2 days ago
የኤቦላ ቫይረስ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን አሳወቀ
የዛሬ ሁለት ወራት ተኩል ገደማ በኮንጎ የተከሰተው የኤቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በአሳሳቢና ባልተጠበቀ ሁኔታ በሀገሪቱ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በምህፃሩ MSF አስታወቀ።
ድርጅቱ እንደሚለው በሽታውን ለመከላከል የህክምና ባለሞያዎች ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፤ ወረርሽኙ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ይገኛል።
እስካሁን ከ3 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በላቦራቶሪ ተረጋገጧል፤ ቁጥራቸው 1 ሺህ 500 የሚጠጋ ሰዎችም ሞተዋል።
በአሁኑ ጊዜ ዋናው ተግዳሮት ባለሥልጣናት በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች መለየት እንደተሳናቸው መሆኑ ነው።
ቡንያ በተባለው አካባቢ የሚገኝ የህክምና ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት በሽተኞች ውስጥ 90 በመቶው ከዚህ ቀደም በኤቦላ ቫይረስ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው የሚታወቅ ነገር የለም።
የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ኃላፊ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከመንግሥት ኃላፊዎችና ከሰብአዊ ድርጅቶች ጋር ለመነጋገር ዛሬ ወደ ኮንጎ ኪንሻሳ ሄደዋል።
ዶክተር ቴዎድሮስ የኤቦላ ወረርሽኝ ከተሰከሰተ ወዲህ ወደ ኮንጎ ሲጓዙ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
የዛሬ ሁለት ወራት ተኩል ገደማ በኮንጎ የተከሰተው የኤቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በአሳሳቢና ባልተጠበቀ ሁኔታ በሀገሪቱ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በምህፃሩ MSF አስታወቀ።
ድርጅቱ እንደሚለው በሽታውን ለመከላከል የህክምና ባለሞያዎች ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፤ ወረርሽኙ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ይገኛል።
እስካሁን ከ3 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በላቦራቶሪ ተረጋገጧል፤ ቁጥራቸው 1 ሺህ 500 የሚጠጋ ሰዎችም ሞተዋል።
በአሁኑ ጊዜ ዋናው ተግዳሮት ባለሥልጣናት በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች መለየት እንደተሳናቸው መሆኑ ነው።
ቡንያ በተባለው አካባቢ የሚገኝ የህክምና ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት በሽተኞች ውስጥ 90 በመቶው ከዚህ ቀደም በኤቦላ ቫይረስ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው የሚታወቅ ነገር የለም።
የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ኃላፊ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከመንግሥት ኃላፊዎችና ከሰብአዊ ድርጅቶች ጋር ለመነጋገር ዛሬ ወደ ኮንጎ ኪንሻሳ ሄደዋል።
ዶክተር ቴዎድሮስ የኤቦላ ወረርሽኝ ከተሰከሰተ ወዲህ ወደ ኮንጎ ሲጓዙ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት)) አደጋው ከተፈጸመ እነሆ አንድ ወር አልፎታል። የ50 ዓመቷን ኢትዮጵያዊት ሰርክአዲስ አበበ በቀለን ህይወት በከፍተኛ ስካር አሽከርክራ የቀጠፈችው የ28 ዓመቷ ማሪ ባህንድዋ፣ አሁን ላይ እስከ 20 ዓመታት ሊደርስ የሚችል የጽኑ እሥራት ፍርድ ከፊቷ ተደቅኗል። በጆርጂያ ግዛት ህግ መሰረት፣ አንደኛ ደረጃ የተሽከርካሪ ግድያ ብቻውን ከ3 እስከ 15 ዓመት የሚያስቀጣ ሲሆን፣ ከዚህ ጋር የተደራረቡት ሁለት የDUI (በስካር ማሽከርከር) እና የቸልተኝነት ወንጀሎች ሲታከሉበት፣ ማሪ የወጣትነት ዘመኗን ሙሉ በጨለማ የብረት አጥር ውስጥ እንድታሳልፍ ሊያደርጋት ይችላል።
ነገሩን ይበልጥ አሳዛኝ እና ልብ ሰባሪ የሚያደርገው ከግድያው ጀርባ ያለው የአደጋው መነሻ ምክንያት ነው። ማሪ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን የነፍስ ደጋፊ ነበረች። አደጋው ከመከሰቱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በአትላንታ ከተማ የተካሄደውን የኮንጎ የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ስትከታተል እና በከፍተኛ ስሜት ስታከብር ውላለች። በዚያች ሌሊት በከፍተኛ ስካር ውስጥ ሆና ስታሽከረክረው የነበረው ጂፕ (Jeep Wrangler) መኪናዋ ላይም፣ የኮንጎ ደጋፊ መሆኗን የሚገልጹ ጽሁፎች እና መፈክሮች ተለጥፈውበት ነበር።
የኮንጎን እግር ኳስ ጨዋታ ድምቀት በከፍተኛ የአልኮል ስካር ታጅባ ስታከብር ያመሸችው ማሪ፣ የራሷን የደስታ ምሽት በንጹህ እግረኛ ደም አጥቅራዋለች። በዚያች የጭለማ ሌሊት ኮርትላንድ አቬኑ ላይ መንገዱን በሰላም እያቋረጠች የነበረችው ምስኪን ኢትዮጵያዊት፣ በመኪናዋ ላይ የኮንጎን መፈክር በለጠፈች እና ራሷን መቆጣጠር ባቃታት ሰካራም አሽከርካሪ የህይወት ጉዞዋ በድንገት እና በአሰቃቂ ሁኔታ ተቋጭቷል።
የአንዲት ሀላፊነት የጎደላት ግለሰብ የደስታ ስካር፣ የአንድን ኢትዮጵያዊት ቤተሰብ ለዘለዓለማዊ የሀዘን ማቅ አልብሷል። አሁን ፍርድ ቤቱ ማሪን ከህብረተሰቡ በማግለል ተመጣጣኝ የሆነውን የጽኑ እሥራት ቅጣት ያስተላልፋል ተብሎ በጉጉት የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ አሳዛኝ ክስተት ግን በስካር የሚመጣ የሰከንድ ስህተት የሁለትን ሰዎች (የገዳይን እና የሟችን) ህይወት እንዴት ለዘለዓለም በጨለማ እንደሚያጠፋው ቁልጭ አድርጎ ያሳየ መሪር ትምህርት ሆኖ አልፏል።
ነገሩን ይበልጥ አሳዛኝ እና ልብ ሰባሪ የሚያደርገው ከግድያው ጀርባ ያለው የአደጋው መነሻ ምክንያት ነው። ማሪ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን የነፍስ ደጋፊ ነበረች። አደጋው ከመከሰቱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በአትላንታ ከተማ የተካሄደውን የኮንጎ የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ስትከታተል እና በከፍተኛ ስሜት ስታከብር ውላለች። በዚያች ሌሊት በከፍተኛ ስካር ውስጥ ሆና ስታሽከረክረው የነበረው ጂፕ (Jeep Wrangler) መኪናዋ ላይም፣ የኮንጎ ደጋፊ መሆኗን የሚገልጹ ጽሁፎች እና መፈክሮች ተለጥፈውበት ነበር።
የኮንጎን እግር ኳስ ጨዋታ ድምቀት በከፍተኛ የአልኮል ስካር ታጅባ ስታከብር ያመሸችው ማሪ፣ የራሷን የደስታ ምሽት በንጹህ እግረኛ ደም አጥቅራዋለች። በዚያች የጭለማ ሌሊት ኮርትላንድ አቬኑ ላይ መንገዱን በሰላም እያቋረጠች የነበረችው ምስኪን ኢትዮጵያዊት፣ በመኪናዋ ላይ የኮንጎን መፈክር በለጠፈች እና ራሷን መቆጣጠር ባቃታት ሰካራም አሽከርካሪ የህይወት ጉዞዋ በድንገት እና በአሰቃቂ ሁኔታ ተቋጭቷል።
የአንዲት ሀላፊነት የጎደላት ግለሰብ የደስታ ስካር፣ የአንድን ኢትዮጵያዊት ቤተሰብ ለዘለዓለማዊ የሀዘን ማቅ አልብሷል። አሁን ፍርድ ቤቱ ማሪን ከህብረተሰቡ በማግለል ተመጣጣኝ የሆነውን የጽኑ እሥራት ቅጣት ያስተላልፋል ተብሎ በጉጉት የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ አሳዛኝ ክስተት ግን በስካር የሚመጣ የሰከንድ ስህተት የሁለትን ሰዎች (የገዳይን እና የሟችን) ህይወት እንዴት ለዘለዓለም በጨለማ እንደሚያጠፋው ቁልጭ አድርጎ ያሳየ መሪር ትምህርት ሆኖ አልፏል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኦገስት 1 ቀን 2026 ጀምሮ ከሰሃራ በታች ባሉ 25 የአፍሪካ ሀገራት በሚገኙ ዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች የሚሰጠውን መደበኛ የቪዛ ማስተናገጃ አገልግሎት ማቋረጡን አስታውቋል። የትራምፕ አስተዳደር ይህንን ውሳኔ በቅርብ ታሪክ ውስጥ ከተደረጉት የአሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ የቪዛ አገልግሎቶች ትልቁ የማሻሻያ መርሃ ግብር ሲል ገልጾታል።
በአዲሱ አሰራር መሰረት የቪዛ አመልካቾች ከዚህ በኋላ በአቅራቢያቸው በሚገኝ የአሜሪካ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ጽህፈት ቤት ቀጠሮ መያዝም ሆነ የቪዛ ሂደታቸውን ማጠናቀቅ አይችሉም። ከዚህ ይልቅ በአህጉሪቱ ወደተመደቡ 20 ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት እንዲያቀኑ ይደረጋል።
የቪዛ አገልግሎታቸው የተቋረጠባቸው 25ቱ ሚሲዮኖች አቡጃ (ናይጄሪያ)፣ አንታናናሪቮ (ማዳጋስካር)፣ አስመራ (ኤርትራ)፣ ባማኮ (ማሊ)፣ ባንጁል (ጋምቢያ)፣ ብራዛቪል (የኮንጎ ሪፐብሊክ)፣ ቡጁምቡራ (ብሩንዲ)፣ ኮናክሪ (ጊኒ)፣ ኮቶኑ (ቤኒን)፣ ደርባን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ፍሪታውን (ሴራሊዮን)፣ ጋቦሮኔ (ቦትስዋና)፣ ሃራሬ (ዚምባብዌ)፣ ጁባ (ደቡብ ሱዳን)፣ ሊብረቪል (ጋቦን)፣ ሊሎንግዌ (ማላዊ)፣ ሉሳካ (ዛምቢያ)፣ ማፑቶ (ሞዛምቢክ)፣ ማሴሩ (ሌሴቶ)፣ ምባባኔ (ኤስዋቲኒ)፣ ንጃሜና (ቻድ)፣ ኒያሜይ (ኒጀር)፣ ኑዋክሾት (ሞሪታኒያ)፣ ዋጋዱጉ (ቡርኪና ፋሶ) እና ዊንድሆክ (ናሚቢያ) ናቸው። በደቡብ አፍሪካ ደርባን የሚገኘው የቪዛ ማዕከል ቢዘጋም፣ በኬፕታውን የሚሰጠው ተመሳሳይ አገልግሎት ግን ሳይቋረጥ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
20ዎቹ አዳዲስ ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት በአቢጃን፣ አክራ፣ አዲስ አበባ፣ ኬፕታውን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ዳካር፣ ዳሬሰላም፣ ጅቡቲ፣ ጆሃንስበርግ፣ ካምፓላ፣ ኪጋሊ፣ ኪንሻሳ፣ ሌጎስ፣ ሎሜ፣ ሉዋንዳ፣ ማላቦ፣ ሞንሮቪያ፣ ናይሮቢ፣ ፖርት ሉዊስ፣ ፕራያ እና ያውንዴ የሚገኙ ይሆናሉ። እያንዳንዱ ማዕከል በርካታ ጎረቤት ሀገራትን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ ለምሳሌ ከማሊ የሚመጡ አመልካቾች በዳካር (ሴኔጋል)፣ እንዲሁም ከቤኒን እና ኒጀር የሚመጡት ደግሞ በሎሜ (ቶጎ) የቪዛ ሂደታቸውን እንዲያከናውኑ ይመራሉ።
ሚኒስቴሩ ውሳኔውን የትራምፕ አስተዳደር ብሔራዊ ደህንነትን ለማጠናከር፣ የማጣራት ሂደቶችን ወጥ ለማድረግ፣ የመንግስት ወጪን ለመቀነስ እና የአሰራር ቅልጥፍናን ለማሻሻል ከሚያደርገው ጥረት አንዱ አካል መሆኑን አብራርቷል። ተመሳሳይ የውህደት ስራዎች በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እና በአውሮፓ ክፍሎች ቀደም ሲል መከናወናቸውን የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ብሔራዊ ደህንነትን በማጠናከር እና የመንግስትን ብክነት በመቀነስ አሜሪካን እና አሜሪካውያንን እያስቀደሙ ነው ብሏል።
ይህ ማሻሻያ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የቪዛ ማመልከቻዎችን የሚያስተናግዱ የአሜሪካ ሚሲዮኖችን ቁጥር ከ50 ገደማ ወደ 20 ዝቅ ያደርገዋል። ይህ በአመልካቾች ላይ ጉልህ የሆነ ተግባራዊ ተጽእኖ የሚያሳድር ሲሆን፣ የአገር ውስጥ የቪዛ አገልግሎት በተቋረጠባቸው ሀገራት የሚገኙ ዜጎች በአካል ለሚደረግ ቃለ ምልልስ እና የጣት አሻራ (ባዮሜትሪክ) ምዝገባ አለም አቀፍ ድንበሮችን አቋርጠው ለመጓዝ ስለሚገደዱ ለተጨማሪ የትራንስፖርት እና የማረፊያ ወጪዎች ይዳረጋሉ።
በአዲሱ አሰራር መሰረት የቪዛ አመልካቾች ከዚህ በኋላ በአቅራቢያቸው በሚገኝ የአሜሪካ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ጽህፈት ቤት ቀጠሮ መያዝም ሆነ የቪዛ ሂደታቸውን ማጠናቀቅ አይችሉም። ከዚህ ይልቅ በአህጉሪቱ ወደተመደቡ 20 ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት እንዲያቀኑ ይደረጋል።
የቪዛ አገልግሎታቸው የተቋረጠባቸው 25ቱ ሚሲዮኖች አቡጃ (ናይጄሪያ)፣ አንታናናሪቮ (ማዳጋስካር)፣ አስመራ (ኤርትራ)፣ ባማኮ (ማሊ)፣ ባንጁል (ጋምቢያ)፣ ብራዛቪል (የኮንጎ ሪፐብሊክ)፣ ቡጁምቡራ (ብሩንዲ)፣ ኮናክሪ (ጊኒ)፣ ኮቶኑ (ቤኒን)፣ ደርባን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ፍሪታውን (ሴራሊዮን)፣ ጋቦሮኔ (ቦትስዋና)፣ ሃራሬ (ዚምባብዌ)፣ ጁባ (ደቡብ ሱዳን)፣ ሊብረቪል (ጋቦን)፣ ሊሎንግዌ (ማላዊ)፣ ሉሳካ (ዛምቢያ)፣ ማፑቶ (ሞዛምቢክ)፣ ማሴሩ (ሌሴቶ)፣ ምባባኔ (ኤስዋቲኒ)፣ ንጃሜና (ቻድ)፣ ኒያሜይ (ኒጀር)፣ ኑዋክሾት (ሞሪታኒያ)፣ ዋጋዱጉ (ቡርኪና ፋሶ) እና ዊንድሆክ (ናሚቢያ) ናቸው። በደቡብ አፍሪካ ደርባን የሚገኘው የቪዛ ማዕከል ቢዘጋም፣ በኬፕታውን የሚሰጠው ተመሳሳይ አገልግሎት ግን ሳይቋረጥ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
20ዎቹ አዳዲስ ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት በአቢጃን፣ አክራ፣ አዲስ አበባ፣ ኬፕታውን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ዳካር፣ ዳሬሰላም፣ ጅቡቲ፣ ጆሃንስበርግ፣ ካምፓላ፣ ኪጋሊ፣ ኪንሻሳ፣ ሌጎስ፣ ሎሜ፣ ሉዋንዳ፣ ማላቦ፣ ሞንሮቪያ፣ ናይሮቢ፣ ፖርት ሉዊስ፣ ፕራያ እና ያውንዴ የሚገኙ ይሆናሉ። እያንዳንዱ ማዕከል በርካታ ጎረቤት ሀገራትን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ ለምሳሌ ከማሊ የሚመጡ አመልካቾች በዳካር (ሴኔጋል)፣ እንዲሁም ከቤኒን እና ኒጀር የሚመጡት ደግሞ በሎሜ (ቶጎ) የቪዛ ሂደታቸውን እንዲያከናውኑ ይመራሉ።
ሚኒስቴሩ ውሳኔውን የትራምፕ አስተዳደር ብሔራዊ ደህንነትን ለማጠናከር፣ የማጣራት ሂደቶችን ወጥ ለማድረግ፣ የመንግስት ወጪን ለመቀነስ እና የአሰራር ቅልጥፍናን ለማሻሻል ከሚያደርገው ጥረት አንዱ አካል መሆኑን አብራርቷል። ተመሳሳይ የውህደት ስራዎች በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እና በአውሮፓ ክፍሎች ቀደም ሲል መከናወናቸውን የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ብሔራዊ ደህንነትን በማጠናከር እና የመንግስትን ብክነት በመቀነስ አሜሪካን እና አሜሪካውያንን እያስቀደሙ ነው ብሏል።
ይህ ማሻሻያ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የቪዛ ማመልከቻዎችን የሚያስተናግዱ የአሜሪካ ሚሲዮኖችን ቁጥር ከ50 ገደማ ወደ 20 ዝቅ ያደርገዋል። ይህ በአመልካቾች ላይ ጉልህ የሆነ ተግባራዊ ተጽእኖ የሚያሳድር ሲሆን፣ የአገር ውስጥ የቪዛ አገልግሎት በተቋረጠባቸው ሀገራት የሚገኙ ዜጎች በአካል ለሚደረግ ቃለ ምልልስ እና የጣት አሻራ (ባዮሜትሪክ) ምዝገባ አለም አቀፍ ድንበሮችን አቋርጠው ለመጓዝ ስለሚገደዱ ለተጨማሪ የትራንስፖርት እና የማረፊያ ወጪዎች ይዳረጋሉ።
11 days ago
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽና ቀጣናዊ ፋይዳው
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ባለፉት አስርት ዓመታት በሰላም ማስከበር፣ በግጭት አፈታት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ፣ በቀጣናዊ ትስስር እና በንግድ ትብብር ረገድ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለቀጣናው የምትሰጠውን ከፍ ያለ ትኩረት ያሳያል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር ወርራ አታውቅም፡፡ ከጎረቤቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊና በትብብር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጎረቤቶቿ ሰላም በራቃቸው ጊዜ ሁሉ፣ ሰላም ለማስከበር ቀድማ በመገኘት ትታወቃለች፡፡ ይህንንም በደቡብ ሱዳን፣ በሱዳን፣ በሶማሊያ እንዲሁም ከጎረቤቶቿ ራቅ ብላም በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በኮንጎ እና በሴራሊዮን በተግባር አስመስክራለች፡፡
በአህጉር ደረጃ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አፍሪካውያን ወንድም እህቶች ነጻ ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት በስልጠና፣ በሎጂስቲክስና በዲፕሎማሲ መስክ ጭምር መደገፏ አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬም የልማት ትሩፋቷን ለብቻዋ ዕድገትና ለውጥ የምትጠቀም ሀገር አይደለችም፡፡ ይልቁንም ልማቷን እና ለውጧን በማጋራት እና ለጎረቤቶቿ አብሮ መለወጥ እየሰራች ትገኛለች፡፡
በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኤሌክትሪክ እየላከች ነው።
ይህ በአካባቢው የኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ እድገት እና የህዝብ ኑሮ መሻሻል ላይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
በንግድ ረገድም ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚያስቀምጧቸውን የክልላዊ ውህደት ግቦች ለማሳካት የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች፣ የድንበር ንግድ ማዕከላት እና የትራንስፖርት ኮሪደሮችን በማስፋፋት በቀጣናዊ ትስስር ማደግና መጠናከር ላይ ግዙፍ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ነው።
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና ልማት አበክራ የሰራቻቸው ስራዎች ለቀጣናውና ለሀገራቱ ያላትን አዎንታዊ ሚና በግልፅ ያሳያል። ሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ሲያገኝ ይህ ቀጣናዊ ገንቢ ሚናዋ በምን ያህል መጠን ሊያድግና ሊባዛ እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም፡፡
በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ህዝብ ህጋዊ ስልጣን በሌለው አካል ህጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷን እንድታጣ ተደርጓል፡፡ የመደመር መንግሥት የተፈጸመውን ኢፍትሃዊና ታሪካዊ በደል በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማስመለስ ጥያቄ አቅርቦ የበርካታ ሃያላን ሀገራትን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋና የህዝብ ቁጥሯ አንጻር የባሕር በር አማራጭ ሊኖራት ይገባል።
በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የባሕር በር እያለ ኢትዮጵያ ተዘግታ ትኑር የሚል ኢፍትሐዊነት ተቀባይነት የለውም።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የንግድ መውጫ መግቢያ ብቻ ሳይሆን፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የጂኦፖለቲካ ስትራቴጂ ቁልፍ ጥያቄ በመሆኑ ጥያቄዋ መልስ እስኪያገኝ አበክራ ትሰራለች፡፡
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ ጥቅሙ ለእርሷ ብቻ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ እና በጎረቤት ሀገራት ዘንድ ከፍ ያለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው የንግድ ኮሪደሮች ስለሚፈጠሩ የወደብ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ በማድረግ የንግድ ትስስርና አዳዲስ የስራ ዕድሎች ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል የምታመነጨው ኤሌክትሪክ ለቀጣናው በበቂ ሁኔታ ማቅረቧ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል።
ከዚህ ባሻገር የቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ሲመጣ በሀገራት መካከል ከግጭት ይልቅ ትብብር እንዲጨምር ያደርጋል። ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት በተጠናከረ ሁኔታ ሲተሳሰሩ ሰላምን የመጠበቅ ፍላጎታቸውም በዛው ልክ ይጨምራል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚጠይቀውን ቀጣናዊ ትስስር ለማጠናከር፣ የነፃ ንግድ ቀጣና ለመመስረት እና የመሠረተ ልማት ትስስርን ለማሳካት ጠንካራ መሠረት ለመጣል ያግዛል።
በመሆኑም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንዲያገኝ ለማድረግ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ቀጣናዊ ተቋማት ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ባለፉት አስርት ዓመታት በሰላም ማስከበር፣ በግጭት አፈታት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ፣ በቀጣናዊ ትስስር እና በንግድ ትብብር ረገድ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለቀጣናው የምትሰጠውን ከፍ ያለ ትኩረት ያሳያል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር ወርራ አታውቅም፡፡ ከጎረቤቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊና በትብብር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጎረቤቶቿ ሰላም በራቃቸው ጊዜ ሁሉ፣ ሰላም ለማስከበር ቀድማ በመገኘት ትታወቃለች፡፡ ይህንንም በደቡብ ሱዳን፣ በሱዳን፣ በሶማሊያ እንዲሁም ከጎረቤቶቿ ራቅ ብላም በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በኮንጎ እና በሴራሊዮን በተግባር አስመስክራለች፡፡
በአህጉር ደረጃ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አፍሪካውያን ወንድም እህቶች ነጻ ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት በስልጠና፣ በሎጂስቲክስና በዲፕሎማሲ መስክ ጭምር መደገፏ አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬም የልማት ትሩፋቷን ለብቻዋ ዕድገትና ለውጥ የምትጠቀም ሀገር አይደለችም፡፡ ይልቁንም ልማቷን እና ለውጧን በማጋራት እና ለጎረቤቶቿ አብሮ መለወጥ እየሰራች ትገኛለች፡፡
በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኤሌክትሪክ እየላከች ነው።
ይህ በአካባቢው የኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ እድገት እና የህዝብ ኑሮ መሻሻል ላይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
በንግድ ረገድም ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚያስቀምጧቸውን የክልላዊ ውህደት ግቦች ለማሳካት የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች፣ የድንበር ንግድ ማዕከላት እና የትራንስፖርት ኮሪደሮችን በማስፋፋት በቀጣናዊ ትስስር ማደግና መጠናከር ላይ ግዙፍ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ነው።
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና ልማት አበክራ የሰራቻቸው ስራዎች ለቀጣናውና ለሀገራቱ ያላትን አዎንታዊ ሚና በግልፅ ያሳያል። ሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ሲያገኝ ይህ ቀጣናዊ ገንቢ ሚናዋ በምን ያህል መጠን ሊያድግና ሊባዛ እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም፡፡
በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ህዝብ ህጋዊ ስልጣን በሌለው አካል ህጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷን እንድታጣ ተደርጓል፡፡ የመደመር መንግሥት የተፈጸመውን ኢፍትሃዊና ታሪካዊ በደል በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማስመለስ ጥያቄ አቅርቦ የበርካታ ሃያላን ሀገራትን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋና የህዝብ ቁጥሯ አንጻር የባሕር በር አማራጭ ሊኖራት ይገባል።
በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የባሕር በር እያለ ኢትዮጵያ ተዘግታ ትኑር የሚል ኢፍትሐዊነት ተቀባይነት የለውም።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የንግድ መውጫ መግቢያ ብቻ ሳይሆን፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የጂኦፖለቲካ ስትራቴጂ ቁልፍ ጥያቄ በመሆኑ ጥያቄዋ መልስ እስኪያገኝ አበክራ ትሰራለች፡፡
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ ጥቅሙ ለእርሷ ብቻ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ እና በጎረቤት ሀገራት ዘንድ ከፍ ያለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው የንግድ ኮሪደሮች ስለሚፈጠሩ የወደብ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ በማድረግ የንግድ ትስስርና አዳዲስ የስራ ዕድሎች ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል የምታመነጨው ኤሌክትሪክ ለቀጣናው በበቂ ሁኔታ ማቅረቧ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል።
ከዚህ ባሻገር የቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ሲመጣ በሀገራት መካከል ከግጭት ይልቅ ትብብር እንዲጨምር ያደርጋል። ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት በተጠናከረ ሁኔታ ሲተሳሰሩ ሰላምን የመጠበቅ ፍላጎታቸውም በዛው ልክ ይጨምራል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚጠይቀውን ቀጣናዊ ትስስር ለማጠናከር፣ የነፃ ንግድ ቀጣና ለመመስረት እና የመሠረተ ልማት ትስስርን ለማሳካት ጠንካራ መሠረት ለመጣል ያግዛል።
በመሆኑም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንዲያገኝ ለማድረግ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ቀጣናዊ ተቋማት ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
Sponsored by
Surafel
11 days ago
የቤኒን፣ ኮንጎ ሪፐብሊክና ሞዛምቢክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አዲስ አበባ ገቡ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቤኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮሪን አሞሪ ብሩኔት፣ የኮንጎ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮንስታንት ሰርጌ ቡንዳ እና የሞዛምቢክ የውጭ ጉዳይና ትብብር ሚኒስትር ማሪያ ሚኑኤላ ሉካስ በ49ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።
በ49ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ የሚሳተፋ የተለያዩ የሕብረቱ አባል ሀገራት የልዑካን ቡድን አባላት ከትናንት ጀምሮ አዲስ አበባ እየገቡ ነው።
የቤኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮሪን አሞሪ ብሩኔት፣ የኮንጎ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮንስታንት ሰርጌ ቡንዳ እና የሞዛምቢክ የውጭ ጉዳይና ትብብር ሚኒስትር ማሪያ ሚኑኤላ ሉካስ በ49ኛው የሕብረቱ ሥራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።
የሶስቱ ሀገራት ሚኒስትሮች ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አቶ መላኩ በዳዳ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የሥራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ "የአፍሪካን አጀንዳ 2063 ለማሳካት ዘላቂ የውኃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንፅህና አጠባበቅ ስርዓት ማንበር" በሚል መሪ ሀሳብ ከነገ ጀምሮ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ የአፍሪካ ሕብረት ዋና መስሪያ ቤት ይካሄዳል።
የሥራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት በአፍሪካ ሕብረት የ2026 የዓመቱ መሪ ሀሳብ ትግበራና አፈፃፀምን በተመለከተ በቀረበው ሪፖርት ላይ በጥልቀት ይመክራል።
የአፍሪካ ሕብረት ስምምነቶች በቅልጥፍና በሚጸድቁበትና ገቢራዊ በሚሆኑባቸው ጉዳዮች እንዲሁም በአጀንዳ 2063 ትግበራ ዙሪያ በቀረበው የኮሚቴው ሪፖርት ላይ ይወያያል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቤኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮሪን አሞሪ ብሩኔት፣ የኮንጎ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮንስታንት ሰርጌ ቡንዳ እና የሞዛምቢክ የውጭ ጉዳይና ትብብር ሚኒስትር ማሪያ ሚኑኤላ ሉካስ በ49ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።
በ49ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ የሚሳተፋ የተለያዩ የሕብረቱ አባል ሀገራት የልዑካን ቡድን አባላት ከትናንት ጀምሮ አዲስ አበባ እየገቡ ነው።
የቤኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮሪን አሞሪ ብሩኔት፣ የኮንጎ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮንስታንት ሰርጌ ቡንዳ እና የሞዛምቢክ የውጭ ጉዳይና ትብብር ሚኒስትር ማሪያ ሚኑኤላ ሉካስ በ49ኛው የሕብረቱ ሥራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።
የሶስቱ ሀገራት ሚኒስትሮች ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አቶ መላኩ በዳዳ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የሥራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ "የአፍሪካን አጀንዳ 2063 ለማሳካት ዘላቂ የውኃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንፅህና አጠባበቅ ስርዓት ማንበር" በሚል መሪ ሀሳብ ከነገ ጀምሮ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ የአፍሪካ ሕብረት ዋና መስሪያ ቤት ይካሄዳል።
የሥራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት በአፍሪካ ሕብረት የ2026 የዓመቱ መሪ ሀሳብ ትግበራና አፈፃፀምን በተመለከተ በቀረበው ሪፖርት ላይ በጥልቀት ይመክራል።
የአፍሪካ ሕብረት ስምምነቶች በቅልጥፍና በሚጸድቁበትና ገቢራዊ በሚሆኑባቸው ጉዳዮች እንዲሁም በአጀንዳ 2063 ትግበራ ዙሪያ በቀረበው የኮሚቴው ሪፖርት ላይ ይወያያል።
13 days ago
በካናዳ የጥገኝነት ጥያቄ ካቀረቡ የአፍሪካ ሀገራት ሪፖርት ውረፈስጥ ኢትዮጵያም ተካታለች
#ethiopia | የካናዳ የኢሚግሬሽን እና የስደተኞች ቦርድ (IRB) እ.ኤ.አ በ2025 በካናዳ የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ አፍሪካውያንን በተመለከተ አዲስ መረጃ ይፋ አድርጓል።
ይፋ በሆነው መረጃ መሠረት በካናዳ ጥገኝነት በመጠየቅ ረገድ ናይጄሪያውያን በ21 ሺህ 573 ጥያቄዎች የአፍሪካን ቀዳሚ ስፍራ ሲይዙ፣ ጋና በ9 ሺህ 784 እንዲሁም ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በ6 ሺህ 752 የጥገኝነት ጥያቄዎች ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
የጥገኝነት ጥያቄዎች ዝርዝር ውስጥ አልጄሪያ በ5 ሺህ 821፣ ጊኒ በ4 ሺህ 709፣ ኬንያ በ3 ሺህ 862 እንዲሁም ካሜሩን እና ሴኔጋል እያንዳንዳቸው በ3 ሺህ 579 ጥያቄዎች በከፍተኛ ደረጃ ከተጠቀሱት ሀገራት መካከል ይገኙበታል።
በተጨማሪም ሩዋንዳ፣ ኮትዲቯር እና ኡጋንዳ በቅደም ተከተል ይከተላሉ።
ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ በ2 ሺህ 203 የጥገኝነት ጥያቄዎች በ12ኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን፣ ቻድ፣ ቡሩንዲ፣ ግብፅ እና ቡርኪና ፋሶም በቅደም ተከተል የሚከተለውን ደረጃ ይዘዋል።
በአንጻሩ ሞሮኮ፣ ሱዳን፣ አንጎላ እና ቶጎ በቅደም ተከተል ከ900 እስከ 1,000 የሚደርሱ የጥገኝነት ጥያቄዎችን በማስመዝገብ በ20ሩ አፍሪካ ሀገራት ዝርዝር ማጠቃለያ ላይ ተቀምጠዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የካናዳ የኢሚግሬሽን እና የስደተኞች ቦርድ (IRB) እ.ኤ.አ በ2025 በካናዳ የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ አፍሪካውያንን በተመለከተ አዲስ መረጃ ይፋ አድርጓል።
ይፋ በሆነው መረጃ መሠረት በካናዳ ጥገኝነት በመጠየቅ ረገድ ናይጄሪያውያን በ21 ሺህ 573 ጥያቄዎች የአፍሪካን ቀዳሚ ስፍራ ሲይዙ፣ ጋና በ9 ሺህ 784 እንዲሁም ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በ6 ሺህ 752 የጥገኝነት ጥያቄዎች ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
የጥገኝነት ጥያቄዎች ዝርዝር ውስጥ አልጄሪያ በ5 ሺህ 821፣ ጊኒ በ4 ሺህ 709፣ ኬንያ በ3 ሺህ 862 እንዲሁም ካሜሩን እና ሴኔጋል እያንዳንዳቸው በ3 ሺህ 579 ጥያቄዎች በከፍተኛ ደረጃ ከተጠቀሱት ሀገራት መካከል ይገኙበታል።
በተጨማሪም ሩዋንዳ፣ ኮትዲቯር እና ኡጋንዳ በቅደም ተከተል ይከተላሉ።
ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ በ2 ሺህ 203 የጥገኝነት ጥያቄዎች በ12ኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን፣ ቻድ፣ ቡሩንዲ፣ ግብፅ እና ቡርኪና ፋሶም በቅደም ተከተል የሚከተለውን ደረጃ ይዘዋል።
በአንጻሩ ሞሮኮ፣ ሱዳን፣ አንጎላ እና ቶጎ በቅደም ተከተል ከ900 እስከ 1,000 የሚደርሱ የጥገኝነት ጥያቄዎችን በማስመዝገብ በ20ሩ አፍሪካ ሀገራት ዝርዝር ማጠቃለያ ላይ ተቀምጠዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
14 days ago
ከ700 በላይ የዓለም መሪዎችንና ፈጣሪዎችን የሚያሰባስበው ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው!
#fastmereja :- ታሪካዊው «የዓለም አቀፍ የሕዝቦች ጉባኤ አፍሪካ» (World Public Summit Africa) ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በዲፕሎማሲያዊቷ መዲና አዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የፈጠራ አውጪዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ የብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች እና የባህል መሪዎች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ይሳተፋሉ።
ጉባኤው በስፖርት አማካኝነት በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ከሚያቀራርበው የዓለም ዋንጫ ጋር በሚመሳሰል መልኩ፡ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አካላትን በማሰባሰብ በጋራ ሀሳብ የመለዋወጥ፣ ጠንካራ አጋርነቶችን የመፍጠር እና ለዓለማችን መሠረታዊ ኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊ፣ ማህበራዊ እና የልማት ጉዳዮች መፍትሔ የመፈለግ ዓላማን ማሰናዳቱን ተገልጿል።
ይህ ታላቅ መድረክ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ይህም አፍሪካ በዓለም አቀፍ የንግድ፣የፈጠራ፣ የዘላቂ ልማት፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ እና የሁለገብ ትብብር ውይይቶች ላይ ያላትን እየጎለበተ የመጣ ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅ እንደሆነ በመግለጫው ወቅት ተመላክቷል።
የጉባኤው ዋና ማዕከል ከሆኑት ዝግጅቶች አንዱ «አንድነት» (Unity) የተሰኘው ዓለም አቀፍ ዘመናዊ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን መሆኑን አዘጋጆቹ ጠቁመዋል።
ኤግዚቢሽኑ ከ16 የአፍሪካ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ካሜሩን፣ ኮንጎ ዲ/ሪ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ማዳጋስካር፣ ናሚቢያ፣ ናይጄሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሱዳን፣ ታንዛኒያ፣ ቱኒዚያ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ) የተጣጣሙ ታዋቂ አርቲስቶችን እንዲሁም የአፍሪካና የዳያስፖራውን ታሪካዊ ቁርኝት የሚያሳይ አፍሮ-ብራዚላዊ አርቲስትን ያሰባስባል።
በተጨማሪም «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሳይንሳዊ ጥናት የሚቀርብ ሲሆን፣ ጥናቱ ወንዙ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት (አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክ) እድገት ላይ ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ በስፋት እንደሚመረምር ነዉ የተገለፀዉ።
የጠቅላላው ምክር ቤት ሊቀመንበር አማካሪ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እንደገለፁት «አንድነት ማለት ወጥ መሆን ማለት አይደለም፤ ይልቁንም ለባህል ብዝሃነት ከሚሰጥ አክብሮት፣ ከእርስ በእርስ እምነት፣ ክፍትነት እና ለመደማመጥ ከሚኖር ፈቃደኝነት የሚወለድ መሆኑን ገልፀዉ ስለዚህም ጥበብ ልክ እንደ ስፖርት ሁሉ የሰው ልጅ የጋራ ቋንቋ እና የሕዝብ ዲፕሎማሲ መሣሪያ ነው። ቃላት ብቻቸውን ማሳካት በማይችሉበት ቦታ ሰዎችን ያቀራርባል።» ብለዋል።
የሰርቭ ግሎባል (Serve Global) ምክትል የሀገርውስጥ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ነጋሽ እንደገለፁት«ጉባኤው በንግድ ድርድር ላይ ሳይሆን አልሞ የተነሳና የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ ይጠርጋል።» ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ጉባኤ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል ዓለም አቀፍ የትብብር መድረክ አካል ሲሆን፣ ቀጣዩ ዓለም አቀፍ መድረክ በመስከረም ወር በሩሲያ ሞስኮ እንደሚካሄድ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እና ታሪኩ ነጋሽ ጨምረው አስታውቀዋል።
#fastmereja :- ታሪካዊው «የዓለም አቀፍ የሕዝቦች ጉባኤ አፍሪካ» (World Public Summit Africa) ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በዲፕሎማሲያዊቷ መዲና አዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የፈጠራ አውጪዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ የብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች እና የባህል መሪዎች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ይሳተፋሉ።
ጉባኤው በስፖርት አማካኝነት በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ከሚያቀራርበው የዓለም ዋንጫ ጋር በሚመሳሰል መልኩ፡ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አካላትን በማሰባሰብ በጋራ ሀሳብ የመለዋወጥ፣ ጠንካራ አጋርነቶችን የመፍጠር እና ለዓለማችን መሠረታዊ ኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊ፣ ማህበራዊ እና የልማት ጉዳዮች መፍትሔ የመፈለግ ዓላማን ማሰናዳቱን ተገልጿል።
ይህ ታላቅ መድረክ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ይህም አፍሪካ በዓለም አቀፍ የንግድ፣የፈጠራ፣ የዘላቂ ልማት፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ እና የሁለገብ ትብብር ውይይቶች ላይ ያላትን እየጎለበተ የመጣ ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅ እንደሆነ በመግለጫው ወቅት ተመላክቷል።
የጉባኤው ዋና ማዕከል ከሆኑት ዝግጅቶች አንዱ «አንድነት» (Unity) የተሰኘው ዓለም አቀፍ ዘመናዊ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን መሆኑን አዘጋጆቹ ጠቁመዋል።
ኤግዚቢሽኑ ከ16 የአፍሪካ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ካሜሩን፣ ኮንጎ ዲ/ሪ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ማዳጋስካር፣ ናሚቢያ፣ ናይጄሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሱዳን፣ ታንዛኒያ፣ ቱኒዚያ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ) የተጣጣሙ ታዋቂ አርቲስቶችን እንዲሁም የአፍሪካና የዳያስፖራውን ታሪካዊ ቁርኝት የሚያሳይ አፍሮ-ብራዚላዊ አርቲስትን ያሰባስባል።
በተጨማሪም «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሳይንሳዊ ጥናት የሚቀርብ ሲሆን፣ ጥናቱ ወንዙ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት (አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክ) እድገት ላይ ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ በስፋት እንደሚመረምር ነዉ የተገለፀዉ።
የጠቅላላው ምክር ቤት ሊቀመንበር አማካሪ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እንደገለፁት «አንድነት ማለት ወጥ መሆን ማለት አይደለም፤ ይልቁንም ለባህል ብዝሃነት ከሚሰጥ አክብሮት፣ ከእርስ በእርስ እምነት፣ ክፍትነት እና ለመደማመጥ ከሚኖር ፈቃደኝነት የሚወለድ መሆኑን ገልፀዉ ስለዚህም ጥበብ ልክ እንደ ስፖርት ሁሉ የሰው ልጅ የጋራ ቋንቋ እና የሕዝብ ዲፕሎማሲ መሣሪያ ነው። ቃላት ብቻቸውን ማሳካት በማይችሉበት ቦታ ሰዎችን ያቀራርባል።» ብለዋል።
የሰርቭ ግሎባል (Serve Global) ምክትል የሀገርውስጥ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ነጋሽ እንደገለፁት«ጉባኤው በንግድ ድርድር ላይ ሳይሆን አልሞ የተነሳና የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ ይጠርጋል።» ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ጉባኤ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል ዓለም አቀፍ የትብብር መድረክ አካል ሲሆን፣ ቀጣዩ ዓለም አቀፍ መድረክ በመስከረም ወር በሩሲያ ሞስኮ እንደሚካሄድ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እና ታሪኩ ነጋሽ ጨምረው አስታውቀዋል።
18 days ago
አሜሪካ ወደ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈች
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም ሀገራትን የፀጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትን በከፍተኛው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዝርዝር ውስጥ አስፍሯል።
ዋሽንግተን የራሷ ዜጎች ወደነዚህ ሀገራት ፍጹም ጉዞ እንዳያደርጉ ያሳሰበችው በእነዚህ ቀጠናዎች ባለው እጅግ አሳሳቢ የፀጥታ ችግር፣ የሽብርተኝነት ስጋት፣ የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የታጠቁ አማፂያን ጥቃት እና ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጠው የቆንስላ ወይም የድንገተኛ ጊዜ ድጋፍ እጅግ ውስን በመሆኑ ነው።
በዚህ የዩናይትድ ስቴትስ የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ቡርኪና ፋሶ፣ ሊቢያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ እንደ ቻድ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ ሀገራት ደግሞ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያገናኟቸው ድንበሮችና የተወሰኑ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ግዛቶቻቸው ላይ ተመሳሳይ የደረጃ 4 እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ዩጋንዳ በደረጃ 3 (Reconsider Travel ወይም ጉዞን መልሶ ማሰብ) ስር የምትገኝ ሲሆን፣ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመጓዛቸው በፊት በወንጀል እና በሽብርተኝነት ስጋቶች ዙሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመክሯል።
ይህ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየጊዜው የሚሻሻለው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከአፍሪካ ውጭ እንደ ሩሲያ፣ ዩክሬን፣ አፍጋኒስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ ኢራን እና ጋዛን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያሉ የዓለማችን አካባቢዎችንም ያጠቃልላል።
Seledadotio
Seledadotio
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም ሀገራትን የፀጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትን በከፍተኛው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዝርዝር ውስጥ አስፍሯል።
ዋሽንግተን የራሷ ዜጎች ወደነዚህ ሀገራት ፍጹም ጉዞ እንዳያደርጉ ያሳሰበችው በእነዚህ ቀጠናዎች ባለው እጅግ አሳሳቢ የፀጥታ ችግር፣ የሽብርተኝነት ስጋት፣ የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የታጠቁ አማፂያን ጥቃት እና ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጠው የቆንስላ ወይም የድንገተኛ ጊዜ ድጋፍ እጅግ ውስን በመሆኑ ነው።
በዚህ የዩናይትድ ስቴትስ የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ቡርኪና ፋሶ፣ ሊቢያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ እንደ ቻድ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ ሀገራት ደግሞ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያገናኟቸው ድንበሮችና የተወሰኑ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ግዛቶቻቸው ላይ ተመሳሳይ የደረጃ 4 እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ዩጋንዳ በደረጃ 3 (Reconsider Travel ወይም ጉዞን መልሶ ማሰብ) ስር የምትገኝ ሲሆን፣ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመጓዛቸው በፊት በወንጀል እና በሽብርተኝነት ስጋቶች ዙሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመክሯል።
ይህ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየጊዜው የሚሻሻለው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከአፍሪካ ውጭ እንደ ሩሲያ፣ ዩክሬን፣ አፍጋኒስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ ኢራን እና ጋዛን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያሉ የዓለማችን አካባቢዎችንም ያጠቃልላል።
Seledadotio
Seledadotio
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና የሩዋንዳ ተወካዮች በምሥራቃዊ ኮንጎ ያለውን የጸጥታ ሁኔታ ለማሻሻልና ሁለቱ ሀገራት የደረሱትን የሰላም ስምምነት ለመተግበር በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ከተማ ስብሰባ ማካሄዳቸውን የጋራ መግለጫቸው አመልክቷል። በጄኔቫ በሚገኘው የአሜሪካ ሚሲዮን ጽሕፈት ቤት ሐምሌ 2018 ዓ.ም (በአውሮፓውያን አቆጣጠር ጁላይ 2026) በተካሄደው አምስተኛው የጋራ የጸጥታ ማስተባበሪያ ሥርዓት ስብሰባ ላይ ሁለቱ ሀገራት ከአሜሪካ፣ ከቃታር፣ ከቶጎ (የአፍሪካ ኅብረት አወያይ) እና ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ተወካዮች ጋር በጋራ መክረዋል። በውይይቱም በምሥራቃዊ ኮንጎ ያለውን ተጨባጭ የጸጥታ ሁኔታ የመገምገም እና በአካባቢው ስላለው ሁኔታ የጋራ ግንዛቤ የመያዝ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ኮንጎ እና ሩዋንዳ ከዚህ ቀደም የፈረሙትን የዋሽንግተን ስምምነት በፍጥነት ተግባራዊ ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህም የኤፍዲኤልአር የተባለውን አማጺ ቡድን የማክሸፍ ተግባራትን ማፋጠን፣ የጦር ኃይሎችን እርስ በርስ ማራቅ እና የመከላከያ እርምጃዎችን ማንሳትን ያጠቃልላል። ሂደቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆን ለማድረግም፣ የዋሽንግተን ስምምነት ተፈጻሚነቱን የሚያረጋግጡ የጋራ የቁጥጥር ሥርዓቶችን ለመዘርጋት ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
በተጨማሪም ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኮንጎ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (ሞኑስኮ) የተዋጊዎችን ትጥቅ መፍታት፣ ከውጊያ ማሰናበትና መልሶ ማቋቋም ሥራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ የአማጺ ቡድኑ አባላት ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የሚደረገው ጥረት ለዋሽንግተን ስምምነት ስኬት ስላለው አስተዋጽኦ በሰፊው ተወያይተዋል። ሁለቱ ሀገራት በምሥራቃዊ ኮንጎ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ ትክክለኛ መረጃ እንዲኖር በየጊዜው መረጃ ለመለዋወጥ ቃል ገብተዋል።
የዋሽንግተን ስምምነት በታላላቅ ሐይቆች አካባቢ ደኅንነትንና ብልጽግናን ለማምጣት ታሪካዊ ዕድል መሆኑን የገለጹት ተሳታፊዎቹ፣ ለሂደቱ ስኬት አሜሪካ፣ ቃታር፣ አፍሪካ ኅብረትና ቶጎ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። ወገኖቹ የተመዘገቡ እቅዶችን እና የተገኙ ውጤቶችን ለመገምገም በሚቀጥሉት ሳምንታት በድጋሚ ለመሰብሰብ ተስማምተዋል።
ኮንጎ እና ሩዋንዳ ከዚህ ቀደም የፈረሙትን የዋሽንግተን ስምምነት በፍጥነት ተግባራዊ ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህም የኤፍዲኤልአር የተባለውን አማጺ ቡድን የማክሸፍ ተግባራትን ማፋጠን፣ የጦር ኃይሎችን እርስ በርስ ማራቅ እና የመከላከያ እርምጃዎችን ማንሳትን ያጠቃልላል። ሂደቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆን ለማድረግም፣ የዋሽንግተን ስምምነት ተፈጻሚነቱን የሚያረጋግጡ የጋራ የቁጥጥር ሥርዓቶችን ለመዘርጋት ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
በተጨማሪም ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኮንጎ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (ሞኑስኮ) የተዋጊዎችን ትጥቅ መፍታት፣ ከውጊያ ማሰናበትና መልሶ ማቋቋም ሥራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ የአማጺ ቡድኑ አባላት ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የሚደረገው ጥረት ለዋሽንግተን ስምምነት ስኬት ስላለው አስተዋጽኦ በሰፊው ተወያይተዋል። ሁለቱ ሀገራት በምሥራቃዊ ኮንጎ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ ትክክለኛ መረጃ እንዲኖር በየጊዜው መረጃ ለመለዋወጥ ቃል ገብተዋል።
የዋሽንግተን ስምምነት በታላላቅ ሐይቆች አካባቢ ደኅንነትንና ብልጽግናን ለማምጣት ታሪካዊ ዕድል መሆኑን የገለጹት ተሳታፊዎቹ፣ ለሂደቱ ስኬት አሜሪካ፣ ቃታር፣ አፍሪካ ኅብረትና ቶጎ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። ወገኖቹ የተመዘገቡ እቅዶችን እና የተገኙ ውጤቶችን ለመገምገም በሚቀጥሉት ሳምንታት በድጋሚ ለመሰብሰብ ተስማምተዋል።
27 days ago
ከፖለቲካ ሽኩቻ የላቀው የጋራ ተቋማችንን እናክብር
****************
የአንድ ሀገር ጥንካሬ ከሚገለጽባቸው መሠረታዊ ጉዳዮች መካከል አንዱ ዜጎች በጋራ የሚግባቡባቸው እና በኩራት የሚጠሯቸው ጠንካራ ብሔራዊ ተቋማት መኖራቸው ነው።
ከእነዚህ ተቋማት መካከል ደግሞ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀዳሚውን እና የክብር ማማውን ስፍራ ይይዛል።
የዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ስንመለከት፣ በሠለጠኑ ዴሞክራሲያዊ ሀገራት የሠራዊት አባላትን ማክበር ከፖለቲካዊ ሽኩቻዎች የላቀ ብሔራዊ መግባባት የተገነባበት ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን።
በአሜሪካ የፖለቲካ ምኅዳር ውስጥ በፓርቲዎች መካከል የጎላ ርዕዮተ ዓለማዊ ልዩነት ቢኖርም፣ ሠራዊቱን ከፖለቲካ ፉክክር ውጪ የማድረግ ብሔራዊ ስምምነት አለ።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የመንግሥትን ፖሊሲ በሚተቹበት ወቅት እንኳ በጦር ግንባር የተሰማሩትን ወታደሮች እንደ ጀግና በመቁጠር ውዳሴ እና ክብር ያቀርባሉ።
በዩናይትድ ኪንግደም "የጦር ኃይሎች ቃል ኪዳን" (Armed Forces Covenant) የተሰኘው ብሔራዊ ሰነድ የሠራዊት አባላት ልዩ ክብር እንዲያገኙ ያደርጋል።
ካናዳ ለአርበኞች ልዩ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ስታቋቁም፣ ፈረንሳይ ደግሞ ሠራዊቷን የሀገሯ የክብር እና የአጋርነት ብሔራዊ ተምሳሌት በማድረግ በትልቅ ማዕረግ ትዘክራለች።
ወደ ሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ስንመጣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በባሕርይው እጅግ ሕዝባዊ የሆነ፣ ከሀገር አልፎ ለዓለም የሰላም ዘብ በመሆን ደሙን የገበረ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።
የኢትዮጵያ ወታደር በኮሪያ ልሳነ ምድር በቃኘው ሻለቃ አማካኝነት "አንድም ወታደር አልተማረከም፤ የሞተ ጓዱንም ጥሎ አልመጣም" የሚል የዓለምን አስደናቂ ሪከርድ ያስመዘገበ ጀግና ነው።
በኮንጎ፣ በሩዋንዳ፣ በቡሩንዲ፣ በላይቤሪያ፣ በአብዬ፣ በዳርፉር እና በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ላይ በመሰማራት አፍሪካውያን ወንድሞቹን ከእልቂት የታደገ፣ የራሱን ሬሽን እያካፈለ የውጭ ሀገር ዜጎችን ያኖረ የሰብአዊነት ተምሳሌት ነው።
ይህ ሠራዊት በሀገር ውስጥም ቢሆን ጦር መሣሪያውን አስቀምጦ በክረምት የገበሬውን ማሳ ሲያርስ እና በመኸር ሲያጭድ፣ የተፈጥሮ አደጋ ሲያጋጥም ከነፍስ አድን ሥራ እስከ አንበጣ መንጋ ማባረር ድረስ ከሕዝቡ ጎን የቆመ ታላቅ አለኝታ ነው።
ነገር ግን አለመታደል ሆኖ፣ የሀገራችን መከላከያ ሠራዊት በፖለቲካ ኃይሎች መካከል በሚደረጉ ፍልሚያዎች ውስጥ የከፉ ምኞቶች ሰለባ ሲሆን ይስተዋላል።
አንዳንዴም የፖለቲካ ልዩነትን እና የሀገርን የፀጥታ ምሰሶ መለየት ያቃታቸው አካላት ሠራዊቱን የማንቋሸሽ አዝማሚያ ያሳያሉ።
የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ማክበር እና ለሀገር ሕልውና የሚከፍለውን ዋጋ ማወቅ የአንድ ማኅበረሰብ የሥልጣኔ መገለጫ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተደጋጋሚ አስገንዝበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ በፓርላማ ባደረጉት ንግግር፣ ሀገርን ጠብቆ የሚያኖርን ኃይል እንደ "ገዳይ" መፈረጅ እና ተቋማዊ ክብሩን አለማወቅ የሲቪል-ወታደራዊ ግንኙነትን አለመረዳት እና ያለመሠልጠን ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
መንግሥት እና ፖሊሲ አውጪዎችን በጥብቅ መተቸት የዴሞክራሲ አካል ነው። ነገር ግን ለሀገር ሕልውና አጥንቱን የሚከሰክሰውን ሠራዊት ከተቋማዊ ትችት ነፃ አድርጎ በጀግንነት መዘከር ይገባል።
በመሠረቱ ሠራዊቱ ሕዝብን የመጠበቅ ግዴታ ሲኖርበት፣ መንግሥት እና ሕዝብ ደግሞ የሠራዊቱን መሥዋዕትነት የመካስ የሞራል ግዴታ አለባቸው።
ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ትኩረት አድርጋ ከሠራችባቸው የሪፎርም ሥራዎች መካከል የፀጥታ ተቋማት ግንባታ ዋነኛው የሆነውም ለዚሁ ነው።
ሠራዊታችን ከፖለቲካ ልዩነቶቻችን በላይ የሆነ የጋራ የብረት አጥራችን እና የሕልውናችን ምሰሶ በመሆኑ ዘወትር ክብር እና ሞገስ ይገባዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #endf #nationalpride #standwithourtroops
****************
የአንድ ሀገር ጥንካሬ ከሚገለጽባቸው መሠረታዊ ጉዳዮች መካከል አንዱ ዜጎች በጋራ የሚግባቡባቸው እና በኩራት የሚጠሯቸው ጠንካራ ብሔራዊ ተቋማት መኖራቸው ነው።
ከእነዚህ ተቋማት መካከል ደግሞ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀዳሚውን እና የክብር ማማውን ስፍራ ይይዛል።
የዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ስንመለከት፣ በሠለጠኑ ዴሞክራሲያዊ ሀገራት የሠራዊት አባላትን ማክበር ከፖለቲካዊ ሽኩቻዎች የላቀ ብሔራዊ መግባባት የተገነባበት ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን።
በአሜሪካ የፖለቲካ ምኅዳር ውስጥ በፓርቲዎች መካከል የጎላ ርዕዮተ ዓለማዊ ልዩነት ቢኖርም፣ ሠራዊቱን ከፖለቲካ ፉክክር ውጪ የማድረግ ብሔራዊ ስምምነት አለ።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የመንግሥትን ፖሊሲ በሚተቹበት ወቅት እንኳ በጦር ግንባር የተሰማሩትን ወታደሮች እንደ ጀግና በመቁጠር ውዳሴ እና ክብር ያቀርባሉ።
በዩናይትድ ኪንግደም "የጦር ኃይሎች ቃል ኪዳን" (Armed Forces Covenant) የተሰኘው ብሔራዊ ሰነድ የሠራዊት አባላት ልዩ ክብር እንዲያገኙ ያደርጋል።
ካናዳ ለአርበኞች ልዩ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ስታቋቁም፣ ፈረንሳይ ደግሞ ሠራዊቷን የሀገሯ የክብር እና የአጋርነት ብሔራዊ ተምሳሌት በማድረግ በትልቅ ማዕረግ ትዘክራለች።
ወደ ሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ስንመጣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በባሕርይው እጅግ ሕዝባዊ የሆነ፣ ከሀገር አልፎ ለዓለም የሰላም ዘብ በመሆን ደሙን የገበረ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።
የኢትዮጵያ ወታደር በኮሪያ ልሳነ ምድር በቃኘው ሻለቃ አማካኝነት "አንድም ወታደር አልተማረከም፤ የሞተ ጓዱንም ጥሎ አልመጣም" የሚል የዓለምን አስደናቂ ሪከርድ ያስመዘገበ ጀግና ነው።
በኮንጎ፣ በሩዋንዳ፣ በቡሩንዲ፣ በላይቤሪያ፣ በአብዬ፣ በዳርፉር እና በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ላይ በመሰማራት አፍሪካውያን ወንድሞቹን ከእልቂት የታደገ፣ የራሱን ሬሽን እያካፈለ የውጭ ሀገር ዜጎችን ያኖረ የሰብአዊነት ተምሳሌት ነው።
ይህ ሠራዊት በሀገር ውስጥም ቢሆን ጦር መሣሪያውን አስቀምጦ በክረምት የገበሬውን ማሳ ሲያርስ እና በመኸር ሲያጭድ፣ የተፈጥሮ አደጋ ሲያጋጥም ከነፍስ አድን ሥራ እስከ አንበጣ መንጋ ማባረር ድረስ ከሕዝቡ ጎን የቆመ ታላቅ አለኝታ ነው።
ነገር ግን አለመታደል ሆኖ፣ የሀገራችን መከላከያ ሠራዊት በፖለቲካ ኃይሎች መካከል በሚደረጉ ፍልሚያዎች ውስጥ የከፉ ምኞቶች ሰለባ ሲሆን ይስተዋላል።
አንዳንዴም የፖለቲካ ልዩነትን እና የሀገርን የፀጥታ ምሰሶ መለየት ያቃታቸው አካላት ሠራዊቱን የማንቋሸሽ አዝማሚያ ያሳያሉ።
የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ማክበር እና ለሀገር ሕልውና የሚከፍለውን ዋጋ ማወቅ የአንድ ማኅበረሰብ የሥልጣኔ መገለጫ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተደጋጋሚ አስገንዝበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ በፓርላማ ባደረጉት ንግግር፣ ሀገርን ጠብቆ የሚያኖርን ኃይል እንደ "ገዳይ" መፈረጅ እና ተቋማዊ ክብሩን አለማወቅ የሲቪል-ወታደራዊ ግንኙነትን አለመረዳት እና ያለመሠልጠን ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
መንግሥት እና ፖሊሲ አውጪዎችን በጥብቅ መተቸት የዴሞክራሲ አካል ነው። ነገር ግን ለሀገር ሕልውና አጥንቱን የሚከሰክሰውን ሠራዊት ከተቋማዊ ትችት ነፃ አድርጎ በጀግንነት መዘከር ይገባል።
በመሠረቱ ሠራዊቱ ሕዝብን የመጠበቅ ግዴታ ሲኖርበት፣ መንግሥት እና ሕዝብ ደግሞ የሠራዊቱን መሥዋዕትነት የመካስ የሞራል ግዴታ አለባቸው።
ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ትኩረት አድርጋ ከሠራችባቸው የሪፎርም ሥራዎች መካከል የፀጥታ ተቋማት ግንባታ ዋነኛው የሆነውም ለዚሁ ነው።
ሠራዊታችን ከፖለቲካ ልዩነቶቻችን በላይ የሆነ የጋራ የብረት አጥራችን እና የሕልውናችን ምሰሶ በመሆኑ ዘወትር ክብር እና ሞገስ ይገባዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #endf #nationalpride #standwithourtroops
28 days ago
ኮንጎ ከፍተኛ ወታደራዊ በጀት በመመደብ ከአህጉሪቱ ቀዳሚ ሆናለች
#ethiopia | የአፍሪካ ሀገራት ወታደራዊ በጀት እንደ ጸጥታ ተግዳሮቶቻቸው ለጂኦፖሊቲካዊ ጉዳዮች ቅድሚያ የሚሰጧቸው ጉዳዮች እና እንደ የኢኮኖሚ አቅማቸው ይለያያል።
የወርልድ ባንክ ኦፕን ዳታ በ2026 ያወጣው ወታደራዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኮንጎ ቀዳሚ ብትሆንም አብዛኛዎቹ የሰሜን አፍሪካ ሀገራት በወታደራዊ ወጪ ቀዳሚውን ስፍራ ይዘዋል።
የሰሃራ በታች ያሉ ሀገራትም በአህጉሪቱ የጸጥታ እቅድ ውስጥ ወሳኝ ሚና አላቸው።
በዚህም መሠረት በመሆኑ ዕድን ሀብቷ የምትታወቀው ኮንጎ ለወታደራዊ ወጪ በአመት 30 ቢሊዮን ዶላር ወጪ በማውጣት ከአህጉሪቱ ቀዳሚ ሆናለች።
የሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አልጀርያ
ከ25 ቢሊዮን ዶላር በላይ በአህጉሪቱ ለወታደራዊ ወጪ በበመደቅ በሁለተኛ ስፍራ ላይ ትገኛለች።
አልጀርያ በአየር በመሬት እና በድንበሯ የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ለሰፊው የበርሃ ድንበሯ ጥበቃና ለአሸባሪዎች መከላከል ስራዎች ቅድሚያ በመስጠት ላይ ትገኛለች።
ከአልጀርያ ጋር በድንበር ጉዳይ የምትወዛገበው ሞሮኮ 13.4 ቢሊዮን ዶላር በወታደራዊ ዘርፏ ላይ ወጪ ታደርጋለች።
የግብፅ ወታደራዊ በጀት በአፍሪካ ትልቅ ከሚባሉት አንዱ ሲሆን በአህጉር ደረጃም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ የተሰማራ ልምድ ያለው ጦር ባለቤት ሆናለች።
በዚህም ግብጽ ለመከላከያ ዘርፏ 6.9 ቢሊዮን ዶላር ትመድባለች።
ከአህጉሪቱ ለመከላከያ ዘርፏ ከፍተኛ ወጪ የምታወጣው አምስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ናይጄርያ ናት።
ሀገሪቷ በየአመቱ 3.4 ቢሊዮን ዶላር ለመከላከያ ዘርፏ ትመድባለች።
እነዚህ ቁጥራዊ አሀዞች በ2026 የተሰበሰቡ መረጃዎች ሲሆኑ እንደ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እድገት እና የጸጥታ ሁኔታ ሊቀያየሩ እንደሚችሉ ነው የተገለጸው።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldbankopendata #africamilitryexpenditure #congo #algeria #egypt #morocco
#ethiopia | የአፍሪካ ሀገራት ወታደራዊ በጀት እንደ ጸጥታ ተግዳሮቶቻቸው ለጂኦፖሊቲካዊ ጉዳዮች ቅድሚያ የሚሰጧቸው ጉዳዮች እና እንደ የኢኮኖሚ አቅማቸው ይለያያል።
የወርልድ ባንክ ኦፕን ዳታ በ2026 ያወጣው ወታደራዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኮንጎ ቀዳሚ ብትሆንም አብዛኛዎቹ የሰሜን አፍሪካ ሀገራት በወታደራዊ ወጪ ቀዳሚውን ስፍራ ይዘዋል።
የሰሃራ በታች ያሉ ሀገራትም በአህጉሪቱ የጸጥታ እቅድ ውስጥ ወሳኝ ሚና አላቸው።
በዚህም መሠረት በመሆኑ ዕድን ሀብቷ የምትታወቀው ኮንጎ ለወታደራዊ ወጪ በአመት 30 ቢሊዮን ዶላር ወጪ በማውጣት ከአህጉሪቱ ቀዳሚ ሆናለች።
የሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አልጀርያ
ከ25 ቢሊዮን ዶላር በላይ በአህጉሪቱ ለወታደራዊ ወጪ በበመደቅ በሁለተኛ ስፍራ ላይ ትገኛለች።
አልጀርያ በአየር በመሬት እና በድንበሯ የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ለሰፊው የበርሃ ድንበሯ ጥበቃና ለአሸባሪዎች መከላከል ስራዎች ቅድሚያ በመስጠት ላይ ትገኛለች።
ከአልጀርያ ጋር በድንበር ጉዳይ የምትወዛገበው ሞሮኮ 13.4 ቢሊዮን ዶላር በወታደራዊ ዘርፏ ላይ ወጪ ታደርጋለች።
የግብፅ ወታደራዊ በጀት በአፍሪካ ትልቅ ከሚባሉት አንዱ ሲሆን በአህጉር ደረጃም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ የተሰማራ ልምድ ያለው ጦር ባለቤት ሆናለች።
በዚህም ግብጽ ለመከላከያ ዘርፏ 6.9 ቢሊዮን ዶላር ትመድባለች።
ከአህጉሪቱ ለመከላከያ ዘርፏ ከፍተኛ ወጪ የምታወጣው አምስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ናይጄርያ ናት።
ሀገሪቷ በየአመቱ 3.4 ቢሊዮን ዶላር ለመከላከያ ዘርፏ ትመድባለች።
እነዚህ ቁጥራዊ አሀዞች በ2026 የተሰበሰቡ መረጃዎች ሲሆኑ እንደ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እድገት እና የጸጥታ ሁኔታ ሊቀያየሩ እንደሚችሉ ነው የተገለጸው።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldbankopendata #africamilitryexpenditure #congo #algeria #egypt #morocco
28 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ከሰላሳ ቀናት በፊት የዓለም ዋንጫው ሲጀመር… ከዚህ ቀደም በውድድሩ ላይ ደምቀው ከነበሩት በርካታ ኮከቦቿ የተላቀቀችው ቤልጂየም ዋንጫውን ልታነሳ ትችላለች ብሎ የገመተ ሰው አልነበረም። በተለይም በጥሎ ማለፉ ጨዋታ ከሴኔጋል ጋር ስትገናኝ እስከ ሰማንያ አምስተኛው ደቂቃ ድረስ ሁለት ለ ባዶ እየተመራች ይህንን ገደል አልፋ ትመጣለች ብሎ ማሰብ ፈጽሞ የማይቻል ነበር። ነገር ግን ቀያዮቹ ሰይጣኖች (ቤልጂየሞች) ሴኔጋልን በማሸነፍ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ከታዩት አስገራሚ የመልሶ ማጥቃት ድሎች አንዱን ካስመዘገቡ በኋላ፣ አስተናጋጇን አሜሪካን በሜዳዋ አራት ለ አንድ በሆነ ሰፊ ውጤት በማሸነፍ በልበ ሙሉነት ወደ ሩብ ፍፃሜው ተቀላቅለዋል።
ምንም እንኳን እንደ ኤደን ሃዛርድ፣ ሙሳ ዴምቤሌ፣ ማሩዋን ፌላኒ እና ቪንሰንት ኮምፓኒ ያሉ ታላላቅ ተጫዋቾች ከቡድኑ ቢሰናበቱም፤ ቲቦ ኩርቱዋ፣ ሮሜሉ ሉካኩ፣ ኬቨን ደብሩይን እና አክሰል ዊትሰልን ያካተተው ስብስብ መካከለኛ የነበረውን የውድድር ጅማሮ ወደ ታላቅ የድል ጉዞ ቀይሮታል። ዛሬ ምሽት ለግማሽ ፍፃሜ ለማለፍ ከስፔን ጋር ለሚያደርጉት ወሳኝ ፍልሚያ ሲዘጋጁ፣ የቤልጂየም ወርቃማ ትውልድ ጊዜው አልፏል ተብሎ በቶሎ ተገምቶ ይሆን? ወይስ አሰልጣኝ ሩዲ ጋርሲያ የተጫዋቾቹን አቅም በተለየ መንገድ እየተጠቀሙበት ነው? የሚለው ጥያቄ በብዙዎች ዘንድ ይነሳል።
ቤልጂየም በሁለት ሺህ አስራ አራት በብራዚል ሩብ ፍፃሜ፣ በሁለት ሺህ አስራ ስምንት በሩሲያ ግማሽ ፍፃሜ በመድረስ በከፍተኛ ብቃት ላይ ብትገኝም፣ በኳታሩ የሁለት ሺህ ሀያ ሁለት የዓለም ዋንጫ ግን ከሞሮኮ እና ክሮኤሺያ በታች በመሆን በምድብ ድልድሉ መሰናበቷ ይታወሳል። በአራተኛ የዓለም ዋንጫው ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የሪያል ማድሪዱ ግብ ጠባቂ ቲቦ ኩርቱዋ ከአሜሪካው ጨዋታ በፊት በሰጠው አስተያየት፣ ይህ ለእኛ አዲስ ዘመን ነው። ከወርቃማው ዘመን የመጡ ተጫዋቾች ቢኖሩም፣ የኳታሩ የዓለም ዋንጫ ለእኛ ጥሩ አልነበረም። አሁን ግን ታላላቅ ነገሮችን ለማድረግ እና ለቤልጂየም አዲስ ታሪክ ለመጻፍ የተዘጋጁ ወጣት እና አዳዲስ ተጫዋቾችን የያዘ ሌላ ትውልድ አለን ብሏል። የኩርቱዋ ንግግር እውነትነት አለው፤ ምክንያቱም ወጣቶቹ ተጫዋቾች የቡድኑን ትልቅ ኃላፊነት ከጫንቃቸው ላይ እየተወጡ ይገኛሉ።
ከሁለት ሺህ አስራ አራት እና አስራ ስምንቱ ስብስብ ውስጥ ከተረፉት አራት ተጫዋቾች መካከል፣ የሰላሳ አራት ዓመቱ ኩርቱዋ በዚህ ውድድር ሁሉንም ደቂቃዎች ተጫውቷል። ነገር ግን ዴብሩይን፣ ሉካኩ እና ዊትሰል በቋሚነት የመሰለፍ እድላቸው ቀንሷል። የሰላሳ ሰባት ዓመቱ የመሀል ሜዳ ተጫዋች አክሰል ዊትሰል በአሜሪካው ጨዋታ መገባደጃ ላይ ለአንድ ደቂቃ ብቻ ነው የተሰለፈው። የሰላሳ ሶስት ዓመቱ ሉካኩ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ድንቅ ብቃት ቢያሳይም፣ አብዛኛውን ጊዜ በተቀያሪነት በመግባት ከሃምሳ በመቶ በታች የሆኑ ደቂቃዎችን ብቻ ነው የተጫወተው። በተለይም የሀያ አምስት ዓመቱ የአታላንታ አጥቂ ቻርለስ ዴኬቴላየር በሚፈጥረው ከፍተኛ ጫና የደከሙ ተከላካዮችን በመጠቀም ሉካኩ የግብ እድሎችን በሚገባ ተጠቅሟል። የሰላሳ አምስት ዓመቱ ዴብሩይን በሴኔጋሉ ጨዋታ ላይ ጉዳት ማስተናገዱ ይታወሳል። እሱ ከሜዳ ከመውጣቱ በፊት ቤልጂየም ከሶስት ጨዋታዎች አንድ ብቻ ያሸነፈች ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ ግን በሁለት ጨዋታዎች ሰባት ግቦችን በማስቆጠር አሸንፋለች።
ይህ ማለት ግን ነባር ተጫዋቾች አስተዋጽኦ አላደረጉም ማለት አይደለም። ኩርቱዋ አሁንም ከዓለም ምርጥ ግብ ጠባቂዎች አንዱ ነው፤ የሉካኩ ግቦች ወሳኝ ነበሩ፤ ዴብሩይንም ከጉዳቱ በፊት የቡድኑ ምርጥ ተጫዋች ነበር። ነገር ግን በቡድኑ ውስጥ ያላቸው ሚና እየተቀየረ ነው። አሁን የቡድኑን አጠቃላይ የጨዋታ ጥራት ከመሸከም ይልቅ፣ በወሳኝ ጊዜያት ላይ ልዩነት በመፍጠር ላይ ትኩረት አድርገዋል። እስካሁን ባለው ሂደት አሰልጣኝ ጋርሲያ እና ቤልጂየም፣ የኮከቦቻቸውን የመዳከም የሽግግር ጊዜ ሌሎች ቡድኖች ከሚያደርጉት በተሻለ ሁኔታ እያስተዳደሩት ይገኛሉ። አሰልጣኙ የዕድሜ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደማይገባ ያምናሉ። በውድድሩ መጀመሪያ ላይ በሰጡት አስተያየት፣ አራቱ መሪዎቼ አዛውንት እየተባሉ ሲጠሩ አልወድም፤ ይህ አስቀያሚ እና አስከፊ ነው። አንዲት ሀገር እንዲህ አይነት ከፍተኛ ብቃት ያላቸው ተጫዋቾች በማግኘቷ እድለኛ ከሆነች፣ ሊበረታቱ ይገባል በማለት ተከላክለውላቸዋል።
ቤልጂየም አሁን ላለችበት ደረጃ.. በሁለት ሺህ አስራ አራት እና አስራ ስምንት ከፍተኛ ጫና ውስጥ ያልነበሩ፣ ነገር ግን በአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች በመጫወት ሰፊ ልምድ ያካበቱ ተጫዋቾች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። የአርሴናሉ ሊያንድሮ ትሮሳርድ በዚህ ውድድር አስራ ሰባት የግብ እድሎችን በመፍጠር ከማንኛውም ተጫዋች የላቀ ብቃት ያሳየ ሲሆን፣ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር እና ሁለት ኳሶችን በማመቻቸት ለቡድኑ ትልቅ አቅም ሆኗል። ዴኬቴላየር ብዙ ግብ ባያስቆጥርም፣ ሁለት ግቦችን አግብቶ አንዱን አመቻችቷል፤ እንዲሁም ለመስመር አጥቂዎች ሰፊ ቦታን ይፈጥራል። የክለብ ብሩጁ የሰላሳ ሶስት ዓመት አማካይ ሃንስ ቫናከን፣ ከቤልጂየም ውጭ ተጫውቶ ባያውቅም አንድ ግብ እና ሁለት አሲስት አስመዝግቧል። አምበሉ ዩሪ ቴሌማንስ ደግሞ በሴኔጋሉ ጨዋታ የአቻነቷን እና የማሸነፊያዋን ግብ አስቆጥሯል። ከሀያ አምስት ዓመት በታች ከሆኑ አስራ ሶስት ተጫዋቾች መካከል፣ የማንችስተር ሲቲው የመስመር አጥቂ ጀረሚ ዶኩ ከፍተኛ ብቃት ያለው ተጫዋች ተደርጎ ይወሰዳል።
ቤልጂየሞች በአስራ ስድስቱ ጥሎ ማለፍ፣ ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር በአሜሪካው አጥቂ ፎላሪን ባሎገን ላይ የጣለውን የአንድ ጨዋታ እገዳ ማንሳቱን ተከትሎ በተፈጠረው ውዝግብ ይበልጥ የተነሳሱ ይመስሉ ነበር። ተጫዋቾቹ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ላይ የሚያሳዩትን ዳንስ በሜዳ ላይ በመድገም መሳቂያ አድርገዋቸዋል። ከጨዋታው በኋላ ጋርሲያ የቡድናቸውን አንድነት ሲያወድሱ፣ ስብስቡ በጣም የበሰለ ነው፤ የሚረዱን መሪዎች አሉን ብለዋል።
የቤልጂየም መሪዎች አንዱ መለያቸው የቋንቋ ብዝሃነት መሆኑ ነው። ቤልጂየም ያላት የታሪክ ዳራ እና የአውሮፓ ህብረት ማዕከል መሆኗ፣ ቡድኑን ከተለያዩ ሀገራት ማለትም ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ጋና፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሴኔጋል፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያን፣ ፖርቱጋል እና ስፔን ዝርያ ካላቸው ተጫዋቾች እንዲዋቀር አድርጎታል። ሉካኩ ብቻውን ስድስት ቋንቋዎችን አቀላጥፎ ይናገራል።
አንዳንድ ተጫዋቾች ከሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የመጡ እና የደች ቋንቋ ተናጋሪዎች ሲሆኑ፣ ሌሎቹ ደግሞ ከፈረንሳይኛ ተናጋሪው ክልል የመጡ ናቸው። ብዙዎቹ ሁለቱንም ቋንቋዎች ቢናገሩም፣ ሁሉም ግን አይችሉም፤ በዚህም ምክንያት ተጫዋቾቹ በጋራ ለመግባባት የእንግሊዝኛ ቋንቋን በስፋት ይጠቀማሉ። በአንትወርፕ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ ጥናት ከፍተኛ መምህር የሆኑት ዶክተር ጂም ዩሬል እንዳሉት፣ ይህ በጣም ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው። ቋንቋ በቤልጂየም ውስጥ ስሱ እና ከማንነት እንዲሁም ከፖለቲካ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ጉዳይ ነው። የደች ተናጋሪዎች ለፈረንሳይኛ ተናጋሪዎች ማዘንበል አይፈልጉም፣ በተቃራኒውም እንዲሁ። ስለዚህ ተጫዋቾቹ አንዱን ቢመርጡ ችግር ሊፈጥር ይችላል። በዚህ ጊዜ እንግሊዝኛ ወሳኝ መፍትሄ ይሆናል፤ በተለይም ወጣት እግር ኳስ ተጫዋቾች ይህን ቋንቋ በሚገባ ስለሚናገሩ እና አብዛኞቹም በእንግሊዝኛ ተናጋሪ ሀገራት ስለሚጫወቱ ልዩነቱን ያጠባዋል።
ቤልጂየም ስፔንን አሸንፋ ጉዞዋን ለመቀጠል ከፈለገች… ሉካኩ እና ሌሎች የቡድኑ መሪዎች በየትኛውም ቋንቋ ቢሆን ተጫዋቾቹን ይበልጥ ማነሳሳት ይጠበቅባቸዋል። ይህ የቤልጂየም ስብስብ የወርቃማው ትውልድ የመጨረሻ ሙከራ ሳይሆን፣ ልምድ ያካበቱ አንጋፋ ተጫዋቾች አዲስ አባታዊ ኃላፊነት ወስደው የነገ ተረካቢዎቻቸውን ወደ ፊት እየመሩበት ያለ አስደናቂ ጉዞ ነው።
ምንም እንኳን እንደ ኤደን ሃዛርድ፣ ሙሳ ዴምቤሌ፣ ማሩዋን ፌላኒ እና ቪንሰንት ኮምፓኒ ያሉ ታላላቅ ተጫዋቾች ከቡድኑ ቢሰናበቱም፤ ቲቦ ኩርቱዋ፣ ሮሜሉ ሉካኩ፣ ኬቨን ደብሩይን እና አክሰል ዊትሰልን ያካተተው ስብስብ መካከለኛ የነበረውን የውድድር ጅማሮ ወደ ታላቅ የድል ጉዞ ቀይሮታል። ዛሬ ምሽት ለግማሽ ፍፃሜ ለማለፍ ከስፔን ጋር ለሚያደርጉት ወሳኝ ፍልሚያ ሲዘጋጁ፣ የቤልጂየም ወርቃማ ትውልድ ጊዜው አልፏል ተብሎ በቶሎ ተገምቶ ይሆን? ወይስ አሰልጣኝ ሩዲ ጋርሲያ የተጫዋቾቹን አቅም በተለየ መንገድ እየተጠቀሙበት ነው? የሚለው ጥያቄ በብዙዎች ዘንድ ይነሳል።
ቤልጂየም በሁለት ሺህ አስራ አራት በብራዚል ሩብ ፍፃሜ፣ በሁለት ሺህ አስራ ስምንት በሩሲያ ግማሽ ፍፃሜ በመድረስ በከፍተኛ ብቃት ላይ ብትገኝም፣ በኳታሩ የሁለት ሺህ ሀያ ሁለት የዓለም ዋንጫ ግን ከሞሮኮ እና ክሮኤሺያ በታች በመሆን በምድብ ድልድሉ መሰናበቷ ይታወሳል። በአራተኛ የዓለም ዋንጫው ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የሪያል ማድሪዱ ግብ ጠባቂ ቲቦ ኩርቱዋ ከአሜሪካው ጨዋታ በፊት በሰጠው አስተያየት፣ ይህ ለእኛ አዲስ ዘመን ነው። ከወርቃማው ዘመን የመጡ ተጫዋቾች ቢኖሩም፣ የኳታሩ የዓለም ዋንጫ ለእኛ ጥሩ አልነበረም። አሁን ግን ታላላቅ ነገሮችን ለማድረግ እና ለቤልጂየም አዲስ ታሪክ ለመጻፍ የተዘጋጁ ወጣት እና አዳዲስ ተጫዋቾችን የያዘ ሌላ ትውልድ አለን ብሏል። የኩርቱዋ ንግግር እውነትነት አለው፤ ምክንያቱም ወጣቶቹ ተጫዋቾች የቡድኑን ትልቅ ኃላፊነት ከጫንቃቸው ላይ እየተወጡ ይገኛሉ።
ከሁለት ሺህ አስራ አራት እና አስራ ስምንቱ ስብስብ ውስጥ ከተረፉት አራት ተጫዋቾች መካከል፣ የሰላሳ አራት ዓመቱ ኩርቱዋ በዚህ ውድድር ሁሉንም ደቂቃዎች ተጫውቷል። ነገር ግን ዴብሩይን፣ ሉካኩ እና ዊትሰል በቋሚነት የመሰለፍ እድላቸው ቀንሷል። የሰላሳ ሰባት ዓመቱ የመሀል ሜዳ ተጫዋች አክሰል ዊትሰል በአሜሪካው ጨዋታ መገባደጃ ላይ ለአንድ ደቂቃ ብቻ ነው የተሰለፈው። የሰላሳ ሶስት ዓመቱ ሉካኩ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ድንቅ ብቃት ቢያሳይም፣ አብዛኛውን ጊዜ በተቀያሪነት በመግባት ከሃምሳ በመቶ በታች የሆኑ ደቂቃዎችን ብቻ ነው የተጫወተው። በተለይም የሀያ አምስት ዓመቱ የአታላንታ አጥቂ ቻርለስ ዴኬቴላየር በሚፈጥረው ከፍተኛ ጫና የደከሙ ተከላካዮችን በመጠቀም ሉካኩ የግብ እድሎችን በሚገባ ተጠቅሟል። የሰላሳ አምስት ዓመቱ ዴብሩይን በሴኔጋሉ ጨዋታ ላይ ጉዳት ማስተናገዱ ይታወሳል። እሱ ከሜዳ ከመውጣቱ በፊት ቤልጂየም ከሶስት ጨዋታዎች አንድ ብቻ ያሸነፈች ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ ግን በሁለት ጨዋታዎች ሰባት ግቦችን በማስቆጠር አሸንፋለች።
ይህ ማለት ግን ነባር ተጫዋቾች አስተዋጽኦ አላደረጉም ማለት አይደለም። ኩርቱዋ አሁንም ከዓለም ምርጥ ግብ ጠባቂዎች አንዱ ነው፤ የሉካኩ ግቦች ወሳኝ ነበሩ፤ ዴብሩይንም ከጉዳቱ በፊት የቡድኑ ምርጥ ተጫዋች ነበር። ነገር ግን በቡድኑ ውስጥ ያላቸው ሚና እየተቀየረ ነው። አሁን የቡድኑን አጠቃላይ የጨዋታ ጥራት ከመሸከም ይልቅ፣ በወሳኝ ጊዜያት ላይ ልዩነት በመፍጠር ላይ ትኩረት አድርገዋል። እስካሁን ባለው ሂደት አሰልጣኝ ጋርሲያ እና ቤልጂየም፣ የኮከቦቻቸውን የመዳከም የሽግግር ጊዜ ሌሎች ቡድኖች ከሚያደርጉት በተሻለ ሁኔታ እያስተዳደሩት ይገኛሉ። አሰልጣኙ የዕድሜ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደማይገባ ያምናሉ። በውድድሩ መጀመሪያ ላይ በሰጡት አስተያየት፣ አራቱ መሪዎቼ አዛውንት እየተባሉ ሲጠሩ አልወድም፤ ይህ አስቀያሚ እና አስከፊ ነው። አንዲት ሀገር እንዲህ አይነት ከፍተኛ ብቃት ያላቸው ተጫዋቾች በማግኘቷ እድለኛ ከሆነች፣ ሊበረታቱ ይገባል በማለት ተከላክለውላቸዋል።
ቤልጂየም አሁን ላለችበት ደረጃ.. በሁለት ሺህ አስራ አራት እና አስራ ስምንት ከፍተኛ ጫና ውስጥ ያልነበሩ፣ ነገር ግን በአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች በመጫወት ሰፊ ልምድ ያካበቱ ተጫዋቾች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። የአርሴናሉ ሊያንድሮ ትሮሳርድ በዚህ ውድድር አስራ ሰባት የግብ እድሎችን በመፍጠር ከማንኛውም ተጫዋች የላቀ ብቃት ያሳየ ሲሆን፣ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር እና ሁለት ኳሶችን በማመቻቸት ለቡድኑ ትልቅ አቅም ሆኗል። ዴኬቴላየር ብዙ ግብ ባያስቆጥርም፣ ሁለት ግቦችን አግብቶ አንዱን አመቻችቷል፤ እንዲሁም ለመስመር አጥቂዎች ሰፊ ቦታን ይፈጥራል። የክለብ ብሩጁ የሰላሳ ሶስት ዓመት አማካይ ሃንስ ቫናከን፣ ከቤልጂየም ውጭ ተጫውቶ ባያውቅም አንድ ግብ እና ሁለት አሲስት አስመዝግቧል። አምበሉ ዩሪ ቴሌማንስ ደግሞ በሴኔጋሉ ጨዋታ የአቻነቷን እና የማሸነፊያዋን ግብ አስቆጥሯል። ከሀያ አምስት ዓመት በታች ከሆኑ አስራ ሶስት ተጫዋቾች መካከል፣ የማንችስተር ሲቲው የመስመር አጥቂ ጀረሚ ዶኩ ከፍተኛ ብቃት ያለው ተጫዋች ተደርጎ ይወሰዳል።
ቤልጂየሞች በአስራ ስድስቱ ጥሎ ማለፍ፣ ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር በአሜሪካው አጥቂ ፎላሪን ባሎገን ላይ የጣለውን የአንድ ጨዋታ እገዳ ማንሳቱን ተከትሎ በተፈጠረው ውዝግብ ይበልጥ የተነሳሱ ይመስሉ ነበር። ተጫዋቾቹ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ላይ የሚያሳዩትን ዳንስ በሜዳ ላይ በመድገም መሳቂያ አድርገዋቸዋል። ከጨዋታው በኋላ ጋርሲያ የቡድናቸውን አንድነት ሲያወድሱ፣ ስብስቡ በጣም የበሰለ ነው፤ የሚረዱን መሪዎች አሉን ብለዋል።
የቤልጂየም መሪዎች አንዱ መለያቸው የቋንቋ ብዝሃነት መሆኑ ነው። ቤልጂየም ያላት የታሪክ ዳራ እና የአውሮፓ ህብረት ማዕከል መሆኗ፣ ቡድኑን ከተለያዩ ሀገራት ማለትም ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ጋና፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሴኔጋል፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያን፣ ፖርቱጋል እና ስፔን ዝርያ ካላቸው ተጫዋቾች እንዲዋቀር አድርጎታል። ሉካኩ ብቻውን ስድስት ቋንቋዎችን አቀላጥፎ ይናገራል።
አንዳንድ ተጫዋቾች ከሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የመጡ እና የደች ቋንቋ ተናጋሪዎች ሲሆኑ፣ ሌሎቹ ደግሞ ከፈረንሳይኛ ተናጋሪው ክልል የመጡ ናቸው። ብዙዎቹ ሁለቱንም ቋንቋዎች ቢናገሩም፣ ሁሉም ግን አይችሉም፤ በዚህም ምክንያት ተጫዋቾቹ በጋራ ለመግባባት የእንግሊዝኛ ቋንቋን በስፋት ይጠቀማሉ። በአንትወርፕ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ ጥናት ከፍተኛ መምህር የሆኑት ዶክተር ጂም ዩሬል እንዳሉት፣ ይህ በጣም ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው። ቋንቋ በቤልጂየም ውስጥ ስሱ እና ከማንነት እንዲሁም ከፖለቲካ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ጉዳይ ነው። የደች ተናጋሪዎች ለፈረንሳይኛ ተናጋሪዎች ማዘንበል አይፈልጉም፣ በተቃራኒውም እንዲሁ። ስለዚህ ተጫዋቾቹ አንዱን ቢመርጡ ችግር ሊፈጥር ይችላል። በዚህ ጊዜ እንግሊዝኛ ወሳኝ መፍትሄ ይሆናል፤ በተለይም ወጣት እግር ኳስ ተጫዋቾች ይህን ቋንቋ በሚገባ ስለሚናገሩ እና አብዛኞቹም በእንግሊዝኛ ተናጋሪ ሀገራት ስለሚጫወቱ ልዩነቱን ያጠባዋል።
ቤልጂየም ስፔንን አሸንፋ ጉዞዋን ለመቀጠል ከፈለገች… ሉካኩ እና ሌሎች የቡድኑ መሪዎች በየትኛውም ቋንቋ ቢሆን ተጫዋቾቹን ይበልጥ ማነሳሳት ይጠበቅባቸዋል። ይህ የቤልጂየም ስብስብ የወርቃማው ትውልድ የመጨረሻ ሙከራ ሳይሆን፣ ልምድ ያካበቱ አንጋፋ ተጫዋቾች አዲስ አባታዊ ኃላፊነት ወስደው የነገ ተረካቢዎቻቸውን ወደ ፊት እየመሩበት ያለ አስደናቂ ጉዞ ነው።
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) እንግሊዝ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ምርጡን ብቃቷን በማሳየት፣ በስሜት እና በደጋፊዎች ጩኸት በተሞላው ታሪካዊው የአዝቴካ ስታዲየም ሜክሲኮን በአስደናቂ ሁኔታ አሸንፋለች። በዚህም ከኖርዌይ ጋር ለምታደርገው የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ቀጠሮ ይዛለች።
በከባድ ማዕበል ምክንያት ከአንድ ሰዓት መዘግየት በኋላ በተጀመረው እና የትያትር ያህል በሚመስለው በዚህ የስፖርት ምሽት፣ የቶማስ ቱኸል ስብስብ በርካታ ፈተናዎችን አልፏል። በሁለተኛው አጋማሽ መጀመሪያ ላይ ጃሬል ኳንሳህ በቀይ ካርድ ከሜዳ ቢወጣበትም፣ ቡድኑ ጫናውን ተቋቁሞ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ካስመዘገባቸው ታላላቅ ድሎች አንዱን አሳክቷል።
ሜክሲኮ በገዛ ሜዳዋ፣ "ምሽጌ" በምትለው አዝቴካ ባደረገቻቸው 89 ተወዳዳሪ ጨዋታዎች የተሸነፈችው በሁለቱ ብቻ ነበር። ነገር ግን የእንግሊዝ የተረጋጋ አቀራረብ ጨዋታውን ቶሎ እንዲቆጣጠሩ አስችሏቸዋል። በተለይም ድንቁ ጁድ ቤሊንግሃም ከእረፍት በፊት በ98 ሰከንዶች ልዩነት ውስጥ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር እንግሊዝን መሪ አድርጓል።
የእንግሊዙ ግብ ጠባቂ ጆርዳን ፒክፎርድ ራውል ሂሜኔዝ ያደረጋቸውን ሁለት አስቆጣሪ ሙከራዎች በሚያስደንቅ ሁኔታ በማዳን ብቃቱን አሳይቷል። ሆኖም ከእረፍት ሶስት ደቂቃዎች በፊት ጁሊያን ኪኖኔስ በኃይለኛ ምት አንድ ግብ ለሜክሲኮ ማስቆጠሩ አልቀረም።
በደጋፊዎቿ ጩኸት ታጅባ ወደ ፊት የተገፋችው ሜክሲኮ፣ ኳንሳህ በሄሱስ ጋላርዶ ላይ በሰራው አደገኛ ጥፋት ቀይ ካርድ አይቶ ሲወጣ ይበልጥ ተነቃቃች። ነገር ግን አንቶኒ ጎርደን በሜክሲኮው ግብ ጠባቂ ራውል ራንጄል የተሰራበትን ጥፋት ተከትሎ የተገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ሃሪ ኬን ወደ ግብ በመቀየር የእንግሊዝን መሪነት አሳደገው።
እንግሊዝ ጨዋታውን ያረጋጋችው ሲመስል፣ ሃሪ ኬን በራሱ የቅጣት ክልል ውስጥ የብራያን ጉቴሬዝን እግር በመምታቱ የተሰጠውን የፍጹም ቅጣት ምት ራውል ሂሜኔዝ ለሜክሲኮ አስቆጠረ። በከፍተኛ ጫና እና አስጨናቂ ድባብ ውስጥ ቶማስ ቱኸል፣ ዳን በርን እና ጄድ ስፔንስን ቀይረው በማስገባት አምስት ተከላካዮችን ወደ መጠቀም ተመለሱ። በዚህም ለ11 ደቂቃዎች የተሰጠውን የባከነ ሰዓት ጀግንነት በተሞላበት መከላከል አሳልፈው ይህን ድንቅ ድል አስመዝግበዋል።
በሜክሲኮ የእግር ኳስ ታሪክ ትልቁ ተብሎ በተጠራው በዚህ ጨዋታ ላይ፣ እንግሊዞች ምን እንደሚጠብቃቸው ጠንቅቀው ያውቁ ነበር። ከባህር ወለል በላይ ከ7,000 ጫማ በላይ ከፍታ ባለው እና እጅግ ፈታኝ በሆነው በዚህ ስታዲየም፣ የቱኸል ቡድን ያሳየው ብስለት እና ጽናት ትልቅ በራስ መተማመንን የሚሰጠው ነው።
የቡድኑ ኮከቦች ለታላቅ ጨዋታ ታላቅ ብቃት አሳይተዋል። በተለይም ጁድ ቤሊንግሃም ሁለት ግቦችን ከማስቆጠሩም ባሻገር፣ ከእረፍት በፊት የሜክሲኮው ተከላካይ ሴዛር ሞንቴስ አቻ የሚያደርጋትን ግብ ሊያስቆጥር ሲል ያደረገው ወሳኝ ሸርተቴ የግሉን ብቃት ከፍ አድርጎታል። የሜክሲኮን የኃይል አጨዋወት ለማቀዝቀዝ እንግሊዝ ወደ ኋላ እንድታፈገፍግ ያደረጉት ቱኸልም ለታክቲክ ብቃታቸው ትልቅ ምስጋና ይገባቸዋል።
በአንዳንድ የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ላይ ማመንታት ታይቶበት የነበረው ጆርዳን ፒክፎርድ (በተለይ በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር በነበረው ጨዋታ ፣ በአዝቴካው ከፍተኛ ጫና ውስጥ በብሔራዊ ቡድን ታሪኩ ምርጡን ብቃት አሳይቷል።
ለ17ኛ ጊዜ በዓለም ዋንጫው የተሰለፈው እና የፒተር ሺልተንን ክብረ ወሰን የተጋራው ፒክፎርድ፣ ለምን የእንግሊዝ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ እንደሆነ በተግባር አሳይቷል። የሂሜኔዝን ኃይለኛ የጭንቅላት ኳሶች ግራ እና ቀኝ እየበረረ ሲያድን፣ በስታዲየሙ ውስጥ የተፈጠረውን ማዕበል ሁሉ ተቆጣጥሮት አምሽቷል። ይህ ለፒክፎርድም ሆነ ለእንግሊዝ የማይረሳ ምሽት ነበር!
በከባድ ማዕበል ምክንያት ከአንድ ሰዓት መዘግየት በኋላ በተጀመረው እና የትያትር ያህል በሚመስለው በዚህ የስፖርት ምሽት፣ የቶማስ ቱኸል ስብስብ በርካታ ፈተናዎችን አልፏል። በሁለተኛው አጋማሽ መጀመሪያ ላይ ጃሬል ኳንሳህ በቀይ ካርድ ከሜዳ ቢወጣበትም፣ ቡድኑ ጫናውን ተቋቁሞ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ካስመዘገባቸው ታላላቅ ድሎች አንዱን አሳክቷል።
ሜክሲኮ በገዛ ሜዳዋ፣ "ምሽጌ" በምትለው አዝቴካ ባደረገቻቸው 89 ተወዳዳሪ ጨዋታዎች የተሸነፈችው በሁለቱ ብቻ ነበር። ነገር ግን የእንግሊዝ የተረጋጋ አቀራረብ ጨዋታውን ቶሎ እንዲቆጣጠሩ አስችሏቸዋል። በተለይም ድንቁ ጁድ ቤሊንግሃም ከእረፍት በፊት በ98 ሰከንዶች ልዩነት ውስጥ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር እንግሊዝን መሪ አድርጓል።
የእንግሊዙ ግብ ጠባቂ ጆርዳን ፒክፎርድ ራውል ሂሜኔዝ ያደረጋቸውን ሁለት አስቆጣሪ ሙከራዎች በሚያስደንቅ ሁኔታ በማዳን ብቃቱን አሳይቷል። ሆኖም ከእረፍት ሶስት ደቂቃዎች በፊት ጁሊያን ኪኖኔስ በኃይለኛ ምት አንድ ግብ ለሜክሲኮ ማስቆጠሩ አልቀረም።
በደጋፊዎቿ ጩኸት ታጅባ ወደ ፊት የተገፋችው ሜክሲኮ፣ ኳንሳህ በሄሱስ ጋላርዶ ላይ በሰራው አደገኛ ጥፋት ቀይ ካርድ አይቶ ሲወጣ ይበልጥ ተነቃቃች። ነገር ግን አንቶኒ ጎርደን በሜክሲኮው ግብ ጠባቂ ራውል ራንጄል የተሰራበትን ጥፋት ተከትሎ የተገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ሃሪ ኬን ወደ ግብ በመቀየር የእንግሊዝን መሪነት አሳደገው።
እንግሊዝ ጨዋታውን ያረጋጋችው ሲመስል፣ ሃሪ ኬን በራሱ የቅጣት ክልል ውስጥ የብራያን ጉቴሬዝን እግር በመምታቱ የተሰጠውን የፍጹም ቅጣት ምት ራውል ሂሜኔዝ ለሜክሲኮ አስቆጠረ። በከፍተኛ ጫና እና አስጨናቂ ድባብ ውስጥ ቶማስ ቱኸል፣ ዳን በርን እና ጄድ ስፔንስን ቀይረው በማስገባት አምስት ተከላካዮችን ወደ መጠቀም ተመለሱ። በዚህም ለ11 ደቂቃዎች የተሰጠውን የባከነ ሰዓት ጀግንነት በተሞላበት መከላከል አሳልፈው ይህን ድንቅ ድል አስመዝግበዋል።
በሜክሲኮ የእግር ኳስ ታሪክ ትልቁ ተብሎ በተጠራው በዚህ ጨዋታ ላይ፣ እንግሊዞች ምን እንደሚጠብቃቸው ጠንቅቀው ያውቁ ነበር። ከባህር ወለል በላይ ከ7,000 ጫማ በላይ ከፍታ ባለው እና እጅግ ፈታኝ በሆነው በዚህ ስታዲየም፣ የቱኸል ቡድን ያሳየው ብስለት እና ጽናት ትልቅ በራስ መተማመንን የሚሰጠው ነው።
የቡድኑ ኮከቦች ለታላቅ ጨዋታ ታላቅ ብቃት አሳይተዋል። በተለይም ጁድ ቤሊንግሃም ሁለት ግቦችን ከማስቆጠሩም ባሻገር፣ ከእረፍት በፊት የሜክሲኮው ተከላካይ ሴዛር ሞንቴስ አቻ የሚያደርጋትን ግብ ሊያስቆጥር ሲል ያደረገው ወሳኝ ሸርተቴ የግሉን ብቃት ከፍ አድርጎታል። የሜክሲኮን የኃይል አጨዋወት ለማቀዝቀዝ እንግሊዝ ወደ ኋላ እንድታፈገፍግ ያደረጉት ቱኸልም ለታክቲክ ብቃታቸው ትልቅ ምስጋና ይገባቸዋል።
በአንዳንድ የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ላይ ማመንታት ታይቶበት የነበረው ጆርዳን ፒክፎርድ (በተለይ በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር በነበረው ጨዋታ ፣ በአዝቴካው ከፍተኛ ጫና ውስጥ በብሔራዊ ቡድን ታሪኩ ምርጡን ብቃት አሳይቷል።
ለ17ኛ ጊዜ በዓለም ዋንጫው የተሰለፈው እና የፒተር ሺልተንን ክብረ ወሰን የተጋራው ፒክፎርድ፣ ለምን የእንግሊዝ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ እንደሆነ በተግባር አሳይቷል። የሂሜኔዝን ኃይለኛ የጭንቅላት ኳሶች ግራ እና ቀኝ እየበረረ ሲያድን፣ በስታዲየሙ ውስጥ የተፈጠረውን ማዕበል ሁሉ ተቆጣጥሮት አምሽቷል። ይህ ለፒክፎርድም ሆነ ለእንግሊዝ የማይረሳ ምሽት ነበር!
1 month ago
እንግሊዝን ስጋት ላይ የጣለው የአዝቴካ ስታዲየም ከፍታና የዲየጎ ማራዶና የእጅ ግብ ታሪክ።
#ethiopia | በአለም ዋንጫ በ16 ጥሎ ማለፍ ከሚጠበቁ ጨዋታዎች መካከል የጥምር አዘጋጇ ሜክሲኮ ከእንግሊዝ የሚያደርጉት ፍልሚያ ነው። ጨዋታው በታሪካዊው አዝቴካ ስታዲየም ይደረጋል። ይህ ስታዲየም 87523 ተመልካቾች መያዝ የሚችል ፣ በላቲን አሜሪካ በግዝፈቱ ተወዳዳሪ የሌለውና በአለም 8ኛው ትልቅ ስታዲየም ነው።
አዝቴካ ስታዲየም የ1970 እና 1986 ሁለት የአለም ዋንጫ ፍጻሜዎችንም አስተናግዷል።ይህ ስታዲየም ከባህር ጠለል በ2240 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን የብዙ እግር ኳስ ቡድኖችን ትንፋሽ ያቆመ ነው። የእንግሊዝና ሜክሲኮን ጨዋታ ከሜዳ ላይ ፍልሚያው ባሻገር መነጋገሪያ እንዲሆን ያደረገው ቀዳሚ ጉዳይም ነው።
ባለ ሜዳዋ ሜክሲኮ በዚህ ከፍታና ግዙፍ ስታዲየም ካደረገቻቸው 89 የነጥብ ጨዋታዎች የተሸነፈችው 2 ጊዜ ብቻ ነው። ባለፉት 22 ጨዋታዎች ደግሞ አንዱንም አልተሸነፈች።16 ጊዜ አሸንፋ በ6ቱ አቻ ተለያይታለች።
እንግሊዝ በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ሮብ እለት በዲሞክራቲክ ኮንጎ ተፈትና 2 ለ 1 ስታሸንፍ የተጫወተችበት የአትላንታ ስታዲየም ከፍታ 300 ሜትር ብቻ ነበር። አርብ እለት ደግሞ ወደ ሜክሲኮ ተጉዘዋል። ለጨዋታ ከተለመደው ጊዜ አንድ ቀን ቀድመው ቢደርሱም ትንፋሽ የሚያቆመውን አየር ለመልመድ በቂ አልሆነም።
ከልክ ያለፈ ከፍታ ተጫዎቾችን ለኦክስጂን እጥረት ይዳርጋል። ሰውነታቸው አየሩን ወደ ሴሎቻቸው የመግፋት አቅም እንዲያጣ ያደርጋል ይላሉ ባለሙያዎች።
ይህ ደግሞ ተጫዎቾቹ የልብ ምታቸው እንዲፈጥን ፣ ትንፋሽ እንዲያጥራቸው ፣ በፍጥነት የፈሳሽ እጥረት እንዲገጥማቸው ፣ ከፍተኛ ድካም ውስጥ እንዲገቡና የማገገሚያ ጊዜያቸውን እንዲራዘም ያደርጋል።
በተጨማሪም የአየር እጥረቱ ኳስ በሚሞከርበትና ለቡድን አጋር በሚሻማበት ጊዜ ፍጥነትና ከፍታውን የማስቀየር አቅም አለው ተብሏል። ስታዲየሙ ሁሉንም ተጫዎቾች ተጨማሪ አቅም የሚጠይቅ ቢሆንም የግብ ጠባቂዎችን ፈተና ያበዛል ተብሏል። ይህ እግር ኳሳዊ ፈተና ግን ለእንግዳዋ እንግሊዝ ብቻ ሳይሆን ለባለቤቷ ሜክሲኮም የሚያጋጥም ነው።
ሜክሲኮ በአዝቴካ ያላት ታሪካዊ የበላይነት ብቻ ሳይሆን በዚሁ አለም ዋንጫ ካደረገቻቸው 4 ጨዋታዎች 3ቱን ተጫውታበት 3ቱንም አሸንፋለች። በመክፈቻው ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 0 ፣ ቸክ ሪፐብሊክን 3 ለ 0 በምድብ ፣ በ32 ጥሎ ማለፍ ደግሞ ኢኳዶርን 3 ለ 0 ድል አድርጋለች። በ2ኛው የምድብ ጨዋታ ደቡብ ኮሪያን 1 ለ 0 የረታችበት ጨዋታ ብቻ ከአዜቲካ ውጭ ተደርጓል። ሜክሲኮ ያደረገቻቸውን 4ቱንም ጨዋታዎች ስታሸንፍ 8 ግቦችን አስቆጥራ አንድም ሳይቆጠርባት በመውጣት የማጥቃትና የመከላከል አቅሟን አስመስክራለች።
የሶስቱ አናብስት አሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል ይህን የአዝቴካ ስታዲየም የከፍታ ፣ የደጋፊ ሁከትና ጩኸት ፈተና ለመወጣት የታክቲክ ለውጥ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ኳስ በመቆጣጠር ፣ የጨዋታውን ፍጥነት በማዘግየት ፣ ጉልበት በመቆጠብ እድል ሲገኝ ብቻ ለማጥቃት ይገባሉ ተብሏል።
እንግሊዝ በዚህ ስታዲየም በ1986ቱ አለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በአርጀንቲና 2 ለ 1 ከተሸነፈች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ትጫወትበታለች። ለዘመናት የሚታወሰው የዲየጎ ማራዶና " የፈጣሪ እጅ ግብ " ለእንግሊዝ ሽንፈት ምክንያት መሆኑ ይታወሳል።
አርብ እለት ከብሪታኒያና ሜክሲኮኮ የወጡ መረጃዎች ዛሬ በሜክሲኮ ሲቲ አውሎ ንፋስና ጎርፍ የሚያስከትል የአየር ሁኔታ ሊከሰት እንደሚችል ስለተገመተ፣ ፊፋ የጨዋታ መርሃብ ግብር የማስተካከል እቅድ እንዳለው ቢነገርም ቀድሞ በተያዘለት ሰአት ይካሄዳል።
በሁሴን ግዛው
#ethiopia | በአለም ዋንጫ በ16 ጥሎ ማለፍ ከሚጠበቁ ጨዋታዎች መካከል የጥምር አዘጋጇ ሜክሲኮ ከእንግሊዝ የሚያደርጉት ፍልሚያ ነው። ጨዋታው በታሪካዊው አዝቴካ ስታዲየም ይደረጋል። ይህ ስታዲየም 87523 ተመልካቾች መያዝ የሚችል ፣ በላቲን አሜሪካ በግዝፈቱ ተወዳዳሪ የሌለውና በአለም 8ኛው ትልቅ ስታዲየም ነው።
አዝቴካ ስታዲየም የ1970 እና 1986 ሁለት የአለም ዋንጫ ፍጻሜዎችንም አስተናግዷል።ይህ ስታዲየም ከባህር ጠለል በ2240 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን የብዙ እግር ኳስ ቡድኖችን ትንፋሽ ያቆመ ነው። የእንግሊዝና ሜክሲኮን ጨዋታ ከሜዳ ላይ ፍልሚያው ባሻገር መነጋገሪያ እንዲሆን ያደረገው ቀዳሚ ጉዳይም ነው።
ባለ ሜዳዋ ሜክሲኮ በዚህ ከፍታና ግዙፍ ስታዲየም ካደረገቻቸው 89 የነጥብ ጨዋታዎች የተሸነፈችው 2 ጊዜ ብቻ ነው። ባለፉት 22 ጨዋታዎች ደግሞ አንዱንም አልተሸነፈች።16 ጊዜ አሸንፋ በ6ቱ አቻ ተለያይታለች።
እንግሊዝ በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ሮብ እለት በዲሞክራቲክ ኮንጎ ተፈትና 2 ለ 1 ስታሸንፍ የተጫወተችበት የአትላንታ ስታዲየም ከፍታ 300 ሜትር ብቻ ነበር። አርብ እለት ደግሞ ወደ ሜክሲኮ ተጉዘዋል። ለጨዋታ ከተለመደው ጊዜ አንድ ቀን ቀድመው ቢደርሱም ትንፋሽ የሚያቆመውን አየር ለመልመድ በቂ አልሆነም።
ከልክ ያለፈ ከፍታ ተጫዎቾችን ለኦክስጂን እጥረት ይዳርጋል። ሰውነታቸው አየሩን ወደ ሴሎቻቸው የመግፋት አቅም እንዲያጣ ያደርጋል ይላሉ ባለሙያዎች።
ይህ ደግሞ ተጫዎቾቹ የልብ ምታቸው እንዲፈጥን ፣ ትንፋሽ እንዲያጥራቸው ፣ በፍጥነት የፈሳሽ እጥረት እንዲገጥማቸው ፣ ከፍተኛ ድካም ውስጥ እንዲገቡና የማገገሚያ ጊዜያቸውን እንዲራዘም ያደርጋል።
በተጨማሪም የአየር እጥረቱ ኳስ በሚሞከርበትና ለቡድን አጋር በሚሻማበት ጊዜ ፍጥነትና ከፍታውን የማስቀየር አቅም አለው ተብሏል። ስታዲየሙ ሁሉንም ተጫዎቾች ተጨማሪ አቅም የሚጠይቅ ቢሆንም የግብ ጠባቂዎችን ፈተና ያበዛል ተብሏል። ይህ እግር ኳሳዊ ፈተና ግን ለእንግዳዋ እንግሊዝ ብቻ ሳይሆን ለባለቤቷ ሜክሲኮም የሚያጋጥም ነው።
ሜክሲኮ በአዝቴካ ያላት ታሪካዊ የበላይነት ብቻ ሳይሆን በዚሁ አለም ዋንጫ ካደረገቻቸው 4 ጨዋታዎች 3ቱን ተጫውታበት 3ቱንም አሸንፋለች። በመክፈቻው ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 0 ፣ ቸክ ሪፐብሊክን 3 ለ 0 በምድብ ፣ በ32 ጥሎ ማለፍ ደግሞ ኢኳዶርን 3 ለ 0 ድል አድርጋለች። በ2ኛው የምድብ ጨዋታ ደቡብ ኮሪያን 1 ለ 0 የረታችበት ጨዋታ ብቻ ከአዜቲካ ውጭ ተደርጓል። ሜክሲኮ ያደረገቻቸውን 4ቱንም ጨዋታዎች ስታሸንፍ 8 ግቦችን አስቆጥራ አንድም ሳይቆጠርባት በመውጣት የማጥቃትና የመከላከል አቅሟን አስመስክራለች።
የሶስቱ አናብስት አሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል ይህን የአዝቴካ ስታዲየም የከፍታ ፣ የደጋፊ ሁከትና ጩኸት ፈተና ለመወጣት የታክቲክ ለውጥ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ኳስ በመቆጣጠር ፣ የጨዋታውን ፍጥነት በማዘግየት ፣ ጉልበት በመቆጠብ እድል ሲገኝ ብቻ ለማጥቃት ይገባሉ ተብሏል።
እንግሊዝ በዚህ ስታዲየም በ1986ቱ አለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በአርጀንቲና 2 ለ 1 ከተሸነፈች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ትጫወትበታለች። ለዘመናት የሚታወሰው የዲየጎ ማራዶና " የፈጣሪ እጅ ግብ " ለእንግሊዝ ሽንፈት ምክንያት መሆኑ ይታወሳል።
አርብ እለት ከብሪታኒያና ሜክሲኮኮ የወጡ መረጃዎች ዛሬ በሜክሲኮ ሲቲ አውሎ ንፋስና ጎርፍ የሚያስከትል የአየር ሁኔታ ሊከሰት እንደሚችል ስለተገመተ፣ ፊፋ የጨዋታ መርሃብ ግብር የማስተካከል እቅድ እንዳለው ቢነገርም ቀድሞ በተያዘለት ሰአት ይካሄዳል።
በሁሴን ግዛው
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ፈረንሳይ ፓራጓይን አሸንፋ ወደ ሩብ ፍጻሜ አለፈች፤
* የአፍሪካ ተወካዮች በመጨረሻ ደቂቃዎች ተሰናበቱ
#ethiopia | በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16 ቡድኖች ጥሎ ማለፍ ዙር ፈረንሳይ ፓራጓይን 1 ለ0 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ አልፋለች።
የጨዋታውን ብቸኛ ግብ በ70ኛው ደቂቃ ኪሊያን ምባፔ ከፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።
በሩብ ፍጻሜውም ፈረንሳይ ከሞሮኮ ጋር ትፋለማለች።
በሌላ በኩል የአፍሪካ ተወካዮች ታሪካዊ ውጤት ለማስመዝገብ በጣም ተቃርበው ቢደርሱም በመጨረሻ ደቂቃዎች ልፋታቸው ሳይሳካ ቀርቷል።
ደቡብ አፍሪካ በ91ኛው ደቂቃ፣
ኮትዲቯር በ87ኛው ደቂቃ፣
ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በ86ኛው ደቂቃ
እንዲሁም ኬፕ ቨርዴ በ111ኛው ደቂቃ ከውድድሩ ተሰናብተዋል።
ሴኔጋልም እስከ ተጨማሪ ሰዓት 120ኛው ደቂቃ ድረስ ተፋልማ በመጨረሻ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
የእነዚህ ቡድኖች መሰናበት የአፍሪካ እግር ኳስ ደጋፊዎችን እጅግ አሳዝኗል፤ ቡድኖቹ ታሪክ ለመጻፍ በጣም ተቃርበው ቢደርሱም በመጨረሻ ደቂቃዎች የውድድሩን ጨካኝ ተፈጥሮ በድጋሚ ተጋፍጠዋል።
* የአፍሪካ ተወካዮች በመጨረሻ ደቂቃዎች ተሰናበቱ
#ethiopia | በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16 ቡድኖች ጥሎ ማለፍ ዙር ፈረንሳይ ፓራጓይን 1 ለ0 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ አልፋለች።
የጨዋታውን ብቸኛ ግብ በ70ኛው ደቂቃ ኪሊያን ምባፔ ከፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።
በሩብ ፍጻሜውም ፈረንሳይ ከሞሮኮ ጋር ትፋለማለች።
በሌላ በኩል የአፍሪካ ተወካዮች ታሪካዊ ውጤት ለማስመዝገብ በጣም ተቃርበው ቢደርሱም በመጨረሻ ደቂቃዎች ልፋታቸው ሳይሳካ ቀርቷል።
ደቡብ አፍሪካ በ91ኛው ደቂቃ፣
ኮትዲቯር በ87ኛው ደቂቃ፣
ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በ86ኛው ደቂቃ
እንዲሁም ኬፕ ቨርዴ በ111ኛው ደቂቃ ከውድድሩ ተሰናብተዋል።
ሴኔጋልም እስከ ተጨማሪ ሰዓት 120ኛው ደቂቃ ድረስ ተፋልማ በመጨረሻ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
የእነዚህ ቡድኖች መሰናበት የአፍሪካ እግር ኳስ ደጋፊዎችን እጅግ አሳዝኗል፤ ቡድኖቹ ታሪክ ለመጻፍ በጣም ተቃርበው ቢደርሱም በመጨረሻ ደቂቃዎች የውድድሩን ጨካኝ ተፈጥሮ በድጋሚ ተጋፍጠዋል።
1 month ago
የአፍሪካ የኳስ ገጽታ
* ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በክብር ተሰናበተች፤ ሴኔጋል በመጨረሻ ደቂቃዎች የልብ ስብራት አስተናገደች
#ethiopia | በዓለም ዋንጫው የጥሎ ማለፍ ፉክክር ሁለት የአፍሪካ ቡድኖች በተለያየ መንገድ ቢሰናበቱም፣ ባሳዩት ተጋድሎና አፈጻጸም የእግር ኳስ አድናቂዎችን ልብ አሸንፈዋል።
ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ፤ ሽንፈት ቢደርስባትም ተስፋን አስመለሰች
ከ1974 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ የተሳተፈችው ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በውድድሩ አስደናቂ ጉዞ አድርጋለች።
ቡድኑ በታሪኩ የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ድል በኡዝቤኪስታን ላይ ሲያስመዘግብ፣ ከፖርቱጋል ጋርም አቻ ተለያይቷል። በጥሎ ማለፉ ደግሞ ከእንግሊዝ ጋር እስከ መጨረሻ ደቂቃዎች ድረስ ተፎካክሮ በጠባብ ልዩነት ተሸንፎ ከውድድሩ ተሰናብቷል።
ምንም እንኳን ጉዞው በሽንፈት ቢያበቃም፣ የ"ሌስ ሌኦፓርድስ" አፈጻጸም በመላው ኮንጎ እንደገና ተስፋና እምነትን አስመልሷል።
ሴኔጋል፤ ከድል ወደ ልብ ስብራት
ሴኔጋል ደግሞ በውድድሩ እጅግ አሳዛኝ ከሆኑ ሽንፈቶች አንዱን አስተናግዳለች።
የታራንጋ አንበሶች እስከ 85ኛው ደቂቃ 2-0 እየመሩ ወደ 16 ቡድኖች ዙር መግባታቸውን አረጋግጠው የነበሩ ቢመስልም፣ ቤልጂየም በመጨረሻ ደቂቃዎች ሁለት ጎሎችን በማስቆጠር ጨዋታውን ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ አሸጋግራለች።
ድራማው ግን በዚያ አላበቃም። በ120+5 ደቂቃ በVAR የተረጋገጠ ፔናሊቲ ለቤልጂየም ተሰጥቶ ወደ ጎል በመቀየሩ ሴኔጋል 3-2 ተሸንፋ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
በአጭር ጊዜ ውስጥ ከድል ተስፋ ወደ መራራ ሽንፈት የተቀየረው ውጤት፣ ለሴኔጋል ተጫዋቾችና ደጋፊዎች የማይረሳ የልብ ስብራት ሆኗል።
* ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በክብር ተሰናበተች፤ ሴኔጋል በመጨረሻ ደቂቃዎች የልብ ስብራት አስተናገደች
#ethiopia | በዓለም ዋንጫው የጥሎ ማለፍ ፉክክር ሁለት የአፍሪካ ቡድኖች በተለያየ መንገድ ቢሰናበቱም፣ ባሳዩት ተጋድሎና አፈጻጸም የእግር ኳስ አድናቂዎችን ልብ አሸንፈዋል።
ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ፤ ሽንፈት ቢደርስባትም ተስፋን አስመለሰች
ከ1974 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ የተሳተፈችው ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በውድድሩ አስደናቂ ጉዞ አድርጋለች።
ቡድኑ በታሪኩ የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ድል በኡዝቤኪስታን ላይ ሲያስመዘግብ፣ ከፖርቱጋል ጋርም አቻ ተለያይቷል። በጥሎ ማለፉ ደግሞ ከእንግሊዝ ጋር እስከ መጨረሻ ደቂቃዎች ድረስ ተፎካክሮ በጠባብ ልዩነት ተሸንፎ ከውድድሩ ተሰናብቷል።
ምንም እንኳን ጉዞው በሽንፈት ቢያበቃም፣ የ"ሌስ ሌኦፓርድስ" አፈጻጸም በመላው ኮንጎ እንደገና ተስፋና እምነትን አስመልሷል።
ሴኔጋል፤ ከድል ወደ ልብ ስብራት
ሴኔጋል ደግሞ በውድድሩ እጅግ አሳዛኝ ከሆኑ ሽንፈቶች አንዱን አስተናግዳለች።
የታራንጋ አንበሶች እስከ 85ኛው ደቂቃ 2-0 እየመሩ ወደ 16 ቡድኖች ዙር መግባታቸውን አረጋግጠው የነበሩ ቢመስልም፣ ቤልጂየም በመጨረሻ ደቂቃዎች ሁለት ጎሎችን በማስቆጠር ጨዋታውን ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ አሸጋግራለች።
ድራማው ግን በዚያ አላበቃም። በ120+5 ደቂቃ በVAR የተረጋገጠ ፔናሊቲ ለቤልጂየም ተሰጥቶ ወደ ጎል በመቀየሩ ሴኔጋል 3-2 ተሸንፋ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
በአጭር ጊዜ ውስጥ ከድል ተስፋ ወደ መራራ ሽንፈት የተቀየረው ውጤት፣ ለሴኔጋል ተጫዋቾችና ደጋፊዎች የማይረሳ የልብ ስብራት ሆኗል።
1 month ago
የኮንጎው "ሕያው ሐውልት" ሉሙምባ ቬያ
#ethiopia | በእግርኳስ ዓለም ውስጥ ለቡድናቸው ያላቸውን ስሜት በተለየና በሚያስገርም መንገድ የሚገልጹ ደጋፊዎች አሉ። ነገር ግን እንደ ሚሼል ንኩካ ወይም በቅጽል ስሙ "ሉሙምባ ቪያ" ያለ ቁርጠኛ እና ልዩ ደጋፊ ማግኘት በላል አይሆንም!
ይህ ሰው በስታዲየም ውስጥ የሚፈጥረው ድባብ የስፖርቱ ዓለም ካያቸው እጅግ አስደናቂ ትዕይንቶች አንዱ ነው።
ሉሙምባ ቬያ ማነው? ለምንስ ልዩ ሆነ?
ይህ ደጋፊ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ በሚያደርግበት ጊዜ ጨዋታው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ ለ90 ደቂቃ ሙሉ ሳያንቀሳቅስ ልክ እንደ ሐውልት ቆሞ ጨዋታውን ይታደማል።
"ሉሙምባ ቬያ'' የኮንጎን ታዋቂ የነጻነት ታጋይ እና የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ፓትሪስ ሉሙምባን በመልክ በመምሰል ነው።
እግርኳስን ከሀገር ታሪክ ጋር በማሰናሰል የኮንጎን ገጽታ በዓለም አቀፍ መድረክ እያስተዋወቀ ይገኛል። እስከ 2026ቱ የዓለም ዋንጫ ጉዞ ድረስ የኮንጎ ብሔራዊ ቡድን በሄደበት ሁሉ ትልቅ ትኩረትን እየሳበ የሚገኝ እውነተኛ ደጋፊ ነው።
አንዳንዶች እግርኳስ ስፖርታዊ ጨዋታ ብቻ ሊሆን ይችላል ለሉሙምባ ቬያ ግን ሀገራዊ ማንነትን ታሪክንና ፍቅርን ለዓለም የሚያሳይበት ትልቅ የጥበብ መድረክ ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በእግርኳስ ዓለም ውስጥ ለቡድናቸው ያላቸውን ስሜት በተለየና በሚያስገርም መንገድ የሚገልጹ ደጋፊዎች አሉ። ነገር ግን እንደ ሚሼል ንኩካ ወይም በቅጽል ስሙ "ሉሙምባ ቪያ" ያለ ቁርጠኛ እና ልዩ ደጋፊ ማግኘት በላል አይሆንም!
ይህ ሰው በስታዲየም ውስጥ የሚፈጥረው ድባብ የስፖርቱ ዓለም ካያቸው እጅግ አስደናቂ ትዕይንቶች አንዱ ነው።
ሉሙምባ ቬያ ማነው? ለምንስ ልዩ ሆነ?
ይህ ደጋፊ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ በሚያደርግበት ጊዜ ጨዋታው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ ለ90 ደቂቃ ሙሉ ሳያንቀሳቅስ ልክ እንደ ሐውልት ቆሞ ጨዋታውን ይታደማል።
"ሉሙምባ ቬያ'' የኮንጎን ታዋቂ የነጻነት ታጋይ እና የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ፓትሪስ ሉሙምባን በመልክ በመምሰል ነው።
እግርኳስን ከሀገር ታሪክ ጋር በማሰናሰል የኮንጎን ገጽታ በዓለም አቀፍ መድረክ እያስተዋወቀ ይገኛል። እስከ 2026ቱ የዓለም ዋንጫ ጉዞ ድረስ የኮንጎ ብሔራዊ ቡድን በሄደበት ሁሉ ትልቅ ትኩረትን እየሳበ የሚገኝ እውነተኛ ደጋፊ ነው።
አንዳንዶች እግርኳስ ስፖርታዊ ጨዋታ ብቻ ሊሆን ይችላል ለሉሙምባ ቬያ ግን ሀገራዊ ማንነትን ታሪክንና ፍቅርን ለዓለም የሚያሳይበት ትልቅ የጥበብ መድረክ ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
1 month ago
ሃሪ ኬን እንግሊዝን ታደገ፤ ሶስቱ አንበሶች ዲሞክራቲክ ኮንጎን አሸንፈው ወደ 16ቱ ተቀላቀሉ
#ethiopia | በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የዲሞክራቲክ ኮንጎን አቻውን 2 ለ 1 በሆነ ጠባብ ውጤት በመርታት ወደ 16ቱ መግባቱን አረጋግጧል።
ጨዋታው እንደተጀመረ ብርቱ ፉክክር ያስመለከተ ሲሆን፣ የዲሞክራቲክ ኮንጎው "ብሪያን ሲፔንጋ" ገና በ7ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠራት ቀደምት ግብ ኮንጎውያንን መሪ ማድረግ ችላ ነበር።
እንግሊዞች ግብ ከተቆጠረባቸው በኋላ የአቻነትን ግብ ለመፈለግ ከፍተኛ ጫና ፈጥረው ቢጫወቱም፣ የመጀመሪያው አጋማሽ በዲሞክራቲክ ኮንጎ 1 ለ 0 መሪነት ተጠናቋል።
በሁለተኛው አጋማሽ ተጭነው መጫወታቸውን የቀጠሉት እንግሊዞች፣ ጨዋታው ሊጠናቀቅ 15 ደቂቃዎች ሲቀሩት ነው የድል አቅጣጫቸውን የቀየሩት።
ድንቅ ብቃቱን ያሳየው አንጋፋው አጥቂ ሪ ኬን በ75ኛው ደቂቃ ላይ የመጀመሪያውን ግብ አስቆጥሮ ቡድኑን አቻ ሲያደርግ፣ ከአስር ደቂቃዎች በኋላ በ86ኛው ደቂቃ ላይ ሁለተኛዋንና ለአሸናፊነት ያበቃቻቸውን ወሳኝ ግብ ከመረብ አሳርፏል።
"ይህ ድል የቡድናችንን የአእምሮ ጥንካሬ ያሳየ ነው፤ ተስፋ ሳንቆርጥ እስከ መጨረሻው ተዋግተናል" — የእንግሊዝ ደጋፊዎች አስተያየት።
የቀጣይ ዙር ፈተና
ዲሞክራቲክ ኮንጎን ያሸነፈችው እንግሊዝ በቀጣዩ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ዙር ከውድድሩ አስተናጋጅ ሜክሲኮ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
ይህ ጨዋታ በደጋፊዎች ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅ ሲሆን፣ እንግሊዝ ከሜክሲኮ ብርቱ ፈተና እንደሚጠብቃት የስፖርት ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።
#ethiopia | በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የዲሞክራቲክ ኮንጎን አቻውን 2 ለ 1 በሆነ ጠባብ ውጤት በመርታት ወደ 16ቱ መግባቱን አረጋግጧል።
ጨዋታው እንደተጀመረ ብርቱ ፉክክር ያስመለከተ ሲሆን፣ የዲሞክራቲክ ኮንጎው "ብሪያን ሲፔንጋ" ገና በ7ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠራት ቀደምት ግብ ኮንጎውያንን መሪ ማድረግ ችላ ነበር።
እንግሊዞች ግብ ከተቆጠረባቸው በኋላ የአቻነትን ግብ ለመፈለግ ከፍተኛ ጫና ፈጥረው ቢጫወቱም፣ የመጀመሪያው አጋማሽ በዲሞክራቲክ ኮንጎ 1 ለ 0 መሪነት ተጠናቋል።
በሁለተኛው አጋማሽ ተጭነው መጫወታቸውን የቀጠሉት እንግሊዞች፣ ጨዋታው ሊጠናቀቅ 15 ደቂቃዎች ሲቀሩት ነው የድል አቅጣጫቸውን የቀየሩት።
ድንቅ ብቃቱን ያሳየው አንጋፋው አጥቂ ሪ ኬን በ75ኛው ደቂቃ ላይ የመጀመሪያውን ግብ አስቆጥሮ ቡድኑን አቻ ሲያደርግ፣ ከአስር ደቂቃዎች በኋላ በ86ኛው ደቂቃ ላይ ሁለተኛዋንና ለአሸናፊነት ያበቃቻቸውን ወሳኝ ግብ ከመረብ አሳርፏል።
"ይህ ድል የቡድናችንን የአእምሮ ጥንካሬ ያሳየ ነው፤ ተስፋ ሳንቆርጥ እስከ መጨረሻው ተዋግተናል" — የእንግሊዝ ደጋፊዎች አስተያየት።
የቀጣይ ዙር ፈተና
ዲሞክራቲክ ኮንጎን ያሸነፈችው እንግሊዝ በቀጣዩ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ዙር ከውድድሩ አስተናጋጅ ሜክሲኮ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
ይህ ጨዋታ በደጋፊዎች ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅ ሲሆን፣ እንግሊዝ ከሜክሲኮ ብርቱ ፈተና እንደሚጠብቃት የስፖርት ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።
1 month ago
እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን 2 ለ 1 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች
**************************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን 2 ለ 1 በመርታት ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋግራለች።
እንግሊዝን ለድል ያበቋትን ሁለት ግቦች ሃሪ ኬን በ75ኛው እና በ86ኛው ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር፤ ለዲሞክራቲክ ኮንጎ ብሪያን ሲፔንጋ በ7ኛው ደቂቃ ላይ ብቸኛ ግብ አስቆጥሯል።
እንግሊዝ በቀጣይ ዙር ጨዋታዋ ከሜክሲኮ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
#worldcup #england #drcongo #sports #ebc #fifa2026
**************************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን 2 ለ 1 በመርታት ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋግራለች።
እንግሊዝን ለድል ያበቋትን ሁለት ግቦች ሃሪ ኬን በ75ኛው እና በ86ኛው ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር፤ ለዲሞክራቲክ ኮንጎ ብሪያን ሲፔንጋ በ7ኛው ደቂቃ ላይ ብቸኛ ግብ አስቆጥሯል።
እንግሊዝ በቀጣይ ዙር ጨዋታዋ ከሜክሲኮ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
#worldcup #england #drcongo #sports #ebc #fifa2026
1 month ago
እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን 2 ለ 1 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቅላለች።
ምሽት 1 ሰዓት ላይ በአትላንታ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የእንግሊዝን የማሸነፊያ ግቦች ሃሪ ኬን አስቆጥሯል፡፡
ዲሞክራቲክ ኮንጎ በጨዋታው ጥሩ እንቅስቃሴ በማድረግ እንዲሁም አስቀድማ ግብ በማስቆጠር ጥሩ ጊዜን ማሳለፍ ብትችልም አሳዛኝ ተሸናፊ በመሆን ከውድድሩ ተሰናብታለች፡፡
እንግሊዝ ሩብ ፍጻሜውን ለመቀላቀል ከሜክሲኮ ጋር በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ትፋለማለች፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን 2 ለ 1 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቅላለች።
ምሽት 1 ሰዓት ላይ በአትላንታ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የእንግሊዝን የማሸነፊያ ግቦች ሃሪ ኬን አስቆጥሯል፡፡
ዲሞክራቲክ ኮንጎ በጨዋታው ጥሩ እንቅስቃሴ በማድረግ እንዲሁም አስቀድማ ግብ በማስቆጠር ጥሩ ጊዜን ማሳለፍ ብትችልም አሳዛኝ ተሸናፊ በመሆን ከውድድሩ ተሰናብታለች፡፡
እንግሊዝ ሩብ ፍጻሜውን ለመቀላቀል ከሜክሲኮ ጋር በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ትፋለማለች፡፡
Sponsored by
Surafel
1 month ago
አሜሪካ በሩዋንዳ ወርቅ ማጣሪያ ላይ ማዕቀብ ጣለች
አሜሪካ በሩዋንዳ የሚገኘውን ጋሳቦ ጎልድ ሪፋይነሪ ጨምሮ ከሶስት የሩዋንዳ ማዕድን ኩባንያዎች እና ከፍተኛ አመራሮቻቸው ላይ አዲስ ማዕቀብ መጣሏን የውጭ ሀብት ቁጥጥር ቢሮ አስታውቋል።
ማዕቀቡ የተጣለባቸው የኩባንያው ሊቀመንበር ዣን ማሊክ ካሊማ እና ዋና ስራ አስኪያጁ ቦስኮ ካዮቦትሲ ሲሆኑ፣ ከእነርሱ ጋር በተያያዘ ቡጋምቢራ ማይንስ፣ዎልፍራም ማይኒንግ እና ርዊንክዋቩ ማይኒንግ ኮርፖሬሽን የተባሉ ተቋማትም በዝርዝሩ ውስጥ ተካተዋል።
እንደ አሜሪካ የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ፣ ማጣሪያው በምስራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኤም23 አማፂያን ቁጥጥር ስር ካሉ አካባቢዎች የሚመጣውን ወርቅ በህገ-ወጥ መንገድ በማሸሽ እና በህጋዊ የንግድ ስርዓት ውስጥ በመደበቅ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል።
በፈረንጆቹ 2026 መጀመሪያ ላይ ብቻ ከ60 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ በህገ-ወጥ መንገድ መተላለፉ የተጠቆመ ሲሆን፣ ሂደቱም በአንዳንድ አጋጣሚዎች በሩዋንዳ መከላከያ ሰራዊት ጥበቃ ታጅቦ እንደነበር የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
ይህ እርምጃ ለአማፂ ቡድኑ የሚፈሰውን የገቢ ምንጭ በማድረቅ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሰላም ስምምነት ለማጠናከር ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
ማዕቀቡ በኢኮኖሚው ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ ከፍተኛ እንደሚሆን የሚጠበቅ ሲሆን፣ የአሜሪካ ዜጎችና ኩባንያዎች ከተጠቀሱት አካላት ጋር የንግድ ግንኙነት እንዳያደርጉ ታግደዋል።
ሩዋንዳ በበኩሏ በአማፂያኑ ላይ ድጋፍ እንደምታደርግ ወይም ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ እንደምታመቻች የሚነገረውን ክስ በይፋ አስተባብላለች።
አሜሪካ በሩዋንዳ የሚገኘውን ጋሳቦ ጎልድ ሪፋይነሪ ጨምሮ ከሶስት የሩዋንዳ ማዕድን ኩባንያዎች እና ከፍተኛ አመራሮቻቸው ላይ አዲስ ማዕቀብ መጣሏን የውጭ ሀብት ቁጥጥር ቢሮ አስታውቋል።
ማዕቀቡ የተጣለባቸው የኩባንያው ሊቀመንበር ዣን ማሊክ ካሊማ እና ዋና ስራ አስኪያጁ ቦስኮ ካዮቦትሲ ሲሆኑ፣ ከእነርሱ ጋር በተያያዘ ቡጋምቢራ ማይንስ፣ዎልፍራም ማይኒንግ እና ርዊንክዋቩ ማይኒንግ ኮርፖሬሽን የተባሉ ተቋማትም በዝርዝሩ ውስጥ ተካተዋል።
እንደ አሜሪካ የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ፣ ማጣሪያው በምስራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኤም23 አማፂያን ቁጥጥር ስር ካሉ አካባቢዎች የሚመጣውን ወርቅ በህገ-ወጥ መንገድ በማሸሽ እና በህጋዊ የንግድ ስርዓት ውስጥ በመደበቅ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል።
በፈረንጆቹ 2026 መጀመሪያ ላይ ብቻ ከ60 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ በህገ-ወጥ መንገድ መተላለፉ የተጠቆመ ሲሆን፣ ሂደቱም በአንዳንድ አጋጣሚዎች በሩዋንዳ መከላከያ ሰራዊት ጥበቃ ታጅቦ እንደነበር የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
ይህ እርምጃ ለአማፂ ቡድኑ የሚፈሰውን የገቢ ምንጭ በማድረቅ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሰላም ስምምነት ለማጠናከር ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
ማዕቀቡ በኢኮኖሚው ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ ከፍተኛ እንደሚሆን የሚጠበቅ ሲሆን፣ የአሜሪካ ዜጎችና ኩባንያዎች ከተጠቀሱት አካላት ጋር የንግድ ግንኙነት እንዳያደርጉ ታግደዋል።
ሩዋንዳ በበኩሏ በአማፂያኑ ላይ ድጋፍ እንደምታደርግ ወይም ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ እንደምታመቻች የሚነገረውን ክስ በይፋ አስተባብላለች።
1 month ago
እንግሊዝ ፓናማን 2-0 አሸነፈች
#ethiopia | በ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ 12 የመጨረሻ ጨዋታ እንግሊዝ ፓናማን 2-0 በማሸነፍ ምድቧን በአንደኝነት አጠናቃለች። በኒው ጀርሲ በሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ እንግሊዝ በመጀመሪያው አጋማሽ ተቸግራ ብትታይም፣ በሁለተኛው 45 ደቂቃ ያሳየችው ብልጫ ድልን አስገኝቶላታል።
ቤሊንግሃም የጨዋታውን አቅጣጫ ቀየረ
የእንግሊዝ አማካይ ጁድ ቤሊንግሃም የጨዋታው ዋነኛ ተጫዋች ሆኖ ተገኝቷል። በ62ኛው ደቂቃ የመጀመሪያውን ጎል ካስቆጠረ በኋላ፣ ከአምስት ደቂቃዎች በኋላ ለካፒቴኑ ሃሪ ኬን ሁለተኛውን ጎል ያስቆጠረ ድንቅ አሲስት አድርጓል።
የስካይ ስፖርትስ ተንታኝ ጋሪ ኔቪል ከጨዋታው በኋላ፣
"ጁድ ቤሊንግሃም ፍጹም ልዕለ ኮከብ ነው፤ የጨዋታውም ምርጥ ተጫዋች ነበር" ሲል አድናቆቱን ገልጿል።
ሃሪ ኬን ታሪክ ሰራ
ካፒቴኑ ሃሪ ኬን በጭንቅላት ያስቆጠረው ጎል በዓለም ዋንጫ 11ኛ ጎሉ ሆኖ ተመዝግቧል። በዚህም ጋሪ ሊኔከርን በመብለጥ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ከፍተኛውን የጎል ቁጥር ያስመዘገበ እንግሊዛዊ ተጫዋች ሆኗል።
እንግሊዝ ያሳየችው ጥንካሬና ድክመት
እንግሊዝ በመጀመሪያው አጋማሽ የፓናማን ዝቅተኛ የመከላከል አደረጃጀት (Low Block) ለመስበር ተቸግራ ነበር። የጎል ዕድሎቿም አነስተኛ ነበሩ፣ የቡድኑም እንቅስቃሴ ከሚጠበቀው በታች መሆኑን ተንታኞች ጠቁመዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በቀኝ ተከላካይ ክፍል የተፈጠረው የጉዳት ችግር ለአሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል አሳሳቢ ሆኗል። ሬስ ጄምስና ትሬንት አሌክሳንደር-አርኖልድ በጉዳት ከሜዳ ውጭ በመሆናቸው በቦታቸው የተሰለፈው ጃሬል ኳንሳ በጨዋታው ውስጥ ጉዳት አስተናግዶ ወጥቷል።
ፓናማ ተጋድላ ተሸነፈች
ፓናማ በመጀመሪያው አጋማሽ እንግሊዝን በጥሩ ሁኔታ በመቆጣጠር በፈጣን መልሶ ማጥቃት አደገኛ እድሎችን ፈጥራለች። ሆሴ ፋጃርዶ ያስቆጠረው ጎልም በኦፍሳይድ ተሰርዟል።
ሆኖም በሁለተኛው አጋማሽ የታክቲክ ትኩረቷን በማጣቷ በአምስት ደቂቃዎች ውስጥ ሁለት ጎሎችን አስተናግዳ ከምድቡ በሽንፈት ተሰናብታለች።
የዓለም ሚዲያ ምላሽ
የዓለም ስፖርት ሚዲያዎች አሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል በሁለተኛው አጋማሽ ያደረገውን ስልታዊ ለውጥ አድንቀዋል።
ቱሄልም ከጨዋታው በኋላ፣
"ውድድሩ እየተራመደ በሄደ ቁጥር እኛም እየጠነከርን እንሄዳለን።"
በማለት በቡድኑ ላይ ያለውን እምነት ገልጿል።
ከ82,000 በላይ ደጋፊዎች በሜትላይፍ ስታዲየም ተገኝተው ጨዋታውን በቀጥታ ተከታትለዋል። የስታዲየሙ ድባብም በበርካቶች "እንደ ዌምብሊ ስታዲየም" ተመሳስሎ ተገልጿል።
ወደ ጥሎ ማለፍ
እንግሊዝ ምድቧን በአንደኝነት በማጠናቀቅ ወደ 32 ቡድኖች ጥሎ ማለፍ በመግባት ጥሩ መነቃቃት ፈጥራለች። የዓለም ስፖርት ሚዲያዎችም ቡድኑ በቀጣዩ ዙር ከሴኔጋል ወይም ከዲ.አር. ኮንጎ ጋር የሚያደርገውን ጨዋታ በተሻለ መንፈስ እንደሚገጥም ትንበያቸውን አቅርበዋል።
አለባቸው ደሳለኝ አበሻ | ለንደን 🇬🇧
#ethiopia | በ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ 12 የመጨረሻ ጨዋታ እንግሊዝ ፓናማን 2-0 በማሸነፍ ምድቧን በአንደኝነት አጠናቃለች። በኒው ጀርሲ በሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ እንግሊዝ በመጀመሪያው አጋማሽ ተቸግራ ብትታይም፣ በሁለተኛው 45 ደቂቃ ያሳየችው ብልጫ ድልን አስገኝቶላታል።
ቤሊንግሃም የጨዋታውን አቅጣጫ ቀየረ
የእንግሊዝ አማካይ ጁድ ቤሊንግሃም የጨዋታው ዋነኛ ተጫዋች ሆኖ ተገኝቷል። በ62ኛው ደቂቃ የመጀመሪያውን ጎል ካስቆጠረ በኋላ፣ ከአምስት ደቂቃዎች በኋላ ለካፒቴኑ ሃሪ ኬን ሁለተኛውን ጎል ያስቆጠረ ድንቅ አሲስት አድርጓል።
የስካይ ስፖርትስ ተንታኝ ጋሪ ኔቪል ከጨዋታው በኋላ፣
"ጁድ ቤሊንግሃም ፍጹም ልዕለ ኮከብ ነው፤ የጨዋታውም ምርጥ ተጫዋች ነበር" ሲል አድናቆቱን ገልጿል።
ሃሪ ኬን ታሪክ ሰራ
ካፒቴኑ ሃሪ ኬን በጭንቅላት ያስቆጠረው ጎል በዓለም ዋንጫ 11ኛ ጎሉ ሆኖ ተመዝግቧል። በዚህም ጋሪ ሊኔከርን በመብለጥ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ከፍተኛውን የጎል ቁጥር ያስመዘገበ እንግሊዛዊ ተጫዋች ሆኗል።
እንግሊዝ ያሳየችው ጥንካሬና ድክመት
እንግሊዝ በመጀመሪያው አጋማሽ የፓናማን ዝቅተኛ የመከላከል አደረጃጀት (Low Block) ለመስበር ተቸግራ ነበር። የጎል ዕድሎቿም አነስተኛ ነበሩ፣ የቡድኑም እንቅስቃሴ ከሚጠበቀው በታች መሆኑን ተንታኞች ጠቁመዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በቀኝ ተከላካይ ክፍል የተፈጠረው የጉዳት ችግር ለአሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል አሳሳቢ ሆኗል። ሬስ ጄምስና ትሬንት አሌክሳንደር-አርኖልድ በጉዳት ከሜዳ ውጭ በመሆናቸው በቦታቸው የተሰለፈው ጃሬል ኳንሳ በጨዋታው ውስጥ ጉዳት አስተናግዶ ወጥቷል።
ፓናማ ተጋድላ ተሸነፈች
ፓናማ በመጀመሪያው አጋማሽ እንግሊዝን በጥሩ ሁኔታ በመቆጣጠር በፈጣን መልሶ ማጥቃት አደገኛ እድሎችን ፈጥራለች። ሆሴ ፋጃርዶ ያስቆጠረው ጎልም በኦፍሳይድ ተሰርዟል።
ሆኖም በሁለተኛው አጋማሽ የታክቲክ ትኩረቷን በማጣቷ በአምስት ደቂቃዎች ውስጥ ሁለት ጎሎችን አስተናግዳ ከምድቡ በሽንፈት ተሰናብታለች።
የዓለም ሚዲያ ምላሽ
የዓለም ስፖርት ሚዲያዎች አሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል በሁለተኛው አጋማሽ ያደረገውን ስልታዊ ለውጥ አድንቀዋል።
ቱሄልም ከጨዋታው በኋላ፣
"ውድድሩ እየተራመደ በሄደ ቁጥር እኛም እየጠነከርን እንሄዳለን።"
በማለት በቡድኑ ላይ ያለውን እምነት ገልጿል።
ከ82,000 በላይ ደጋፊዎች በሜትላይፍ ስታዲየም ተገኝተው ጨዋታውን በቀጥታ ተከታትለዋል። የስታዲየሙ ድባብም በበርካቶች "እንደ ዌምብሊ ስታዲየም" ተመሳስሎ ተገልጿል።
ወደ ጥሎ ማለፍ
እንግሊዝ ምድቧን በአንደኝነት በማጠናቀቅ ወደ 32 ቡድኖች ጥሎ ማለፍ በመግባት ጥሩ መነቃቃት ፈጥራለች። የዓለም ስፖርት ሚዲያዎችም ቡድኑ በቀጣዩ ዙር ከሴኔጋል ወይም ከዲ.አር. ኮንጎ ጋር የሚያደርገውን ጨዋታ በተሻለ መንፈስ እንደሚገጥም ትንበያቸውን አቅርበዋል።
አለባቸው ደሳለኝ አበሻ | ለንደን 🇬🇧
1 month ago
የ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች ተጠናቅቀዋል።
ከየምድቦቻቸው 1ኛ እና 2ኛ በመሆን 24 ሀገራት በቀጥታ እንዲሁም ተጨማሪ 8 ሀገራት ምርጥ 3ኛ በመሆን የ32ቱን ጥሎ ማለፍ ተቀላቅለዋል።
በዚህም መሰረት የ32ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ከምድብ 1 እና 2 ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቁት ደቡብ አፍሪካ እና አዘጋጇ ሀገር ካናዳ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀምራል።
ምድብ ሦስትን በበላይነት ያጠናቀቀችው ብራዚል ከጃፓን እንዲሁም የምድብ 5 አሸናፊዋ ጀርመን ከፓራጓይ ተደልድለዋል።
ኔዘርላንድስ ከሞሮኮ፣ ኮትዲቯር ከኖርዌይ፣ ፈረንሳይ ከስዊድን፣ ሜክሲኮ ከኢኳዶር፣ እንግሊዝ ከዲሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ እንዲሁም ቤልጂዬም ከሴኔጋል ይገናኛሉ።
አሜሪካ ከቦሲኒያ ሄርዞጎቪና፣ ስፔን ከኦስትሪያ፣ ፖርቹጋል ከክሮሺያ፣ ስዊዘርላንድ ከአልጄሪያ፣ አውስትራሊያ ከግብጽ፣ አርጀንቲና ከኬፕቨርዴ እንዲሁም ኮሎምቢያ ከጋና ተደልድለዋል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች ተጠናቅቀዋል።
ከየምድቦቻቸው 1ኛ እና 2ኛ በመሆን 24 ሀገራት በቀጥታ እንዲሁም ተጨማሪ 8 ሀገራት ምርጥ 3ኛ በመሆን የ32ቱን ጥሎ ማለፍ ተቀላቅለዋል።
በዚህም መሰረት የ32ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ከምድብ 1 እና 2 ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቁት ደቡብ አፍሪካ እና አዘጋጇ ሀገር ካናዳ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀምራል።
ምድብ ሦስትን በበላይነት ያጠናቀቀችው ብራዚል ከጃፓን እንዲሁም የምድብ 5 አሸናፊዋ ጀርመን ከፓራጓይ ተደልድለዋል።
ኔዘርላንድስ ከሞሮኮ፣ ኮትዲቯር ከኖርዌይ፣ ፈረንሳይ ከስዊድን፣ ሜክሲኮ ከኢኳዶር፣ እንግሊዝ ከዲሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ እንዲሁም ቤልጂዬም ከሴኔጋል ይገናኛሉ።
አሜሪካ ከቦሲኒያ ሄርዞጎቪና፣ ስፔን ከኦስትሪያ፣ ፖርቹጋል ከክሮሺያ፣ ስዊዘርላንድ ከአልጄሪያ፣ አውስትራሊያ ከግብጽ፣ አርጀንቲና ከኬፕቨርዴ እንዲሁም ኮሎምቢያ ከጋና ተደልድለዋል።
1 month ago
ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ 32ቱን ተቀላቀለች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ 32ቱን መቀላቀሏን አረጋግጣለች።
በምድብ-11 የመጨረሻ ጨዋታ ኡዝቤክስታንን የገጠመችው አፍሪካዊቷ ሀገር ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ 3 ለ 1 አሸንፋለች።
ውጤቱን ተከትሎ በ4 ነጥብ ከምድቧ 3ኛ ደረጃ በመያዝ ያጠናቀቀች ሲሆን፥ ምርጥ 3ኛ በመሆን የ32ቱን ጥሎ ማለፍ ተቀላቅላለች።
በዚሁ ምድብ ፖርቹጋል ከኮሎምቢያ ያደረጉት የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል።
ውጤቱን ተከትሎ ኮሎምቢያ ምድቡን በበላይነት ያጠናቀቀች ሲሆን፥ ፖርቹጋል 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቃለች።
በምድብ-12 በተደረገ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ክሮሺያ ጋናን 2 ለ 1 በማሸነፍ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅላለች።
በዚሁ ምድብ እንግሊዝ ፓናማን 2 ለ ዐ አሸንፋለች።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ 32ቱን መቀላቀሏን አረጋግጣለች።
በምድብ-11 የመጨረሻ ጨዋታ ኡዝቤክስታንን የገጠመችው አፍሪካዊቷ ሀገር ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ 3 ለ 1 አሸንፋለች።
ውጤቱን ተከትሎ በ4 ነጥብ ከምድቧ 3ኛ ደረጃ በመያዝ ያጠናቀቀች ሲሆን፥ ምርጥ 3ኛ በመሆን የ32ቱን ጥሎ ማለፍ ተቀላቅላለች።
በዚሁ ምድብ ፖርቹጋል ከኮሎምቢያ ያደረጉት የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል።
ውጤቱን ተከትሎ ኮሎምቢያ ምድቡን በበላይነት ያጠናቀቀች ሲሆን፥ ፖርቹጋል 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቃለች።
በምድብ-12 በተደረገ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ክሮሺያ ጋናን 2 ለ 1 በማሸነፍ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅላለች።
በዚሁ ምድብ እንግሊዝ ፓናማን 2 ለ ዐ አሸንፋለች።
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል ትልልቅ ጨዋታዎች ሲመጡ ቡድኑም አብሮ እንደሚያድግ በጽኑ ያምናሉ። ይህ እምነታቸው ትክክል ካልሆነ ግን፣ ዘንድሮ በዓለም ዋንጫው ያላቸው ቆይታ እጅግ አጭር መሆኑ አይቀርም።
እንግሊዝ ፓናማን በማሸነፍ በምድብ 'ኤል' አንደኛ በመውጣት የመጀመሪያውን ምዕራፍ ተልዕኮ በስኬት አጠናቃለች። አሁን ፊቷን ወደ 32ቱ ጥሎ ማለፍ በማዞር፣ ረቡዕ ዕለት በአትላንታ ከተማ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ትገጥማለች። ነገር ግን የጥሎ ማለፉ ጉዞ ገና ከወዲሁ ከባድ ስጋቶችን ይዞ ብቅ ብሏል።
የጁድ ቤሊንግሀም በቋሚ አሰላለፍ ውስጥ መካተት ከውድድሩ በፊት አነጋጋሪ ሆኖ ነበር። ሆኖም ቱሄል የቤሊንግሀምን ልዩ ክህሎት እና የትልልቅ መድረኮች ልምድ ወደ ጎን ሊተውት አልቻለም። የቱሄል ውሳኔም ፍሬ አፍርቶ፣ ፓናማውያን ቤሊንግሀምን ከጨዋታ ውጭ ለማድረግ በፈጸሙት እልህ አስጨራሽ ጥረት ውስጥም ቢሆን፣ ተጫዋቹ ልዩ አቅሙን አውጥቶ አሳይቷል።
ጉዳት ላይ ያለውን ዴክላን ራይስን በማሳረፍ ከሞርጋን ሮጀርስ ጋር የነበረው ቤሊንግሀም፣ የመጀመርያዋን ግብ ራሱ ከመረብ አሳርፎ፣ ለሁለተኛዋ ግብ ደግሞ ለሃሪ ኬን እጅግ ማራኪ ኳስ አመቻችቶ በማቀበል የጨዋታው ኮከብ ሆኗል።
ቤሊንግሀም ያቀበለውን ኳስ በግሩም ሁኔታ በጭንቅላቱ ገጭቶ ያስቆጠረው ሃሪ ኬን፣ በዓለም ዋንጫ ታሪክ 11ኛ ግቡን በማስቆጠር ታላቁን ጋሪ ሊንከርን በአንድ ጎል በልጦ የእንግሊዝ የምንግዜም ከፍተኛ የዓለም ዋንጫ ግብ አስቆጣሪ የሚለውን ታሪካዊ ክብር በብቸኝነት ተቆጣጥሯል!
እንግሊዝ ጨዋታውን ብታሸንፍም፣ የኋላ መስመሯ ግን በእጅጉ የሚያሰጋ ነበር። የዓለም 42ኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ፓናማ በእንግሊዝ ግብ ላይ 13 ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ማድረጓ የተከላካይ መስመሩን ተጋላጭነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል።
የቀኝ መስመር ተከላካዩ ሪስ ጄምስ ዳግም መጎዳቱን ተከትሎ፣ ቱሄል ማዕከላዊ ተከላካዩን ጃሬል ኳንሳህን በቀኝ በኩል አሰልፈውት ነበር። ሆኖም ኳንሳህ በሁለተኛው አጋማሽ ተጎድቶ ወጥቷል። ይህ ውሳኔ ብዙዎች፣ "እውነት ቱሄል የተፈጥሮ ቀኝ ተከላካይ የሆነውን ክህሎታሙን ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድን ከቡድኑ በማግለላቸው አይጸጸቱም?" የሚል ጠንካራ ጥያቄ እንዲያነሱ አስገድዷቸዋል።
የቀድሞው የእንግሊዝ አምበል ዋይኒ ሩኒ ሲናገር ሜዳ ላይ መረጋጋት የምትፈልግበት ቦታ ግብ ጠባቂህ እና አራቱ ተከላካዮችህ ጋር ነው፤ እኛ ጋር ግን ያ ፈጽሞ አልታየም" ሲል ቅሬታውን አሰምቷል። በእርግጥ ለቀጣዩ ወሳኝ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ዴክላን ራይስ ወደ ሜዳ መመለሱ የተከላካይ መስመሩን ከፊት ሆኖ ለመታደግ ትልቅ እፎይታ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
ከአንቶኒ ጎርደን ደካማ እንቅስቃሴ በኋላ በመጨረሻ ቋሚ የመሰለፍ እድል ያገኘው ማርከስ ራሽፎርድ፣ በመጀመሪያው አጋማሽ የእንግሊዝ ብሩህ ኮከብ ነበር። ምንም እንኳን አንዳንድ የግብ እድሎችን ቢያመክንም እና ከቡድን አጋሮቹ በቂ ድጋፍ ባያገኝም፣ የተጋጣሚን ተከላካዮች እረፍት ሲነሳ ውሏል።
ቱሄል ከጨዋታው በኋላ በሰጠው አስተያየት "ማርከስ ትንሽ ዕድል አልቀናውም እንጂ ሁሌም እምነት የሚጣልበት እና ጠንክሮ የሚሰራ ተጫዋች ነው፤ ጥረቱን አደንቃለሁ" ሲል አድናቆቱን ችሮታል።
አሁን ጥያቄው፣ እንግሊዝ ይህንን አሸናፊነቷን አጠናክራ የተከላካይ መስመር ክፍተቷን በመድፈን የዓለም ዋንጫን ህልሟን ታሳካለች ወይስ በጠንካራ ተጋጣሚዎች ፈተና ውስጥ ትወድቃለች? የሚለው ነው። ቱሄል እና አናብሥቶቹ በአትላንታው "ምዕራፍ ሶስት" ፍልሚያ መልሱን የሚሰጡን ይሆናል!
እንግሊዝ ፓናማን በማሸነፍ በምድብ 'ኤል' አንደኛ በመውጣት የመጀመሪያውን ምዕራፍ ተልዕኮ በስኬት አጠናቃለች። አሁን ፊቷን ወደ 32ቱ ጥሎ ማለፍ በማዞር፣ ረቡዕ ዕለት በአትላንታ ከተማ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ትገጥማለች። ነገር ግን የጥሎ ማለፉ ጉዞ ገና ከወዲሁ ከባድ ስጋቶችን ይዞ ብቅ ብሏል።
የጁድ ቤሊንግሀም በቋሚ አሰላለፍ ውስጥ መካተት ከውድድሩ በፊት አነጋጋሪ ሆኖ ነበር። ሆኖም ቱሄል የቤሊንግሀምን ልዩ ክህሎት እና የትልልቅ መድረኮች ልምድ ወደ ጎን ሊተውት አልቻለም። የቱሄል ውሳኔም ፍሬ አፍርቶ፣ ፓናማውያን ቤሊንግሀምን ከጨዋታ ውጭ ለማድረግ በፈጸሙት እልህ አስጨራሽ ጥረት ውስጥም ቢሆን፣ ተጫዋቹ ልዩ አቅሙን አውጥቶ አሳይቷል።
ጉዳት ላይ ያለውን ዴክላን ራይስን በማሳረፍ ከሞርጋን ሮጀርስ ጋር የነበረው ቤሊንግሀም፣ የመጀመርያዋን ግብ ራሱ ከመረብ አሳርፎ፣ ለሁለተኛዋ ግብ ደግሞ ለሃሪ ኬን እጅግ ማራኪ ኳስ አመቻችቶ በማቀበል የጨዋታው ኮከብ ሆኗል።
ቤሊንግሀም ያቀበለውን ኳስ በግሩም ሁኔታ በጭንቅላቱ ገጭቶ ያስቆጠረው ሃሪ ኬን፣ በዓለም ዋንጫ ታሪክ 11ኛ ግቡን በማስቆጠር ታላቁን ጋሪ ሊንከርን በአንድ ጎል በልጦ የእንግሊዝ የምንግዜም ከፍተኛ የዓለም ዋንጫ ግብ አስቆጣሪ የሚለውን ታሪካዊ ክብር በብቸኝነት ተቆጣጥሯል!
እንግሊዝ ጨዋታውን ብታሸንፍም፣ የኋላ መስመሯ ግን በእጅጉ የሚያሰጋ ነበር። የዓለም 42ኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ፓናማ በእንግሊዝ ግብ ላይ 13 ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ማድረጓ የተከላካይ መስመሩን ተጋላጭነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል።
የቀኝ መስመር ተከላካዩ ሪስ ጄምስ ዳግም መጎዳቱን ተከትሎ፣ ቱሄል ማዕከላዊ ተከላካዩን ጃሬል ኳንሳህን በቀኝ በኩል አሰልፈውት ነበር። ሆኖም ኳንሳህ በሁለተኛው አጋማሽ ተጎድቶ ወጥቷል። ይህ ውሳኔ ብዙዎች፣ "እውነት ቱሄል የተፈጥሮ ቀኝ ተከላካይ የሆነውን ክህሎታሙን ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድን ከቡድኑ በማግለላቸው አይጸጸቱም?" የሚል ጠንካራ ጥያቄ እንዲያነሱ አስገድዷቸዋል።
የቀድሞው የእንግሊዝ አምበል ዋይኒ ሩኒ ሲናገር ሜዳ ላይ መረጋጋት የምትፈልግበት ቦታ ግብ ጠባቂህ እና አራቱ ተከላካዮችህ ጋር ነው፤ እኛ ጋር ግን ያ ፈጽሞ አልታየም" ሲል ቅሬታውን አሰምቷል። በእርግጥ ለቀጣዩ ወሳኝ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ዴክላን ራይስ ወደ ሜዳ መመለሱ የተከላካይ መስመሩን ከፊት ሆኖ ለመታደግ ትልቅ እፎይታ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
ከአንቶኒ ጎርደን ደካማ እንቅስቃሴ በኋላ በመጨረሻ ቋሚ የመሰለፍ እድል ያገኘው ማርከስ ራሽፎርድ፣ በመጀመሪያው አጋማሽ የእንግሊዝ ብሩህ ኮከብ ነበር። ምንም እንኳን አንዳንድ የግብ እድሎችን ቢያመክንም እና ከቡድን አጋሮቹ በቂ ድጋፍ ባያገኝም፣ የተጋጣሚን ተከላካዮች እረፍት ሲነሳ ውሏል።
ቱሄል ከጨዋታው በኋላ በሰጠው አስተያየት "ማርከስ ትንሽ ዕድል አልቀናውም እንጂ ሁሌም እምነት የሚጣልበት እና ጠንክሮ የሚሰራ ተጫዋች ነው፤ ጥረቱን አደንቃለሁ" ሲል አድናቆቱን ችሮታል።
አሁን ጥያቄው፣ እንግሊዝ ይህንን አሸናፊነቷን አጠናክራ የተከላካይ መስመር ክፍተቷን በመድፈን የዓለም ዋንጫን ህልሟን ታሳካለች ወይስ በጠንካራ ተጋጣሚዎች ፈተና ውስጥ ትወድቃለች? የሚለው ነው። ቱሄል እና አናብሥቶቹ በአትላንታው "ምዕራፍ ሶስት" ፍልሚያ መልሱን የሚሰጡን ይሆናል!
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አፍሪካውያን ሀገራት እርስ በእርስ ለሚያደርጉት የንግድ ልውውጥ በውጭ ምንዛሬ (በተለይም በዶላር እና ዩሮ) ላይ ያላቸውን ጥገኝነት ለመቀነስ፣ የፓን-አፍሪካ የክፍያ እና ማቋቋሚያ ስርዓትን (PAPSS) አጠቃቀም በከፍተኛ ፍጥነት እያሳደጉ መሆኑን የአፍሪካ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ የ2026 ሪፖርት አጋለጠ። ይህ የክፍያ ስርዓት ሀገራቱ በራሳቸው የሀገር ውስጥ ገንዘብ ቀጥታ ግብይት እንዲፈጽሙ በማስቻል፣ የውጭ ባንኮችን ጣልቃ ገብነት እና የግብይት ወጪን በእጅጉ የቀነሰ መሆኑ ተጠቁሟል።
ባንኩ ይህንን የዲጂታል ክፍያ መሰረተ ልማት ማስፋፋት አስቸኳይ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው ያለው፣ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ ያለውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና የንግድ ጥበቃ ፖሊሲዎችን ታሳቢ በማድረግ ነው። በተለይም በአዲሱ የአሜሪካ አስተዳደር የንግድ ፖሊሲ ላይ የታየውን ለውጥ ተከትሎ በ57 የአፍሪካ ሀገራት ላይ የታሪፍ ጭማሪ (በሌሴቶ ላይ እስከ 50 በመቶ የደረሰ) መጣሉ፣ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት የጨርቃጨርቅ ኤክስፖርት ገበያ ላይ ከፍተኛ ጫና እያንዣበበ መሆኑን ሪፖርቱ አትቷል። የአጎዋ (AGOA) ተጠቃሚ ሀገራትም ቢሆኑ ከተጨማሪው የ10 በመቶ ታሪፍ ጫና ማምለጥ አልቻሉም። ከዚህም በተጨማሪ በቀይ ባህር አካባቢ ያለው አለመረጋጋት፣ አፍሪካ የራሷን የውስጥ ንግድ ትስስር እንድታጠናክር አስገዳጅ ሁኔታ ፈጥሯል።
ምንም እንኳን የአፍሪካ አጠቃላይ የዓለም አቀፍ ንግድ ድርሻ አሁንም ዝቅተኛ (3.1 በመቶ) ቢሆንም፣ በ2025 የአፍሪካ የውስጥ እርስ በእርስ ንግድ በ5.47 በመቶ በማደግ ወደ 213.8 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ማለቱ ተመዝግቧል። ለዚህ ዕድገት ኢትዮጵያ፣ ዩጋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ዛምቢያ እና ደቡብ አፍሪካ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውተዋል።
ሪፖርቱ አክሎም፣ የአፍሪካ ሀገራት አሁን ላይ ከገጠማቸው የታሪፍ ጫና፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የውጭ ተጽዕኖ ለማምለጥ፣ ንግዳቸውን ይበልጥ ወደ ብሪክስ ሀገራት ማለትም ወደ ቻይና፣ ህንድ፣ ብራዚል እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በማዞር አማራጭ ገበያዎችን መፍጠር እንዳለባቸው አጥብቆ መክሯል።
ባንኩ ይህንን የዲጂታል ክፍያ መሰረተ ልማት ማስፋፋት አስቸኳይ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው ያለው፣ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ ያለውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና የንግድ ጥበቃ ፖሊሲዎችን ታሳቢ በማድረግ ነው። በተለይም በአዲሱ የአሜሪካ አስተዳደር የንግድ ፖሊሲ ላይ የታየውን ለውጥ ተከትሎ በ57 የአፍሪካ ሀገራት ላይ የታሪፍ ጭማሪ (በሌሴቶ ላይ እስከ 50 በመቶ የደረሰ) መጣሉ፣ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት የጨርቃጨርቅ ኤክስፖርት ገበያ ላይ ከፍተኛ ጫና እያንዣበበ መሆኑን ሪፖርቱ አትቷል። የአጎዋ (AGOA) ተጠቃሚ ሀገራትም ቢሆኑ ከተጨማሪው የ10 በመቶ ታሪፍ ጫና ማምለጥ አልቻሉም። ከዚህም በተጨማሪ በቀይ ባህር አካባቢ ያለው አለመረጋጋት፣ አፍሪካ የራሷን የውስጥ ንግድ ትስስር እንድታጠናክር አስገዳጅ ሁኔታ ፈጥሯል።
ምንም እንኳን የአፍሪካ አጠቃላይ የዓለም አቀፍ ንግድ ድርሻ አሁንም ዝቅተኛ (3.1 በመቶ) ቢሆንም፣ በ2025 የአፍሪካ የውስጥ እርስ በእርስ ንግድ በ5.47 በመቶ በማደግ ወደ 213.8 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ማለቱ ተመዝግቧል። ለዚህ ዕድገት ኢትዮጵያ፣ ዩጋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ዛምቢያ እና ደቡብ አፍሪካ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውተዋል።
ሪፖርቱ አክሎም፣ የአፍሪካ ሀገራት አሁን ላይ ከገጠማቸው የታሪፍ ጫና፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የውጭ ተጽዕኖ ለማምለጥ፣ ንግዳቸውን ይበልጥ ወደ ብሪክስ ሀገራት ማለትም ወደ ቻይና፣ ህንድ፣ ብራዚል እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በማዞር አማራጭ ገበያዎችን መፍጠር እንዳለባቸው አጥብቆ መክሯል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የዓለም ዋንጫው የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዎች…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ መርሐ ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡
በምድብ-11 አስቀድመው 32ቱን መቀላቀላቸውን ያረጋገጡት ፖርቹጋል እና ኮሎምቢያ ምድቡን በበላይነት ለማጠናቀቅ ሌሊት 8 ሰዓት ከ30 የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በምድቡ 2ኛ ጨዋታ ለሀገሩ ፖርቹጋል 2 ግቦችን በማስቆጠር አዳዲስ ክብረወሰኖችን ያስመዘገበው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በምሽቱ ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በዚሁ ምድብ በተመሳሳይ ሰዓት ኡዝቤክስታንን የምትገጥመው ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ ይህንን ጨዋታ ካሸነፈች ምርጥ 3ኛ በመሆን 32ቱን ትቀላቀላለች፡፡
በሊዮኔል ሜሲ አምስት ግቦች ታግዛ የምድቧን ሁለቱንም ጨዋታዎች በማሸነፍ 32ቱን የተቀላቀለችው አርጀንቲና ንጋት 11 ሰዓት ላይ በምድቡ ግርጌ የምትገኘውን ጆርዳን ትገጥማለች፡፡
በ18 ግቦች የዓለም ዋንጫው የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰንን የግሉ ያደረገው ሊዮኔል ሜሲ በዚህም ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በዚህ ምድብ የምትገኘው ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አልጄሪያ 32ቱን ለመቀላቀል በተመሳሳይ ሰዓት ከኦስትሪያ ጋር በምታደርገው ጨዋታ አቻ መውጣት ይበቃታል፡፡
ከመጨረሻው ምድብ ከዛሬ ምሽቱ ጨዋታ አስቀድማ ማለፏን ያረጋገጠችው እንግሊዝ መሰናበቷን ካረጋገጠችው ፓናማ ጋር እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ላይ ትጫወታለች፡፡
በተመሳሳይ 32ቱን መቀላቀሏን ያረጋገጠችው የአፍሪካ ተወካይዋ ጋና በበኩሏ ከክሮሺያ ጋር በተመሳሳይ ሰዓት የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ መርሐ ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡
በምድብ-11 አስቀድመው 32ቱን መቀላቀላቸውን ያረጋገጡት ፖርቹጋል እና ኮሎምቢያ ምድቡን በበላይነት ለማጠናቀቅ ሌሊት 8 ሰዓት ከ30 የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በምድቡ 2ኛ ጨዋታ ለሀገሩ ፖርቹጋል 2 ግቦችን በማስቆጠር አዳዲስ ክብረወሰኖችን ያስመዘገበው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በምሽቱ ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በዚሁ ምድብ በተመሳሳይ ሰዓት ኡዝቤክስታንን የምትገጥመው ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ ይህንን ጨዋታ ካሸነፈች ምርጥ 3ኛ በመሆን 32ቱን ትቀላቀላለች፡፡
በሊዮኔል ሜሲ አምስት ግቦች ታግዛ የምድቧን ሁለቱንም ጨዋታዎች በማሸነፍ 32ቱን የተቀላቀለችው አርጀንቲና ንጋት 11 ሰዓት ላይ በምድቡ ግርጌ የምትገኘውን ጆርዳን ትገጥማለች፡፡
በ18 ግቦች የዓለም ዋንጫው የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰንን የግሉ ያደረገው ሊዮኔል ሜሲ በዚህም ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በዚህ ምድብ የምትገኘው ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አልጄሪያ 32ቱን ለመቀላቀል በተመሳሳይ ሰዓት ከኦስትሪያ ጋር በምታደርገው ጨዋታ አቻ መውጣት ይበቃታል፡፡
ከመጨረሻው ምድብ ከዛሬ ምሽቱ ጨዋታ አስቀድማ ማለፏን ያረጋገጠችው እንግሊዝ መሰናበቷን ካረጋገጠችው ፓናማ ጋር እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ላይ ትጫወታለች፡፡
በተመሳሳይ 32ቱን መቀላቀሏን ያረጋገጠችው የአፍሪካ ተወካይዋ ጋና በበኩሏ ከክሮሺያ ጋር በተመሳሳይ ሰዓት የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
1 month ago
የልጅነት እንባ እና የድል መንገድ - ሮናልዶ ከትላንት እስከ ዛሬ
**********************
የ2004 አውሮፓ ዋንጫ ብዙ ትዝታዎች አሉት። የኦቶ ሪሃግሎቹ ግሪኮች ፖርቹጋሎችን በጥብቅ መከላከል በገዛ ሜዳቸው የአውሮፓ ዋንጫውን መንጠቃቸው ብቻ ሳይሆን፤ ሊመጣ ብቅ እያለ ያለው አዲስ ኮከብ ትኩስ እንባ በሊዝበኑ ስታዲዮ ዳሉዝ ሲፈስ ትዝታው ዛሬም ርቆ ያልራቀ ቅርብ ነው።
ያን የዘመናዊ እግር ኳስ ህልው ትዝታ አስታከን ወደ ዛሬ እንዘልቃለን። ብዙ ውብ ትላንቶችን፣ ደማቅ ቀኖችን እና ውብ ምሽቶችን አልፎ እውን ወደሆነው ዛሬ እንመጣለን። ትዝታ ቢርቅም አያረጀምና፣ በዘመን መፈራረቅም አይደበዝዝምና ብትውስታ ጎዳና እንመላለሳለን።
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ዶስ ሳንቶስ አቪየሮ የሚባል ስም፣ በአባቱ መሻት የሮናልድ ሬገንን መጠሪያ እንዲጋራ የሆነ፣ በልጅነቱ አይጋፈጡትን ፈተና የተጋፈጠ፣ የሊዝበን ሰዎች በአፍላነቱ ሳይጠግቡ የተለዩት፣ የላንክ ሻየር ሰዎች ደግሞ ውብ ማለዳውን የተጋሩት፣ ውለታን የማይረሳው ዛሬም በስኬት ደጃፎች እየተመላለሰ ያለ ህያው ኮከብ ነው።
በሰር አሌክስ ፈርጉሰን እና በማንቸስተር ዩናይትድ መልማዮች ዓይን ውስጥ ከገባባት ከዚያች የወዳጅነት ጨዋታ ዕለት አንስቶ ዘመናዊ እግር ኳስ ሌላ መልክ ነው የያዘው። ማንቸስተር ዩናይትድ ከዚህ ኮከብ ጋር በበርካታ ዋንጫዎች የተገመደ ብዙ የድል ቀናትን አልፏል።
ወደ ሎስ ብላንኮዎቹ ቅፅር ዘልቆም በነጩ መለያ ለሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥም በአውሮፓ መድረክም የሚደረገውን ሁሉ አድርጓል። ቱሪንም እጇን ዘርግታ ነው የተቀበለችው። እዚያም ስኬት ከእርሱ ጋር ነበረች።
በድኅረ ኮቪድ 19 የመጀመሪያ ወቅቶች ወደ ኦልድትራፎርድ ሲመለስ የቀዮቹ ደጋፊዎች ትዝታቸውን እንደሸከፉ ነበርና “እንኳን መጣህልን” ነበር ያሉት።
ሆኖም የማቸስተር ዩናይትድ ዳግም ምልሰቱ እንደ ትላንት ስል፣ እንደ ዕድሜውም በውጤት ብስል አልሆነም። ከኤሪክ ቴንሀግ ጋር የጋባበት መቃቃር ደግሞ ወደ መውጫው በር እንዲያማትር ዋነኛ ምክኒያት ሆነ።
ወደ መካከለኛው ምስራቅ ዘለቀ፤ በእግር ኳስ ብዙ መዋዕለ ንዋይ አፍስሳ ግዙፍ ለውጥ ወደ ሻተችው ሳዑዲ አረቢያ አቀና። ከሳምንታት በፊትም ለሦስት ዓመታት የተጠበቀውን የሳዑዲ ፕሮ ሊግ ሻምፒዮንነት ከክለቡ ዐል-ናስር ጋር አነሳ።
ሆኖም ጥያቄ ነበር። እነዚህን ሁሉ ቁጥራቸው የበረከቱ ስኬቶች ወደ ብሔራዊ ቡድን የሚተረጉማቸውስ መቼ ነው? የሚል።
በእርግጥ የ2016ቱን አውሮፓ ዋንጫ ሲያነሳ ይህ ጥያቄ በከፊል የተመለሰ መስሎ ነበር። የአውሮፓ ሀገራት ዋንጫ/ ኔሽንስ ሊግንም አንስቷል።
ግን ግዙፉ የዓለም ዋንጫስ? እግር ኳስ በታሪኩ ካስመለከታቸው ኮከቦች ለምሉዕነት አንድ መስፈርቱ ይኸው መድረክ ነውና፤ የእርሱስ ቀን አይመጣም ወይ? ተብሎ ተጠብቋል። እስካሁን ያ ቀን አልመጣም።
በእርግጥ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ በተቆጠሩ ግቦች ከሊዮኔል ሜሲ እና ከኢራናዊው ዓሊ ዳይ በእጅጉ ርቋል። በዚህ በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ደግሞ በመድረኩ ከተሳተፉ አንጋፋ ተጫዋቾች አንዱ ሆኖ ወደ አሜሪካ ምድር ሲዘልቅ ብዙ ጥበቃዎች ነበሩ። እነዛ ጥበቃዎች ግን በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ያለግብ ሲለያዩ ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገቡ ያደረገ ሆነ። በርከት ያሉ ትችቶች እርሱም ሆነ የቡድን አጋሮቹ ላይ መሰንዘራቸው አልቀረም።
ቀን ጠብቆ በአሉታ ለተቹትም፣ በበጎ ለጠበቁትም ምላሽ ሰጥቷል። ኡዝቤኪስታንን 5 ለ 0 በረቱበት ጨዋታ ከመረብ ያሳረፋቸው እነዚያ ሁለት ግቦች ትችቶቹን አቅጣጫ ማስቀየሪያ ብቻ አልሆኑም። አዳዲስ ክብረ ወሰኖችንም አስከትለዋል።
ሮናልዶ ከካሜሩናዊው ሮጀር ሚላ በመቀጠል በመድረኩ ግብ ያስቆጠረ አንጋፋ ተጫዋች ተሰኝቷል፤ ከ2006 የጀርመን ዓለም ዋንጫ እስከ 23ኛው የአሜሪካ ምድር ዓለም ዋንጫ በተሳተፈባቸው 6 ውድድሮች በሁሉም ግብ በማስቆጠር ደግሞ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል።
በጨዋታ ዘመኑ ያስቆጠራቸው ግቦችም 975 ደርሰዋል። በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ደግሞ 145ኛ ግቡን በማስቆጠር ከተከታዩ ሊዮኔል ሜሲ ጋር ያለውን ልዩነት ወደ 23 አስፍቷል።
በጨለማ ከመሰለው አስቸጋሪ ሳምንት በኋላ፣ ትችት ከበረከተባቸው ሰሞናት በኋላ “ተመልሰናል” ብሏል ሮናልዶ። በግል የሚመዘገቡ ክብረ ወሰኖች መልካም ቢሆኑም፤ ቀዳሚ ግቡ ግን ቡድኑን መርዳትና ለአሸናፊነት ማብቃት መሆኑን ነው የገለፀው።
ያ መንገድ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ዛሬም ቀጥሏል። እንደ ትላንቱ ባይሰላም ለተባለው ሁሉ ተግባራዊ ምላሽ እየሰጠ አለ። የትችት ወጀብ ሳይገታው፣ የዕድሜ መግፋትም ሳይረታው እንደ ጥንቱ ስል ባይሆንም አለሁ እያለ ነው።
ዋይኒ ሩኒ የተናገው ይህን በሚገባ ይገልፃል።ሮናልዶ ትችትን ማስተናገድ፣ ለትችቱም አስፈላጊውን ተግባራዊ ምለሽ መስጠት በእግር ኳስ ዘመኑ ሁሉ የተጓዘበት እውነት ነው።
“ትዝታ አያረጅም” ሲባል በጎም ይሁን መጥፎ በአዕምሮ ጓዳ ደጋግሞ ስለሚመላለስ ነው። ሮናልዶ ግን ያለፈ ትዝታ፤ ያላለፈ ዛሬ ነው።
እነዚያ በፅናት የተጓዘባቸው ውጤታማ ዓመታት፣ ያንን የሊዝበን ሰታዲየም እንባ ይገልፃሉ። ያ የእልህ እና የቁጭት እንባ፤ ከዓመታት በኋላ ዛሬም ትኩስ ነው፣ አልቀዘቀዘም!
በእድሪስ አህመድ
Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት #sports #ronaldo #football
**********************
የ2004 አውሮፓ ዋንጫ ብዙ ትዝታዎች አሉት። የኦቶ ሪሃግሎቹ ግሪኮች ፖርቹጋሎችን በጥብቅ መከላከል በገዛ ሜዳቸው የአውሮፓ ዋንጫውን መንጠቃቸው ብቻ ሳይሆን፤ ሊመጣ ብቅ እያለ ያለው አዲስ ኮከብ ትኩስ እንባ በሊዝበኑ ስታዲዮ ዳሉዝ ሲፈስ ትዝታው ዛሬም ርቆ ያልራቀ ቅርብ ነው።
ያን የዘመናዊ እግር ኳስ ህልው ትዝታ አስታከን ወደ ዛሬ እንዘልቃለን። ብዙ ውብ ትላንቶችን፣ ደማቅ ቀኖችን እና ውብ ምሽቶችን አልፎ እውን ወደሆነው ዛሬ እንመጣለን። ትዝታ ቢርቅም አያረጀምና፣ በዘመን መፈራረቅም አይደበዝዝምና ብትውስታ ጎዳና እንመላለሳለን።
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ዶስ ሳንቶስ አቪየሮ የሚባል ስም፣ በአባቱ መሻት የሮናልድ ሬገንን መጠሪያ እንዲጋራ የሆነ፣ በልጅነቱ አይጋፈጡትን ፈተና የተጋፈጠ፣ የሊዝበን ሰዎች በአፍላነቱ ሳይጠግቡ የተለዩት፣ የላንክ ሻየር ሰዎች ደግሞ ውብ ማለዳውን የተጋሩት፣ ውለታን የማይረሳው ዛሬም በስኬት ደጃፎች እየተመላለሰ ያለ ህያው ኮከብ ነው።
በሰር አሌክስ ፈርጉሰን እና በማንቸስተር ዩናይትድ መልማዮች ዓይን ውስጥ ከገባባት ከዚያች የወዳጅነት ጨዋታ ዕለት አንስቶ ዘመናዊ እግር ኳስ ሌላ መልክ ነው የያዘው። ማንቸስተር ዩናይትድ ከዚህ ኮከብ ጋር በበርካታ ዋንጫዎች የተገመደ ብዙ የድል ቀናትን አልፏል።
ወደ ሎስ ብላንኮዎቹ ቅፅር ዘልቆም በነጩ መለያ ለሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥም በአውሮፓ መድረክም የሚደረገውን ሁሉ አድርጓል። ቱሪንም እጇን ዘርግታ ነው የተቀበለችው። እዚያም ስኬት ከእርሱ ጋር ነበረች።
በድኅረ ኮቪድ 19 የመጀመሪያ ወቅቶች ወደ ኦልድትራፎርድ ሲመለስ የቀዮቹ ደጋፊዎች ትዝታቸውን እንደሸከፉ ነበርና “እንኳን መጣህልን” ነበር ያሉት።
ሆኖም የማቸስተር ዩናይትድ ዳግም ምልሰቱ እንደ ትላንት ስል፣ እንደ ዕድሜውም በውጤት ብስል አልሆነም። ከኤሪክ ቴንሀግ ጋር የጋባበት መቃቃር ደግሞ ወደ መውጫው በር እንዲያማትር ዋነኛ ምክኒያት ሆነ።
ወደ መካከለኛው ምስራቅ ዘለቀ፤ በእግር ኳስ ብዙ መዋዕለ ንዋይ አፍስሳ ግዙፍ ለውጥ ወደ ሻተችው ሳዑዲ አረቢያ አቀና። ከሳምንታት በፊትም ለሦስት ዓመታት የተጠበቀውን የሳዑዲ ፕሮ ሊግ ሻምፒዮንነት ከክለቡ ዐል-ናስር ጋር አነሳ።
ሆኖም ጥያቄ ነበር። እነዚህን ሁሉ ቁጥራቸው የበረከቱ ስኬቶች ወደ ብሔራዊ ቡድን የሚተረጉማቸውስ መቼ ነው? የሚል።
በእርግጥ የ2016ቱን አውሮፓ ዋንጫ ሲያነሳ ይህ ጥያቄ በከፊል የተመለሰ መስሎ ነበር። የአውሮፓ ሀገራት ዋንጫ/ ኔሽንስ ሊግንም አንስቷል።
ግን ግዙፉ የዓለም ዋንጫስ? እግር ኳስ በታሪኩ ካስመለከታቸው ኮከቦች ለምሉዕነት አንድ መስፈርቱ ይኸው መድረክ ነውና፤ የእርሱስ ቀን አይመጣም ወይ? ተብሎ ተጠብቋል። እስካሁን ያ ቀን አልመጣም።
በእርግጥ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ በተቆጠሩ ግቦች ከሊዮኔል ሜሲ እና ከኢራናዊው ዓሊ ዳይ በእጅጉ ርቋል። በዚህ በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ደግሞ በመድረኩ ከተሳተፉ አንጋፋ ተጫዋቾች አንዱ ሆኖ ወደ አሜሪካ ምድር ሲዘልቅ ብዙ ጥበቃዎች ነበሩ። እነዛ ጥበቃዎች ግን በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ያለግብ ሲለያዩ ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገቡ ያደረገ ሆነ። በርከት ያሉ ትችቶች እርሱም ሆነ የቡድን አጋሮቹ ላይ መሰንዘራቸው አልቀረም።
ቀን ጠብቆ በአሉታ ለተቹትም፣ በበጎ ለጠበቁትም ምላሽ ሰጥቷል። ኡዝቤኪስታንን 5 ለ 0 በረቱበት ጨዋታ ከመረብ ያሳረፋቸው እነዚያ ሁለት ግቦች ትችቶቹን አቅጣጫ ማስቀየሪያ ብቻ አልሆኑም። አዳዲስ ክብረ ወሰኖችንም አስከትለዋል።
ሮናልዶ ከካሜሩናዊው ሮጀር ሚላ በመቀጠል በመድረኩ ግብ ያስቆጠረ አንጋፋ ተጫዋች ተሰኝቷል፤ ከ2006 የጀርመን ዓለም ዋንጫ እስከ 23ኛው የአሜሪካ ምድር ዓለም ዋንጫ በተሳተፈባቸው 6 ውድድሮች በሁሉም ግብ በማስቆጠር ደግሞ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል።
በጨዋታ ዘመኑ ያስቆጠራቸው ግቦችም 975 ደርሰዋል። በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ደግሞ 145ኛ ግቡን በማስቆጠር ከተከታዩ ሊዮኔል ሜሲ ጋር ያለውን ልዩነት ወደ 23 አስፍቷል።
በጨለማ ከመሰለው አስቸጋሪ ሳምንት በኋላ፣ ትችት ከበረከተባቸው ሰሞናት በኋላ “ተመልሰናል” ብሏል ሮናልዶ። በግል የሚመዘገቡ ክብረ ወሰኖች መልካም ቢሆኑም፤ ቀዳሚ ግቡ ግን ቡድኑን መርዳትና ለአሸናፊነት ማብቃት መሆኑን ነው የገለፀው።
ያ መንገድ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ዛሬም ቀጥሏል። እንደ ትላንቱ ባይሰላም ለተባለው ሁሉ ተግባራዊ ምላሽ እየሰጠ አለ። የትችት ወጀብ ሳይገታው፣ የዕድሜ መግፋትም ሳይረታው እንደ ጥንቱ ስል ባይሆንም አለሁ እያለ ነው።
ዋይኒ ሩኒ የተናገው ይህን በሚገባ ይገልፃል።ሮናልዶ ትችትን ማስተናገድ፣ ለትችቱም አስፈላጊውን ተግባራዊ ምለሽ መስጠት በእግር ኳስ ዘመኑ ሁሉ የተጓዘበት እውነት ነው።
“ትዝታ አያረጅም” ሲባል በጎም ይሁን መጥፎ በአዕምሮ ጓዳ ደጋግሞ ስለሚመላለስ ነው። ሮናልዶ ግን ያለፈ ትዝታ፤ ያላለፈ ዛሬ ነው።
እነዚያ በፅናት የተጓዘባቸው ውጤታማ ዓመታት፣ ያንን የሊዝበን ሰታዲየም እንባ ይገልፃሉ። ያ የእልህ እና የቁጭት እንባ፤ ከዓመታት በኋላ ዛሬም ትኩስ ነው፣ አልቀዘቀዘም!
በእድሪስ አህመድ
Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት #sports #ronaldo #football
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ሚሼል ኩካ ምቦላዲንጋ፣ በብዙዎች ዘንድ 'ሉሙምባ ቬያ' ወይም "ህያው ሐውልት" በመባል የሚታወቀው ይህ ግለሰብ፣ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ከተገኙ ተመልካቾች ሁሉ እጅግ የተለየ እና በቀላሉ የሚለይ አስገራሚ ደጋፊ ነው።
በቅርቡ በዲ.አር. ኮንጎ በተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ምክንያት በተጣለበት አስገዳጅ የለይቶ ማቆያ ህግ፣ ሀገሩ ያደረገችውን የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ጨዋታ በስታዲየም ተገኝቶ ለማየት ባይታደልም፤ ዛሬ ግን ከኮሎምቢያ ጋር በተደረገው ወሳኝ የምድብ ጨዋታ በሜክሲኮ በከፍተኛ የሞራል ጥንካሬ እና ደስታ ሲፍነከነክ ታይቷል።
የዚህን ደጋፊ ታሪክ ልዩ የሚያደርገው አጨብጫቢነቱ፣ ዝላዩ ወይም ጩኸቱ አይደለም! ሀገሩ ዲ.አር. ኮንጎ በምትጫወትበት ጊዜ ሙሉ 90 ደቂቃ ልክ እንደ ሐውልት ደርቆ እና አንድ እጁን ወደ ላይ አንስቶ ምንም ሳይንቀሳቀስ መቆሙ እንጂ! ይህንን በሚያደርግበት ጊዜም የዲ.አር. ኮንጎን የባንዲራ ቀለማት (ቢጫ፣ ሰማያዊ እና ቀይ) የሚያንጸባርቅ ጃኬት፣ ሸሚዝ፣ ከረባት እና የሱፍ ሱሪ ዘንጦ ይለብሳል።
ይህ በአድናቆት አድርቆ የሚያስቀር አቋቋሙ ዝም ብሎ ለታይታ የመጣ አይደለም። በዲ.አር. ኮንጎ ዋና ከተማ ኪንሻሳ የሚገኘውን ታዋቂውን የፓትሪስ ሉሙምባ ሐውልት አቋቋም ለመወከል እና ለማስታወስ የሚያደርገው ነው። ፓትሪስ ሉሙምባ በ1960 የኮንጎ ሪፐብሊክ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩ የነጻነት ታጋይ ሲሆኑ፣ የደጋፊው የቅጽል ስም "ሉሙምባ ቬያ" የመጣውም ከዚሁ ታላቅ መሪ ስም ነው።
ይህ የዲ.አር. ኮንጎ የቁርጥ ቀን ደጋፊ ይህንን ልዩ የማበረታታት ጥበብ የጀመረው ከ2013 ጀምሮ ቢሆንም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት ታዋቂነትን ያተረፈው እና የካሜራዎችን ትኩረት የሳበው ግን በታህሳስ 2025 እና በጥር 2026 በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ባሳየው አስደናቂ ትዕይንት ነው።
በቅርቡ በዲ.አር. ኮንጎ በተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ምክንያት በተጣለበት አስገዳጅ የለይቶ ማቆያ ህግ፣ ሀገሩ ያደረገችውን የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ጨዋታ በስታዲየም ተገኝቶ ለማየት ባይታደልም፤ ዛሬ ግን ከኮሎምቢያ ጋር በተደረገው ወሳኝ የምድብ ጨዋታ በሜክሲኮ በከፍተኛ የሞራል ጥንካሬ እና ደስታ ሲፍነከነክ ታይቷል።
የዚህን ደጋፊ ታሪክ ልዩ የሚያደርገው አጨብጫቢነቱ፣ ዝላዩ ወይም ጩኸቱ አይደለም! ሀገሩ ዲ.አር. ኮንጎ በምትጫወትበት ጊዜ ሙሉ 90 ደቂቃ ልክ እንደ ሐውልት ደርቆ እና አንድ እጁን ወደ ላይ አንስቶ ምንም ሳይንቀሳቀስ መቆሙ እንጂ! ይህንን በሚያደርግበት ጊዜም የዲ.አር. ኮንጎን የባንዲራ ቀለማት (ቢጫ፣ ሰማያዊ እና ቀይ) የሚያንጸባርቅ ጃኬት፣ ሸሚዝ፣ ከረባት እና የሱፍ ሱሪ ዘንጦ ይለብሳል።
ይህ በአድናቆት አድርቆ የሚያስቀር አቋቋሙ ዝም ብሎ ለታይታ የመጣ አይደለም። በዲ.አር. ኮንጎ ዋና ከተማ ኪንሻሳ የሚገኘውን ታዋቂውን የፓትሪስ ሉሙምባ ሐውልት አቋቋም ለመወከል እና ለማስታወስ የሚያደርገው ነው። ፓትሪስ ሉሙምባ በ1960 የኮንጎ ሪፐብሊክ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩ የነጻነት ታጋይ ሲሆኑ፣ የደጋፊው የቅጽል ስም "ሉሙምባ ቬያ" የመጣውም ከዚሁ ታላቅ መሪ ስም ነው።
ይህ የዲ.አር. ኮንጎ የቁርጥ ቀን ደጋፊ ይህንን ልዩ የማበረታታት ጥበብ የጀመረው ከ2013 ጀምሮ ቢሆንም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት ታዋቂነትን ያተረፈው እና የካሜራዎችን ትኩረት የሳበው ግን በታህሳስ 2025 እና በጥር 2026 በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ባሳየው አስደናቂ ትዕይንት ነው።
Comments