የ1 ሚሊዮን ብር ሽልማት የሚያስገኘው የቤላ ስፖርት የክረምት የፉትሳል ውድድር ቅዳሜ ይጀመራል
#fastmereja I የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከቤላ ስፖርት ትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁትና አሸናፊውን ቡድን የ1 ሚሊዮን ብር ባለቤት የሚያደርገው 2ኛው ዙር የቤላ ስፖርት የክረምት የፉትሳል ውድድር በሚመጣው ቅዳሜ በይፋ እንደሚጀመር በጋዜጣዊ መግለጫ ተገለጸ።
ከሐምሌ 11 እስከ ነሐሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በጨፌ ሜዳ ለአንድ ወር በሚቆየው በዚህ ውድድር ላይ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ፣ በከፍተኛ ሊግ እና በሱፐር ሊግ የሚሳተፉ ተጨዋቾች ይሳተፋሉ።
ሁለቱ አካላት ውድድሩን በጋራ ለማዘጋጀት የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን፣ ዝግጅቱ ክለቦች አዲሱ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት አቋማቸውን ለመለካት ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርላቸው ታውቋል። ውድድሩን አሸናፊ ለሚሆን ቡድን ከተዘጋጀው 1 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሽልማት በተጨማሪ፣ ለውድድሩ ኮከብ ተጫዋች፣ ኮከብ ግብ አግቢ እና ኮከብ በረኛ እያንዳንዳቸው የ20 ሺህ ብር የክብር ሽልማት እንደሚሰጣቸው ተገልጿል። #ኹነት
#fastmereja I የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከቤላ ስፖርት ትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁትና አሸናፊውን ቡድን የ1 ሚሊዮን ብር ባለቤት የሚያደርገው 2ኛው ዙር የቤላ ስፖርት የክረምት የፉትሳል ውድድር በሚመጣው ቅዳሜ በይፋ እንደሚጀመር በጋዜጣዊ መግለጫ ተገለጸ።
ከሐምሌ 11 እስከ ነሐሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በጨፌ ሜዳ ለአንድ ወር በሚቆየው በዚህ ውድድር ላይ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ፣ በከፍተኛ ሊግ እና በሱፐር ሊግ የሚሳተፉ ተጨዋቾች ይሳተፋሉ።
ሁለቱ አካላት ውድድሩን በጋራ ለማዘጋጀት የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን፣ ዝግጅቱ ክለቦች አዲሱ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት አቋማቸውን ለመለካት ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርላቸው ታውቋል። ውድድሩን አሸናፊ ለሚሆን ቡድን ከተዘጋጀው 1 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሽልማት በተጨማሪ፣ ለውድድሩ ኮከብ ተጫዋች፣ ኮከብ ግብ አግቢ እና ኮከብ በረኛ እያንዳንዳቸው የ20 ሺህ ብር የክብር ሽልማት እንደሚሰጣቸው ተገልጿል። #ኹነት
21 days ago