13 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በ2022ቱ የኳታር ዓለም ዋንጫ ማሳረጊያ ላይ ፈረንሳይ በፍጻሜው ብትሸነፍም ኪሊያን ምባፔ ሃት-ትሪክ ሰርቶ የወርቅ ጫማውን ሲቀበል ፊቱ ላይ ምንም ዓይነት ፈገግታ አልነበረም። ግቦች ለቡድን ድል ሙሉ ዋስትና ባይሆኑም፣ አንድ አደገኛ አጥቂ ግን ለቡድኑ ሁሌም ትልቅ ተስፋ እና ዕድል ፈጣሪ ነው። የ2026ቱ ታላቁ እና ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማዕበል እየተቃረበ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የወርቅ ጫማ አሸናፊዎችን ታሪካዊ ዳራ እና ቀጣዮቹን አጓጊ ተገማቾች በጥልቀት እንቃኛለን።
ለእንግሊዛዊው ኮከብ ሃሪ ኬን ጥሩ ያልሆነ ዜና አለ ታሪክ እንደሚነግረን በ30 ዓመት እና ከዚያ በላይ ዕድሜ ላይ ሆኖ የወርቅ ጫማ ማሸነፍ እጅግ ከባድ ነው። ይህ ክስተት በታሪክ የተመዘገበው አንድ ጊዜ ብቻ ሲሆን፣ በ1998ቱ የፈረንሳይ ዓለም ዋንጫ ክሮኤሺያዊው ዳቮር ሱከር በ30 ዓመቱ 6 ግቦችን በማስቆጠር ነበር ይህን ተአምር ያሳካው። ሱከር ለዚህ ሕግ ብቸኛው ልዩ ማሳያ ሲሆን፣ በአማካይ የወርቅ ጫማ አሸናፊዎች ዕድሜ 24.7 ዓመት ነው። በ2022 ምባፔ በ24 ዓመቱ 35 ዓመት የነበረውን ሊዮኔል ሜሲን በአንድ ግብ ብቻ በልጦ ማሸነፉ የዕድሜ አማካዩን በትንሹ ዝቅ አድርጎታል። በታሪክ በለጋ ዕድሜው ይህን ክብር ያገኘው ሀንጋሪያዊው ፍሎሪያን አልበርት ሲሆን፣ በ1962ቱ የቺሊ ውድድር ላይ በ20 ዓመት ከስምንት ወር ዕድሜው አሸንፏል። ይህንን ታሪካዊ ሪከርድ ለመስበር የስፔኑ የ18 ዓመት ታዳጊ ላሚን ያማል በአሁኑ ወቅት በጉጉት ዓይኑን ጥሏል።
በሌላ በኩል ደግሞ ብቻውን የሚያጨበጭብ እጅ የለምና አንድ ስኬታማ አጥቂ ጥሩ የኳስ አቅርቦት እና ቡድኑ በውድድሩ ሩቅ መጓዝ መቻል ያስፈልገዋል። አምስት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያነሳችው ብራዚል፣ ከ1938ቱ ሊዮኒዳስ እስከ 2002ቱ ሮናልዶ ድረስ ስድስት አደገኛ የወርቅ ጫማ አሸናፊዎችን ማፍራቷ አያስገርምም። በምድብ ጨዋታዎች ብዙ ግብ ማስቆጠር ጥሩ ጅምር ቢሆንም፣ ቡድንዎ ወደ ጥሎ ማለፍ ካላደገ ግን ትልቅ ኪሳራ ነው። ለምሳሌ በ2018ቱ የሩሲያ ውድድር ክርስቲያኖ ሮናልዶ በምድብ ጨዋታዎች 4 ግቦችን ቢያገባም ፖርቱጋል በ16ቱ ዙር በመውደቋ ዕድሉን አጥቷል፤ በአንጻሩ 6 ግቦችን አግብቶ ከእንግሊዝ ጋር ግማሽ ፍጻሜ የደረሰው ሃሪ ኬን አሸናፊ ሆኗል። የዚህ ሕግ ብቸኛው ልዩነት የ1994ቱ ኦሌግ ሳሌንኮ ሲሆን፣ ሩሲያ ከምድቧ ባትሻገርም በካሜሩን ላይ በምድብ ጨዋታ 5 ግቦችን (በድምሩ 6 ግቦች) በማስቆጠር ሀገሩ ከመመለሱ በፊት የወርቅ ጫማውን አረጋግጦ ነበር።
በክለብ ደረጃ የሚታይ ስኬትም ለዓለም ዋንጫው ትልቅ መነሻ ነው። ጀርመናዊው ቶማስ ሙለር በ2010 ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያቀና ለሀገሩ አንድም ግብ አግብቶ ባያውቅም፣ በባየር ሙኒክ ስኬታማ የውድድር ዓመት አሳልፎ መምጣቱ በዓለም ዋንጫው የወርቅ ጫማ እንዲያሸንፍ ረድቶታል። ታሪክ እንደሚጠቅሰው ክለባቸው ከምርጥ አራት ውጪ ሆኖ የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አግቢ በመሆን ያጠናቀቁ ተጫዋቾች በታሪክ ሁለት ብቻ ናቸው። ግብ ሲገጣጠም ደግሞ ፊፋ አሸናፊውን ለመለየት አሲስትን የሚቆጥር ሲሆን፣ በ2010 ሙለር፣ ቪያ፣ ስናይደር እና ፎርላን እኩል 5 ግቦች በነበራቸው ወቅት ሙለር በ3 አሲስት አሸንፏል። አሲስትም እኩል ከሆነ ደግሞ አነስተኛ ደቂቃ የተጫወተው ተጫዋች የወርቅ ጫማውን በበላይነት ይወስዳል።
የ2026ቱ የወርቅ ጫማ ፉክክርም እጅግ የበረታ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ማንም ተጫዋች የወርቅ ጫማን ከሁለት ጊዜ በላይ አላሸነፈም፤ ዘንድሮ ግን ምባፔ እና ሃሪ ኬን ይህንን ታሪክ ለመጻፍ ትልቅ ዕድል አላቸው። ምባፔ በማጣሪያው 4 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን ጠንካራዋ ፈረንሳይ ሩቅ ስለምትጓዝ ተመራጭ ነው። የ32 ዓመቱ ሃሪ ኬን ዕድሜው ቢገፋም፣ በዘንድሮው የክለብ ቆይታው 54 ግቦችን አስቆጥሮ በታላቅ ብቃት ላይ ይገኛል። በሌላ በኩል የ38 ዓመቱ ሜሲ ካቢኔ ውስጥ 8 የባሎን ዶር ክብሮች ቢኖሩም የወርቅ ጫማ ባለመኖሩ ይህ ውድድር የመጨረሻ ዕድሉ ነው። አርጀንቲና ከእርሱ በተጨማሪ በኮፓ አሜሪካ 2024 የወርቅ ጫማ ያሸነፈውን ላውታሮ ማርቲኔዝን እና በአትሌቲኮ ማድሪድ ድንቅ ጊዜ ያሳለፈውን ጁሊያን አልቫሬዝን ይዛ ትቀርባለች። የስፔኑ ታዳጊ ላሚን ያማል፣ የ41 ዓመቱ ፖርቱጋላዊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ለማንችስተር ሲቲ 26 የሊግ ግቦችን ያገባው ኤርሊንግ ሀላንድ፣ በሪያል ማድሪድ ድንቅ ጊዜ ያሳለፈው ቪኒሽየስ ጁኒየር እና ፈረንሳዊው ኡስማን ዴምቤሌም ዋናዎቹ ተፎካካሪዎች ናቸው።
ከነዚህ ዋና ዋና ተገማቾች በተጨማሪ ያልተጠበቁ ድብቅ አደጋዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ። የዩሮ 2024 የፍጻሜ አሸናፊ ግብ ያስቆጠረው የስፔኑ ሚኬል ኦያርዛባል በማጣሪያው ድንቅ ብቃት ያሳየ ሲሆን፣ ስዊድናውያኑ አሌክሳንደር ኢሳክ እና ቪክቶር ዮከረስ፣ እንዲሁም ብራዚላውያኑ ራፊንሃ እና ኢጎር ቲያጎ አስገራሚ ተፎካካሪዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ለባየር ሙኒክ 22 ግቦችን እና 30 አሲስቶችን ያደረገው ፈረንሳዊው ማይክል ኦሊሴ እና በማንኛውም ሰዓት ጨዋታን መለወጥ የሚችለው የናፖሊው አጥቂ ቤልጅየማዊው ሮሜሉ ሉካኩ የውድድሩ አስገራሚ ድብቅ ዕጩዎች ተብለው ተጠቅሰዋል።
ለእንግሊዛዊው ኮከብ ሃሪ ኬን ጥሩ ያልሆነ ዜና አለ ታሪክ እንደሚነግረን በ30 ዓመት እና ከዚያ በላይ ዕድሜ ላይ ሆኖ የወርቅ ጫማ ማሸነፍ እጅግ ከባድ ነው። ይህ ክስተት በታሪክ የተመዘገበው አንድ ጊዜ ብቻ ሲሆን፣ በ1998ቱ የፈረንሳይ ዓለም ዋንጫ ክሮኤሺያዊው ዳቮር ሱከር በ30 ዓመቱ 6 ግቦችን በማስቆጠር ነበር ይህን ተአምር ያሳካው። ሱከር ለዚህ ሕግ ብቸኛው ልዩ ማሳያ ሲሆን፣ በአማካይ የወርቅ ጫማ አሸናፊዎች ዕድሜ 24.7 ዓመት ነው። በ2022 ምባፔ በ24 ዓመቱ 35 ዓመት የነበረውን ሊዮኔል ሜሲን በአንድ ግብ ብቻ በልጦ ማሸነፉ የዕድሜ አማካዩን በትንሹ ዝቅ አድርጎታል። በታሪክ በለጋ ዕድሜው ይህን ክብር ያገኘው ሀንጋሪያዊው ፍሎሪያን አልበርት ሲሆን፣ በ1962ቱ የቺሊ ውድድር ላይ በ20 ዓመት ከስምንት ወር ዕድሜው አሸንፏል። ይህንን ታሪካዊ ሪከርድ ለመስበር የስፔኑ የ18 ዓመት ታዳጊ ላሚን ያማል በአሁኑ ወቅት በጉጉት ዓይኑን ጥሏል።
በሌላ በኩል ደግሞ ብቻውን የሚያጨበጭብ እጅ የለምና አንድ ስኬታማ አጥቂ ጥሩ የኳስ አቅርቦት እና ቡድኑ በውድድሩ ሩቅ መጓዝ መቻል ያስፈልገዋል። አምስት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያነሳችው ብራዚል፣ ከ1938ቱ ሊዮኒዳስ እስከ 2002ቱ ሮናልዶ ድረስ ስድስት አደገኛ የወርቅ ጫማ አሸናፊዎችን ማፍራቷ አያስገርምም። በምድብ ጨዋታዎች ብዙ ግብ ማስቆጠር ጥሩ ጅምር ቢሆንም፣ ቡድንዎ ወደ ጥሎ ማለፍ ካላደገ ግን ትልቅ ኪሳራ ነው። ለምሳሌ በ2018ቱ የሩሲያ ውድድር ክርስቲያኖ ሮናልዶ በምድብ ጨዋታዎች 4 ግቦችን ቢያገባም ፖርቱጋል በ16ቱ ዙር በመውደቋ ዕድሉን አጥቷል፤ በአንጻሩ 6 ግቦችን አግብቶ ከእንግሊዝ ጋር ግማሽ ፍጻሜ የደረሰው ሃሪ ኬን አሸናፊ ሆኗል። የዚህ ሕግ ብቸኛው ልዩነት የ1994ቱ ኦሌግ ሳሌንኮ ሲሆን፣ ሩሲያ ከምድቧ ባትሻገርም በካሜሩን ላይ በምድብ ጨዋታ 5 ግቦችን (በድምሩ 6 ግቦች) በማስቆጠር ሀገሩ ከመመለሱ በፊት የወርቅ ጫማውን አረጋግጦ ነበር።
በክለብ ደረጃ የሚታይ ስኬትም ለዓለም ዋንጫው ትልቅ መነሻ ነው። ጀርመናዊው ቶማስ ሙለር በ2010 ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያቀና ለሀገሩ አንድም ግብ አግብቶ ባያውቅም፣ በባየር ሙኒክ ስኬታማ የውድድር ዓመት አሳልፎ መምጣቱ በዓለም ዋንጫው የወርቅ ጫማ እንዲያሸንፍ ረድቶታል። ታሪክ እንደሚጠቅሰው ክለባቸው ከምርጥ አራት ውጪ ሆኖ የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አግቢ በመሆን ያጠናቀቁ ተጫዋቾች በታሪክ ሁለት ብቻ ናቸው። ግብ ሲገጣጠም ደግሞ ፊፋ አሸናፊውን ለመለየት አሲስትን የሚቆጥር ሲሆን፣ በ2010 ሙለር፣ ቪያ፣ ስናይደር እና ፎርላን እኩል 5 ግቦች በነበራቸው ወቅት ሙለር በ3 አሲስት አሸንፏል። አሲስትም እኩል ከሆነ ደግሞ አነስተኛ ደቂቃ የተጫወተው ተጫዋች የወርቅ ጫማውን በበላይነት ይወስዳል።
የ2026ቱ የወርቅ ጫማ ፉክክርም እጅግ የበረታ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ማንም ተጫዋች የወርቅ ጫማን ከሁለት ጊዜ በላይ አላሸነፈም፤ ዘንድሮ ግን ምባፔ እና ሃሪ ኬን ይህንን ታሪክ ለመጻፍ ትልቅ ዕድል አላቸው። ምባፔ በማጣሪያው 4 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን ጠንካራዋ ፈረንሳይ ሩቅ ስለምትጓዝ ተመራጭ ነው። የ32 ዓመቱ ሃሪ ኬን ዕድሜው ቢገፋም፣ በዘንድሮው የክለብ ቆይታው 54 ግቦችን አስቆጥሮ በታላቅ ብቃት ላይ ይገኛል። በሌላ በኩል የ38 ዓመቱ ሜሲ ካቢኔ ውስጥ 8 የባሎን ዶር ክብሮች ቢኖሩም የወርቅ ጫማ ባለመኖሩ ይህ ውድድር የመጨረሻ ዕድሉ ነው። አርጀንቲና ከእርሱ በተጨማሪ በኮፓ አሜሪካ 2024 የወርቅ ጫማ ያሸነፈውን ላውታሮ ማርቲኔዝን እና በአትሌቲኮ ማድሪድ ድንቅ ጊዜ ያሳለፈውን ጁሊያን አልቫሬዝን ይዛ ትቀርባለች። የስፔኑ ታዳጊ ላሚን ያማል፣ የ41 ዓመቱ ፖርቱጋላዊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ለማንችስተር ሲቲ 26 የሊግ ግቦችን ያገባው ኤርሊንግ ሀላንድ፣ በሪያል ማድሪድ ድንቅ ጊዜ ያሳለፈው ቪኒሽየስ ጁኒየር እና ፈረንሳዊው ኡስማን ዴምቤሌም ዋናዎቹ ተፎካካሪዎች ናቸው።
ከነዚህ ዋና ዋና ተገማቾች በተጨማሪ ያልተጠበቁ ድብቅ አደጋዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ። የዩሮ 2024 የፍጻሜ አሸናፊ ግብ ያስቆጠረው የስፔኑ ሚኬል ኦያርዛባል በማጣሪያው ድንቅ ብቃት ያሳየ ሲሆን፣ ስዊድናውያኑ አሌክሳንደር ኢሳክ እና ቪክቶር ዮከረስ፣ እንዲሁም ብራዚላውያኑ ራፊንሃ እና ኢጎር ቲያጎ አስገራሚ ተፎካካሪዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ለባየር ሙኒክ 22 ግቦችን እና 30 አሲስቶችን ያደረገው ፈረንሳዊው ማይክል ኦሊሴ እና በማንኛውም ሰዓት ጨዋታን መለወጥ የሚችለው የናፖሊው አጥቂ ቤልጅየማዊው ሮሜሉ ሉካኩ የውድድሩ አስገራሚ ድብቅ ዕጩዎች ተብለው ተጠቅሰዋል።
4 days ago
በኢትዮጵያ ታሪክ የመራጮችና የዕጩዎች ቁጥር ሪከርድ የተሰበረበት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ
https://youtu.be/1duvno4In...
#ethiopia #generalelection #voterscard #የዜጎች_ድምፅ #የዕጩዎች_ሪከርድ
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በህንድ ኮልካታ ከተማ የሚገኘው ግዙፉ የሊዮኔል ሜሲ ሀውልት የተተከለው በዲሴምበር ወር ተጨዋቹ በአገሪቱ ውስጥ ያደረገውን ጉብኝት በማስመልከት ነበር፡፡ ይህ 21 ሜትር የሚረዝመውና ወርቃማ ቀለም የተቀባው ሀውልት በዌስት ቤንጋል ግዛት ኮልካታ ከተማ እምብርት ላይ ቆሞ ቆይቷል፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ይህ ሀውልት በንፋስ እየወዛወዘ ይገኛል፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ሰራተኞች ሀውልቱ እንዳይወድቅ የተለያዩ ገመዶችን በመጠቀም እንዲጠናከር አድርገውታል፡፡
ይሁን እንጂ የከተማው ባለስልጣናት ዛሬ በሰጡት መግለጫ ሀውልቱ ከዚህ በኋላ ለደህንነት አስጊ በመሆኑ እንደሚነሳ አስታውቀዋል፡፡ የዌስት ቤንጋል ግዛት የፓርላማ አባል የሆኑት ሻራዳዋት ሙከርጂ ለኤኤፍፒ ሲናገሩ ‹‹ሀውልቱ በንፋስ እየተወዛወዘ መሆኑን ሰምተናል፡፡ የግዛቱ መሀንዲሶችም ለደህንነት አስጊ መሆኑን ገልፀውልናል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሀውልቱን ማንሳት ከማቆም የበለጠ ቀላል ነው፡፡ ስለዚህም በተቻለ ፍጥነት የምናነሳው ይሆናል›› ያሉ ሲሆን ሀውልቱ ሌላ ቦታ ስለመተከል አለመተከሉ ያሉት ነገር የለም፡፡
ህንድ 1.4 ቢሊዮን ህዝብ ያላት አገር ብትሆንም በአገሪቱ ውስጥ ተወዳጅ የሆነው ስፖርት ክሪኬትስ ነው፡፡ በእግር ኳስ ከአለም በ142ተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የፊፋ መረጃ ያሳያል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አርጀንቲናዊው የ38 አመቱ የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ከሳምንታት በኋላ በሚጀመረው የአለም ዋንጫ ላይ እንደሚሳተፍ እስካሁን በይፋ ማረጋገጫ አልሰጠም፡፡ በውድድሩ የሚሳተፍ ከሆነ ግን በአለም ዋንጫ ላይ 6 ጊዜ በመሳተፍ ሪከርድን የሚጋራ ይሆናል፡፡
ይሁን እንጂ የከተማው ባለስልጣናት ዛሬ በሰጡት መግለጫ ሀውልቱ ከዚህ በኋላ ለደህንነት አስጊ በመሆኑ እንደሚነሳ አስታውቀዋል፡፡ የዌስት ቤንጋል ግዛት የፓርላማ አባል የሆኑት ሻራዳዋት ሙከርጂ ለኤኤፍፒ ሲናገሩ ‹‹ሀውልቱ በንፋስ እየተወዛወዘ መሆኑን ሰምተናል፡፡ የግዛቱ መሀንዲሶችም ለደህንነት አስጊ መሆኑን ገልፀውልናል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሀውልቱን ማንሳት ከማቆም የበለጠ ቀላል ነው፡፡ ስለዚህም በተቻለ ፍጥነት የምናነሳው ይሆናል›› ያሉ ሲሆን ሀውልቱ ሌላ ቦታ ስለመተከል አለመተከሉ ያሉት ነገር የለም፡፡
ህንድ 1.4 ቢሊዮን ህዝብ ያላት አገር ብትሆንም በአገሪቱ ውስጥ ተወዳጅ የሆነው ስፖርት ክሪኬትስ ነው፡፡ በእግር ኳስ ከአለም በ142ተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የፊፋ መረጃ ያሳያል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አርጀንቲናዊው የ38 አመቱ የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ከሳምንታት በኋላ በሚጀመረው የአለም ዋንጫ ላይ እንደሚሳተፍ እስካሁን በይፋ ማረጋገጫ አልሰጠም፡፡ በውድድሩ የሚሳተፍ ከሆነ ግን በአለም ዋንጫ ላይ 6 ጊዜ በመሳተፍ ሪከርድን የሚጋራ ይሆናል፡፡
10 days ago
"ለመላው የአርሰናል ደጋፊዎች እንኳን ደስ አላችሁ፣ የማንችስተር ሲቲም 2 ዋንጫ በልቷል እንኳን ደስ አላችሁ፣ የዩናይትድ ደጋፊዎችም ብሩኖ ሪከርድ ሰብሯል እንኳን ደስ አላችሁ በቀጣይ ሲዝን በሪከርድ ሳይሆን በዋንጫ ለመደሰት ያብቃችሁ!" ወ/ሪት ሄርመን ከቦሌ
11 days ago
ብሩኖ ፈርናንዴዝ 21 ለግብ የሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል አዲስ ሪከርድ ሰበረ
#ethiopia | ብሩኖ ፈርናንዴዝ በቴሪ ሄነሪ እና በኬቨን ዴብሩይነ ተይዞ የነበረውን ለግብ ኳስ አመቻችቶ የማቀበል ሪከርድ ሰበረ።
በሊጉ የመጨረሻ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናይትድ ከብራይተን ጋር እያደረጉት ባለው ጨዋታ 33ኛው ደቂቃ ላይ ፓትሪክ ዶርጉ ላስቆጠረው ግብ ኳስ አመቻችቶ በማቀበሉ ሪከርዱን ሊሰብር ችሏል።
የማንችስተር ዩናይትዱ አማካይ ብሩኖ ፈርናንዴዝ በዚህ ዓመት በሊጉ 21 ለግብ የሆነ ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ብሩኖ ፈርናንዴዝ በቴሪ ሄነሪ እና በኬቨን ዴብሩይነ ተይዞ የነበረውን ለግብ ኳስ አመቻችቶ የማቀበል ሪከርድ ሰበረ።
በሊጉ የመጨረሻ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናይትድ ከብራይተን ጋር እያደረጉት ባለው ጨዋታ 33ኛው ደቂቃ ላይ ፓትሪክ ዶርጉ ላስቆጠረው ግብ ኳስ አመቻችቶ በማቀበሉ ሪከርዱን ሊሰብር ችሏል።
የማንችስተር ዩናይትዱ አማካይ ብሩኖ ፈርናንዴዝ በዚህ ዓመት በሊጉ 21 ለግብ የሆነ ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
11 days ago
አትሌት አበባ አረጋዊ በኦታዋ ማራቶን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ጻፈች
#ethiopia | በአንድ ወቅት በ1,500 ሜትር የሩጫ ውድድር ላይ በነበራት ተደጋጋሚ ስኬት የርቀቱ ልዩ ባለሙያ በመባል የምትታወቀው ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የ2026 የኦታዋ ማራቶንን በሴቶች ዘርፍ በአንደኝነት አጠናቃለች።
በዚሁ ውድድር ላይ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ኩፍቱ ታሂር በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ33 ሰከንድ ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ኬንያዊቷ ቤቲ ቺፕኮሪር ደግሞ በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ ሦስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
በውድድሩ ላይ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መሰረት በለጠ 4ኛ፣ መስከረም አሰፋ 5ኛ፣ መሰረት ደከቦ 7ኛ እንዲሁም ታደለች በቀለ 10ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን ፈጽመዋል።
በ2012 የለንደን ኦሎምፒክ የትውልድ ሀገሯን ኢትዮጵያን ወክላ በ1,500 ሜትር የብር ሜዳሊያ ያገኘችውና በ2013 የሞስኮ አለም ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ያሸነፈችው አበባ አረጋዊ በ2014 የቤት ውስጥ አለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደግሞ ስዊድንን ወክላ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኘቷ ይታወሳል።
የሁለት ጊዜ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊዋ አትሌት አበባ አረጋዊ ከዚህ የድል ጉዞዋ በኋላ በሰጠችው አስተያየት ለኦታዋ ማራቶን ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጓንና በማሸነፏም ታላቅ ደስታ እንደተሰማት ገልጻለች።
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷና ስዊድናዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የኦታዋ ማራቶንን ለማሸነፍ የፈጀባት ጊዜ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ነው።
የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆነው ባለቤቷ አትሌት የማነ ፀጋይም በ2014 እና በ2018 የካናዳን የቦታው ሪከርድ በመስበር ማሸነፉ ይታወሳል።
ይህ አጋጣሚ ባልና ሚስቱ የኦታዋ ማራቶንን በተለያዩ አመታት በማሸነፍ አዲስ ታሪክ በጋራ እንዲጽፉ አድርጓቸዋል።
✍️ በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል
#marathon #ottawamarathon #athletics #running #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
)
#ethiopia | በአንድ ወቅት በ1,500 ሜትር የሩጫ ውድድር ላይ በነበራት ተደጋጋሚ ስኬት የርቀቱ ልዩ ባለሙያ በመባል የምትታወቀው ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የ2026 የኦታዋ ማራቶንን በሴቶች ዘርፍ በአንደኝነት አጠናቃለች።
በዚሁ ውድድር ላይ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ኩፍቱ ታሂር በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ33 ሰከንድ ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ኬንያዊቷ ቤቲ ቺፕኮሪር ደግሞ በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ ሦስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
በውድድሩ ላይ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መሰረት በለጠ 4ኛ፣ መስከረም አሰፋ 5ኛ፣ መሰረት ደከቦ 7ኛ እንዲሁም ታደለች በቀለ 10ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን ፈጽመዋል።
በ2012 የለንደን ኦሎምፒክ የትውልድ ሀገሯን ኢትዮጵያን ወክላ በ1,500 ሜትር የብር ሜዳሊያ ያገኘችውና በ2013 የሞስኮ አለም ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ያሸነፈችው አበባ አረጋዊ በ2014 የቤት ውስጥ አለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደግሞ ስዊድንን ወክላ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኘቷ ይታወሳል።
የሁለት ጊዜ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊዋ አትሌት አበባ አረጋዊ ከዚህ የድል ጉዞዋ በኋላ በሰጠችው አስተያየት ለኦታዋ ማራቶን ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጓንና በማሸነፏም ታላቅ ደስታ እንደተሰማት ገልጻለች።
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷና ስዊድናዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የኦታዋ ማራቶንን ለማሸነፍ የፈጀባት ጊዜ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ነው።
የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆነው ባለቤቷ አትሌት የማነ ፀጋይም በ2014 እና በ2018 የካናዳን የቦታው ሪከርድ በመስበር ማሸነፉ ይታወሳል።
ይህ አጋጣሚ ባልና ሚስቱ የኦታዋ ማራቶንን በተለያዩ አመታት በማሸነፍ አዲስ ታሪክ በጋራ እንዲጽፉ አድርጓቸዋል።
✍️ በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል
#marathon #ottawamarathon #athletics #running #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
)
14 days ago
የዓለም አጭሯ ሴት በግራፊክ ዲዛይን በከፍተኛ ውጤት ተመረቀች
#ethiopia | በ72 ሴንቲ ሜትር ቁመት በጊነስ ወርልድ ሪከርድስ የዓለም አጭሯ በራሷ መንቀሳቀስ የማትችል ሴት ክብረ ወሰን ባለቤት የሆነችው አሜሪካዊቷ ዊልዲን አውሞይት፥ በቨርጂኒያ ከሚገኘው ሊበርቲ ዩኒቨርሲቲ በግራፊክ ዲዛይን የመጀመሪያ ዲግሪዋን አግኝታለች።
ዊልዲን የዓለማችን አጭሯ ፕሮፌሽናል ሞዴል በመሆንም የምትታወቅ ሲሆን አሁን ደግሞ ከአራት ዓመታት የዩኒቨርሲቲ ቆይታ በኋላ፣የግል የግራፊክ ዲዛይን ሥራዋን ለመጀመር ዝግጅቷን ጨርሳ የራሷን ድረ-ገጽ በይፋ አስመርቃለች።
ዊልዲን ስለ ስኬቷ ስትናገር፥ "ትምህርቴን በማጠናቀቄ በጣም ደስ ብሎኛል። መንገዱ ረጅም ቢሆንም፣ መጨረሻው የሚያስደስት ነው" ብላለች።
ዊልዲን ከምርቃቷ በኋላ ያቀደቻቸውን ግቦች፥ ቋሚ ሥራ ማግኘት፣ የራሷን የግራፊክ ዲዛይን ድርጅት በይፋ ማስጀመር፣ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲ ስትገባ ያቋረጠችውን የሞዴሊንግ ስራ በድጋሚ በመጀመር በኒውዮርክ ፋሽን ሳምንት መድረክ ላይ መታየት እና ትልልቅ የማስታወቂያ ሥራዎችን መሥራት መሆናቸውን ገልጻለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc
#ethiopia | በ72 ሴንቲ ሜትር ቁመት በጊነስ ወርልድ ሪከርድስ የዓለም አጭሯ በራሷ መንቀሳቀስ የማትችል ሴት ክብረ ወሰን ባለቤት የሆነችው አሜሪካዊቷ ዊልዲን አውሞይት፥ በቨርጂኒያ ከሚገኘው ሊበርቲ ዩኒቨርሲቲ በግራፊክ ዲዛይን የመጀመሪያ ዲግሪዋን አግኝታለች።
ዊልዲን የዓለማችን አጭሯ ፕሮፌሽናል ሞዴል በመሆንም የምትታወቅ ሲሆን አሁን ደግሞ ከአራት ዓመታት የዩኒቨርሲቲ ቆይታ በኋላ፣የግል የግራፊክ ዲዛይን ሥራዋን ለመጀመር ዝግጅቷን ጨርሳ የራሷን ድረ-ገጽ በይፋ አስመርቃለች።
ዊልዲን ስለ ስኬቷ ስትናገር፥ "ትምህርቴን በማጠናቀቄ በጣም ደስ ብሎኛል። መንገዱ ረጅም ቢሆንም፣ መጨረሻው የሚያስደስት ነው" ብላለች።
ዊልዲን ከምርቃቷ በኋላ ያቀደቻቸውን ግቦች፥ ቋሚ ሥራ ማግኘት፣ የራሷን የግራፊክ ዲዛይን ድርጅት በይፋ ማስጀመር፣ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲ ስትገባ ያቋረጠችውን የሞዴሊንግ ስራ በድጋሚ በመጀመር በኒውዮርክ ፋሽን ሳምንት መድረክ ላይ መታየት እና ትልልቅ የማስታወቂያ ሥራዎችን መሥራት መሆናቸውን ገልጻለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc
Sponsored by
Surafel
14 days ago
የዓለም አጭሯ ሴት በግራፊክ ዲዛይን በከፍተኛ ውጤት ተመረቀች
በ72 ሴንቲ ሜትር ቁመት በጊነስ ወርልድ ሪከርድስ የዓለም አጭሯ በራሷ መንቀሳቀስ የማትችል ሴት ክብረ ወሰን ባለቤት የሆነችው አሜሪካዊቷ ዊልዲን አውሞይት፥ በቨርጂኒያ ከሚገኘው ሊበርቲ ዩኒቨርሲቲ በግራፊክ ዲዛይን የመጀመሪያ ዲግሪዋን አግኝታለች።
ዊልዲን የዓለማችን አጭሯ ፕሮፌሽናል ሞዴል በመሆንም የምትታወቅ ሲሆን አሁን ደግሞ ከአራት ዓመታት የዩኒቨርሲቲ ቆይታ በኋላ፣የግል የግራፊክ ዲዛይን ሥራዋን ለመጀመር ዝግጅቷን ጨርሳ የራሷን ድረ-ገጽ በይፋ አስመርቃለች።
ዊልዲን ስለ ስኬቷ ስትናገር፥ "ትምህርቴን በማጠናቀቄ በጣም ደስ ብሎኛል። መንገዱ ረጅም ቢሆንም፣ መጨረሻው የሚያስደስት ነው" ብላለች።
ዊልዲን ከምርቃቷ በኋላ ያቀደቻቸውን ግቦች፥ ቋሚ ሥራ ማግኘት፣ የራሷን የግራፊክ ዲዛይን ድርጅት በይፋ ማስጀመር፣ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲ ስትገባ ያቋረጠችውን የሞዴሊንግ ስራ በድጋሚ በመጀመር በኒውዮርክ ፋሽን ሳምንት መድረክ ላይ መታየት እና ትልልቅ የማስታወቂያ ሥራዎችን መሥራት መሆናቸውን ገልጻለች።
ዘገባው የጊነስ ወርልድ ሪከርድስ ነው
በ- ዳንኤል መኮንን
seledadotio
seledadotio
በ72 ሴንቲ ሜትር ቁመት በጊነስ ወርልድ ሪከርድስ የዓለም አጭሯ በራሷ መንቀሳቀስ የማትችል ሴት ክብረ ወሰን ባለቤት የሆነችው አሜሪካዊቷ ዊልዲን አውሞይት፥ በቨርጂኒያ ከሚገኘው ሊበርቲ ዩኒቨርሲቲ በግራፊክ ዲዛይን የመጀመሪያ ዲግሪዋን አግኝታለች።
ዊልዲን የዓለማችን አጭሯ ፕሮፌሽናል ሞዴል በመሆንም የምትታወቅ ሲሆን አሁን ደግሞ ከአራት ዓመታት የዩኒቨርሲቲ ቆይታ በኋላ፣የግል የግራፊክ ዲዛይን ሥራዋን ለመጀመር ዝግጅቷን ጨርሳ የራሷን ድረ-ገጽ በይፋ አስመርቃለች።
ዊልዲን ስለ ስኬቷ ስትናገር፥ "ትምህርቴን በማጠናቀቄ በጣም ደስ ብሎኛል። መንገዱ ረጅም ቢሆንም፣ መጨረሻው የሚያስደስት ነው" ብላለች።
ዊልዲን ከምርቃቷ በኋላ ያቀደቻቸውን ግቦች፥ ቋሚ ሥራ ማግኘት፣ የራሷን የግራፊክ ዲዛይን ድርጅት በይፋ ማስጀመር፣ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲ ስትገባ ያቋረጠችውን የሞዴሊንግ ስራ በድጋሚ በመጀመር በኒውዮርክ ፋሽን ሳምንት መድረክ ላይ መታየት እና ትልልቅ የማስታወቂያ ሥራዎችን መሥራት መሆናቸውን ገልጻለች።
ዘገባው የጊነስ ወርልድ ሪከርድስ ነው
በ- ዳንኤል መኮንን
seledadotio
seledadotio
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ለረጅም ጊዜ አዲስ አበባ በሚገኘው ማዕከላዊ መስሪያ ቤት ብቻ ሲሰጥ የቆየው እና ለበርካታ ዜጎች እንግልት ሲፈጥር የነበረው የወንጀል ነፃ ማስረጃ አሰጣጥ ሂደት ከዛሬ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተሻሽሎ በአካባቢ ደረጃ እንዲሰጥ መወሰኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ውሳኔው በተለይም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለስራ ለሚሰማሩ ዜጎች የነበረባቸውን የቢሮክራሲ ውጣ ውረድ የሚቀርፍ ትልቅ እፎይታን ይዞ መጥቷል።
ዘ-ሐበሻ የተመለከተው፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ እንዳብራራው ማንኛውም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመጓዝ የወንጀል ነፃ ሰርተፊኬት የሚፈልግ ተገልጋይ ከዛሬ ጀምሮ በአካል አዲስ አበባ ወደሚገኘው የፎረንሲክ ወንጀል ምርመራ እና አሻራ ምርመራ ዋና ክፍል መምጣት አይጠበቅበትም። ከዚህ ይልቅ አገልግሎት ፈላጊዎች በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በተዘጋጁ ማዕከላት አማካኝነት በየአካባቢያቸው፣ እንዲሁም የጉዞ ሂደቱን በሚያስፈጽሙላቸው ህጋዊ ኤጀንሲዎች በኩል ማስረጃውን በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ይህ አዲስ አሰራር ዜጎች ከየክልሉ ወደ ዋና ከተማው የሚያደርጉትን አላስፈላጊ ጉዞ በማስቀረት ጊዜያቸውን እና ገንዘባቸውን የሚቆጥብ ዘመናዊ አካሄድ መሆኑ ተገልጿል።
በየዓመቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የተሻለ ህይወት ፍለጋ በህጋዊ መንገድ ወደ ተለያዩ የአረብ አገራት ያቀናሉ። ይህንን ጉዞ ለማድረግ ከሚጠየቁት ዋነኛ ሰነዶች መካከል አንዱ ተጓዡ የወንጀል ሪከርድ እንደሌለበት የሚያረጋግጠው ሰርተፊኬት ሲሆን ከዚህ ቀደም ዜጎች ይህንን ሰነድ ለማግኘት ብቻ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ለቀናት ለእንግልት፣ ለሙስና እና ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጉ እንደነበር ይታወቃል። ይህንንም በተደጋጋሚ በዘ-ሐበሻ ዜና ስንዘግብ ቆይተናል። የፌደራል ፖሊስ ይህንን የቆየ እና አሳሳቢ ክፍተት በመረዳት ከስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ታግዞ ተደራሽ ማድረጉ፣ መንግስት የዜጎችን ደህንነት እና ምቾት ለመጠበቅ፣ እንዲሁም ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን በመቀነስ ህጋዊ የጉዞ መስመሩን ለማሳለጥ እያደረገ ባለው ጥረት ውስጥ እንደ አንድ ትልቅ እና ሚዛናዊ እርምጃ የሚታይ ነው። ፖሊስ አዲሱ አሰራር ዜጎችን በሰብዓዊነት ከማገልገል መርህ ጋር የተቆራኘ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥቷል።
ዘ-ሐበሻ የተመለከተው፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ እንዳብራራው ማንኛውም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመጓዝ የወንጀል ነፃ ሰርተፊኬት የሚፈልግ ተገልጋይ ከዛሬ ጀምሮ በአካል አዲስ አበባ ወደሚገኘው የፎረንሲክ ወንጀል ምርመራ እና አሻራ ምርመራ ዋና ክፍል መምጣት አይጠበቅበትም። ከዚህ ይልቅ አገልግሎት ፈላጊዎች በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በተዘጋጁ ማዕከላት አማካኝነት በየአካባቢያቸው፣ እንዲሁም የጉዞ ሂደቱን በሚያስፈጽሙላቸው ህጋዊ ኤጀንሲዎች በኩል ማስረጃውን በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ይህ አዲስ አሰራር ዜጎች ከየክልሉ ወደ ዋና ከተማው የሚያደርጉትን አላስፈላጊ ጉዞ በማስቀረት ጊዜያቸውን እና ገንዘባቸውን የሚቆጥብ ዘመናዊ አካሄድ መሆኑ ተገልጿል።
በየዓመቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የተሻለ ህይወት ፍለጋ በህጋዊ መንገድ ወደ ተለያዩ የአረብ አገራት ያቀናሉ። ይህንን ጉዞ ለማድረግ ከሚጠየቁት ዋነኛ ሰነዶች መካከል አንዱ ተጓዡ የወንጀል ሪከርድ እንደሌለበት የሚያረጋግጠው ሰርተፊኬት ሲሆን ከዚህ ቀደም ዜጎች ይህንን ሰነድ ለማግኘት ብቻ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ለቀናት ለእንግልት፣ ለሙስና እና ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጉ እንደነበር ይታወቃል። ይህንንም በተደጋጋሚ በዘ-ሐበሻ ዜና ስንዘግብ ቆይተናል። የፌደራል ፖሊስ ይህንን የቆየ እና አሳሳቢ ክፍተት በመረዳት ከስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ታግዞ ተደራሽ ማድረጉ፣ መንግስት የዜጎችን ደህንነት እና ምቾት ለመጠበቅ፣ እንዲሁም ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን በመቀነስ ህጋዊ የጉዞ መስመሩን ለማሳለጥ እያደረገ ባለው ጥረት ውስጥ እንደ አንድ ትልቅ እና ሚዛናዊ እርምጃ የሚታይ ነው። ፖሊስ አዲሱ አሰራር ዜጎችን በሰብዓዊነት ከማገልገል መርህ ጋር የተቆራኘ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥቷል።
23 days ago
አትሌቷ ዛሬ ማለዳ በጃንሜዳ ልምምድ እየሰራች ወድቃ ህይወቷ አለፈ
ዝነኛዋ የረጅም ርቀት ሯጭ የብርጓል መለሰ ዛሬ ግንቦት 4/2018 ዓ.ም ማለዳ በጃንሜዳ ልምምድ እየሰራች ሳለ በድንገት ወድቃ ነው ህይወቷ ማለፉ ተሰማ። አስክሬኗ በአሁኑ ሰዓት ለምርመራ ወደ ምኒልክ ሆስፒታል ተወስዷል።
እ.ኤ.አ በ2015 በኮንጎ ብራዛቪል በተካሄደው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ሀገሯን ወክላ በግማሽ ማራቶን የነሃስ ማራቶን ያመጣችው አትሌቷ በዛው ዓመት በአሜሪካ ቺካጎ ማራቶን 2ኛ መውጣቷ ይታወሳል። በ2018 ደግሞ በቻይና ሻንጋይ ማራቶን 2:20.37 በሆነ ጊዜ ከሶስት ዓመታት በፊት በሀገሯ ልጅ ትዕግስት ቱፋ ተይዞ የነበረውን የቦታውን ሪከርድ (2:21.52) ከአንድ ደቂቃ በላይ በማሻሻል ማሸነፏ ይታወሳል።
በ2022 በፖርቹጋል ሊዝበን ግማሽ ማራቶን 1:07.18 በሆነ ጊዜ የቦታውን ሪከርድ ሰብራ አሸንፋለች። ባለፈው ዓመት በተካሄደው የፍራንክፈርት ማራቶን 2:2047 በሆነ ሰዓት 2ኛ ወጥታ ነበር። በ2018 በዱባይ ማራቶን 2:19.36 የገባችበት በማራቶን የግል ምርጥ ሰዓቷ ነው።
የፊታችን ግንቦት 16 በካናዳ በሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ከሚሳተፉት 12 ሴት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መካከል አንዷ የነበረችው ጀግናዋ አትሌት የብርጓል መለሰ ለአሸናፊነት የሚረዳትን ጠንካራ ልምምዷን በመስራት ላይ ሳለች ነው ዛሬ ማለዳ በድንገት ወድቃ ህይወቷ ያለፈው።
የብርጓል ባለትዳርና የሁለት ልጆች እናት ነበረች። አስክሬኗ ነገ ጠዋት ወደ ቤተሰቦቿ ወደ ወሎ ሽኝት ይደረግለታል።
ዝነኛዋ የረጅም ርቀት ሯጭ የብርጓል መለሰ ዛሬ ግንቦት 4/2018 ዓ.ም ማለዳ በጃንሜዳ ልምምድ እየሰራች ሳለ በድንገት ወድቃ ነው ህይወቷ ማለፉ ተሰማ። አስክሬኗ በአሁኑ ሰዓት ለምርመራ ወደ ምኒልክ ሆስፒታል ተወስዷል።
እ.ኤ.አ በ2015 በኮንጎ ብራዛቪል በተካሄደው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ሀገሯን ወክላ በግማሽ ማራቶን የነሃስ ማራቶን ያመጣችው አትሌቷ በዛው ዓመት በአሜሪካ ቺካጎ ማራቶን 2ኛ መውጣቷ ይታወሳል። በ2018 ደግሞ በቻይና ሻንጋይ ማራቶን 2:20.37 በሆነ ጊዜ ከሶስት ዓመታት በፊት በሀገሯ ልጅ ትዕግስት ቱፋ ተይዞ የነበረውን የቦታውን ሪከርድ (2:21.52) ከአንድ ደቂቃ በላይ በማሻሻል ማሸነፏ ይታወሳል።
በ2022 በፖርቹጋል ሊዝበን ግማሽ ማራቶን 1:07.18 በሆነ ጊዜ የቦታውን ሪከርድ ሰብራ አሸንፋለች። ባለፈው ዓመት በተካሄደው የፍራንክፈርት ማራቶን 2:2047 በሆነ ሰዓት 2ኛ ወጥታ ነበር። በ2018 በዱባይ ማራቶን 2:19.36 የገባችበት በማራቶን የግል ምርጥ ሰዓቷ ነው።
የፊታችን ግንቦት 16 በካናዳ በሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ከሚሳተፉት 12 ሴት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መካከል አንዷ የነበረችው ጀግናዋ አትሌት የብርጓል መለሰ ለአሸናፊነት የሚረዳትን ጠንካራ ልምምዷን በመስራት ላይ ሳለች ነው ዛሬ ማለዳ በድንገት ወድቃ ህይወቷ ያለፈው።
የብርጓል ባለትዳርና የሁለት ልጆች እናት ነበረች። አስክሬኗ ነገ ጠዋት ወደ ቤተሰቦቿ ወደ ወሎ ሽኝት ይደረግለታል።
24 days ago
ባርሴሎና ሪያል ማድሪድን አንበረከከ
#ethiopia | የካታላኑ ኩራት ባርሴሎና በታሪካዊው የኤል ክላሲኮ ጨዋታ চিরተቀናቃኙን ሪያል ማድሪድን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዘንድሮውን የስፔን ላሊጋ ሻምፒዮን መሆኑን በይፋ አረጋግጧል፡፡
ሊጉ ለመጠናቀቅ ገና ሦስት ጨዋታዎች ቢቀሩትም ባርሴሎና ለ29ኛ ጊዜ የሊጉን የክብር ዋንጫ ማንሳት ችሏል፡፡
በኑካምፕ ስታዲየም በተደረገው በዚህ 264ኛው የኤል ክላሲኮ ፍልሚያ ማርከስ ራሽፎርድ እና ፌራን ቶሬስ የባርሴሎናን የድል ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
በውድድር ዓመቱ 30ኛ ድሉን ያስመዘገበው ባርሴሎና ነጥቡን 91 በማድረስ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት አሸናፊነቱን አስጠብቋል፡፡
የዛሬው ጨዋታ በኤል ክላሲኮ ታሪክ የላሊጋው ዋንጫ አሸናፊ የተለየበት ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑም ልዩ ያደርገዋል፡፡
በአሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክ የሚመራው ባርሴሎና በውድድር ዓመቱ አስፈሪ እና የተደራጀ ብቃቱን ያሳየ ሲሆን በተቃራኒው ሪያል ማድሪድ በውጤት ማጣት እና በውስጥ ቀውስ የታመሰበት የውድድር ጊዜ ሆኖበታል፡፡
በጨዋታው በ9ኛው ደቂቃ ላይ ማርከስ ራሽፎርድ ባስቆጠራት ድንቅ የቅጣት ምት ግብ ባርሴሎናን መሪ ሲያደርግ በ18ኛው ደቂቃ ላይ ፌራን ቶሬስ ሁለተኛውን ግብ በማስቆጠር የድሉን መንገድ አቅንቷል፡፡
ተጫዋቾቹ ግቦቹን ካስቆጠሩ በኋላ በአሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክ ላይ ያሳዩት አጋርነት የቡድኑን አንድነት ያሳየ ነበር፡፡ አሰልጣኙ አባታቸውን በሞት በማጣታቸው ምክንያት ተጫዋቾቹ ድላቸውን ለእሳቸው መታሰቢያ አድርገውታል፡፡
በሌላ በኩል ሪያል ማድሪድ በአሰልጣኝ አልቫሮ አርቤሎዋ ስር ደካማ አፈጻጸም ያሳየ ሲሆን የቡድኑ የውስጥ አለመግባባት በሜዳ ላይ በግልጽ ታይቷል፡፡
ባርሴሎና በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሜዳው ባደረጋቸው 18 ጨዋታዎች በሙሉ ድል በመቀናጀት እና በሊጉ 11 ተከታታይ ጨዋታዎችን በማሸነፍ አስደናቂ ሪከርድ አስመዝግቧል፡፡
በአሁኑ ወቅት ከሪያል ማድሪድ በ14 ነጥቦች ርቆ የሚገኘው ባርሴሎና በኑካምፕ ስታዲየም በደጋፊዎቹ ደማቅ ዝማሬ ታጅቦ የሻምፒዮንነት ክብሩን ተቀብሏል፡፡
#barcelona #realmadrid #laliga #football #elclasico #spain #soccer #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የካታላኑ ኩራት ባርሴሎና በታሪካዊው የኤል ክላሲኮ ጨዋታ চিরተቀናቃኙን ሪያል ማድሪድን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዘንድሮውን የስፔን ላሊጋ ሻምፒዮን መሆኑን በይፋ አረጋግጧል፡፡
ሊጉ ለመጠናቀቅ ገና ሦስት ጨዋታዎች ቢቀሩትም ባርሴሎና ለ29ኛ ጊዜ የሊጉን የክብር ዋንጫ ማንሳት ችሏል፡፡
በኑካምፕ ስታዲየም በተደረገው በዚህ 264ኛው የኤል ክላሲኮ ፍልሚያ ማርከስ ራሽፎርድ እና ፌራን ቶሬስ የባርሴሎናን የድል ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
በውድድር ዓመቱ 30ኛ ድሉን ያስመዘገበው ባርሴሎና ነጥቡን 91 በማድረስ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት አሸናፊነቱን አስጠብቋል፡፡
የዛሬው ጨዋታ በኤል ክላሲኮ ታሪክ የላሊጋው ዋንጫ አሸናፊ የተለየበት ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑም ልዩ ያደርገዋል፡፡
በአሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክ የሚመራው ባርሴሎና በውድድር ዓመቱ አስፈሪ እና የተደራጀ ብቃቱን ያሳየ ሲሆን በተቃራኒው ሪያል ማድሪድ በውጤት ማጣት እና በውስጥ ቀውስ የታመሰበት የውድድር ጊዜ ሆኖበታል፡፡
በጨዋታው በ9ኛው ደቂቃ ላይ ማርከስ ራሽፎርድ ባስቆጠራት ድንቅ የቅጣት ምት ግብ ባርሴሎናን መሪ ሲያደርግ በ18ኛው ደቂቃ ላይ ፌራን ቶሬስ ሁለተኛውን ግብ በማስቆጠር የድሉን መንገድ አቅንቷል፡፡
ተጫዋቾቹ ግቦቹን ካስቆጠሩ በኋላ በአሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክ ላይ ያሳዩት አጋርነት የቡድኑን አንድነት ያሳየ ነበር፡፡ አሰልጣኙ አባታቸውን በሞት በማጣታቸው ምክንያት ተጫዋቾቹ ድላቸውን ለእሳቸው መታሰቢያ አድርገውታል፡፡
በሌላ በኩል ሪያል ማድሪድ በአሰልጣኝ አልቫሮ አርቤሎዋ ስር ደካማ አፈጻጸም ያሳየ ሲሆን የቡድኑ የውስጥ አለመግባባት በሜዳ ላይ በግልጽ ታይቷል፡፡
ባርሴሎና በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሜዳው ባደረጋቸው 18 ጨዋታዎች በሙሉ ድል በመቀናጀት እና በሊጉ 11 ተከታታይ ጨዋታዎችን በማሸነፍ አስደናቂ ሪከርድ አስመዝግቧል፡፡
በአሁኑ ወቅት ከሪያል ማድሪድ በ14 ነጥቦች ርቆ የሚገኘው ባርሴሎና በኑካምፕ ስታዲየም በደጋፊዎቹ ደማቅ ዝማሬ ታጅቦ የሻምፒዮንነት ክብሩን ተቀብሏል፡፡
#barcelona #realmadrid #laliga #football #elclasico #spain #soccer #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
25 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የዘንድሮው ኤል ክላሲኮ የሁለት ተቃራኒ ዓለማት መገናኛ ሆኖ አልፏል። በአንድ በኩል በአሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክ ስር እንደ አንድ ልብ የሚመታው፣ የተደራጀው እና የማይበገረው ባርሴሎና፤ በሌላ በኩል ደግሞ በውስጥ ቀውስ እና በውጤት ማጣት የሚታመሰው የክፉ ጊዜው ሪያል ማድሪድ። ኑካምፕ ላይ በተደረገው በዚህ ታሪካዊ ፍልሚያ፣ ካታላኖቹ ተቀናቃኛቸውን 2-0 በሆነ ውጤት በማንበርከክ የውድድር ዓመቱ ሊጠናቀቅ 3 ጨዋታዎች እየቀሩት የ29ኛው ላሊጋ ሻምፒዮንነታቸውን በይፋ አረጋግጠዋል።
ጨዋታው በጀመረ በ9ኛው ደቂቃ ብቻ ኑካምፕ በደስታ ጩኸት ተናወጠች። ከማንችስተር ዩናይትድ በውሰት የመጣው እንግሊዛዊው አጥቂ ማርከስ ራሽፎርድ፣ ያገኘውን የቅጣት ምት ልክ እንደ ዴክላን ራይስ ስታይል በድንቅ ሁኔታ አስቆጥሮ ባርሴሎናን መሪ አደረገ። የሪያል ማድሪዱ ግብ ጠባቂ ቲቦ ኮርቱዋ ኳሷን በጣቶቹ ጫፍ ቢነካትም ወደ መረብ ከመግባት ሊያግታት አልቻለም።
ባርሴሎናዎች የጀመሩትን ማዕበላዊ ጥቃት አላቆሙም። በ18ኛው ደቂቃ ላይ ፈርሚን ሎፔዝ ያቀበለውን ኳስ ዳኒ ኦልሞ በአስማታዊ የተረከዝ ንክኪ ሲያመቻቸው፣ ፌራን ቶሬስ ያለምንም ስህተት ከመረብ አዋህዶ መሪነቱን ወደ 2-0 ከፍ አደረገው። ገና በ20 ደቂቃ ውስጥ ጨዋታው የተጠናቀቀ ይመስል ነበር!
የባርሴሎና ተጫዋቾች ግቦቹን ካስቆጠሩ በኋላ ያሳዩት ስሜት የቡድኑን አንድነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነበር። ሁለቱም ግብ አስቆጣሪዎች (ራሽፎርድ እና ፌራን) በቀጥታ የሮጡት ወደ አሰልጣኛቸው ሀንሲ ፍሊክ ነበር። አሰልጣኙ ከቀናት በፊት አባታቸውን በሞት ያጡ ሲሆን፣ ተጫዋቾቹም ሀዘናቸውን ለመጋራት እና አብሮነታቸውን ለማሳየት በሞቀ እቅፍ አጽናንተዋቸዋል።
ለሪያል ማድሪድ ይህ ጨዋታ የከፋ ሳምንት፣ መጥፎ ወር እና አስፈሪ የውድድር ዓመት ማሳያ ነበር። አሰልጣኝ አልቫሮ አርቤሎዋ በከፍተኛ ጫና ውስጥ ሆነው ወደ ሜዳ የገቡ ሲሆን፣ ከጨዋታው ቀናት በፊት በልምምድ ሜዳ ላይ ከፌዴሪኮ ቫልቬርዴ ጋር ተጣልቶ ጉዳት ያደረሰበት ኦሪሊየን ቹዋሜኒ በቋሚነት መግባቱ የክለቡን የውስጥ ቀውስ ያጋለጠ ክስተት ነበር። ቪኒሲየስ ጁኒየር በአምበልነት ቡድኑን ቢመራም፣ ጎንዛሎ ጋርሺያ ያገኘውን ወርቃማ እድል ቢያመክንም ማድሪዶች ባርሴሎናን መፈተን አልቻሉም።
የባርሴሎና አስፈሪ ጉዞ በቁጥሮች ሲገለጽ፡
▪ ባርሴሎና በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሜዳው ባደረጋቸው 18 ጨዋታዎች በሙሉ 18 ድሎችን አስመዝግቧል!
▪በላሊጋው 11 ተከታታይ ጨዋታዎችን በማሸነፍ አስገራሚ ሪከርድ ሰርተዋል።
▪ ሻምፒዮናነታቸውን ሲያረጋግጡ ከሪያል ማድሪድ በ14 ነጥቦች ርቀዋል።
▪ካታላኖቹ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የላሊጋውን ዋንጫ በማንሳት ታሪክ ደግመዋል (በአጠቃላይ 29 ጊዜ - ከሪያል ማድሪድ ክብረወሰን በ7 ዋንጫዎች ብቻ ዝቅ ብለው)።
በዛሬው ጨዋታ ሮበርት ሌዋንዶውስኪ፣ ራፊንሃ እና ፍሬንኪ ዴ ጆንግ ተቀይረው በመግባት የክብረ በዓሉ ተካፋይ ሲሆኑ፣ የኑካምፕ ስታዲየም ደጋፊዎች "ካምፒዮኔስ! ካምፒዮኔስ!" (Championes!) በሚል ዝማሬ ስታዲየሙን አድምቀውታል። የሀንሲ ፍሊኩ ባርሴሎና በእርግጥም የተሟላ እና አስፈሪ ቡድን መሆኑን ለዓለም አሳይቷል!
ጨዋታው በጀመረ በ9ኛው ደቂቃ ብቻ ኑካምፕ በደስታ ጩኸት ተናወጠች። ከማንችስተር ዩናይትድ በውሰት የመጣው እንግሊዛዊው አጥቂ ማርከስ ራሽፎርድ፣ ያገኘውን የቅጣት ምት ልክ እንደ ዴክላን ራይስ ስታይል በድንቅ ሁኔታ አስቆጥሮ ባርሴሎናን መሪ አደረገ። የሪያል ማድሪዱ ግብ ጠባቂ ቲቦ ኮርቱዋ ኳሷን በጣቶቹ ጫፍ ቢነካትም ወደ መረብ ከመግባት ሊያግታት አልቻለም።
ባርሴሎናዎች የጀመሩትን ማዕበላዊ ጥቃት አላቆሙም። በ18ኛው ደቂቃ ላይ ፈርሚን ሎፔዝ ያቀበለውን ኳስ ዳኒ ኦልሞ በአስማታዊ የተረከዝ ንክኪ ሲያመቻቸው፣ ፌራን ቶሬስ ያለምንም ስህተት ከመረብ አዋህዶ መሪነቱን ወደ 2-0 ከፍ አደረገው። ገና በ20 ደቂቃ ውስጥ ጨዋታው የተጠናቀቀ ይመስል ነበር!
የባርሴሎና ተጫዋቾች ግቦቹን ካስቆጠሩ በኋላ ያሳዩት ስሜት የቡድኑን አንድነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነበር። ሁለቱም ግብ አስቆጣሪዎች (ራሽፎርድ እና ፌራን) በቀጥታ የሮጡት ወደ አሰልጣኛቸው ሀንሲ ፍሊክ ነበር። አሰልጣኙ ከቀናት በፊት አባታቸውን በሞት ያጡ ሲሆን፣ ተጫዋቾቹም ሀዘናቸውን ለመጋራት እና አብሮነታቸውን ለማሳየት በሞቀ እቅፍ አጽናንተዋቸዋል።
ለሪያል ማድሪድ ይህ ጨዋታ የከፋ ሳምንት፣ መጥፎ ወር እና አስፈሪ የውድድር ዓመት ማሳያ ነበር። አሰልጣኝ አልቫሮ አርቤሎዋ በከፍተኛ ጫና ውስጥ ሆነው ወደ ሜዳ የገቡ ሲሆን፣ ከጨዋታው ቀናት በፊት በልምምድ ሜዳ ላይ ከፌዴሪኮ ቫልቬርዴ ጋር ተጣልቶ ጉዳት ያደረሰበት ኦሪሊየን ቹዋሜኒ በቋሚነት መግባቱ የክለቡን የውስጥ ቀውስ ያጋለጠ ክስተት ነበር። ቪኒሲየስ ጁኒየር በአምበልነት ቡድኑን ቢመራም፣ ጎንዛሎ ጋርሺያ ያገኘውን ወርቃማ እድል ቢያመክንም ማድሪዶች ባርሴሎናን መፈተን አልቻሉም።
የባርሴሎና አስፈሪ ጉዞ በቁጥሮች ሲገለጽ፡
▪ ባርሴሎና በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሜዳው ባደረጋቸው 18 ጨዋታዎች በሙሉ 18 ድሎችን አስመዝግቧል!
▪በላሊጋው 11 ተከታታይ ጨዋታዎችን በማሸነፍ አስገራሚ ሪከርድ ሰርተዋል።
▪ ሻምፒዮናነታቸውን ሲያረጋግጡ ከሪያል ማድሪድ በ14 ነጥቦች ርቀዋል።
▪ካታላኖቹ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የላሊጋውን ዋንጫ በማንሳት ታሪክ ደግመዋል (በአጠቃላይ 29 ጊዜ - ከሪያል ማድሪድ ክብረወሰን በ7 ዋንጫዎች ብቻ ዝቅ ብለው)።
በዛሬው ጨዋታ ሮበርት ሌዋንዶውስኪ፣ ራፊንሃ እና ፍሬንኪ ዴ ጆንግ ተቀይረው በመግባት የክብረ በዓሉ ተካፋይ ሲሆኑ፣ የኑካምፕ ስታዲየም ደጋፊዎች "ካምፒዮኔስ! ካምፒዮኔስ!" (Championes!) በሚል ዝማሬ ስታዲየሙን አድምቀውታል። የሀንሲ ፍሊኩ ባርሴሎና በእርግጥም የተሟላ እና አስፈሪ ቡድን መሆኑን ለዓለም አሳይቷል!
26 days ago
ዝነኛው የተፈጥሮ ተመራማሪ ዴቪድ አተንበራ 100ኛ ዓመት ልደታቸውን አከበሩ
*****************
ታዋቂው ብሪታንያዊ የተፈጥሮ ተመራማሪ እና የዶክመንተሪ አዘጋጅ ሰር ዴቪድ አተንበራ 100ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን አክብረዋል።
በዝነኞቹ "Planet Earth" እና "Blue Planet" ፊልሞቻቸው የምናውቃቸው እኚህ ታላቅ ሰው፣ ለሰባት አስርተ ዓመታት ዓለምን ስለ ተፈጥሮ ሲያስተምሩ ቆይተዋል።
"መጠበቅም ሆነ ማጥፋት እንችላለን፣ ምርጫው የእኛ ነው" በማለት ለተፈጥሮ ጥበቃ የሚሟገቱት አተንበራ፣ ዛሬም በ100 ዓመታቸው ለዓለም ተስፋን እየሰጡ ይገኛሉ።
ሰር ዴቪድ አተንበራ፦
• በቴሌቪዥን ታሪክ ረጅሙን የሥራ ዘመን በማሳለፍ የጊነስ ወርልድ ሪከርድ ባለቤት ናቸው።
• ሁለት ጊዜ የ"ሰር" ማዕረግ ያገኙ ሲሆን፣ ለኖቤል የሰላም ሽልማትም ታጭተዋል።
• ቴሌቪዥን ከጥቁር እና ነጭ ወደ ቀለም፣ ከዚያም ወደ HD እና 4K ሲቀየር በሁሉም ዘመን ሽልማት ያገኙ ብቸኛ ሰው ናቸው።
• እ.አ.አ በ1979 ከጎሪላዎች ጋር ያደረጉት ዝነኛ ቆይታ በተፈጥሮ ዶክመንተሪ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ ትዕይንት ነው።
• ከ40 በላይ የሚሆኑ የእፅዋት እና የእንስሳት ዝርያዎች በእርሳቸው ስም ተሰይመዋል።
• ገዳይ እባቦችንና ጊንጦችን የማይፈሩት ሰር ዴቪድ አተንበራ፣ አይጥ በጣም ይፈራሉ።
#davidattenborough #100years #nature #planetearth #ebc
*****************
ታዋቂው ብሪታንያዊ የተፈጥሮ ተመራማሪ እና የዶክመንተሪ አዘጋጅ ሰር ዴቪድ አተንበራ 100ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን አክብረዋል።
በዝነኞቹ "Planet Earth" እና "Blue Planet" ፊልሞቻቸው የምናውቃቸው እኚህ ታላቅ ሰው፣ ለሰባት አስርተ ዓመታት ዓለምን ስለ ተፈጥሮ ሲያስተምሩ ቆይተዋል።
"መጠበቅም ሆነ ማጥፋት እንችላለን፣ ምርጫው የእኛ ነው" በማለት ለተፈጥሮ ጥበቃ የሚሟገቱት አተንበራ፣ ዛሬም በ100 ዓመታቸው ለዓለም ተስፋን እየሰጡ ይገኛሉ።
ሰር ዴቪድ አተንበራ፦
• በቴሌቪዥን ታሪክ ረጅሙን የሥራ ዘመን በማሳለፍ የጊነስ ወርልድ ሪከርድ ባለቤት ናቸው።
• ሁለት ጊዜ የ"ሰር" ማዕረግ ያገኙ ሲሆን፣ ለኖቤል የሰላም ሽልማትም ታጭተዋል።
• ቴሌቪዥን ከጥቁር እና ነጭ ወደ ቀለም፣ ከዚያም ወደ HD እና 4K ሲቀየር በሁሉም ዘመን ሽልማት ያገኙ ብቸኛ ሰው ናቸው።
• እ.አ.አ በ1979 ከጎሪላዎች ጋር ያደረጉት ዝነኛ ቆይታ በተፈጥሮ ዶክመንተሪ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ ትዕይንት ነው።
• ከ40 በላይ የሚሆኑ የእፅዋት እና የእንስሳት ዝርያዎች በእርሳቸው ስም ተሰይመዋል።
• ገዳይ እባቦችንና ጊንጦችን የማይፈሩት ሰር ዴቪድ አተንበራ፣ አይጥ በጣም ይፈራሉ።
#davidattenborough #100years #nature #planetearth #ebc
28 days ago
ሰውዬው "አትርሱኝ" የሚለውን ቃል እንደ እናቱ ምርቃት ሳይሆን እንደ ታክስ መክፈያ ደረሰኝ ነው የሚያየው። አንዳንዱ "አትርሱኝ" ባይ ደግሞ "አትርሱኝ" የሚለውን ቃል ሲጠቀም፣ ቃልኪዳን እየገባ ሳይሆን "ሪከርድ" እያደረገ ነው የሚመስለው።
ለካስ ሳናውቀው "አትርሱኝ" ማለት ያለ እረፍት እኔን በማሰብ ተሰቃዩ ማለት ሆኗል!
ይህ ሰውዬ አገር ሰላም ሆኖ፣ ፀሐይ ወጥቶ ሲገባም ጭምር "አትርሱኝ" ይላል። ቆይ ምን ያህል ቢረሳ ነው? ወይስ ረሺው ብዙ ነው? እኔ የምለው... ሰውዬው "የረሳኝ" ብሎ የሚጠረጥራቸው ሰዎች ብዛት፣ በምርጫ ወቅት "ያልመረጠኝ" ብሎ ከሚቆጥር ፖለቲከኛ ይበልጣል።
ለሠርግ ተጠርቶ "እንኳን ደስ አላችሁ" ከማለት ይልቅ "አትርሱኝ" ይላል። ሙሽሮቹ በጫጉላ ሰዓት እንኳ የእርሱን ፊት እያሰቡ "እንዴት ይረሳል?" እያሉ እንዲጨነቁ ይፈልጋል። ደግሞ እኮ የሚረሳ ነገር ቢኖረው አይቆጭም። ሰውዬው እንደ ድሮ ስልክ "ኮንታክት" በቃሉ የያዘው ቁጥር የለም፤ ግን "አትርሱኝ" ማለቱን አይረሳም።
አንድ ቀን እንዲያውም እንዲህ ሆነ... ሞት መጥቶ በሩን ሲያንኳኳ፣ ሰውዬው መርዶውን ከመቀበሉ በፊት "እሺ መሞቴንስ እሞታለሁ፤ ግን በኋላ ስትመለስ እንዳትረሳኝ" ብሎታል ይባላል። መቃብሩ ላይ "አትርሱኝ" የሚል ፅሁፍ ካልተፃፈማ፣ ትንሳኤ ቀን መጥቶ "አልተፃፈም" ብሎ "ሪፖርት" እንደሚያደርግ አልጠራጠርም።
እሱ "አትርሱኝ" የሚለው ቃል ለእርሱ የህይወት "ሴፍቲ ቤልት" ናት። አየር በነፃ እንደምናገኘው ሁሉ እርሱም ትዝታን በነፃ ማግኘት ይፈልጋል። ግን የሚገርመው ነገር፣ እርሱን ለማስታወስ ስትሞክር የምታስታውሰው ብቸኛ ነገር እርሱ "አትርሱኝ" ማለቱን ብቻ ነው።
ወዳጄ... የዚህን ሰውዬ ስም ከረሳኸው አይከፋም፤ "አትርሱኝ" ማለቱን ከረሳህ ግን እራሱ መጥቶ "ለምን ረሳኸኝ?" ብሎ ትዝታህን "አፕዴት" ያደርገዋል። እንዲያውም እኮ "አትርሱኝ" ማለት የአማርኛ ቋንቋ "ቫይረስ" ሆኗል። አንድን ነገር ለመናገር መግቢያህ "አትርሱኝ" ከሆነ፣ ንግግሩ ሳይጀምር ሰልችቶሃል ማለት ነው።
በእውነት ለመናገር... ሰውዬው ከሞተ በኋላ እንኳ በመንፈስ መጥቶ የቁም ጓደኞቹን "ቅምጥል ትዝታ" እያሳከከ "እንዴ... የዛሬ አምስት ዓመት እንዲህ ብዬህ አልነበር? እንዴት ረሳኸኝ?" ሳይላቸው አይቀርም።
እኔ የምለው... ሐኪም ቤት ሄዶ "ዶክተር... መታመሜን እንዳትረሳው" ቢል ሐኪሙ መድኃኒት ይፅፍለታል ወይስ "የመርሳት በሽታ" ያለበት እራሱ ሐኪሙ እንደሆነ ይቆጥራል?
ለማንኛውም... ይህንን ወግ አንብባችሁ ስትጨርሱ "አትርሱኝ" እንዳትሉኝ። ምክንያቱም እኔ "ረሱኝ" ብዬ ኮርጃለሁ!
አበጀ በለው የላኩልን
ለካስ ሳናውቀው "አትርሱኝ" ማለት ያለ እረፍት እኔን በማሰብ ተሰቃዩ ማለት ሆኗል!
ይህ ሰውዬ አገር ሰላም ሆኖ፣ ፀሐይ ወጥቶ ሲገባም ጭምር "አትርሱኝ" ይላል። ቆይ ምን ያህል ቢረሳ ነው? ወይስ ረሺው ብዙ ነው? እኔ የምለው... ሰውዬው "የረሳኝ" ብሎ የሚጠረጥራቸው ሰዎች ብዛት፣ በምርጫ ወቅት "ያልመረጠኝ" ብሎ ከሚቆጥር ፖለቲከኛ ይበልጣል።
ለሠርግ ተጠርቶ "እንኳን ደስ አላችሁ" ከማለት ይልቅ "አትርሱኝ" ይላል። ሙሽሮቹ በጫጉላ ሰዓት እንኳ የእርሱን ፊት እያሰቡ "እንዴት ይረሳል?" እያሉ እንዲጨነቁ ይፈልጋል። ደግሞ እኮ የሚረሳ ነገር ቢኖረው አይቆጭም። ሰውዬው እንደ ድሮ ስልክ "ኮንታክት" በቃሉ የያዘው ቁጥር የለም፤ ግን "አትርሱኝ" ማለቱን አይረሳም።
አንድ ቀን እንዲያውም እንዲህ ሆነ... ሞት መጥቶ በሩን ሲያንኳኳ፣ ሰውዬው መርዶውን ከመቀበሉ በፊት "እሺ መሞቴንስ እሞታለሁ፤ ግን በኋላ ስትመለስ እንዳትረሳኝ" ብሎታል ይባላል። መቃብሩ ላይ "አትርሱኝ" የሚል ፅሁፍ ካልተፃፈማ፣ ትንሳኤ ቀን መጥቶ "አልተፃፈም" ብሎ "ሪፖርት" እንደሚያደርግ አልጠራጠርም።
እሱ "አትርሱኝ" የሚለው ቃል ለእርሱ የህይወት "ሴፍቲ ቤልት" ናት። አየር በነፃ እንደምናገኘው ሁሉ እርሱም ትዝታን በነፃ ማግኘት ይፈልጋል። ግን የሚገርመው ነገር፣ እርሱን ለማስታወስ ስትሞክር የምታስታውሰው ብቸኛ ነገር እርሱ "አትርሱኝ" ማለቱን ብቻ ነው።
ወዳጄ... የዚህን ሰውዬ ስም ከረሳኸው አይከፋም፤ "አትርሱኝ" ማለቱን ከረሳህ ግን እራሱ መጥቶ "ለምን ረሳኸኝ?" ብሎ ትዝታህን "አፕዴት" ያደርገዋል። እንዲያውም እኮ "አትርሱኝ" ማለት የአማርኛ ቋንቋ "ቫይረስ" ሆኗል። አንድን ነገር ለመናገር መግቢያህ "አትርሱኝ" ከሆነ፣ ንግግሩ ሳይጀምር ሰልችቶሃል ማለት ነው።
በእውነት ለመናገር... ሰውዬው ከሞተ በኋላ እንኳ በመንፈስ መጥቶ የቁም ጓደኞቹን "ቅምጥል ትዝታ" እያሳከከ "እንዴ... የዛሬ አምስት ዓመት እንዲህ ብዬህ አልነበር? እንዴት ረሳኸኝ?" ሳይላቸው አይቀርም።
እኔ የምለው... ሐኪም ቤት ሄዶ "ዶክተር... መታመሜን እንዳትረሳው" ቢል ሐኪሙ መድኃኒት ይፅፍለታል ወይስ "የመርሳት በሽታ" ያለበት እራሱ ሐኪሙ እንደሆነ ይቆጥራል?
ለማንኛውም... ይህንን ወግ አንብባችሁ ስትጨርሱ "አትርሱኝ" እንዳትሉኝ። ምክንያቱም እኔ "ረሱኝ" ብዬ ኮርጃለሁ!
አበጀ በለው የላኩልን
28 days ago
በሰው ላይ ጥቃት በማድረስ የተከሰሰው ድምፃዊ አህመድ ማንጁስ የ300 ብር ቅጣት እንዲከፍል ተፈረደበት።
በሴት ልጅ ላይ አካላዊ ጥቃት በማድረስ ወንጀል የተከሰሰው ድምፃዊ አህመድ ሁሴን ወይንም ማንጁስ ላይ የገንዘብ ቅጣቱን ያስተላለፈው ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ነው።
ድምፃዊው ለዚህ ቅጣት የተዳረገው የካቲት 22 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት ከንጋቱ 12 ሰዓት ከ10 ላይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ስታር ሆቴል በተባለው ውስጥ የግል ተበዳይ የሆነችውን መድሃኒት ይልማ ላይ ጥቃት ፈጽሞ ጥፋተኛ በመባሉ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ላይ አብራርቷል።
ፍርድ ቤቱ የቅጣት ውሳኔውን ከመስጠቱ በፊት የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት የመረመረ ሲሆን፣ አቃቤ ህግ ወንጀሉ የተፈጸመው በሴት ላይ በመሆኑና ተከሳሽ ድርጊቱን የፈጸመው በምሽት በመሆኑ ቅጣቱ ሊከብድበት ይገባል ሲል አመልክቷል።
ተከሳሽ በበኩሉ ቀደም ሲል የጥፋተኝነት ሪከርድ የሌለበት መሆኑን፣ ድርጊቱን መፈጸሙን አምኖ በመጸጸቱ እንዲሁም የሁለት ልጆች አባትና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆኑን በመጥቀስ የሚጣልበት ቅጣት እንዲቀልለት ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ በውሳኔው የአቃቤ ህግን የቅጣት ማክበጃ በመተው፣ ተከሳሹ ያቀረባቸውን የቅጣት ማቅለያዎች ተቀብሎ የእስራት ቅጣቱን ወደ ገንዘብ ቅጣት ቀይሮለታል።
በዚህም መሰረት ተከሳሹ የ300 ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል እንደተወሰነበት በፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ላይ ተመልክተናል።
Via ኢትዮጲካሊንክ
seledadotio
seledadotio
በሴት ልጅ ላይ አካላዊ ጥቃት በማድረስ ወንጀል የተከሰሰው ድምፃዊ አህመድ ሁሴን ወይንም ማንጁስ ላይ የገንዘብ ቅጣቱን ያስተላለፈው ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ነው።
ድምፃዊው ለዚህ ቅጣት የተዳረገው የካቲት 22 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት ከንጋቱ 12 ሰዓት ከ10 ላይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ስታር ሆቴል በተባለው ውስጥ የግል ተበዳይ የሆነችውን መድሃኒት ይልማ ላይ ጥቃት ፈጽሞ ጥፋተኛ በመባሉ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ላይ አብራርቷል።
ፍርድ ቤቱ የቅጣት ውሳኔውን ከመስጠቱ በፊት የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት የመረመረ ሲሆን፣ አቃቤ ህግ ወንጀሉ የተፈጸመው በሴት ላይ በመሆኑና ተከሳሽ ድርጊቱን የፈጸመው በምሽት በመሆኑ ቅጣቱ ሊከብድበት ይገባል ሲል አመልክቷል።
ተከሳሽ በበኩሉ ቀደም ሲል የጥፋተኝነት ሪከርድ የሌለበት መሆኑን፣ ድርጊቱን መፈጸሙን አምኖ በመጸጸቱ እንዲሁም የሁለት ልጆች አባትና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆኑን በመጥቀስ የሚጣልበት ቅጣት እንዲቀልለት ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ በውሳኔው የአቃቤ ህግን የቅጣት ማክበጃ በመተው፣ ተከሳሹ ያቀረባቸውን የቅጣት ማቅለያዎች ተቀብሎ የእስራት ቅጣቱን ወደ ገንዘብ ቅጣት ቀይሮለታል።
በዚህም መሰረት ተከሳሹ የ300 ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል እንደተወሰነበት በፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ላይ ተመልክተናል።
Via ኢትዮጲካሊንክ
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
28 days ago
ድምፃዊ አህመድ ማንጁስ በገንዘብ ቅጣት ከእስር እንዲፈታ ተወሰነ
#fastmereja I በሴት ላይ ጥቃት በማድረስ የተከሰሰው ድምፃዊ አህመድ ማንጁስ በ300 ብር ቅጣት ተቀጣ።
የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት፣ በድምፃዊ አህመድ ሁሴን (ማንጁስ) ላይ የ300 ብር የገንዘብ ቅጣት አስተላለፈ። ድምፃዊው የተቀጣው የካቲት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ መድሃኒት ይልማ በተባለች ግለሰብ ላይ አካላዊ ጥቃት በመፈጸም ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ነው።
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ከመስጠቱ በፊት የአቃቤ ህግን “ጥቃቱ በሴት ላይ እና በምሽት ተፈጽሟል” የሚል የቅጣት ማክበጃ የቀረበለት ቢሆንም፣ የተከሳሹን የቅጣት ማቅለያዎች ተመልክቷል። ድምፃዊው ቀደም ሲል የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን፣ ጥፋቱን አምኖ መጸጸቱን እና የሁለት ልጆች አባት መሆኑን በመጥቀስ ቅጣት እንዲቀልለት ያቀረበውን ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ተቀብሏል።
በዚህም መሰረት ችሎቱ የእስር ቅጣቱን ወደ 300 ብር የገንዘብ ቅጣት የቀየረው ሲሆን፣ ተከሳሹ የተበየነበትን ገንዘብ እንደከፈለ የዋስትናው ተመላሽ ተደርጎለት ከእስር እንዲፈታ ታዟል። ዘገባው የኢትዮጲካሊንክ ነው።
#fastmereja I በሴት ላይ ጥቃት በማድረስ የተከሰሰው ድምፃዊ አህመድ ማንጁስ በ300 ብር ቅጣት ተቀጣ።
የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት፣ በድምፃዊ አህመድ ሁሴን (ማንጁስ) ላይ የ300 ብር የገንዘብ ቅጣት አስተላለፈ። ድምፃዊው የተቀጣው የካቲት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ መድሃኒት ይልማ በተባለች ግለሰብ ላይ አካላዊ ጥቃት በመፈጸም ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ነው።
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ከመስጠቱ በፊት የአቃቤ ህግን “ጥቃቱ በሴት ላይ እና በምሽት ተፈጽሟል” የሚል የቅጣት ማክበጃ የቀረበለት ቢሆንም፣ የተከሳሹን የቅጣት ማቅለያዎች ተመልክቷል። ድምፃዊው ቀደም ሲል የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን፣ ጥፋቱን አምኖ መጸጸቱን እና የሁለት ልጆች አባት መሆኑን በመጥቀስ ቅጣት እንዲቀልለት ያቀረበውን ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ተቀብሏል።
በዚህም መሰረት ችሎቱ የእስር ቅጣቱን ወደ 300 ብር የገንዘብ ቅጣት የቀየረው ሲሆን፣ ተከሳሹ የተበየነበትን ገንዘብ እንደከፈለ የዋስትናው ተመላሽ ተደርጎለት ከእስር እንዲፈታ ታዟል። ዘገባው የኢትዮጲካሊንክ ነው።
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የስፔን ላሊጋ የዋንጫ ሽሚያ ሌላ አስገራሚ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ሪያል ማድሪድ ከሜዳው ውጭ ኤስፓኞልን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በመርታት፣ የባርሴሎናን የዋንጫ አከባበር ለጊዜው እንዲዘገይ አድርጓል። ይህ ውጤት ግን አንድ ትልቅ ታሪካዊ አጋጣሚን ይዟል። ባርሴሎና የላሊጋውን ዋንጫ በሚቀጥለው እሁድ በሚካሄደው ታላቁ "ኤል ክላሲኮ" ጨዋታ ላይ የመቀዳጀት ዕድል አግኝቷል። በአር ሲ ዲ ኢ ስታዲየም ማድሪዶች ድል እንዲቀናቸው ያደረገው ብራዚላዊው ኮከብ ቪኒሺየስ ጁኒየር ነው። በመጀመሪያው አጋማሽ የኤስፓኞል ግብ ብረት የመለሰበት ቪኒሺየስ፣ በሁለተኛው አጋማሽ ግን ሊታገስ አልቻለም። ከጎንካሎ ጋርሲያ ጋር በጥሩ አንድ ሁለት ቅብብል የመጀመሪያውን ግብ ከመረብ ካሳረፈ በኋላ፣ ብዙም ሳይቆይ ከጁድ ቤሊንግሃም በድንቅ ተረከዝ የተመለሰለትን ኳስ ወደ ግብነት በመቀየር የማድሪድን የበላይነት አረጋግጧል።
በጨዋታው ላይ የኤስፓኞሉ ኦማር ኤል ሂላሊ በቪኒሺየስ ላይ በሰራው ጥፋት ቀይ ካርድ ቢሰጠውም፣ በቪኤአር ታይቶ ውሳኔው ተሰርዟል። ሆኖም ማድሪድ ነጥብ ባለመጣሉ ባርሴሎናን በክብር አጀብ የመቀበል አስገዳጅ አጣብቂኝ ውስጥ ከመግባት ለጊዜው ድኗል። አሁን የዓለም እግር ኳስ አድናቂዎች አይን በሚቀጥለው እሁድ ወደ ኑ ካምፕ ስታዲየም አምርቷል። በላሊጋው የ97 ዓመታት ታሪክ ውስጥ ዋንጫ በኤል ክላሲኮ ጨዋታ ተወስኖ አያውቅም። ባርሴሎና ግን ከዘላለም ተቀናቃኙ ሪያል ማድሪድ ጋር አቻ ቢለያይ እንኳን የዘንድሮውን ዋንጫ በታሪካዊው ምሽት ከፍ የማድረግ ዕድል አለው።
ባርሴሎና ዋንጫውን ለማንሳት ብቻ ሳይሆን ሌሎች ታሪካዊ ሪከርዶችን ለመስበርም ተቃርቧል። በአሁኑ ወቅት ከማድሪድ በ11 ነጥብ ርቀው የሚገኙት ባርሳዎች፣ የቀሩትን አራት ጨዋታዎች ካሸነፉ እ.ኤ.አ በ2012-13 ያስመዘገቡትን የ15 ነጥብ የሻምፒዮናነት ልዩነት ሪከርድ መስበር ይችላሉ። በቀሪ ጨዋታዎች ድል የሚቀናቸው ከሆነም፣ በሊጉ ታሪክ 100 ነጥብ በመሰብሰብ ሪያል ማድሪድ እና ራሱ ባርሳ ቀደም ሲል የሰሩትን ሪከርድ ይጋራሉ። በተጨማሪም እስካሁን አንድ ጊዜ ብቻ አቻ የተለዩት ካታላኖች፣ 33 ጨዋታዎችን በማሸነፍ አዲስ የላሊጋ ሪከርድ ለመፃፍ ተቃርበዋል። ለሪያል ማድሪድ ግን የዘንድሮው የውድድር ዘመን መራራ እየሆነ ነው። ይህ የውድድር ዓመት ያለ ዋንጫ የሚጠናቀቅ ከሆነ፣ ከ2009-10 ወዲህ ክለቡ ለሁለተኛ ጊዜ ምንም ዓይነት ዋንጫ ሳይበላ የቀረበት ዓመት ሆኖ ይመዘገባል።
በጨዋታው ላይ የኤስፓኞሉ ኦማር ኤል ሂላሊ በቪኒሺየስ ላይ በሰራው ጥፋት ቀይ ካርድ ቢሰጠውም፣ በቪኤአር ታይቶ ውሳኔው ተሰርዟል። ሆኖም ማድሪድ ነጥብ ባለመጣሉ ባርሴሎናን በክብር አጀብ የመቀበል አስገዳጅ አጣብቂኝ ውስጥ ከመግባት ለጊዜው ድኗል። አሁን የዓለም እግር ኳስ አድናቂዎች አይን በሚቀጥለው እሁድ ወደ ኑ ካምፕ ስታዲየም አምርቷል። በላሊጋው የ97 ዓመታት ታሪክ ውስጥ ዋንጫ በኤል ክላሲኮ ጨዋታ ተወስኖ አያውቅም። ባርሴሎና ግን ከዘላለም ተቀናቃኙ ሪያል ማድሪድ ጋር አቻ ቢለያይ እንኳን የዘንድሮውን ዋንጫ በታሪካዊው ምሽት ከፍ የማድረግ ዕድል አለው።
ባርሴሎና ዋንጫውን ለማንሳት ብቻ ሳይሆን ሌሎች ታሪካዊ ሪከርዶችን ለመስበርም ተቃርቧል። በአሁኑ ወቅት ከማድሪድ በ11 ነጥብ ርቀው የሚገኙት ባርሳዎች፣ የቀሩትን አራት ጨዋታዎች ካሸነፉ እ.ኤ.አ በ2012-13 ያስመዘገቡትን የ15 ነጥብ የሻምፒዮናነት ልዩነት ሪከርድ መስበር ይችላሉ። በቀሪ ጨዋታዎች ድል የሚቀናቸው ከሆነም፣ በሊጉ ታሪክ 100 ነጥብ በመሰብሰብ ሪያል ማድሪድ እና ራሱ ባርሳ ቀደም ሲል የሰሩትን ሪከርድ ይጋራሉ። በተጨማሪም እስካሁን አንድ ጊዜ ብቻ አቻ የተለዩት ካታላኖች፣ 33 ጨዋታዎችን በማሸነፍ አዲስ የላሊጋ ሪከርድ ለመፃፍ ተቃርበዋል። ለሪያል ማድሪድ ግን የዘንድሮው የውድድር ዘመን መራራ እየሆነ ነው። ይህ የውድድር ዓመት ያለ ዋንጫ የሚጠናቀቅ ከሆነ፣ ከ2009-10 ወዲህ ክለቡ ለሁለተኛ ጊዜ ምንም ዓይነት ዋንጫ ሳይበላ የቀረበት ዓመት ሆኖ ይመዘገባል።
1 month ago
ለዋንጫ የሚሆን በቂ ነዳጅ አለን፡- የቬንገርን ሪከርድ ለመስበር የሚጫወተው ሚኬል አርቴታ
********************
በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሊጉ መሪ አርሰናል በለንደን ደርቢ ዛሬ በሜዳው ከፉልሀም ይጫወታል፡፡ ከሁለት የሊጉ ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ባለፈው ሳምንት ኒውካስትልን በማሸነፍ ወደ ድል የተመለሰው የሰሜን ለንደኑ ክለብ ወደ ዋንጫው ለመቅረብ በሚያደርገው ጨዋታ ከፉልሀም ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል፡፡
ጨዋታው ምሽት 1 ሰዓት ከ 30 ላይ በኤምሬትስ የሚደረግ ሲሆን አርሰናል በሜዳው ከፉልሀም ባደረጋቸው ያለፉት 32 ጨዋታዎች አልተሸነፈም፡፡ 25 ጨዋታዎችን ሲያሸንፍ በሰባቱ አቻ ተለያይቷል፡፡ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ከ20 ዓመት በኋላ ለፍጻሜ ለመድረስ ከአትሌቲኮ ማድሪድ አንድ የ90 ደቂቃ ፍልሚያ ብቻ የሚቀረው አርሰናል ዛሬ በሜዳው የሚያደርገውን ጨዋታ ካሸነፍ የማንችስተር ሲቲ ሁለት ተስተካካይ ጨዋታዎች እንደተጠበቁ ሆነው የነጥብ ልዩነቱን ወደ ስድስት ከፍ የሚያደርግ ይሆናል።
ከወሳኙ ጨዋታ በፊት ሚኬልል አርቴታ በሰጠው ሃሳብ አርሰናል ለዋንጫ የሚያበቃው ነዳጅ (አቅም) አለው ብሏል፡፡ ስፔናዊው አሰልጣኝ “ሊጉ ሊጠናቀቅ አራት ጨዋታዎች ሲቀሩት መገኘት ያለብን ደረጃ ላይ ተገኝተናል ለሁሉም ፈተና ዝግጁ ነን በውድድር ዓመቱ ሁሉ ስናደርግ የነበረውን የማሸነፍ ፍላጎት ይዘን እስከ መጨረሻው እንጓዘለን” ብሏል፡፡ ደጋፊዎች በእያንዳንዱ እንቅስቃሴ ላይ ለተጫዋቾች የሚያሳዩት አዎንታዊ ድጋፍ ውጤቱን ይበልጥ የተሻለ እንደሚያደርገውም ገልጿል፡፡
በሌላ በኩል፣ ሚኬል አርቴታ የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈ በአንድ የውድድር ዓመት አርሰን ቬንገር ካስመዘገቡት የድል ብዛት በላይ በማሸነፍ በክለቡ አዲስ ታሪክ ይጽፋል። ፈረንሳዊው አሰልጣኝ አርሰን ቬንገር በ2001/02 የውድድር ዓመት በ60 ጨዋታዎች 39 ድሎችን ያስመዘገቡ ሲሆን፤ አርቴታ በበኩሉ በዘንድሮው የውድድር ዓመት እስካሁን ባደረጋቸው 57 ጨዋታዎች 39ኙን በማሸነፍ የአንጋፋውን ሰው ታሪክ ተጋርቷል። በመሆኑም ዛሬ ፉልሃምን ማሸነፍ የሚችል ከሆነ የቬንገርን የቆየ ክብረ ወሰን በማሻሻል በክለቡ ታሪክ በአንድ የውድድር ዓመት ብዙ ጨዋታዎችን ያሸነፈ የመጀመሪያው አሰልጣኝ ሆኖ ስሙን በደመቀ ሁኔታ ይጽፋል።
የፉልሀሙ አሰልጣኝ ማርኮ ሲልቫ እንዲህ አይነት ጨዋታዎችን ማድረግ ያስደስተኛል በመሆኑም ለዋንጫ ከሚፋለመው አርሰናል የምንጫወተው ሦስት ነጥብ ለማግኝት ነው ብለዋል፡፡ በጨዋታው ካይ ሀቨርዝ እና ዩሪየን ቲምበር በጉዳት ከስብስቡ ወጭ ሲሆኑ ማርቲን ኦዴጋርድ ለጨዋታው እንደሚደርስ ሚኬል አርቴታ ተናግሯል፡፡
በሌላ ጨዋታ በሊጉ ለመቆየት እየታገለ የሚገኘው ዌስትሀም ዩናይትድ 11 ሰዓት ላይ ከሜዳው ወጭ ከብሬንትፎርድ ይጫወታል፡፡ በ36 ነጥብ 17ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ዌስትሀም ከባለፉት ስድስት የሊግ ጨዋታዎች የተሸነፈው በአንዱ ብቻ ሲሆን 18ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ቶተንሀም እንዳይደርስበት የሚፋለም ይሆናል፡፡
ኒውካስትል ዩናይትድ ከብራይተን እና ከሊጉ መሰናበቱን ያረጋገጠመው ዎልቭስ ከሰንደርላንድ በተመሳሳይ 11 ሰዓት የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
#ethiopiabroadcastingcorporation #epl #arsenal #fulham
********************
በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሊጉ መሪ አርሰናል በለንደን ደርቢ ዛሬ በሜዳው ከፉልሀም ይጫወታል፡፡ ከሁለት የሊጉ ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ባለፈው ሳምንት ኒውካስትልን በማሸነፍ ወደ ድል የተመለሰው የሰሜን ለንደኑ ክለብ ወደ ዋንጫው ለመቅረብ በሚያደርገው ጨዋታ ከፉልሀም ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል፡፡
ጨዋታው ምሽት 1 ሰዓት ከ 30 ላይ በኤምሬትስ የሚደረግ ሲሆን አርሰናል በሜዳው ከፉልሀም ባደረጋቸው ያለፉት 32 ጨዋታዎች አልተሸነፈም፡፡ 25 ጨዋታዎችን ሲያሸንፍ በሰባቱ አቻ ተለያይቷል፡፡ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ከ20 ዓመት በኋላ ለፍጻሜ ለመድረስ ከአትሌቲኮ ማድሪድ አንድ የ90 ደቂቃ ፍልሚያ ብቻ የሚቀረው አርሰናል ዛሬ በሜዳው የሚያደርገውን ጨዋታ ካሸነፍ የማንችስተር ሲቲ ሁለት ተስተካካይ ጨዋታዎች እንደተጠበቁ ሆነው የነጥብ ልዩነቱን ወደ ስድስት ከፍ የሚያደርግ ይሆናል።
ከወሳኙ ጨዋታ በፊት ሚኬልል አርቴታ በሰጠው ሃሳብ አርሰናል ለዋንጫ የሚያበቃው ነዳጅ (አቅም) አለው ብሏል፡፡ ስፔናዊው አሰልጣኝ “ሊጉ ሊጠናቀቅ አራት ጨዋታዎች ሲቀሩት መገኘት ያለብን ደረጃ ላይ ተገኝተናል ለሁሉም ፈተና ዝግጁ ነን በውድድር ዓመቱ ሁሉ ስናደርግ የነበረውን የማሸነፍ ፍላጎት ይዘን እስከ መጨረሻው እንጓዘለን” ብሏል፡፡ ደጋፊዎች በእያንዳንዱ እንቅስቃሴ ላይ ለተጫዋቾች የሚያሳዩት አዎንታዊ ድጋፍ ውጤቱን ይበልጥ የተሻለ እንደሚያደርገውም ገልጿል፡፡
በሌላ በኩል፣ ሚኬል አርቴታ የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈ በአንድ የውድድር ዓመት አርሰን ቬንገር ካስመዘገቡት የድል ብዛት በላይ በማሸነፍ በክለቡ አዲስ ታሪክ ይጽፋል። ፈረንሳዊው አሰልጣኝ አርሰን ቬንገር በ2001/02 የውድድር ዓመት በ60 ጨዋታዎች 39 ድሎችን ያስመዘገቡ ሲሆን፤ አርቴታ በበኩሉ በዘንድሮው የውድድር ዓመት እስካሁን ባደረጋቸው 57 ጨዋታዎች 39ኙን በማሸነፍ የአንጋፋውን ሰው ታሪክ ተጋርቷል። በመሆኑም ዛሬ ፉልሃምን ማሸነፍ የሚችል ከሆነ የቬንገርን የቆየ ክብረ ወሰን በማሻሻል በክለቡ ታሪክ በአንድ የውድድር ዓመት ብዙ ጨዋታዎችን ያሸነፈ የመጀመሪያው አሰልጣኝ ሆኖ ስሙን በደመቀ ሁኔታ ይጽፋል።
የፉልሀሙ አሰልጣኝ ማርኮ ሲልቫ እንዲህ አይነት ጨዋታዎችን ማድረግ ያስደስተኛል በመሆኑም ለዋንጫ ከሚፋለመው አርሰናል የምንጫወተው ሦስት ነጥብ ለማግኝት ነው ብለዋል፡፡ በጨዋታው ካይ ሀቨርዝ እና ዩሪየን ቲምበር በጉዳት ከስብስቡ ወጭ ሲሆኑ ማርቲን ኦዴጋርድ ለጨዋታው እንደሚደርስ ሚኬል አርቴታ ተናግሯል፡፡
በሌላ ጨዋታ በሊጉ ለመቆየት እየታገለ የሚገኘው ዌስትሀም ዩናይትድ 11 ሰዓት ላይ ከሜዳው ወጭ ከብሬንትፎርድ ይጫወታል፡፡ በ36 ነጥብ 17ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ዌስትሀም ከባለፉት ስድስት የሊግ ጨዋታዎች የተሸነፈው በአንዱ ብቻ ሲሆን 18ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ቶተንሀም እንዳይደርስበት የሚፋለም ይሆናል፡፡
ኒውካስትል ዩናይትድ ከብራይተን እና ከሊጉ መሰናበቱን ያረጋገጠመው ዎልቭስ ከሰንደርላንድ በተመሳሳይ 11 ሰዓት የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
#ethiopiabroadcastingcorporation #epl #arsenal #fulham
1 month ago
አዲስ የሙዚቃ ጉዞ ተጀመረ፤
ድምፃዊት ዳግማዊት ፀሐዬ የአልበም ስምምነት ተፈራረመች
#ethiopia | ታዋቂዋ ድምፃዊት ዳግማዊት ፀሐዬ ከናሆም ሪከርድስ ጋር አዲስ የሙዚቃ አልበም ለማሳተም በይፋ ስምምነት ተፈራረሙ።
ይህ ጥምረት በሙዚቃው ኢንዱስትሪ ውስጥ የጥበብ ስራዋን ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ታምኖበታል።
ናሆም ሪከርድስ ባለው ሰፊ ልምድ እና በድምፃዊቷ ልዩ ብቃት የታጀበው ይህ አዲስ ስራ የሀገራችንን ባህል እና ዘመናዊ የሙዚቃ ስልት አጣምሮ የያዘ ጥራት ያለው ስራ ' በጥቂት በአመታት ውስጥ ' ለታዳሚዎች እንደሚያቀርብ ተገልጿል።
ይህ አልበም ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገበት መሆኑም ተጠቁሟል።
A Major Milestone in Music: Artist Dagmawit Tsehaye Joins Nahom Records Inc
#ethiopia | Acclaimed artist Dagmawit Tsehaye has officially entered into an exclusive album production agreement with Nahom Records Inc. (NRI), signaling the start of a transformative era in her professional career.
This collaboration is poised to deliver a significant impact on the music scene, blending her exceptional vocal prowess with the renowned production expertise of NRI.
The upcoming project is expected to be a masterpiece of cultural expression and contemporary sound, driven by a shared vision for artistic excellence. Fans can look forward to a deeply passionate collection of music that highlights both heritage and innovation.
This partnership underscores a commitment to elevating Ethiopian music to new heights, with more details on the high-profile release expected soon.
#dagmawittsehaye #nahomrecords #ethiopianmusic #newalbum #musicindustry #comingsoon #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa #ዳግማዊትፀሐይ #ናሆምሪከርድስ #የኢትዮጵያሙዚቃ #አዲስአልበም #ጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
ድምፃዊት ዳግማዊት ፀሐዬ የአልበም ስምምነት ተፈራረመች
#ethiopia | ታዋቂዋ ድምፃዊት ዳግማዊት ፀሐዬ ከናሆም ሪከርድስ ጋር አዲስ የሙዚቃ አልበም ለማሳተም በይፋ ስምምነት ተፈራረሙ።
ይህ ጥምረት በሙዚቃው ኢንዱስትሪ ውስጥ የጥበብ ስራዋን ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ታምኖበታል።
ናሆም ሪከርድስ ባለው ሰፊ ልምድ እና በድምፃዊቷ ልዩ ብቃት የታጀበው ይህ አዲስ ስራ የሀገራችንን ባህል እና ዘመናዊ የሙዚቃ ስልት አጣምሮ የያዘ ጥራት ያለው ስራ ' በጥቂት በአመታት ውስጥ ' ለታዳሚዎች እንደሚያቀርብ ተገልጿል።
ይህ አልበም ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገበት መሆኑም ተጠቁሟል።
A Major Milestone in Music: Artist Dagmawit Tsehaye Joins Nahom Records Inc
#ethiopia | Acclaimed artist Dagmawit Tsehaye has officially entered into an exclusive album production agreement with Nahom Records Inc. (NRI), signaling the start of a transformative era in her professional career.
This collaboration is poised to deliver a significant impact on the music scene, blending her exceptional vocal prowess with the renowned production expertise of NRI.
The upcoming project is expected to be a masterpiece of cultural expression and contemporary sound, driven by a shared vision for artistic excellence. Fans can look forward to a deeply passionate collection of music that highlights both heritage and innovation.
This partnership underscores a commitment to elevating Ethiopian music to new heights, with more details on the high-profile release expected soon.
#dagmawittsehaye #nahomrecords #ethiopianmusic #newalbum #musicindustry #comingsoon #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa #ዳግማዊትፀሐይ #ናሆምሪከርድስ #የኢትዮጵያሙዚቃ #አዲስአልበም #ጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢራን የአንድ ዶላር ምንዛሬ 1.8 ሚሊዮን ሪያል መድረሱ ተዘገበ፡፡ የኢራን ብሄራዊ መገበያያ የሆነው ሪያል በዛሬው እለት በከፍተኛ ሁኔታ መውደቁ ተዘገበ፡፡ ኤቢሲ ኒውስ እንደዘገበው ፌብሩዋሪ 28 የተጀመረውን ጦርነት ተከትሎ የኢራን ሪያል ያን ያህል ለውጥ አላሳየም ነበር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ አገሪቱ ከውጭ የምታስገባቸው ምርቶች አነስተኛ ስለነበሩ ነው፡፡
ይሁንና ካለፉት ሁለት ቀናት ወዲህ ግን ሪያል በከፍተኛ ደረጃ መውደቅ ጀምሮ ዛሬ ሪከርድ በያዘ ሁኔታ ቅናሽ አሳይቷል፡፡ እንደዘገባው በአገሪቱ ይፋዊ ምንዛሬ ዛሬ የአንድ ዶላር ዋጋ 1.3 ሚሊዮን ሪያል ቢሆንም በጥቁር ገበያ ግን ከ1.8 ሚሊዮን ሪያል በበለጠ ዋጋ እየተመነዘረ ነው፡፡ ይህን በሁለት ቀናት ውስጥ የ15 ፐርሰንት ጭማሪ እንደታየበት ያመለክታል፡፡ ዘገባው እንደሚገልፀው ኢራን ከምግብ እስከ መድሀኒትና ከኤሌክትሮኒክስ እስከ ጥሬ እቃ ከውጭ የምታስገባ አገር እንደመሆኗ የምንዛሬዋ መውደቅ በአገሪቱ ገበያ ላይ ትልቅ ተፅእኖ የሚፈጥር ይሆናል፡፡
ይሁንና ካለፉት ሁለት ቀናት ወዲህ ግን ሪያል በከፍተኛ ደረጃ መውደቅ ጀምሮ ዛሬ ሪከርድ በያዘ ሁኔታ ቅናሽ አሳይቷል፡፡ እንደዘገባው በአገሪቱ ይፋዊ ምንዛሬ ዛሬ የአንድ ዶላር ዋጋ 1.3 ሚሊዮን ሪያል ቢሆንም በጥቁር ገበያ ግን ከ1.8 ሚሊዮን ሪያል በበለጠ ዋጋ እየተመነዘረ ነው፡፡ ይህን በሁለት ቀናት ውስጥ የ15 ፐርሰንት ጭማሪ እንደታየበት ያመለክታል፡፡ ዘገባው እንደሚገልፀው ኢራን ከምግብ እስከ መድሀኒትና ከኤሌክትሮኒክስ እስከ ጥሬ እቃ ከውጭ የምታስገባ አገር እንደመሆኗ የምንዛሬዋ መውደቅ በአገሪቱ ገበያ ላይ ትልቅ ተፅእኖ የሚፈጥር ይሆናል፡፡
1 month ago
♦️"አንድም የፌዴሬሽን አመራር ደውሎ "እንኳን ደስ አላችሁ" ባለማለታቸው እኔም ታሪክ የሠሩት አትሌቶችም በእጅጉ አዝነናል"
♦️አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴና አትሌት ደራርቱ ቱሉ አትሌቶቹ ላባቸው ሳይደርቅ ደውለው መልካም ምኞታቸውን መግለፃቸው ትልቅ የሞራል ስንቅና መፅናኛ ሆኖናል"
አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ
#ethiopia | ትናንት ለኢትዮጵያውያንና ለአትሌቲክሱ ልዩና ታሪካዊ ቀን ነበር ማለት ይቻላል፤በማራቶን ታሪክ በወርቅ ቀለም የተፃፉ አዳዲስ ታሪኮች የተመዘገቡበት ልዩ ቀንም ነበር።
ጀግናዋ አትሌታችን ትዕግስት አሠፋ የለንደንን ማራቶንን ለሁለት ተከታታይ ዓመታት በማሸነፍ ክብሯን ከማስጠበቋም በላይ በሴቶች ብቻ(Only Womens)በራስዋ ተይዞ የነበረውን አዲስ የአለም ሪከርድ በማስመዝገብ አለምን ሁሉ ጉድ አሠኝታለች።
በወንዶች የለንደን ማራቶን ሌላ አዲስ ታሪክ በኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጄልቻ ተሠርቶ አለም ጉድ ሲል አድሯል፣ውሏል፤
አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ በውድድሩ በሁለተኛነት ቢያጠናቅቅም በመጀመሪያ የማራቶን ተሳትፎው ከ2:00:00 በታች ማራቶንን መሮጥ እንደሚቻል ያሳየበትን አዲስ ታሪክ ማፃፍ ቾሏል።
ከእነዚህና ከበርካታ ሪከርድ ሠባሪና ውጤታማ አትሌቶች ጀርባ የሚገኘው አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ጀግናዎቹን አትሌቶች ደራርቱ ቱሉና አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ሳይቀሩ ሁሉም ከየአቅጣጫው ደስታውን በግል ስልካችንም በኢሜልም እየገለፀ ባለበት በዚህ ሠዓት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች አንዳቸውም በቀጥታ ደውለው ደስታችንን ባለመካፈላቸው አዝነናል፤ከዚህ በፊት ዮሚፍም፣ፎቴንም አለምን ጉድ ያሠኘ ታሪክ አፅፈው ሲመለሱ ኤርፖርት የተቀበላቸው የለም፤ ታሪክ እንደሠራ እንደ ጀግና ሳይሆን እንደ ተራ መግባታቸውን በቁጭት እናስታውሳለን።
አሁንም አንድም አመራር ስልክ ደውሎ ስሜቱን አለመግለፁ አሳዝኖናል፤በዚህም ፌዴሬሽኑ ሊወቀስ ይገባል።
የቀድሞ የፌዴሬሽኑ አመራር ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ስልጣን ላይ እያለች እኮ ስልክ መደወሉን ተወው ያለንበት ወይም ኤርፖርት ድረስ መጥታ ነበር የምትቀበለን፣ደስታችንን የምትጋራው፤አሁን ግን አንድም የአትሌቲክሱ አመራር ደስታችንን ሊጋራ ባለመፍቀዱ በእጅጉ ተሠምቶናል፣በዚህ ወቀሳ እናቀርባለን።ብሏል አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ።
" ከየአቅጣጫው ከማይጠበቁ ሠዎች የእንኳን ደስ አላችሁ ጋጋታ ለእኔም ለአትሌቶቹ ሲመጣ ጉዳዩ በዋናነት የሚመለከተው የአትሌቲክሱ አመራር እስከዚህ ቃለ-ምልልስ ድረስ አንዳቸውም አትሌቶቹጋም ሆነ እኔጋ ደውለው ደስታችንና ታሪካችንን ሊጋሩ፣ሊያበረታቱን ባለመሞከራቸው እጅግ በጣም አዝነናል፣አትሌቶቹም በድርጊቱ ውስጣቸው ተሠብሯል"የሚለው አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ"በኃላፊነት ላይ የሌሉት ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴና ጀግናዋ አትሌት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ በኃላፊነት ላይ ሳይሆኑ የተመዘገበው ሪከርድም፣ውጤቱም የሀገር ስኬት ነው ብለው በደስታ ስሜት ውስጥ ሆነው የአትሌቶቹ ላብ ሳይደርቅ ደስታችንን በትኩሱ መጋራታቸው ሌላ ደስታን ፈጥሮልናል ብቻ ሳይሆን መፅናኛም ሆኖናል፤የኢትዮጵያ ህዝብም እንዲያመሠግንልን እንፈልጋለን"በማለት የበርካታ የማራቶን ሯጮች የስኬታማነት ምስጥር የሆነውና ከእነሱ ስኬት ጀርባ የሚገኘው የሪከርዱ ሸበኛ፣የማራቶን አሠልጣኞች ንጉስ የሆነው ገመዶ ደደፎ።
"እነዚህ አትሌቶች ያስመዘገቡት ታሪክ የሀገር ነው፣በድሉ ስሟ ከፍ ብሎ የሚጠራውም የሀገራችን ነው፤ዕውነታው ይሄ ሆኖ እንዴት አንድ አመራር እንኳን ደውሎ አትሌቶቹን አያበረታታም?እስቲ ኬንያዊያኖችን ምን እያደረጉ እንደሆነ እንዴት ደስታቸውን እየገለፁ እንደሆነ ተመልከት በስልክም፣በእንኳን ደስ አለህ መልዕክትም አጨናንቀውታል፤የእኛ ግን ከዚህ በተቃራኒ በመሆኑ እኔም ልጆቼም ተሠምቶናል፣ውስጣችንም በጣም አዝኗል"ሲል አሠልጠኝ ገመዶ ደደፎ በአስተያየቱ መጨረሻ በተለይ ለሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ተናግሯል።በዚህ ጉዳይ ላይ ምላሽ አለኝ የሚል አካል ካለ ለማስተናገድ ዝግጁ መሆናችንን እንገልፃለን።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል
♦️አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴና አትሌት ደራርቱ ቱሉ አትሌቶቹ ላባቸው ሳይደርቅ ደውለው መልካም ምኞታቸውን መግለፃቸው ትልቅ የሞራል ስንቅና መፅናኛ ሆኖናል"
አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ
#ethiopia | ትናንት ለኢትዮጵያውያንና ለአትሌቲክሱ ልዩና ታሪካዊ ቀን ነበር ማለት ይቻላል፤በማራቶን ታሪክ በወርቅ ቀለም የተፃፉ አዳዲስ ታሪኮች የተመዘገቡበት ልዩ ቀንም ነበር።
ጀግናዋ አትሌታችን ትዕግስት አሠፋ የለንደንን ማራቶንን ለሁለት ተከታታይ ዓመታት በማሸነፍ ክብሯን ከማስጠበቋም በላይ በሴቶች ብቻ(Only Womens)በራስዋ ተይዞ የነበረውን አዲስ የአለም ሪከርድ በማስመዝገብ አለምን ሁሉ ጉድ አሠኝታለች።
በወንዶች የለንደን ማራቶን ሌላ አዲስ ታሪክ በኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጄልቻ ተሠርቶ አለም ጉድ ሲል አድሯል፣ውሏል፤
አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ በውድድሩ በሁለተኛነት ቢያጠናቅቅም በመጀመሪያ የማራቶን ተሳትፎው ከ2:00:00 በታች ማራቶንን መሮጥ እንደሚቻል ያሳየበትን አዲስ ታሪክ ማፃፍ ቾሏል።
ከእነዚህና ከበርካታ ሪከርድ ሠባሪና ውጤታማ አትሌቶች ጀርባ የሚገኘው አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ጀግናዎቹን አትሌቶች ደራርቱ ቱሉና አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ሳይቀሩ ሁሉም ከየአቅጣጫው ደስታውን በግል ስልካችንም በኢሜልም እየገለፀ ባለበት በዚህ ሠዓት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች አንዳቸውም በቀጥታ ደውለው ደስታችንን ባለመካፈላቸው አዝነናል፤ከዚህ በፊት ዮሚፍም፣ፎቴንም አለምን ጉድ ያሠኘ ታሪክ አፅፈው ሲመለሱ ኤርፖርት የተቀበላቸው የለም፤ ታሪክ እንደሠራ እንደ ጀግና ሳይሆን እንደ ተራ መግባታቸውን በቁጭት እናስታውሳለን።
አሁንም አንድም አመራር ስልክ ደውሎ ስሜቱን አለመግለፁ አሳዝኖናል፤በዚህም ፌዴሬሽኑ ሊወቀስ ይገባል።
የቀድሞ የፌዴሬሽኑ አመራር ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ስልጣን ላይ እያለች እኮ ስልክ መደወሉን ተወው ያለንበት ወይም ኤርፖርት ድረስ መጥታ ነበር የምትቀበለን፣ደስታችንን የምትጋራው፤አሁን ግን አንድም የአትሌቲክሱ አመራር ደስታችንን ሊጋራ ባለመፍቀዱ በእጅጉ ተሠምቶናል፣በዚህ ወቀሳ እናቀርባለን።ብሏል አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ።
" ከየአቅጣጫው ከማይጠበቁ ሠዎች የእንኳን ደስ አላችሁ ጋጋታ ለእኔም ለአትሌቶቹ ሲመጣ ጉዳዩ በዋናነት የሚመለከተው የአትሌቲክሱ አመራር እስከዚህ ቃለ-ምልልስ ድረስ አንዳቸውም አትሌቶቹጋም ሆነ እኔጋ ደውለው ደስታችንና ታሪካችንን ሊጋሩ፣ሊያበረታቱን ባለመሞከራቸው እጅግ በጣም አዝነናል፣አትሌቶቹም በድርጊቱ ውስጣቸው ተሠብሯል"የሚለው አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ"በኃላፊነት ላይ የሌሉት ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴና ጀግናዋ አትሌት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ በኃላፊነት ላይ ሳይሆኑ የተመዘገበው ሪከርድም፣ውጤቱም የሀገር ስኬት ነው ብለው በደስታ ስሜት ውስጥ ሆነው የአትሌቶቹ ላብ ሳይደርቅ ደስታችንን በትኩሱ መጋራታቸው ሌላ ደስታን ፈጥሮልናል ብቻ ሳይሆን መፅናኛም ሆኖናል፤የኢትዮጵያ ህዝብም እንዲያመሠግንልን እንፈልጋለን"በማለት የበርካታ የማራቶን ሯጮች የስኬታማነት ምስጥር የሆነውና ከእነሱ ስኬት ጀርባ የሚገኘው የሪከርዱ ሸበኛ፣የማራቶን አሠልጣኞች ንጉስ የሆነው ገመዶ ደደፎ።
"እነዚህ አትሌቶች ያስመዘገቡት ታሪክ የሀገር ነው፣በድሉ ስሟ ከፍ ብሎ የሚጠራውም የሀገራችን ነው፤ዕውነታው ይሄ ሆኖ እንዴት አንድ አመራር እንኳን ደውሎ አትሌቶቹን አያበረታታም?እስቲ ኬንያዊያኖችን ምን እያደረጉ እንደሆነ እንዴት ደስታቸውን እየገለፁ እንደሆነ ተመልከት በስልክም፣በእንኳን ደስ አለህ መልዕክትም አጨናንቀውታል፤የእኛ ግን ከዚህ በተቃራኒ በመሆኑ እኔም ልጆቼም ተሠምቶናል፣ውስጣችንም በጣም አዝኗል"ሲል አሠልጠኝ ገመዶ ደደፎ በአስተያየቱ መጨረሻ በተለይ ለሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ተናግሯል።በዚህ ጉዳይ ላይ ምላሽ አለኝ የሚል አካል ካለ ለማስተናገድ ዝግጁ መሆናችንን እንገልፃለን።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል
1 month ago
አቶ ዳዊት ገበየሁ እና አቶ ገደኖ ካዋይታ ተፈረደባቸው።
⚫ ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ እንዲሆን የተለገሰ 6,594 የቤት ክዳን ቆርቆሮ ተሸጦ ለግል ጥቅም ውሏል ፤ 3,702,466.67 ብር ነው ተሽጦ የተበላው።
የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞ የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ ዳዊት ገበየሁ እና የግብርና መምሪያ የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኃላፊ የነበሩት አቶ ገደኖ ካዋይታ ላይ የፍርድ ውሳኔ ማሳለፉን የፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሀባ ቀውያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ግለሰቦቹ " የመንግስትን የሥራ ኃላፊነት በማይመች አኳኋን መምራት እና የሙስና ወንጀል " ጥፋተኛ መሆናቸውን ፍርድ ቤቱ አረጋግጧል ሲሉ ፕሬዚዳንቱ አሳውቀዋል።
ተከሳሾቹ በ2014 ዓ.ም በኮንሶ ዞን ሰገን ዙሪያ ወረዳ በግጭት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ እንዲሆን ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የተለገሰውን 6,594 የቤት ክዳን ቆርቆሮ ሸጠው ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው በማስረጃ መረጋገጡን አቶ ሙሀባ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ተከሳሾች ለግል ጥቅማቸው ያዋሉት ሀብት ግምቱ ብር 3,702,466.67 (ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሁለት ሺህ አራት መቶ ስልሳ ስልስት ብር ከስልስ ሰባት ሳንቲም) መሆኑን ጠቅሰው ፤ የተገኘው ጥቅምና በህዝብ ላይ የደረሰው ጉዳት እንዲሁም የወንጀሉ ዓላማ ከባድ መሆኑን ፍርድ ቤቱ ግምት ውስጥ ማስገባቱን ገልጸዋል።
እንደ ፕሬዚዳንቱ ገለጻ፣ ፍርድ ቤቱ በመመሪያው መሠረት ተከሳሾቹ እያንዳንዳቸው በ15 ዓመት ጽኑ እስራትና በ50,000 ብር መቀጮ እንዲቀጡ መነሻ ቅጣት ወስኖ ነበር።
ይሁን እንጂ ተከሳሾቹ ፦
- ከዚህ በፊት የወንጀል ሪከርድ የሌላቸው፣
- የቤተሰብ አስተዳዳሪና ለረዥም ጊዜያት ያገለገሉ በመሆናቸው፤
- በተለይ 1ኛ ተከሳሽ "እምርታ" የተሰኘ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራችና ስራ አስኪያጅ የነበሩ መሆናቸውን ከግምት ውስጥ በማስገባት ለእያንዳንዳቸው ሦስት የቅጣት ማቅለያዎች መያዛቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አብራርተዋል።
የግራ ቀኙን ክርክር ያደመጠው ፍርድ ቤት የሚከተለውን የመጨረሻ ውሳኔ ማስተላለፉን አቶ ሙሀባ ቀውያ ገልጸዋል።
1ኛ ተከሳሽ አቶ ዳዊት ገበየሁ ፦ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ከሰኔ 25 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በሚቆጠር በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000 የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ፤
2ኛ ተከሳሽ አቶ ገደኖ ካዋይታ ፦ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ከመስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሚቆጠር በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000 የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኗል።
በተጨማሪም ተከሳሾቹ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉትን ብር 3,702,466.67 ለመንግስት በጋራ እንዲመልሱ መወሰኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
አቶ ዳዊት ገበየሁ በዚሁ ፍ/ቤት በሌላ የወንጀል መዝገብ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በ7 ዓመት ጽኑ እስራትና በ5,000 ብር መቀጮ ተፈርዶባቸው የነበረ መሆኑን አቶ ሙሀባ ገልጸው፤ ሁለቱም የወንጀል ቅጣቶች ተደምረው ተከሳሹ በአጠቃላይ በ20 ዓመት ጽኑ እስራትና በ25,000 ብር የገንዘብ መቀጮ የሚቀጡ መሆኑን አስታውቀዋል።
tikvahethiopia
⚫ ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ እንዲሆን የተለገሰ 6,594 የቤት ክዳን ቆርቆሮ ተሸጦ ለግል ጥቅም ውሏል ፤ 3,702,466.67 ብር ነው ተሽጦ የተበላው።
የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞ የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ ዳዊት ገበየሁ እና የግብርና መምሪያ የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኃላፊ የነበሩት አቶ ገደኖ ካዋይታ ላይ የፍርድ ውሳኔ ማሳለፉን የፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሀባ ቀውያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ግለሰቦቹ " የመንግስትን የሥራ ኃላፊነት በማይመች አኳኋን መምራት እና የሙስና ወንጀል " ጥፋተኛ መሆናቸውን ፍርድ ቤቱ አረጋግጧል ሲሉ ፕሬዚዳንቱ አሳውቀዋል።
ተከሳሾቹ በ2014 ዓ.ም በኮንሶ ዞን ሰገን ዙሪያ ወረዳ በግጭት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ እንዲሆን ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የተለገሰውን 6,594 የቤት ክዳን ቆርቆሮ ሸጠው ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው በማስረጃ መረጋገጡን አቶ ሙሀባ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ተከሳሾች ለግል ጥቅማቸው ያዋሉት ሀብት ግምቱ ብር 3,702,466.67 (ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሁለት ሺህ አራት መቶ ስልሳ ስልስት ብር ከስልስ ሰባት ሳንቲም) መሆኑን ጠቅሰው ፤ የተገኘው ጥቅምና በህዝብ ላይ የደረሰው ጉዳት እንዲሁም የወንጀሉ ዓላማ ከባድ መሆኑን ፍርድ ቤቱ ግምት ውስጥ ማስገባቱን ገልጸዋል።
እንደ ፕሬዚዳንቱ ገለጻ፣ ፍርድ ቤቱ በመመሪያው መሠረት ተከሳሾቹ እያንዳንዳቸው በ15 ዓመት ጽኑ እስራትና በ50,000 ብር መቀጮ እንዲቀጡ መነሻ ቅጣት ወስኖ ነበር።
ይሁን እንጂ ተከሳሾቹ ፦
- ከዚህ በፊት የወንጀል ሪከርድ የሌላቸው፣
- የቤተሰብ አስተዳዳሪና ለረዥም ጊዜያት ያገለገሉ በመሆናቸው፤
- በተለይ 1ኛ ተከሳሽ "እምርታ" የተሰኘ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራችና ስራ አስኪያጅ የነበሩ መሆናቸውን ከግምት ውስጥ በማስገባት ለእያንዳንዳቸው ሦስት የቅጣት ማቅለያዎች መያዛቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አብራርተዋል።
የግራ ቀኙን ክርክር ያደመጠው ፍርድ ቤት የሚከተለውን የመጨረሻ ውሳኔ ማስተላለፉን አቶ ሙሀባ ቀውያ ገልጸዋል።
1ኛ ተከሳሽ አቶ ዳዊት ገበየሁ ፦ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ከሰኔ 25 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በሚቆጠር በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000 የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ፤
2ኛ ተከሳሽ አቶ ገደኖ ካዋይታ ፦ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ከመስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሚቆጠር በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000 የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኗል።
በተጨማሪም ተከሳሾቹ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉትን ብር 3,702,466.67 ለመንግስት በጋራ እንዲመልሱ መወሰኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
አቶ ዳዊት ገበየሁ በዚሁ ፍ/ቤት በሌላ የወንጀል መዝገብ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በ7 ዓመት ጽኑ እስራትና በ5,000 ብር መቀጮ ተፈርዶባቸው የነበረ መሆኑን አቶ ሙሀባ ገልጸው፤ ሁለቱም የወንጀል ቅጣቶች ተደምረው ተከሳሹ በአጠቃላይ በ20 ዓመት ጽኑ እስራትና በ25,000 ብር የገንዘብ መቀጮ የሚቀጡ መሆኑን አስታውቀዋል።
tikvahethiopia
1 month ago
ከሪከርዶችና ከአሸናፊ አትሌቶች ጀርባ ከፍ ብሎ የሚውለበለበው ስም አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ
በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
እስቲ ሁላችንም ባርኔጣችንን ከፍ አድርገን እናንሳለት፤ምክንያቱም በየጊዜው የሚሠባበሩት ሪከርዶችና ድሎቹ ለአለም የማራቶን አሠልጣኞች ንጉስ ለሆነው አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ይሄን እንድናደርግ ያስገድዳሉና።
የቅርቡን ለጊዜው እናቆየውና አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ የሚለው ስም ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት ድሎች፣ሜዳልያዎችና ሪከርዶች ጀርባ ከፍ ብሎ ሲሠማና ሲውለበለብ ይታያል
♦️2016 ሪዮ ኦሎምፒክ
🥉በ10ሺ ሜትር
በአትሌት ታምራት ቶላ የነሐስ ሜዳልያ
♦️በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ በማራቶን
🥇በአትሌት ታምራት ቶላ(ወርቅ)
🥈በአትሌት ትዕግስት አሠፋ(ብር)
♦️በ2009 የአለም ሻምፒዮና በርሊን በማራቶን
🥉አትሌት አሠለፈች መርጊያ(ነሐስ)
♦️በ2017 የአለም ሻምፒዮና በርሊን በማራቶን
🥈አትሌት ታምራት ቶላ (ብር)
♦️በ2022 የአለም ሻምፒዮና አሜሪካ ኦሪገን በማራቶን
🥇አትሌት ታምራት ቶላ (ወርቅ)
♦️በ2023 የአለም ሻምፒዮና ሀንጋሪ ቡዳፔስት በማራቶን
🥇አትሌት አማኒ በሪሶ (ወርቅ)
♦️WR አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ በ21ኪ.ሜ አዲስ ሪከርድ
♦️አትሌት ትዕግስት አሠፋ ሶስት ጊዜ የአለም ሪከርድ ባለቤት
♦️በቅርቡ ደግሞ አትሌት ፎቴን ተስፋይ ሁለተኛው የማራቶን ምርጥ ሠዓት ሪከርድ ባለቤት
ከእነዚሁ ሁሉ ስኬቶችና ሪከርዶች ጀርባ በውጤት ያሸበረቀ በወርቅ ቀለም ስሙን በደማቁ ያፃፈ የሀገር ኩራት የሆነ ታላቅ ሠው አለ እሱም አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ።
ትናንት በለንደን ሠማይ ስር በማራቶን ታሪክ ሲሠራ የእሱ የስልጠና በረከት ያረፈባቸው አትሌት ትዕግስት አሠፋ አንደኛ ከመውጣት በተከታታይ ዓመት የለንደንን ማራቶን ከማሸነፍ በዘለለ በሴቶች ብቻ (Only Womens) ተይዞ የነበረውን የራሷን ሪከርድ አሻሽላለች።
ሌላኛው የአሠልጣኝ ገመዶ የስልጠና ውጤት የሆነው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ በመጀመሪያው የማራቶን ተሳትፎው ሁለተኛ ከመውጣት ባለፈ የሠው ልጅ በዚህ ዘመን ማራቶንን ከ2:00:00 በታች እንደሚገባ በተግባር ካሳየው ዮሚፍ ቀጄልቻ ጀርባም ይሄ የአለማችን የማራቶን አሠልጣኞች ንጉስ ገመዶ ደደፎ አለ።
የአሸናፊነትና የሪከርዶች ባለቤት ከሆኑት አትሌቶች ጀርባ ወይም የውጤታማነት ምስጢራቸው የሆነው የአሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ስም ዛሬም እንደ ትላንቱ እንደ ባንዲራ ከፍ ብሎ ሲውለበለብ ይታያል።
👉የስኬታማና የሪከርድ ሠባሪ አትሌቶችን ስም አንስተን ገመዶ ደደፎ የሚለውን ስም አለማንሳት የሀገር ባለውለታውን ውለታ ከመብላቴም ያስቆጥራል።
እንኳን ደስ አለህ!! አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ
በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
እስቲ ሁላችንም ባርኔጣችንን ከፍ አድርገን እናንሳለት፤ምክንያቱም በየጊዜው የሚሠባበሩት ሪከርዶችና ድሎቹ ለአለም የማራቶን አሠልጣኞች ንጉስ ለሆነው አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ይሄን እንድናደርግ ያስገድዳሉና።
የቅርቡን ለጊዜው እናቆየውና አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ የሚለው ስም ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት ድሎች፣ሜዳልያዎችና ሪከርዶች ጀርባ ከፍ ብሎ ሲሠማና ሲውለበለብ ይታያል
♦️2016 ሪዮ ኦሎምፒክ
🥉በ10ሺ ሜትር
በአትሌት ታምራት ቶላ የነሐስ ሜዳልያ
♦️በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ በማራቶን
🥇በአትሌት ታምራት ቶላ(ወርቅ)
🥈በአትሌት ትዕግስት አሠፋ(ብር)
♦️በ2009 የአለም ሻምፒዮና በርሊን በማራቶን
🥉አትሌት አሠለፈች መርጊያ(ነሐስ)
♦️በ2017 የአለም ሻምፒዮና በርሊን በማራቶን
🥈አትሌት ታምራት ቶላ (ብር)
♦️በ2022 የአለም ሻምፒዮና አሜሪካ ኦሪገን በማራቶን
🥇አትሌት ታምራት ቶላ (ወርቅ)
♦️በ2023 የአለም ሻምፒዮና ሀንጋሪ ቡዳፔስት በማራቶን
🥇አትሌት አማኒ በሪሶ (ወርቅ)
♦️WR አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ በ21ኪ.ሜ አዲስ ሪከርድ
♦️አትሌት ትዕግስት አሠፋ ሶስት ጊዜ የአለም ሪከርድ ባለቤት
♦️በቅርቡ ደግሞ አትሌት ፎቴን ተስፋይ ሁለተኛው የማራቶን ምርጥ ሠዓት ሪከርድ ባለቤት
ከእነዚሁ ሁሉ ስኬቶችና ሪከርዶች ጀርባ በውጤት ያሸበረቀ በወርቅ ቀለም ስሙን በደማቁ ያፃፈ የሀገር ኩራት የሆነ ታላቅ ሠው አለ እሱም አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ።
ትናንት በለንደን ሠማይ ስር በማራቶን ታሪክ ሲሠራ የእሱ የስልጠና በረከት ያረፈባቸው አትሌት ትዕግስት አሠፋ አንደኛ ከመውጣት በተከታታይ ዓመት የለንደንን ማራቶን ከማሸነፍ በዘለለ በሴቶች ብቻ (Only Womens) ተይዞ የነበረውን የራሷን ሪከርድ አሻሽላለች።
ሌላኛው የአሠልጣኝ ገመዶ የስልጠና ውጤት የሆነው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ በመጀመሪያው የማራቶን ተሳትፎው ሁለተኛ ከመውጣት ባለፈ የሠው ልጅ በዚህ ዘመን ማራቶንን ከ2:00:00 በታች እንደሚገባ በተግባር ካሳየው ዮሚፍ ቀጄልቻ ጀርባም ይሄ የአለማችን የማራቶን አሠልጣኞች ንጉስ ገመዶ ደደፎ አለ።
የአሸናፊነትና የሪከርዶች ባለቤት ከሆኑት አትሌቶች ጀርባ ወይም የውጤታማነት ምስጢራቸው የሆነው የአሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ስም ዛሬም እንደ ትላንቱ እንደ ባንዲራ ከፍ ብሎ ሲውለበለብ ይታያል።
👉የስኬታማና የሪከርድ ሠባሪ አትሌቶችን ስም አንስተን ገመዶ ደደፎ የሚለውን ስም አለማንሳት የሀገር ባለውለታውን ውለታ ከመብላቴም ያስቆጥራል።
እንኳን ደስ አለህ!! አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ
Sponsored by
Surafel
1 month ago
📌ከሪከርዶችና ከአሸናፊ አትሌቶች ጀርባ ከፍ ብሎ የሚውለበለበው ስም አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ
#ethiopia | እስቲ ሁላችንም ባርኔጣችንን ከፍ አድርገን እናንሳለት፤ምክንያቱም በየጊዜው የሚሠባበሩት ሪከርዶችና ድሎቹ ለአለም የማራቶን አሠልጣኞች ንጉስ ለሆነው አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ይሄን እንድናደርግ ያስገድዳሉና።
የቅርቡን ለጊዜው እናቆየውና አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ የሚለው ስም ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት ድሎች፣ሜዳልያዎችና ሪከርዶች ጀርባ ከፍ ብሎ ሲሠማና ሲውለበለብ ይታያል
♦️2016 ሪዮ ኦሎምፒክ
🥉በ10ሺ ሜትር
በአትሌት ታምራት ቶላ የነሐስ ሜዳልያ
♦️በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ በማራቶን
🥇በአትሌት ታምራት ቶላ(ወርቅ)
🥈በአትሌት ትዕግስት አሠፋ(ብር)
♦️በ2009 የአለም ሻምፒዮና በርሊን በማራቶን
🥉አትሌት አሠለፈች መርጊያ(ነሐስ)
♦️በ2017 የአለም ሻምፒዮና በርሊን በማራቶን
🥈አትሌት ታምራት ቶላ (ብር)
♦️በ2022 የአለም ሻምፒዮና አሜሪካ ኦሪገን በማራቶን
🥇አትሌት ታምራት ቶላ (ወርቅ)
♦️በ2023 የአለም ሻምፒዮና ሀንጋሪ ቡዳፔስት በማራቶን
🥇አትሌት አማኒ በሪሶ (ወርቅ)
♦️WR አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ በ21ኪ.ሜ አዲስ ሪከርድ
♦️አትሌት ትዕግስት አሠፋ ሶስት ጊዜ የአለም ሪከርድ ባለቤት
♦️በቅርቡ ደግሞ አትሌት ፎቴን ተስፋይ ሁለተኛው የማራቶን ምርጥ ሠዓት ሪከርድ ባለቤት
ከእነዚሁ ሁሉ ስኬቶችና ሪከርዶች ጀርባ በውጤት ያሸበረቀ በወርቅ ቀለም ስሙን በደማቁ ያፃፈ የሀገር ኩራት የሆነ ታላቅ ሠው አለ እሱም አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ።
ዛሬም በለንደን ሠማይ ስር በማራቶን ታሪክ ሲሠራ የእሱ የስልጠና በረከት ያረፈባቸው አትሌት ትዕግስት አሠፋ አንደኛ ከመውጣት በተከታታይ ዓመት የለንደንን ማራቶን ከማሸነፍ በዘለለ በሴቶች ብቻ(Only Womens)ተይዞ የነበረውን የራሷን ሪከርድ አሻሽላለች።
ሌላኛው የአሠልጣኝ ገመዶ የስልጠና ውጤት የሆነው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ በመጀመሪያው የማራቶን ተሳትፎው ሁለተኛ ከመውጣት ባለፈ የሠው ልጅ በዚህ ዘመን ማራቶንን ከ2:00:00 በታች እንደሚገባ በተግባር ካሳየው ዮሚፍ ቀጄልቻ ጀርባም ይሄ የአለማችን የማራቶን አሠልጣኞች ንጉስ ገመዶ ደደፎ አለ።
የአሸናፊነትና የሪከርዶች ባለቤት ከሆኑት አትሌቶች ጀርባ ወይም የውጤታማነት ምስጢራቸው የሆነው የአሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ስም ዛሬም እንደ ትላንቱ እንደ ባንዲራ ከፍ ብሎ ሲውለበለብ ይታያል።
👉የስኬታማና የሪከርድ ሠባሪ አቴሌቶችን ስም አንስተን ገመዶ ደደፎ የሚለውን ስም አለማንሳት የሀገር ባለውለታውን ውለታ ከመብላቴም ያስቆጥራል።
እንኳን ደስ አለህ!! አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
#ethiopia | እስቲ ሁላችንም ባርኔጣችንን ከፍ አድርገን እናንሳለት፤ምክንያቱም በየጊዜው የሚሠባበሩት ሪከርዶችና ድሎቹ ለአለም የማራቶን አሠልጣኞች ንጉስ ለሆነው አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ይሄን እንድናደርግ ያስገድዳሉና።
የቅርቡን ለጊዜው እናቆየውና አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ የሚለው ስም ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት ድሎች፣ሜዳልያዎችና ሪከርዶች ጀርባ ከፍ ብሎ ሲሠማና ሲውለበለብ ይታያል
♦️2016 ሪዮ ኦሎምፒክ
🥉በ10ሺ ሜትር
በአትሌት ታምራት ቶላ የነሐስ ሜዳልያ
♦️በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ በማራቶን
🥇በአትሌት ታምራት ቶላ(ወርቅ)
🥈በአትሌት ትዕግስት አሠፋ(ብር)
♦️በ2009 የአለም ሻምፒዮና በርሊን በማራቶን
🥉አትሌት አሠለፈች መርጊያ(ነሐስ)
♦️በ2017 የአለም ሻምፒዮና በርሊን በማራቶን
🥈አትሌት ታምራት ቶላ (ብር)
♦️በ2022 የአለም ሻምፒዮና አሜሪካ ኦሪገን በማራቶን
🥇አትሌት ታምራት ቶላ (ወርቅ)
♦️በ2023 የአለም ሻምፒዮና ሀንጋሪ ቡዳፔስት በማራቶን
🥇አትሌት አማኒ በሪሶ (ወርቅ)
♦️WR አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ በ21ኪ.ሜ አዲስ ሪከርድ
♦️አትሌት ትዕግስት አሠፋ ሶስት ጊዜ የአለም ሪከርድ ባለቤት
♦️በቅርቡ ደግሞ አትሌት ፎቴን ተስፋይ ሁለተኛው የማራቶን ምርጥ ሠዓት ሪከርድ ባለቤት
ከእነዚሁ ሁሉ ስኬቶችና ሪከርዶች ጀርባ በውጤት ያሸበረቀ በወርቅ ቀለም ስሙን በደማቁ ያፃፈ የሀገር ኩራት የሆነ ታላቅ ሠው አለ እሱም አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ።
ዛሬም በለንደን ሠማይ ስር በማራቶን ታሪክ ሲሠራ የእሱ የስልጠና በረከት ያረፈባቸው አትሌት ትዕግስት አሠፋ አንደኛ ከመውጣት በተከታታይ ዓመት የለንደንን ማራቶን ከማሸነፍ በዘለለ በሴቶች ብቻ(Only Womens)ተይዞ የነበረውን የራሷን ሪከርድ አሻሽላለች።
ሌላኛው የአሠልጣኝ ገመዶ የስልጠና ውጤት የሆነው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ በመጀመሪያው የማራቶን ተሳትፎው ሁለተኛ ከመውጣት ባለፈ የሠው ልጅ በዚህ ዘመን ማራቶንን ከ2:00:00 በታች እንደሚገባ በተግባር ካሳየው ዮሚፍ ቀጄልቻ ጀርባም ይሄ የአለማችን የማራቶን አሠልጣኞች ንጉስ ገመዶ ደደፎ አለ።
የአሸናፊነትና የሪከርዶች ባለቤት ከሆኑት አትሌቶች ጀርባ ወይም የውጤታማነት ምስጢራቸው የሆነው የአሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ስም ዛሬም እንደ ትላንቱ እንደ ባንዲራ ከፍ ብሎ ሲውለበለብ ይታያል።
👉የስኬታማና የሪከርድ ሠባሪ አቴሌቶችን ስም አንስተን ገመዶ ደደፎ የሚለውን ስም አለማንሳት የሀገር ባለውለታውን ውለታ ከመብላቴም ያስቆጥራል።
እንኳን ደስ አለህ!! አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
1 month ago
ትዕግስት አሰፋ የለንደን ማራቶንን በታሪካዊ ድል አሸነፈች
የለንደን ጎዳናዎች ዛሬም የኢትዮጵያዊቷን የጥንካሬ አሻራ ተመልክተዋል! በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ የተሰጠውና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የለንደን ማራቶን፣ በአትሌት ትዕግስት አሰፋ ፍጹም የበላይነት ተጠናቅቋል።
ትዕግስት አሰፋ የለንደን ማራቶንን ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመታት በማሸነፍ ታሪክ ሰርታለች።
በከፍተኛ ፉክክርና በታላላቅ አትሌቶች መካከል በተደረገው በዚህ ውድድር፣ ትዕግስት ብቃቷ ምን ያህል አስተማማኝ መሆኑን አሳይታለች።
የትዕግስት ድል የለንደንን አየር በኢትዮጵያዊነት ወኔ እንዲሞላ አድርጎታል።
ትዕግስት አሰፋ ማለት የጽናትና የትጋት ተምሳሌት ነች። ለሁለተኛ ጊዜ የለንደንን አክሊል መድፋት ቀላል ስራ አይደለም። በበርሊን የዓለም ሪከርድን የሰበረችበትን ወኔ ዛሬ ለንደን ላይ ደግማዋለች። እንኳን ደስ አለሽ ትዕግስት! እንኳን ደስ አለን ኢትዮጵያውያን!
የአትሌቲክስ ንግሥቲቷ ለንደንን ዳግም ድል አድርጋለች!
#getu #tigistassefa #londonmarathon2026 #ethiopianathletics #champion #worldathletics #breakingnews #londonmarathon #ትዕግስትአሰፋ #የለንደንማራቶን #ኢትዮጵያ #ሰበርመረጃ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የለንደን ጎዳናዎች ዛሬም የኢትዮጵያዊቷን የጥንካሬ አሻራ ተመልክተዋል! በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ የተሰጠውና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የለንደን ማራቶን፣ በአትሌት ትዕግስት አሰፋ ፍጹም የበላይነት ተጠናቅቋል።
ትዕግስት አሰፋ የለንደን ማራቶንን ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመታት በማሸነፍ ታሪክ ሰርታለች።
በከፍተኛ ፉክክርና በታላላቅ አትሌቶች መካከል በተደረገው በዚህ ውድድር፣ ትዕግስት ብቃቷ ምን ያህል አስተማማኝ መሆኑን አሳይታለች።
የትዕግስት ድል የለንደንን አየር በኢትዮጵያዊነት ወኔ እንዲሞላ አድርጎታል።
ትዕግስት አሰፋ ማለት የጽናትና የትጋት ተምሳሌት ነች። ለሁለተኛ ጊዜ የለንደንን አክሊል መድፋት ቀላል ስራ አይደለም። በበርሊን የዓለም ሪከርድን የሰበረችበትን ወኔ ዛሬ ለንደን ላይ ደግማዋለች። እንኳን ደስ አለሽ ትዕግስት! እንኳን ደስ አለን ኢትዮጵያውያን!
የአትሌቲክስ ንግሥቲቷ ለንደንን ዳግም ድል አድርጋለች!
#getu #tigistassefa #londonmarathon2026 #ethiopianathletics #champion #worldathletics #breakingnews #londonmarathon #ትዕግስትአሰፋ #የለንደንማራቶን #ኢትዮጵያ #ሰበርመረጃ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
የሰው ልጅ በጠፈር ምርምር ታሪክ ውስጥ ሌላ አዲስ ድንቅ ምዕራፍ አስመዝግቧል።
የጨረቃ ተጓዦቹ የአርቴሚስ II (Artemis II) ጠፈርተኞች በፓስፊክ ውቅያኖስ ላይ በሰላም አርፈዋል።
የናሳው ኦራይን መንኩራኩር በአርቴሚስ II ተልዕኮ ጨረቃን ዙረው አስደናቂ ታሪክ የሰሩትን አራት ጠፈርተኞች አሳፍሮ አርብ ምሽት በፓስፊክ ውቅያኖስ ላይ በሰላም አርፏል።
ይህ ታሪካዊ ጉዞ በምስራቅ አቆጣጠር ከምሽቱ 8 ሰዓት ገደማ መንኩራኩሯ ውቅያኖስ ላይ ስታርፍ በታላቅ ስኬት ተጠናቋል።
ጠፈርተኞቹ ከዚህ ቀደም የሰው ልጅ ተጉዞት የማያውቀውን ርቀት ወደ ጥልቅ ህዋ በመጓዝ አዲስ የዓለም ሪከርድ ማስመዝገብ ችለዋል።
የኦራይን መንኩራኩር በሰላም ወደ ምድር መመለስ ናሳ የሰው ልጅን በድጋሚ በጨረቃ ላይ ለማሳረፍ ለሚያደርገው ቀጣይ ጉዞ ትልቅ መተማመንን ፈጥሯል።
መላው ዓለም በጉጉት ሲከታተለው የነበረው ይህ ተልዕኮ የሰው ልጅ ወደፊት ወደ ማርስ ለሚያደርገው ጉዞ እንደ ትልቅ መነሻ ተወስዷል።
አራቱ ጀግና ጠፈርተኞች አሁን ላይ ደህንነታቸው ተጠብቆ ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
የጨረቃ ተጓዦቹ የአርቴሚስ II (Artemis II) ጠፈርተኞች በፓስፊክ ውቅያኖስ ላይ በሰላም አርፈዋል።
የናሳው ኦራይን መንኩራኩር በአርቴሚስ II ተልዕኮ ጨረቃን ዙረው አስደናቂ ታሪክ የሰሩትን አራት ጠፈርተኞች አሳፍሮ አርብ ምሽት በፓስፊክ ውቅያኖስ ላይ በሰላም አርፏል።
ይህ ታሪካዊ ጉዞ በምስራቅ አቆጣጠር ከምሽቱ 8 ሰዓት ገደማ መንኩራኩሯ ውቅያኖስ ላይ ስታርፍ በታላቅ ስኬት ተጠናቋል።
ጠፈርተኞቹ ከዚህ ቀደም የሰው ልጅ ተጉዞት የማያውቀውን ርቀት ወደ ጥልቅ ህዋ በመጓዝ አዲስ የዓለም ሪከርድ ማስመዝገብ ችለዋል።
የኦራይን መንኩራኩር በሰላም ወደ ምድር መመለስ ናሳ የሰው ልጅን በድጋሚ በጨረቃ ላይ ለማሳረፍ ለሚያደርገው ቀጣይ ጉዞ ትልቅ መተማመንን ፈጥሯል።
መላው ዓለም በጉጉት ሲከታተለው የነበረው ይህ ተልዕኮ የሰው ልጅ ወደፊት ወደ ማርስ ለሚያደርገው ጉዞ እንደ ትልቅ መነሻ ተወስዷል።
አራቱ ጀግና ጠፈርተኞች አሁን ላይ ደህንነታቸው ተጠብቆ ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
የጨረቃ ተጓዦች በሰላም ምድር ደረሱ!
#ethiopia | የሰው ልጅ በጠፈር ምርምር ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተው የናሳው **አርቴሚስ II (Artemis II) ተልዕኮ በታላቅ ስኬት ተጠናቋል። አራት ጠፈርተኞችን ያሳፈረችው የኦራይን (Orion) መንኩራኩር፣ ጨረቃን ዙራ ካደረገችው አስደናቂ ቆይታ በኋላ አርብ ምሽት በፓስፊክ ውቅያኖስ ላይ በሰላም አርፋለች።
የዚህን ታሪካዊ ጉዞ ዋና ዋና ኩነቶች እነሆ፦
በምስራቅ አቆጣጠር ከምሽቱ 8 ሰዓት ገደማ መንኩራኩሯ ውቅያኖስ ላይ ስታርፍ፣ የአንድ ዓመት ዝግጅትና የሰባት ቀናት የጠፈር ቆይታ በድል ተደምድሟል።
ተጓዦቹ የሰው ልጅ ከዚህ ቀደም ደርሶበት የማያውቀውን ጥልቅ ህዋ በማሰስ እና ከምድር በጣም ርቆ በመጓዝ አዲስ የዓለም ሪከርድ ማስመዝገብ ችለዋል።
የዚህ ተልዕኮ ስኬት ናሳ የሰው ልጅን በድጋሚ በጨረቃ ላይ ለማሳረፍ ለሚጠብቀው አርቴሚስ III ተልዕኮ ትልቅ መተማመንን የፈጠረ ሲሆን፣ ወደ ማርስ ለሚደረገው ጉዞም እንደ ትልቅ መነሻ ተወስዷል።
በአሁኑ ወቅት አራቱ ጀግና ጠፈርተኞች በጥሩ ጤንነት ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ አስፈላጊው የሕክምና ክትትል ተደርጎላቸው ወደ ቤተሰቦቻቸው በመመለስ ላይ ናቸው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #artemisii #nasa #spaceexploration #orion #moonmission #technews #science #የጠፈር_ምርምር #አርቴሚስ2 #ናሳ
#ethiopia | የሰው ልጅ በጠፈር ምርምር ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተው የናሳው **አርቴሚስ II (Artemis II) ተልዕኮ በታላቅ ስኬት ተጠናቋል። አራት ጠፈርተኞችን ያሳፈረችው የኦራይን (Orion) መንኩራኩር፣ ጨረቃን ዙራ ካደረገችው አስደናቂ ቆይታ በኋላ አርብ ምሽት በፓስፊክ ውቅያኖስ ላይ በሰላም አርፋለች።
የዚህን ታሪካዊ ጉዞ ዋና ዋና ኩነቶች እነሆ፦
በምስራቅ አቆጣጠር ከምሽቱ 8 ሰዓት ገደማ መንኩራኩሯ ውቅያኖስ ላይ ስታርፍ፣ የአንድ ዓመት ዝግጅትና የሰባት ቀናት የጠፈር ቆይታ በድል ተደምድሟል።
ተጓዦቹ የሰው ልጅ ከዚህ ቀደም ደርሶበት የማያውቀውን ጥልቅ ህዋ በማሰስ እና ከምድር በጣም ርቆ በመጓዝ አዲስ የዓለም ሪከርድ ማስመዝገብ ችለዋል።
የዚህ ተልዕኮ ስኬት ናሳ የሰው ልጅን በድጋሚ በጨረቃ ላይ ለማሳረፍ ለሚጠብቀው አርቴሚስ III ተልዕኮ ትልቅ መተማመንን የፈጠረ ሲሆን፣ ወደ ማርስ ለሚደረገው ጉዞም እንደ ትልቅ መነሻ ተወስዷል።
በአሁኑ ወቅት አራቱ ጀግና ጠፈርተኞች በጥሩ ጤንነት ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ አስፈላጊው የሕክምና ክትትል ተደርጎላቸው ወደ ቤተሰቦቻቸው በመመለስ ላይ ናቸው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #artemisii #nasa #spaceexploration #orion #moonmission #technews #science #የጠፈር_ምርምር #አርቴሚስ2 #ናሳ
Sponsored by
Surafel
2 months ago
"ማንችስተር ሲቲን የማንረታበት ምክንያት የለም" ሊያም ሮሴንየር
#ethiopia | የቼልሲው አሰልጣኝ ሊያም ሮሴንየር ቡድናቸው ከማንችስተር ሲቲ ጋር ከሚያደርገው ወሳኝ የሊግ ፍልሚያ በፊት ለተጋጣሚያቸው ያላቸውን አክብሮት ቢገልጹም፣ በድል ላይ ያላቸው እምነት ግን ፍጹም አልተናወጠም።
ሮሴንየር በሰጡት መግለጫ ላይ ያተኮሩባቸው ዋና ዋና ነጥቦች እነሆ፦
"ለፔፕ ትልቅ ክብር አለኝ፤ እሱ የማይታመንና ለሁላችንም መነሳሳት የሆነ አሰልጣኝ ነው" በማለት ለተቃራኒው ጎራ አድናቆታቸውን ችረዋል።
ምንም እንኳን ጨዋታው ከባድ ፈተና እንደሚሆን ቢገነዘቡም፣ ቡድናቸው እሁድ ዕለት በሜዳ ላይ ምን መስራት እንደሚችል ለማሳየት በጉጉት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።
አሰልጣኙ በልበ ሙሉነት "ማንችስተር ሲቲን ማሸነፍ እንችላለን" በማለት ለተጫዋቾቻቸውና ለደጋፊዎቻቸው የድል መልእክት አስተላልፈዋል።
ከዚህ ቀደም ከሲቲ ጋር የነበራቸው ሪከርድ ለአሁኑ ጨዋታ ምንም አይነት ጥቅም እንደሌለውና ትኩረታቸው በአሁኑ 90 ደቂቃ ላይ ብቻ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ሮሴንየር እና ልጆቻቸው የፔፕን ስብስብ በመግጠም ጥንካሬያቸውን ለማሳየት ቆርጠው የተነሱ ይመስላሉ። እሁድ የሚደረገው ጨዋታ የሮሴንየር ታክቲክ በሲቲ ላይ ይሰራ እንደሆነ የሚታይበት ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#tikvahsport #getutemesgen #getu #chelseafc #mancity #liamrosenior #premierleague #footballnews #matchday #ethiopia
#ethiopia | የቼልሲው አሰልጣኝ ሊያም ሮሴንየር ቡድናቸው ከማንችስተር ሲቲ ጋር ከሚያደርገው ወሳኝ የሊግ ፍልሚያ በፊት ለተጋጣሚያቸው ያላቸውን አክብሮት ቢገልጹም፣ በድል ላይ ያላቸው እምነት ግን ፍጹም አልተናወጠም።
ሮሴንየር በሰጡት መግለጫ ላይ ያተኮሩባቸው ዋና ዋና ነጥቦች እነሆ፦
"ለፔፕ ትልቅ ክብር አለኝ፤ እሱ የማይታመንና ለሁላችንም መነሳሳት የሆነ አሰልጣኝ ነው" በማለት ለተቃራኒው ጎራ አድናቆታቸውን ችረዋል።
ምንም እንኳን ጨዋታው ከባድ ፈተና እንደሚሆን ቢገነዘቡም፣ ቡድናቸው እሁድ ዕለት በሜዳ ላይ ምን መስራት እንደሚችል ለማሳየት በጉጉት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።
አሰልጣኙ በልበ ሙሉነት "ማንችስተር ሲቲን ማሸነፍ እንችላለን" በማለት ለተጫዋቾቻቸውና ለደጋፊዎቻቸው የድል መልእክት አስተላልፈዋል።
ከዚህ ቀደም ከሲቲ ጋር የነበራቸው ሪከርድ ለአሁኑ ጨዋታ ምንም አይነት ጥቅም እንደሌለውና ትኩረታቸው በአሁኑ 90 ደቂቃ ላይ ብቻ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ሮሴንየር እና ልጆቻቸው የፔፕን ስብስብ በመግጠም ጥንካሬያቸውን ለማሳየት ቆርጠው የተነሱ ይመስላሉ። እሁድ የሚደረገው ጨዋታ የሮሴንየር ታክቲክ በሲቲ ላይ ይሰራ እንደሆነ የሚታይበት ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#tikvahsport #getutemesgen #getu #chelseafc #mancity #liamrosenior #premierleague #footballnews #matchday #ethiopia
2 months ago
♦️የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ዳግም ውልደት
♦️አትሌቲክሱ ከማንዋል ወደ ዲጂታል መሸጋገሩን ያበሠረው ሻምፒዮና
♦️ልዩ ምስጋና የሚገባቸው ሁሉም የፌዴሬሽኑ ባለሙያዎች እና የአትሌቲክስ ዳኞች
👉1057 አትሌቶች ለሜዳልያ የተናነቁበት 55ኛው
ሻምፒዮና
#ethiopia | 36 ክለቦችና ተቋማት፣ 9 ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች፣621 ወንዶች፣ 436 ሴቶች በድምሩ 1057 አትሌቶች ለሜዳልያ የተናነቁበት 55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተመልካቾችን ቁጭ ብድግ አድርጎ፣አዳዲስ ሪከርዶች ተሠባብረውበት፣ በተለይ በአጭር ርቀት የነገ የርቀቱ ንጉሶች ሊሆኑ ይችላሉ ተብለው የተገመቱ ተስፋዎች በብዛት ታይተውበት፣በዘመናዊ የውጤት መመዝገቢያ መሣሪያ(Time Tronics) ታጅቦና ዘምኖ በልዩ ድምቀት ተጠናቋል።
👉የሻምፒዮናው አጠቃላይ የአሸናፊነትን ዘውድ
የደፋው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
በውድድሩ ለመሸናነፍና ለሜዳልያ ከሚደረገው ትንንቅ ባለፈ ለተተኪ አትሌቶች የውድድር እድል የመፍጠር፣የነገ ብቁና ውጤታማ አትሌቶችን ማፍራት ዋነኛ አላማው አድርጎ በተካሄደው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሻምፒዮናው አጠቃላይ የአሸናፊነትን ዘውድ ደፍቶ፣መቻል እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ እንደየቅደም ተከተላቸው ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ተጠናቋል።
👉 ዳግም የተወለደው ዕድሜ ጠገቡ ሻምፒዮና
ከመክፈቻው እስከ መዝጊያው የነበረው ድባብ፣ሪከርዶች መሠባበራቸው፣በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ54 ዓመታት በኃላ በ Time Tronix መሳሪያ ታግዞና ዘምኖ የተጠናቀቀውን የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ልብ ብሎ ለተመለከተው ዕድሜ ጠገቡ ሻምፒዮና ዳግም ተወልዷል ቢባል ቃሉ ግነት የለውም።
ከምንም በላይ ዘመኑን የዋጀ፣ከማንዋል ወደ ዲጂታል መሸጋገሩን ያበሠረ ታይም ትሮኒክስን በሻምፒዮናው መጠቀሙ ለአትሌቲክሱ ትንሳኤ፣ለአትሌቱ ደግሞ ከፍተኛ ደስታን ከማጎናፀፋቸው ሌላ በሁለቱም ፆታ በቦትስዋና ጋብሮኒ ለሚደረገው የአለም አትሌቲክስ ሪሌሚኒማ ለማሟላት ወደ ሌላ ሀገር የሚደረግ ስደትን፣የገንዘብ ብክነትንና ድካምን ያስወገደ ከመሆኑም በላይ በቀጣይ ፌዴሬሽኑ እያሠበ ላለው የብ/ቡድን ምስረታም አመላካችም ሆኖም ታይቷል።
👉የማይካደው የኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን የላቀ ሚና
ከ54 ዓመታት በኃላ የደመቀ ሻምፒዮና እንዲታይ የበርካቶች ጥረት እንዳለ መካድ ባይቻልም በተለይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ሚና ግን የላቀውን ቦታ ይይዛል።
ፕሬዝዳንቱ ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ሰባቱንም ቀን በአካል በመገኘት፣አስፈላጊውን መመሪያና አቅጣጫ በመስጠት፣በተለይ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶበት ተጥሎ የነበረው ታይም ትሮኒክስ ከወደቀበት ተነስቶ አዋራው ተራግፎ ዳግም እንዲጠገን፣4 ባለሙያዎችን(2 ከቤልጅየም 1ከናይጄሪያ፣1 ዛምቢያ) በማስመጣት ለአገልግሎት እንዲውልና የውድድሩ ድምቀት እንዲሆን በሀገሪቱ የሚገኙ የስፖርት ሳይንስ ሙሁራንና ባለሙያዎችን በማሠባሠብ ብቁ የሠው ኃይል ለማፍራትና በሀገር አቅም ለመጠቀም ከውጪ በመጡ ባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት በቀጣይ ውድድሮች በራሳችን ባለሙያዎች የሚመራበት ዕድል እንዲፈጠር ፕሬዝዳንቱ በቃላት የማይገለፅ ሚና መጫወታቸው ነው የተሠማው፤
ይሄ ብቻም አይደለም አራቱ የታይም ትሮኒክስ ባለሙያዎችም በቆይታቸው ተደስተው እንዲሄዱ፣በመንከባከብ፣የሽኝት እራት ፕሮግራም በማዘጋጀት፣በግላቸው ለውድድር የሚሆን ዶላር በማውጣትና ወጪዎቹን በመሸፈንና፣ከአለም አትሌቲክስ ጋር ፌዴሬሽኑ መልካም ግንኙነት እንዲኖረውም ከፍተኛ ስራ ሠርቷል፤ ስለዚህም ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን
ምስጋና የሚያንሠው ካልሆነ የሚበዛበት አይሆንም።
ውድድሩን በማስተባበር፣ቴክኖሎጂው እንዲተገበር በማድረግ በኩል የውድድሩ ዳይሬክተር አቶ ጊዜ አድነው እንዲሁም የአጭር ርቀት ውድድሮች ብ/ቡድን በመመስረት ጥሩ ስራ ሠርቷል፤የፅ/ቤት ኃላፊው አመንሲሳ ከበደ(ዶ/ር) በቦትስዋና የሚደረገው ውድድር ላይ ሚኒማ ለማሟላት ከዚህ በፊት ናይጄሪያ ድረስ ብዙ ወጪ ይወጣ የነበረውን የሚያስቀር አሠራር በመዘርጋታቸው የውድድሩን ከፍታ በመጨመራቸው እና ተስፋ ሰጪ መንገድ በማሳየታቸው ሁለቱ ምስጋና ይገባቸዋል ።
👉ሊመሠገኑ የሚገባቸው ባለሙያዎች
ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ ላለፉት 7 ቀናት የተካሄደው ሻምፒዮና እጅግ አድካሚና ፈታኝ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ውስጥ ያሉ የውድድር ባለሙያዎች፣አጠቃላይ የፌዴሬሽኑ ሙያተኞችና እና የአትሌቲክስ ዳኞችም ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ በመስራት የውድድሩ ቅመሞች ሆነው በስኬት እንዲጠናቀቅ በማድረጋቸው ሁሉም የምስጋናው ፀበል ሊደርሳቸው ይገባል።
👉 ከ60 በላይ ጋዜጠኞች መታደማቸው ሌላኛው
የውድድሩ ሪከርድ
ቀደም ሲል ለአንድና ሁለት ሚዲያዎችና ጋዜጠኞች ብቻ በሩ ተከፍቶ ለሌሎች በመከርቸሙ ወደ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ደጃፍ ደርሠው የማያውቁትን ስመ-ጥር እና አንጋፋዎቹን ጨምሮ ከ60 በላይ ጋዜጠኞች ሻምፒዮናውን መታደማቸው ሌላኛው የፌዴሬሽኑ ስኬት ሲሆን የኮሚኒኬሽን(የህዝብ ግንኙነት)ከፍተኛ ባለሙያው መሀሪ ነጋሽ ሁሉም ጋዜጠኞች የቤታቸው ያህል እንዲሠማቸው፣አመለካከታቸው እንዲቀየር በማድረግ በኩል አኩሪ ስራ አከናውኗል ።
በተጨማሪም ወጣት መሀሪ ነጋሽ በፌዴሬሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ፈጣን፣ቀልጣፋ ፣ተደራሽና ትኩስ መረጃ በማድረስ ቤተሠባዊነቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የዘየደው ዘዴና የዘረጋው መስመር በመላው አለም ቀጥታ ስርጭት በማስተባበር እና ከውጭ የመጡት እንግዶችን አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ በጎ ተግባር አከናውኗል ።
በተጨማሪም ውድድሩ ካለፋት ዓመታት በጣም በተሻለ የብራንዲንግ ስራ በመስራት ውድድሩ በውጪ አገር የሚካሄድ እስኪ መስል ድረስ ደረጃውን ከፍ በማድረግ የስፖርት ቤተሰቡን አስደምመዋል።
በዶክተር አያሌው የተመራው የህክምና ክፍልም ሳምንቱን ሙሉ ተቀናጅቶ በመስራትና ለተጎዱ አትሌቶች ተሎ በመድረስ ካለፈው ዓመት የተሻለ ስራ ሲሠራ ተስተውሏል።
በመዝጊያው መርሀ ግብር ላይ ሁሉም የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በሚባል ደረጃ ባልተለመደ መልኩ በአካል ተገኝተው መከታተላቸው እና እየተዘዋወሩ አትሌቶችን ማበረታታቸው የሚደነቅ አዲስ ጅምርም ሆኖ ታይቷል።
👉ማጠቃለያ:-ይታሠብበት
👉ሻምፒዮናው የደመቀ ቢሆንም እንከን
አልባ አልነበረም ማለት አይቻልም
በእርግጥ ውድድሩ ያማረና የደመቀ፣በተመልካችና በፉክክር የታጀበ፣በታይም ትሮኒክስ የታገዘ ሆኖ በድምቀት የተጠናቀቀ እንደሆነ ባይካድም እንከን አልባ አልነበረም ማለት ግን አይቻልም፤በዚህ በኩል በተለይ በታይም ትሮኒክስ አጠቃቀምና አተገባበር ዙሪያ ይስተዋሉ የነበሩ ክፍተቶች አትሌቶች ለውድድር ተዘጋጅተው ትራክ ላይ 20 እና 25 ደቂቃ የሚቆሙበት ክፍተት የሚጋነን ባይሆንም የውድድሩ ሠባራ ጎን ነበር፤
ይህ ትንሽ የሚመስል ስህተት በ One day meeting (ኮንትኔንታል ቱር)ላይ ክፍተት እንዳይፈጥር ከወዲሁ ስራ ሊሠራበትና ሊታሠብበት እንደሚገባ እየጠቆምን ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ትራክ ከማዘጋጀት ጀምሮ ሶስት ሚኒስትሮች በመክፈቻው ዕለት በመገኘት ከቀን ጀምሮ እሰከማታ ከፌዴሬሽኑና ከውድድሩ ጎን በመቆም አትሌቶችን ማበረታታቸው ያስመሠግናቸዋል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
ፎቶ ክሬዲት: የኢ.አ.ፌ ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ
♦️አትሌቲክሱ ከማንዋል ወደ ዲጂታል መሸጋገሩን ያበሠረው ሻምፒዮና
♦️ልዩ ምስጋና የሚገባቸው ሁሉም የፌዴሬሽኑ ባለሙያዎች እና የአትሌቲክስ ዳኞች
👉1057 አትሌቶች ለሜዳልያ የተናነቁበት 55ኛው
ሻምፒዮና
#ethiopia | 36 ክለቦችና ተቋማት፣ 9 ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች፣621 ወንዶች፣ 436 ሴቶች በድምሩ 1057 አትሌቶች ለሜዳልያ የተናነቁበት 55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተመልካቾችን ቁጭ ብድግ አድርጎ፣አዳዲስ ሪከርዶች ተሠባብረውበት፣ በተለይ በአጭር ርቀት የነገ የርቀቱ ንጉሶች ሊሆኑ ይችላሉ ተብለው የተገመቱ ተስፋዎች በብዛት ታይተውበት፣በዘመናዊ የውጤት መመዝገቢያ መሣሪያ(Time Tronics) ታጅቦና ዘምኖ በልዩ ድምቀት ተጠናቋል።
👉የሻምፒዮናው አጠቃላይ የአሸናፊነትን ዘውድ
የደፋው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
በውድድሩ ለመሸናነፍና ለሜዳልያ ከሚደረገው ትንንቅ ባለፈ ለተተኪ አትሌቶች የውድድር እድል የመፍጠር፣የነገ ብቁና ውጤታማ አትሌቶችን ማፍራት ዋነኛ አላማው አድርጎ በተካሄደው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሻምፒዮናው አጠቃላይ የአሸናፊነትን ዘውድ ደፍቶ፣መቻል እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ እንደየቅደም ተከተላቸው ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ተጠናቋል።
👉 ዳግም የተወለደው ዕድሜ ጠገቡ ሻምፒዮና
ከመክፈቻው እስከ መዝጊያው የነበረው ድባብ፣ሪከርዶች መሠባበራቸው፣በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ54 ዓመታት በኃላ በ Time Tronix መሳሪያ ታግዞና ዘምኖ የተጠናቀቀውን የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ልብ ብሎ ለተመለከተው ዕድሜ ጠገቡ ሻምፒዮና ዳግም ተወልዷል ቢባል ቃሉ ግነት የለውም።
ከምንም በላይ ዘመኑን የዋጀ፣ከማንዋል ወደ ዲጂታል መሸጋገሩን ያበሠረ ታይም ትሮኒክስን በሻምፒዮናው መጠቀሙ ለአትሌቲክሱ ትንሳኤ፣ለአትሌቱ ደግሞ ከፍተኛ ደስታን ከማጎናፀፋቸው ሌላ በሁለቱም ፆታ በቦትስዋና ጋብሮኒ ለሚደረገው የአለም አትሌቲክስ ሪሌሚኒማ ለማሟላት ወደ ሌላ ሀገር የሚደረግ ስደትን፣የገንዘብ ብክነትንና ድካምን ያስወገደ ከመሆኑም በላይ በቀጣይ ፌዴሬሽኑ እያሠበ ላለው የብ/ቡድን ምስረታም አመላካችም ሆኖም ታይቷል።
👉የማይካደው የኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን የላቀ ሚና
ከ54 ዓመታት በኃላ የደመቀ ሻምፒዮና እንዲታይ የበርካቶች ጥረት እንዳለ መካድ ባይቻልም በተለይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ሚና ግን የላቀውን ቦታ ይይዛል።
ፕሬዝዳንቱ ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ሰባቱንም ቀን በአካል በመገኘት፣አስፈላጊውን መመሪያና አቅጣጫ በመስጠት፣በተለይ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶበት ተጥሎ የነበረው ታይም ትሮኒክስ ከወደቀበት ተነስቶ አዋራው ተራግፎ ዳግም እንዲጠገን፣4 ባለሙያዎችን(2 ከቤልጅየም 1ከናይጄሪያ፣1 ዛምቢያ) በማስመጣት ለአገልግሎት እንዲውልና የውድድሩ ድምቀት እንዲሆን በሀገሪቱ የሚገኙ የስፖርት ሳይንስ ሙሁራንና ባለሙያዎችን በማሠባሠብ ብቁ የሠው ኃይል ለማፍራትና በሀገር አቅም ለመጠቀም ከውጪ በመጡ ባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት በቀጣይ ውድድሮች በራሳችን ባለሙያዎች የሚመራበት ዕድል እንዲፈጠር ፕሬዝዳንቱ በቃላት የማይገለፅ ሚና መጫወታቸው ነው የተሠማው፤
ይሄ ብቻም አይደለም አራቱ የታይም ትሮኒክስ ባለሙያዎችም በቆይታቸው ተደስተው እንዲሄዱ፣በመንከባከብ፣የሽኝት እራት ፕሮግራም በማዘጋጀት፣በግላቸው ለውድድር የሚሆን ዶላር በማውጣትና ወጪዎቹን በመሸፈንና፣ከአለም አትሌቲክስ ጋር ፌዴሬሽኑ መልካም ግንኙነት እንዲኖረውም ከፍተኛ ስራ ሠርቷል፤ ስለዚህም ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን
ምስጋና የሚያንሠው ካልሆነ የሚበዛበት አይሆንም።
ውድድሩን በማስተባበር፣ቴክኖሎጂው እንዲተገበር በማድረግ በኩል የውድድሩ ዳይሬክተር አቶ ጊዜ አድነው እንዲሁም የአጭር ርቀት ውድድሮች ብ/ቡድን በመመስረት ጥሩ ስራ ሠርቷል፤የፅ/ቤት ኃላፊው አመንሲሳ ከበደ(ዶ/ር) በቦትስዋና የሚደረገው ውድድር ላይ ሚኒማ ለማሟላት ከዚህ በፊት ናይጄሪያ ድረስ ብዙ ወጪ ይወጣ የነበረውን የሚያስቀር አሠራር በመዘርጋታቸው የውድድሩን ከፍታ በመጨመራቸው እና ተስፋ ሰጪ መንገድ በማሳየታቸው ሁለቱ ምስጋና ይገባቸዋል ።
👉ሊመሠገኑ የሚገባቸው ባለሙያዎች
ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ ላለፉት 7 ቀናት የተካሄደው ሻምፒዮና እጅግ አድካሚና ፈታኝ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ውስጥ ያሉ የውድድር ባለሙያዎች፣አጠቃላይ የፌዴሬሽኑ ሙያተኞችና እና የአትሌቲክስ ዳኞችም ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ በመስራት የውድድሩ ቅመሞች ሆነው በስኬት እንዲጠናቀቅ በማድረጋቸው ሁሉም የምስጋናው ፀበል ሊደርሳቸው ይገባል።
👉 ከ60 በላይ ጋዜጠኞች መታደማቸው ሌላኛው
የውድድሩ ሪከርድ
ቀደም ሲል ለአንድና ሁለት ሚዲያዎችና ጋዜጠኞች ብቻ በሩ ተከፍቶ ለሌሎች በመከርቸሙ ወደ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ደጃፍ ደርሠው የማያውቁትን ስመ-ጥር እና አንጋፋዎቹን ጨምሮ ከ60 በላይ ጋዜጠኞች ሻምፒዮናውን መታደማቸው ሌላኛው የፌዴሬሽኑ ስኬት ሲሆን የኮሚኒኬሽን(የህዝብ ግንኙነት)ከፍተኛ ባለሙያው መሀሪ ነጋሽ ሁሉም ጋዜጠኞች የቤታቸው ያህል እንዲሠማቸው፣አመለካከታቸው እንዲቀየር በማድረግ በኩል አኩሪ ስራ አከናውኗል ።
በተጨማሪም ወጣት መሀሪ ነጋሽ በፌዴሬሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ፈጣን፣ቀልጣፋ ፣ተደራሽና ትኩስ መረጃ በማድረስ ቤተሠባዊነቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የዘየደው ዘዴና የዘረጋው መስመር በመላው አለም ቀጥታ ስርጭት በማስተባበር እና ከውጭ የመጡት እንግዶችን አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ በጎ ተግባር አከናውኗል ።
በተጨማሪም ውድድሩ ካለፋት ዓመታት በጣም በተሻለ የብራንዲንግ ስራ በመስራት ውድድሩ በውጪ አገር የሚካሄድ እስኪ መስል ድረስ ደረጃውን ከፍ በማድረግ የስፖርት ቤተሰቡን አስደምመዋል።
በዶክተር አያሌው የተመራው የህክምና ክፍልም ሳምንቱን ሙሉ ተቀናጅቶ በመስራትና ለተጎዱ አትሌቶች ተሎ በመድረስ ካለፈው ዓመት የተሻለ ስራ ሲሠራ ተስተውሏል።
በመዝጊያው መርሀ ግብር ላይ ሁሉም የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በሚባል ደረጃ ባልተለመደ መልኩ በአካል ተገኝተው መከታተላቸው እና እየተዘዋወሩ አትሌቶችን ማበረታታቸው የሚደነቅ አዲስ ጅምርም ሆኖ ታይቷል።
👉ማጠቃለያ:-ይታሠብበት
👉ሻምፒዮናው የደመቀ ቢሆንም እንከን
አልባ አልነበረም ማለት አይቻልም
በእርግጥ ውድድሩ ያማረና የደመቀ፣በተመልካችና በፉክክር የታጀበ፣በታይም ትሮኒክስ የታገዘ ሆኖ በድምቀት የተጠናቀቀ እንደሆነ ባይካድም እንከን አልባ አልነበረም ማለት ግን አይቻልም፤በዚህ በኩል በተለይ በታይም ትሮኒክስ አጠቃቀምና አተገባበር ዙሪያ ይስተዋሉ የነበሩ ክፍተቶች አትሌቶች ለውድድር ተዘጋጅተው ትራክ ላይ 20 እና 25 ደቂቃ የሚቆሙበት ክፍተት የሚጋነን ባይሆንም የውድድሩ ሠባራ ጎን ነበር፤
ይህ ትንሽ የሚመስል ስህተት በ One day meeting (ኮንትኔንታል ቱር)ላይ ክፍተት እንዳይፈጥር ከወዲሁ ስራ ሊሠራበትና ሊታሠብበት እንደሚገባ እየጠቆምን ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ትራክ ከማዘጋጀት ጀምሮ ሶስት ሚኒስትሮች በመክፈቻው ዕለት በመገኘት ከቀን ጀምሮ እሰከማታ ከፌዴሬሽኑና ከውድድሩ ጎን በመቆም አትሌቶችን ማበረታታቸው ያስመሠግናቸዋል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
ፎቶ ክሬዲት: የኢ.አ.ፌ ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ
2 months ago
ያንጎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ. በ2025 ላይ የነበሩትን ዋና ዋና የሚባሉ የደንበኞቹን አዝማሚያዎች (ትሬንድ) ይፋ አደረገ!
#ethiopia የዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያው የያንጎ ግሩፕ አካል የሆነው - ያንጎ ኢትዮጵያ፣ እ.አ.አ. ከታኅሣሥ 2024 እስከ ታኅሣሥ 2025 በኢትዮጵያ የኢንተርኔት ዓለም ውስጥ የታዩ ዋና ዋና አዝማሚያዎችን ይፋ ሲያደርግ በታላቅ ደስታ ነው። መረጃው ሲሰበሰብ እና ትንተና ሲደረግበት፣ በዋናነት የዕለታዊ እንቅስቃሴዎች ሁኔታ፣ የአየር መንገድ ፈጣን ክንውኖች፣ ሙያዊ ተግባራት እና አስደሳች የሌሊት ሕይወት እና መሰል ጉዳዮችን ታሳቢ ያደረገ ሲሆን፣ በሀገሪቱ ውስጥ የዲጂታል አገልግሎቶች ተፈላጊነት እና ተጠቃሚነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑም ታይቷል።
በዚህ የከተማ ልማት ላይ በመሪነት የሚገኘው የያንጎ መተግበሪያ፣ ኢትዮጵያውያን የከተማ ሕይወታቸውን እንዴት እንደሚመሩ እና በሁኔታዎች ውስጥ ምን ያህል ተሣታፊ እንደሆኑ ለማሳየት ከፍተኛውን ሚና ተጫውቷል፡፡
● የኢኮኖሚ ደረጃ በትራንስፖርቱ ዘርፍ ቀዳሚ ተመራጭ ሆኗል፡፡እ.አ.አ. በ2025 ዓ.ም. የያንጎ ራይድ ተሳፋሪዎች መካከል የ“ኢኮኖሚ” ታሪፍ በከፍተኛ ደረጃ ተመራጭ መሆኑ ታይቷል። የያንጎ ጉዞ፣ በተመጣጠነ ዋጋ አስተማማኝ የጉዞ አገልግሎት በመስጠቱ፣ በኢትዮጵያ የትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ውስጥ ለዕለታዊ ጉዞ ቀዳሚ ተመራጭ ሆኗል፡፡
● አንድ ግለሰብ በዓመት 1000 የያንጎ ጉዞዎችን በማድረግ ሪከርድ አስመዘገበ፡፡ ወደ 1,000 የሚጠጉ ጉዞዎችን በማድረግ፣ አንድ ተሳፋሪ በኢትዮጵያ አስገራሚ የጉዞ ሪከርድ አስመዝግቧል፡፡ አንዳንድ ግለሰቦች ያንጎን በዕለታዊ ሕይወታቸው ውስጥ በቋሚነት በማስገባት ሕይወታቸውን ቀላል አድርገዋል። ይህ ተሳፋሪ፣ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ ያደረጋቸው 845 የያንጎ ጉዞዎች፣ በቀን ሲሰሉ በአማካይ ወደ 3 ጉዞዎችን እንደሚያደርግ ያሳያል! አስገራሚ ነው!
● ቶዮታ ቪትዝ የያንጎ ጉዞ ኮከብ ሆነ፡፡ ቶዮታ ቪትዝ የአዲስ አበባን መንገዶች በበላይነት የተቆጣጠረ የመኪና ዓይነት ሲሆን በያንጎ ጉዞ ላይም በስፋት አገልግሎት በመስጠት ይታወቃል። ነዳጅ ቆጣቢ በመሆኑ፣ በአስተማማኝነቱ እና ለጥገናም የሚጠይቀው ወጪ ከሌሎች አንጻር ዝቅተኛ በመሆኑ፣ በአገልግሎት ሰጪ አሽከርካሪዎች፣ አጋር ድርጅቶች እና ተሳፋሪዎች ዘንድ ቀዳሚ ምርጫ ለመሆን ችሏል፡፡
● ኢትዮጵያውያን በብዛት ወደየትኞቹ መንገዶች መጓዝ ያዘወትራሉ? አየር መንገድ፣ ሃይማኖታዊ ሥፍራዎች እና ምግብ ቤቶች በፈረንጆቹ 2025 ላይ በብዛት ጉዞ የተደረገባቸው ስፍራዎች ሲሆኑ ተጓዦች በብዛት የሚያዘወትሯቸው ቦታዎች ደግሞ የሚከተሉት ሆነው ተመዝግበዋል፡፡
● አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር መንገድ
● ቦሌ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን
● ሰሚት ፍየል ቤት (ሰሚት-የሰዓሊተ ምሕረት መንገድ - ቦሌ)
● የአየር መንገድ ጉዞዎች: በ2025 የአየር መንገድ ጉዞዎች ጨምረዋል፡፡ በያንጎ መተግበሪያ በኩል ወደአየር መንገድ ብቻ የተደረጉ ከ86,401 በላይ ጉዞዎች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ጉዞዎቹም ከንጋት እስከለሊት ድረስ የተደረጉ ናቸው፡፡ ያንጎም ለተሳፋሪዎቹ፣ ወደ አየር መንገድ የሚያደርሱ እና ከአየር መንገድ የሚነሡ ጉዞዎችን ቀላልና ምቹ አድርጎ አቅርቧል።
“እነዚህ መረጃዎች፣ ያንጎ በኢትዮጵያ ውስጥ በግለሰቦች ዕለታዊ ተሞክሮ ውስጥ የሚጫውተውን ከፍተኛ ሚና አጉልተው ያሳያሉ። ዓላማችን፣ ምቹ እና ተመራጭ አገልግሎትን መስጠት ብቻ ሳይሆን በቀላሉ የሚደረስባቸውና አስተማማኝ የሆኑ አገልግሎቶችን ማቅረብ ነው። አገልግሎቶቻችንን ከአካባቢያዊ ሁኔታዎች ጋር በሚገባ እንዲጣጣሙ ለማድረግ እና በአዲስ አበባና በመላው ኢትዮጵያ ያሉ ተጠቃሚዎችን ፍላጎቶች ለማሟላት እንጥራለን። በተጠቃሚዎች ላይ የተመረኮዙ መፍትሔዎችን በመጠቀም እና ከማህበረሰቡ ጋር ያለንን ተሳትፎ በማጠናከርም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ቀላልና ምቹ እንዲሁም ተደራሽ የሆነ የትራንስፖርት አገልግሎትን መስጠት እንፈልጋለን፡፡ ጎን ለጎንም፣ በዕለታዊ የኑሮ ሁኔታቸው ላይ አዎንታዊ አስተዋፅኦ ለማበርከት እንጥራለን።” ሲሉ በኢትዮጵያ፣ የያንጎ ራይድ ተወካይ የሆኑት ዶ/ር የቀናለም አበበ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተናግረዋል።
ያንጎ በኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ማድረጉን በቁርጠኝነት የሚቀጥል ሲሆን፣ ትኩረቱን - ደህንነትን በማሻሻል፣ የአገልግሎት ጥራትን በማሳደግ እና ለተሳፋሪዎች፣ ለአጋር አሽከርካሪዎች፣ ለአድራሽ (delivery) አጋሮች እና ለአነስተኛና መካከለኛ ተቋማት አጠቃላይ ተሞክሮን በማሻሻል ላይ በማድረግ ሥራውን ይቀጥላል። በዚህም መንገድ፣ ያንጎ በመላው ኢትዮጵያ ከተሞች ውስጥ የቴክኖሎጂና የኢኮኖሚ እድገትን ለማስፋፋት ከፍተኛውን ሚና ይጫወታል፡፡
#ethiopia የዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያው የያንጎ ግሩፕ አካል የሆነው - ያንጎ ኢትዮጵያ፣ እ.አ.አ. ከታኅሣሥ 2024 እስከ ታኅሣሥ 2025 በኢትዮጵያ የኢንተርኔት ዓለም ውስጥ የታዩ ዋና ዋና አዝማሚያዎችን ይፋ ሲያደርግ በታላቅ ደስታ ነው። መረጃው ሲሰበሰብ እና ትንተና ሲደረግበት፣ በዋናነት የዕለታዊ እንቅስቃሴዎች ሁኔታ፣ የአየር መንገድ ፈጣን ክንውኖች፣ ሙያዊ ተግባራት እና አስደሳች የሌሊት ሕይወት እና መሰል ጉዳዮችን ታሳቢ ያደረገ ሲሆን፣ በሀገሪቱ ውስጥ የዲጂታል አገልግሎቶች ተፈላጊነት እና ተጠቃሚነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑም ታይቷል።
በዚህ የከተማ ልማት ላይ በመሪነት የሚገኘው የያንጎ መተግበሪያ፣ ኢትዮጵያውያን የከተማ ሕይወታቸውን እንዴት እንደሚመሩ እና በሁኔታዎች ውስጥ ምን ያህል ተሣታፊ እንደሆኑ ለማሳየት ከፍተኛውን ሚና ተጫውቷል፡፡
● የኢኮኖሚ ደረጃ በትራንስፖርቱ ዘርፍ ቀዳሚ ተመራጭ ሆኗል፡፡እ.አ.አ. በ2025 ዓ.ም. የያንጎ ራይድ ተሳፋሪዎች መካከል የ“ኢኮኖሚ” ታሪፍ በከፍተኛ ደረጃ ተመራጭ መሆኑ ታይቷል። የያንጎ ጉዞ፣ በተመጣጠነ ዋጋ አስተማማኝ የጉዞ አገልግሎት በመስጠቱ፣ በኢትዮጵያ የትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ውስጥ ለዕለታዊ ጉዞ ቀዳሚ ተመራጭ ሆኗል፡፡
● አንድ ግለሰብ በዓመት 1000 የያንጎ ጉዞዎችን በማድረግ ሪከርድ አስመዘገበ፡፡ ወደ 1,000 የሚጠጉ ጉዞዎችን በማድረግ፣ አንድ ተሳፋሪ በኢትዮጵያ አስገራሚ የጉዞ ሪከርድ አስመዝግቧል፡፡ አንዳንድ ግለሰቦች ያንጎን በዕለታዊ ሕይወታቸው ውስጥ በቋሚነት በማስገባት ሕይወታቸውን ቀላል አድርገዋል። ይህ ተሳፋሪ፣ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ ያደረጋቸው 845 የያንጎ ጉዞዎች፣ በቀን ሲሰሉ በአማካይ ወደ 3 ጉዞዎችን እንደሚያደርግ ያሳያል! አስገራሚ ነው!
● ቶዮታ ቪትዝ የያንጎ ጉዞ ኮከብ ሆነ፡፡ ቶዮታ ቪትዝ የአዲስ አበባን መንገዶች በበላይነት የተቆጣጠረ የመኪና ዓይነት ሲሆን በያንጎ ጉዞ ላይም በስፋት አገልግሎት በመስጠት ይታወቃል። ነዳጅ ቆጣቢ በመሆኑ፣ በአስተማማኝነቱ እና ለጥገናም የሚጠይቀው ወጪ ከሌሎች አንጻር ዝቅተኛ በመሆኑ፣ በአገልግሎት ሰጪ አሽከርካሪዎች፣ አጋር ድርጅቶች እና ተሳፋሪዎች ዘንድ ቀዳሚ ምርጫ ለመሆን ችሏል፡፡
● ኢትዮጵያውያን በብዛት ወደየትኞቹ መንገዶች መጓዝ ያዘወትራሉ? አየር መንገድ፣ ሃይማኖታዊ ሥፍራዎች እና ምግብ ቤቶች በፈረንጆቹ 2025 ላይ በብዛት ጉዞ የተደረገባቸው ስፍራዎች ሲሆኑ ተጓዦች በብዛት የሚያዘወትሯቸው ቦታዎች ደግሞ የሚከተሉት ሆነው ተመዝግበዋል፡፡
● አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር መንገድ
● ቦሌ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን
● ሰሚት ፍየል ቤት (ሰሚት-የሰዓሊተ ምሕረት መንገድ - ቦሌ)
● የአየር መንገድ ጉዞዎች: በ2025 የአየር መንገድ ጉዞዎች ጨምረዋል፡፡ በያንጎ መተግበሪያ በኩል ወደአየር መንገድ ብቻ የተደረጉ ከ86,401 በላይ ጉዞዎች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ጉዞዎቹም ከንጋት እስከለሊት ድረስ የተደረጉ ናቸው፡፡ ያንጎም ለተሳፋሪዎቹ፣ ወደ አየር መንገድ የሚያደርሱ እና ከአየር መንገድ የሚነሡ ጉዞዎችን ቀላልና ምቹ አድርጎ አቅርቧል።
“እነዚህ መረጃዎች፣ ያንጎ በኢትዮጵያ ውስጥ በግለሰቦች ዕለታዊ ተሞክሮ ውስጥ የሚጫውተውን ከፍተኛ ሚና አጉልተው ያሳያሉ። ዓላማችን፣ ምቹ እና ተመራጭ አገልግሎትን መስጠት ብቻ ሳይሆን በቀላሉ የሚደረስባቸውና አስተማማኝ የሆኑ አገልግሎቶችን ማቅረብ ነው። አገልግሎቶቻችንን ከአካባቢያዊ ሁኔታዎች ጋር በሚገባ እንዲጣጣሙ ለማድረግ እና በአዲስ አበባና በመላው ኢትዮጵያ ያሉ ተጠቃሚዎችን ፍላጎቶች ለማሟላት እንጥራለን። በተጠቃሚዎች ላይ የተመረኮዙ መፍትሔዎችን በመጠቀም እና ከማህበረሰቡ ጋር ያለንን ተሳትፎ በማጠናከርም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ቀላልና ምቹ እንዲሁም ተደራሽ የሆነ የትራንስፖርት አገልግሎትን መስጠት እንፈልጋለን፡፡ ጎን ለጎንም፣ በዕለታዊ የኑሮ ሁኔታቸው ላይ አዎንታዊ አስተዋፅኦ ለማበርከት እንጥራለን።” ሲሉ በኢትዮጵያ፣ የያንጎ ራይድ ተወካይ የሆኑት ዶ/ር የቀናለም አበበ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተናግረዋል።
ያንጎ በኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ማድረጉን በቁርጠኝነት የሚቀጥል ሲሆን፣ ትኩረቱን - ደህንነትን በማሻሻል፣ የአገልግሎት ጥራትን በማሳደግ እና ለተሳፋሪዎች፣ ለአጋር አሽከርካሪዎች፣ ለአድራሽ (delivery) አጋሮች እና ለአነስተኛና መካከለኛ ተቋማት አጠቃላይ ተሞክሮን በማሻሻል ላይ በማድረግ ሥራውን ይቀጥላል። በዚህም መንገድ፣ ያንጎ በመላው ኢትዮጵያ ከተሞች ውስጥ የቴክኖሎጂና የኢኮኖሚ እድገትን ለማስፋፋት ከፍተኛውን ሚና ይጫወታል፡፡
Sponsored by
Surafel