3 months ago
የመኖሪያ ቤት እጥረትን ትርጉም ባለው መልኩ ለመቅረፍ ይሠራል፦ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን
**************
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ላለፉት ቀናት በድሬዳዋ ባካሄዳቸው የተለያዩ ደማቅ ዝግጅቶች የ50ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓሉን አጠቃልሏል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር፣ ኮርፖሬሽኑ የወርቅ እዮቤልዩውን ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በድሬዳዋ በተለያዩ መርሀ ግብሮች በማክበሩ አመስግነዋል።
ድሬዳዋ ከለውጡ ወዲህ ሰላምና አንድነቷን አስጠብቃ በማስቀጠል የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፋይዳ ያላቸው የልማት ሥራዎችን በማከናወን ላይ መሆኗን ገልጸዋል።
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በዚህ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አንስተዋል።
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የኮርፖሬት ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኃይለብርሃን ዜና፣ ኮርፖሬሽኑ ባለፉት 8 ዓመታት ዕድሜና ልምዱን የሚመጥኑ ውጤታማ ተግባራትን በማከናወን ገቢውን ከ30 እጥፍ በላይ አሳድጓል ብለዋል።
በቀጣይም አዳዲስ የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የመኖሪያ ቤት እጥረትን ትርጉም ባለው መልኩ ለመቅረፍ ይሠራል ብለዋል።
ኮርፖሬሽኑ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወጠነውን 1.5 ሚሊዮን ቤቶች የመገንባት ዕቅድ በውጤታማነት ለመተግበር በትኩረት እንደሚሠራም ተናግረዋል።
የኮርፖራሽኑ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ እውነቱ ወርቅነህ፣ ኮርፖሬሽኑ ካጋጠመው ውድቀት በመነሳት ባለፉት 8 ዓመታት ባከናወናቸው የለውጥ ሥራዎች የቤቶች ግንባታ ዘርፍ የልህቀት ማዕከል መሆን ችሏል ብለዋል።
ኮርፖሬሽኑ የወርቅ እዮቤልዩ በዓሉን ከአዲስ አበባ በመቀጠል ከግንቦት 10 እስከ 17 በድሬዳዋ በተለያዩ መርሐ ግብሮች ሲያከብር ቆይቶ ነው በዛሬው ዕለት አጠቃልሏል።
በቴዎድሮስ ታደሰ
#ethiopia #housingcorporation #50years #goldenjubilee #diredawa #ebc
**************
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ላለፉት ቀናት በድሬዳዋ ባካሄዳቸው የተለያዩ ደማቅ ዝግጅቶች የ50ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓሉን አጠቃልሏል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር፣ ኮርፖሬሽኑ የወርቅ እዮቤልዩውን ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በድሬዳዋ በተለያዩ መርሀ ግብሮች በማክበሩ አመስግነዋል።
ድሬዳዋ ከለውጡ ወዲህ ሰላምና አንድነቷን አስጠብቃ በማስቀጠል የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፋይዳ ያላቸው የልማት ሥራዎችን በማከናወን ላይ መሆኗን ገልጸዋል።
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በዚህ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አንስተዋል።
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የኮርፖሬት ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኃይለብርሃን ዜና፣ ኮርፖሬሽኑ ባለፉት 8 ዓመታት ዕድሜና ልምዱን የሚመጥኑ ውጤታማ ተግባራትን በማከናወን ገቢውን ከ30 እጥፍ በላይ አሳድጓል ብለዋል።
በቀጣይም አዳዲስ የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የመኖሪያ ቤት እጥረትን ትርጉም ባለው መልኩ ለመቅረፍ ይሠራል ብለዋል።
ኮርፖሬሽኑ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወጠነውን 1.5 ሚሊዮን ቤቶች የመገንባት ዕቅድ በውጤታማነት ለመተግበር በትኩረት እንደሚሠራም ተናግረዋል።
የኮርፖራሽኑ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ እውነቱ ወርቅነህ፣ ኮርፖሬሽኑ ካጋጠመው ውድቀት በመነሳት ባለፉት 8 ዓመታት ባከናወናቸው የለውጥ ሥራዎች የቤቶች ግንባታ ዘርፍ የልህቀት ማዕከል መሆን ችሏል ብለዋል።
ኮርፖሬሽኑ የወርቅ እዮቤልዩ በዓሉን ከአዲስ አበባ በመቀጠል ከግንቦት 10 እስከ 17 በድሬዳዋ በተለያዩ መርሐ ግብሮች ሲያከብር ቆይቶ ነው በዛሬው ዕለት አጠቃልሏል።
በቴዎድሮስ ታደሰ
#ethiopia #housingcorporation #50years #goldenjubilee #diredawa #ebc
4 months ago
የትንሳኤ በዓል አስመልክቶ የጸሎት መርሐ-ግብር ተዘጋጀ
📌 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ጸሎት ይደረጋል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል እና የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል በማስመልከት፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አማኞች የሚሳተፉበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በመጪው እሁድ ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስቴዲየም እንደሚያካሂድ በዛሬው ዕለት በይፋ አስታውቋል።
ይህ ታላቅ መድረክ ከሃይማኖታዊ ስነ-ሥርዓት ባለፈ፣ መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላምና በታማኝነት እንዲጠናቀቅ "የአደባባይ ጸሎት" የሚደረግበት ልዩ ሀገራዊ መርሃ-ግብር እንደሆነም በሰፊው ተገልጿል።
ህብረቱ በ1968 ዓ.ም በአዳማ ከተማ የመጀመሪያውን ጉባኤ ካካሄደበት ጊዜ አንስቶ ያለፈባቸውን አምስት አስርት ዓመታት ለመዘከር ልዩ ዝግጅቶችን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን፣ የዕለቱ ዝግጅትም የዚህ ታሪካዊ ጉዞና የኢዮቤልዩ በዓል አንድ አካል ተደርጎ ተወስዷል።
የህብረቱ ፕሬዝዳንት ፓስተር ደረጀ ታፈሰ እንደገለጹት፣ ዋናው የኢዮቤልዩ በዓል በሐምሌ ወር የሚከበር ቢሆንም፣ በትንሳኤ በዓል ዕለት የሚከናወነው ጉባኤ የህብረቱን ምስረታ የሚዘክሩ የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽኖች እና የታሪክ ምስክርነቶች የሚቀርቡበት ይሆናል።
ፓስተር ደረጀ ቤተክርስቲያን ለሀገር መረጋጋትና ለአንድነት ያላትን ኃላፊነት በይፋ እንደምትወጣ አረጋግጠው፣ በሃይማኖትና በብሔር ስም የሚነሱ የመለያየት አስተምህሮዎችን ህብረቱ በጽኑ እንደሚቃወም ገልጸዋል።
እውነተኛው የወንጌል አስተምህሮ ሰላምና ፍቅር እንጂ መቃቃር እንዳልሆነ በመጠቆም፣ በመጪው ምርጫ ዙሪያ አደባባይ ላይ የሚደረገው ጸሎት ለሀገር ትልቅ ሰላምን የሚያመጣ መሆኑን በንግግራቸው አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በተጨማሪም ህብረቱ "ትንሳኤና ሕይወት እኔ ነኝ" የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል መሪ በማድረግ፣ በዕለቱ የተቸገሩ ወገኖችን የመርዳትና የማዕድ ማጋራት መርሐ-ግብር አዘጋጅቷል። ይህ ማህበራዊ አገልግሎት ህብረቱ በየዓመቱ በታላላቅ በዓላት የሚያከናውነው ልማድ ሲሆን፣ ዘንድሮም በከፍተኛ ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተነግሯል።
ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስቴዲየም በሚካሄደው በዚህ ታላቅ መርሐ-ግብር ላይ፣ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አማኞች ተገኝተው የትንሳኤውን በዓል በጋራ እንዲያከብሩና ስለ ሀገር ሰላም እንዲጸልዩ ጥሪ ተላልፏል።
#ethiopia #easterinethiopia #evangelicalchurchesfellowship #nationalprayer #goldenjubilee #addisababastadium #peaceandunity #resurrectionpower
📌 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ጸሎት ይደረጋል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል እና የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል በማስመልከት፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አማኞች የሚሳተፉበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በመጪው እሁድ ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስቴዲየም እንደሚያካሂድ በዛሬው ዕለት በይፋ አስታውቋል።
ይህ ታላቅ መድረክ ከሃይማኖታዊ ስነ-ሥርዓት ባለፈ፣ መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላምና በታማኝነት እንዲጠናቀቅ "የአደባባይ ጸሎት" የሚደረግበት ልዩ ሀገራዊ መርሃ-ግብር እንደሆነም በሰፊው ተገልጿል።
ህብረቱ በ1968 ዓ.ም በአዳማ ከተማ የመጀመሪያውን ጉባኤ ካካሄደበት ጊዜ አንስቶ ያለፈባቸውን አምስት አስርት ዓመታት ለመዘከር ልዩ ዝግጅቶችን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን፣ የዕለቱ ዝግጅትም የዚህ ታሪካዊ ጉዞና የኢዮቤልዩ በዓል አንድ አካል ተደርጎ ተወስዷል።
የህብረቱ ፕሬዝዳንት ፓስተር ደረጀ ታፈሰ እንደገለጹት፣ ዋናው የኢዮቤልዩ በዓል በሐምሌ ወር የሚከበር ቢሆንም፣ በትንሳኤ በዓል ዕለት የሚከናወነው ጉባኤ የህብረቱን ምስረታ የሚዘክሩ የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽኖች እና የታሪክ ምስክርነቶች የሚቀርቡበት ይሆናል።
ፓስተር ደረጀ ቤተክርስቲያን ለሀገር መረጋጋትና ለአንድነት ያላትን ኃላፊነት በይፋ እንደምትወጣ አረጋግጠው፣ በሃይማኖትና በብሔር ስም የሚነሱ የመለያየት አስተምህሮዎችን ህብረቱ በጽኑ እንደሚቃወም ገልጸዋል።
እውነተኛው የወንጌል አስተምህሮ ሰላምና ፍቅር እንጂ መቃቃር እንዳልሆነ በመጠቆም፣ በመጪው ምርጫ ዙሪያ አደባባይ ላይ የሚደረገው ጸሎት ለሀገር ትልቅ ሰላምን የሚያመጣ መሆኑን በንግግራቸው አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በተጨማሪም ህብረቱ "ትንሳኤና ሕይወት እኔ ነኝ" የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል መሪ በማድረግ፣ በዕለቱ የተቸገሩ ወገኖችን የመርዳትና የማዕድ ማጋራት መርሐ-ግብር አዘጋጅቷል። ይህ ማህበራዊ አገልግሎት ህብረቱ በየዓመቱ በታላላቅ በዓላት የሚያከናውነው ልማድ ሲሆን፣ ዘንድሮም በከፍተኛ ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተነግሯል።
ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስቴዲየም በሚካሄደው በዚህ ታላቅ መርሐ-ግብር ላይ፣ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አማኞች ተገኝተው የትንሳኤውን በዓል በጋራ እንዲያከብሩና ስለ ሀገር ሰላም እንዲጸልዩ ጥሪ ተላልፏል።
#ethiopia #easterinethiopia #evangelicalchurchesfellowship #nationalprayer #goldenjubilee #addisababastadium #peaceandunity #resurrectionpower
4 months ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የወርቅ ኢዮቤልዩ ተጠናቀቀ፤
የቤት አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት ቃል ተገባ
#ethiopia | ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ምስረታ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ዛሬ በማጠቃለያ መድረክና ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል።
በኮርፖሬሽኑ የተገነቡ አዳዲስ ሕንጻዎች የተመረቁ ሲሆን፣ የተቋሙን የሪፎርም ስኬት የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ክፍት ሆኖ ቆይቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በቀጣይ ዓመታት የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሰፋፊ ዕቅዶች ተይዘዋል።
ዕውቅና፦ ለተቋሙ ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞና ለተመዘገቡ ስኬቶች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ልዩ ዕውቅና ተሰጥቷል።
ዶ/ር ረሻድ ተቋሙ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመው፣ የቤት ፍላጎት የሰው ልጅ መሠረታዊ መብት በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #federalhousingcorporation #goldenjubilee #housingethiopia #drreshadkemal #realestateethiopia #urbandevelopment #addisababa #ethiopianews #የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ወርቅኢዮቤልዩ #ቤትልማት #ሪልስቴት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የቤት አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት ቃል ተገባ
#ethiopia | ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ምስረታ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ዛሬ በማጠቃለያ መድረክና ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል።
በኮርፖሬሽኑ የተገነቡ አዳዲስ ሕንጻዎች የተመረቁ ሲሆን፣ የተቋሙን የሪፎርም ስኬት የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ክፍት ሆኖ ቆይቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በቀጣይ ዓመታት የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሰፋፊ ዕቅዶች ተይዘዋል።
ዕውቅና፦ ለተቋሙ ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞና ለተመዘገቡ ስኬቶች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ልዩ ዕውቅና ተሰጥቷል።
ዶ/ር ረሻድ ተቋሙ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመው፣ የቤት ፍላጎት የሰው ልጅ መሠረታዊ መብት በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #federalhousingcorporation #goldenjubilee #housingethiopia #drreshadkemal #realestateethiopia #urbandevelopment #addisababa #ethiopianews #የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ወርቅኢዮቤልዩ #ቤትልማት #ሪልስቴት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ
ከውድቀት ስጋት ወደ ከፍታ!
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል ሰዒድ ለተቋሙ 50ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ባስተላለፉት መልዕክት፣ ተቋሙ ካለበት የመክሰም አፋፍ ወጥቶ አሁን ላይ ለሀገር ተምሳሌት የሚሆን ስኬት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ሲኤምሲ (CMC) ያሉ ዘመናዊ መንደሮችን በመገንባት ለከተማዋ ውበትና እድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከተበት ወቅት።
የመቀጨጭ ዘመን (1980ዎቹ - 2010)፦ ለ28 ዓመታት ያህል ተቋሙ ትኩረት ተነፍጎት፣ ከቤት ግንባታ ርቆ እስከ መክሰም አፋፍ ደርሶ የነበረበት ፈታኝ ጊዜ።
የዳግም ልደት ዘመን (ከ2010 ወዲህ)፦ በአገራዊ ለውጡና በተቋማዊ ሪፎርም ታግዞ፣ የተቋሙ ገቢ በ30 እጥፍ እንዲያድግ የተደረገበትና ስኬት የነገሰበት ወቅት።
ኮርፖሬሽኑ አሁን ላይ "ቤት ከመገንባት ወደ ማምረት" ተሸጋግሯል፦
3D ኮንክሪት ፕሪንቲንግ፦ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ዘመናዊ የቤት ግንባታ ቴክኖሎጂን አስተዋውቋል።
የጣሊያኑን የፕሪካስት ፋብሪካ ተከላ በማጠናቀቅ የግንባታ ፍጥነትን ለማሳደግ ተዘጋጅቷል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን የ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታ ዕቅድ ለማሳካት ለሠራተኞች፣ ለመካከለኛ ገቢ ላላቸው ዜጎችና ለዳያስፖራው ጥራት ያላቸው ቤቶችን ለማቅረብ እየሰራ ይገኛል።
🙏 የምስጋና መልዕክት
"የሀገራችን ብልጽግና አይቀሬ ነው፣ ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ተምሳሌታዊ አገር የመሆን ጥረቷ እውን ይሆናል፡፡"
— ዶ/ር ረሻድ ከማል
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለተቋሙ ሰራተኞች፣ ለደጋፊዎችና ለሀገር መሪዎች ምስጋናቸውን እያቀረቡ፣ ለቀጣዩ አገራዊ ኃላፊነት ሁሉም እንዲተጋ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#ethiopia #federalhousingcorporation #fhc50years #goldenjubilee #housingdevelopment #urbanbeauty #innovation InConstruction #drreshadkemal #ethiopianprosperity #buildingthefuture
ከውድቀት ስጋት ወደ ከፍታ!
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል ሰዒድ ለተቋሙ 50ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ባስተላለፉት መልዕክት፣ ተቋሙ ካለበት የመክሰም አፋፍ ወጥቶ አሁን ላይ ለሀገር ተምሳሌት የሚሆን ስኬት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ሲኤምሲ (CMC) ያሉ ዘመናዊ መንደሮችን በመገንባት ለከተማዋ ውበትና እድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከተበት ወቅት።
የመቀጨጭ ዘመን (1980ዎቹ - 2010)፦ ለ28 ዓመታት ያህል ተቋሙ ትኩረት ተነፍጎት፣ ከቤት ግንባታ ርቆ እስከ መክሰም አፋፍ ደርሶ የነበረበት ፈታኝ ጊዜ።
የዳግም ልደት ዘመን (ከ2010 ወዲህ)፦ በአገራዊ ለውጡና በተቋማዊ ሪፎርም ታግዞ፣ የተቋሙ ገቢ በ30 እጥፍ እንዲያድግ የተደረገበትና ስኬት የነገሰበት ወቅት።
ኮርፖሬሽኑ አሁን ላይ "ቤት ከመገንባት ወደ ማምረት" ተሸጋግሯል፦
3D ኮንክሪት ፕሪንቲንግ፦ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ዘመናዊ የቤት ግንባታ ቴክኖሎጂን አስተዋውቋል።
የጣሊያኑን የፕሪካስት ፋብሪካ ተከላ በማጠናቀቅ የግንባታ ፍጥነትን ለማሳደግ ተዘጋጅቷል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን የ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታ ዕቅድ ለማሳካት ለሠራተኞች፣ ለመካከለኛ ገቢ ላላቸው ዜጎችና ለዳያስፖራው ጥራት ያላቸው ቤቶችን ለማቅረብ እየሰራ ይገኛል።
🙏 የምስጋና መልዕክት
"የሀገራችን ብልጽግና አይቀሬ ነው፣ ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ተምሳሌታዊ አገር የመሆን ጥረቷ እውን ይሆናል፡፡"
— ዶ/ር ረሻድ ከማል
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለተቋሙ ሰራተኞች፣ ለደጋፊዎችና ለሀገር መሪዎች ምስጋናቸውን እያቀረቡ፣ ለቀጣዩ አገራዊ ኃላፊነት ሁሉም እንዲተጋ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#ethiopia #federalhousingcorporation #fhc50years #goldenjubilee #housingdevelopment #urbanbeauty #innovation InConstruction #drreshadkemal #ethiopianprosperity #buildingthefuture
Comments