Logo
Getu Temesgen
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የወርቅ ኢዮቤልዩ ተጠናቀቀ፤
የቤት አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት ቃል ተገባ
#ethiopia | ​ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ምስረታ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ዛሬ በማጠቃለያ መድረክና ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል።

​በኮርፖሬሽኑ የተገነቡ አዳዲስ ሕንጻዎች የተመረቁ ሲሆን፣ የተቋሙን የሪፎርም ስኬት የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ክፍት ሆኖ ቆይቷል።

​ዋና ሥራ አስፈጻሚው ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በቀጣይ ዓመታት የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሰፋፊ ዕቅዶች ተይዘዋል።
​ዕውቅና፦ ለተቋሙ ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞና ለተመዘገቡ ስኬቶች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ልዩ ዕውቅና ተሰጥቷል።

ዶ/ር ረሻድ ተቋሙ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመው፣ የቤት ፍላጎት የሰው ልጅ መሠረታዊ መብት በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።

​#getu #federalhousingcorporation #goldenjubilee #housingethiopia #drreshadkemal #realestateethiopia #urbandevelopment #addisababa #ethiopianews #የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ወርቅኢዮቤልዩ #ቤትልማት #ሪልስቴት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen

2 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.