናገጃ፣ የክትትል ካሜራዎች እና የተለዋዋጭ ዲጂታል ክፍያ አማራጮች መካተታቸው አሠራሩን ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት ያደርገዋል።
ይህ ዓይነቱ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አዲስ ስምሪት በመንግሥት አገልግሎት ላይ የሚታየውን አሰልቺ ቢሮክራሲ በመቀነስ፣ ሕገ ወጥ ደላሎችን እና ብልሹ አሠራሮችን ከአምራቹ ማኅበረሰብ ትከሻ ላይ ያወርዳል። የአገልግሎት አሰጣጥ ሲፋጠን የሚቆጠበው ጊዜ እና ጉልበት ደግሞ በቀጥታ ወደ ምርታማነትና ወደ ሀገር ሀብት ይቀየራል።
ይሁን እንጂ ይህ የተጀመረው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ ውጤታማና ዘላቂ እንዲሆን የዜጎች እና የሚመለከታቸው አካላት ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው።
የቆየውን ተቋማዊ እና ግለሰባዊ ልምምድ ቀይሮ በፈገግታና በታማኝነት ማገልገል ቀላል ባይሆንም፣ ቴክኖሎጂው ግን ይህንን የሥራ ባህል ለውጥ እያፋጠነው ይገኛል። በመሆኑም ዜጎች እነዚህን ዘመናዊና ምቹ አገልግሎቶች በባለቤትነት ስሜት በመጠቀም፣ የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት በመሆን ጊዜያቸውንና ገንዘባቸውን ሊቆጥቡ ይገባል።
በሌላ በኩል፣ የአመራር አካላት እና የሚመለከታቸው ተቋማት ይህ አመርቂ ጅምር ይበልጥ እንዲስፋፋ፣ መሠረተ ልማቱ እንዲጠናከር እና ኢትዮጵያውያን ባሉበት ስፍራ ሆነው በሞባይላቸው ሙሉ አገልግሎት የሚያገኙበት ደረጃ ላይ እስኪደርስ በትጋት ሊሠሩ ይገባል።
ቴክኖሎጂ የሀገር ብልጽግና ምሰሶ ከመሆኑም በላይ የዜጎችን ክብር የሚመልስ መሣሪያ በመሆኑ፣ የአገልግሎት ማነቆዎችን የመስበር ይህ አመርቂ ጅምር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #mesob #digitalization
2 months ago
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ሁለት አዳዲስ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶችን ስራ አስጀመሩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለአዲስ አበባ 10ኛ እና 11ኛ የሆኑ ሁለት የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶችን በይፋ መርቀው ስራ አስጀምረዋል።
ከንቲባዋ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፥ በ2018 በተገባው ቃል መሰረት በአዲስ አበባ 11 የአዲስ መሶብ ማዕከላትን መክፈት ችለናል ብለዋል።
ማዕከላቱ በቃሊቲ እና በለሚ ኩራ ክፍለከተሞች መገንባታቸውን ጠቅሰው፤ የማዕከላቱ ወደስራ መግባት የተገልጋዮችን እንግልት በመግታት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችል አብራርተዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶት የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን ማዘመን የተቻለበት መሆኑን ተናግረዋል።
የመሶብ ማዕከላቱ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደራጁ በመሆናቸው ማንኛውም የከተማዋ ነዋሪ በፈለገው ማዕከል አገልግሎት ማግኘት ይችላል ያሉት ከንቲባዋ፤ ዲጂታል ቴክኖሎጂዎቹ በሀገር ውስጥ አቅም የበለጸጉ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ማዕከላቱ ከ50 በመቶ በላይ የመንግሥት አገልግሎቶችን የሚሰጡና ለእናቶችና ህፃናት የተመቸ የመጫወቻ ስፍራም እንዳካተቱ ገልጸዋል።
መሠል ዘርፎችን ማልማት የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ እንደሚያጠናክሩ ገልጸው፤ ህዝብና መንግሥት ይበልጥ በተቀናጁ ቁጥር ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚያስችል አመልክተዋል።
በሔኖክ ለሜ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለአዲስ አበባ 10ኛ እና 11ኛ የሆኑ ሁለት የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶችን በይፋ መርቀው ስራ አስጀምረዋል።
ከንቲባዋ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፥ በ2018 በተገባው ቃል መሰረት በአዲስ አበባ 11 የአዲስ መሶብ ማዕከላትን መክፈት ችለናል ብለዋል።
ማዕከላቱ በቃሊቲ እና በለሚ ኩራ ክፍለከተሞች መገንባታቸውን ጠቅሰው፤ የማዕከላቱ ወደስራ መግባት የተገልጋዮችን እንግልት በመግታት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችል አብራርተዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶት የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን ማዘመን የተቻለበት መሆኑን ተናግረዋል።
የመሶብ ማዕከላቱ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደራጁ በመሆናቸው ማንኛውም የከተማዋ ነዋሪ በፈለገው ማዕከል አገልግሎት ማግኘት ይችላል ያሉት ከንቲባዋ፤ ዲጂታል ቴክኖሎጂዎቹ በሀገር ውስጥ አቅም የበለጸጉ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ማዕከላቱ ከ50 በመቶ በላይ የመንግሥት አገልግሎቶችን የሚሰጡና ለእናቶችና ህፃናት የተመቸ የመጫወቻ ስፍራም እንዳካተቱ ገልጸዋል።
መሠል ዘርፎችን ማልማት የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ እንደሚያጠናክሩ ገልጸው፤ ህዝብና መንግሥት ይበልጥ በተቀናጁ ቁጥር ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚያስችል አመልክተዋል።
በሔኖክ ለሜ
2 months ago
ከቴክኖሎጂ ጥገኝነት ወደ ቴክኖሎጂ አመንጪነት
***************
ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ የነበራትን የጥገኝነት ምዕራፍ በታሪክ ሰነድነት በማስቀመጥ በአፍሪካ ደረጃ አዲስ የፈጠራ ምዕራፍ ከፍታለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የተጀመረው ‘ዲጂታል ለልህቀት’ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ወደ ቴክኖሎጂ አመንጪነት መሸጋገሯን በተግባር ያረጋገጠ እና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በዘላቂነት ለማምረት የተዘረጋው የስትራቴጂያዊ ማዕቀፍ መገለጫ ነው።
በጉባኤው በይፋ የተመረቀው በአፍሪካ ቀዳሚው የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ የተለያዩ ተቋማትን አገልግሎት በአንድ መድረክ በማምጣት የቢሮክራሲ ሂደትን የሚያቀል ነው።
ይህን መተግበሪያ ጨምሮ እንደ መሶብ ያሉ በሀገር በቀል ዕውቀት የተደራጁ ዲጂታል መድረኮች፣ የዜጎችን የዕለት ተለት ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ እንቅስቃሴዎች በዘመናዊ መረብ የሚያስተሳስሩ የፈጠራ ውጤቶች ናቸው።
በዚህ መልኩ አገልግሎቶችን በዲጂታል መንገድ ማቅረብ የዜጎችን ጊዜ፣ ጉልበት እና ወጪ በመቆጠብ የሀገርን ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል።
ቴክኖሎጂ ለልማት ሥራዎች ሲውል፣ ለሀገር ውስጥ አቅም ግንባታ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። አገልግሎቶች በአንድ መድረክ ሲሰባሰቡ ለምርታማነት ዕድገት፣ ለፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል እና ለዘመናዊ የንግድ አሠራር መሠረት ይጥላሉ።
የዲጂታል ሽግግር አሠራሮችን ግልጽ እና ቀልጣፋ በማድረግ በዘመናዊው ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን የሚደረገውን ጥረት ያፋጥነዋል።
አዲሱ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ ለነገው ዲጂታል ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት በመሆን ዲጂታል የንግድ ልውውጥን ከማዘመን፣ መሠረታዊ አገልግሎት እስከ መስጠት ባለው ሰንሰለት ውስጥ የሚጫወተው ሚና የላቀ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #digitaltransformation #digitalexcellence #techdevelopment #digitalservices #ebc
***************
ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ የነበራትን የጥገኝነት ምዕራፍ በታሪክ ሰነድነት በማስቀመጥ በአፍሪካ ደረጃ አዲስ የፈጠራ ምዕራፍ ከፍታለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የተጀመረው ‘ዲጂታል ለልህቀት’ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ወደ ቴክኖሎጂ አመንጪነት መሸጋገሯን በተግባር ያረጋገጠ እና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በዘላቂነት ለማምረት የተዘረጋው የስትራቴጂያዊ ማዕቀፍ መገለጫ ነው።
በጉባኤው በይፋ የተመረቀው በአፍሪካ ቀዳሚው የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ የተለያዩ ተቋማትን አገልግሎት በአንድ መድረክ በማምጣት የቢሮክራሲ ሂደትን የሚያቀል ነው።
ይህን መተግበሪያ ጨምሮ እንደ መሶብ ያሉ በሀገር በቀል ዕውቀት የተደራጁ ዲጂታል መድረኮች፣ የዜጎችን የዕለት ተለት ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ እንቅስቃሴዎች በዘመናዊ መረብ የሚያስተሳስሩ የፈጠራ ውጤቶች ናቸው።
በዚህ መልኩ አገልግሎቶችን በዲጂታል መንገድ ማቅረብ የዜጎችን ጊዜ፣ ጉልበት እና ወጪ በመቆጠብ የሀገርን ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል።
ቴክኖሎጂ ለልማት ሥራዎች ሲውል፣ ለሀገር ውስጥ አቅም ግንባታ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። አገልግሎቶች በአንድ መድረክ ሲሰባሰቡ ለምርታማነት ዕድገት፣ ለፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል እና ለዘመናዊ የንግድ አሠራር መሠረት ይጥላሉ።
የዲጂታል ሽግግር አሠራሮችን ግልጽ እና ቀልጣፋ በማድረግ በዘመናዊው ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን የሚደረገውን ጥረት ያፋጥነዋል።
አዲሱ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ ለነገው ዲጂታል ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት በመሆን ዲጂታል የንግድ ልውውጥን ከማዘመን፣ መሠረታዊ አገልግሎት እስከ መስጠት ባለው ሰንሰለት ውስጥ የሚጫወተው ሚና የላቀ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #digitaltransformation #digitalexcellence #techdevelopment #digitalservices #ebc
2 months ago
ከተመሠረተ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ፣ መሶብ የኢትዮጵያን የሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት መሠረታዊ በሆነ መንገድ ለውጦታል።
ውጤቶቹም በራሳቸው ይናገራሉ።
#pmoethiopia
ውጤቶቹም በራሳቸው ይናገራሉ።
#pmoethiopia
Sponsored by
Surafel
2 months ago
መሶብ ለአገልጋይነታችን፡ የዲጂታል ትጋትና የሕዝብ አደራ
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ቴክኖሎጂ የአንድን ሀገር የኢኮኖሚ መሠረተ ልማት የሚያጠናክርና የዜጎችን ሕይወት በብዙ መንገድ የሚቀይር እውነተኛ የለውጥ ሞተር ነው።
በተለይም የመንግሥት አገልግሎቶችን በማቀላጠፍ ለዜጎች የሚሰጠውን ክብር፣ የጊዜና የገንዘብ ትርፍ ስንመለከት እንዲሁም በተቋማት መካከል የሚፈጥረውን ቅንጅት ስናስተውል ሀገራችን በለውጥና በዕድገት ጎዳና ላይ መሆኗን በግልጽ ያሳያል።
ይሁንናይህ አስደማሚ ጅማሮና በዲጂታል ዘርፉ የተመዘገቡት ድሎች የዜጎችን እርካታ ጫፍ ላይ አድርሰዋል ማለት አይደለም ገና ብዙ የሚቀሩና ትኩረት የሚሹ የቤት ሥራዎች እንዳሉብን መዘንጋት የለብንም።
በባህላችን «መሶብ» የጥጋብ፣ የአንድነት መገለጫ ነው።በዚህ እሳቤ የተገነባው የ«መሶብ» መተግበሪያም የሀገርን በረከትና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለሕዝብ ለማቅረብ ያለመ የቴክኖሎጂ ውጤት ነው።
መሶቡ የበረከት ምንጭ እንዲሆንና አገልግሎቱ ሙሉዕነት እንዲኖረው ከተፈለገ፣ በውስጡ የሚቀመጠው «እንጀራ» ማለትም የአሠራር ሥርዓቱና አስፈጻሚው አገልጋይ—ከሌብነት፣ ከሙስናና ከእጅ መንሻ የጠራ መሆን አለበት።
እጅግ ዘመናዊና የተራቀቀ ቴክኖሎጂ በየተቋማቱ ቢዘረጋም፣ በአገልጋዩ ዘንድ ያለው የቆየ ልማድ፣ የሌብነት አስተሳሰብና የአገልግሎት መስተጓጎል ካልተወገደ የቴክኖሎጂው ፋይዳ ለዜጎች ትርጉም አልባ ሆኖ ይቀራል።
በመሆኑም በመሶብ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩትን እጅ መንሻዎችና ሕገ-ወጥ አሠራሮች ሙሉ በሙሉ ማስወገድ የነገ የማይባል ቀዳሚ ተግባራችን ነው።
ቴክኖሎጂ ጊዜንና ገንዘብን ከመቆጠብ ባለፈ፣ ዜጎች በቢሮክራሲ ብስጭትና በጭንቀት የሚሸከሙትን አሉታዊ ኃይል አስወግዶ ደስተኛ ማኅበረሰብ የመፍጠር ትልቅ አቅም አለው።
ይህንን አቅም ወደ መሬት ማውረድ የሚቻለው ደግሞ እያንዳንዱ አገልጋይና የመንግሥት ተቋም የኃላፊነት ስሜቱን በተግባር ሲያሳይ ነው። የዚህ ሁሉ ጥረትና ስኬት ማዕከል ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው።
ባለፈው ምርጫ ሕዝባችን ከሌሊት እስከ ሌሊት በሰላማዊ መንገድ ተሰልፎ ስለ ሀገሩ ያለውን ፍቅር፣ ለተቋማዊ ዕድገትና ለመበልጸግ ያለውን ጉጉት በተግባር አሳይቷል።
ይህንን ታላቅ እምነትና አደራ በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት መወጣት ግድ ይላል። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በግልጽ እንዳሳሰቡት "የኢትዮጵያ ሕዝብ ስላከበረን አብዝተን ልናከብረው፣ ስላከበረን አብዝተን ልናገለግለው፣ ባከበረን ልክ ታምነን ልንገኝ ይገባል።"
«ያበደረ መልሶ ያገኛል፣ የዘራ ያጭዳል» እንደሚባለው የሕዝቡን ክብርና አመኔታ መመለስ የሚቻለው በታማኝነትና በቅንነት በማገልገል ብቻ ነው።
እስካሁን የተመዘገበው ስኬት ከዜጎችን ሰፊ ፍላጎት አንድ በመቶ (1%) ያህል ብቻ በመሆኑ፣ በቀሪው ሰፊ መንገድ ላይ በፍጥነት ለመራመድ በተሻለ ቁመና መገኘት፣ ራስን ከብልሹ አሠራር ማጥራትና በበለጠ ትጋት መረባረብ ያስፈልጋል።
መላው የሥራ ኃላፊዎችና በየተቋማቱ የምትገኙ አገልጋዮች በመደመርና በአንድነት በመቆም፣ የዜጎችን እሮሮ ማክሰምና የሀገራችንን ብልጽግና በጽኑ መሠረት ላይ መገንባት ይጠበቅባችኋል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #mesob #ethiopia #መሶብ
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ቴክኖሎጂ የአንድን ሀገር የኢኮኖሚ መሠረተ ልማት የሚያጠናክርና የዜጎችን ሕይወት በብዙ መንገድ የሚቀይር እውነተኛ የለውጥ ሞተር ነው።
በተለይም የመንግሥት አገልግሎቶችን በማቀላጠፍ ለዜጎች የሚሰጠውን ክብር፣ የጊዜና የገንዘብ ትርፍ ስንመለከት እንዲሁም በተቋማት መካከል የሚፈጥረውን ቅንጅት ስናስተውል ሀገራችን በለውጥና በዕድገት ጎዳና ላይ መሆኗን በግልጽ ያሳያል።
ይሁንናይህ አስደማሚ ጅማሮና በዲጂታል ዘርፉ የተመዘገቡት ድሎች የዜጎችን እርካታ ጫፍ ላይ አድርሰዋል ማለት አይደለም ገና ብዙ የሚቀሩና ትኩረት የሚሹ የቤት ሥራዎች እንዳሉብን መዘንጋት የለብንም።
በባህላችን «መሶብ» የጥጋብ፣ የአንድነት መገለጫ ነው።በዚህ እሳቤ የተገነባው የ«መሶብ» መተግበሪያም የሀገርን በረከትና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለሕዝብ ለማቅረብ ያለመ የቴክኖሎጂ ውጤት ነው።
መሶቡ የበረከት ምንጭ እንዲሆንና አገልግሎቱ ሙሉዕነት እንዲኖረው ከተፈለገ፣ በውስጡ የሚቀመጠው «እንጀራ» ማለትም የአሠራር ሥርዓቱና አስፈጻሚው አገልጋይ—ከሌብነት፣ ከሙስናና ከእጅ መንሻ የጠራ መሆን አለበት።
እጅግ ዘመናዊና የተራቀቀ ቴክኖሎጂ በየተቋማቱ ቢዘረጋም፣ በአገልጋዩ ዘንድ ያለው የቆየ ልማድ፣ የሌብነት አስተሳሰብና የአገልግሎት መስተጓጎል ካልተወገደ የቴክኖሎጂው ፋይዳ ለዜጎች ትርጉም አልባ ሆኖ ይቀራል።
በመሆኑም በመሶብ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩትን እጅ መንሻዎችና ሕገ-ወጥ አሠራሮች ሙሉ በሙሉ ማስወገድ የነገ የማይባል ቀዳሚ ተግባራችን ነው።
ቴክኖሎጂ ጊዜንና ገንዘብን ከመቆጠብ ባለፈ፣ ዜጎች በቢሮክራሲ ብስጭትና በጭንቀት የሚሸከሙትን አሉታዊ ኃይል አስወግዶ ደስተኛ ማኅበረሰብ የመፍጠር ትልቅ አቅም አለው።
ይህንን አቅም ወደ መሬት ማውረድ የሚቻለው ደግሞ እያንዳንዱ አገልጋይና የመንግሥት ተቋም የኃላፊነት ስሜቱን በተግባር ሲያሳይ ነው። የዚህ ሁሉ ጥረትና ስኬት ማዕከል ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው።
ባለፈው ምርጫ ሕዝባችን ከሌሊት እስከ ሌሊት በሰላማዊ መንገድ ተሰልፎ ስለ ሀገሩ ያለውን ፍቅር፣ ለተቋማዊ ዕድገትና ለመበልጸግ ያለውን ጉጉት በተግባር አሳይቷል።
ይህንን ታላቅ እምነትና አደራ በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት መወጣት ግድ ይላል። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በግልጽ እንዳሳሰቡት "የኢትዮጵያ ሕዝብ ስላከበረን አብዝተን ልናከብረው፣ ስላከበረን አብዝተን ልናገለግለው፣ ባከበረን ልክ ታምነን ልንገኝ ይገባል።"
«ያበደረ መልሶ ያገኛል፣ የዘራ ያጭዳል» እንደሚባለው የሕዝቡን ክብርና አመኔታ መመለስ የሚቻለው በታማኝነትና በቅንነት በማገልገል ብቻ ነው።
እስካሁን የተመዘገበው ስኬት ከዜጎችን ሰፊ ፍላጎት አንድ በመቶ (1%) ያህል ብቻ በመሆኑ፣ በቀሪው ሰፊ መንገድ ላይ በፍጥነት ለመራመድ በተሻለ ቁመና መገኘት፣ ራስን ከብልሹ አሠራር ማጥራትና በበለጠ ትጋት መረባረብ ያስፈልጋል።
መላው የሥራ ኃላፊዎችና በየተቋማቱ የምትገኙ አገልጋዮች በመደመርና በአንድነት በመቆም፣ የዜጎችን እሮሮ ማክሰምና የሀገራችንን ብልጽግና በጽኑ መሠረት ላይ መገንባት ይጠበቅባችኋል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #mesob #ethiopia #መሶብ
2 months ago
የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያው የተዋሃደ አቀራረብን በመከተል በአፍሪካ ቀዳሚ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዛሬው ዕለት ሥራ የጀመረው የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ የተዋሃደ አቀራረብን በመከተል በአፍሪካ የመጀመሪያው ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ኢትዮጵያ በመሶብ አገልግሎት አማካኝነት ዜጎች በርካታ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያገኙበት የተቀናጀ ሥርዓት በመገንባት በአህጉሪቱ ተጠቃሽ የሆነ የቴክኖሎጂ ሽግግር እያስመዘገበች ነው።
በብዙ የአፍሪካ ሀገራት የዲጂታል አገልግሎት ሽግግር አሁንም በጥቂት ዘርፎች ወይም በተናጠል ተቋማት ብቻ የተወሰነ መሆኑን ገልጸው÷ እንደ መሶብ ያሉ በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ የተዋሃደ ሥርዓት በስፋት የሚያቀርብ ሞዴል በአህጉሪቱ ገና ያልተለመደ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ጉዞ ከአንድ ተነስቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ 70 ቅርንጫፎች ማደጉ ልዩ ውጤት ነው፤ ይህ ስኬት በርካታ ሀገራት ካስመዘገቡት በላይ መሆኑንም አመልክተዋል።
የቴክኖሎጂ ሽግግሩን ለማጠናከር አገልግሎቱን ከቋሚ ማዕከላት ወደ ተንቀሳቃሽ እና የሞባይል መድረኮች የማሸጋገር ሥራ መጀመሩን እና ይህም ዜጎች ለአገልግሎት ወደ ተለያዩ ማዕከላት ከመመላለስ ይልቅ ከየቤታቸው ሆነው በስልካቸው እንዲገለገሉ የሚያስችል ምቹ አቅጣጫ መሆኑን አስረድተዋል።
የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ለማቀላጠፍ ወደ አውቶቡስ መሶብ አገልግሎት መሸጋገሩን እና በዚህም ሶስት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በጋዝ እና ኤሌክትሪክ ኃይል የሚንቅሳቀሱ አውቶቡሶችን በመሶብ ሥርዓት ውስጥ ማካተት መቻሉን አንስተዋል።
በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያጣምረው የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያም በሁሉም መስክ የተዋሃደ አቀራረብን በመከተል በአፍሪካ ቀዳሚው መሆኑን ነው ነው ያስረዱት፡፡
ይህ ሒደት የዲጂታል መንግሥት ግንባታን ወደ ቀጣይ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዐቢይ (ዶ/ር) አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዛሬው ዕለት ሥራ የጀመረው የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ የተዋሃደ አቀራረብን በመከተል በአፍሪካ የመጀመሪያው ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ኢትዮጵያ በመሶብ አገልግሎት አማካኝነት ዜጎች በርካታ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያገኙበት የተቀናጀ ሥርዓት በመገንባት በአህጉሪቱ ተጠቃሽ የሆነ የቴክኖሎጂ ሽግግር እያስመዘገበች ነው።
በብዙ የአፍሪካ ሀገራት የዲጂታል አገልግሎት ሽግግር አሁንም በጥቂት ዘርፎች ወይም በተናጠል ተቋማት ብቻ የተወሰነ መሆኑን ገልጸው÷ እንደ መሶብ ያሉ በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ የተዋሃደ ሥርዓት በስፋት የሚያቀርብ ሞዴል በአህጉሪቱ ገና ያልተለመደ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ጉዞ ከአንድ ተነስቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ 70 ቅርንጫፎች ማደጉ ልዩ ውጤት ነው፤ ይህ ስኬት በርካታ ሀገራት ካስመዘገቡት በላይ መሆኑንም አመልክተዋል።
የቴክኖሎጂ ሽግግሩን ለማጠናከር አገልግሎቱን ከቋሚ ማዕከላት ወደ ተንቀሳቃሽ እና የሞባይል መድረኮች የማሸጋገር ሥራ መጀመሩን እና ይህም ዜጎች ለአገልግሎት ወደ ተለያዩ ማዕከላት ከመመላለስ ይልቅ ከየቤታቸው ሆነው በስልካቸው እንዲገለገሉ የሚያስችል ምቹ አቅጣጫ መሆኑን አስረድተዋል።
የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ለማቀላጠፍ ወደ አውቶቡስ መሶብ አገልግሎት መሸጋገሩን እና በዚህም ሶስት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በጋዝ እና ኤሌክትሪክ ኃይል የሚንቅሳቀሱ አውቶቡሶችን በመሶብ ሥርዓት ውስጥ ማካተት መቻሉን አንስተዋል።
በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያጣምረው የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያም በሁሉም መስክ የተዋሃደ አቀራረብን በመከተል በአፍሪካ ቀዳሚው መሆኑን ነው ነው ያስረዱት፡፡
ይህ ሒደት የዲጂታል መንግሥት ግንባታን ወደ ቀጣይ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዐቢይ (ዶ/ር) አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
በዮናስ ጌትነት
2 months ago
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
#ethiopia | '‘ዲጂታል ለልህቀት'’ በሚል ስያሜ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ፣ በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን፣ በአፍሪካ ቀዳሚ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ ዛሬ በይፋ መርቀናል።
ይህ ታላቅ ስኬት ለሀገራችን ከፍተኛ ኩራት ከመሆኑም በላይ በቴክኖሎጂ የሚመራ እና ዓላማ ተኮር ኢንቨስትመንት ምን ሊያስገኝ እንደሚችል ማረጋገጫ ነው።
የኢኮኖሚ ወሳኝ መሠረተ ልማት የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የዜጎችን ጊዜ ይቆጥባል፣ የሙስና ቀዳዳዎችን ይደፍናል፣ እንዲሁም በመንግሥት በኩል የተቋማትን ታማኝነትና ጥንካሬ ያጎለብታል።
ከሁሉም በላይ የኢትዮጵያ ትልሞች ተራ ምኞት ሳይሆኑ፣ በራሳችን እጆችና አቅም የምንገነባቸው እውነታዎች መሆናቸውን በግልጽ የሚያሳይ ምስክር ነው።
ይህን ስኬት እንድናጠናክር፣ ተሞክሯችንን ለአፍሪካውያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እንድናካፍል፣ እንዲሁም ከዚህ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት እንድንጓዝ ጥሪዬን አቀርባለሁ!
#ethiopia | '‘ዲጂታል ለልህቀት'’ በሚል ስያሜ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ፣ በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን፣ በአፍሪካ ቀዳሚ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ ዛሬ በይፋ መርቀናል።
ይህ ታላቅ ስኬት ለሀገራችን ከፍተኛ ኩራት ከመሆኑም በላይ በቴክኖሎጂ የሚመራ እና ዓላማ ተኮር ኢንቨስትመንት ምን ሊያስገኝ እንደሚችል ማረጋገጫ ነው።
የኢኮኖሚ ወሳኝ መሠረተ ልማት የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የዜጎችን ጊዜ ይቆጥባል፣ የሙስና ቀዳዳዎችን ይደፍናል፣ እንዲሁም በመንግሥት በኩል የተቋማትን ታማኝነትና ጥንካሬ ያጎለብታል።
ከሁሉም በላይ የኢትዮጵያ ትልሞች ተራ ምኞት ሳይሆኑ፣ በራሳችን እጆችና አቅም የምንገነባቸው እውነታዎች መሆናቸውን በግልጽ የሚያሳይ ምስክር ነው።
ይህን ስኬት እንድናጠናክር፣ ተሞክሯችንን ለአፍሪካውያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እንድናካፍል፣ እንዲሁም ከዚህ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት እንድንጓዝ ጥሪዬን አቀርባለሁ!
2 months ago
የአገልግሎት አሰጣጥ ባሕል ለውጥ በመሶብ አንድ ማዕከል…
ባሕል የአንድ ማኅበረሰብ፣ የድርጅት ወይም የሕዝብ የጋራ መገለጫ የሆነና በጥልቅ ሥር የሰደደ የአስተሳሰብ፣ የእሴት፣ የእምነት፣ የልማድና የባሕርይ ድምር ውጤት ነው።
የአገልግሎት ዘርፍ ባሕል ተቋማትና ሰራተኞቻቸው ከተገልጋዮች ጋር የሚገናኙበት እና ሥራዎችን የሚያከናውኑበት ያልተጻፉ ግን በተግባር የሚታዩ ልማዶችን የሚያካትት ነው፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ በአንዳንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የተለያዩ የመልካም አስተዳደርና ብልሹ አሰራሮች ይስተዋላሉ።
ይህ የአገልግሎት አሰጣጥ ባሕል የዜጎችን እንግልት ማብዛቱ ብቻ ሳይሆን፤ በሀገር ልማት እና በሕዝብ አመኔታ ላይ ትልቅ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ይህን የቆየ የአገልግሎት አሰጣጥ ባህል በመሠረታዊነት ለመቀየር እየሰራ ይገኛል።
የተለያዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር አቀናጅቶ የያዘው መሶብ ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ባለፈ፣ በመንግሥት ሠራተኛና በተገልጋዩ መካከል የነበረውን የግንኙነት ባሕል ቀይሯል፡፡
ቀደም ሲል አንድ ሰው ማንኛውንም ዓይነት አገልግሎት ለማግኘት ጊዜውን፣ ጉልበቱንና ገንዘቡን እንዲጨርስ የሚያስገድድ አሰልቺ አሰራር የነበረ ሲሆን ይህም ለሙስና እና ለብልሹ አሰራር ዋነኛ በር ከፋች ሆኖ ቆይቷል።
አሁን በመሶብ ማዕከል አገልግሎቶችን የሚሰጡ የፌደራል እና ሌሎች የመንግስት ተቋማት በአንድ ዲጂታል ሥርዓት ተቀናጅተው ዜጎች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ገንዘባቸውን እንዲቆጥቡ እያስቻለ ይገኛል።
ተቋማት ተቀናጅተው በአንድነት የሚሰሩበትን አዲስ የቅንጅት ባህል በመፍጠር በአገልግሎት አሰጣጥ ዘርፍ ውስጥ ትልቁ ክፍተት ሆኖ የዘለቀውን ይህንን ባሕል ለመቀየር ወጣቶችንና ባለሙያዎችን በልዩ ሁኔታ አሰልጥኖ ወደ ሥራ አስገብቷል።
በማዕከሉ የሚሰጡት አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፉ በመሆናቸው የአገልግሎት አሰጣጡን የተቀላጠፈ አድርጎታል፡፡
ዜጎች በዲጂታል ሥርዓት ተራቸውን ጠብቀው የሚስተናገዱበት ሁኔታ የተፈጠረ ሲሆን ይህ ለውጥ የመንግሥት አገልግሎት የዜጎች መብት እንጂ የኃላፊዎች በጎ ፈቃድ አለመሆኑን በተግባር ያሳየ ነው።
በዚህ መልኩ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በኢትዮጵያ የአገልግሎት አሰጣጥ ውስጥ በታማኝነት፣ በቅልጥፍና፣ በግልጽነትና በዲጂታል አሰራር ላይ የተመሰረተ አዲስ የአገልግሎት ባሕል እየገነባ ነው።
የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ ተጀምሮ አሁን ወደ ተለያዩ ክልሎችና ከተማ መስተዳደሮች እየተስፋፋ መጥቷል፡፡
በዚህም በሀገር አቀፍ ደረጃ ሥር ነቀል የሆነ የአገልግሎት ባሕል ለውጥ ለማምጣት ትልቅ መሠረት ጥሏል።
ይህም የመንግሥትን አገልግሎት ለዜጎች ቀላል በማድረግ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ ከፍቷል፡፡
በዮናስ ጌትነት
ባሕል የአንድ ማኅበረሰብ፣ የድርጅት ወይም የሕዝብ የጋራ መገለጫ የሆነና በጥልቅ ሥር የሰደደ የአስተሳሰብ፣ የእሴት፣ የእምነት፣ የልማድና የባሕርይ ድምር ውጤት ነው።
የአገልግሎት ዘርፍ ባሕል ተቋማትና ሰራተኞቻቸው ከተገልጋዮች ጋር የሚገናኙበት እና ሥራዎችን የሚያከናውኑበት ያልተጻፉ ግን በተግባር የሚታዩ ልማዶችን የሚያካትት ነው፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ በአንዳንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የተለያዩ የመልካም አስተዳደርና ብልሹ አሰራሮች ይስተዋላሉ።
ይህ የአገልግሎት አሰጣጥ ባሕል የዜጎችን እንግልት ማብዛቱ ብቻ ሳይሆን፤ በሀገር ልማት እና በሕዝብ አመኔታ ላይ ትልቅ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ይህን የቆየ የአገልግሎት አሰጣጥ ባህል በመሠረታዊነት ለመቀየር እየሰራ ይገኛል።
የተለያዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር አቀናጅቶ የያዘው መሶብ ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ባለፈ፣ በመንግሥት ሠራተኛና በተገልጋዩ መካከል የነበረውን የግንኙነት ባሕል ቀይሯል፡፡
ቀደም ሲል አንድ ሰው ማንኛውንም ዓይነት አገልግሎት ለማግኘት ጊዜውን፣ ጉልበቱንና ገንዘቡን እንዲጨርስ የሚያስገድድ አሰልቺ አሰራር የነበረ ሲሆን ይህም ለሙስና እና ለብልሹ አሰራር ዋነኛ በር ከፋች ሆኖ ቆይቷል።
አሁን በመሶብ ማዕከል አገልግሎቶችን የሚሰጡ የፌደራል እና ሌሎች የመንግስት ተቋማት በአንድ ዲጂታል ሥርዓት ተቀናጅተው ዜጎች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ገንዘባቸውን እንዲቆጥቡ እያስቻለ ይገኛል።
ተቋማት ተቀናጅተው በአንድነት የሚሰሩበትን አዲስ የቅንጅት ባህል በመፍጠር በአገልግሎት አሰጣጥ ዘርፍ ውስጥ ትልቁ ክፍተት ሆኖ የዘለቀውን ይህንን ባሕል ለመቀየር ወጣቶችንና ባለሙያዎችን በልዩ ሁኔታ አሰልጥኖ ወደ ሥራ አስገብቷል።
በማዕከሉ የሚሰጡት አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፉ በመሆናቸው የአገልግሎት አሰጣጡን የተቀላጠፈ አድርጎታል፡፡
ዜጎች በዲጂታል ሥርዓት ተራቸውን ጠብቀው የሚስተናገዱበት ሁኔታ የተፈጠረ ሲሆን ይህ ለውጥ የመንግሥት አገልግሎት የዜጎች መብት እንጂ የኃላፊዎች በጎ ፈቃድ አለመሆኑን በተግባር ያሳየ ነው።
በዚህ መልኩ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በኢትዮጵያ የአገልግሎት አሰጣጥ ውስጥ በታማኝነት፣ በቅልጥፍና፣ በግልጽነትና በዲጂታል አሰራር ላይ የተመሰረተ አዲስ የአገልግሎት ባሕል እየገነባ ነው።
የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ ተጀምሮ አሁን ወደ ተለያዩ ክልሎችና ከተማ መስተዳደሮች እየተስፋፋ መጥቷል፡፡
በዚህም በሀገር አቀፍ ደረጃ ሥር ነቀል የሆነ የአገልግሎት ባሕል ለውጥ ለማምጣት ትልቅ መሠረት ጥሏል።
ይህም የመንግሥትን አገልግሎት ለዜጎች ቀላል በማድረግ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ ከፍቷል፡፡
በዮናስ ጌትነት
2 months ago
የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር እመርታ
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ዓለማችን በቴክኖሎጂ እና በኢኖቬሽን ፈጣን ግስጋሴ ውስጥ ትገኛለች። ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፋዊ እውነት በውል በመገንዘብ፣ ሁለንተናዊ ኢኮኖሚዋን ከመሠረቱ የሚቀይር ታሪካዊ የዲጂታል ሽግግር እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት ዓመታት ሀገራችን ያለባትን ዘላቂ የቢሮክራሲ እና የኢኮኖሚ ፈተናዎች ለመቅረፍ ዲጂታላይዜሽንን እንደ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ መሣሪያ በመውሰድ በቁርጠኝነት እየሠራችበት ነው።
ይህ ጉዞ የሀገርን የልማት ምሰሶ በጠንካራ መሠረት ላይ የሚያጸና የመንግሥት የረጅም ጊዜ ራዕይ ማሳያ ነው።
በአንድ ወቅት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ሩቅ ሕልም ይታይ የነበረ ቢሆንም በ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂ በተከናወኑት መሠረታዊ ሥራዎች ዛሬ ውጤት መገኘት ችሏል።
አሁን ደግሞ የሀገራችንን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥን እና ይበልጥ ስኬታማ የሚያደርገው “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ በትግበራ ላይ መዋሉ የሂደቱን ቀጣይነት ያረጋግጣል።
ከዚህ ጎን ለጎን የሰው ሠራሽ አስተውሎት (ኤአይ) በየተቋመት ጥቅም ላይ መዋል ለሚሰጠው አገልግሎት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል።
የ“ፋይዳ” ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራምም ለጠቅላላው የዲጂታል ሥነ ምኅዳር ግንባታው መሠረት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።
እስከ 90 ሚሊዮን ዜጎችን በሥርዓቱ ውስጥ ለማቀፍ የታቀደው ይህ ግዙፍ መርሐ ግብር ለባንክ፣ ለፋይናንስ፣ ለንግድ እንቅስቃሴ እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ ነው።
የሀገርን የሰው ኃይል በዕውቀት ሳያደራጁ ዘላቂ ስኬትን ማሰብ ስለማይቻል፣ ከዚህ መሠረት ጋር ተያይዞ በ“ኢትዮ ኮደርስ” ኢኒሼቲቭ 5 ሚሊዮን ዜጎች የዲጂታል ክህሎት ሥልጠና መጀመሩ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚረከቡ ባለሙያዎችን ለማፍራት የተጣለ ታላቅ መሠረት ነው።
ይህ የዲጂታል መሠረት የዜጎችን እንግልት ወደሚቀንስ የሲቪል ሰርቪስ ዝማኔ በተግባር ተሻግሯል።
የአገልግሎት አሰጣጥን በዘመናዊ መልክ ለመቅረጽ በሁሉም አካባቢዎች እየተገነባ የሚገኘው “የመሶብ” የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተንዛዛ ቢሮክራሲን በማስቀረት የመንግሥትን ግልጽነት እና ተጠያቂነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ዓይነቱ የተቀናጀ አሠራር ሙስና እና ብክነትን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል አስተማማኝ ተቋማዊ አቅም እየፈጠረ ይገኛል።
በፋይናንስ ዘርፍም ቢሆን በዲጂታል የተከናወነው የግብይት ዋጋ 16 ትሪሊዮን ብር መድረሱ የዲጂታል ኢኮኖሚው ምን ያህል ውጤታማ እና ተደራሽ እየሆነ ለመምጣቱ ማሳያ ነው።
ይህ ስኬት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ አካታችነትን በተግባር አረጋግጧል።
ለወደፊቱም መሠረታዊ የመንግሥት አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ፕላትፎርሞች ተደራሽ ለማድረግ የታቀደው ዕቅድ የሀገራችንን የነገ ገጽታ በእጅጉ የሚቀይር ነው።
መንግሥት የሳይበር ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ እና የስታርትአፕ ሥነ ምኅዳርን በማጠናከር፣ የዲጂታል ሽግግር ሂደቱን አስተማማኝ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ እያደረገው ይገኛል።
ይህ ታሪካዊ ጉዞ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያቀልል፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ እና የኢኮኖሚ ልማታችንን ከሕልም ወደ እውነት የለወጠ የጋራ ብሔራዊ ስኬታችን በመሆኑ ሁሉም አካላት ለስኬቱ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #ai #technology
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ዓለማችን በቴክኖሎጂ እና በኢኖቬሽን ፈጣን ግስጋሴ ውስጥ ትገኛለች። ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፋዊ እውነት በውል በመገንዘብ፣ ሁለንተናዊ ኢኮኖሚዋን ከመሠረቱ የሚቀይር ታሪካዊ የዲጂታል ሽግግር እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት ዓመታት ሀገራችን ያለባትን ዘላቂ የቢሮክራሲ እና የኢኮኖሚ ፈተናዎች ለመቅረፍ ዲጂታላይዜሽንን እንደ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ መሣሪያ በመውሰድ በቁርጠኝነት እየሠራችበት ነው።
ይህ ጉዞ የሀገርን የልማት ምሰሶ በጠንካራ መሠረት ላይ የሚያጸና የመንግሥት የረጅም ጊዜ ራዕይ ማሳያ ነው።
በአንድ ወቅት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ሩቅ ሕልም ይታይ የነበረ ቢሆንም በ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂ በተከናወኑት መሠረታዊ ሥራዎች ዛሬ ውጤት መገኘት ችሏል።
አሁን ደግሞ የሀገራችንን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥን እና ይበልጥ ስኬታማ የሚያደርገው “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ በትግበራ ላይ መዋሉ የሂደቱን ቀጣይነት ያረጋግጣል።
ከዚህ ጎን ለጎን የሰው ሠራሽ አስተውሎት (ኤአይ) በየተቋመት ጥቅም ላይ መዋል ለሚሰጠው አገልግሎት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል።
የ“ፋይዳ” ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራምም ለጠቅላላው የዲጂታል ሥነ ምኅዳር ግንባታው መሠረት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።
እስከ 90 ሚሊዮን ዜጎችን በሥርዓቱ ውስጥ ለማቀፍ የታቀደው ይህ ግዙፍ መርሐ ግብር ለባንክ፣ ለፋይናንስ፣ ለንግድ እንቅስቃሴ እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ ነው።
የሀገርን የሰው ኃይል በዕውቀት ሳያደራጁ ዘላቂ ስኬትን ማሰብ ስለማይቻል፣ ከዚህ መሠረት ጋር ተያይዞ በ“ኢትዮ ኮደርስ” ኢኒሼቲቭ 5 ሚሊዮን ዜጎች የዲጂታል ክህሎት ሥልጠና መጀመሩ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚረከቡ ባለሙያዎችን ለማፍራት የተጣለ ታላቅ መሠረት ነው።
ይህ የዲጂታል መሠረት የዜጎችን እንግልት ወደሚቀንስ የሲቪል ሰርቪስ ዝማኔ በተግባር ተሻግሯል።
የአገልግሎት አሰጣጥን በዘመናዊ መልክ ለመቅረጽ በሁሉም አካባቢዎች እየተገነባ የሚገኘው “የመሶብ” የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተንዛዛ ቢሮክራሲን በማስቀረት የመንግሥትን ግልጽነት እና ተጠያቂነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ዓይነቱ የተቀናጀ አሠራር ሙስና እና ብክነትን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል አስተማማኝ ተቋማዊ አቅም እየፈጠረ ይገኛል።
በፋይናንስ ዘርፍም ቢሆን በዲጂታል የተከናወነው የግብይት ዋጋ 16 ትሪሊዮን ብር መድረሱ የዲጂታል ኢኮኖሚው ምን ያህል ውጤታማ እና ተደራሽ እየሆነ ለመምጣቱ ማሳያ ነው።
ይህ ስኬት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ አካታችነትን በተግባር አረጋግጧል።
ለወደፊቱም መሠረታዊ የመንግሥት አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ፕላትፎርሞች ተደራሽ ለማድረግ የታቀደው ዕቅድ የሀገራችንን የነገ ገጽታ በእጅጉ የሚቀይር ነው።
መንግሥት የሳይበር ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ እና የስታርትአፕ ሥነ ምኅዳርን በማጠናከር፣ የዲጂታል ሽግግር ሂደቱን አስተማማኝ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ እያደረገው ይገኛል።
ይህ ታሪካዊ ጉዞ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያቀልል፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ እና የኢኮኖሚ ልማታችንን ከሕልም ወደ እውነት የለወጠ የጋራ ብሔራዊ ስኬታችን በመሆኑ ሁሉም አካላት ለስኬቱ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #ai #technology
2 months ago
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት፡-
ዛሬ የከተማ አስተዳደራችን የ90 ቀናት የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች ዕቅድ ላይ ከመላው የከተማችን አመራሮች ጋር ተወያይተን ወደ ተግባር አስገብተናል።
በድህረ ምርጫ በፍጥነት ፈታችንን ወደ ሥራ በመመለስ ፈጣን ውጤቶችን ማስመዝገብ፣ ተከታታይና አዳዲስ ነገሮችን መተግበር፣ ህብረተሰባችን ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በላቀ ትጋትና ያለ እረፍት መፈጸም የሚያስችል እቅድ ይዘን በልዩ ትኩረት የምንፈፅም ይሆናል።
ከሰኔ 9 እስከ ጳጉሜ 5 በሚቆየው 90 ቀናት ውስጥ የምንፈፅማቸው ዋና ዋና ግቦች፤ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት፣ አገልግሎት የማሻሻል ስራን በማጠናከር የመሶብ አንድ ማእከል ዲጂታል አገልግሎትን ማስፋት፣ የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት ፣ የንግድ ስርዓቱን መግራት፣ የስራ እድል ፈጠራ እና የወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነት ላይ መስራት፣ በአረንጓዴ አሻራ ልማት፣ የከተማ ግብርና እና የሌማት ትሩፋት፣ የሰላም ግንባታ ስራዎች፣ የገቢ አሰባሰብ፣ ልመናንና ተረጂነትን መቀነስ፣ የበጎ ፍቃድ መርሃ ግብርን በተቀናጀ የህብረተሰብ ተሳትፎ መተግበር፣ የኢትዮዽያ ታምርት ንቅናቄን በአዲስ ቅኝት መምራት፣ ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ፣ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎችን በጥራት እና በተያዘላቸው የጊዜና በጀት ገደብ ማጠናቀቅ፣ የሚዲያና የህዝብ ግንኙነት ስራዎችን ማጠናከር … ወዘተ ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመፈፀም ተዘጋጅተናል።
የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ዝግጅት ላይ በትኩረት በመስራት አዲሱ በጀት ዓመት ህዝባችንን ይበልጥ የምናገለግልበት፣ አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ጉዟችንን የምናረጋግጥበት እንዲሆን ከእቅድ ዝግጅት እስከ ተግባር አፈፃፀም በጠንካራ ክትትልና ድጋፍ የምንፈፅም ይሆናል።
ዛሬ የከተማ አስተዳደራችን የ90 ቀናት የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች ዕቅድ ላይ ከመላው የከተማችን አመራሮች ጋር ተወያይተን ወደ ተግባር አስገብተናል።
በድህረ ምርጫ በፍጥነት ፈታችንን ወደ ሥራ በመመለስ ፈጣን ውጤቶችን ማስመዝገብ፣ ተከታታይና አዳዲስ ነገሮችን መተግበር፣ ህብረተሰባችን ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በላቀ ትጋትና ያለ እረፍት መፈጸም የሚያስችል እቅድ ይዘን በልዩ ትኩረት የምንፈፅም ይሆናል።
ከሰኔ 9 እስከ ጳጉሜ 5 በሚቆየው 90 ቀናት ውስጥ የምንፈፅማቸው ዋና ዋና ግቦች፤ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት፣ አገልግሎት የማሻሻል ስራን በማጠናከር የመሶብ አንድ ማእከል ዲጂታል አገልግሎትን ማስፋት፣ የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት ፣ የንግድ ስርዓቱን መግራት፣ የስራ እድል ፈጠራ እና የወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነት ላይ መስራት፣ በአረንጓዴ አሻራ ልማት፣ የከተማ ግብርና እና የሌማት ትሩፋት፣ የሰላም ግንባታ ስራዎች፣ የገቢ አሰባሰብ፣ ልመናንና ተረጂነትን መቀነስ፣ የበጎ ፍቃድ መርሃ ግብርን በተቀናጀ የህብረተሰብ ተሳትፎ መተግበር፣ የኢትዮዽያ ታምርት ንቅናቄን በአዲስ ቅኝት መምራት፣ ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ፣ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎችን በጥራት እና በተያዘላቸው የጊዜና በጀት ገደብ ማጠናቀቅ፣ የሚዲያና የህዝብ ግንኙነት ስራዎችን ማጠናከር … ወዘተ ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመፈፀም ተዘጋጅተናል።
የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ዝግጅት ላይ በትኩረት በመስራት አዲሱ በጀት ዓመት ህዝባችንን ይበልጥ የምናገለግልበት፣ አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ጉዟችንን የምናረጋግጥበት እንዲሆን ከእቅድ ዝግጅት እስከ ተግባር አፈፃፀም በጠንካራ ክትትልና ድጋፍ የምንፈፅም ይሆናል።
2 months ago
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የወልቂጤ መሶብ የአንድ ማዕከልን አገልግሎት ሥራ አስጀመሩ
**********************
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በክልሉ ወልቂጤ ከተማ በክልሉ 3ኛውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ በይፋ መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በ7 ተቋማት 22 አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል፡፡
የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ያለባቸው፣ ተገልጋይ የሚበዛባቸው፣ ለሙስናና ብልሹ አሠራር የተጋለጡ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸው ተቋማት ተለይተው ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ መደረጋቸው በወቅቱ ተጠቁሟል፡፡
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች በአንድ ቦታ ብዙ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ፣ ጊዜና ወጪ እንዲቆጥቡ እና የአገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል የሚያስችል ዘመናዊ የአገልግሎት ሥርዓት መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎን ጨምሮ የተለያዩ የክልልና ዞን መንግሥት ስራ ኃላፊዎች መገኘታውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #mesob #onestopservice
**********************
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በክልሉ ወልቂጤ ከተማ በክልሉ 3ኛውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ በይፋ መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በ7 ተቋማት 22 አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል፡፡
የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ያለባቸው፣ ተገልጋይ የሚበዛባቸው፣ ለሙስናና ብልሹ አሠራር የተጋለጡ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸው ተቋማት ተለይተው ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ መደረጋቸው በወቅቱ ተጠቁሟል፡፡
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች በአንድ ቦታ ብዙ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ፣ ጊዜና ወጪ እንዲቆጥቡ እና የአገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል የሚያስችል ዘመናዊ የአገልግሎት ሥርዓት መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎን ጨምሮ የተለያዩ የክልልና ዞን መንግሥት ስራ ኃላፊዎች መገኘታውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #mesob #onestopservice
2 months ago
የወልቂጤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመረቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወልቂጤ ከተማ የክልሉን 3ኛ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ሥራ አስጀምረዋል፡፡
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች በአንድ ቦታ ብዙ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ፣ ጊዜና ወጪ እንዲቆጥቡና የአገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል የሚያስችል ሥርዓት ነው።
በተቀናጀ መረጃ አሰጣጥ የዜጎችን እርካታ በማሳደግና የመንግሥት ተቋማት ቅንጅታዊ አሰራርን በማጎልበት ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ተመላክቷል፡፡
የወልቂጤ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በውስጡ 6 ተቋማት የያዘ ሲሆን÷ በአጠቃላይ 42 የተለያዩ አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡
ከፍተኛ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ያለባቸው፣ ተገልጋይ የሚበዛባቸው፣ ለሙስናና ብልሹ አሠራር የተጋለጡ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸው ተቋማት ተለይተው ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ ተደርጓል።
ተቋማትን ከወረቀት ንክኪ ነጻ እና በውጤት ወደሚለካ አሠራር ለማሸጋገር እየተተገበሩ ካሉ የለውጥ ሥራዎች መካከል "የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት" ተጠቃሽ ነው፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወልቂጤ ከተማ የክልሉን 3ኛ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ሥራ አስጀምረዋል፡፡
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች በአንድ ቦታ ብዙ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ፣ ጊዜና ወጪ እንዲቆጥቡና የአገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል የሚያስችል ሥርዓት ነው።
በተቀናጀ መረጃ አሰጣጥ የዜጎችን እርካታ በማሳደግና የመንግሥት ተቋማት ቅንጅታዊ አሰራርን በማጎልበት ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ተመላክቷል፡፡
የወልቂጤ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በውስጡ 6 ተቋማት የያዘ ሲሆን÷ በአጠቃላይ 42 የተለያዩ አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡
ከፍተኛ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ያለባቸው፣ ተገልጋይ የሚበዛባቸው፣ ለሙስናና ብልሹ አሠራር የተጋለጡ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸው ተቋማት ተለይተው ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ ተደርጓል።
ተቋማትን ከወረቀት ንክኪ ነጻ እና በውጤት ወደሚለካ አሠራር ለማሸጋገር እየተተገበሩ ካሉ የለውጥ ሥራዎች መካከል "የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት" ተጠቃሽ ነው፡፡
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ምክክር፦ ብቸኛው የፈተናዎቻችን ማለፊያ
*****************
ኢትዮጵያ በዘመናት ፈተና ውስጥ አልፋ ለዛሬ የደረሰችው በሕዝቦቿ ልዩ መስተጋብር እና ጥብቅ አንድነት ነው።
ታሪካችንን ወደኋላ ስንቃኝ በሕብረት ጦርነቶችን አሸንፈን የጋራ ነጻነታችንን ያስከበርን፣ በአንድ መሶብ ዙሪያ ከብበን በጋራ የበላን፣ "እኔ ልደፋልህ/ልደፋልሽ" መባባልን የመሰለ ድንቅ ባህል ያዳበርን ሕዝቦች ነን።
ሀገር በባዕዳን ተደፈረች ሲባል የውስጥ ልዩነታችንን ወደ ጎን ትተን ወደ ጦር ሜዳ የተመምነው እና ኢትዮጵያን በፈተናዎች ውስጥ ጠብቀን ያኖርነው በዚህ የጋራ ሥነ-ልቦና ነው።
ይሁን እና ይህ ሁሉ ታሪክ እያለን ዛሬ ላይ "በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለን በመመካከር ችግሮቻችንን መፍታት ለምን ተሳነን?" የሚለው ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ የሚሻ ጉዳይ ነው።
የዘመናዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አመጣጥ ከታሪካዊ እሴቶቻችን ጋር በእጅጉ የተላተመ ነው። የፖለቲካው ስብራት ያመጣው ትልቁ መጥፎ ጠባሳ የጋራ ትርክትን አዳክሞ የልዩነት፣ የመጠፋፋት እና የጥላቻ ትርክትን ማንገሡ ነው።
አንዱን አግልሎ እና ሙሉ ለሙሉ አሸንፎ ሥልጣን ላይ የመውጣት የዜሮ ድምር ፖለቲካ የኢትዮጵያ ትልቁ በሽታ ነው።
ይህ አካሄድ እርስ በርስ የመደጋገፍና ችግርን የመካፈል መልካም ባህላችንን በመሸርሸር፣ “እኔ ካልመራሁ ሀገር ትፍረስ” ወደሚል አደገኛና ራስ ወዳድነት የተሞላበት አስተሳሰብ አሸጋግሮናል።
ይህ የውስጥ መከፋፈልና ቀውስ ደግሞ ለውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ተፅዕኖ ሰፊ በር ከፍቷል።
ኢትዮጵያ በዚህ የታሪክ አዙሪት ውስጥ ስታልፍ ሥጣኔዋን ማስቀጠል ተስኗታል። በሕብረት ለነጻነት በጦር የተዋደቁት ልጆቿ ድህነትን ለማጥፋት ባለመተባበራቸው የተሟላ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ተስኗት ኖራለች።
የሚያሳዝነው እውነታ ይህን የፖለቲካ ቋጠሮ ለመፍታት የሚያስችል ለዘመናት የኖረ ድንቅ ሀገር በቀል የሽምግልና እና የዕርቅ ባህል እያለን በበቂ ሁኔታ አለመጠቀማችን ነው።
ችግሮቻችንን ከማኅበረሰባዊ እሴቶቻችን፣ ከሃይማኖት አባቶች ተሰሚነት እንዲሁም እንደ ገዳ፣ የጆካ፣ አባጋር፣ መካባን ከመሳሰሉ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ የፍትሕ እና የዕርቅ ሥርዓቶቻችን ማዕቀፍ ውጪ በሆነ መንገድ ለመፍታት መሞከራችን ከባድ ዋጋ አስከፍሎናል።
ከውጭ በገቡ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለሞች ብቻ ለመጓዝ መሞከራችን እና ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓቶቻችንን ከፖለቲካ መጠቀሚያነት ነጻ አድርገን አለማጎልበታችን ለዛሬው የውይይት ባህል መጥፋት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል።
ታዲያ አሁን ምን ማድረግ አለብን?
መፍትሔው ወደ አውዳችን መመለስ ነው። የውጭ ተፅዕኖን ለመቋቋም መጀመሪያ የራስን ቤት ማጽዳት እና ሕብረትን ማጠናከር የግድ ይላል።
ፖለቲከኞች እና የሐሳብ መሪዎች የመሸናነፍ ሳይሆን የመደማመጥ እንዲሁም ለሀገር ሰላም ሲሉ ግትር የሆነ አቋምን የማለዘብ ባህልን በተግባር ሊያሳዩ ይገባል።
በተለይም ወጣቱ ትውልድ በዲጂታሉ ዓለም ያለውን ስሜታዊነት ወደ ጎን በመተው ምክንያታዊ ውይይቶችን ሊያበረታታ ይገባል።
ሚዲያው፣ የትምህርት ሥርዓቱ፣ የኪነ-ጥበብ ዘርፉ ካለፉት ቁስሎች ይልቅ ወደ ፊት በሚያገናኙን የጋራ እሴቶች እና የወደፊት ዕጣ ፈንታችን ላይ ሊያተኩር ግድ ይላል።
በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሚና እጅግ የጎላ ነው። ኮሚሽኑ የጠፋውን የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ለመመለስ የተዘረጋ ዘመናዊ የቤተሰብ መሶባችን ሊሆን ይገባዋል።
አሁን የተጀመሩት የምክክር ሂደቶች ሁሉን አሳታፊ፣ ከፖለቲካዊ ጨዋታ ነጻ የሆኑ እና እውነተኛ ማኅበረሰባዊ ስብራቶቻችንን የሚጠግኑ እንዲሆኑ የሚቻለው ሁሉ ተደርጓል።
ሀገራዊ ምክክሩ ባህላዊ የዕርቅ እሴቶቻችንን ከዘመናዊ የመንግሥት ግንባታ ጋር አዋሕዶ የዘለቄታ ሰላም የምናመጣበት ታላቅ ዕድል ነው።
በጠረጴዛ ዙሪያ የማይፈታ የትኛውም የፖለቲካ ችግር በጦር ሜዳ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያገኝ ታሪካችን ከበቂ በላይ አስተምሮናል።
በመሆኑም ሁላችንም ወደኋላ ከጎተተን የ“እኔ እበልጥ” ክፉ ልማድ ወጥተን ለምክክሩ ስኬት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dotstream #peacebuilding #nationalunity
*****************
ኢትዮጵያ በዘመናት ፈተና ውስጥ አልፋ ለዛሬ የደረሰችው በሕዝቦቿ ልዩ መስተጋብር እና ጥብቅ አንድነት ነው።
ታሪካችንን ወደኋላ ስንቃኝ በሕብረት ጦርነቶችን አሸንፈን የጋራ ነጻነታችንን ያስከበርን፣ በአንድ መሶብ ዙሪያ ከብበን በጋራ የበላን፣ "እኔ ልደፋልህ/ልደፋልሽ" መባባልን የመሰለ ድንቅ ባህል ያዳበርን ሕዝቦች ነን።
ሀገር በባዕዳን ተደፈረች ሲባል የውስጥ ልዩነታችንን ወደ ጎን ትተን ወደ ጦር ሜዳ የተመምነው እና ኢትዮጵያን በፈተናዎች ውስጥ ጠብቀን ያኖርነው በዚህ የጋራ ሥነ-ልቦና ነው።
ይሁን እና ይህ ሁሉ ታሪክ እያለን ዛሬ ላይ "በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለን በመመካከር ችግሮቻችንን መፍታት ለምን ተሳነን?" የሚለው ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ የሚሻ ጉዳይ ነው።
የዘመናዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አመጣጥ ከታሪካዊ እሴቶቻችን ጋር በእጅጉ የተላተመ ነው። የፖለቲካው ስብራት ያመጣው ትልቁ መጥፎ ጠባሳ የጋራ ትርክትን አዳክሞ የልዩነት፣ የመጠፋፋት እና የጥላቻ ትርክትን ማንገሡ ነው።
አንዱን አግልሎ እና ሙሉ ለሙሉ አሸንፎ ሥልጣን ላይ የመውጣት የዜሮ ድምር ፖለቲካ የኢትዮጵያ ትልቁ በሽታ ነው።
ይህ አካሄድ እርስ በርስ የመደጋገፍና ችግርን የመካፈል መልካም ባህላችንን በመሸርሸር፣ “እኔ ካልመራሁ ሀገር ትፍረስ” ወደሚል አደገኛና ራስ ወዳድነት የተሞላበት አስተሳሰብ አሸጋግሮናል።
ይህ የውስጥ መከፋፈልና ቀውስ ደግሞ ለውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ተፅዕኖ ሰፊ በር ከፍቷል።
ኢትዮጵያ በዚህ የታሪክ አዙሪት ውስጥ ስታልፍ ሥጣኔዋን ማስቀጠል ተስኗታል። በሕብረት ለነጻነት በጦር የተዋደቁት ልጆቿ ድህነትን ለማጥፋት ባለመተባበራቸው የተሟላ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ተስኗት ኖራለች።
የሚያሳዝነው እውነታ ይህን የፖለቲካ ቋጠሮ ለመፍታት የሚያስችል ለዘመናት የኖረ ድንቅ ሀገር በቀል የሽምግልና እና የዕርቅ ባህል እያለን በበቂ ሁኔታ አለመጠቀማችን ነው።
ችግሮቻችንን ከማኅበረሰባዊ እሴቶቻችን፣ ከሃይማኖት አባቶች ተሰሚነት እንዲሁም እንደ ገዳ፣ የጆካ፣ አባጋር፣ መካባን ከመሳሰሉ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ የፍትሕ እና የዕርቅ ሥርዓቶቻችን ማዕቀፍ ውጪ በሆነ መንገድ ለመፍታት መሞከራችን ከባድ ዋጋ አስከፍሎናል።
ከውጭ በገቡ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለሞች ብቻ ለመጓዝ መሞከራችን እና ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓቶቻችንን ከፖለቲካ መጠቀሚያነት ነጻ አድርገን አለማጎልበታችን ለዛሬው የውይይት ባህል መጥፋት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል።
ታዲያ አሁን ምን ማድረግ አለብን?
መፍትሔው ወደ አውዳችን መመለስ ነው። የውጭ ተፅዕኖን ለመቋቋም መጀመሪያ የራስን ቤት ማጽዳት እና ሕብረትን ማጠናከር የግድ ይላል።
ፖለቲከኞች እና የሐሳብ መሪዎች የመሸናነፍ ሳይሆን የመደማመጥ እንዲሁም ለሀገር ሰላም ሲሉ ግትር የሆነ አቋምን የማለዘብ ባህልን በተግባር ሊያሳዩ ይገባል።
በተለይም ወጣቱ ትውልድ በዲጂታሉ ዓለም ያለውን ስሜታዊነት ወደ ጎን በመተው ምክንያታዊ ውይይቶችን ሊያበረታታ ይገባል።
ሚዲያው፣ የትምህርት ሥርዓቱ፣ የኪነ-ጥበብ ዘርፉ ካለፉት ቁስሎች ይልቅ ወደ ፊት በሚያገናኙን የጋራ እሴቶች እና የወደፊት ዕጣ ፈንታችን ላይ ሊያተኩር ግድ ይላል።
በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሚና እጅግ የጎላ ነው። ኮሚሽኑ የጠፋውን የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ለመመለስ የተዘረጋ ዘመናዊ የቤተሰብ መሶባችን ሊሆን ይገባዋል።
አሁን የተጀመሩት የምክክር ሂደቶች ሁሉን አሳታፊ፣ ከፖለቲካዊ ጨዋታ ነጻ የሆኑ እና እውነተኛ ማኅበረሰባዊ ስብራቶቻችንን የሚጠግኑ እንዲሆኑ የሚቻለው ሁሉ ተደርጓል።
ሀገራዊ ምክክሩ ባህላዊ የዕርቅ እሴቶቻችንን ከዘመናዊ የመንግሥት ግንባታ ጋር አዋሕዶ የዘለቄታ ሰላም የምናመጣበት ታላቅ ዕድል ነው።
በጠረጴዛ ዙሪያ የማይፈታ የትኛውም የፖለቲካ ችግር በጦር ሜዳ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያገኝ ታሪካችን ከበቂ በላይ አስተምሮናል።
በመሆኑም ሁላችንም ወደኋላ ከጎተተን የ“እኔ እበልጥ” ክፉ ልማድ ወጥተን ለምክክሩ ስኬት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dotstream #peacebuilding #nationalunity
2 months ago
በስሉጥ ከተማ፤ ስሉጥ አገልግሎት - አዲስ መሶብ!
*************
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ፣ በከተማችን ከታየው አስደማሚ የከተሜነት ትራንስፎርሜሽን ጎን ለጎን የህበረተሰብ ተጠቃሚነትን ማዕከል ያደረጉ ዘመን ተሸጋሪ ሰው ተኮር ስራዎች ተሰርቷል፤ እየተሰሩም ይገኛሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ የህዝባችን የዘመናት ጥያቄ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለት ስር-ነቀል የሆነ ለውጥ ለማምጣትም መጠነ ሰፊ የሆነ የመሰረተ-ልማት እና የሰው ሃይል ልማት እየተሰራ ይግኛል፡፡
ዕድገቷን እና ስሉጥ ከተማነቷን (Smart-city) የሚመጥን አገልግሎት ለማቅረብ ቴክኖሎጂን ግብር ላይ የማዋል ሂደት አጠናክራ ይዛለች፡፡ ይኸውም የመሶብ አንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ቀዳሚው ተጠቃሽ ነው፡፡
አዲስ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በከተማችን ሁሉም ክፍለከተሞ ተደራሽ በማድረግ የህብረተሰቡን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን ቀን ከሌሊት እየተሰራ ይገኛል፤ የላቀ ውጤትም ተመዝግቦበታል፡፡
እስከአሁን በማዕከል እና በዘጠኝ ክፍለ-ከተሞች እንዲሁም፣ በተንቀሳቃሽ አውቶብስ የተደራጀ፣ ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ የሚደረግባቸው፣ የበቁ የሰው ሃይል የተማላላቸው ማዕከሎች አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
በቴክኖሎጂ በታገዘ በተደረገ ዳሰሳ እንደሚያሳየው ተገልጋዩ ከ99 በመቶ በላይ እርካታ ያመላክታል፡፡ ቀሪ ሁለት ክፍለ-ከተሞችም ግንባታቸው ተጠናቆ በጥቂት ቀናት አገልግሎት ይጀምራሉ፡፡
የአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለትን ታሪክ ለማድረግ በቁርጠኝነት ተግብረን፣ የህብተሰባችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማላቅ አበክረን እንሰራለን!
Ethiopian Broadcasting Corporation #smartcity #አዲስአበባ
*************
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ፣ በከተማችን ከታየው አስደማሚ የከተሜነት ትራንስፎርሜሽን ጎን ለጎን የህበረተሰብ ተጠቃሚነትን ማዕከል ያደረጉ ዘመን ተሸጋሪ ሰው ተኮር ስራዎች ተሰርቷል፤ እየተሰሩም ይገኛሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ የህዝባችን የዘመናት ጥያቄ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለት ስር-ነቀል የሆነ ለውጥ ለማምጣትም መጠነ ሰፊ የሆነ የመሰረተ-ልማት እና የሰው ሃይል ልማት እየተሰራ ይግኛል፡፡
ዕድገቷን እና ስሉጥ ከተማነቷን (Smart-city) የሚመጥን አገልግሎት ለማቅረብ ቴክኖሎጂን ግብር ላይ የማዋል ሂደት አጠናክራ ይዛለች፡፡ ይኸውም የመሶብ አንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ቀዳሚው ተጠቃሽ ነው፡፡
አዲስ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በከተማችን ሁሉም ክፍለከተሞ ተደራሽ በማድረግ የህብረተሰቡን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን ቀን ከሌሊት እየተሰራ ይገኛል፤ የላቀ ውጤትም ተመዝግቦበታል፡፡
እስከአሁን በማዕከል እና በዘጠኝ ክፍለ-ከተሞች እንዲሁም፣ በተንቀሳቃሽ አውቶብስ የተደራጀ፣ ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ የሚደረግባቸው፣ የበቁ የሰው ሃይል የተማላላቸው ማዕከሎች አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
በቴክኖሎጂ በታገዘ በተደረገ ዳሰሳ እንደሚያሳየው ተገልጋዩ ከ99 በመቶ በላይ እርካታ ያመላክታል፡፡ ቀሪ ሁለት ክፍለ-ከተሞችም ግንባታቸው ተጠናቆ በጥቂት ቀናት አገልግሎት ይጀምራሉ፡፡
የአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለትን ታሪክ ለማድረግ በቁርጠኝነት ተግብረን፣ የህብተሰባችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማላቅ አበክረን እንሰራለን!
Ethiopian Broadcasting Corporation #smartcity #አዲስአበባ
2 months ago
የዲጂታል ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ - ከስትራቴጂ ወደ ስኬት
***********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ዛሬ ዓለማችን በቴክኖሎጂ እና በኢኖቬሽን ፈጣን ግስጋሴ ውስጥ ትገኛለች። ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፋዊ እውነት በውል በመገንዘብ፣ ሁለንተናዊ ኢኮኖሚዋን ከመሠረቱ የሚቀይር ታሪካዊ የዲጂታል ሽግግር እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት ሀገራችን ያለባትን ዘላቂ የቢሮክራሲ እና የኢኮኖሚ ፈተናዎች ለመቅረፍ ዲጂታላይዜሽንን እንደ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ መሣሪያ በመውሰድ እየሠራችበት ትገኛለች።
ይህ ጉዞ የሀገርን የልማት ምሰሶ በጽኑ መሠረት ላይ የሚያጸና የመንግሥት የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ብለን እናምናለን።
በአንድ ወቅት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ሩቅ ሕልም ይታይ እንደነበር አይዘነጋም፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑት መሠረታዊ ሥራዎች ግን ዛሬ ላይ ሊሻር በማይችል እውነታ ላይ የቆመ መሠረት ተጥሏል።
መንግሥት ያደረጋቸው ሰፊ የፖሊሲ እና የሕግ ማሻሻያዎች “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂን በስኬት ለማጠናቀቅ አስችለዋል።
አሁን ደግሞ የሀገራችንን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥን እና ይበልጥ ስኬታማ የሚያደርገው “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ ፀድቆ ወደ ሥራ እንዲገባ መደረጉ የሂደቱን ቀጣይነት ያረጋግጣል።
ከዚህ ጎን ለጎን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ለችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ መፍትሔዎች መበልጸግ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ የሚበረታታ እርምጃ ነው።
በዚህ ዘመናዊ የታሪክ እጥፋት ውስጥ የ“ፋይዳ” ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም እና የ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ ሚና እጅግ የላቀ ነው።
የዲጂታል መታወቂያ ለኢኮኖሚው ግንባታ ልክ እንደ ቤት መሠረት ነው። እስከ 90 ሚሊዮን ዜጎችን በሥርዓቱ ውስጥ ለማቀፍ የታቀደው ይህ ግዙፍ መርሐ ግብር ለባንክ፣ ለፋይናንስ፣ ለንግድ እንቅስቃሴ እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ ነው።
“የቆጠሩት እህል አያልቅም” እንደሚባለው የሀገርን የሰው ኃይል በዕውቀት ሳያደራጁ ዘላቂ ስኬትን ማሰብ አይቻልም። በመሆኑም በ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ 5 ሚሊዮን ዜጎች የዲጂታል ክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚረከቡ ባለሙያዎችን ለማፍራት የተጣለ ታላቅ መሠረት ነው።
የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን በሁሉም አካባቢዎች እየተገነባ ያለው “የመሶብ” የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የተንዛዛ ቢሮክራሲን እና የዜጎችን እንግልት በማስቀረት የመንግሥትን ግልጽነት እና ተጠያቂነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። ይህ ዓይነቱ አሠራር ሙስና እና ብክነትን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል አስተማማኝ ተቋማዊ አቅም ይፈጥራል።
በፋይናንስ ዘርፍም ቢሆን በ2017 በጀት ዓመት ብቻ በዲጂታል የተከናወነው የግብይት ዋጋ 16 ትሪሊዮን ብር መድረሱ የዲጂታል ኢኮኖሚው ምን ያህል ውጤታማ እና ተደራሽ እየሆነ ለመምጣቱ ሕያው ማሳያ ነው።
ይህ ስኬት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ አካታችነትን በተግባር አረጋግጧል።
ለወደፊቱም መሠረታዊ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ፕላትፎርሞች ተደራሽ ለማድረግ የታቀደው ዕቅድ የሀገራችንን የነገ ገጽታ በእጅጉ የሚቀይር ነው።
መንግሥት የሳይበር ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ እና የስታርትአፕ ሥነ ምኅዳርን በማጠናከር፣ የዲጂታል ሽግግር ሂደቱን አስተማማኝ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ እያደረገው ይገኛል።
በአጠቃላይ ይህ ታሪካዊ ጉዞ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያቀልል፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ እና የኢኮኖሚ ልማታችንን ከሕልም ወደ እውነት የለወጠ የጋራ ብሔራዊ ስኬታችን በመሆኑ ሁሉም አካላት ለስኬቱ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #5millioncoders #success #𝐃𝐢𝐠𝐢𝐭𝐚𝐥𝐄𝐜𝐨𝐧𝐨𝐦𝐲
***********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ዛሬ ዓለማችን በቴክኖሎጂ እና በኢኖቬሽን ፈጣን ግስጋሴ ውስጥ ትገኛለች። ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፋዊ እውነት በውል በመገንዘብ፣ ሁለንተናዊ ኢኮኖሚዋን ከመሠረቱ የሚቀይር ታሪካዊ የዲጂታል ሽግግር እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት ሀገራችን ያለባትን ዘላቂ የቢሮክራሲ እና የኢኮኖሚ ፈተናዎች ለመቅረፍ ዲጂታላይዜሽንን እንደ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ መሣሪያ በመውሰድ እየሠራችበት ትገኛለች።
ይህ ጉዞ የሀገርን የልማት ምሰሶ በጽኑ መሠረት ላይ የሚያጸና የመንግሥት የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ብለን እናምናለን።
በአንድ ወቅት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ሩቅ ሕልም ይታይ እንደነበር አይዘነጋም፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑት መሠረታዊ ሥራዎች ግን ዛሬ ላይ ሊሻር በማይችል እውነታ ላይ የቆመ መሠረት ተጥሏል።
መንግሥት ያደረጋቸው ሰፊ የፖሊሲ እና የሕግ ማሻሻያዎች “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂን በስኬት ለማጠናቀቅ አስችለዋል።
አሁን ደግሞ የሀገራችንን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥን እና ይበልጥ ስኬታማ የሚያደርገው “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ ፀድቆ ወደ ሥራ እንዲገባ መደረጉ የሂደቱን ቀጣይነት ያረጋግጣል።
ከዚህ ጎን ለጎን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ለችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ መፍትሔዎች መበልጸግ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ የሚበረታታ እርምጃ ነው።
በዚህ ዘመናዊ የታሪክ እጥፋት ውስጥ የ“ፋይዳ” ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም እና የ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ ሚና እጅግ የላቀ ነው።
የዲጂታል መታወቂያ ለኢኮኖሚው ግንባታ ልክ እንደ ቤት መሠረት ነው። እስከ 90 ሚሊዮን ዜጎችን በሥርዓቱ ውስጥ ለማቀፍ የታቀደው ይህ ግዙፍ መርሐ ግብር ለባንክ፣ ለፋይናንስ፣ ለንግድ እንቅስቃሴ እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ ነው።
“የቆጠሩት እህል አያልቅም” እንደሚባለው የሀገርን የሰው ኃይል በዕውቀት ሳያደራጁ ዘላቂ ስኬትን ማሰብ አይቻልም። በመሆኑም በ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ 5 ሚሊዮን ዜጎች የዲጂታል ክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚረከቡ ባለሙያዎችን ለማፍራት የተጣለ ታላቅ መሠረት ነው።
የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን በሁሉም አካባቢዎች እየተገነባ ያለው “የመሶብ” የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የተንዛዛ ቢሮክራሲን እና የዜጎችን እንግልት በማስቀረት የመንግሥትን ግልጽነት እና ተጠያቂነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። ይህ ዓይነቱ አሠራር ሙስና እና ብክነትን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል አስተማማኝ ተቋማዊ አቅም ይፈጥራል።
በፋይናንስ ዘርፍም ቢሆን በ2017 በጀት ዓመት ብቻ በዲጂታል የተከናወነው የግብይት ዋጋ 16 ትሪሊዮን ብር መድረሱ የዲጂታል ኢኮኖሚው ምን ያህል ውጤታማ እና ተደራሽ እየሆነ ለመምጣቱ ሕያው ማሳያ ነው።
ይህ ስኬት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ አካታችነትን በተግባር አረጋግጧል።
ለወደፊቱም መሠረታዊ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ፕላትፎርሞች ተደራሽ ለማድረግ የታቀደው ዕቅድ የሀገራችንን የነገ ገጽታ በእጅጉ የሚቀይር ነው።
መንግሥት የሳይበር ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ እና የስታርትአፕ ሥነ ምኅዳርን በማጠናከር፣ የዲጂታል ሽግግር ሂደቱን አስተማማኝ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ እያደረገው ይገኛል።
በአጠቃላይ ይህ ታሪካዊ ጉዞ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያቀልል፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ እና የኢኮኖሚ ልማታችንን ከሕልም ወደ እውነት የለወጠ የጋራ ብሔራዊ ስኬታችን በመሆኑ ሁሉም አካላት ለስኬቱ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #5millioncoders #success #𝐃𝐢𝐠𝐢𝐭𝐚𝐥𝐄𝐜𝐨𝐧𝐨𝐦𝐲
2 months ago
የጸና ቃልኪዳን፤ በለውጥ ላይ ያለች ሀገር!
▸ የአፍሪካ ግዙፉ ግድብ፣
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ፣
▸ የ48+ ቢሊዮን ችግኞች ተከላ፤ ለተፈጥሮና ለሥነ-ምህዳር መታደስ
▸ ከተሞች ፈክተዋል፣ ገጠሮች እየዘመኑ ነው፣ መንገዶች፣ አረንጓዴ ልማትና ዘመናዊ መሠረተ-ልማቶች ተደራሽ እየሆኑ ነው
▸መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፦ ምቹና ከቢሮክራሲ የጸዳ የመንግሥት አገልግሎትን ለዜጎች ማድረስ
#pmoethiopia
Comments