2 hours ago
2 days ago
በኮንታ ዞን ሙሉ በሙሉ ተፈጥሯዊነቱን የጠበቀ አዲስ የጫካ ቡና መገኘቱ ተበሰረ!
#fastmereja :-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚገኘው ታሪካዊው ኮንታ ዞን፣ እስከ ዛሬ በሰው እጅ ያልተነካና ተፈጥሮአዊ ይዘቱን ሙሉ በሙሉ ጠብቆ የቆየ አዲስ የጫካ ቡና (Wild Forest Coffee) ተበሰረ።
ይህ በሰው እጅ ያልተተከለና «ያልተመነዘረ አረንጓዴ ወርቅ» የተባለው አዲስ የቡና ዘር የተገኘው፣ በኮንታ ዞን «ኦሽካ ዴንቻ» ጥቅጥቅ ጫካ ውስጥ በሚገኘው «አሜክ ኤጄቻ» በተሰኘ ልዩ ቦታ ላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን አካባቢው ሰውና የዱር እንስሳት በተስማማ ሁኔታ የሚኖሩበት በመሆኑ፣ የቡናው ተፈጥሯዊ መዓዛና ጣዕም እጅግ ልዩ እንደሆነ ተገልጿል።
ድርጅቱ አዲሱ የቡና ዘር መገኘቱ ለሀገራችን አዲስ ዓለም አቀፍ ብራንድ ይዞ የሚመጣ መሆኑን ጠቁሞ፤ እንደ ጅማ፣ ይርጋጨፌ እና ሐረር ሁሉ «Konta Coffee» በሚል ስም ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ በመቅረብ፣ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ብሏል።
በተጨማሪም ያልተነካውን የኮንታ የተፈጥሮ ጫካ እና የቡና መገኛ ቦታዎችን ለዓለም በማስተዋወቅ የኢኮ-ቱሪዝም ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያነቃቃው ገልጿል።
የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ አቀንቃኝና የባህል አምባሳደር አርቲስት ወንድወሰን አበበ (ወንዴ ኮንታ) በበኩሉ፣ “«ኑ ቡና ጠጡ» የሚለው ጥሪ የቡና መጠጣት ሥነ-ሥርዓት ብቻ ሳይሆን የሰላም፣ የፍቅር፣ የጽኑ ጉርብትና እና የኢትዮጵያዊነት መስተጋብር ማሳያ ነው” ሲል ተናግሯል።
አርቲስቱ አክሎም ይህንን ውድ ተፈጥሮአዊ ሀብት ጠብቆ ላቆየው ማኅበረሰብ እውቅና መስጠትና ባህሉን ከኪነ-ጥበብ ጋር አዋህዶ ማቅረብ ታሪካዊ ኃላፊነት መሆኑን አብራርቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ ለዕይታ ያልበቁና በምስል ያልተቀረፁ የባህል ትውፊቶችን ቅርፃቸውን እንደጠበቁ ለዓለም መድረክ ለማብቃት ሰፊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገልጿል።
ይህንን ታሪካዊ ግኝት አስመልክቶ «ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም» (Konta Coffee) በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አዲሱን የጫካ ቡና ይፋ ለማድረግ "ኑ ቡና ጠጡ" የተሰኘ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪና የመርሃ ግብር ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
በዚሁ መሠረት ቶካ ፊልም መንደር ከ«ኪን-ኢትዮጵያ የባህል ቡድን» እና ከ«ቤራ ኢንተርቴይንመንትና ኤቨንትስ» ጋር የጋራ የሥራ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ በቅርቡም በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
#fastmereja :-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚገኘው ታሪካዊው ኮንታ ዞን፣ እስከ ዛሬ በሰው እጅ ያልተነካና ተፈጥሮአዊ ይዘቱን ሙሉ በሙሉ ጠብቆ የቆየ አዲስ የጫካ ቡና (Wild Forest Coffee) ተበሰረ።
ይህ በሰው እጅ ያልተተከለና «ያልተመነዘረ አረንጓዴ ወርቅ» የተባለው አዲስ የቡና ዘር የተገኘው፣ በኮንታ ዞን «ኦሽካ ዴንቻ» ጥቅጥቅ ጫካ ውስጥ በሚገኘው «አሜክ ኤጄቻ» በተሰኘ ልዩ ቦታ ላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን አካባቢው ሰውና የዱር እንስሳት በተስማማ ሁኔታ የሚኖሩበት በመሆኑ፣ የቡናው ተፈጥሯዊ መዓዛና ጣዕም እጅግ ልዩ እንደሆነ ተገልጿል።
ድርጅቱ አዲሱ የቡና ዘር መገኘቱ ለሀገራችን አዲስ ዓለም አቀፍ ብራንድ ይዞ የሚመጣ መሆኑን ጠቁሞ፤ እንደ ጅማ፣ ይርጋጨፌ እና ሐረር ሁሉ «Konta Coffee» በሚል ስም ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ በመቅረብ፣ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ብሏል።
በተጨማሪም ያልተነካውን የኮንታ የተፈጥሮ ጫካ እና የቡና መገኛ ቦታዎችን ለዓለም በማስተዋወቅ የኢኮ-ቱሪዝም ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያነቃቃው ገልጿል።
የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ አቀንቃኝና የባህል አምባሳደር አርቲስት ወንድወሰን አበበ (ወንዴ ኮንታ) በበኩሉ፣ “«ኑ ቡና ጠጡ» የሚለው ጥሪ የቡና መጠጣት ሥነ-ሥርዓት ብቻ ሳይሆን የሰላም፣ የፍቅር፣ የጽኑ ጉርብትና እና የኢትዮጵያዊነት መስተጋብር ማሳያ ነው” ሲል ተናግሯል።
አርቲስቱ አክሎም ይህንን ውድ ተፈጥሮአዊ ሀብት ጠብቆ ላቆየው ማኅበረሰብ እውቅና መስጠትና ባህሉን ከኪነ-ጥበብ ጋር አዋህዶ ማቅረብ ታሪካዊ ኃላፊነት መሆኑን አብራርቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ ለዕይታ ያልበቁና በምስል ያልተቀረፁ የባህል ትውፊቶችን ቅርፃቸውን እንደጠበቁ ለዓለም መድረክ ለማብቃት ሰፊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገልጿል።
ይህንን ታሪካዊ ግኝት አስመልክቶ «ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም» (Konta Coffee) በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አዲሱን የጫካ ቡና ይፋ ለማድረግ "ኑ ቡና ጠጡ" የተሰኘ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪና የመርሃ ግብር ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
በዚሁ መሠረት ቶካ ፊልም መንደር ከ«ኪን-ኢትዮጵያ የባህል ቡድን» እና ከ«ቤራ ኢንተርቴይንመንትና ኤቨንትስ» ጋር የጋራ የሥራ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ በቅርቡም በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
2 days ago
"ኑ ቡና ጠጡ" ተብላቹኋል
* በኮንታ ዞን አዲስ የተፈጥሮ የጫካ ቡና መገኘቱን ይፋ ተደረገ
#ethiopia | በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በሚገኘው በታሪካዊው ኮንታ ዞን እስከ ዛሬ በሰው እጅ ያልተነካና ተፈጥሮአዊነቱን ፍጹም ጠብቆ የቆየ አዲስ የተፈጥሮ ጫካ ቡና መገኘቱ ተበሰረ።
በኮንታ ዞን ጥቁርና ጥቅጥቅ ባለው «አሜክ ኤጄቻ» ጫካ ውስጥ የተገኘው የቡና ዘር የሀገራችንን የቡና ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የሚያስጀምር መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ታሪካዊ ግኝት አስመልክቶ «ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም» (Konta Coffee) በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አዲሱን የጫካ ቡና ይፋ ለማድረግ "ኑ ቡና ጠጡ" የተሰኘ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪና የመርሃ ግብር ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
ድርጅቱ አዲሱ የቡና ዘር መገኘቱ ለሀገራችን አዲስ ዓለም አቀፍ ብራንድ ይዞ የሚመጣ መሆኑን ገልጿል።
እንደ ጅማ ይርጋጨፌ እና ሐረር ሁሉ «Konta Coffee» በሚል ስም ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ በመቅረብ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል።
ያልተነካውን የኮንታ የተፈጥሮ ጫካ እና የቡና መገኛ ቦታዎችን ለዓለም በማስተዋወቅ የዘርፉን ቱሪዝም በከፍተኛ ሁኔታ ያነቃቃዋል ብሏል።
የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ አቀንቃኝና የባህል አምባሳደር አርቲስት ወንዴ ኮንታ እንዳለው "ኑ ቡና ጠጡ" የሚለው ጥሪ የቡና መጠጣት ሥነ-ሥርዓት ብቻ ሳይሆን የሰላም የፍቅር የጽኑ ጉርብትና እና የኢትዮጵያዊነት መስተጋብር ማሳያ ነው ።
ይህንን ውድ ተፈጥሮአዊ ሀብት ጠብቆ ላቆየው ማኅበረሰብ እውቅና መስጠትና ባህሉን ከኪነ ጥበብ ጋር አዋህዶ ማቅረብ ታሪካዊ ኃላፊነት ነው" ሲል ተናግሯል ።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ለዕይታ ያልበቁ የባህል ትውፊቶችን ለዓለም ለማስተዋወቅ ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም ከኢትዮጵያ የባህል ቡድን እና ከቤራ ኢንተርቴይንመንት ጋር የጋራ የሥራ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #discoverethiopia #kontacoffee #nubunatetu #ethiopiancoffee #wendekonta
* በኮንታ ዞን አዲስ የተፈጥሮ የጫካ ቡና መገኘቱን ይፋ ተደረገ
#ethiopia | በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በሚገኘው በታሪካዊው ኮንታ ዞን እስከ ዛሬ በሰው እጅ ያልተነካና ተፈጥሮአዊነቱን ፍጹም ጠብቆ የቆየ አዲስ የተፈጥሮ ጫካ ቡና መገኘቱ ተበሰረ።
በኮንታ ዞን ጥቁርና ጥቅጥቅ ባለው «አሜክ ኤጄቻ» ጫካ ውስጥ የተገኘው የቡና ዘር የሀገራችንን የቡና ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የሚያስጀምር መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ታሪካዊ ግኝት አስመልክቶ «ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም» (Konta Coffee) በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አዲሱን የጫካ ቡና ይፋ ለማድረግ "ኑ ቡና ጠጡ" የተሰኘ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪና የመርሃ ግብር ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
ድርጅቱ አዲሱ የቡና ዘር መገኘቱ ለሀገራችን አዲስ ዓለም አቀፍ ብራንድ ይዞ የሚመጣ መሆኑን ገልጿል።
እንደ ጅማ ይርጋጨፌ እና ሐረር ሁሉ «Konta Coffee» በሚል ስም ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ በመቅረብ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል።
ያልተነካውን የኮንታ የተፈጥሮ ጫካ እና የቡና መገኛ ቦታዎችን ለዓለም በማስተዋወቅ የዘርፉን ቱሪዝም በከፍተኛ ሁኔታ ያነቃቃዋል ብሏል።
የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ አቀንቃኝና የባህል አምባሳደር አርቲስት ወንዴ ኮንታ እንዳለው "ኑ ቡና ጠጡ" የሚለው ጥሪ የቡና መጠጣት ሥነ-ሥርዓት ብቻ ሳይሆን የሰላም የፍቅር የጽኑ ጉርብትና እና የኢትዮጵያዊነት መስተጋብር ማሳያ ነው ።
ይህንን ውድ ተፈጥሮአዊ ሀብት ጠብቆ ላቆየው ማኅበረሰብ እውቅና መስጠትና ባህሉን ከኪነ ጥበብ ጋር አዋህዶ ማቅረብ ታሪካዊ ኃላፊነት ነው" ሲል ተናግሯል ።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ለዕይታ ያልበቁ የባህል ትውፊቶችን ለዓለም ለማስተዋወቅ ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም ከኢትዮጵያ የባህል ቡድን እና ከቤራ ኢንተርቴይንመንት ጋር የጋራ የሥራ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #discoverethiopia #kontacoffee #nubunatetu #ethiopiancoffee #wendekonta
2 days ago
በቀሃ ፊልምስ ተዘጋጅቶ የቀረበው የሰርክአዲስ መጋቢያው '' መቀነት '' አዲስ ፊልም ከነገ ጀምሮ በአለም ሲኒማ ብቻ ቦሌ እና መገናኛ መታየት ይጀምራል ።
በመቀነት የታሰረ ህመም፡፡
አንድ መቀነት ሁለትእውነታ!
#qehafilms
serkadis_m qeha_films solina_desta energy_film_production selamawit_mare adiam_shemelis official_tamirat_belete dagne_art yosephbazezew @_.raphuuuuuuu._ official_samuel_tilahun abrham_gizat absun47 endegena_demeke mish_kassa haileabebaw_densa wubete_takele habtamu_mulat1 henok_baba
በመቀነት የታሰረ ህመም፡፡
አንድ መቀነት ሁለትእውነታ!
#qehafilms
serkadis_m qeha_films solina_desta energy_film_production selamawit_mare adiam_shemelis official_tamirat_belete dagne_art yosephbazezew @_.raphuuuuuuu._ official_samuel_tilahun abrham_gizat absun47 endegena_demeke mish_kassa haileabebaw_densa wubete_takele habtamu_mulat1 henok_baba
2 days ago
በቀሃ ፊልምስ ተዘጋጅቶ የቀረበው የሰርክአዲስ መጋቢያው '' መቀነት '' አዲስ ፊልም ከነገ ጀምሮ በአለም ሲኒማ ብቻ ቦሌ እና መገናኛ መታየት ይጀምራል ።
በመቀነት የታሰረ ህመም፡፡
አንድ መቀነት ሁለትእውነታ!
#qehafilms
serkadis_m qeha_films solina_desta energy_film_production selamawit_mare adiam_shemelis official_tamirat_belete dagne_art yosephbazezew @_.raphuuuuuuu._ official_samuel_tilahun abrham_gizat absun47 endegena_demeke mish_kassa haileabebaw_densa wubete_takele habtamu_mulat1 henok_baba
በመቀነት የታሰረ ህመም፡፡
አንድ መቀነት ሁለትእውነታ!
#qehafilms
serkadis_m qeha_films solina_desta energy_film_production selamawit_mare adiam_shemelis official_tamirat_belete dagne_art yosephbazezew @_.raphuuuuuuu._ official_samuel_tilahun abrham_gizat absun47 endegena_demeke mish_kassa haileabebaw_densa wubete_takele habtamu_mulat1 henok_baba
2 days ago
ቴሌቲቪ አዳዲስ ሀገርኛ ፊልሞችን ይዞ መጣ!
ቴሌቲቪ ተመርቆ ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ድንቅ እና የተመረጡ የሀገራችንን የአማርኛ ፊልሞች ለተመልካች ሲያቀርብ መቆየቱ ይታወቃል። አሁንም በተመሳሳይ አዳዲስ እና አዝናኝ ፊልሞችን በመተግበሪያው (App) ላይ ይዞላችሁ መጥቷል።
በዚህም መሠረት «ዲያስፖራው» እና «ሹምሽረት» የተሰኙት አዳዲስ ፊልሞች ሐሙስ መጋቢት 30 ቀን ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በቴሌቲቪ መተግበሪያ ላይ መታየት ይጀምራሉ።
ዲያስፋራው
የሮማንቲክ ኮሜዲ ዘውግ ያለው «ዲያስፖራው» ፊልም፣ ተወዳጁ ተዋናይ አለምሰገድ ተስፋዬ ከ6 ዓመታት ቆይታ በኋላ የተወነበት ድንቅ ሥራ ነው። በተጨማሪም በበርካታ ፊልሞቿ የምናደንቃት ተዋናይት ማክዳ አፈወርቅ ከ10 ዓመታት በኋላ ወደ ፊልም ኢንዱስትሪው የተመለሰችበት ሲሆን፤ ታዋቂዋ ቲክቶከር ባምቢ ሀበሻ (ሐና ግደይ) ለመጀመሪያ ጊዜ የሠራችበት እንዲሁም ተሻለ ወርቁ እና ሌሎችም ተዋንያን የተሳተፉበት አዝናኝ ፊልም ነው። በተጨማሪም በሲኒማ ቆይታውም ከ6 ወር በላይ በመታየት ሪከርድ መስበር የቻለ ተወዳጅ ፊልም ነው።
ሹምሽረት
በወንዶች ጉዳይና በሌሎች በርካታ ፊልሞች ተወዳጅነትን ያተረፈው ተዋናይ አድማሱ ከበደ ፈታኝና ጥሩ የታሪክ ፍሰት ያለው ስክሪፕት በማጣቱ ምክንያት ከሲኒማው ለረጅም ጊዜ ርቆ ከቆየ በኋላ፣ በቅርቡ በዩልያን ተክለማርያም ተደርሶ በተዘጋጀው “ሹም ሽረት” በተሰኘው አዲስ ፊልም ወደ ፊልም ተመልሷል። በዚህ ፊልም ላይ አንጋፋዋ ተዋናይት ፍቅርተ ደሳለኝ በተለየ ገጸ-ባህሪ የተሳተፈች ሲሆን፣ በተጨማሪም ማስተዋል ወንደሰን እና ሌሎችም ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል።
እነዚህን 2 ፊልሞች ሐሙስ ዕለት በቴሌቲቪ መተግበሪያ ጠብቋቸው!
ቴሌቲቪን ለማውረድ
https://teletv.et/download
ቴሌቲቪ ተመርቆ ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ድንቅ እና የተመረጡ የሀገራችንን የአማርኛ ፊልሞች ለተመልካች ሲያቀርብ መቆየቱ ይታወቃል። አሁንም በተመሳሳይ አዳዲስ እና አዝናኝ ፊልሞችን በመተግበሪያው (App) ላይ ይዞላችሁ መጥቷል።
በዚህም መሠረት «ዲያስፖራው» እና «ሹምሽረት» የተሰኙት አዳዲስ ፊልሞች ሐሙስ መጋቢት 30 ቀን ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በቴሌቲቪ መተግበሪያ ላይ መታየት ይጀምራሉ።
ዲያስፋራው
የሮማንቲክ ኮሜዲ ዘውግ ያለው «ዲያስፖራው» ፊልም፣ ተወዳጁ ተዋናይ አለምሰገድ ተስፋዬ ከ6 ዓመታት ቆይታ በኋላ የተወነበት ድንቅ ሥራ ነው። በተጨማሪም በበርካታ ፊልሞቿ የምናደንቃት ተዋናይት ማክዳ አፈወርቅ ከ10 ዓመታት በኋላ ወደ ፊልም ኢንዱስትሪው የተመለሰችበት ሲሆን፤ ታዋቂዋ ቲክቶከር ባምቢ ሀበሻ (ሐና ግደይ) ለመጀመሪያ ጊዜ የሠራችበት እንዲሁም ተሻለ ወርቁ እና ሌሎችም ተዋንያን የተሳተፉበት አዝናኝ ፊልም ነው። በተጨማሪም በሲኒማ ቆይታውም ከ6 ወር በላይ በመታየት ሪከርድ መስበር የቻለ ተወዳጅ ፊልም ነው።
ሹምሽረት
በወንዶች ጉዳይና በሌሎች በርካታ ፊልሞች ተወዳጅነትን ያተረፈው ተዋናይ አድማሱ ከበደ ፈታኝና ጥሩ የታሪክ ፍሰት ያለው ስክሪፕት በማጣቱ ምክንያት ከሲኒማው ለረጅም ጊዜ ርቆ ከቆየ በኋላ፣ በቅርቡ በዩልያን ተክለማርያም ተደርሶ በተዘጋጀው “ሹም ሽረት” በተሰኘው አዲስ ፊልም ወደ ፊልም ተመልሷል። በዚህ ፊልም ላይ አንጋፋዋ ተዋናይት ፍቅርተ ደሳለኝ በተለየ ገጸ-ባህሪ የተሳተፈች ሲሆን፣ በተጨማሪም ማስተዋል ወንደሰን እና ሌሎችም ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል።
እነዚህን 2 ፊልሞች ሐሙስ ዕለት በቴሌቲቪ መተግበሪያ ጠብቋቸው!
ቴሌቲቪን ለማውረድ
https://teletv.et/download
Sponsored by
Surafel
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ቤርናርዶ ሲልቫን ስንመለከት እግር ኳስ ተጫዋች ሳይሆን፣ የታሸን የጥበብ መጻሕፍትን በፀጥታ የሚያነብ አርክቴክት (የኪነ-ህንፃ ባለሙያ) ነው የሚመስለው።
ለዓይን የማይጮሁ ቀለል ያሉ ቲሸርቶች፣ የሊነን አልባሳት፣ ሰፋፊ ሱሪዎች፣ የበርከንስቶክ ጫማዎች እና ከክር የተሰሩ ፖሎ ሹራቦች፤ አካላዊ ገጽታውም ሆነ አለባበሱ አንዳችም ትኩረትን አይሻም።
እንደ እውነቱ ከሆነ አእምሮው የተገራ አማካይ የግድ እንደ ፊልም ኮከብ መታየት አያስፈልገውም። በሜዳ ላይ ሁሉም ነገር በከፍተኛ ፍጥነት በሚምዘገዘግበት እና ውጥረት በነገሰበት ፍልሚያ ውስጥ፣ በእርጋታ እና በሰከነ መንፈስ ማሰብ የሚችል መሪ መሆን ብቻ በቂው ነው።
ልዩ የፈጠራ አቅም... ጥልቅ ብስለት... አስገራሚ ትዕግስት... እና ረቂቅ ስሜት!
ቤርናርዶ ሲልቫ ልክ እንደ አለባበሱ ነው የሚጫወተው። በሜዳ ላይ ታላላቅ እና ወሳኝ ነገሮች በዙሪያው እንዲከናወኑ ያደርጋል እንጂ፣ እሱ ራሱ የሁሉ ነገር ማዕከል ሆኖ ጎልቶ ለመታየት አይሞክርም። አለባበሱም፣ አጨዋወቱም — የፍፁም እርጋታ እና የጥበብ መገለጫ ነው!
ለዓይን የማይጮሁ ቀለል ያሉ ቲሸርቶች፣ የሊነን አልባሳት፣ ሰፋፊ ሱሪዎች፣ የበርከንስቶክ ጫማዎች እና ከክር የተሰሩ ፖሎ ሹራቦች፤ አካላዊ ገጽታውም ሆነ አለባበሱ አንዳችም ትኩረትን አይሻም።
እንደ እውነቱ ከሆነ አእምሮው የተገራ አማካይ የግድ እንደ ፊልም ኮከብ መታየት አያስፈልገውም። በሜዳ ላይ ሁሉም ነገር በከፍተኛ ፍጥነት በሚምዘገዘግበት እና ውጥረት በነገሰበት ፍልሚያ ውስጥ፣ በእርጋታ እና በሰከነ መንፈስ ማሰብ የሚችል መሪ መሆን ብቻ በቂው ነው።
ልዩ የፈጠራ አቅም... ጥልቅ ብስለት... አስገራሚ ትዕግስት... እና ረቂቅ ስሜት!
ቤርናርዶ ሲልቫ ልክ እንደ አለባበሱ ነው የሚጫወተው። በሜዳ ላይ ታላላቅ እና ወሳኝ ነገሮች በዙሪያው እንዲከናወኑ ያደርጋል እንጂ፣ እሱ ራሱ የሁሉ ነገር ማዕከል ሆኖ ጎልቶ ለመታየት አይሞክርም። አለባበሱም፣ አጨዋወቱም — የፍፁም እርጋታ እና የጥበብ መገለጫ ነው!
4 days ago
"Why Are You Not Here?"
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአማዞን ፕራይም ቪዲዮ ፕሪሚየር!
#ethiopia | "Why Are You Not Here?" የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ የቴሌቪዥን ተከታታይ ሲሪዝ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ ይመረቃል።
ይህ በአማዞን ፕራይም ቪዲዮ ለዓለም አቀፍ ተመልካቾች የሚቀርበው ሥራ፣ የኢትዮጵያን ውበት፣ ባህል፣ ቅርስ እና የሕዝቧን እንግዳ ተቀባይነት በልዩ መንገድ ያሳያል።
ታሪኩ ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ አፍሪካዊ-አሜሪካዊ ገጣሚ በሀገሪቱ፣ በባህሏ፣ በቅርሶቿ እና በሕዝቧ ፍቅር እንዴት እንደተማረከ የሚተርክ ነው።
በምርቃቱ ላይ ሲገኙ
✅ በነፃ ይታደማሉ
✅ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ይጎበኛሉ
✅ ከአገር ውስጥና ከውጭ እንግዶች ጋር የመተዋወቅ ዕድል ያገኛሉ
ቦታ: ዓድዋ ድል መታሰቢያ
ቅዳሜ፣ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. (August 8, 2026)
ከቀኑ 9:00 (3:00 PM) ሰዓት
መግቢያ: በነፃ
ቀድመው ይመዝገቡ: EthiopianRSVP.com
ቦታዎን አሁኑኑ ያስይዙ፤ ይህን ልዩ የፊልም ምርቃት እንዳያመልጥዎ ለወዳጆችዎም ያጋሩ!
#whyareyounothere #amazonprimevideo #moviepremiere #visitethiopia #addisababa #ethiopiancinema #getutemesgen #ጌጡተመስገን
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአማዞን ፕራይም ቪዲዮ ፕሪሚየር!
#ethiopia | "Why Are You Not Here?" የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ የቴሌቪዥን ተከታታይ ሲሪዝ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ ይመረቃል።
ይህ በአማዞን ፕራይም ቪዲዮ ለዓለም አቀፍ ተመልካቾች የሚቀርበው ሥራ፣ የኢትዮጵያን ውበት፣ ባህል፣ ቅርስ እና የሕዝቧን እንግዳ ተቀባይነት በልዩ መንገድ ያሳያል።
ታሪኩ ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ አፍሪካዊ-አሜሪካዊ ገጣሚ በሀገሪቱ፣ በባህሏ፣ በቅርሶቿ እና በሕዝቧ ፍቅር እንዴት እንደተማረከ የሚተርክ ነው።
በምርቃቱ ላይ ሲገኙ
✅ በነፃ ይታደማሉ
✅ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ይጎበኛሉ
✅ ከአገር ውስጥና ከውጭ እንግዶች ጋር የመተዋወቅ ዕድል ያገኛሉ
ቦታ: ዓድዋ ድል መታሰቢያ
ቅዳሜ፣ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. (August 8, 2026)
ከቀኑ 9:00 (3:00 PM) ሰዓት
መግቢያ: በነፃ
ቀድመው ይመዝገቡ: EthiopianRSVP.com
ቦታዎን አሁኑኑ ያስይዙ፤ ይህን ልዩ የፊልም ምርቃት እንዳያመልጥዎ ለወዳጆችዎም ያጋሩ!
#whyareyounothere #amazonprimevideo #moviepremiere #visitethiopia #addisababa #ethiopiancinema #getutemesgen #ጌጡተመስገን
4 days ago
በመሰልቸትም ይሁን እንዲሁ ተስፋ ቆርጬ ለአመታት የለፋውበትን ፊልም ለማውጣት ሰንፌ ነበር ። በተለይ ባለፉት ሁለትና ሶስት ወራቶች በገጠመኝ ሀዘን ምክኒያት ሁሉም ነገር ድብርብር ብሎኝ ነበር ። በሆነችዋ ምርጥዬ ቀን ግን የሰራነውን ፊልም ለማየት ከሸዊት ጋር ቀጠሮ ያዝን... ፊልሙን አይተን ከጨረስን በኃላ ሸዊት ያወራችኝ ነገር... ሁሉ ነገሬን ቀየረው ! ጥቂት ለማይባሉ ወራቶች አጥቼ የነበረውን ሞራል በአንዴ መለሰችው ..! እንደዛ ቀን ፊልሜን ጨርሶ ለማውጣት ሞራል ያገኘውበት ቀን የለም ።
ሸዊት ሚዲያ ላይ እንደምታወራው በጣም ቅን ሰው ናት ። የምታወራውን የምትኖር ፀዴ ሰው ናት ። ቅንነቷን ደግነቷን ደግሞ በነበረን የስራ ግኑኝነት ሁሉ አይቼዋለው ። ከልቧ ሰው ናት ። ሰዎች ሰርተው አጊንተው እንዲሳካላቸው የምትፈልግ ሰው ናት ። በፍፁም ክፋት የሚባል ነገር አታይባትም ። ለዛም ነው እኔ ሳላውቅ በራሷ ፍቃድ ሞራልም ማስታወቂያም እንዲሆነኝ በዛሬው በሰይፉ ሾ ላይ ፊልሜን ያስተዋወቀችልኝ ።
እንዲሁ ሸዊት ስለሆነች ብቻና በቅርቡ ብር አምባር ቲያትርን ከሀገር ውጪ ለማሳየት እንደምትሄድ ስለማውቅ ፕሮግራሙን መከታተል ጀመርኩ መጨረሻ ላይ ግን በቅርቡ አዲሱ ፊልሜ ይወጣል ብላ ፊልማችንን ስታስተዋውቅ ወላሂ ገረመችኝ ፤ ምን አይነት ቅን ልብ ቢኖራት ነው በዚህ ልክ ይኼን ያህል ርቀት የምትሄደው አልኩ ። ሰይፉ ሾ ላይ የሄደችው ቲያትሩን ለማስተዋወቅ ቢሆንም በመልካምነቷና ቅን በማሰቧ ፊልማችን እንዲተዋወቅ አድርጋለች ።
ከሸዊት ጋር በነበረን ቆይታ ያሳየችኝ መልካምነት እንዳለ ሆኖ ይኼን ግን አልጠበኩም ነበር ። ሸዋዬ ሲበዛ አክባሪሽና ወዳጅ ነሽ ። ስለምትሰጪኝ ምክር ፤ ስለምትሰጪኝ ብርታት ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ ። በስራ ላይ ሌላ ስራ ያስደጋግመን ። ከዚህም በላይ ካንቺ ጋር ለመስራት ያብቃን 👐
"ወንዶቹ አልተወለዱም " በቅርቡ ለእናተም የሚደርስ ይሆናል ..!
ሸዊት ሚዲያ ላይ እንደምታወራው በጣም ቅን ሰው ናት ። የምታወራውን የምትኖር ፀዴ ሰው ናት ። ቅንነቷን ደግነቷን ደግሞ በነበረን የስራ ግኑኝነት ሁሉ አይቼዋለው ። ከልቧ ሰው ናት ። ሰዎች ሰርተው አጊንተው እንዲሳካላቸው የምትፈልግ ሰው ናት ። በፍፁም ክፋት የሚባል ነገር አታይባትም ። ለዛም ነው እኔ ሳላውቅ በራሷ ፍቃድ ሞራልም ማስታወቂያም እንዲሆነኝ በዛሬው በሰይፉ ሾ ላይ ፊልሜን ያስተዋወቀችልኝ ።
እንዲሁ ሸዊት ስለሆነች ብቻና በቅርቡ ብር አምባር ቲያትርን ከሀገር ውጪ ለማሳየት እንደምትሄድ ስለማውቅ ፕሮግራሙን መከታተል ጀመርኩ መጨረሻ ላይ ግን በቅርቡ አዲሱ ፊልሜ ይወጣል ብላ ፊልማችንን ስታስተዋውቅ ወላሂ ገረመችኝ ፤ ምን አይነት ቅን ልብ ቢኖራት ነው በዚህ ልክ ይኼን ያህል ርቀት የምትሄደው አልኩ ። ሰይፉ ሾ ላይ የሄደችው ቲያትሩን ለማስተዋወቅ ቢሆንም በመልካምነቷና ቅን በማሰቧ ፊልማችን እንዲተዋወቅ አድርጋለች ።
ከሸዊት ጋር በነበረን ቆይታ ያሳየችኝ መልካምነት እንዳለ ሆኖ ይኼን ግን አልጠበኩም ነበር ። ሸዋዬ ሲበዛ አክባሪሽና ወዳጅ ነሽ ። ስለምትሰጪኝ ምክር ፤ ስለምትሰጪኝ ብርታት ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ ። በስራ ላይ ሌላ ስራ ያስደጋግመን ። ከዚህም በላይ ካንቺ ጋር ለመስራት ያብቃን 👐
"ወንዶቹ አልተወለዱም " በቅርቡ ለእናተም የሚደርስ ይሆናል ..!
4 days ago
ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የባለቤቷን ህመም (FTD) ለመከታተል የሚያስችል ህግ እንዲፀድቅ ግፊት አደረገች
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
4 days ago
🎯🎯 መቀነት 🎯🎯 የተሰኘው አዲሱ የሰርክአዲስ መጋቢያው ፊልም በትላንትናው እለት ፍላሚንጎ በሚገኘው ህፃናት እና ወጣቶች ቲያትር ታላላቅ የፊልም ባለሙያዎች እና የክብር እንግዶች በተገኙበት በቀይ ምንጣፍ ስነ -ስርዓት በታላቅ ድምቀት ተመረቀ ።
ከነሀሴ 1 ጀምሮ በተመረጡ ሲኒማ ቤቶች መታየት ይጀምራል ።
በመቀነት የታሰረ ህመም፡፡
አንድ መቀነት ሁለትእውነታ!
በቀሀ ፊልምስ ተዘጋጅቶ የቀረበ መቀነት በሰርክአዲስ መጋቢያው አዲስ ፊልም #qehafilms
ከነሀሴ 1 ጀምሮ በተመረጡ ሲኒማ ቤቶች መታየት ይጀምራል ።
በመቀነት የታሰረ ህመም፡፡
አንድ መቀነት ሁለትእውነታ!
በቀሀ ፊልምስ ተዘጋጅቶ የቀረበ መቀነት በሰርክአዲስ መጋቢያው አዲስ ፊልም #qehafilms
Sponsored by
Surafel
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) አዲሱ የሱፐርማን ፊልም በጉጉት ሲጠበቅ የነበረ ሲሆን፣ የጄምስ ገን የዲሲ ኮሚክስ ዩኒቨርስ የመጀመሪያው ትልቅ የሲኒማ ፊልም በመሆኑ የተለየ ትኩረት ስቦለታል። በዚህ ፊልም ላይ ከተለመዱት የሱፐርማን ገጸ-ባህሪያት በተጨማሪ ሚስተር ቴሪፊክ የተባለው ገጸ-ባህሪ ተካቷል። ይህ ገጸ-ባህሪ ከፍተኛ የቴክኖሎጂ አቅም ያለው፣ ምጡቅ መሃንዲስ እና ሳይንቲስት፣ እንዲሁም በሰው ለሰው ውጊያ የተካነ ነው። ሚስተር ቴሪፊክን ወክሎ የሚጫወተው ኤዲ ጋቴጊ፣ ለረጅም ጊዜ በፊልም እና ቴሌቪዥን ኢንዱስትሪ ውስጥ የቆየ ቢሆንም፣ የፊቱ ገጽታ እንጂ ስሙ በብዙዎች ዘንድ በደንብ አይታወቅም።
የትውልደ ኬንያዊው አሜሪካዊ ተዋናይ የፊልም ህይወት በ2006 በ'ክራንክ' ፊልም ላይ በታክሲ ሹፌርነት የጀመረ ሲሆን፣ በመቀጠልም በ'ሀውስ'፣ 'ሲኤስአይ፡ ማያሚ' እና የመሳሰሉት የቴሌቪዥን ተከታታይ ፊልሞች ላይ ተሳትፏል። 'ሱፐርማን' ለጋቴጊ የመጀመሪያው የሱፐርሂሮ ፊልም አይደለም። ከዚህ ቀደም በ2011 በወጣው 'ኤክስ-ሜን፡ ፈርስት ክላስ' ፊልም ላይ 'ዳርዊን' የተባለውን ማናቸውንም አደጋዎች ተቋቁሞ በህይወት መቆየት የሚችል የ'ማርቨል' ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከታዋቂ ተዋንያን ጋር ተጫውቷል።
ጋቴጊ ከ'ኤክስ-ሜን' በፊት በታዋቂው የ'ትዋይላይት' ፊልም ላይ ሎረንት የተባለውን ቫምፓየር ሆኖ በመተወን ይታወቃል። ምንም እንኳን ገጸ-ባህሪው በፊልሙ ላይ ቢገደልም፣ ቫምፓየር ሆኖ የመተወን የረጅም ጊዜ ህልም እንደነበረው ተዋናዩ ይናገራል። ከዚህ በተጨማሪ በታዋቂው የ'ብላክሊስት' ተከታታይ ፊልም ላይ፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የጦር ወንጀል የፈጸመውን እና የሲአይኤ ሰላይ የነበረውን ማቲያስ ሰለሞን የተባለ አደገኛ ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከ20 በላይ ክፍሎች ላይ ተሳትፏል።
ተዋናዩ በ2016 በታየው 'ስታርትአፕ' ላይም ሮናልድ ዴሲ በተባለ ዋና ገጸ-ባህሪነት የተጫወተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በአፕል ቲቪ+ (Apple TV+) 'ፎር ኦል ማንካይንድ'በተሰኘው የሳይንስ ልብወለድ ተከታታይ ፊልም ላይ ዴቭ አዬሳ የተባለውን ታዋቂ መሃንዲስ፣ የኩባንያ መስራች እና ነጋዴ ወክሎ በመተወን ላይ ይገኛል። አሁን ደግሞ በ'ሱፐርማን' ፊልም ላይ በሚጫወተው የሚስተር ቴሪፊክ ሚና በድጋሚ የብዙዎችን ትኩረት ወደ ራሱ እየሳበ ይገኛል።
የትውልደ ኬንያዊው አሜሪካዊ ተዋናይ የፊልም ህይወት በ2006 በ'ክራንክ' ፊልም ላይ በታክሲ ሹፌርነት የጀመረ ሲሆን፣ በመቀጠልም በ'ሀውስ'፣ 'ሲኤስአይ፡ ማያሚ' እና የመሳሰሉት የቴሌቪዥን ተከታታይ ፊልሞች ላይ ተሳትፏል። 'ሱፐርማን' ለጋቴጊ የመጀመሪያው የሱፐርሂሮ ፊልም አይደለም። ከዚህ ቀደም በ2011 በወጣው 'ኤክስ-ሜን፡ ፈርስት ክላስ' ፊልም ላይ 'ዳርዊን' የተባለውን ማናቸውንም አደጋዎች ተቋቁሞ በህይወት መቆየት የሚችል የ'ማርቨል' ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከታዋቂ ተዋንያን ጋር ተጫውቷል።
ጋቴጊ ከ'ኤክስ-ሜን' በፊት በታዋቂው የ'ትዋይላይት' ፊልም ላይ ሎረንት የተባለውን ቫምፓየር ሆኖ በመተወን ይታወቃል። ምንም እንኳን ገጸ-ባህሪው በፊልሙ ላይ ቢገደልም፣ ቫምፓየር ሆኖ የመተወን የረጅም ጊዜ ህልም እንደነበረው ተዋናዩ ይናገራል። ከዚህ በተጨማሪ በታዋቂው የ'ብላክሊስት' ተከታታይ ፊልም ላይ፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የጦር ወንጀል የፈጸመውን እና የሲአይኤ ሰላይ የነበረውን ማቲያስ ሰለሞን የተባለ አደገኛ ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከ20 በላይ ክፍሎች ላይ ተሳትፏል።
ተዋናዩ በ2016 በታየው 'ስታርትአፕ' ላይም ሮናልድ ዴሲ በተባለ ዋና ገጸ-ባህሪነት የተጫወተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በአፕል ቲቪ+ (Apple TV+) 'ፎር ኦል ማንካይንድ'በተሰኘው የሳይንስ ልብወለድ ተከታታይ ፊልም ላይ ዴቭ አዬሳ የተባለውን ታዋቂ መሃንዲስ፣ የኩባንያ መስራች እና ነጋዴ ወክሎ በመተወን ላይ ይገኛል። አሁን ደግሞ በ'ሱፐርማን' ፊልም ላይ በሚጫወተው የሚስተር ቴሪፊክ ሚና በድጋሚ የብዙዎችን ትኩረት ወደ ራሱ እየሳበ ይገኛል።
5 days ago
ገዳይ ሲያረፋፍድ ....
#ethiopia | የኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ የትረካ ጥበብ እና የካሜራ ቴክኖሎጂን አዋህዶ በዘመናዊ አቀራረብ እያደገ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የፊልም አፍቃሪዎችን እና የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ትኩረት ከሳቡ የሀገር ውስጥ የጥበብ ስራዎች መካከል «ገዳይ ሲያረፋፍድ» የተሰኘው የናኦድ ለማ ፊልም ይጠቀሳል።
ይህ ፊልም ይዘቱ፣ የገጸ-ባህሪያት አሳሳሉ እንዲሁም በፖስተሩ ላይ ከሚታየው ጥበብ የሞላበት የቀለምና የብርሃን አጠቃቀም ጀምሮ አቀራረቡ አዳዲስ የትረካ መስመሮችን የሚዳስስ ለመሆኑ ማመላከቻዎችን ያሳያል።
የፊልሙ ርዕስ፡ ገዳይ ሲያረፋፍድ (GEDAY SIYAREFAFID)
ዳይሬክተር / የፊልም አዘጋጅ፡ ናኦድ ለማ (A film by Naod Lemma)
ደራሲ - ስለሺ አምባው
ዋና ተዋንያን፡
መለስ ታደሰ
መስከረም ነጋ በበላይ
ጌታነት አዳነ
ልዑል ተፈራ
አዘጋጅ/ፕሮዳክሽን፡ ታና ኢንተርቴይንመንት (Tana Entertainment) እና አዲቃ (Adika)
የፖስተሩ ጥበባዊ ዳሰሳ እና ጭብጥ (Visual & Storyline Analysis)
የከባቢ አየር እና ድባብ (Atmosphere & Tone):
የፖስተሩ የጀርባ ቀለም (ደመናማና ብርቱካናማ የቀን መግቢያ/መውጫ ብርሃን) የጥርጣሬ፣ የጉጉት እና የድራማ ስሜትን ይፈጥራል።
በግርጌ እና በጎን የሚታዩት የሁለቱ ዋና ገጸ-ባህሪያት ፊት (መጨናነቅ፣ ቁጣ እና ጥልቅ ሀሳብ) ፊልሙ ከባድ የስነ-ልቦና ድራማ ወይም የወንጀልና የበቀል/የውጥረት (Suspense/Thriller) ታሪክ ሊኖረው እንደሚችል ያመላክታል።
ተምሳሌታዊ ምስሎች (Symbolism):
በፖስተሩ መካከለኛ ክፍል ላይ በጥቁር ጥላ (Silhouette) የሚታዩት ሁለት ሰዎች እና ትንሽ ጎጆ ቤት በፊልሙ ውስጥ ያለውን የገጠር ወይም የርቅ ቦታ ዳራ፣ እንዲሁም የሁለት ሰዎች ሚስጥራዊ ግንኙነት ወይም ግጭት ያሳያሉ።
ፊልሙ ከተለመዱት የፍቅርና የኮሜዲ መስመሮች ወጣ ባለ መልኩ የሰዎችን ጥልቅ ስነ-ልቦና እና ያልተጠበቁ ሁነቶችን (Plot Twists) በማቀናጀት የቀረበ እንደሆነ ይነገርለታል።
በተለይም የነመለስ ታደሰ እና ጌታነት አዳነ ገጸ-ባህሪያትን የማቅረብ ተፈጥሯዊ ብቃት ለፊልሙ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ይገለጻል።
በምስል ጥራት፣ በድምጽ ቅንብር እና በምስል ቅንብር (Editing) በኩል የሀገር ውስጥ ፊልም ወደ አዲስ ደረጃ ለማሸጋገር የተደረገው ጥረት አዎንታዊ ግምገማዎችን አግኝቷል።
«ገዳይ ሲያረፋፍድ» የኢትዮጵያ ፊልም ኢንዱስትሪ የትረካ አቅሙን እና የቴክኒክ ብቃቱን ለማሳደግ የሚያደርገውን ጉዞ የሚያሳይ፣ የፊልም አፍቃሪያን ሊመለከቱት የሚገባ አሳቢና ውጥረት አዘል የጥበብ ሥራ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ የትረካ ጥበብ እና የካሜራ ቴክኖሎጂን አዋህዶ በዘመናዊ አቀራረብ እያደገ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የፊልም አፍቃሪዎችን እና የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ትኩረት ከሳቡ የሀገር ውስጥ የጥበብ ስራዎች መካከል «ገዳይ ሲያረፋፍድ» የተሰኘው የናኦድ ለማ ፊልም ይጠቀሳል።
ይህ ፊልም ይዘቱ፣ የገጸ-ባህሪያት አሳሳሉ እንዲሁም በፖስተሩ ላይ ከሚታየው ጥበብ የሞላበት የቀለምና የብርሃን አጠቃቀም ጀምሮ አቀራረቡ አዳዲስ የትረካ መስመሮችን የሚዳስስ ለመሆኑ ማመላከቻዎችን ያሳያል።
የፊልሙ ርዕስ፡ ገዳይ ሲያረፋፍድ (GEDAY SIYAREFAFID)
ዳይሬክተር / የፊልም አዘጋጅ፡ ናኦድ ለማ (A film by Naod Lemma)
ደራሲ - ስለሺ አምባው
ዋና ተዋንያን፡
መለስ ታደሰ
መስከረም ነጋ በበላይ
ጌታነት አዳነ
ልዑል ተፈራ
አዘጋጅ/ፕሮዳክሽን፡ ታና ኢንተርቴይንመንት (Tana Entertainment) እና አዲቃ (Adika)
የፖስተሩ ጥበባዊ ዳሰሳ እና ጭብጥ (Visual & Storyline Analysis)
የከባቢ አየር እና ድባብ (Atmosphere & Tone):
የፖስተሩ የጀርባ ቀለም (ደመናማና ብርቱካናማ የቀን መግቢያ/መውጫ ብርሃን) የጥርጣሬ፣ የጉጉት እና የድራማ ስሜትን ይፈጥራል።
በግርጌ እና በጎን የሚታዩት የሁለቱ ዋና ገጸ-ባህሪያት ፊት (መጨናነቅ፣ ቁጣ እና ጥልቅ ሀሳብ) ፊልሙ ከባድ የስነ-ልቦና ድራማ ወይም የወንጀልና የበቀል/የውጥረት (Suspense/Thriller) ታሪክ ሊኖረው እንደሚችል ያመላክታል።
ተምሳሌታዊ ምስሎች (Symbolism):
በፖስተሩ መካከለኛ ክፍል ላይ በጥቁር ጥላ (Silhouette) የሚታዩት ሁለት ሰዎች እና ትንሽ ጎጆ ቤት በፊልሙ ውስጥ ያለውን የገጠር ወይም የርቅ ቦታ ዳራ፣ እንዲሁም የሁለት ሰዎች ሚስጥራዊ ግንኙነት ወይም ግጭት ያሳያሉ።
ፊልሙ ከተለመዱት የፍቅርና የኮሜዲ መስመሮች ወጣ ባለ መልኩ የሰዎችን ጥልቅ ስነ-ልቦና እና ያልተጠበቁ ሁነቶችን (Plot Twists) በማቀናጀት የቀረበ እንደሆነ ይነገርለታል።
በተለይም የነመለስ ታደሰ እና ጌታነት አዳነ ገጸ-ባህሪያትን የማቅረብ ተፈጥሯዊ ብቃት ለፊልሙ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ይገለጻል።
በምስል ጥራት፣ በድምጽ ቅንብር እና በምስል ቅንብር (Editing) በኩል የሀገር ውስጥ ፊልም ወደ አዲስ ደረጃ ለማሸጋገር የተደረገው ጥረት አዎንታዊ ግምገማዎችን አግኝቷል።
«ገዳይ ሲያረፋፍድ» የኢትዮጵያ ፊልም ኢንዱስትሪ የትረካ አቅሙን እና የቴክኒክ ብቃቱን ለማሳደግ የሚያደርገውን ጉዞ የሚያሳይ፣ የፊልም አፍቃሪያን ሊመለከቱት የሚገባ አሳቢና ውጥረት አዘል የጥበብ ሥራ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
8 days ago
በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ የክህሎትና የመዋቅር ችግሮችን ለመቅረፍ አዲስ የጋራ ስምምነት ተደረገ!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ መዋቅራዊና የክህሎት ችግሮችን ለመቅረፍ የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ በጋራ ለመስራት በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ።
በአዲሱ አስተዳደራዊ መዋቅር ስር የሚገኙትን ብሔራዊ ቴአትር፣ ሀገርፍቅር ቴአትር፣ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም (ባህል አዳራሽ)፣ ራስ ቴአትር እና የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትርን የሚያስተዳድረው ተቋሙ፤ ከግል ዘርፍ አጋሮች ጋር አብሮ ለመሥራት ባቀደው መሠረት ይፋዊ ስምምነቱን አድርጓል።
በስምምነቱ መሠረት የአስተዳደሩን የዘመናት የታሪክና የልምድ ክምችት ከአካዳሚው ዘመናዊና ፈጠራ የታከለበት የአሰልጠና ዘዴ ጋር በማዋሃድ በቴአትር፣ በሙዚቃ፣ በፊልምና ተዛማጅ የኪነ-ጥበብ ዘርፎች ሰፊ ስልጠናዎች በጋራ እንደሚሰጡ ተገልጿል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክና ወግ የሚያንፀባርቁ ጥበባዊ ሁነቶችንና ትላልቅ ፕሮዳክሽኖችን በጋራ በማዘጋጀት ለሕዝብ ለማቅረብ፣ እንዲሁም ከግጥም ምሽቶች እስከ ታላላቅ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫሎች ድረስ ያሉ መድረኮችን ለማስፋፋት መታቀዱም ነዉ የተገለፀዉ።
የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ ዋና መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሌንጮ ፍቅሩ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደገለጹት፤ አካዳሚው ከተመሠረተበት ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በርካታ ወጣትና ህጻናት
ተማሪዎችን አብቅቶ ያስመረቀ ሲሆን፣ በተለይም በልጆች አክቲንግ ዘርፍ አበራች አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ሌንጮ አክለው እንደገለጹት፣ አካዳሚው እስካሁን በነበረው ጉዞ የቦታ፣ የሎኬሽን እና የትወና ቁሳቁሶች (Props) እጥረት ዋና ዋና ማነቆዎች እንደነበሩበት አስታውሰዋል።
ሆኖም ከአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ጋር የተደረገው ይህ ይፋዊ ስምምነት እነዚህን የሎጅስቲክስና የቦታ ችግሮች በዘላቂነት በመቅረፍ፣ የሰለጠኑ አዳዲስ ከዋክብትን ወደ ታሪካዊ የቴአትር መድረኮች ለማውጣት ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ መዋቅራዊና የክህሎት ችግሮችን ለመቅረፍ የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ በጋራ ለመስራት በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ።
በአዲሱ አስተዳደራዊ መዋቅር ስር የሚገኙትን ብሔራዊ ቴአትር፣ ሀገርፍቅር ቴአትር፣ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም (ባህል አዳራሽ)፣ ራስ ቴአትር እና የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትርን የሚያስተዳድረው ተቋሙ፤ ከግል ዘርፍ አጋሮች ጋር አብሮ ለመሥራት ባቀደው መሠረት ይፋዊ ስምምነቱን አድርጓል።
በስምምነቱ መሠረት የአስተዳደሩን የዘመናት የታሪክና የልምድ ክምችት ከአካዳሚው ዘመናዊና ፈጠራ የታከለበት የአሰልጠና ዘዴ ጋር በማዋሃድ በቴአትር፣ በሙዚቃ፣ በፊልምና ተዛማጅ የኪነ-ጥበብ ዘርፎች ሰፊ ስልጠናዎች በጋራ እንደሚሰጡ ተገልጿል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክና ወግ የሚያንፀባርቁ ጥበባዊ ሁነቶችንና ትላልቅ ፕሮዳክሽኖችን በጋራ በማዘጋጀት ለሕዝብ ለማቅረብ፣ እንዲሁም ከግጥም ምሽቶች እስከ ታላላቅ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫሎች ድረስ ያሉ መድረኮችን ለማስፋፋት መታቀዱም ነዉ የተገለፀዉ።
የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ ዋና መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሌንጮ ፍቅሩ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደገለጹት፤ አካዳሚው ከተመሠረተበት ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በርካታ ወጣትና ህጻናት
ተማሪዎችን አብቅቶ ያስመረቀ ሲሆን፣ በተለይም በልጆች አክቲንግ ዘርፍ አበራች አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ሌንጮ አክለው እንደገለጹት፣ አካዳሚው እስካሁን በነበረው ጉዞ የቦታ፣ የሎኬሽን እና የትወና ቁሳቁሶች (Props) እጥረት ዋና ዋና ማነቆዎች እንደነበሩበት አስታውሰዋል።
ሆኖም ከአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ጋር የተደረገው ይህ ይፋዊ ስምምነት እነዚህን የሎጅስቲክስና የቦታ ችግሮች በዘላቂነት በመቅረፍ፣ የሰለጠኑ አዳዲስ ከዋክብትን ወደ ታሪካዊ የቴአትር መድረኮች ለማውጣት ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ለሳምሰንግ አዲሱ የጋላክሲ ዜድ ፎልድ 8 ተከታታይ ስማርት ስልክ፤ ሰዎች እንደ ስልክ፣ ታብሌት፣ የስራ መሳሪያ፣ የመዝናኛ ስክሪን እና አሁን ደግሞ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አጋር ሆኖ ከሚያገለግል መሳሪያ ምን እንደሚፈልጉ ባለፉት ሰባት ተከታታይ ስሪቶች (ትውልዶች) ውስጥ ከተማረው ልምድ የተገኘ ውጤት ነው። በለንደን በተዘጋጀ የሚዲያ መድረክ ላይ፣ የሳምሰንግ የሞባይል ምርምር እና ልማት የሃርድዌር ኃላፊ እና ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ሱንግሁን ሙን እንዳሉት፣ የኩባንያው የቅርብ ጊዜ ተጣጣፊ ስልኮች የደንበኞችን አስተያየት፣ የአስተማማኝነት መረጃዎችን እና የምህንድስና ትምህርቶችን መሰረት አድርገው የተሰሩ ናቸው። ኃላፊው "ላለፉት ሰባት ተከታታይ ሞዴሎቻችን የደንበኞቻችንን እና የተለዋዋጭ አጠቃቀም ስርዓቶችን በቅርበት በመከታተል ውሳኔያችንን አሳልፈናል" ብለዋል።
ይህ የደንበኞችን ፍላጎት ማዕከል ያደረገ አሰራር የአዲሱ ጋላክሲ ዜድ ተከታታይ ስልኮች የጀርባ አጥንት ነው። ሳምሰንግ እንደሚለው፣ ተጠቃሚዎች ይበልጥ ሰፊ እና ማራኪ ማሳያዎች ቀጭን እና ቀላል አካል፣ የተሻለ ጥንካሬ፣ እንዲሁም ከፍተኛ አፈጻጸም እንዲኖራቸው ሲጠይቁ ቆይተዋል። ይህንን ሁሉ በአንድ ጊዜ ማሳካት ግን ከባድ ፈተና ነበር። ለዚህም የሳምሰንግ መፍትሄ የተጣጣፊ ስልኩን የውስጥ እና የውጭ አሰራር ሙሉ በሙሉ መቀየር ነበር።
ከትላልቆቹ የሃርድዌር ለውጦች አንዱ፣ ተጣጣፊውን ስክሪን ይበልጥ ቀጭን፣ ጠንካራ እና ማራኪ ለማድረግ የተነደፈው አዲሱ የማሳያ ድጋፍ ቴክኖሎጂ የሆነው 'ፍሌክስ ቲታኒየም' ነው። ኃላፊው ሱንግሁን ሙን ቲታኒየም ለቅርብ ጊዜው ስሪት ዋነኛ ግብዓት የሆነው፣ ሳምሰንግ በተጣጣፊ ማሳያዎች ዙሪያ የነበሩትን የረጅም ጊዜ ተግዳሮቶች ሊፈታ ይችላል ብሎ ስላመነ መሆኑን አስረድተዋል። "በተጣጣፊ ስልኮች የእድገት ደረጃዎች ውስጥ ስናልፍ ቁጥር ስፍር የሌላቸውን ግብዓቶች ተጠቅመናል፤ በዚህኛው ስሪት ግን ቲታኒየም የተጣጣፊ ስልክ ቴክኖሎጂን ወደ ላቀ ደረጃ ሊያሸጋግረው የሚችል ጥራት እንዳለው አምነናል" ብለዋል።
በየቀኑ ለሚታጠፍ መሳሪያ ቲታኒየም ተመራጭነት ያለው ግብዓት ላይመስል ይችላል። ኃላፊውም ቲታኒየምን ለተጣጣፊ ስልክ ምቹ ወደሆነ መዋቅር መቀየር ለሳምሰንግ መሀንዲሶች እጅግ በጣም ፈታኝ ከነበሩት ጉዳዮች አንዱ እንደነበር አምነዋል። ይህ 'ፍሌክስ ቲታኒየም' ቴክኖሎጂ ሁለት በቲታኒየም ላይ የተመሰረቱ አካላትን ይጠቀማል፤ እነሱም ከማሳያው ስር የሚገኝ የተጣራ የቲታኒየም ንጣፍ እና እጅግ በጣም ቀጭን የሆነ የቲታኒየም-አሎይ ፊልም ናቸው። ይህ ፊልም የሰውን ልጅ ፀጉር ውፍረት አንድ ሶስተኛ በሚያህል እጅግ በጣም ስስ በሆነ ውፍረት የተሰራ ነው። ይህም የማሳያውን መዋቅር ለማጠናከር፣ የማጠፊያ መስመሩን እምብዛም እንዳይታይ ለማድረግ እና የእይታ ጥራትን ለማሻሻል እንደሚረዳ ሳምሰንግ ገልጿል።
ይህ አስደናቂ የምህንድስና ጥበብ በሌሎች የስልኩ ክፍሎችም ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ አሳድሯል። የማሳያውን ሞጁል ውፍረት በ10 በመቶ በመቀነስ፣ ሳምሰንግ ለባትሪ፣ ለሙቀት መቆጣጠሪያ ስርዓት እና ለካሜራ የሚሆን ተጨማሪ የውስጥ ክፍተት መፍጠር ችሏል። አዲሱ Galaxy Z Fold8 Ultra ይበልጥ ቀጭን በሆነው አካሉ ውስጥ 5,000mAh አቅም ያለው ባትሪ የያዘ ሲሆን፣ በ45W ፈጣን ቻርጅ በ30 ደቂቃ ውስጥ ብቻ እስከ 67 በመቶ መሙላት ያስችላል። ኃላፊው እንዳብራሩት ይህ መሻሻል የባትሪን ግብዓት በመቀየር ብቻ የመጣ ሳይሆን፣ በአጠቃላይ የባትሪ ስርዓቱ እና አወቃቀሩ ላይ የተደረገ ሁለንተናዊ ማሻሻያ ነው።
በተጨማሪም አዲሶቹ የጋላክሲ ዜድ ተከታታይ ስልኮች ከመውደቅ፣ ደጋግሞ ከመታጠፍ፣ ከጫና፣ ከእርጥበት፣ ከቆሻሻ እና ከሌሎች የዕለት ተዕለት አደጋዎች አንጻር ከመቶ በላይ የአስተማማኝነት ማረጋገጫ ፈተናዎችን ማለፋቸው ተገልጿል። እነዚህ ተጣጣፊ ስልኮች አሁን ላይ ለሙከራ የሚቀርቡ ሳይሆኑ፣ በተለይም የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ከሞባይል አጠቃቀም ጋር ይበልጥ እየተዋሃደ በመምጣቱ የዕለት ተዕለት የህይወት አጋር እና ቀዳሚ ስልኮች እንዲሆኑ ታስበው የተሰሩ ናቸው። ሱንግሁን ሙን በማጠቃለያቸው "ይህ ስኬት የተጣጣፊ ስልክ ቴክኖሎጂን ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው እናምናለን" ብለዋል።
ይህ የደንበኞችን ፍላጎት ማዕከል ያደረገ አሰራር የአዲሱ ጋላክሲ ዜድ ተከታታይ ስልኮች የጀርባ አጥንት ነው። ሳምሰንግ እንደሚለው፣ ተጠቃሚዎች ይበልጥ ሰፊ እና ማራኪ ማሳያዎች ቀጭን እና ቀላል አካል፣ የተሻለ ጥንካሬ፣ እንዲሁም ከፍተኛ አፈጻጸም እንዲኖራቸው ሲጠይቁ ቆይተዋል። ይህንን ሁሉ በአንድ ጊዜ ማሳካት ግን ከባድ ፈተና ነበር። ለዚህም የሳምሰንግ መፍትሄ የተጣጣፊ ስልኩን የውስጥ እና የውጭ አሰራር ሙሉ በሙሉ መቀየር ነበር።
ከትላልቆቹ የሃርድዌር ለውጦች አንዱ፣ ተጣጣፊውን ስክሪን ይበልጥ ቀጭን፣ ጠንካራ እና ማራኪ ለማድረግ የተነደፈው አዲሱ የማሳያ ድጋፍ ቴክኖሎጂ የሆነው 'ፍሌክስ ቲታኒየም' ነው። ኃላፊው ሱንግሁን ሙን ቲታኒየም ለቅርብ ጊዜው ስሪት ዋነኛ ግብዓት የሆነው፣ ሳምሰንግ በተጣጣፊ ማሳያዎች ዙሪያ የነበሩትን የረጅም ጊዜ ተግዳሮቶች ሊፈታ ይችላል ብሎ ስላመነ መሆኑን አስረድተዋል። "በተጣጣፊ ስልኮች የእድገት ደረጃዎች ውስጥ ስናልፍ ቁጥር ስፍር የሌላቸውን ግብዓቶች ተጠቅመናል፤ በዚህኛው ስሪት ግን ቲታኒየም የተጣጣፊ ስልክ ቴክኖሎጂን ወደ ላቀ ደረጃ ሊያሸጋግረው የሚችል ጥራት እንዳለው አምነናል" ብለዋል።
በየቀኑ ለሚታጠፍ መሳሪያ ቲታኒየም ተመራጭነት ያለው ግብዓት ላይመስል ይችላል። ኃላፊውም ቲታኒየምን ለተጣጣፊ ስልክ ምቹ ወደሆነ መዋቅር መቀየር ለሳምሰንግ መሀንዲሶች እጅግ በጣም ፈታኝ ከነበሩት ጉዳዮች አንዱ እንደነበር አምነዋል። ይህ 'ፍሌክስ ቲታኒየም' ቴክኖሎጂ ሁለት በቲታኒየም ላይ የተመሰረቱ አካላትን ይጠቀማል፤ እነሱም ከማሳያው ስር የሚገኝ የተጣራ የቲታኒየም ንጣፍ እና እጅግ በጣም ቀጭን የሆነ የቲታኒየም-አሎይ ፊልም ናቸው። ይህ ፊልም የሰውን ልጅ ፀጉር ውፍረት አንድ ሶስተኛ በሚያህል እጅግ በጣም ስስ በሆነ ውፍረት የተሰራ ነው። ይህም የማሳያውን መዋቅር ለማጠናከር፣ የማጠፊያ መስመሩን እምብዛም እንዳይታይ ለማድረግ እና የእይታ ጥራትን ለማሻሻል እንደሚረዳ ሳምሰንግ ገልጿል።
ይህ አስደናቂ የምህንድስና ጥበብ በሌሎች የስልኩ ክፍሎችም ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ አሳድሯል። የማሳያውን ሞጁል ውፍረት በ10 በመቶ በመቀነስ፣ ሳምሰንግ ለባትሪ፣ ለሙቀት መቆጣጠሪያ ስርዓት እና ለካሜራ የሚሆን ተጨማሪ የውስጥ ክፍተት መፍጠር ችሏል። አዲሱ Galaxy Z Fold8 Ultra ይበልጥ ቀጭን በሆነው አካሉ ውስጥ 5,000mAh አቅም ያለው ባትሪ የያዘ ሲሆን፣ በ45W ፈጣን ቻርጅ በ30 ደቂቃ ውስጥ ብቻ እስከ 67 በመቶ መሙላት ያስችላል። ኃላፊው እንዳብራሩት ይህ መሻሻል የባትሪን ግብዓት በመቀየር ብቻ የመጣ ሳይሆን፣ በአጠቃላይ የባትሪ ስርዓቱ እና አወቃቀሩ ላይ የተደረገ ሁለንተናዊ ማሻሻያ ነው።
በተጨማሪም አዲሶቹ የጋላክሲ ዜድ ተከታታይ ስልኮች ከመውደቅ፣ ደጋግሞ ከመታጠፍ፣ ከጫና፣ ከእርጥበት፣ ከቆሻሻ እና ከሌሎች የዕለት ተዕለት አደጋዎች አንጻር ከመቶ በላይ የአስተማማኝነት ማረጋገጫ ፈተናዎችን ማለፋቸው ተገልጿል። እነዚህ ተጣጣፊ ስልኮች አሁን ላይ ለሙከራ የሚቀርቡ ሳይሆኑ፣ በተለይም የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ከሞባይል አጠቃቀም ጋር ይበልጥ እየተዋሃደ በመምጣቱ የዕለት ተዕለት የህይወት አጋር እና ቀዳሚ ስልኮች እንዲሆኑ ታስበው የተሰሩ ናቸው። ሱንግሁን ሙን በማጠቃለያቸው "ይህ ስኬት የተጣጣፊ ስልክ ቴክኖሎጂን ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው እናምናለን" ብለዋል።
Sponsored by
Surafel
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) እግር ኳስ አንዳንዴ ከስፖርትነት አልፎ ድንቅ እና ስሜት ቀስቃሽ ታሪኮችን ይጽፋል። የ8 ወር ህጻን እያለ በሀገሩ ሄይቲ በደረሰው እና ከ300 ሺህ በላይ ሰዎችን ህይወት በከፋ ሁኔታ በቀጠፈው አሰቃቂ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት፣ ከተአምር በተጠጋ ሁኔታ የተረፈው ወጣት፤ ዛሬ በዓለም እግር ኳስ ታላቁን ሰማያዊ እና ነጭ ማሊያ ለብሶ አዲስ ታሪክ ጽፏል።
የ17 ዓመቱ ስቲቨን "ኪኪ" ራሞስ ለአርጀንቲና ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በመሰለፍ፣ በሄይቲ ተወልዶ የታላቋን ደቡብ አሜሪካ ሀገር ማሊያ የለበሰ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል!
በታዋቂው የቬሌዝ ሳርስፊልድ አካዳሚ ውስጥ በክንፍ አጥቂነት የሚያበራው ይህ ታዳጊ፣ አርጀንቲና ኢኳዶርን 2ለ1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ለአልቢሴሌስቴዎች የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በጨዋታው ላይ ድንቅ እንቅስቃሴ በማሳየት እና ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ቡድኑን ለድል ያበቃው ኪኪ ራሞስ፣ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ባላቸው አርጀንቲናውያን ዘንድ ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል።
በ2009 በፖርት-ኦ-ፕሪንስ ሄይቲ የተወለደው ኪኪ፣ ለአርጀንቲና በማንኛውም የዕድሜ እርከን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የተሰለፈ የመጀመሪያው በሄይቲ የተወለደ ጥቁር ተጫዋች በመሆን አዲስ የኢንተርናሽናል እግር ኳስ ምዕራፍ ከፍቷል።
የኪኪ የህይወት ታሪክ ልክ እንደ አስደናቂ የፊልም ስክሪፕት ነው። እ.ኤ.አ በ2010 በሄይቲ ደርሶ በነበረው አውዳሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት ገና የ8 ወር ህጻን የነበረው ኪኪ፣ በነበረበት የሕፃናት ማደሪያ ጣቢያ ውስጥ ጉዳት ሳይደርስበት ከተረፉት በጣም ጥቂት ህጻናት አንዱ ነበር።
ባዮሎጂካል ወላጆቹ አርጀንቲናውያን ባይሆኑም፣ አንድ ደግ ልብ ያላቸው አርጀንቲናውያን ባልና ሚስት በጉዲፈቻ ወስደው ወደ ቦነስ አይረስ አመጡት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህይወቱን ሙሉ በአርጀንቲና ያሳለፈው፣ ቋንቋውን እና ባህሉን ለምዶ ያደገው ኪኪ፣ የሀገሪቱን ዜግነት በመያዝ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጫወት ህጋዊ መብትን አግኝቷል።
የኪኪ ራሞስ ታሪክ ይፋ መሆንን ተከትሎ በአርጀንቲናውያን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ደስታ እና ኩራት ተፈጥሯል። በጨዋታው ካሳየው ከፍተኛ ተሰጥኦ ባሻገር፣ ከሞት አፍ ወጥቶ ለአርጀንቲና ማሊያ እስከመበቃት ያደረገውን ተአምራዊ ጉዞ የተመለከቱ የስፖርቱ ተከታታዮች፣ "እግር ኳስ ሰዎችን የሚያስተስርር ድንቅ ድልድይ ነው" ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ገና በ17 ዓመቱ በአርጀንቲና እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ የያዘው ይህ ፈጣን የክንፍ መስመር ተጫዋች፣ በቀጣይ በታላቁ የአርጀንቲና ዋና ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የመሰለፍ ህልሙን ያሳካ ይሆን? የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከወዲሁ የዚህን ድንቅ ወጣት ቀጣይ እርምጃዎች በትልቅ ጉጉት እየተከታተሉ ይገኛሉ።
የ17 ዓመቱ ስቲቨን "ኪኪ" ራሞስ ለአርጀንቲና ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በመሰለፍ፣ በሄይቲ ተወልዶ የታላቋን ደቡብ አሜሪካ ሀገር ማሊያ የለበሰ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል!
በታዋቂው የቬሌዝ ሳርስፊልድ አካዳሚ ውስጥ በክንፍ አጥቂነት የሚያበራው ይህ ታዳጊ፣ አርጀንቲና ኢኳዶርን 2ለ1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ለአልቢሴሌስቴዎች የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በጨዋታው ላይ ድንቅ እንቅስቃሴ በማሳየት እና ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ቡድኑን ለድል ያበቃው ኪኪ ራሞስ፣ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ባላቸው አርጀንቲናውያን ዘንድ ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል።
በ2009 በፖርት-ኦ-ፕሪንስ ሄይቲ የተወለደው ኪኪ፣ ለአርጀንቲና በማንኛውም የዕድሜ እርከን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የተሰለፈ የመጀመሪያው በሄይቲ የተወለደ ጥቁር ተጫዋች በመሆን አዲስ የኢንተርናሽናል እግር ኳስ ምዕራፍ ከፍቷል።
የኪኪ የህይወት ታሪክ ልክ እንደ አስደናቂ የፊልም ስክሪፕት ነው። እ.ኤ.አ በ2010 በሄይቲ ደርሶ በነበረው አውዳሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት ገና የ8 ወር ህጻን የነበረው ኪኪ፣ በነበረበት የሕፃናት ማደሪያ ጣቢያ ውስጥ ጉዳት ሳይደርስበት ከተረፉት በጣም ጥቂት ህጻናት አንዱ ነበር።
ባዮሎጂካል ወላጆቹ አርጀንቲናውያን ባይሆኑም፣ አንድ ደግ ልብ ያላቸው አርጀንቲናውያን ባልና ሚስት በጉዲፈቻ ወስደው ወደ ቦነስ አይረስ አመጡት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህይወቱን ሙሉ በአርጀንቲና ያሳለፈው፣ ቋንቋውን እና ባህሉን ለምዶ ያደገው ኪኪ፣ የሀገሪቱን ዜግነት በመያዝ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጫወት ህጋዊ መብትን አግኝቷል።
የኪኪ ራሞስ ታሪክ ይፋ መሆንን ተከትሎ በአርጀንቲናውያን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ደስታ እና ኩራት ተፈጥሯል። በጨዋታው ካሳየው ከፍተኛ ተሰጥኦ ባሻገር፣ ከሞት አፍ ወጥቶ ለአርጀንቲና ማሊያ እስከመበቃት ያደረገውን ተአምራዊ ጉዞ የተመለከቱ የስፖርቱ ተከታታዮች፣ "እግር ኳስ ሰዎችን የሚያስተስርር ድንቅ ድልድይ ነው" ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ገና በ17 ዓመቱ በአርጀንቲና እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ የያዘው ይህ ፈጣን የክንፍ መስመር ተጫዋች፣ በቀጣይ በታላቁ የአርጀንቲና ዋና ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የመሰለፍ ህልሙን ያሳካ ይሆን? የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከወዲሁ የዚህን ድንቅ ወጣት ቀጣይ እርምጃዎች በትልቅ ጉጉት እየተከታተሉ ይገኛሉ።
14 days ago
በህይወት እያሉ ተመሰገኑ
(በዕዝራ እጅጉ)
.የመዲናዋ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና እንዲያገኙ ወሰነ
#ethiopia | አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ ዛሬ ጋቢ በተደረበላቸው ዕለት ደስታቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር።
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት እነዚህ ጉምቱ ባለሙያዎች ከ 35 አመት በላይ በትጋት ያገለገሉ ሲሆን በሙያ አጋሮቻቸው ተከበው አድናቆት ሲቸራቸው ውለዋል።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም ከ 4 ሰዓት ጀምሮ በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በተደረገው መርሀ ግብር የሚድያ ባለሙያዎች እና ወዳጆቻቸው ተገኝተው እኛም አመስጋኞቻችሁ ነን በማለት ለመርሀ ግብሩ ድምቀት ሰጥተዋል።
ባለሙያዎቹን ለማመስገን ራሱን የቻለ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን ይህም ኮሚቴ ባለሙያዎቹ በዘለቄታዊነት የሚታገዙበት መንገድ ያመቻቸ ነው።
ለዝግጅቱ መሳካት በተከፈተው የwhat is up ገፅ ኮሚቴው ውስጥ ተግባራቸውን የተወጡት ጥላሁን ካሣ ፣ሀብታሙ ድረስ ፣ሰለሞን ሀይለኢየሱስ፣ዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)፣ አለም ታደሰ፣ሠናይት ሀይሌ፣እሸቱ ገለቱ፣ ጌጡ ተመስገን እና ግደይ ገብረ ሲሆኑ እነርሱም በዕለቱ እንደተናገሩት ሥራው በአጭር ጊዜ ታስቦ ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ለአንጋፋ ባለሙያዎቹ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና የሚያገኙበት መንገድ ያመቻቸ ሲሆን ይህ የመረዳዳት ባህል ወደፊትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተነግሯል።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
"ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን "የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች እንደነበሩ በዕለቱ ምስክርነት የሰጡ ባልደረቦቻቸው የተናገሩ ሲሆን የምስጋና ቀን መዘጋጀቱ አዲስ የሚመጣውንም ባለሙያ የሚያበረታታ ነው ሲሉ ሀሣብ ሰንዝረዋል።
በዕለቱ የሚድያ ሥራን ከ1950ዎቹ ጀምሮ ያስቃኘ አጭር የትዝታ ዘጋቢ ፊልም የቀረበ ሲሆን ተመስጋኞቹ ከዚህ ቀደም አየር ላይ ያዋሏቸው ሥራዎችም በዕለቱ ለታደሙት እንግዶች ቀርበዋል።
በባልደረቦቻቸው የምስጋና ዝግጅት የተደረገላቸው አዲስአለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ እንደዛሬ ደስ ብሎንም አያውቅ ፣ ይህን መርሀ ግብር በተሳካ መንገድ ዕውን እንዲሆን የጣራችሁ ሁሉ ፈጣሪ መንገዳችሁን ያቃና ሲሉ መርቀዋል።
የአዘጋጅ ኮሚቴው አባል እሸቱ ገለቱ እንዳለው በኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚሠሩ ባልደረቦች የመጠያየቅ ባህልን ከጀመሩ ሁለት አመት እንደሆናቸው ጠቅሰው ይህ የምስጋና መርሀ ግብር የዚያ መጠያየቅ አካል እንደሆነ ጠቁሟል።
ባለሙያዎች ጡረታ ሲወጡ የሚደገፉበት፣ በተለይም በኢኮኖሚ እገዛ የሚያገኙበት ስልት መነደፍ እንዳለበትም ጋዜጠኛ እሸቱ ጥቆማ ሰጥቷል። በተጨማሪም የጤና ሁኔታቸውን፣ የሚከታተሉበት መንገድ መፈጠር እንዳለበትም ተናግሯል።
ከጡረታ በኃላ ምክር በመስጠት ባለሙያዎቹ ልምዳቸውን ማጋራት አለባቸውም ብሏል።ይህንኑ ትልቅ ርዕይ ለማሳካት መንግሥትና የሚመለከታቸው የሚድያ ማህበራት ሊተባበሩ ይገባልም ሲል ሀሣብ አንስቷል።
የእለቱን የምስጋና መሰናዶ እንዲሳካ አቶ ሠርፀፍሬ ስብሓት አዳራሽ በመስጠት ፣ ጋዜጠኛ ማህደረ ታሪኩ ፕሮጀክተር በመለገስ እንዲሁም አልፋ ውሃ፣ ለታዳሚዎች የመስተንግዶ ውሃ በማቅረብ መርሀ ግብሩ የተሳካ እንዲሆን አድርገዋል።
(በዕዝራ እጅጉ)
.የመዲናዋ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና እንዲያገኙ ወሰነ
#ethiopia | አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ ዛሬ ጋቢ በተደረበላቸው ዕለት ደስታቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር።
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት እነዚህ ጉምቱ ባለሙያዎች ከ 35 አመት በላይ በትጋት ያገለገሉ ሲሆን በሙያ አጋሮቻቸው ተከበው አድናቆት ሲቸራቸው ውለዋል።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም ከ 4 ሰዓት ጀምሮ በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በተደረገው መርሀ ግብር የሚድያ ባለሙያዎች እና ወዳጆቻቸው ተገኝተው እኛም አመስጋኞቻችሁ ነን በማለት ለመርሀ ግብሩ ድምቀት ሰጥተዋል።
ባለሙያዎቹን ለማመስገን ራሱን የቻለ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን ይህም ኮሚቴ ባለሙያዎቹ በዘለቄታዊነት የሚታገዙበት መንገድ ያመቻቸ ነው።
ለዝግጅቱ መሳካት በተከፈተው የwhat is up ገፅ ኮሚቴው ውስጥ ተግባራቸውን የተወጡት ጥላሁን ካሣ ፣ሀብታሙ ድረስ ፣ሰለሞን ሀይለኢየሱስ፣ዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)፣ አለም ታደሰ፣ሠናይት ሀይሌ፣እሸቱ ገለቱ፣ ጌጡ ተመስገን እና ግደይ ገብረ ሲሆኑ እነርሱም በዕለቱ እንደተናገሩት ሥራው በአጭር ጊዜ ታስቦ ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ለአንጋፋ ባለሙያዎቹ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና የሚያገኙበት መንገድ ያመቻቸ ሲሆን ይህ የመረዳዳት ባህል ወደፊትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተነግሯል።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
"ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን "የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች እንደነበሩ በዕለቱ ምስክርነት የሰጡ ባልደረቦቻቸው የተናገሩ ሲሆን የምስጋና ቀን መዘጋጀቱ አዲስ የሚመጣውንም ባለሙያ የሚያበረታታ ነው ሲሉ ሀሣብ ሰንዝረዋል።
በዕለቱ የሚድያ ሥራን ከ1950ዎቹ ጀምሮ ያስቃኘ አጭር የትዝታ ዘጋቢ ፊልም የቀረበ ሲሆን ተመስጋኞቹ ከዚህ ቀደም አየር ላይ ያዋሏቸው ሥራዎችም በዕለቱ ለታደሙት እንግዶች ቀርበዋል።
በባልደረቦቻቸው የምስጋና ዝግጅት የተደረገላቸው አዲስአለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ እንደዛሬ ደስ ብሎንም አያውቅ ፣ ይህን መርሀ ግብር በተሳካ መንገድ ዕውን እንዲሆን የጣራችሁ ሁሉ ፈጣሪ መንገዳችሁን ያቃና ሲሉ መርቀዋል።
የአዘጋጅ ኮሚቴው አባል እሸቱ ገለቱ እንዳለው በኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚሠሩ ባልደረቦች የመጠያየቅ ባህልን ከጀመሩ ሁለት አመት እንደሆናቸው ጠቅሰው ይህ የምስጋና መርሀ ግብር የዚያ መጠያየቅ አካል እንደሆነ ጠቁሟል።
ባለሙያዎች ጡረታ ሲወጡ የሚደገፉበት፣ በተለይም በኢኮኖሚ እገዛ የሚያገኙበት ስልት መነደፍ እንዳለበትም ጋዜጠኛ እሸቱ ጥቆማ ሰጥቷል። በተጨማሪም የጤና ሁኔታቸውን፣ የሚከታተሉበት መንገድ መፈጠር እንዳለበትም ተናግሯል።
ከጡረታ በኃላ ምክር በመስጠት ባለሙያዎቹ ልምዳቸውን ማጋራት አለባቸውም ብሏል።ይህንኑ ትልቅ ርዕይ ለማሳካት መንግሥትና የሚመለከታቸው የሚድያ ማህበራት ሊተባበሩ ይገባልም ሲል ሀሣብ አንስቷል።
የእለቱን የምስጋና መሰናዶ እንዲሳካ አቶ ሠርፀፍሬ ስብሓት አዳራሽ በመስጠት ፣ ጋዜጠኛ ማህደረ ታሪኩ ፕሮጀክተር በመለገስ እንዲሁም አልፋ ውሃ፣ ለታዳሚዎች የመስተንግዶ ውሃ በማቅረብ መርሀ ግብሩ የተሳካ እንዲሆን አድርገዋል።
16 days ago
ለ6 ዓመታት ከኦክስጂን ማሽን ጋር የሕይወት ትግል
– አርቲስት ታደሰ (ዳኒ ጋጋኖ) የእርዳታ ጥሪ
#ethiopia | ለ6 ዓመታት ሙሉ በየሰከንዱ ለመተንፈስ በኦክስጂን ማሽን ላይ ተመርኩዞ መኖር ምን ያህል ከባድ እና ልብን የሚሰብር እንደሆነ ለአፍታ እናስብ።
በኢትዮጵያ የፊልምና የቲያትር ዘርፍ በ"ሳምራዊ"፣ "አፍሮኒዝም"፣ "ቀን ዘራፊ" እና "ሄሎ ኢትዮጵያ" ጨምሮ በበርካታ ስራዎች የሚታወቀው ተወዳጁ አርቲስት ታደሰ (ዳኒ ጋጋኖ) በከባድ የጤና እክል ምክንያት ከ6 ዓመታት በላይ በኦክስጂን ማሽን ተደግፎ ሕይወቱን ለማስቀጠል እየታገለ ይገኛል።
በተነገረው መሰረት፣ ህመሙ በሳንባውና በአጥንቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሶበታል። በቅርቡም በሆስፒታል ቆይታው ወቅት ከባድ የደም መፍሰስ አጋጥሞት እንደነበር ተገልጿል።
ዳኒ በሙያው ሀገሩን በመወከል እስከ ስፔንና ስዊድን ድረስ በመጓዝ እውቅና ያገኘ ሲሆን፣ ከእርሱ ጋር የሠሩ የሙያ ባልደረቦቹ እንደሚናገሩት ችግሩን ለሰው ማካፈል የማይወድ እና ህመሙን በጸጥታ የሚታገል ሰው ነው።
በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ የህክምና ወጪው ከፍተኛ በመሆኑ፣ ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ከአቅማቸው በላይ እየጣሩ ቢሆንም፣ የህብረተሰቡን ድጋፍ እንደሚፈልጉ ተገልጿል።
የእርዳታ መለያ
- ባንክ: CBE
- የሂሳብ ቁጥር: 1000522370456
- ስም: ዳንኤል ታደሰ በላይነህ
- ስልክ: 0913 523751
ለዳኒ ፈጣን ማገገም እንመኛለን። መርዳት ለሚችሉ ሁሉ፣ በአቅማችሁ መጠን ድጋፍ ማድረግ እና መረጃውን ለሌሎች ማጋራት ትልቅ አስተዋጽኦ ሊሆን ይችላል።
#የፍቅርስጦታ
– አርቲስት ታደሰ (ዳኒ ጋጋኖ) የእርዳታ ጥሪ
#ethiopia | ለ6 ዓመታት ሙሉ በየሰከንዱ ለመተንፈስ በኦክስጂን ማሽን ላይ ተመርኩዞ መኖር ምን ያህል ከባድ እና ልብን የሚሰብር እንደሆነ ለአፍታ እናስብ።
በኢትዮጵያ የፊልምና የቲያትር ዘርፍ በ"ሳምራዊ"፣ "አፍሮኒዝም"፣ "ቀን ዘራፊ" እና "ሄሎ ኢትዮጵያ" ጨምሮ በበርካታ ስራዎች የሚታወቀው ተወዳጁ አርቲስት ታደሰ (ዳኒ ጋጋኖ) በከባድ የጤና እክል ምክንያት ከ6 ዓመታት በላይ በኦክስጂን ማሽን ተደግፎ ሕይወቱን ለማስቀጠል እየታገለ ይገኛል።
በተነገረው መሰረት፣ ህመሙ በሳንባውና በአጥንቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሶበታል። በቅርቡም በሆስፒታል ቆይታው ወቅት ከባድ የደም መፍሰስ አጋጥሞት እንደነበር ተገልጿል።
ዳኒ በሙያው ሀገሩን በመወከል እስከ ስፔንና ስዊድን ድረስ በመጓዝ እውቅና ያገኘ ሲሆን፣ ከእርሱ ጋር የሠሩ የሙያ ባልደረቦቹ እንደሚናገሩት ችግሩን ለሰው ማካፈል የማይወድ እና ህመሙን በጸጥታ የሚታገል ሰው ነው።
በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ የህክምና ወጪው ከፍተኛ በመሆኑ፣ ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ከአቅማቸው በላይ እየጣሩ ቢሆንም፣ የህብረተሰቡን ድጋፍ እንደሚፈልጉ ተገልጿል።
የእርዳታ መለያ
- ባንክ: CBE
- የሂሳብ ቁጥር: 1000522370456
- ስም: ዳንኤል ታደሰ በላይነህ
- ስልክ: 0913 523751
ለዳኒ ፈጣን ማገገም እንመኛለን። መርዳት ለሚችሉ ሁሉ፣ በአቅማችሁ መጠን ድጋፍ ማድረግ እና መረጃውን ለሌሎች ማጋራት ትልቅ አስተዋጽኦ ሊሆን ይችላል።
#የፍቅርስጦታ
16 days ago
የአፋር ሕዝብ የህልውና ትግል እና የአሰብ እውነታ
***************
ከዳህላክ እና ምጽዋ ጀምሮ እስከ ታጁራ ድረስ ከአንድ ሺህ ኪሎሜትር በላይ በተዘረጋው የቀይ ባሕር ጠረፍ ላይ በመሃል ሌላ ማኅበረሰብ ሳይኖር ብቸኛ ነዋሪ የሆነው የአፋር ሕዝብ፣ ከእናት ሀገሩ ኢትዮጵያ እና ከተፈጥሮ መኖሪያ ምድሩ የተነጠለው በፍላጎቱ አልነበረም።
ይህ ሰፊ የባሕር ጠረፍ የሕዝቡ ተፈጥሯዊ መተንፈሻ እና የህልውናው መሠረት ቢሆንም፣ በፖለቲካዊ ሤራ ከባሕሩ እና ከወንድሞቹ እንዲገነጠል መደረጉን ኢቢሲ በጉዳዩ ዙሪያ ያሰናዳው ዘጋቢ ፊልም ይገልጻል።
በወቅቱ የአፋር ሕዝብ መሪ የነበሩት ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፈሬ በጊዜው የተደረገውን አፋርን ለሁለት ቆርጦ የመገንጠል ድርጊት አጥብቀው ተቃውመውት ነበር።
ሱልጣኑ የኤርትራ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን መብት አለው በሚል የአፋርን ሕዝብ ለሁለት በከፈለው የኤርትራ ሪፈረንደም ላይ የአፋር ሕዝብ ጥያቄ እንዳለው ጠቅሰው፣ "አፋር ከኢትዮጵያ ጋር ነው የሚገናኘው" በማለት በግልጽ ሞግተዋል።
የአፋር ቋንቋ ባህልና ታሪክ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀቢብ መሐመድ እንደሚሉት፣ ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፈሬ በወቅቱ አፋርን ለሁለት ከፍሎ የመገንጠልን ድርጊት በጽኑ ተቃውመዋል።
የአፋሮች መኖሪያ የሆነው የአሰብ አካባቢ እንዳይለማ እና እንዲራቆት መደረጉን የሚጠቅሱት ሀቢብ መሐመድ፣ ይህ የተደረገው አፋር ኢትዮጵያዊነቱን ስለሚያውቅ አንድ ቀን መመለሱ አይቀርም ብለው ስለሚፈሩ እንደሆነ ይናገራሉ።
የቀድሞ የአሰብ ከተማ ምክትል ከንቲባ አሊ ኢሳ መሐመድ፣ ሱልጣኑ "ዴሞክራሲ ከሆነ ኤርትራ ላለው የአፋር ሕዝብ ለምን የመምረጥ ዕድል አይሰጠውም?" ብለው ሲናገሩ፤ አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ስብሰባውን ረግጠው ወጥተው እንደነበር ያስታውሳሉ።
ይህ የዴሞክራሲ ጥያቄ ምላሽ በማጣቱ ሱልጣኑ ሀገር ለቅቀው እንዲወጡ ተገደዱ፤ አፋርም ሳይወድ በግድ ተከፈለ።
ኤርትራ ነጻ ሀገር ከሆነች በኋላ በቀይ ባሕር አፋሮች ላይ የደረሰው ሰቆቃ ዋነኛ ዓላማ ሕዝቡን ከተፈጥሮ ምድሩ ማላቀቅ እንደነበር አስተያየት ሰጪዎቹ ይናገራሉ።
አቶ ሀቢብ መሐመድ እንዳብራሩት፣ ኢሳይያስ አፈወርቂ ሥልጣን ከያዙ በኋላ የነበራቸው ድብቅ አጀንዳ አፋርን ከቀይ ባሕር ጠረፍ ሙሉ በሙሉ ማጽዳት ነበር።
የተፈለገው መሬቱ እንጂ ሕዝቡ ባለመሆኑ ማፈናቀል፣ ግድያ እና ንብረት መውረስ ስልታዊ በሆነ መንገድ ተፈጽሟል።
ከማፈናቀል ባለፈ ወጣቶችን ከ12ኛ ክፍል በኋላ ወደ ሳዋ ወታደራዊ ካምፕ በግድ በመውሰድ፣ ባህላቸውን እንዲረሱ የማድረግ የማንነት ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሟል።
የአፋር ቀይ ባሕር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር ኢብራሂም ሀሩን እንደሚሉት፣ ሳዋ የባህል እና የቋንቋ መጥፊያ ሲሆን፤ ሕዝቡ ሀገሩን ለቅቆ እንዲሄድ፣ የቀረው ደግሞ ቋንቋ እና ባህሉን እንዲተው ተገድዷል።
አሊ ኢሳ መሐመድ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በአካባቢው የነበረው የአፋር ሕዝብ ተፈጥሯዊ የዓሣ ማጥመድ ሥራ በማፊያዎች እና በሕገወጥ መረቦች እንዲወድም ተደርጓል።
ዓሣ የሚኖርበትን እና ኮራል ያለበትን አካባቢ ጠራርጎ በሚወስድ መረብ ባሕሩ እንዲቀየር ከመደረጉም በላይ፣ ማፊያዎች ሚሊዮን ዶላሮች እየተቀበሉ መርዛማ ቆሻሻዎችን ባሕሩ ውስጥ እንዲጥሉ ተደርጓል።
አፋሮች በተፈጥሮ ሀብታቸው እንዳይሠሩ መከልከላቸው እና ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ለእስር መዳረጋቸውም የዚሁ ግፍ አካል ነው።
የቀድሞው የአሰብ ምክትል ከንቲባ ለ13 ዓመታት ያለ ፍርድ መታሰራቸውን ገልጸው፣ ጉዳያቸው ለባህላዊው የአፋር ፍርድ (መድዓ) እንዳይቀርብ መከልከሉም የሕዝቡን ሕግ እና ባህል ለማጥፋት እንደሆነ አብራርተዋል።
የቀድሞው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ኤታማዦር ሹም ሌ/ጄኔራል ጻድቃን ገ/ተንሣይ እንዳብራሩት፣ የባህላዊው አውሳ ሱልጣኔት ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ፖለቲካዊ ማዕከል ኢትዮጵያ ውስጥ ነው።
ምንም እንኳን አርቲፊሻል ድንበሮች ተሰምረው ሕዝቡን ከባሕሩ ቢያርቁትም፣ የአፋር ሕዝብ ማዕከል ምንጊዜም ኢትዮጵያ መሆኗን ጄኔራል ጻድቃን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይህን እውነት ሲያጠናክሩ፣ የኤርትራም ሆነ የጅቡቲ አፋሮች በውክልና መጥተው ባህላዊ መሪያቸውን የሚመርጡት አሳይታ ላይ መሆኑን ጠቅሰው፣ የአውሳ ሱልጣኔት ማዕከሉ ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን አስምረውበታል።
ከሰላሳ ዓመታት ዝምታ በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰብን ጉዳይ ማንሳታቸው በአፋር ሕዝብ ዘንድ የፈጠረውን ወደር የለሽ ደስታ በተመለከተ ሀቢብ መሐመድ ሲገልጹ፣ "የአፋር ስሜቱ ገንፍሎ ወጥቷል፤ ከልክ በላይም ተደስቷል" ብለዋል።
ጥያቄያችን የዴሞክራሲ አይደለም የሚሉት የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር ኢብራሂም ሀሩን፣ ምክንያቱንም ሲያስረዱ "የአፋር ሕዝብ ይኖራል ወይስ አይኖርም?" የሚል የሕልውና ትግል ውስጥ በመገባቱ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
የተነጠቀውን ጠረፍ በመመለስ የአፋርን አንድነት ማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማስፈን እንዲሁም ታሪክን ከመደለዝ መታደግ የአፋር ሕዝብ አንገብጋቢ ጥያቄ መሆኑን ሊቀመንበሩ ያብራራሉ።
የቀይ ባሕር ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ከማንም በላይ ጥቅሙ የአፋር ሕዝብ መሆኑን የጠቀሱት ሀቢብ መሐመድ፣ ባሕሩ ወደ ባለቤቱ እንዲመለስ አፋር አስፈላጊውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #afar #seaaccess #seaport #redsea #assab #hornofafrica #ebc
***************
ከዳህላክ እና ምጽዋ ጀምሮ እስከ ታጁራ ድረስ ከአንድ ሺህ ኪሎሜትር በላይ በተዘረጋው የቀይ ባሕር ጠረፍ ላይ በመሃል ሌላ ማኅበረሰብ ሳይኖር ብቸኛ ነዋሪ የሆነው የአፋር ሕዝብ፣ ከእናት ሀገሩ ኢትዮጵያ እና ከተፈጥሮ መኖሪያ ምድሩ የተነጠለው በፍላጎቱ አልነበረም።
ይህ ሰፊ የባሕር ጠረፍ የሕዝቡ ተፈጥሯዊ መተንፈሻ እና የህልውናው መሠረት ቢሆንም፣ በፖለቲካዊ ሤራ ከባሕሩ እና ከወንድሞቹ እንዲገነጠል መደረጉን ኢቢሲ በጉዳዩ ዙሪያ ያሰናዳው ዘጋቢ ፊልም ይገልጻል።
በወቅቱ የአፋር ሕዝብ መሪ የነበሩት ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፈሬ በጊዜው የተደረገውን አፋርን ለሁለት ቆርጦ የመገንጠል ድርጊት አጥብቀው ተቃውመውት ነበር።
ሱልጣኑ የኤርትራ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን መብት አለው በሚል የአፋርን ሕዝብ ለሁለት በከፈለው የኤርትራ ሪፈረንደም ላይ የአፋር ሕዝብ ጥያቄ እንዳለው ጠቅሰው፣ "አፋር ከኢትዮጵያ ጋር ነው የሚገናኘው" በማለት በግልጽ ሞግተዋል።
የአፋር ቋንቋ ባህልና ታሪክ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀቢብ መሐመድ እንደሚሉት፣ ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፈሬ በወቅቱ አፋርን ለሁለት ከፍሎ የመገንጠልን ድርጊት በጽኑ ተቃውመዋል።
የአፋሮች መኖሪያ የሆነው የአሰብ አካባቢ እንዳይለማ እና እንዲራቆት መደረጉን የሚጠቅሱት ሀቢብ መሐመድ፣ ይህ የተደረገው አፋር ኢትዮጵያዊነቱን ስለሚያውቅ አንድ ቀን መመለሱ አይቀርም ብለው ስለሚፈሩ እንደሆነ ይናገራሉ።
የቀድሞ የአሰብ ከተማ ምክትል ከንቲባ አሊ ኢሳ መሐመድ፣ ሱልጣኑ "ዴሞክራሲ ከሆነ ኤርትራ ላለው የአፋር ሕዝብ ለምን የመምረጥ ዕድል አይሰጠውም?" ብለው ሲናገሩ፤ አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ስብሰባውን ረግጠው ወጥተው እንደነበር ያስታውሳሉ።
ይህ የዴሞክራሲ ጥያቄ ምላሽ በማጣቱ ሱልጣኑ ሀገር ለቅቀው እንዲወጡ ተገደዱ፤ አፋርም ሳይወድ በግድ ተከፈለ።
ኤርትራ ነጻ ሀገር ከሆነች በኋላ በቀይ ባሕር አፋሮች ላይ የደረሰው ሰቆቃ ዋነኛ ዓላማ ሕዝቡን ከተፈጥሮ ምድሩ ማላቀቅ እንደነበር አስተያየት ሰጪዎቹ ይናገራሉ።
አቶ ሀቢብ መሐመድ እንዳብራሩት፣ ኢሳይያስ አፈወርቂ ሥልጣን ከያዙ በኋላ የነበራቸው ድብቅ አጀንዳ አፋርን ከቀይ ባሕር ጠረፍ ሙሉ በሙሉ ማጽዳት ነበር።
የተፈለገው መሬቱ እንጂ ሕዝቡ ባለመሆኑ ማፈናቀል፣ ግድያ እና ንብረት መውረስ ስልታዊ በሆነ መንገድ ተፈጽሟል።
ከማፈናቀል ባለፈ ወጣቶችን ከ12ኛ ክፍል በኋላ ወደ ሳዋ ወታደራዊ ካምፕ በግድ በመውሰድ፣ ባህላቸውን እንዲረሱ የማድረግ የማንነት ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሟል።
የአፋር ቀይ ባሕር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር ኢብራሂም ሀሩን እንደሚሉት፣ ሳዋ የባህል እና የቋንቋ መጥፊያ ሲሆን፤ ሕዝቡ ሀገሩን ለቅቆ እንዲሄድ፣ የቀረው ደግሞ ቋንቋ እና ባህሉን እንዲተው ተገድዷል።
አሊ ኢሳ መሐመድ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በአካባቢው የነበረው የአፋር ሕዝብ ተፈጥሯዊ የዓሣ ማጥመድ ሥራ በማፊያዎች እና በሕገወጥ መረቦች እንዲወድም ተደርጓል።
ዓሣ የሚኖርበትን እና ኮራል ያለበትን አካባቢ ጠራርጎ በሚወስድ መረብ ባሕሩ እንዲቀየር ከመደረጉም በላይ፣ ማፊያዎች ሚሊዮን ዶላሮች እየተቀበሉ መርዛማ ቆሻሻዎችን ባሕሩ ውስጥ እንዲጥሉ ተደርጓል።
አፋሮች በተፈጥሮ ሀብታቸው እንዳይሠሩ መከልከላቸው እና ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ለእስር መዳረጋቸውም የዚሁ ግፍ አካል ነው።
የቀድሞው የአሰብ ምክትል ከንቲባ ለ13 ዓመታት ያለ ፍርድ መታሰራቸውን ገልጸው፣ ጉዳያቸው ለባህላዊው የአፋር ፍርድ (መድዓ) እንዳይቀርብ መከልከሉም የሕዝቡን ሕግ እና ባህል ለማጥፋት እንደሆነ አብራርተዋል።
የቀድሞው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ኤታማዦር ሹም ሌ/ጄኔራል ጻድቃን ገ/ተንሣይ እንዳብራሩት፣ የባህላዊው አውሳ ሱልጣኔት ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ፖለቲካዊ ማዕከል ኢትዮጵያ ውስጥ ነው።
ምንም እንኳን አርቲፊሻል ድንበሮች ተሰምረው ሕዝቡን ከባሕሩ ቢያርቁትም፣ የአፋር ሕዝብ ማዕከል ምንጊዜም ኢትዮጵያ መሆኗን ጄኔራል ጻድቃን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይህን እውነት ሲያጠናክሩ፣ የኤርትራም ሆነ የጅቡቲ አፋሮች በውክልና መጥተው ባህላዊ መሪያቸውን የሚመርጡት አሳይታ ላይ መሆኑን ጠቅሰው፣ የአውሳ ሱልጣኔት ማዕከሉ ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን አስምረውበታል።
ከሰላሳ ዓመታት ዝምታ በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰብን ጉዳይ ማንሳታቸው በአፋር ሕዝብ ዘንድ የፈጠረውን ወደር የለሽ ደስታ በተመለከተ ሀቢብ መሐመድ ሲገልጹ፣ "የአፋር ስሜቱ ገንፍሎ ወጥቷል፤ ከልክ በላይም ተደስቷል" ብለዋል።
ጥያቄያችን የዴሞክራሲ አይደለም የሚሉት የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር ኢብራሂም ሀሩን፣ ምክንያቱንም ሲያስረዱ "የአፋር ሕዝብ ይኖራል ወይስ አይኖርም?" የሚል የሕልውና ትግል ውስጥ በመገባቱ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
የተነጠቀውን ጠረፍ በመመለስ የአፋርን አንድነት ማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማስፈን እንዲሁም ታሪክን ከመደለዝ መታደግ የአፋር ሕዝብ አንገብጋቢ ጥያቄ መሆኑን ሊቀመንበሩ ያብራራሉ።
የቀይ ባሕር ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ከማንም በላይ ጥቅሙ የአፋር ሕዝብ መሆኑን የጠቀሱት ሀቢብ መሐመድ፣ ባሕሩ ወደ ባለቤቱ እንዲመለስ አፋር አስፈላጊውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #afar #seaaccess #seaport #redsea #assab #hornofafrica #ebc
Sponsored by
Surafel
17 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) በሆሊውድ ዝነኛ የብሎክባስተር ፊልሞች "Godzilla vs. Kong" እና "Godzilla x Kong: The New Empire" ላይ “ጂያ” የተሰኘውን ቁልፍ ገጸ-ባህሪ በመወከል የምትታወቀው የ18 ዓመቷ መስማት የተሳናት ወጣት ተዋናይት ኬይሊ ሆትል ማክሰኞ ጠዋት በደረሰባት ድንገተኛ የመኪና አደጋ ሕይወቷ ማለፉን ፎክስ ኒውስ ዲጂታል አረጋግጧል።
የተዋናይቷ አባት ጆሹዋ ሆትል በሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ስለደረሰው አደጋ በሰጠውና በፌስቡክ በኩል ባስተላለፈው የ23 ደቂቃ የአሜሪካ የምልክት ቋንቋ (ASL) ቀጥታ ስርጭት መግለጫ፣ ልጁ ወደ ሆስፒታል በመጓዝ ላይ እያለች ልቧ መቆሙን በለቅሶ አስታውቋል። ከተከታታይ መስማት የተሳናቸው ትውልዶች በተገኘችውና የቨርጂኒያ ተወላጅ በሆነችው ኬይሊ ሆትል ሞት ሳቢያ መላው የሆሊውድ የኪነ-ጥበብ ማኅበረሰብ በከባድ ሐዘን ውስጥ ወድቋል።
ይህንን ልብ ሰባሪ ክስተት እና የተዋናይቷን አጭር የሕይወት ጉዞ በጥልቀት ስንመለከተው ኬይሊ በሆሊውድ ውስጥ በገንዘብና በጥቅም ብቻ በሚመራው የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ መስማት ለተሳናቸው አካላት እውነተኛና ተጨባጭ የውክልና መድረክ የፈጠረች ስልታዊ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆኗን ያሳያል። በ2021 ዓ.ም. “ጎድዚላ ቨርሰስ ኮንግ” በተሰኘው ታላቅ ፊልም ላይ ከግዙፉ “ኮንግ” ጋር ልዩ የልብ ትስስር ያላትን የጂያን ገጸ-ባህሪ ወክላ ስትወጣ፣ በሆሊውድ ታሪክ ውስጥ መስማት የተሳናቸው ተዋናዮች በትልልቅ የሳይንስ ልብወለድ ፊልሞች ላይ የመሪነት ሚና መጫወት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየች ድንቅ ተሰጥኦ ነበረች።
በ2024 ዓ.ም. በወጣው ሁለተኛው ፊልም ላይም የምልክት ቋንቋን በፊልሙ ውስጥ በስፋት በማስተዋወቅ የራሷን ደማቅ አሻራ አኑራለች።
በተጨማሪም፣ ኬይሊ ሆትል ወደ ትልቁ የፊልም ዓለም ከመግባቷ በፊትም ቢሆን በተለያዩ የንግድ ማስታወቂያዎችና የጥበቃ ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ መስማት ለተሳናቸው ማኅበረሰቦች እኩል ዕድል እንዲሰጥ ስትሟገት የቆየች የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ጭምር ነበረች። ምንም እንኳን ገና በለጋ ዕድሜዋ መክሰሟ እና በሲኒማው ዓለም የጀመረችው ደማቅ ጉዞ በአሰቃቂ የመኪና አደጋ በአጭር የተቀጨ ቢሆንም፣ በሆሊውድ ውስጥ ያሉ መስማት የተሳናቸው ወጣት ተዋናዮች የወደፊት ዕድል እንዲቀየርና ማግለል እንዲቆም ያደረገችው ተጋድሎ ግን ዘላቂ ውርስ ሆኖ የሚቀጥል መሆኑን የፊልም ኢንዱስትሪ ተንታኞች በጥብቅ ያመለክታሉ።
የተዋናይቷ አባት ጆሹዋ ሆትል በሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ስለደረሰው አደጋ በሰጠውና በፌስቡክ በኩል ባስተላለፈው የ23 ደቂቃ የአሜሪካ የምልክት ቋንቋ (ASL) ቀጥታ ስርጭት መግለጫ፣ ልጁ ወደ ሆስፒታል በመጓዝ ላይ እያለች ልቧ መቆሙን በለቅሶ አስታውቋል። ከተከታታይ መስማት የተሳናቸው ትውልዶች በተገኘችውና የቨርጂኒያ ተወላጅ በሆነችው ኬይሊ ሆትል ሞት ሳቢያ መላው የሆሊውድ የኪነ-ጥበብ ማኅበረሰብ በከባድ ሐዘን ውስጥ ወድቋል።
ይህንን ልብ ሰባሪ ክስተት እና የተዋናይቷን አጭር የሕይወት ጉዞ በጥልቀት ስንመለከተው ኬይሊ በሆሊውድ ውስጥ በገንዘብና በጥቅም ብቻ በሚመራው የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ መስማት ለተሳናቸው አካላት እውነተኛና ተጨባጭ የውክልና መድረክ የፈጠረች ስልታዊ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆኗን ያሳያል። በ2021 ዓ.ም. “ጎድዚላ ቨርሰስ ኮንግ” በተሰኘው ታላቅ ፊልም ላይ ከግዙፉ “ኮንግ” ጋር ልዩ የልብ ትስስር ያላትን የጂያን ገጸ-ባህሪ ወክላ ስትወጣ፣ በሆሊውድ ታሪክ ውስጥ መስማት የተሳናቸው ተዋናዮች በትልልቅ የሳይንስ ልብወለድ ፊልሞች ላይ የመሪነት ሚና መጫወት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየች ድንቅ ተሰጥኦ ነበረች።
በ2024 ዓ.ም. በወጣው ሁለተኛው ፊልም ላይም የምልክት ቋንቋን በፊልሙ ውስጥ በስፋት በማስተዋወቅ የራሷን ደማቅ አሻራ አኑራለች።
በተጨማሪም፣ ኬይሊ ሆትል ወደ ትልቁ የፊልም ዓለም ከመግባቷ በፊትም ቢሆን በተለያዩ የንግድ ማስታወቂያዎችና የጥበቃ ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ መስማት ለተሳናቸው ማኅበረሰቦች እኩል ዕድል እንዲሰጥ ስትሟገት የቆየች የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ጭምር ነበረች። ምንም እንኳን ገና በለጋ ዕድሜዋ መክሰሟ እና በሲኒማው ዓለም የጀመረችው ደማቅ ጉዞ በአሰቃቂ የመኪና አደጋ በአጭር የተቀጨ ቢሆንም፣ በሆሊውድ ውስጥ ያሉ መስማት የተሳናቸው ወጣት ተዋናዮች የወደፊት ዕድል እንዲቀየርና ማግለል እንዲቆም ያደረገችው ተጋድሎ ግን ዘላቂ ውርስ ሆኖ የሚቀጥል መሆኑን የፊልም ኢንዱስትሪ ተንታኞች በጥብቅ ያመለክታሉ።
19 days ago
ዓለምን ዳግም ወደ ስጋት የከተተው የቴህራን እና ዋሽንግተን ወታደራዊ ግጭት
**********************
ባለፈው ወር በፓኪስታን አጋዥነት የተደረሰው የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ መፍረሱን ተከትሎ፣ በሁለቱ ኃይላት መካከል ለቀናት የቀጠለው ጥቃት የቀጣናውን የጸጥታና የዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ መስመር ከባድ ሥጋት ላይ ጥሎታል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፍ ሕግጋትን ወደ መጣስ እና የኒውክሌር ተቋማትን ወደ ማጥቃት የተሸጋገረው ይህ አደገኛ ምዕራፍ፣ መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ሊከተው የሚችል አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የግጭቱ መነሻ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ይፋ ባደረገው መግለጫ መሠረት፣ በዮርዳኖስ በሚገኝ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ በተሰነዘረ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውንና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች መውደማቸውን ተከትሎ የተከሰተ ነው።
ዋሽንግተን ለዚህ አጸፋዊ ምላሽ ይሆን ዘንድ በደቡባዊና ደቡብ ምዕራብ ኢራን በሚገኘው የዳርክሆቨይን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ ቦታ ላይ ሳይቀር ያነጣጠረ የሚሳኤል ጥቃት ፈጽማለች።
ፔንታገን ጥቃቱን በቀጥታ ከማረጋገጥም ሆነ ከመካድ የተቆጠበ ቢሆንም፣ "አሜሪካ ወታደሮቿን ከጥቃት ለመከላከልና የኢራንን የማጥቃት አቅም ለማዳከም ማንኛውንም እርምጃ ትወስዳለች" ሲል ድርጊቱን በተዘዋዋሪ ተከላክሏል፤ ጥቃቶቹም በዋናነት የኢራንን ወታደራዊ የሎጅስቲክስ መሠረተ-ልማቶች ላይ ያነጣጠሩ መሆቸውን ትሟገታለች።
ይሁን እንጂ የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ጥቃቱን "የሀገሪቱን የሳይንስ ዕድገትና ነጻነት ለማደናቀፍ የታለመ አረመኔያዊ የሽብር ድርጊት" ሲል በጽኑ ኮንኖታል።
ቴህራን ተቋሙ ሙሉ በሙሉ ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የደኅንነት ጥበቃ ሥርዓት ተገዢና ሰላማዊ መሆኑን በመጥቀስ፣ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሕግን በግልጽ መጣሷን አስታውቃለች።
በአሜሪካ የአየር ጥቃቶች ሳቢያ እስካሁን በኢራን ቢያንስ 50 ሰዎች መገደላቸውንና ከ500 በላይ መቁሰላቸውን የገለጸው የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር፣ በርካታ ድልድዮችና ሲቪል መሠረተ-ልማቶች መውደማቸውን አረጋግጧል።
ለአሜሪካ ጥቃት የኢራን ወታደራዊ ምላሽ ፈጣንና መጠነ-ሰፊ የነበረ ሲሆን፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኃይል "ናስር-2" የተሰኘውንና 20ኛ ምዕራፍ ላይ የደረሰውን የሚሳኤልና የድሮን ጥቃት የሰነዘረ ሲሆን፣ የኢራን መደበኛ ጦር በበኩሉ "ሳዕቃ" የተሰኘውን 15ኛ ምዕራፍ የጥቃት ዘመቻ አካሂዷል።
በጥቃቶቹ በኩዌት የሚገኘው አሊ አል-ሳሌም የአየር ኃይል ሰፈር፣ ካምፕ አሪፍጃን፣ ካምፕ አዳይሪ እና ሚና አብዱላህ የተሰኘው የሎጂስቲክስ ማዕከል በከባድ ሁኔታ ተመተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ፣ በባህሬን የሚገኘው የአሜሪካ አምስተኛ ፍሊት ዋና መሥሪያ ቤት እና በዮርዳኖስ በሚገኘው አል-አዝራቅ የአየር ኃይል ሰፈር ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። ምንም እንኳ የአሜሪካ እና የባሕረ-ሰላጤው አገራት መከላከያ ተቋማት አብዛኞቹን የኢራን ሚሳኤሎችና ድሮኖች ማክሸፋቸውን በይፋ ቢገልጹም፣ የወጡ የሳተላይት ምስሎች ግን የተለየ እውነታ እያሳዩ ነው።
የዋሽንግተን ፖስት የምርመራ ሪፖርት እንደሚያመለክተው፣ በክልሉ በሚገኙ 15 የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ውስጥ የራዳር ሥርዓቶች፣ የፓትሪዮት መከላከያ መሣሪያዎች እና የመጋዘን ተቋማትን ጨምሮ 228 መዋቅሮች በከፊልም ሆነ በሙሉ መውደማቸውን አረጋግጧል።
ይህ ወታደራዊ መካረር በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ መናወጥን አስከትሏል። የኢራንን ይፋዊ አቤቱታ ተከትሎ፣ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ባወጡት መግለጫ፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች ቁጥር 444 እና 533 መሠረት፣ በሰላማዊ የኒውክሌር ተቋማት ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት ዓለም አቀፍ ሕግን የሚጥስ መሆኑን አስታውሰዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ በበኩላቸው፣ የኒውክሌር ተቋማትን ኢላማ ማድረግ የቀጣናውን ውጥረት ወደማይመለስ አደገኛ አደጋ ሊቀይረው እንደሚችል አስጠንቅቀው፣ የጸጥታው ምክር ቤት በአስቸኳይ እንዲመክርና ሁለቱም ወገኖች ራስን የመግታት እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል።
"የኒውክሌር መሠረተ-ልማቶችን ማጥቃት ቀጣናውን ብቻ ሳይሆን መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ውስጥ የሚከት አደገኛ ድርጊት ነው" የሚለው የሰላም ጥሪ መግለጫ የሁኔታውን አሳሳቢነት በግልጽ ያሳያል።
በፖለቲካው ረገድ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የቃላት መለዋወጥ ይበልጥ ጠንክሯል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን በኩዌትና ባህሬን ላሉት የጦር ሰፈሮቿ ተጨማሪ የአየር መከላከያ ዘዴዎችን በፍጥነት ለማስፈር እያቀደች መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ኢራን የኒውክሌር ታጣቂ እንድትሆን ፈጽሞ እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን መንፈሣዊ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ እና የፓርላማው አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባቄር ቃሊባፍ፣ ዋሽንግተን ስምምነቱን በተጠቀሰው መሠረት ደጋግማ መጣሷ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ፊርማ ፍጹም ዋጋ ቢስ መሆኑን ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የሀገሪቱን ደኅንነት ለማረጋገጥ መላው የኢራን ሕዝብ ቅዱስ ያሉት "አንድነት" እንዲኖረው ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዋሽንግተን በኢራን ወደቦች ላይ የባሕር እገዳ ለመጣል መሞከሯን ተከትሎ፣ ቴህራን በበኩሏ የዓለም የነዳጅ ንግድ ወሳኝ የደም ሥር የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥ ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆኑን አውጃለች።
ይህንን የባሕረ-ሰላጤው መዘጋት ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋ (Brent Crude) በአንድ ጀምበር ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ተንታኞች ውጥረቱ በዚህ የሚቀጥል ከሆነ በተለይ በእስያ እና በአውሮፓ አገራት ላይ ከባድ የነዳጅ እጥረትና የዋጋ ግሽበት ሊከሰት እንደሚችልና የንግድ መርከቦች ረጅም ርቀት ወደሚጠይቀው የአፍሪካ አቅጣጫ መስመራቸውን ለመቀየር እየተገደዱ መሆኑን እየገለጹ ይገኛሉ።
ፍጥጫው ወታደራዊ ጡንቻን ከማሳየት አልፎ የዓለምን መደበኛ የኢኮኖሚና የጸጥታ መዋቅር የቀየረ ታሪካዊ ቀውስ ሆኗል።
በሰለሞን ገዳ
**********************
ባለፈው ወር በፓኪስታን አጋዥነት የተደረሰው የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ መፍረሱን ተከትሎ፣ በሁለቱ ኃይላት መካከል ለቀናት የቀጠለው ጥቃት የቀጣናውን የጸጥታና የዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ መስመር ከባድ ሥጋት ላይ ጥሎታል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፍ ሕግጋትን ወደ መጣስ እና የኒውክሌር ተቋማትን ወደ ማጥቃት የተሸጋገረው ይህ አደገኛ ምዕራፍ፣ መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ሊከተው የሚችል አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የግጭቱ መነሻ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ይፋ ባደረገው መግለጫ መሠረት፣ በዮርዳኖስ በሚገኝ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ በተሰነዘረ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውንና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች መውደማቸውን ተከትሎ የተከሰተ ነው።
ዋሽንግተን ለዚህ አጸፋዊ ምላሽ ይሆን ዘንድ በደቡባዊና ደቡብ ምዕራብ ኢራን በሚገኘው የዳርክሆቨይን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ ቦታ ላይ ሳይቀር ያነጣጠረ የሚሳኤል ጥቃት ፈጽማለች።
ፔንታገን ጥቃቱን በቀጥታ ከማረጋገጥም ሆነ ከመካድ የተቆጠበ ቢሆንም፣ "አሜሪካ ወታደሮቿን ከጥቃት ለመከላከልና የኢራንን የማጥቃት አቅም ለማዳከም ማንኛውንም እርምጃ ትወስዳለች" ሲል ድርጊቱን በተዘዋዋሪ ተከላክሏል፤ ጥቃቶቹም በዋናነት የኢራንን ወታደራዊ የሎጅስቲክስ መሠረተ-ልማቶች ላይ ያነጣጠሩ መሆቸውን ትሟገታለች።
ይሁን እንጂ የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ጥቃቱን "የሀገሪቱን የሳይንስ ዕድገትና ነጻነት ለማደናቀፍ የታለመ አረመኔያዊ የሽብር ድርጊት" ሲል በጽኑ ኮንኖታል።
ቴህራን ተቋሙ ሙሉ በሙሉ ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የደኅንነት ጥበቃ ሥርዓት ተገዢና ሰላማዊ መሆኑን በመጥቀስ፣ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሕግን በግልጽ መጣሷን አስታውቃለች።
በአሜሪካ የአየር ጥቃቶች ሳቢያ እስካሁን በኢራን ቢያንስ 50 ሰዎች መገደላቸውንና ከ500 በላይ መቁሰላቸውን የገለጸው የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር፣ በርካታ ድልድዮችና ሲቪል መሠረተ-ልማቶች መውደማቸውን አረጋግጧል።
ለአሜሪካ ጥቃት የኢራን ወታደራዊ ምላሽ ፈጣንና መጠነ-ሰፊ የነበረ ሲሆን፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኃይል "ናስር-2" የተሰኘውንና 20ኛ ምዕራፍ ላይ የደረሰውን የሚሳኤልና የድሮን ጥቃት የሰነዘረ ሲሆን፣ የኢራን መደበኛ ጦር በበኩሉ "ሳዕቃ" የተሰኘውን 15ኛ ምዕራፍ የጥቃት ዘመቻ አካሂዷል።
በጥቃቶቹ በኩዌት የሚገኘው አሊ አል-ሳሌም የአየር ኃይል ሰፈር፣ ካምፕ አሪፍጃን፣ ካምፕ አዳይሪ እና ሚና አብዱላህ የተሰኘው የሎጂስቲክስ ማዕከል በከባድ ሁኔታ ተመተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ፣ በባህሬን የሚገኘው የአሜሪካ አምስተኛ ፍሊት ዋና መሥሪያ ቤት እና በዮርዳኖስ በሚገኘው አል-አዝራቅ የአየር ኃይል ሰፈር ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። ምንም እንኳ የአሜሪካ እና የባሕረ-ሰላጤው አገራት መከላከያ ተቋማት አብዛኞቹን የኢራን ሚሳኤሎችና ድሮኖች ማክሸፋቸውን በይፋ ቢገልጹም፣ የወጡ የሳተላይት ምስሎች ግን የተለየ እውነታ እያሳዩ ነው።
የዋሽንግተን ፖስት የምርመራ ሪፖርት እንደሚያመለክተው፣ በክልሉ በሚገኙ 15 የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ውስጥ የራዳር ሥርዓቶች፣ የፓትሪዮት መከላከያ መሣሪያዎች እና የመጋዘን ተቋማትን ጨምሮ 228 መዋቅሮች በከፊልም ሆነ በሙሉ መውደማቸውን አረጋግጧል።
ይህ ወታደራዊ መካረር በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ መናወጥን አስከትሏል። የኢራንን ይፋዊ አቤቱታ ተከትሎ፣ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ባወጡት መግለጫ፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች ቁጥር 444 እና 533 መሠረት፣ በሰላማዊ የኒውክሌር ተቋማት ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት ዓለም አቀፍ ሕግን የሚጥስ መሆኑን አስታውሰዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ በበኩላቸው፣ የኒውክሌር ተቋማትን ኢላማ ማድረግ የቀጣናውን ውጥረት ወደማይመለስ አደገኛ አደጋ ሊቀይረው እንደሚችል አስጠንቅቀው፣ የጸጥታው ምክር ቤት በአስቸኳይ እንዲመክርና ሁለቱም ወገኖች ራስን የመግታት እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል።
"የኒውክሌር መሠረተ-ልማቶችን ማጥቃት ቀጣናውን ብቻ ሳይሆን መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ውስጥ የሚከት አደገኛ ድርጊት ነው" የሚለው የሰላም ጥሪ መግለጫ የሁኔታውን አሳሳቢነት በግልጽ ያሳያል።
በፖለቲካው ረገድ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የቃላት መለዋወጥ ይበልጥ ጠንክሯል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን በኩዌትና ባህሬን ላሉት የጦር ሰፈሮቿ ተጨማሪ የአየር መከላከያ ዘዴዎችን በፍጥነት ለማስፈር እያቀደች መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ኢራን የኒውክሌር ታጣቂ እንድትሆን ፈጽሞ እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን መንፈሣዊ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ እና የፓርላማው አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባቄር ቃሊባፍ፣ ዋሽንግተን ስምምነቱን በተጠቀሰው መሠረት ደጋግማ መጣሷ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ፊርማ ፍጹም ዋጋ ቢስ መሆኑን ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የሀገሪቱን ደኅንነት ለማረጋገጥ መላው የኢራን ሕዝብ ቅዱስ ያሉት "አንድነት" እንዲኖረው ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዋሽንግተን በኢራን ወደቦች ላይ የባሕር እገዳ ለመጣል መሞከሯን ተከትሎ፣ ቴህራን በበኩሏ የዓለም የነዳጅ ንግድ ወሳኝ የደም ሥር የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥ ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆኑን አውጃለች።
ይህንን የባሕረ-ሰላጤው መዘጋት ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋ (Brent Crude) በአንድ ጀምበር ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ተንታኞች ውጥረቱ በዚህ የሚቀጥል ከሆነ በተለይ በእስያ እና በአውሮፓ አገራት ላይ ከባድ የነዳጅ እጥረትና የዋጋ ግሽበት ሊከሰት እንደሚችልና የንግድ መርከቦች ረጅም ርቀት ወደሚጠይቀው የአፍሪካ አቅጣጫ መስመራቸውን ለመቀየር እየተገደዱ መሆኑን እየገለጹ ይገኛሉ።
ፍጥጫው ወታደራዊ ጡንቻን ከማሳየት አልፎ የዓለምን መደበኛ የኢኮኖሚና የጸጥታ መዋቅር የቀየረ ታሪካዊ ቀውስ ሆኗል።
በሰለሞን ገዳ
19 days ago
(ዘ-ሐበሻ መዝናኛ ዜና) ኪነ-ጥበብ ድንበር የለውም፤ የሀገርን ማንነት፣ ባህልና ታሪክ ተሸክሞ የዓለምን ማዕዘናት ሁሉ ያቋርጣል። አሁን ደግሞ ተራው የኢትዮጵያ ሲኒማ ሆኗል። በዳይሬክተር አብርሃም ገዛኸኝ ልዩ ጥበባዊ እይታ እና በፕሮዲውሰር ታማራ ማርያም ዳዊት ስልታዊ ዝግጅት የተጠነሰሰው «መሀል ሰፋሪ» የተሰኘው አዲስ የኢትዮጵያ ፊልም፣ በዓለም ፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ እጅግ ስመ-ጥር በሆነው በ83ኛው የቬኒስ ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል ላይ በኩራት እንዲመረጥ ሆኗል። ይህ ምርጫ ተራ ስኬት አይደለም፤ ፊልሙ በፌስቲቫሉ እጅግ ተፈላጊ በሆነው "Final Cut" መርሃ ግብር ላይ ከተመረጡ ስድስት ምርጥ የመጀመሪያ ደረጃ ኤዲቲንግ ረቂቅ ፊልሞች መካከል አንዱ መሆን መቻሉን የሚያበስር ትልቅ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
ይህ ጥበባዊ ፍጥረት በመጪው መስከረም ወር ማራኪ ውበት ወደተላበሰችው የጣሊያን ምድር በመጓዝ፣ ለዓለም አቀፍ የፊልም ባለሙያዎች፣ የፊልም ሽያጭ ድርጅቶች፣ አከፋፋዮችና አዘጋጆች ለእይታ ይበቃል። መድረኩ በመጀርያ ደረጃ ኤዲቲንግ ላይ ለሚገኙ የፈጠራ ሥራዎች የድህረ ፕሮዳክሽን ሥራዎቻቸውን በከፍተኛ የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ አጠናቀው ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲገቡ ሰፊ በር የሚከፍት ታላቅ የዕድል ድልድይ ነው። የፊልሙ ፈጣሪዎች የኢትዮጵያን ጥልቅ ታሪክና ባህል ይዘው በዚህ ታሪካዊ መድረክ ላይ ለመቅረብ በመቻላቸው የተሰማቸውን ታላቅ ኩራትና የላቀ ደስታ ሲገልጹ፣ ሥራው እዚህ እንዲደርስ ከጎናቸው ለቆሙትና በሀገራችን የመዝናኛ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንደ "በስንቱ" እና "የእግር እሳት" ባሉ ተወዳጅ ድራማዎች ስሙ በግንባር ቀደምትነት ለሚነሳው አብሪኮም መልቲሚዲያ፣ እንዲሁም ለጎበዝ፣ ቱ ፓይለትስ፣ ባሬንትስ እና ኒው አምስተርዳም የፊልም ኩባንያዎች የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የአንድ ፊልም ነፍስ በገጸ-ባህሪያቱ ውስጥ በሚነፍሱ ተዋናዮች ላይ የተመሠረተ ነው። «መሀል ሰፋሪ» በሀገራችን የኪነ-ጥበብ አድማስ ውስጥ ትልቅ ክብርና ተወዳጅነትን ያተረፉትን የነጋሲዎቹን ተዋናዮች ብቃት ይዞ ብቅ ብሏል። ታዋቂዎቹ አርቲስቶች ግሩም ዘነበ፣ አበበ ባልቻ እና ፀደይ ፋንታሁን በፊልሙ ላይ ላሳዩት ወሳኝና ተደናቂ አስተዋጽኦ የፊልሙ አዘጋጆች ትልቅ አድናቆት የቸሯቸው ሲሆን፣ የእነሱ ድንቅ አተዋወን ፊልሙን ዓለም አቀፍ መስፈርት እንዲያሟላ ማድረጉም ይነገራል።
እ.ኤ.አ በ1932 የተመሠረተው የቬኒስ የፊልም ፌስቲቫል በዓለም ላይ ካሉ እጅግ አንጋፋና ጥንታዊ መድረኮች አንዱ እንደመሆኑ መጠን፣ «መሀል ሰፋሪ» በዚህ መድረክ ላይ መመረጡ የኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ወደ አዲስ ከፍታ እየተጋገዘ መሆኑን ያበስራል።
በሀገር ውስጥ የጥበብ አሻራውን እያኖረ ያለው አብሪኮም መልቲሚዲያ እና ቡድኑ በጣሊያን መድረክ ላይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ አድርገው ለማንሳትና የሀገራችንን ታሪክ ለዓለም ለማስተዋወቅ በጉጉት መስከረምን እየተጠባበቁ ይገኛሉ።
ይህ ጥበባዊ ፍጥረት በመጪው መስከረም ወር ማራኪ ውበት ወደተላበሰችው የጣሊያን ምድር በመጓዝ፣ ለዓለም አቀፍ የፊልም ባለሙያዎች፣ የፊልም ሽያጭ ድርጅቶች፣ አከፋፋዮችና አዘጋጆች ለእይታ ይበቃል። መድረኩ በመጀርያ ደረጃ ኤዲቲንግ ላይ ለሚገኙ የፈጠራ ሥራዎች የድህረ ፕሮዳክሽን ሥራዎቻቸውን በከፍተኛ የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ አጠናቀው ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲገቡ ሰፊ በር የሚከፍት ታላቅ የዕድል ድልድይ ነው። የፊልሙ ፈጣሪዎች የኢትዮጵያን ጥልቅ ታሪክና ባህል ይዘው በዚህ ታሪካዊ መድረክ ላይ ለመቅረብ በመቻላቸው የተሰማቸውን ታላቅ ኩራትና የላቀ ደስታ ሲገልጹ፣ ሥራው እዚህ እንዲደርስ ከጎናቸው ለቆሙትና በሀገራችን የመዝናኛ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንደ "በስንቱ" እና "የእግር እሳት" ባሉ ተወዳጅ ድራማዎች ስሙ በግንባር ቀደምትነት ለሚነሳው አብሪኮም መልቲሚዲያ፣ እንዲሁም ለጎበዝ፣ ቱ ፓይለትስ፣ ባሬንትስ እና ኒው አምስተርዳም የፊልም ኩባንያዎች የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የአንድ ፊልም ነፍስ በገጸ-ባህሪያቱ ውስጥ በሚነፍሱ ተዋናዮች ላይ የተመሠረተ ነው። «መሀል ሰፋሪ» በሀገራችን የኪነ-ጥበብ አድማስ ውስጥ ትልቅ ክብርና ተወዳጅነትን ያተረፉትን የነጋሲዎቹን ተዋናዮች ብቃት ይዞ ብቅ ብሏል። ታዋቂዎቹ አርቲስቶች ግሩም ዘነበ፣ አበበ ባልቻ እና ፀደይ ፋንታሁን በፊልሙ ላይ ላሳዩት ወሳኝና ተደናቂ አስተዋጽኦ የፊልሙ አዘጋጆች ትልቅ አድናቆት የቸሯቸው ሲሆን፣ የእነሱ ድንቅ አተዋወን ፊልሙን ዓለም አቀፍ መስፈርት እንዲያሟላ ማድረጉም ይነገራል።
እ.ኤ.አ በ1932 የተመሠረተው የቬኒስ የፊልም ፌስቲቫል በዓለም ላይ ካሉ እጅግ አንጋፋና ጥንታዊ መድረኮች አንዱ እንደመሆኑ መጠን፣ «መሀል ሰፋሪ» በዚህ መድረክ ላይ መመረጡ የኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ወደ አዲስ ከፍታ እየተጋገዘ መሆኑን ያበስራል።
በሀገር ውስጥ የጥበብ አሻራውን እያኖረ ያለው አብሪኮም መልቲሚዲያ እና ቡድኑ በጣሊያን መድረክ ላይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ አድርገው ለማንሳትና የሀገራችንን ታሪክ ለዓለም ለማስተዋወቅ በጉጉት መስከረምን እየተጠባበቁ ይገኛሉ።
21 days ago
የግብጽ ሚዲያዎች ተንኮል
"ከአባይ እስከ ሩፊጂ"
*ይህ የግብጽ የቴሌቪዥን ጣበያዎች የሰሩት ዶክመንተሪ ፊልም ነው።
#ethiopia | በግብጽ ሚዲያዎች የተሰራው ይህ ዶክመንተሪ ፊልም በታንዛኒያ የተገነባውን የጁሊየስ ኔሬሬ የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ግድብ ላይ ያጠነጥናል።
ግን የግብጽ ሚዲያዎች ሆን ብለው የእኛው ሀብት የሆነው የአባይ ወንዝ
የዶክመንተሪው ዋና እርዕስ አድርገው ተጠቅመውታል።
ከአባይ እስከ ሩፊጂ (From the Nile to Rufiji) በሚል ርዕስ የቀረበው ይህ ዘጋቢ ፊልም በሩፊጂ ወንዝ ላይ የተገነባውን ግድብ እና የኃይል ማመንጫ ግንባታ ሂደት እንደሚተርክ አልጀዚራ ገልጿል።
ግብፅ ይህን ፕሮጀክት በአፍሪካ አህጉር የመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላትን ተሳትፎ የሚያሳይ እንደሆነ ትገልጻለች።
ዘጋቢ ፊልሙ በፕሮጀክቱ ላይ የተሳተፉ ከ12,000 በላይ መሐንዲሶችን እና ሠራተኞችን ጥረት ይዳስሳል።
በተለይም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ጨምሮ ፈታኝ በሆኑ የአየር ንብረት ሁኔታዎች ውስጥ የተከናወነውን የቴክኒክ እና የሎጂስቲክስ ስራ አጉልቶ ያሳያል።
ታድያ የግብጽ ሚዲያዎች የኢትዮጵያ ሀብት የሆነውን የአባይ ወንዝ ለምን መጠቀም ፈለጉ?
የዘርፉ ባለሙያዎች ለዚህ ጉዳይ አስታየታቸውን ሰጥተዋል።
የአባይ ወንዝ ከታንዛኒያ ግድብ ጋር የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ ባይኖርም የግብጽ ሚዲያዎች አባይን በዶክመንተሪው መግብያ ላይ የተጠቀሙበት ምክንያት መኖሩን ይናገራሉ።
ባለሙያዎቹ በዋናነት የሚያነሱት ምክንያት እንደዚህ ያሉ ርዕሶች በተመልካቹና አድማጩ ዘንድ ትኩረት ለመሳብ የተመረጡ ናቸው ይላሉ።
እንደዚሁም የፊልሙ ርዕስ የአባይን ስም መጠቀሙ ተመልካቹ ለዘጋቢ ፊልሙ የበለጠ ፍላጎት እንዲኖረው ለማድረግ ነው ብለዋል።
ከዚህ ውጭ የፊልሙ ርዕስ በአካላዊ ወይም በተፈጥሮአዊ መንገድ የኢትዮጵያን ሀብት የሆነው አባይ ወንዝ በታንዛኒያው ሩፊጂ ወንዝ ግንባታ ላይ እንደ አንድ የልማት ተዋናይ ለማያያዝ የታሰበ አይደለም ይላሉ።
ይልቁንም የግብጽ ሚዲያዎች ለአፍሪካዊያን ማስተላለፍ የፈለጉት በአባይ ወንዝ ላይ የግብጽ የፖለቲካ ፍላጎት ለማጉላት የተጠቀሙበት ስልት ነው ሲሉ ገልጸዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fromniletorufiji #egyptmediadocumentary #ethiopianileriver
"ከአባይ እስከ ሩፊጂ"
*ይህ የግብጽ የቴሌቪዥን ጣበያዎች የሰሩት ዶክመንተሪ ፊልም ነው።
#ethiopia | በግብጽ ሚዲያዎች የተሰራው ይህ ዶክመንተሪ ፊልም በታንዛኒያ የተገነባውን የጁሊየስ ኔሬሬ የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ግድብ ላይ ያጠነጥናል።
ግን የግብጽ ሚዲያዎች ሆን ብለው የእኛው ሀብት የሆነው የአባይ ወንዝ
የዶክመንተሪው ዋና እርዕስ አድርገው ተጠቅመውታል።
ከአባይ እስከ ሩፊጂ (From the Nile to Rufiji) በሚል ርዕስ የቀረበው ይህ ዘጋቢ ፊልም በሩፊጂ ወንዝ ላይ የተገነባውን ግድብ እና የኃይል ማመንጫ ግንባታ ሂደት እንደሚተርክ አልጀዚራ ገልጿል።
ግብፅ ይህን ፕሮጀክት በአፍሪካ አህጉር የመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላትን ተሳትፎ የሚያሳይ እንደሆነ ትገልጻለች።
ዘጋቢ ፊልሙ በፕሮጀክቱ ላይ የተሳተፉ ከ12,000 በላይ መሐንዲሶችን እና ሠራተኞችን ጥረት ይዳስሳል።
በተለይም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ጨምሮ ፈታኝ በሆኑ የአየር ንብረት ሁኔታዎች ውስጥ የተከናወነውን የቴክኒክ እና የሎጂስቲክስ ስራ አጉልቶ ያሳያል።
ታድያ የግብጽ ሚዲያዎች የኢትዮጵያ ሀብት የሆነውን የአባይ ወንዝ ለምን መጠቀም ፈለጉ?
የዘርፉ ባለሙያዎች ለዚህ ጉዳይ አስታየታቸውን ሰጥተዋል።
የአባይ ወንዝ ከታንዛኒያ ግድብ ጋር የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ ባይኖርም የግብጽ ሚዲያዎች አባይን በዶክመንተሪው መግብያ ላይ የተጠቀሙበት ምክንያት መኖሩን ይናገራሉ።
ባለሙያዎቹ በዋናነት የሚያነሱት ምክንያት እንደዚህ ያሉ ርዕሶች በተመልካቹና አድማጩ ዘንድ ትኩረት ለመሳብ የተመረጡ ናቸው ይላሉ።
እንደዚሁም የፊልሙ ርዕስ የአባይን ስም መጠቀሙ ተመልካቹ ለዘጋቢ ፊልሙ የበለጠ ፍላጎት እንዲኖረው ለማድረግ ነው ብለዋል።
ከዚህ ውጭ የፊልሙ ርዕስ በአካላዊ ወይም በተፈጥሮአዊ መንገድ የኢትዮጵያን ሀብት የሆነው አባይ ወንዝ በታንዛኒያው ሩፊጂ ወንዝ ግንባታ ላይ እንደ አንድ የልማት ተዋናይ ለማያያዝ የታሰበ አይደለም ይላሉ።
ይልቁንም የግብጽ ሚዲያዎች ለአፍሪካዊያን ማስተላለፍ የፈለጉት በአባይ ወንዝ ላይ የግብጽ የፖለቲካ ፍላጎት ለማጉላት የተጠቀሙበት ስልት ነው ሲሉ ገልጸዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fromniletorufiji #egyptmediadocumentary #ethiopianileriver
Sponsored by
Surafel
23 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ባርሴሎና ኒኮ ዊሊያምስን ከአትሌቲክ ክለብ ለማስፈረም ጥረት አድርጎ ሳይሳካለት ከቀረና ተጫዋቹ የረጅም ጊዜ የኮንትራት ማራዘሚያ ከፈረመ አንድ ዓመት አልፎታል። ከአንድ ዓመት በኋላ፣ ኒኮ እና ወንድሙ ኢናኪ ዊሊያምስ በ 'አርቲቪኢ' ዘጋቢ ፊልም ላይ ስለዚህ ያልተሳካ ዝውውር ዝርዝር መረጃዎችን ሰጥተዋል።
የወደፊት እጣ ፈንታውን እስከ 2035 ከአትሌቲክ ክለብ ጋር ያሰረው ኒኮ... የዝውውር ዜናው በእርሱና በቤተሰቡ ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ እንደነበር አምኗል። "ያሳለፍኩት ዓመት የተለየ ነበር። በጣም ከባድ ክረምት ነበረ፤ በእኔና በቤተሰቤ ላይ ብዙ ጫና ነበር፤ በመጨረሻም ይህን ሁሉ ማሳለፍ ቀላል አልነበረም" ሲል ስፔናዊው ኢንተርናሽናል አስረድቷል።
የአትሌቲክ ክለብ አምበል የሆነው ወንድሙ ኢናኪ፣ የማያቋርጡ ግምታዊ ወሬዎች በኒኮ ህይወት ላይ ትልቅ ለውጥ ሊያመጣ የሚችልን ውሳኔ አስመልክቶ ኢ-ፍትሃዊ ትርክት ፈጥሮ እንደነበር ገልጿል። "ወንድሜ በአንድ ጀንበር ውሳኔ ላይ ባይደርስ፣ ወይም ዝም ቢል፣ አሊያም ለሱ ትልቅ የህይወት ለውጥ የሆነውን ጉዳይ ጊዜ ወስዶ ቢያስብበት፣ ሰዎች ልክ መጥፎ ነገር እያደረገ እንዳለ አድርገው ያስቡ ነበር" ብሏል።
ጋናዊው ኢንተርናሽናል ኢናኪ አክሎም፣ በዚያን ወቅት ቤተሰቡ ያሳለፋቸውን አስቀያሚ ገጠመኞች አስታውሷል። "ከሁሉም የከፋው ጊዜ ግድግዳ ላይ የተሳለውን ምስል ያበላሹበት ወቅት ነበር። በተለይም ወንድሜ ከፍቅረኛው ጋር ከእረፍት ሲመለስ የመኪናው መስታወት ተሰባብሮ ማግኘታችን አስደንጋጭ ነበር" ብሏል።
በተጨማሪም በየቀኑ የሚወጡት የሚጣረሱ መረጃዎች ነገሩን ይበልጥ አወሳስበውት እንደነበር አብራርቷል። "አንድ የስፖርቲንግ ዳይሬክተር አንዱን ሲናገር፣ በትዊተር ላይ ደግሞ ሌላ ወሬ ይወራ ነበር" በማለት የነበረውን ትርምስ አስታውሷል።
እንደ ኢናኪ ገለጻ የውሳኔው መቋጫ የመጣው ባልታሰበ ሁኔታ ኢቢዛ ውስጥ በእረፍት ላይ እያለ ነበር። "በቪዲዮ ደወለልኝና፣ 'ኢናኪ፣ እዚሁ ለመቆየት ወስኛለሁ' አለኝ። እኔም 'እየቀለድክ ነው እንዴ?' አልኩት። ከዚያም ለባለቤቴ 'ይህ ልጅ አድጓል፣ ወንድሜ ከእንግዲህ ህጻን አይደለም' አልኳት" ሲል ኢናኪ ምስጢሩን አጋርቷል።
ከአንድ ዓመት በኋላ ባርሴሎና እርሱ ሳይኖር የላሊጋውን ዋንጫ ቢያነሳም፣ ኒኮ በመረጠው መንገድ ላይ ምንም ዓይነት ጥርጣሬ እንደሌለው ይናገራል።
"ትክክለኛውን ውሳኔ ነው የወሰንኩት። አምስት የሻምፒዮንስ ሊግ ወይም ሁለት የላሊጋ ዋንጫዎችን ከማንሳት ይልቅ በዚህ ክለብ ውስጥ መሆንን እመርጣለሁ፤ ይህንንም በተግባር አሳይቻለሁ" ሲል ኮከቡ በልበ ሙሉነት ተናግሯል።
በአሁኑ ሰዓት ኒኮ ሙሉ ትኩረቱን በዓለም ዋንጫው ላይ ያደረገ ሲሆን፣ የቅርብ ጓደኛው ለሆነው ላሚን ያማል አድናቆቱን ከመቸር ወደ ኋላ አላለም።
የወደፊት እጣ ፈንታውን እስከ 2035 ከአትሌቲክ ክለብ ጋር ያሰረው ኒኮ... የዝውውር ዜናው በእርሱና በቤተሰቡ ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ እንደነበር አምኗል። "ያሳለፍኩት ዓመት የተለየ ነበር። በጣም ከባድ ክረምት ነበረ፤ በእኔና በቤተሰቤ ላይ ብዙ ጫና ነበር፤ በመጨረሻም ይህን ሁሉ ማሳለፍ ቀላል አልነበረም" ሲል ስፔናዊው ኢንተርናሽናል አስረድቷል።
የአትሌቲክ ክለብ አምበል የሆነው ወንድሙ ኢናኪ፣ የማያቋርጡ ግምታዊ ወሬዎች በኒኮ ህይወት ላይ ትልቅ ለውጥ ሊያመጣ የሚችልን ውሳኔ አስመልክቶ ኢ-ፍትሃዊ ትርክት ፈጥሮ እንደነበር ገልጿል። "ወንድሜ በአንድ ጀንበር ውሳኔ ላይ ባይደርስ፣ ወይም ዝም ቢል፣ አሊያም ለሱ ትልቅ የህይወት ለውጥ የሆነውን ጉዳይ ጊዜ ወስዶ ቢያስብበት፣ ሰዎች ልክ መጥፎ ነገር እያደረገ እንዳለ አድርገው ያስቡ ነበር" ብሏል።
ጋናዊው ኢንተርናሽናል ኢናኪ አክሎም፣ በዚያን ወቅት ቤተሰቡ ያሳለፋቸውን አስቀያሚ ገጠመኞች አስታውሷል። "ከሁሉም የከፋው ጊዜ ግድግዳ ላይ የተሳለውን ምስል ያበላሹበት ወቅት ነበር። በተለይም ወንድሜ ከፍቅረኛው ጋር ከእረፍት ሲመለስ የመኪናው መስታወት ተሰባብሮ ማግኘታችን አስደንጋጭ ነበር" ብሏል።
በተጨማሪም በየቀኑ የሚወጡት የሚጣረሱ መረጃዎች ነገሩን ይበልጥ አወሳስበውት እንደነበር አብራርቷል። "አንድ የስፖርቲንግ ዳይሬክተር አንዱን ሲናገር፣ በትዊተር ላይ ደግሞ ሌላ ወሬ ይወራ ነበር" በማለት የነበረውን ትርምስ አስታውሷል።
እንደ ኢናኪ ገለጻ የውሳኔው መቋጫ የመጣው ባልታሰበ ሁኔታ ኢቢዛ ውስጥ በእረፍት ላይ እያለ ነበር። "በቪዲዮ ደወለልኝና፣ 'ኢናኪ፣ እዚሁ ለመቆየት ወስኛለሁ' አለኝ። እኔም 'እየቀለድክ ነው እንዴ?' አልኩት። ከዚያም ለባለቤቴ 'ይህ ልጅ አድጓል፣ ወንድሜ ከእንግዲህ ህጻን አይደለም' አልኳት" ሲል ኢናኪ ምስጢሩን አጋርቷል።
ከአንድ ዓመት በኋላ ባርሴሎና እርሱ ሳይኖር የላሊጋውን ዋንጫ ቢያነሳም፣ ኒኮ በመረጠው መንገድ ላይ ምንም ዓይነት ጥርጣሬ እንደሌለው ይናገራል።
"ትክክለኛውን ውሳኔ ነው የወሰንኩት። አምስት የሻምፒዮንስ ሊግ ወይም ሁለት የላሊጋ ዋንጫዎችን ከማንሳት ይልቅ በዚህ ክለብ ውስጥ መሆንን እመርጣለሁ፤ ይህንንም በተግባር አሳይቻለሁ" ሲል ኮከቡ በልበ ሙሉነት ተናግሯል።
በአሁኑ ሰዓት ኒኮ ሙሉ ትኩረቱን በዓለም ዋንጫው ላይ ያደረገ ሲሆን፣ የቅርብ ጓደኛው ለሆነው ላሚን ያማል አድናቆቱን ከመቸር ወደ ኋላ አላለም።
23 days ago
የአንጋፋው ጋዜጠኛና የኮሙኒኬሽን ባለሙያ እሸቱ ዱብ
የቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ ተፈጽሟል
#ethiopia | በጋዜጠኝነት፣ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን፣ በቢዝነስ ስትራቴጂ፣ በሥነ ጽሑፍና በፊልም ዘርፍ የሚታወቁት አንጋፋው ጋዜጠኛ እሸቱ ዱብ በ50 ዓመታቸው አርፈዋል።
እሸቱ ዱብ ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕይወት ማለፋቸው የተነገረ ሲሆን፣ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸውም ዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. በጣፎ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።
ከ30 ዓመታት በላይ በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ያገለገሉት እሸቱ፣ በ1987 ዓ.ም. ፋና ሬዲዮ ሲመሠረት ከመጀመሪያዎቹ ባልደረቦች አንዱ በመሆን የመዝናኛ ክፍሉን በመምራት ዘርፉ ላይ የማይረሳ አሻራ አሳርፈዋል።
ከጋዜጠኝነት ባሻገር በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን፣ ብራንዲንግ፣ ማርኬቲንግ እና የቢዝነስ ስትራቴጂ ዘርፎች በሰፊው ሠርተዋል።
በCRDA የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር፣ በዋፋ ማርኬቲንግ የብራንዲንግና መልቲሚዲያ ፕሮዳክሽን ኃላፊ እንዲሁም በተለያዩ ተቋማት አማካሪና አሠልጣኝ ሆነው አገልግለዋል።
በሥነ ጽሑፍ ዘርፍም "ቀይ ልበሽ" የግጥም መድበል እና "የቅርብ ሩቅ" የተሰኘ ተውኔትን ጨምሮ በርካታ ሥራዎችን አበርክተዋል።
በኢኮኖሚ፣ በፖሊሲና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ጽሑፎቻቸውም በስፋት ተነብበዋል።
በእውቀታቸው፣ በትህትናቸው፣ በሙያዊ ብቃታቸው እና ወጣት ጋዜጠኞችን በማብቃት በኢትዮጵያ ሚዲያ ዘርፍ ዘላቂ አሻራ አስቀምጠው አልፈዋል።
ነፍሳቸውን ይማር።
የቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ ተፈጽሟል
#ethiopia | በጋዜጠኝነት፣ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን፣ በቢዝነስ ስትራቴጂ፣ በሥነ ጽሑፍና በፊልም ዘርፍ የሚታወቁት አንጋፋው ጋዜጠኛ እሸቱ ዱብ በ50 ዓመታቸው አርፈዋል።
እሸቱ ዱብ ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕይወት ማለፋቸው የተነገረ ሲሆን፣ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸውም ዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. በጣፎ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።
ከ30 ዓመታት በላይ በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ያገለገሉት እሸቱ፣ በ1987 ዓ.ም. ፋና ሬዲዮ ሲመሠረት ከመጀመሪያዎቹ ባልደረቦች አንዱ በመሆን የመዝናኛ ክፍሉን በመምራት ዘርፉ ላይ የማይረሳ አሻራ አሳርፈዋል።
ከጋዜጠኝነት ባሻገር በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን፣ ብራንዲንግ፣ ማርኬቲንግ እና የቢዝነስ ስትራቴጂ ዘርፎች በሰፊው ሠርተዋል።
በCRDA የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር፣ በዋፋ ማርኬቲንግ የብራንዲንግና መልቲሚዲያ ፕሮዳክሽን ኃላፊ እንዲሁም በተለያዩ ተቋማት አማካሪና አሠልጣኝ ሆነው አገልግለዋል።
በሥነ ጽሑፍ ዘርፍም "ቀይ ልበሽ" የግጥም መድበል እና "የቅርብ ሩቅ" የተሰኘ ተውኔትን ጨምሮ በርካታ ሥራዎችን አበርክተዋል።
በኢኮኖሚ፣ በፖሊሲና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ጽሑፎቻቸውም በስፋት ተነብበዋል።
በእውቀታቸው፣ በትህትናቸው፣ በሙያዊ ብቃታቸው እና ወጣት ጋዜጠኞችን በማብቃት በኢትዮጵያ ሚዲያ ዘርፍ ዘላቂ አሻራ አስቀምጠው አልፈዋል።
ነፍሳቸውን ይማር።
23 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የዘመናችን ታላቁ የእግር ኳስ ጠበብት እና በባርሴሎና የቀኝ መስመር ላይ የክብሩ ወራሽ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው ድንቁ ወጣት... እሁድ ዕለት አርጀንቲና ከስፔን በሚያደርጉት የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት ይፋጠጣሉ። ሊዮኔል ሜሲ በ39 ዓመቱ፣ ላሚን ያማል ደግሞ ገና በ19 ዓመቱ በዚህ ታላቅ የእግር ኳስ መድረክ ላይ መገናኘታቸው፣ የሜሲን አስደናቂ ጽናት እና የያማልን ልዩ የተፈጥሮ ተሰጥኦ በግልጽ የሚያሳይ ነው።
ይሁን እንጂ የሁለቱ ተጫዋቾች መንገድ ሲገናኝ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ አይደለም። ጊዜው እ.ኤ.አ 2007 ነበር፤ የ20 ዓመቱ ወጣት ሊዮኔል ሜሲ በባርሴሎና ዋናው ቡድን ውስጥ ቋሚ ተሰላፊ መሆን በጀመረበት በዚያን ወቅት፣ ላሚን ያማል ገና የ5 ወር ጡት ጠባቂ ሕፃን ነበር። ይህን አስገራሚ ታሪካዊ አጋጣሚ በካሜራው ሌንስ ያስቀረው ፎቶግራፍ አንሺ ጆአን ሞንፎርት ነው። ፎቶግራፎቹ ከሁለት ዓመት በፊት ያማል ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር ዩሮ 2024ን ሲያነሳ፣ አባቱ «የሁለት ጀግኖች ጅማሮ» በሚል ጽሑፍ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እስካጋራው ጊዜ ድረስ ተዘንግተው ቆይተው ነበር። በምስሉ ላይ ፊቱ በፈገግታ የተሞላው ሜሲ፣ ከዓመታት በኋላ የእሱን የእግር ኳስ ፈለግ በጥብቅ የሚከተለውን አንድ ትንሽ ሕፃን በውሃ ገንዳ ውስጥ እያጠበና እያጫወተ ይታያል።
ፎቶግራፍ አንሺው ጆአን ሞንፎርትሲናገር "...ይህ እውነተኛ የዕጣ ፈንታ ተአምር ነው" ይለዋል። "ይህን ታሪክ ለፊልም ጽሑፍ ብታቀርበው እንኳን አሳማኝ አይሆንም። ከምትገምተው በላይ እጅግ ልዩ የሆነ ነገር ስታገኝ የሚሰማህ ስሜት ነው" በማለት ይገልጸዋል።
የፎቶግራፍ መነሳቱ መርሃ ግብር የተከናወነው በባርሴሎናው ካምፕ ኑ ስታዲየም የመልበሻ ክፍል ውስጥ ነበር። የያማል ቤተሰቦች በወቅቱ እዚያ ሊገኙ የቻሉት በእጣ አሸናፊነት ነው። ትውልደ ሞሮኳዊው አባቱ ሙኒር ናስራውይ እና ኢኳቶሪያል ጊኒያዊቷ እናቱ ሺላ ኢባና፣ በልጅነታቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ካታሎንያ ከመጡ በኋላ ነበር የተዋወቁት። ላሚን ያማል የመጀመሪያ ልጃቸው ሲሆን፣ እሱ በተወለደበት ወቅት የካታላኑ ስፖርት ጋዜጣ ከባርሴሎና ማሊያ ስፖንሰር ዩኒሴፍ (Unicef) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት የእጣ ውድድር ላይ ተሳትፈው አሸናፊ ሆኑ። የውድድሩ አሸናፊዎች ከባርሴሎና ዋናው ቡድን ተጫዋች ጋር የልጃቸውን ፎቶግራፍ በሙያዊ መንገድ የማንሳት ዕድል ያገኛሉ። የያማል ቤተሰቦች በዕለቱ ስታዲየም ሲደርሱ፣ በዕጣ ፈንታ ከሊዮኔል ሜሲ ጋር እንዲነሱ ተመደቡ።
ፎቶግራፍ አንሺው ሞንፎርት ያንን ቀን ሲያስታውስ፣ "ሜሲ በጣም አይን አፋር እና ዝምተኛ ልጅ ነው። ወደ መልበሻ ክፍሉ ገብቶ በድንገት ከዚህ ሕፃን ጋር ፎቶ መነሳት እንዳለበት ሲነገረው፣ ሕፃኑን ምን እንደሚያደርገው ግራ ገብቶት ፊቱ ተለዋውጦ ነበር" ይላል። "ለአንድ ወጣት ልጅ ከባድ ቢሆንም፣ ላሚን ግን በጣም ደስተኛ እና ፈገግታ የማያጣ ሕፃን ነበር። እናቱ ሺላም ታግዘን ነበር፤ በጣም ደሀ ቤተሰቦች ቢሆኑም አብሮ ለመስራት እጅግ ጥሩ ሰዎች ነበሩ። ሜሲ እንዲህ ባሉ ነገሮች ላይ ሁልጊዜም ፕሮፌሽናል ስለሆነ፣ ከሁኔታው ጋር ቶሎ ተላመደ።"
ላሚን ያማል ሰኞ ዕለት 19ኛ ዓመቱን ሲያከብር፣ አስገራሚ የእግር ኳስ ጉዞን አስመዝግቧል። ሜሲ 19 ዓመት ሲሞላው 11 የክለብ ግቦችን አስቆጥሮ አንድ የላሊጋ እና አንድ የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አሸንፎ ነበር። ያማል ግን በአንጻሩ 56 ግቦችን ከመረብ አሳርፎ፣ ሦስት የላሊጋ ዋንጫዎችን፣ አንድ የኮፓ ዴል ሬይ እና የዩሮ 2024 ዋንጫን ማንሳት ችሏል።
የሚገርመው ነገር «ያማል» የልጁ የአባት ስም ሳይሆን፣ ሁለተኛው መጠሪያ ስሙ መሆኑ ነው። ሙሉ ስሙ ላሚን ያማል ናስራውይ ኢባና ሲሆን፣ በማሊያው ጀርባ ላይ የሚጠቀመው የመጀመሪያዎቹን ሁለት ስሞቹን ነው። ይህ የሆነበት ምክንያት ደግሞ፣ እሱ በሚወለድበት ወቅት ቤተሰቡ በከፍተኛ የገንዘብ ችግር ውስጥ ወድቆ በነበረበት ሰዓት የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉላቸው ሁለት የቅርብ ወዳጆቻቸው ክብር ሲሉ አባቱ ቃል በገባው መሠረት የተሰየመ ነው።
በአረብኛ «ላሚን» ማለት ታማኝ ማለት ሲሆን፣ «ያማል» ደግሞ የጀማል ሌላኛው አጠራር ሆኖ ውበት ወይም ግርማ ሞገስ ማለት ነው። ያማል ባስቆጠራቸው ግቦች ላይ በጣቶቹ «3-0-4» የሚል ምልክት በማሳየት ደስታውን ይገልጻል፤ ይህ ደግሞ ያደገበትንና ከባርሴሎና 20 ማይል ርቃ የምትገኘውን የሮካፎንዳ ሰፈር የፖስታ ኮድ የሚያመላክት ነው። ያማል ስለ ቤተሰቦቹ ሲናገር... "ወላጆቼ ያደረጉልኝን ነገር እኔ ልጄ ላልሆነ ሰው ማድረግ አልችልም። ገንዘብ ከሌለህ ልጅህ እግር ኳስ እንዲጫወት መርዳት በጣም ከባድ ነው፤ ወላጆቼ ግን ይህን ሁሉ አሳክተዋል። ውለታቸውን መቼም ልመልስላቸው አልችልም" ብሏል።
ለካታላኑ እና የባርሴሎና ደጋፊ ለሆነው ፎቶግራፍ አንሺ ሞንፎርት፣ የሁለቱ ተጫዋቾች በዓለም ዋንጫ የፍጻሜ መድረክ ላይ መገናኘት ከሁለት አሥርት ዓመታት በፊት ለጀመረው ታሪክ ፍጹም ማሳረጊያ ነው። የ58 ዓመቱ ሞንፎርት፣ "የታሪካቸውን ዑደት እየዘጋን ይመስለኛል፤ አስደሳች ፍጻሜ ነው። እኔ የባርሴሎና ደጋፊ ነኝ፤ ለሜሲ የእግር ኳስ ህይወቱን ሁለተኛውን የዓለም ዋንጫ በማንሳት ቢያጠናቅቅ ፍጹም ይገባዋል እላለሁ። ላሚን ደግሞ ገና ወደፊት የዓለም ዋንጫን የሚያነሳበት ብዙ ጊዜ አለው። ነገር ግን ስፔን እና ላሚን አሁን በጥሩ ሞራል ላይ ይገኛሉ፤ ይህንን ዋንጫ ቢያነሳ ከሌሎች ክብሮቹ ሁሉ የላቀ ይሆናል። ስለዚህ ምርጫው ለእኔ በጣም ከባድ ነው፤ ልቤ ለሁለት እየተሰነጠቀ ነው" በማለት ስሜቱን ገልጿል።
ይሁን እንጂ የሁለቱ ተጫዋቾች መንገድ ሲገናኝ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ አይደለም። ጊዜው እ.ኤ.አ 2007 ነበር፤ የ20 ዓመቱ ወጣት ሊዮኔል ሜሲ በባርሴሎና ዋናው ቡድን ውስጥ ቋሚ ተሰላፊ መሆን በጀመረበት በዚያን ወቅት፣ ላሚን ያማል ገና የ5 ወር ጡት ጠባቂ ሕፃን ነበር። ይህን አስገራሚ ታሪካዊ አጋጣሚ በካሜራው ሌንስ ያስቀረው ፎቶግራፍ አንሺ ጆአን ሞንፎርት ነው። ፎቶግራፎቹ ከሁለት ዓመት በፊት ያማል ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር ዩሮ 2024ን ሲያነሳ፣ አባቱ «የሁለት ጀግኖች ጅማሮ» በሚል ጽሑፍ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እስካጋራው ጊዜ ድረስ ተዘንግተው ቆይተው ነበር። በምስሉ ላይ ፊቱ በፈገግታ የተሞላው ሜሲ፣ ከዓመታት በኋላ የእሱን የእግር ኳስ ፈለግ በጥብቅ የሚከተለውን አንድ ትንሽ ሕፃን በውሃ ገንዳ ውስጥ እያጠበና እያጫወተ ይታያል።
ፎቶግራፍ አንሺው ጆአን ሞንፎርትሲናገር "...ይህ እውነተኛ የዕጣ ፈንታ ተአምር ነው" ይለዋል። "ይህን ታሪክ ለፊልም ጽሑፍ ብታቀርበው እንኳን አሳማኝ አይሆንም። ከምትገምተው በላይ እጅግ ልዩ የሆነ ነገር ስታገኝ የሚሰማህ ስሜት ነው" በማለት ይገልጸዋል።
የፎቶግራፍ መነሳቱ መርሃ ግብር የተከናወነው በባርሴሎናው ካምፕ ኑ ስታዲየም የመልበሻ ክፍል ውስጥ ነበር። የያማል ቤተሰቦች በወቅቱ እዚያ ሊገኙ የቻሉት በእጣ አሸናፊነት ነው። ትውልደ ሞሮኳዊው አባቱ ሙኒር ናስራውይ እና ኢኳቶሪያል ጊኒያዊቷ እናቱ ሺላ ኢባና፣ በልጅነታቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ካታሎንያ ከመጡ በኋላ ነበር የተዋወቁት። ላሚን ያማል የመጀመሪያ ልጃቸው ሲሆን፣ እሱ በተወለደበት ወቅት የካታላኑ ስፖርት ጋዜጣ ከባርሴሎና ማሊያ ስፖንሰር ዩኒሴፍ (Unicef) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት የእጣ ውድድር ላይ ተሳትፈው አሸናፊ ሆኑ። የውድድሩ አሸናፊዎች ከባርሴሎና ዋናው ቡድን ተጫዋች ጋር የልጃቸውን ፎቶግራፍ በሙያዊ መንገድ የማንሳት ዕድል ያገኛሉ። የያማል ቤተሰቦች በዕለቱ ስታዲየም ሲደርሱ፣ በዕጣ ፈንታ ከሊዮኔል ሜሲ ጋር እንዲነሱ ተመደቡ።
ፎቶግራፍ አንሺው ሞንፎርት ያንን ቀን ሲያስታውስ፣ "ሜሲ በጣም አይን አፋር እና ዝምተኛ ልጅ ነው። ወደ መልበሻ ክፍሉ ገብቶ በድንገት ከዚህ ሕፃን ጋር ፎቶ መነሳት እንዳለበት ሲነገረው፣ ሕፃኑን ምን እንደሚያደርገው ግራ ገብቶት ፊቱ ተለዋውጦ ነበር" ይላል። "ለአንድ ወጣት ልጅ ከባድ ቢሆንም፣ ላሚን ግን በጣም ደስተኛ እና ፈገግታ የማያጣ ሕፃን ነበር። እናቱ ሺላም ታግዘን ነበር፤ በጣም ደሀ ቤተሰቦች ቢሆኑም አብሮ ለመስራት እጅግ ጥሩ ሰዎች ነበሩ። ሜሲ እንዲህ ባሉ ነገሮች ላይ ሁልጊዜም ፕሮፌሽናል ስለሆነ፣ ከሁኔታው ጋር ቶሎ ተላመደ።"
ላሚን ያማል ሰኞ ዕለት 19ኛ ዓመቱን ሲያከብር፣ አስገራሚ የእግር ኳስ ጉዞን አስመዝግቧል። ሜሲ 19 ዓመት ሲሞላው 11 የክለብ ግቦችን አስቆጥሮ አንድ የላሊጋ እና አንድ የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አሸንፎ ነበር። ያማል ግን በአንጻሩ 56 ግቦችን ከመረብ አሳርፎ፣ ሦስት የላሊጋ ዋንጫዎችን፣ አንድ የኮፓ ዴል ሬይ እና የዩሮ 2024 ዋንጫን ማንሳት ችሏል።
የሚገርመው ነገር «ያማል» የልጁ የአባት ስም ሳይሆን፣ ሁለተኛው መጠሪያ ስሙ መሆኑ ነው። ሙሉ ስሙ ላሚን ያማል ናስራውይ ኢባና ሲሆን፣ በማሊያው ጀርባ ላይ የሚጠቀመው የመጀመሪያዎቹን ሁለት ስሞቹን ነው። ይህ የሆነበት ምክንያት ደግሞ፣ እሱ በሚወለድበት ወቅት ቤተሰቡ በከፍተኛ የገንዘብ ችግር ውስጥ ወድቆ በነበረበት ሰዓት የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉላቸው ሁለት የቅርብ ወዳጆቻቸው ክብር ሲሉ አባቱ ቃል በገባው መሠረት የተሰየመ ነው።
በአረብኛ «ላሚን» ማለት ታማኝ ማለት ሲሆን፣ «ያማል» ደግሞ የጀማል ሌላኛው አጠራር ሆኖ ውበት ወይም ግርማ ሞገስ ማለት ነው። ያማል ባስቆጠራቸው ግቦች ላይ በጣቶቹ «3-0-4» የሚል ምልክት በማሳየት ደስታውን ይገልጻል፤ ይህ ደግሞ ያደገበትንና ከባርሴሎና 20 ማይል ርቃ የምትገኘውን የሮካፎንዳ ሰፈር የፖስታ ኮድ የሚያመላክት ነው። ያማል ስለ ቤተሰቦቹ ሲናገር... "ወላጆቼ ያደረጉልኝን ነገር እኔ ልጄ ላልሆነ ሰው ማድረግ አልችልም። ገንዘብ ከሌለህ ልጅህ እግር ኳስ እንዲጫወት መርዳት በጣም ከባድ ነው፤ ወላጆቼ ግን ይህን ሁሉ አሳክተዋል። ውለታቸውን መቼም ልመልስላቸው አልችልም" ብሏል።
ለካታላኑ እና የባርሴሎና ደጋፊ ለሆነው ፎቶግራፍ አንሺ ሞንፎርት፣ የሁለቱ ተጫዋቾች በዓለም ዋንጫ የፍጻሜ መድረክ ላይ መገናኘት ከሁለት አሥርት ዓመታት በፊት ለጀመረው ታሪክ ፍጹም ማሳረጊያ ነው። የ58 ዓመቱ ሞንፎርት፣ "የታሪካቸውን ዑደት እየዘጋን ይመስለኛል፤ አስደሳች ፍጻሜ ነው። እኔ የባርሴሎና ደጋፊ ነኝ፤ ለሜሲ የእግር ኳስ ህይወቱን ሁለተኛውን የዓለም ዋንጫ በማንሳት ቢያጠናቅቅ ፍጹም ይገባዋል እላለሁ። ላሚን ደግሞ ገና ወደፊት የዓለም ዋንጫን የሚያነሳበት ብዙ ጊዜ አለው። ነገር ግን ስፔን እና ላሚን አሁን በጥሩ ሞራል ላይ ይገኛሉ፤ ይህንን ዋንጫ ቢያነሳ ከሌሎች ክብሮቹ ሁሉ የላቀ ይሆናል። ስለዚህ ምርጫው ለእኔ በጣም ከባድ ነው፤ ልቤ ለሁለት እየተሰነጠቀ ነው" በማለት ስሜቱን ገልጿል።
23 days ago
🎞 የፊልም ባለሙያ መሆን ለምትፈልጉ ምርጥ ዕድል!!!
🎥 በልቀት ኮሌጅ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ የፊልም ባለሙያዎች ልዩ የአጭር ጊዜ የፊልም ጥበብ ስልጠና ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፤
✍ አሰልጣኞች
👉 ደራሲና አዘጋጅ መዓዛ ወርቁ
👉 የፊልም ዳይሬክተር እና ደራሲ ብሩክ ሞላ፤
👉 ዳይሬክተር አብርሀም ገዛኸኝ፤
👉 ሲኒማቶግራፈር ዳንኤል ግርማ፤
🎞 የስልጠና አይነቶች
👉 የፊልም አክቲንግ
👉 ዳይሬክቲንግ
👉 ሲኒማቶግራፊ
👉 በፊልም ጽሑፍ አጻጻፍ
🗓 የምዝገባ ቀን ሐምሌ10/2018 ያበቃል
ስልጠናው ከሀምሌ 11/2018 ጀምሮ ቅዳሜና እሁድ በቀን መርሐ -ግብር ይሰጣል።
💡ለምዝገባ
አራት ኪሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኮሌጁ ሬጅስትራር ጽ/ቤት በመምጣት መመዝገብ ይችላሉ።
📱 ለበለጠ መረጃ
2519 84 71 71 44/251940 08 99 99 /251930325090 መደወል ይችላሉ።
በተጨማሪም በቴሌግራም
Liketcollege መመዝገብ ይችላል።
🎥 በልቀት ኮሌጅ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ የፊልም ባለሙያዎች ልዩ የአጭር ጊዜ የፊልም ጥበብ ስልጠና ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፤
✍ አሰልጣኞች
👉 ደራሲና አዘጋጅ መዓዛ ወርቁ
👉 የፊልም ዳይሬክተር እና ደራሲ ብሩክ ሞላ፤
👉 ዳይሬክተር አብርሀም ገዛኸኝ፤
👉 ሲኒማቶግራፈር ዳንኤል ግርማ፤
🎞 የስልጠና አይነቶች
👉 የፊልም አክቲንግ
👉 ዳይሬክቲንግ
👉 ሲኒማቶግራፊ
👉 በፊልም ጽሑፍ አጻጻፍ
🗓 የምዝገባ ቀን ሐምሌ10/2018 ያበቃል
ስልጠናው ከሀምሌ 11/2018 ጀምሮ ቅዳሜና እሁድ በቀን መርሐ -ግብር ይሰጣል።
💡ለምዝገባ
አራት ኪሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኮሌጁ ሬጅስትራር ጽ/ቤት በመምጣት መመዝገብ ይችላሉ።
📱 ለበለጠ መረጃ
2519 84 71 71 44/251940 08 99 99 /251930325090 መደወል ይችላሉ።
በተጨማሪም በቴሌግራም
Liketcollege መመዝገብ ይችላል።
Sponsored by
Surafel
25 days ago
"ካምፓስ" ተከታታይ ድራማ፤
የጥራት እና የጥልቅ ትረካ አዲስ ምዕራፍ
በአሌክስ ዘ መላዕክ
#ethiopia | በፋና ቴሌቪዥን ሲተላለፍ የቆየው "ካምፓስ" ተከታታይ ድራማ የመጀመሪያ ምዕራፉን በተሳካ ሁኔታ ሲያጠናቅቅ፣ ሁለተኛ ምዕራፉን ለመጀመር መዘጋጀቱ ተነግሯል።
ድራማው በከፍተኛ የፕሮዳክሽን ጥራት ከመቅረቡ በተጨማሪ፣ የታሪኩ ጥልቀት እና የሚያነሳቸው ማኅበራዊ ጉዳዮች በብዙዎች ዘንድ ትኩረት ማግኘታቸው ተገልጿል።
የመጀመሪያ ምዕራፉ "ሆራይዘን" በተባለ ምናባዊ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚኖሩ ወጣቶችን ሕይወት በመከታተል፣ የወጣትነት ፈተናዎችን፣ ጓደኝነትን፣ ታማኝነትን፣ የገንዘብ ተጽዕኖን እና በማኅበራዊ ሚዲያ ሽፋን የሚፈጸሙ የወሲብ ንግድ ወጥመዶችን በጥልቀት ማሳየት ችሏል።
በአቀራረብ ረገድም ድራማው የካሜራ አጠቃቀም፣ የብርሃን አዋቂነት፣ የምስል ቅንብር (Composition) እና የሲኒማቶግራፊ ሥራ ታሪኩን እንዲያጠናክር በተሳካ ሁኔታ መዋሉን ግምገማው ያመለክታል።
ድራማው ከታዋቂ ፊቶች ይልቅ አዳዲስ ተዋንያንን በዋና ሚና ማቅረቡም ለተመልካቾች አዲስ ተሞክሮ ፈጥሯል።
የድራማው ፈጣሪ፣ ዋና ጸሐፊ፣ ዳይሬክተር እና ፕሮዲውሰር አብይ ጌታሁን በፊልም ዘርፍ ያለውን ረጅም ልምድና ሙያዊ ዕውቀት በማጣመር ይህን ሥራ እንዳቀረበ ተጠቅሷል።
የመጀመሪያ ምዕራፉ ያስመዘገበውን ስኬት መነሻ በማድረግ፣ በቅርቡ የሚጀምረው ሁለተኛ ምዕራፍ በተመልካቾች ዘንድ ከፍተኛ ጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል።
የጥራት እና የጥልቅ ትረካ አዲስ ምዕራፍ
በአሌክስ ዘ መላዕክ
#ethiopia | በፋና ቴሌቪዥን ሲተላለፍ የቆየው "ካምፓስ" ተከታታይ ድራማ የመጀመሪያ ምዕራፉን በተሳካ ሁኔታ ሲያጠናቅቅ፣ ሁለተኛ ምዕራፉን ለመጀመር መዘጋጀቱ ተነግሯል።
ድራማው በከፍተኛ የፕሮዳክሽን ጥራት ከመቅረቡ በተጨማሪ፣ የታሪኩ ጥልቀት እና የሚያነሳቸው ማኅበራዊ ጉዳዮች በብዙዎች ዘንድ ትኩረት ማግኘታቸው ተገልጿል።
የመጀመሪያ ምዕራፉ "ሆራይዘን" በተባለ ምናባዊ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚኖሩ ወጣቶችን ሕይወት በመከታተል፣ የወጣትነት ፈተናዎችን፣ ጓደኝነትን፣ ታማኝነትን፣ የገንዘብ ተጽዕኖን እና በማኅበራዊ ሚዲያ ሽፋን የሚፈጸሙ የወሲብ ንግድ ወጥመዶችን በጥልቀት ማሳየት ችሏል።
በአቀራረብ ረገድም ድራማው የካሜራ አጠቃቀም፣ የብርሃን አዋቂነት፣ የምስል ቅንብር (Composition) እና የሲኒማቶግራፊ ሥራ ታሪኩን እንዲያጠናክር በተሳካ ሁኔታ መዋሉን ግምገማው ያመለክታል።
ድራማው ከታዋቂ ፊቶች ይልቅ አዳዲስ ተዋንያንን በዋና ሚና ማቅረቡም ለተመልካቾች አዲስ ተሞክሮ ፈጥሯል።
የድራማው ፈጣሪ፣ ዋና ጸሐፊ፣ ዳይሬክተር እና ፕሮዲውሰር አብይ ጌታሁን በፊልም ዘርፍ ያለውን ረጅም ልምድና ሙያዊ ዕውቀት በማጣመር ይህን ሥራ እንዳቀረበ ተጠቅሷል።
የመጀመሪያ ምዕራፉ ያስመዘገበውን ስኬት መነሻ በማድረግ፣ በቅርቡ የሚጀምረው ሁለተኛ ምዕራፍ በተመልካቾች ዘንድ ከፍተኛ ጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል።
25 days ago
25 days ago
🎞 ተወዳጆቹ የፊልም ባለሙያዎች ስልጠና ሊሰጧችሁ ነው!!!
🎥 በልቀት ኮሌጅ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ የፊልም ባለሙያዎች ልዩ የአጭር ጊዜ የፊልም ጥበብ ስልጠና ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፤
✍ አሰልጣኞች
👉 ደራሲና አዘጋጅ መዓዛ ወርቁ
👉 የፊልም ዳይሬክተር እና ደራሲ ብሩክ ሞላ፤
👉 ዳይሬክተር አብርሀም ገዛኸኝ፤
👉 ሲኒማቶግራፈር ዳንኤል ግርማ፤
🎞 የስልጠና አይነቶች
👉 የፊልም አክቲንግ
👉 ዳይሬክቲንግ
👉 ሲኒማቶግራፊ
👉 በፊልም ጽሑፍ አጻጻፍ
🗓 የምዝገባ ቀን ሐምሌ10/2018 ያበቃል
ስልጠናው ከሀምሌ 11/2018 ጀምሮ ቅዳሜና እሁድ በቀን መርሐ -ግብር ይሰጣል።
💡ለምዝገባ
አራት ኪሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኮሌጁ ሬጅስትራር ጽ/ቤት በመምጣት መመዝገብ ይችላሉ።
📱 ለበለጠ መረጃ
2519 84 71 71 44/251940 08 99 99 /251930325090 መደወል ይችላሉ።
በተጨማሪም በቴሌግራም
Liketcollege መመዝገብ ይችላል።
🎥 በልቀት ኮሌጅ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ የፊልም ባለሙያዎች ልዩ የአጭር ጊዜ የፊልም ጥበብ ስልጠና ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፤
✍ አሰልጣኞች
👉 ደራሲና አዘጋጅ መዓዛ ወርቁ
👉 የፊልም ዳይሬክተር እና ደራሲ ብሩክ ሞላ፤
👉 ዳይሬክተር አብርሀም ገዛኸኝ፤
👉 ሲኒማቶግራፈር ዳንኤል ግርማ፤
🎞 የስልጠና አይነቶች
👉 የፊልም አክቲንግ
👉 ዳይሬክቲንግ
👉 ሲኒማቶግራፊ
👉 በፊልም ጽሑፍ አጻጻፍ
🗓 የምዝገባ ቀን ሐምሌ10/2018 ያበቃል
ስልጠናው ከሀምሌ 11/2018 ጀምሮ ቅዳሜና እሁድ በቀን መርሐ -ግብር ይሰጣል።
💡ለምዝገባ
አራት ኪሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኮሌጁ ሬጅስትራር ጽ/ቤት በመምጣት መመዝገብ ይችላሉ።
📱 ለበለጠ መረጃ
2519 84 71 71 44/251940 08 99 99 /251930325090 መደወል ይችላሉ።
በተጨማሪም በቴሌግራም
Liketcollege መመዝገብ ይችላል።
Comments