2 days ago
በጅማ ዞን ለሚካሄደው የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ የተለያዩ እንግዶች ጅማ ገቡ!
በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሰቃ ወረዳ በቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚካሄደውና ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ የቀረበበት የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ዝግጅት መጠጠናቀቁ ተገለጸ። በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ግብ መሠረት የሚከናወነው ይህ መርሃ-ግብር፤ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ-ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዘጋጅነት የቀረበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን ቴክኒካል ድጋፍ በማድረግ ተሳትፏል።።
ለዝግጅቱ ስኬት በጅማ ከተማ የደረሱ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ቲክቶክሮች እና የጥሪው ተጋባዦች በዞኑ እና በከተማ አስተዳደሩ፣ በአባ ገዳዎች፣ በሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ነገ በሚካሄደው በዚህ ታሪካዊ ኹነት ህብረተሰቡ በነቃ ሁኔታ እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።
በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሰቃ ወረዳ በቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚካሄደውና ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ የቀረበበት የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ዝግጅት መጠጠናቀቁ ተገለጸ። በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ግብ መሠረት የሚከናወነው ይህ መርሃ-ግብር፤ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ-ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዘጋጅነት የቀረበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን ቴክኒካል ድጋፍ በማድረግ ተሳትፏል።።
ለዝግጅቱ ስኬት በጅማ ከተማ የደረሱ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ቲክቶክሮች እና የጥሪው ተጋባዦች በዞኑ እና በከተማ አስተዳደሩ፣ በአባ ገዳዎች፣ በሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ነገ በሚካሄደው በዚህ ታሪካዊ ኹነት ህብረተሰቡ በነቃ ሁኔታ እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።
5 days ago
“አደይ አዲስ ዓመት ታላቅ የንግድ ኤክስፖ እና ፌስቲቫል” ይፋ ሆነ
#fastmereja I የ2019 አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በአዲስ ኮንቬንሽን ሴንተር ሊካሄድ የታቀደው “አደይ አዲስ ዓመት ታላቅ የንግድ ኤክስፖ እና ፌስቲቫል” ይፋ ተደርጓል። ኤክስፖው ከነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለ15 ቀናት እንደሚቆይ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
ይህ ታላቅ የንግድ እና የፌስቲቫል መድረክ በማስተር ፒስ ትሬዲንግ እና ራይት ኤቨንትስ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ለሚዲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከቱት ዝግጅቱ ለስሚት እና ለአካባቢው ነዋሪዎች የገበያ አማራጮችን በቅርበት የሚያቀርብ ነው። በኤክስፖው ላይ ከ200 በላይ የሀገር ውስጥ አምራቾች፣ አስመጪዎች፣ የዕደ-ጥበብ ባለሙያዎች እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምርትና አገልግሎታቸውን በተፎካካሪ እና በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
ከንግድ እንቅስቃሴው ጎን ለጎን ፌስቲቫሉ በየቀኑ 15 አርቲስቶች የሚሳተፉበት የቀጥታ የሙዚቃ ኮንሰርት፣ የፋሽን ሾው፣ የህፃናት መጫወቻዎች እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ያካተተ እንደሚሆን ተጠቅሷል። በተጨማሪም የኪነ-ጥበብ መድረኮችን ጨምሮ የመጽሐፍት አውደ ርዕይ እና ሽያጭ ይካሄዳል።
በ15 ቀናቱ የፌስቲቫል ቆይታ ከ80,000 በላይ ጎብኚዎች እና ደንበኞች ይገበያያሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቀው የኤግዚቢሽን ቦታዎችን በመሸጥ ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
#ኹነት
#fastmereja I የ2019 አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በአዲስ ኮንቬንሽን ሴንተር ሊካሄድ የታቀደው “አደይ አዲስ ዓመት ታላቅ የንግድ ኤክስፖ እና ፌስቲቫል” ይፋ ተደርጓል። ኤክስፖው ከነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለ15 ቀናት እንደሚቆይ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
ይህ ታላቅ የንግድ እና የፌስቲቫል መድረክ በማስተር ፒስ ትሬዲንግ እና ራይት ኤቨንትስ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ለሚዲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከቱት ዝግጅቱ ለስሚት እና ለአካባቢው ነዋሪዎች የገበያ አማራጮችን በቅርበት የሚያቀርብ ነው። በኤክስፖው ላይ ከ200 በላይ የሀገር ውስጥ አምራቾች፣ አስመጪዎች፣ የዕደ-ጥበብ ባለሙያዎች እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምርትና አገልግሎታቸውን በተፎካካሪ እና በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
ከንግድ እንቅስቃሴው ጎን ለጎን ፌስቲቫሉ በየቀኑ 15 አርቲስቶች የሚሳተፉበት የቀጥታ የሙዚቃ ኮንሰርት፣ የፋሽን ሾው፣ የህፃናት መጫወቻዎች እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ያካተተ እንደሚሆን ተጠቅሷል። በተጨማሪም የኪነ-ጥበብ መድረኮችን ጨምሮ የመጽሐፍት አውደ ርዕይ እና ሽያጭ ይካሄዳል።
በ15 ቀናቱ የፌስቲቫል ቆይታ ከ80,000 በላይ ጎብኚዎች እና ደንበኞች ይገበያያሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቀው የኤግዚቢሽን ቦታዎችን በመሸጥ ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
#ኹነት
19 days ago
በሊንክድኢን ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና የይዘት ፈጣሪዎች ሊሸለሙ ነው
#fastmereja :-በኢትዮጵያ በሊንክድኢን (LinkedIn) መድረክ ላይ ንቁ ተሳትፎ ላላቸው የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና ባለሙያዎች እውቅና ለመስጠት የተቋቋመው "የሊንክድኢን ቼንጅሜከርስ አዋርድስ ኢትዮጵያ (LCAE)" የመጀመሪያውን የሽልማት ስነ-ስርዓት ሊያካሂድ መሆኑን በዛሬዉ እለት በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ይህ መርሃ ግብር የፊታችን ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (August 1, 2026) በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ቲያትር አዳራሽ በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል።
በጉሩጂ ኤአር ኢትዮጵያ ከዥማ ሚዲያና ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚህ የክብር ምሸት ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎችና የልማት አጋሮች የሚታደሙ ሲሆን፤ በህዝብ ጥቆማ፣ በድምፅ አሰጣጥ እና በባለሙያዎች ጥብቅ ግምገማ ያለፉ ድንቅ እጩዎች ሽልማት ይበረከትላቸዋል።
የጉሩጂ ኤአር ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ያብስራ መካሻ እንደገለጹት፤ ሽልማቱ በሀገሪቱ የሙያ ስነ-ምህዳር ውስጥ የነበረውን ክፍተት ለመሙላትና ይዘታቸው ሌሎችን የሚያነቃቃና ትርጉም ያለው ሙያዊ ውይይት የሚፈጥሩ ሰዎችን ለማበረታታት ያለመ ነው፡፡
ይህ አገር አቀፍ ሽልማት በሳይንስና ቴክኖሎጂ (STEM)፣ በጤና፣ በስራ ፈጠራ፣ በአየር ንብረት እና በማርኬቲንግ ጨምሮ በ6 ዋና ዋና ምድቦች የተከፋፈለ ሲሆን፤ ከዲጂታል መድረክ ባሻገር በተጨባጭ ማህበረሰባዊ ተፅዕኖ የፈጠሩ ባለሙያዎችን ይሸልማል።
የሊንክድኢን ተፅእኖ ፈጣሪዎች ሽልማት ኢትዮጵያ (LCAE) በሀገሪቱ ሙያዊ እና ማህበራዊ መልክዓ-ምድር ላይ በተጨባጭ የሚለካ ተፅዕኖ እያሳደሩ ያሉ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን እውቅና የሚሰጥ የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ብሔራዊ፣ ሁለገብ ዘርፍ መድረክ ነው።
#ኹነት
#fastmereja :-በኢትዮጵያ በሊንክድኢን (LinkedIn) መድረክ ላይ ንቁ ተሳትፎ ላላቸው የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና ባለሙያዎች እውቅና ለመስጠት የተቋቋመው "የሊንክድኢን ቼንጅሜከርስ አዋርድስ ኢትዮጵያ (LCAE)" የመጀመሪያውን የሽልማት ስነ-ስርዓት ሊያካሂድ መሆኑን በዛሬዉ እለት በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ይህ መርሃ ግብር የፊታችን ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (August 1, 2026) በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ቲያትር አዳራሽ በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል።
በጉሩጂ ኤአር ኢትዮጵያ ከዥማ ሚዲያና ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚህ የክብር ምሸት ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎችና የልማት አጋሮች የሚታደሙ ሲሆን፤ በህዝብ ጥቆማ፣ በድምፅ አሰጣጥ እና በባለሙያዎች ጥብቅ ግምገማ ያለፉ ድንቅ እጩዎች ሽልማት ይበረከትላቸዋል።
የጉሩጂ ኤአር ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ያብስራ መካሻ እንደገለጹት፤ ሽልማቱ በሀገሪቱ የሙያ ስነ-ምህዳር ውስጥ የነበረውን ክፍተት ለመሙላትና ይዘታቸው ሌሎችን የሚያነቃቃና ትርጉም ያለው ሙያዊ ውይይት የሚፈጥሩ ሰዎችን ለማበረታታት ያለመ ነው፡፡
ይህ አገር አቀፍ ሽልማት በሳይንስና ቴክኖሎጂ (STEM)፣ በጤና፣ በስራ ፈጠራ፣ በአየር ንብረት እና በማርኬቲንግ ጨምሮ በ6 ዋና ዋና ምድቦች የተከፋፈለ ሲሆን፤ ከዲጂታል መድረክ ባሻገር በተጨባጭ ማህበረሰባዊ ተፅዕኖ የፈጠሩ ባለሙያዎችን ይሸልማል።
የሊንክድኢን ተፅእኖ ፈጣሪዎች ሽልማት ኢትዮጵያ (LCAE) በሀገሪቱ ሙያዊ እና ማህበራዊ መልክዓ-ምድር ላይ በተጨባጭ የሚለካ ተፅዕኖ እያሳደሩ ያሉ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን እውቅና የሚሰጥ የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ብሔራዊ፣ ሁለገብ ዘርፍ መድረክ ነው።
#ኹነት
19 days ago
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያዘጋጀው ታላቅ የሥራ ትስስር (Job Fair) ተካሄደ
#fastmereja I የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ምሩቃንን እና ሌሎች የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን በቀጥታ ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር ለማገናኘት ያለመ የመጀመሪያው የሥራ ትስስር (Job Fair) ዛሬ ሐምሌ 09 ቀን 2018 ዓ.ም. በታላቅ ድምቀት አካሂዷል።
የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፌይሳ ዋክቶሌ ለፋስት መረጃ በሰጡት ቃል እንደገለጹት፤ ይህ የሥራ አውደሪ የተዘጋጀው ቀጣሪ ኢንዱስትሪዎችንና ሥራ ፈላጊ ሰልጣኞችን በአንድ መድረክ በማገናኘት፣ ሁለቱም ወገኖች ተፈላጊ ሰራተኛና የሥራ ዕድል ፍለጋ የሚያባክኑትን ጊዜና እንግልት ለመቀነስ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ኮሌጁ ይህንን መድረክ በተቋም ደረጃ ሲያዘጋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በሌሎች መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና አማካሪዎች አማካኝነት ይዘጋጅ የነበረውን መርሃ ግብር ተቋሙ በባለቤትነት ተረክቦ ከተማ አቀፍ በሆነ መልኩ ማዘጋጀቱን አስረድተዋል።
በአውደሪው ላይ የኮሌጁ 967 መደበኛና የአጭር ጊዜ ሰልጣኞች ብቻ ሳይሆኑ፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ 14ቱም ኮሌጆች ሰልጣኞቻቸውን ይዘው እንዲገኙ ጥሪ ተላልፎላቸዋል። ሰልጣኞቹ ከቀጣሪዎች ጋር ከመገናኘታቸው አስቀድሞ የሲቪ (CV) አጻጻፍ፣ የቃለ መጠይቅ ዝግጅት፣ አለባበስ እና የስራ ፈጠራ አስተሳሰብን በሚመለከት ሰፊ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል። ይህ ዝግጅት ምሩቃኑ በራስ የመተማመን ስሜት ኖሯቸው ወደ ሥራው ዓለም እንዲቀላቀሉ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግላቸው ታምኖበታል።
በዕለቱ በተካሄደው የሥራ አውደሪ ላይ ከሆቴል፣ ከኮንስትራክሽን፣ ከማኑፋክቸሪንግ፣ ከዘመናዊው የፈጠራ ግሪን ቴክኖሎጂ እና ከኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፎች የተውጣጡ ከ35 በላይ ኢንዱስትሪዎች ተገኝተው የቅጥር ሂደቶችን ሲያከናውኑ ውለዋል። ከተለመደው የቅጥር ሁኔታ በተጨማሪ በኮሌጁ በቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፍ የተደራጁና የሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ (AI) መተግበሪያዎችን በመጠቀም ድረ-ገጾችንና የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን የሚሰሩ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የራሳቸውን ማሳያ ጥግ ይዘው ስራዎቻቸውን ለእይታ አቅርበዋል።
ለአንድ ቀን ብቻ የሚቆየው ይህ የሥራ አውደሪ መርሃ ግብር፣ በቀጣይም በየዓመቱ ከምረቃ ሥነ-ሥርዓት አስቀድሞ በቋሚነትና በስፋት የሚዘጋጅ ዓመታዊ መርሃ ግብር ሆኖ እንደሚቀጥል ዋና ዲኑ አቶ ተሾመ ፌይሳ ጨምረው ገልጸዋል።
#ኹነት
#fastmereja I የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ምሩቃንን እና ሌሎች የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን በቀጥታ ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር ለማገናኘት ያለመ የመጀመሪያው የሥራ ትስስር (Job Fair) ዛሬ ሐምሌ 09 ቀን 2018 ዓ.ም. በታላቅ ድምቀት አካሂዷል።
የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፌይሳ ዋክቶሌ ለፋስት መረጃ በሰጡት ቃል እንደገለጹት፤ ይህ የሥራ አውደሪ የተዘጋጀው ቀጣሪ ኢንዱስትሪዎችንና ሥራ ፈላጊ ሰልጣኞችን በአንድ መድረክ በማገናኘት፣ ሁለቱም ወገኖች ተፈላጊ ሰራተኛና የሥራ ዕድል ፍለጋ የሚያባክኑትን ጊዜና እንግልት ለመቀነስ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ኮሌጁ ይህንን መድረክ በተቋም ደረጃ ሲያዘጋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በሌሎች መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና አማካሪዎች አማካኝነት ይዘጋጅ የነበረውን መርሃ ግብር ተቋሙ በባለቤትነት ተረክቦ ከተማ አቀፍ በሆነ መልኩ ማዘጋጀቱን አስረድተዋል።
በአውደሪው ላይ የኮሌጁ 967 መደበኛና የአጭር ጊዜ ሰልጣኞች ብቻ ሳይሆኑ፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ 14ቱም ኮሌጆች ሰልጣኞቻቸውን ይዘው እንዲገኙ ጥሪ ተላልፎላቸዋል። ሰልጣኞቹ ከቀጣሪዎች ጋር ከመገናኘታቸው አስቀድሞ የሲቪ (CV) አጻጻፍ፣ የቃለ መጠይቅ ዝግጅት፣ አለባበስ እና የስራ ፈጠራ አስተሳሰብን በሚመለከት ሰፊ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል። ይህ ዝግጅት ምሩቃኑ በራስ የመተማመን ስሜት ኖሯቸው ወደ ሥራው ዓለም እንዲቀላቀሉ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግላቸው ታምኖበታል።
በዕለቱ በተካሄደው የሥራ አውደሪ ላይ ከሆቴል፣ ከኮንስትራክሽን፣ ከማኑፋክቸሪንግ፣ ከዘመናዊው የፈጠራ ግሪን ቴክኖሎጂ እና ከኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፎች የተውጣጡ ከ35 በላይ ኢንዱስትሪዎች ተገኝተው የቅጥር ሂደቶችን ሲያከናውኑ ውለዋል። ከተለመደው የቅጥር ሁኔታ በተጨማሪ በኮሌጁ በቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፍ የተደራጁና የሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ (AI) መተግበሪያዎችን በመጠቀም ድረ-ገጾችንና የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን የሚሰሩ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የራሳቸውን ማሳያ ጥግ ይዘው ስራዎቻቸውን ለእይታ አቅርበዋል።
ለአንድ ቀን ብቻ የሚቆየው ይህ የሥራ አውደሪ መርሃ ግብር፣ በቀጣይም በየዓመቱ ከምረቃ ሥነ-ሥርዓት አስቀድሞ በቋሚነትና በስፋት የሚዘጋጅ ዓመታዊ መርሃ ግብር ሆኖ እንደሚቀጥል ዋና ዲኑ አቶ ተሾመ ፌይሳ ጨምረው ገልጸዋል።
#ኹነት
20 days ago
የ1 ሚሊዮን ብር ሽልማት የሚያስገኘው የቤላ ስፖርት የክረምት የፉትሳል ውድድር ቅዳሜ ይጀመራል
#fastmereja I የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከቤላ ስፖርት ትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁትና አሸናፊውን ቡድን የ1 ሚሊዮን ብር ባለቤት የሚያደርገው 2ኛው ዙር የቤላ ስፖርት የክረምት የፉትሳል ውድድር በሚመጣው ቅዳሜ በይፋ እንደሚጀመር በጋዜጣዊ መግለጫ ተገለጸ።
ከሐምሌ 11 እስከ ነሐሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በጨፌ ሜዳ ለአንድ ወር በሚቆየው በዚህ ውድድር ላይ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ፣ በከፍተኛ ሊግ እና በሱፐር ሊግ የሚሳተፉ ተጨዋቾች ይሳተፋሉ።
ሁለቱ አካላት ውድድሩን በጋራ ለማዘጋጀት የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን፣ ዝግጅቱ ክለቦች አዲሱ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት አቋማቸውን ለመለካት ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርላቸው ታውቋል። ውድድሩን አሸናፊ ለሚሆን ቡድን ከተዘጋጀው 1 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሽልማት በተጨማሪ፣ ለውድድሩ ኮከብ ተጫዋች፣ ኮከብ ግብ አግቢ እና ኮከብ በረኛ እያንዳንዳቸው የ20 ሺህ ብር የክብር ሽልማት እንደሚሰጣቸው ተገልጿል። #ኹነት
#fastmereja I የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከቤላ ስፖርት ትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁትና አሸናፊውን ቡድን የ1 ሚሊዮን ብር ባለቤት የሚያደርገው 2ኛው ዙር የቤላ ስፖርት የክረምት የፉትሳል ውድድር በሚመጣው ቅዳሜ በይፋ እንደሚጀመር በጋዜጣዊ መግለጫ ተገለጸ።
ከሐምሌ 11 እስከ ነሐሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በጨፌ ሜዳ ለአንድ ወር በሚቆየው በዚህ ውድድር ላይ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ፣ በከፍተኛ ሊግ እና በሱፐር ሊግ የሚሳተፉ ተጨዋቾች ይሳተፋሉ።
ሁለቱ አካላት ውድድሩን በጋራ ለማዘጋጀት የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን፣ ዝግጅቱ ክለቦች አዲሱ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት አቋማቸውን ለመለካት ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርላቸው ታውቋል። ውድድሩን አሸናፊ ለሚሆን ቡድን ከተዘጋጀው 1 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሽልማት በተጨማሪ፣ ለውድድሩ ኮከብ ተጫዋች፣ ኮከብ ግብ አግቢ እና ኮከብ በረኛ እያንዳንዳቸው የ20 ሺህ ብር የክብር ሽልማት እንደሚሰጣቸው ተገልጿል። #ኹነት
21 days ago
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በታላቅ ድምቀት ሊያከብር ነው
#fastmereja I የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የተመሰረተበትን 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ ከሐምሌ 7/2018 ዓ.ም በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ የተለያዩ ዝግጅቶችን እያከናወነ እንደሚገኝ ተነግሯል። ኢንስቲትዩቱ የክፍለ ዘመኑን ጉዞ ለመዘከርና በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡ አዳዲስ ምርምሮችን ለማቅረብ መዘጋጀቱን አስታውቋል።
የኢንስቲትዩቱ ይፋዊ መርሃ-ግብር እንደሚያሳየው፣ ዋናው በዓልና ሳይንሳዊ ጉባኤው ከሐምሌ 9 እስከ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት በልዩ ሁኔታ ይካሄዳል። በዓሉ የኢንስቲትዩቱን የ100 ዓመታት ጉዞ የሚያሳዩ ፎቶግራፎችና ቪዲዮዎች፣ የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ ስነ-ስርዓቶች እንዲሁም በጤናው ዘርፍ ተስፋ ሰጪ በሆኑ አዳዲስ ግኝቶች ላይ ያተኮሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች የሚቀርቡበት መድረክ እንደሚሆን ተነግሯል።
#ኹነት
#fastmereja I የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የተመሰረተበትን 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ ከሐምሌ 7/2018 ዓ.ም በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ የተለያዩ ዝግጅቶችን እያከናወነ እንደሚገኝ ተነግሯል። ኢንስቲትዩቱ የክፍለ ዘመኑን ጉዞ ለመዘከርና በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡ አዳዲስ ምርምሮችን ለማቅረብ መዘጋጀቱን አስታውቋል።
የኢንስቲትዩቱ ይፋዊ መርሃ-ግብር እንደሚያሳየው፣ ዋናው በዓልና ሳይንሳዊ ጉባኤው ከሐምሌ 9 እስከ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት በልዩ ሁኔታ ይካሄዳል። በዓሉ የኢንስቲትዩቱን የ100 ዓመታት ጉዞ የሚያሳዩ ፎቶግራፎችና ቪዲዮዎች፣ የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ ስነ-ስርዓቶች እንዲሁም በጤናው ዘርፍ ተስፋ ሰጪ በሆኑ አዳዲስ ግኝቶች ላይ ያተኮሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች የሚቀርቡበት መድረክ እንደሚሆን ተነግሯል።
#ኹነት
Sponsored by
Surafel
1 month ago
🇪🇹🤝🇮🇹 የንግድና የቴክኖሎጂ ትስስርን የሚያጠናክረው “የጣሊያን ዘመናዊ አኗኗር 2026” (Italian Smart Living) በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው
በኢትዮጵያ እና በጣሊያን መካከል ያለውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የዲዛይን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመው ከፍተኛ የቢዝነስ እና የዲዛይን ኹነት በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም ሊካሄድ ዝግጅቱ ተጠናቋል።
📅 የሁነቱ መርሃ-ግብር
ቀን፦ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም (እ.ኤ.አ ከጁላይ 7 እስከ 9 ቀን 2026
*ቦታ፦በአዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም
✨ በሁነቱ ላይ ምን ምን ይጠበቃል?
🛍️ ልዩ ኤግዚቢሽን እና የB2B ትስስር
ከፍተኛ ጥራት ያላቸው የጣሊያን የቤት ዕቃዎች (Furniture)፣ የሥነ-ሕንጻ ብርሃን ቴክኖሎጂዎች፣ ሴራሚክስ እና እብነበረድ የሚቀርቡበት ሲሆን፤ የሁለቱን ሀገራት ኩባንያዎች በቀጥታ የሚያገናኝ የንግድ ትስስር መድረክ ተዘጋጅቷል።
🏗️ ሙያዊ ሴሚናሮች፦
በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባለው ‘Interni Magazine’ አወያይነት በዘላቂ የከተማ ልማት፣ በሃይል ቆጣቢ ህንፃዎች እና በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት እድሎች ዙሪያ የሀገር ውስጥ፣ የጣሊያንና የቀጣናው (ሩዋንዳ እና ኡጋንዳ) ምሁራንና ጋዜጠኞች የሚሳተፉበት ውይይት ይደረጋል።
🎓 የዲዛይን ማስተር ክላስ እና ልዩ ውድድር፦
በታዋቂው አርክቴክት ዱቺዮ ግራሲ (Arch. Duccio Grassi) የሚመራ ልዩ የስልጠና መርሃ-ግብር የሚሰጥ ሲሆን፤ በታሪካዊው የመርካቶ የንግድ ቀጠና ላይ ያተኮረ የመርካቶ ከተማ መልሶ ማልማት ውድድር (Merkato Urban Regeneration Competition) በይፋ ይጀመራል።
🏛️ የMade in Italy” ታሪክ ትዕይንት
በአለም አቀፍ የ“Made in Italy” ቀን ምክንያት በማድረግ በጣሊያን የምርት መለያዎች ሙዚየም አማካኝነት ታዋቂ ብራንዶች ያለፉበትን የዲዛይን እድገት የሚያሳይ ልዩ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ይቀርባል።
📌 ለተደራሲያን የቀረበ ማሳሰቢያ
ሁነቱ ለመጀመሪያዎቹ ቀናት ለባለሙያዎችና ለቢዝነስ ተቋማት (B2B) ብቻ ክፍት የሚሆን ሲሆን፤ በመጨረሻው ቀን ማለትም በሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም (እ.ኤ.አ ጁላይ 9) ለማንኛውም ፍላጎት ላለው የህዝብ ክፍል እና ለዲዛይን አፍቃሪዎች ሙሉ በሙሉ ነፃ ሆኖ ክፍት ይደረጋል።
#italiansmart Living2026 #addisababa #ethiopia #italy #business #design #architecture #innovation
በኢትዮጵያ እና በጣሊያን መካከል ያለውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የዲዛይን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመው ከፍተኛ የቢዝነስ እና የዲዛይን ኹነት በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም ሊካሄድ ዝግጅቱ ተጠናቋል።
📅 የሁነቱ መርሃ-ግብር
ቀን፦ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም (እ.ኤ.አ ከጁላይ 7 እስከ 9 ቀን 2026
*ቦታ፦በአዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም
✨ በሁነቱ ላይ ምን ምን ይጠበቃል?
🛍️ ልዩ ኤግዚቢሽን እና የB2B ትስስር
ከፍተኛ ጥራት ያላቸው የጣሊያን የቤት ዕቃዎች (Furniture)፣ የሥነ-ሕንጻ ብርሃን ቴክኖሎጂዎች፣ ሴራሚክስ እና እብነበረድ የሚቀርቡበት ሲሆን፤ የሁለቱን ሀገራት ኩባንያዎች በቀጥታ የሚያገናኝ የንግድ ትስስር መድረክ ተዘጋጅቷል።
🏗️ ሙያዊ ሴሚናሮች፦
በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባለው ‘Interni Magazine’ አወያይነት በዘላቂ የከተማ ልማት፣ በሃይል ቆጣቢ ህንፃዎች እና በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት እድሎች ዙሪያ የሀገር ውስጥ፣ የጣሊያንና የቀጣናው (ሩዋንዳ እና ኡጋንዳ) ምሁራንና ጋዜጠኞች የሚሳተፉበት ውይይት ይደረጋል።
🎓 የዲዛይን ማስተር ክላስ እና ልዩ ውድድር፦
በታዋቂው አርክቴክት ዱቺዮ ግራሲ (Arch. Duccio Grassi) የሚመራ ልዩ የስልጠና መርሃ-ግብር የሚሰጥ ሲሆን፤ በታሪካዊው የመርካቶ የንግድ ቀጠና ላይ ያተኮረ የመርካቶ ከተማ መልሶ ማልማት ውድድር (Merkato Urban Regeneration Competition) በይፋ ይጀመራል።
🏛️ የMade in Italy” ታሪክ ትዕይንት
በአለም አቀፍ የ“Made in Italy” ቀን ምክንያት በማድረግ በጣሊያን የምርት መለያዎች ሙዚየም አማካኝነት ታዋቂ ብራንዶች ያለፉበትን የዲዛይን እድገት የሚያሳይ ልዩ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ይቀርባል።
📌 ለተደራሲያን የቀረበ ማሳሰቢያ
ሁነቱ ለመጀመሪያዎቹ ቀናት ለባለሙያዎችና ለቢዝነስ ተቋማት (B2B) ብቻ ክፍት የሚሆን ሲሆን፤ በመጨረሻው ቀን ማለትም በሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም (እ.ኤ.አ ጁላይ 9) ለማንኛውም ፍላጎት ላለው የህዝብ ክፍል እና ለዲዛይን አፍቃሪዎች ሙሉ በሙሉ ነፃ ሆኖ ክፍት ይደረጋል።
#italiansmart Living2026 #addisababa #ethiopia #italy #business #design #architecture #innovation
1 month ago
በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ ሊከፍት የሚችል የመጀመሪያው አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን ሊካሄድ ነው
በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ ታሪክ አዲስ የኢንዱስትሪ ዕንቅስቃሴ ለመጀመር እና ስፖርትን ከመዝናኛነት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ምንጭነት ለማሸጋገር ያለመ ታላቅ አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ።
ይህንን በአገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን ታላቅ ኹነት ያዘጋጁት አዱሊያን ማስታወቂያ እና ዳይመንድ ማርኬቲንግ ኤንድ ኮሚኒኬሽን ሲሆኑ፣ ዝግጅቱ የኢትዮጵያን ስፖርት ከባሕላዊ የሩጫ እና የእግር ኳስ ማዕቀፍ አውጥቶ ወደ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የንግድ ትስስር እና የኢንዱስትሪ ምርታማነት የሚያሸጋግር የለውጥ ምዕራፍ እንደሚሆን አዘጋጆቹ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል።
ይህ አውደ ርዕይ እና አገራዊ መድረክ በርካታ ዘርፈ ብዙ ፋይዳዎችን ይዞ የሚቀርብ ሲሆን፣ የስፖርት ዕቃ አምራቾችን፣ አከፋፋዮችን፣ ስፖርተኞችን እና የስፖርት ማሕበራትን በአንድ መድረክ በማገናኘት የአገር ውስጥ ምርትን ማበረታታት እና የገበያ ትስስር መፍጠር፤ በዓለም ላይ ያሉ ዘመናዊ የስፖርት ስልጠና ቴክኖሎጂዎችን (Digital Sports Solutions)፣ የስፖርት ሕክምና፣ አመጋገብ እና ሳይንስ ላይ ያተኮሩ የውይይት መድረኮችን ለኢትዮጵያ ስፖርተኞችና አሰልጣኞች ማስተዋወቅ፤ ወጣቶች እና ቤተሰቦች በአካል ተገኝተው የተለያዩ የስፖርት አይነቶችን እንዲሞክሩ በማድረግ፣ በአካላዊ ብቃት፣ በእንቅስቃሴ እና በጤናማ የአኗኗር ዘይቤ ላይ ሰፊ ግንዛቤ መፍጠር እንዲሁም የስፖርት ዝግጅቶችን በንግድ መልክ በማደራጀት ለሀገር ውስጥ አምራቾች ሰፊ እድል መስጠት፤ ይህም የውጭ ምንዛሪ ወጪን በመቀነስ የአገር ውስጥ አቅምን ለመገንባት እና ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል።
### ለሀገር የሚሰጠው ስልታዊ ጠቀሜታ
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፖርቱ መስክ የጎላ ዝና ያላት ቢሆንም፣ ይህንን እውቅና ወደ ስፖርት ኢንዱስትሪ ለመቀየር የሚያስችል የተቀናጀ የንግድ እና የልውውጥ መድረክ ክፍተት እንደነበረበት ይነገራል። ዳይመንድ ማርኬቲንግ እና አዱሊያን ማስታወቂያ ይህንን ክፍተት በመሙላት የኢትዮጵያን ስፖርት ከ"ሞያ" ወደ "ኢንዱስትሪ" ለማሸጋገር አቅኚ የለውጥ ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ዝግጅቱ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን (MDF-based) የኤግዚቢሽን ስታንዳርዶችን የሚጠቀም በመሆኑ፣ ለወደፊት በሀገሪቱ ለሚካሄዱ ስፖርታዊ ኹነቶች አዲስ የጥራት ደረጃ (Benchmark) ያስቀምጣል። ይህም ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፖርት አስተናጋጅነት (Sports Event Hub) እንድትታወቅ በማድረግ ረገድ ለስፖርት ዲፕሎማሲው ትልቅ አጋዥ እንደሚሆን ታምኖበታል።
ኩባንያዎቹ ከዚህ ቀደም መሰል ዝግጅቶችን የማካሄድ ልምድ እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማሕበር ጋር በመተባበር "የአመለካከት እና አስተሳሰብ ለውጥ ኤግዚቢሽን" እንዲሁም ከአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ጋር በመተባበር በጃን ሜዳ "የባሕል እና ስፖርት ፌስቲቫል" በተሳካ ሁኔታ ማከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ለተሳታፊዎች እና ለጎብኚዎች ደህንነት ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ሲሆን፣ እያንዳንዱ የኤግዚቢሽን ቦታ (Zone) በዓለም አቀፍ የደሕንነት መመዘኛዎች መሰረት እንደሚዋቀር ተገልጿል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከፌዴሬሽኖች፣ ከጤና ባለሞያዎች እና ከሚመለከታቸው የደህንነት አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ላይ መሆናቸውንና የህክምና እና የድንገተኛ አደጋ ዝግጅቶች በተሟላ ሁኔታ እንደሚቀርቡ አዘጋጆቹ አረጋግጠዋል።
ይህ አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን የአንድ ጊዜ ክስተት ብቻ ሆኖ እንደማይቀረና ዋና ዓላማው በየዓመቱ የሚካሄድ ብሔራዊ የስፖርት ክብረ በዓል (Annual Sports Exhibition) ማድረግ መሆኑ ተገልጿል። የዘንድሮውን የመጀመሪያ ዝግጅት ስኬት እንደ ግብዓት በመጠቀም፣ በቀጣይ ዓመታት የክልል እና የዓለም አቀፍ ተሳታፊዎችን በማካተት ዝግጅቱን ይበልጥ ለማስፋት ታቅዷል።
በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ ታሪክ አዲስ የኢንዱስትሪ ዕንቅስቃሴ ለመጀመር እና ስፖርትን ከመዝናኛነት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ምንጭነት ለማሸጋገር ያለመ ታላቅ አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ።
ይህንን በአገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን ታላቅ ኹነት ያዘጋጁት አዱሊያን ማስታወቂያ እና ዳይመንድ ማርኬቲንግ ኤንድ ኮሚኒኬሽን ሲሆኑ፣ ዝግጅቱ የኢትዮጵያን ስፖርት ከባሕላዊ የሩጫ እና የእግር ኳስ ማዕቀፍ አውጥቶ ወደ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የንግድ ትስስር እና የኢንዱስትሪ ምርታማነት የሚያሸጋግር የለውጥ ምዕራፍ እንደሚሆን አዘጋጆቹ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል።
ይህ አውደ ርዕይ እና አገራዊ መድረክ በርካታ ዘርፈ ብዙ ፋይዳዎችን ይዞ የሚቀርብ ሲሆን፣ የስፖርት ዕቃ አምራቾችን፣ አከፋፋዮችን፣ ስፖርተኞችን እና የስፖርት ማሕበራትን በአንድ መድረክ በማገናኘት የአገር ውስጥ ምርትን ማበረታታት እና የገበያ ትስስር መፍጠር፤ በዓለም ላይ ያሉ ዘመናዊ የስፖርት ስልጠና ቴክኖሎጂዎችን (Digital Sports Solutions)፣ የስፖርት ሕክምና፣ አመጋገብ እና ሳይንስ ላይ ያተኮሩ የውይይት መድረኮችን ለኢትዮጵያ ስፖርተኞችና አሰልጣኞች ማስተዋወቅ፤ ወጣቶች እና ቤተሰቦች በአካል ተገኝተው የተለያዩ የስፖርት አይነቶችን እንዲሞክሩ በማድረግ፣ በአካላዊ ብቃት፣ በእንቅስቃሴ እና በጤናማ የአኗኗር ዘይቤ ላይ ሰፊ ግንዛቤ መፍጠር እንዲሁም የስፖርት ዝግጅቶችን በንግድ መልክ በማደራጀት ለሀገር ውስጥ አምራቾች ሰፊ እድል መስጠት፤ ይህም የውጭ ምንዛሪ ወጪን በመቀነስ የአገር ውስጥ አቅምን ለመገንባት እና ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል።
### ለሀገር የሚሰጠው ስልታዊ ጠቀሜታ
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፖርቱ መስክ የጎላ ዝና ያላት ቢሆንም፣ ይህንን እውቅና ወደ ስፖርት ኢንዱስትሪ ለመቀየር የሚያስችል የተቀናጀ የንግድ እና የልውውጥ መድረክ ክፍተት እንደነበረበት ይነገራል። ዳይመንድ ማርኬቲንግ እና አዱሊያን ማስታወቂያ ይህንን ክፍተት በመሙላት የኢትዮጵያን ስፖርት ከ"ሞያ" ወደ "ኢንዱስትሪ" ለማሸጋገር አቅኚ የለውጥ ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ዝግጅቱ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን (MDF-based) የኤግዚቢሽን ስታንዳርዶችን የሚጠቀም በመሆኑ፣ ለወደፊት በሀገሪቱ ለሚካሄዱ ስፖርታዊ ኹነቶች አዲስ የጥራት ደረጃ (Benchmark) ያስቀምጣል። ይህም ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፖርት አስተናጋጅነት (Sports Event Hub) እንድትታወቅ በማድረግ ረገድ ለስፖርት ዲፕሎማሲው ትልቅ አጋዥ እንደሚሆን ታምኖበታል።
ኩባንያዎቹ ከዚህ ቀደም መሰል ዝግጅቶችን የማካሄድ ልምድ እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማሕበር ጋር በመተባበር "የአመለካከት እና አስተሳሰብ ለውጥ ኤግዚቢሽን" እንዲሁም ከአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ጋር በመተባበር በጃን ሜዳ "የባሕል እና ስፖርት ፌስቲቫል" በተሳካ ሁኔታ ማከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ለተሳታፊዎች እና ለጎብኚዎች ደህንነት ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ሲሆን፣ እያንዳንዱ የኤግዚቢሽን ቦታ (Zone) በዓለም አቀፍ የደሕንነት መመዘኛዎች መሰረት እንደሚዋቀር ተገልጿል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከፌዴሬሽኖች፣ ከጤና ባለሞያዎች እና ከሚመለከታቸው የደህንነት አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ላይ መሆናቸውንና የህክምና እና የድንገተኛ አደጋ ዝግጅቶች በተሟላ ሁኔታ እንደሚቀርቡ አዘጋጆቹ አረጋግጠዋል።
ይህ አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን የአንድ ጊዜ ክስተት ብቻ ሆኖ እንደማይቀረና ዋና ዓላማው በየዓመቱ የሚካሄድ ብሔራዊ የስፖርት ክብረ በዓል (Annual Sports Exhibition) ማድረግ መሆኑ ተገልጿል። የዘንድሮውን የመጀመሪያ ዝግጅት ስኬት እንደ ግብዓት በመጠቀም፣ በቀጣይ ዓመታት የክልል እና የዓለም አቀፍ ተሳታፊዎችን በማካተት ዝግጅቱን ይበልጥ ለማስፋት ታቅዷል።
2 months ago
ከ18 በላይ ሀገራት የሚሳተፉበት ዓለም አቀፍ የንግድ ኤግዚቢሽን ሊካሄድ ነው
በኢትዮጵያ የንግድና የኢንቨስትመንት ዕድገት ላይ ከፍተኛ አዎንታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቀው 8ኛው አግሮፉድ እና ፕላስትፕሪንትፓክ እንዲሁም 2ኛው የኢትዮጵያ የምግብና የኤክስፖርት የቡና ንግድ ትርዒት ጥምር ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ሊካሄድ ሙሉ ዝግጅቱ መጠናቀቁ ተገለጠ ።
ይህ በዓነቱ ግዙፍ የሆነው የኢንዱስትሪ መድረክ በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት እያሳየች ባለው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ከብራዚል፣ ቻይና፣ ጣሊያን፣ ጀርመን እና ፈረንሳይ ጨምሮ ከ18 በላይ ሀገራት የተውጣጡ በርካታ ዓለም አቀፍና ሀገር በቀል ኩባንያዎችን በአንድ ጣሪያ ስር የሚያገናኝ ልዩ ኹነት መሆኑ ተጠቁሟል ።
ዝግጅቱ በተለይም በምግብ፣ በግብርና፣ በቡና፣ በላስቲክና ማሸጊያ ቴክኖሎጂዎች ዙሪያ አዳዲስ ፈጠራዎችንና የንግድ ትስስሮችን ይዞ እንደሚቀርብ የወጣው መርሃ-ግብር ያሳያል ።
ይህ ታላቅ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን ከሰኔ 18 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም (June 25–27, 2026) በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ለሶስት ቀናት ተከፍቶ እንደሚቆይ ታውቋል ።
በኢትዮጵያ የንግድና የኢንቨስትመንት ዕድገት ላይ ከፍተኛ አዎንታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቀው 8ኛው አግሮፉድ እና ፕላስትፕሪንትፓክ እንዲሁም 2ኛው የኢትዮጵያ የምግብና የኤክስፖርት የቡና ንግድ ትርዒት ጥምር ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ሊካሄድ ሙሉ ዝግጅቱ መጠናቀቁ ተገለጠ ።
ይህ በዓነቱ ግዙፍ የሆነው የኢንዱስትሪ መድረክ በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት እያሳየች ባለው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ከብራዚል፣ ቻይና፣ ጣሊያን፣ ጀርመን እና ፈረንሳይ ጨምሮ ከ18 በላይ ሀገራት የተውጣጡ በርካታ ዓለም አቀፍና ሀገር በቀል ኩባንያዎችን በአንድ ጣሪያ ስር የሚያገናኝ ልዩ ኹነት መሆኑ ተጠቁሟል ።
ዝግጅቱ በተለይም በምግብ፣ በግብርና፣ በቡና፣ በላስቲክና ማሸጊያ ቴክኖሎጂዎች ዙሪያ አዳዲስ ፈጠራዎችንና የንግድ ትስስሮችን ይዞ እንደሚቀርብ የወጣው መርሃ-ግብር ያሳያል ።
ይህ ታላቅ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን ከሰኔ 18 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም (June 25–27, 2026) በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ለሶስት ቀናት ተከፍቶ እንደሚቆይ ታውቋል ።
4 months ago
ሁሌ ቅርጫ የዲጂታል ቅርጫ አገልግሎት ሥራ ጀመረ
ሁሌ ቅርጫ የተባለ የቅርጫ አገልግሎትን በዲጂታል መንገድ የሚሰጥ አሠራር ተግባር ላይ መዋሉን የሁሌ ቅርጫ የሥራ መሪ አቶ ቶማስ መለሰ አስታውቀዋል። ከኢትዮ ቴሌኮምም ጋር ይህን ሥራ ለመሥራት የሥራ ውል ስምምነት ተፈራርመዋል።
በኢትዮ ቴሌኮም በኩል የዘመን ገበያ ኦፕሬሽን ማኔጀር አቶ ቸርነት ሰኢድ የውል ስምምነቱ ላይ ፊርማቸውን ያኖሩ ሲሆን በቴሌብር በዘመን ገበያ አማካይነት ግብይቱ እንደሚከናወን ታውቋል።
ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በጋራ የተዘጋጀው ይህ አገልግሎት ከዛሬ ጀምሮ የትንሣኤ በዓል አስመልክቶ ለተገልጋዮች ክፍት ይሆናል ተብሏል።
አፓርትመንት እንዲሁም የጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ የሚኖሩ ሰዎች፣ ቅርጫ ለማግኘት እንደሚቸገሩ ያስታወሱት አቶ ቶማስ፣ አገልግሎቱ አንድም ይህን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በተጨማሪም፣ ሰዉ በኑሮ ሩጫ መካከል ሆኖ ጊዜ እያጠረው ከመሆኑ አንጻር፣ ቅርጫ የሚገቡ ሰዎችን ማፈላለግና ማሰባሰብ፣ በሬ ለመግዛት ገበያ ማቅናት እንዲሁም አራጆችን መፈለግ አስቸጋሪ መሆኑን አንስተዋል። ሁሌ ቅርጫ ይህን ሁሉ ድካም በማስቀረት ለኅብረተሰቡ ትልቅ ጠቀሜታ የሚሰጥ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ከዚህም ባሻገር ከእርድ የሚተርፉ እንደ በሬ ቆዳ፣ ጭንቅላት እና የመሳሰሉት፣ ፅዱና ንፁህ በሆነች ከተማ ላይ በየአካባቢው መጣሉ ለነዋሪዎች ጤንነት እክል እንደሚሆን አንስተዋል። ሁሌ ቅርጫም ይህን በማስቀረት ትልቅ ሚና ይጫወታል ብለዋል።
ከሃገር ውጭ የሚኖሩ ሰዎችም ያለምንም ውጣ ውረድ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው የቅርጫ ሥጋ የሚገዙበት መልካም አጋጣሚ መሆኑን አቶ ቶማስ አስረድተዋል።
ዋጋውን በተመለከተ ቅናሽ ያለው ሲሆን፣ ከመደበኛ ግብይት በተሻለ ደንበኞች የመረጡትን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት የሚችሉበት ነው። በኢትዮ ቴሌኮም የዘመን ገበያ አገልግሎት በኩልም፣ ደንበኞች በኢትዮ ቴሌኮም ክፍያ ከፈፀሙ በኃላ በየቤታቸው የሚደርስበት የዴሊቨሪ አገልግሎት መኖሩንም ታውቋል። ሁሌ ቅርጫ ከሸጠው ላይ 2 % አቅም ለሌላቸው የበዓል ድጋፍ እንደሚያውልም ታውቋል።
'ሁሌ ቅርጫ' ላለፉት ዓመታት ጥራቱን እና ደረጃውን የጠበቀ፣ ደኅንነቱም የተረጋገጠ ስጋን ለውጭ ገበያ ሲልክ ቆይቷል። አሁን ላይ ይህን ተመሳሳይ አገልግሎት ለሀገር ውስጥ ገበያ መስጠት ጀምሯል።
አቶ ቶማስ እንደገለጹት፣ ይህ ግብይት አሁን በዓሉን በማስመልከት ይጀመር እንጂ በአዘቦት ቀናትም የሚቀጥል ነው። ከዓመት ዓመት የበግ እና የፍየል እርድን ጨምሮ፣ ለተለያየ ኹነትም ሰብሰብ ብለው ቅርጫ ለፈለጉም አገልግሎቱ ተደራሽ እንደሚሆን አሳውቀዋል።
ቅርጫ የሚለው ባህል እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ቀለል ባለና ደኅንነቱ እና ደረጃው በተጠበቀ መንገድ አገልግሎትን መስጠት የሁሌ ቅርጫ ዓላማ መሆኑንም አቶ ቶማስ ተናግረዋል።
ሁሌ ቅርጫ የተባለ የቅርጫ አገልግሎትን በዲጂታል መንገድ የሚሰጥ አሠራር ተግባር ላይ መዋሉን የሁሌ ቅርጫ የሥራ መሪ አቶ ቶማስ መለሰ አስታውቀዋል። ከኢትዮ ቴሌኮምም ጋር ይህን ሥራ ለመሥራት የሥራ ውል ስምምነት ተፈራርመዋል።
በኢትዮ ቴሌኮም በኩል የዘመን ገበያ ኦፕሬሽን ማኔጀር አቶ ቸርነት ሰኢድ የውል ስምምነቱ ላይ ፊርማቸውን ያኖሩ ሲሆን በቴሌብር በዘመን ገበያ አማካይነት ግብይቱ እንደሚከናወን ታውቋል።
ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በጋራ የተዘጋጀው ይህ አገልግሎት ከዛሬ ጀምሮ የትንሣኤ በዓል አስመልክቶ ለተገልጋዮች ክፍት ይሆናል ተብሏል።
አፓርትመንት እንዲሁም የጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ የሚኖሩ ሰዎች፣ ቅርጫ ለማግኘት እንደሚቸገሩ ያስታወሱት አቶ ቶማስ፣ አገልግሎቱ አንድም ይህን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በተጨማሪም፣ ሰዉ በኑሮ ሩጫ መካከል ሆኖ ጊዜ እያጠረው ከመሆኑ አንጻር፣ ቅርጫ የሚገቡ ሰዎችን ማፈላለግና ማሰባሰብ፣ በሬ ለመግዛት ገበያ ማቅናት እንዲሁም አራጆችን መፈለግ አስቸጋሪ መሆኑን አንስተዋል። ሁሌ ቅርጫ ይህን ሁሉ ድካም በማስቀረት ለኅብረተሰቡ ትልቅ ጠቀሜታ የሚሰጥ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ከዚህም ባሻገር ከእርድ የሚተርፉ እንደ በሬ ቆዳ፣ ጭንቅላት እና የመሳሰሉት፣ ፅዱና ንፁህ በሆነች ከተማ ላይ በየአካባቢው መጣሉ ለነዋሪዎች ጤንነት እክል እንደሚሆን አንስተዋል። ሁሌ ቅርጫም ይህን በማስቀረት ትልቅ ሚና ይጫወታል ብለዋል።
ከሃገር ውጭ የሚኖሩ ሰዎችም ያለምንም ውጣ ውረድ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው የቅርጫ ሥጋ የሚገዙበት መልካም አጋጣሚ መሆኑን አቶ ቶማስ አስረድተዋል።
ዋጋውን በተመለከተ ቅናሽ ያለው ሲሆን፣ ከመደበኛ ግብይት በተሻለ ደንበኞች የመረጡትን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት የሚችሉበት ነው። በኢትዮ ቴሌኮም የዘመን ገበያ አገልግሎት በኩልም፣ ደንበኞች በኢትዮ ቴሌኮም ክፍያ ከፈፀሙ በኃላ በየቤታቸው የሚደርስበት የዴሊቨሪ አገልግሎት መኖሩንም ታውቋል። ሁሌ ቅርጫ ከሸጠው ላይ 2 % አቅም ለሌላቸው የበዓል ድጋፍ እንደሚያውልም ታውቋል።
'ሁሌ ቅርጫ' ላለፉት ዓመታት ጥራቱን እና ደረጃውን የጠበቀ፣ ደኅንነቱም የተረጋገጠ ስጋን ለውጭ ገበያ ሲልክ ቆይቷል። አሁን ላይ ይህን ተመሳሳይ አገልግሎት ለሀገር ውስጥ ገበያ መስጠት ጀምሯል።
አቶ ቶማስ እንደገለጹት፣ ይህ ግብይት አሁን በዓሉን በማስመልከት ይጀመር እንጂ በአዘቦት ቀናትም የሚቀጥል ነው። ከዓመት ዓመት የበግ እና የፍየል እርድን ጨምሮ፣ ለተለያየ ኹነትም ሰብሰብ ብለው ቅርጫ ለፈለጉም አገልግሎቱ ተደራሽ እንደሚሆን አሳውቀዋል።
ቅርጫ የሚለው ባህል እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ቀለል ባለና ደኅንነቱ እና ደረጃው በተጠበቀ መንገድ አገልግሎትን መስጠት የሁሌ ቅርጫ ዓላማ መሆኑንም አቶ ቶማስ ተናግረዋል።
4 months ago
የፓን አፍሪካ ሮቦቲክስ ሻምፒዮንሺፕ በአዲስ አበባ በድምቀት ተጀመረ
#fastmereja I አዲስ አበባ
በቴክኖሎጂ የታነጸ ትውልድ ለመፍጠር ያለመው የፓን አፍሪካ ሮቦቲክስ ሻምፒዮንሺፕ ውድድር "እኔ ችግር ፈቺ ነኝ" በሚል መሪ ቃል ዛሬ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በይፋ ተጀምሯል። የኢትዮ ሮቦቲክስ የትምህርትና ስልጠና ማዕከል ባዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ ከአንደኛ ደረጃ እስከ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ተማሪዎች በሮቦቲክስ፣ በኮዲንግ እና በዲዛይኒንግ ዘርፎች የፈጠራ ብቃታቸውን እንደሚያሳዩ ታውቋል።
በመክፈቻው ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ባይሳ በዳዳ፣ መንግስት ለወጣቶች የፈጠራ ስራ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠሩንና መሰል ውድድሮች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስጠራት ያላቸውን ሚና ገልጸዋል። የኢትዮ ሮቦቲክስ መስራች አቶ ሰናይክረም መኮንን በበኩላቸው፣ መጪው ዘመን ድህነትና በሽታ በቴክኖሎጂ የሚሸነፉበት መሆኑን በመጥቀስ ታዳጊዎች ለችግር ፈቺነት እንዲተጉ ጥሪ አቅርበዋል።
ባለፉት 15 ዓመታት ወጣቶችን በዓለም አቀፍ መድረኮች ሲያሳትፍ የቆየው ኢትዮ ሮቦቲክስ፣ የዘንድሮው የፓን አፍሪካ ውድድር ተማሪዎች ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነታቸውን የሚያጎለብቱበት ወሳኝ ድልድይ እንደሚሆን ይጠበቃል። ድርጅቱ ከዚህ ቀደም በቻይና፣ ካናዳና አሜሪካ በሚካሄዱ ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያን በመወከል ስኬታማ ተሳትፎ ማድረጉ ይታወሳል።
#ኹነት
#fastmereja I አዲስ አበባ
በቴክኖሎጂ የታነጸ ትውልድ ለመፍጠር ያለመው የፓን አፍሪካ ሮቦቲክስ ሻምፒዮንሺፕ ውድድር "እኔ ችግር ፈቺ ነኝ" በሚል መሪ ቃል ዛሬ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በይፋ ተጀምሯል። የኢትዮ ሮቦቲክስ የትምህርትና ስልጠና ማዕከል ባዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ ከአንደኛ ደረጃ እስከ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ተማሪዎች በሮቦቲክስ፣ በኮዲንግ እና በዲዛይኒንግ ዘርፎች የፈጠራ ብቃታቸውን እንደሚያሳዩ ታውቋል።
በመክፈቻው ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ባይሳ በዳዳ፣ መንግስት ለወጣቶች የፈጠራ ስራ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠሩንና መሰል ውድድሮች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስጠራት ያላቸውን ሚና ገልጸዋል። የኢትዮ ሮቦቲክስ መስራች አቶ ሰናይክረም መኮንን በበኩላቸው፣ መጪው ዘመን ድህነትና በሽታ በቴክኖሎጂ የሚሸነፉበት መሆኑን በመጥቀስ ታዳጊዎች ለችግር ፈቺነት እንዲተጉ ጥሪ አቅርበዋል።
ባለፉት 15 ዓመታት ወጣቶችን በዓለም አቀፍ መድረኮች ሲያሳትፍ የቆየው ኢትዮ ሮቦቲክስ፣ የዘንድሮው የፓን አፍሪካ ውድድር ተማሪዎች ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነታቸውን የሚያጎለብቱበት ወሳኝ ድልድይ እንደሚሆን ይጠበቃል። ድርጅቱ ከዚህ ቀደም በቻይና፣ ካናዳና አሜሪካ በሚካሄዱ ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያን በመወከል ስኬታማ ተሳትፎ ማድረጉ ይታወሳል።
#ኹነት
4 months ago
10ኛው የኢትዮ ኸልዝ ዓለምአቀፍ አውደ ርዕይና 2ኛው የሀገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርት ኤግዚቢሽን በይፋ ተከፈተ
#fastmereja I 10ኛው የኢትዮ ኸልዝ ዓለምአቀፍ አውደ ርዕይና ጉባኤ እንዲሁም 2ኛው የሀገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ዛሬ በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር (AICC) በይፋ ተከፍቷል። በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) እና በፕራና ኢቨንትስ ትብብር የተዘጋጀው ይህ ታላቅ ኹነት ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን፣ ከ8 ሀገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎታቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።
በአዲስ አበባ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ አውደ ርዕይ በጤናው ዘርፍ ያለውን የቴክኖሎጂ ፍላጎት ለመሙላትና የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም ለማሳየት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። የዘንድሮው መርሃ ግብር ከኤግዚቢሽኑ ባሻገር ከ40 በላይ የሙያ ማጎልበቻ (CPD) ስልጠናዎችን እና 3ኛው የዲጂታል ኸልዝ ሃካቶንን ያካተተ በመሆኑ ለባለሙያዎች ልዩ የዕውቀት መጋሪያ መድረክ ፈጥሯል።
ኢትዮጵያ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ ሩሲያ፣ ቱርክ፣ ባንግላዴሽ፣ ዩኤኢ እና አሜሪካ ሀገራት ተሳታፊ ሲሆኑ ከ20 በላይ የሙያ ማህበራት ጋር በመተባበር የሚከናወኑ ሳይንሳዊ ፎረሞች እና የንግድ ትስስር መድረኮች ተዘጋጅተዋል።
መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
#ኹነት
#fastmereja I 10ኛው የኢትዮ ኸልዝ ዓለምአቀፍ አውደ ርዕይና ጉባኤ እንዲሁም 2ኛው የሀገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ዛሬ በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር (AICC) በይፋ ተከፍቷል። በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) እና በፕራና ኢቨንትስ ትብብር የተዘጋጀው ይህ ታላቅ ኹነት ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን፣ ከ8 ሀገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎታቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።
በአዲስ አበባ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ አውደ ርዕይ በጤናው ዘርፍ ያለውን የቴክኖሎጂ ፍላጎት ለመሙላትና የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም ለማሳየት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። የዘንድሮው መርሃ ግብር ከኤግዚቢሽኑ ባሻገር ከ40 በላይ የሙያ ማጎልበቻ (CPD) ስልጠናዎችን እና 3ኛው የዲጂታል ኸልዝ ሃካቶንን ያካተተ በመሆኑ ለባለሙያዎች ልዩ የዕውቀት መጋሪያ መድረክ ፈጥሯል።
ኢትዮጵያ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ ሩሲያ፣ ቱርክ፣ ባንግላዴሽ፣ ዩኤኢ እና አሜሪካ ሀገራት ተሳታፊ ሲሆኑ ከ20 በላይ የሙያ ማህበራት ጋር በመተባበር የሚከናወኑ ሳይንሳዊ ፎረሞች እና የንግድ ትስስር መድረኮች ተዘጋጅተዋል።
መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
#ኹነት
4 months ago
አዲስ አበባ አህጉራዊ የሪል ስቴት ጉባኤና ኤክስፖን ልታስተናግድ ነው!
#fastmereja I የኢትዮጵያ የሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር "አዲስ አፍሪካ ሪል እስቴት ኤክስፖ 2026" የተሰኘውን የመጀመሪያውን አህጉራዊ የኤግዚቢሽን መድረክ በመጪው ሚያዚያ ወር በአዲስ አበባ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።
ማህበሩ ከዶክሳ ኢቨንትስ ጋር በመተባበር ከሚያዚያ 15 እስከ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሙዚየም ለአራት ተከታታይ ቀናት የሚያካሂደው ይህ ታላቅ ኩነት፤ የኤክስፖውን ያህል ትልቅ አገራዊ ፋይዳ ያላቸውን መርሀ-ግብሮችን የያዘ መሆኑንም ገልፀዋል።
በእለቱ ከሚከናወኑ መርሀ-ግብሮች የማህበሩ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ፣የአፍሪካ ሪል ስቴት ማህበር(AFRES) የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤ እና አልሚዎች ያላቸዉን ያሏቸዉን ግብአቶች እና ፕሮጀክቶቿቸዉን ለህዝብ እና ለተሳታፊዎች የሚያሳዩባቸዉ መድረኮች መሆናቸዉ ተገልጿል።
የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ከተማ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ሪል ስቴት ማህበር የአባላቱን መብት ከማስጠበቅ ባለፈ፣ ደንበኞች ጥራት ያለውና በውል በተገባው ጊዜ የሚረከቡትን ቤት እንዲያገኙ የሚያስችል የክትትልና የሙያ ስነ-ምግባር ደንብ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ገልጿል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ የሚሳተፉት የማህበሩ አባል የሆኑ ህጋዊና እውቅና ያላቸው አልሚዎች ብቻ በመሆናቸው፣ ቤት ፈላጊው ማህበረሰብ ካልተገባ እንግልት እንዲጠበቅ እንደሚያደርገው ተመልክቷል።
ይህ መድረክ በተለይ የማህበሩ አባላት የሆኑ አልሚዎች የተለያዩ የቤትና የህንፃ ፕሮጀክቶቻቸውን ይዘው የሚቀርቡበት በመሆኑ፣ ቤትና የንግድ ቦታ ፈለጊ ማህበረሰብ አማራጮችን በአንድ ቦታ እንዲያገኝ ሰፊ ዕድል እንደሚፈጥር ታውቋል።
ከሪል ስቴት አልሚዎች በተጨማሪ የፋይናንስ ተቋማት፣ የኮንስትራክሽን ድርጅቶች እና ከዘርፉ ጋር ግንኙነት ያላቸው አካላት በዝግጅቱ ላይ የሚሳተፉ በመሆኑ ለዘርፉ እድገት ትልቅ አቅም ይፈጥራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነዉ የተገለፀዉ።
በኤክስፖው ላይ የሚሳተፉ የውጭ አገር እንግዶችና ባለሀብቶች አዲስ አበባ በቅርቡ ያስገነባቻቸውን አዳዲስ የቱሪስት መስህቦችና የኮሪደር ልማቶችን እንዲጎበኙ ፕሮግራም መያዙ ተያይዞ ተገልጿል።
ይህም አገሪቱ ከኮንፈረንስ ቱሪዝም የምታገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግና የአዲስ አበባን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ዳግም ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
#ኹነት
#fastmereja I የኢትዮጵያ የሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር "አዲስ አፍሪካ ሪል እስቴት ኤክስፖ 2026" የተሰኘውን የመጀመሪያውን አህጉራዊ የኤግዚቢሽን መድረክ በመጪው ሚያዚያ ወር በአዲስ አበባ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።
ማህበሩ ከዶክሳ ኢቨንትስ ጋር በመተባበር ከሚያዚያ 15 እስከ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሙዚየም ለአራት ተከታታይ ቀናት የሚያካሂደው ይህ ታላቅ ኩነት፤ የኤክስፖውን ያህል ትልቅ አገራዊ ፋይዳ ያላቸውን መርሀ-ግብሮችን የያዘ መሆኑንም ገልፀዋል።
በእለቱ ከሚከናወኑ መርሀ-ግብሮች የማህበሩ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ፣የአፍሪካ ሪል ስቴት ማህበር(AFRES) የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤ እና አልሚዎች ያላቸዉን ያሏቸዉን ግብአቶች እና ፕሮጀክቶቿቸዉን ለህዝብ እና ለተሳታፊዎች የሚያሳዩባቸዉ መድረኮች መሆናቸዉ ተገልጿል።
የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ከተማ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ሪል ስቴት ማህበር የአባላቱን መብት ከማስጠበቅ ባለፈ፣ ደንበኞች ጥራት ያለውና በውል በተገባው ጊዜ የሚረከቡትን ቤት እንዲያገኙ የሚያስችል የክትትልና የሙያ ስነ-ምግባር ደንብ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ገልጿል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ የሚሳተፉት የማህበሩ አባል የሆኑ ህጋዊና እውቅና ያላቸው አልሚዎች ብቻ በመሆናቸው፣ ቤት ፈላጊው ማህበረሰብ ካልተገባ እንግልት እንዲጠበቅ እንደሚያደርገው ተመልክቷል።
ይህ መድረክ በተለይ የማህበሩ አባላት የሆኑ አልሚዎች የተለያዩ የቤትና የህንፃ ፕሮጀክቶቻቸውን ይዘው የሚቀርቡበት በመሆኑ፣ ቤትና የንግድ ቦታ ፈለጊ ማህበረሰብ አማራጮችን በአንድ ቦታ እንዲያገኝ ሰፊ ዕድል እንደሚፈጥር ታውቋል።
ከሪል ስቴት አልሚዎች በተጨማሪ የፋይናንስ ተቋማት፣ የኮንስትራክሽን ድርጅቶች እና ከዘርፉ ጋር ግንኙነት ያላቸው አካላት በዝግጅቱ ላይ የሚሳተፉ በመሆኑ ለዘርፉ እድገት ትልቅ አቅም ይፈጥራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነዉ የተገለፀዉ።
በኤክስፖው ላይ የሚሳተፉ የውጭ አገር እንግዶችና ባለሀብቶች አዲስ አበባ በቅርቡ ያስገነባቻቸውን አዳዲስ የቱሪስት መስህቦችና የኮሪደር ልማቶችን እንዲጎበኙ ፕሮግራም መያዙ ተያይዞ ተገልጿል።
ይህም አገሪቱ ከኮንፈረንስ ቱሪዝም የምታገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግና የአዲስ አበባን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ዳግም ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
#ኹነት
4 months ago
“ኢትዮ ሆም-ኤክስፖ 2026” በለንደን ከተማ ሊካሄድ ነዉ!
#fastmereja I በዩናይትድ ኪንግደም ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው አስተማማኝ የቤት ባለቤት እንዲሆኑ የሚያስችል “ኢትዮ ሆም-ኤክስፖ 2026" የተሰኘ ታላቅ የሪል ስቴት ኤክስፖ በለንደን ከተማ እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት ተገለፀ።
በለንደን የሚገኘው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ፣ ከኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ሪልስቴት አልሚዎች ማህበር፣ ከአዲስ አበባ ንግድ ምክርቤት እና ኤድማርቬንቸርስ ከተባለ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተቋም ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
ኤክስፖው ከግንቦት 15 እስከ 17 ቀን 2018 (May 23-25, 2026) ለሶሰት ተከታታይ ቀናት በለንደን ከተማ የሚካሄድ ሲሆን ከ3000 በላይ ተሳታፊዎች እንደሚኖሩም ነዉ የተገለፀዉ።
ይህ ኤክስፖ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ቤት የማፍራት ህልማቸውን እውን እንዲያደርጉ፣ በአልሚዎችና በተጠቃሚዎች መካከል ያለውን መተማመን ማሳደግና አስተማማኝ የግብይት ሥርዓት ማስተዋወቅ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት በኤክስፖው የሚሳተፉ አልሚዎችን በግንባታ አፈፃፀማቸው፣ በጥራትና በሰነድ ህጋዊነት የመለየትና የማጣራት ስራ በመስራት የዲያስፖራውን ስጋት ለመቅረፍ እንደሚሰራ የኤድማር ቬንቸር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ፋሲካ አብዛ ገልፀዋል።
ኤክስፖዉ በዘርፉ ስላሉ አዳዲስ ፖሊሲዎችና የቤት ግዢ አማራጮች ከመንግስትና ከግል ተቋማት ጋር የመረጃ ልውውጥና የፓናል ውይይቶች የሚደረጉ ሲሆን የንግድ ባንኮች ለዲያስፖራው ማህበረሰብ የሚሆኑ ልዩ የፋይናንስ ድጋፎችንና የቤት ባለቤት የሚያደርጉ የብድር አማራጮችን ለተሳታፊዎች እንደሚያስተዋዉቁም ነዉ የተገለፀዉ።
በዛሬዉ እለት በተከናወነ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አዘጋጁ ኤድማር ቬንቸር እና አዲስ ቻምበር በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸዉን የፌርማ ስነ-ስርአት አከናዉነዋል።
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍፁም አረጋን ጨምሮ የኢትዮጵያ ሪልስቴት አልሚዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ከተማ፣ የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሐንስ ወልደገብርኤል እንዲሁም የኤድማር ቬንቸርስ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ፋሲካ አብዛ ተገኝተዋል።
#ኹነት
#fastmereja I በዩናይትድ ኪንግደም ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው አስተማማኝ የቤት ባለቤት እንዲሆኑ የሚያስችል “ኢትዮ ሆም-ኤክስፖ 2026" የተሰኘ ታላቅ የሪል ስቴት ኤክስፖ በለንደን ከተማ እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት ተገለፀ።
በለንደን የሚገኘው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ፣ ከኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ሪልስቴት አልሚዎች ማህበር፣ ከአዲስ አበባ ንግድ ምክርቤት እና ኤድማርቬንቸርስ ከተባለ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተቋም ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
ኤክስፖው ከግንቦት 15 እስከ 17 ቀን 2018 (May 23-25, 2026) ለሶሰት ተከታታይ ቀናት በለንደን ከተማ የሚካሄድ ሲሆን ከ3000 በላይ ተሳታፊዎች እንደሚኖሩም ነዉ የተገለፀዉ።
ይህ ኤክስፖ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ቤት የማፍራት ህልማቸውን እውን እንዲያደርጉ፣ በአልሚዎችና በተጠቃሚዎች መካከል ያለውን መተማመን ማሳደግና አስተማማኝ የግብይት ሥርዓት ማስተዋወቅ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት በኤክስፖው የሚሳተፉ አልሚዎችን በግንባታ አፈፃፀማቸው፣ በጥራትና በሰነድ ህጋዊነት የመለየትና የማጣራት ስራ በመስራት የዲያስፖራውን ስጋት ለመቅረፍ እንደሚሰራ የኤድማር ቬንቸር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ፋሲካ አብዛ ገልፀዋል።
ኤክስፖዉ በዘርፉ ስላሉ አዳዲስ ፖሊሲዎችና የቤት ግዢ አማራጮች ከመንግስትና ከግል ተቋማት ጋር የመረጃ ልውውጥና የፓናል ውይይቶች የሚደረጉ ሲሆን የንግድ ባንኮች ለዲያስፖራው ማህበረሰብ የሚሆኑ ልዩ የፋይናንስ ድጋፎችንና የቤት ባለቤት የሚያደርጉ የብድር አማራጮችን ለተሳታፊዎች እንደሚያስተዋዉቁም ነዉ የተገለፀዉ።
በዛሬዉ እለት በተከናወነ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አዘጋጁ ኤድማር ቬንቸር እና አዲስ ቻምበር በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸዉን የፌርማ ስነ-ስርአት አከናዉነዋል።
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍፁም አረጋን ጨምሮ የኢትዮጵያ ሪልስቴት አልሚዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ከተማ፣ የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሐንስ ወልደገብርኤል እንዲሁም የኤድማር ቬንቸርስ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ፋሲካ አብዛ ተገኝተዋል።
#ኹነት
4 months ago
የፊቼ ጫምባላላ በዓል በአዲስ አበባ በልዩ ድምቀት ተከበረ!
#fastmereja I የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫና በዩኔስኮ (UNESCO) በማይዳሰስ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበው የፊቼ ጫምባላላ በዓል በዛሬዉ እለት በወዳጅነት አደባባይ በድምቀት ተከበረ።
በዓሉ በመዲናዋ ለ7ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን ዋና ዓላማውም የሰላም፣ የእርቅና የአንድነት እሴቶችን ለሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች ማጋራት እንደሆነ ተገልፆ በዓሉ ለሰው ልጅ ብቻ ሳይሆን ለእንስሳትና ለተፈጥሮም ጭምር ሰላምን የሚመኝ ጥልቅ ባህላዊ ትርጉም ያለው መሆኑም ተመላክቷል።
ፊቼ ጨምበላላ ትልቅ የመንፈሳዊና የቁሳዊ ባህል እሴት የሚታይበት በዓል መሆኑን እና፤ የጨረቃንና የከዋክብትን ፈለግና ዑደት ለዘመናት የቀመረ ነባር ሀገር በቀል የእውቀት መገለጫ መሆኑን አስረድተዉ በበዓሉ ላይ የሚታየው የባህሎች መስተጋብርም ኢትዮጵያ የምታልማትን የጋራና ማንነት የሚያንፀባርቅ መሆኑን የባህልና ስፖርት ሚኒስትርዴኤታ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ ገልፀዋል።
በዓሉ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ መሪነትና ድጋፍ በየዓመቱ እየተከበረ የቆየ ሲሆን፣ አሁን ላይ ለከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት የሚሰጥ ትልቅ ህዝባዊ ፌስቲቫል ለመሆን መብቃቱ ነዉ የተገለፀዉ።
በዛሬዉ እለት በተከናወነዉ መርሀ-ግብር ላይ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የሲዳማ ማህበረሰብ አባቶች፣ አባ ገዳዎችና ሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም በርካታ የሲዳማ ተወላጆች ታድመዋል።
#ኹነት
#fastmereja I የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫና በዩኔስኮ (UNESCO) በማይዳሰስ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበው የፊቼ ጫምባላላ በዓል በዛሬዉ እለት በወዳጅነት አደባባይ በድምቀት ተከበረ።
በዓሉ በመዲናዋ ለ7ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን ዋና ዓላማውም የሰላም፣ የእርቅና የአንድነት እሴቶችን ለሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች ማጋራት እንደሆነ ተገልፆ በዓሉ ለሰው ልጅ ብቻ ሳይሆን ለእንስሳትና ለተፈጥሮም ጭምር ሰላምን የሚመኝ ጥልቅ ባህላዊ ትርጉም ያለው መሆኑም ተመላክቷል።
ፊቼ ጨምበላላ ትልቅ የመንፈሳዊና የቁሳዊ ባህል እሴት የሚታይበት በዓል መሆኑን እና፤ የጨረቃንና የከዋክብትን ፈለግና ዑደት ለዘመናት የቀመረ ነባር ሀገር በቀል የእውቀት መገለጫ መሆኑን አስረድተዉ በበዓሉ ላይ የሚታየው የባህሎች መስተጋብርም ኢትዮጵያ የምታልማትን የጋራና ማንነት የሚያንፀባርቅ መሆኑን የባህልና ስፖርት ሚኒስትርዴኤታ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ ገልፀዋል።
በዓሉ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ መሪነትና ድጋፍ በየዓመቱ እየተከበረ የቆየ ሲሆን፣ አሁን ላይ ለከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት የሚሰጥ ትልቅ ህዝባዊ ፌስቲቫል ለመሆን መብቃቱ ነዉ የተገለፀዉ።
በዛሬዉ እለት በተከናወነዉ መርሀ-ግብር ላይ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የሲዳማ ማህበረሰብ አባቶች፣ አባ ገዳዎችና ሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም በርካታ የሲዳማ ተወላጆች ታድመዋል።
#ኹነት
4 months ago
በኢትዮጵያ የሕክምና ዘርፍ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ሚና ላይ ያተኮረው 62ኛው የኢሕማ ዓመታዊ ጉባኤ በሂልተን ሆቴል ተከፈተ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሕክምና ማኅበር (ኢሕማ) "የሰው ሠራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) በሕክምና ትምህርት፣ በጤና አገልግሎት አሰጣጥ እና በምርምር ዘርፍ ያለውን ሚና ማሳደግ" በሚል መሪ ቃል 62ኛ ዓመታዊ ጉባኤውንና ዓለም አቀፍ የጤና ኤግዚቢሽኑን ዛሬ በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል በይፋ ጀምሯል።
በመክፈቻው ላይ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሃረላ አብዱላሂን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የሕክምና ስፔሻሊስቶች ተገኝተዋል። ጉባኤው በዋናነት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የኢትዮጵያን የሕክምና ጥራትና ተደራሽነት ማዘመን በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ያተኮረ ምክክር እያካሄደ ይገኛል።
የዘንድሮው መሪ ቃል በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ እምብዛም ያልተለመደውን የAI ቴክኖሎጂን ለምርምርና ለታካሚዎች ፈጣን ሕክምና እንዴት ማዋል እንደሚቻል አዳዲስ አቅጣጫዎችን የሚያመላክት መሆኑ ተገልጿል። በተጓዳኝ እየተካሄደ ባለው ኤግዚቢሽን ላይም ከቴክኖሎጂው ጋር የተያያዙ የሕክምና መሣሪያዎችና ዲጂታል መፍትሔዎች ለጉብኝት ቀርበዋል።
በዛሬው መርሃ ግብር ላይ የኢሕማ አዋርድ ላይ ተካሂዷል።
#ኹነት
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሕክምና ማኅበር (ኢሕማ) "የሰው ሠራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) በሕክምና ትምህርት፣ በጤና አገልግሎት አሰጣጥ እና በምርምር ዘርፍ ያለውን ሚና ማሳደግ" በሚል መሪ ቃል 62ኛ ዓመታዊ ጉባኤውንና ዓለም አቀፍ የጤና ኤግዚቢሽኑን ዛሬ በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል በይፋ ጀምሯል።
በመክፈቻው ላይ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሃረላ አብዱላሂን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የሕክምና ስፔሻሊስቶች ተገኝተዋል። ጉባኤው በዋናነት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የኢትዮጵያን የሕክምና ጥራትና ተደራሽነት ማዘመን በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ያተኮረ ምክክር እያካሄደ ይገኛል።
የዘንድሮው መሪ ቃል በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ እምብዛም ያልተለመደውን የAI ቴክኖሎጂን ለምርምርና ለታካሚዎች ፈጣን ሕክምና እንዴት ማዋል እንደሚቻል አዳዲስ አቅጣጫዎችን የሚያመላክት መሆኑ ተገልጿል። በተጓዳኝ እየተካሄደ ባለው ኤግዚቢሽን ላይም ከቴክኖሎጂው ጋር የተያያዙ የሕክምና መሣሪያዎችና ዲጂታል መፍትሔዎች ለጉብኝት ቀርበዋል።
በዛሬው መርሃ ግብር ላይ የኢሕማ አዋርድ ላይ ተካሂዷል።
#ኹነት
4 months ago
በሐዋሳ ከተማ ታላቅ የጎዳና ላይ ሩጫ ሊካሄድ ነው!
#fastmereja “አብረን እንሩጥ፣ ለሐዋሳ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ የሚካሄድ ታላቅ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ መዘጋጀቱ በዛሬዉ እለት በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ይህ በዓይነቱ ለየት ያለ ስፖርታዊ ኩነት የሚዘጋጀው ለስድስት አስርት ዓመታት በታማኝነት ሲያገለግል በቆየውና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለቤትነት በሚተዳደረው ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና በታዋቂው አትሌት ገዝሀኝ አበራ ትብብር መሆኑ ተገልጿል።
በዝግጅቱ ላይ ከ15 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ታዋቂ አትሌቶች፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች እንዲሁም የሐዋሳ ከተማና የአካባቢው ነዋሪዎች የሩጫው አካል እንደሚሆኑ ታውቋል።
ውድድሩን በአሸናፊነት ለሚያጠናቅቁ ሯጮችም ከፍተኛ የገንዘብ እና የሜዳሊያ ሽልማት እንደሚበረከት አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
የዝግጅቱ ዋና ዓላማዎች የማህበረሰቡን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ባህል ማሳደግ፤በከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ያለውን ማህበራዊ ትስስር፣ ሰላምና አብሮነት ማጠናከር፤የሐዋሳን የቱሪዝም ዘርፍ ማነቃቃት እንዲሁም የከተማዋን ገጽታ መገንባት መሆኑ ነዉ የተገለፀዉ።
ኮሜርሻል ኖሚኒስ በቀጣይም ከታዋቂው አትሌት ገዝሀኝ አበራ ጋር በመሆን መሰል የጎዳና ላይ ሩጫዎችን በተመረጡ የሀገሪቱ ከተሞች ለማካሄድ እቅድ እንዳለው ገልጿል።
#ስፖርት #ኹነት
#fastmereja “አብረን እንሩጥ፣ ለሐዋሳ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ የሚካሄድ ታላቅ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ መዘጋጀቱ በዛሬዉ እለት በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ይህ በዓይነቱ ለየት ያለ ስፖርታዊ ኩነት የሚዘጋጀው ለስድስት አስርት ዓመታት በታማኝነት ሲያገለግል በቆየውና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለቤትነት በሚተዳደረው ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና በታዋቂው አትሌት ገዝሀኝ አበራ ትብብር መሆኑ ተገልጿል።
በዝግጅቱ ላይ ከ15 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ታዋቂ አትሌቶች፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች እንዲሁም የሐዋሳ ከተማና የአካባቢው ነዋሪዎች የሩጫው አካል እንደሚሆኑ ታውቋል።
ውድድሩን በአሸናፊነት ለሚያጠናቅቁ ሯጮችም ከፍተኛ የገንዘብ እና የሜዳሊያ ሽልማት እንደሚበረከት አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
የዝግጅቱ ዋና ዓላማዎች የማህበረሰቡን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ባህል ማሳደግ፤በከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ያለውን ማህበራዊ ትስስር፣ ሰላምና አብሮነት ማጠናከር፤የሐዋሳን የቱሪዝም ዘርፍ ማነቃቃት እንዲሁም የከተማዋን ገጽታ መገንባት መሆኑ ነዉ የተገለፀዉ።
ኮሜርሻል ኖሚኒስ በቀጣይም ከታዋቂው አትሌት ገዝሀኝ አበራ ጋር በመሆን መሰል የጎዳና ላይ ሩጫዎችን በተመረጡ የሀገሪቱ ከተሞች ለማካሄድ እቅድ እንዳለው ገልጿል።
#ስፖርት #ኹነት
4 months ago
170,000,000 ብር የእንጦጦ ኪዳነምሕረት የገቢ ማሰባሰቢያ
ሪከርድ በመስበር ተጠናቀቀ
ከመጋቢት 11 እሰ መጋቢት 12/2018 በእንጦጦ ኪዳነምሕረት አዳራሽ ሲከናወን የነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 170,000,000.000 /አንድ መቶ ሰባ ሚሊያን/ ብር በመሰብሰብ ተጠናቀቀ።
ከዚኽ ውስጥ 139,000,000.00 ሚሊዬን ብር የተረጋገጠ ሲሆን ቀሪው 31 ሚሊዬ ብር ደግሞ ቃል የተገባ ሲሆን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይኽንን መሥሐግብር ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ አሚን ቆሞስ አባ ገብረ ሥላሴ ይርሳው የገዳሟ ዋና አበመኔት፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ መምህራን፣ ዘማርያን፣ ምእመናን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሦስቱንም ሌሊት በንቃት ተሳትፈውበታል።
ቲክታከሮች፣ ዩቱበሮች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች ዶክመንተሪ፣ ማስታወቂያ፣ ቀጥታ ሥርጭት መርሐግብሩን በትሩፋት በማገልገላቸው ከገዳሟ አበው መነኮሳት ማስታወሻ እንዲኾናቸው መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ እና ሠርተፍኬት በስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ይኽንን ኹነት ከኮሚቴው ጋር በመተባበር የማስተባበር እና የማማከር ተግባር ለአንድ ወር ያከናወነው ሎዛ ኹነቶች - Liza Events በትሩፋት በማገልገሉ መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ፣ የወርቅ ካባ እና ሠርተፍኬት ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ እና ከገዳሙ አበመኔት እጅ በስጦታ ተበርክቶለታል።
ሪከርድ በመስበር ተጠናቀቀ
ከመጋቢት 11 እሰ መጋቢት 12/2018 በእንጦጦ ኪዳነምሕረት አዳራሽ ሲከናወን የነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 170,000,000.000 /አንድ መቶ ሰባ ሚሊያን/ ብር በመሰብሰብ ተጠናቀቀ።
ከዚኽ ውስጥ 139,000,000.00 ሚሊዬን ብር የተረጋገጠ ሲሆን ቀሪው 31 ሚሊዬ ብር ደግሞ ቃል የተገባ ሲሆን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይኽንን መሥሐግብር ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ አሚን ቆሞስ አባ ገብረ ሥላሴ ይርሳው የገዳሟ ዋና አበመኔት፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ መምህራን፣ ዘማርያን፣ ምእመናን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሦስቱንም ሌሊት በንቃት ተሳትፈውበታል።
ቲክታከሮች፣ ዩቱበሮች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች ዶክመንተሪ፣ ማስታወቂያ፣ ቀጥታ ሥርጭት መርሐግብሩን በትሩፋት በማገልገላቸው ከገዳሟ አበው መነኮሳት ማስታወሻ እንዲኾናቸው መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ እና ሠርተፍኬት በስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ይኽንን ኹነት ከኮሚቴው ጋር በመተባበር የማስተባበር እና የማማከር ተግባር ለአንድ ወር ያከናወነው ሎዛ ኹነቶች - Liza Events በትሩፋት በማገልገሉ መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ፣ የወርቅ ካባ እና ሠርተፍኬት ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ እና ከገዳሙ አበመኔት እጅ በስጦታ ተበርክቶለታል።
Sponsored by
Surafel
4 months ago
የእንጦጦ ኪዳነምሕረት የገቢ ማሰባሰቢያ
ሪከርድ በመስበር ተጠናቀቀ
ከመጋቢት 11 እሰ መጋቢት 12/2018 በእንጦጦ ኪዳነምሕረት አዳራሽ ሲከናወን የነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 170,000,000.000 /አንድ መቶ ሰባ ሚሊያን/ ብር በመሰብሰብ ተጠናቀቀ።
ከዚኽ ውስጥ 139,000,000.00 ሚሊዬን ብር የተረጋገጠ ሲሆን ቀሪው 31 ሚሊዬ ብር ደግሞ ቃል የተገባ ሲሆን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይኽንን መሥሐግብር ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ አሚን ቆሞስ አባ ገብረ ሥላሴ ይርሳው የገዳሟ ዋና አበመኔት፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ መምህራን፣ ዘማርያን፣ ምእመናን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሦስቱንም ሌሊት በንቃት ተሳትፈውበታል።
ቲክታከሮች፣ ዩቱበሮች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች ዶክመንተሪ፣ ማስታወቂያ፣ ቀጥታ ሥርጭት መርሐግብሩን በትሩፋት በማገልገላቸው ከገዳሟ አበው መነኮሳት ማስታወሻ እንዲኾናቸው መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ እና ሠርተፍኬት በስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ይኽንን ኹነት ከኮሚቴው ጋር በመተባበር የማስተባበር እና የማማከር ተግባር ለአንድ ወር ያከናወነው ሎዛ ኹነቶች - Liza Events በትሩፋት በማገልገሉ መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ፣ የወርቅ ካባ እና ሠርተፍኬት ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ እና ከገዳሙ አበመኔት እጅ በስጦታ ተበርክቶለታል።
ሪከርድ በመስበር ተጠናቀቀ
ከመጋቢት 11 እሰ መጋቢት 12/2018 በእንጦጦ ኪዳነምሕረት አዳራሽ ሲከናወን የነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 170,000,000.000 /አንድ መቶ ሰባ ሚሊያን/ ብር በመሰብሰብ ተጠናቀቀ።
ከዚኽ ውስጥ 139,000,000.00 ሚሊዬን ብር የተረጋገጠ ሲሆን ቀሪው 31 ሚሊዬ ብር ደግሞ ቃል የተገባ ሲሆን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይኽንን መሥሐግብር ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ አሚን ቆሞስ አባ ገብረ ሥላሴ ይርሳው የገዳሟ ዋና አበመኔት፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ መምህራን፣ ዘማርያን፣ ምእመናን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሦስቱንም ሌሊት በንቃት ተሳትፈውበታል።
ቲክታከሮች፣ ዩቱበሮች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች ዶክመንተሪ፣ ማስታወቂያ፣ ቀጥታ ሥርጭት መርሐግብሩን በትሩፋት በማገልገላቸው ከገዳሟ አበው መነኮሳት ማስታወሻ እንዲኾናቸው መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ እና ሠርተፍኬት በስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ይኽንን ኹነት ከኮሚቴው ጋር በመተባበር የማስተባበር እና የማማከር ተግባር ለአንድ ወር ያከናወነው ሎዛ ኹነቶች - Liza Events በትሩፋት በማገልገሉ መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ፣ የወርቅ ካባ እና ሠርተፍኬት ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ እና ከገዳሙ አበመኔት እጅ በስጦታ ተበርክቶለታል።
5 months ago
10ኛው "ኢትዮ ኸልዝ" ዓለምአቀፍ አውደርዕይ እና ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው
#fastmereja I በአስርተ ዓመታት የጤናው ዘርፍ ጉዞ ታላቅ ስም ያተረፈው ኢትዮ ኸልዝ ዓለምአቀፍ አውደርዕይና ጉባኤ፣ ለ10ኛ ጊዜ ከመጋቢት 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር (AICC) እንደሚካሄድ ዛሬ መጋቢት 08 ቀን 2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ፕራና ኢቨንትስ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ከአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ ከ8 ሀገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ያቀርባሉ።
የዘንድሮው ኹነት 2ኛው የሀገር ውስጥ የሕክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ጎን ለጎን የሚካሄድ ሲሆን፣ ዓላማውም የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም ማሳየትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከ20 በላይ ከሚሆኑ የሙያ ማኅበራት ጋር በመተባበር፣ ከ40 በላይ የሙያ ማጎልበቻ ስልጠናዎች ለጤና ባለሙያዎች ይሰጣሉ።
2ኛው ዓመታዊ ሳይንሳዊ ፎረም፣ የጤና አመራር ጉባኤ እና 3ኛው የዲጂታል ኸልዝ ሃካቶን በኹነቱ ውስጥ የተካተቱ አቢይ መድረኮች ናቸው።
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ከባንግላዴሽ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ ሩሲያ፣ ቱርክ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ እና አሜሪካ የመጡ ኩባንያዎች ይሳተፋሉ።
ይህ መድረክ በኢትዮጵያ የጤናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፋጠን፣ የንግድ ትስስር እንዲጎለብትና የሕክምና አገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል። በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) እና በሌሎችም ተቋማት ሙሉ ዕውቅና የተሰጠው ይህ አውደርዕይ፣ የዘርፉ ተዋናዮች የሚገናኙበት ትልቁ ሀገራዊ መድረክ ነው።
#ኹነት
#fastmereja I በአስርተ ዓመታት የጤናው ዘርፍ ጉዞ ታላቅ ስም ያተረፈው ኢትዮ ኸልዝ ዓለምአቀፍ አውደርዕይና ጉባኤ፣ ለ10ኛ ጊዜ ከመጋቢት 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር (AICC) እንደሚካሄድ ዛሬ መጋቢት 08 ቀን 2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ፕራና ኢቨንትስ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ከአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ ከ8 ሀገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ያቀርባሉ።
የዘንድሮው ኹነት 2ኛው የሀገር ውስጥ የሕክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ጎን ለጎን የሚካሄድ ሲሆን፣ ዓላማውም የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም ማሳየትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከ20 በላይ ከሚሆኑ የሙያ ማኅበራት ጋር በመተባበር፣ ከ40 በላይ የሙያ ማጎልበቻ ስልጠናዎች ለጤና ባለሙያዎች ይሰጣሉ።
2ኛው ዓመታዊ ሳይንሳዊ ፎረም፣ የጤና አመራር ጉባኤ እና 3ኛው የዲጂታል ኸልዝ ሃካቶን በኹነቱ ውስጥ የተካተቱ አቢይ መድረኮች ናቸው።
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ከባንግላዴሽ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ ሩሲያ፣ ቱርክ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ እና አሜሪካ የመጡ ኩባንያዎች ይሳተፋሉ።
ይህ መድረክ በኢትዮጵያ የጤናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፋጠን፣ የንግድ ትስስር እንዲጎለብትና የሕክምና አገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል። በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) እና በሌሎችም ተቋማት ሙሉ ዕውቅና የተሰጠው ይህ አውደርዕይ፣ የዘርፉ ተዋናዮች የሚገናኙበት ትልቁ ሀገራዊ መድረክ ነው።
#ኹነት
5 months ago
የአእምሮ እድገት ውስንነት ቀንን አስመልክቶ የተዘጋጀዉ ስፖርታዊ ውድድር በይፋ ተከፈተ!
#fastmereja | 11ኛው የዓለም የዳውን ሲንድሮም ቀን በኢትዮጵያ “ብቸኝነትን በአንድነት እንመክት” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀዉ ስፖርታዊ ዉድድር በዛሬዉ እለት በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ በይፋ ተከፍቷል።
በዛሬዉ የመክፈቻ ስነ-ስርአት ላይ የኢትዮጵያ ባህልና ቱሪዝም ሚንስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ እንዲሁም የስፔሻል ኦሎምፒክ ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ግዛቸዉ ግርማን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች በተገኙበት ነዉ የተከናወነዉ።
ስፔሻል ኦሊምፒክስ ኢትዮጵያ ከ“ፍቅር የኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማኅበር” ጋር በመተባበር የተዘጋጀዉ ይህ ሀገር አቀፍ ጨዋታ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ዉድድሩ ሁሉንም የኦሎምፒክ ስፖርት ዓይነቶች ያካተተ ሲሆን፣ ውድድሩም የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ተወዳዳሪዎች ባማከለ ልዩ የስፖርት ሕግ መሠረት እየተከናወነ ይገኛል።
የፍቅር ኢትዮጵያ ማህበር የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች አስተምሮና አሰልጥኖ በማኅበሩ ውስጥ የሥራ ቅጥር እንዲያገኙ በማድረግ ጭምር አርአያነት ያለው ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት በአፍሪካና በኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ወገኖች ላይ የሚደርሰው መገለልና መድልዎ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እንዲህ ያሉ ስፖርታዊ መድረኮች ግንዛቤን ለመፍጠርና ብቸኝነትን ለመቀነስ ትልቅ ፋይዳ አላቸው።
በዛሬዉ የመክፈቻ መርሀ-ግብር ላይ ደራሲ፣ዳይሬክተር እንዲሁም ፕሮዲዉሰር የሆነችዉን የራስወርቅ ግርማ የስፔሻል ኦሎምፒክ በጎ ፍቃድ አምባሳደር ሆና ተሾማለች።
#ኹነት #ስፖርት
#fastmereja | 11ኛው የዓለም የዳውን ሲንድሮም ቀን በኢትዮጵያ “ብቸኝነትን በአንድነት እንመክት” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀዉ ስፖርታዊ ዉድድር በዛሬዉ እለት በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ በይፋ ተከፍቷል።
በዛሬዉ የመክፈቻ ስነ-ስርአት ላይ የኢትዮጵያ ባህልና ቱሪዝም ሚንስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ እንዲሁም የስፔሻል ኦሎምፒክ ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ግዛቸዉ ግርማን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች በተገኙበት ነዉ የተከናወነዉ።
ስፔሻል ኦሊምፒክስ ኢትዮጵያ ከ“ፍቅር የኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማኅበር” ጋር በመተባበር የተዘጋጀዉ ይህ ሀገር አቀፍ ጨዋታ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ዉድድሩ ሁሉንም የኦሎምፒክ ስፖርት ዓይነቶች ያካተተ ሲሆን፣ ውድድሩም የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ተወዳዳሪዎች ባማከለ ልዩ የስፖርት ሕግ መሠረት እየተከናወነ ይገኛል።
የፍቅር ኢትዮጵያ ማህበር የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች አስተምሮና አሰልጥኖ በማኅበሩ ውስጥ የሥራ ቅጥር እንዲያገኙ በማድረግ ጭምር አርአያነት ያለው ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት በአፍሪካና በኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ወገኖች ላይ የሚደርሰው መገለልና መድልዎ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እንዲህ ያሉ ስፖርታዊ መድረኮች ግንዛቤን ለመፍጠርና ብቸኝነትን ለመቀነስ ትልቅ ፋይዳ አላቸው።
በዛሬዉ የመክፈቻ መርሀ-ግብር ላይ ደራሲ፣ዳይሬክተር እንዲሁም ፕሮዲዉሰር የሆነችዉን የራስወርቅ ግርማ የስፔሻል ኦሎምፒክ በጎ ፍቃድ አምባሳደር ሆና ተሾማለች።
#ኹነት #ስፖርት
5 months ago
ሲቢኢ ኑር ኢድ ኤክስፖ 2018 በአዲስ አበባ ኤግዚብሽን ማዕከል ተከፈተ!
#fastmereja I "ሲቢኢ ኑር ኢድ ኤክስፖ 2018" በታላቅ ድምቀት ዛሬ ተከፈተ! በNiembek Event Organization አዘጋጅነት የቀረበው ይህ ታላቅ የንግድ ትርኢት እና ባዛር በአዲስ አበባ ኤግዚብሽን ማዕከል በይፋ ተከፍቷል። ኤክስፖው እስከ ኢድ ዋዜማ ድረስ ለተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል።
በኤክስፖው ላይ ተገኝተው ግብይት የሚፈጽሙ ጎብኚዎች በመግቢያ ቲኬታቸው ብቻ የታደሉ ሆነው ከተገኙ ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) ተሸላሚ የሚሆኑበት ልዩ ዕድል ተዘጋጅቷል!
ልዩ ልዩ የቤት እና የቢሮ ቁሳቁሶች አልባሳት፣ ጫማዎች እና መዋቢያዎች ለየት ያሉ የበዓል ቅናሾች እና ስጦታዎች በኤክስፖ ይገኛል።
#ኹነት
#fastmereja I "ሲቢኢ ኑር ኢድ ኤክስፖ 2018" በታላቅ ድምቀት ዛሬ ተከፈተ! በNiembek Event Organization አዘጋጅነት የቀረበው ይህ ታላቅ የንግድ ትርኢት እና ባዛር በአዲስ አበባ ኤግዚብሽን ማዕከል በይፋ ተከፍቷል። ኤክስፖው እስከ ኢድ ዋዜማ ድረስ ለተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል።
በኤክስፖው ላይ ተገኝተው ግብይት የሚፈጽሙ ጎብኚዎች በመግቢያ ቲኬታቸው ብቻ የታደሉ ሆነው ከተገኙ ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) ተሸላሚ የሚሆኑበት ልዩ ዕድል ተዘጋጅቷል!
ልዩ ልዩ የቤት እና የቢሮ ቁሳቁሶች አልባሳት፣ ጫማዎች እና መዋቢያዎች ለየት ያሉ የበዓል ቅናሾች እና ስጦታዎች በኤክስፖ ይገኛል።
#ኹነት
Sponsored by
Surafel
5 months ago
3ኛው ታላቁ የኢትዮ ኢድ ኤክስፖ በጊዮን ሆቴል በደመቀ ሁኔታ ተከፈተ!
#fastmereja I እምነትን፣ ባህልንና ንግድን በአንድ መድረክ የሚያገናኘው "3ኛው ታላቁ የኢትዮ ኢድ ኤክስፖ" በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ጊዮን ሆቴል በይፋ ተከፈተ። በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ምሁራንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ባህልንና አንድነትን የሚያጠናክር መድረክ
የኤክስፖው አዘጋጆች በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት፤ የዝግጅቱ ዋና ዓላማ ኤግዚቢሽን ከማሳየት ባለፈ ቤተሰቦች፣ ሥራ ፈጣሪዎች፣ ሊቃውንትና ወጣቶች በአንድነትና በአነሳሽነት የሚሰባሰቡበት ብሔራዊ መድረክ መፍጠር ነው።
ኢትዮጵያ ያላትን የበለፀገ ባህልና የሰላማዊ አብሮ መኖር እሴት ማጠናከር እንዲሁም ለሀገር ውስጥ የንግድ ተቋማትና ለወጣት ባለተሰጥኦዎች ዕድል መፍጠር የኤክስፖው ዋነኛ ግብ መሆኑ ተጠቅሷል።
የአዛን ውድድር እና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
የዘንድሮውን ኤክስፖ ልዩ የሚያደርጉ ሁለት ዋና ዋና ተነሳሽነቶች ይፋ ተደርገዋል፦
የመጀመርያው ሙአዚን ቢላል ኢብኑ ረባህ (ረ.ዐ) ያስጀመረውን የእኩልነትና የአንድነት ጥሪ ለማዘከርና ወጣቶች ከመንፈሳዊ ውበቱ ጋር እንዲገናኙ ለማድረግ የታለመ ውድድር መዘጋጀቱ ተገልጿል።
ኤክስፖው ማህበረሰባዊ አገልግሎትን ታሳቢ በማድረግ ከሚናሬት ኢንጂነሪንግና ከሌሎች አጋሮች ጋር በመተባበር፣ ከቲኬት ሽያጭ በሚገኝ ገቢና በሪል እስቴት ልገሳ ለችግረኞች ቤት የመገንባት የበጎ አድራጎት ዕቅድ ይፋ ሆኗል።
የአጋሮችና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ለዝግጅቱ መሳካት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ሂጅራ ባንክ፣ ሚናሬት ኢንጂነሪንግና ሌሎች ስፖንሰሮች ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጋቸው በመክፈቻው ላይ ተጠቅሷል።
በመጨረሻም "ንግዶች የሚገናኙበትና ባህል የሚከበርበት ይሁን" በሚል ምርቃት ኤክስፖው በይፋ የተከፈተ ሲሆን፤ ነዋሪዎችና ጎብኝዎች በኤክስፖው ላይ በመገኘት የባህልና የንግድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።
ይህ የኢድ ኤክስፖ እስከ ዋዜማው ድረስ እንደሚቆይም ነው የተገለፀው።
#ኹነት
#fastmereja I እምነትን፣ ባህልንና ንግድን በአንድ መድረክ የሚያገናኘው "3ኛው ታላቁ የኢትዮ ኢድ ኤክስፖ" በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ጊዮን ሆቴል በይፋ ተከፈተ። በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ምሁራንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ባህልንና አንድነትን የሚያጠናክር መድረክ
የኤክስፖው አዘጋጆች በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት፤ የዝግጅቱ ዋና ዓላማ ኤግዚቢሽን ከማሳየት ባለፈ ቤተሰቦች፣ ሥራ ፈጣሪዎች፣ ሊቃውንትና ወጣቶች በአንድነትና በአነሳሽነት የሚሰባሰቡበት ብሔራዊ መድረክ መፍጠር ነው።
ኢትዮጵያ ያላትን የበለፀገ ባህልና የሰላማዊ አብሮ መኖር እሴት ማጠናከር እንዲሁም ለሀገር ውስጥ የንግድ ተቋማትና ለወጣት ባለተሰጥኦዎች ዕድል መፍጠር የኤክስፖው ዋነኛ ግብ መሆኑ ተጠቅሷል።
የአዛን ውድድር እና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
የዘንድሮውን ኤክስፖ ልዩ የሚያደርጉ ሁለት ዋና ዋና ተነሳሽነቶች ይፋ ተደርገዋል፦
የመጀመርያው ሙአዚን ቢላል ኢብኑ ረባህ (ረ.ዐ) ያስጀመረውን የእኩልነትና የአንድነት ጥሪ ለማዘከርና ወጣቶች ከመንፈሳዊ ውበቱ ጋር እንዲገናኙ ለማድረግ የታለመ ውድድር መዘጋጀቱ ተገልጿል።
ኤክስፖው ማህበረሰባዊ አገልግሎትን ታሳቢ በማድረግ ከሚናሬት ኢንጂነሪንግና ከሌሎች አጋሮች ጋር በመተባበር፣ ከቲኬት ሽያጭ በሚገኝ ገቢና በሪል እስቴት ልገሳ ለችግረኞች ቤት የመገንባት የበጎ አድራጎት ዕቅድ ይፋ ሆኗል።
የአጋሮችና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ለዝግጅቱ መሳካት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ሂጅራ ባንክ፣ ሚናሬት ኢንጂነሪንግና ሌሎች ስፖንሰሮች ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጋቸው በመክፈቻው ላይ ተጠቅሷል።
በመጨረሻም "ንግዶች የሚገናኙበትና ባህል የሚከበርበት ይሁን" በሚል ምርቃት ኤክስፖው በይፋ የተከፈተ ሲሆን፤ ነዋሪዎችና ጎብኝዎች በኤክስፖው ላይ በመገኘት የባህልና የንግድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።
ይህ የኢድ ኤክስፖ እስከ ዋዜማው ድረስ እንደሚቆይም ነው የተገለፀው።
#ኹነት
5 months ago
ሀገር አቀፍ የስፔሻል ኦሊምፒክ ውድድር ሊካሄድ ነው
#fastmereja | 11ኛው የዓለም የዳውን ሲንድሮም ቀን በኢትዮጵያ “ብቸኝነትን በአንድነት እንመክት” በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት 4 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚከበር ተገለጸ።
ስፔሻል ኦሊምፒክስ ኢትዮጵያ ከ“ፍቅር የኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማኅበር” ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ይህ ሀገር አቀፍ ጨዋታ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ለሦስት ቀናት ይካሄዳል።
ዝግጅቱ ሁሉንም የኦሊምፒክ ስፖርት ዓይነቶች የሚያካትት ሲሆን፣ ውድድሩም የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ተወዳዳሪዎች ባማከለ ልዩ የስፖርት ሕግ መሠረት የሚከናወን ይሆናል።
የኢትዮጵያ ስፔሻል ኦሊምፒክ ኮሚቴ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ዕውቅና አግኝቶ ከተደራጀበት ጊዜ ጀምሮ፣ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ዜጎች በስፖርት ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሀገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር እየሠራ ይገኛል።
የፍቅር ኢትዮጵያ ማህበር የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች አስተምሮና አሰልጥኖ በማኅበሩ ውስጥ የሥራ ቅጥር እንዲያገኙ በማድረግ ጭምር አርአያነት ያለው ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት በአፍሪካና በኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ወገኖች ላይ የሚደርሰው መገለልና መድልዎ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እንዲህ ያሉ ስፖርታዊ መድረኮች ግንዛቤን ለመፍጠርና ብቸኝነትን ለመቀነስ ትልቅ ፋይዳ አላቸው።
#ኹነት
#fastmereja | 11ኛው የዓለም የዳውን ሲንድሮም ቀን በኢትዮጵያ “ብቸኝነትን በአንድነት እንመክት” በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት 4 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚከበር ተገለጸ።
ስፔሻል ኦሊምፒክስ ኢትዮጵያ ከ“ፍቅር የኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማኅበር” ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ይህ ሀገር አቀፍ ጨዋታ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ለሦስት ቀናት ይካሄዳል።
ዝግጅቱ ሁሉንም የኦሊምፒክ ስፖርት ዓይነቶች የሚያካትት ሲሆን፣ ውድድሩም የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ተወዳዳሪዎች ባማከለ ልዩ የስፖርት ሕግ መሠረት የሚከናወን ይሆናል።
የኢትዮጵያ ስፔሻል ኦሊምፒክ ኮሚቴ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ዕውቅና አግኝቶ ከተደራጀበት ጊዜ ጀምሮ፣ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ዜጎች በስፖርት ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሀገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር እየሠራ ይገኛል።
የፍቅር ኢትዮጵያ ማህበር የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች አስተምሮና አሰልጥኖ በማኅበሩ ውስጥ የሥራ ቅጥር እንዲያገኙ በማድረግ ጭምር አርአያነት ያለው ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት በአፍሪካና በኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ወገኖች ላይ የሚደርሰው መገለልና መድልዎ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እንዲህ ያሉ ስፖርታዊ መድረኮች ግንዛቤን ለመፍጠርና ብቸኝነትን ለመቀነስ ትልቅ ፋይዳ አላቸው።
#ኹነት
5 months ago
5ኛው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት በአዲስ አበባ በይፋ ተከፈተ!
#fastmereja I “ራስን መቻል ለዘላቂ ሰላምና ለአካታች ልማት” በሚል መሪ ቃል፣ 5ኛው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ዛሬ በየካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር በይፋ ተከፍቷል።
ከ120 በላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስራዎቻቸውን ለህዝብ በኤግዚቢሽን የሚያቀርቡበት ሲሆን፣ እስከ 20 ሺህ የሚደርሱ ጎብኚዎች እንደሚገኙ ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይቆያል።
በቆይታው በስምንት አበይት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ። ከነዚህም መካከል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና በጠቅላላ ምርጫ፣ በሰላም ግንባታ፣ በስርዓተ ጾታ እና በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ውይይቶች ይገኙበታል።
በመድረኩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት፣ የልማት አጋሮች እና የሚዲያ አካላት ተገኝተዋል።
ይህ መድረክ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እርስ በርስ እንዲተዋወቁና ከህዝብ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያጠናክሩ ትልቅ እድል እንደሚፈጥር ታምኖበታል።
#ኹነት
#fastmereja I “ራስን መቻል ለዘላቂ ሰላምና ለአካታች ልማት” በሚል መሪ ቃል፣ 5ኛው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ዛሬ በየካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር በይፋ ተከፍቷል።
ከ120 በላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስራዎቻቸውን ለህዝብ በኤግዚቢሽን የሚያቀርቡበት ሲሆን፣ እስከ 20 ሺህ የሚደርሱ ጎብኚዎች እንደሚገኙ ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይቆያል።
በቆይታው በስምንት አበይት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ። ከነዚህም መካከል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና በጠቅላላ ምርጫ፣ በሰላም ግንባታ፣ በስርዓተ ጾታ እና በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ውይይቶች ይገኙበታል።
በመድረኩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት፣ የልማት አጋሮች እና የሚዲያ አካላት ተገኝተዋል።
ይህ መድረክ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እርስ በርስ እንዲተዋወቁና ከህዝብ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያጠናክሩ ትልቅ እድል እንደሚፈጥር ታምኖበታል።
#ኹነት
5 months ago
የ"ሮቦቲክስ ለበጎ ዓላማ" የወጣቶች ውድድር በኢትዮጵያ ሊካሄድ ነው።
📌 አሸናፊዎች ስዊዘርላንድ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ውድድር ይሳተፋሉ!
#fastmereja I ዕድሜያቸው ከ10 እስከ 18 ለሆኑ ወጣቶች የተዘጋጀውና በዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ህብረት (ITU) የሚመራው "ሮቦቲክስ ለበጎ ዓላማ" የወጣቶች ሀገራዊ ውድድር በይፋ መጀመሩ ተበሰረ።
በዘንድሮው ዓመት ተወዳዳሪዎች በምግብ ዋስትና እና በግብርና ላይ ለሚታዩ ችግሮች መፍትሔ የሚሆኑ ሮቦቶችን ይሠራሉ።
ውድድሩ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
በጁኒየር እና ሲኒየር ምድብ አሸናፊ የሚሆኑ ሁለት ቡድኖች በጄኔቫ፣ ስዊዘርላንድ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ውድድር ላይ እንዲሳተፉ ሙሉ ወጪያቸው የተሸፈነ ጉዞ ይበረከትላቸዋል።
ውድድሩ ወጣቶች በሳይንስና ቴክኖሎጂ (STEM) የታገዘ የችግር አፈታት ክህሎት እንዲያዳብሩና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ መድረክ እንዲወክሉ ለማስቻል የታለመ ነው።
የውድድሩ አዘጋጅ የኤግዚት ሲስተምስ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሰጡት መግለጫ፣ ይህ ፕሮግራም ኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ መፍትሔ ፈጣሪ ለማድረግ የሚደረግ ሀገራዊ ንቅናቄ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ብቻ ሳትሆን የመፍትሔ ፈጣሪ እንድትሆን እናስቀምጣት የተባለ ሲሆን በጋራ በመሆን 'ሮቦቲክስ ለበጎ ዓላማ' (Robotics for Good)ን ውድድር ብቻ ሳይሆን፣
ሀገራዊ ንቅናቄ እናደርገዋለን ብሏል።
#ኹነት
📌 አሸናፊዎች ስዊዘርላንድ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ውድድር ይሳተፋሉ!
#fastmereja I ዕድሜያቸው ከ10 እስከ 18 ለሆኑ ወጣቶች የተዘጋጀውና በዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ህብረት (ITU) የሚመራው "ሮቦቲክስ ለበጎ ዓላማ" የወጣቶች ሀገራዊ ውድድር በይፋ መጀመሩ ተበሰረ።
በዘንድሮው ዓመት ተወዳዳሪዎች በምግብ ዋስትና እና በግብርና ላይ ለሚታዩ ችግሮች መፍትሔ የሚሆኑ ሮቦቶችን ይሠራሉ።
ውድድሩ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
በጁኒየር እና ሲኒየር ምድብ አሸናፊ የሚሆኑ ሁለት ቡድኖች በጄኔቫ፣ ስዊዘርላንድ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ውድድር ላይ እንዲሳተፉ ሙሉ ወጪያቸው የተሸፈነ ጉዞ ይበረከትላቸዋል።
ውድድሩ ወጣቶች በሳይንስና ቴክኖሎጂ (STEM) የታገዘ የችግር አፈታት ክህሎት እንዲያዳብሩና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ መድረክ እንዲወክሉ ለማስቻል የታለመ ነው።
የውድድሩ አዘጋጅ የኤግዚት ሲስተምስ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሰጡት መግለጫ፣ ይህ ፕሮግራም ኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ መፍትሔ ፈጣሪ ለማድረግ የሚደረግ ሀገራዊ ንቅናቄ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ብቻ ሳትሆን የመፍትሔ ፈጣሪ እንድትሆን እናስቀምጣት የተባለ ሲሆን በጋራ በመሆን 'ሮቦቲክስ ለበጎ ዓላማ' (Robotics for Good)ን ውድድር ብቻ ሳይሆን፣
ሀገራዊ ንቅናቄ እናደርገዋለን ብሏል።
#ኹነት
Sponsored by
Surafel
5 months ago
2ኛው የኢትዮጵያ የቡና ባህል ፌስቲቫል በአድዋ ድል መታሰቢያ ተካሄደ!
#fastmereja I ዋርካ ኮፊ ኃ/የተ/የግ/ማህበር "የቡና ባህላችን ለሀገራዊ አንድነታችንና ለኢኮኖሚ እድገታችን" በሚል መሪ ቃል 2ኛውን የኢትዮጵያ የቡና ባህል ቀን ፌስቲቫል በዛሬዉ እለት በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በድምቀት አክብሯል።
ይህ ፌስቲቫል ዝም ብሎ የቡና መጠጫ ፕሮግራም ብቻ ሳይሆን የሀገር ኩራት የሆነውን የቡና ባህላችንን በዓለም አቀፉ የቅርስ ተቋም (UNESCO) እንዲመዘገብ የሚደረግበት ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ መሆኑን የዋርካ ኮፊ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሰአዳ ሙስጠፋ ገልፀዋል።
በዛሬዉ መርሀ-ግብር የአስራ አንዱም ክልሎች ውብ የቡና ባህል አልባሳት እና የቁሳቁስ አውደ-ርዕይ፣በእናቶቻችን እጅ የሚፈሉ ጣፋጭ ቡናዎችና የባህል የቡና ቁርሶች፣የስዕል ኤግዚቢሽን፣ የእደ ጥበብ ስራዎች ባዛርና ልዩ ልዩ ጌሞች እንዲሁም ሌሎች መርሀ-ግብሮች ተከናዉነዋል።
በፌስቲቫሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የክልል ተወካዮች፣ዲፕሎማቶች፣በአዲስ አበባ የሚገኙ የኤምባሲ አምባሳደሮች፣የቅርስ ጥበቃ ባለሙያዎች እንዲሁም የቡና ላኪዎችና ተመራማሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተገኝተዋል።
#ኹነት
#fastmereja I ዋርካ ኮፊ ኃ/የተ/የግ/ማህበር "የቡና ባህላችን ለሀገራዊ አንድነታችንና ለኢኮኖሚ እድገታችን" በሚል መሪ ቃል 2ኛውን የኢትዮጵያ የቡና ባህል ቀን ፌስቲቫል በዛሬዉ እለት በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በድምቀት አክብሯል።
ይህ ፌስቲቫል ዝም ብሎ የቡና መጠጫ ፕሮግራም ብቻ ሳይሆን የሀገር ኩራት የሆነውን የቡና ባህላችንን በዓለም አቀፉ የቅርስ ተቋም (UNESCO) እንዲመዘገብ የሚደረግበት ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ መሆኑን የዋርካ ኮፊ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሰአዳ ሙስጠፋ ገልፀዋል።
በዛሬዉ መርሀ-ግብር የአስራ አንዱም ክልሎች ውብ የቡና ባህል አልባሳት እና የቁሳቁስ አውደ-ርዕይ፣በእናቶቻችን እጅ የሚፈሉ ጣፋጭ ቡናዎችና የባህል የቡና ቁርሶች፣የስዕል ኤግዚቢሽን፣ የእደ ጥበብ ስራዎች ባዛርና ልዩ ልዩ ጌሞች እንዲሁም ሌሎች መርሀ-ግብሮች ተከናዉነዋል።
በፌስቲቫሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የክልል ተወካዮች፣ዲፕሎማቶች፣በአዲስ አበባ የሚገኙ የኤምባሲ አምባሳደሮች፣የቅርስ ጥበቃ ባለሙያዎች እንዲሁም የቡና ላኪዎችና ተመራማሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተገኝተዋል።
#ኹነት
6 months ago
‹ተወዳጅ ሚድያ› 22ኛ ዓመቱን ሌሎችን በማመስገን እያከበረ ይገኛል!
በታሪክ ስነዳ፣ በመጽሐፎችና በኹነት ዝግጅት በጋዜጣ ሥራና በሌሎችም የሚታወቀው ‹ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን › 22ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን፣ በየወቅቱ ዐብረው የነበሩ ባለሙያዎችንና ተቋማትን በማመስገን ሊያሳልፍ ነው።
‹ማክበር መሠልጠን ነው› በሚል መሪ አርእስት ከፊት፣ ከጐንና ከጀርባ የነበሩትን የሥራውን ዋና አንቀሳቃሾች ማመስገን ግድና ተገቢ ነው›› ሲል የድርጅቱ መሥራች ጋዜጠኛ ዕዝራ እጅጉ ተናግሯል።
ሰው ሕልም ቢኖረውም፣ እግዚአብሔር ግን ትክክለኛ ዐቅም ያላቸውን ሰዎች ለባለሕልመኛ እንደሚሰጠው የሚያምነው ዕዝራ እጅጉ፣ በእነዚህ ሰዎች ምክንያት ‹ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን › ለዚህ ደረጃ መብቃቱን ይናገራል። ‹ተወዳጅ ሚድያ›፣ በተለይ ባለፉት 9 ዓመታት፣ ለ25 ሰዎች ወቅታዊ የሥራ ዕድሎች የፈጠረ ሲኾን፣ ብዙዎችም ዐቅማቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲጠቀሙና እንዲያውቁ አድርጓል።
የካቲት 2፣ 1996 ዓ.ም በይፋ ሕጋዊ ሰውነቱን አግኝቶ ሥራውን የጀመረው ‹ተወዳጅ ሚድያ›፣ ‹‹ተወዳጅ›› የተሠኘ በነፃ የሚሠራጭ የማስታወቂያ ጋዜጣ በማሳተም ወደ ሚድያው ሥራ ዘልቋል፡፡ ‹‹በጊዜው ሥራው ሲጀምር፣ በየሱቁ እየዞሩ የማስታወቂያ ደንበኞች መፈለጉ ፈታኝ ነበር›› የምትለው የ‹ተወዳጅ› የመጀመሪያዋ ደሞዝ ተከፋይ የሽያጭ ባለሙያ ቅድስት ደበበ ናት። ቅድስት በጊዜው በ500 ብር ደሞዝ ሥራ መጀመሯን የምትናገር ሲኾን፣ ‹‹ከ22 ዓመታት በኋላ ‹ተወዳጅ› ሚድያ ዐዲስ ዐሳብ፣ ብቃትና ዐቅም ያላቸውን ባለሙያዎች አፍርቶ በማየቴ ርካታ ይሰማኛል›› ብላለች።
በአኹኑ ሰዓት ‹ተወዳጅ› ሚድያ ታሪክ በመሰነድ ሥራ ላይ ትኵረት ሰጥቶ ከ23 በላይ መጻሕፍትን ለአንባቢ ማቅረብ ችሏል። በዚህ ብቻ ሳይወሰን፣ 45 ታሪኮችን በሲዲና በዲቪዲ ያቀረበ ሲኾን፣ ልዩ-ልዩ ኹነቶችንም በማዘጋጀት አሻራ ማኖር ችሏል።
‹ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን›፣ በተለይ የሰዎች የሕይወት ታሪክ ከጉግል ላይ በቀላሉ ተፈልጎ እንዲገኝ ሲያደርግ፣ ለዚህ ጥረቱም ዳላስ ከሚገኘው ‹የአርኣያ ሰው› ሽልማት ለማግኘት በቅቷል። እንደ ‹ቻት ጂፒቲ› ያሉ ዘመኑ የወለዳቸው የመረጃ ምንጮችም የ‹ተወዳጅ› ሚድያን ታሪኮች እንደ ተአማኒ የመረጃ ምንጭ አድርገው ይወስዷቸዋል።
‹ተወዳጅ› ሚድያ ለባለሙያ ዕድል በመስጠት የሚያምን ድርጅት መኾኑን መሥራቹ ዕዝራ ያስረዳል፣ ‹‹ልዩ-ልዩ ተቋማትና ግለሰቦች የሚያግዙት፣ ትብብር ለማሳየት ኹሌም ዐብረውት የሚኾኑ ተቋም ነው›› ሲልም ሀሣቡን ገልጿል።
በተለይ ተወዳጅ ከ2009 ዓ.ም ወዲህ ባለፉት 9 ዓመታት ትኵረቱን ሙሉ በሙሉ ታሪክ ላይ በማድረግ ዐዲስ አካኼድና ስልት በመንደፍ የበኩሉን የአገር አሻራ እያኖረ የሚገኝ ድርጅት ነው።
‹ተወዳጅ›፣ ኅትመቶችን ወደ ድምፅ በመቀየር ‹‹የኤርትራ ጕዳይ››ን (አምባሳደር ዘውዴ) የመሰሉ ከ30 በላይ መጽሐፎችንም በትረካ መልክ በማቅረብ በቀላሉ ሰዎች ሥራ እየሠሩና መንገድ ላይ እየኼዱ ማዳመጥ የሚችሉበትን ስልት ነድፏል።
ሚድያው የኢንሳይክሎፒዲያ ፕሮጀክት በመቅረፅ ከሚያዝያ 13፣ 2013 ዓ.ም ጀምሮ ‹‹መዝገበ አእምሮ›› የተሠኘውን መጽሐፍ በ2 ቅጽ ያሳተመ ሲኾን፣ በአጠቃላይ የ400 የሚድያና የጥበብ ሰዎችን ታሪክ ይዘዋል፡፡
የአባት የእናቶቻቸው ታሪክ እንዲጻፍ የሚፈልጉ በአገር ውስጥና በባሕር ማዶ የሚገኙ ደንበኞችም ‹ተወዳጅ›ን መርጠው የቤተሰቦቻቸው ታሪክ እንዲሰነድ ያደረጉ ሲኾን፣ እስከ ዛሬም 23 መጽሐፎች ለኅትመት በቅተዋል።መፅሀፍ ከመፃፍ ባሻገርም ደረጃውን የጠበቀ የአርትኦት ተግባር እያከናወነ ይገኛል።
አንድ የቈየ ምስል፣ ሰነድ ወይም ታሪክ አመላካች ወረቀት የቤት ሥርቻ ስር ከሚቀመጥ፣ በ‹ተወዳጅ› ዲጂታይዝ እየተደረገ ሲኾን፣ እስከ ዛሬም ከ10,000 በላይ ፋይሎች በቀላሉ ለትውልድ ተደራሽ እንዲኾኑ ተደርጓል።
‹‹ማክበር መሠልጠን ነው›› በሚል መሪ ዐሳብ ‹ተወዳጅ› ሚድያ እዚህ ለመድረሱ ምስጋና የሚቸራቸው ከ140 በላይ የሚኾኑ ባለሙያዎች፣ ግለሰቦችና ተቋማት በtewedajewikipedia.com ድረ ገጽ በtewedajemedia የፌስ ቡክ ገጽ ላይ ስማቸው በዝርዝር የተቀመጠ ሲኾን፣ የ22ኛ ዓመት ክብረ በዓሉም ያለምንም ድግስ በማኅበራዊ ድረ ገጾችና በተመረጡ ሬድዮ ጣቢያዎች መረጃዎችን መጥኖና ከፍ አድርጎ በማስተላለፍ እንደሚከበር ታውቋል።
የተመሰገኑ ሰዎችንና ተቋማትን ብሎም 22 የተወዳጅ ሚድያ እውነታዎችን ለማግኘት ሊንኩን ከፍተው ይመልከቱ።https://tewedajewikipedia....
በታሪክ ስነዳ፣ በመጽሐፎችና በኹነት ዝግጅት በጋዜጣ ሥራና በሌሎችም የሚታወቀው ‹ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን › 22ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን፣ በየወቅቱ ዐብረው የነበሩ ባለሙያዎችንና ተቋማትን በማመስገን ሊያሳልፍ ነው።
‹ማክበር መሠልጠን ነው› በሚል መሪ አርእስት ከፊት፣ ከጐንና ከጀርባ የነበሩትን የሥራውን ዋና አንቀሳቃሾች ማመስገን ግድና ተገቢ ነው›› ሲል የድርጅቱ መሥራች ጋዜጠኛ ዕዝራ እጅጉ ተናግሯል።
ሰው ሕልም ቢኖረውም፣ እግዚአብሔር ግን ትክክለኛ ዐቅም ያላቸውን ሰዎች ለባለሕልመኛ እንደሚሰጠው የሚያምነው ዕዝራ እጅጉ፣ በእነዚህ ሰዎች ምክንያት ‹ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን › ለዚህ ደረጃ መብቃቱን ይናገራል። ‹ተወዳጅ ሚድያ›፣ በተለይ ባለፉት 9 ዓመታት፣ ለ25 ሰዎች ወቅታዊ የሥራ ዕድሎች የፈጠረ ሲኾን፣ ብዙዎችም ዐቅማቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲጠቀሙና እንዲያውቁ አድርጓል።
የካቲት 2፣ 1996 ዓ.ም በይፋ ሕጋዊ ሰውነቱን አግኝቶ ሥራውን የጀመረው ‹ተወዳጅ ሚድያ›፣ ‹‹ተወዳጅ›› የተሠኘ በነፃ የሚሠራጭ የማስታወቂያ ጋዜጣ በማሳተም ወደ ሚድያው ሥራ ዘልቋል፡፡ ‹‹በጊዜው ሥራው ሲጀምር፣ በየሱቁ እየዞሩ የማስታወቂያ ደንበኞች መፈለጉ ፈታኝ ነበር›› የምትለው የ‹ተወዳጅ› የመጀመሪያዋ ደሞዝ ተከፋይ የሽያጭ ባለሙያ ቅድስት ደበበ ናት። ቅድስት በጊዜው በ500 ብር ደሞዝ ሥራ መጀመሯን የምትናገር ሲኾን፣ ‹‹ከ22 ዓመታት በኋላ ‹ተወዳጅ› ሚድያ ዐዲስ ዐሳብ፣ ብቃትና ዐቅም ያላቸውን ባለሙያዎች አፍርቶ በማየቴ ርካታ ይሰማኛል›› ብላለች።
በአኹኑ ሰዓት ‹ተወዳጅ› ሚድያ ታሪክ በመሰነድ ሥራ ላይ ትኵረት ሰጥቶ ከ23 በላይ መጻሕፍትን ለአንባቢ ማቅረብ ችሏል። በዚህ ብቻ ሳይወሰን፣ 45 ታሪኮችን በሲዲና በዲቪዲ ያቀረበ ሲኾን፣ ልዩ-ልዩ ኹነቶችንም በማዘጋጀት አሻራ ማኖር ችሏል።
‹ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን›፣ በተለይ የሰዎች የሕይወት ታሪክ ከጉግል ላይ በቀላሉ ተፈልጎ እንዲገኝ ሲያደርግ፣ ለዚህ ጥረቱም ዳላስ ከሚገኘው ‹የአርኣያ ሰው› ሽልማት ለማግኘት በቅቷል። እንደ ‹ቻት ጂፒቲ› ያሉ ዘመኑ የወለዳቸው የመረጃ ምንጮችም የ‹ተወዳጅ› ሚድያን ታሪኮች እንደ ተአማኒ የመረጃ ምንጭ አድርገው ይወስዷቸዋል።
‹ተወዳጅ› ሚድያ ለባለሙያ ዕድል በመስጠት የሚያምን ድርጅት መኾኑን መሥራቹ ዕዝራ ያስረዳል፣ ‹‹ልዩ-ልዩ ተቋማትና ግለሰቦች የሚያግዙት፣ ትብብር ለማሳየት ኹሌም ዐብረውት የሚኾኑ ተቋም ነው›› ሲልም ሀሣቡን ገልጿል።
በተለይ ተወዳጅ ከ2009 ዓ.ም ወዲህ ባለፉት 9 ዓመታት ትኵረቱን ሙሉ በሙሉ ታሪክ ላይ በማድረግ ዐዲስ አካኼድና ስልት በመንደፍ የበኩሉን የአገር አሻራ እያኖረ የሚገኝ ድርጅት ነው።
‹ተወዳጅ›፣ ኅትመቶችን ወደ ድምፅ በመቀየር ‹‹የኤርትራ ጕዳይ››ን (አምባሳደር ዘውዴ) የመሰሉ ከ30 በላይ መጽሐፎችንም በትረካ መልክ በማቅረብ በቀላሉ ሰዎች ሥራ እየሠሩና መንገድ ላይ እየኼዱ ማዳመጥ የሚችሉበትን ስልት ነድፏል።
ሚድያው የኢንሳይክሎፒዲያ ፕሮጀክት በመቅረፅ ከሚያዝያ 13፣ 2013 ዓ.ም ጀምሮ ‹‹መዝገበ አእምሮ›› የተሠኘውን መጽሐፍ በ2 ቅጽ ያሳተመ ሲኾን፣ በአጠቃላይ የ400 የሚድያና የጥበብ ሰዎችን ታሪክ ይዘዋል፡፡
የአባት የእናቶቻቸው ታሪክ እንዲጻፍ የሚፈልጉ በአገር ውስጥና በባሕር ማዶ የሚገኙ ደንበኞችም ‹ተወዳጅ›ን መርጠው የቤተሰቦቻቸው ታሪክ እንዲሰነድ ያደረጉ ሲኾን፣ እስከ ዛሬም 23 መጽሐፎች ለኅትመት በቅተዋል።መፅሀፍ ከመፃፍ ባሻገርም ደረጃውን የጠበቀ የአርትኦት ተግባር እያከናወነ ይገኛል።
አንድ የቈየ ምስል፣ ሰነድ ወይም ታሪክ አመላካች ወረቀት የቤት ሥርቻ ስር ከሚቀመጥ፣ በ‹ተወዳጅ› ዲጂታይዝ እየተደረገ ሲኾን፣ እስከ ዛሬም ከ10,000 በላይ ፋይሎች በቀላሉ ለትውልድ ተደራሽ እንዲኾኑ ተደርጓል።
‹‹ማክበር መሠልጠን ነው›› በሚል መሪ ዐሳብ ‹ተወዳጅ› ሚድያ እዚህ ለመድረሱ ምስጋና የሚቸራቸው ከ140 በላይ የሚኾኑ ባለሙያዎች፣ ግለሰቦችና ተቋማት በtewedajewikipedia.com ድረ ገጽ በtewedajemedia የፌስ ቡክ ገጽ ላይ ስማቸው በዝርዝር የተቀመጠ ሲኾን፣ የ22ኛ ዓመት ክብረ በዓሉም ያለምንም ድግስ በማኅበራዊ ድረ ገጾችና በተመረጡ ሬድዮ ጣቢያዎች መረጃዎችን መጥኖና ከፍ አድርጎ በማስተላለፍ እንደሚከበር ታውቋል።
የተመሰገኑ ሰዎችንና ተቋማትን ብሎም 22 የተወዳጅ ሚድያ እውነታዎችን ለማግኘት ሊንኩን ከፍተው ይመልከቱ።https://tewedajewikipedia....
7 months ago
በሚሊዮኖች የሚጠበቀው መንፈሳዊ ኹነት
#fastmereja : ዛሬ በመዲናዋ እምብርት በሚገኘው ታሪካዊው የመስቀል አደባባይ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን በጉጉት ሲጠብቁት የነበረው "የአእላፋት ዝማሬ" በታላቅ ድምቀት ይካሄዳል። ይህ መርሐ-ግብር ከዝማሬው ባለፈ የቤተክርስቲያኒቱን አንድነትና መንፈሳዊ ጥንካሬ ለዓለም የሚያሳይ አጋጣሚ እንደሚሆን ይጠበቃል።
በሺዎች የሚቆጠሩ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን በአንድ ዓይነት ልብስና ድምፅ በመታጀብ፣ ጥንታዊና ዘመናዊ ያሬዳዊ መዝሙራትን ያቀርባሉ።
ከሁሉም የአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት የተሰባሰቡ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን አደባባዩን በነጭ ልብስ እንደሚያስውቡት ይጠበቃል።
ዝግጅቱ በተለያዩ በበርካታ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችና በማኅበራዊ ሚዲያዎች ለዓለም አቀፍ ምዕመናን በቀጥታ ይተላለፋል።
#fastmereja : ዛሬ በመዲናዋ እምብርት በሚገኘው ታሪካዊው የመስቀል አደባባይ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን በጉጉት ሲጠብቁት የነበረው "የአእላፋት ዝማሬ" በታላቅ ድምቀት ይካሄዳል። ይህ መርሐ-ግብር ከዝማሬው ባለፈ የቤተክርስቲያኒቱን አንድነትና መንፈሳዊ ጥንካሬ ለዓለም የሚያሳይ አጋጣሚ እንደሚሆን ይጠበቃል።
በሺዎች የሚቆጠሩ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን በአንድ ዓይነት ልብስና ድምፅ በመታጀብ፣ ጥንታዊና ዘመናዊ ያሬዳዊ መዝሙራትን ያቀርባሉ።
ከሁሉም የአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት የተሰባሰቡ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን አደባባዩን በነጭ ልብስ እንደሚያስውቡት ይጠበቃል።
ዝግጅቱ በተለያዩ በበርካታ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችና በማኅበራዊ ሚዲያዎች ለዓለም አቀፍ ምዕመናን በቀጥታ ይተላለፋል።
7 months ago
አንጋፋ አርቲስቶች እና ጋዜጠኞች የሚሳተፉበት ልዩ የገና ጨዋታ ሊካሄድ ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር፤ የዘንድሮን የገና በዓል አስመልክቶ ልዩ የገና ጨዋታ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።
ይህ ልዩ የበዓል መዳረሻ ኹነት፤ የፊታችን እሁድ ታኅሣሥ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በድምቀት ይከናወናል።
በዝግጅቱ ላይ የሁለቱ ተቋማት የሥራ አመራሮች፣ እውቅናን ያተረፉ አንጋፋ አርቲስቶች እና ጋዜጠኞች በጨዋታው ላይ በይፋ እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
የገና ጨዋታ ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ጋር ቀጥተኛ ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ቁርኝት ያለው ነው። ክርስቶስ በተወለደ ጊዜ ዜናውን የሰሙ እረኞች በደስታ ብዛት፣ በእጃቸው በያዙት በትር (ዱላ) እና ሩር እንደተጫወቱ የሃይማኖት ሊቃውንት ያስረዳሉ።
ይህ መርሐ ግብርም ታኅሣሥ 29 ለሚከበረው በዓል እንደ መዳረሻ እና ይህንን ቱባ ባህል ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
#ethiopia | የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር፤ የዘንድሮን የገና በዓል አስመልክቶ ልዩ የገና ጨዋታ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።
ይህ ልዩ የበዓል መዳረሻ ኹነት፤ የፊታችን እሁድ ታኅሣሥ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በድምቀት ይከናወናል።
በዝግጅቱ ላይ የሁለቱ ተቋማት የሥራ አመራሮች፣ እውቅናን ያተረፉ አንጋፋ አርቲስቶች እና ጋዜጠኞች በጨዋታው ላይ በይፋ እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
የገና ጨዋታ ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ጋር ቀጥተኛ ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ቁርኝት ያለው ነው። ክርስቶስ በተወለደ ጊዜ ዜናውን የሰሙ እረኞች በደስታ ብዛት፣ በእጃቸው በያዙት በትር (ዱላ) እና ሩር እንደተጫወቱ የሃይማኖት ሊቃውንት ያስረዳሉ።
ይህ መርሐ ግብርም ታኅሣሥ 29 ለሚከበረው በዓል እንደ መዳረሻ እና ይህንን ቱባ ባህል ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
Comments