19 days ago
ነገ በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ይደረጋል። ሰልፉ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።
በትግራይ ክልል እየተባባሰ የመጣውን ቀውስ ለመቃወምና ለማስቆም እንዲሁም ለፌደራል መንግስትና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ''አፈሳ ይቁም ሰላም ይስፈን'' በሚል መሪ ቃል ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፉ ይደረጋል።
ሰልፉ ተጀምሮ እስከ ሚጠናቀቅበት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
በዝህም መሰረት:-
# ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ቅ/ዑራኤል አደባባይ
# በቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባ ኦሎምፒያ አደባባይ
# ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ
# ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል ለገሀር መብራት
# ከለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታዲዮም ለገሀር ቴሌ ማቋረጫ
# ከአራት ኪሎ ወደ መሰቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ-መንግስት
# ከካሳንቺስ በመቅረዝ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ መቅረዝ ሆስፒታል አጠገብ
# ከአምባሳደር ቴአትር ወደ መሰቀል አደባባይ ሐራምቤ መብራት የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
ከዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በመስቀል አደባባይና በዙሪያው ባሉ መንገዶች ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ ለአጭርም ሆነ ረዥም ሠዓት ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።
Addis Ababa police
በትግራይ ክልል እየተባባሰ የመጣውን ቀውስ ለመቃወምና ለማስቆም እንዲሁም ለፌደራል መንግስትና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ''አፈሳ ይቁም ሰላም ይስፈን'' በሚል መሪ ቃል ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፉ ይደረጋል።
ሰልፉ ተጀምሮ እስከ ሚጠናቀቅበት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
በዝህም መሰረት:-
# ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ቅ/ዑራኤል አደባባይ
# በቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባ ኦሎምፒያ አደባባይ
# ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ
# ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል ለገሀር መብራት
# ከለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታዲዮም ለገሀር ቴሌ ማቋረጫ
# ከአራት ኪሎ ወደ መሰቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ-መንግስት
# ከካሳንቺስ በመቅረዝ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ መቅረዝ ሆስፒታል አጠገብ
# ከአምባሳደር ቴአትር ወደ መሰቀል አደባባይ ሐራምቤ መብራት የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
ከዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በመስቀል አደባባይና በዙሪያው ባሉ መንገዶች ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ ለአጭርም ሆነ ረዥም ሠዓት ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።
Addis Ababa police
20 days ago
ነገ በአዲስ አበባ ለሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆኑ‼️
ሰልፉ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።
በትግራይ ክልል እየተባባሰ የመጣውን ቀውስ ለመቃወምና ለማስቆም እንዲሁም ለፌደራል መንግሥትና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ”አፈሳ ይቁም ሰላም ይስፈን” በሚል መሪ ቃል ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፉ ይደረጋል።
ሰልፉ ተጀምሮ እስከ ሚጠናቀቅበት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
በዚህም መሰረት:-
👉 ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ቅ/ዑራኤል አደባባይ
👉 በቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባ ኦሎምፒያ አደባባይ
👉 ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ
👉 ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል ለገሀር መብራት
👉 ከለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታዲዮም ለገሀር ቴሌ ማቋረጫ
👉 ከአራት ኪሎ ወደ መሰቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ-መንግስት
👉ከካሳንቺስ በመቅረዝ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ መቅረዝ ሆስፒታል አጠገብ
👉ከአምባሳደር ቴአትር ወደ መስቀል አደባባይ ሐራምቤ መብራት የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
ከዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በመስቀል አደባባይና በዙሪያው ባሉ መንገዶች ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ ለአጭርም ሆነ ረዥም ሠዓት ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
ሰልፉ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።
በትግራይ ክልል እየተባባሰ የመጣውን ቀውስ ለመቃወምና ለማስቆም እንዲሁም ለፌደራል መንግሥትና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ”አፈሳ ይቁም ሰላም ይስፈን” በሚል መሪ ቃል ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፉ ይደረጋል።
ሰልፉ ተጀምሮ እስከ ሚጠናቀቅበት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
በዚህም መሰረት:-
👉 ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ቅ/ዑራኤል አደባባይ
👉 በቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባ ኦሎምፒያ አደባባይ
👉 ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ
👉 ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል ለገሀር መብራት
👉 ከለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታዲዮም ለገሀር ቴሌ ማቋረጫ
👉 ከአራት ኪሎ ወደ መሰቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ-መንግስት
👉ከካሳንቺስ በመቅረዝ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ መቅረዝ ሆስፒታል አጠገብ
👉ከአምባሳደር ቴአትር ወደ መስቀል አደባባይ ሐራምቤ መብራት የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
ከዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በመስቀል አደባባይና በዙሪያው ባሉ መንገዶች ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ ለአጭርም ሆነ ረዥም ሠዓት ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
የእሥራኤል 78ኛ ዓመት የነፃነት ቀን፤
የሰባ ዓመታት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት
#ethiopia | በአዲስ አበባ የሚገኘው የእሥራኤል ኤምባሲ የሀገሪቱን 78ኛ ዓመት የነፃነት ቀን ዮም ሃአትዝማውትን ደማቅ በሆነ ስነ ስርዓት አክብሯል።
በዓሉ በእሥራኤል የቀን አቆጣጠር መሰረት በሚያዝያ ወር መከበር የነበረበት ቢሆንም በወቅቱ በነበሩ አካባቢያዊ ክስተቶች ሳቢያ ወደ ሌላ ጊዜ መሸጋገሩ ተገልጾ በተለይ የዕለቱ የክብር እንግዶች ላሳዩት ትዕግስትና ላበረከቱት ወዳጅነት ምስጋና ቀርቧል።
በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የእሥራኤል አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ንጉሤ ሀገራቸው እ.ኤ.አ. በ1948 ነፃነቷን ካወጀችበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የህልውና ፈተናዎችን በጽናት መወጣቷን አስታውሰዋል።
እሥራኤል በዘመናዊ መዋቅር የ78 ዓመት ወጣት ሀገር ብትሆንም ታሪኳ ከአብርሃምና ከሙሴ ዘመን የሚቀዳ የ4 ሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርስና የነፃነት ታሪክ መሠረት እንዳለው አብራርተዋል።
ይህ የዘንድሮ በዓል በኢትዮጵያና በእሥራኤል መካከል የተጀመረውን ዘመናዊ የሁለትዮሽ መደበኛ ግንኙነት 70ኛ ዓመት ወርቃማ ኢዮቤልዩ የሚዘክር በመሆኑ ልዩ ትርጉም አለው።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ሰፊ ገለጻ አኳያ እ.ኤ.አ. በ1956 በአዲስ አበባ የመጀመሪያው የእሥራኤል ቆንስላ መከፈቱ ለዘመናዊው ትስስር መነሻ ቢሆንም የሁለቱ ሕዝቦች ወዳጅነት ግን በንግሥተ ሳባና በንጉሥ ሰሎሞን ታሪክ ላይ የተገነባ የ3 ሺህ ዓመታት ጥልቅ ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑ ተገልጿል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከ1973 እስከ 1989 ላለፉት 16 ዓመታት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም በሕዝቦች ልብ ውስጥ ባለው ጠንካራ ትስስር ምክንያት ይበልጥ በጠነከረ መሠረት ላይ ሊመለስ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቱ እጅግ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ባለፉት ወራት የእስራኤሉ ፕሬዚዳንት ይስሐቅ ሄርዞግ በአዲስ አበባ ያደረጉት ታሪካዊ ጉብኝት እንዲሁም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሐደራ አበራ በእስራኤል ያደረጉት የፖለቲካ ምክክር የዚህ ማረጋገጫዎች ናቸው ብለዋል።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም አያይዘውም ሀገራቱ በማሻቭ በኩል በግብርና ቴክኖሎጂ፣ በውሃ አጠቃቀም፣ በጤና እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች በጋራ እያከናወኗቸው ያሉ የልማት ሥራዎች ስኬታማ መሆናቸው ተነስቷል። የባህል ትስስሩን ይበልጥ ለማሳደግም በቅርቡ የሁለቱ ሀገራት የሙዚቃ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የእሥራኤል-ኢትዮጵያ የባህል ምሽት ተካሂዷል።
ከ35 ዓመታት በፊት በሰሎሞን ዘመቻ በ36 ሰዓታት ውስጥ ከ14 ሺህ በላይ የቤተ እሥራኤል ማህበረሰብ አባላት ወደ እስራኤል መጓዛቸውና በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸው ከ180 ሺህ በላይ የደረሱት ቤተእስራኤላውያን ለሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዋነኛ የሕዝብ ድልድይ መሆናቸው አውስተዋል።
በመጨረሻም ጥቅምት 2023 የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እሥራኤል አሁንም የደኅንነት ስጋቶች ቢገጥሟትም የታገቱ ዜጎቿን በሙሉ ባለፈው ጥቅምት ወር ማስመለስ መቻሏ ትልቅ እፎይታን የፈጠረ ሲሆን የሀገሪቱ ኢኮኖሚና ቴክኖሎጂ አሁንም በጠንካራ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ ለሦስት ዓመታት በምክትል አምባሳደርነት ያገለገሉትን ቶመር ባር-ላቪን የሥራ ዘመን መጠናቀቅን አስመልክቶ በኤምባሲው ስም ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና የቀረበላቸው ሲሆን የበዓሉ ታዳሚዎች በባህላዊ የሙዚቃና የምግብ ዝግጅቶች እጅግ ደስ የሚል ጊዜን አሳልፈዋል።
በዚህ ልዩ የክብር ሥነ ሥርዓት ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰሎሞን ሶካ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምስራቅ፣ እስያና ፓስፊክ ሀገራት ጉዳዮች ምክትል ዋና ዳይሬክተር አምሃ ኃይለጊዮርጊስ፣ የፓርላማ አባላት፣ አምባሳደሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።
#israel #yomhaatzmaut #ethioisrael #diplomacy #history #culture #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የሰባ ዓመታት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት
#ethiopia | በአዲስ አበባ የሚገኘው የእሥራኤል ኤምባሲ የሀገሪቱን 78ኛ ዓመት የነፃነት ቀን ዮም ሃአትዝማውትን ደማቅ በሆነ ስነ ስርዓት አክብሯል።
በዓሉ በእሥራኤል የቀን አቆጣጠር መሰረት በሚያዝያ ወር መከበር የነበረበት ቢሆንም በወቅቱ በነበሩ አካባቢያዊ ክስተቶች ሳቢያ ወደ ሌላ ጊዜ መሸጋገሩ ተገልጾ በተለይ የዕለቱ የክብር እንግዶች ላሳዩት ትዕግስትና ላበረከቱት ወዳጅነት ምስጋና ቀርቧል።
በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የእሥራኤል አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ንጉሤ ሀገራቸው እ.ኤ.አ. በ1948 ነፃነቷን ካወጀችበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የህልውና ፈተናዎችን በጽናት መወጣቷን አስታውሰዋል።
እሥራኤል በዘመናዊ መዋቅር የ78 ዓመት ወጣት ሀገር ብትሆንም ታሪኳ ከአብርሃምና ከሙሴ ዘመን የሚቀዳ የ4 ሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርስና የነፃነት ታሪክ መሠረት እንዳለው አብራርተዋል።
ይህ የዘንድሮ በዓል በኢትዮጵያና በእሥራኤል መካከል የተጀመረውን ዘመናዊ የሁለትዮሽ መደበኛ ግንኙነት 70ኛ ዓመት ወርቃማ ኢዮቤልዩ የሚዘክር በመሆኑ ልዩ ትርጉም አለው።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ሰፊ ገለጻ አኳያ እ.ኤ.አ. በ1956 በአዲስ አበባ የመጀመሪያው የእሥራኤል ቆንስላ መከፈቱ ለዘመናዊው ትስስር መነሻ ቢሆንም የሁለቱ ሕዝቦች ወዳጅነት ግን በንግሥተ ሳባና በንጉሥ ሰሎሞን ታሪክ ላይ የተገነባ የ3 ሺህ ዓመታት ጥልቅ ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑ ተገልጿል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከ1973 እስከ 1989 ላለፉት 16 ዓመታት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም በሕዝቦች ልብ ውስጥ ባለው ጠንካራ ትስስር ምክንያት ይበልጥ በጠነከረ መሠረት ላይ ሊመለስ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቱ እጅግ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ባለፉት ወራት የእስራኤሉ ፕሬዚዳንት ይስሐቅ ሄርዞግ በአዲስ አበባ ያደረጉት ታሪካዊ ጉብኝት እንዲሁም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሐደራ አበራ በእስራኤል ያደረጉት የፖለቲካ ምክክር የዚህ ማረጋገጫዎች ናቸው ብለዋል።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም አያይዘውም ሀገራቱ በማሻቭ በኩል በግብርና ቴክኖሎጂ፣ በውሃ አጠቃቀም፣ በጤና እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች በጋራ እያከናወኗቸው ያሉ የልማት ሥራዎች ስኬታማ መሆናቸው ተነስቷል። የባህል ትስስሩን ይበልጥ ለማሳደግም በቅርቡ የሁለቱ ሀገራት የሙዚቃ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የእሥራኤል-ኢትዮጵያ የባህል ምሽት ተካሂዷል።
ከ35 ዓመታት በፊት በሰሎሞን ዘመቻ በ36 ሰዓታት ውስጥ ከ14 ሺህ በላይ የቤተ እሥራኤል ማህበረሰብ አባላት ወደ እስራኤል መጓዛቸውና በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸው ከ180 ሺህ በላይ የደረሱት ቤተእስራኤላውያን ለሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዋነኛ የሕዝብ ድልድይ መሆናቸው አውስተዋል።
በመጨረሻም ጥቅምት 2023 የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እሥራኤል አሁንም የደኅንነት ስጋቶች ቢገጥሟትም የታገቱ ዜጎቿን በሙሉ ባለፈው ጥቅምት ወር ማስመለስ መቻሏ ትልቅ እፎይታን የፈጠረ ሲሆን የሀገሪቱ ኢኮኖሚና ቴክኖሎጂ አሁንም በጠንካራ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ ለሦስት ዓመታት በምክትል አምባሳደርነት ያገለገሉትን ቶመር ባር-ላቪን የሥራ ዘመን መጠናቀቅን አስመልክቶ በኤምባሲው ስም ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና የቀረበላቸው ሲሆን የበዓሉ ታዳሚዎች በባህላዊ የሙዚቃና የምግብ ዝግጅቶች እጅግ ደስ የሚል ጊዜን አሳልፈዋል።
በዚህ ልዩ የክብር ሥነ ሥርዓት ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰሎሞን ሶካ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምስራቅ፣ እስያና ፓስፊክ ሀገራት ጉዳዮች ምክትል ዋና ዳይሬክተር አምሃ ኃይለጊዮርጊስ፣ የፓርላማ አባላት፣ አምባሳደሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።
#israel #yomhaatzmaut #ethioisrael #diplomacy #history #culture #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ኳሷ በተከላካዮች መሃል መሬት ለመሬት ተሰንጥቃ ለህዋንግ ኢን-ቢዮም ስትደርሰው... ተጫዋቹ ያሳየው መረጋጋት እና ኳሷን በጥበብ ወደ ቀኝ እግሩ ያጠፈበት መንገድ እጅግ ያስደምማል። ደቡብ ኮሪያውያን በሜዳው ላይ የተሻለ ብልጫ ሲያሳዩ ስለነበር፣ ይህች ግብ በእርግጥም የልፋታቸው ፍሬ ናት።
አጥቂው ተከላካዩን በሚያምር ሁኔታ አታሎ... ግብ ጠባቂውንም ጭምር በብልሃት በማስቀረት ነው ኳሷን ከመረብ ያዋሃዳት። ኳሷን በጥበብ ቀለል አድርጎ በማንሳት (በቺፕ) ሩቅ ወዳለው የግብ ማዕዘን ሲያስቆጥራት ያሳየው አጨራረስ በእውነትም የክህሎቱ ማሳያ ነበር! #worldcup
አጥቂው ተከላካዩን በሚያምር ሁኔታ አታሎ... ግብ ጠባቂውንም ጭምር በብልሃት በማስቀረት ነው ኳሷን ከመረብ ያዋሃዳት። ኳሷን በጥበብ ቀለል አድርጎ በማንሳት (በቺፕ) ሩቅ ወዳለው የግብ ማዕዘን ሲያስቆጥራት ያሳየው አጨራረስ በእውነትም የክህሎቱ ማሳያ ነበር! #worldcup
Sponsored by
Surafel
2 months ago
"በመጀመርያ አርሲ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው የሞት አደጋ የተሰማኝን ሀዘን እየገለፅኩ ሀዘኑ የደረሰባቹ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ፈጣሪ መፅናናቱን እንዲስጠን እየፀለይኩ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ እስታድዮም ላቀርበው የነበረው የሙዚቃ ዝግጅት መሰረዜን እና ኮንሰርቱንም እማልሳተፍ መሆኔን በትህትና እገልፃለሁ ። በስተመጨረሻም ለኤቨንቱ አዘጋጆች ለተፈጠረው ነገር እጅግ ይቅርታ እጠይቃለሁ። እግዝያብሔር ይብቃቹ ይበለን!"
ድምጻዊ ታደለ ሮባ
ድምጻዊ ታደለ ሮባ
2 months ago
የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ሶላት በመጠናቀቁ ለተሽከርካሪ ዝግ የነበሩ መንገዶች ተከፍተዋል
#ethiopia | የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓልን አስመልክቶ የእስልምና እምነት ተከታዮች በአዲስ አበባ ስታዲዮም የሶላት ስነ- ስርዓት አካሂደዋል።
የኃይማኖት አባቶች እና የእምነቱ ተከታዮች፣ የውጭ ሀገር ዜጎች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የተካሄደው የሶላት ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡
የሶላት ስነ-ስርዓቱ እስከሚጠናቀቅ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም ተብሎ ለተሽከርካሪ ዝግ የነበሩ መንገዶቸ መከፈታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
ለፕሮግራሙ ስኬታማነት አስተዋፆኦ ላደረጉ አካላት፣ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ የፀጥታ ተቋማት አመራሮች እና አባላት ዋና ጠቅላይ መምሪያው ምስጋናውን በማቅረብ ለመላው የእምነቱ ተከታዮች በዓሉ የሠላም እና የደስታ እንዲሆንም መልካም ምኞቱን ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓልን አስመልክቶ የእስልምና እምነት ተከታዮች በአዲስ አበባ ስታዲዮም የሶላት ስነ- ስርዓት አካሂደዋል።
የኃይማኖት አባቶች እና የእምነቱ ተከታዮች፣ የውጭ ሀገር ዜጎች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የተካሄደው የሶላት ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡
የሶላት ስነ-ስርዓቱ እስከሚጠናቀቅ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም ተብሎ ለተሽከርካሪ ዝግ የነበሩ መንገዶቸ መከፈታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
ለፕሮግራሙ ስኬታማነት አስተዋፆኦ ላደረጉ አካላት፣ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ የፀጥታ ተቋማት አመራሮች እና አባላት ዋና ጠቅላይ መምሪያው ምስጋናውን በማቅረብ ለመላው የእምነቱ ተከታዮች በዓሉ የሠላም እና የደስታ እንዲሆንም መልካም ምኞቱን ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 months ago
በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት ያደረጉ 13 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ
የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት ያደረጉ 13 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ።
ተከሳሾቹም 1ኛ አቶ ዲባራ ፉፋ፣ 2ኛ አቶ ሹምአለም ብርሃኔ፣ 3ኛ አቶ እስጢፋኖስ ጌትነት፣ 4ኛ አቶ ይላቅ አወቀ፣ 5ኛ አቶ አበላ ግዛው፣ 6ኛ አቶ ጌታቸው አሞኘ፣ 7ኛ ወ/ሮ በረከት ወርቁ፣ 8ኛ አቡሽ አያለ ገነት፣ 9ኛ አቶ ይልቃል የኔሰው፣ 10ኛ የኛ ፔትሮሊዮም ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ 11ኛ አቶ እስማለም ምህረቱ፣ 12ኛ አቶ አባይነህ አወል እና 13ኛ አቶ ብስራት አበባው ናቸው።
ተከሳሾቹ ከ70 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ነዳጅና ነጭ ናፍጣ ከመንግሥት ቁጥጥር ውጭ በማድረግ በገበያ ላይ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጋቸው በክሱ ላይ ተመላክቷል፡፡
የክስ መዝገቡ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ቀርቧል፡፡
1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች እንደ ቅደምተከተላቸው የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርና የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ክትትል ባለሙያ ከኩባንያዎች በቀጥታ በመግዛት ለሚጠቀሙ ተቋማት የፍቃድ አሰጣጥ መመሪያ መተላለፋቸው በክሱ ተመላክቷል፡፡
ሦስቱ ተከሳሾች በግል የሥራ ዘርፍ ከተሰማራችው 7ኛ ተከሳሽ ጋር በመመሳጠር 466 ሺህ 58 ሊትር ነጭ ናፍጣ ያለአግባብ እንድታገኝና በኮንትሮባንድ ለወርቅ አምራቾች እንድትሸጥ ማድረጋቸው በክሱ ላይ ተጠቅሷል፡፡
በመንግሥት ላይ ከ8 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት እንዲደርስና በገበያ ላይ እጥረት እንዲከሰት በማድረግ ስልጣንን ያለአግባብ መገልግል ከባድ የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ሲል ዐቃቤ ህግ አስረድቷል፡፡
በሌላ በኩል በ2ኛ ክስ 1ኛ፣ 6ኛ እና 8ኛ ተከሳሾች በጥቅም በመመሳጠር 8ኛ ተከሳሽ በድምሩ ከ1 ሚሊየን 284 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ያለአግባብ እንዲያገኝ በማድረግ በመንግሥት ላይ ከ22 ነጥብ 59 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት እንዲደርስና የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል ብሏል፡፡
በዚህም 1ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት እንዲሁም 8ኛ ተከሳሽ በልዩ ወንጀል አድራጊነት ስልጣንን ያለአግባብ በመገልግል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡
በ3ኛ ክስ 9ኛ ተከሳሽ (የኛ ፔትሮሊዮም ኃ/የተ/የግ/ማህበር ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ) ከህግ አግባብ ውጪ የነዳጅ አከፋፋይነት ፍቃድ እንዲያገኝ በማድረግ በመንግሥት ላይ ከ21 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ላይ ጉዳት መድረሱን ክሱ ያመለክታል፡፡
በዚህም መሰረት 1ኛ፣ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት እንዲሁም 9ኛ ተከሳሽ በልዩ ወንጀል አድራጊነት በፈጸሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልግል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል።
በ4ኛው ክስ ላይ 11ኛ፣ 12ኛ እና 13ኛ ተከሳሾች የነዳጅ ጭነትና ግዥ ሀገር አቀፍ የነዳጅ ሰንሰለት ስርዓትን በመጣስ በአጠቃላይ 1 ነጥብ 9 ሚሊየን ሊትር ነዳጅ መንግሥት እንዳይቆጣጠረው ማድረጋቸውን ክሱ አመልክቷል፡፡
በዚህም መንግሥት ድጎማ ያደረገበትን ነዳጅ ከጅቡቲ በመጫን 17 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በላይና በገንዘብ የማይገመት ጉዳት በማድረስ በዋና ወንጀል አድራጊነት የመንግሥትን ሥራ በማይመች አኳኋን በመምራት ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል።
በ5ኛው ክስ ላይ 11ኛ ተከሳሽ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 346 የብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ (ማሻሻያ) አዋጅ ቁጥር 1359/2017 አንቀጽ 51(1)(መ) እንዲሁም ብሔራዊ ባንክ ያወጣውን መመሪያ ቁጥር FXD/04/2024” አንቀጽ 22.8.5/ለ ስር ላይ የተመለከተውን በመተላለፉ ክስ ተመስርቷል።
በዚህም ተከሳሹ በዕለቱ ለመያዝ ምንም አይነት ፍቃድ ሳይኖረው በቀን 30/07/2018 ዓ.ም ከቀኑ በግምት 10፡30 ሰዓት ሲሆን፤ ከፍርድ ቤት በስልክ በተገኘ የብርበራ ፍቃድ ቂርቆስ ክ/ከተማ በሚገኘው የመኖሪያ ቤቱ እና በቢሮ ላይ በተደረገ ብርበራ 1ኛ 58 ሺህ 503 የአሜሪካን ዶላር 2ኛ 6 ሺህ 250 ዩሮ 3ኛ 630 የእንግሊዝ ፓወንድ አስቀምጦ የተገኘ በመሆኑ በፈጸመው በህገ ወጥ መንገድ የውጭ ሀገር ገንዘብ ያለፈቃድ መያዝ/ማስቀመጥ ወንጀል ተከሷል፡፡
ፍርድ ቤቱ የክስ መቃወሚያ ለመስማት ለግንቦት 10 ቀጠሮ መያዙ ተገልጿል።
Fbc
የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት ያደረጉ 13 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ።
ተከሳሾቹም 1ኛ አቶ ዲባራ ፉፋ፣ 2ኛ አቶ ሹምአለም ብርሃኔ፣ 3ኛ አቶ እስጢፋኖስ ጌትነት፣ 4ኛ አቶ ይላቅ አወቀ፣ 5ኛ አቶ አበላ ግዛው፣ 6ኛ አቶ ጌታቸው አሞኘ፣ 7ኛ ወ/ሮ በረከት ወርቁ፣ 8ኛ አቡሽ አያለ ገነት፣ 9ኛ አቶ ይልቃል የኔሰው፣ 10ኛ የኛ ፔትሮሊዮም ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ 11ኛ አቶ እስማለም ምህረቱ፣ 12ኛ አቶ አባይነህ አወል እና 13ኛ አቶ ብስራት አበባው ናቸው።
ተከሳሾቹ ከ70 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ነዳጅና ነጭ ናፍጣ ከመንግሥት ቁጥጥር ውጭ በማድረግ በገበያ ላይ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጋቸው በክሱ ላይ ተመላክቷል፡፡
የክስ መዝገቡ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ቀርቧል፡፡
1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች እንደ ቅደምተከተላቸው የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርና የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ክትትል ባለሙያ ከኩባንያዎች በቀጥታ በመግዛት ለሚጠቀሙ ተቋማት የፍቃድ አሰጣጥ መመሪያ መተላለፋቸው በክሱ ተመላክቷል፡፡
ሦስቱ ተከሳሾች በግል የሥራ ዘርፍ ከተሰማራችው 7ኛ ተከሳሽ ጋር በመመሳጠር 466 ሺህ 58 ሊትር ነጭ ናፍጣ ያለአግባብ እንድታገኝና በኮንትሮባንድ ለወርቅ አምራቾች እንድትሸጥ ማድረጋቸው በክሱ ላይ ተጠቅሷል፡፡
በመንግሥት ላይ ከ8 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት እንዲደርስና በገበያ ላይ እጥረት እንዲከሰት በማድረግ ስልጣንን ያለአግባብ መገልግል ከባድ የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ሲል ዐቃቤ ህግ አስረድቷል፡፡
በሌላ በኩል በ2ኛ ክስ 1ኛ፣ 6ኛ እና 8ኛ ተከሳሾች በጥቅም በመመሳጠር 8ኛ ተከሳሽ በድምሩ ከ1 ሚሊየን 284 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ያለአግባብ እንዲያገኝ በማድረግ በመንግሥት ላይ ከ22 ነጥብ 59 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት እንዲደርስና የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል ብሏል፡፡
በዚህም 1ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት እንዲሁም 8ኛ ተከሳሽ በልዩ ወንጀል አድራጊነት ስልጣንን ያለአግባብ በመገልግል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡
በ3ኛ ክስ 9ኛ ተከሳሽ (የኛ ፔትሮሊዮም ኃ/የተ/የግ/ማህበር ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ) ከህግ አግባብ ውጪ የነዳጅ አከፋፋይነት ፍቃድ እንዲያገኝ በማድረግ በመንግሥት ላይ ከ21 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ላይ ጉዳት መድረሱን ክሱ ያመለክታል፡፡
በዚህም መሰረት 1ኛ፣ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት እንዲሁም 9ኛ ተከሳሽ በልዩ ወንጀል አድራጊነት በፈጸሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልግል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል።
በ4ኛው ክስ ላይ 11ኛ፣ 12ኛ እና 13ኛ ተከሳሾች የነዳጅ ጭነትና ግዥ ሀገር አቀፍ የነዳጅ ሰንሰለት ስርዓትን በመጣስ በአጠቃላይ 1 ነጥብ 9 ሚሊየን ሊትር ነዳጅ መንግሥት እንዳይቆጣጠረው ማድረጋቸውን ክሱ አመልክቷል፡፡
በዚህም መንግሥት ድጎማ ያደረገበትን ነዳጅ ከጅቡቲ በመጫን 17 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በላይና በገንዘብ የማይገመት ጉዳት በማድረስ በዋና ወንጀል አድራጊነት የመንግሥትን ሥራ በማይመች አኳኋን በመምራት ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል።
በ5ኛው ክስ ላይ 11ኛ ተከሳሽ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 346 የብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ (ማሻሻያ) አዋጅ ቁጥር 1359/2017 አንቀጽ 51(1)(መ) እንዲሁም ብሔራዊ ባንክ ያወጣውን መመሪያ ቁጥር FXD/04/2024” አንቀጽ 22.8.5/ለ ስር ላይ የተመለከተውን በመተላለፉ ክስ ተመስርቷል።
በዚህም ተከሳሹ በዕለቱ ለመያዝ ምንም አይነት ፍቃድ ሳይኖረው በቀን 30/07/2018 ዓ.ም ከቀኑ በግምት 10፡30 ሰዓት ሲሆን፤ ከፍርድ ቤት በስልክ በተገኘ የብርበራ ፍቃድ ቂርቆስ ክ/ከተማ በሚገኘው የመኖሪያ ቤቱ እና በቢሮ ላይ በተደረገ ብርበራ 1ኛ 58 ሺህ 503 የአሜሪካን ዶላር 2ኛ 6 ሺህ 250 ዩሮ 3ኛ 630 የእንግሊዝ ፓወንድ አስቀምጦ የተገኘ በመሆኑ በፈጸመው በህገ ወጥ መንገድ የውጭ ሀገር ገንዘብ ያለፈቃድ መያዝ/ማስቀመጥ ወንጀል ተከሷል፡፡
ፍርድ ቤቱ የክስ መቃወሚያ ለመስማት ለግንቦት 10 ቀጠሮ መያዙ ተገልጿል።
Fbc
3 months ago
ኢራን የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቿን በአሜሪካ ታደርጋለች - ፊፋ
****************
ኢራን የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቿን በአሜሪካ እንደምታከናውን የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ማኅበር (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በድጋሚ አረጋገጡ።
ኢንፋንቲኖ ይህንን ያስታወቁት በቫንኩቨር፣ ካናዳ መካሄድ የጀመረውን የፊፋ ጉባኤን በንግግር በከፈቱበት ወቅት ነው።
በመካከለኛው ምሥራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ኢራን በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና አሜሪካ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ስለመሳተፏ ጥርጣሬ ላይ ወድቆ ነበር።
ይሁን እንጂ ኢንፋንቲኖ ለጉባኤው በሰጡት መግለጫ፣ "በመጀመሪያ ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው ኢራን በ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ ላይ በእርግጠኝነት ትሳተፋለች፤ ጨዋታዎቿንም በአሜሪካ ታደርጋለች" ብለዋል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፊፋው ፕሬዚዳንት መግለጫ በኋላ ስለሁኔታው ተጠይቀው በሰጡት መልስ፣ “አዎ መጫወት ይችላሉ” ሲሉ መመለሳቸውን አናዶሉ ዘግቧል።
ቀደም ሲል የኢራን ባለሥልጣናት የምድብ ጨዋታዎቻቸው ከአሜሪካ ወደ ሜክሲኮ እንዲዛወሩ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም፣ ጥያቄው በፊፋው ፕሬዚዳንት ጁሊያኒ ኢንፋንቲኖ ውድቅ ተደርጎ ነበር።
ባለፈው ሳምንት ደግሞ የጣሊያን ተወላጅ የሆኑት የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ፓውሎ ዛምፖሊ "ከዓለም ዋንጫ ተሳትፎው ኢራን ተቀንሳ ጣሊያን ትተካ" የሚል ሐሳብ አቅርበው የነበረ ቢሆንም፣ የአሜሪካ መንግሥት ከዚህ ሐሳብ ራሱን ማራቁን የዘገበው ደግሞ ቲአርቲ ነው።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮም የኢራን እግር ኳስ ተጫዋቾች በአሜሪካ መልካም አቀባበል እንደሚደረግላቸው መግለጻቸው ይታወሳል።
#ebc #worldcup #iran #usa #fifa
****************
ኢራን የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቿን በአሜሪካ እንደምታከናውን የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ማኅበር (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በድጋሚ አረጋገጡ።
ኢንፋንቲኖ ይህንን ያስታወቁት በቫንኩቨር፣ ካናዳ መካሄድ የጀመረውን የፊፋ ጉባኤን በንግግር በከፈቱበት ወቅት ነው።
በመካከለኛው ምሥራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ኢራን በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና አሜሪካ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ስለመሳተፏ ጥርጣሬ ላይ ወድቆ ነበር።
ይሁን እንጂ ኢንፋንቲኖ ለጉባኤው በሰጡት መግለጫ፣ "በመጀመሪያ ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው ኢራን በ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ ላይ በእርግጠኝነት ትሳተፋለች፤ ጨዋታዎቿንም በአሜሪካ ታደርጋለች" ብለዋል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፊፋው ፕሬዚዳንት መግለጫ በኋላ ስለሁኔታው ተጠይቀው በሰጡት መልስ፣ “አዎ መጫወት ይችላሉ” ሲሉ መመለሳቸውን አናዶሉ ዘግቧል።
ቀደም ሲል የኢራን ባለሥልጣናት የምድብ ጨዋታዎቻቸው ከአሜሪካ ወደ ሜክሲኮ እንዲዛወሩ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም፣ ጥያቄው በፊፋው ፕሬዚዳንት ጁሊያኒ ኢንፋንቲኖ ውድቅ ተደርጎ ነበር።
ባለፈው ሳምንት ደግሞ የጣሊያን ተወላጅ የሆኑት የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ፓውሎ ዛምፖሊ "ከዓለም ዋንጫ ተሳትፎው ኢራን ተቀንሳ ጣሊያን ትተካ" የሚል ሐሳብ አቅርበው የነበረ ቢሆንም፣ የአሜሪካ መንግሥት ከዚህ ሐሳብ ራሱን ማራቁን የዘገበው ደግሞ ቲአርቲ ነው።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮም የኢራን እግር ኳስ ተጫዋቾች በአሜሪካ መልካም አቀባበል እንደሚደረግላቸው መግለጻቸው ይታወሳል።
#ebc #worldcup #iran #usa #fifa
5 months ago
በረመዳን መጨረሻ እናታቸውን በወርቅ ስጦታ ያስደነገጡት ፓኪስታናዊ ወንድማማቾች
በፓኪስታን እስላማባድ የሚኖሩ ሦስት ወንድማማቾች፣ ረመዳንን ሙሉ በሰህርና ኢፍጣር ስታገለግላቸው ለከረመችው እናታቸው የከበረ የወርቅ ቀለበት በድንገት በስጦታ በማበርከት አስደንግጠዋታል።
ይህንን ተግባራቸውን "ሀቅ አል-ሙልህ" (የድካም ዋጋ) በማለት የገለጹት ልጆቹ፣ እናታቸው በመስዋዕትነቷ ተገቢውን እውቅና እንድታገኝ ፈልገዋል።
እናትየው በልጆቿ አንድነትና ፍቅር ተደስታ ምርቃቷን የለገሰች ሲሆን፣ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው ቪዲዮም የብዙዎችን ልብ ነክቷል።
ድርጊቱ ወጣቶች ለወላጆቻቸው ሊኖራቸው የሚገባውን ክብርና እንክብካቤ የሚያሳይ ግሩም አርአያ ነው ሲሉ በርካቶች በማህበራዊ ሚዲያ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በፓኪስታን እስላማባድ የሚኖሩ ሦስት ወንድማማቾች፣ ረመዳንን ሙሉ በሰህርና ኢፍጣር ስታገለግላቸው ለከረመችው እናታቸው የከበረ የወርቅ ቀለበት በድንገት በስጦታ በማበርከት አስደንግጠዋታል።
ይህንን ተግባራቸውን "ሀቅ አል-ሙልህ" (የድካም ዋጋ) በማለት የገለጹት ልጆቹ፣ እናታቸው በመስዋዕትነቷ ተገቢውን እውቅና እንድታገኝ ፈልገዋል።
እናትየው በልጆቿ አንድነትና ፍቅር ተደስታ ምርቃቷን የለገሰች ሲሆን፣ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው ቪዲዮም የብዙዎችን ልብ ነክቷል።
ድርጊቱ ወጣቶች ለወላጆቻቸው ሊኖራቸው የሚገባውን ክብርና እንክብካቤ የሚያሳይ ግሩም አርአያ ነው ሲሉ በርካቶች በማህበራዊ ሚዲያ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
5 months ago
"ዮም" የተሰኘ በኦቲዝም ዙሪያ የሚያጠነጥነው የእውነተኛ ታሪክ መጽሐፍ ለንባብ በቃ
በኦቲዝም ጥላ ስር ያለ ልጅ ያለው አባት ልጁን ለማሳደግ የሚያልፈበትን እውነተኛ የሕይወት ውጣ ውረድ የሚተርከውና "ዮም" የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በሳምንቱ መጨረሻ ተመርቆ ለንባብ በቅቷል።
በደራሲ ንሴብሖ ፍቅሬ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ፣ በኦቲዝም ጥላ ስር ያሉ ልጆች የሚገጥሟቸውን ማኅበራዊ ጫናዎችና ቤተሰቦቻቸው የሚጋፈጡትን መሪር የሕይወት ፈተና ከራሳቸው ገጠመኝ በመነሳት በዝርዝር ዳስሰዋል።
መጽሃፉ በዚህ የህይወት ሰልፍ ውስጥ ያሉ ልጆችን ህይወት በማሳየት ለበርካት ቤተሰቦች መንገድ መሪ መሆን የሚችል መሆኑ በምርቃት መድረኩ ተገልጿል፡፡
ደራሲው የ11 ዓመት ዕድሜ ያለው "ዮም" የተባለ በኦቲዝም ጥላ ስር ያለ ልጅ አባት ሲሆኑ፣ ልጃቸው የሕይወት ዘመን ክትትልና ድጋፍ የሚሻ በመሆኑ ሁኔታው በቤተሰቡ ላይ የሚፈጥረው ጫና ማለቂያ የሌለው መሆኑን በመጽሐፋቸው ገልጸዋል።
በመሆኑም ይህ ችግር በአንድ ቤተሰብ ጥረት ብቻ የሚፈታ ሳይሆን ማኅበረሰቡ፣ የግል ድርጅቶችና መንግሥት በጋራ ሊረባረቡበት እንደሚገባ ደራሲው አጽንኦት ሰጥተዋል።
በተለይም ትምህርት ቤቶች ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ልጆች ተቀብለው ለማስተማርና ተገቢውን ትኩረት ለመስጠት ዝግጁ ሊሆኑ እንደሚገባ ደራሲ ንሴብሖ ከራሳቸው የሕይወት ተሞክሮ በመነሳት ጥሪ አቅርበዋል።
በ254 ገጾች ተቀንብቦ ለንባብ የበቃው ይህ መጽሐፍ፣ በዘርፉ ያለውን የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላትና ለሌሎች ወላጆችም የሞራል ጥንካሬ ለመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል።
በኦቲዝም ጥላ ስር ያለ ልጅ ያለው አባት ልጁን ለማሳደግ የሚያልፈበትን እውነተኛ የሕይወት ውጣ ውረድ የሚተርከውና "ዮም" የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በሳምንቱ መጨረሻ ተመርቆ ለንባብ በቅቷል።
በደራሲ ንሴብሖ ፍቅሬ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ፣ በኦቲዝም ጥላ ስር ያሉ ልጆች የሚገጥሟቸውን ማኅበራዊ ጫናዎችና ቤተሰቦቻቸው የሚጋፈጡትን መሪር የሕይወት ፈተና ከራሳቸው ገጠመኝ በመነሳት በዝርዝር ዳስሰዋል።
መጽሃፉ በዚህ የህይወት ሰልፍ ውስጥ ያሉ ልጆችን ህይወት በማሳየት ለበርካት ቤተሰቦች መንገድ መሪ መሆን የሚችል መሆኑ በምርቃት መድረኩ ተገልጿል፡፡
ደራሲው የ11 ዓመት ዕድሜ ያለው "ዮም" የተባለ በኦቲዝም ጥላ ስር ያለ ልጅ አባት ሲሆኑ፣ ልጃቸው የሕይወት ዘመን ክትትልና ድጋፍ የሚሻ በመሆኑ ሁኔታው በቤተሰቡ ላይ የሚፈጥረው ጫና ማለቂያ የሌለው መሆኑን በመጽሐፋቸው ገልጸዋል።
በመሆኑም ይህ ችግር በአንድ ቤተሰብ ጥረት ብቻ የሚፈታ ሳይሆን ማኅበረሰቡ፣ የግል ድርጅቶችና መንግሥት በጋራ ሊረባረቡበት እንደሚገባ ደራሲው አጽንኦት ሰጥተዋል።
በተለይም ትምህርት ቤቶች ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ልጆች ተቀብለው ለማስተማርና ተገቢውን ትኩረት ለመስጠት ዝግጁ ሊሆኑ እንደሚገባ ደራሲ ንሴብሖ ከራሳቸው የሕይወት ተሞክሮ በመነሳት ጥሪ አቅርበዋል።
በ254 ገጾች ተቀንብቦ ለንባብ የበቃው ይህ መጽሐፍ፣ በዘርፉ ያለውን የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላትና ለሌሎች ወላጆችም የሞራል ጥንካሬ ለመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል።
5 months ago
"ዮም"፦
በኦቲዝም ጥላ ሥር ያለ የሕይወት ተጋድሎና የተስፋ ስንቅ! ✨
#ethiopia | በኦቲዝም ጥላ ሥር የሚኖርን ልጅ የማሳደግ ፈተና፣ የወላጆች የሥነ-ልቦና ጫና እና ማህበራዊ መገለልን የሚዳስሰው "ዮም" የተሰኘ መጽሐፍ በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል።
የአባትነት ፍቅር፦
ደራሲው የ11 ዓመት የኦቲዝም ተማሪ የሆነው የዮም አባት ሲሆኑ፣ ልጃቸውን ለማሳደግ የከፈሉትን መስዋዕትነትና ያጋጠማቸውን የኢኮኖሚና የማህበራዊ ጫና በ254 ገጾች ተርከዋል።
የግንዛቤ ጥሪ፦
መጽሐፉ ማህበረሰቡ ለኦቲዝም ያለውን የተሳሳተ አመለካከት እንዲቀይርና ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ዜጎች በዕኩልነት እንዲቀበል ያሳስባል።
የመንግሥት ድርሻ፦
ለኦቲዝም ልዩ ትኩረት የሚሰጡ የትምህርትና የሕክምና ተቋማት እንዲስፋፉ ጥሪ ቀርቧል።
ይህ መጽሐፍ ለወላጆች መመሪያ፣ ለባለሙያዎች ግብዓት፣ ለተስፋ ለቆረጡ ደግሞ የሞራል ስንቅ ነው!
ኦቲዝም ያለባቸው ልጆች ካልታወቀላቸውና ድጋፍ ካላገኙ በቤታቸው ተዘግተው እንዲቀሩ ይገደዳሉ። "ዮም" ይህንን ግድግዳ ሰብሮ በመውጣት ለውጥ ለማምጣት የመጣ የብርሃን መጽሐፍ ነው።
#ኦቲዝም #ዮም #አዲስመጽሐፍ #ግንዛቤ #ኢትዮጵያ #autismawareness #yombook #ethiopia #inclusion #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
በኦቲዝም ጥላ ሥር ያለ የሕይወት ተጋድሎና የተስፋ ስንቅ! ✨
#ethiopia | በኦቲዝም ጥላ ሥር የሚኖርን ልጅ የማሳደግ ፈተና፣ የወላጆች የሥነ-ልቦና ጫና እና ማህበራዊ መገለልን የሚዳስሰው "ዮም" የተሰኘ መጽሐፍ በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል።
የአባትነት ፍቅር፦
ደራሲው የ11 ዓመት የኦቲዝም ተማሪ የሆነው የዮም አባት ሲሆኑ፣ ልጃቸውን ለማሳደግ የከፈሉትን መስዋዕትነትና ያጋጠማቸውን የኢኮኖሚና የማህበራዊ ጫና በ254 ገጾች ተርከዋል።
የግንዛቤ ጥሪ፦
መጽሐፉ ማህበረሰቡ ለኦቲዝም ያለውን የተሳሳተ አመለካከት እንዲቀይርና ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ዜጎች በዕኩልነት እንዲቀበል ያሳስባል።
የመንግሥት ድርሻ፦
ለኦቲዝም ልዩ ትኩረት የሚሰጡ የትምህርትና የሕክምና ተቋማት እንዲስፋፉ ጥሪ ቀርቧል።
ይህ መጽሐፍ ለወላጆች መመሪያ፣ ለባለሙያዎች ግብዓት፣ ለተስፋ ለቆረጡ ደግሞ የሞራል ስንቅ ነው!
ኦቲዝም ያለባቸው ልጆች ካልታወቀላቸውና ድጋፍ ካላገኙ በቤታቸው ተዘግተው እንዲቀሩ ይገደዳሉ። "ዮም" ይህንን ግድግዳ ሰብሮ በመውጣት ለውጥ ለማምጣት የመጣ የብርሃን መጽሐፍ ነው።
#ኦቲዝም #ዮም #አዲስመጽሐፍ #ግንዛቤ #ኢትዮጵያ #autismawareness #yombook #ethiopia #inclusion #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
Sponsored by
Surafel
5 months ago
የSocial midea platform ሲድሮ የተሰኘ ለቪዲዮ ጊፍት መስጠት የሚያስችል መተግበሪያ ይፋ የሆነ ።
ኢንፍራቴክ ሶፍትዌር ሰርቪስ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር የተለያዩ አፕሊኬሽን እና ሶፍትዌሮች እያበለጸገ ይገኛል። በዛሬው ዕለት ለኢትዮጵያውያን የተሰራ "ሲድሮ" (Sydor) የተባለ አዲስ የሶሻል ሚዲያ አፕሊኬሽን እና የድርጅት ምስረታ ማካሄዱን የተጽዕኖ ፈጣሪ እና የድርጅቱ ሼር ሆልደር የሆነው አዶናይ ብርሃነ ተናግሯል።
ይህ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያውያንን በራሳቸው ዲጂታል መድረክ ላይ በቀላሉ ለማገናኘት ታስቦ የተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
ከማህበራዊ ሚዲያ አዝናኝነት አልፎ የራሱን የቴክኖሎጂ ድርጅት በመክፈት ትልቅ እርምጃ የወሰደው የዚህ ወጣት አዲስ አፕሊኬሽን፤ በዛሬው እለት በይፋ ተመርቋል።
በኢትዮጵያ በአሁን ሰዓት ከ7 እስከ 10 ሚሊዮን የሚደርስ የቲክቶክ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መኖራቸው የተገለጸ ሲሆን ጊፍቱ ጊፍት በቴሌብር መግዛት የሚቻል መሆኑ ተነግሯል ። International የሆነ ድርጅት እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ አዲስ የSocial midea platform ቴሌብርን በመጠቀም Live ላይ ሰዎች Gift ማድረግ የምትችሉበት፣ ከዛም አልፎ Social media ላይ ያሉ ሰዎች ስራቸውን በቪዲዮም ጊፍት ማግኘት የሚችሉበትን፣ ስራ መስራት የሚችሉበትን፣ ከዛም አልፎ ደግሞ የተለያዩ ንግዶች ይሄንን የSocial midea platform በመጠቀም ራሳቸውን ማስተዋወቅ የሚችሉበት Sydro የተሰኘ አዲስ የSocial midea platform መጥቷል። የዚህን Platform ከ Influencer ጋር ቅዳሜ ዉይይት ተደርጎበታል።በቅርብ ቀን ደግሞ Announce ተደርጎ Official የሚሆን ይሆናል። እንግዲህ ይሄ አስደሳች የሆነ ዜና በቅርብ ጊዜ ጠብቁ !
ኢንፍራቴክ ሶፍትዌር ሰርቪስ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር የተለያዩ አፕሊኬሽን እና ሶፍትዌሮች እያበለጸገ ይገኛል። በዛሬው ዕለት ለኢትዮጵያውያን የተሰራ "ሲድሮ" (Sydor) የተባለ አዲስ የሶሻል ሚዲያ አፕሊኬሽን እና የድርጅት ምስረታ ማካሄዱን የተጽዕኖ ፈጣሪ እና የድርጅቱ ሼር ሆልደር የሆነው አዶናይ ብርሃነ ተናግሯል።
ይህ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያውያንን በራሳቸው ዲጂታል መድረክ ላይ በቀላሉ ለማገናኘት ታስቦ የተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
ከማህበራዊ ሚዲያ አዝናኝነት አልፎ የራሱን የቴክኖሎጂ ድርጅት በመክፈት ትልቅ እርምጃ የወሰደው የዚህ ወጣት አዲስ አፕሊኬሽን፤ በዛሬው እለት በይፋ ተመርቋል።
በኢትዮጵያ በአሁን ሰዓት ከ7 እስከ 10 ሚሊዮን የሚደርስ የቲክቶክ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መኖራቸው የተገለጸ ሲሆን ጊፍቱ ጊፍት በቴሌብር መግዛት የሚቻል መሆኑ ተነግሯል ። International የሆነ ድርጅት እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ አዲስ የSocial midea platform ቴሌብርን በመጠቀም Live ላይ ሰዎች Gift ማድረግ የምትችሉበት፣ ከዛም አልፎ Social media ላይ ያሉ ሰዎች ስራቸውን በቪዲዮም ጊፍት ማግኘት የሚችሉበትን፣ ስራ መስራት የሚችሉበትን፣ ከዛም አልፎ ደግሞ የተለያዩ ንግዶች ይሄንን የSocial midea platform በመጠቀም ራሳቸውን ማስተዋወቅ የሚችሉበት Sydro የተሰኘ አዲስ የSocial midea platform መጥቷል። የዚህን Platform ከ Influencer ጋር ቅዳሜ ዉይይት ተደርጎበታል።በቅርብ ቀን ደግሞ Announce ተደርጎ Official የሚሆን ይሆናል። እንግዲህ ይሄ አስደሳች የሆነ ዜና በቅርብ ጊዜ ጠብቁ !
5 months ago
📚 "ዮም"፦
በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆችና የወላጆቻቸው የጽናት መስታወት! ✨
#ethiopia | በኦቲዝም ጥላ ሥር የሚኖሩ ልጆችን የማሳደግ ውጣ ውረድ፣ የወላጆች እሮሮ እና የጽናት ጉዞ እንደ መስታወት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል!
📖 ስለ መጽሐፉ፦
"ዮም" የተሰኘው ይህ መጽሐፍ በአቶ ንሴብሆ ፍቅሬ እና በወ/ሮ ሳምራዊት ድንቁ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የራሳቸውን ልጅ በማሳደግ ሂደት ውስጥ ያለፉበትን ፈታኝ መንገድና መሰል ኢትዮጵያውያን ወላጆች የሚገጥሟቸውን ተግዳሮቶች በጥልቀት ይዳስሳል።
🗓 የምረቃ ሥነ-ሥርዓት መርሃ-ግብር፦
ቀን፦ እሁድ የካቲት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
ሰዓት፦ ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ
ቦታ፦ ሀይሌ ግራንድ ኢንተርናሽናል ሆቴል (Haile Grand International Hotel)
🌟 የጥሪ መልዕክት፦
በምረቃው መርሃ-ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና እንግዶች የሚገኙ ሲሆን፣ እርስዎም በዚህ ታሪካዊ መድረክ ላይ በመገኘት በኦቲዝም ጥላ ሥር ላሉ ልጆችና ለሚደክሙ ወላጆቻቸው ድምፅ እንዲሆኑ በአክብሮት ተጋብዘዋል።
💰 ማሳሰቢያ፦
መጽሐፉ በዕለቱ በአዳራሹ መግቢያ በር ላይ ለሽያጭ የሚቀርብ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
"የኦቲዝም ልጆችን እና የወላጆቻቸውን የጽናት ጉዞ አብረን እንደግፍ!"
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ Share በማድረግ ይተባበሩ።
#ዮም #ኦቲዝም #autismawareness #ethiopia #booklaunch #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆችና የወላጆቻቸው የጽናት መስታወት! ✨
#ethiopia | በኦቲዝም ጥላ ሥር የሚኖሩ ልጆችን የማሳደግ ውጣ ውረድ፣ የወላጆች እሮሮ እና የጽናት ጉዞ እንደ መስታወት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል!
📖 ስለ መጽሐፉ፦
"ዮም" የተሰኘው ይህ መጽሐፍ በአቶ ንሴብሆ ፍቅሬ እና በወ/ሮ ሳምራዊት ድንቁ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የራሳቸውን ልጅ በማሳደግ ሂደት ውስጥ ያለፉበትን ፈታኝ መንገድና መሰል ኢትዮጵያውያን ወላጆች የሚገጥሟቸውን ተግዳሮቶች በጥልቀት ይዳስሳል።
🗓 የምረቃ ሥነ-ሥርዓት መርሃ-ግብር፦
ቀን፦ እሁድ የካቲት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
ሰዓት፦ ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ
ቦታ፦ ሀይሌ ግራንድ ኢንተርናሽናል ሆቴል (Haile Grand International Hotel)
🌟 የጥሪ መልዕክት፦
በምረቃው መርሃ-ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና እንግዶች የሚገኙ ሲሆን፣ እርስዎም በዚህ ታሪካዊ መድረክ ላይ በመገኘት በኦቲዝም ጥላ ሥር ላሉ ልጆችና ለሚደክሙ ወላጆቻቸው ድምፅ እንዲሆኑ በአክብሮት ተጋብዘዋል።
💰 ማሳሰቢያ፦
መጽሐፉ በዕለቱ በአዳራሹ መግቢያ በር ላይ ለሽያጭ የሚቀርብ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
"የኦቲዝም ልጆችን እና የወላጆቻቸውን የጽናት ጉዞ አብረን እንደግፍ!"
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ Share በማድረግ ይተባበሩ።
#ዮም #ኦቲዝም #autismawareness #ethiopia #booklaunch #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
7 months ago
ገንዘብን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመር ብሄራዊ ደህንነትን እንደሚያስጠብቅ ባለሙያዎች ገለጹ
በቅርቡ "የፋይናንስ እምርታ በኢትዮጵያ" በሚል በተዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ገንዘቧን በሀገር ውስጥ ማሳተም እንደምትጀምር መግለፃቸው ይታወሳል፡፡
መናኸሪያ ሬዲዮም ይህንን መነሻ በማድረግ ያነጋገራቸው የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች፣ በሀገር ውስጥ ገንዘብ ማሳተም መጀመሩ እጅግ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው፤ የገንዘብ (የብር) አስተዳደርንም አብሮ ማዘመን እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡
የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ክቡር ገና ኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት ገንዘቧን በውጭ ሀገር ስታሳትም መቆየቷንና በዚህም ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪ ስትዳረግ መቆየቷን ጠቅሰው፤ ብርን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመር ብሄራዊ ደህንነትን የሚያረጋግጥ ጭምር ነው ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ጎረቤት ሀገራት ገንዘባቸውን ኢትዮጵያ እንድታሳትምላቸው ጥያቄ ያቀርባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና ይህም ለሀገሪቱ ተጨማሪ ገቢ ሊያስገኝ እንደሚችል ገልጸዋል።
ገንዘባቸውን በሀገር ውስጥ በማተማቸው ውጤታማ የሆኑ ሀገራትን እንደ ምሳሌ በማንሳት፣ ኢትዮጵያ ቀደም ብላ እንደ ፓስፖርት ያሉ ሰነዶችን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመሯ ለዚህ ስራ አጋዥ እንደሚሆንና ጥንቃቄ የተሞላበት የገበያ ጥናት በማድረግ ውጤታማ መሆን እንደሚቻል አስረድተዋል፡፡
ሌላኛው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ዶክተር ሞላ አለማየሁ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ገንዘቧን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመሯ በመልካም የሚወሰድና ለህትመት ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስቀር ነው ብለዋል፡፡
ይሁን እንጂ ብር በሀገር ውስጥ ሲታተም ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም ብር ያለ አግባብ ገበያ ውስጥ እንዳይሰራጭና የዋጋ ግሽበትን እንዳያስከትል ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ይገባል ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል፡፡
በ"የፋይናንስ እምርታ በኢትዮጵያ" የውይይት መድረክ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ብርን በሀገር ውስጥ ማሳተም የሚያስችል አቅም መፍጠሩን መግለፃቸው የሚታወስ ነው፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም፡፡ምስል - AI
በቅርቡ "የፋይናንስ እምርታ በኢትዮጵያ" በሚል በተዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ገንዘቧን በሀገር ውስጥ ማሳተም እንደምትጀምር መግለፃቸው ይታወሳል፡፡
መናኸሪያ ሬዲዮም ይህንን መነሻ በማድረግ ያነጋገራቸው የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች፣ በሀገር ውስጥ ገንዘብ ማሳተም መጀመሩ እጅግ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው፤ የገንዘብ (የብር) አስተዳደርንም አብሮ ማዘመን እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡
የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ክቡር ገና ኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት ገንዘቧን በውጭ ሀገር ስታሳትም መቆየቷንና በዚህም ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪ ስትዳረግ መቆየቷን ጠቅሰው፤ ብርን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመር ብሄራዊ ደህንነትን የሚያረጋግጥ ጭምር ነው ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ጎረቤት ሀገራት ገንዘባቸውን ኢትዮጵያ እንድታሳትምላቸው ጥያቄ ያቀርባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና ይህም ለሀገሪቱ ተጨማሪ ገቢ ሊያስገኝ እንደሚችል ገልጸዋል።
ገንዘባቸውን በሀገር ውስጥ በማተማቸው ውጤታማ የሆኑ ሀገራትን እንደ ምሳሌ በማንሳት፣ ኢትዮጵያ ቀደም ብላ እንደ ፓስፖርት ያሉ ሰነዶችን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመሯ ለዚህ ስራ አጋዥ እንደሚሆንና ጥንቃቄ የተሞላበት የገበያ ጥናት በማድረግ ውጤታማ መሆን እንደሚቻል አስረድተዋል፡፡
ሌላኛው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ዶክተር ሞላ አለማየሁ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ገንዘቧን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመሯ በመልካም የሚወሰድና ለህትመት ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስቀር ነው ብለዋል፡፡
ይሁን እንጂ ብር በሀገር ውስጥ ሲታተም ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም ብር ያለ አግባብ ገበያ ውስጥ እንዳይሰራጭና የዋጋ ግሽበትን እንዳያስከትል ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ይገባል ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል፡፡
በ"የፋይናንስ እምርታ በኢትዮጵያ" የውይይት መድረክ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ብርን በሀገር ውስጥ ማሳተም የሚያስችል አቅም መፍጠሩን መግለፃቸው የሚታወስ ነው፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም፡፡ምስል - AI
8 months ago
ዩናይትድ ስቴትስ የ«ዲቪ» ሎተሪ እድልን አገደች
የዩናይትድ ስቴትስ ብራውን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ከተፈጸመው የተኩስ እሩምታ እና ግድያ በኋላ የ«ዲቪ» ሎተሪ እድልን ማገዷን ዐሳወቀች ።
የዩናይትድ ስቴትስ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ኃላፊ ክሪስቲ ኖዬም፦ በብራውን ዩኒቨርሲቲ የተኩስ እሩምታ ግድያ የተጠረጠረው ግለሰብ «አሁን በተቋረጠው የዲቪ መርኀ-ግብር ተጠቃሚ ከሆነ አገር የመጣ ነው» ብለዋል ።
ለኃላፊዋ የዲቪ ሎተሪ እድል መርኀግብሩን እንዲያቋርጡ «አቋርጪ» ሲሉ ትናንት ሐሙስ፤ ታኅሣሥ 9 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ማምሻውን ትእዛዝ ያስተላለፉላቸው የአገሪቱ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ናቸው ።
«በፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ መመሪያ መሠረት ከእንግዲህ በዚህ አደገኛ መርኀ-ግብር አንድም አሜሪካዊ እንደማይጎዳ እርግጠኛ እስክንሆን ድረስ የዲቪ ሎተሪን መርኀ-ግብር እንዲያቋርጥ ለዩናይትድ ስቴትስ ዜግነት እና ኢሚግሬሽን አገልግሎት ወዲያውኑ አስተላልፌያለሁ» ሲሉ ክሪስቲ ናዮም ዐሳውቀዋል ።
ኃላፊዋ በይፋዊ የኤክስ ማኅበራዊ መገናኛ አውታራቸው እንደጻፉትም በብራውን ዩኒቨርሲቲ የተኩስ እሩምታ ገዳዩ ክላውዲዮ ማኑዌል ኔቬስ ቫሌንቴ፦ «እንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር በ2017 የዲቪ ሎተሪ መርኀ ግብር ግሪን ካርድ አግኝቶ» ዩናይትድ ስቴትስ የገባ ነው ።
የዲቪ ሎተሪ መርኀ-ግብር በየዓመቱ 50,000 ፍልሰተኞች ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዲገቡ የሚያስችል እድል እንደነበር ነው የተገለጸው ። በዚህ እድል በርካታ ኢትዮጵያውያንም ተጠቃሚዎች ናቸው ።
Ethio Fm
የዩናይትድ ስቴትስ ብራውን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ከተፈጸመው የተኩስ እሩምታ እና ግድያ በኋላ የ«ዲቪ» ሎተሪ እድልን ማገዷን ዐሳወቀች ።
የዩናይትድ ስቴትስ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ኃላፊ ክሪስቲ ኖዬም፦ በብራውን ዩኒቨርሲቲ የተኩስ እሩምታ ግድያ የተጠረጠረው ግለሰብ «አሁን በተቋረጠው የዲቪ መርኀ-ግብር ተጠቃሚ ከሆነ አገር የመጣ ነው» ብለዋል ።
ለኃላፊዋ የዲቪ ሎተሪ እድል መርኀግብሩን እንዲያቋርጡ «አቋርጪ» ሲሉ ትናንት ሐሙስ፤ ታኅሣሥ 9 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ማምሻውን ትእዛዝ ያስተላለፉላቸው የአገሪቱ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ናቸው ።
«በፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ መመሪያ መሠረት ከእንግዲህ በዚህ አደገኛ መርኀ-ግብር አንድም አሜሪካዊ እንደማይጎዳ እርግጠኛ እስክንሆን ድረስ የዲቪ ሎተሪን መርኀ-ግብር እንዲያቋርጥ ለዩናይትድ ስቴትስ ዜግነት እና ኢሚግሬሽን አገልግሎት ወዲያውኑ አስተላልፌያለሁ» ሲሉ ክሪስቲ ናዮም ዐሳውቀዋል ።
ኃላፊዋ በይፋዊ የኤክስ ማኅበራዊ መገናኛ አውታራቸው እንደጻፉትም በብራውን ዩኒቨርሲቲ የተኩስ እሩምታ ገዳዩ ክላውዲዮ ማኑዌል ኔቬስ ቫሌንቴ፦ «እንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር በ2017 የዲቪ ሎተሪ መርኀ ግብር ግሪን ካርድ አግኝቶ» ዩናይትድ ስቴትስ የገባ ነው ።
የዲቪ ሎተሪ መርኀ-ግብር በየዓመቱ 50,000 ፍልሰተኞች ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዲገቡ የሚያስችል እድል እንደነበር ነው የተገለጸው ። በዚህ እድል በርካታ ኢትዮጵያውያንም ተጠቃሚዎች ናቸው ።
Ethio Fm
8 months ago
ጋይስ ይሄን እድል ተጠቀሙበት አዲሰ onlin ስራነዉ 100%ይከፍላል ስሙ buzzer app ይባላል በ 3 መንገድ ይከፍላል
1ኛ እንደ ቲክቶክ ስፖርታዊ አጫጭር ቪዲዩ በመልቀቅ ከቲክቶክ እያወረዳቹ በ 1k view ጀምሮ ይከፍላችሆል
2ኛ በኢንቫይት ሰው በመጋበዝ 0.15 ዶላር በናንተ ሊንክ ብቻ ስለከፈቱ ይከፍላችሆል
3ኛ ታስኮች አለ ቪዲዩ በማየት ላይክ በማድረግ ኮሜንት በመፃፍ ይከፍላል
🤑ልክ $10 ሲሞላ ማውጣት ትችላላችሁ
🧲አካውንት ለመክፈት ይህን step ተከተሉ
✔️ይህን ሊንክ ተጭናችሁ አፑን ከplaystore or appstore አውረዱ 👇
https://app.buzzerfan.com/...
በመቀጠል email ካላችሁ n emailላችሁ መግባት ትችላላችሁ ካልሆነ ግን create account ሚለውን ተጭናችሁ email እና የማረሱትን password አስገቡ ከዛ በemail የላከላችሁን ኮድ አስገቡ
✔️በመቀጠል username,first & last name አስገቡ ከዛ gender,age አስገቡ
✔️በመቀጠል referral code የሚል ሲመጣላችሁ bonus point ለማግኘት ይህን ኮድ አስገቡ 👉 6AF10E
✔️አሁን አካውንት ከፍታችኋል ከዚህ በኋላ ቪዲዮ እየጫናችሁ በ1k view ትከፈላላችሁ
በተጨማሪም 1ሰው ስጋብዙ $0.15 ታገኛላችሁ
✔️ከዚህ በኋላ መስራት ነው እድሉን ተጠቀሙ ሞክሩት ቪዲዮም ሙሉ ማብራሪያ ከፈለጋቹ አከፋፈቱን ከላይ የሰራነውን video ይመልከቱ
referral code 👉 6AF10E ይቺን ማስገባት
እንዳይረሳ አብረን ብዙ ስራዎችን ስለምንሰራ አዳዲስ መረጃም ካለ አሳዉቃለሁኝ
1ኛ እንደ ቲክቶክ ስፖርታዊ አጫጭር ቪዲዩ በመልቀቅ ከቲክቶክ እያወረዳቹ በ 1k view ጀምሮ ይከፍላችሆል
2ኛ በኢንቫይት ሰው በመጋበዝ 0.15 ዶላር በናንተ ሊንክ ብቻ ስለከፈቱ ይከፍላችሆል
3ኛ ታስኮች አለ ቪዲዩ በማየት ላይክ በማድረግ ኮሜንት በመፃፍ ይከፍላል
🤑ልክ $10 ሲሞላ ማውጣት ትችላላችሁ
🧲አካውንት ለመክፈት ይህን step ተከተሉ
✔️ይህን ሊንክ ተጭናችሁ አፑን ከplaystore or appstore አውረዱ 👇
https://app.buzzerfan.com/...
በመቀጠል email ካላችሁ n emailላችሁ መግባት ትችላላችሁ ካልሆነ ግን create account ሚለውን ተጭናችሁ email እና የማረሱትን password አስገቡ ከዛ በemail የላከላችሁን ኮድ አስገቡ
✔️በመቀጠል username,first & last name አስገቡ ከዛ gender,age አስገቡ
✔️በመቀጠል referral code የሚል ሲመጣላችሁ bonus point ለማግኘት ይህን ኮድ አስገቡ 👉 6AF10E
✔️አሁን አካውንት ከፍታችኋል ከዚህ በኋላ ቪዲዮ እየጫናችሁ በ1k view ትከፈላላችሁ
በተጨማሪም 1ሰው ስጋብዙ $0.15 ታገኛላችሁ
✔️ከዚህ በኋላ መስራት ነው እድሉን ተጠቀሙ ሞክሩት ቪዲዮም ሙሉ ማብራሪያ ከፈለጋቹ አከፋፈቱን ከላይ የሰራነውን video ይመልከቱ
referral code 👉 6AF10E ይቺን ማስገባት
እንዳይረሳ አብረን ብዙ ስራዎችን ስለምንሰራ አዳዲስ መረጃም ካለ አሳዉቃለሁኝ
8 months ago
ኢቢሲ በአፍሪካ ሚዲያ አዋርድ ልዩ ተሸላሚ ሆነ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በአፍሪካ ሚዲያ አዋርድ ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።
በሬድዮም ሆነ በቴሌቪዥን ቀዳሚ እና የኢትዮጵያ የበኩር ድምፅ የሆነው ኢቢሲ ላለፉት ዓመታት በዘርፉ ከፍተኛ አበርክቶ ያለው መሆኑ ይታወቃል።
ብሔራዊ ሚዲያው ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካውያን አንድነት፣ ትብብር እና በጋራ መቆም ትልቅ ድርሻ የነበረው ነው።
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን በማፋፋም፣ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሠረት በማገዝ እንዲሁም አፍሪካውያን ከቅኝ ግዛት ለመውጣት የነፃነት ትግል እንዲያደርጉ በማነቃነቅ ታሪካዊ ሚናን ተጫውቷል።
በአሁኑ ወቅትም ኢትዮጵያ የምታከናውናቸውን የልማት ሥራዎች በዘርፈ ብዙ አማራጮቹ ከማሳለጥ እና ለዓለም ከማስተዋወቅ ባሻገር፣ አፍሪካ የጋራ ልማት እና ተጠቃሚነቷን ታረጋግጥ ዘንድ በአባል ሀገራት መካከል የትብብር መንፈስን ለማጠናከር እየሠራ ይገኛል።
የአፍሪካ መገናኛ ብዙኃን በተለያዩ መንገዶች ለአፍሪካ ዕድገትና ከፍታ እየሠሩ ላለው ሥራ እውቅና ለመስጠት በተካሄደው የአፍሪካ ሚዲያ አዋርድ፤ ኢቢሲ ያበረከተው አስተዋፅዖ ከሌሎች ሚዲያዎች ጋር ተወዳድሮ ልቆ በመገኘቱ ነው ልዩ ተሸላሚ መሆን የቻለው።
በአዲስ አበባ በተካሄደው የሽልማት ሥነ-ሥርዓት በምርጥ ቪድዮ ፕሮዳክሽን ዘርፍ፣ በአፍሪካን ኢንዲፔንደንት ዘርፍ (African Independent Category) እንዲሁም በአፍሪካ የባህል ጥበቃ ዘርፍ (African Cultural Heritage) ለአሸናፊዎች ሽልማት ተበርክቷል።
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በአፍሪካ ሚዲያ አዋርድ ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።
በሬድዮም ሆነ በቴሌቪዥን ቀዳሚ እና የኢትዮጵያ የበኩር ድምፅ የሆነው ኢቢሲ ላለፉት ዓመታት በዘርፉ ከፍተኛ አበርክቶ ያለው መሆኑ ይታወቃል።
ብሔራዊ ሚዲያው ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካውያን አንድነት፣ ትብብር እና በጋራ መቆም ትልቅ ድርሻ የነበረው ነው።
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን በማፋፋም፣ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሠረት በማገዝ እንዲሁም አፍሪካውያን ከቅኝ ግዛት ለመውጣት የነፃነት ትግል እንዲያደርጉ በማነቃነቅ ታሪካዊ ሚናን ተጫውቷል።
በአሁኑ ወቅትም ኢትዮጵያ የምታከናውናቸውን የልማት ሥራዎች በዘርፈ ብዙ አማራጮቹ ከማሳለጥ እና ለዓለም ከማስተዋወቅ ባሻገር፣ አፍሪካ የጋራ ልማት እና ተጠቃሚነቷን ታረጋግጥ ዘንድ በአባል ሀገራት መካከል የትብብር መንፈስን ለማጠናከር እየሠራ ይገኛል።
የአፍሪካ መገናኛ ብዙኃን በተለያዩ መንገዶች ለአፍሪካ ዕድገትና ከፍታ እየሠሩ ላለው ሥራ እውቅና ለመስጠት በተካሄደው የአፍሪካ ሚዲያ አዋርድ፤ ኢቢሲ ያበረከተው አስተዋፅዖ ከሌሎች ሚዲያዎች ጋር ተወዳድሮ ልቆ በመገኘቱ ነው ልዩ ተሸላሚ መሆን የቻለው።
በአዲስ አበባ በተካሄደው የሽልማት ሥነ-ሥርዓት በምርጥ ቪድዮ ፕሮዳክሽን ዘርፍ፣ በአፍሪካን ኢንዲፔንደንት ዘርፍ (African Independent Category) እንዲሁም በአፍሪካ የባህል ጥበቃ ዘርፍ (African Cultural Heritage) ለአሸናፊዎች ሽልማት ተበርክቷል።
8 months ago
የ95 ዓመቷ ቻይናዊት ሞቱ ከተባሉ ከስድስት ቀን በኋላ ምግብ ሲያበስሉ ታይተው እንደነበረ ተነገረ
#ethiopia | ድርጊቱ ከ 13 አመት በፊት ቢከሰትም የእንግሊዙ ሚረር በሰሞኑ እትሙ ዜናውን ይዞ ወጥቶታል።
ሊ ዢዩፌንግ የተባሉት አሮጊት ሞቱ ተብለው ሬሳ ሳጥን ውስጥ ተከተው በአካባቢው ባህል መሰረት ዘመድ ለመቀበር ዘመድ እስኪሰባሰብ እየተጠበቀ ነበር።
ሞቱ ከተባሉ ከስድስት ቀን በኋላ ለቀብር ሲሰናዳ ሳጥናቸው ሲከፈት ሴትዯ በሳጥን ውስጥ የሉም።
ጎረቤት ደነገጠ። በማድቤት ውስጥ ምግብ ሲያበስሉ ታዩ ።
ሴትዮም እንዲህ አሉ" ለረጅም ጊዜ ተኝቼ ነበር። ከእንቅልፌ ስነሳ በጣም ረሃብ ተሰማኝና የምበላው ነገር ማብሰል ፈለግኩ። ለመውጣት የአስከሬን ሳጥኑን ክዳን ለረጅም ጊዜ ገፍቼ ነበር።”
በመጀመሪያ ሐኪሞቹ ግራ ተጋብተው ነበር። ሆኖም ሴትዮን ከመረመሩ በኋላ፣ የአንድ ሰው አተነፋፈስ የሚቆምበት ነገር ግን ሰውነቱ ሙቀት የሚይዝበት "ሰው ሰራሽ ሞት" (artificial death) በመባል የሚታወቅ ያልተለመደ ሁኔታ እንዳጋጠማቸው ደምድመዋል።
ዶክተሮቹ አክለውም ፡"ለበርካታ ቀናት አስከሬኑን በቤት ውስጥ የማቆየት የአካባቢው ባህል ምስጋና ይግባውና ሴትዯ መዳን ችላለች" ብለዋል ያለው ፊደል ፖስት ነው።
#ethiopia | ድርጊቱ ከ 13 አመት በፊት ቢከሰትም የእንግሊዙ ሚረር በሰሞኑ እትሙ ዜናውን ይዞ ወጥቶታል።
ሊ ዢዩፌንግ የተባሉት አሮጊት ሞቱ ተብለው ሬሳ ሳጥን ውስጥ ተከተው በአካባቢው ባህል መሰረት ዘመድ ለመቀበር ዘመድ እስኪሰባሰብ እየተጠበቀ ነበር።
ሞቱ ከተባሉ ከስድስት ቀን በኋላ ለቀብር ሲሰናዳ ሳጥናቸው ሲከፈት ሴትዯ በሳጥን ውስጥ የሉም።
ጎረቤት ደነገጠ። በማድቤት ውስጥ ምግብ ሲያበስሉ ታዩ ።
ሴትዮም እንዲህ አሉ" ለረጅም ጊዜ ተኝቼ ነበር። ከእንቅልፌ ስነሳ በጣም ረሃብ ተሰማኝና የምበላው ነገር ማብሰል ፈለግኩ። ለመውጣት የአስከሬን ሳጥኑን ክዳን ለረጅም ጊዜ ገፍቼ ነበር።”
በመጀመሪያ ሐኪሞቹ ግራ ተጋብተው ነበር። ሆኖም ሴትዮን ከመረመሩ በኋላ፣ የአንድ ሰው አተነፋፈስ የሚቆምበት ነገር ግን ሰውነቱ ሙቀት የሚይዝበት "ሰው ሰራሽ ሞት" (artificial death) በመባል የሚታወቅ ያልተለመደ ሁኔታ እንዳጋጠማቸው ደምድመዋል።
ዶክተሮቹ አክለውም ፡"ለበርካታ ቀናት አስከሬኑን በቤት ውስጥ የማቆየት የአካባቢው ባህል ምስጋና ይግባውና ሴትዯ መዳን ችላለች" ብለዋል ያለው ፊደል ፖስት ነው።
8 months ago
የ95 ዓመቷ ቻይናዊት ሞቱ ከተባሉ ከስድስት ቀን በኋላ ምግብ ሲያበስሉ ታይተው እንደነበረ ተነገረ
ድርጊቱ ከ 13 አመት በፊት ቢከሰትም የእንግሊዙ ሚረር በሰሞኑ እትሙ ዜናውን ይዞ ወጥቶታል።
ሊ ዢዩፌንግ የተባሉት አሮጊት ሞቱ ተብለው ሬሳ ሳጥን ውስጥ ተከተው በአካባቢው ባህል መሰረት ዘመድ ለመቀበር ዘመድ እስኪሰባሰብ እየተጠበቀ ነበር።
ሞቱ ከተባሉ ከስድስት ቀን በኋላ ለቀብር ሲሰናዳ ሳጥናቸው ሲከፈት ሴትዯ በሳጥን ውስጥ የሉም።
ጎረቤት ደነገጠ። በማድቤት ውስጥ ምግብ ሲያበስሉ ታዩ ።
ሴትዮም እንዲህ አሉ" ለረጅም ጊዜ ተኝቼ ነበር። ከእንቅልፌ ስነሳ በጣም ረሃብ ተሰማኝና የምበላው ነገር ማብሰል ፈለግኩ። ለመውጣት የአስከሬን ሳጥኑን ክዳን ለረጅም ጊዜ ገፍቼ ነበር።”
በመጀመሪያ ሐኪሞቹ ግራ ተጋብተው ነበር። ሆኖም ሴትዮን ከመረመሩ በኋላ፣ የአንድ ሰው አተነፋፈስ የሚቆምበት ነገር ግን ሰውነቱ ሙቀት የሚይዝበት "ሰው ሰራሽ ሞት" (artificial death) በመባል የሚታወቅ ያልተለመደ ሁኔታ እንዳጋጠማቸው ደምድመዋል።
ዶክተሮቹ አክለውም ፡"ለበርካታ ቀናት አስከሬኑን በቤት ውስጥ የማቆየት የአካባቢው ባህል ምስጋና ይግባውና ሴትዯ መዳን ችላለች" ብለዋል።
ድርጊቱ ከ 13 አመት በፊት ቢከሰትም የእንግሊዙ ሚረር በሰሞኑ እትሙ ዜናውን ይዞ ወጥቶታል።
ሊ ዢዩፌንግ የተባሉት አሮጊት ሞቱ ተብለው ሬሳ ሳጥን ውስጥ ተከተው በአካባቢው ባህል መሰረት ዘመድ ለመቀበር ዘመድ እስኪሰባሰብ እየተጠበቀ ነበር።
ሞቱ ከተባሉ ከስድስት ቀን በኋላ ለቀብር ሲሰናዳ ሳጥናቸው ሲከፈት ሴትዯ በሳጥን ውስጥ የሉም።
ጎረቤት ደነገጠ። በማድቤት ውስጥ ምግብ ሲያበስሉ ታዩ ።
ሴትዮም እንዲህ አሉ" ለረጅም ጊዜ ተኝቼ ነበር። ከእንቅልፌ ስነሳ በጣም ረሃብ ተሰማኝና የምበላው ነገር ማብሰል ፈለግኩ። ለመውጣት የአስከሬን ሳጥኑን ክዳን ለረጅም ጊዜ ገፍቼ ነበር።”
በመጀመሪያ ሐኪሞቹ ግራ ተጋብተው ነበር። ሆኖም ሴትዮን ከመረመሩ በኋላ፣ የአንድ ሰው አተነፋፈስ የሚቆምበት ነገር ግን ሰውነቱ ሙቀት የሚይዝበት "ሰው ሰራሽ ሞት" (artificial death) በመባል የሚታወቅ ያልተለመደ ሁኔታ እንዳጋጠማቸው ደምድመዋል።
ዶክተሮቹ አክለውም ፡"ለበርካታ ቀናት አስከሬኑን በቤት ውስጥ የማቆየት የአካባቢው ባህል ምስጋና ይግባውና ሴትዯ መዳን ችላለች" ብለዋል።
Sponsored by
Surafel
8 months ago
"የራስን የባሕር በር ማግኘት የሚባለው አጀንዳ አደገኛ ነው"
-ኤርትራ-
#ethiopia | የኢትዮጵያው ገዥ ብልጽግና ፓርቲ፣ ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ የማቋቋም ፍላጎቱ "የደኅንነት አመክንዮም" ሆነ "የደኅንነት ትሩፋት" የለውም ሲሉ የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል አጣጣሉ።
የጉዳዩ ዋና ውዝግብ የባሕር በር አይደለም ያሉት የማነ፣ ኢትዮጵያ ለንግድ አገልግሎት አዋጭ የሆኑ ስምምነቶች ላይ ለመድረስ በርካታ አማራጮች አሏት ብለዋል።
የማነ፣ "የራስን የባሕር በር ማግኘት" የሚባለው አጀንዳ ግን "አደገኛ" እና "የኢትዮጵያ ጎረቤቶችን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት የሚጥስ" መሆኑን ገልጸዋል።
" ሌላኛው የብልጽግና ፓርቲ አስገራሚ የራስን የባሕር በር ጥያቄ፣ ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ ለማቋቋም ፍላጎት ያለው መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጡ ነው" ሲሉም ተችተዋል።
የንግድ ልውውጡን በቀይ ባሕር በኩል የሚያደርግ ማንኛውም አገር ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ የማቋቋም ሕጋዊ መብት ይኖረዋል ማለት እንዳልሆነም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
ብልጽግና ፓርቲ የውጭ ወታደራዊ አዛዦች በአዲስ አበባ አንዳንድ ጊዜ የሚያደርጓቸውን "ተራ" ጉብኝቶች አጣሞ የማቅረብ አሰልቺ አካሄድ ጀምሯል በማለት የማነ አያይዘው የተቹ ሲሆን፣ ፓርቲው የአሜሪካው የአፍሪካ ወታደራዊ ዕዝ እንዲሁም የጣሊያን ባሕር ኃይልና የፈረንሳይ ጦር ኃይል አዛዦች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የባሕር በር የማግኘት ፍላጎቱን የሚደግፉ አስመስሎ አቅርቧቸዋል ማለታቸውን ዋዜማ ሬዲዮ ዘግባለች፡፡
-ኤርትራ-
#ethiopia | የኢትዮጵያው ገዥ ብልጽግና ፓርቲ፣ ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ የማቋቋም ፍላጎቱ "የደኅንነት አመክንዮም" ሆነ "የደኅንነት ትሩፋት" የለውም ሲሉ የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል አጣጣሉ።
የጉዳዩ ዋና ውዝግብ የባሕር በር አይደለም ያሉት የማነ፣ ኢትዮጵያ ለንግድ አገልግሎት አዋጭ የሆኑ ስምምነቶች ላይ ለመድረስ በርካታ አማራጮች አሏት ብለዋል።
የማነ፣ "የራስን የባሕር በር ማግኘት" የሚባለው አጀንዳ ግን "አደገኛ" እና "የኢትዮጵያ ጎረቤቶችን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት የሚጥስ" መሆኑን ገልጸዋል።
" ሌላኛው የብልጽግና ፓርቲ አስገራሚ የራስን የባሕር በር ጥያቄ፣ ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ ለማቋቋም ፍላጎት ያለው መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጡ ነው" ሲሉም ተችተዋል።
የንግድ ልውውጡን በቀይ ባሕር በኩል የሚያደርግ ማንኛውም አገር ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ የማቋቋም ሕጋዊ መብት ይኖረዋል ማለት እንዳልሆነም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
ብልጽግና ፓርቲ የውጭ ወታደራዊ አዛዦች በአዲስ አበባ አንዳንድ ጊዜ የሚያደርጓቸውን "ተራ" ጉብኝቶች አጣሞ የማቅረብ አሰልቺ አካሄድ ጀምሯል በማለት የማነ አያይዘው የተቹ ሲሆን፣ ፓርቲው የአሜሪካው የአፍሪካ ወታደራዊ ዕዝ እንዲሁም የጣሊያን ባሕር ኃይልና የፈረንሳይ ጦር ኃይል አዛዦች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የባሕር በር የማግኘት ፍላጎቱን የሚደግፉ አስመስሎ አቅርቧቸዋል ማለታቸውን ዋዜማ ሬዲዮ ዘግባለች፡፡
8 months ago
"የራስን የባሕር በር ማግኘት የሚባለው አጀንዳ አደገኛ ነው" - ኤርትራ-
የኢትዮጵያው ገዥ ብልጽግና ፓርቲ፣ ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ የማቋቋም ፍላጎቱ "የደኅንነት አመክንዮም" ሆነ "የደኅንነት ትሩፋት" የለውም ሲሉ የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል አጣጣሉ።
የጉዳዩ ዋና ውዝግብ የባሕር በር አይደለም ያሉት የማነ፣ ኢትዮጵያ ለንግድ አገልግሎት አዋጭ የሆኑ ስምምነቶች ላይ ለመድረስ በርካታ አማራጮች አሏት ብለዋል።
የማነ፣ "የራስን የባሕር በር ማግኘት" የሚባለው አጀንዳ ግን "አደገኛ" እና "የኢትዮጵያ ጎረቤቶችን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት የሚጥስ" መሆኑን ገልጸዋል።
"ሌላኛው የብልጽግና ፓርቲ አስገራሚ የራስን የባሕር በር ጥያቄ፣ ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ ለማቋቋም ፍላጎት ያለው መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጡ ነው" ሲሉም ተችተዋል።
የንግድ ልውውጡን በቀይ ባሕር በኩል የሚያደርግ ማንኛውም አገር ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ የማቋቋም ሕጋዊ መብት ይኖረዋል ማለት እንዳልሆነም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
ብልጽግና ፓርቲ የውጭ ወታደራዊ አዛዦች በአዲስ አበባ አንዳንድ ጊዜ የሚያደርጓቸውን "ተራ" ጉብኝቶች አጣሞ የማቅረብ አሰልቺ አካሄድ ጀምሯል በማለት የማነ አያይዘው የተቹ ሲሆን፣ ፓርቲው የአሜሪካው የአፍሪካ ወታደራዊ ዕዝ እንዲሁም የጣሊያን ባሕር ኃይልና የፈረንሳይ ጦር ኃይል አዛዦች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የባሕር በር የማግኘት ፍላጎቱን የሚደግፉ አስመስሎ አቅርቧቸዋል ማለታቸውን ዋዜማ ሬዲዮ ዘግባለች፡፡
seledadotio
seledadotio
የኢትዮጵያው ገዥ ብልጽግና ፓርቲ፣ ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ የማቋቋም ፍላጎቱ "የደኅንነት አመክንዮም" ሆነ "የደኅንነት ትሩፋት" የለውም ሲሉ የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል አጣጣሉ።
የጉዳዩ ዋና ውዝግብ የባሕር በር አይደለም ያሉት የማነ፣ ኢትዮጵያ ለንግድ አገልግሎት አዋጭ የሆኑ ስምምነቶች ላይ ለመድረስ በርካታ አማራጮች አሏት ብለዋል።
የማነ፣ "የራስን የባሕር በር ማግኘት" የሚባለው አጀንዳ ግን "አደገኛ" እና "የኢትዮጵያ ጎረቤቶችን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት የሚጥስ" መሆኑን ገልጸዋል።
"ሌላኛው የብልጽግና ፓርቲ አስገራሚ የራስን የባሕር በር ጥያቄ፣ ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ ለማቋቋም ፍላጎት ያለው መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጡ ነው" ሲሉም ተችተዋል።
የንግድ ልውውጡን በቀይ ባሕር በኩል የሚያደርግ ማንኛውም አገር ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ የማቋቋም ሕጋዊ መብት ይኖረዋል ማለት እንዳልሆነም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
ብልጽግና ፓርቲ የውጭ ወታደራዊ አዛዦች በአዲስ አበባ አንዳንድ ጊዜ የሚያደርጓቸውን "ተራ" ጉብኝቶች አጣሞ የማቅረብ አሰልቺ አካሄድ ጀምሯል በማለት የማነ አያይዘው የተቹ ሲሆን፣ ፓርቲው የአሜሪካው የአፍሪካ ወታደራዊ ዕዝ እንዲሁም የጣሊያን ባሕር ኃይልና የፈረንሳይ ጦር ኃይል አዛዦች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የባሕር በር የማግኘት ፍላጎቱን የሚደግፉ አስመስሎ አቅርቧቸዋል ማለታቸውን ዋዜማ ሬዲዮ ዘግባለች፡፡
seledadotio
seledadotio
9 months ago
ዮም
ንሴብሖ ፍቅሬ
አሰናኝ፡፦ ጥላሁን ክፍሌ እርገጤ
#ethiopia | በተለያዩ ጊዜያት፣ በተለያዩ የዓለማችን ሀገራት፣ ከተለያዩ ቤተሰቦች የኦቲዝም ተጠቂ የሆኑ ህጻናት ይወለዳሉ፡፡ በስልጣኔና በአመለካከት የበለጸጉት ሀገራትም ኦቲዝምን እንደአንድ የተፈጥሮ ጸጋ በመቀበል በኦቲዝም ጥላ ሥር ለመኖር ዓለማችንን የተቀላቀሉትን ህጻናት እንደየፍላጎታቸው ተንከባክበው በማሳደግ፣ እንደማንኛውም የሰው ልጅ ሁሉ ለሚኖሩባት ዓለም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ብቁ ዜጋ እንዲሆኑ ይሠራሉ፡፡
በእርግጥ ከዓለማችን ሀገሮች ብዛት አንጻር በዚህ መልኩ የሚተጉት ጥቂት ናቸው፡፡ ቀላል ቁጥር የማይዘው የዓለማችን በተለይም የሀገራችን ማህበረሰብ ኦቲዝምን ድጋፍና እንክብካቤ የሚሻ እክል አድርጎ ከመቁጠር ይልቅ፣ “ርግማን” እንደሆነ አምኖ ይህንኑ የሚያስተጋባ ነው፡፡
የበኩር ልጃችን ዮም ንሴብሖ፣ የኦቲዝም ተጠቂ መሆኑን ካወቅንበት ዕለት ጀምሮ እኔና ቤተሰቤ እያደረግናቸው ያሉትን ወሰን አልባ ጥረቶች በመጽሐፍ ሰንዶ ለአንባቢያን ለማድረስ መነሳቱን ከተፈጠሩት ምክንያቶች አንዱም ኦቲዝምን በሚመለከት ያለን መረዳት ለማረቅ መሻት ነው፡፡
በሀገራችን በኦቲዝም ዙሪያ ያለውን የተዛባ አረዳድ በማስተካከል ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖር የሚረዳ ተጠቃሽ መጽሐፍ' ካበረከተው ከዶክተር ዮናስ ባህረጥበብ ጋር በዮም ምክንያት በተደጋጋሚ የመገናኘት አጋጣሚ ነበረኝ።
ከእነዚህ ቀናት በአንዱ ዶክተር ዮናስ፣ “የሕይወት ተሞክሮህ በመጽሐፍ ተዘጋጅቶ ለአንባቢ ቢቀርብ ብዙ ነገር ሊያስተምርይችላል" በሚል የሰነዘረው አስተያየት ልቤን ሰቅዞ ይዞት፣ ለረጅም ጊዜ ሳስብበት ቆየሁ:: የዶክተር ዮናስ ሃሳብ በልቤ ውስጥ ብቻ አልቀረም:: ከወዳጄ እና አብሮ አድጌ ጥላሁን ክፍሌ ጋር በመሆን ይህንን በእጃችሁ ላይ የሚገኘው መጽሐፍ እንዲወለድ ሆነ፡፡ በእርግጥም ምጡ ቀላል አልነበረም!
ከጥላሁን ጋር መጽሐፉን ለማዘጋጀት በምንተጋበት ጊዜ፣ እጅግ የሚወዳቸውና የሚሳሳላቸው እናቱ ወ/ሮ ጥሩወርቅ በጠና ታመው ሆስፒታል ገቡ፡፡ በዚህ ሁኔታ የመጽሐፉን ዝግጅት ማስቀጠል፣ ሙሉ ጊዜውን ተጠቅሞ እናቱን ለሚያስታምመው ጥላሁን ከባድ ነበርና፣ ሂደቱ ለጊዜውም ቢሆን እንዲቋረጥ ሆነ:: ሆኖም የፈጣሪ ፈቃድ ሆነና፣ ለአምስት ወራት ያህል በሕክምና ሲረዱ የቆዩት እናቱ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ፡፡ ጥላሁን ክፍሌን የሚያውቅ ማንም ሰው እናቱን ያውቃል፧ ሁለቱን የሚያውቅ ደግሞ በመካከላቸው ያለውን የተለየ ፍቅር ያውቃል:: ያን ጊዜ፣ ጥላሁን የቀድሞው ጥንካሬ እና ሞራል ኖሮት ይህን ሥራ እንጨርሰዋለን
ምክንያት አለው ብዬ ራሴን አሳመንኩ። እንዴት ይበረታ ይሆን? እያልኩ ብጨነቅም ምስጋና ለፈጣሪ ይሁንና አጽናኝ መላእኩን ልኮ እኒያን ጥቋቁር የሐዘን ቀናት በጸጋው አሳለፋቸው:: ብርቱው ባለተሰጥኦ ጥላሁንም በሚያስደንቅ ትጋትና ብርታት መጽሐፉን አጠናቆ እነሆኝ አለኝ፡
ባሳለፍኩት የሕይወት መንገድ ያጋጠሙኝን የደስታም ሆነ የሐዘን፣ የከፍታም ሆነ የዝቅታ፣ የስኬትም ሆነ የመፈተን ውጣ ውረዶችን በዚህ መጽሐፍ ለማጋራት ሞክሬአለሁ፡፡ በተለይም ልጃችን ዮም ንሴብሖ የኦቲዝም ተጠቂ መሆኑን ካወቅንበት ዕለት ጀምሮ እኔና ቤተሰቤ መፍትሔና ፈውስ ፍለጋ፣ የወጣን የወረድንባቸው ጎዳናዎች፣ ያንኳኳናቸው ደጆች፣ የገፋናቸው የመከፋትና የመፈተን ወራት እና ለዐይን ጥቅሻ ዕድሜ እንኳን ከጎናችን ባልተለየንና ይልቁንም ከፊታችን ይቀድም በነበረው እግዚአብሔር የቻልናቸውን ስኬቶች በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ታነባላችሁ፡፡
ከሕይወት ልምዴ ከተወሰደ ቀጥተኛ ተሞክሮ በተጨማሪ፣ በጉዳዩ ዙሪያ ከንባብ እና በኦቲዝም የተጠቁ ልጆች ካላቸው ወላጆችም ጋርበነበረኝ ማኅበራዊ ግንኙነቶች የተረዳኋቸውን ግንዛቤዎች በመጽሐፉ ለማካተት ሞክሪያለሁ፡፡
እንደሚታወቀው ኦቲዝምን በተመለከተ ህብረተሰባችን ያለው ግንዛቤ በአብዛኛው የተዛባ ነው፡፡ ይህም ወላጆች/አሳዳጊዎች ሊሻሻል በሚችለው በዚህ የአእምሮ ዕድገት እክል የተጠቁ ልጆቻቸውን ለማገዝ የሚችሉትን እንዳያደርጉ፣ በዚህም የእነሱና የልጆቻቸው ስቃይ ቀጣይና ማብቂያ የሌለው እንዲሆን አድርጓል፡፡
ይህ መጽሐፍ በኦቲዝም የተጠቁ ልጆች ላላቸው ወላጆች እና በኦቲዝም ሳቢያ የሚፈጠሩ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመቅረፍ ለሚሰሩ አካላት እንዲሁም ለመላው ማኅበረሰባችን የተሻለ ግንዛቤን በማስጨበጥ አዎንታዊ ተጽዕኖ ይፈጥራል የሚል እምነት አለኝ፡፡
መጽሀፉ በአራት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን የመጀመሪያ ምዕራፍ ዮም ከመወለዱ በፊት የነበረኝን ህይወት በመጠኑም ቢሆን የሚያስቃኝ ነው:: ሁለተኛው ምዕራፍ የመጽሃፉ ዋና አስኳል ሲሆን ይህም ዮም ከተወለደ ጀምሮ ይህ መጽሀፍ እስኪዘጋጅ ድረስ የተኖረውን ዋና ዋና የህይወት ክፍል ይዳስሳል:: ሶስተኛው ምዕራፍ ደግሞ ልጆቻቸው በኦቲዝም የተጠቁ እና በእኔ ማህበራዊ ህይወት ዙሪያ የነበሩ ወላጆች ቅንጫቢ ታሪኮች ስብስብ ነው:: በመጨረሻው ምዕራፍ ከእኔ የህይወት ልምድ እና ትዝብት በተጨማሪ በኦቲዝም ዙሪያ ከተለያዩ ምንጮች የቃረምኳቸው ጠቃሚ እውነታዎች ተገልፀዋል:: በእኔ እና በልጄ እውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ ለበጎ አላማና ተግባር የተዘጋጀውን ይህን መፅሃፍ በአክብሮት ታነቡልኝ ዘንድ የምጋብዛችሁ በፍፁም ትህትና ዝቅ ብዬ ነው፡፡
መልካም ንባብ!
ንሴብሖ ፍቅሬ ወንድማገኝ
***
አቶ ንሴብሖ ፍቅሪ ከባለቤቱ ጋር በመሆን የኦቲዝም ተግዳሮት ያለበትን ልጃቸውን በመንከባከብ ያለፉበትንና እያደረጉ ያለውን ልምድ ለህብረተሰቡ ለማካፈል ይህን መጽሐፍ በማዘጋጀቱ እጅግ እመሰግነዋለሁ።
ጥንዶቹ ባጋጠማቸው ተግዳሮት ተስፋ ላይቆርጡ ስለሁኔታውና መወለድ ስለሚገባቸው እርምጃዎች በራሳቸው ጥረት ተረድተው አስፈላጊውን እንክብካቤ ሁሉ በፍጹም ፍቅር እያደረጉ መገኘታቸው የሚደነቅ ነው።
ይህ ልምዳቸውም በመጽሐፍ መታተሙ፣ ተመሳሳይ ተግዳሮት በቤተሰባቸው ውስጥ ኖሮ ፣ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ግራ ለተጋቡና፣ ምናልባትም የማይገቡ እርምጃዎችን ለሚተገብሩ ቤተሰቦች ተገቢውን መንገድ በማመላከት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ ትልቅ ነው።
በህብረተሰቡ ውስጥ ከሚወለዱ እንድ መቶ ህፃናት አንዱ ወይም ሁለቱ የኦቲዝም ተግዳሮት የሆነ የነርቭ እና የእድገት ልዩነት ሊያጋጥማቸው ይችላል ፤ ነገሩ እጣ ነው። እጣው በማንኛውም ጊዜ፣ በማንኛችንም ቤት ሊከሰት ይችላል። ስለዚህ ሁላችንም በተጨባጭ ልምድ ከካበተው ንሴብሖና ቤተሰቡ በመማር ስለጉዳዩ እውቀት እንዲኖረን እመክራለሁ። ለዚህም የዚህ መጽሐፍ አስተዋጽኦ የጎላ ነው።
ዶ/ር ምኒልክ ደስታ
የአዋቂዎችና ህፃናት አእምሮ ሐኪም
***
ልጆቻቸው የኦቲዝም ችግር ያለባቸው በርካታ ወላጆች ፣ የሰዎችን አላዋቂ አንደበትና መገለል በመፍራት የልጆቻቸውንና የቤተሰቦቻቸውን ችግርና ስቃይ በሚደብቁበት ወቅት፣ ንሴብሖ የኦቲዝም ተጠቂ የሆነውን ልጁን ችግርና የቤተሰቡን ውጣ ውረድ በመጽሐፍ መተረኩ የሚያስመሰግነው ነው።
እርግጥ ነው ንሴብሖ በልጁ ዮም ምክንያት በብዙ መረበሸ፤ እንቅልፍ ማጣት፤ ማህበራዊ መገለል ተከብቦ ያሳለፈውን ህይወት እና የከፈለው ዋጋ ቀላል አልነበረም፤ ይህም ሆኖ "የዮም መፃኢ እድል ፈንታ ምን ይሆን?'' የሚለው ከባድ የሃሳብ ሸክም አሁንም ከትከሻው አልወረደም።
ይህ ግለ ታሪክ በዚህ ችግር ውሰጥ የምናልፍ ቤተሰቦችን ችግሮች ገልጦና አጉልቶ የሚያሳይ ሲሆን ፣ መጽሐፉን ልዩ የሚያደረገው ዋናው ነገር እንደተለመደው ስለ ችግሩ እውቀት ባላቸው ባለሞያዎች ሳይሆን የችግሩ ገፈት ቀማሽ በሆነ አባት መቅረቡ ነው።
መልዕክቱ የኦቲዝምን ችግር እየተጋፈጡ ላሉ ቤተሰቦች አስተማሪና ጉልበትን የሚሰጥ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ ተጋብተው መውለድ ለሚያቅዱ ጥንዶች፣ ለእምነትና ለትምህርት ተቋማት፣ በኦቲዝም ላይ ለሚሰሩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ እንዲሁም ለመላው ማህበረሰብ ጥልቅ ግንዛቤን በማስጨበጥ ረገድ የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው።
ይህንን መጽሐፍ ሳነብ ፣ በፈተና ውስጥም ሆነን በጎ ማሰብና ፣ ከችግራችን በላይ በሆነ ጠንካራ ማንነት መታነጽ እንደሚቻል አይቻለሁና ሁሉም እንዲያነበው እመኛለሁ።
ዶ/ር ፍርድአወቀ ማሞ የቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት
***
ለብዙዎቻችን ፈተና (መከራ) ሁልጊዜ የኃጢአት ውጤት ይመስለናል። አንድ ሰው ጤናን፣ ሀብትን፣ ልጅንና የመሳሰሉትን ሲያጣ እግዚአብሔር በኃጢአቱ እየቀጣው ነው ብለን እንደመድማለን፡፡
አቶ ንሴብሖ ፍቅሬና ባለቤቱ ወይዘሮ ሳምራዊት ድንቁ ፈተናን በመጋፈጥ የጽናት ተምሳሌት ሆነውናል… አቶ ንሴብሖ በኦቲዝም የተጠቁ ልጆችን ለሚያሳድጉ ወላጆች/ አሳዳጊዎች ጉልበትን የሚሰጥ፣ ጥበብን የሚያመላክት ሥራን መሥራቱ ደስ ያሰኛል።
ይኸውም ያላዋቂዎችን ትችት በመፍራት በእንዲህ ዓይነት ሕይወት ያሉ ወገኖችን ከማግለል ይልቅ ማቀፍና መንከባከብ፣ ሰብአዊና ሃይማኖታዊ ግዴታ መሆኑን በመጽሐፍ ሰንዶ በማቅረቡ ሊመሰገን ይገባል።
በብዙ ፈተና ውስጥ ቢያልፍም ንሴብሖ አሁንም አምላኩን አመስጋኝ መሆኑ ሌላው በጣም ደስ የሚያሰኝ ነገር ነው። ይህንን መጽሐፍም ማንበብ ለሁሉም፣ በሁሉ መንገድ አቅም ይሰጣል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
***
ንሴብሖ ፍቅሬ
ስልክ
+251911212012
ኢ-ሜይል
yomnesebehogmail.com
ንሴብሖ ፍቅሬ
አሰናኝ፡፦ ጥላሁን ክፍሌ እርገጤ
#ethiopia | በተለያዩ ጊዜያት፣ በተለያዩ የዓለማችን ሀገራት፣ ከተለያዩ ቤተሰቦች የኦቲዝም ተጠቂ የሆኑ ህጻናት ይወለዳሉ፡፡ በስልጣኔና በአመለካከት የበለጸጉት ሀገራትም ኦቲዝምን እንደአንድ የተፈጥሮ ጸጋ በመቀበል በኦቲዝም ጥላ ሥር ለመኖር ዓለማችንን የተቀላቀሉትን ህጻናት እንደየፍላጎታቸው ተንከባክበው በማሳደግ፣ እንደማንኛውም የሰው ልጅ ሁሉ ለሚኖሩባት ዓለም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ብቁ ዜጋ እንዲሆኑ ይሠራሉ፡፡
በእርግጥ ከዓለማችን ሀገሮች ብዛት አንጻር በዚህ መልኩ የሚተጉት ጥቂት ናቸው፡፡ ቀላል ቁጥር የማይዘው የዓለማችን በተለይም የሀገራችን ማህበረሰብ ኦቲዝምን ድጋፍና እንክብካቤ የሚሻ እክል አድርጎ ከመቁጠር ይልቅ፣ “ርግማን” እንደሆነ አምኖ ይህንኑ የሚያስተጋባ ነው፡፡
የበኩር ልጃችን ዮም ንሴብሖ፣ የኦቲዝም ተጠቂ መሆኑን ካወቅንበት ዕለት ጀምሮ እኔና ቤተሰቤ እያደረግናቸው ያሉትን ወሰን አልባ ጥረቶች በመጽሐፍ ሰንዶ ለአንባቢያን ለማድረስ መነሳቱን ከተፈጠሩት ምክንያቶች አንዱም ኦቲዝምን በሚመለከት ያለን መረዳት ለማረቅ መሻት ነው፡፡
በሀገራችን በኦቲዝም ዙሪያ ያለውን የተዛባ አረዳድ በማስተካከል ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖር የሚረዳ ተጠቃሽ መጽሐፍ' ካበረከተው ከዶክተር ዮናስ ባህረጥበብ ጋር በዮም ምክንያት በተደጋጋሚ የመገናኘት አጋጣሚ ነበረኝ።
ከእነዚህ ቀናት በአንዱ ዶክተር ዮናስ፣ “የሕይወት ተሞክሮህ በመጽሐፍ ተዘጋጅቶ ለአንባቢ ቢቀርብ ብዙ ነገር ሊያስተምርይችላል" በሚል የሰነዘረው አስተያየት ልቤን ሰቅዞ ይዞት፣ ለረጅም ጊዜ ሳስብበት ቆየሁ:: የዶክተር ዮናስ ሃሳብ በልቤ ውስጥ ብቻ አልቀረም:: ከወዳጄ እና አብሮ አድጌ ጥላሁን ክፍሌ ጋር በመሆን ይህንን በእጃችሁ ላይ የሚገኘው መጽሐፍ እንዲወለድ ሆነ፡፡ በእርግጥም ምጡ ቀላል አልነበረም!
ከጥላሁን ጋር መጽሐፉን ለማዘጋጀት በምንተጋበት ጊዜ፣ እጅግ የሚወዳቸውና የሚሳሳላቸው እናቱ ወ/ሮ ጥሩወርቅ በጠና ታመው ሆስፒታል ገቡ፡፡ በዚህ ሁኔታ የመጽሐፉን ዝግጅት ማስቀጠል፣ ሙሉ ጊዜውን ተጠቅሞ እናቱን ለሚያስታምመው ጥላሁን ከባድ ነበርና፣ ሂደቱ ለጊዜውም ቢሆን እንዲቋረጥ ሆነ:: ሆኖም የፈጣሪ ፈቃድ ሆነና፣ ለአምስት ወራት ያህል በሕክምና ሲረዱ የቆዩት እናቱ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ፡፡ ጥላሁን ክፍሌን የሚያውቅ ማንም ሰው እናቱን ያውቃል፧ ሁለቱን የሚያውቅ ደግሞ በመካከላቸው ያለውን የተለየ ፍቅር ያውቃል:: ያን ጊዜ፣ ጥላሁን የቀድሞው ጥንካሬ እና ሞራል ኖሮት ይህን ሥራ እንጨርሰዋለን
ምክንያት አለው ብዬ ራሴን አሳመንኩ። እንዴት ይበረታ ይሆን? እያልኩ ብጨነቅም ምስጋና ለፈጣሪ ይሁንና አጽናኝ መላእኩን ልኮ እኒያን ጥቋቁር የሐዘን ቀናት በጸጋው አሳለፋቸው:: ብርቱው ባለተሰጥኦ ጥላሁንም በሚያስደንቅ ትጋትና ብርታት መጽሐፉን አጠናቆ እነሆኝ አለኝ፡
ባሳለፍኩት የሕይወት መንገድ ያጋጠሙኝን የደስታም ሆነ የሐዘን፣ የከፍታም ሆነ የዝቅታ፣ የስኬትም ሆነ የመፈተን ውጣ ውረዶችን በዚህ መጽሐፍ ለማጋራት ሞክሬአለሁ፡፡ በተለይም ልጃችን ዮም ንሴብሖ የኦቲዝም ተጠቂ መሆኑን ካወቅንበት ዕለት ጀምሮ እኔና ቤተሰቤ መፍትሔና ፈውስ ፍለጋ፣ የወጣን የወረድንባቸው ጎዳናዎች፣ ያንኳኳናቸው ደጆች፣ የገፋናቸው የመከፋትና የመፈተን ወራት እና ለዐይን ጥቅሻ ዕድሜ እንኳን ከጎናችን ባልተለየንና ይልቁንም ከፊታችን ይቀድም በነበረው እግዚአብሔር የቻልናቸውን ስኬቶች በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ታነባላችሁ፡፡
ከሕይወት ልምዴ ከተወሰደ ቀጥተኛ ተሞክሮ በተጨማሪ፣ በጉዳዩ ዙሪያ ከንባብ እና በኦቲዝም የተጠቁ ልጆች ካላቸው ወላጆችም ጋርበነበረኝ ማኅበራዊ ግንኙነቶች የተረዳኋቸውን ግንዛቤዎች በመጽሐፉ ለማካተት ሞክሪያለሁ፡፡
እንደሚታወቀው ኦቲዝምን በተመለከተ ህብረተሰባችን ያለው ግንዛቤ በአብዛኛው የተዛባ ነው፡፡ ይህም ወላጆች/አሳዳጊዎች ሊሻሻል በሚችለው በዚህ የአእምሮ ዕድገት እክል የተጠቁ ልጆቻቸውን ለማገዝ የሚችሉትን እንዳያደርጉ፣ በዚህም የእነሱና የልጆቻቸው ስቃይ ቀጣይና ማብቂያ የሌለው እንዲሆን አድርጓል፡፡
ይህ መጽሐፍ በኦቲዝም የተጠቁ ልጆች ላላቸው ወላጆች እና በኦቲዝም ሳቢያ የሚፈጠሩ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመቅረፍ ለሚሰሩ አካላት እንዲሁም ለመላው ማኅበረሰባችን የተሻለ ግንዛቤን በማስጨበጥ አዎንታዊ ተጽዕኖ ይፈጥራል የሚል እምነት አለኝ፡፡
መጽሀፉ በአራት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን የመጀመሪያ ምዕራፍ ዮም ከመወለዱ በፊት የነበረኝን ህይወት በመጠኑም ቢሆን የሚያስቃኝ ነው:: ሁለተኛው ምዕራፍ የመጽሃፉ ዋና አስኳል ሲሆን ይህም ዮም ከተወለደ ጀምሮ ይህ መጽሀፍ እስኪዘጋጅ ድረስ የተኖረውን ዋና ዋና የህይወት ክፍል ይዳስሳል:: ሶስተኛው ምዕራፍ ደግሞ ልጆቻቸው በኦቲዝም የተጠቁ እና በእኔ ማህበራዊ ህይወት ዙሪያ የነበሩ ወላጆች ቅንጫቢ ታሪኮች ስብስብ ነው:: በመጨረሻው ምዕራፍ ከእኔ የህይወት ልምድ እና ትዝብት በተጨማሪ በኦቲዝም ዙሪያ ከተለያዩ ምንጮች የቃረምኳቸው ጠቃሚ እውነታዎች ተገልፀዋል:: በእኔ እና በልጄ እውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ ለበጎ አላማና ተግባር የተዘጋጀውን ይህን መፅሃፍ በአክብሮት ታነቡልኝ ዘንድ የምጋብዛችሁ በፍፁም ትህትና ዝቅ ብዬ ነው፡፡
መልካም ንባብ!
ንሴብሖ ፍቅሬ ወንድማገኝ
***
አቶ ንሴብሖ ፍቅሪ ከባለቤቱ ጋር በመሆን የኦቲዝም ተግዳሮት ያለበትን ልጃቸውን በመንከባከብ ያለፉበትንና እያደረጉ ያለውን ልምድ ለህብረተሰቡ ለማካፈል ይህን መጽሐፍ በማዘጋጀቱ እጅግ እመሰግነዋለሁ።
ጥንዶቹ ባጋጠማቸው ተግዳሮት ተስፋ ላይቆርጡ ስለሁኔታውና መወለድ ስለሚገባቸው እርምጃዎች በራሳቸው ጥረት ተረድተው አስፈላጊውን እንክብካቤ ሁሉ በፍጹም ፍቅር እያደረጉ መገኘታቸው የሚደነቅ ነው።
ይህ ልምዳቸውም በመጽሐፍ መታተሙ፣ ተመሳሳይ ተግዳሮት በቤተሰባቸው ውስጥ ኖሮ ፣ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ግራ ለተጋቡና፣ ምናልባትም የማይገቡ እርምጃዎችን ለሚተገብሩ ቤተሰቦች ተገቢውን መንገድ በማመላከት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ ትልቅ ነው።
በህብረተሰቡ ውስጥ ከሚወለዱ እንድ መቶ ህፃናት አንዱ ወይም ሁለቱ የኦቲዝም ተግዳሮት የሆነ የነርቭ እና የእድገት ልዩነት ሊያጋጥማቸው ይችላል ፤ ነገሩ እጣ ነው። እጣው በማንኛውም ጊዜ፣ በማንኛችንም ቤት ሊከሰት ይችላል። ስለዚህ ሁላችንም በተጨባጭ ልምድ ከካበተው ንሴብሖና ቤተሰቡ በመማር ስለጉዳዩ እውቀት እንዲኖረን እመክራለሁ። ለዚህም የዚህ መጽሐፍ አስተዋጽኦ የጎላ ነው።
ዶ/ር ምኒልክ ደስታ
የአዋቂዎችና ህፃናት አእምሮ ሐኪም
***
ልጆቻቸው የኦቲዝም ችግር ያለባቸው በርካታ ወላጆች ፣ የሰዎችን አላዋቂ አንደበትና መገለል በመፍራት የልጆቻቸውንና የቤተሰቦቻቸውን ችግርና ስቃይ በሚደብቁበት ወቅት፣ ንሴብሖ የኦቲዝም ተጠቂ የሆነውን ልጁን ችግርና የቤተሰቡን ውጣ ውረድ በመጽሐፍ መተረኩ የሚያስመሰግነው ነው።
እርግጥ ነው ንሴብሖ በልጁ ዮም ምክንያት በብዙ መረበሸ፤ እንቅልፍ ማጣት፤ ማህበራዊ መገለል ተከብቦ ያሳለፈውን ህይወት እና የከፈለው ዋጋ ቀላል አልነበረም፤ ይህም ሆኖ "የዮም መፃኢ እድል ፈንታ ምን ይሆን?'' የሚለው ከባድ የሃሳብ ሸክም አሁንም ከትከሻው አልወረደም።
ይህ ግለ ታሪክ በዚህ ችግር ውሰጥ የምናልፍ ቤተሰቦችን ችግሮች ገልጦና አጉልቶ የሚያሳይ ሲሆን ፣ መጽሐፉን ልዩ የሚያደረገው ዋናው ነገር እንደተለመደው ስለ ችግሩ እውቀት ባላቸው ባለሞያዎች ሳይሆን የችግሩ ገፈት ቀማሽ በሆነ አባት መቅረቡ ነው።
መልዕክቱ የኦቲዝምን ችግር እየተጋፈጡ ላሉ ቤተሰቦች አስተማሪና ጉልበትን የሚሰጥ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ ተጋብተው መውለድ ለሚያቅዱ ጥንዶች፣ ለእምነትና ለትምህርት ተቋማት፣ በኦቲዝም ላይ ለሚሰሩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ እንዲሁም ለመላው ማህበረሰብ ጥልቅ ግንዛቤን በማስጨበጥ ረገድ የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው።
ይህንን መጽሐፍ ሳነብ ፣ በፈተና ውስጥም ሆነን በጎ ማሰብና ፣ ከችግራችን በላይ በሆነ ጠንካራ ማንነት መታነጽ እንደሚቻል አይቻለሁና ሁሉም እንዲያነበው እመኛለሁ።
ዶ/ር ፍርድአወቀ ማሞ የቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት
***
ለብዙዎቻችን ፈተና (መከራ) ሁልጊዜ የኃጢአት ውጤት ይመስለናል። አንድ ሰው ጤናን፣ ሀብትን፣ ልጅንና የመሳሰሉትን ሲያጣ እግዚአብሔር በኃጢአቱ እየቀጣው ነው ብለን እንደመድማለን፡፡
አቶ ንሴብሖ ፍቅሬና ባለቤቱ ወይዘሮ ሳምራዊት ድንቁ ፈተናን በመጋፈጥ የጽናት ተምሳሌት ሆነውናል… አቶ ንሴብሖ በኦቲዝም የተጠቁ ልጆችን ለሚያሳድጉ ወላጆች/ አሳዳጊዎች ጉልበትን የሚሰጥ፣ ጥበብን የሚያመላክት ሥራን መሥራቱ ደስ ያሰኛል።
ይኸውም ያላዋቂዎችን ትችት በመፍራት በእንዲህ ዓይነት ሕይወት ያሉ ወገኖችን ከማግለል ይልቅ ማቀፍና መንከባከብ፣ ሰብአዊና ሃይማኖታዊ ግዴታ መሆኑን በመጽሐፍ ሰንዶ በማቅረቡ ሊመሰገን ይገባል።
በብዙ ፈተና ውስጥ ቢያልፍም ንሴብሖ አሁንም አምላኩን አመስጋኝ መሆኑ ሌላው በጣም ደስ የሚያሰኝ ነገር ነው። ይህንን መጽሐፍም ማንበብ ለሁሉም፣ በሁሉ መንገድ አቅም ይሰጣል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
***
ንሴብሖ ፍቅሬ
ስልክ
+251911212012
ኢ-ሜይል
yomnesebehogmail.com
9 months ago
ብሔራዊ ጥቅም
(የሀብታሙ ደባሱ የግል ሀሳብ)
#ethiopia | የአለምአቀፍ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ ንድፍ አውጭ በመባል በዓለም ደረጃ ስሙ የናኝው ሄንሪ ኪሲንጀር (Henry Kissinger) በተለያየ ጊዜያት ሀገር እና ብሔራዊ ጥቅምን በተመለከተ ያስቀመጣቸውን ትንታኔዎች መሰረት በማድረግ ግንዛቤን ለማዳበር ይረዳ ዘንድ እሳቤዎቹን ለማካፈል እሞክራለሁ።ይህ አንጋፋ ዲፕሎማት በዲፕሎማሲ ላይ ያለው አመለካከት በዓለም አቀፍ ግንኙነት ውስጥ እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ ጽንሰ-ሐሳቦች አንዱ ነው።ብሔራዊ ጥቅምን በተመለከተ የእሱ አቋም "እውነታዊነት" (Realism) ከሚባለው አስተሳሰብ የሚመነጭ ሲሆን፣ ዋና ትኩረቱ በብሔራዊ ጥቅም እና በስልጣን ሚዛን ላይ ነው።
🔴."እውነታዊነት" (Realpolitik- የኃይል ፖለቲካ):-ኪሲንጀር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በዋነኛነት በሀገራት ጥቅም (National Interest) መመራት እንዳለበት ያምናል-ከሞራል፣ከርዕዮተ ዓለም ወይም ከውስጥ ፖለቲካዊ ጉዳዮች በላይ ዲፕሎማሲ የሀገራትን ብሔራዊ ጥቅም ለመጠበቅና ለማራመድ የሚደረግ ተግባራዊና ስልታዊ ውይይት ነው። የሁለትዮሽ ድርድሮች እና ጥምረቶች (alliances) የሚፈጠሩት በጋራ እሴቶች ሳይሆን በጋራ ስጋቶች እና ጥቅሞች ላይ ተመስርተው ነው።
🔴.የስልጣን ሚዛን (Balance of Power):-ኪሲንጀር የዓለም አቀፍ ሥርዓት መረጋጋት (Stability) የሚረጋገጠው በስልጣን ሚዛን እንደሆነ አጥብቆ ያምናል።ዲፕሎማሲያዊ ሚና ዲፕሎማሲ በአንድ ሀገር የበላይነት እንዳይፈጠር የኃይል ክፍፍሉን በተከታታይ "የማስተካከል"ጥበብ ነው።ኃይለኛ የሆኑ ሀገራትን (Great Powers) በመካከላቸው የጥቅም ትስስር እንዲኖር በማድረግ ጦርነትን መከላከል እና ዓለም አቀፉን ሥርዓት ማረጋጋት እንደሆነ ይናገራል ።
🔴.የሕጋዊነት ጽንሰ-ሐሳብ (Legitimacy):-በኪሲንጀር አመለካከት፣ የዓለም አቀፍ ሥርዓት ሕጋዊነት ማለት ሁሉም ዋና ዋና ተዋናዮች (ሀገራት) አሁን ያለውን የሥርዓት አሠራር እና የወሰን መስመሮችን የሚቀበሉበት ሁኔታ ነው።ዲፕሎማሲ የሀገራትን ፍላጎት ሁሉ የሚያረካ ሳይሆን፣ ሁሉም ተዋናይ ምንም እንኳ ባይወደውም ከሥርዓቱ መውጣት የማይፈልግበትን የጋራ የመግባቢያ መሬት መፍጠር ነው።
🔴በታሪክ የተረጋገጠ ብሔራዊ ጥቅም:-ኪሲንጀር በዲፕሎማሲ ታሪክ ላይ ከፍተኛ ግንዛቤ ያለው ሲሆን፣ የዘመናዊ ዲፕሎማሲ መሠረት የተጣለው በ17ኛው ክፍለ ዘመን በካርዲናል ሪሼልዮ (Cardinal Richelieu) እና በ19ኛው ክፍለ ዘመን በኦስትሪያው ልዑል ሜተርኒች (Prince Metternich) መሆኑን ይጠቅሳል።
✍️እንደ መውጫ⁉️
በተግባር፣የኪሲንጀር ዲፕሎማሲ በታሪክ ውስጥ በሁለት ዋና ዋና ተግባራት ይታወቃል ከቻይና ጋር ያለውን ግንኙነት መክፈት (Opening China)በ1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ ከአሜሪካ ጠላት ከነበረችው ከኮሙኒስት ቻይና ጋር በድብቅ ድርድር በመጀመር፣ ለሶቭየት ህብረት ምላሽ የሚሆን ስልታዊ "ትሪያንግል" ፈጠሯል።
የሸትል ዲፕሎማሲ (Shuttle Diplomacy) በ1973 የዮም ኪፑር ጦርነት (Yom Kippur War) በኋላ በእስራኤል እና በአረብ ሀገራት መሪዎች መካከል በተደጋጋሚ በመመላለስ ግጭቶችን ለመፍታት የተጠቀመበት ዘዴ ልዩ ነበር
በአጭሩ፣ ኪሲንጀር ዲፕሎማሲን እና ብሔራዊ ጥቅምን ጉዳይ የሚያየው የኃይል ፖለቲካ መሳሪያ አድርጎ ነው ሀገራት ጦርነት ሳይገቡ ጥቅማቸውን እንዲያስጠብቁ እና በዓለም አቀፉ ሥርዓት ውስጥ የሚመጣውን ለውጥ በተግባራዊና ስልታዊ መንገድ እንዲያስተዳድሩ የሚያስችል ጥበብ ነው።
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መሳካት የድርሻዬን እወጣለሁ !
#ethiopia 🇪🇹
ለበለጠ ወዳጅነት የፃሃፊውን የኤክስ(X) እና የፌስቡክ ገፅ ይከታተሉ :-
🔗የኤክስ(X)ገፅ:-https://x.com/HDebasu?t=eR...
🔗የፌስቡክ:-https://www.facebook.com/s...
(የሀብታሙ ደባሱ የግል ሀሳብ)
#ethiopia | የአለምአቀፍ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ ንድፍ አውጭ በመባል በዓለም ደረጃ ስሙ የናኝው ሄንሪ ኪሲንጀር (Henry Kissinger) በተለያየ ጊዜያት ሀገር እና ብሔራዊ ጥቅምን በተመለከተ ያስቀመጣቸውን ትንታኔዎች መሰረት በማድረግ ግንዛቤን ለማዳበር ይረዳ ዘንድ እሳቤዎቹን ለማካፈል እሞክራለሁ።ይህ አንጋፋ ዲፕሎማት በዲፕሎማሲ ላይ ያለው አመለካከት በዓለም አቀፍ ግንኙነት ውስጥ እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ ጽንሰ-ሐሳቦች አንዱ ነው።ብሔራዊ ጥቅምን በተመለከተ የእሱ አቋም "እውነታዊነት" (Realism) ከሚባለው አስተሳሰብ የሚመነጭ ሲሆን፣ ዋና ትኩረቱ በብሔራዊ ጥቅም እና በስልጣን ሚዛን ላይ ነው።
🔴."እውነታዊነት" (Realpolitik- የኃይል ፖለቲካ):-ኪሲንጀር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በዋነኛነት በሀገራት ጥቅም (National Interest) መመራት እንዳለበት ያምናል-ከሞራል፣ከርዕዮተ ዓለም ወይም ከውስጥ ፖለቲካዊ ጉዳዮች በላይ ዲፕሎማሲ የሀገራትን ብሔራዊ ጥቅም ለመጠበቅና ለማራመድ የሚደረግ ተግባራዊና ስልታዊ ውይይት ነው። የሁለትዮሽ ድርድሮች እና ጥምረቶች (alliances) የሚፈጠሩት በጋራ እሴቶች ሳይሆን በጋራ ስጋቶች እና ጥቅሞች ላይ ተመስርተው ነው።
🔴.የስልጣን ሚዛን (Balance of Power):-ኪሲንጀር የዓለም አቀፍ ሥርዓት መረጋጋት (Stability) የሚረጋገጠው በስልጣን ሚዛን እንደሆነ አጥብቆ ያምናል።ዲፕሎማሲያዊ ሚና ዲፕሎማሲ በአንድ ሀገር የበላይነት እንዳይፈጠር የኃይል ክፍፍሉን በተከታታይ "የማስተካከል"ጥበብ ነው።ኃይለኛ የሆኑ ሀገራትን (Great Powers) በመካከላቸው የጥቅም ትስስር እንዲኖር በማድረግ ጦርነትን መከላከል እና ዓለም አቀፉን ሥርዓት ማረጋጋት እንደሆነ ይናገራል ።
🔴.የሕጋዊነት ጽንሰ-ሐሳብ (Legitimacy):-በኪሲንጀር አመለካከት፣ የዓለም አቀፍ ሥርዓት ሕጋዊነት ማለት ሁሉም ዋና ዋና ተዋናዮች (ሀገራት) አሁን ያለውን የሥርዓት አሠራር እና የወሰን መስመሮችን የሚቀበሉበት ሁኔታ ነው።ዲፕሎማሲ የሀገራትን ፍላጎት ሁሉ የሚያረካ ሳይሆን፣ ሁሉም ተዋናይ ምንም እንኳ ባይወደውም ከሥርዓቱ መውጣት የማይፈልግበትን የጋራ የመግባቢያ መሬት መፍጠር ነው።
🔴በታሪክ የተረጋገጠ ብሔራዊ ጥቅም:-ኪሲንጀር በዲፕሎማሲ ታሪክ ላይ ከፍተኛ ግንዛቤ ያለው ሲሆን፣ የዘመናዊ ዲፕሎማሲ መሠረት የተጣለው በ17ኛው ክፍለ ዘመን በካርዲናል ሪሼልዮ (Cardinal Richelieu) እና በ19ኛው ክፍለ ዘመን በኦስትሪያው ልዑል ሜተርኒች (Prince Metternich) መሆኑን ይጠቅሳል።
✍️እንደ መውጫ⁉️
በተግባር፣የኪሲንጀር ዲፕሎማሲ በታሪክ ውስጥ በሁለት ዋና ዋና ተግባራት ይታወቃል ከቻይና ጋር ያለውን ግንኙነት መክፈት (Opening China)በ1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ ከአሜሪካ ጠላት ከነበረችው ከኮሙኒስት ቻይና ጋር በድብቅ ድርድር በመጀመር፣ ለሶቭየት ህብረት ምላሽ የሚሆን ስልታዊ "ትሪያንግል" ፈጠሯል።
የሸትል ዲፕሎማሲ (Shuttle Diplomacy) በ1973 የዮም ኪፑር ጦርነት (Yom Kippur War) በኋላ በእስራኤል እና በአረብ ሀገራት መሪዎች መካከል በተደጋጋሚ በመመላለስ ግጭቶችን ለመፍታት የተጠቀመበት ዘዴ ልዩ ነበር
በአጭሩ፣ ኪሲንጀር ዲፕሎማሲን እና ብሔራዊ ጥቅምን ጉዳይ የሚያየው የኃይል ፖለቲካ መሳሪያ አድርጎ ነው ሀገራት ጦርነት ሳይገቡ ጥቅማቸውን እንዲያስጠብቁ እና በዓለም አቀፉ ሥርዓት ውስጥ የሚመጣውን ለውጥ በተግባራዊና ስልታዊ መንገድ እንዲያስተዳድሩ የሚያስችል ጥበብ ነው።
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መሳካት የድርሻዬን እወጣለሁ !
#ethiopia 🇪🇹
ለበለጠ ወዳጅነት የፃሃፊውን የኤክስ(X) እና የፌስቡክ ገፅ ይከታተሉ :-
🔗የኤክስ(X)ገፅ:-https://x.com/HDebasu?t=eR...
🔗የፌስቡክ:-https://www.facebook.com/s...
9 months ago
" ያለ ስራ ስነምግባር በስራ ቦታ ባልተገባ መንገድ ሰራተኛን የደበደበ ቻይናዊን ጨምሮ በአራት ሰዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል " - የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ
➡️ " ልጁ ሕክምና ተደርጎለት በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛል "
በሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የሚሰሩ ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባደረሱት ቅሬታ በፓርኩ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት በውጭ ሀገራት ዜጎች አካላዊና ስነልቦናዊ ጥቃት እንደሚደርስባቸው ገልጸዋል።
ባሳለፍነው እሁድም በፓርኩ ውስጥ በሚገኝ 'ቶዮ ሶላር' በተባለ ኩባንያ አንድ ቻይናዊ አንድን ኢትዮጵያዊ ሲደበደበዉና ልጁም መሬት ላይ ወድቆ የሚያሳይ ቪዲዮም ልከዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ቪዲዮዉን ከተመለከተ በኋላ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ ሰራተኞችንና አመራሮች እንዲሁም የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ሥራ አስኪያጅ ለማነጋገር ሞክሯል።
ሰራተኞች ምን አሉ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ ሰራተኞች አግኝቶ ለማነጋገር ቢሞክርም ለደህንነታቸው ሲሉ ለጊዜዉ ያለውን ችግር ለማውራት እንዳልተመቻቸው ገልፀው በሌላ ጊዜ መረጃ እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
በሌላ መልኩ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ አመራሮችን ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም ስልክ ባለማንሳታቸው ለጊዜው አልተሳካም።
ነገር ግን በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚሰሩ ሌሎች ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " መብታችን ተረግጦ ነው እየሰራን ያለነው። የዚህ ልጅ ድብደባ በቪድዮ ወጣ እንጂ ሌሎችም ብዙ መሰል ነገር ያጋጥማቸዋል። ለሰው ኃይል ክፍል ሲከሱ ብር ይቀጧቸውና ወደ ስራ ነው የሚመልሷቸው " ብለዋል።
" አቤት የምንልበት አጥተናል ሰው እንዴት በሀገሩ እንዲህ ይደረጋል ? የምንሰራው አስራ ሁለት ሰዓት ነው። በዛ ላይ ክፍያው ልፋታችንን የሚመጥን አይደለም ለመኖር ነው የምንሰራው። እንደዛም ሆኖ ግን ክብር በሌለበት ነው የምንሰራው። ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ድብደባ፣ ስድብ ፣ ማንቋሸሽ ይደርስባቸዋል፤ የጉልበት ስራ እንደ አህያ እያሸከሙ ነው የሚያሰሩት " ሲሉ ገልጸዋል።
" ይሄን ነገር መንግሥት ያውቀዋል ? ከባድ ነገር ነው እየገጠመን ያለው፤ ድምጻችንን ስሙልን " ብለዋል።
ፓርኩ ምን ምላሽ ሰጠ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ስራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አሸናፊን አግኝቶ አነጋግሯል።
አቶ ማቴዎስ ፤ " በፓርኩ በሚገኘዉ ቶዮ ሶላር ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ በሚሰራ ኢትዮጵያዊ ሞያተኛ እና የውጪ ሀገር (ቻይናዊ) ዜግነት ባለው ሱፐር ቫይዘር መካከል በስራ ቦታቸዉ ላይ በተፈጠረ አለመግባባት የተስተዋለው ጠብና ድብድብ ፍፁም ከስራ መርህ ውጭ የሆነና የፓርኩን መተዳደሪያ ደንብ የሚፃረር ነው ፤ የሚወገዝም ተግባር ነው " ብለዋል።
ፓርኩ ከኢትዮጵያ ኢንዱትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በመሆን አስፈላጊውን ማጣራት አድርጎ በሂደቱ ውሰጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ የነበራቸውን ሁለት የውጪ ዜጎች ከስራ እንዲባረሩና #ከሀገር_እንዲወጡ እንዲሁም በካምፓኒዉ ውስጥ ያሉ በጉዳዩ ቀጥተኛ ተሳታፊ ያልሆኑ ሶስት አመራሮች ደግሞ ከባድ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲደርሳቸው መደረጉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
ከዚህ ባለፈ ፥ ካምፓኒው ጉዳዩ በቪዲዮ ከተላለፈው በዘለለ በሰራተኛውና በቅርብ አለቃው መካከል ለተስተዋለው ግጭት መነሻ የነበሩ ምክንያቶችን በመዘርዘር ሁለቱም የተጋጩበትን መንገድ ፤ ኢትዮጵያዊውም የነበረውን ጥፋቶች በመዘርዘር ከስራ እንዲባረር ወስኖ የነበረ ሲሆን ፓርኩ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ወደ ስራ እንዲመለስ መወሰኑን ተናግረዋል።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚዘዋወሩ መረጃዎች መበራከታቸውን በመግለፅ " ልጁ ሞቷል፣ አጥንቱ ተሰብሯል " የሚሉና መሰል መረጃዎች የተሳሳቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
" ልጁ ሕክምና ተደርጎለት በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛል " ሲሉ አክለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawssa
tikvahethiopia
➡️ " ልጁ ሕክምና ተደርጎለት በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛል "
በሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የሚሰሩ ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባደረሱት ቅሬታ በፓርኩ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት በውጭ ሀገራት ዜጎች አካላዊና ስነልቦናዊ ጥቃት እንደሚደርስባቸው ገልጸዋል።
ባሳለፍነው እሁድም በፓርኩ ውስጥ በሚገኝ 'ቶዮ ሶላር' በተባለ ኩባንያ አንድ ቻይናዊ አንድን ኢትዮጵያዊ ሲደበደበዉና ልጁም መሬት ላይ ወድቆ የሚያሳይ ቪዲዮም ልከዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ቪዲዮዉን ከተመለከተ በኋላ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ ሰራተኞችንና አመራሮች እንዲሁም የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ሥራ አስኪያጅ ለማነጋገር ሞክሯል።
ሰራተኞች ምን አሉ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ ሰራተኞች አግኝቶ ለማነጋገር ቢሞክርም ለደህንነታቸው ሲሉ ለጊዜዉ ያለውን ችግር ለማውራት እንዳልተመቻቸው ገልፀው በሌላ ጊዜ መረጃ እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
በሌላ መልኩ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ አመራሮችን ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም ስልክ ባለማንሳታቸው ለጊዜው አልተሳካም።
ነገር ግን በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚሰሩ ሌሎች ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " መብታችን ተረግጦ ነው እየሰራን ያለነው። የዚህ ልጅ ድብደባ በቪድዮ ወጣ እንጂ ሌሎችም ብዙ መሰል ነገር ያጋጥማቸዋል። ለሰው ኃይል ክፍል ሲከሱ ብር ይቀጧቸውና ወደ ስራ ነው የሚመልሷቸው " ብለዋል።
" አቤት የምንልበት አጥተናል ሰው እንዴት በሀገሩ እንዲህ ይደረጋል ? የምንሰራው አስራ ሁለት ሰዓት ነው። በዛ ላይ ክፍያው ልፋታችንን የሚመጥን አይደለም ለመኖር ነው የምንሰራው። እንደዛም ሆኖ ግን ክብር በሌለበት ነው የምንሰራው። ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ድብደባ፣ ስድብ ፣ ማንቋሸሽ ይደርስባቸዋል፤ የጉልበት ስራ እንደ አህያ እያሸከሙ ነው የሚያሰሩት " ሲሉ ገልጸዋል።
" ይሄን ነገር መንግሥት ያውቀዋል ? ከባድ ነገር ነው እየገጠመን ያለው፤ ድምጻችንን ስሙልን " ብለዋል።
ፓርኩ ምን ምላሽ ሰጠ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ስራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አሸናፊን አግኝቶ አነጋግሯል።
አቶ ማቴዎስ ፤ " በፓርኩ በሚገኘዉ ቶዮ ሶላር ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ በሚሰራ ኢትዮጵያዊ ሞያተኛ እና የውጪ ሀገር (ቻይናዊ) ዜግነት ባለው ሱፐር ቫይዘር መካከል በስራ ቦታቸዉ ላይ በተፈጠረ አለመግባባት የተስተዋለው ጠብና ድብድብ ፍፁም ከስራ መርህ ውጭ የሆነና የፓርኩን መተዳደሪያ ደንብ የሚፃረር ነው ፤ የሚወገዝም ተግባር ነው " ብለዋል።
ፓርኩ ከኢትዮጵያ ኢንዱትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በመሆን አስፈላጊውን ማጣራት አድርጎ በሂደቱ ውሰጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ የነበራቸውን ሁለት የውጪ ዜጎች ከስራ እንዲባረሩና #ከሀገር_እንዲወጡ እንዲሁም በካምፓኒዉ ውስጥ ያሉ በጉዳዩ ቀጥተኛ ተሳታፊ ያልሆኑ ሶስት አመራሮች ደግሞ ከባድ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲደርሳቸው መደረጉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
ከዚህ ባለፈ ፥ ካምፓኒው ጉዳዩ በቪዲዮ ከተላለፈው በዘለለ በሰራተኛውና በቅርብ አለቃው መካከል ለተስተዋለው ግጭት መነሻ የነበሩ ምክንያቶችን በመዘርዘር ሁለቱም የተጋጩበትን መንገድ ፤ ኢትዮጵያዊውም የነበረውን ጥፋቶች በመዘርዘር ከስራ እንዲባረር ወስኖ የነበረ ሲሆን ፓርኩ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ወደ ስራ እንዲመለስ መወሰኑን ተናግረዋል።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚዘዋወሩ መረጃዎች መበራከታቸውን በመግለፅ " ልጁ ሞቷል፣ አጥንቱ ተሰብሯል " የሚሉና መሰል መረጃዎች የተሳሳቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
" ልጁ ሕክምና ተደርጎለት በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛል " ሲሉ አክለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawssa
tikvahethiopia
10 months ago
በኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በዓል ወቅት ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚደረጉ መንገዶች
#ethiopia | በኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በዓል አከባበር ወቅት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ለተሽከርካሪዎች የሚዘጉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ይፋ አደረገ፡፡
በርካታ ህዝብ የሚታደምበት እና አባገዳዎች፣ ሀደ ስንቄዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚገኙበት የኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይከበራል፡፡
በዓሉ በሠላም እንዲከበር የፀጥታ አካላት ትኩረት ሰጥተው ወደ ተግባር በመግባት እየሰሩ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጾ÷ በተለይ በዓሉ ወደሚከበርበት ስፍራ የሚመጡ ታዳሚዎች ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ መኖሩን ተገንዝበው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ተጠይቋል፡፡
ከዚህ ቀደም የተከበሩ ኃይማኖታዊና ብሔራዊ በዓላት በሠላም እንዲከበሩ ህብረተሰቡ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር ወሳኝ ስራ ማከናወኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውሷል።
የዘንድሮው የኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በዓል በሠላም እንዲከበር የበዓሉ ታዳሚዎች እና የከተማው ነዋሪ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርጉ በፀጥታ አካላት ስም ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
በመሆኑም የኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በዓል ተከብሮ እስከሚጠናቀቅ፦
👉 ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ሜክሲኮ፣
👉ከወሎ ሠፈር መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ፣
👉ከቄራ ሜክሲኮ የሚወስደው መንገድ ቡልጋሪያ፣
👉ከመርካቶ በአቡነ ተ/ኃይማኖት ወደ ጥቁር አንበሳ የሚወስደው መንገድ አቡነ ተ/ኃይማኖት ቤ/ክ፣
👉ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
፨ ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
👉ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
👉ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
👉ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
👉ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
👉ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
👉ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
👉ከአዲሱ ገበያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባንኮዲሮማ፣
👉ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
👉ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ ሼል አጠገብ እንዲሁም
👉ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወስደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ
ከመስከረም 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አስታውቋል፡፡
በአዲስ አበባ ዙሪያ ከሚገኙ የሸገር ከተማ አካባቢዎች በርካታ ህዝብ በዓሉን ለማክበር ከዋዜማው ጀምሮ ወደ ከተማችን የሚገባ በመሆኑ መላው ህብረተሰብ ተገቢውን አክብሮት በመስጠት የእንግዳ ተቀባይነት እሴታችንን አጉልቶ ሊያሳይ እንደሚገባ ፖሊስ አስታውሶ፤ በዓሉ በሚከበርበት ዙሪያ እና በአካባቢው በግራና በቀኝ ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን ገልጿል፡፡
በመጨረሻም ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-26-43-59 ፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች ጥቆማ በመስጠትና አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
#ethiopia | በኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በዓል አከባበር ወቅት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ለተሽከርካሪዎች የሚዘጉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ይፋ አደረገ፡፡
በርካታ ህዝብ የሚታደምበት እና አባገዳዎች፣ ሀደ ስንቄዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚገኙበት የኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይከበራል፡፡
በዓሉ በሠላም እንዲከበር የፀጥታ አካላት ትኩረት ሰጥተው ወደ ተግባር በመግባት እየሰሩ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጾ÷ በተለይ በዓሉ ወደሚከበርበት ስፍራ የሚመጡ ታዳሚዎች ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ መኖሩን ተገንዝበው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ተጠይቋል፡፡
ከዚህ ቀደም የተከበሩ ኃይማኖታዊና ብሔራዊ በዓላት በሠላም እንዲከበሩ ህብረተሰቡ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር ወሳኝ ስራ ማከናወኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውሷል።
የዘንድሮው የኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በዓል በሠላም እንዲከበር የበዓሉ ታዳሚዎች እና የከተማው ነዋሪ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርጉ በፀጥታ አካላት ስም ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
በመሆኑም የኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በዓል ተከብሮ እስከሚጠናቀቅ፦
👉 ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ሜክሲኮ፣
👉ከወሎ ሠፈር መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ፣
👉ከቄራ ሜክሲኮ የሚወስደው መንገድ ቡልጋሪያ፣
👉ከመርካቶ በአቡነ ተ/ኃይማኖት ወደ ጥቁር አንበሳ የሚወስደው መንገድ አቡነ ተ/ኃይማኖት ቤ/ክ፣
👉ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
፨ ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
👉ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
👉ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
👉ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
👉ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
👉ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
👉ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
👉ከአዲሱ ገበያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባንኮዲሮማ፣
👉ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
👉ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ ሼል አጠገብ እንዲሁም
👉ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወስደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ
ከመስከረም 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አስታውቋል፡፡
በአዲስ አበባ ዙሪያ ከሚገኙ የሸገር ከተማ አካባቢዎች በርካታ ህዝብ በዓሉን ለማክበር ከዋዜማው ጀምሮ ወደ ከተማችን የሚገባ በመሆኑ መላው ህብረተሰብ ተገቢውን አክብሮት በመስጠት የእንግዳ ተቀባይነት እሴታችንን አጉልቶ ሊያሳይ እንደሚገባ ፖሊስ አስታውሶ፤ በዓሉ በሚከበርበት ዙሪያ እና በአካባቢው በግራና በቀኝ ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን ገልጿል፡፡
በመጨረሻም ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-26-43-59 ፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች ጥቆማ በመስጠትና አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
10 months ago
የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከመስከረም 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች:-
፨ ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ሜክሲኮ፣
፨ ከወሎ ሠፈር መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ፣
፨ ከቄራ ሜክሲኮ የሚወስደው መንገድ ቡልጋሪያ፣
፨ ከመርካቶ በአቡነ ተ/ኃይማኖት ወደ ጥቁር አንበሳ የሚወስደው መንገድ አቡነ ተ/ኃይማኖት ቤ/ክ፣
፨ ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
፨ ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
፨ ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
፨ ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
፨ ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
፨ ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
፨ ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
፨ ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
፨ ከአዲሱ ገበያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባንኮዲሮማ፣
፨ ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
፨ ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ ሼል አጠገብ እንዲሁም
፨ ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወስደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ
፨ ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ሜክሲኮ፣
፨ ከወሎ ሠፈር መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ፣
፨ ከቄራ ሜክሲኮ የሚወስደው መንገድ ቡልጋሪያ፣
፨ ከመርካቶ በአቡነ ተ/ኃይማኖት ወደ ጥቁር አንበሳ የሚወስደው መንገድ አቡነ ተ/ኃይማኖት ቤ/ክ፣
፨ ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
፨ ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
፨ ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
፨ ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
፨ ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
፨ ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
፨ ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
፨ ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
፨ ከአዲሱ ገበያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባንኮዲሮማ፣
፨ ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
፨ ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ ሼል አጠገብ እንዲሁም
፨ ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወስደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ
Sponsored by
Surafel
10 months ago
የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚው ሰይፉ ፋንታሁን
ከዕዝራ እጅጉ-(ተወዳጅ ሚድያ)
#ethiopia | ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል። ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
ከእነዚህ ውስጥ የሚድያ ሰዎችም ይገኙበታል። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን አመራሮች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
በዚህ ፅሁፍ የህይወት ታሪኩን የምናቀርብለት ሰው ሰይፉ ፋንታሁን ሲባል ወደ ራሱ የግል ሚድያ ከገባ 29 ዓመቱን አስቆጥሯል። ከሆሊዉድ ጋዜጣ እስከ ኢትዮ ኤፍኤም 107.8 የተጓዘበት መንገድ አስተማሪ ሆኖ ስላገኘነው ታሪኩን ሰንደናል። ዕዝራ እጅጉ ተአማኒነት ያላቸው የሰነድ እና የምስል መረጃዎችን በመያዝ ታሪኩን አጠናክሮታል ። በቅርቡ በአሜሪካ የሚደረገው የኣፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚ ከሆኑት አንዱ የሚድያ ሰው አንዱ ሰይፉ ሲሆን የህይወት ታሪኩንም ታነቡ ዘንድ ተጋብዛችኋል።
ሰይፉ ፋንታሁን፣ ጷግሜ ወር 1968 በአዲስ አበባ በጋንዲ ሆስፒታል ተወለደ። ወላጅ አባቱ አቶ ፋንታዬ ብዙነህ ሲባሉ እናቱ ደግሞ ወይዘሮ አለሚቱ ሰንደቁ ይባላሉ። ሰይፉ ባሳደጉት አጎቱ ማለትም በእናቱ ወንድም በአቶ ፋንታሁን ሰንደቁ የሚጠራ ሲሆን የአዲስ አበባ ዕድገቱም ልደታ "ቢርሞ ሜዳ" ከሚባለው አካባቢ ነው።የሰይፉ ወላጅ አባት አቶ ፋንታዬ ብዙነህ በ 1970ዎቹ ግድም ያረፉ ሲሆን እርሳቸውም ባቡር በመንዳት ሥራ ላይ የተሠማሩ ነበሩ።
ሰይፉ ፋንታሁን ፣በልጅነቱ ከአካባቢው ልጆች ጋር ኳስ እየተጫወተ ያደገ ሲሆን ለኪነ ጥበብ ልዩ ፍቅር ያደረበት ገና በልጅነቱ ነበር። የቅርብ ቤተሰቦቹ እንደሚናገሩት ሰይፉ ዝንባሌውን በተመለከተ ከሌሎች የቤተሰብ አባላት ያየው ነገር ሳይኖር በተፈጥሮው ክህሎትን የታደለ ነው።
የሰይፉ ወላጅ አባት አቶ ፋንታዬ ብዙነህ እና እናቱ ወይዘሮ አለሚቱ ሰንደቁ በሐረር ይኖሩ የነበር ሲሆን ቤተሰቡም በሆቴል ቤት ሥራ ላይ ተሠማርቶ ነበር።
ሰይፉ ምንም እንኳን አዲስ አበባ ተወልዶ የልጅነት ጊዜውን ቢያሳልፍም ሐረርም ይመላለስ ነበር ። ሐረር በሄደበት ጊዜም የኪነ -ጥበብ ፍቅሩን ለመወጣት ሙከራ አድርጓል ።
ሰይፉ አዲስ አበባ ሳለ ልደታ አካባቢ የሚገኘው ተስፋ ኮከብ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ተምሯል።የት/ቤቱ የሥነ ፅሁፍ ክበብን ይመሩ የነበሩት ደግሞ የታገል ሰይፉ ወላጅ እናት ወ/ሮ ሠናይት ሙልጌታ ነበሩ። እርሳቸው ሰይፉ ለኪነ- ጥበብ ያለውን ልዩ ክህሎት በመመልከት ከልጃቸው ታገል ሰይፉ ጋር ለገዳዲ ሬድዮ ጣቢያ እንዲሄድ ሁኔታዎችን አመቻቹለት። ወይዘሮ ሠናይት በዚያን ጊዜ ተሰጥዖ የታደሉ ታዳጊዎች ወደ መድረኮች እንዲመጡ ይጥሩ ነበር።ታገልም ከወላጅ እናቱ የተሰጠውን ትዕዛዝ በመቀበል ሰይፉን ወደ ለገዳዲ ሬዲዮ ጣቢያ ወስዶ ያሰተዋውቀዋል። ሰይፉም የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪ ሆኖ የመጀመሪያ የሬዲዮ ሥራውን በለገዳዲ ሬዲዮ በትምህርት በሬዲዮ ጀመረ። ታገል እና ሰይፉ በልጅነታቸው "ቢሪሞ ሜዳ "ላይ ኳስ ተጫውተዋል። በጣም ፈጣን እና ቀልጣፋ መሆኑንም ታገል መስክሮለታል።
ሰይፉ በልጅነት ዕድሜው ማለትም ከ1982 ዓ.ም አንስቶ መኖሪያውን ሐረር ያደረገ በመሆኑ እዚያም የጥበብ ፍቅሩን እንዲወጣ ያስቻለው ዕድል ተፈጠረለት።
"ሀረር ላይ ኖሯል። ፀጉሩ ግጥም ያለ ነበር፣ ጥበብ ከልጅነቱ ጀምሮ የኖረበት ነው። ገና በልጅነቱ የቀይ መስቀል ድራማዎች ላይ ይሰራ ነበር።" በማለት የሐረሩ መምህር መክብብ አስራት ምስክርነቱን ይሰጣል።
ሰይፉ በዚያን ጊዜ፣የቤተክርስቲያን ቴአትሮችን ፅፎ አዘጋጅቷል። ከእነ አበባው መላኩ ጋርም ተውኗል።በ 1980ዎቹ ሐረር ላይ የነበሩ የአማተር ክበቦች ላይ የነቃ ተሳትፎ ነበረው። ግጥምም ይፅፍ ነበር፣ትወና ላይ በጣም ጎበዝ፣ ተዋናይነቱም በብዙዎች የተመሰከረለት ነው።
በተለይ ኮሜዲ ገፀ -ባህሪያት ላይ የተዋጣለት ነበር። ለዓላማው ፅኑ ነው አንድ ነገር አደርጋለሁ ካለ ያደርጋል። የኢቲቪ 120 የመዝናኛ ፕሮግራሞች ላይ ከእነ እንግዳ ዘር ነጋ ጋር ጭውውቶችን ይሰራ ነበር። ከዛ በኃላም ከእነ ሱራፌል እና ተመስገን ጋር የሙዚቃ ዝግጅት ያቀርብ ነበር።
መምህር መክብብ እንደሚናገረው"ሰይፉ ምስጋናም ወቀሳም የማያስደነግጠው በነገሮች የማይሰበር ጠንካራ ሰው ነው ሲል ይመሰክርለታል።
ሰይፉ አይጥ እና ሊጥ በተለየ ሁኔታ መጥላቱን አብሮ አደጎቹ ይመሰክራሉ።
"...በልጅነቱ የሚያደንቃቸው ታላላቅ ሰዎች ዛሬ አብረውት ይሠራሉ፣ ይሄ በጣም ትልቅ ስኬት ነው። ሰይፉ ወርቅ ፀባይ ያለው ትሁት ሰው ነው ሲል መስክሮለታል መምህር መክብብ አስራት።
ሙሉጌታ አክሊሉ ሰይፉን ከሐረር ጀምሮ ያውቀዋል። ወደ ኃላ ተጉዞ ምስክርነቱንም ሲሰጥም፦
" ሐረር የቦቴ ሰፈር ልጅ ነው። ብራና የኪነ-ጥበብ ቡድን ውስጥ ይሳተፍ ነበር፣
ማዕዶት የቤተክርስቲያን የቴአትር ክበብ የሙሉ ሰዓት ቴአትሮችን በጋራ እንሠራ ነበር፣ ከሐረር እስከ አ.አ ቴአትሮችን ይዘን መጥተን ሀገር ፍቅር እና ብሔራዊ ቴአትር ከእነ አበባው መላኩ ጋር መድረኮችን ሠርተናል ። ሐረር ላይ ከአዲስ አበባ የሚመጡ አርቲስቶችን የማስተባበር ስራ ይሰራ ነበር፣ሰዎችን የማሳቅ ልዩ ችሎታም ነበረው፣ የፀጉሩ ሉጫነት ወደ ራሰ በራነት ይቀየራል የማይባል ነበር፣እራሱ ሰይፉ ያዘጋጀው ድራማ ላይ አባት እና ልጅ ሆነን እንደሠራን አስታውሳለሁ ይላል ሙሉጌታ።
ሰይፉ ከልጅነቱ ጀምሮ ለጥበብ እና ለጋዜጠኝነት ፍቅር ነበረው።ሥራ አይንቅም ሁሌም አብሮ ለመሥራት ዝግጁ ነበር። ለዚህም ማሳያ አጃኢባ ያሲን የተባለች ሁለት እጆች ስለሌላት በወላጆቿ ተጥላ የነበረች እና በህይወት ተርፋ በእግሮቿ ብዙ ሥራዎችን ትሰራለች። ይህን ታሪክ ወደ ሰይፉ እንዲደርስ ያደረገው ደግሞ ሙልጌታ ነበር። ሰይፉ እንዲህ ላሉ ጉዳዮች በትኩረት ጊዜ ሰጥቶ ይሰራል በማለት ሙልጌታ ለሰይፉ አድናቆት ይቸረዋል።
አስፋው ሰንበቶ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሐረሪ ክልል ጽ/ቤት ኃላፊ ነው። ስለ ሰይፉ ሲመሰክርም፦
" ሰይፉ፣የቀይ መስቀል በጎ ፍቃደኛ አገልጋይ ነበር። የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ድራማዎች ላይ ይሳተፍ ነበር፣ሰይፉ ጨዋታ ይችላል፣ ያስቃል፣ እስክስታም ይጨፍር ነበር።ሰይፉ የጥበብ ራእዩን አሳክቷል። ያኔ በልጅነቱም ሰብአዊ ድጋፉ ከፍተኛ ነው። ደም ልገሳ እና ማህበረሰብ ተኮር ተግባራት ላይ ከፊት ተሰላፊ እና ሲሠራም ደከመኝን ፈፅሞ የማያውቅ ነው።ቴአትሮቹንም ሲሠራ የሚከፈለው ክፍያ አልነበረም።"በማለት ስለ ሰይፉ ተናግሯል ።
"ሆሊውድ እና ሰይፉ ፋንታሁን " ሲል ጋዜጠኛ ዕዝራ እጅጉ በፃፈው የግል ማስታወሻ እንዲህ ይላል፦
"......የ1989 አዲስ ዓመት ሲገባ የ 12ኛ ክፍል ማትሪክ ወሳጅ ነበርኩ፡፡ በቦሌ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ቤት የሚኒ ሚድያ ሊቀመንበር ነበርኩ፡፡ የኢቲቪው ፋንታሁን ኃይለማሪያም አንድ ሰይፉ የሚባል ልጅ አለ ላስተዋውቅህ ብሎ ፒያሳ ቲሩም አካባቢ ቀጠረኝ። ያኔ ሰይፉ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ተዋወቅኩ።
በ17 ዐመቴ አካፑልኮ ቤይ ፊልምን ለቦሌ ሀይስኩል ተማሪዎች መተርጎም ጀምሬ ነበር ጥቅምት 11 1989 ። ሆሊዉድ ደግሞ የዚያን ሰሞን ነበር አንድ ተብላ የተጀመረችው።
ሰይፉ ፋንታሁን እና ተመስገን አፈወርቅ ሆሊዉድ ጋዜጣን መሠረቱ፡፡ በጊዜው ሁለቱ ዕድሜያቸው ከ 22 አይዘልም፡፡
ሆሊዉድ ስትጀመር በ 15 ቀን የምትወጣ ጋዜጣ ነበረች።
ሰይፉ እስከማውቀው ድረስ የጋዜጣው ባለቤት ሲሆን ሆሊዉድ ላይ እንድሳተፍ ዕድሉን የከፈተልኝ ነው፡፡ በዐመቱ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቴን እየተከታተልኩ ደግሞ ፒያሳ እየመጣሁ ለሆሊዉድ የሚሆኑ ዜናዎችን እተረጉም ነበር፡፡ ሰይፉም እየከፈለኝ እሠራ ነበር፡፡ ያኔም የጋዜጣ ባለቤትነት እንደ ትልቅ በሚቆጠርበት ዘመን ሰይፉ በ 22 ዐመቱ የጋዜጣ አሳታሚ ነበር፡፡ እንዴት በትጋት ይሠራ እንደነበርም አልዘነጋውም፡፡ የፊያሜታውን ዳዊት ከበደ ወየሳንም የዚያን ሰሞን ነበር ያወቅኩት፡፡
ለፊት ገፅ የሚሆኑ ዜናዎችን እንድተረጉም ይሰጠኝ ነበር። ሰይፉ ብር ስጠኝ እንጂ ስለው በዚህ ወር ብዙ አልሠራንም እያለ ትንሽ ብር ሲሸጉጥልኝ ትዝ ይለኛል።
ብቻ ሰይፉ በመዝናኛ ኢንዱስትሪ ላይ ቀዳሚ አሻራ በማሳረፍ ታሪክ ያነሳዋል፡፡ ሁል ጊዜ ከትህትና የተነሳ እኔ ምን ሰርቼ ቢልም ከሆሊዉድ ተነስቶ የሬድዮ ጣቢያ ባለቤት የሆነበት ትልቁ ሚስጥር የሥራ ሠው ስለሆነ ነው፡፡ ይህን ጥረቱን ደግሞ ከ 1989 ጀምሮ ሳጤን ነበር፡፡ ሆሊዉድ ምን አይነት ይዘት እንደነበራት ለማወቅ ከዚህ ፅሁፍ ጋር የተያያዘዉን የጋዜጣዋን ቅጂ ይመልከቱ፡፡ እና ወዳጃችን ሰይፉ ብዙ ሰው ስለ ጋዜጣ በማያውቅበት ፣ጋዜጣን አሳትሞ ማሰራጨት ፈተና በሆነበት ጊዜ ሆሊዉድን ለህትመት ሲያበቃ ነበር፡፡ በዚህ አደንቀዋለሁ፡፡
ሰይፉ በጋዜጣ፡ በሬድዮ እና በቲቪ በ ሶስቱም ሚድየሞች በመስራት ማዝናናት እንደሚቻል አሳይቷል፡፡ ከሆሊዉድ በፊት ደግም ሞገድ ላይ የጥበበ ዐምድ ላይ ይፅፍ ነበር። ሰይፉ፣ የበጎ ሰው ሽልማት የ 2014 የሚድያ ዘርፍ ዕጬ በነበረ ጊዜ ለሽልማት ድርጅቱ የህይወት ታሪኩን የምሠራው እኔ ስለነበርኩ ብዙ የሥራ ታሪኮቹን ሳሰባስብ ነበር።
ያኔ የተረዳሁት ነገር የሰው ልጅ ትልቅ ጥረት ካሳየ ካሰበበት ቦታ ሊደርስ እንደሚችል ነው፡፡ የሚድያ ሥራ ፈጣሪዎች ቁጥራቸው ትንሽ በሆነበት ሀገር የእነ ሰይፉ ታሪክ ብዙ ያስተምራል፡፡ ታሪክ ሰናጅ ስለሆንኩ ለምፅፈው ሁሉ የሰነድ ማስረጃ አብሮኝ ነው፡፡ የጋዜጣ ታሪክ የሚፃፈው ጋዜጣ ላይ የሚፅፍ ሰው ስለ ሁኔታው ሲናገር ብቻ ነው፡፡ የጥንቱ ወዳጄ፣ አሠሪ ሰይፉ ለመዝናኛው ኢንዱስትሪ ላበረከትከው አስተዋፅኦ መሸለም ሲያንስህ ነው ሲል ዕዝራ እጅጉ ምስክርነቱን ሰጥቷል።
የመክብብ አስራት ትዝታ ስለ ሰይፉ
እዝራ፥ የሆሊውድ ነገር ከተነሳ አንድ ምሥጢር ላውጋህ። ሐረር እያለ እኔ ቤት ይመጣና ሁሌ እንደምናደርገው የልባችንን እንጫወታለን። አንድ ዕለት መጣና፦
" አዲስ አበባ ልሄድ ነው!" ይለኛል።
"ምንም ሳናወራበት በድንገት? እና ምን ለመሥራት ዐሰብክ?" ግራ ገብቶኝ ጠየኩት።
" ባክህ በቅርቡ አሜሪካ ሆሊዉድ ነው የምታገኘኝ!" ሲል ከት ብዬ ስቄ ሽኘሁት። ከወራት በኋላ ደወለልኝ።
"ባለፈው ሆሊዉድ እሄዳለሁ ስልህ ስቀህ ነበር አይደል?" አለኝ።
"ያንተ ነገር እኮ አይታወቅም ልሄድ ነው እንዳትለኝ?!" ስለው በተራው ስቆብኝ፣
"ባክህ ሆሊዉድ መሄድ ቢያቅተኝ፣ 'ሆሊዉድ' የሚል ጋዜጣ ማሳተም ጀመርኩ። ልኬልሃለሁና አንብበህ አስተያየት ስጥ!" ያለኝ አይረሳኝም። ሰይፉ አንድ ነገር ከወሰነ ፈጽሞ ወደ ኋላ አይልም። ሐረር ላይ 1982 ዓ.ም ለዓመታዊው የቀይ መስቀል በዓል ለህዝብ የሚታይ ድራማ ሠርተን ነበር። ያኔ ዕድሜው ዐሥራ ዐራት ቢኾነው ነው። ድርሰቱም ዝግጅቱም የእኔ ስለነበር ገጸ- ባሕርያቱን የመምረጥ መብቱ ስለነበረኝ እረኛ አድርጌ መደብኩት። የክብር እንግዳው የሐረርጌ ክፍለ ሀገር ኢሠፓ ጽ/ኃላፊው ነበሩ። እርሳቸውን ጨምሮ በሳቅ የአዳራሹን ተመልካች ፍንድት ነበር ያደረጋቸው። ያን ጊዜ ከተወኑት ውስጥ ነፍሱን ይማርና መስፍን ጌታቸው እና ዛሬ ትንታግ ተንታኝ የኾነው ጋዜጠኛ ዐቢይ ደምለው ይገኙበት ነበር። በእዚህ እጋጣሚ ሦስት የብዙዎች ጥያቄዎችን አረጋግጬ ልለፍ፤
፩- አንዳንዶች በዕድሜው ላይ ይከራከራሉ። እሱም በራሱ ስለሚቀልድ ሰባ ዓመት የሚመስላቸው አይጠፉምና የሰይፉን ዕድሜ ተወዳጅ ሚድያ ካቀረበው ጋር ማመሳከር ቢችሉ፤
፪- ፀጉሩን የመለጡት አዲሶች ይመስሉኛል። (ሃሃሃሃሃ) ሐረር እያለ ፀጉሩ ከግንባሩ ድፍት ያለ ሉጫ የሚሉት ዓይነት ነበረ። ነበረ ኾኖ ተመልጦ ቀረ እንጂ! አዲስ ስንገናኝ "ከክቡር ገና ቀንተህ ነው መላጨት የጀመርከው!?" እለው ነበር፤ ለካ ጉዳዩ ሌላ ኾኖ ነው።
፫- ብዙዎች መተወን የሚችል አይመስላቸውም። ሐረር ላይ ከኛ ጋር ያልተወነበት መድረክ የለም። አንዴ ከአስረስ በቀለ ጋር ከአዲስ አበባ ጋብዘናቸው ብዙ ከተሞች ላይ ስናሳይ፣ ድንገት ጅግጅጋ ከተማ ላይ አስረስ ካልዘፈንኩ ይለኛል። ማይኩን ይዞ ወጣ። ሙዚቀኞቹ " ብርቱካን ትርንጎ መሳይ' የሚለውን ማጀብ ቀጠሉ። አስረስ በምርጥ ድምፁ አዳራሹን አናጋው! ሽልማት በሽልማት ይኾናል። ከመድረክ ጀርባ ኾኖ ሰይፉ ያያል። በቅናት መንፈስ ማይኩን ይዞ ወደ መድረክ ወጥቶ መዝፈን ሲጀምር አስረስ ደንግጦ ቆመ። ለካንስ እየዘፈነ የነበረው ከጀርባ ኾኖ ሰይፍሻ ነበር። ተመልካቹን በሳቅ አንፈራፈረው። እናም ልጃችን ከልጅነቱ ጀምሮ ነው ጥበብ የጠራችው ለማለት ነው! የእሱ ገጠመኞች ብዙ ቢኾኑም ለዛሬ ይብቃኝ!
የሰይፉ የሚድያ ጅማሮ (ከ1989-2018)
ሰይፉ ፣ከ1986-1989 ባሉት 4 ዓመታት በልዩ ልዩ ጋዜጦች ላይ ፅሑፎችን በማበርከት፣ ለ120 ፕሮግራም የሚሆን ድራማዎችን በመፃፍና በመተወን የጥበብ ፍላጎቱን ሲወጣ ነበር። ከእንግዳዘር ነጋ፣ከአስረስ በቀለ እና ከሌሎችም ጋር በመተወን ብዙዎችን ዘና ሲያደርግ ነበር። ያኔ የተወነባቸው አጫጭር ጭውውቶች አልፎ አልፎ በማህበራዊ ድረ ገፆች ላይ ይታዩ ነበር። ሰይፉ፣ በዚያን ሰዐት ይህን ሁሉ ሲሠራ ገና 19 ዓመቱ ነበር።20 ዓመቱን ካከበረ በኃላ ግን የራሱን ድርጅት የመመሥረት ህልም ሰነቀ።
በጊዜው የሪፖርተር ጋዜጣ ለህትመት በቅታ በአንባቢያን ዘንድ ከበሬታን ያተረፈችበት ጊዜ ነበር። ወጣቱ ሰይፉም የሪፖርተር ጋዜጣ መሥራች አቶ አማረ አረጋዊ ዘንድ ቀርቦ እንዲህ አለ፦" እኔ አቶ አማረ የሪፖርተር ጋዜጣ አድናቂ ነኝ። ከፖለቲካ ውጭ የሆነ ጋዜጣ መጀመርም ፈልጋለሁ። ስለ ፊልም የሚያወራ ሆሊዉድ የተባለ ጋዜጣ እንዲኖረኝ እሻለሁ። ነገር ግን ለማሳተሚያም ሆነ ድርጅቱን ለማቋቋም ገንዘብ የለኝም "ሲል ሰይፉ በሀዘኔታ ፊት ሀሣቡን ገለፀ።
ወጣቶችን ማገዝ የሚሆንለት አቶ አማረ አረጋዊም አንተ ሆሊዉድን ጀምረው እንጂ ህትመቱን አታስብ እኔ እሸፍናለሁ ሲል ሞራል ሰጠው። ገንዘቡንም ወዲያው ሰጠው። የ21 ዓመቱ ሰይፉም በ1989 ዓ.ም የጋዜጣ ባለቤት ሆነ። ከጥቂት ወራት በኃላም አቶ አማረ ዘንድ ሄዶ፦" አሁን ማስታወቂያ ማግኘት ጀምሬያለሁ ። ሥራም ጥሩ እየሆነ ነው። ጋሽ አማረ አንተም ትልቁ ባለውለታዬ ነህ ሲል " ሰይፉ የከበረ ምስጋናውን አቀረበ።
ሰይፉና አቶ አማረ ዛሬ የልብ ወዳጆች ናቸው። አልፎ አልፎም ምሣ ለመብላት እየተገናኙ ይጨዋወታሉ። አቶ አማረን ስለ ሰይፉ ጠይቄው ለዚህ ደረጃ መብቃቱ ያረካዋል። ሰይፉ በጋዜጣ፣በሬድዮ፣በቲቪ አቅሙን ያሳየና ከራሱ አልፎ ለሌሎችም የሥራ ዕድል የፈጠረ ታታሪ ሰው ነው " ሲል አድናቆቱን ይቸረዋል።
ሰይፉ በታህሳስ 1989 ዓ.ም ሆሊዉድን ሲጀምር ተመስገን አፈወርቅ እና ብርሀኑ ድጋፌ አብረውት ነበሩ። በወቅቱ፣ ተመስገን እና ሰይፉ የፊልም ጉዳዮችን ፣ ብርሀኑ ድጋፌ ደግሞ የሙዚቃ ርዕሰ -ነገሮችን ለአንባብያን ያቀርቡ ነበር። ያኔ ብርሀኑ ድጋፌ፣ የውጭ መፅሔቶችን እንደ ልብ ያገኝ ስለነበር ሆሊዉድ የአንባቢያንን ቀልብ በቶሎ መያዝ ቻለች።
ሆሊዉድ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለህትመት ስትበቃ ቅጂዋ 2000 ነበር። የምትወጣውም በ 15ቀን አንድ ጊዜ ነበር። ያኔ የጋዜጣው የንድፍ ሥራ ይሠራ የነበረው ፒያሳ ቲሩም አካባቢ ሲሆን ጥበበ ታምራትም በዲዛይን ሥራ አሻራ ነበረው። ኃላ ላይም የፊያሜታው ዳዊት ከበደ ወዬሳ የሆሊዉድን የገፅ ንድፍ ይሠራ ነበር።
ጋዜጣው የተጀመረ ሰሞን ሰይፉ ከአንድ ጋዜጣ 400 ብር ትርፍ ያገኝ ነበር። በሂደት እንደ ሼል ኢትዮጵያ ያሉ ተቋማት ስፖንሰር ሆነው ከመጡ በኃላ የድርጅቱ ገቢም አደገ። ሰይፉ መጀመሪያ መኖሪያው ሰሜን ሆቴል አካባቢ አጎቱ ጋር የነበረ ሲሆን ቀጥሎም ሊሴ ገብረማሪያም ተማሪ ቤት ፊት ለፊት የ250 ብር ቤት ተከራይቶ ይኖር ነበር። በመቀጠልም አለምነህ ዋሴ ይኖርበት የነበረውን ዳትሰን ሰፈር የሚገኝ ቤትን በ850 ብር ተከራየ። እያለ እያለ ሰይፉ ራሱን ለማሳደግ እና በሚድያው ኢንዱስትሪ ለውጥ ለማምጣት መትጋት ጀመረ።
በ1990 ግድም በኢቲቪ ፣ ኢቲቪ ሚዩዚክን የተሰኘ መሰናዶን ከብርሀኔ ንጉሴ ና ከሱራፌል ወንድሙ ጋር ማቅረብ ጀመረ። በዚህም ከተመልካች ጋር የበለጠ ቅርርብ መፍጠር ችሏል።
በ1992 ዓ ም ኤፍ ኤም አዲስ 97 ነጥብ አንድ ሲጀመር ከዲጄ ኪን ጋር አዲስ ዜማን በመጀመር የራሱን የአየር ሰዓት ወስዶ መሥራት ጀመረ። ሰይፉ የበለጠ በመዝናኛው ኢንዱስትሪ ላይ ተፅእኖ ማሳደር የጀመረውም በዚህ ወቅት ነበር። አዳዲስ የመዝናኛ ወሬዎችም የሚገኙበት የሬድዮ ፕሮግራም ለመሆን በቃ። ከ1992-2000 ለ 8 ዓመታት የዘለቀው በሰይፉ ይመራ የነበረው አዲስ ዜማ በየዕለቱ እያደገ አድማጭን ለመቆጣጠር በቃ።
በ 2000 ዓ.ም ሸገር ሬድዮ ሲጀመር ሰይፉም "ታዲያስ አዲስ" በተሰኘ አዲስ የመዝናኛ ፕሮግራም በአዲስ መልክ የአድማጭን ጆሮ ለመያዝ ጣረ። ሸገር በሄደበት ጊዜ ሰይፉ የ11 ዓመት የመዝናኛ ሚድያ ልምድ አካብቶ ስለነበር ሥራው ብዙም ፈታኝ አልሆነበትም። ሸገር ከመግባቱ ቀደም ብሎ በ 1996 "መዝናኛ "ጋዜጣን ከፍ ባለ ደረጃ ጀምሮ አንባቢያንን ለመሳብ ቻለ።
ሰይፉ ፣በአንድ በኩል ሸገር ላይ "ታዲያስ አዲስ"ን እየሠራ በሌላ ደግሞ ኢቤኤስ ላይ ሰይፉ በኢቢኤስን በመጀመር ላለፉት 15 ዓመታት ተመልካቹን እያዝናና ይገኛል። ሁሉም የሬድዮም ሆነ የቲቪ ፕሮግራሞቹ፣በዩቲዩብ ከፍተኛ የተመልካች ቁጥር ያላቸው ሲሆኑ ከአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀምሮ ሌሎች ታዋቂ ሰዎችንም በፕሮግራሙ ላይ ማቅረብ ችሏል።
ከ2009 ጀምሮ ደግሞ ከሁለት አጋሮቹ ጋር በመሆን ኢትዮ ኤፍ ኤም _107.8 ለማቋቋም ችሏል።
የሚድያ ሰው ሰይፉ ፋንታሁን ባለፉት 29 ዓመታት በሚድያው ኢንዱስትሪ ላይ ያለ አንዳች ዕረፍት እየሠራ ስኬታማ ሥራ ፈጣሪ የሚድያ ሰውና ባለቤት ለመሆን ችሏል። በ 13 ዓመቱ ለገዳዲ ላይ የጀመረው ጥረት ኢትዮ ኤፍ ኤም ላይ አድርሶታል። በመጠነኛ ካፒታል አንድ ብሎ የጀመረው ሆሊውድ ጋዜጣ ወደ ሬድዮ፣ከዛም ወደ ኢቲቪ፣ ቀጥሎም ወደ መዝናኛ ጋዜጣ አቃርቦታል። ሐረር ቀይ መስቀል አሀዱ ያለው በጎነቱ ለሜቄዶንያም ተርፏል።
በበጎ አድራጊነት ሥራው ምስጋና የሚቸረው ሰይፉ ለታይታ የማይጓጓ፣ ስለ ራሱ እንዲነገርለት የማይሻ እንደሆነ የቅርቦቹ ይመሰክራሉ። ሰብዕናው ለሌሎች መድረስን ያስቀድማል። ያለውን የሚድያ ተፅዕኖ ፈጣሪነት ግምት ውስጥ በማስገባት ለመቁጠር የሚያዳግቱ በጎ ተግባራትን አከናውኗል። ይህም ርካታ ይሰጠዋል እንጂ ሌሎች እንዲያወሩለት አይሻም። ሰይፉ የሕይወት ታሪኩ እንዲሰነድ በተወዳጅ ሚድያ የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ተጠይቆ እኔ ምን ሰርቼ? በሚል ትህትና ይለፈኝ ብሎ ነበር። እኛም መረጃዎችን አሰባስበን ታሪኩን ሳናወጣው አቆይተን ነበር። አሁን ግን ጊዜው ስለሆነ የሰይፉን ታሪክ ከተሟላ መረጃ እና ብዙም ካልታዩ ምስሎች ጋር እነሆ አስነብበናል። ቀሪ መረጃዎችን በቀጣይ የምናካትት ይሆናል። የዝግጅት ክፍሉ ይህን ፅሁፍ ለማጠናከር የቅርብ ሰዎችን እና ተአማኒነት ያላቸውን ምንጮች ያነጋገረ ሲሆን መረጃ የሰጡንን ሁሉ ልባዊ ምስጋናን ማቅረብ እንወዳለን።
በተለይም መምህር መክብብ አስራት፣ አቶ አማረ አረጋዊ፣ አቶ በዛብህ ተክሉ
ነፍሱን ይማረውና ዳዊት ከበደ ወዬሳን እናመሰግናለን ።
ከዕዝራ እጅጉ-(ተወዳጅ ሚድያ)
#ethiopia | ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል። ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
ከእነዚህ ውስጥ የሚድያ ሰዎችም ይገኙበታል። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን አመራሮች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
በዚህ ፅሁፍ የህይወት ታሪኩን የምናቀርብለት ሰው ሰይፉ ፋንታሁን ሲባል ወደ ራሱ የግል ሚድያ ከገባ 29 ዓመቱን አስቆጥሯል። ከሆሊዉድ ጋዜጣ እስከ ኢትዮ ኤፍኤም 107.8 የተጓዘበት መንገድ አስተማሪ ሆኖ ስላገኘነው ታሪኩን ሰንደናል። ዕዝራ እጅጉ ተአማኒነት ያላቸው የሰነድ እና የምስል መረጃዎችን በመያዝ ታሪኩን አጠናክሮታል ። በቅርቡ በአሜሪካ የሚደረገው የኣፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚ ከሆኑት አንዱ የሚድያ ሰው አንዱ ሰይፉ ሲሆን የህይወት ታሪኩንም ታነቡ ዘንድ ተጋብዛችኋል።
ሰይፉ ፋንታሁን፣ ጷግሜ ወር 1968 በአዲስ አበባ በጋንዲ ሆስፒታል ተወለደ። ወላጅ አባቱ አቶ ፋንታዬ ብዙነህ ሲባሉ እናቱ ደግሞ ወይዘሮ አለሚቱ ሰንደቁ ይባላሉ። ሰይፉ ባሳደጉት አጎቱ ማለትም በእናቱ ወንድም በአቶ ፋንታሁን ሰንደቁ የሚጠራ ሲሆን የአዲስ አበባ ዕድገቱም ልደታ "ቢርሞ ሜዳ" ከሚባለው አካባቢ ነው።የሰይፉ ወላጅ አባት አቶ ፋንታዬ ብዙነህ በ 1970ዎቹ ግድም ያረፉ ሲሆን እርሳቸውም ባቡር በመንዳት ሥራ ላይ የተሠማሩ ነበሩ።
ሰይፉ ፋንታሁን ፣በልጅነቱ ከአካባቢው ልጆች ጋር ኳስ እየተጫወተ ያደገ ሲሆን ለኪነ ጥበብ ልዩ ፍቅር ያደረበት ገና በልጅነቱ ነበር። የቅርብ ቤተሰቦቹ እንደሚናገሩት ሰይፉ ዝንባሌውን በተመለከተ ከሌሎች የቤተሰብ አባላት ያየው ነገር ሳይኖር በተፈጥሮው ክህሎትን የታደለ ነው።
የሰይፉ ወላጅ አባት አቶ ፋንታዬ ብዙነህ እና እናቱ ወይዘሮ አለሚቱ ሰንደቁ በሐረር ይኖሩ የነበር ሲሆን ቤተሰቡም በሆቴል ቤት ሥራ ላይ ተሠማርቶ ነበር።
ሰይፉ ምንም እንኳን አዲስ አበባ ተወልዶ የልጅነት ጊዜውን ቢያሳልፍም ሐረርም ይመላለስ ነበር ። ሐረር በሄደበት ጊዜም የኪነ -ጥበብ ፍቅሩን ለመወጣት ሙከራ አድርጓል ።
ሰይፉ አዲስ አበባ ሳለ ልደታ አካባቢ የሚገኘው ተስፋ ኮከብ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ተምሯል።የት/ቤቱ የሥነ ፅሁፍ ክበብን ይመሩ የነበሩት ደግሞ የታገል ሰይፉ ወላጅ እናት ወ/ሮ ሠናይት ሙልጌታ ነበሩ። እርሳቸው ሰይፉ ለኪነ- ጥበብ ያለውን ልዩ ክህሎት በመመልከት ከልጃቸው ታገል ሰይፉ ጋር ለገዳዲ ሬድዮ ጣቢያ እንዲሄድ ሁኔታዎችን አመቻቹለት። ወይዘሮ ሠናይት በዚያን ጊዜ ተሰጥዖ የታደሉ ታዳጊዎች ወደ መድረኮች እንዲመጡ ይጥሩ ነበር።ታገልም ከወላጅ እናቱ የተሰጠውን ትዕዛዝ በመቀበል ሰይፉን ወደ ለገዳዲ ሬዲዮ ጣቢያ ወስዶ ያሰተዋውቀዋል። ሰይፉም የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪ ሆኖ የመጀመሪያ የሬዲዮ ሥራውን በለገዳዲ ሬዲዮ በትምህርት በሬዲዮ ጀመረ። ታገል እና ሰይፉ በልጅነታቸው "ቢሪሞ ሜዳ "ላይ ኳስ ተጫውተዋል። በጣም ፈጣን እና ቀልጣፋ መሆኑንም ታገል መስክሮለታል።
ሰይፉ በልጅነት ዕድሜው ማለትም ከ1982 ዓ.ም አንስቶ መኖሪያውን ሐረር ያደረገ በመሆኑ እዚያም የጥበብ ፍቅሩን እንዲወጣ ያስቻለው ዕድል ተፈጠረለት።
"ሀረር ላይ ኖሯል። ፀጉሩ ግጥም ያለ ነበር፣ ጥበብ ከልጅነቱ ጀምሮ የኖረበት ነው። ገና በልጅነቱ የቀይ መስቀል ድራማዎች ላይ ይሰራ ነበር።" በማለት የሐረሩ መምህር መክብብ አስራት ምስክርነቱን ይሰጣል።
ሰይፉ በዚያን ጊዜ፣የቤተክርስቲያን ቴአትሮችን ፅፎ አዘጋጅቷል። ከእነ አበባው መላኩ ጋርም ተውኗል።በ 1980ዎቹ ሐረር ላይ የነበሩ የአማተር ክበቦች ላይ የነቃ ተሳትፎ ነበረው። ግጥምም ይፅፍ ነበር፣ትወና ላይ በጣም ጎበዝ፣ ተዋናይነቱም በብዙዎች የተመሰከረለት ነው።
በተለይ ኮሜዲ ገፀ -ባህሪያት ላይ የተዋጣለት ነበር። ለዓላማው ፅኑ ነው አንድ ነገር አደርጋለሁ ካለ ያደርጋል። የኢቲቪ 120 የመዝናኛ ፕሮግራሞች ላይ ከእነ እንግዳ ዘር ነጋ ጋር ጭውውቶችን ይሰራ ነበር። ከዛ በኃላም ከእነ ሱራፌል እና ተመስገን ጋር የሙዚቃ ዝግጅት ያቀርብ ነበር።
መምህር መክብብ እንደሚናገረው"ሰይፉ ምስጋናም ወቀሳም የማያስደነግጠው በነገሮች የማይሰበር ጠንካራ ሰው ነው ሲል ይመሰክርለታል።
ሰይፉ አይጥ እና ሊጥ በተለየ ሁኔታ መጥላቱን አብሮ አደጎቹ ይመሰክራሉ።
"...በልጅነቱ የሚያደንቃቸው ታላላቅ ሰዎች ዛሬ አብረውት ይሠራሉ፣ ይሄ በጣም ትልቅ ስኬት ነው። ሰይፉ ወርቅ ፀባይ ያለው ትሁት ሰው ነው ሲል መስክሮለታል መምህር መክብብ አስራት።
ሙሉጌታ አክሊሉ ሰይፉን ከሐረር ጀምሮ ያውቀዋል። ወደ ኃላ ተጉዞ ምስክርነቱንም ሲሰጥም፦
" ሐረር የቦቴ ሰፈር ልጅ ነው። ብራና የኪነ-ጥበብ ቡድን ውስጥ ይሳተፍ ነበር፣
ማዕዶት የቤተክርስቲያን የቴአትር ክበብ የሙሉ ሰዓት ቴአትሮችን በጋራ እንሠራ ነበር፣ ከሐረር እስከ አ.አ ቴአትሮችን ይዘን መጥተን ሀገር ፍቅር እና ብሔራዊ ቴአትር ከእነ አበባው መላኩ ጋር መድረኮችን ሠርተናል ። ሐረር ላይ ከአዲስ አበባ የሚመጡ አርቲስቶችን የማስተባበር ስራ ይሰራ ነበር፣ሰዎችን የማሳቅ ልዩ ችሎታም ነበረው፣ የፀጉሩ ሉጫነት ወደ ራሰ በራነት ይቀየራል የማይባል ነበር፣እራሱ ሰይፉ ያዘጋጀው ድራማ ላይ አባት እና ልጅ ሆነን እንደሠራን አስታውሳለሁ ይላል ሙሉጌታ።
ሰይፉ ከልጅነቱ ጀምሮ ለጥበብ እና ለጋዜጠኝነት ፍቅር ነበረው።ሥራ አይንቅም ሁሌም አብሮ ለመሥራት ዝግጁ ነበር። ለዚህም ማሳያ አጃኢባ ያሲን የተባለች ሁለት እጆች ስለሌላት በወላጆቿ ተጥላ የነበረች እና በህይወት ተርፋ በእግሮቿ ብዙ ሥራዎችን ትሰራለች። ይህን ታሪክ ወደ ሰይፉ እንዲደርስ ያደረገው ደግሞ ሙልጌታ ነበር። ሰይፉ እንዲህ ላሉ ጉዳዮች በትኩረት ጊዜ ሰጥቶ ይሰራል በማለት ሙልጌታ ለሰይፉ አድናቆት ይቸረዋል።
አስፋው ሰንበቶ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሐረሪ ክልል ጽ/ቤት ኃላፊ ነው። ስለ ሰይፉ ሲመሰክርም፦
" ሰይፉ፣የቀይ መስቀል በጎ ፍቃደኛ አገልጋይ ነበር። የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ድራማዎች ላይ ይሳተፍ ነበር፣ሰይፉ ጨዋታ ይችላል፣ ያስቃል፣ እስክስታም ይጨፍር ነበር።ሰይፉ የጥበብ ራእዩን አሳክቷል። ያኔ በልጅነቱም ሰብአዊ ድጋፉ ከፍተኛ ነው። ደም ልገሳ እና ማህበረሰብ ተኮር ተግባራት ላይ ከፊት ተሰላፊ እና ሲሠራም ደከመኝን ፈፅሞ የማያውቅ ነው።ቴአትሮቹንም ሲሠራ የሚከፈለው ክፍያ አልነበረም።"በማለት ስለ ሰይፉ ተናግሯል ።
"ሆሊውድ እና ሰይፉ ፋንታሁን " ሲል ጋዜጠኛ ዕዝራ እጅጉ በፃፈው የግል ማስታወሻ እንዲህ ይላል፦
"......የ1989 አዲስ ዓመት ሲገባ የ 12ኛ ክፍል ማትሪክ ወሳጅ ነበርኩ፡፡ በቦሌ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ቤት የሚኒ ሚድያ ሊቀመንበር ነበርኩ፡፡ የኢቲቪው ፋንታሁን ኃይለማሪያም አንድ ሰይፉ የሚባል ልጅ አለ ላስተዋውቅህ ብሎ ፒያሳ ቲሩም አካባቢ ቀጠረኝ። ያኔ ሰይፉ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ተዋወቅኩ።
በ17 ዐመቴ አካፑልኮ ቤይ ፊልምን ለቦሌ ሀይስኩል ተማሪዎች መተርጎም ጀምሬ ነበር ጥቅምት 11 1989 ። ሆሊዉድ ደግሞ የዚያን ሰሞን ነበር አንድ ተብላ የተጀመረችው።
ሰይፉ ፋንታሁን እና ተመስገን አፈወርቅ ሆሊዉድ ጋዜጣን መሠረቱ፡፡ በጊዜው ሁለቱ ዕድሜያቸው ከ 22 አይዘልም፡፡
ሆሊዉድ ስትጀመር በ 15 ቀን የምትወጣ ጋዜጣ ነበረች።
ሰይፉ እስከማውቀው ድረስ የጋዜጣው ባለቤት ሲሆን ሆሊዉድ ላይ እንድሳተፍ ዕድሉን የከፈተልኝ ነው፡፡ በዐመቱ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቴን እየተከታተልኩ ደግሞ ፒያሳ እየመጣሁ ለሆሊዉድ የሚሆኑ ዜናዎችን እተረጉም ነበር፡፡ ሰይፉም እየከፈለኝ እሠራ ነበር፡፡ ያኔም የጋዜጣ ባለቤትነት እንደ ትልቅ በሚቆጠርበት ዘመን ሰይፉ በ 22 ዐመቱ የጋዜጣ አሳታሚ ነበር፡፡ እንዴት በትጋት ይሠራ እንደነበርም አልዘነጋውም፡፡ የፊያሜታውን ዳዊት ከበደ ወየሳንም የዚያን ሰሞን ነበር ያወቅኩት፡፡
ለፊት ገፅ የሚሆኑ ዜናዎችን እንድተረጉም ይሰጠኝ ነበር። ሰይፉ ብር ስጠኝ እንጂ ስለው በዚህ ወር ብዙ አልሠራንም እያለ ትንሽ ብር ሲሸጉጥልኝ ትዝ ይለኛል።
ብቻ ሰይፉ በመዝናኛ ኢንዱስትሪ ላይ ቀዳሚ አሻራ በማሳረፍ ታሪክ ያነሳዋል፡፡ ሁል ጊዜ ከትህትና የተነሳ እኔ ምን ሰርቼ ቢልም ከሆሊዉድ ተነስቶ የሬድዮ ጣቢያ ባለቤት የሆነበት ትልቁ ሚስጥር የሥራ ሠው ስለሆነ ነው፡፡ ይህን ጥረቱን ደግሞ ከ 1989 ጀምሮ ሳጤን ነበር፡፡ ሆሊዉድ ምን አይነት ይዘት እንደነበራት ለማወቅ ከዚህ ፅሁፍ ጋር የተያያዘዉን የጋዜጣዋን ቅጂ ይመልከቱ፡፡ እና ወዳጃችን ሰይፉ ብዙ ሰው ስለ ጋዜጣ በማያውቅበት ፣ጋዜጣን አሳትሞ ማሰራጨት ፈተና በሆነበት ጊዜ ሆሊዉድን ለህትመት ሲያበቃ ነበር፡፡ በዚህ አደንቀዋለሁ፡፡
ሰይፉ በጋዜጣ፡ በሬድዮ እና በቲቪ በ ሶስቱም ሚድየሞች በመስራት ማዝናናት እንደሚቻል አሳይቷል፡፡ ከሆሊዉድ በፊት ደግም ሞገድ ላይ የጥበበ ዐምድ ላይ ይፅፍ ነበር። ሰይፉ፣ የበጎ ሰው ሽልማት የ 2014 የሚድያ ዘርፍ ዕጬ በነበረ ጊዜ ለሽልማት ድርጅቱ የህይወት ታሪኩን የምሠራው እኔ ስለነበርኩ ብዙ የሥራ ታሪኮቹን ሳሰባስብ ነበር።
ያኔ የተረዳሁት ነገር የሰው ልጅ ትልቅ ጥረት ካሳየ ካሰበበት ቦታ ሊደርስ እንደሚችል ነው፡፡ የሚድያ ሥራ ፈጣሪዎች ቁጥራቸው ትንሽ በሆነበት ሀገር የእነ ሰይፉ ታሪክ ብዙ ያስተምራል፡፡ ታሪክ ሰናጅ ስለሆንኩ ለምፅፈው ሁሉ የሰነድ ማስረጃ አብሮኝ ነው፡፡ የጋዜጣ ታሪክ የሚፃፈው ጋዜጣ ላይ የሚፅፍ ሰው ስለ ሁኔታው ሲናገር ብቻ ነው፡፡ የጥንቱ ወዳጄ፣ አሠሪ ሰይፉ ለመዝናኛው ኢንዱስትሪ ላበረከትከው አስተዋፅኦ መሸለም ሲያንስህ ነው ሲል ዕዝራ እጅጉ ምስክርነቱን ሰጥቷል።
የመክብብ አስራት ትዝታ ስለ ሰይፉ
እዝራ፥ የሆሊውድ ነገር ከተነሳ አንድ ምሥጢር ላውጋህ። ሐረር እያለ እኔ ቤት ይመጣና ሁሌ እንደምናደርገው የልባችንን እንጫወታለን። አንድ ዕለት መጣና፦
" አዲስ አበባ ልሄድ ነው!" ይለኛል።
"ምንም ሳናወራበት በድንገት? እና ምን ለመሥራት ዐሰብክ?" ግራ ገብቶኝ ጠየኩት።
" ባክህ በቅርቡ አሜሪካ ሆሊዉድ ነው የምታገኘኝ!" ሲል ከት ብዬ ስቄ ሽኘሁት። ከወራት በኋላ ደወለልኝ።
"ባለፈው ሆሊዉድ እሄዳለሁ ስልህ ስቀህ ነበር አይደል?" አለኝ።
"ያንተ ነገር እኮ አይታወቅም ልሄድ ነው እንዳትለኝ?!" ስለው በተራው ስቆብኝ፣
"ባክህ ሆሊዉድ መሄድ ቢያቅተኝ፣ 'ሆሊዉድ' የሚል ጋዜጣ ማሳተም ጀመርኩ። ልኬልሃለሁና አንብበህ አስተያየት ስጥ!" ያለኝ አይረሳኝም። ሰይፉ አንድ ነገር ከወሰነ ፈጽሞ ወደ ኋላ አይልም። ሐረር ላይ 1982 ዓ.ም ለዓመታዊው የቀይ መስቀል በዓል ለህዝብ የሚታይ ድራማ ሠርተን ነበር። ያኔ ዕድሜው ዐሥራ ዐራት ቢኾነው ነው። ድርሰቱም ዝግጅቱም የእኔ ስለነበር ገጸ- ባሕርያቱን የመምረጥ መብቱ ስለነበረኝ እረኛ አድርጌ መደብኩት። የክብር እንግዳው የሐረርጌ ክፍለ ሀገር ኢሠፓ ጽ/ኃላፊው ነበሩ። እርሳቸውን ጨምሮ በሳቅ የአዳራሹን ተመልካች ፍንድት ነበር ያደረጋቸው። ያን ጊዜ ከተወኑት ውስጥ ነፍሱን ይማርና መስፍን ጌታቸው እና ዛሬ ትንታግ ተንታኝ የኾነው ጋዜጠኛ ዐቢይ ደምለው ይገኙበት ነበር። በእዚህ እጋጣሚ ሦስት የብዙዎች ጥያቄዎችን አረጋግጬ ልለፍ፤
፩- አንዳንዶች በዕድሜው ላይ ይከራከራሉ። እሱም በራሱ ስለሚቀልድ ሰባ ዓመት የሚመስላቸው አይጠፉምና የሰይፉን ዕድሜ ተወዳጅ ሚድያ ካቀረበው ጋር ማመሳከር ቢችሉ፤
፪- ፀጉሩን የመለጡት አዲሶች ይመስሉኛል። (ሃሃሃሃሃ) ሐረር እያለ ፀጉሩ ከግንባሩ ድፍት ያለ ሉጫ የሚሉት ዓይነት ነበረ። ነበረ ኾኖ ተመልጦ ቀረ እንጂ! አዲስ ስንገናኝ "ከክቡር ገና ቀንተህ ነው መላጨት የጀመርከው!?" እለው ነበር፤ ለካ ጉዳዩ ሌላ ኾኖ ነው።
፫- ብዙዎች መተወን የሚችል አይመስላቸውም። ሐረር ላይ ከኛ ጋር ያልተወነበት መድረክ የለም። አንዴ ከአስረስ በቀለ ጋር ከአዲስ አበባ ጋብዘናቸው ብዙ ከተሞች ላይ ስናሳይ፣ ድንገት ጅግጅጋ ከተማ ላይ አስረስ ካልዘፈንኩ ይለኛል። ማይኩን ይዞ ወጣ። ሙዚቀኞቹ " ብርቱካን ትርንጎ መሳይ' የሚለውን ማጀብ ቀጠሉ። አስረስ በምርጥ ድምፁ አዳራሹን አናጋው! ሽልማት በሽልማት ይኾናል። ከመድረክ ጀርባ ኾኖ ሰይፉ ያያል። በቅናት መንፈስ ማይኩን ይዞ ወደ መድረክ ወጥቶ መዝፈን ሲጀምር አስረስ ደንግጦ ቆመ። ለካንስ እየዘፈነ የነበረው ከጀርባ ኾኖ ሰይፍሻ ነበር። ተመልካቹን በሳቅ አንፈራፈረው። እናም ልጃችን ከልጅነቱ ጀምሮ ነው ጥበብ የጠራችው ለማለት ነው! የእሱ ገጠመኞች ብዙ ቢኾኑም ለዛሬ ይብቃኝ!
የሰይፉ የሚድያ ጅማሮ (ከ1989-2018)
ሰይፉ ፣ከ1986-1989 ባሉት 4 ዓመታት በልዩ ልዩ ጋዜጦች ላይ ፅሑፎችን በማበርከት፣ ለ120 ፕሮግራም የሚሆን ድራማዎችን በመፃፍና በመተወን የጥበብ ፍላጎቱን ሲወጣ ነበር። ከእንግዳዘር ነጋ፣ከአስረስ በቀለ እና ከሌሎችም ጋር በመተወን ብዙዎችን ዘና ሲያደርግ ነበር። ያኔ የተወነባቸው አጫጭር ጭውውቶች አልፎ አልፎ በማህበራዊ ድረ ገፆች ላይ ይታዩ ነበር። ሰይፉ፣ በዚያን ሰዐት ይህን ሁሉ ሲሠራ ገና 19 ዓመቱ ነበር።20 ዓመቱን ካከበረ በኃላ ግን የራሱን ድርጅት የመመሥረት ህልም ሰነቀ።
በጊዜው የሪፖርተር ጋዜጣ ለህትመት በቅታ በአንባቢያን ዘንድ ከበሬታን ያተረፈችበት ጊዜ ነበር። ወጣቱ ሰይፉም የሪፖርተር ጋዜጣ መሥራች አቶ አማረ አረጋዊ ዘንድ ቀርቦ እንዲህ አለ፦" እኔ አቶ አማረ የሪፖርተር ጋዜጣ አድናቂ ነኝ። ከፖለቲካ ውጭ የሆነ ጋዜጣ መጀመርም ፈልጋለሁ። ስለ ፊልም የሚያወራ ሆሊዉድ የተባለ ጋዜጣ እንዲኖረኝ እሻለሁ። ነገር ግን ለማሳተሚያም ሆነ ድርጅቱን ለማቋቋም ገንዘብ የለኝም "ሲል ሰይፉ በሀዘኔታ ፊት ሀሣቡን ገለፀ።
ወጣቶችን ማገዝ የሚሆንለት አቶ አማረ አረጋዊም አንተ ሆሊዉድን ጀምረው እንጂ ህትመቱን አታስብ እኔ እሸፍናለሁ ሲል ሞራል ሰጠው። ገንዘቡንም ወዲያው ሰጠው። የ21 ዓመቱ ሰይፉም በ1989 ዓ.ም የጋዜጣ ባለቤት ሆነ። ከጥቂት ወራት በኃላም አቶ አማረ ዘንድ ሄዶ፦" አሁን ማስታወቂያ ማግኘት ጀምሬያለሁ ። ሥራም ጥሩ እየሆነ ነው። ጋሽ አማረ አንተም ትልቁ ባለውለታዬ ነህ ሲል " ሰይፉ የከበረ ምስጋናውን አቀረበ።
ሰይፉና አቶ አማረ ዛሬ የልብ ወዳጆች ናቸው። አልፎ አልፎም ምሣ ለመብላት እየተገናኙ ይጨዋወታሉ። አቶ አማረን ስለ ሰይፉ ጠይቄው ለዚህ ደረጃ መብቃቱ ያረካዋል። ሰይፉ በጋዜጣ፣በሬድዮ፣በቲቪ አቅሙን ያሳየና ከራሱ አልፎ ለሌሎችም የሥራ ዕድል የፈጠረ ታታሪ ሰው ነው " ሲል አድናቆቱን ይቸረዋል።
ሰይፉ በታህሳስ 1989 ዓ.ም ሆሊዉድን ሲጀምር ተመስገን አፈወርቅ እና ብርሀኑ ድጋፌ አብረውት ነበሩ። በወቅቱ፣ ተመስገን እና ሰይፉ የፊልም ጉዳዮችን ፣ ብርሀኑ ድጋፌ ደግሞ የሙዚቃ ርዕሰ -ነገሮችን ለአንባብያን ያቀርቡ ነበር። ያኔ ብርሀኑ ድጋፌ፣ የውጭ መፅሔቶችን እንደ ልብ ያገኝ ስለነበር ሆሊዉድ የአንባቢያንን ቀልብ በቶሎ መያዝ ቻለች።
ሆሊዉድ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለህትመት ስትበቃ ቅጂዋ 2000 ነበር። የምትወጣውም በ 15ቀን አንድ ጊዜ ነበር። ያኔ የጋዜጣው የንድፍ ሥራ ይሠራ የነበረው ፒያሳ ቲሩም አካባቢ ሲሆን ጥበበ ታምራትም በዲዛይን ሥራ አሻራ ነበረው። ኃላ ላይም የፊያሜታው ዳዊት ከበደ ወዬሳ የሆሊዉድን የገፅ ንድፍ ይሠራ ነበር።
ጋዜጣው የተጀመረ ሰሞን ሰይፉ ከአንድ ጋዜጣ 400 ብር ትርፍ ያገኝ ነበር። በሂደት እንደ ሼል ኢትዮጵያ ያሉ ተቋማት ስፖንሰር ሆነው ከመጡ በኃላ የድርጅቱ ገቢም አደገ። ሰይፉ መጀመሪያ መኖሪያው ሰሜን ሆቴል አካባቢ አጎቱ ጋር የነበረ ሲሆን ቀጥሎም ሊሴ ገብረማሪያም ተማሪ ቤት ፊት ለፊት የ250 ብር ቤት ተከራይቶ ይኖር ነበር። በመቀጠልም አለምነህ ዋሴ ይኖርበት የነበረውን ዳትሰን ሰፈር የሚገኝ ቤትን በ850 ብር ተከራየ። እያለ እያለ ሰይፉ ራሱን ለማሳደግ እና በሚድያው ኢንዱስትሪ ለውጥ ለማምጣት መትጋት ጀመረ።
በ1990 ግድም በኢቲቪ ፣ ኢቲቪ ሚዩዚክን የተሰኘ መሰናዶን ከብርሀኔ ንጉሴ ና ከሱራፌል ወንድሙ ጋር ማቅረብ ጀመረ። በዚህም ከተመልካች ጋር የበለጠ ቅርርብ መፍጠር ችሏል።
በ1992 ዓ ም ኤፍ ኤም አዲስ 97 ነጥብ አንድ ሲጀመር ከዲጄ ኪን ጋር አዲስ ዜማን በመጀመር የራሱን የአየር ሰዓት ወስዶ መሥራት ጀመረ። ሰይፉ የበለጠ በመዝናኛው ኢንዱስትሪ ላይ ተፅእኖ ማሳደር የጀመረውም በዚህ ወቅት ነበር። አዳዲስ የመዝናኛ ወሬዎችም የሚገኙበት የሬድዮ ፕሮግራም ለመሆን በቃ። ከ1992-2000 ለ 8 ዓመታት የዘለቀው በሰይፉ ይመራ የነበረው አዲስ ዜማ በየዕለቱ እያደገ አድማጭን ለመቆጣጠር በቃ።
በ 2000 ዓ.ም ሸገር ሬድዮ ሲጀመር ሰይፉም "ታዲያስ አዲስ" በተሰኘ አዲስ የመዝናኛ ፕሮግራም በአዲስ መልክ የአድማጭን ጆሮ ለመያዝ ጣረ። ሸገር በሄደበት ጊዜ ሰይፉ የ11 ዓመት የመዝናኛ ሚድያ ልምድ አካብቶ ስለነበር ሥራው ብዙም ፈታኝ አልሆነበትም። ሸገር ከመግባቱ ቀደም ብሎ በ 1996 "መዝናኛ "ጋዜጣን ከፍ ባለ ደረጃ ጀምሮ አንባቢያንን ለመሳብ ቻለ።
ሰይፉ ፣በአንድ በኩል ሸገር ላይ "ታዲያስ አዲስ"ን እየሠራ በሌላ ደግሞ ኢቤኤስ ላይ ሰይፉ በኢቢኤስን በመጀመር ላለፉት 15 ዓመታት ተመልካቹን እያዝናና ይገኛል። ሁሉም የሬድዮም ሆነ የቲቪ ፕሮግራሞቹ፣በዩቲዩብ ከፍተኛ የተመልካች ቁጥር ያላቸው ሲሆኑ ከአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀምሮ ሌሎች ታዋቂ ሰዎችንም በፕሮግራሙ ላይ ማቅረብ ችሏል።
ከ2009 ጀምሮ ደግሞ ከሁለት አጋሮቹ ጋር በመሆን ኢትዮ ኤፍ ኤም _107.8 ለማቋቋም ችሏል።
የሚድያ ሰው ሰይፉ ፋንታሁን ባለፉት 29 ዓመታት በሚድያው ኢንዱስትሪ ላይ ያለ አንዳች ዕረፍት እየሠራ ስኬታማ ሥራ ፈጣሪ የሚድያ ሰውና ባለቤት ለመሆን ችሏል። በ 13 ዓመቱ ለገዳዲ ላይ የጀመረው ጥረት ኢትዮ ኤፍ ኤም ላይ አድርሶታል። በመጠነኛ ካፒታል አንድ ብሎ የጀመረው ሆሊውድ ጋዜጣ ወደ ሬድዮ፣ከዛም ወደ ኢቲቪ፣ ቀጥሎም ወደ መዝናኛ ጋዜጣ አቃርቦታል። ሐረር ቀይ መስቀል አሀዱ ያለው በጎነቱ ለሜቄዶንያም ተርፏል።
በበጎ አድራጊነት ሥራው ምስጋና የሚቸረው ሰይፉ ለታይታ የማይጓጓ፣ ስለ ራሱ እንዲነገርለት የማይሻ እንደሆነ የቅርቦቹ ይመሰክራሉ። ሰብዕናው ለሌሎች መድረስን ያስቀድማል። ያለውን የሚድያ ተፅዕኖ ፈጣሪነት ግምት ውስጥ በማስገባት ለመቁጠር የሚያዳግቱ በጎ ተግባራትን አከናውኗል። ይህም ርካታ ይሰጠዋል እንጂ ሌሎች እንዲያወሩለት አይሻም። ሰይፉ የሕይወት ታሪኩ እንዲሰነድ በተወዳጅ ሚድያ የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ተጠይቆ እኔ ምን ሰርቼ? በሚል ትህትና ይለፈኝ ብሎ ነበር። እኛም መረጃዎችን አሰባስበን ታሪኩን ሳናወጣው አቆይተን ነበር። አሁን ግን ጊዜው ስለሆነ የሰይፉን ታሪክ ከተሟላ መረጃ እና ብዙም ካልታዩ ምስሎች ጋር እነሆ አስነብበናል። ቀሪ መረጃዎችን በቀጣይ የምናካትት ይሆናል። የዝግጅት ክፍሉ ይህን ፅሁፍ ለማጠናከር የቅርብ ሰዎችን እና ተአማኒነት ያላቸውን ምንጮች ያነጋገረ ሲሆን መረጃ የሰጡንን ሁሉ ልባዊ ምስጋናን ማቅረብ እንወዳለን።
በተለይም መምህር መክብብ አስራት፣ አቶ አማረ አረጋዊ፣ አቶ በዛብህ ተክሉ
ነፍሱን ይማረውና ዳዊት ከበደ ወዬሳን እናመሰግናለን ።
10 months ago
በመዲናዋ ለመስቀል ደመራ በዓል ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች
የአዲስ አበባ ፖሊስ በነገው ዕለት በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም መሠረት፦
• ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
• ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
• ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
• ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
• ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
• ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
• ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣ እንዲሁም
• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ይዘጋሉ፡፡
በተገለጹት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ ሲሆን፥ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ተጠይቋል፡፡
#ዳጉ_ጆርናልበመዲናዋ ለመስቀል ደመራ በዓል ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች…
የአዲስ አበባ ፖሊስ በነገው ዕለት በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም መሠረት፦
• ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
• ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
• ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
• ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
• ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
• ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
• ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣ እንዲሁም
• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ይዘጋሉ፡፡
በተገለጹት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ ሲሆን፥ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ተጠይቋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ በነገው ዕለት በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም መሠረት፦
• ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
• ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
• ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
• ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
• ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
• ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
• ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣ እንዲሁም
• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ይዘጋሉ፡፡
በተገለጹት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ ሲሆን፥ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ተጠይቋል፡፡
#ዳጉ_ጆርናልበመዲናዋ ለመስቀል ደመራ በዓል ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች…
የአዲስ አበባ ፖሊስ በነገው ዕለት በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም መሠረት፦
• ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
• ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
• ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
• ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
• ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
• ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
• ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣ እንዲሁም
• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ይዘጋሉ፡፡
በተገለጹት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ ሲሆን፥ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ተጠይቋል፡፡
10 months ago
ነገ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ።
ነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ ከሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ጋር በተያያዘ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ይፋ አደርጓል።
በዚህም መሠረት ፦
- ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
- ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
- ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
- ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
- ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
- ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
- ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
- ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
- ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣
- ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ መንገድ ይዘጋል።
በተገለፁት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አሳስቧል።
አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ተላልፏል።
#addisababapolice
ነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ ከሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ጋር በተያያዘ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ይፋ አደርጓል።
በዚህም መሠረት ፦
- ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
- ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
- ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
- ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
- ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
- ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
- ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
- ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
- ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣
- ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ መንገድ ይዘጋል።
በተገለፁት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አሳስቧል።
አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ተላልፏል።
#addisababapolice
10 months ago
ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ተደረጉ
#ethiopia | ነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል፡፡
የ2018 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሠላም እንዲከበር የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን ያስታወሰው ጠቅላይ መምሪያው፤ ነገ ከረፋዱ 4:00 ሠዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም መሠረት፦
• ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
• ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
• ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
• ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
• ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
• ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
• ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣ እንዲሁም
• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ሕንጻ አጠገብ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ መንገድ የሚዘጋ መሆኑን አስታውቋል፡፡
በተጨማሪም በተገለጹት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጥሪውን አቅርቧል።
ሕብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ በመስጠትና አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣም ጥሪ አስተላልፏል፡፡
#ethiopia
#ethiopia | ነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል፡፡
የ2018 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሠላም እንዲከበር የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን ያስታወሰው ጠቅላይ መምሪያው፤ ነገ ከረፋዱ 4:00 ሠዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም መሠረት፦
• ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
• ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
• ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
• ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
• ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
• ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
• ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣ እንዲሁም
• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ሕንጻ አጠገብ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ መንገድ የሚዘጋ መሆኑን አስታውቋል፡፡
በተጨማሪም በተገለጹት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጥሪውን አቅርቧል።
ሕብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ በመስጠትና አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣም ጥሪ አስተላልፏል፡፡
#ethiopia
Sponsored by
Surafel
Comments