11 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ለፊፋ ፕሬዝደንት ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታወቀ፡፡ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን(ካፍ) ለፊፋ ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በሙሉ ድምፅ ድጋፍ ለመስጠት መወሰኑን ገለፀ፡፡ በኢንፋንቲኖ አመራር ላይ በመላው አለም ተቃውሞ እየተነሳ ባለበት በዚህ ወቅት ካፍ ተቃራኒ አቋም በማንፀባረቅ ፕሬዝደንቱን ደግፏል፡፡ ካፍ ይህንን አቋሙን ዛሬ ይፋ ያደረገው የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ኢንፋንቲኖ በስልጣን ላይ የሚቆዩ ከሆነ በፊፋ ውድድሮች ራሱን እንደሚያገል ማስታወቁን ተከትሎ ነው፡፡ ለአህጉሪቱ እግር ኳስ እድገት ያበረከቱትን አስተዋፅኦ ያደነቀው ካፍ የፊፋ ፕሬዝደንትና ዋና ፀሀፊው ያቀረቡለትን ወቅታዊ ገለፃ እንደተቀበለው አስረድቷል፡፡
በዚህም በፊፋ ውስጥ ግልፅነት ያለው መልካም አስተዳደር ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት እንደሚደግፍ አስታውቋል፡፡ የካፍ ፕሬዝደንት ፓትሪስ ሞትሴፕ ሲናገሩ ‹‹ለእኛ ለአፍሪካዊያን በአስተዳደርና በፍትህ ሂደት ውስጥ ግልፅነት ለድርድር የማይቀርብ ነው፡፡
ስለዚህም ከመንግስቶቻችን፣ ከንግድ ድርጅቶችና ከሌሎችም ተቋማት ይህንን እንጠብቃለን፡፡›› ያሉ ሲሆን ካፍ እነዚህን መርሆዎች በማክበር ከፊፋ፣ ከአባል ማህበራትና ሌሎችም አህጉራዊ ኮንፌዴሬሽኖችና የእግር ኳስ ባለድርሻ አካላት ጋር መስራቱን እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ የካፍ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውይይት አድርጎ በሙሉ ድምፅ ለኢንፋንቲኖ ድጋፍ ለመስጠት ውሳኔ እንደደረሰም አስታውቀዋል፡፡
በዚህም በፊፋ ውስጥ ግልፅነት ያለው መልካም አስተዳደር ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት እንደሚደግፍ አስታውቋል፡፡ የካፍ ፕሬዝደንት ፓትሪስ ሞትሴፕ ሲናገሩ ‹‹ለእኛ ለአፍሪካዊያን በአስተዳደርና በፍትህ ሂደት ውስጥ ግልፅነት ለድርድር የማይቀርብ ነው፡፡
ስለዚህም ከመንግስቶቻችን፣ ከንግድ ድርጅቶችና ከሌሎችም ተቋማት ይህንን እንጠብቃለን፡፡›› ያሉ ሲሆን ካፍ እነዚህን መርሆዎች በማክበር ከፊፋ፣ ከአባል ማህበራትና ሌሎችም አህጉራዊ ኮንፌዴሬሽኖችና የእግር ኳስ ባለድርሻ አካላት ጋር መስራቱን እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ የካፍ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውይይት አድርጎ በሙሉ ድምፅ ለኢንፋንቲኖ ድጋፍ ለመስጠት ውሳኔ እንደደረሰም አስታውቀዋል፡፡
14 hours ago
አርትስ ፕላስ እና ተራኪ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን አጋርነት መስረቱ
#ethiopia | አዲስ አበባ - አርትስ ፕላስ የድምፅ መጻሕፍትን ለአድማጮች በማቅረብ ከሚታወቀው ተራኪ መተግበሪያ ጋር የይዘት ስምምነት ተበየነ። ይህ ስምምነት በተራኪ መተግበሪያ ላይ የሚገኙ የድምፅ መጻሕፍትን በአርትስ ፕላስ በኩል ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ነው።
ተራኪ መጻሕፍትን በድምፅ በማቅረብ በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነት ያገኘ ሲሆን፣ በዚህ ትብብር አማካኝነት ይዘቶቹን ለተጨማሪ ተጠቃሚዎች ማቅረብ ያስችለዋል።
በትብብሩ የመጀመሪያ ምዕራፍ በተራኪ የሚገኙ የልጆች የድምፅ መጻሕፍት በአርትስ ፕላስ መተግበሪያ ላይ ይቀርባሉ። እነዚህ ይዘቶች በአርትስ ፕላስ ኪድስ ምድብ ስር የሚስተናገዱ ሲሆን፣ ለሕፃናት እና ለታዳጊዎች በጎ ሥነ ምግባርን፣ እውቀትን እና የፈጠራ ክህሎትን የሚያጎለብቱ ይሆናሉ።
የሁለቱም ተቋማት አመራሮች ይህ አጋርነት የሀገሪቱን የኪነ ጥበብ እና የፈጠራ ዘርፍ ለማጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።
አርትስ ፕላስ በቅርቡ አገልግሎቱን በይፋ የሚጀምር ሲሆን፣ በሂደቱ ስለሚካተቱ መጻሕፍት እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮች ወደፊት ይፋ ይደረጋሉ።
ድረ ገጽ https://artsplus.tv/
አንድሮይድ https://play.google.com/st...
አይኦኤስ https://apps.apple.com/app... #artsplus #teraki #audiobooks #ethiopianliterature #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | አዲስ አበባ - አርትስ ፕላስ የድምፅ መጻሕፍትን ለአድማጮች በማቅረብ ከሚታወቀው ተራኪ መተግበሪያ ጋር የይዘት ስምምነት ተበየነ። ይህ ስምምነት በተራኪ መተግበሪያ ላይ የሚገኙ የድምፅ መጻሕፍትን በአርትስ ፕላስ በኩል ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ነው።
ተራኪ መጻሕፍትን በድምፅ በማቅረብ በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነት ያገኘ ሲሆን፣ በዚህ ትብብር አማካኝነት ይዘቶቹን ለተጨማሪ ተጠቃሚዎች ማቅረብ ያስችለዋል።
በትብብሩ የመጀመሪያ ምዕራፍ በተራኪ የሚገኙ የልጆች የድምፅ መጻሕፍት በአርትስ ፕላስ መተግበሪያ ላይ ይቀርባሉ። እነዚህ ይዘቶች በአርትስ ፕላስ ኪድስ ምድብ ስር የሚስተናገዱ ሲሆን፣ ለሕፃናት እና ለታዳጊዎች በጎ ሥነ ምግባርን፣ እውቀትን እና የፈጠራ ክህሎትን የሚያጎለብቱ ይሆናሉ።
የሁለቱም ተቋማት አመራሮች ይህ አጋርነት የሀገሪቱን የኪነ ጥበብ እና የፈጠራ ዘርፍ ለማጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።
አርትስ ፕላስ በቅርቡ አገልግሎቱን በይፋ የሚጀምር ሲሆን፣ በሂደቱ ስለሚካተቱ መጻሕፍት እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮች ወደፊት ይፋ ይደረጋሉ።
ድረ ገጽ https://artsplus.tv/
አንድሮይድ https://play.google.com/st...
አይኦኤስ https://apps.apple.com/app... #artsplus #teraki #audiobooks #ethiopianliterature #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
16 hours ago
በሁለቱ የኢሕአፓ ፖለቲከኞች እና በተቃዋሚዎች ጠበቃው አበራ ንጉሥ ላይ 12 የምርመራ ቀናት ተፈቀደ
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት "በሽብር ወንጀል" የተጠረጠሩት ፖለቲከኞቹ አበበ አካሉ እና ይሳቅ ወልዳይ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ ላይ የ12 የምርመራ ቀናት መፍቀዱን ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።
ዛሬ አርብ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም. ረፋድ ላይ የተሰየመው ችሎት የመርማሪ ፖሊስን ጥያቄ የተቀበለው፣ ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ለተነሳው ጥርጣሬ በማስረጃነት የቀረቡት ቃለ መጠይቆች ላይ "የሽብር መነሻ ሐሳብ በማግኘታቸው" እንደሆነ ጠበቃው ገልጸዋል።
ሁለቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ፖለቲከኞች እና ለተቃዋሚዎች ጥብቅና በመቆም የሚታወቁት አበራ በቁጥጥር ስር የዋሉት ሰኞ ሐምሌ 27 ነበር። በፌደራል ፖሊስ አባላት በተያዙ ሁለተኛው ቀን ረቡዕ ዕለት በከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።
መርማሪ ፖሊስ ሦስቱ ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ "በመንግሥት የፀጥታ ተቋማት እና በመንግሥትት ከፍተኛ አመራሮች ላይ የሽብር ጥቃት" ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ለፍርድ ቤት ገልጿል።
ድርጊቱን ሊፈጽሙ የነበሩት "ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ድብቅ ግንኙነት በማድረግ" እንደሆነ የገለጸው ፖሊስ፤ "ጽምዶ [ተ]ብሎ ከሚጠራው ኃይል ጋር በቀናጀት" ምልመላ እና ስለላ ሲያከናውኑ እንደነበር በመጥቀስም ወንጅሏል።
በዚህ ጉዳይ ላይ "ሥራውን አጠናቅቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የሕግ አካል ለመላክ" እንዲችልም 14 የምርመራ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ፣ በሦስቱ ግለሰቦች ላይ የቀረበውን ውንጀላ ለማስረዳት በቀረቡት በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ የተደረጉ ቃለ መጠይቆች 'የሽብር ይዘት አላቸው ወይስ የላቸውም' የሚለውን ለመወሰን ለዛሬ አርብ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ፍርድ ቤቱ በዛሬው ችሎት በመርማሪ ፖሊስ ቀረቡትን "የሐሰት ፕሮፓጋንዳ" ቪድዮ ሊንኮች መመልከቱን እንደገለጸ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ዳኞች በቀረቡላቸው የቪዲዮ ሊንኮች ላይ "የሽብር ይዘት" የሚያገኙ ከሆነ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ሊፈቀድ እንደሚችል፤ ካልሆነ ደግሞ በዋስትና ሊወጡ ይችሉ እንደነበር ጠበቃው አስረድተዋል።
እንደ ጠበቃው ገለጻ፣ ቪዲዮዎቹን የተመለከቱን ዳኞች ለፖሊስ ጥርጣሪ "መነሻ የሚሆኑ ይዘቶችን አግኝተናል" ብለዋል።
ዳኞች "በሰማነው ድምፅ ላይ ድርጊቱ የሽብር ሊመስል የሚችል የመነሻ ሀሳብ አግኝተናል። በተወሰነ መልኩ የመነሻ ሀሳብ ስላገኘን ለፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል" እንዳሉ ጠበቃው አስረድተዋል።
በዚህም መሠረት መርማሪ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት ውስጥ ተጠርጣሪዎቹ "ፍርድ ቤት ከቀረቡበት ቀን ጀምሮ የሚታሰብ የ12 ቀን የምርመራ ጊዜ" መፍቀዳቸውን ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ በቀጣዩ በሚኖረው ቀጠሮ ላይ "ፖሊስ ምርመራውን ጨርሶ" እንዲቀርብ ትዕዛዝ መሰጠቱንም ጠበቃ ሰለሞን ተናግረዋል።
BBC Amharic
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት "በሽብር ወንጀል" የተጠረጠሩት ፖለቲከኞቹ አበበ አካሉ እና ይሳቅ ወልዳይ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ ላይ የ12 የምርመራ ቀናት መፍቀዱን ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።
ዛሬ አርብ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም. ረፋድ ላይ የተሰየመው ችሎት የመርማሪ ፖሊስን ጥያቄ የተቀበለው፣ ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ለተነሳው ጥርጣሬ በማስረጃነት የቀረቡት ቃለ መጠይቆች ላይ "የሽብር መነሻ ሐሳብ በማግኘታቸው" እንደሆነ ጠበቃው ገልጸዋል።
ሁለቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ፖለቲከኞች እና ለተቃዋሚዎች ጥብቅና በመቆም የሚታወቁት አበራ በቁጥጥር ስር የዋሉት ሰኞ ሐምሌ 27 ነበር። በፌደራል ፖሊስ አባላት በተያዙ ሁለተኛው ቀን ረቡዕ ዕለት በከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።
መርማሪ ፖሊስ ሦስቱ ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ "በመንግሥት የፀጥታ ተቋማት እና በመንግሥትት ከፍተኛ አመራሮች ላይ የሽብር ጥቃት" ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ለፍርድ ቤት ገልጿል።
ድርጊቱን ሊፈጽሙ የነበሩት "ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ድብቅ ግንኙነት በማድረግ" እንደሆነ የገለጸው ፖሊስ፤ "ጽምዶ [ተ]ብሎ ከሚጠራው ኃይል ጋር በቀናጀት" ምልመላ እና ስለላ ሲያከናውኑ እንደነበር በመጥቀስም ወንጅሏል።
በዚህ ጉዳይ ላይ "ሥራውን አጠናቅቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የሕግ አካል ለመላክ" እንዲችልም 14 የምርመራ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ፣ በሦስቱ ግለሰቦች ላይ የቀረበውን ውንጀላ ለማስረዳት በቀረቡት በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ የተደረጉ ቃለ መጠይቆች 'የሽብር ይዘት አላቸው ወይስ የላቸውም' የሚለውን ለመወሰን ለዛሬ አርብ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ፍርድ ቤቱ በዛሬው ችሎት በመርማሪ ፖሊስ ቀረቡትን "የሐሰት ፕሮፓጋንዳ" ቪድዮ ሊንኮች መመልከቱን እንደገለጸ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ዳኞች በቀረቡላቸው የቪዲዮ ሊንኮች ላይ "የሽብር ይዘት" የሚያገኙ ከሆነ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ሊፈቀድ እንደሚችል፤ ካልሆነ ደግሞ በዋስትና ሊወጡ ይችሉ እንደነበር ጠበቃው አስረድተዋል።
እንደ ጠበቃው ገለጻ፣ ቪዲዮዎቹን የተመለከቱን ዳኞች ለፖሊስ ጥርጣሪ "መነሻ የሚሆኑ ይዘቶችን አግኝተናል" ብለዋል።
ዳኞች "በሰማነው ድምፅ ላይ ድርጊቱ የሽብር ሊመስል የሚችል የመነሻ ሀሳብ አግኝተናል። በተወሰነ መልኩ የመነሻ ሀሳብ ስላገኘን ለፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል" እንዳሉ ጠበቃው አስረድተዋል።
በዚህም መሠረት መርማሪ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት ውስጥ ተጠርጣሪዎቹ "ፍርድ ቤት ከቀረቡበት ቀን ጀምሮ የሚታሰብ የ12 ቀን የምርመራ ጊዜ" መፍቀዳቸውን ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ በቀጣዩ በሚኖረው ቀጠሮ ላይ "ፖሊስ ምርመራውን ጨርሶ" እንዲቀርብ ትዕዛዝ መሰጠቱንም ጠበቃ ሰለሞን ተናግረዋል።
BBC Amharic
1 day ago
ቋሚ ሲኖዶስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጉዳይ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ማስረጃ እንዲቀርብ ጥሪ አቀረበ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ምርመራ ለማካሄድ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሕዝብ መረጃና ማስረጃ እንዲያቀርብ ጥሪ አቀረበ።
ኮሚቴው እንደገለጸው፣ በሀገረ ስብከቱና በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃ የተከሰቱ ሕገ-ወጥ ቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር፣ ሕገ-ወጥ የፋይናንስ አሠራሮችና የገንዘብ ዝውውሮች፣ ሕገ-ወጥ የቦታና የቤት ኪራይ ውሎች፣ ተደራራቢ ሥራዎችና መሰል ጉዳዮችን በዝርዝር በማጣራት ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ሪፖርት ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀርባል።
በዚህ ሂደት የማጣራት ሥራው በማስረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ተቋም ተኮርና ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጣ እንዲሆን መረጃዎችን መሰብሰብ፣ መተንተን እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት ዋና የሥራ አቅጣጫው መሆኑን ገልጿል።
ኮሚቴው በተለይም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተጠቀሱት እና ተመሳሳይ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምክንያት ተጎጂ የሆኑ እና በቂ ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች፣ በሥራ ሰዓት የማስረጃቸውን ኮፒ በመያዝ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በተከፈተው የመረጃ መሰብሰቢያ ቢሮ በመቅረብ፣ በጽሑፍ፣ በድምፅ ወይም በምስል መረጃ እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
በተጨማሪም መረጃ የሚያቀርቡ ሰዎች በዚህ ምክንያት ማንኛውም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው በቋሚ ሲኖዶስ ዋስትና መሰጠቱን አስታውቆ፣ ማንኛውም አካል ያለውን መረጃና ማስረጃ በነጻነት እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርቧል።
መግለጫው በአጣሪ ኮሚቴው በሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ምርመራ ለማካሄድ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሕዝብ መረጃና ማስረጃ እንዲያቀርብ ጥሪ አቀረበ።
ኮሚቴው እንደገለጸው፣ በሀገረ ስብከቱና በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃ የተከሰቱ ሕገ-ወጥ ቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር፣ ሕገ-ወጥ የፋይናንስ አሠራሮችና የገንዘብ ዝውውሮች፣ ሕገ-ወጥ የቦታና የቤት ኪራይ ውሎች፣ ተደራራቢ ሥራዎችና መሰል ጉዳዮችን በዝርዝር በማጣራት ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ሪፖርት ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀርባል።
በዚህ ሂደት የማጣራት ሥራው በማስረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ተቋም ተኮርና ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጣ እንዲሆን መረጃዎችን መሰብሰብ፣ መተንተን እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት ዋና የሥራ አቅጣጫው መሆኑን ገልጿል።
ኮሚቴው በተለይም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተጠቀሱት እና ተመሳሳይ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምክንያት ተጎጂ የሆኑ እና በቂ ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች፣ በሥራ ሰዓት የማስረጃቸውን ኮፒ በመያዝ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በተከፈተው የመረጃ መሰብሰቢያ ቢሮ በመቅረብ፣ በጽሑፍ፣ በድምፅ ወይም በምስል መረጃ እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
በተጨማሪም መረጃ የሚያቀርቡ ሰዎች በዚህ ምክንያት ማንኛውም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው በቋሚ ሲኖዶስ ዋስትና መሰጠቱን አስታውቆ፣ ማንኛውም አካል ያለውን መረጃና ማስረጃ በነጻነት እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርቧል።
መግለጫው በአጣሪ ኮሚቴው በሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
2 days ago
ቋሚ ሲኖዶስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጉዳይ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ማስረጃ እንዲቀርብ ጥሪ አቀረበ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ምርመራ ለማካሄድ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሕዝብ መረጃና ማስረጃ እንዲያቀርብ ጥሪ አቀረበ።
ኮሚቴው እንደገለጸው፣ በሀገረ ስብከቱና በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃ የተከሰቱ ሕገ-ወጥ ቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር፣ ሕገ-ወጥ የፋይናንስ አሠራሮችና የገንዘብ ዝውውሮች፣ ሕገ-ወጥ የቦታና የቤት ኪራይ ውሎች፣ ተደራራቢ ሥራዎችና መሰል ጉዳዮችን በዝርዝር በማጣራት ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ሪፖርት ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀርባል።
በዚህ ሂደት የማጣራት ሥራው በማስረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ተቋም ተኮርና ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጣ እንዲሆን መረጃዎችን መሰብሰብ፣ መተንተን እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት ዋና የሥራ አቅጣጫው መሆኑን ገልጿል።
ኮሚቴው በተለይም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተጠቀሱት እና ተመሳሳይ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምክንያት ተጎጂ የሆኑ እና በቂ ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች፣ በሥራ ሰዓት የማስረጃቸውን ኮፒ በመያዝ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በተከፈተው የመረጃ መሰብሰቢያ ቢሮ በመቅረብ፣ በጽሑፍ፣ በድምፅ ወይም በምስል መረጃ እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
በተጨማሪም መረጃ የሚያቀርቡ ሰዎች በዚህ ምክንያት ማንኛውም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው በቋሚ ሲኖዶስ ዋስትና መሰጠቱን አስታውቆ፣ ማንኛውም አካል ያለውን መረጃና ማስረጃ በነጻነት እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርቧል።
መግለጫው በአጣሪ ኮሚቴው በሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ምርመራ ለማካሄድ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሕዝብ መረጃና ማስረጃ እንዲያቀርብ ጥሪ አቀረበ።
ኮሚቴው እንደገለጸው፣ በሀገረ ስብከቱና በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃ የተከሰቱ ሕገ-ወጥ ቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር፣ ሕገ-ወጥ የፋይናንስ አሠራሮችና የገንዘብ ዝውውሮች፣ ሕገ-ወጥ የቦታና የቤት ኪራይ ውሎች፣ ተደራራቢ ሥራዎችና መሰል ጉዳዮችን በዝርዝር በማጣራት ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ሪፖርት ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀርባል።
በዚህ ሂደት የማጣራት ሥራው በማስረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ተቋም ተኮርና ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጣ እንዲሆን መረጃዎችን መሰብሰብ፣ መተንተን እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት ዋና የሥራ አቅጣጫው መሆኑን ገልጿል።
ኮሚቴው በተለይም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተጠቀሱት እና ተመሳሳይ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምክንያት ተጎጂ የሆኑ እና በቂ ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች፣ በሥራ ሰዓት የማስረጃቸውን ኮፒ በመያዝ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በተከፈተው የመረጃ መሰብሰቢያ ቢሮ በመቅረብ፣ በጽሑፍ፣ በድምፅ ወይም በምስል መረጃ እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
በተጨማሪም መረጃ የሚያቀርቡ ሰዎች በዚህ ምክንያት ማንኛውም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው በቋሚ ሲኖዶስ ዋስትና መሰጠቱን አስታውቆ፣ ማንኛውም አካል ያለውን መረጃና ማስረጃ በነጻነት እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርቧል።
መግለጫው በአጣሪ ኮሚቴው በሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ምክክር ለዘላቂ ሠላም
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከጥንታዊ ነጻ ሀገረ መንግሥታት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በበርካታ ባህሎች፣ ቋንቋዎችና እሴቶች የተዋቀረች ኅብረብሔራዊት ሀገር ናት፡፡
ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ መኖሪያ የሆነችው ሀገራችን ህልውናዋን አጽንታ ዘመናትን መሻገር የቻለችው በልጆቿ የተባበረ ክንድ ስለመሆኑ ታሪክ ህያው ምስክር ነው።
በእነዚያ ጊዜያት ውስጥ ሰላሟንና ልማቷን ሲፈታተኑ የዘለቁ ቅራኔዎችን በሰላማዊ ውይይት በመፍታት ነገዋን የተሻለ ለማድረግ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ትገኛለች፡፡
ዜጎቿ ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋግጥ የጋራ መግባባት ላይ የሚያደርስ መፍትሄ እንዲያበጁ በገለልተኛ የምክክር ኮሚሽን የሚመራ አሳታፊና አካታች ሀገራዊ መድረክ አበጅታለች፡፡
ይህ አሳታፊነት ምክከሩ በሀገሪቱ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከታዩ እጅግ ሰፊና ለውጥ አምጪ እንቅስቃሴዎች መካከል አንዱ መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡
ለብዙ ዓመታት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶች ዛሬም ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚቀሰቀሱ ግጭቶችና የሰላም እጦት በምክንያትነት ሲቀርቡ ይስተዋላል፡፡
ሀገር በቀል እውቀቶችንና ባህላዊ የውይይት እሴቶችን ማዕከል በማድረግ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር እነዚህን የቆዩ ቁርሾዎች በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል፡፡
የጋራ ሀገራዊ ራዕይ እውን የሚሆንበት ይህ መድረክ ከጊዜያዊ ፖለቲካዊ ጥቅም በላይ የሀገሪቱን የዘላቂ ሰላም ጉዞ የሚያሳልጥ ታሪካዊ እድል ነው፡፡
የሁሉም ኢትዮጵያውያን ድምፅ እኩል የሚሰማበት ይህ ሀገራዊ ምክክር የአሸናፊና ተሸናፊ ትርክትን በጋራ መግባባት ላይ በተመሠረተ ባህል የሚተካ ወሳኝ መድረክ ነው።
አንዲት ሀገር ለትናንት ቅራኔዎች ሕዝብን ባሳተፈ መንገድ እውነተኛ መፍትሄ ሳትሰጥ ሰላማዊ ነገን መገንባት አትችልም።
በዚህ መንፈስ በእኩልነት ላይ በተመሰረተ፣ ግልጽ፣ ነጻ እና አሳታፊ ሂደት እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፥ ሀገሪቱን ወደ ብልጽግና የሚያሸጋግር ድልድይ እንዲሁም ከውርስ ህመሟ የሚፈውስ ፍቱን መድሃኒት ነው፡፡
ግጭትና የሕዝቦች መለያየት የሀገርን ሀብት የሚያወድሙና ልማትን የሚያደናቅፉ በመሆናቸው፤ የሀገርን ጥቅም ባስቀደመ የጋራ መግባባት የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሁኔታን በመፍጠር ብሔራዊ ምክክሩ ለጠንካራ ኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት ይጥላል።
የዜጎችን የጋራ መግባባት ጽኑ መሰረት አድርጋ የምትገነባው ሰላማዊት ኢትዮጵያ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቴክኖሎጂና ሌሎች የመሠረተ ልማት ዘርፎች ያላትን አቅም ሙሉ በሙሉ በመጠቀም የዜጎቿን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ትችላለች፡፡
ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ማዕከል እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ እንደመሆኗ፤ አለመግባባትን በውይይት ለመፍታት የጀመረችው ጉዞ አፍሪካውያን ችግሮችን በራሳቸው ለመፍታት ለሚያደርጉት ጥረት መልካም አርአያ ነው።
የተዋሃደችና ደህንነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን በማረጋጋት የቀጣናውን የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድና የጋራ ደህንነት ማረጋገጥ ይቻላታል፡፡
ምክክሩ የአንድ ጊዜ ሁነት ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን ሀገራዊ ተቆርቋሪነት የሚጠይቅ የታሰበበት ረጅም ጉዞ ነው።
አለመግባባቶች የማህበረሰብ ተፈጥሯዊ አካል ቢሆኑም ጠንካራ ሀገር የሚገነባው ግን እነዚህን ልዩነቶች ባስተናገዱበት ጤናማ መንገድ እንደሆነ ይታመናል፡፡
ኢትዮጵያ ከግጭት ይልቅ ውይይትን በማስቀደም እያከናወነች የምትገኘው ሀገራዊ ምክክር አንድነት፣ የተቋማት ጥንካሬና ዘላቂ ሰላም የሚጸናበት አዲስ ምዕራፍ ነው፡፡
ከምንጊዜውም በላይ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በመጠቀም ለወደፊቱ ትውልድ ምቹ ሀገር ለመገንባት ጊዜው አሁን ነው።
በምሕረት ደምሴ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከጥንታዊ ነጻ ሀገረ መንግሥታት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በበርካታ ባህሎች፣ ቋንቋዎችና እሴቶች የተዋቀረች ኅብረብሔራዊት ሀገር ናት፡፡
ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ መኖሪያ የሆነችው ሀገራችን ህልውናዋን አጽንታ ዘመናትን መሻገር የቻለችው በልጆቿ የተባበረ ክንድ ስለመሆኑ ታሪክ ህያው ምስክር ነው።
በእነዚያ ጊዜያት ውስጥ ሰላሟንና ልማቷን ሲፈታተኑ የዘለቁ ቅራኔዎችን በሰላማዊ ውይይት በመፍታት ነገዋን የተሻለ ለማድረግ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ትገኛለች፡፡
ዜጎቿ ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋግጥ የጋራ መግባባት ላይ የሚያደርስ መፍትሄ እንዲያበጁ በገለልተኛ የምክክር ኮሚሽን የሚመራ አሳታፊና አካታች ሀገራዊ መድረክ አበጅታለች፡፡
ይህ አሳታፊነት ምክከሩ በሀገሪቱ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከታዩ እጅግ ሰፊና ለውጥ አምጪ እንቅስቃሴዎች መካከል አንዱ መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡
ለብዙ ዓመታት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶች ዛሬም ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚቀሰቀሱ ግጭቶችና የሰላም እጦት በምክንያትነት ሲቀርቡ ይስተዋላል፡፡
ሀገር በቀል እውቀቶችንና ባህላዊ የውይይት እሴቶችን ማዕከል በማድረግ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር እነዚህን የቆዩ ቁርሾዎች በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል፡፡
የጋራ ሀገራዊ ራዕይ እውን የሚሆንበት ይህ መድረክ ከጊዜያዊ ፖለቲካዊ ጥቅም በላይ የሀገሪቱን የዘላቂ ሰላም ጉዞ የሚያሳልጥ ታሪካዊ እድል ነው፡፡
የሁሉም ኢትዮጵያውያን ድምፅ እኩል የሚሰማበት ይህ ሀገራዊ ምክክር የአሸናፊና ተሸናፊ ትርክትን በጋራ መግባባት ላይ በተመሠረተ ባህል የሚተካ ወሳኝ መድረክ ነው።
አንዲት ሀገር ለትናንት ቅራኔዎች ሕዝብን ባሳተፈ መንገድ እውነተኛ መፍትሄ ሳትሰጥ ሰላማዊ ነገን መገንባት አትችልም።
በዚህ መንፈስ በእኩልነት ላይ በተመሰረተ፣ ግልጽ፣ ነጻ እና አሳታፊ ሂደት እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፥ ሀገሪቱን ወደ ብልጽግና የሚያሸጋግር ድልድይ እንዲሁም ከውርስ ህመሟ የሚፈውስ ፍቱን መድሃኒት ነው፡፡
ግጭትና የሕዝቦች መለያየት የሀገርን ሀብት የሚያወድሙና ልማትን የሚያደናቅፉ በመሆናቸው፤ የሀገርን ጥቅም ባስቀደመ የጋራ መግባባት የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሁኔታን በመፍጠር ብሔራዊ ምክክሩ ለጠንካራ ኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት ይጥላል።
የዜጎችን የጋራ መግባባት ጽኑ መሰረት አድርጋ የምትገነባው ሰላማዊት ኢትዮጵያ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቴክኖሎጂና ሌሎች የመሠረተ ልማት ዘርፎች ያላትን አቅም ሙሉ በሙሉ በመጠቀም የዜጎቿን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ትችላለች፡፡
ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ማዕከል እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ እንደመሆኗ፤ አለመግባባትን በውይይት ለመፍታት የጀመረችው ጉዞ አፍሪካውያን ችግሮችን በራሳቸው ለመፍታት ለሚያደርጉት ጥረት መልካም አርአያ ነው።
የተዋሃደችና ደህንነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን በማረጋጋት የቀጣናውን የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድና የጋራ ደህንነት ማረጋገጥ ይቻላታል፡፡
ምክክሩ የአንድ ጊዜ ሁነት ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን ሀገራዊ ተቆርቋሪነት የሚጠይቅ የታሰበበት ረጅም ጉዞ ነው።
አለመግባባቶች የማህበረሰብ ተፈጥሯዊ አካል ቢሆኑም ጠንካራ ሀገር የሚገነባው ግን እነዚህን ልዩነቶች ባስተናገዱበት ጤናማ መንገድ እንደሆነ ይታመናል፡፡
ኢትዮጵያ ከግጭት ይልቅ ውይይትን በማስቀደም እያከናወነች የምትገኘው ሀገራዊ ምክክር አንድነት፣ የተቋማት ጥንካሬና ዘላቂ ሰላም የሚጸናበት አዲስ ምዕራፍ ነው፡፡
ከምንጊዜውም በላይ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በመጠቀም ለወደፊቱ ትውልድ ምቹ ሀገር ለመገንባት ጊዜው አሁን ነው።
በምሕረት ደምሴ
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ጃኬን አሳታሚ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ በድርጅቱ፣ በሰራተኞቹ እና በንብረቶቹ ላይ የተፈጸሙ ተከታታይ እና ከባድ ጥቃቶችን አስመልክቶ ለአጋሮቹ፣ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ፣ ለሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና ለመላው ህዝብ ይፋዊ መግለጫ አውጥቷል።
በመግለጫው መሰረት ቅዳሜ ኦገስት 1 ቀን 2026 የ'አዲስ ስታንዳርድ' ዋና አዘጋጅ የሆነው ዮናስ ከድር በጸጥታ ኃይሎች ታፍኖ ከተወሰደ በኋላ ለ24 ሰዓታት ያህል አካላዊ ጥቃት እና የተራዘመ ምርመራ ተፈጽሞበታል። ዋና አዘጋጁ ከተለቀቀ በኋላ በደረሰበት ጥቃት ዙሪያ ዝርዝር የጽሁፍ ሪፖርት ለድርጅቱ የህግ ክፍል ያቀረበ ሲሆን፣ ይህም ማስረጃ ለቀጣይ የህግ ሂደት አካል ሆኖ መያዙን አሳታሚው ገልጿል።
በማግስቱ እሁድ ኦገስት 2 ቀን 2026 ደግሞ ከባድ መሳሪያ የታጠቁ የጸጥታ እና የደህንነት ኃይሎች ያለምንም ህጋዊ ሂደት ወደ አዲስ ስታንዳርድ ቢሮ በመግባት በልዩ ሁኔታ ከተገነባው የፕሮዳክሽን ስቱዲዮ ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያላቸውን የመልቲሚዲያ እቃዎች ወስደዋል። ከጥቃቱ በኋላ የድርጅቱ የሰው ሀብት አስተዳደር እና የህንፃው አስተዳደር ባደረጉት ማጣራት፣ በርካታ ፕሮፌሽናል 4K የቪዲዮ ካሜራዎች፣ ትሪፖዶች፣ የድምፅ መቅረጫ መሳሪያዎች እና ሌሎች ለስራው እጅግ አስፈላጊ የሆኑ የብሮድካስት ግብዓቶች መወሰዳቸውን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በስቱዲዮው የብርሃን ስርዓቶች እና በተያያዥ መሳሪያዎች ላይ ሆን ተብሎ የተፈጸመ የውድመት ድርጊት መስተዋሉን አሳታሚው ጠቁሟል። የጠፉት እና የወደሙት ንብረቶች ሙሉ ዝርዝር እና ግምት ለህግ ሂደት እንዲያገለግል ተሰንዶ ተቀምጧል።
በድርጅቱ ላይ ያለው ጫና ይበልጥ ተባብሶ ሰኞ ኦገስት 3 ቀን 2026፣ ጃኬን አሳታሚ ላለፉት 16 ዓመታት ሲሰራበት የነበረው ህንፃ አስተዳደር በፖሊስ በተደረገበት ጫና ምክንያት ኩባንያው በሶስት ቀናት ውስጥ ቢሮውን ለቆ እንዲወጣ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንዲሰጥ ተገዷል። ሆኖም የጃኬን የህግ ክፍል ይህ የማስወጣት እርምጃ ህጋዊ የውል መሰረት የሌለው እና አስገዳጅ የሆነውን የኪራይ ውል የሚጥስ መሆኑን በመግለጽ ማስጠንቀቂያውን ለመቃወም ህጋዊ እርምጃ መጀመሩን አስታውቋል።
እነዚህ ተከታታይ ክስተቶች የተፈጸሙት ጃኬን አሳታሚ የኢትዮጵያ ሚዲያ ባለስልጣን የ'አዲስ ስታንዳርድ'ን የኦንላይን ሚዲያ ምዝገባ ፈቃድ ለመሰረዝ ያሳለፈውን ውሳኔ በመቃወም ፍርድ ቤት ባቀረበው አቤቱታ ላይ የህግ ክትትል እያደረገ ባለበት ወቅት ነው። ይህ የድርጊቶች ቅደም ተከተል ነጻ የሚዲያ ተቋማት ከማስፈራራት እና ከህገ-ወጥ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው ለመስራት ያላቸውን አቅም፣ እንዲሁም የህግ የበላይነት መኖር ላይ ጥልቅ ስጋት የሚፈጥር ነው ሲል ድርጅቱ ገልጿል።
ጃኬን አሳታሚ የፍትህ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የድርጅቱ የህግ ክፍል በሚያደርገው ማጣራት ላይ ሙሉ ትብብር እንዲያደርጉ፣ የተወሰደው እርምጃ ህጋዊ መሰረት እንዲገለጽ እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጥሪ አቅርቧል። እንዲሁም የሀገሪቱ የፍትህ ተቋማት የህግ ሂደትን እንዲያከብሩ እና በህገ-መንግስቱ የተረጋገጠውን የሀሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የፕሬስ ነጻነት እና የህግ የበላይነት መብቶችን እንዲያስጠብቁ አሳስቧል።
ጃኬን አሳታሚ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና አዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ ይህ ሁሉ ያልተጠበቀ ፈታኝ ሁኔታ ቢኖርም፣ ለነጻ፣ ሙያዊ እና የህዝብን ጥቅም ለሚያስቀድም የጋዜጠኝነት ስራ ያላቸውን ቁርጠኝነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ድርጅቱም የሰራተኞቹን ደህንነት ለመጠበቅ እና መብቱን ለማስከበር ሁሉንም ህጋዊ አማራጮች እንደሚጠቀም አስታውቋል።
በመግለጫው መሰረት ቅዳሜ ኦገስት 1 ቀን 2026 የ'አዲስ ስታንዳርድ' ዋና አዘጋጅ የሆነው ዮናስ ከድር በጸጥታ ኃይሎች ታፍኖ ከተወሰደ በኋላ ለ24 ሰዓታት ያህል አካላዊ ጥቃት እና የተራዘመ ምርመራ ተፈጽሞበታል። ዋና አዘጋጁ ከተለቀቀ በኋላ በደረሰበት ጥቃት ዙሪያ ዝርዝር የጽሁፍ ሪፖርት ለድርጅቱ የህግ ክፍል ያቀረበ ሲሆን፣ ይህም ማስረጃ ለቀጣይ የህግ ሂደት አካል ሆኖ መያዙን አሳታሚው ገልጿል።
በማግስቱ እሁድ ኦገስት 2 ቀን 2026 ደግሞ ከባድ መሳሪያ የታጠቁ የጸጥታ እና የደህንነት ኃይሎች ያለምንም ህጋዊ ሂደት ወደ አዲስ ስታንዳርድ ቢሮ በመግባት በልዩ ሁኔታ ከተገነባው የፕሮዳክሽን ስቱዲዮ ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያላቸውን የመልቲሚዲያ እቃዎች ወስደዋል። ከጥቃቱ በኋላ የድርጅቱ የሰው ሀብት አስተዳደር እና የህንፃው አስተዳደር ባደረጉት ማጣራት፣ በርካታ ፕሮፌሽናል 4K የቪዲዮ ካሜራዎች፣ ትሪፖዶች፣ የድምፅ መቅረጫ መሳሪያዎች እና ሌሎች ለስራው እጅግ አስፈላጊ የሆኑ የብሮድካስት ግብዓቶች መወሰዳቸውን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በስቱዲዮው የብርሃን ስርዓቶች እና በተያያዥ መሳሪያዎች ላይ ሆን ተብሎ የተፈጸመ የውድመት ድርጊት መስተዋሉን አሳታሚው ጠቁሟል። የጠፉት እና የወደሙት ንብረቶች ሙሉ ዝርዝር እና ግምት ለህግ ሂደት እንዲያገለግል ተሰንዶ ተቀምጧል።
በድርጅቱ ላይ ያለው ጫና ይበልጥ ተባብሶ ሰኞ ኦገስት 3 ቀን 2026፣ ጃኬን አሳታሚ ላለፉት 16 ዓመታት ሲሰራበት የነበረው ህንፃ አስተዳደር በፖሊስ በተደረገበት ጫና ምክንያት ኩባንያው በሶስት ቀናት ውስጥ ቢሮውን ለቆ እንዲወጣ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንዲሰጥ ተገዷል። ሆኖም የጃኬን የህግ ክፍል ይህ የማስወጣት እርምጃ ህጋዊ የውል መሰረት የሌለው እና አስገዳጅ የሆነውን የኪራይ ውል የሚጥስ መሆኑን በመግለጽ ማስጠንቀቂያውን ለመቃወም ህጋዊ እርምጃ መጀመሩን አስታውቋል።
እነዚህ ተከታታይ ክስተቶች የተፈጸሙት ጃኬን አሳታሚ የኢትዮጵያ ሚዲያ ባለስልጣን የ'አዲስ ስታንዳርድ'ን የኦንላይን ሚዲያ ምዝገባ ፈቃድ ለመሰረዝ ያሳለፈውን ውሳኔ በመቃወም ፍርድ ቤት ባቀረበው አቤቱታ ላይ የህግ ክትትል እያደረገ ባለበት ወቅት ነው። ይህ የድርጊቶች ቅደም ተከተል ነጻ የሚዲያ ተቋማት ከማስፈራራት እና ከህገ-ወጥ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው ለመስራት ያላቸውን አቅም፣ እንዲሁም የህግ የበላይነት መኖር ላይ ጥልቅ ስጋት የሚፈጥር ነው ሲል ድርጅቱ ገልጿል።
ጃኬን አሳታሚ የፍትህ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የድርጅቱ የህግ ክፍል በሚያደርገው ማጣራት ላይ ሙሉ ትብብር እንዲያደርጉ፣ የተወሰደው እርምጃ ህጋዊ መሰረት እንዲገለጽ እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጥሪ አቅርቧል። እንዲሁም የሀገሪቱ የፍትህ ተቋማት የህግ ሂደትን እንዲያከብሩ እና በህገ-መንግስቱ የተረጋገጠውን የሀሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የፕሬስ ነጻነት እና የህግ የበላይነት መብቶችን እንዲያስጠብቁ አሳስቧል።
ጃኬን አሳታሚ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና አዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ ይህ ሁሉ ያልተጠበቀ ፈታኝ ሁኔታ ቢኖርም፣ ለነጻ፣ ሙያዊ እና የህዝብን ጥቅም ለሚያስቀድም የጋዜጠኝነት ስራ ያላቸውን ቁርጠኝነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ድርጅቱም የሰራተኞቹን ደህንነት ለመጠበቅ እና መብቱን ለማስከበር ሁሉንም ህጋዊ አማራጮች እንደሚጠቀም አስታውቋል።
2 days ago
የድምፃዊ ፍቃዱ ትዛዙ ~ "ቁንጅና"
#ethiopia | ድምፃዊ ፍቃዱ ትዛዙ ከዚህ ቀደም የድምፃዊ ተፈራ ነጋሽን ሙሉ አልበም በማቀናበርና በማዘጋጀት ከሙዚቃ አፍቃሪያን ከፍተኛ ተቀባይነትን ያገኘ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ በራሱ አዲስ ሥራ "ቁንጅና" በሚል ርዕስ ለአድማጮች አቅርቧል።
ሙዚቃው በተለቀቀ በጥቂት ቀናት ውስጥ ከ100,000 በላይ እይታዎችን በማስመዝገብ የአድማጮችን ቀልብ የሳበ ተወዳጅ ሥራ ሆኗል።
"ቁንጅና" የሙዚቃ ክሬዲት
ግጥምና ዜማ፡ ፍቃዱ ትዛዙ
ሙዚቃ ቅንብር እና ሚክሲንግ፡ አቤል ጳውሎስ
ማስተሪንግ፡ አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ
ድምፅ ቅጂ፡ ታምራት ድሪባ (Tamnote Studio)
ቤዝ ጊታር፡ አቤል ጳውሎስ
ሊድ ጊታር፡ በረከት ተስፋዝጊ (ቤኪ)
ሙዚቃው በናሆም ሬከርድስ አማካይነት ለአድማጮች ቀርቧል።
https://youtu.be/QjhgZNHig...
#ethiopia | ድምፃዊ ፍቃዱ ትዛዙ ከዚህ ቀደም የድምፃዊ ተፈራ ነጋሽን ሙሉ አልበም በማቀናበርና በማዘጋጀት ከሙዚቃ አፍቃሪያን ከፍተኛ ተቀባይነትን ያገኘ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ በራሱ አዲስ ሥራ "ቁንጅና" በሚል ርዕስ ለአድማጮች አቅርቧል።
ሙዚቃው በተለቀቀ በጥቂት ቀናት ውስጥ ከ100,000 በላይ እይታዎችን በማስመዝገብ የአድማጮችን ቀልብ የሳበ ተወዳጅ ሥራ ሆኗል።
"ቁንጅና" የሙዚቃ ክሬዲት
ግጥምና ዜማ፡ ፍቃዱ ትዛዙ
ሙዚቃ ቅንብር እና ሚክሲንግ፡ አቤል ጳውሎስ
ማስተሪንግ፡ አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ
ድምፅ ቅጂ፡ ታምራት ድሪባ (Tamnote Studio)
ቤዝ ጊታር፡ አቤል ጳውሎስ
ሊድ ጊታር፡ በረከት ተስፋዝጊ (ቤኪ)
ሙዚቃው በናሆም ሬከርድስ አማካይነት ለአድማጮች ቀርቧል።
https://youtu.be/QjhgZNHig...
3 days ago
የCPJ የ2026 ዓለም አቀፍ የፕሬስ ነፃነት ሽልማት አሸናፊዎች ተገለጹ
#ethiopia | የጋዜጠኞችን ጥበቃ ኮሚቴ (CPJ) ለ36ኛ ጊዜ የሚያዘጋጀውን ዓመታዊ International Press Freedom Awards (IPFA) የ2026 ተሸላሚ ጋዜጠኞችን ይፋ አድርጓል።
የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ኅዳር 19 ቀን 2026 በኒውዮርክ ከተማ የሚካሄድ ሲሆን፣ ከተለያዩ አገራት የተውጣጡ ጋዜጠኞች በድፍረታቸውና በሙያዊ ተግባራቸው ይሸለማሉ።
በዚህ ዓመት ከተሸለሙት መካከል ከሊባኖስ፣ ከኤርትራ፣ ከሀንጋሪ፣ ከኮሎምቢያ እና ከሚያንማር የመጡ ጋዜጠኞች ይገኛሉ።
ክርስቲና አሲ – ሊባኖስ
የAFP ፎቶ ጋዜጠኛ ክርስቲና አሲ በጥቅምት 2023 በእስራኤል–ሊባኖስ ድንበር ዘገባ ስትሰራ በደረሰባት ጥቃት ቀኝ እግሯን አጥታለች፤ የሮይተርስ ጋዜጠኛ ኢሳም አብዳላህም በዚያው ጥቃት ተገድሏል።
CPJ እንደሚለው፣ በዚህ ጉዳይ እስካሁን ተጠያቂ የሆነ አካል የለም። አሲ ከዚያ በኋላ ለጋዜጠኞች ደኅንነትና ለፍትሕ ድምፅ ሆና እየሠራች ነው።
"ኤርትራ 16"
CPJ በዚህ ዓመት ለ25 ዓመታት ያለ ፍርድ ታስረው የቆዩትን "ኤርትራ 16" የተባሉ 16 ጋዜጠኞች በጋራ ሸልሟል።
እነዚህ ጋዜጠኞች በ2001 የግል ሚዲያዎች ከተዘጉ በኋላ ታስረው ሲሆን፣ እስካሁን ክስ አልቀረበባቸውም፣ ፍርድ ቤትም አልቀረቡም። የጤናቸውና የሕይወታቸው ሁኔታ እንኳን በግልፅ አይታወቅም።
ሳቦልች ፓንዪ – ሀንጋሪ
የምርመራ ጋዜጠኛው ሳቦልች ፓንዪ የሩሲያ ተፅዕኖ፣ ሙስናና የፖለቲካ ሥልጣን ላይ በሠራቸው ዘገባዎች የሚታወቅ ሲሆን፣ በ2026 የሀንጋሪ ምርጫ ዋዜማ ከባድ ጫናና የስለላ ክስ ተጋፍጦበታል።
ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ – ኮሎምቢያ
በአሜሪካ የስፓኒሽ ቋንቋ ሚዲያ Nashville Noticias ዘጋቢ የሆነችው ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ በ2026 በICE ተይዛ ታስራ ነበር።
CPJ ጉዳዩ በስደተኞች ጉዳይ ላይ በምታደርገው ዘገባ ምክንያት በጋዜጠኞች ላይ የሚደረግ ጫናን የሚያሳይ ነው ብሏል።
ሳይ ዛው ታይክ – ሚያንማር
የMyanmar Now ፎቶ ጋዜጠኛ ሳይ ዛው ታይክ በ2023 የCyclone Mocha ጉዳትን ሲዘግብ ተይዞ 20 ዓመት ከባድ እስራት ተፈርዶበታል።
CPJ እንደሚለው ሚያንማር በዓለም ላይ ጋዜጠኞችን በእስር ከሚያቆዩ አገራት መካከል ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
የGwen Ifill የፕሬስ ነፃነት ሽልማት
የ2026 Gwen Ifill Press Freedom Award የኤል ሳልቫዶር ጋዜጠኛና El Faro መስራች ካርሎስ ዳዳ ተሸላሚ ሆኗል።
ዳዳ ለዓመታት በሙስና፣ በወንጀለኛ ቡድኖች፣ በሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና በመንግሥት አሰራር ላይ የምርመራ ዘገባዎችን በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከመንግሥታዊ ጫና የተነሳ በስደት እየኖረ ነው።
CPJ እንደገለጸው፣ የ2026 ተሸላሚዎች የተመረጡት ከፍተኛ አደጋና ጫና ውስጥ ሆነው ለሕዝብ እውነታን ለማድረስ ባሳዩት ድፍረትና ቁርጠኝነት መሠረት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የጋዜጠኞችን ጥበቃ ኮሚቴ (CPJ) ለ36ኛ ጊዜ የሚያዘጋጀውን ዓመታዊ International Press Freedom Awards (IPFA) የ2026 ተሸላሚ ጋዜጠኞችን ይፋ አድርጓል።
የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ኅዳር 19 ቀን 2026 በኒውዮርክ ከተማ የሚካሄድ ሲሆን፣ ከተለያዩ አገራት የተውጣጡ ጋዜጠኞች በድፍረታቸውና በሙያዊ ተግባራቸው ይሸለማሉ።
በዚህ ዓመት ከተሸለሙት መካከል ከሊባኖስ፣ ከኤርትራ፣ ከሀንጋሪ፣ ከኮሎምቢያ እና ከሚያንማር የመጡ ጋዜጠኞች ይገኛሉ።
ክርስቲና አሲ – ሊባኖስ
የAFP ፎቶ ጋዜጠኛ ክርስቲና አሲ በጥቅምት 2023 በእስራኤል–ሊባኖስ ድንበር ዘገባ ስትሰራ በደረሰባት ጥቃት ቀኝ እግሯን አጥታለች፤ የሮይተርስ ጋዜጠኛ ኢሳም አብዳላህም በዚያው ጥቃት ተገድሏል።
CPJ እንደሚለው፣ በዚህ ጉዳይ እስካሁን ተጠያቂ የሆነ አካል የለም። አሲ ከዚያ በኋላ ለጋዜጠኞች ደኅንነትና ለፍትሕ ድምፅ ሆና እየሠራች ነው።
"ኤርትራ 16"
CPJ በዚህ ዓመት ለ25 ዓመታት ያለ ፍርድ ታስረው የቆዩትን "ኤርትራ 16" የተባሉ 16 ጋዜጠኞች በጋራ ሸልሟል።
እነዚህ ጋዜጠኞች በ2001 የግል ሚዲያዎች ከተዘጉ በኋላ ታስረው ሲሆን፣ እስካሁን ክስ አልቀረበባቸውም፣ ፍርድ ቤትም አልቀረቡም። የጤናቸውና የሕይወታቸው ሁኔታ እንኳን በግልፅ አይታወቅም።
ሳቦልች ፓንዪ – ሀንጋሪ
የምርመራ ጋዜጠኛው ሳቦልች ፓንዪ የሩሲያ ተፅዕኖ፣ ሙስናና የፖለቲካ ሥልጣን ላይ በሠራቸው ዘገባዎች የሚታወቅ ሲሆን፣ በ2026 የሀንጋሪ ምርጫ ዋዜማ ከባድ ጫናና የስለላ ክስ ተጋፍጦበታል።
ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ – ኮሎምቢያ
በአሜሪካ የስፓኒሽ ቋንቋ ሚዲያ Nashville Noticias ዘጋቢ የሆነችው ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ በ2026 በICE ተይዛ ታስራ ነበር።
CPJ ጉዳዩ በስደተኞች ጉዳይ ላይ በምታደርገው ዘገባ ምክንያት በጋዜጠኞች ላይ የሚደረግ ጫናን የሚያሳይ ነው ብሏል።
ሳይ ዛው ታይክ – ሚያንማር
የMyanmar Now ፎቶ ጋዜጠኛ ሳይ ዛው ታይክ በ2023 የCyclone Mocha ጉዳትን ሲዘግብ ተይዞ 20 ዓመት ከባድ እስራት ተፈርዶበታል።
CPJ እንደሚለው ሚያንማር በዓለም ላይ ጋዜጠኞችን በእስር ከሚያቆዩ አገራት መካከል ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
የGwen Ifill የፕሬስ ነፃነት ሽልማት
የ2026 Gwen Ifill Press Freedom Award የኤል ሳልቫዶር ጋዜጠኛና El Faro መስራች ካርሎስ ዳዳ ተሸላሚ ሆኗል።
ዳዳ ለዓመታት በሙስና፣ በወንጀለኛ ቡድኖች፣ በሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና በመንግሥት አሰራር ላይ የምርመራ ዘገባዎችን በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከመንግሥታዊ ጫና የተነሳ በስደት እየኖረ ነው።
CPJ እንደገለጸው፣ የ2026 ተሸላሚዎች የተመረጡት ከፍተኛ አደጋና ጫና ውስጥ ሆነው ለሕዝብ እውነታን ለማድረስ ባሳዩት ድፍረትና ቁርጠኝነት መሠረት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
3 days ago
መዝሙረ ሄላም ላይ የተደረገ አጭር ኂሳዊ ንባብ
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
3 days ago
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
*********************
ኢትዮጵያ በታሪኳ ትልቅ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ሀገራችንን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ ልዩነቶችን በሠለጠነ መንገድ ለመፍታት እና በዋና ዋና ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የዚህ ዘመን ትልቁ ታሪካዊ ክስተት ነው።
እንደ ሀገር የገጠሙንን ዘመናት የተሻገሩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ውጥንቅጦችን በዘላቂነት ለመፍታት ከግጭት ይልቅ ውይይትን፣ ከመግፋት ይልቅ አሳታፊነትን ማስቀደም ብቸኛው ዘላቂ መንገድ መሆኑ ግልጽ እውነታ ሆኗል።
የሀገራዊ ምክክሩ ዋነኛ ዓላማ በሕዝቦች መካከል ለዘመናት የዘለቁ እና መፍትሔ ያላገኙ መዋቅራዊ እና ፖለቲካዊ ልዩነቶችን ማጥበብ ነው። ሕዝቡ በነጻነት አስተያየቱን እንዲሰጥ በማድረግ የጋራ እሴቶችን መቅረጽ እንዲሁም ሀገራዊ አንድነትን እና ብዝኃነትን ያጣጣመ የጋራ የወደፊት ራዕይ በመቅረጽ የወል ትርክትን መገንባት ነው።
ይህንን የምክክር ሒደት ልዩ የሚያደርገው ከላይ ወደ ታች የሚወርድ ውሳኔ ሳይሆን፣ ከታች ወደ ላይ የኅብረተሰቡን ድምፅ የሚሰበስብ መሆኑ ነው። እውነተኛ ሀገር ግንባታ የሚጀምረውም የእያንዳንዱ ዜጋ ድምፅ እኩል ዋጋ አግኝቶ ሲደመጥ ብቻ ነው።
የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሃይማኖት አባቶች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማኅበራት በተወካዮቻቸው አማካኝነት የአጀንዳ ግብዓት ማቅረባቸው የሒደቱን ተቀባይነት እና ሕጋዊነት በማጎልበት አሳታፊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በየክልሎቹ እና በከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የተወካዮች መረጣ ሒደቶችን ባከናወነበት ወቅት ሒደቱ ግልጽነት ያለው እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲሄድ ማድረጉ ለምክክሩ ተዓማኒነት የራሱን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የትውልድ አደራ እና የጠንካራ ሀገር ግንባታ መሠረት ሲሆን፣ የዚህ ጉባኤ ስኬት የሚወሰነውም በኮሚሽኑ ጥረት ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዳችን በጎ ፈቃድ፣ አዳምጦ የመረዳት ባህል እና ለሀገራዊ አንድነት በምናሳየው ቁርጠኝነት ነው።
ውጤታማ ምክክር ያደረጉ ሀገራት ከቀውስ ወጥተው ወደ ብልጽግና እንደተሸጋገሩ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በዚሁ መንገድ በሰላም፣ በእኩልነት እና በብልጽግና ላይ የተመሠረተች ሀገር ሆና እንደምትቀጥል እምነታችን የጸና ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dialogue
*********************
ኢትዮጵያ በታሪኳ ትልቅ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ሀገራችንን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ ልዩነቶችን በሠለጠነ መንገድ ለመፍታት እና በዋና ዋና ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የዚህ ዘመን ትልቁ ታሪካዊ ክስተት ነው።
እንደ ሀገር የገጠሙንን ዘመናት የተሻገሩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ውጥንቅጦችን በዘላቂነት ለመፍታት ከግጭት ይልቅ ውይይትን፣ ከመግፋት ይልቅ አሳታፊነትን ማስቀደም ብቸኛው ዘላቂ መንገድ መሆኑ ግልጽ እውነታ ሆኗል።
የሀገራዊ ምክክሩ ዋነኛ ዓላማ በሕዝቦች መካከል ለዘመናት የዘለቁ እና መፍትሔ ያላገኙ መዋቅራዊ እና ፖለቲካዊ ልዩነቶችን ማጥበብ ነው። ሕዝቡ በነጻነት አስተያየቱን እንዲሰጥ በማድረግ የጋራ እሴቶችን መቅረጽ እንዲሁም ሀገራዊ አንድነትን እና ብዝኃነትን ያጣጣመ የጋራ የወደፊት ራዕይ በመቅረጽ የወል ትርክትን መገንባት ነው።
ይህንን የምክክር ሒደት ልዩ የሚያደርገው ከላይ ወደ ታች የሚወርድ ውሳኔ ሳይሆን፣ ከታች ወደ ላይ የኅብረተሰቡን ድምፅ የሚሰበስብ መሆኑ ነው። እውነተኛ ሀገር ግንባታ የሚጀምረውም የእያንዳንዱ ዜጋ ድምፅ እኩል ዋጋ አግኝቶ ሲደመጥ ብቻ ነው።
የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሃይማኖት አባቶች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማኅበራት በተወካዮቻቸው አማካኝነት የአጀንዳ ግብዓት ማቅረባቸው የሒደቱን ተቀባይነት እና ሕጋዊነት በማጎልበት አሳታፊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በየክልሎቹ እና በከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የተወካዮች መረጣ ሒደቶችን ባከናወነበት ወቅት ሒደቱ ግልጽነት ያለው እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲሄድ ማድረጉ ለምክክሩ ተዓማኒነት የራሱን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የትውልድ አደራ እና የጠንካራ ሀገር ግንባታ መሠረት ሲሆን፣ የዚህ ጉባኤ ስኬት የሚወሰነውም በኮሚሽኑ ጥረት ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዳችን በጎ ፈቃድ፣ አዳምጦ የመረዳት ባህል እና ለሀገራዊ አንድነት በምናሳየው ቁርጠኝነት ነው።
ውጤታማ ምክክር ያደረጉ ሀገራት ከቀውስ ወጥተው ወደ ብልጽግና እንደተሸጋገሩ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በዚሁ መንገድ በሰላም፣ በእኩልነት እና በብልጽግና ላይ የተመሠረተች ሀገር ሆና እንደምትቀጥል እምነታችን የጸና ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dialogue
5 days ago
በሰሜን ኸዋ ሀገረ ስብከት በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ድንገት በተከሰተ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በ5 ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ሀገረ ስብከቱ አስታወቀ ።
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በታላቋ ገዳም ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ገዳም ከክረምቱ መግባት ጋር ተያይዞ በተከሰተው ከፍተኛ የዝናብና የመባርቅት ድምፅ በደረሰ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት ለጸበል ፣ ለሱባኤና ለመሳለም ከአራቱም አቅጣጫ በተሰበሰቡ በጻድቃኔ ማርያም ልጆችና ወዳጆች ላይ የደረሰው ድንገተኛ አደጋ እጅግ አስደንጋጭና ልብ ሰባሪ ኃዘን መኾኑ ተገልጧል።
በዚህ ድንገተኛ አደጋም የ14 ወገኖቻችን ሕይወት ሲያልፍ በ5 ወገኖቻችን ላይ ከፍተኛና በ2 ወገኖች ላይ መለስተኛ ጉዳት መድረሱም ተመላክቷል።
የሀገረ ስብከቱ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ በስፍራው በመገኘት ለሞቱ ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት ለተጎዱት ጸሎት ላዘኑ ወገኖቻችን የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ።
© የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት አቡቀለምሲስ ሚዲያ
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በታላቋ ገዳም ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ገዳም ከክረምቱ መግባት ጋር ተያይዞ በተከሰተው ከፍተኛ የዝናብና የመባርቅት ድምፅ በደረሰ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት ለጸበል ፣ ለሱባኤና ለመሳለም ከአራቱም አቅጣጫ በተሰበሰቡ በጻድቃኔ ማርያም ልጆችና ወዳጆች ላይ የደረሰው ድንገተኛ አደጋ እጅግ አስደንጋጭና ልብ ሰባሪ ኃዘን መኾኑ ተገልጧል።
በዚህ ድንገተኛ አደጋም የ14 ወገኖቻችን ሕይወት ሲያልፍ በ5 ወገኖቻችን ላይ ከፍተኛና በ2 ወገኖች ላይ መለስተኛ ጉዳት መድረሱም ተመላክቷል።
የሀገረ ስብከቱ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ በስፍራው በመገኘት ለሞቱ ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት ለተጎዱት ጸሎት ላዘኑ ወገኖቻችን የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ።
© የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት አቡቀለምሲስ ሚዲያ
6 days ago
ከባንኮክ እስከ ፉኬትና ፓታያ ( በወፍ በረር ... )
* ታይላንድ በዓይኔ ያየኋት፣ በእጄ የነካኋት፣ በልቤ የቀረች የባሕር ነፍስ…!
በገብረማርያም ይርጋ [ የጉዞ ማስታወሻ ]
#ethiopia | እውነተኛ ጉዞ የሚጀምረው ሰው ከራሱ ጋር ሲገናኝ ነው። እውነተኛ ጉዞ አውሮፕላኑ ሲያርፍ አያበቃም፤ ትዝታ በልብ ውስጥ ሲቀጥል እንጂ።
ዓለም አቀፍ የባህልና ጥበባት ልማት ሙያዊ ሽልማቴን ለመቀበል ወደ ደቡብ ምስራቅ እስያዋ እንቁ — ታይላንድ — ስጓዝ፣ አእምሮዬን የሞላው የጉዞው ዓላማ ብቻ ነበር።
ነገር ግን እግሬ የታይላንድን ምድር ሲረግጥ የተቀበለኝ የከተማዋ የሲሚንቶና የአስፋልት ግለት ወይም የዘመናዊነት ጫጫታ አልነበረም፤ ከሩቅ የባሕር ጥልቀት እየነፈሰ በፊቴ ላይ እንደ አሮጌ ወዳጅ ቀስ ብሎ የተራመደው ቀዝቃዛ የባሕር ነፋስ እንጂ።
ደቡባዊቷ እንቁ — ፉኬትና የፓታያ ሞገዶች
በውሃው ላይ የተበተኑት ባህላዊ የረጅም ጅራት (Long-tail) ጀልባዎች፣ የፀሐይ ወርቃማ ብርሃን በውሃው ላይ ሲያርፍ የሚፈጥረው ብልጭታ፣ የሰማዩና የባሕሩ አድማስ ላይ መገናኘት… እነዚህ ሁሉ ተደምረው እንደ ተአምራዊ ሕልም ይታዩ ነበር። በዚያ ቅጽበት እኔ ባሕሩን አልተመለከትኩትም፤ ባሕሩ እኔን በጥልቀቱ እየተመለከተኝ ነበር።
በጄትስኪ (Jet Ski) አየርና ውሃውን ሰንጥቄ ስነጥቅ፣ የነጭ አረፋ መስመር ከኋላዬ እንደ ግጥም ይሰመር ነበር። በወቅቱ የተረዳሁት ነገር ቢኖር—ፍጥነት ሰውን ከምድር አያርቀውም፤ ይልቁንም በውስጡ የተሸሸገውን እውነተኛ ደስታ ቅርብ ያደርገዋል!
የሰማይ ላይ በረራ (Parasailing)፦ገመዱ ተለቆ ሰማይ ሲከፈትልኝ፣ ከላይ ሆኜ ስመለከት ባሕሩ እንደ ታላቅ ሰማያዊ መስታወት ተንጣሎ ታየኝ።
በዚያ ከፍታ ላይ ዓለም ትንሽ ስትሆን፣ ሰውን የሚያስጨንቀው የዕለት ተዕለት ጭነቷም አብሮ ትንሽ ይሆናል። እንደ ልጅ ሆኜ የነፋሱን ሹክሹክታ ብቻ እሰማ ነበር… ወጣሁ፣ ተነጠቅሁ!
በፉኬት ነጭ አሸዋው በእግር ስር ሲለሰልስ፣ ግልጽና ሰማያዊው ውሃ እስከ ጉልበት ሲደርስ፣ ፀሐይ በቆዳ ላይ ወርቃማ ሙቀቷን ስትረጭ ዓለምና ጭንቋ ሙሉ በሙሉ የተረሱ ይመስላሉ።
የባንኮክ ድቅቅ ያለ ውበትና የሌሊት ከዋክብት
ባንኮክ በቀን በገዥና ሻጭ፣ በበዛ እንቅስቃሴና ህይወት ስትደምቅ፤ ሌሊት ደግሞ በምድር ላይ እንደወረዱ ከዋክብት የሚያበሩ መብራቶች ያሏት አስማተኛ ከተማ ትሆናለች። የከተማዋ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች መብራት በውሃው ላይ ሲሰበር፣ ወርቅና አልማዝ በውሃ ላይ የተበተነ ይመስላል።
በቻኦ ፕራያ (Chao Phraya) ወንዝ ላይ ያለ ምሽት
ከጉዞዬ ሁሉ በላይ በልቤ የተቀረፀው በመርከብ ላይ ያሳለፍኩት ምሽት ነው።
የምስራቃዊው የሙዚቃ ዜማ፣ የሰዎች ወዳጃዊ ሳቅ፣ ጣፋጭ እራት…
በወንዙ ላይ እያለፈች ባለው መርከብ ላይ ሆነን በከተማዋ መብራቶች መካከል ስንሳፈፍ፣ በአንድ ቅጽበት ውስጥ ዓለም በሙሉ የተሰበሰበች ያህል ተሰማኝ።
በዚያ ምሽት አንድ ታላቅ እውነት ተረዳሁ—ደስታ ታላቅና ውስብስብ ነገር አይፈልግም፤ በሙሉ ልብ የሚኖር አንድ ቅጽበት ብቻ ይበቃዋል።
በሻንጣ ያልተያዘ፣ በልብ የተያዘ ሀብት
ታይላንድ ከዚህ በኋላ ከእኔ አትጠፋም፤ በውስጤ ዘላለማዊ ቦታዋን ይዛለች። የፓታያ ነፋስ አሁንም በፊቴ ላይ ይነፍሳል፣ የፉኬት ሞገድ በልቤ ይመታል፣ የባንኮክ የሌሊት መብራት በዓይኔ ላይ ይበራል።
ከዚህ ጉዞ ስመለስ በሻንጣዬ ውስጥ ያሸግኩት ያበደሩኝን ልብስ ብቻ አይደለም፤
የሞገዱን ዘላለማዊ ድምፅ፣ ...
የፀሐይዋን አፍቃሪ ሙቀት፣ ...
የአሸዋውን ልስላሴ፣ ...
የሌሊት መብራቶቿን ብሩህነት፣ ...
እና ...
የልቤን ሙሉ ደስታ ነው።
እውነተኛ ጉዞ አውሮፕላኑ ሲያርፍ አይጨርስም፤ ትዝታው በልባችን ውስጥ መኖር ሲቀጥል እንጂ!
ታይላንድ በዓይኔ ያየኋት፣ በእጄ የነካኋት፣ በልቤ የቀረች የባሕር ነፍስ…!
Sponsored by
Surafel
7 days ago
በቅንነትና በትጋት ለሚያገለግል አመራር ህዝቡ ጠንካራ ጋሻና ደጋፊ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
***************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡ ድንቅ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በማረጋገጥ፣ በቀጣዮቹ ዓመታት የሚጠበቁት የኢኮኖሚና የፖለቲካ እመርታዎች ለአመራሩ እንቅልፍ የሚነሱ ከባድ ኃላፊነቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የህዝብ አደራ ከምረጡኝ ዘመቻው በላይ እጅግ የሚከብድ መሆኑን በንግግራቸው አጽንዖት ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ህዝብ አደራ ሲሰጥ የጥይት ድምፅ፣ ግርግርና ማስፈራራት እንዳላገደው ሁሉ፤ ይህ አደራ በአግባቡ ካልተያዘ ህዝቡ መብቱን ለማስከበር ወደኋላ እንደማይል አስገንዝበዋል።
አመራሩ በታመነበት ልክ በቅንነትና በትጋት ሲመላለስ ህዝቡ እንደሚጠብቀው፣ እንደሚከላከልለት እና ለስኬቱም ጠንካራ ጋሻና ደጋፊ እንደሚሆነው አብራርተዋል።
በተቃራኒው ግን አመራሩ አደራውን ሲያጎድልና ከህዝብ ፍላጎት ሲያፈነግጥ የሰጠውን አደራ የመንጠቅና መብቱን የማስከበር ሙሉ አቅምና ታሪክ እንዳለው በግልጽ አመልክተዋል።
በቀጣዮቹ ዓመታት በሀገሪቱ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ዘርፍ የሚፈለገውን ትልቅ እመርታ ለማምጣት መንግስት በከፍተኛ ቁርጠኝነት እንደሚሰራ እና ህዝቡ የጣለበትን ከባድ አደራ ለመወጣት ሌት ተቀን እንደሚተጋ አረጋግጠዋል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#ethiopia #leadership #publictrust #abiyahmed #politics
***************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡ ድንቅ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በማረጋገጥ፣ በቀጣዮቹ ዓመታት የሚጠበቁት የኢኮኖሚና የፖለቲካ እመርታዎች ለአመራሩ እንቅልፍ የሚነሱ ከባድ ኃላፊነቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የህዝብ አደራ ከምረጡኝ ዘመቻው በላይ እጅግ የሚከብድ መሆኑን በንግግራቸው አጽንዖት ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ህዝብ አደራ ሲሰጥ የጥይት ድምፅ፣ ግርግርና ማስፈራራት እንዳላገደው ሁሉ፤ ይህ አደራ በአግባቡ ካልተያዘ ህዝቡ መብቱን ለማስከበር ወደኋላ እንደማይል አስገንዝበዋል።
አመራሩ በታመነበት ልክ በቅንነትና በትጋት ሲመላለስ ህዝቡ እንደሚጠብቀው፣ እንደሚከላከልለት እና ለስኬቱም ጠንካራ ጋሻና ደጋፊ እንደሚሆነው አብራርተዋል።
በተቃራኒው ግን አመራሩ አደራውን ሲያጎድልና ከህዝብ ፍላጎት ሲያፈነግጥ የሰጠውን አደራ የመንጠቅና መብቱን የማስከበር ሙሉ አቅምና ታሪክ እንዳለው በግልጽ አመልክተዋል።
በቀጣዮቹ ዓመታት በሀገሪቱ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ዘርፍ የሚፈለገውን ትልቅ እመርታ ለማምጣት መንግስት በከፍተኛ ቁርጠኝነት እንደሚሰራ እና ህዝቡ የጣለበትን ከባድ አደራ ለመወጣት ሌት ተቀን እንደሚተጋ አረጋግጠዋል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#ethiopia #leadership #publictrust #abiyahmed #politics
7 days ago
ከታች ያለው የአርሚ 70 አባል የፃፈው ነው!
ሸረሪና! አርሚ 70!
"አንድ የአርሚ 70 አባል የሆነ የቤተሰቤ አባል ከሱዳን ወሰን ሸረሪና አካባቢ ደውሎልኝ ነበር።
ዛሬ ማታ ሑመራ እንገባለን፤ ተዘጋጁ የሚል ትዕዛዝ ወርዶልናል።
ሙሉ ሌሊት ስንጓዝ አድረናል። ሲነጋ አካባቢ የመጣበት ቦታ የማይታወቅ፣ ከሰማይ ሲወርድ ምንም ድምፅ የሌለውና መሬት ላይ ሲያርፍ ብቻ ድምፅ የሚያሰማ ተኩስ ይፈነዳ ጀመር። ሩቅ ሆነን ስናያቸው የነበሩ የመካናይዝድ ተሽከርካሪዎች በሙሉ ማለት ይቻላል ተቃጥለው እሳት ሲነድ ብቻ ይታያል።
እግረኛ የሆንነው ደግሞ የመካናይዝድ ተሽከርካሪዎች እየጠፋ እንደሆነ ስለተረዳን ሁላችንም ተበታትነናል። ከእኛ ጋር አንድ የሬዲዮ ኦፕሬተር እና የሬዲዮ መገናኛ የያዘ አለ፤ ነገር ግን ከኃላፊዎች የደረሳቸው ምንም ዓይነት መረጃ የለም።
ለኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል እጃችንን እንዳንሰጥ በፊታችን የሚታይ ሠራዊት የለም። ጨንቆናል!
እኔም የምናገረው ጠፍቶኛል!!
የህወሓት ቡድን አፈቀላጤዎች ስራችሁን ስለጀመራችሁ እንኳን ደስ አላችሁ።
via wedi shambel
Seledadotio
Seledadotio
ሸረሪና! አርሚ 70!
"አንድ የአርሚ 70 አባል የሆነ የቤተሰቤ አባል ከሱዳን ወሰን ሸረሪና አካባቢ ደውሎልኝ ነበር።
ዛሬ ማታ ሑመራ እንገባለን፤ ተዘጋጁ የሚል ትዕዛዝ ወርዶልናል።
ሙሉ ሌሊት ስንጓዝ አድረናል። ሲነጋ አካባቢ የመጣበት ቦታ የማይታወቅ፣ ከሰማይ ሲወርድ ምንም ድምፅ የሌለውና መሬት ላይ ሲያርፍ ብቻ ድምፅ የሚያሰማ ተኩስ ይፈነዳ ጀመር። ሩቅ ሆነን ስናያቸው የነበሩ የመካናይዝድ ተሽከርካሪዎች በሙሉ ማለት ይቻላል ተቃጥለው እሳት ሲነድ ብቻ ይታያል።
እግረኛ የሆንነው ደግሞ የመካናይዝድ ተሽከርካሪዎች እየጠፋ እንደሆነ ስለተረዳን ሁላችንም ተበታትነናል። ከእኛ ጋር አንድ የሬዲዮ ኦፕሬተር እና የሬዲዮ መገናኛ የያዘ አለ፤ ነገር ግን ከኃላፊዎች የደረሳቸው ምንም ዓይነት መረጃ የለም።
ለኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል እጃችንን እንዳንሰጥ በፊታችን የሚታይ ሠራዊት የለም። ጨንቆናል!
እኔም የምናገረው ጠፍቶኛል!!
የህወሓት ቡድን አፈቀላጤዎች ስራችሁን ስለጀመራችሁ እንኳን ደስ አላችሁ።
via wedi shambel
Seledadotio
Seledadotio
7 days ago
የጥቃቱ መነሻ‼️
👉 የጥቃቱ መነሻና ቦታ፡ አካባቢውን በኃይል ለመቆጣጠር በማሰብ፣ በሱዳን በኩል የተደራጁ የ'ሳምሪ' ታጣቂ ኃይሎች ዛሬ ጠዋት በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ላይ ወታደራዊ ጥቃት ከፍተዋል። ታጣቂዎቹ ጦርነቱን የጀመሩት በሱዳን ድንበር በኩል በ'ሸረሪና' እና በወልቃይት ጠገዴ ዞን፣ ቃብትያ ሁመራ ወረዳ ስር በምትተዳደረው የበረከት ከተማ አቅጣጫ ድንበር ጥሰው በመግባት ነው።
👉 የሜዳ ላይ ውጊያ ሁኔታ፡ በበረከት ከተማ እና በሸረሪና አቅጣጫ ጥቃቱን የጀመሩት ከሱዳን ሰርጎ የገቡት ታጣቂዎች ('አርሚ 70' ላይ) በቀላል መሳሪያዎች ትንኮሳ የከፈቱ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መጠነ ሰፊ የአፀፋ እርምጃ መውሰድ ጀምሯል።
👉 በድሮንና በመድፍ የታገዘ አፀፋ፡ አሁን ላይ ከሁመራ ወደ በረከት ከተማ እና ሸረሪና አቅጣጫ ከፍተኛ የሆነ የመድፍ ድብደባ እየተካሄደ ሲሆን፣ በሰማይ ላይም የድሮን እንቅስቃሴ በግልፅ እየታየ ነው። የከባድ መሳሪያው (መድፍ) ተኩስ እጅግ ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ርቀት ላይ በምትገኘው ሁመራ ከተማ ውስጥ ያሉ መኖሪያ ቤቶችን በከፍተኛ ሁኔታ እያነዘረ እንደሚገኝ ነዋሪዎች አረጋግጠዋል።
👉 የመከላከያ ሠራዊት እርምጃ፡ በበረከት እና ሸረሪና አቅጣጫ የተጀመረውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ በአካባቢው ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረት ያንዣበበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተከፈተበትን ይህንን ጥቃት ሙሉ በሙሉ ለመመከት እና ለመደምሰስ በከፍተኛ ዝግጅት ላይ መሆኑን ከስፍራው የወጡ መረጃዎች አረጋግጠዋል።
👉በድምፅ አልባ መሳሪያ (መሬት ላይ ሲደርስ ብቻ የሚፈነዳ መሳሪያ) በርካታ የአርሚ 70 ታጣቂዎች ላይ ጉዳት ማድረሱን ምንጮች ጠቁመዋል።
👉ታጣቂዎቹ ዛሬ ሁመራን ለመያዝ እቅድ እንደሰጣቸው ገልፀዋል።
👉ህወሓት በበኩሉ የፌደራል መንግስቱ ከበባ ሲፈፅም ከርሞ ዛሬ ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም በምዕራብ ትግራይ ተኩስ ከፍቶብናል ሲል መግለጫ አውጥቷል።
Seledadotio
Seledadotio
👉 የጥቃቱ መነሻና ቦታ፡ አካባቢውን በኃይል ለመቆጣጠር በማሰብ፣ በሱዳን በኩል የተደራጁ የ'ሳምሪ' ታጣቂ ኃይሎች ዛሬ ጠዋት በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ላይ ወታደራዊ ጥቃት ከፍተዋል። ታጣቂዎቹ ጦርነቱን የጀመሩት በሱዳን ድንበር በኩል በ'ሸረሪና' እና በወልቃይት ጠገዴ ዞን፣ ቃብትያ ሁመራ ወረዳ ስር በምትተዳደረው የበረከት ከተማ አቅጣጫ ድንበር ጥሰው በመግባት ነው።
👉 የሜዳ ላይ ውጊያ ሁኔታ፡ በበረከት ከተማ እና በሸረሪና አቅጣጫ ጥቃቱን የጀመሩት ከሱዳን ሰርጎ የገቡት ታጣቂዎች ('አርሚ 70' ላይ) በቀላል መሳሪያዎች ትንኮሳ የከፈቱ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መጠነ ሰፊ የአፀፋ እርምጃ መውሰድ ጀምሯል።
👉 በድሮንና በመድፍ የታገዘ አፀፋ፡ አሁን ላይ ከሁመራ ወደ በረከት ከተማ እና ሸረሪና አቅጣጫ ከፍተኛ የሆነ የመድፍ ድብደባ እየተካሄደ ሲሆን፣ በሰማይ ላይም የድሮን እንቅስቃሴ በግልፅ እየታየ ነው። የከባድ መሳሪያው (መድፍ) ተኩስ እጅግ ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ርቀት ላይ በምትገኘው ሁመራ ከተማ ውስጥ ያሉ መኖሪያ ቤቶችን በከፍተኛ ሁኔታ እያነዘረ እንደሚገኝ ነዋሪዎች አረጋግጠዋል።
👉 የመከላከያ ሠራዊት እርምጃ፡ በበረከት እና ሸረሪና አቅጣጫ የተጀመረውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ በአካባቢው ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረት ያንዣበበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተከፈተበትን ይህንን ጥቃት ሙሉ በሙሉ ለመመከት እና ለመደምሰስ በከፍተኛ ዝግጅት ላይ መሆኑን ከስፍራው የወጡ መረጃዎች አረጋግጠዋል።
👉በድምፅ አልባ መሳሪያ (መሬት ላይ ሲደርስ ብቻ የሚፈነዳ መሳሪያ) በርካታ የአርሚ 70 ታጣቂዎች ላይ ጉዳት ማድረሱን ምንጮች ጠቁመዋል።
👉ታጣቂዎቹ ዛሬ ሁመራን ለመያዝ እቅድ እንደሰጣቸው ገልፀዋል።
👉ህወሓት በበኩሉ የፌደራል መንግስቱ ከበባ ሲፈፅም ከርሞ ዛሬ ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም በምዕራብ ትግራይ ተኩስ ከፍቶብናል ሲል መግለጫ አውጥቷል።
Seledadotio
Seledadotio
7 days ago
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች፤ የሀገራዊ ምክክር ታሪካዊ ምዕራፍ
***************
የግጭትን መንገድ ትቶ ወደ ሰላማዊ ውይይት በመምጣት በአንድ መድረክ ላይ በእጃቸው መሳሪያ ሳይሆን ብዕርን በመያዝ ሀሳባቸውን ለማስፈር መላው ኢትዮጵያውያን ተገናኝተዋል።
የሀገር ግንባታ መሠረቱ የሚጠነክረው በግጭት ሳይሆን በመደማመጥ፣ እንዲሁም በጋራ በሚገነባ የሀሳብ ራዕይ መሆኑን በማስረፅ።
በዚህ እሳቤ መሠረት ነው የሀገራዊ ምክክር ሂደት "የሁሉም ሀሳብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል" በሚል መርህ የሁሉንም ድምፅ ለማዳመጥ በር የከፈተው።
ሀገራዊ ምክክር ዓላማው ልክ እንደ ውድድር አሸናፊና ተሸናፊ መለየት ሳይሆን በሕዝቦች ዘንድ የተወከሉ ተወካዮች ተጠናክረው የጋራ መፍትሔ በመፈለግ በሁሉም ውስጥ ኢትዮጵያን አሸናፊ ማድረግ ነው።
ለዚህም ዋና ማሳያ የሆነው ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች በስምንት ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ከመላው ኢትዮጵያ የተወከሉ በቡድን ተከፋፍለው እየተወያዩ ይገኛሉ።
ዓመታትን በትጥቅ ትግል ያሳለፉ ተመካካሪዎች ዛሬ መሣሪያን አስቀምጠው ብዕር በመያዝ ሐሳባቸውን በውይይት እያቀረቡ ይገኛሉ፤ ይህ የሚጠቁመው ምልክት የጦርነትን ኃይል ሳይሆን በመመካከር ችግሮች ሊፈቱ እንደሚችሉ የሚያሳይ ተስፋ ሰጪ ምልክት እና የሰላም መንገድ ለሁሉም ክፍት መሆኑን ያረጋግጣል።
ተመካካሪዎቹ ከ250 አባላት ወደ 50 አባላት፣ በመጨረሻም ወደ 10 አባላት በመከፋፈል ሁሉም ተመካካሪ ያመጣውን የማኅበረሰብ ጥያቄና ሐሳብ ያለ ግፊት፣ ያለ ፍርሃት እና ያለ ተፅዕኖ በነፃነት እንዲያቀርብ ዕድል ተፈጥሮለታል።
ልዩነታቸው ውበታቸው የሆነው የኢትዮጵያውያን ሐሳቦች ሲገናኙ፣ ልዩነቶች ሲከበሩ እና ሁሉም ድምፅ የመደመጥ ዕድል ሲያገኝ፣ የነገዋ ኢትዮጵያ በተስፋ እና በመተማመን የተመሠረተች ትሆናለች። ለዘመናት የቆዩ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የሰላም ባህልን ማጠናከር የዚህ ሂደት ትልቁ ስኬት ነው።
በዚህ መድረክ ላይ የሚጻፉት ቃላት በወረቀት ላይ ብቻ አይቀሩም፤ ወደ ታሪክ በመሻገር ከአዳራሹ አልፈው የቀጣዮቹን ትውልዶች ሊመሩ የሚችሉ እና ተስፋን፣ ይቅርታን፣ የጋራ ራዕይን የሚተክሉ ናቸው።
በዚህም ሀገር የምትገነባው በዜጎቿ የተረጋጋ ውይይት በመሆኑ ወደ ምክክር መምጣት የድክመት ምልክት ሳይሆን የብስለት፣ የኃላፊነት እና የጋራ የወደፊት ዕጣ ፈንታን በሰላማዊ መንገድ ለመወሰን የተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ነው።
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች የሚጽፉት የአንድ ቡድን ታሪክ አይደለም፤ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ የወደፊት ምዕራፍን ነው።
በልዩ እሸቱ
#nationaldialogue #peacebuilding #futureethiopia #inclusion #unityindiversity #reconciliation
***************
የግጭትን መንገድ ትቶ ወደ ሰላማዊ ውይይት በመምጣት በአንድ መድረክ ላይ በእጃቸው መሳሪያ ሳይሆን ብዕርን በመያዝ ሀሳባቸውን ለማስፈር መላው ኢትዮጵያውያን ተገናኝተዋል።
የሀገር ግንባታ መሠረቱ የሚጠነክረው በግጭት ሳይሆን በመደማመጥ፣ እንዲሁም በጋራ በሚገነባ የሀሳብ ራዕይ መሆኑን በማስረፅ።
በዚህ እሳቤ መሠረት ነው የሀገራዊ ምክክር ሂደት "የሁሉም ሀሳብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል" በሚል መርህ የሁሉንም ድምፅ ለማዳመጥ በር የከፈተው።
ሀገራዊ ምክክር ዓላማው ልክ እንደ ውድድር አሸናፊና ተሸናፊ መለየት ሳይሆን በሕዝቦች ዘንድ የተወከሉ ተወካዮች ተጠናክረው የጋራ መፍትሔ በመፈለግ በሁሉም ውስጥ ኢትዮጵያን አሸናፊ ማድረግ ነው።
ለዚህም ዋና ማሳያ የሆነው ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች በስምንት ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ከመላው ኢትዮጵያ የተወከሉ በቡድን ተከፋፍለው እየተወያዩ ይገኛሉ።
ዓመታትን በትጥቅ ትግል ያሳለፉ ተመካካሪዎች ዛሬ መሣሪያን አስቀምጠው ብዕር በመያዝ ሐሳባቸውን በውይይት እያቀረቡ ይገኛሉ፤ ይህ የሚጠቁመው ምልክት የጦርነትን ኃይል ሳይሆን በመመካከር ችግሮች ሊፈቱ እንደሚችሉ የሚያሳይ ተስፋ ሰጪ ምልክት እና የሰላም መንገድ ለሁሉም ክፍት መሆኑን ያረጋግጣል።
ተመካካሪዎቹ ከ250 አባላት ወደ 50 አባላት፣ በመጨረሻም ወደ 10 አባላት በመከፋፈል ሁሉም ተመካካሪ ያመጣውን የማኅበረሰብ ጥያቄና ሐሳብ ያለ ግፊት፣ ያለ ፍርሃት እና ያለ ተፅዕኖ በነፃነት እንዲያቀርብ ዕድል ተፈጥሮለታል።
ልዩነታቸው ውበታቸው የሆነው የኢትዮጵያውያን ሐሳቦች ሲገናኙ፣ ልዩነቶች ሲከበሩ እና ሁሉም ድምፅ የመደመጥ ዕድል ሲያገኝ፣ የነገዋ ኢትዮጵያ በተስፋ እና በመተማመን የተመሠረተች ትሆናለች። ለዘመናት የቆዩ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የሰላም ባህልን ማጠናከር የዚህ ሂደት ትልቁ ስኬት ነው።
በዚህ መድረክ ላይ የሚጻፉት ቃላት በወረቀት ላይ ብቻ አይቀሩም፤ ወደ ታሪክ በመሻገር ከአዳራሹ አልፈው የቀጣዮቹን ትውልዶች ሊመሩ የሚችሉ እና ተስፋን፣ ይቅርታን፣ የጋራ ራዕይን የሚተክሉ ናቸው።
በዚህም ሀገር የምትገነባው በዜጎቿ የተረጋጋ ውይይት በመሆኑ ወደ ምክክር መምጣት የድክመት ምልክት ሳይሆን የብስለት፣ የኃላፊነት እና የጋራ የወደፊት ዕጣ ፈንታን በሰላማዊ መንገድ ለመወሰን የተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ነው።
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች የሚጽፉት የአንድ ቡድን ታሪክ አይደለም፤ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ የወደፊት ምዕራፍን ነው።
በልዩ እሸቱ
#nationaldialogue #peacebuilding #futureethiopia #inclusion #unityindiversity #reconciliation
7 days ago
«ከለውጡ በኋላ የነበረውን የመታፈን ስሜት ለማናፈስ በተደረገው ጥረት ውስጥ የተቀላቀሉ ቢምቢዎች ነበሩ»- ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ2010 ዓ.ም. የለውጥ ጉዞንና ከዚያ በኋላ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የታዩትን ኩነቶች አስመልክተው ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በሰጡት ማብራሪያ፣ የዐማራ ሕዝብ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ሕዝብ ለለውጥና ለዕድገት ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጉን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ከለውጡ ማግሥት የነበረው ጉዞ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ተስፋ የተሞላበት፣ «በዚህ ለውጥ እሠራለሁ፣ አተርፋለሁ፣ ሀገር አጠናለሁ» የሚል ሕልም በሰፊው የተገለጸበት ወቅት ነበር። ከለውጡ በፊት በነበረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት ውስጥ የመዘጋትና የመታፈን ምልክቶች እንደነበሩ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የተዘጋን ቤት መስኮት ከፍቶ እንደማናፈስ ሁሉ ፖለቲካውንም ማናፈስ አስፈላጊ ነበር ብለዋል።
ሆኖም መስኮቶች ሲከፈቱ ንጹሕ አየር ብቻ ሳይሆን «ቢምቢዎችና ትንኞችም» አብረው እንደሚገቡ በመግለጽ፣ በፖለቲካው ምህዳር መከፈት ምክንያት አጋጣሚውን በመጠቀም ሁኔታዎችን ወደ ሥጋትና ድንግዝግዝነት ለመቀየር የሞከሩ አካላት እንደነበሩ አስረድተዋል።
«ቢምቢ በሳይዟ በጣም ትንሽ ናት፤ ነገር ግን ድምፅ በማሰማት እንዳትተኛ ታውክሃለች። ሁለተኛውና ከዚያ የሚከፋው ደግሞ በመንደፍ ደምን መምጠጧና በሽታ ማምጣቷ ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዓውድ ውስጥም ከፍተኛ ድምፅ በማሰማት ለማወክ የሚሞክሩ፣ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማደናቀፍና ህልውናዋን ለመገዳደር ከሚፈልጉ ኃይሎች ጋር እስከመሰለፍ የሄዱ አካላት ነበሩ።»
በወቅቱ በተፈጠሩት ነገሮች ምክንያት በሕዝቡ ዘንድ ምንድን ነው የመጣብን ሥጋት ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ ነገሮች እያዋሉ እያደሩ ሲመጡ ግን የ«መደመር» መንገድ ብቸኛው አማራጭ መሆኑንና ለመበልጸግ የሚደረገው ጥረት ተገቢ መሆኑን ሕዝቡ ማመኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም፣ ሕዝቡ ይህንን እምነቱን በምርጫ ማረጋገጡን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ብቸኛው ኢትዮጵያን የማጽኛ መንገድ ታሪካዊውን ውህደትና እህትነት በሚያርቅ፣ በሚያድስና በሚያሰፋ መንገድ መሄድ፣ ተከባብሮና ተዋዶ በጋራ በመስራት ሀገርን ማጽናት ብቻ መሆኑን አብራርተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ2010 ዓ.ም. የለውጥ ጉዞንና ከዚያ በኋላ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የታዩትን ኩነቶች አስመልክተው ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በሰጡት ማብራሪያ፣ የዐማራ ሕዝብ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ሕዝብ ለለውጥና ለዕድገት ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጉን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ከለውጡ ማግሥት የነበረው ጉዞ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ተስፋ የተሞላበት፣ «በዚህ ለውጥ እሠራለሁ፣ አተርፋለሁ፣ ሀገር አጠናለሁ» የሚል ሕልም በሰፊው የተገለጸበት ወቅት ነበር። ከለውጡ በፊት በነበረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት ውስጥ የመዘጋትና የመታፈን ምልክቶች እንደነበሩ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የተዘጋን ቤት መስኮት ከፍቶ እንደማናፈስ ሁሉ ፖለቲካውንም ማናፈስ አስፈላጊ ነበር ብለዋል።
ሆኖም መስኮቶች ሲከፈቱ ንጹሕ አየር ብቻ ሳይሆን «ቢምቢዎችና ትንኞችም» አብረው እንደሚገቡ በመግለጽ፣ በፖለቲካው ምህዳር መከፈት ምክንያት አጋጣሚውን በመጠቀም ሁኔታዎችን ወደ ሥጋትና ድንግዝግዝነት ለመቀየር የሞከሩ አካላት እንደነበሩ አስረድተዋል።
«ቢምቢ በሳይዟ በጣም ትንሽ ናት፤ ነገር ግን ድምፅ በማሰማት እንዳትተኛ ታውክሃለች። ሁለተኛውና ከዚያ የሚከፋው ደግሞ በመንደፍ ደምን መምጠጧና በሽታ ማምጣቷ ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዓውድ ውስጥም ከፍተኛ ድምፅ በማሰማት ለማወክ የሚሞክሩ፣ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማደናቀፍና ህልውናዋን ለመገዳደር ከሚፈልጉ ኃይሎች ጋር እስከመሰለፍ የሄዱ አካላት ነበሩ።»
በወቅቱ በተፈጠሩት ነገሮች ምክንያት በሕዝቡ ዘንድ ምንድን ነው የመጣብን ሥጋት ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ ነገሮች እያዋሉ እያደሩ ሲመጡ ግን የ«መደመር» መንገድ ብቸኛው አማራጭ መሆኑንና ለመበልጸግ የሚደረገው ጥረት ተገቢ መሆኑን ሕዝቡ ማመኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም፣ ሕዝቡ ይህንን እምነቱን በምርጫ ማረጋገጡን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ብቸኛው ኢትዮጵያን የማጽኛ መንገድ ታሪካዊውን ውህደትና እህትነት በሚያርቅ፣ በሚያድስና በሚያሰፋ መንገድ መሄድ፣ ተከባብሮና ተዋዶ በጋራ በመስራት ሀገርን ማጽናት ብቻ መሆኑን አብራርተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
8 days ago
በምክክር ሂደቱ የቀረቡ የአጀንዳ ምክረ ሀሳቦች በ75 በመቶ አባላት ተቀባይነት ካገኙ ከመግባባት እንደተደረሰ ጠቋሚ ነዉ የተባለለት የምክክር ምዕራፍ በመጪዉ ሰኞ ይጀመራል ተባለ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በባለፉት ሁለት ቀናት 250 ተመካካሪዎች በቡድን በመከፋፈል ዉይይት ሲያደርጉ መቆየታቸዉን ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ አሳዉቋል።
በዚህ የምክክር ምዕራፍ የተጀራጁ ምክረ ሀሳቦች 5መቶ አባላት ወዳሉት ቀርበዉ ፤ እነዚህ የ5 መቶ አባላት ተመካካሪዎች ቡድን ለውሳኔ መግባቢያ ሀሳብ ያደራጁታል ተብሏል።
እንደ ኮሚሽኑ መረጃ 5መቶ አባላት ያሏቸው ተመካካሪ ቡድኖች እያንዳንዳቸው በአንድ አጀንዳ ላይ የሚወያዩ ሲሆን፤በአጀንዳው ላይ ከመግባባት ደረሰ የሚባለው በዉይይቱ የመነጩ የመፍትሄ ሀሳቦች በ75 በመቶ አባላቱ ከመግባባት የተደረሰባቸው ወይም ተቀባይነት ያገኙ እንደሆነ ነው።
ሌላዉ የምክክሩ የውሳኔ አሰጣጥ አካል የሆነው አካሄድ ከክልል እና ከፌደራል አባላት ተመርጠዉ የሚዋቀረዉ የክልላዊ ጉባኤ ሲሆን፤በዛሬዉ ዕለት 330 ተወካዮች እንደተመረጡ ኮሚሽኑ በሰጠዉ መግለጫ ተናግሯል።
12 ክልሎች እና 2 ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የፌደራል ተቋማት ከእያንዳንዳቸው 22 ተወካዮች ተወጣጥተው የተዋቀረ ቡድን መሆኑን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ ገልፀዋል።
በዚህ ቡድን 70% ድምጽ ባለማግኘቱ ውድቅ በተደረገ የአጀንዳ የምክር ሀሳብ ላይ ቢያንስ ሶስት ክልሎች ቅሬታ ያቀረቡ እንደሆነ ያንን የሚፈቱበት አግባብ የሚኖር ነዉ ተብሏል። በቀደሙት የድምፅ አሰጣጥ ሂደቶች 70 በመቶ ድምጽ ማግኘት ሳይችል የቀረ የአጀንዳ ምክረ ሀሳብ በዚህ ቡድን በድጋሚ ታይቶ የሚጠበቀውን ዝቅተኛ የ70 በመቶ መስፈርት ካሟላ ወደ ሚቀጥለው ምዕራፍ የሚሸጋገር ይሆናል።
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በባለፉት ሁለት ቀናት 250 ተመካካሪዎች በቡድን በመከፋፈል ዉይይት ሲያደርጉ መቆየታቸዉን ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ አሳዉቋል።
በዚህ የምክክር ምዕራፍ የተጀራጁ ምክረ ሀሳቦች 5መቶ አባላት ወዳሉት ቀርበዉ ፤ እነዚህ የ5 መቶ አባላት ተመካካሪዎች ቡድን ለውሳኔ መግባቢያ ሀሳብ ያደራጁታል ተብሏል።
እንደ ኮሚሽኑ መረጃ 5መቶ አባላት ያሏቸው ተመካካሪ ቡድኖች እያንዳንዳቸው በአንድ አጀንዳ ላይ የሚወያዩ ሲሆን፤በአጀንዳው ላይ ከመግባባት ደረሰ የሚባለው በዉይይቱ የመነጩ የመፍትሄ ሀሳቦች በ75 በመቶ አባላቱ ከመግባባት የተደረሰባቸው ወይም ተቀባይነት ያገኙ እንደሆነ ነው።
ሌላዉ የምክክሩ የውሳኔ አሰጣጥ አካል የሆነው አካሄድ ከክልል እና ከፌደራል አባላት ተመርጠዉ የሚዋቀረዉ የክልላዊ ጉባኤ ሲሆን፤በዛሬዉ ዕለት 330 ተወካዮች እንደተመረጡ ኮሚሽኑ በሰጠዉ መግለጫ ተናግሯል።
12 ክልሎች እና 2 ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የፌደራል ተቋማት ከእያንዳንዳቸው 22 ተወካዮች ተወጣጥተው የተዋቀረ ቡድን መሆኑን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ ገልፀዋል።
በዚህ ቡድን 70% ድምጽ ባለማግኘቱ ውድቅ በተደረገ የአጀንዳ የምክር ሀሳብ ላይ ቢያንስ ሶስት ክልሎች ቅሬታ ያቀረቡ እንደሆነ ያንን የሚፈቱበት አግባብ የሚኖር ነዉ ተብሏል። በቀደሙት የድምፅ አሰጣጥ ሂደቶች 70 በመቶ ድምጽ ማግኘት ሳይችል የቀረ የአጀንዳ ምክረ ሀሳብ በዚህ ቡድን በድጋሚ ታይቶ የሚጠበቀውን ዝቅተኛ የ70 በመቶ መስፈርት ካሟላ ወደ ሚቀጥለው ምዕራፍ የሚሸጋገር ይሆናል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የኒውካስሉ ተወዳጅ የቀድሞ አሰልጣኝ ኬቨን ኪጋን ካረፉ ገና አስር ቀናት ብቻ ቢቆጠሩም፣ ክለቡ ሌላ ያልተጠበቀ መርዶ አስተናግዷል፦ የኪጋንን ህልም እውን በማድረግ ክለቡን ለክብር ያበቁት አሰልጣኝ ኤዲ ሃው ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ይፋ አድርገዋል።
ከእጅግ አስከፊው የ2025-26 የውድድር ዘመን በኋላ በኃላፊነታቸው ለመቀጠል እና ክለቡን መልሰው ለመገንባት ቃል ገብተው የነበሩት ኤዲ ሃው፣ አዲሱ የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ሊጀመር ሶስት ሳምንታት ብቻ ሲቀሩት ውሳኔያቸውን ቀልብሰዋል።
ማክሰኞ ምሽት በቅድመ-ውድድር ዝግጅት ኒውካስል ከብሪስቶል ሲቲ ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 4-1 በሆነ አሳፋሪ ውጤት መሸነፉ ብዙ ነገሮችን የቀየረ ይመስላል። ከሜዳቸው ውጪ ስታዲየሙን ሞልተው የነበሩት የኒውካስል ደጋፊዎች ያሰሙት የተቃውሞ እና የቁጣ ድምፅ፣ ይህ "ትርጉም አልባ" የሚመስል የወዳጅነት ጨዋታ ትልቅ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ አመላካች ነበር።
በማግስቱ ረቡዕ ጠዋት እንደተሰማው ኤዲ ሃው ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ ወስነዋል። የቅርብ ምንጮች እንደሚያሳዩት ይህ ውሳኔ የቅጽበት የብስጭት ውሳኔ ሳይሆን፣ ከከባዱ የውድድር ዘመን መገባደጃ አንስቶ አሰልጣኙ በውስጣቸው ሲያብሰለስሉት የቆዩት እና ሊሸከሙት ያልቻሉት ከባድ ሸክም ውጤት ነው።
ለኤዲ ሃው፣ ይህ ስንብት እጅግ አስደናቂ ለነበረው የኒውካስል ቆይታቸው የማይመጥን አሳዛኝ ማብቂያ ነው። ከ30 ዓመታት በፊት ኬቨን ኪጋን እጅግ ተቃርበውት የነበረውን፣ ደጋፊውም ለ70 ዓመታት ሲናፍቀው የነበረውን ትልቅ ዋንጫ ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ ያመጡት እርሳቸው ነበሩ።
እ.ኤ.አ በ2021 ክለቡ በፕሪሚየር ሊጉ 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ወደ መውረድ አፋፍ በደረሰበት ወቅት ኃላፊነቱን የተረከቡት ሃው፣ ኒውካስልን በሊጉ ማቆየት ብቻ ሳይሆን በሚቀጥለው ዓመት ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ መድረክ መልሰውታል። በ2024-25 ደግሞ በካራባኦ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ የሊጉን ሻምፒዮን ሊቨርፑልን በዌምብሌይ አሸንፈው ታሪካዊ ዋንጫ በማንሳት ስማቸውን በኒውካስል ታሪክ በወርቅ ቀለም አጽፈው ነበር።
ይህ የዋንጫ ድል የሳዑዲው የኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) በባለቤትነት ለሚያስተዳድረው እና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለሚያልመው ኒውካስል እንደ ትልቅ መነሻ መታየት ነበረበት። ሆኖም፣ የ2025ቱ ክረምት የሁሉንም ነገር አቅጣጫ ቀየረው።
በተለይም አሌክሳንደር ኢሳክን በክለቡ ለማቆየት የተደረገው ተስፋ አስቆራጭ እና መራር ትግል፣ በመጨረሻም ስዊድናዊው አጥቂ በብሪታንያ የዝውውር ሪከርድ በዝውውር መስኮቱ መዘጋጃ ዕለት ወደ ሊቨርፑል ማምራቱ ክለቡን ክፉኛ ጎድቶታል። ኒውካስል የኢሳክን ክፍተት ሊተካ የሚችል ተጫዋች ማምጣት አልቻለም። እንደ ሁጎ ኤኪቲኬ፣ ቤንጃሚን ሴስኮ እና ጆአዎ ፔድሮ ያሉ ታላላቅ ኢላማዎቹን ለተቀናቃኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሳልፎ ሰጠ።
በምትኩ ክለቡ እና ኤዲ ሃው በጋራ ያመጧቸው ኒክ ዎልቴማዴ፣ ዮአን ዊሳ እና አንቶኒ ኤላንጋ አጠቃላይ 180 ሚሊዮን ፓውንድ ($243m) ቢወጣባቸውም፣ ያሳዩት አቋም እና የገጠማቸው የጉዳት ችግር የተከፈለባቸውን ዋጋ ፈጽሞ ሊያጸድቅ አልቻለም። የኤላንጋ እና ዎልቴማዴ ብቃት ሲዋዥቅ፣ አጥቂው ዊሳ በሙሉ የውድድር ዘመኑ በሊጉ ያስቆጠረው አንድ ጎል ብቻ ነበር። በ43 ሚሊዮን ፓውንድ የመጣው ጃኮብ ራምሴይም በቁርጭምጭሚት ጉዳት ሲሰቃይ ጊዜውን አሳልፏል።
የዝውውር ውድቀቱ በሜዳ ላይ ውጤት ቢሸፈን ኖሮ የኤዲ ሃው ጫና ያን ያህል አይከፋም ነበር። ሆኖም የ2025-26 የውድድር ዘመን ለኒውካስል እውነተኛ ቅዠት ሆኖ አለፈ።
በዓመቱ መጀመሪያ ጥሩ አጀማመር ያሳየው ክለቡ፣ ከአዲሱ ዓመት በኋላ ግን የመውረድ ስጋት ወዳለባቸው ቡድኖች ወረደ። ከጥር መጨረሻ አንስቶ እስከ የውድድር ዘመኑ ማብቂያ ድረስ ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በ10ሩ በመሸነፉ፣ ከ6ኛ ደረጃ ወደ 12ኛ ደረጃ በማሽቆልቆል ደጋፊውን በሀዘን እና በቁጣ ሞላው።
ይባስ ብሎ በኤፍኤ ካፕ እና በካራባኦ ካፕ በማንችስተር ሲቲ በቀላሉ ሲሰናበት፣ በቻምፒዮንስ ሊጉ ደግሞ ባርሴሎና በድምር ውጤት 8-3 በሆነ አሳፋሪ የጎል ናዳ አዋርዶ ከውድድሩ አስወጣው።
የኤዲ ሃው የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ የገባው ገና በጊዜ ነበር። በሚያዝያ ወር ኒውካስል በተከታታይ ለሶስተኛ ጊዜ በቦርንማውዝ ከተሸነፈ በኋላ፣ የክለቡ ታሪካዊ ሌጀንድ አላን ሺረር እንዲህ ብሎ ነበር፦ "ለኤዲ ምን ያህል ከባድ ጊዜ እንደሆነ ባውቅም፣ የወደፊት እጣ ፈንታው ምን እንደሚሆን አላውቅም። ዳግም የመዋጋት እና ክለቡን የማንሳት አቅሙ ያለው አይመስለኝም። በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ኤዲ ሃው ኒውካስልን ያሰለጥናል ብዬ አላስብም።"
ሺረር እንዳለውም ሆነ ኤዲ ሃው ኒውካስልን ወደ ቀደመ ክብሩ የመመለስ ትልቅ ታሪክ ሰርተው፣ ነገር ግን በኋለኛው አመታቸው በዝውውር ውድቀት እና በሜዳ ላይ አስከፊ ውጤቶች ታጅበው የሴንት ጀምስ ፓርኩን በር ዘግተው ወጥተዋል።
ከእጅግ አስከፊው የ2025-26 የውድድር ዘመን በኋላ በኃላፊነታቸው ለመቀጠል እና ክለቡን መልሰው ለመገንባት ቃል ገብተው የነበሩት ኤዲ ሃው፣ አዲሱ የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ሊጀመር ሶስት ሳምንታት ብቻ ሲቀሩት ውሳኔያቸውን ቀልብሰዋል።
ማክሰኞ ምሽት በቅድመ-ውድድር ዝግጅት ኒውካስል ከብሪስቶል ሲቲ ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 4-1 በሆነ አሳፋሪ ውጤት መሸነፉ ብዙ ነገሮችን የቀየረ ይመስላል። ከሜዳቸው ውጪ ስታዲየሙን ሞልተው የነበሩት የኒውካስል ደጋፊዎች ያሰሙት የተቃውሞ እና የቁጣ ድምፅ፣ ይህ "ትርጉም አልባ" የሚመስል የወዳጅነት ጨዋታ ትልቅ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ አመላካች ነበር።
በማግስቱ ረቡዕ ጠዋት እንደተሰማው ኤዲ ሃው ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ ወስነዋል። የቅርብ ምንጮች እንደሚያሳዩት ይህ ውሳኔ የቅጽበት የብስጭት ውሳኔ ሳይሆን፣ ከከባዱ የውድድር ዘመን መገባደጃ አንስቶ አሰልጣኙ በውስጣቸው ሲያብሰለስሉት የቆዩት እና ሊሸከሙት ያልቻሉት ከባድ ሸክም ውጤት ነው።
ለኤዲ ሃው፣ ይህ ስንብት እጅግ አስደናቂ ለነበረው የኒውካስል ቆይታቸው የማይመጥን አሳዛኝ ማብቂያ ነው። ከ30 ዓመታት በፊት ኬቨን ኪጋን እጅግ ተቃርበውት የነበረውን፣ ደጋፊውም ለ70 ዓመታት ሲናፍቀው የነበረውን ትልቅ ዋንጫ ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ ያመጡት እርሳቸው ነበሩ።
እ.ኤ.አ በ2021 ክለቡ በፕሪሚየር ሊጉ 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ወደ መውረድ አፋፍ በደረሰበት ወቅት ኃላፊነቱን የተረከቡት ሃው፣ ኒውካስልን በሊጉ ማቆየት ብቻ ሳይሆን በሚቀጥለው ዓመት ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ መድረክ መልሰውታል። በ2024-25 ደግሞ በካራባኦ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ የሊጉን ሻምፒዮን ሊቨርፑልን በዌምብሌይ አሸንፈው ታሪካዊ ዋንጫ በማንሳት ስማቸውን በኒውካስል ታሪክ በወርቅ ቀለም አጽፈው ነበር።
ይህ የዋንጫ ድል የሳዑዲው የኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) በባለቤትነት ለሚያስተዳድረው እና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለሚያልመው ኒውካስል እንደ ትልቅ መነሻ መታየት ነበረበት። ሆኖም፣ የ2025ቱ ክረምት የሁሉንም ነገር አቅጣጫ ቀየረው።
በተለይም አሌክሳንደር ኢሳክን በክለቡ ለማቆየት የተደረገው ተስፋ አስቆራጭ እና መራር ትግል፣ በመጨረሻም ስዊድናዊው አጥቂ በብሪታንያ የዝውውር ሪከርድ በዝውውር መስኮቱ መዘጋጃ ዕለት ወደ ሊቨርፑል ማምራቱ ክለቡን ክፉኛ ጎድቶታል። ኒውካስል የኢሳክን ክፍተት ሊተካ የሚችል ተጫዋች ማምጣት አልቻለም። እንደ ሁጎ ኤኪቲኬ፣ ቤንጃሚን ሴስኮ እና ጆአዎ ፔድሮ ያሉ ታላላቅ ኢላማዎቹን ለተቀናቃኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሳልፎ ሰጠ።
በምትኩ ክለቡ እና ኤዲ ሃው በጋራ ያመጧቸው ኒክ ዎልቴማዴ፣ ዮአን ዊሳ እና አንቶኒ ኤላንጋ አጠቃላይ 180 ሚሊዮን ፓውንድ ($243m) ቢወጣባቸውም፣ ያሳዩት አቋም እና የገጠማቸው የጉዳት ችግር የተከፈለባቸውን ዋጋ ፈጽሞ ሊያጸድቅ አልቻለም። የኤላንጋ እና ዎልቴማዴ ብቃት ሲዋዥቅ፣ አጥቂው ዊሳ በሙሉ የውድድር ዘመኑ በሊጉ ያስቆጠረው አንድ ጎል ብቻ ነበር። በ43 ሚሊዮን ፓውንድ የመጣው ጃኮብ ራምሴይም በቁርጭምጭሚት ጉዳት ሲሰቃይ ጊዜውን አሳልፏል።
የዝውውር ውድቀቱ በሜዳ ላይ ውጤት ቢሸፈን ኖሮ የኤዲ ሃው ጫና ያን ያህል አይከፋም ነበር። ሆኖም የ2025-26 የውድድር ዘመን ለኒውካስል እውነተኛ ቅዠት ሆኖ አለፈ።
በዓመቱ መጀመሪያ ጥሩ አጀማመር ያሳየው ክለቡ፣ ከአዲሱ ዓመት በኋላ ግን የመውረድ ስጋት ወዳለባቸው ቡድኖች ወረደ። ከጥር መጨረሻ አንስቶ እስከ የውድድር ዘመኑ ማብቂያ ድረስ ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በ10ሩ በመሸነፉ፣ ከ6ኛ ደረጃ ወደ 12ኛ ደረጃ በማሽቆልቆል ደጋፊውን በሀዘን እና በቁጣ ሞላው።
ይባስ ብሎ በኤፍኤ ካፕ እና በካራባኦ ካፕ በማንችስተር ሲቲ በቀላሉ ሲሰናበት፣ በቻምፒዮንስ ሊጉ ደግሞ ባርሴሎና በድምር ውጤት 8-3 በሆነ አሳፋሪ የጎል ናዳ አዋርዶ ከውድድሩ አስወጣው።
የኤዲ ሃው የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ የገባው ገና በጊዜ ነበር። በሚያዝያ ወር ኒውካስል በተከታታይ ለሶስተኛ ጊዜ በቦርንማውዝ ከተሸነፈ በኋላ፣ የክለቡ ታሪካዊ ሌጀንድ አላን ሺረር እንዲህ ብሎ ነበር፦ "ለኤዲ ምን ያህል ከባድ ጊዜ እንደሆነ ባውቅም፣ የወደፊት እጣ ፈንታው ምን እንደሚሆን አላውቅም። ዳግም የመዋጋት እና ክለቡን የማንሳት አቅሙ ያለው አይመስለኝም። በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ኤዲ ሃው ኒውካስልን ያሰለጥናል ብዬ አላስብም።"
ሺረር እንዳለውም ሆነ ኤዲ ሃው ኒውካስልን ወደ ቀደመ ክብሩ የመመለስ ትልቅ ታሪክ ሰርተው፣ ነገር ግን በኋለኛው አመታቸው በዝውውር ውድቀት እና በሜዳ ላይ አስከፊ ውጤቶች ታጅበው የሴንት ጀምስ ፓርኩን በር ዘግተው ወጥተዋል።
8 days ago
የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነት አለም አቀፍ አልበም በይፋ ተመረቀ
#ethiopia | የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነት የባህላዊ ሙዚቃ አልበም ትናንት በጎንደር ከተማ በተካሄደ ደማቅ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት በይፋ ተመረቀ።
በሙዚቃዊ፣ በሰላም ኢትዮጵያ እና በጎንደር ከተማ አስተዳደር ባህልና ኪነጥበብ ቢሮ ትብብር የተዘጋጀው አልበም፣ የጎንደርን እና የአማራ ክልልን የባህል ሙዚቃ ለአለም አቀፍ አድማጮች ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የመንግስት ተወካዮች፣ አርቲስቶች፣ የባህል ባለሙያዎች፣ አጋር ተቋማት፣ የሚዲያ ተወካዮችና በርካታ የጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል። የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነትም የቀጥታ የሙዚቃና የውዝዋዜ ትርኢት በማቅረብ ታዳሚዎችን አስደስቷል።
በአልበሙ ውስጥ የቡድኑ ድምፃውያን ሕይወት እያሱ፣ እህተነሽ ፋንታ፣ ሰሎሞን ጥጋቤን ጨምሮ ሌሎች የቡድኑ አባላት ተሳትፈዋል።
የሙዚቃ ዳይሬክተርነቱንም ሙዚቀኛ ምሳሌ ለገሰ መርተዋል። አልበሙ በባህላዊ የኢትዮጵያ መሳሪያዎች የተቀናበረ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ተቀርጾ የድምፅ ማስተካከያውና ማስተሪንጉ በጣሊያን በሚገኘው ማክስሳውንድ ቫይብ ስቱዲዮ ተከናውኗል።
በዝግጅቱ ላይ የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነትን ከ50 ዓመታት በላይ የሚያስቆጥር ታሪክ የሚያሳይ የፎቶግራፍ አውደ ርዕይም ለእንግዶች ቀርቧል። አውደ ርዕዩ የቡድኑን እድገት፣ ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ትዕይንት ጥበባት ያበረከተውን አስተዋፅኦ እንዲሁም ያፈራቸውን ታዋቂ አርቲስቶች የሚያስታውሱ ታሪካዊ ፎቶግራፎችና ሰነዶችን አካቷል።
በዝግጅቱ ላይ የሙዚቃዊ ተወካይ ሲሳይ መንግስቴ፣ አልበሙ ከመደበኛ የሙዚቃ ስራ በላይ የኢትዮጵያን የባህል ሀብት ለማስጠበቅና ለአለም አቀፍ ተደራሽነት ለማብቃት የተደረገ ኢንቨስትመንት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ስራ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ በዓለም አቀፍ የሙዚቃ ገበያ ተወዳዳሪ ለማድረግ እና ለአዲስ ትውልድ ለማስተላለፍ ጠቃሚ እርምጃ መሆኑን ጠቁመዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #gondarfasilidesculture #የጎንደርፋሲለደስባህልኪነት #ethiopianmusic #ethiopianculture #gondar #traditionalmusic #ethiopia
#ethiopia | የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነት የባህላዊ ሙዚቃ አልበም ትናንት በጎንደር ከተማ በተካሄደ ደማቅ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት በይፋ ተመረቀ።
በሙዚቃዊ፣ በሰላም ኢትዮጵያ እና በጎንደር ከተማ አስተዳደር ባህልና ኪነጥበብ ቢሮ ትብብር የተዘጋጀው አልበም፣ የጎንደርን እና የአማራ ክልልን የባህል ሙዚቃ ለአለም አቀፍ አድማጮች ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የመንግስት ተወካዮች፣ አርቲስቶች፣ የባህል ባለሙያዎች፣ አጋር ተቋማት፣ የሚዲያ ተወካዮችና በርካታ የጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል። የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነትም የቀጥታ የሙዚቃና የውዝዋዜ ትርኢት በማቅረብ ታዳሚዎችን አስደስቷል።
በአልበሙ ውስጥ የቡድኑ ድምፃውያን ሕይወት እያሱ፣ እህተነሽ ፋንታ፣ ሰሎሞን ጥጋቤን ጨምሮ ሌሎች የቡድኑ አባላት ተሳትፈዋል።
የሙዚቃ ዳይሬክተርነቱንም ሙዚቀኛ ምሳሌ ለገሰ መርተዋል። አልበሙ በባህላዊ የኢትዮጵያ መሳሪያዎች የተቀናበረ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ተቀርጾ የድምፅ ማስተካከያውና ማስተሪንጉ በጣሊያን በሚገኘው ማክስሳውንድ ቫይብ ስቱዲዮ ተከናውኗል።
በዝግጅቱ ላይ የጎንደር ፋሲለደስ ባህል ኪነትን ከ50 ዓመታት በላይ የሚያስቆጥር ታሪክ የሚያሳይ የፎቶግራፍ አውደ ርዕይም ለእንግዶች ቀርቧል። አውደ ርዕዩ የቡድኑን እድገት፣ ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ትዕይንት ጥበባት ያበረከተውን አስተዋፅኦ እንዲሁም ያፈራቸውን ታዋቂ አርቲስቶች የሚያስታውሱ ታሪካዊ ፎቶግራፎችና ሰነዶችን አካቷል።
በዝግጅቱ ላይ የሙዚቃዊ ተወካይ ሲሳይ መንግስቴ፣ አልበሙ ከመደበኛ የሙዚቃ ስራ በላይ የኢትዮጵያን የባህል ሀብት ለማስጠበቅና ለአለም አቀፍ ተደራሽነት ለማብቃት የተደረገ ኢንቨስትመንት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ስራ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ በዓለም አቀፍ የሙዚቃ ገበያ ተወዳዳሪ ለማድረግ እና ለአዲስ ትውልድ ለማስተላለፍ ጠቃሚ እርምጃ መሆኑን ጠቁመዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #gondarfasilidesculture #የጎንደርፋሲለደስባህልኪነት #ethiopianmusic #ethiopianculture #gondar #traditionalmusic #ethiopia
8 days ago
የባለ ብዙ ወገን ዲፕሎማሲ - ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን መሰረት ያደረገ እና ባለብዙ ወገን የውጭ ግንኙነት መርህን በመከተል አማራጮቿን እያሰፋች ትገኛለች።
ሀገሪቱ ለአንድ ወገን ባደላ አካሄድ ሳይሆን ብሔራዊ ጥቅሟን ሊያስከብሩ ከሚችሉ ወገኖች ሁሉ የጋራ ተጠቃሚነትን የጠበቀ ግንኙነት የመመስረት አቋም አላት።
ይህም አቋሟ በሀገራት መካከል ልዩነቶች ተፈጥረው ግንኙነታቸው ቢሻክርም ከሁለቱም ተቃራኒ ወገኖች ጋር ወዳጅነቷን አቻችላ ለመቀጠል አስችሏታል።
ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር በሚኖራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት "እኔ ብቻ ልጠቀም" የሚል መንገድ ሳትከተል የጋራ ተጠቃሚነትን ማዕከል አድርጋ ትንቀሳቀሳለች።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ የማደግ ፍላጎት ያላት ኢትዮጵያ፤ የተፈጥሮ የውሃ ሀብቶቿን ለመጠቀም ስታቅድም ሌሎችን ሳይጎዳ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትሰራለች።
ከዚህ ባለፈም የቀጣናው ሰላም እና ደህንነት እንዲጠበቅ ሰራዊቷን በማሰማራት ረገድ የጎላ ሚና ስታበረክት ቆይታለች።
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ከወሰደቻቸው ርምጃዎች መካከል የብሪክስ ስብስብ አባል መሆኗ አንዱ ነው። ይህ አባልነቷ ከምዕራባውያን ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት በጠበቀ መልኩ የተከናወነ ሲሆን፤ ይህም ሀገሪቱ ለጋራ ጥቅም በጋራ የመስራት ቁርጠኝነቷ ማሳያ ነው።
የብሪክስ አባልነት ታዳጊ ሀገራት ያላቸውን የድምፅ መስጠት አቅም ይጨምራል፤ የወጪ ንግድ አቅምን ለማሳደግና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እድል ከመስጠት ባሻገር የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመፍታት ያግዛል፡፡
በተጨማሪም በሀገራቱ መካከል የእውቀት ልውውጦች እንዲፈጠሩ፣ ደህንነት በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንዲቻል፤ እንዲሁም እርስ በርስ ያሉ ግንኙነቶችን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል።
በቤተልሔም ግርማ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን መሰረት ያደረገ እና ባለብዙ ወገን የውጭ ግንኙነት መርህን በመከተል አማራጮቿን እያሰፋች ትገኛለች።
ሀገሪቱ ለአንድ ወገን ባደላ አካሄድ ሳይሆን ብሔራዊ ጥቅሟን ሊያስከብሩ ከሚችሉ ወገኖች ሁሉ የጋራ ተጠቃሚነትን የጠበቀ ግንኙነት የመመስረት አቋም አላት።
ይህም አቋሟ በሀገራት መካከል ልዩነቶች ተፈጥረው ግንኙነታቸው ቢሻክርም ከሁለቱም ተቃራኒ ወገኖች ጋር ወዳጅነቷን አቻችላ ለመቀጠል አስችሏታል።
ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር በሚኖራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት "እኔ ብቻ ልጠቀም" የሚል መንገድ ሳትከተል የጋራ ተጠቃሚነትን ማዕከል አድርጋ ትንቀሳቀሳለች።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ የማደግ ፍላጎት ያላት ኢትዮጵያ፤ የተፈጥሮ የውሃ ሀብቶቿን ለመጠቀም ስታቅድም ሌሎችን ሳይጎዳ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትሰራለች።
ከዚህ ባለፈም የቀጣናው ሰላም እና ደህንነት እንዲጠበቅ ሰራዊቷን በማሰማራት ረገድ የጎላ ሚና ስታበረክት ቆይታለች።
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ከወሰደቻቸው ርምጃዎች መካከል የብሪክስ ስብስብ አባል መሆኗ አንዱ ነው። ይህ አባልነቷ ከምዕራባውያን ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት በጠበቀ መልኩ የተከናወነ ሲሆን፤ ይህም ሀገሪቱ ለጋራ ጥቅም በጋራ የመስራት ቁርጠኝነቷ ማሳያ ነው።
የብሪክስ አባልነት ታዳጊ ሀገራት ያላቸውን የድምፅ መስጠት አቅም ይጨምራል፤ የወጪ ንግድ አቅምን ለማሳደግና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እድል ከመስጠት ባሻገር የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመፍታት ያግዛል፡፡
በተጨማሪም በሀገራቱ መካከል የእውቀት ልውውጦች እንዲፈጠሩ፣ ደህንነት በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንዲቻል፤ እንዲሁም እርስ በርስ ያሉ ግንኙነቶችን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል።
በቤተልሔም ግርማ
9 days ago
ይድረስ ለአራቱ ድምፃውያን
– “ማንም የላት” ከተሰኘው የኅብረት ዜማ ጋር በተያያዘ
ከተመስገን ኡካሬ (የሐጌ ልጅ)
#ethiopia | "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ሙዚቃ ብቻ አይደለም፤ የህሊና ጥሪ፣ የማህበራዊ ኃላፊነት ማንቂያ እና የሰብአዊነት መልዕክት ነው። ይህ ስራ የአካል ጉዳተኞችንና የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያላቸውን ወገኖች በርኅራኄ ከመመልከት ይልቅ፣ እንደ ሙሉ መብት ባለቤቶች እንድናያቸው ያስጠይቃል።
ሙዚቃው የሚያነሳው ዋና ጥያቄ አካል ጉዳተኝነት ሳይሆን፣ እኛ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እጥረት ነው። ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ስራ፣ የህዝብ አገልግሎቶች እና ማህበራዊ ተሳትፎ ለሁሉም እኩል ተደራሽ ናቸው ወይ? የሚለውን ጥያቄ በጥልቅ ያቀርባል።
የኅብረት ዜማዎች ሁልጊዜም የዘመናቸውን ማህበራዊ ጉዳይ ያንጸባርቃሉ። "ማለባበስ ይቅር"፣ "ስደት"፣ "ሰላም ለሀገራችን" እና ሌሎችም እንደ ነበሩት ሁሉ፣ "ማንም የላት" ደግሞ የዚህ ዘመን የህሊና ጥሪ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ ስራ በስሜት ብቻ የተሞላ አይደለም፤ መፍትሄ የሚፈልግ ጥያቄ ያቀርባል። "ማንም የላት" የሚለውን አባባል "እኛም አለን" በሚል ተግባራዊ መልስ እንድንተካው ይጋብዘናል።
በዚህ ዜማ ላይ የተሳተፉት ድምፃዊ ማስተዋል እያዩ፣ ድምፃዊት ሀና ግርማ፣ ድምፃዊ አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) እና ድምፃዊት ሄዋን ገብረወልድ እያንዳንዳቸው መልዕክቱን በሚመጥን ስሜት አቅርበዋል።
ግጥሙን ናትናኤል ግርማቸው፣ ዜማውን አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ ቅንብሩን ደግሞ ታምሩ አማረ (ቶሚ) በሙያዊ ብቃት አስውበውታል። የግጥሙ፣ የዜማው፣ የድምፅ አቀራረቡና የቅንብሩ መዋሃድ ሙዚቃውን ከመዝናኛነት በላይ ወደ ማህበራዊ ንቅናቄ አሳድጎታል።
ይህ ዜማ የሚያስታውሰን አንድ እውነት አለ፤ ሰብአዊነት በቃላት ሳይሆን በተግባር ይለካል። አካል ጉዳተኞች ርኅራኄ አይፈልጉም፤ እኩል ዕድል፣ ተደራሽነትና ክብር ይፈልጋሉ።
ይድረስ ለአራቱ ድምፃውያን፤ ለህዝብ የሚያስብ፣ ህሊናን የሚያነቃ እና ማህበረሰብን ወደ በጎ ለውጥ የሚጋብዝ ስራ ስላቀረባችሁ ምስጋና ይገባችኋል። ይህ ዜማ በሙዚቃ ታሪክ ውስጥ እንደ ዜማ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ማህበራዊ ጥሪ የሚታወስ ስራ ይሆናል።
አቶ ሳሚ ተድላ ( የተድላ አምቡላንስ መሥራችና ባለቤት ) "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ፕሮውዲሰር ምስጋና ይገባቸዋል።
በተለይም ጥበብንና በጎ አድራጎትን አጣምሮ በመያዝ፣ አቅም የሌላቸውንና ረዳት ያጡ ወገኖችን ድምፅ ለማሰማት ያደረጉት ጥረትና ያወጡት ወጪ የሚወደስ ነው።
በተጨማሪም በተድላ አምቡላንስ በኩል የሚያደርጉት ድገስ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴ፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ ትልቅ አክብሮትና ምስጋና የሚያሰጣቸው ያደርጋቸዋል። እንደዚህ ያሉ በጎ አድራጊ ባለሃብቶችና ድርጅቶች ለሌላውም አርአያ የሚሆኑ ናቸው።
– “ማንም የላት” ከተሰኘው የኅብረት ዜማ ጋር በተያያዘ
ከተመስገን ኡካሬ (የሐጌ ልጅ)
#ethiopia | "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ሙዚቃ ብቻ አይደለም፤ የህሊና ጥሪ፣ የማህበራዊ ኃላፊነት ማንቂያ እና የሰብአዊነት መልዕክት ነው። ይህ ስራ የአካል ጉዳተኞችንና የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያላቸውን ወገኖች በርኅራኄ ከመመልከት ይልቅ፣ እንደ ሙሉ መብት ባለቤቶች እንድናያቸው ያስጠይቃል።
ሙዚቃው የሚያነሳው ዋና ጥያቄ አካል ጉዳተኝነት ሳይሆን፣ እኛ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እጥረት ነው። ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ስራ፣ የህዝብ አገልግሎቶች እና ማህበራዊ ተሳትፎ ለሁሉም እኩል ተደራሽ ናቸው ወይ? የሚለውን ጥያቄ በጥልቅ ያቀርባል።
የኅብረት ዜማዎች ሁልጊዜም የዘመናቸውን ማህበራዊ ጉዳይ ያንጸባርቃሉ። "ማለባበስ ይቅር"፣ "ስደት"፣ "ሰላም ለሀገራችን" እና ሌሎችም እንደ ነበሩት ሁሉ፣ "ማንም የላት" ደግሞ የዚህ ዘመን የህሊና ጥሪ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ ስራ በስሜት ብቻ የተሞላ አይደለም፤ መፍትሄ የሚፈልግ ጥያቄ ያቀርባል። "ማንም የላት" የሚለውን አባባል "እኛም አለን" በሚል ተግባራዊ መልስ እንድንተካው ይጋብዘናል።
በዚህ ዜማ ላይ የተሳተፉት ድምፃዊ ማስተዋል እያዩ፣ ድምፃዊት ሀና ግርማ፣ ድምፃዊ አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) እና ድምፃዊት ሄዋን ገብረወልድ እያንዳንዳቸው መልዕክቱን በሚመጥን ስሜት አቅርበዋል።
ግጥሙን ናትናኤል ግርማቸው፣ ዜማውን አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ ቅንብሩን ደግሞ ታምሩ አማረ (ቶሚ) በሙያዊ ብቃት አስውበውታል። የግጥሙ፣ የዜማው፣ የድምፅ አቀራረቡና የቅንብሩ መዋሃድ ሙዚቃውን ከመዝናኛነት በላይ ወደ ማህበራዊ ንቅናቄ አሳድጎታል።
ይህ ዜማ የሚያስታውሰን አንድ እውነት አለ፤ ሰብአዊነት በቃላት ሳይሆን በተግባር ይለካል። አካል ጉዳተኞች ርኅራኄ አይፈልጉም፤ እኩል ዕድል፣ ተደራሽነትና ክብር ይፈልጋሉ።
ይድረስ ለአራቱ ድምፃውያን፤ ለህዝብ የሚያስብ፣ ህሊናን የሚያነቃ እና ማህበረሰብን ወደ በጎ ለውጥ የሚጋብዝ ስራ ስላቀረባችሁ ምስጋና ይገባችኋል። ይህ ዜማ በሙዚቃ ታሪክ ውስጥ እንደ ዜማ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ማህበራዊ ጥሪ የሚታወስ ስራ ይሆናል።
አቶ ሳሚ ተድላ ( የተድላ አምቡላንስ መሥራችና ባለቤት ) "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ፕሮውዲሰር ምስጋና ይገባቸዋል።
በተለይም ጥበብንና በጎ አድራጎትን አጣምሮ በመያዝ፣ አቅም የሌላቸውንና ረዳት ያጡ ወገኖችን ድምፅ ለማሰማት ያደረጉት ጥረትና ያወጡት ወጪ የሚወደስ ነው።
በተጨማሪም በተድላ አምቡላንስ በኩል የሚያደርጉት ድገስ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴ፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ ትልቅ አክብሮትና ምስጋና የሚያሰጣቸው ያደርጋቸዋል። እንደዚህ ያሉ በጎ አድራጊ ባለሃብቶችና ድርጅቶች ለሌላውም አርአያ የሚሆኑ ናቸው።
9 days ago
በየመንገዱ ቆመው ብዙዎቻችንን ያቀራረቡ፣ ወረፋ እስኪደርሰን ትዕግስትን ያለማመዱን፣ የሳንቲም ድምፅ እየሰማን የተነጋገርንባቸው #የሕዝብ_ስልኮች 🤩
🙋♂️🙋♀️ በእነዚህ የሕዝብ ስልኮች የተጠቀማችሁ
✍️ ከትዝታዎቻችሁ የማትረሱትን አጋሩን
#ትውስታ #throwbackthursday #ethiotelecom #telebirr #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
🙋♂️🙋♀️ በእነዚህ የሕዝብ ስልኮች የተጠቀማችሁ
✍️ ከትዝታዎቻችሁ የማትረሱትን አጋሩን
#ትውስታ #throwbackthursday #ethiotelecom #telebirr #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
Sponsored by
Surafel
9 days ago
የ«ሁሉ ስፖርት» የፈቃድ ስረዛ በከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሻረ፤ አገልግሎቱ ግን አሁንም ታግዷል
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት እና የገቢዎች ሚኒስቴር በ«ሁሉ ስፖርት» ላይ አስተላልፈውት የነበረውን የንግድ ፈቃድ ስረዛ ውሳኔ በሙሉ ድምፅ ሻረ። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን የሻረው ተቋማቱ የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት ሕግን ሳይከተሉ እና የተቋሙን የመሰማት መብት ጥሰው ፈቃድ መሰረዛቸውን በመግለፅ ነው።
መንግሥት ድርጅቶቹ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ግብር ሰውረዋል ቢልም፣ ፍርድ ቤቱ ይህ በወንጀል ሕግ የሚታይ እንጂ በደፈናው ለአስተዳደራዊ ፈቃድ ስረዛ ምክንያት ሊሆን አይችልም ብሏል።
ሆኖም የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በውሳኔው ላይ ይግባኝ ማቅረቡን ተከትሎ፣ የፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ አፈጻጸም ከሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ15 ቀናት እንዲታገድ ተደርጓል።
በመሆኑም ጉዳዩ በጠቅላይ ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ «ሁሉ ስፖርት» ወደ ሥራ አይመለስም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሎተሪ አገልግሎቱ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ሕጋዊ ፈቃድ ያለው ምንም ዓይነት የስፖርት ውርርድ (ቤቲንግ) ድርጅት እንደሌለ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት እና የገቢዎች ሚኒስቴር በ«ሁሉ ስፖርት» ላይ አስተላልፈውት የነበረውን የንግድ ፈቃድ ስረዛ ውሳኔ በሙሉ ድምፅ ሻረ። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን የሻረው ተቋማቱ የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት ሕግን ሳይከተሉ እና የተቋሙን የመሰማት መብት ጥሰው ፈቃድ መሰረዛቸውን በመግለፅ ነው።
መንግሥት ድርጅቶቹ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ግብር ሰውረዋል ቢልም፣ ፍርድ ቤቱ ይህ በወንጀል ሕግ የሚታይ እንጂ በደፈናው ለአስተዳደራዊ ፈቃድ ስረዛ ምክንያት ሊሆን አይችልም ብሏል።
ሆኖም የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በውሳኔው ላይ ይግባኝ ማቅረቡን ተከትሎ፣ የፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ አፈጻጸም ከሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ15 ቀናት እንዲታገድ ተደርጓል።
በመሆኑም ጉዳዩ በጠቅላይ ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ «ሁሉ ስፖርት» ወደ ሥራ አይመለስም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሎተሪ አገልግሎቱ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ሕጋዊ ፈቃድ ያለው ምንም ዓይነት የስፖርት ውርርድ (ቤቲንግ) ድርጅት እንደሌለ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የቀድሞው የአሜሪካ ከፍተኛ የኢንፌክሽን በሽታዎች ኤክስፐርት ዶክተር አንቶኒ ፋውቺ፣ ረቡዕ ዕለት በሴኔት ሀገር ውስጥ ደኅንነት ኮሚቴ ፊት ቀርበው ከኮሚቴው ሰብሳቢ ሪፐብሊካኑ ሴናተር ራንድ ፖል ጋር የከረረ ፍጥጫ ውስጥ ገብተዋል። ዶክተር ፋውቺ በችሎቱ ላይ የቀረቡት በሴናተር ፖል መጥሪያ አዛዥነት ሲሆን፣ ውጥረት በነገሰበት በዚህ ችሎት ላይ ማንኛውንም ጥያቄ ላለመመለስ አምስተኛውን የሕገ-መንግስት ማሻሻያ መብታቸውን እንደሚጠቀሙ ይፋ አድርገዋል።
ዶክተር ፋውቺ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ሴናተር ራንድ ፖል በቅርቡ የግል ማስታወሻ ደብተራቸውን ይፋ ማድረጋቸውን በመኮነን ጥብቅ መግለጫ ሰጥተዋል። "ሴናተር ፖል እኔን ለፍርድ ለማቅረብ ካለው ግልጽ እብደት፣ ስለ እኔ ከተናገራቸው ስም አጥፊ ንግግሮች እና እኔን ለማሳፈርና ለማስፈራራት ሲል ይፋ ካደረገው የግል ማስታወሻ ደብተሬ በመነሳት፤ እኔ ልደርስበት የምችለው አንድ መደምደሚያ ብቻ ነው። እሱ እኔን ወደዚህ ኮሚቴ የጠራበት ብቸኛ ምክንያት እስር ቤት እንድገባ የገባውን ቃል የሚያረጋግጥልኝን ማንኛውንም ቃል ከእኔ አፍ ለማውጣት ነው" ብለዋል። አክለውም በህግ አማካሪዎቻቸው ምክር መሰረት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሙሉ ምላሽ ከመስጠት እንደሚቆጠቡ አስታውቀዋል።
በችሎቱ ወቅት ሴናተር ራንድ ፖል እና ሌሎች ሪፐብሊካን ሴናተሮች በቻይና ውሃን ላቦራቶሪ ስለተደረገው የቫይረስ ምርምር፣ ስለ ኮቪድ-19 ክትባቶች እና በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ስለተሰጣቸው የፕሬዝዳንታዊ ምህረት ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን ቢያቀርቡም፣ ዶክተር ፋውቺ "በጠበቃዬ ምክር መሰረት በአምስተኛው ማሻሻያ መብቴ በመጠቀም ምላሽ ከመስጠት እቆጠባለሁ" የሚለውን አቋማቸውን አልቀየሩም።
በችሎቱ መሀል ድባቡ ይበልጥ የከረረው ሴናተር ራንድ ፖል የዶክተር ፋውቺን ጠበቃ "ያለ ፈቃድ ተናግረሃል" በሚል ከችሎት ክፍሉ በደኅንነት አባላት አስወጥተው እንዲባረሩ ሲያደርጉ ነው። ይህንን ተከትሎ የፋውቺ ጠበቃ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ደንበኛቸው ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን የመጠቀም ሙሉ ህጋዊ መብት እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሴናተር ራንድ ፖል፣ ዶክተር ፋውቺ ከቀድሞው ፕሬዝዳንት ባይደን ሙሉ የፕሬዝዳንት ምህረት የተሰጣቸው በመሆኑ ይህንን የምስክርነት መብት የመቃወም መብት የላቸውም ሲሉ ሞግተዋል። ፋውቺ ጥያቄዎችን ባለመመለሳቸው ምክንያት ኮሚቴው በሚቀጥለው ሳምንት በዶክተር ፋውቺ ላይ "የኮንግረስ ንቀት" ውሳኔ ለማስተላለፍ ድምፅ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
በሌላ በኩል በኮሚቴው ውስጥ የሚገኙት የዴሞክራቲክ ፓርቲ አባላት እና የኮሚቴው ከፍተኛ አባል ሴናተር ጋሪ ፒተርስ፣ ሴናተር ፖል የምርጫ እና የፖለቲካ አጀንዳቸውን ለማስፈጸም ያለፈውን ታሪክ እየቆፈሩ የምርመራ ሂደቱን ለፓርቲ ጥቅም እያዋሉት ነው ሲሉ አጥብቀው ተችተዋል።
ለሶስት ሰዓታት የቆየውን ይህንን ችሎት ያጠናቀቁት ሴናተር ራንድ ፖል "ዛሬ የፋውቺ የ40 ዓመት የቁጥጥር እና የስልጣን አጠቃቀም ማጠቃለያ ነው" ካሉ በኋላ፣ የፋውቺ ውሳኔዎች በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ሰው ሰራሽ ወረርሽኝ እንዲከሰት ምክንያት ሆነው እንደሆነ አሁንም በህሊናቸው ሊጠየቁ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ዶክተር ፋውቺ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ሴናተር ራንድ ፖል በቅርቡ የግል ማስታወሻ ደብተራቸውን ይፋ ማድረጋቸውን በመኮነን ጥብቅ መግለጫ ሰጥተዋል። "ሴናተር ፖል እኔን ለፍርድ ለማቅረብ ካለው ግልጽ እብደት፣ ስለ እኔ ከተናገራቸው ስም አጥፊ ንግግሮች እና እኔን ለማሳፈርና ለማስፈራራት ሲል ይፋ ካደረገው የግል ማስታወሻ ደብተሬ በመነሳት፤ እኔ ልደርስበት የምችለው አንድ መደምደሚያ ብቻ ነው። እሱ እኔን ወደዚህ ኮሚቴ የጠራበት ብቸኛ ምክንያት እስር ቤት እንድገባ የገባውን ቃል የሚያረጋግጥልኝን ማንኛውንም ቃል ከእኔ አፍ ለማውጣት ነው" ብለዋል። አክለውም በህግ አማካሪዎቻቸው ምክር መሰረት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሙሉ ምላሽ ከመስጠት እንደሚቆጠቡ አስታውቀዋል።
በችሎቱ ወቅት ሴናተር ራንድ ፖል እና ሌሎች ሪፐብሊካን ሴናተሮች በቻይና ውሃን ላቦራቶሪ ስለተደረገው የቫይረስ ምርምር፣ ስለ ኮቪድ-19 ክትባቶች እና በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ስለተሰጣቸው የፕሬዝዳንታዊ ምህረት ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን ቢያቀርቡም፣ ዶክተር ፋውቺ "በጠበቃዬ ምክር መሰረት በአምስተኛው ማሻሻያ መብቴ በመጠቀም ምላሽ ከመስጠት እቆጠባለሁ" የሚለውን አቋማቸውን አልቀየሩም።
በችሎቱ መሀል ድባቡ ይበልጥ የከረረው ሴናተር ራንድ ፖል የዶክተር ፋውቺን ጠበቃ "ያለ ፈቃድ ተናግረሃል" በሚል ከችሎት ክፍሉ በደኅንነት አባላት አስወጥተው እንዲባረሩ ሲያደርጉ ነው። ይህንን ተከትሎ የፋውቺ ጠበቃ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ደንበኛቸው ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን የመጠቀም ሙሉ ህጋዊ መብት እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሴናተር ራንድ ፖል፣ ዶክተር ፋውቺ ከቀድሞው ፕሬዝዳንት ባይደን ሙሉ የፕሬዝዳንት ምህረት የተሰጣቸው በመሆኑ ይህንን የምስክርነት መብት የመቃወም መብት የላቸውም ሲሉ ሞግተዋል። ፋውቺ ጥያቄዎችን ባለመመለሳቸው ምክንያት ኮሚቴው በሚቀጥለው ሳምንት በዶክተር ፋውቺ ላይ "የኮንግረስ ንቀት" ውሳኔ ለማስተላለፍ ድምፅ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
በሌላ በኩል በኮሚቴው ውስጥ የሚገኙት የዴሞክራቲክ ፓርቲ አባላት እና የኮሚቴው ከፍተኛ አባል ሴናተር ጋሪ ፒተርስ፣ ሴናተር ፖል የምርጫ እና የፖለቲካ አጀንዳቸውን ለማስፈጸም ያለፈውን ታሪክ እየቆፈሩ የምርመራ ሂደቱን ለፓርቲ ጥቅም እያዋሉት ነው ሲሉ አጥብቀው ተችተዋል።
ለሶስት ሰዓታት የቆየውን ይህንን ችሎት ያጠናቀቁት ሴናተር ራንድ ፖል "ዛሬ የፋውቺ የ40 ዓመት የቁጥጥር እና የስልጣን አጠቃቀም ማጠቃለያ ነው" ካሉ በኋላ፣ የፋውቺ ውሳኔዎች በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ሰው ሰራሽ ወረርሽኝ እንዲከሰት ምክንያት ሆነው እንደሆነ አሁንም በህሊናቸው ሊጠየቁ እንደሚገባ ተናግረዋል።
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ጄኔራል አልብሩሀን ‹‹አልፋሽር የእኛ ነው›› አሉ፡፡ የሱዳን ወታደራዊ መንግስት መሪና የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን ከተቀናቃኛቸው መልሰው የተቆጣጠሩትን ቦታዎች ጎበኙ፡፡ አልብሩሀን በሄሊኮፕተር ተጉዘው ይህንን ጉብኝት ያደረጉት ከዳርፉር ገዥ ሚኒ አርኮ ሚናዊ፣ ከኮርዶፋን ገዥ አብደልካሊቅና ከሱዳን ሺልድ ሀይሎች ዋና አዛዥ አቡ አግላ ጋር በመሆን ሲሆን ጉብኝታቸውም ባራ፣ ጀብራ አልሼክና ኡም ሳያላ የተሰኙትን ከተሞች ያካተተ ነበር፡፡
እንደሬዲዮ ዳባንጋ ዘገባ አልብሩሀን ከሄሊኮፕተር እንደወረዱ ‹‹አልፋሽር የእኛ ነው›› በማለት በከፍተኛ ድምፅ መፈክር ያሰሙ ሲሆን በስፍራው የነበሩ ወታደሮችም ‹‹የእኛ ነው›› በማለት አጅበዋቸዋል፡፡ ዘገባው እንደገለፀው የእነዚህ ከተሞችና ኦምድሩማንን ከአልኦቢድ ጋር የሚያገናኘው መንገድ በጦር ሀይሉ በቁጥጥር ስር መዋል ትልቅ ወታደራዊ ጠቀሜታ የሚሰጠው ነው፡፡
ይህም ወደምእራባዊ ኮርዶፋን ለሚያደርገው ቀጣይ ዘመቻ አስተዋፅኦ የሚያደርገለት ይሆናል፡፡ በጄኔራል አልብሩሀን በዚህ ጉብኝት የአል ኦቢድ ነዋሪዎች ደስታቸውን መግለፃቸውን የጠቀሰው ዘገባው ይሁንና ተቀናቃኙ ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ግን ወሳኝ ድል እያስመዘገበ መሆኑን መስማቱን አስታውቋል፡፡ በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ውስጥ የሚገኙ ወታደራዊ ምንጭን በዋቢነት የጠቀሰው ዘገባው ሀይላቸው አሁንም አልኦቢድን መክበቡን ጠቅሷል፡፡
እንደሬዲዮ ዳባንጋ ዘገባ አልብሩሀን ከሄሊኮፕተር እንደወረዱ ‹‹አልፋሽር የእኛ ነው›› በማለት በከፍተኛ ድምፅ መፈክር ያሰሙ ሲሆን በስፍራው የነበሩ ወታደሮችም ‹‹የእኛ ነው›› በማለት አጅበዋቸዋል፡፡ ዘገባው እንደገለፀው የእነዚህ ከተሞችና ኦምድሩማንን ከአልኦቢድ ጋር የሚያገናኘው መንገድ በጦር ሀይሉ በቁጥጥር ስር መዋል ትልቅ ወታደራዊ ጠቀሜታ የሚሰጠው ነው፡፡
ይህም ወደምእራባዊ ኮርዶፋን ለሚያደርገው ቀጣይ ዘመቻ አስተዋፅኦ የሚያደርገለት ይሆናል፡፡ በጄኔራል አልብሩሀን በዚህ ጉብኝት የአል ኦቢድ ነዋሪዎች ደስታቸውን መግለፃቸውን የጠቀሰው ዘገባው ይሁንና ተቀናቃኙ ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ግን ወሳኝ ድል እያስመዘገበ መሆኑን መስማቱን አስታውቋል፡፡ በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ውስጥ የሚገኙ ወታደራዊ ምንጭን በዋቢነት የጠቀሰው ዘገባው ሀይላቸው አሁንም አልኦቢድን መክበቡን ጠቅሷል፡፡
10 days ago
#tecno_spark_50
እጅግ ጫጫታ የሆነ ቦታ ሆነው በጣም የሚፈልጉት ስልክ ተደውሎ የት ሄጄ ላውራ የሚል ስጋት ገብቶት ያውቃል፡፡ አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 ጋር እንደዚህ እይነት ስጋት ታሪክ ነው፡፡ ለምን ካላችሁ የፈለገ ጫጫታ ቦታ ቢሆኑ እንኳን ባዶ ክፍል ውስጥ ሆነው እያወሩ እስኪመስል ድረስ ፅጥ የሚያደርግ የNoise Cancellation ቴክኖሎጂ ስላለው የፈለጉትን ስልክ በፈለጉት ቦታ ያለምንም ድምፅ ብክለት ማውራት ያስችሎታል፡፡ ቴክኖ ስፓርክ 50 በልዩነት የሚመርጡት ስልክ!!
#spark50 #spark50series #tecnoai #tecnoet
tecno_et
እጅግ ጫጫታ የሆነ ቦታ ሆነው በጣም የሚፈልጉት ስልክ ተደውሎ የት ሄጄ ላውራ የሚል ስጋት ገብቶት ያውቃል፡፡ አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 ጋር እንደዚህ እይነት ስጋት ታሪክ ነው፡፡ ለምን ካላችሁ የፈለገ ጫጫታ ቦታ ቢሆኑ እንኳን ባዶ ክፍል ውስጥ ሆነው እያወሩ እስኪመስል ድረስ ፅጥ የሚያደርግ የNoise Cancellation ቴክኖሎጂ ስላለው የፈለጉትን ስልክ በፈለጉት ቦታ ያለምንም ድምፅ ብክለት ማውራት ያስችሎታል፡፡ ቴክኖ ስፓርክ 50 በልዩነት የሚመርጡት ስልክ!!
#spark50 #spark50series #tecnoai #tecnoet
tecno_et
10 days ago
u12e8u1275u130du122bu12ed u12c8u1323u1276u127d u12f5u121du1345 - u12e8u1325u12edu1275u1295 u1325u134bu1275 u12e8u121au12ebu12cdu1245 u12e8u121au1218u122du1320u12cd u121du12adu12adu122du1295 u1290u12cd
#ebcdotstream #nationaldiaperbanknetworklogue #ebc #ethiopia ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የትግራይ ወጣቶች ድምፅ - የጥይትን ጥፋት የሚያውቅ የሚመርጠው ምክክርን ነው
#ebcdotstream #nationaldiaperbanknetworklogue #ebc #ethiopia
11 days ago
በሆነ በዘመን የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም!
የአህመድ ተሸመ (ዲንቢ) “ጊዜ አይሄድም”!
ተስፋዬ እሸቱ (ረ/ፕሮፌሰር)
#ethiopia | መቸም የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ድንቅ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፡፡ ለራሱ የሠራቸውን ዘግየት እናድርግና ለሌሎች የሙያ አጋሮቹ ሠርቶላቸው በብዙኋን አድማጮች ዘንድ ሰፊ ተቀባይነትን ያገኙትን የዜማ ድርሰቶቹን እንዘርዝር ብንል ጊዜም ሥፍራም አይበቃንም፡፡
እንደው ከግምታችን በላይ ስለሆነው ስለዲንቢ የላቀ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና መሠረታዊ ግንዛቤ ሊያስጨብጠን ቢችል ግን ጥቂቱን ብቻ ከዚህ እንደሚከተለው እዘረዝርላችኋለሁ፡—
ለአሊ ቢራና ሄለን በርሄ - “ሲያዴ”፤ ለፀሀዬ ዮሐንስ - “ማን ልበልሽ”፤ ለማዲንጎ አፈወርቅ - “ላላተርፍ”፤ ለብዙአየሁ ደምሴ - “የህልሜ ንግስት”፤ ለዘቢባ ግርማ - “ገራገር”፤ ለኢሳያስ ታምራት - “እያዳነ ያማል”፤ ለታረቀኝ ሙሉ - “ስሚያቸው”፤ ለሚኪያስ ቸርነት - “ግርማ ሞገሴ”፤ ለሃይማኖት ግርማ - “ከዚራ ቁ-2”፤ ለግርማ ተፈራ - “ልዩ”፤ ለሀመልማል አባተ - “ሀሴት”፤ እና የመሳሰሉቱን የአህመድ ዲንቢን የዜማ ፈጠራዎች ከብዙ በጥቂቱ ማስታወስ ይቻላል፡፡
አንዳንድ ሙዚቃዎች ለጆሮ ብቻ አይሰሩም፤ ለስሜት ይደርሳሉ፤ ዛሬ ተሰርተው ግን ትዝታችንን ይመልሱልናል፡፡
አንዳንድ ዜማዎች፣ በውስጣችን የተከረቸሙ የጊዜ በሮችን ያንኳኳሉ፤ ይከፍታሉምም፡፡ በሮቹ ሲከፈቱ ደግሞ የተዘነጉ ፊቶች፣ የተለየናቸው ጓደኞች፣ የተራመድንባቸውን ጎዳናዎች… ብቻ ምኑ ቅጡ ትላንታችንን እንደ መጽሀፍ ይገልጡልናል፡፡ በሆነ ዘመን የቀረውን ማንነታችንን እንደገና ይመልሱልናል።
አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ከ14 ዓመታት በኋላ በአዲስ አልበሙ ሲመለስ፣ እኔ የሰማሁት የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብን አይደለም። አንድ በሆነ ዘመን የነበረ የዜማ ሰዋሰውና በዚሁ ዜማ ምክንያት የተሰፋ፣ የምናፍቀውን ዘመን የመለሰልኝ ያህል ነው የተሰማኝ፡፡
ያ የኔ ዘመን የምለው “ዘጠናዎቹ”ን ነው፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሆኜ የገባሁት በ1997 ዓ.ም. ነው። አይ፣ ተማሪነት! እንዴት ያለ ጣፋጭ፣ እንዴት ያለ የማይደገም ዘመን ነበር! ያ ዘመን ለእኔ የወጣትነት ወርቃማ ጠዋት ነበር። ዓለምን እንደ አዲስ ማየት የጀመርኩበት፤ ከተማዋን፣ ሕይወትን፣ ፍቅርን፣ ሐሳብንና ነፃነትን ለመጀመሪያ ጊዜ በሙሉ ልብ ያጣጣምኩበት ዘመን ነበር።
ያ ዘመን ከጓደኞቸ ጋር እንደፈለግን የኖርንበት ዘመን ነበር። በአደባባይ የተከራከርንበት፣ አለምን የጠየቅንበት፣ መንግሥትን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቃወምንበት፣ ነፃነትን ያየንበት፣ ዜማን ያጣጣምንበት ወቅት ነበር። ያ ዘመን “ዘጠናዎቹ” ነበር፡፡
ያንን ዘመን ሁሌም እናፍቀዋለሁ፤ ምናልባትም የምናፍቀው ዘመኑን ራሱን አይደለም፤ በዚያ ዘመን ውስጥ የነበርነውን እሱን፣ እሷን፣እኔን፣እኛን ነው። እንደገና እንዲመጣም እመኛለሁ።
ማርሴል ፕሩስት የተባለ ፈረንሳያዊ የልብ ወለድ ጸሀፊና ሀያሲ ጥልቅ የሆነን ትዝታ አስበን ለማስታወስ በምናደርገው ጥረት አይመለስም፤ ነገር ግን የስሜት ሕዋሳችን በሚነካ አንድ ድንገተኛ ልምድ ሊቀሰቀስ ይችላል ይላል፡፡ ሙዚቃም ከእነዚህ የትዝታ ቀስቃሾች መካከል እጅግ ኃይለኛው ሳይሆን አይቀርም።
በዚህ ረገድ እንደ አህመድ ተሾመ ጥንቅቅ ተደርጎ የተሰራ ዜማ የተረሳ ግን ተደበቀ ስሜትን ይቀሰቅሳል፤ የጠፋ የሚመስለውን የዜማ ስልተ ምት ይመልሳል፤ በዘመን ጥላ ሥር ተደብቆ የኖረ ማንነት እንደገና ያነቃቃል።
በ1990ዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ የራሱ የሆነ የዜማ ሰዋሰው፣ ቀለምና የአወራረድ ለዛ ነበረው። ያ ዘመን ለእኔ ሙዚቃን ከመስማት ወደ ማዳመጥ የተሸጋገርኩበት ጊዜ ነው። ስለዚህ የዚያ ዘመን ዜማዎች በጆሮዬ ብቻ ተደምጠው አልቀሩም፤ በማንነቴ ውስጥ ህያው ናቸው።
እኔ የሙዚቃ ባለሙያ አይደለሁም፤ ሙዚቃን ግን በልቤ አዳምጠዋለሁ። በእኔ የዜማ አረዳድ፣ የዚያ ዘመን የዜማ አሠራሮች በቀላሉ የሚደገሙ አይደሉም። ምክንያቱም ዜማው የተፈጠረው በድምፅ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመኑ መንፈስም ጭምር ነው። ከዚያ በኋላ የመጡት ዘመናት የራሳቸውን የሙዚቃ ቋንቋ ፈጥረዋል።
ያው ዘመን ሲለወጥ የዜማ ሰዋሰውም የሚለወጥ ይመስለኛል፡፡ ይህም የሥነ ጥበብ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው፤ ዋናው ጉዳይ ግን በ1990ዎቹና ከዚያ በኋላ በመጡት ዜማዎች መካከል የተቋረጠ ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡ መቆራረጡ ለሙዚቃ ባለሙያዎች ትልቅ የጥናት ርዕስ የሚሆንም ነው፡፡
ታዲያ የአህመድ ተሾመ አዲስ አልበም፣ የ1990ዎቹን የዜማ መንፈስ አገኘሁበት፤ የቀድሞውን በቀጥታ ሳይደግም፣ ያንን ለዛ በአዲስ ስልተ ምት የቀነበበ ዜማ ሆኖ አዳመጥኩት። ጉዳዩን ሳይንቲፊካሊ መግለጽ ባልችልም ልቤ ግን አልበሙ በዚያን ጊዜና በዛሬው የሙዚቃ ዘመን መካከል የተዘረጋ የዜማ ድልድይ እንደሆነ ይነግረኛል።
በአጠቃላይ ለእኔ፣ የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ጊዜ አይሄድም አዲስ አልበም የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ካለፈ ጊዜና ትዝታ ጋር የተደረገ ውይይት ነው፤ ትናንትን ከዛሬ ጋር ያስታረቀ የዜማ ድልድይ ነው፤ በዘጠናዎቹ የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም ነው። ይመችሽ ዲንቢ!!
ካላመናችሁኝ ደግሞ ከአዲስ አልበሙ መካከል "ጊዜ አይሄድም"፣"አይሽና"፣ "ይረፍዳል" እና "ህልም ነው" አድመጣችሁ ፍረዱኝ፤ ካጠፋሁ እኔ ሳልሆን ዲንቢ ይቀጣል፡፡
የአህመድ ተሸመ (ዲንቢ) “ጊዜ አይሄድም”!
ተስፋዬ እሸቱ (ረ/ፕሮፌሰር)
#ethiopia | መቸም የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ድንቅ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፡፡ ለራሱ የሠራቸውን ዘግየት እናድርግና ለሌሎች የሙያ አጋሮቹ ሠርቶላቸው በብዙኋን አድማጮች ዘንድ ሰፊ ተቀባይነትን ያገኙትን የዜማ ድርሰቶቹን እንዘርዝር ብንል ጊዜም ሥፍራም አይበቃንም፡፡
እንደው ከግምታችን በላይ ስለሆነው ስለዲንቢ የላቀ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና መሠረታዊ ግንዛቤ ሊያስጨብጠን ቢችል ግን ጥቂቱን ብቻ ከዚህ እንደሚከተለው እዘረዝርላችኋለሁ፡—
ለአሊ ቢራና ሄለን በርሄ - “ሲያዴ”፤ ለፀሀዬ ዮሐንስ - “ማን ልበልሽ”፤ ለማዲንጎ አፈወርቅ - “ላላተርፍ”፤ ለብዙአየሁ ደምሴ - “የህልሜ ንግስት”፤ ለዘቢባ ግርማ - “ገራገር”፤ ለኢሳያስ ታምራት - “እያዳነ ያማል”፤ ለታረቀኝ ሙሉ - “ስሚያቸው”፤ ለሚኪያስ ቸርነት - “ግርማ ሞገሴ”፤ ለሃይማኖት ግርማ - “ከዚራ ቁ-2”፤ ለግርማ ተፈራ - “ልዩ”፤ ለሀመልማል አባተ - “ሀሴት”፤ እና የመሳሰሉቱን የአህመድ ዲንቢን የዜማ ፈጠራዎች ከብዙ በጥቂቱ ማስታወስ ይቻላል፡፡
አንዳንድ ሙዚቃዎች ለጆሮ ብቻ አይሰሩም፤ ለስሜት ይደርሳሉ፤ ዛሬ ተሰርተው ግን ትዝታችንን ይመልሱልናል፡፡
አንዳንድ ዜማዎች፣ በውስጣችን የተከረቸሙ የጊዜ በሮችን ያንኳኳሉ፤ ይከፍታሉምም፡፡ በሮቹ ሲከፈቱ ደግሞ የተዘነጉ ፊቶች፣ የተለየናቸው ጓደኞች፣ የተራመድንባቸውን ጎዳናዎች… ብቻ ምኑ ቅጡ ትላንታችንን እንደ መጽሀፍ ይገልጡልናል፡፡ በሆነ ዘመን የቀረውን ማንነታችንን እንደገና ይመልሱልናል።
አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ከ14 ዓመታት በኋላ በአዲስ አልበሙ ሲመለስ፣ እኔ የሰማሁት የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብን አይደለም። አንድ በሆነ ዘመን የነበረ የዜማ ሰዋሰውና በዚሁ ዜማ ምክንያት የተሰፋ፣ የምናፍቀውን ዘመን የመለሰልኝ ያህል ነው የተሰማኝ፡፡
ያ የኔ ዘመን የምለው “ዘጠናዎቹ”ን ነው፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሆኜ የገባሁት በ1997 ዓ.ም. ነው። አይ፣ ተማሪነት! እንዴት ያለ ጣፋጭ፣ እንዴት ያለ የማይደገም ዘመን ነበር! ያ ዘመን ለእኔ የወጣትነት ወርቃማ ጠዋት ነበር። ዓለምን እንደ አዲስ ማየት የጀመርኩበት፤ ከተማዋን፣ ሕይወትን፣ ፍቅርን፣ ሐሳብንና ነፃነትን ለመጀመሪያ ጊዜ በሙሉ ልብ ያጣጣምኩበት ዘመን ነበር።
ያ ዘመን ከጓደኞቸ ጋር እንደፈለግን የኖርንበት ዘመን ነበር። በአደባባይ የተከራከርንበት፣ አለምን የጠየቅንበት፣ መንግሥትን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቃወምንበት፣ ነፃነትን ያየንበት፣ ዜማን ያጣጣምንበት ወቅት ነበር። ያ ዘመን “ዘጠናዎቹ” ነበር፡፡
ያንን ዘመን ሁሌም እናፍቀዋለሁ፤ ምናልባትም የምናፍቀው ዘመኑን ራሱን አይደለም፤ በዚያ ዘመን ውስጥ የነበርነውን እሱን፣ እሷን፣እኔን፣እኛን ነው። እንደገና እንዲመጣም እመኛለሁ።
ማርሴል ፕሩስት የተባለ ፈረንሳያዊ የልብ ወለድ ጸሀፊና ሀያሲ ጥልቅ የሆነን ትዝታ አስበን ለማስታወስ በምናደርገው ጥረት አይመለስም፤ ነገር ግን የስሜት ሕዋሳችን በሚነካ አንድ ድንገተኛ ልምድ ሊቀሰቀስ ይችላል ይላል፡፡ ሙዚቃም ከእነዚህ የትዝታ ቀስቃሾች መካከል እጅግ ኃይለኛው ሳይሆን አይቀርም።
በዚህ ረገድ እንደ አህመድ ተሾመ ጥንቅቅ ተደርጎ የተሰራ ዜማ የተረሳ ግን ተደበቀ ስሜትን ይቀሰቅሳል፤ የጠፋ የሚመስለውን የዜማ ስልተ ምት ይመልሳል፤ በዘመን ጥላ ሥር ተደብቆ የኖረ ማንነት እንደገና ያነቃቃል።
በ1990ዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ የራሱ የሆነ የዜማ ሰዋሰው፣ ቀለምና የአወራረድ ለዛ ነበረው። ያ ዘመን ለእኔ ሙዚቃን ከመስማት ወደ ማዳመጥ የተሸጋገርኩበት ጊዜ ነው። ስለዚህ የዚያ ዘመን ዜማዎች በጆሮዬ ብቻ ተደምጠው አልቀሩም፤ በማንነቴ ውስጥ ህያው ናቸው።
እኔ የሙዚቃ ባለሙያ አይደለሁም፤ ሙዚቃን ግን በልቤ አዳምጠዋለሁ። በእኔ የዜማ አረዳድ፣ የዚያ ዘመን የዜማ አሠራሮች በቀላሉ የሚደገሙ አይደሉም። ምክንያቱም ዜማው የተፈጠረው በድምፅ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመኑ መንፈስም ጭምር ነው። ከዚያ በኋላ የመጡት ዘመናት የራሳቸውን የሙዚቃ ቋንቋ ፈጥረዋል።
ያው ዘመን ሲለወጥ የዜማ ሰዋሰውም የሚለወጥ ይመስለኛል፡፡ ይህም የሥነ ጥበብ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው፤ ዋናው ጉዳይ ግን በ1990ዎቹና ከዚያ በኋላ በመጡት ዜማዎች መካከል የተቋረጠ ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡ መቆራረጡ ለሙዚቃ ባለሙያዎች ትልቅ የጥናት ርዕስ የሚሆንም ነው፡፡
ታዲያ የአህመድ ተሾመ አዲስ አልበም፣ የ1990ዎቹን የዜማ መንፈስ አገኘሁበት፤ የቀድሞውን በቀጥታ ሳይደግም፣ ያንን ለዛ በአዲስ ስልተ ምት የቀነበበ ዜማ ሆኖ አዳመጥኩት። ጉዳዩን ሳይንቲፊካሊ መግለጽ ባልችልም ልቤ ግን አልበሙ በዚያን ጊዜና በዛሬው የሙዚቃ ዘመን መካከል የተዘረጋ የዜማ ድልድይ እንደሆነ ይነግረኛል።
በአጠቃላይ ለእኔ፣ የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ጊዜ አይሄድም አዲስ አልበም የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ካለፈ ጊዜና ትዝታ ጋር የተደረገ ውይይት ነው፤ ትናንትን ከዛሬ ጋር ያስታረቀ የዜማ ድልድይ ነው፤ በዘጠናዎቹ የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም ነው። ይመችሽ ዲንቢ!!
ካላመናችሁኝ ደግሞ ከአዲስ አልበሙ መካከል "ጊዜ አይሄድም"፣"አይሽና"፣ "ይረፍዳል" እና "ህልም ነው" አድመጣችሁ ፍረዱኝ፤ ካጠፋሁ እኔ ሳልሆን ዲንቢ ይቀጣል፡፡
Sponsored by
Surafel
Comments