2 days ago
“ታሪክ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም-የነፍስ መገለጥ እንጂ”
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
3 days ago
በአማራ ክልል በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአማራ ክልል በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከአሚኮ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ በአማራ ክልል በገጠር ያለው ነዋሪ የመብራት፣ የውሃ፣ የጤና የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም በክልሉ በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል ብለዋል፡፡
በመስኖ፣ በቴክኖሎጂ፣ ምርታማነትን የማሳደግ ጉዳይ አሁን ካለው ጋር ለውድድር የሚበቃ ነው ብዬ አላስብም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አምራች ዘርፉ፣ ኢንዱስትሪው በብዙ ደረጃ ይቀየራል ሲሉ ጠቁመዋል።
የዲጂታል ኢኮኖሚ በኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት እንደሚረጋገጥ አንስተዋል።
አሁን ያለው ትውልድ በከፋፋይ፣ በውሸት፣ መሰረት በሌለው ታሪክ ላይ ቆሞ የሚነታረክ መሆኑ አብቅቶ የሚጠቅመውንና የሚፈይደውን የሀገርን ጥቅም ማዕከል ያደረገውን ትርክት ገንብቶ ለጋራ ጥቅም መረባረብ እንዳለበትም አመልክተዋል።
አማራን ብቻ ሳይሆን አካባቢን የሚጠቅም ብልጽግና እናረጋግጣለን፤ ብልጽግናውንም የሚያስተዳድር ትውልድን አብረን እንፈጥራለን ብለዋል።
ይህ ጉዳይ የሁሉንም ርብርብ እንደሚጠይቅ ገልጸው፤ ይህ ትውልድ ስራውን ከሰራ መጪው ትውልድ የተሻለ ህይወት እንደሚኖረውና የአማራም ህዝብ ከዚህ እንደሚጠቀም ተስፋ አደርጋለሁ ነው ያሉት፡፡
FBC
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአማራ ክልል በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከአሚኮ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ በአማራ ክልል በገጠር ያለው ነዋሪ የመብራት፣ የውሃ፣ የጤና የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም በክልሉ በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል ብለዋል፡፡
በመስኖ፣ በቴክኖሎጂ፣ ምርታማነትን የማሳደግ ጉዳይ አሁን ካለው ጋር ለውድድር የሚበቃ ነው ብዬ አላስብም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አምራች ዘርፉ፣ ኢንዱስትሪው በብዙ ደረጃ ይቀየራል ሲሉ ጠቁመዋል።
የዲጂታል ኢኮኖሚ በኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት እንደሚረጋገጥ አንስተዋል።
አሁን ያለው ትውልድ በከፋፋይ፣ በውሸት፣ መሰረት በሌለው ታሪክ ላይ ቆሞ የሚነታረክ መሆኑ አብቅቶ የሚጠቅመውንና የሚፈይደውን የሀገርን ጥቅም ማዕከል ያደረገውን ትርክት ገንብቶ ለጋራ ጥቅም መረባረብ እንዳለበትም አመልክተዋል።
አማራን ብቻ ሳይሆን አካባቢን የሚጠቅም ብልጽግና እናረጋግጣለን፤ ብልጽግናውንም የሚያስተዳድር ትውልድን አብረን እንፈጥራለን ብለዋል።
ይህ ጉዳይ የሁሉንም ርብርብ እንደሚጠይቅ ገልጸው፤ ይህ ትውልድ ስራውን ከሰራ መጪው ትውልድ የተሻለ ህይወት እንደሚኖረውና የአማራም ህዝብ ከዚህ እንደሚጠቀም ተስፋ አደርጋለሁ ነው ያሉት፡፡
FBC
3 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሚኮ ጋር ያደረጉት ቆይታ - ክፍል 2
#ethiopia #ebc #pmabiyahmed #currentaffairs
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
#ethiopia #ebc #pmabiyahmed #currentaffairs
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
3 days ago
የአርሶ አደሩን ድካም የሚያቃልል አዲስ ማሽን በደብረ ታቦር ተፈጠረ
#ethiopia | የደብረ ታቦር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች በረከት ፀጋው እና ቤዛዊት ሲሳይ ሰብልን በአንድ ጊዜ የሚወቃና የሚያበጥር አዲስ የግብርና ማሽን በመፍጠር ትኩረት ስበዋል።
አዲሱ ማሽን አርሶ አደሮች እህል ለመውቃት ይጠቀሙበት የነበረውን ብዙ የሰው ኃይልና የእንስሳት ጉልበት የሚተካ ሲሆን፣ ሥራውን በሁለት ሰዎች ብቻ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ያስችላል። ይህም የምርት ሂደቱን በማፋጠን የሥራ ወጪን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
ወጣቶቹ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ይህን ፈጠራ ማበልጸጋቸው ለሌሎች ወጣቶች በፈጠራና በራስ አቅም ሥራ ፈጠራ ረገድ አርአያ ሆኗል።
የደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደርም ለፈጠራው ቀጣይ እድገት የቦታ፣ የሼድ እና የብድር ድጋፍ በማድረግ ከፈጣሪዎቹ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።
አሚኮ (AMICO)
#ethiopia #debretabor #innovation #agritech #tvet #ethiopianyouth #agriculture #ግብርና #ፈጠራ
#ethiopia | የደብረ ታቦር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች በረከት ፀጋው እና ቤዛዊት ሲሳይ ሰብልን በአንድ ጊዜ የሚወቃና የሚያበጥር አዲስ የግብርና ማሽን በመፍጠር ትኩረት ስበዋል።
አዲሱ ማሽን አርሶ አደሮች እህል ለመውቃት ይጠቀሙበት የነበረውን ብዙ የሰው ኃይልና የእንስሳት ጉልበት የሚተካ ሲሆን፣ ሥራውን በሁለት ሰዎች ብቻ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ያስችላል። ይህም የምርት ሂደቱን በማፋጠን የሥራ ወጪን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
ወጣቶቹ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ይህን ፈጠራ ማበልጸጋቸው ለሌሎች ወጣቶች በፈጠራና በራስ አቅም ሥራ ፈጠራ ረገድ አርአያ ሆኗል።
የደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደርም ለፈጠራው ቀጣይ እድገት የቦታ፣ የሼድ እና የብድር ድጋፍ በማድረግ ከፈጣሪዎቹ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።
አሚኮ (AMICO)
#ethiopia #debretabor #innovation #agritech #tvet #ethiopianyouth #agriculture #ግብርና #ፈጠራ
Sponsored by
Surafel
3 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በወቅታዊ ሀገራዊ እና የአማራ ክልል ጉዳዮች ዙሪያ ከአሚኮ ጋር ያደረጉት ቆይታ ክፍል ሁለት #pmabiyahemed #ethiopia
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
4 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በወቅታዊ ሀገራዊ እና የአማራ ክልል ጉዳዮች ዙሪያ ከአሚኮ ጋር ያደረጉት ቆይታ ክፍል ሁለት
#pmabiyahemed #ethiopia
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
#pmabiyahemed #ethiopia
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
4 days ago
u1320u1245u120bu12ed u121au1292u1235u1275u122d u12d0u1262u12ed u12a0u1215u1218u12f5 (u12f6/u122d) u1260u12c8u1245u1273u12ca u1200u1308u122bu12ca u12a5u1293 u12e8u12a0u121bu122b u12adu120du120d u1309u12f3u12eeu127d u12d9u122au12eb u12a8u12a0u121au12ae u130bu122d u12ebu12f0u1228u1309u1275 u1246u12edu1273 u12adu134du120d u1201u1208u1275
#pmabiyahemed Ethiopian Broadcasting Corporation","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በወቅታዊ ሀገራዊ እና የአማራ ክልል ጉዳዮች ዙሪያ ከአሚኮ ጋር ያደረጉት ቆይታ ክፍል ሁለት
#pmabiyahemed Ethiopian Broadcasting Corporation
4 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ያደረጉትን ቆይታ - ክፍል 2 ዛሬ ምሽት ከ2:30 ጀምሮ በፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ሁሉም የሚዲያ አማራጮች ይጠብቁን
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) [የሰኔ 16ቱ ጉዳይ] የፖለቲካ ሴራ ተንታኞች መጠቀምያም ሆኗል። ታስታውስ ከሆነ እለቱ ቅዳሜ ነበር፣ ዊኬንድ ነበር፣ ማምሻ ላይ ነበር ይሄ ጉዳይ የተፈጠረው። እና እኔ እዚህ ቢሮ ቆይቼ ከቢሮ ስወጣ ነው መረጃው የሰማሁት። እና ለሚዲያ መነገር አለበት የሚል ሀሳብ መጥቶ የሚዲያ አካላት ይጠሩ ብለን ፋና፣ ኢቢሲ፣ አሚኮ ተጠርተው ነበር። መግለጫ የሰጠሁበትን ቦታ እስከዛሬ አስታውሰዋለሁ እኔ። ነገር ግን ፋና እና ኢቢሲ ምናልባትም ዊኬንድ ስለሆነ ምሽትም ስለነበረ ስንጠራቸው በዚያ ፍጥነት አልመጡልንም፣ አሚኮ ግን ጎረቤት ነው እዚህ 4 ኪሎ ነው መስሪያ ቤቱ፣ መኪናም ላያስፈልገው ይችላል - እዚሁ ስለሆነ። ልክ ጥሪው ሲደረግ ወዲያው አሚኮ መጣ፣ አሚኮ መጥቶ የተወሰነ ደቂቃ ጠበቀን እነዚያ ቢደርሱ ብለን፣ ዘገዩብን። እና መጨረሻ የመጣው ሀሳብ 'ምንም እኮ ችግር የለውም አሚኮ ወስዶ ለሁሉም ሊያከፋፍል ስለሚችል ለአሚኮ ይሰጥ ተብሎ እኔ ቤት ነው ለአሚኮ የሰጠሁት። በኋላ ግን ባህርዳር ላይ ሆኖ መግለጫ የሰጠው ወደሚል የሴራ ትንተና ተቀይሯል። እንደዚህ ያለው ከእውነት የተፋታ፣ ዛሬም ለነገም የማይበጅ፣ ውስጥህ እያወቀ የሚሸነገል፣ የሚዋሽ ነገር ጥፋት ብቻ ነው የሚያመጣው እና... ያ ክስተት ከመነሻው የሚሳካ ነው፣ ከመነሻው አንድ ግብ የሚያሟላ ነው ባትልም፣ እንደ ጥቁር ጠባሳ የሚወሰድ መጥፎ ክስተት ነው ብዬ ነው የማየው።"
ጠቅላይ ሚ/ር ዐቢይ አህመድ
ጠቅላይ ሚ/ር ዐቢይ አህመድ
Sponsored by
Surafel
4 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች፡-
👉 ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በከፍተኛ ወታደራዊና የመንግሥት አመራሮች ላይ የተፈጸመው ግድያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትምምን ውስጥ ጠባሳ ፈጥሯል፡፡
👉 የፖለቲካ መተማመን በጣም እንዲቀዘቅዝ አድርጓል፣ በሰዎች መካከል አብረህ እየኖርክ፤ እየሰራህ፤ እየተሰበሰብክ የመተማመን ዝንባሌው በእጅጉ እንዲቀንስ አደርጓል፡፡
👉 አብረህ ስለ ሀገር ከምትመክረው ሰው አደጋ ያጋጥመኛል ብለህ እያሰብክ መምከር በእጅጉ ትምምንን የሚቀንስ ጉዳይ ስለሆነ እንደ አንድ ጠባሳ የሚታይ ክስተት ነው፡፡
👉 ክስተቱ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል አበላሽቶታል፤ ከንግግር ከውይይት ይልቅ በመሳሪያና በጉልበት ግለሰቦችን በማፈንና በመግደል ስልጣን የመጎናጸፍ ልምምድን የሚያስቀጥል ጠባሳ ሆኗል፡፡
👉 ገዳይንም፣ ሟችንም ሁለቱንም ወገኖች በጀግንነት ያወሳ የፖለቲካ ትርክት የታየበት ክስተት ነው፤ ይህንን አሁንም ቆም ብለን ማየት ይገባናል፡፡
👉 ታሪክን እየመረጥን፣ እያንሻፈፍን እና በፈለግነው መንገድ የማቆየት የትርክት ስብራት ጉዳይ አሁን ላለንበት አጠቃላይ ውጥንቅጥ ዋናው መሰረት ነው፡፡
👉 በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እስካሁን ከሚስተዋለው ከዚህ ውጥንቅጥ ወጥተን፤ ታሪክን እንዳለ አስቀምጠን ከመልካሙም ከስህተቱም መማር ይገባናል፡፡
👉 አሁን እዚህ እንደ ዋዛ በብሄርተኝነት ስሜት በአውራጃዊነት ስሜት ታሪክን አንሻፍፈን ብንጽፍ፣ ብንናገር ነገ ልጆቻችንን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን ማሰብ አለመቻል ደግሞ ያሳዝነኛል፡፡
👉 ይሄ ጉዳይ እንዳለ ታሪኩን አስቀምጠህ ከተቀመጠው ታሪክ ተነስተህ በሚኖረው ትንተና የፈለግከውን ነገር ወደ ቀኝ ወደ ግራ ወስደህ መማር ትችላለህ፡፡
👉 ታሪክን ማዛባት ግን እምብዛም ጠቃሚ አይደለም፤ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ነገም ዋጋ ያስከፍላል፣ ትውልድ ዋጋ ይከፍልበታል፡፡
👉 እኛ በህይወት እያለን የምናውቀውን ጉዳይ በተንሸዋረረ የታሪክ አረዳድ የምናስቀምጥ ከሆነ እኛ በማንኖርበት ሰዓት የሚኖረው ትወልድ እንዴት እንደሚወስደው አሁን ባለው የኢትዮጵያ ታሪክ መመልከት ይቻላል፡፡
👉 አሁን ያለው የኢትዮጵያ ታሪክ የዚህ የተንሸዋረረ የፖለቲካ ትርክት ውጤት ነው፡፡
👉 ታሪክን እንዳለ ማስቀመጥ ሳይሆን አዛብተን በማስቀመጣችን ምክንያት የሚፈጠር ችግር ነው፤ ከዚያም ሻገር ሲል የፖለቲካ ሴራ ተንታኞች መጠቀሚያም ሆኗል፡፡
👉 ያ ክስተት በተፈጠረበት ወቅት አሚኮን ጠርተን ለሕዝቡ መግለጫ የሰጠነው እዚሁ አዲስ አበባ መሆኑን ታውቃለህ፥ በኋላ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባህር ዳር ሆነው መግለጫ ሰጡ በሚል የሴራ ተንታኔ ተቀይሯል፡፡
👉 እንደዚህ ያለ ከእውነት የተፋታ፤ ለዛሬም ለነገም የማይበጅ፤ የሚሸነገል የሚዋሽ ነገር ጥፋት ብቻ ነው የሚያመጣው፡፡
👉 ክስተቱ እንደ ጥቁር ጠባሳ የሚወሰድ መጥፎ ክስተት ነው፡፡
በአቤል ነዋይ
👉 ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በከፍተኛ ወታደራዊና የመንግሥት አመራሮች ላይ የተፈጸመው ግድያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትምምን ውስጥ ጠባሳ ፈጥሯል፡፡
👉 የፖለቲካ መተማመን በጣም እንዲቀዘቅዝ አድርጓል፣ በሰዎች መካከል አብረህ እየኖርክ፤ እየሰራህ፤ እየተሰበሰብክ የመተማመን ዝንባሌው በእጅጉ እንዲቀንስ አደርጓል፡፡
👉 አብረህ ስለ ሀገር ከምትመክረው ሰው አደጋ ያጋጥመኛል ብለህ እያሰብክ መምከር በእጅጉ ትምምንን የሚቀንስ ጉዳይ ስለሆነ እንደ አንድ ጠባሳ የሚታይ ክስተት ነው፡፡
👉 ክስተቱ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል አበላሽቶታል፤ ከንግግር ከውይይት ይልቅ በመሳሪያና በጉልበት ግለሰቦችን በማፈንና በመግደል ስልጣን የመጎናጸፍ ልምምድን የሚያስቀጥል ጠባሳ ሆኗል፡፡
👉 ገዳይንም፣ ሟችንም ሁለቱንም ወገኖች በጀግንነት ያወሳ የፖለቲካ ትርክት የታየበት ክስተት ነው፤ ይህንን አሁንም ቆም ብለን ማየት ይገባናል፡፡
👉 ታሪክን እየመረጥን፣ እያንሻፈፍን እና በፈለግነው መንገድ የማቆየት የትርክት ስብራት ጉዳይ አሁን ላለንበት አጠቃላይ ውጥንቅጥ ዋናው መሰረት ነው፡፡
👉 በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እስካሁን ከሚስተዋለው ከዚህ ውጥንቅጥ ወጥተን፤ ታሪክን እንዳለ አስቀምጠን ከመልካሙም ከስህተቱም መማር ይገባናል፡፡
👉 አሁን እዚህ እንደ ዋዛ በብሄርተኝነት ስሜት በአውራጃዊነት ስሜት ታሪክን አንሻፍፈን ብንጽፍ፣ ብንናገር ነገ ልጆቻችንን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን ማሰብ አለመቻል ደግሞ ያሳዝነኛል፡፡
👉 ይሄ ጉዳይ እንዳለ ታሪኩን አስቀምጠህ ከተቀመጠው ታሪክ ተነስተህ በሚኖረው ትንተና የፈለግከውን ነገር ወደ ቀኝ ወደ ግራ ወስደህ መማር ትችላለህ፡፡
👉 ታሪክን ማዛባት ግን እምብዛም ጠቃሚ አይደለም፤ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ነገም ዋጋ ያስከፍላል፣ ትውልድ ዋጋ ይከፍልበታል፡፡
👉 እኛ በህይወት እያለን የምናውቀውን ጉዳይ በተንሸዋረረ የታሪክ አረዳድ የምናስቀምጥ ከሆነ እኛ በማንኖርበት ሰዓት የሚኖረው ትወልድ እንዴት እንደሚወስደው አሁን ባለው የኢትዮጵያ ታሪክ መመልከት ይቻላል፡፡
👉 አሁን ያለው የኢትዮጵያ ታሪክ የዚህ የተንሸዋረረ የፖለቲካ ትርክት ውጤት ነው፡፡
👉 ታሪክን እንዳለ ማስቀመጥ ሳይሆን አዛብተን በማስቀመጣችን ምክንያት የሚፈጠር ችግር ነው፤ ከዚያም ሻገር ሲል የፖለቲካ ሴራ ተንታኞች መጠቀሚያም ሆኗል፡፡
👉 ያ ክስተት በተፈጠረበት ወቅት አሚኮን ጠርተን ለሕዝቡ መግለጫ የሰጠነው እዚሁ አዲስ አበባ መሆኑን ታውቃለህ፥ በኋላ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባህር ዳር ሆነው መግለጫ ሰጡ በሚል የሴራ ተንታኔ ተቀይሯል፡፡
👉 እንደዚህ ያለ ከእውነት የተፋታ፤ ለዛሬም ለነገም የማይበጅ፤ የሚሸነገል የሚዋሽ ነገር ጥፋት ብቻ ነው የሚያመጣው፡፡
👉 ክስተቱ እንደ ጥቁር ጠባሳ የሚወሰድ መጥፎ ክስተት ነው፡፡
በአቤል ነዋይ
4 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሚኮ ጋር ያደረጉት ልዩ ቃለ መጠይቅ | ወቅታዊ ሀገራዊ እና የክልሉ ጉዳዮች
#ebcdotstream Ethiopia #pmabiyahmed #amhara #oromia #amico
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
#ebcdotstream Ethiopia #pmabiyahmed #amhara #oromia #amico
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
4 days ago
"ዘመናዊቷን ኢትዮጵያ ከአማራና ኦሮሞ ውህደት ውጭ ማየት አይቻልም"
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገሪቱን ለመቀየር ፖለቲካውንም ሆነ ኢኮኖሚውን ጎን ለጎን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበር ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩም የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአማራና ከኦሮሞ ሕዝቦች ጥብቅ ውህደትና ትስስር ውጭ ሊታይ አይችልም። የዓድዋ ድልም የዚሁ ታሪካዊ አንድነት ትልቁ ማሳያ ነው፤ አብሮ የመኖር ባህልም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ በሀገራችን ስልጣንን በኃይልና በሰው ግድያ ለመያዝ የመሞከር አጥፊ ባህል እንደነበር አውስተዋል። በዚህም የሰኔ 15ቱ ክስተት በለውጡ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሰዎች ያጣንበት የሕመም ጠባሳችን ነው ብለዋል።
ሆኖም ሕዝቡ ለውጡን በሙሉ ልብ የተቀበለ ሲሆን፣ በአንድነትና በትብብር አንዲት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደምንችል በምርጫው ወቅት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
***
“የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎች ለአጭር ጊዜ እፎይታ ተብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት መመለስ አይቻልም”
በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚነሡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ለአጭር ጊዜ እፎይታ ብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ መመለስ እንደማይቻል እና ጉዳዩ በሕግ አግባብ እና በሀገራዊ ምክክር ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የወልቃይትን ጉዳይ እንደ አብነት በማንሣት በትግራይም ሆነ በአማራ ክልል በኩል የሚነሡ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ዘላቂ መፍትሔው የሁለቱንም ሕዝቦች ጥቅም በማይጎዳ፣ በውይይት እና ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት ሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ካልሆነ መልሶ ለግጭት የሚዳርግ ቆይቶ የሚፈነዳ ቦምብ ይሆናል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በዚህም በፓርቲ ውስጥ የነበረውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራር ማስተካከል እና የክልሎችን ራስን የማስተዳደር መብት ማክበር ተችሏል ብለዋል ።
በተጨማሪም በመንግሥት ተቋማት አካታችነትን ማረጋገጥ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በካቢኔ እና በፖለቲካ ምኅዳር ማሳተፍ እንዲሁም አግላይ የነበሩ ትርክቶችን ማረቅም ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።
***
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል-
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሰኔ 15ቱን መጥፎ ክስተት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታሪክን ማዛባት ለነገው ትውልድ የሚተርፍ እዳ ነው ብለዋል።
ለውጥን ለማምጣት በጽናት ሲሰሩ የነበሩ የለውጥ አበጋዞችን ያጣንበት፣ በፖለቲካው መካከል የመተማመን መንፈስ እንዲሸረሸር ያደረገ እና የስልጣን ሽሚያ በሃይል የማስከበር መጥፎ ባህልን ያስቀጠለ አጋጣሚ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ እለቱና ስለተፈጠረው ክስተት ሲያብራሩ፤ እለቱ ቅዳሜ ነበረ፤ መረጃውን እንደሰማሁ ለህዝብ መግለጫ እንዲሰጥ ሚዲያዎች እንዲጠሩ አደረግኩ፤ ፋና እና ኢቢሲ በምሽቱ ፈጥነው አልደረሱም ነበር፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ግን እዚሁ 4 ኪሎ አቅራቢያ ስለነበር በፍጥነት ደረሰ ብለዋል።
መግለጫውን እኔ ቤት ሆኜ ለአሚኮ ሰጠሁ፤ በኋላ ግን 'ባህር ዳር ሆኖ መግለጫ ሰጠ' ተብሎ የሴራ ትንተና ተፈበረከበት በማለት አስታውሰዋል።
ይህ ክስተት ያስተማረን ትልቅ ሀቅም ታሪክን በትክክል አለማስቀመጥና ማዛባት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ እዳ ያተርፋል ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳይም ሟችም በአንድ ላይ 'ጀግና' የሚደረግበት የታሪክ ስብራት ሊቆም እንደሚገባም በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
***
"በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች በዘመናት መካከል አብረው ሲኖሩ በብዙ መልኩ የተጋመዱ፣ የተሳሰሩ፣ የተጋቡ፣ የተዋለዱ በጋራ የኖሩ ናቸው''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ethiopia #pmabiyahmed #currentaffairs #pmabiyahmed #amico #ethiopia #medemer #amharaandoromo #ethiopianunity
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገሪቱን ለመቀየር ፖለቲካውንም ሆነ ኢኮኖሚውን ጎን ለጎን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበር ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩም የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአማራና ከኦሮሞ ሕዝቦች ጥብቅ ውህደትና ትስስር ውጭ ሊታይ አይችልም። የዓድዋ ድልም የዚሁ ታሪካዊ አንድነት ትልቁ ማሳያ ነው፤ አብሮ የመኖር ባህልም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ በሀገራችን ስልጣንን በኃይልና በሰው ግድያ ለመያዝ የመሞከር አጥፊ ባህል እንደነበር አውስተዋል። በዚህም የሰኔ 15ቱ ክስተት በለውጡ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሰዎች ያጣንበት የሕመም ጠባሳችን ነው ብለዋል።
ሆኖም ሕዝቡ ለውጡን በሙሉ ልብ የተቀበለ ሲሆን፣ በአንድነትና በትብብር አንዲት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደምንችል በምርጫው ወቅት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
***
“የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎች ለአጭር ጊዜ እፎይታ ተብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት መመለስ አይቻልም”
በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚነሡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ለአጭር ጊዜ እፎይታ ብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ መመለስ እንደማይቻል እና ጉዳዩ በሕግ አግባብ እና በሀገራዊ ምክክር ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የወልቃይትን ጉዳይ እንደ አብነት በማንሣት በትግራይም ሆነ በአማራ ክልል በኩል የሚነሡ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ዘላቂ መፍትሔው የሁለቱንም ሕዝቦች ጥቅም በማይጎዳ፣ በውይይት እና ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት ሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ካልሆነ መልሶ ለግጭት የሚዳርግ ቆይቶ የሚፈነዳ ቦምብ ይሆናል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በዚህም በፓርቲ ውስጥ የነበረውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራር ማስተካከል እና የክልሎችን ራስን የማስተዳደር መብት ማክበር ተችሏል ብለዋል ።
በተጨማሪም በመንግሥት ተቋማት አካታችነትን ማረጋገጥ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በካቢኔ እና በፖለቲካ ምኅዳር ማሳተፍ እንዲሁም አግላይ የነበሩ ትርክቶችን ማረቅም ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።
***
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል-
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሰኔ 15ቱን መጥፎ ክስተት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታሪክን ማዛባት ለነገው ትውልድ የሚተርፍ እዳ ነው ብለዋል።
ለውጥን ለማምጣት በጽናት ሲሰሩ የነበሩ የለውጥ አበጋዞችን ያጣንበት፣ በፖለቲካው መካከል የመተማመን መንፈስ እንዲሸረሸር ያደረገ እና የስልጣን ሽሚያ በሃይል የማስከበር መጥፎ ባህልን ያስቀጠለ አጋጣሚ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ እለቱና ስለተፈጠረው ክስተት ሲያብራሩ፤ እለቱ ቅዳሜ ነበረ፤ መረጃውን እንደሰማሁ ለህዝብ መግለጫ እንዲሰጥ ሚዲያዎች እንዲጠሩ አደረግኩ፤ ፋና እና ኢቢሲ በምሽቱ ፈጥነው አልደረሱም ነበር፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ግን እዚሁ 4 ኪሎ አቅራቢያ ስለነበር በፍጥነት ደረሰ ብለዋል።
መግለጫውን እኔ ቤት ሆኜ ለአሚኮ ሰጠሁ፤ በኋላ ግን 'ባህር ዳር ሆኖ መግለጫ ሰጠ' ተብሎ የሴራ ትንተና ተፈበረከበት በማለት አስታውሰዋል።
ይህ ክስተት ያስተማረን ትልቅ ሀቅም ታሪክን በትክክል አለማስቀመጥና ማዛባት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ እዳ ያተርፋል ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳይም ሟችም በአንድ ላይ 'ጀግና' የሚደረግበት የታሪክ ስብራት ሊቆም እንደሚገባም በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
***
"በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች በዘመናት መካከል አብረው ሲኖሩ በብዙ መልኩ የተጋመዱ፣ የተሳሰሩ፣ የተጋቡ፣ የተዋለዱ በጋራ የኖሩ ናቸው''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ethiopia #pmabiyahmed #currentaffairs #pmabiyahmed #amico #ethiopia #medemer #amharaandoromo #ethiopianunity
5 days ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከጎንደር ወደ ሁመራ ቋሚ በረራ ሊጀምር ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከነገ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ከጎንደር ወደ ሁመራ ቋሚ የበረራ አገልግሎት እንደሚጀምር አስታውቋል።
በአዲሱ መርሃ ግብር መሠረት ዘወትር ቅዳሜ ከጎንደር ወደ ሁመራ እንዲሁም ዘወትር ሰኞ ከሁመራ ወደ ጎንደር ቋሚ የበረራ አገልግሎት ይሰጣል።
አየር መንገዱ የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎቹን በማስፋፋት ለተጓዦች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እየሠራ መሆኑን ገልጿል።
አዲሱ የበረራ መስመር የማኅበራዊና የኢኮኖሚ ትስስርን በማጠናከር የክልሉን ተንቀሳቃሽነት እንደሚያበረታታም ተጠቁሟል።
አሚኮ
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከነገ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ከጎንደር ወደ ሁመራ ቋሚ የበረራ አገልግሎት እንደሚጀምር አስታውቋል።
በአዲሱ መርሃ ግብር መሠረት ዘወትር ቅዳሜ ከጎንደር ወደ ሁመራ እንዲሁም ዘወትር ሰኞ ከሁመራ ወደ ጎንደር ቋሚ የበረራ አገልግሎት ይሰጣል።
አየር መንገዱ የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎቹን በማስፋፋት ለተጓዦች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እየሠራ መሆኑን ገልጿል።
አዲሱ የበረራ መስመር የማኅበራዊና የኢኮኖሚ ትስስርን በማጠናከር የክልሉን ተንቀሳቃሽነት እንደሚያበረታታም ተጠቁሟል።
አሚኮ
5 days ago
u1320u1245u120bu12ed u121au1292u1235u1275u122d u12d0u1262u12ed u12a0u1215u1218u12f5 (u12f6/u122d) u12a8u12a0u121au12ae u130bu122d u12ebu12f0u1228u1309u1275 u1246u12edu1273 - u12adu134du120d 1
u12dbu122c u121du123du1275 2:30 u120bu12ed u1260u12a2u1272u126a u12dcu1293 u127bu1293u120du1363 u1260u12a2u1275u12eeu1335u12eb u122cu12f2u12eeu1363 u1260u12a4u134d.u12a4u121d u12a0u12f2u1235 97.1 u12a5u1293 u1260u1201u1209u121d u12e8u12a2u1262u1232 u12f6u1275u1235u1275u122au121d u12e8u121bu1285u1260u122bu12ca u121au12f2u12eb u12a0u121bu122bu132eu127bu127du1295 u12edu1320u1265u1241u1295! #ethiopia #ebc #pmabiyahmed #currentaffairs ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሚኮ ጋር ያደረጉት ቆይታ - ክፍል 1
ዛሬ ምሽት 2:30 ላይ በኢቲቪ ዜና ቻናል፣ በኢትዮጵያ ሬዲዮ፣ በኤፍ.ኤም አዲስ 97.1 እና በሁሉም የኢቢሲ ዶትስትሪም የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን ይጠብቁን! #ethiopia #ebc #pmabiyahmed #currentaffairs
Sponsored by
Surafel
5 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ያደረጉት ቆይታ ክፍል 1 ዛሬ ምሽት 2:30 ይጠብቁ።
#ethiopia #ebc #pmabiyahmed #currentaffairs
6 days ago
u1320u1245u120bu12ed u121au1292u1235u1275u122d u12d0u1262u12ed u12a0u1215u1218u12f5 (u12f6/u122d) u12a8u12a0u121bu122b u121au12f2u12eb u12aeu122du1356u122cu123du1295 (u12a0u121au12ae) u130bu122d u12ebu12f0u1228u1309u1275 u1246u12edu1273 u12adu134du120d 1 u12a0u122du1265 u121du123du1275 2:30 u12edu1320u1265u1241u1362
#pmoethiopia #ethiopia #pmabiyahmed ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ያደረጉት ቆይታ ክፍል 1 አርብ ምሽት 2:30 ይጠብቁ።
#pmoethiopia #ethiopia #pmabiyahmed
6 days ago
14 days ago
የወረቀት ሳሙናን ለገበያ ያቀረበችው የባቲ ከተማዋ ወጣት
ባቲ፣ ኢትዮጵያ — አብዛኞቻችን ሳሙናን በደረቅ (በቁራጭ)፣ በዱቄት ወይም በፈሳሽ መልክ ብቻ አውቀን ለለመድነው አጠቃቀም፣ የባቲ ከተማ ነዋሪዋ ወጣት ኢክራም ሙሐመድ አዲስና ምቹ አማራጭ ይዛ ብቅ ብላለች።
ወጣቷ ከአካባቢዋ ችግሮች በመነሳት ለእጅ መታጠቢያ የሚሆን «የወረቀት ሳሙና» በመፍጠር የብዙዎችን ትኩረት ስባለች።
ኢክራም ለዚህ የፈጠራ ሥራዋ መነሻ የሆነውን አጋጣሚ ስታብራራ፤ በተለያዩ ቦታዎች ለስራና ለጉዞ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት እጅ ለመታጠብ የሚሆን ሳሙና ማጣት የተለመደ ፈተና በመሆኑ፣ ይህንን ክፍተት የሚሞላ መፍትሔ ለመፈለግ መነሳቷን ትናገራለች።
ይህ የወረቀት ሳሙና ከባህላዊ የሳሙና አይነቶች የሚለዩት በርካታ አዎንታዊ ጎኖች አሉት፦
* ቀደም ሲል ከምናውቃቸውና ለተላላፊ በሽታዎች ሊያጋልጡ ከሚችሉ የጋራ መጠቀሚያ ሳሙናዎች በተለየ፣ እያንዳንዱ ሰው ለብቻው በግል ለመጠቀም በሚመች መልኩ የተዘጋጀ ነው።
* በቦታ፣ በሁኔታዎችና በቦርሳ ጥበት ሳይገደቡ በየትኛውም ስፍራ ይዞ ለመንቀሳቀስ እና ለመጠቀም አጅግ ምቹ ነው።
* ከአንዱ ጥቅል ላይ አንድ ቀጭን ወረቀት በመለየት በእጅ ላይ አድርጎ በጥቂት ውሃ በማሸት ብቻ በቀላሉ መጠቀም ይቻላል።
ምርቱን ለማዘጋጀት በአካባቢዋ በቀላሉ የሚገኙ ጥሬ እቃዎችን የተጠቀመች ሲሆን፣ የእጅ ቆዳን በማይጎዳ መልኩ የኬሚካል ውህዶችን በራሷ በማቀናጀት ለወረቀት ሳሙናው የሚፈለገውን ቅርጽ አስይዛዋለች። ለዚህ ስኬቷም የአባቷ እገዛና ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበረ ትገልጻለች።
ምርቷን በአካባቢዋ መጠሪያ «ገንደዳዩ» በሚል ስያሜ ሰይማ ወደ ገበያ ያቀረበችው ወጣት ኢክራም፤ በተለያዩ ባዛሮች ላይ በማሳተፍ ከተጠቃሚዎች እጅግ አዎንታዊ እና አበረታች ግብረ-መልስ ማግኘቷን ተናግራለች።
በቀጣይም የዚሁን የወረቀት ሳሙና ጥራትና መጠን በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር በስፋት ለሀገር ውስጥ ገበያ ለማቅረብ ጠንክራ እየሰራች እንደሆነና የወደፊት አላማዋም ምርቱን ማስፋፋት እንደሆነ ገልጻለች።
Via አሚኮ
Seledadotio
Seledadotio
ባቲ፣ ኢትዮጵያ — አብዛኞቻችን ሳሙናን በደረቅ (በቁራጭ)፣ በዱቄት ወይም በፈሳሽ መልክ ብቻ አውቀን ለለመድነው አጠቃቀም፣ የባቲ ከተማ ነዋሪዋ ወጣት ኢክራም ሙሐመድ አዲስና ምቹ አማራጭ ይዛ ብቅ ብላለች።
ወጣቷ ከአካባቢዋ ችግሮች በመነሳት ለእጅ መታጠቢያ የሚሆን «የወረቀት ሳሙና» በመፍጠር የብዙዎችን ትኩረት ስባለች።
ኢክራም ለዚህ የፈጠራ ሥራዋ መነሻ የሆነውን አጋጣሚ ስታብራራ፤ በተለያዩ ቦታዎች ለስራና ለጉዞ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት እጅ ለመታጠብ የሚሆን ሳሙና ማጣት የተለመደ ፈተና በመሆኑ፣ ይህንን ክፍተት የሚሞላ መፍትሔ ለመፈለግ መነሳቷን ትናገራለች።
ይህ የወረቀት ሳሙና ከባህላዊ የሳሙና አይነቶች የሚለዩት በርካታ አዎንታዊ ጎኖች አሉት፦
* ቀደም ሲል ከምናውቃቸውና ለተላላፊ በሽታዎች ሊያጋልጡ ከሚችሉ የጋራ መጠቀሚያ ሳሙናዎች በተለየ፣ እያንዳንዱ ሰው ለብቻው በግል ለመጠቀም በሚመች መልኩ የተዘጋጀ ነው።
* በቦታ፣ በሁኔታዎችና በቦርሳ ጥበት ሳይገደቡ በየትኛውም ስፍራ ይዞ ለመንቀሳቀስ እና ለመጠቀም አጅግ ምቹ ነው።
* ከአንዱ ጥቅል ላይ አንድ ቀጭን ወረቀት በመለየት በእጅ ላይ አድርጎ በጥቂት ውሃ በማሸት ብቻ በቀላሉ መጠቀም ይቻላል።
ምርቱን ለማዘጋጀት በአካባቢዋ በቀላሉ የሚገኙ ጥሬ እቃዎችን የተጠቀመች ሲሆን፣ የእጅ ቆዳን በማይጎዳ መልኩ የኬሚካል ውህዶችን በራሷ በማቀናጀት ለወረቀት ሳሙናው የሚፈለገውን ቅርጽ አስይዛዋለች። ለዚህ ስኬቷም የአባቷ እገዛና ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበረ ትገልጻለች።
ምርቷን በአካባቢዋ መጠሪያ «ገንደዳዩ» በሚል ስያሜ ሰይማ ወደ ገበያ ያቀረበችው ወጣት ኢክራም፤ በተለያዩ ባዛሮች ላይ በማሳተፍ ከተጠቃሚዎች እጅግ አዎንታዊ እና አበረታች ግብረ-መልስ ማግኘቷን ተናግራለች።
በቀጣይም የዚሁን የወረቀት ሳሙና ጥራትና መጠን በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር በስፋት ለሀገር ውስጥ ገበያ ለማቅረብ ጠንክራ እየሰራች እንደሆነና የወደፊት አላማዋም ምርቱን ማስፋፋት እንደሆነ ገልጻለች።
Via አሚኮ
Seledadotio
Seledadotio
23 days ago
''አትመጣም ወይ ማርቆስ ከተድላው ከተማ
ቢሻህ በአውሮፕላን ቢሻህ በሎንቺና''
📌የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ተመረቀ፤ ለከተማዋ የኢንዱስትሪ አብዮት በር ከፈተ
#ethiopia | ለበርካታ ዓመታት በናፍቆት ሲጠበቅ የነበረው የደብረ ማርቆስ ንጉስ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ ራዕዩን ዕውን አድርጎ በዛሬው እለት በይፋ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል።
የአውሮፕላን ማረፊያው አገልግሎት መጀመር ለከተማዋና ለአካባቢው ከፍተኛ የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይዞ የመጣ ሲሆን በቀጣይም በከተማዋ ላይ ትልቅ የኢንዱስትሪ አብዮት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ መደበኛ የሥራ መጀመሪያ ከዚህ ቀደም ተቀዛቅዞ የነበረውን የከተማዋን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት አልሚ ባለሀብቶች ያለምንም ስጋት መጥተው እንዲያለሙ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
ከአሚኮ እንደሰማነው ከሆነ በአውሮፕላን ማረፊያው የሙከራ በረራ ወቅት ትልልቅ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች መምጣት የጀመሩ ሲሆን አሁን ደግሞ የውጭ ባለሀብቶችም ጭምር መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ በርከት ብለው መምጣት ጀምረዋል።
ከዚህም ባሻገር የአውሮፕላን ማረፊያው አገልግሎት አምራቾች ምርቶቻቸው ሳይበላሹ በአጭር ጊዜ ለገበያ እንዲያቀርቡ በማስቻል የምርት እጥረትን በዘላቂነት ይረዳል፤ ጥራትንም በእጅጉ ይጨምራል።
ከኢንቨስትመንት ባለፈ የከተማዋን የቱሪዝም ዘርፍና አጠቃላይ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ የሚያነቃቃው ይህ ዕድል ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ይዞ የመጣ በመሆኑ ባለሀብቶች መጥተው በከተማዋ እንዲያለሙ የከተማው አስተዳደር ጥሪውን አቅርቧል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
ቢሻህ በአውሮፕላን ቢሻህ በሎንቺና''
📌የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ተመረቀ፤ ለከተማዋ የኢንዱስትሪ አብዮት በር ከፈተ
#ethiopia | ለበርካታ ዓመታት በናፍቆት ሲጠበቅ የነበረው የደብረ ማርቆስ ንጉስ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ ራዕዩን ዕውን አድርጎ በዛሬው እለት በይፋ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል።
የአውሮፕላን ማረፊያው አገልግሎት መጀመር ለከተማዋና ለአካባቢው ከፍተኛ የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይዞ የመጣ ሲሆን በቀጣይም በከተማዋ ላይ ትልቅ የኢንዱስትሪ አብዮት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ መደበኛ የሥራ መጀመሪያ ከዚህ ቀደም ተቀዛቅዞ የነበረውን የከተማዋን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት አልሚ ባለሀብቶች ያለምንም ስጋት መጥተው እንዲያለሙ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
ከአሚኮ እንደሰማነው ከሆነ በአውሮፕላን ማረፊያው የሙከራ በረራ ወቅት ትልልቅ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች መምጣት የጀመሩ ሲሆን አሁን ደግሞ የውጭ ባለሀብቶችም ጭምር መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ በርከት ብለው መምጣት ጀምረዋል።
ከዚህም ባሻገር የአውሮፕላን ማረፊያው አገልግሎት አምራቾች ምርቶቻቸው ሳይበላሹ በአጭር ጊዜ ለገበያ እንዲያቀርቡ በማስቻል የምርት እጥረትን በዘላቂነት ይረዳል፤ ጥራትንም በእጅጉ ይጨምራል።
ከኢንቨስትመንት ባለፈ የከተማዋን የቱሪዝም ዘርፍና አጠቃላይ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ የሚያነቃቃው ይህ ዕድል ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ይዞ የመጣ በመሆኑ ባለሀብቶች መጥተው በከተማዋ እንዲያለሙ የከተማው አስተዳደር ጥሪውን አቅርቧል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የወፍ ዋሻ ጥብቅ ደን ብሔራዊ ፓርክ ሆኖ እንዲተዳደር ተወሰነ
*******************
የአማራ ክልል መሥተዳድር ምክር ቤት በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘው የወፍ ዋሻ ጥብቅ ደን፣ ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በብሔራዊ ፓርኮች የአስተዳደር ሥርዓት እንዲመራ የቀረበውን የደንብ ረቂቅ ሙሉ በሙሉ አጽድቋል።
የአማራ ክልል የአካባቢ እና ደን ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ እንደገለጹት፤ የወፍ ዋሻ ጥብቅ ደን ከ8 ሺህ 732 ሄክታር በላይ ስፋት ያለው ሲሆን፣ በአንኮበር፣ በባሶና ወራና እንዲሁም በጣርማ በር ወረዳዎች በሚዋሰኑ 15 የገጠር ቀበሌዎች የተከበበ ደን ነው።
ጥብቅ ደኑ የበርካታ ብዝኃ-ሕይወት ሀብቶች መኖሪያ በመሆኑ፣ ጥበቃና ልማት እየተደረገለት ወደ ብሔራዊ ፓርክነት እንዲያድግ ተከታታይ ሳይንሳዊ ጥናቶች ሲካሄዱበት መቆየታቸውን ኃላፊው አብራርተዋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ጥብቅ ደኑ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት መሠረት በማድረግ በርካታ የጥበቃና የልማት ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን የገለጹት አቶ ተስፋሁን፤ ስፍራው በክልሉና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሚገኙ ብሔራዊ ፓርኮች ጋር እኩል ጥበቃና ልማት እንዲደረግለት የሚያስችል የጥበቃና ልማት ደንብ በማዘጋጀት ለክልሉ መሥተዳድር ምክር ቤት አቅርበው ሲያስፈጽሙ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
አካባቢው በብሔራዊ ፓርክነት በይፋ ተመዝግቦ የቀጣይ የቱሪዝም ተስፋ እንዲሆን ውሳኔ በመተላለፉ፣ የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ኃላፊ ለክልሉ መሥተዳድር ምክር ቤት የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።
የአማራ ክልል የአካባቢ እና ደን ጥበቃ ባለሥልጣን በአሁኑ ወቅት በክልሉ ውስጥ አምስት ብሔራዊ ፓርኮችን እና ሰባት የማኅበረሰብ ጥብቅ ስፍራዎችን በበላይነት በማስተዳደር የጥበቃና ልማት ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አሚኮ ዘግቧል።
#ethiopia #northshewa #wofwashapark #nationalpark #biodiversity #ecotourism
*******************
የአማራ ክልል መሥተዳድር ምክር ቤት በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘው የወፍ ዋሻ ጥብቅ ደን፣ ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በብሔራዊ ፓርኮች የአስተዳደር ሥርዓት እንዲመራ የቀረበውን የደንብ ረቂቅ ሙሉ በሙሉ አጽድቋል።
የአማራ ክልል የአካባቢ እና ደን ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ እንደገለጹት፤ የወፍ ዋሻ ጥብቅ ደን ከ8 ሺህ 732 ሄክታር በላይ ስፋት ያለው ሲሆን፣ በአንኮበር፣ በባሶና ወራና እንዲሁም በጣርማ በር ወረዳዎች በሚዋሰኑ 15 የገጠር ቀበሌዎች የተከበበ ደን ነው።
ጥብቅ ደኑ የበርካታ ብዝኃ-ሕይወት ሀብቶች መኖሪያ በመሆኑ፣ ጥበቃና ልማት እየተደረገለት ወደ ብሔራዊ ፓርክነት እንዲያድግ ተከታታይ ሳይንሳዊ ጥናቶች ሲካሄዱበት መቆየታቸውን ኃላፊው አብራርተዋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ጥብቅ ደኑ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት መሠረት በማድረግ በርካታ የጥበቃና የልማት ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን የገለጹት አቶ ተስፋሁን፤ ስፍራው በክልሉና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሚገኙ ብሔራዊ ፓርኮች ጋር እኩል ጥበቃና ልማት እንዲደረግለት የሚያስችል የጥበቃና ልማት ደንብ በማዘጋጀት ለክልሉ መሥተዳድር ምክር ቤት አቅርበው ሲያስፈጽሙ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
አካባቢው በብሔራዊ ፓርክነት በይፋ ተመዝግቦ የቀጣይ የቱሪዝም ተስፋ እንዲሆን ውሳኔ በመተላለፉ፣ የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ኃላፊ ለክልሉ መሥተዳድር ምክር ቤት የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።
የአማራ ክልል የአካባቢ እና ደን ጥበቃ ባለሥልጣን በአሁኑ ወቅት በክልሉ ውስጥ አምስት ብሔራዊ ፓርኮችን እና ሰባት የማኅበረሰብ ጥብቅ ስፍራዎችን በበላይነት በማስተዳደር የጥበቃና ልማት ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አሚኮ ዘግቧል።
#ethiopia #northshewa #wofwashapark #nationalpark #biodiversity #ecotourism
1 month ago
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከ2,800 በላይ ተማሪዎችን ነገ ያስመርቃል
#ethiopia | እንጅባራ – እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ (አረንጓዴው ግቢ) ለ7ኛ ጊዜ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 2,812 ተማሪዎች ነገ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት እንደሚያስመርቅ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጋርዳቸው ወርቁ አስታውቀዋል።
ዩኒቨርሲቲው በ52 የትምህርት ፕሮግራሞች በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች የሚያስመርቅ ሲሆን፣ ከተመራቂዎቹ ውስጥ 40 በመቶዎቹ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።
የዘንድሮውን የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ለየት ከሚያደርጉት ጉዳዮች መካከል ዩኒቨርሲቲው በአንስቴዢያ፣ በሶፍትዌር ምህንድስና፣ በአገወኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ እንዲሁም በመምህራን ትምህርትና ካሪኩለም ዘርፎች በአዳዲስ ፕሮግራሞች ለመጀመሪያ ጊዜ ተመራቂዎችን ማፍራቱ ይገኝበታል።
ፕሬዝዳንቱ እንዳስረዱት፣ የአገወኛ ቋንቋ፣ ባህልና ታሪክ ጥናትና ልማት የዩኒቨርሲቲው ዋነኛ የትኩረት መስኮች መካከል አንዱ ሲሆን፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በአገወኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ በመደበኛና በተከታታይ ፕሮግራሞች የሰለጠኑ 150 ተማሪዎችን ያስመርቃል።
የምረቃ ፕሮግራሙ በአሚኮ የቀጥታ ስርጭት የሚተላለፍ ሲሆን፣ በመርሃ ግብሩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ ምሁራን እና አርቲስቶች እንደሚገኙም ተገልጿል።
በመጨረሻም ዶ/ር ጋርዳቸው ወርቁ ለተማሪዎቹ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ላደረጉ መምህራን፣ ሠራተኞች እና የአካባቢው ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
#ethiopia | እንጅባራ – እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ (አረንጓዴው ግቢ) ለ7ኛ ጊዜ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 2,812 ተማሪዎች ነገ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት እንደሚያስመርቅ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጋርዳቸው ወርቁ አስታውቀዋል።
ዩኒቨርሲቲው በ52 የትምህርት ፕሮግራሞች በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች የሚያስመርቅ ሲሆን፣ ከተመራቂዎቹ ውስጥ 40 በመቶዎቹ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።
የዘንድሮውን የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ለየት ከሚያደርጉት ጉዳዮች መካከል ዩኒቨርሲቲው በአንስቴዢያ፣ በሶፍትዌር ምህንድስና፣ በአገወኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ እንዲሁም በመምህራን ትምህርትና ካሪኩለም ዘርፎች በአዳዲስ ፕሮግራሞች ለመጀመሪያ ጊዜ ተመራቂዎችን ማፍራቱ ይገኝበታል።
ፕሬዝዳንቱ እንዳስረዱት፣ የአገወኛ ቋንቋ፣ ባህልና ታሪክ ጥናትና ልማት የዩኒቨርሲቲው ዋነኛ የትኩረት መስኮች መካከል አንዱ ሲሆን፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በአገወኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ በመደበኛና በተከታታይ ፕሮግራሞች የሰለጠኑ 150 ተማሪዎችን ያስመርቃል።
የምረቃ ፕሮግራሙ በአሚኮ የቀጥታ ስርጭት የሚተላለፍ ሲሆን፣ በመርሃ ግብሩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ ምሁራን እና አርቲስቶች እንደሚገኙም ተገልጿል።
በመጨረሻም ዶ/ር ጋርዳቸው ወርቁ ለተማሪዎቹ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ላደረጉ መምህራን፣ ሠራተኞች እና የአካባቢው ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
2 months ago
በምዕራብ ጎጃም ዞን 418 ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለዋል
************************
በአማራ ክልል የፀጥታ ችግሩ ካጋጠመ ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት መንግሥት የሰላም ጥሪዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል።
ይህንንም ተከትሎ በክልሉ በርካታ ታጣቂዎች የኃይል አማራጭን በመተው እና የሰላም ጥሪውን በመቀበል ወደ መደበኛ ሕይወታቸው ተመልሰዋል።
የምዕራብ ጎጃም ዞን የሰላም እና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር አዱኛ አዳሙ፣ በዚህ ዓመት 418 ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ መከተላቸውን ገልጸዋል።
የሰላም አማራጭን የተቀበሉ ታጣቂዎች የተሃድሶ ሥልጠና እንዲወስዱ በማድረግ መደበኛ ሕይወታቸውን መጀመራቸውንም ጠቅሰዋል።
አሁን ላይ በተለያዩ ዘርፎች በመሠማራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው፣ ኅብረተሰቡ በየጊዜው የሰላም ሁኔታው እንዲረጋጋ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጀት ትልቁን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
አሁንም የሰላም በሩ ክፍት መሆኑን አንስተው፣ ይህን በማይቀበሉ ታጣቂዎች ላይ ሕግ የማስከበር ሥራው በተጠናከረ መንገድ እንደሚቀጥል መናገራቸውን አሚኮ ዘግቧል።
#ebc #ethiopia #peace
************************
በአማራ ክልል የፀጥታ ችግሩ ካጋጠመ ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት መንግሥት የሰላም ጥሪዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል።
ይህንንም ተከትሎ በክልሉ በርካታ ታጣቂዎች የኃይል አማራጭን በመተው እና የሰላም ጥሪውን በመቀበል ወደ መደበኛ ሕይወታቸው ተመልሰዋል።
የምዕራብ ጎጃም ዞን የሰላም እና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር አዱኛ አዳሙ፣ በዚህ ዓመት 418 ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ መከተላቸውን ገልጸዋል።
የሰላም አማራጭን የተቀበሉ ታጣቂዎች የተሃድሶ ሥልጠና እንዲወስዱ በማድረግ መደበኛ ሕይወታቸውን መጀመራቸውንም ጠቅሰዋል።
አሁን ላይ በተለያዩ ዘርፎች በመሠማራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው፣ ኅብረተሰቡ በየጊዜው የሰላም ሁኔታው እንዲረጋጋ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጀት ትልቁን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
አሁንም የሰላም በሩ ክፍት መሆኑን አንስተው፣ ይህን በማይቀበሉ ታጣቂዎች ላይ ሕግ የማስከበር ሥራው በተጠናከረ መንገድ እንደሚቀጥል መናገራቸውን አሚኮ ዘግቧል።
#ebc #ethiopia #peace
2 months ago
የሟቾች ቁጥር 31 ደረሰ🕯🕯
በተከሰተው የመኪና አደጋ የሟቾች ቁጥር 31 መድረሱን የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።
ዛሬ ጠዋት በደሴ እና ኮምቦልቻ መካከል ሐረጎ በተባለ ሥፍራ በደረሰ የመኪና አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን መዘገባችን ይታወሰል።
አሁን ደግሞ የሟቾች ቁጥር መጨመሩን ፖሊስ አስታውቋል። የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ እንደገለጸው በአደጋው ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች 31 ደርሷል።
አደጋው የደረሰው በተለምዶ ከደሴ ወደ ኮምቦልቻ በሚወስደው ሐረጎ "S" መንገድ መታጠፊያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ከንጋቱ 12:00 መኾኑን የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ጌታቸው ሙህዬ ተናግረዋል።
ተሽከርካሪው ከ100 ሜትር በላይ ርዝመት ያለው ገደል ውስጥ በመግባቱ ሹፌሩን ጨምሮ የ31 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በ33 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱንም ኮማንደር ጌታቸው ለአሚኮ ገልጸዋል።
ተሽከርካሪው 64 ሰዎችን አሳፍሮ በመጓዝ ላይ እንደነበር ያነሱት ኮማንደር ጌታቸው ተጎጅዎች በደሴ እና በኮምቦልቻ ሆስፒታሎች ሕክምና እየተደረገላቸው እንደኾነም አንስተዋል።
የአደጋው መንስኤም እየተጣራ መኾኑን አስታውቀዋል።
ለተጎጅ ቤተሰቦችም መጽናናትን እንመኛለን።
Seledadotio
Seledadotio
በተከሰተው የመኪና አደጋ የሟቾች ቁጥር 31 መድረሱን የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።
ዛሬ ጠዋት በደሴ እና ኮምቦልቻ መካከል ሐረጎ በተባለ ሥፍራ በደረሰ የመኪና አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን መዘገባችን ይታወሰል።
አሁን ደግሞ የሟቾች ቁጥር መጨመሩን ፖሊስ አስታውቋል። የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ እንደገለጸው በአደጋው ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች 31 ደርሷል።
አደጋው የደረሰው በተለምዶ ከደሴ ወደ ኮምቦልቻ በሚወስደው ሐረጎ "S" መንገድ መታጠፊያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ከንጋቱ 12:00 መኾኑን የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ጌታቸው ሙህዬ ተናግረዋል።
ተሽከርካሪው ከ100 ሜትር በላይ ርዝመት ያለው ገደል ውስጥ በመግባቱ ሹፌሩን ጨምሮ የ31 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በ33 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱንም ኮማንደር ጌታቸው ለአሚኮ ገልጸዋል።
ተሽከርካሪው 64 ሰዎችን አሳፍሮ በመጓዝ ላይ እንደነበር ያነሱት ኮማንደር ጌታቸው ተጎጅዎች በደሴ እና በኮምቦልቻ ሆስፒታሎች ሕክምና እየተደረገላቸው እንደኾነም አንስተዋል።
የአደጋው መንስኤም እየተጣራ መኾኑን አስታውቀዋል።
ለተጎጅ ቤተሰቦችም መጽናናትን እንመኛለን።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ።
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል።
አደጋው የደረሰው ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ ነው።
ዛሬ ሰኔ 08/10/18ዓ.ም ማለዳ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ አውቶቡስ በተለምዶ ሐረጎ እየተባለ በሚጠራው መንገድ ላይ በደረሠበት አደጋ እስካሁን የ28 ሰው ሕይወት ሲያልፍ በርካቶች ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባተቸዋል።
የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ገብቶ ነው አደጋው የደረሠው። በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ አሁንም ርብርብ እየተደረገ መኾኑን የገለጸው ፓሊስ የአደጋውን ምክንያት በመጣራት ላይ መኾኑን አስታውቋል።
አሚኮ
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል።
አደጋው የደረሰው ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ ነው።
ዛሬ ሰኔ 08/10/18ዓ.ም ማለዳ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ አውቶቡስ በተለምዶ ሐረጎ እየተባለ በሚጠራው መንገድ ላይ በደረሠበት አደጋ እስካሁን የ28 ሰው ሕይወት ሲያልፍ በርካቶች ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባተቸዋል።
የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ገብቶ ነው አደጋው የደረሠው። በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ አሁንም ርብርብ እየተደረገ መኾኑን የገለጸው ፓሊስ የአደጋውን ምክንያት በመጣራት ላይ መኾኑን አስታውቋል።
አሚኮ
2 months ago
በደሴ እና በኮምቦልቻ መካከል
በትራፊክ አደጋ የ28 ሕይወት ተቀጠፈ
#ethiopia | ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ በነበረ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ላይ በደረሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የ28 ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ ገለጸ።
አደጋው የተከሰተው በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል ልዩ ስሙ ሐረጎ በሚባለው አካባቢ መሆኑ ታውቋል።
ዛሬ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ማለዳ ላይ ሲጓዝ የነበረው ይህ አውቶቡስ መንገዱን ስቶ በግምት 100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል በመግባቱ የ28 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ሊያልፍ ችሏል።
በተጨማሪም በጉዞው ላይ በነበሩ ሌሎች በርካታ ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በአሁኑ ወቅት ከአደጋው የተረፉትን ተጎጂዎች በፍጥነት ወደ ህክምና ተቋማት ለማድረስ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ የገለጸው ፖሊስ፣ አደጋው የተከሰተበትን ትክክለኛ መንስኤ ለማወቅ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን አስታውቋል።
ሳሙኤል ኪሮስ
አሚኮ
#የጎዳናአደጋ #የትራፊክአደጋ #ደሴ #ኮምቦልቻ #አሚኮ #የአደጋመረጃ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
በትራፊክ አደጋ የ28 ሕይወት ተቀጠፈ
#ethiopia | ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ በነበረ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ላይ በደረሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የ28 ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ ገለጸ።
አደጋው የተከሰተው በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል ልዩ ስሙ ሐረጎ በሚባለው አካባቢ መሆኑ ታውቋል።
ዛሬ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ማለዳ ላይ ሲጓዝ የነበረው ይህ አውቶቡስ መንገዱን ስቶ በግምት 100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል በመግባቱ የ28 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ሊያልፍ ችሏል።
በተጨማሪም በጉዞው ላይ በነበሩ ሌሎች በርካታ ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በአሁኑ ወቅት ከአደጋው የተረፉትን ተጎጂዎች በፍጥነት ወደ ህክምና ተቋማት ለማድረስ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ የገለጸው ፖሊስ፣ አደጋው የተከሰተበትን ትክክለኛ መንስኤ ለማወቅ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን አስታውቋል።
ሳሙኤል ኪሮስ
አሚኮ
#የጎዳናአደጋ #የትራፊክአደጋ #ደሴ #ኮምቦልቻ #አሚኮ #የአደጋመረጃ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ወጣቶች በሚያደርጉት የነቃ ተሳትፎ ሀገር ይገነባል - አቶ አረጋ ከበደ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በወቅታዊ የልማትና የሰላም ሥራዎች ዙሪያ ከወጣቶች ጋር በባሕር ዳር ተወያይተዋል፡፡
በመድረኩ የሰላም እና የልማት ሥራዎችን በትጋት በማከናወን ሀገርን ወደ ላቀ ከፍታ ለመውሰድ የወጣቶች ሚና ምን መሆን እንዳለበት ተነስቷል።
በዚሁ ወቅት አቶ አረጋ ከበደ ፥ በወጣቶች ሁለንተናዊና የነቃ ተሳትፎ ሀገር ይገነባል፤ የሕዝብ ሰላም በዘላቂነት ይረጋገጣል፤ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችም ከዳር ይደርሳሉ ብለዋል።
የባሕር ዳር ከተማ ብሎም የክልሉ ወጣቶች በትላልቅ ሀገራዊ ሁነቶች በንቃት የሚሳተፉ፣ በውጤትም አጅበው ሥራዎችን የሚፈጽሙ ናቸው ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
ወጣቶች በተለይም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላሙ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ሚናቸው ከፍተኛ እንደነበር አንስተው÷ ከመሪዎቻቸው ጋር በመተባበር የልማት ሥራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ አንስተዋል።
ወጣቶች በሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑና የራሳቸውን ብሎም የሀገራቸውን ኢኮኖሚያዊ ልዕልና እንዲያረጋግጡ እንሠራለን ነው ያሉት፡፡
ለሕዝብ ሰላምና ልማት የሚተጉ ወጣቶች የሀገር መሠረቶች ናቸው፤ ወጣቶች ሀገርን በሚጠቅሙ ዘርፎች ላይ ሁሉ በንቃት በመሳተፍ የልማት አርበኛ ሊሆኑ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በወቅታዊ የልማትና የሰላም ሥራዎች ዙሪያ ከወጣቶች ጋር በባሕር ዳር ተወያይተዋል፡፡
በመድረኩ የሰላም እና የልማት ሥራዎችን በትጋት በማከናወን ሀገርን ወደ ላቀ ከፍታ ለመውሰድ የወጣቶች ሚና ምን መሆን እንዳለበት ተነስቷል።
በዚሁ ወቅት አቶ አረጋ ከበደ ፥ በወጣቶች ሁለንተናዊና የነቃ ተሳትፎ ሀገር ይገነባል፤ የሕዝብ ሰላም በዘላቂነት ይረጋገጣል፤ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችም ከዳር ይደርሳሉ ብለዋል።
የባሕር ዳር ከተማ ብሎም የክልሉ ወጣቶች በትላልቅ ሀገራዊ ሁነቶች በንቃት የሚሳተፉ፣ በውጤትም አጅበው ሥራዎችን የሚፈጽሙ ናቸው ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
ወጣቶች በተለይም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላሙ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ሚናቸው ከፍተኛ እንደነበር አንስተው÷ ከመሪዎቻቸው ጋር በመተባበር የልማት ሥራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ አንስተዋል።
ወጣቶች በሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑና የራሳቸውን ብሎም የሀገራቸውን ኢኮኖሚያዊ ልዕልና እንዲያረጋግጡ እንሠራለን ነው ያሉት፡፡
ለሕዝብ ሰላምና ልማት የሚተጉ ወጣቶች የሀገር መሠረቶች ናቸው፤ ወጣቶች ሀገርን በሚጠቅሙ ዘርፎች ላይ ሁሉ በንቃት በመሳተፍ የልማት አርበኛ ሊሆኑ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
Sponsored by
Surafel
2 months ago
"ሀገር የተሟላ ሉዓላዊነት እና ነፃነት የሚኖራት በሁሉም መስክ ራስን መቻል ሲቻል ነው" - የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
*******************
የአማራ ክልል "ኢትዮጵያ ታምርት" የንቅናቄ ማጠቃለያ መርሐ ግብር "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ መልዕክት በኮምቦልቻ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ ክልሉን ተወዳዳሪ እና ቀዳሚ ለማድረግ ሁሉም አካል በቅንጅት እና በትብብር ሊሠራ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ በራስ አቅም የማደግ፣ የራስን ምርት የማሳደግ እና የመጠቀም እንዲሁም ሀገርን በአንድነት የማበልጸግ እሳቤ የወለደው መሆኑን አቶ አረጋ ገልጸዋል።
"ሀገር የተሟላ ሉዓላዊነት እና ነፃነት የሚኖራት በሁሉም መስክ ራስን መቻል ሲቻል ነው" ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በምርት ራሱን ያልቻለ ሀገር የሌሎች ሀገራት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማኅበራዊ ጥገኛ መሆኑ እንደማይቀር አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያ በቀኝ ግዛት ያልተገዛች ሀገር ብትሆንም፣ የተሟላ ነፃነት እና ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ሕዝቡን ከድህነት እና ኋላቀርነት ማላቀቅ እንዲሁም በምርት ራስን መቻል የውዴታ ሳይሆን ግዴታ መሆኑን አብራርተዋል።
የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዕድገት በከፍተኛ ደረጃ እየቀየረው መምጣቱን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የነበሩ የኃይል፣ የፋይናንስ አቅርቦት እና ሌሎች ማነቆዎች በሂደት እየተፈቱ መምጣታቸውን ተናግረዋል።
በሀገር አቀፍም ሆነ በክልል ደረጃ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የማምረት አቅም ከበፊቱ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን ጠቁመው፣ አሁንም ግን ለአነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ዕድገት ብዙ መሥራት እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
የክልሉ ኢንዱስትሪ በፀጥታ ችግር ውስጥ ማለፉን በማስታወስም፣ ኢንዱስትሪዎችን ማስፋፋት ራሱ የፀጥታ ችግሩን እንደሚፈታው ተናግረዋል።
"ኢኮኖሚው ያደገ ሀገር እና ሕዝብ ወደ ግጭት አይገባም" በማለትም የኢንዱስትሪው ዕድገት ለሰላም ያለውን አስተዋፅኦ አጉልተዋል።
ይህንንም መሠረት በማድረግ፣ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የክልሉ የ25 ዓመታት የአሻጋሪ ዕድገት እና የዘላቂ ልማት ዕቅድ ቁልፍ የትኩረት አቅጣጫ መደረጉን ገልጸዋል።
የፀጥታ ችግር ሳይበግራቸው በክልሉ በመሥራት ለውጤት የበቁ ባለሀብቶችን አመስግነዋል።
"የኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ የክልሉን ጸጋ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ባለሀብቶች ለማስተዋወቅ፣ የገበያ ትሥሥር ለመፍጠር እና የመንግሥት እና የባለሀብቱን ቅርርብ ለማሻሻል ዓይነተኛ ሚና መጫወቱን አብራርተዋል።
የክልሉ መንግሥት አዳዲስም ሆነ ነባር ባለሀብቶችን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሌሎች ባለሀብቶችም ወደ ሥራ እንዲገቡ ጥሪ ማቅረባቸውን አሚኮ ዘግቧል።
#ethiopia #ebc #madeinethiopia #industry
*******************
የአማራ ክልል "ኢትዮጵያ ታምርት" የንቅናቄ ማጠቃለያ መርሐ ግብር "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ መልዕክት በኮምቦልቻ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ ክልሉን ተወዳዳሪ እና ቀዳሚ ለማድረግ ሁሉም አካል በቅንጅት እና በትብብር ሊሠራ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ በራስ አቅም የማደግ፣ የራስን ምርት የማሳደግ እና የመጠቀም እንዲሁም ሀገርን በአንድነት የማበልጸግ እሳቤ የወለደው መሆኑን አቶ አረጋ ገልጸዋል።
"ሀገር የተሟላ ሉዓላዊነት እና ነፃነት የሚኖራት በሁሉም መስክ ራስን መቻል ሲቻል ነው" ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በምርት ራሱን ያልቻለ ሀገር የሌሎች ሀገራት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማኅበራዊ ጥገኛ መሆኑ እንደማይቀር አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያ በቀኝ ግዛት ያልተገዛች ሀገር ብትሆንም፣ የተሟላ ነፃነት እና ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ሕዝቡን ከድህነት እና ኋላቀርነት ማላቀቅ እንዲሁም በምርት ራስን መቻል የውዴታ ሳይሆን ግዴታ መሆኑን አብራርተዋል።
የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዕድገት በከፍተኛ ደረጃ እየቀየረው መምጣቱን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የነበሩ የኃይል፣ የፋይናንስ አቅርቦት እና ሌሎች ማነቆዎች በሂደት እየተፈቱ መምጣታቸውን ተናግረዋል።
በሀገር አቀፍም ሆነ በክልል ደረጃ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የማምረት አቅም ከበፊቱ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን ጠቁመው፣ አሁንም ግን ለአነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ዕድገት ብዙ መሥራት እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
የክልሉ ኢንዱስትሪ በፀጥታ ችግር ውስጥ ማለፉን በማስታወስም፣ ኢንዱስትሪዎችን ማስፋፋት ራሱ የፀጥታ ችግሩን እንደሚፈታው ተናግረዋል።
"ኢኮኖሚው ያደገ ሀገር እና ሕዝብ ወደ ግጭት አይገባም" በማለትም የኢንዱስትሪው ዕድገት ለሰላም ያለውን አስተዋፅኦ አጉልተዋል።
ይህንንም መሠረት በማድረግ፣ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የክልሉ የ25 ዓመታት የአሻጋሪ ዕድገት እና የዘላቂ ልማት ዕቅድ ቁልፍ የትኩረት አቅጣጫ መደረጉን ገልጸዋል።
የፀጥታ ችግር ሳይበግራቸው በክልሉ በመሥራት ለውጤት የበቁ ባለሀብቶችን አመስግነዋል።
"የኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ የክልሉን ጸጋ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ባለሀብቶች ለማስተዋወቅ፣ የገበያ ትሥሥር ለመፍጠር እና የመንግሥት እና የባለሀብቱን ቅርርብ ለማሻሻል ዓይነተኛ ሚና መጫወቱን አብራርተዋል።
የክልሉ መንግሥት አዳዲስም ሆነ ነባር ባለሀብቶችን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሌሎች ባለሀብቶችም ወደ ሥራ እንዲገቡ ጥሪ ማቅረባቸውን አሚኮ ዘግቧል።
#ethiopia #ebc #madeinethiopia #industry
2 months ago
አዲስ ዓለም አቀፍ የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር አዲስ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ በጋራ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
ይህ አዲስ የቪዛ ካርድ ደንበኞች ወደተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚጓዙበት ወቅት የገንዘብ ክፍያዎችን በቀላሉ ለመፈጸም የሚያስችላቸው ሲሆን፣ ካርዱን በሚጠቀሙበት ጊዜም የሸባ ማይልስ ማበረታቻ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
አገልግሎቱን ለማግኘት ግን የሁለቱም ተቋማት ማለትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኛ መሆን ያስፈልጋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ እንደገለጹት፣ የአሁኑ ዘመን የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በስፋት የሚፈልግ በመሆኑ ይህ ይፋ የተደረገው ዓለም አቀፍ ካርድ የባንኩን ደንበኞች የውጭ ሀገር የንግድና የገንዘብ ዝውውር በእጅጉ የሚያቀላጥፍ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ በበኩላቸው፣ አየር መንገዱ የደንበኞቹን የአገልግሎት እርካታ ለማሳደግና አሠራሩን ዘመናዊ ለማድረግ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ አዲሱ የክፍያ ካርድ የሁለቱንም አንጋፋ ተቋማት ደንበኞች በእጅጉ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ማብራራታቸውን አሚኮ በዘገባው አስፍሯል።
#የኢትዮጵያንግድባንክ #የኢትዮጵያአየርመንገድ #ቪዛካርድ #የዲጂታልክፍያ #የባንክአገልግሎት #የአየርጉዞ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር አዲስ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ በጋራ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
ይህ አዲስ የቪዛ ካርድ ደንበኞች ወደተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚጓዙበት ወቅት የገንዘብ ክፍያዎችን በቀላሉ ለመፈጸም የሚያስችላቸው ሲሆን፣ ካርዱን በሚጠቀሙበት ጊዜም የሸባ ማይልስ ማበረታቻ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
አገልግሎቱን ለማግኘት ግን የሁለቱም ተቋማት ማለትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኛ መሆን ያስፈልጋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ እንደገለጹት፣ የአሁኑ ዘመን የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በስፋት የሚፈልግ በመሆኑ ይህ ይፋ የተደረገው ዓለም አቀፍ ካርድ የባንኩን ደንበኞች የውጭ ሀገር የንግድና የገንዘብ ዝውውር በእጅጉ የሚያቀላጥፍ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ በበኩላቸው፣ አየር መንገዱ የደንበኞቹን የአገልግሎት እርካታ ለማሳደግና አሠራሩን ዘመናዊ ለማድረግ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ አዲሱ የክፍያ ካርድ የሁለቱንም አንጋፋ ተቋማት ደንበኞች በእጅጉ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ማብራራታቸውን አሚኮ በዘገባው አስፍሯል።
#የኢትዮጵያንግድባንክ #የኢትዮጵያአየርመንገድ #ቪዛካርድ #የዲጂታልክፍያ #የባንክአገልግሎት #የአየርጉዞ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Comments