2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ጋዜጠኛው የቀድሞውን የማን.ዩናይትድ ተከላካይ ፓትሪስ ኤቭራን "አርሰናል ብሩኖ ጊማሬስን በ75 ሚሊዮን ፓውንድ ሲያስፈርመው እያየህ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ከዩሪ ቴሌማንስ ይልቅ እሱን ቢያመጣው ትመርጥ ነበር?" ሲል ጠየቀው።
ኤቭራ ሲመልስም.. "በፍጹም። ሰዎች ትኩረት የሚያደርጉት በተከፈለው የዝውውር ሂሳብ ላይ ብቻ ነው፤ እኔ ግን የምመለከተው ተጫዋቹን ነው። ቴሌማንስ እና ጊማሬስ እኩዮች ናቸው። ዩሪ አስቶንቪላን በሊጉ አራተኛ ደረጃ ይዞ እንዲያጠናቅቅ በጀግንነት ከረዳ በኋላ ነው በ35 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ እኛ የመጣው። የቡድናቸው ኮከብ ተጫዋች ከመሆኑም በላይ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን ማንሳት ችሏል። ይህ ለእኔ እጅግ አስደናቂ የዝውውር ስኬት እንጂ፣ በምንም መለኪያ መጥፎ ስራ አይባልም።
"በእርግጥ ዩሪ ዩናይትድን ሲቀላቀል 'እንኳን ደህና መጣህ' ለማለት ስልክ ደውዬለት ነበር። ለጥቂት ጊዜ አወራን፤ ሆኖም በንግግራችን መሀል የተናገራት አንዲት አረፍተ ነገር አእምሮዬ ውስጥ ታትማ ቀርታለች። 'ፓትሪስ... በመጨረሻም የልጅነት ህልሜ ወደሆነው ክለብ መጣሁ' አለኝ። በመቀጠል ግን ፈጽሞ ያልጠበቅኩትን ነገር አነሳ።
"'ከምንም በላይ ውስጤን በደስታ የሞላው ምን እንደሆነ ታውቃለህ?' ሲል ጠየቀኝ። እኔም 'ታላቁ ኦልድ ትራፎርድ ነው?' አልኩት። እየሳቀ 'አይደለም፣ ማይክል ካሪክ ነው' አለኝ።
ምክንያቱን ስጠይቀው እንዲህ ሲል መለሰልኝ፡
'ከኮቢ ማይኑ ጋር የሰራውን ተአምር ተመልክቻለሁ። ዩናይትድ የውድድር ዓመቱን እንዴት በሚገርም ብቃት እንዳጠናቀቀ አይቻለሁ። አንድ አሰልጣኝ አማካዮችን እንደ ማይክል ካሪክ በጥልቀት የሚረዳ ከሆነ... ከእሱ ጋር መስራት አለመፈለግ እብደት ነው የሚሆነው።'
ይሄኔ ነበር በደስታ ፈገግ ያልኩት። በአሰልጣኙ ላይ ሙሉ እምነት ያለው አማካይ፣ ዝም ብሎ ትልቅ ኮንትራት ከሚፈርም ተጫዋች እጅግ የላቀ ዋጋ አለው።"
ኤቭራ ሲመልስም.. "በፍጹም። ሰዎች ትኩረት የሚያደርጉት በተከፈለው የዝውውር ሂሳብ ላይ ብቻ ነው፤ እኔ ግን የምመለከተው ተጫዋቹን ነው። ቴሌማንስ እና ጊማሬስ እኩዮች ናቸው። ዩሪ አስቶንቪላን በሊጉ አራተኛ ደረጃ ይዞ እንዲያጠናቅቅ በጀግንነት ከረዳ በኋላ ነው በ35 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ እኛ የመጣው። የቡድናቸው ኮከብ ተጫዋች ከመሆኑም በላይ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን ማንሳት ችሏል። ይህ ለእኔ እጅግ አስደናቂ የዝውውር ስኬት እንጂ፣ በምንም መለኪያ መጥፎ ስራ አይባልም።
"በእርግጥ ዩሪ ዩናይትድን ሲቀላቀል 'እንኳን ደህና መጣህ' ለማለት ስልክ ደውዬለት ነበር። ለጥቂት ጊዜ አወራን፤ ሆኖም በንግግራችን መሀል የተናገራት አንዲት አረፍተ ነገር አእምሮዬ ውስጥ ታትማ ቀርታለች። 'ፓትሪስ... በመጨረሻም የልጅነት ህልሜ ወደሆነው ክለብ መጣሁ' አለኝ። በመቀጠል ግን ፈጽሞ ያልጠበቅኩትን ነገር አነሳ።
"'ከምንም በላይ ውስጤን በደስታ የሞላው ምን እንደሆነ ታውቃለህ?' ሲል ጠየቀኝ። እኔም 'ታላቁ ኦልድ ትራፎርድ ነው?' አልኩት። እየሳቀ 'አይደለም፣ ማይክል ካሪክ ነው' አለኝ።
ምክንያቱን ስጠይቀው እንዲህ ሲል መለሰልኝ፡
'ከኮቢ ማይኑ ጋር የሰራውን ተአምር ተመልክቻለሁ። ዩናይትድ የውድድር ዓመቱን እንዴት በሚገርም ብቃት እንዳጠናቀቀ አይቻለሁ። አንድ አሰልጣኝ አማካዮችን እንደ ማይክል ካሪክ በጥልቀት የሚረዳ ከሆነ... ከእሱ ጋር መስራት አለመፈለግ እብደት ነው የሚሆነው።'
ይሄኔ ነበር በደስታ ፈገግ ያልኩት። በአሰልጣኙ ላይ ሙሉ እምነት ያለው አማካይ፣ ዝም ብሎ ትልቅ ኮንትራት ከሚፈርም ተጫዋች እጅግ የላቀ ዋጋ አለው።"
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) አቅራቢ፦ "ካሉት አዳዲስ የማንቸስተር ዩናይትድ ፈራሚዎች አኳያ፤ በቀጣዩ የውድድር ዘመን በብሩኖ ፈርናንዴዝ፣ ዩሪ ቴሌማንስ፣ ኮቢ ማይኖ እና አንድሬ ሳንቶስ መካከል ያለውን የመሃል ሜዳ ፉክክር እና ስብጥር እንዴት ትመለከተዋለህ?"
ሮይ ኪን፦ "አንድ በእርግጠኝነት ልናገር የምችለው ነገር ቢኖር ዩሪ ቴሌማንስ በቀጥታ የመጀመሪያውን ቋሚ አሰላለፍ (Starting XI) እንደሚቀላቀል ነው።
"እሱ ወደ ክለቡ የሚመጣው የካበተ ልምድ ይዞ፣ የተረጋጋ አጨዋወትን ተላብሶ እና የእግርኳስ ጨዋታዎችን እንቅስቃሴ የመቆጣጠር ብቃት አዳብሮ ነው። እነዚህ ሶስት ነገሮች ደግሞ ማንቸስተር ዩናይትድ በመሃል ሜዳው ለረጅም ጊዜ ሲናፍቃቸው የነበሩ ወሳኝ ጥራቶች ናቸው።
"ብሩኖ ፈርናንዴዝም በተመሳሳይ ቋሚ ተሰላፊ መሆኑ አይቀርም።
"ከዚያ በኋላ የሚቀረው አንዱና የመጨረሻው የመሃል ሜዳ ቦታ የጤናማ ፉክክር መድረክ ይሆናል። ተጫዋቹ ኮቢ ማይኖ፣ አንድሬ ሳንቶስ ወይም ሌላም ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን ከቴሌማንስ ጎን ለመሰለፍ ትግል እና ፉክክር የሚያደርጉት እነሱ ናቸው እንጂ ቴሌማንስ አይደለም።
"ይህ ደግሞ ማንቸስተር ዩናይትድ ክፉኛ ተርቦት የነበረው አይነት የቦታ ፉክክር ነው።"
ሮይ ኪን፦ "አንድ በእርግጠኝነት ልናገር የምችለው ነገር ቢኖር ዩሪ ቴሌማንስ በቀጥታ የመጀመሪያውን ቋሚ አሰላለፍ (Starting XI) እንደሚቀላቀል ነው።
"እሱ ወደ ክለቡ የሚመጣው የካበተ ልምድ ይዞ፣ የተረጋጋ አጨዋወትን ተላብሶ እና የእግርኳስ ጨዋታዎችን እንቅስቃሴ የመቆጣጠር ብቃት አዳብሮ ነው። እነዚህ ሶስት ነገሮች ደግሞ ማንቸስተር ዩናይትድ በመሃል ሜዳው ለረጅም ጊዜ ሲናፍቃቸው የነበሩ ወሳኝ ጥራቶች ናቸው።
"ብሩኖ ፈርናንዴዝም በተመሳሳይ ቋሚ ተሰላፊ መሆኑ አይቀርም።
"ከዚያ በኋላ የሚቀረው አንዱና የመጨረሻው የመሃል ሜዳ ቦታ የጤናማ ፉክክር መድረክ ይሆናል። ተጫዋቹ ኮቢ ማይኖ፣ አንድሬ ሳንቶስ ወይም ሌላም ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን ከቴሌማንስ ጎን ለመሰለፍ ትግል እና ፉክክር የሚያደርጉት እነሱ ናቸው እንጂ ቴሌማንስ አይደለም።
"ይህ ደግሞ ማንቸስተር ዩናይትድ ክፉኛ ተርቦት የነበረው አይነት የቦታ ፉክክር ነው።"
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ማርከስ ራሽፎርድ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ ስለመመለሱ የተናገረው ልብ የሚነካ ንግግር "ለማንቸስተር ዩናይትድ የመጨረሻ ጨዋታዬን ተጫውቼ አብቅቼ ይሆን? እያልኩ ራሴን ስጠይቅ ወራትን አሳልፌያለሁ። ይህንን ማሰብ ብቻ... በህይወቴ ከገጠሙኝ ትችቶች ሁሉ በላይ ልቤን ክፉኛ ያደማው ነበር።
"የሌሎች ክለቦችን ማልያ ለብሼ ሜዳ ላይ ወጥቻለሁ፤ ሆኖም አንዳቸውም እንደገዛ ቤቴ ሞቅታ አልሰጡኝም። ወደ ሌላ ክለብ መልበሻ ክፍል እርምጃዬን ባቀናሁ ቁጥር፣ የውስጤ አንዱ አካል አሁንም ድረስ በግድግዳው ላይ የዩናይትድን አርማ ለማየት ይመኝ ነበር።
"ለዚህም ነው የባርሴሎናው ምዕራፍ እንደተጠናቀቀ ለወኪሌ እንዲህ ያልኩት 'ወደ ዩናይትድ መመለስ የማይቻል ከሆነ፣ እዚሁ ውጪ ሀገር እንድቆይ አድርገኝ። ከዩናይትድ ውጪ ሌላ የፕሪሚየር ሊግ ክለብ ስም እንዳታነሳልኝ!'
"ካሪክ መቼም ቢሆን ከህሊናዬ የማይጠፋ አንድ ቃል ነገረኝ። 'ማርከስ... የምትመለሰው ሰዎች ስለ አንተ ያላቸው አመለካከት ስህተት መሆኑን ለማረጋገጥ አይሁን፤ ይልቁንም የምትመለሰው ትክክለኛ ማንነትህ ማን እንደሆነ ለራስህ ለማስታወስ ይሁን' አለኝ።
"ይህ ንግግሩ የልቤን በር ነው ያንኳኳው። በዙሪያዬ ያሉትን ጩኸቶች እና ትችቶች ዝም ለማሰኘት ስታገል፣ በነጻነት ኳስ መጫወት ምን አይነት ስሜት እንዳለው ጭራሹኑ ረስቼው ነበር። ያ ቃል ለእኔ ከበቂ በላይ ነበር። ደግሞም፣ አንዳንድ ታሪኮች ከጀመሩበት ውጪ ሌላ ስፍራ ላይ ሊያልቁ አልተጻፈላቸውም።"
"የሌሎች ክለቦችን ማልያ ለብሼ ሜዳ ላይ ወጥቻለሁ፤ ሆኖም አንዳቸውም እንደገዛ ቤቴ ሞቅታ አልሰጡኝም። ወደ ሌላ ክለብ መልበሻ ክፍል እርምጃዬን ባቀናሁ ቁጥር፣ የውስጤ አንዱ አካል አሁንም ድረስ በግድግዳው ላይ የዩናይትድን አርማ ለማየት ይመኝ ነበር።
"ለዚህም ነው የባርሴሎናው ምዕራፍ እንደተጠናቀቀ ለወኪሌ እንዲህ ያልኩት 'ወደ ዩናይትድ መመለስ የማይቻል ከሆነ፣ እዚሁ ውጪ ሀገር እንድቆይ አድርገኝ። ከዩናይትድ ውጪ ሌላ የፕሪሚየር ሊግ ክለብ ስም እንዳታነሳልኝ!'
"ካሪክ መቼም ቢሆን ከህሊናዬ የማይጠፋ አንድ ቃል ነገረኝ። 'ማርከስ... የምትመለሰው ሰዎች ስለ አንተ ያላቸው አመለካከት ስህተት መሆኑን ለማረጋገጥ አይሁን፤ ይልቁንም የምትመለሰው ትክክለኛ ማንነትህ ማን እንደሆነ ለራስህ ለማስታወስ ይሁን' አለኝ።
"ይህ ንግግሩ የልቤን በር ነው ያንኳኳው። በዙሪያዬ ያሉትን ጩኸቶች እና ትችቶች ዝም ለማሰኘት ስታገል፣ በነጻነት ኳስ መጫወት ምን አይነት ስሜት እንዳለው ጭራሹኑ ረስቼው ነበር። ያ ቃል ለእኔ ከበቂ በላይ ነበር። ደግሞም፣ አንዳንድ ታሪኮች ከጀመሩበት ውጪ ሌላ ስፍራ ላይ ሊያልቁ አልተጻፈላቸውም።"
7 days ago
ማንቸስተር ዩናይትድ፣ አርሰናል እና ቶተንሃም በዝውውር መስኮቱ ትኩረት ስቧል፦ የብሩኖ ጊማራኤስ፣ ሊዊስ ኦል እና ክርስቲያን ሮሜሮ አዳዲስ መረጃዎች
በአውሮፓ የእግር ኳስ የዝውውር መስኮት ታላላቅ ክለቦች ስብስባቸውን ለማጠናከር በሚያደርጉት እንቅስቃሴ በርካታ ትኩረት ሳቢ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ።
በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ አርሰናል የኒውካስል ዩናይትድ አማካኝና አጋዥ ብሩኖ ጊማራኤስን ለማስፈረም የሚያደርገውን ንግግር አፋጥኗል። እንደ ዘ ታይምስ (The Times)፣ ዘ ሳን (The Sun) እና ኢኤስፒኤን (ESPN) ዘገባዎች ከሆነ፤ አርሰናል ተጨማሪ ክፍያዎችን (add-ons) ጨምሮ 80 ሚሊዮን ፓውንድ በሚጠጋ ሂሳብ ዝውውሩን ለማጠናቀቅ ከጫፍ ደርሷል። በተለይም አሰልጣኝ ኤዲ ሃው ከኒውካስል ለመልቀቃቸው ተከትሎ አርሰናል ተጫዋቹን ለማስፈረም ያለው እምነት ከፍ ማለቱ ተጠቁሟል።
በሌላ በኩል ማንቸስተር ዩናይትድ የኒውካስሉን የግራ መስመር ተከላካይ ሊዊስ ኦልን በዝውውር አማራጭነት እየተመለከተው ይገኛል። በተመሳሳይ የዩናይትዱ አጥቂ ማርከስ ራሽፎርድ ወደ ጣሊያኑ ክለብ ሮማ የመዛወር ምንም አይነት ፍላጎት እንደሌለው ታውቋል።
በተጨማሪም ከአሰልጣኝ አንጌ ፖስቴኮግሉ ስብስብ ቶተንሃም ጋር በተያያዘ የስፓኒሹ አትሌቲኮ ማድሪድ የአርጀንቲናውን ማዕከላዊ ተከላካይ ክርስቲያን ሮሜሮን ለማስፈረም ያለውን ፍላጎት ዳግም ያቀጣጠለው ሲሆን፤ የፖርቱጋሉ ፖርቶ ደግሞ የቶተንሃሙን የግራ መስመር ተከላካይ ሶውዛን ለማስፈረም ፍላጎት ማሳየቱ ተገልጿል።
በአውሮፓ የእግር ኳስ የዝውውር መስኮት ታላላቅ ክለቦች ስብስባቸውን ለማጠናከር በሚያደርጉት እንቅስቃሴ በርካታ ትኩረት ሳቢ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ።
በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ አርሰናል የኒውካስል ዩናይትድ አማካኝና አጋዥ ብሩኖ ጊማራኤስን ለማስፈረም የሚያደርገውን ንግግር አፋጥኗል። እንደ ዘ ታይምስ (The Times)፣ ዘ ሳን (The Sun) እና ኢኤስፒኤን (ESPN) ዘገባዎች ከሆነ፤ አርሰናል ተጨማሪ ክፍያዎችን (add-ons) ጨምሮ 80 ሚሊዮን ፓውንድ በሚጠጋ ሂሳብ ዝውውሩን ለማጠናቀቅ ከጫፍ ደርሷል። በተለይም አሰልጣኝ ኤዲ ሃው ከኒውካስል ለመልቀቃቸው ተከትሎ አርሰናል ተጫዋቹን ለማስፈረም ያለው እምነት ከፍ ማለቱ ተጠቁሟል።
በሌላ በኩል ማንቸስተር ዩናይትድ የኒውካስሉን የግራ መስመር ተከላካይ ሊዊስ ኦልን በዝውውር አማራጭነት እየተመለከተው ይገኛል። በተመሳሳይ የዩናይትዱ አጥቂ ማርከስ ራሽፎርድ ወደ ጣሊያኑ ክለብ ሮማ የመዛወር ምንም አይነት ፍላጎት እንደሌለው ታውቋል።
በተጨማሪም ከአሰልጣኝ አንጌ ፖስቴኮግሉ ስብስብ ቶተንሃም ጋር በተያያዘ የስፓኒሹ አትሌቲኮ ማድሪድ የአርጀንቲናውን ማዕከላዊ ተከላካይ ክርስቲያን ሮሜሮን ለማስፈረም ያለውን ፍላጎት ዳግም ያቀጣጠለው ሲሆን፤ የፖርቱጋሉ ፖርቶ ደግሞ የቶተንሃሙን የግራ መስመር ተከላካይ ሶውዛን ለማስፈረም ፍላጎት ማሳየቱ ተገልጿል።
Sponsored by
Surafel
12 days ago
ሮናልዶ እናት ክለቡን ለመቅጣት ተነስቷል
#ethiopia | ክርስቲያኖ ሮናልዶ የማንችስተር ዩናይትዱን ብሩኖ ፈርናንዴዝ የሳውዲ አረቢያውን ክለብ አል ናስርን እንዲቀላቀል የማሳመን ስራ እየሰራ መሆኑ ተነገረ።
ሮናልዶ ቡርኖን ለማሳመን ከፍተኛ እና ተከታታይ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ነው የተዘገበው።
የማንቸስተር ዩናይት የአማካይ ክፍል አንቀሳቃሽ ብሩኖ ፈርናንዴዝ በዝውውር መስኮቱ ከተለያዩ ክለቦች ጥያቄዎች የሚቀርቡለት ቢሆንም ባለፈው የዝውውር መስኮት የወደፊት እጣ ፈንታውን ክለቡ እንዲወስን አድርጎ ነበር።
በወቅቱ በኦልድ ትራፎርድ የመቆየት ፍላጎት የነበረው ቢሆንም ክለቡ እሱን ለመሸጥ ከፈለገ ግን ለመልቀቅ ዝግጁ እንደነበር ይታወሳል።
ነገር ግን ማንቸስተር ዩናይትድ ተጫዋቹን ላለመሸጥ የሰጠውን ውሳኔ ተከትሎ ፈርናንዴዝ በክለቡ የተጣለበትን እምነት በብቃት መልሷል።
በውድድር ዘመኑ 21 ግቦችን አመቻችቶ በማሲያዝ የኢንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የአንድ ውድድር ዘመን ከፍተኛ የጎል አሲስት (Assist) ታሪክን በስሙ ማስመዝገብ ችሏል።
አሁን ላይ ደግሞ ሮናልዶ የቀድሞ የቡድን አጋሩን ወደ ሳውዲ ፕሮ ሊግ ለመውሰድ የሚያደርገው ጥረት በዝውውር መስኮቱ ከሚጠበቁት የዝውውር ወሬዎች አንዱ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #manchesterunited #cristianoronaldo #burunoferenandez
#ethiopia | ክርስቲያኖ ሮናልዶ የማንችስተር ዩናይትዱን ብሩኖ ፈርናንዴዝ የሳውዲ አረቢያውን ክለብ አል ናስርን እንዲቀላቀል የማሳመን ስራ እየሰራ መሆኑ ተነገረ።
ሮናልዶ ቡርኖን ለማሳመን ከፍተኛ እና ተከታታይ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ነው የተዘገበው።
የማንቸስተር ዩናይት የአማካይ ክፍል አንቀሳቃሽ ብሩኖ ፈርናንዴዝ በዝውውር መስኮቱ ከተለያዩ ክለቦች ጥያቄዎች የሚቀርቡለት ቢሆንም ባለፈው የዝውውር መስኮት የወደፊት እጣ ፈንታውን ክለቡ እንዲወስን አድርጎ ነበር።
በወቅቱ በኦልድ ትራፎርድ የመቆየት ፍላጎት የነበረው ቢሆንም ክለቡ እሱን ለመሸጥ ከፈለገ ግን ለመልቀቅ ዝግጁ እንደነበር ይታወሳል።
ነገር ግን ማንቸስተር ዩናይትድ ተጫዋቹን ላለመሸጥ የሰጠውን ውሳኔ ተከትሎ ፈርናንዴዝ በክለቡ የተጣለበትን እምነት በብቃት መልሷል።
በውድድር ዘመኑ 21 ግቦችን አመቻችቶ በማሲያዝ የኢንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የአንድ ውድድር ዘመን ከፍተኛ የጎል አሲስት (Assist) ታሪክን በስሙ ማስመዝገብ ችሏል።
አሁን ላይ ደግሞ ሮናልዶ የቀድሞ የቡድን አጋሩን ወደ ሳውዲ ፕሮ ሊግ ለመውሰድ የሚያደርገው ጥረት በዝውውር መስኮቱ ከሚጠበቁት የዝውውር ወሬዎች አንዱ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #manchesterunited #cristianoronaldo #burunoferenandez
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ማንቸስተር ዩናይትድ ለአዲሱ የውድድር ዘመን ዝግጅት የሚያደርገውን የመጀመሪያ የቅድመ-ውድድር የወዳጅነት ጨዋታውን በፊንላንድ መዲና ሄልሲንኪ ከሬክስሃም ጋር ሊያደርግ መሆኑን በይፋዊ መጽሔቱ ባወጣው ዘገባ አስታውቋል። ይህ ጨዋታ ነገ ቅዳሜ ከቀኑ 10፡00 ላይ የሚጀመር ሲሆን፣ ክለቡ በዚህ በጋ የሚያደርጋቸውን ሁሉንም ጨዋታዎች በክለቡ የቪዲዮ ቻናል አማካኝነት በቀጥታ እንደሚያስተላልፍ ገልጿል።
የማንቸስተር ዩናይትድ የሚዲያ ቡድን ከስፍራው ባጠናቀረው ዘገባ መሠረት፣ በነገው ጨዋታ ዙሪያ ትኩረት የሳቡ ዋና ዋና ነ 3 ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
1ኛ. የአዲሱ ፈራሚ አንድሬ ሳንቶስ የመጀመሪያ ጨዋታ ጉጉት
በዚህ በጋ ከሌላው የፕሪሚየር ሊግ ክለብ ቼልሲ የተዛወረው ብራዚላዊው አማካኝ አንድሬ ሳንቶስ፣ ከክለቡ ጋር ለአንድ ሳምንት ልምምድ ካደረገ በኋላ ከቡድኑ ጋር ወደ ሄልሲንኪ መጓዙ ተረጋግጧል። በመሆኑም ነገ በቀይ ማልያ የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደርጋል ወይ የሚለው የብዙዎች ጉጉት ሆኗል። በሌላ በኩል፣ ሌላኛው አዲስ ፈራሚ ዩሪ ቲሌማንስ ከቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን ጋር በፊፋ የዓለም ዋንጫ ላይ ከነበረው ተሳትፎ በኋላ እረፍት ላይ በመሆኑ እንዲሁም ግብ ጠባቂው ካርል ዳርሎው ካደረገው የሕክምና ክትትል እያገገመ በመሆኑ ከቡድኑ ጋር አልተጓዙም።
2ኛ. የአካዳሚ ወጣቶች እና አንጋፋ ተጫዋቾች ጥምረት
በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ በሚመራው በዚህ ስብስብ ውስጥ እንደ ብራያን ምቤውሞ፣ ሉክ ሾው እና ፓትሪክ ዶርጉ ያሉ የዋናው ቡድን ቁልፍ ተጫዋቾች የተካተቱ ቢሆንም፣ በርካታ የታዳጊ ቡድን (አካዳሚ) ተሰጥኦዎችም ዕድል ለማግኘት አብረው ተጉዘዋል። ባለፈው የውድድር ዘመን በስኮትላንዱ ሴንት ሚሬን በውሰት ያሳለፈው የ19 ዓመቱ አማካኝ ጄኮብ ዴቫኒ፣ እንዲሁም ጄዳን ካማሰን፣ ጂም ትዋይትስ፣ ዳን አርመር እና ኤታን ዊሊያምስ ለአዲሱ የውድድር ዘመን በአሰልጣኙ አእምሮ ውስጥ ቦታ ለማግኘት ነገ ዕድል ሊሰጣቸው እንደሚችል ይጠበቃል። በተጨማሪም ቺዶ ኦቢ፣ ሺ ላሴ እና ሃሪ አማስ በቡድኑ ውስጥ ተጨማሪ የመጫወቻ ጊዜ ለማግኘት የሚፎካከሩ ይሆናል።
3ኛ. የግብ ጠባቂዎች መስመር ፈተና እና አዲስ ዕድል
የክለቡ ግብ ጠባቂዎች የነበሩት ሴኔ ላመንስ እና አልታይ ባይንድር ከዓለም ዋንጫ ተሳትፏቸው በኋላ እረፍት ላይ በመሆናቸው እና አንድሬ ኦናና በውሰት ወደ ትራብዞንስፖር በማንቀሳቀሱ፣ አንጋፋው ቶም ሄተን ቡድኑን በዋና ግብ ጠባቂነት እየመራ ይገኛል። ሄተን ውሉን እስከ 2026/27 የውድድር ዘመን ማጠናቀቂያ ማራዘሙ ይታወቃል። ሆኖም አሰልጣኝ ካሪክ ለወጣቶቹ ደርሞት ሚ እና ራዴክ ቪቴክ ዕድል ሊሰጣቸው ይችላል። በተለይም ቪቴክ ባለፈው የውድድር ዘመን በብሪስቶል ሲቲ በውሰት ቆይታው የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን ጠራርጎ በመውሰድ ያሳየው ድንቅ ብቃት፣ ነገ በማንቸስተር ዩናይትድ ማልያ በሚያሳየው አፈጻጸም ላይ ከፍተኛ ትኩረት እንዲያገኝ አድርጎታል።
የማንቸስተር ዩናይትድ የሚዲያ ቡድን ከስፍራው ባጠናቀረው ዘገባ መሠረት፣ በነገው ጨዋታ ዙሪያ ትኩረት የሳቡ ዋና ዋና ነ 3 ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
1ኛ. የአዲሱ ፈራሚ አንድሬ ሳንቶስ የመጀመሪያ ጨዋታ ጉጉት
በዚህ በጋ ከሌላው የፕሪሚየር ሊግ ክለብ ቼልሲ የተዛወረው ብራዚላዊው አማካኝ አንድሬ ሳንቶስ፣ ከክለቡ ጋር ለአንድ ሳምንት ልምምድ ካደረገ በኋላ ከቡድኑ ጋር ወደ ሄልሲንኪ መጓዙ ተረጋግጧል። በመሆኑም ነገ በቀይ ማልያ የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደርጋል ወይ የሚለው የብዙዎች ጉጉት ሆኗል። በሌላ በኩል፣ ሌላኛው አዲስ ፈራሚ ዩሪ ቲሌማንስ ከቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን ጋር በፊፋ የዓለም ዋንጫ ላይ ከነበረው ተሳትፎ በኋላ እረፍት ላይ በመሆኑ እንዲሁም ግብ ጠባቂው ካርል ዳርሎው ካደረገው የሕክምና ክትትል እያገገመ በመሆኑ ከቡድኑ ጋር አልተጓዙም።
2ኛ. የአካዳሚ ወጣቶች እና አንጋፋ ተጫዋቾች ጥምረት
በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ በሚመራው በዚህ ስብስብ ውስጥ እንደ ብራያን ምቤውሞ፣ ሉክ ሾው እና ፓትሪክ ዶርጉ ያሉ የዋናው ቡድን ቁልፍ ተጫዋቾች የተካተቱ ቢሆንም፣ በርካታ የታዳጊ ቡድን (አካዳሚ) ተሰጥኦዎችም ዕድል ለማግኘት አብረው ተጉዘዋል። ባለፈው የውድድር ዘመን በስኮትላንዱ ሴንት ሚሬን በውሰት ያሳለፈው የ19 ዓመቱ አማካኝ ጄኮብ ዴቫኒ፣ እንዲሁም ጄዳን ካማሰን፣ ጂም ትዋይትስ፣ ዳን አርመር እና ኤታን ዊሊያምስ ለአዲሱ የውድድር ዘመን በአሰልጣኙ አእምሮ ውስጥ ቦታ ለማግኘት ነገ ዕድል ሊሰጣቸው እንደሚችል ይጠበቃል። በተጨማሪም ቺዶ ኦቢ፣ ሺ ላሴ እና ሃሪ አማስ በቡድኑ ውስጥ ተጨማሪ የመጫወቻ ጊዜ ለማግኘት የሚፎካከሩ ይሆናል።
3ኛ. የግብ ጠባቂዎች መስመር ፈተና እና አዲስ ዕድል
የክለቡ ግብ ጠባቂዎች የነበሩት ሴኔ ላመንስ እና አልታይ ባይንድር ከዓለም ዋንጫ ተሳትፏቸው በኋላ እረፍት ላይ በመሆናቸው እና አንድሬ ኦናና በውሰት ወደ ትራብዞንስፖር በማንቀሳቀሱ፣ አንጋፋው ቶም ሄተን ቡድኑን በዋና ግብ ጠባቂነት እየመራ ይገኛል። ሄተን ውሉን እስከ 2026/27 የውድድር ዘመን ማጠናቀቂያ ማራዘሙ ይታወቃል። ሆኖም አሰልጣኝ ካሪክ ለወጣቶቹ ደርሞት ሚ እና ራዴክ ቪቴክ ዕድል ሊሰጣቸው ይችላል። በተለይም ቪቴክ ባለፈው የውድድር ዘመን በብሪስቶል ሲቲ በውሰት ቆይታው የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን ጠራርጎ በመውሰድ ያሳየው ድንቅ ብቃት፣ ነገ በማንቸስተር ዩናይትድ ማልያ በሚያሳየው አፈጻጸም ላይ ከፍተኛ ትኩረት እንዲያገኝ አድርጎታል።
24 days ago
ማንቸስተር ዩናይትድ ዩሪ ቲሌማንስን ከአስቶን ቪላ አስፈረመ
*****************
ማንቸስተር ዩናይትድ ቤልጂየማዊውን አማካይ ዩሪ ቲሌማንስን ከአስቶን ቪላ በ36 ሚሊዮን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ አስፈርሟል።
የ29 ዓመቱ ተጫዋች በኦልድ ትራፎርድ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የኮንትራት ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ ይህም ዝውውር የክለቡን የአማካይ ክፍል ይበልጥ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ቲሌማንስ ዝውውሩን ተከትሎ በሰጠው አስተያየት፣ "እንደ ማንቸስተር ዩናይትድ ያለ ታላቅ እና ልዩ ክለብ መቀላቀሌ የሚሰማኝን ስሜት በቃላት መግለጽ ይከብደኛል፤ ይህ ዝውውር እግር ኳስን መውደድ ከጀመርኩበት ጊዜ አንስቶ ለለፋሁት ልፋት ትልቁ ስኬቴ ነው" ብሏል።
አክሎም፣ የክለቡ አመራሮች እና ተጫዋቾች በቀጣይ ዓመታት ታላላቅ ዋንጫዎችን ለማሸነፍ ያላቸው ጽኑ ፍላጎት እጅግ ግልጽ እንደሆነና እሱም ለዚህ ስኬት የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ መጓጓቱን ተናግሯል።
በዘረንቶስ ሰለሞን
#manutd #tielemans #transfernews #premierleague #footballethiopia
*****************
ማንቸስተር ዩናይትድ ቤልጂየማዊውን አማካይ ዩሪ ቲሌማንስን ከአስቶን ቪላ በ36 ሚሊዮን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ አስፈርሟል።
የ29 ዓመቱ ተጫዋች በኦልድ ትራፎርድ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የኮንትራት ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ ይህም ዝውውር የክለቡን የአማካይ ክፍል ይበልጥ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ቲሌማንስ ዝውውሩን ተከትሎ በሰጠው አስተያየት፣ "እንደ ማንቸስተር ዩናይትድ ያለ ታላቅ እና ልዩ ክለብ መቀላቀሌ የሚሰማኝን ስሜት በቃላት መግለጽ ይከብደኛል፤ ይህ ዝውውር እግር ኳስን መውደድ ከጀመርኩበት ጊዜ አንስቶ ለለፋሁት ልፋት ትልቁ ስኬቴ ነው" ብሏል።
አክሎም፣ የክለቡ አመራሮች እና ተጫዋቾች በቀጣይ ዓመታት ታላላቅ ዋንጫዎችን ለማሸነፍ ያላቸው ጽኑ ፍላጎት እጅግ ግልጽ እንደሆነና እሱም ለዚህ ስኬት የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ መጓጓቱን ተናግሯል።
በዘረንቶስ ሰለሞን
#manutd #tielemans #transfernews #premierleague #footballethiopia
25 days ago
ያልተጠበቀው ዝውውር
#ethiopia | ማንችስተር ዩናይትድ ከብርሀን ፍጥነት ቴሌማንስን አስፈረመ።
ማንችስተር ዩናይትድ 41 ሚሊዮን ዩሮ የውል ማፍረሻ በመክፈል ዩሪ ቴሌማንስን የግሉ አደረገ።
ቤልጄሚያዊው አማካይ ማንቸስተር ዩናይትድን በመቀላቀል ይሁንታውን ሰጥቷል።
ዩናይትድ ለአስቶን ቪላ የ€41 ሚሊዮን የውል ማፍረሻውን በመክፈል የተጫዋቹን የግል ስምምነት አጠናቋል።
ቲሌማንስ ከአንድሬ ሳንቶስ በመቀጠል የክለቡ ሁለተኛው ፈራሚ ሆኗል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #manunited #astinvilla
#ethiopia | ማንችስተር ዩናይትድ ከብርሀን ፍጥነት ቴሌማንስን አስፈረመ።
ማንችስተር ዩናይትድ 41 ሚሊዮን ዩሮ የውል ማፍረሻ በመክፈል ዩሪ ቴሌማንስን የግሉ አደረገ።
ቤልጄሚያዊው አማካይ ማንቸስተር ዩናይትድን በመቀላቀል ይሁንታውን ሰጥቷል።
ዩናይትድ ለአስቶን ቪላ የ€41 ሚሊዮን የውል ማፍረሻውን በመክፈል የተጫዋቹን የግል ስምምነት አጠናቋል።
ቲሌማንስ ከአንድሬ ሳንቶስ በመቀጠል የክለቡ ሁለተኛው ፈራሚ ሆኗል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #manunited #astinvilla
29 days ago
በክሪስቲያኖ ሮናልዶ የስልክ ጥሪ በኦልድትራፎርድ የደመቁት መንትዮች - ራፋኤል እና ፋቢዮ ዳ ሲልቫ
********************************
ቁመናቸው፣ መልካቸው እና የአጨዋወት ዘይቤያቸው እጅግ በመመሳሰሉ ምክንያት፣ ታላቁ አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን እንኳን ለመለየት እንደሚቸገሩ የሚነገርላቸው ራፋኤል እና ፋቢዮ ዳ ሲልቫ፤ በኦልድ ትራፎርድ በነበራቸው ቆይታ የማንቸስተር ዩናይትድ ደጋፊዎችን ልብ የገዙ ተጫዋቾች ናቸው።
ብራዚላውያኑ የሪዮ ዲ ጄኔሮ ተወላጅ መንትዮች ከልጅነታቸው ጀምሮ በአንድ ቡድን፣ በአንድ ክፍልና በአንድ ህልም ያደጉት መንትዮቹ፤ በ15 ዓመታቸው እ.አ.አ በ2005 በሆንግ ኮንግ በተደረገ የወጣቶች ውድድር ላይ በዩናይትድ የስካውቲንግ ቡድን አይን ውስጥ ገቡ።
በወቅቱ አርሰናልን ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች ተጫዋቾቹን ለማስፈረም ከፍተኛ ፉክክር ውስጥ ቢገቡም፣ የውሳኔያቸውን አቅጣጫ የቀየረው ያልተጠበቀ የስልክ ጥሪ ነበር።
በወቅቱ የዩናይትድ ኮከብ የነበረው ክርስቲያኖ ሮናልዶ በቀጥታ ደውሎ፣ "ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ ኑ፤ በፍጹም አትቆጩም!" በማለት አበረታታቸው። ይህ ጥሪ የመንትዮቹን ውሳኔ አስቀይሮ፣ በጥር 2008 በይፋ የ"ቲያትር ኦፍ ድሪምስ" አባል እንዲሆኑ አደረጋቸው።
በወቅቱ የአውሮፓ እግር ኳስን በበላይነት ለሚመራው ማንቸስተር ዩናይትድ አዲስ ጉልበትና ተስፋ ይዘው የመጡት ታዳጊዎች፤ በአሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ዘንድ "የወደፊቶቹ ኮከቦች" የሚል ታላቅ ሙገሳን አገኙ።
ሆኖም በመጀመሪያዎቹ ቀናት ሁለቱን መለየት እጅግ አስቸጋሪ ነበር። ተጫዋቾች፣ የክለቡ ሰራተኞች እና ሰር አሌክስ ራሳቸው ጭምር ብዙ ጊዜ ያሳስቷቸው ነበር።
በአንድ ወቅት በዩናይትድ ፖድካስት ላይ እንደተናገሩት፤ በአንድ ጨዋታ ላይ ራፋኤል ስህተት ይሰራል። በእረፍት ሰዓት ፈርጉሰን በቁጣ ወደ መልበሻ ክፍል በመግባት ፋቢዮን ራፋኤል መስሏቸው አጥብቀው ገሰጹት። ሪዮ ፈርዲናንድ እና ማይክል ካሪክ ግን "ያ ራፋኤል አይደለም፣ ፋቢዮ ነው" ብለው ሲነግሯቸው፤ ፈርጉሰን "ሁለቱም አንድ ናቸው!" ብለው ቁጣቸውን መቀጠላቸው እስከዛሬ በዩናይትድ ደጋፊዎች ዘንድ በፈገግታ ይታወሳል።
አንዳንድ ጊዜ ፋቢዮ ጥፋት አጥፍቶ ራፋኤል ካርድ የተቀበለበት አጋጣሚም ነበር። በልምምድ ሜዳም አሰልጣኞችን ለማደናገር ሆን ብለው ማሊያቸውንና ጫማቸውን እንደሚቀያይሩ ከዓመታት በኋላ በሳቅ ታጅበው የገለጡት የኦልድትራፎርድ ምስጢራቸው ነው።
መንትዮቹ በዩናይትድ ቆይታቸው በርካታ ስኬቶችን አስመዝግበዋል። በተለይም ራፋኤል በቀኝ ተከላካይ መስመር የጋሪ ኔቪልን ቦታ በብቃት መተካት የቻለ ድንቅ ተጫዋች ነው። 170 ጨዋታዎችን አድርጎ 5 ግቦችን አስቆጥሯል፤ 3 የፕሪሚየር ሊግ፣ 1 የሊግ ካፕ እና 1 የክለቦች ዓለም ዋንጫ አንስቷል።
በሌላ በኩል ፋቢዮ በግራ ተከላካይ መስመር ላይ ከፓትሪስ ኤቭራ ጋር ከባድ ፉክክር ነበረበት። ለዩናይትድ 56 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 3 ግቦችን አስቆጥሯል፤ 1 የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫንም አሽንፏል። 2011 ላይ ዩናይትድ በባርሴሎና በተሸነፈበት የሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ላይ በቋሚነት የመጀመር ዕድል አግኝቷል።
የሰር አሌክስ ፈርጉሰን ከማንቸስተር መልቀቅና የሉዊስ ቫን ሀል ወደ አሰልጣኝነት መምጣት ለመንትዮቹ የኦልድትራፎርድ ቆይታ ማብቃት ምክንያት ሆነ።
ቫን ሀል ለብራዚላውያኑ መንትዮች ዕድል የመስጠት ፍላጎት እንዳልነበራቸው ራፋኤል ከዓመታት በኋላ ለሚዲያ በግልጽ ተናግሯል።
በዚህም ምክንያት ራፋኤል በ2015 ወደ ፈረንሳዩ ሊዮን አቀና። በዚያም ለ5 ዓመታት ስኬታማ ቆይታ ካደረገ በኋላ፣ ወደ ቱርኩ ባሻክሼሂር አምርቶ በሻምፒዮንስ ሊግ የቀድሞ ክለቡ ማንቸስተር ዩናይትድን በመግጠም ጭምር አሸንፏል።
ፋቢዮ ደግሞ ከዩናይትድ በኋላ በካርዲፍ ሲቲ፣ ሚድልስብሮ እና በፈረንሳዩ ናንትስ ክለቦች ተጫውቷል።
ትላንት 36ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ያከበሩት መንትዮቹ፤ በአሁኑ ሰዓት በትውልድ ሀገራቸው ብራዚል ይገኛሉ። ራፋኤል ለቦታፎጎ፣ ፋቢዮ ደግሞ በግሬሚዮ በመጫወት ላይ ናቸው።
ዛሬም ቢሆን ማንቸስተር ዩናይትድ ያላቸው ፍቅር አልቀነሰም። በቅርቡ በ"ኢንሳይድ ካሪንግተን" ፖድካስት ላይ ተገኝተው ስለ ዩናይትድ የቆይታ ዘመናቸው፣ ስለ ፈርጉሰን እና ስለ ማይክል ካሪክ በኩራት ተናግረዋል። አሁንም የዩናይትድን ውጤቶች በቅርበት እንደሚከታተሉና ልባቸው ኦልድትራፎርድ እንደሚገኝ ይገልጻሉ።
ራፋኤል እና ፋቢዮ ዳ ሲልቫ በዩናይትድ ታሪክ ውስጥ እንደ ሮናልዶ ወይም ሩኒ በግንባር ቀደምትነት ላይጠቀሱ ይችላሉ፤ ነገር ግን ባሳዩት የማይበገር የብራዚላውያን ስሜት፣ ለክለቡ በሰጡት ታማኝነትና ሜዳ ላይ በሚያሳዩት ውብ ፈገግታ በደጋፊዎች ልብ ውስጥ ምንጊዜም የማይረሳ አሻራ ጥለው ያለፉ ድንቅ መንትዮች ናቸው።
በአዲስ የሺዋስ
#manchesterunited #theatreofdreams #cr7cristianoronaldo #fabiodasilva #rafaeldasilva #twinbrothers #football #sports
********************************
ቁመናቸው፣ መልካቸው እና የአጨዋወት ዘይቤያቸው እጅግ በመመሳሰሉ ምክንያት፣ ታላቁ አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን እንኳን ለመለየት እንደሚቸገሩ የሚነገርላቸው ራፋኤል እና ፋቢዮ ዳ ሲልቫ፤ በኦልድ ትራፎርድ በነበራቸው ቆይታ የማንቸስተር ዩናይትድ ደጋፊዎችን ልብ የገዙ ተጫዋቾች ናቸው።
ብራዚላውያኑ የሪዮ ዲ ጄኔሮ ተወላጅ መንትዮች ከልጅነታቸው ጀምሮ በአንድ ቡድን፣ በአንድ ክፍልና በአንድ ህልም ያደጉት መንትዮቹ፤ በ15 ዓመታቸው እ.አ.አ በ2005 በሆንግ ኮንግ በተደረገ የወጣቶች ውድድር ላይ በዩናይትድ የስካውቲንግ ቡድን አይን ውስጥ ገቡ።
በወቅቱ አርሰናልን ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች ተጫዋቾቹን ለማስፈረም ከፍተኛ ፉክክር ውስጥ ቢገቡም፣ የውሳኔያቸውን አቅጣጫ የቀየረው ያልተጠበቀ የስልክ ጥሪ ነበር።
በወቅቱ የዩናይትድ ኮከብ የነበረው ክርስቲያኖ ሮናልዶ በቀጥታ ደውሎ፣ "ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ ኑ፤ በፍጹም አትቆጩም!" በማለት አበረታታቸው። ይህ ጥሪ የመንትዮቹን ውሳኔ አስቀይሮ፣ በጥር 2008 በይፋ የ"ቲያትር ኦፍ ድሪምስ" አባል እንዲሆኑ አደረጋቸው።
በወቅቱ የአውሮፓ እግር ኳስን በበላይነት ለሚመራው ማንቸስተር ዩናይትድ አዲስ ጉልበትና ተስፋ ይዘው የመጡት ታዳጊዎች፤ በአሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ዘንድ "የወደፊቶቹ ኮከቦች" የሚል ታላቅ ሙገሳን አገኙ።
ሆኖም በመጀመሪያዎቹ ቀናት ሁለቱን መለየት እጅግ አስቸጋሪ ነበር። ተጫዋቾች፣ የክለቡ ሰራተኞች እና ሰር አሌክስ ራሳቸው ጭምር ብዙ ጊዜ ያሳስቷቸው ነበር።
በአንድ ወቅት በዩናይትድ ፖድካስት ላይ እንደተናገሩት፤ በአንድ ጨዋታ ላይ ራፋኤል ስህተት ይሰራል። በእረፍት ሰዓት ፈርጉሰን በቁጣ ወደ መልበሻ ክፍል በመግባት ፋቢዮን ራፋኤል መስሏቸው አጥብቀው ገሰጹት። ሪዮ ፈርዲናንድ እና ማይክል ካሪክ ግን "ያ ራፋኤል አይደለም፣ ፋቢዮ ነው" ብለው ሲነግሯቸው፤ ፈርጉሰን "ሁለቱም አንድ ናቸው!" ብለው ቁጣቸውን መቀጠላቸው እስከዛሬ በዩናይትድ ደጋፊዎች ዘንድ በፈገግታ ይታወሳል።
አንዳንድ ጊዜ ፋቢዮ ጥፋት አጥፍቶ ራፋኤል ካርድ የተቀበለበት አጋጣሚም ነበር። በልምምድ ሜዳም አሰልጣኞችን ለማደናገር ሆን ብለው ማሊያቸውንና ጫማቸውን እንደሚቀያይሩ ከዓመታት በኋላ በሳቅ ታጅበው የገለጡት የኦልድትራፎርድ ምስጢራቸው ነው።
መንትዮቹ በዩናይትድ ቆይታቸው በርካታ ስኬቶችን አስመዝግበዋል። በተለይም ራፋኤል በቀኝ ተከላካይ መስመር የጋሪ ኔቪልን ቦታ በብቃት መተካት የቻለ ድንቅ ተጫዋች ነው። 170 ጨዋታዎችን አድርጎ 5 ግቦችን አስቆጥሯል፤ 3 የፕሪሚየር ሊግ፣ 1 የሊግ ካፕ እና 1 የክለቦች ዓለም ዋንጫ አንስቷል።
በሌላ በኩል ፋቢዮ በግራ ተከላካይ መስመር ላይ ከፓትሪስ ኤቭራ ጋር ከባድ ፉክክር ነበረበት። ለዩናይትድ 56 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 3 ግቦችን አስቆጥሯል፤ 1 የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫንም አሽንፏል። 2011 ላይ ዩናይትድ በባርሴሎና በተሸነፈበት የሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ላይ በቋሚነት የመጀመር ዕድል አግኝቷል።
የሰር አሌክስ ፈርጉሰን ከማንቸስተር መልቀቅና የሉዊስ ቫን ሀል ወደ አሰልጣኝነት መምጣት ለመንትዮቹ የኦልድትራፎርድ ቆይታ ማብቃት ምክንያት ሆነ።
ቫን ሀል ለብራዚላውያኑ መንትዮች ዕድል የመስጠት ፍላጎት እንዳልነበራቸው ራፋኤል ከዓመታት በኋላ ለሚዲያ በግልጽ ተናግሯል።
በዚህም ምክንያት ራፋኤል በ2015 ወደ ፈረንሳዩ ሊዮን አቀና። በዚያም ለ5 ዓመታት ስኬታማ ቆይታ ካደረገ በኋላ፣ ወደ ቱርኩ ባሻክሼሂር አምርቶ በሻምፒዮንስ ሊግ የቀድሞ ክለቡ ማንቸስተር ዩናይትድን በመግጠም ጭምር አሸንፏል።
ፋቢዮ ደግሞ ከዩናይትድ በኋላ በካርዲፍ ሲቲ፣ ሚድልስብሮ እና በፈረንሳዩ ናንትስ ክለቦች ተጫውቷል።
ትላንት 36ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ያከበሩት መንትዮቹ፤ በአሁኑ ሰዓት በትውልድ ሀገራቸው ብራዚል ይገኛሉ። ራፋኤል ለቦታፎጎ፣ ፋቢዮ ደግሞ በግሬሚዮ በመጫወት ላይ ናቸው።
ዛሬም ቢሆን ማንቸስተር ዩናይትድ ያላቸው ፍቅር አልቀነሰም። በቅርቡ በ"ኢንሳይድ ካሪንግተን" ፖድካስት ላይ ተገኝተው ስለ ዩናይትድ የቆይታ ዘመናቸው፣ ስለ ፈርጉሰን እና ስለ ማይክል ካሪክ በኩራት ተናግረዋል። አሁንም የዩናይትድን ውጤቶች በቅርበት እንደሚከታተሉና ልባቸው ኦልድትራፎርድ እንደሚገኝ ይገልጻሉ።
ራፋኤል እና ፋቢዮ ዳ ሲልቫ በዩናይትድ ታሪክ ውስጥ እንደ ሮናልዶ ወይም ሩኒ በግንባር ቀደምትነት ላይጠቀሱ ይችላሉ፤ ነገር ግን ባሳዩት የማይበገር የብራዚላውያን ስሜት፣ ለክለቡ በሰጡት ታማኝነትና ሜዳ ላይ በሚያሳዩት ውብ ፈገግታ በደጋፊዎች ልብ ውስጥ ምንጊዜም የማይረሳ አሻራ ጥለው ያለፉ ድንቅ መንትዮች ናቸው።
በአዲስ የሺዋስ
#manchesterunited #theatreofdreams #cr7cristianoronaldo #fabiodasilva #rafaeldasilva #twinbrothers #football #sports
29 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የቀድሞው የቼልሲ እና አርሰናል ኮከብ ሴስክ ፋብሪጋስ፣ ቼልሲ ወጣቱን ብሩህ አማካይ አንድሬ ሳንቶስን ለቀጥታ ተቀናቃኙ ማንቸስተር ዩናይትድ በ£50 ሚሊዮን ፓውንድ አሳልፎ መሸጡን አስመልክቶ ጠንከር ያለ ስፖርታዊ ትችቱን ሰንዝሯል። ፋብሪጋስ የቼልሲን የዝውውር ፖሊሲ በጽኑ የተቸበትን ሐሳብ እንደሚከተለው አቅርቦታል፦
"ይህ ውሳኔ ፈጽሞ ሊገባኝ አልቻለም። በዓለም እግር ኳስ ውስጥ ካሉ እጅግ ተሰጥኦ ያላቸው ወጣት አማካዮች አንዱን በቀጥታ የፕሪሚየር ሊግ ተቀናቃኛችሁ ለሆነ ክለብ በ£50 ሚሊዮን ፓውንድ አሳልፋችሁ ሰጥታችሁ፣ ትልቅ የንግድ ስራ እንደሰራችሁ ታስባላችሁ። አንድሬ ሳንቶስ ብዙዎች እንደሚጠብቁት ዓይነት ተጫዋች ሆኖ ከወጣ፣ የቼልሲ ደጋፊዎች ይህንን ዝውውር ለዓመታት በማዘን ያስታውሱታል።
"ነገሩን ይበልጥ ግራ የሚያጋባው ደግሞ፣ ቼልሲዎች በቋሚነት ሜዳ ላይ የማይገኙ ተጫዋቾችን ለማቆየት መወሰናቸው ነው። ሮሜዮ ላቪያ የማይታመን አቅም አለው፣ ይህን ማንም አይጠራጠርም፤ ነገር ግን እግር ኳስ የሚጫወተው ሜዳ ላይ እንጂ በህክምና ክፍል ውስጥ አይደለም። ጉዳት የልጁን አቅም እንድናይ እያገደው ባለበት ሁኔታ፣ አማካይ ክፍልህን በተስፋ ላይ ብቻ ልትገነባ አትችልም።
"አንድ ተጫዋች ጤንነቱን ጠብቆ ለመቆየት እየተቸገረ እና በበርካታ የውድድር ዘመናት ጥቂት ጨዋታዎችን ብቻ በሚያደርግበት ሁኔታ፣ ሌላኛው ወጣት አማካይ በየሳምንቱ ጠንካራ አስተዋጽኦ ለማድረግ ዝግጁ ሆኖ ሳለ፣ በውሳኔያችሁ ላይ ከባድ ጥያቄ ሊነሳ ይገባል። በእግር ኳስ ውስጥ 'ሁልጊዜ ዝግጁ ሆኖ መገኘት' ከሁሉ የላቀው ብቃት ነው።
"ማንቸስተር ዩናይትዶች ለሚነሳው ትችት ምንም ደንታ አይኖራቸውም። የእንግሊዝን እግር ኳስ ጥንካሬ በሚገባ የተረዳ እና ከፍተኛ አቅም ያለውን ተጫዋች በማስፈረማቸው በደስታ ፈገግ ይላሉ። አንዳንዴ በዝውውር መስኮት ትልቁ ስኬትህ ውድ ተጫዋች ማስፈረምህ ሳይሆን፣ ተቀናቃኝህ በራሱ ፍቃድ የለቀቀውን ዕንቁ ጠልፎ መውሰድ ነው።
"ቼልሲዎች ለዓመታት ስለ 'የወደፊት ቡድን ግንባታ' ሲያወሩ ኖረዋል፤ አሁን ግን ከምርጥ ወጣት አማካዮቻቸው አንዱን በየዓመቱ ከሚፎካከሩት ክለብ ጋር እንዲቀላቀል ፈቅደዋል። ይህ ነው ፈጽሞ ሊገባኝ ያልቻለው።
"አንድሬ ሳንቶስ ወደ ኦልድ ትራፎርድ አቅንቶ ከፕሪሚየር ሊጉ ምርጥ አማካዮች አንዱ ቢሆን፣ መጥፎ ዕድልን አትውቀሱ፤ ውሳኔያችሁን መለስ ብላችሁ እዩ። አንዳንዴ ክለቦች ድንቅ ተጫዋቾችን የሚያጡት መሸጥ ስላለባቸው ሳይሆን፣ በእጃቸው ያለውን ወርቅ ማወቅ ስለሚሳናቸው ነው።
"ቼልሲዎች ከባድ ቁማር ተጫውተዋል። ማንቸስተር ዩናይትድ ምናልባትም የዚህን አስርት ዓመት ምርጥ ዝውውር በቅናሽ ዋጋ አግኝቶ ይሆናል። ማነው ትክክል የሚለውን ጊዜ ይፈታዋል፤ ነገር ግን ሳንቶስ ብዙዎች እንደሚጠብቁት ብቃቱ ፈንድቶ ከወጣ፣ በስታምፎርድ ብሪጅ የሚነሳው አንድ ጥያቄ ብቻ ይሆናል፤ 'ለምን አሳልፈን ሰጠነው?'"
"ይህ ውሳኔ ፈጽሞ ሊገባኝ አልቻለም። በዓለም እግር ኳስ ውስጥ ካሉ እጅግ ተሰጥኦ ያላቸው ወጣት አማካዮች አንዱን በቀጥታ የፕሪሚየር ሊግ ተቀናቃኛችሁ ለሆነ ክለብ በ£50 ሚሊዮን ፓውንድ አሳልፋችሁ ሰጥታችሁ፣ ትልቅ የንግድ ስራ እንደሰራችሁ ታስባላችሁ። አንድሬ ሳንቶስ ብዙዎች እንደሚጠብቁት ዓይነት ተጫዋች ሆኖ ከወጣ፣ የቼልሲ ደጋፊዎች ይህንን ዝውውር ለዓመታት በማዘን ያስታውሱታል።
"ነገሩን ይበልጥ ግራ የሚያጋባው ደግሞ፣ ቼልሲዎች በቋሚነት ሜዳ ላይ የማይገኙ ተጫዋቾችን ለማቆየት መወሰናቸው ነው። ሮሜዮ ላቪያ የማይታመን አቅም አለው፣ ይህን ማንም አይጠራጠርም፤ ነገር ግን እግር ኳስ የሚጫወተው ሜዳ ላይ እንጂ በህክምና ክፍል ውስጥ አይደለም። ጉዳት የልጁን አቅም እንድናይ እያገደው ባለበት ሁኔታ፣ አማካይ ክፍልህን በተስፋ ላይ ብቻ ልትገነባ አትችልም።
"አንድ ተጫዋች ጤንነቱን ጠብቆ ለመቆየት እየተቸገረ እና በበርካታ የውድድር ዘመናት ጥቂት ጨዋታዎችን ብቻ በሚያደርግበት ሁኔታ፣ ሌላኛው ወጣት አማካይ በየሳምንቱ ጠንካራ አስተዋጽኦ ለማድረግ ዝግጁ ሆኖ ሳለ፣ በውሳኔያችሁ ላይ ከባድ ጥያቄ ሊነሳ ይገባል። በእግር ኳስ ውስጥ 'ሁልጊዜ ዝግጁ ሆኖ መገኘት' ከሁሉ የላቀው ብቃት ነው።
"ማንቸስተር ዩናይትዶች ለሚነሳው ትችት ምንም ደንታ አይኖራቸውም። የእንግሊዝን እግር ኳስ ጥንካሬ በሚገባ የተረዳ እና ከፍተኛ አቅም ያለውን ተጫዋች በማስፈረማቸው በደስታ ፈገግ ይላሉ። አንዳንዴ በዝውውር መስኮት ትልቁ ስኬትህ ውድ ተጫዋች ማስፈረምህ ሳይሆን፣ ተቀናቃኝህ በራሱ ፍቃድ የለቀቀውን ዕንቁ ጠልፎ መውሰድ ነው።
"ቼልሲዎች ለዓመታት ስለ 'የወደፊት ቡድን ግንባታ' ሲያወሩ ኖረዋል፤ አሁን ግን ከምርጥ ወጣት አማካዮቻቸው አንዱን በየዓመቱ ከሚፎካከሩት ክለብ ጋር እንዲቀላቀል ፈቅደዋል። ይህ ነው ፈጽሞ ሊገባኝ ያልቻለው።
"አንድሬ ሳንቶስ ወደ ኦልድ ትራፎርድ አቅንቶ ከፕሪሚየር ሊጉ ምርጥ አማካዮች አንዱ ቢሆን፣ መጥፎ ዕድልን አትውቀሱ፤ ውሳኔያችሁን መለስ ብላችሁ እዩ። አንዳንዴ ክለቦች ድንቅ ተጫዋቾችን የሚያጡት መሸጥ ስላለባቸው ሳይሆን፣ በእጃቸው ያለውን ወርቅ ማወቅ ስለሚሳናቸው ነው።
"ቼልሲዎች ከባድ ቁማር ተጫውተዋል። ማንቸስተር ዩናይትድ ምናልባትም የዚህን አስርት ዓመት ምርጥ ዝውውር በቅናሽ ዋጋ አግኝቶ ይሆናል። ማነው ትክክል የሚለውን ጊዜ ይፈታዋል፤ ነገር ግን ሳንቶስ ብዙዎች እንደሚጠብቁት ብቃቱ ፈንድቶ ከወጣ፣ በስታምፎርድ ብሪጅ የሚነሳው አንድ ጥያቄ ብቻ ይሆናል፤ 'ለምን አሳልፈን ሰጠነው?'"
30 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ማንቸስተር ዩናይትድ ወጣቱን ብራዚላዊ አማካይ አንድሬ ሳንቶስን ለማስፈረም ከቼልሲ ጋር ከስምምነት መድረሱ ተረጋገጠ። ዩናይትድ ለዝውውሩ 48 ሚሊዮን የብሪታንያ ፓውንድ እና በቀላሉ ሊሳኩ የሚችሉ የ2 ሚሊዮን ፓውንድ ተጨማሪ ክፍያዎችን የሚፈጽም ሲሆን፣ ቼልሲ ተጫዋቹ ወደፊት ለሌላ ክለብ ሲሸጥ ከሚያወጣው የዝውውር ሂሳብ የ10 በመቶ ድርሻ እንዲኖረው ስምምነት ላይ ተደርሷል።
የ22 ዓመቱ ወጣት በአማካይ ስፍራ ላይ በተለያዩ ሚናዎች መጫወት የሚችል ሲሆን፣ ከዩናይትድ ጋር በግል ጥቅማጥቅሞች ዙሪያ ተስማምቷል። ቼልሲም ተጫዋቹ ተጉዞ የህክምና ምርመራውን እንዲያጠናቅቅ እና ዝውውሩን እንዲቋጭ ፈቃድ ሰጥቶታል። እስከ 2030 ዓ.ም ድረስ በቼልሲ የሚያቆየው ውል የነበረው ሳንቶስ፣ ቋሚ ተሰላፊ ለመሆን ቢፈልግም፣ ሞይሰስ ካይሴዶ ውሉን እስከ 2033 ማራዘሙን ተከትሎ በቼልሲ ቋሚ የመሰለፍ እድሉ ጠባብ መሆኑን በመረዳቱ መልቀቅን መርጧል።
በጥር 2023 ከብራዚሉ ቫስኮ ዳጋማ ክለብ ቼልሲን የተቀላቀለው ሳንቶስ፣ በ2025-26 የውድድር ዓመት በሁሉም ውድድሮች 43 ጨዋታዎችን አድርጎ ሶስት ግቦችን ሲያስቆጥር አራት ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል። ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን ስድስት ጊዜ የተሰለፈ ቢሆንም፣ በዚህ ክረምት በካርሎ አንቼሎቲ እየተመራ በዓለም ዋንጫው ከተሳተፈው ስብስብ ውጪ ነበር። ከዚህ ቀደም በኖቲንግሃም ፎረስት በውሰት አጭር ጊዜ አሳልፎ፣ በመቀጠልም በፈረንሳዩ ስትራስቡርግ ለአንድ ዓመት ተኩል በቆየበት ጊዜ በ45 ጨዋታዎች 12 ግቦችን አስቆጥሮ አምስት ኳሶችን በማቀበል ድንቅ ብቃት አሳይቷል።
አማካይ ስፍራን ማጠናከር ለማንቸስተር ዩናይትድ የዚህ ክረምት ቀዳሚ የትኩረት አቅጣጫ ሆኖ ቆይቷል። ካሴሚሮ በ2025-26 የውድድር ዓመት መጨረሻ ውሉ ሲጠናቀቅ ከክለቡ መሰናበቱን እና ማኑኤል ኡጋርቴ በዓለም ዋንጫው ኡራጓይ ከስፔን ጋር ባደረገችው ጨዋታ ላይ ባጋጠመው የጉልበት ጉዳት ለረጅም ጊዜ ከሜዳ መራቁ ክለቡን ለአዲስ ግዢ አስገድዶታል። ዩናይትድ ከሳንቶስ በፊት ሌሎች አማካዮችን ለማስፈረም ጥረት ቢያደርግም ሳይሳካ ቀርቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ክለቡ ሌላኛውን አማካይ ኤደርሰንን ከጣሊያኑ አታላንታ ለማስፈረም በ40.5 ሚሊዮን ዩሮ ቋሚ እና 4.5 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ክፍያ ከስምምነት መድረሱም ተዘግቧል።
የአትሌቲክ ስፖርት ትንታኔዎች እንደሚያሳዩት፣ ሳንቶስን ማስፈረም ለዩናይትድ ክፍተቱን የሚሸፍን ተመራጭ ውሳኔ ነው። ተጫዋቹ ኳስን ከተከላካይ ጀርባ በመቀበል ወደ ፊት በማሻገር እና ኳስ በማስጣል ከፍተኛ ብቃት አለው። በቼልሲ በኩልም ቢሆን፣ ተጫዋቹ በአሰልጣኙ ቋሚ ምርጫ ውስጥ ባለመካተቱ፣ ይህ ሽያጭ ለክለቡ ከፍተኛ የገንዘብ ትርፍ በማስገኘት ለሌሎች ዝውውሮች እንደሚያግዝ ተገምቷል። በአማካይ ስፍራ ላይ እንደነ ሞይሰስ ካይሴዶ፣ ኤንዞ ፈርናንዴዝ እና ሮሜዮ ላቪያ ያሉ ተጫዋቾች መኖራቸው ቼልሲ ወጣቱን ተጫዋች አሳልፎ እንዲሰጥ አድርጎታል። ይሁን እንጂ፣ ተስፈኛ የሆነን ወጣት ተጫዋች ለቀጥተኛ ተቀናቃኝ ክለብ አሳልፎ መስጠት በአንዳንድ የቼልሲ ደጋፊዎች ዘንድ ቅሬታን ሊፈጥር እንደሚችል እየተነገረ ይገኛል።
የ22 ዓመቱ ወጣት በአማካይ ስፍራ ላይ በተለያዩ ሚናዎች መጫወት የሚችል ሲሆን፣ ከዩናይትድ ጋር በግል ጥቅማጥቅሞች ዙሪያ ተስማምቷል። ቼልሲም ተጫዋቹ ተጉዞ የህክምና ምርመራውን እንዲያጠናቅቅ እና ዝውውሩን እንዲቋጭ ፈቃድ ሰጥቶታል። እስከ 2030 ዓ.ም ድረስ በቼልሲ የሚያቆየው ውል የነበረው ሳንቶስ፣ ቋሚ ተሰላፊ ለመሆን ቢፈልግም፣ ሞይሰስ ካይሴዶ ውሉን እስከ 2033 ማራዘሙን ተከትሎ በቼልሲ ቋሚ የመሰለፍ እድሉ ጠባብ መሆኑን በመረዳቱ መልቀቅን መርጧል።
በጥር 2023 ከብራዚሉ ቫስኮ ዳጋማ ክለብ ቼልሲን የተቀላቀለው ሳንቶስ፣ በ2025-26 የውድድር ዓመት በሁሉም ውድድሮች 43 ጨዋታዎችን አድርጎ ሶስት ግቦችን ሲያስቆጥር አራት ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል። ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን ስድስት ጊዜ የተሰለፈ ቢሆንም፣ በዚህ ክረምት በካርሎ አንቼሎቲ እየተመራ በዓለም ዋንጫው ከተሳተፈው ስብስብ ውጪ ነበር። ከዚህ ቀደም በኖቲንግሃም ፎረስት በውሰት አጭር ጊዜ አሳልፎ፣ በመቀጠልም በፈረንሳዩ ስትራስቡርግ ለአንድ ዓመት ተኩል በቆየበት ጊዜ በ45 ጨዋታዎች 12 ግቦችን አስቆጥሮ አምስት ኳሶችን በማቀበል ድንቅ ብቃት አሳይቷል።
አማካይ ስፍራን ማጠናከር ለማንቸስተር ዩናይትድ የዚህ ክረምት ቀዳሚ የትኩረት አቅጣጫ ሆኖ ቆይቷል። ካሴሚሮ በ2025-26 የውድድር ዓመት መጨረሻ ውሉ ሲጠናቀቅ ከክለቡ መሰናበቱን እና ማኑኤል ኡጋርቴ በዓለም ዋንጫው ኡራጓይ ከስፔን ጋር ባደረገችው ጨዋታ ላይ ባጋጠመው የጉልበት ጉዳት ለረጅም ጊዜ ከሜዳ መራቁ ክለቡን ለአዲስ ግዢ አስገድዶታል። ዩናይትድ ከሳንቶስ በፊት ሌሎች አማካዮችን ለማስፈረም ጥረት ቢያደርግም ሳይሳካ ቀርቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ክለቡ ሌላኛውን አማካይ ኤደርሰንን ከጣሊያኑ አታላንታ ለማስፈረም በ40.5 ሚሊዮን ዩሮ ቋሚ እና 4.5 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ክፍያ ከስምምነት መድረሱም ተዘግቧል።
የአትሌቲክ ስፖርት ትንታኔዎች እንደሚያሳዩት፣ ሳንቶስን ማስፈረም ለዩናይትድ ክፍተቱን የሚሸፍን ተመራጭ ውሳኔ ነው። ተጫዋቹ ኳስን ከተከላካይ ጀርባ በመቀበል ወደ ፊት በማሻገር እና ኳስ በማስጣል ከፍተኛ ብቃት አለው። በቼልሲ በኩልም ቢሆን፣ ተጫዋቹ በአሰልጣኙ ቋሚ ምርጫ ውስጥ ባለመካተቱ፣ ይህ ሽያጭ ለክለቡ ከፍተኛ የገንዘብ ትርፍ በማስገኘት ለሌሎች ዝውውሮች እንደሚያግዝ ተገምቷል። በአማካይ ስፍራ ላይ እንደነ ሞይሰስ ካይሴዶ፣ ኤንዞ ፈርናንዴዝ እና ሮሜዮ ላቪያ ያሉ ተጫዋቾች መኖራቸው ቼልሲ ወጣቱን ተጫዋች አሳልፎ እንዲሰጥ አድርጎታል። ይሁን እንጂ፣ ተስፈኛ የሆነን ወጣት ተጫዋች ለቀጥተኛ ተቀናቃኝ ክለብ አሳልፎ መስጠት በአንዳንድ የቼልሲ ደጋፊዎች ዘንድ ቅሬታን ሊፈጥር እንደሚችል እየተነገረ ይገኛል።
1 month ago
ማንቸስተር ዩናይትድ ፊቱን ወደ ሌላኛው ብራዚላዊ አዙሯል
#ethiopia | ዩናይትዶች ብራዚላዊው የቼልሲ አማካይ አንድሬ ሳንቶስን ለማስፈረም የመጀመሪያ የዝውውር እንቅስቃሴያቸውን ጀምረዋል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት የመሀል ሜዳ ክፍሉን ለማጠናከር ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ዩናይትድ አሁን የ22 ዓመቱን ብራዚላዊ አማካይ አንድሬ ሳንቶስን በዝውውር ዕቅዱ ውስጥ አካቷል።
እስካሁን ለተጫዋቹ ይፋዊ የገንዘብ ጥያቄ ባይቀርብም የክለቡ ተወካዮች ስለ ተጫዋቹ የዝውውር ሁኔታ መረጃዎችን እየሰበሰቡ ይገኛሉ ተብሏል።
የተጫዋቹ ባለቤት የሆኑት ቼልሲዎች ተጫዋቹን ለሽያጭ አይቀርብም ብለው አለማሳወቃቸው ዩናይትዶች ፍላጎታቸው እንዲጨምር አድርጓል።
ቼልሲዎች የፈለጉትን የገንዘብ መጠን ከቀረበላቸው ተጫዋቹን ለመልቀቅ ዝግጁ መሆናቸው ተገልጿል።
አንዳንድ ምንጮች እንዳሉት ከሆነ ለተጫዋቹ እስከ 50 ሚሊዮን ፓውንድ የሚደርስ ዋጋ ቼልሲዎች እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
አንድሬ ሳንቶስ በቼልሲ በሞይሰስ ካይሰዶ እና በኤንዞ ፈርናንዴዝ ጥላ ስር በመውደቁ በቂ የመጫወቻ ጊዜ ለማግኘት ወደ ሌላ ክለብ መሄድ እንደሚፈልግ ተጠቅሷል።
ቶናሊን ለቶትንሃም አሳልፎ የሰጠው ኒውካስትል ዩናይትድም የተጫዎቹ ፈላጊ መሆኑም ፋብሪዝዮ ሮማኖ አስነብቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #manchesterunitedfc #chelsea #andreysantos #fabrizioromano
#ethiopia | ዩናይትዶች ብራዚላዊው የቼልሲ አማካይ አንድሬ ሳንቶስን ለማስፈረም የመጀመሪያ የዝውውር እንቅስቃሴያቸውን ጀምረዋል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት የመሀል ሜዳ ክፍሉን ለማጠናከር ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ዩናይትድ አሁን የ22 ዓመቱን ብራዚላዊ አማካይ አንድሬ ሳንቶስን በዝውውር ዕቅዱ ውስጥ አካቷል።
እስካሁን ለተጫዋቹ ይፋዊ የገንዘብ ጥያቄ ባይቀርብም የክለቡ ተወካዮች ስለ ተጫዋቹ የዝውውር ሁኔታ መረጃዎችን እየሰበሰቡ ይገኛሉ ተብሏል።
የተጫዋቹ ባለቤት የሆኑት ቼልሲዎች ተጫዋቹን ለሽያጭ አይቀርብም ብለው አለማሳወቃቸው ዩናይትዶች ፍላጎታቸው እንዲጨምር አድርጓል።
ቼልሲዎች የፈለጉትን የገንዘብ መጠን ከቀረበላቸው ተጫዋቹን ለመልቀቅ ዝግጁ መሆናቸው ተገልጿል።
አንዳንድ ምንጮች እንዳሉት ከሆነ ለተጫዋቹ እስከ 50 ሚሊዮን ፓውንድ የሚደርስ ዋጋ ቼልሲዎች እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
አንድሬ ሳንቶስ በቼልሲ በሞይሰስ ካይሰዶ እና በኤንዞ ፈርናንዴዝ ጥላ ስር በመውደቁ በቂ የመጫወቻ ጊዜ ለማግኘት ወደ ሌላ ክለብ መሄድ እንደሚፈልግ ተጠቅሷል።
ቶናሊን ለቶትንሃም አሳልፎ የሰጠው ኒውካስትል ዩናይትድም የተጫዎቹ ፈላጊ መሆኑም ፋብሪዝዮ ሮማኖ አስነብቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #manchesterunitedfc #chelsea #andreysantos #fabrizioromano
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ማይክል ካሪክ - የኦልድ ትራፎርድ የልብ ትርታ፣ በታላላቅ ኮከቦች ጥላ ስር ተደብቆ የኖረ ድንቅ ጥበበኛ
***********************
ስለ እርሱ ሲታሰብ አምስት የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችና የሻምፒዮንስ ሊጉ ድል ትዝ ሊሉን ይችላሉ። ነገር ግን እውነተኛው ማይክል ካሪክ የተገነባው በብዙዎች ዘንድ በማይታወቁ፣ ልብ በሚነኩና አስገራሚ በሆኑ ድብቅ ታሪኮች ውስጥ ነው።
ዛሬ የምናውቀው ካሪክ በኳስ ቁጥጥሩና አርቆ አሳቢነቱ የሚታወቅ የአማካይ ስፍራ ኮከብ ነው። ነገር ግን ወደ ዌስትሃም አካዳሚ በ15 ዓመቱ ሲቀላቀል ሕልሙ ሌላ ነበር፤ ያኔ የፊት መስመር አጥቂ ነበር።
ካሪክ ያደገው እንደ አላን ሺረር እና ፒተር ቤርድስሌይ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን ባፈራው ታዋቂው የዎልሰንድ ቦይስ አካዳሚ ውስጥ ነው። የኒውካስል ዩናይትድ ደጋፊ የነበረ ቢሆንም፣ በ15 ዓመቱ ኒውካስልን ትቶ ወደ ዌስትሃም ዩናይትድ አቀና።
በ15 ዓመቱ ወደ ዌስትሃም አካዳሚ ሲቀላቀል የመስመር አጥቂ ነበር። በአንድ ጨዋታ ላይ ግን የመሃል አማካይ በመጥፋቱ በአጋጣሚ ቦታው ተቀይሮ የክፍለ ዘመኑ ብልህ አማካይ ሊሆን አጋጣሚው ተፈጠረ።
ካሪክ በቦታው መጀመሪያ ባይደሰትም ያለ እንቢታ ተጫወተ። ይህ አጋጣሚ ግን የእግር ኳስን ታሪኩን ቀየረች፤ አጥቂው ካሪክ ቀርቶ፣ የአውሮፓን መድረክ የሚገዛው ብልሁ አማካይ ተወለደ።
የካሪክ የጉርምስና ዕድሜ ደግሞ ሌላ አስገራሚ ፈተናን ይዞ መጣ። 17 ዓመቱ ላይ በአንድ ጊዜ 8 ኢንች ያህል ቁመት ጨመረ። በወቅቱ የነበረው ቀጭን ሰውነቱ ከቁመቱ ጋር ባለመመጣጠኑ ሜዳ ላይ መሮጥ እስኪያቅተው ተቸግሮ እንደነበር የቀድሞ አሰልጣኙ ሃሪ ሬድናፕ ያስታውሳሉ።
ብዙዎች የወደፊት መንገዱን ተስፋ ሲያጡበት፣ እርሱ ግን በትጋትና በጽናት ሰውነቱን ገነባ፤ በመጨረሻም ከሪዮ ፈርዲናንድ እና ፍራንክ ላምፓርድ ጋር የዌስትሃም ወርቃማ ትውልድ አካል ሆነ።
ካሪክ ገና በወጣትነቱ ጨዋታን የማንበብ ብቃቱ ድንቅ ነበር። ከዌስትሃም፣ ስዊንደን፣ በርሚንግሃም እና ቶተንሃም በኋላ በ2006 ታላቁን ማንችስተር ዩናይትድን ሲቀላቀል፣ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በሮይ ኪን መልቀቅ የዛለውን የመሃል ሜዳ የሚያክምላቸውን የፈጠራ ሰው አገኙ።
በእንግሊዝ እግር ኳስ ታሪክ ስቲቨን ጄራርድ እና ፍራንክ ላምፓርድ በችሎታ እንደማይደረስባቸው የመሀል ሜዳ ጣኦታት ይታዩ ነበር። ነገር ግን ታላቁ አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ልብ ውስጥ የነበረው እውነተኛው ንጉሥ ካሪክ ብቻ ነበር።
ፈርጉሰን በግል ማስታወሻቸው ላይ “...ላምፓርድና ጄራርድ ታላላቅ ስብዕና የነበራቸው ተጫዋቾች ናቸው፤ እውነተኛ ምርጥ ተጫዋቾች ግን አልነበሩም ፤ ካሪክ ግን የእግር ኳስ አዕምሮ ነበረው። የእንግሊዝ ሚዲያዎች ስለ እነርሱ አብዝተው በማወደስ ሲጮሁ፣ ካሪክ ግን በትህትናውና በአይናፋርነቱ ምክንያት በነርሱ ጥላ ስር ተደብቆ ተበደለ።” ሲሉ ነበር እንጋፋው አሰልጣኝ በብዕራችው ከትበው ስለካሪክ የመሰከሩት።
ማይክል ካሪክ ዛሬም ቢሆን ያው ነው - ዝምተኛ፣ አስተዋይና ልባም። የዩናይትድን ታላቅ ስም ለመታደግ በዋና አሰልጣኝነት ተሰይሟል። ትናንት በዝምታ ሜዳውን እንደገዛው ሁሉ፣ ዛሬም በዚያው ጥንቁቅ አዕምሮው የታላቁን ክለብ ታሪክ ለመጻፍ እየተዘጋጀ ነው።
ካሪክ እ.አ.አ በ2006 ከቶተንሃም ማንቸስተር ዩናይትድን ከተቀላቀለ በኋላ በ12 ወርቃማ ዓመታት 5 የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን፣ የሻምፒዮንስ ሊግን እና የኤፍኤ ካፕን ጨምሮ በርካታ የክብር አክሊሎችን ደፍቷል።
ሆኖም ግን እንደ ፖል ስኮልስ ፣ ጄራርድ እና ላምፓርድ ባሉ ደማቅ ስሞች ጥላ ስር ተደብቆ አሳልፏል። ነገር ግን ሳይታይ የሚደምቅ የቡድኑ የጀርባ አጥንት ነበር።
በኦልድ ትራፎርድ የነበረው ስፍራ ከብዙ ተጫዋቾች የተለየ ነበር። ግቦችን ብዙ አያስቆጥርም፣ አስደናቂ ትርዒቶችንም አያሳይም፤ ነገር ግን ጨዋታው በእርሱ እግር ይጀምር፣ በእርሱም አዕምሮ ይመራ ነበር።
ከተጫዋችነት በኋላ በሞሪንሆ እና ሶልሻየር ስር በረዳትነት የሰራው ካሪክ በ2021 ለአጭር ጊዜ ዩናይትድን በጊዜያዊነት መርቶ ጥሩ ውጤት አሳይቷል።
በመቀጠል ሚድልስብሮን በዋና አሰልጣኝነት ይዞ አስደናቂ ጊዜ ካሳለፈ በኋላ፣ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በሩበን አሞሪም ስር የተንኮታኮተውን ማንችስተር ዩናይትድን ለመታደግ በጊዜያዊ አሰልጣኝነት ኦልትራፎርድ ሲደርስ ብዙዎች እምነት አልጣሉበትም ነበር።
ነገር ግን ዝምተኛው ካሪክ ፤ ትናንት በዝምታ ሜዳውን እንደገዛው ሁሉ፣ ታላቁን ክለብ ከመውረድ ውርደት ታድጎ ለሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ አበቃው።
ማይክል ካሪክ በተጫዋችነት ዘመኑ በማንቸስተር ዩናይትድ የቡድን አጋሮቹ "ሃቮክ" በሚል ቅጽል ስም ይጠሩት ነበር። ይህ ስም የመጣው በወቅቱ ተጫዋቾቹ በፒኤስፒ (PSP) ላይ "SOCOM US Navy SEALs: Fireteam Bravo" የተሰኘውን ታክቲካዊና ስውር የጦርነት ጨዋታ(ኮምፒዩተር ጌም) በጋራ ሲጫወቱ ከነበራቸው ትውስታ ነው።
ዌይን ሩኒ እንደተናገረው ይህ ጨዋታና የካሪክ መሪነት ቡድኑን አንድ ላይ ለማሰባሰብ ትልቅ ሚና ነበረው። ካሪክ በጨዋታው ላይ ብቻ ሳይሆን በሜዳው ላይም ያንን ስውር እና ጥንቁቅ ታክቲክ የሚተገብር መሪ ነበር።
ካሪክ ብዙ ጊዜ በሚያወሩ ኮከቦች መካከል በዝምታ የበራ ኮከብ ነበር። የጨዋታውን ስልተ-ምት በአንድ ንክኪ የሚቀይር፣ የቡድኑን ልብ በጸጥታ የሚያስመታ ረቂቅ የሙዚቃ መሪ።
እሱን የሚለየው ያሸነፋቸው ዋንጫዎች ብቻ አይደሉም፤ ያለ ጩኸት ታሪክ መፍጠር የቻለ ሰው መሆኑ ነው። አንዳንድ ኮከቦች በብርሃን ይደምቃሉ፤ ካሪክ ግን በዝምታው ታላቅ ሆነ።
ለዚህም ነው ዛሬም በኦልድ ትራፎርድ ታሪክ ውስጥ ከማይረሱ ስሞች አንዱ ሆኖ የሚጠራው፤ እየመጡ ያሉትን ብሩህ የአሰልጣኝነት ዘመናቱንም ያስናፈቀው።
በአዲስ የሺዋስ
Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት #football
***********************
ስለ እርሱ ሲታሰብ አምስት የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችና የሻምፒዮንስ ሊጉ ድል ትዝ ሊሉን ይችላሉ። ነገር ግን እውነተኛው ማይክል ካሪክ የተገነባው በብዙዎች ዘንድ በማይታወቁ፣ ልብ በሚነኩና አስገራሚ በሆኑ ድብቅ ታሪኮች ውስጥ ነው።
ዛሬ የምናውቀው ካሪክ በኳስ ቁጥጥሩና አርቆ አሳቢነቱ የሚታወቅ የአማካይ ስፍራ ኮከብ ነው። ነገር ግን ወደ ዌስትሃም አካዳሚ በ15 ዓመቱ ሲቀላቀል ሕልሙ ሌላ ነበር፤ ያኔ የፊት መስመር አጥቂ ነበር።
ካሪክ ያደገው እንደ አላን ሺረር እና ፒተር ቤርድስሌይ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን ባፈራው ታዋቂው የዎልሰንድ ቦይስ አካዳሚ ውስጥ ነው። የኒውካስል ዩናይትድ ደጋፊ የነበረ ቢሆንም፣ በ15 ዓመቱ ኒውካስልን ትቶ ወደ ዌስትሃም ዩናይትድ አቀና።
በ15 ዓመቱ ወደ ዌስትሃም አካዳሚ ሲቀላቀል የመስመር አጥቂ ነበር። በአንድ ጨዋታ ላይ ግን የመሃል አማካይ በመጥፋቱ በአጋጣሚ ቦታው ተቀይሮ የክፍለ ዘመኑ ብልህ አማካይ ሊሆን አጋጣሚው ተፈጠረ።
ካሪክ በቦታው መጀመሪያ ባይደሰትም ያለ እንቢታ ተጫወተ። ይህ አጋጣሚ ግን የእግር ኳስን ታሪኩን ቀየረች፤ አጥቂው ካሪክ ቀርቶ፣ የአውሮፓን መድረክ የሚገዛው ብልሁ አማካይ ተወለደ።
የካሪክ የጉርምስና ዕድሜ ደግሞ ሌላ አስገራሚ ፈተናን ይዞ መጣ። 17 ዓመቱ ላይ በአንድ ጊዜ 8 ኢንች ያህል ቁመት ጨመረ። በወቅቱ የነበረው ቀጭን ሰውነቱ ከቁመቱ ጋር ባለመመጣጠኑ ሜዳ ላይ መሮጥ እስኪያቅተው ተቸግሮ እንደነበር የቀድሞ አሰልጣኙ ሃሪ ሬድናፕ ያስታውሳሉ።
ብዙዎች የወደፊት መንገዱን ተስፋ ሲያጡበት፣ እርሱ ግን በትጋትና በጽናት ሰውነቱን ገነባ፤ በመጨረሻም ከሪዮ ፈርዲናንድ እና ፍራንክ ላምፓርድ ጋር የዌስትሃም ወርቃማ ትውልድ አካል ሆነ።
ካሪክ ገና በወጣትነቱ ጨዋታን የማንበብ ብቃቱ ድንቅ ነበር። ከዌስትሃም፣ ስዊንደን፣ በርሚንግሃም እና ቶተንሃም በኋላ በ2006 ታላቁን ማንችስተር ዩናይትድን ሲቀላቀል፣ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በሮይ ኪን መልቀቅ የዛለውን የመሃል ሜዳ የሚያክምላቸውን የፈጠራ ሰው አገኙ።
በእንግሊዝ እግር ኳስ ታሪክ ስቲቨን ጄራርድ እና ፍራንክ ላምፓርድ በችሎታ እንደማይደረስባቸው የመሀል ሜዳ ጣኦታት ይታዩ ነበር። ነገር ግን ታላቁ አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ልብ ውስጥ የነበረው እውነተኛው ንጉሥ ካሪክ ብቻ ነበር።
ፈርጉሰን በግል ማስታወሻቸው ላይ “...ላምፓርድና ጄራርድ ታላላቅ ስብዕና የነበራቸው ተጫዋቾች ናቸው፤ እውነተኛ ምርጥ ተጫዋቾች ግን አልነበሩም ፤ ካሪክ ግን የእግር ኳስ አዕምሮ ነበረው። የእንግሊዝ ሚዲያዎች ስለ እነርሱ አብዝተው በማወደስ ሲጮሁ፣ ካሪክ ግን በትህትናውና በአይናፋርነቱ ምክንያት በነርሱ ጥላ ስር ተደብቆ ተበደለ።” ሲሉ ነበር እንጋፋው አሰልጣኝ በብዕራችው ከትበው ስለካሪክ የመሰከሩት።
ማይክል ካሪክ ዛሬም ቢሆን ያው ነው - ዝምተኛ፣ አስተዋይና ልባም። የዩናይትድን ታላቅ ስም ለመታደግ በዋና አሰልጣኝነት ተሰይሟል። ትናንት በዝምታ ሜዳውን እንደገዛው ሁሉ፣ ዛሬም በዚያው ጥንቁቅ አዕምሮው የታላቁን ክለብ ታሪክ ለመጻፍ እየተዘጋጀ ነው።
ካሪክ እ.አ.አ በ2006 ከቶተንሃም ማንቸስተር ዩናይትድን ከተቀላቀለ በኋላ በ12 ወርቃማ ዓመታት 5 የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን፣ የሻምፒዮንስ ሊግን እና የኤፍኤ ካፕን ጨምሮ በርካታ የክብር አክሊሎችን ደፍቷል።
ሆኖም ግን እንደ ፖል ስኮልስ ፣ ጄራርድ እና ላምፓርድ ባሉ ደማቅ ስሞች ጥላ ስር ተደብቆ አሳልፏል። ነገር ግን ሳይታይ የሚደምቅ የቡድኑ የጀርባ አጥንት ነበር።
በኦልድ ትራፎርድ የነበረው ስፍራ ከብዙ ተጫዋቾች የተለየ ነበር። ግቦችን ብዙ አያስቆጥርም፣ አስደናቂ ትርዒቶችንም አያሳይም፤ ነገር ግን ጨዋታው በእርሱ እግር ይጀምር፣ በእርሱም አዕምሮ ይመራ ነበር።
ከተጫዋችነት በኋላ በሞሪንሆ እና ሶልሻየር ስር በረዳትነት የሰራው ካሪክ በ2021 ለአጭር ጊዜ ዩናይትድን በጊዜያዊነት መርቶ ጥሩ ውጤት አሳይቷል።
በመቀጠል ሚድልስብሮን በዋና አሰልጣኝነት ይዞ አስደናቂ ጊዜ ካሳለፈ በኋላ፣ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በሩበን አሞሪም ስር የተንኮታኮተውን ማንችስተር ዩናይትድን ለመታደግ በጊዜያዊ አሰልጣኝነት ኦልትራፎርድ ሲደርስ ብዙዎች እምነት አልጣሉበትም ነበር።
ነገር ግን ዝምተኛው ካሪክ ፤ ትናንት በዝምታ ሜዳውን እንደገዛው ሁሉ፣ ታላቁን ክለብ ከመውረድ ውርደት ታድጎ ለሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ አበቃው።
ማይክል ካሪክ በተጫዋችነት ዘመኑ በማንቸስተር ዩናይትድ የቡድን አጋሮቹ "ሃቮክ" በሚል ቅጽል ስም ይጠሩት ነበር። ይህ ስም የመጣው በወቅቱ ተጫዋቾቹ በፒኤስፒ (PSP) ላይ "SOCOM US Navy SEALs: Fireteam Bravo" የተሰኘውን ታክቲካዊና ስውር የጦርነት ጨዋታ(ኮምፒዩተር ጌም) በጋራ ሲጫወቱ ከነበራቸው ትውስታ ነው።
ዌይን ሩኒ እንደተናገረው ይህ ጨዋታና የካሪክ መሪነት ቡድኑን አንድ ላይ ለማሰባሰብ ትልቅ ሚና ነበረው። ካሪክ በጨዋታው ላይ ብቻ ሳይሆን በሜዳው ላይም ያንን ስውር እና ጥንቁቅ ታክቲክ የሚተገብር መሪ ነበር።
ካሪክ ብዙ ጊዜ በሚያወሩ ኮከቦች መካከል በዝምታ የበራ ኮከብ ነበር። የጨዋታውን ስልተ-ምት በአንድ ንክኪ የሚቀይር፣ የቡድኑን ልብ በጸጥታ የሚያስመታ ረቂቅ የሙዚቃ መሪ።
እሱን የሚለየው ያሸነፋቸው ዋንጫዎች ብቻ አይደሉም፤ ያለ ጩኸት ታሪክ መፍጠር የቻለ ሰው መሆኑ ነው። አንዳንድ ኮከቦች በብርሃን ይደምቃሉ፤ ካሪክ ግን በዝምታው ታላቅ ሆነ።
ለዚህም ነው ዛሬም በኦልድ ትራፎርድ ታሪክ ውስጥ ከማይረሱ ስሞች አንዱ ሆኖ የሚጠራው፤ እየመጡ ያሉትን ብሩህ የአሰልጣኝነት ዘመናቱንም ያስናፈቀው።
በአዲስ የሺዋስ
Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት #football
1 month ago
የልጅነት እንባ እና የድል መንገድ - ሮናልዶ ከትላንት እስከ ዛሬ
**********************
የ2004 አውሮፓ ዋንጫ ብዙ ትዝታዎች አሉት። የኦቶ ሪሃግሎቹ ግሪኮች ፖርቹጋሎችን በጥብቅ መከላከል በገዛ ሜዳቸው የአውሮፓ ዋንጫውን መንጠቃቸው ብቻ ሳይሆን፤ ሊመጣ ብቅ እያለ ያለው አዲስ ኮከብ ትኩስ እንባ በሊዝበኑ ስታዲዮ ዳሉዝ ሲፈስ ትዝታው ዛሬም ርቆ ያልራቀ ቅርብ ነው።
ያን የዘመናዊ እግር ኳስ ህልው ትዝታ አስታከን ወደ ዛሬ እንዘልቃለን። ብዙ ውብ ትላንቶችን፣ ደማቅ ቀኖችን እና ውብ ምሽቶችን አልፎ እውን ወደሆነው ዛሬ እንመጣለን። ትዝታ ቢርቅም አያረጀምና፣ በዘመን መፈራረቅም አይደበዝዝምና ብትውስታ ጎዳና እንመላለሳለን።
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ዶስ ሳንቶስ አቪየሮ የሚባል ስም፣ በአባቱ መሻት የሮናልድ ሬገንን መጠሪያ እንዲጋራ የሆነ፣ በልጅነቱ አይጋፈጡትን ፈተና የተጋፈጠ፣ የሊዝበን ሰዎች በአፍላነቱ ሳይጠግቡ የተለዩት፣ የላንክ ሻየር ሰዎች ደግሞ ውብ ማለዳውን የተጋሩት፣ ውለታን የማይረሳው ዛሬም በስኬት ደጃፎች እየተመላለሰ ያለ ህያው ኮከብ ነው።
በሰር አሌክስ ፈርጉሰን እና በማንቸስተር ዩናይትድ መልማዮች ዓይን ውስጥ ከገባባት ከዚያች የወዳጅነት ጨዋታ ዕለት አንስቶ ዘመናዊ እግር ኳስ ሌላ መልክ ነው የያዘው። ማንቸስተር ዩናይትድ ከዚህ ኮከብ ጋር በበርካታ ዋንጫዎች የተገመደ ብዙ የድል ቀናትን አልፏል።
ወደ ሎስ ብላንኮዎቹ ቅፅር ዘልቆም በነጩ መለያ ለሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥም በአውሮፓ መድረክም የሚደረገውን ሁሉ አድርጓል። ቱሪንም እጇን ዘርግታ ነው የተቀበለችው። እዚያም ስኬት ከእርሱ ጋር ነበረች።
በድኅረ ኮቪድ 19 የመጀመሪያ ወቅቶች ወደ ኦልድትራፎርድ ሲመለስ የቀዮቹ ደጋፊዎች ትዝታቸውን እንደሸከፉ ነበርና “እንኳን መጣህልን” ነበር ያሉት።
ሆኖም የማቸስተር ዩናይትድ ዳግም ምልሰቱ እንደ ትላንት ስል፣ እንደ ዕድሜውም በውጤት ብስል አልሆነም። ከኤሪክ ቴንሀግ ጋር የጋባበት መቃቃር ደግሞ ወደ መውጫው በር እንዲያማትር ዋነኛ ምክኒያት ሆነ።
ወደ መካከለኛው ምስራቅ ዘለቀ፤ በእግር ኳስ ብዙ መዋዕለ ንዋይ አፍስሳ ግዙፍ ለውጥ ወደ ሻተችው ሳዑዲ አረቢያ አቀና። ከሳምንታት በፊትም ለሦስት ዓመታት የተጠበቀውን የሳዑዲ ፕሮ ሊግ ሻምፒዮንነት ከክለቡ ዐል-ናስር ጋር አነሳ።
ሆኖም ጥያቄ ነበር። እነዚህን ሁሉ ቁጥራቸው የበረከቱ ስኬቶች ወደ ብሔራዊ ቡድን የሚተረጉማቸውስ መቼ ነው? የሚል።
በእርግጥ የ2016ቱን አውሮፓ ዋንጫ ሲያነሳ ይህ ጥያቄ በከፊል የተመለሰ መስሎ ነበር። የአውሮፓ ሀገራት ዋንጫ/ ኔሽንስ ሊግንም አንስቷል።
ግን ግዙፉ የዓለም ዋንጫስ? እግር ኳስ በታሪኩ ካስመለከታቸው ኮከቦች ለምሉዕነት አንድ መስፈርቱ ይኸው መድረክ ነውና፤ የእርሱስ ቀን አይመጣም ወይ? ተብሎ ተጠብቋል። እስካሁን ያ ቀን አልመጣም።
በእርግጥ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ በተቆጠሩ ግቦች ከሊዮኔል ሜሲ እና ከኢራናዊው ዓሊ ዳይ በእጅጉ ርቋል። በዚህ በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ደግሞ በመድረኩ ከተሳተፉ አንጋፋ ተጫዋቾች አንዱ ሆኖ ወደ አሜሪካ ምድር ሲዘልቅ ብዙ ጥበቃዎች ነበሩ። እነዛ ጥበቃዎች ግን በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ያለግብ ሲለያዩ ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገቡ ያደረገ ሆነ። በርከት ያሉ ትችቶች እርሱም ሆነ የቡድን አጋሮቹ ላይ መሰንዘራቸው አልቀረም።
ቀን ጠብቆ በአሉታ ለተቹትም፣ በበጎ ለጠበቁትም ምላሽ ሰጥቷል። ኡዝቤኪስታንን 5 ለ 0 በረቱበት ጨዋታ ከመረብ ያሳረፋቸው እነዚያ ሁለት ግቦች ትችቶቹን አቅጣጫ ማስቀየሪያ ብቻ አልሆኑም። አዳዲስ ክብረ ወሰኖችንም አስከትለዋል።
ሮናልዶ ከካሜሩናዊው ሮጀር ሚላ በመቀጠል በመድረኩ ግብ ያስቆጠረ አንጋፋ ተጫዋች ተሰኝቷል፤ ከ2006 የጀርመን ዓለም ዋንጫ እስከ 23ኛው የአሜሪካ ምድር ዓለም ዋንጫ በተሳተፈባቸው 6 ውድድሮች በሁሉም ግብ በማስቆጠር ደግሞ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል።
በጨዋታ ዘመኑ ያስቆጠራቸው ግቦችም 975 ደርሰዋል። በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ደግሞ 145ኛ ግቡን በማስቆጠር ከተከታዩ ሊዮኔል ሜሲ ጋር ያለውን ልዩነት ወደ 23 አስፍቷል።
በጨለማ ከመሰለው አስቸጋሪ ሳምንት በኋላ፣ ትችት ከበረከተባቸው ሰሞናት በኋላ “ተመልሰናል” ብሏል ሮናልዶ። በግል የሚመዘገቡ ክብረ ወሰኖች መልካም ቢሆኑም፤ ቀዳሚ ግቡ ግን ቡድኑን መርዳትና ለአሸናፊነት ማብቃት መሆኑን ነው የገለፀው።
ያ መንገድ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ዛሬም ቀጥሏል። እንደ ትላንቱ ባይሰላም ለተባለው ሁሉ ተግባራዊ ምላሽ እየሰጠ አለ። የትችት ወጀብ ሳይገታው፣ የዕድሜ መግፋትም ሳይረታው እንደ ጥንቱ ስል ባይሆንም አለሁ እያለ ነው።
ዋይኒ ሩኒ የተናገው ይህን በሚገባ ይገልፃል።ሮናልዶ ትችትን ማስተናገድ፣ ለትችቱም አስፈላጊውን ተግባራዊ ምለሽ መስጠት በእግር ኳስ ዘመኑ ሁሉ የተጓዘበት እውነት ነው።
“ትዝታ አያረጅም” ሲባል በጎም ይሁን መጥፎ በአዕምሮ ጓዳ ደጋግሞ ስለሚመላለስ ነው። ሮናልዶ ግን ያለፈ ትዝታ፤ ያላለፈ ዛሬ ነው።
እነዚያ በፅናት የተጓዘባቸው ውጤታማ ዓመታት፣ ያንን የሊዝበን ሰታዲየም እንባ ይገልፃሉ። ያ የእልህ እና የቁጭት እንባ፤ ከዓመታት በኋላ ዛሬም ትኩስ ነው፣ አልቀዘቀዘም!
በእድሪስ አህመድ
Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት #sports #ronaldo #football
**********************
የ2004 አውሮፓ ዋንጫ ብዙ ትዝታዎች አሉት። የኦቶ ሪሃግሎቹ ግሪኮች ፖርቹጋሎችን በጥብቅ መከላከል በገዛ ሜዳቸው የአውሮፓ ዋንጫውን መንጠቃቸው ብቻ ሳይሆን፤ ሊመጣ ብቅ እያለ ያለው አዲስ ኮከብ ትኩስ እንባ በሊዝበኑ ስታዲዮ ዳሉዝ ሲፈስ ትዝታው ዛሬም ርቆ ያልራቀ ቅርብ ነው።
ያን የዘመናዊ እግር ኳስ ህልው ትዝታ አስታከን ወደ ዛሬ እንዘልቃለን። ብዙ ውብ ትላንቶችን፣ ደማቅ ቀኖችን እና ውብ ምሽቶችን አልፎ እውን ወደሆነው ዛሬ እንመጣለን። ትዝታ ቢርቅም አያረጀምና፣ በዘመን መፈራረቅም አይደበዝዝምና ብትውስታ ጎዳና እንመላለሳለን።
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ዶስ ሳንቶስ አቪየሮ የሚባል ስም፣ በአባቱ መሻት የሮናልድ ሬገንን መጠሪያ እንዲጋራ የሆነ፣ በልጅነቱ አይጋፈጡትን ፈተና የተጋፈጠ፣ የሊዝበን ሰዎች በአፍላነቱ ሳይጠግቡ የተለዩት፣ የላንክ ሻየር ሰዎች ደግሞ ውብ ማለዳውን የተጋሩት፣ ውለታን የማይረሳው ዛሬም በስኬት ደጃፎች እየተመላለሰ ያለ ህያው ኮከብ ነው።
በሰር አሌክስ ፈርጉሰን እና በማንቸስተር ዩናይትድ መልማዮች ዓይን ውስጥ ከገባባት ከዚያች የወዳጅነት ጨዋታ ዕለት አንስቶ ዘመናዊ እግር ኳስ ሌላ መልክ ነው የያዘው። ማንቸስተር ዩናይትድ ከዚህ ኮከብ ጋር በበርካታ ዋንጫዎች የተገመደ ብዙ የድል ቀናትን አልፏል።
ወደ ሎስ ብላንኮዎቹ ቅፅር ዘልቆም በነጩ መለያ ለሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥም በአውሮፓ መድረክም የሚደረገውን ሁሉ አድርጓል። ቱሪንም እጇን ዘርግታ ነው የተቀበለችው። እዚያም ስኬት ከእርሱ ጋር ነበረች።
በድኅረ ኮቪድ 19 የመጀመሪያ ወቅቶች ወደ ኦልድትራፎርድ ሲመለስ የቀዮቹ ደጋፊዎች ትዝታቸውን እንደሸከፉ ነበርና “እንኳን መጣህልን” ነበር ያሉት።
ሆኖም የማቸስተር ዩናይትድ ዳግም ምልሰቱ እንደ ትላንት ስል፣ እንደ ዕድሜውም በውጤት ብስል አልሆነም። ከኤሪክ ቴንሀግ ጋር የጋባበት መቃቃር ደግሞ ወደ መውጫው በር እንዲያማትር ዋነኛ ምክኒያት ሆነ።
ወደ መካከለኛው ምስራቅ ዘለቀ፤ በእግር ኳስ ብዙ መዋዕለ ንዋይ አፍስሳ ግዙፍ ለውጥ ወደ ሻተችው ሳዑዲ አረቢያ አቀና። ከሳምንታት በፊትም ለሦስት ዓመታት የተጠበቀውን የሳዑዲ ፕሮ ሊግ ሻምፒዮንነት ከክለቡ ዐል-ናስር ጋር አነሳ።
ሆኖም ጥያቄ ነበር። እነዚህን ሁሉ ቁጥራቸው የበረከቱ ስኬቶች ወደ ብሔራዊ ቡድን የሚተረጉማቸውስ መቼ ነው? የሚል።
በእርግጥ የ2016ቱን አውሮፓ ዋንጫ ሲያነሳ ይህ ጥያቄ በከፊል የተመለሰ መስሎ ነበር። የአውሮፓ ሀገራት ዋንጫ/ ኔሽንስ ሊግንም አንስቷል።
ግን ግዙፉ የዓለም ዋንጫስ? እግር ኳስ በታሪኩ ካስመለከታቸው ኮከቦች ለምሉዕነት አንድ መስፈርቱ ይኸው መድረክ ነውና፤ የእርሱስ ቀን አይመጣም ወይ? ተብሎ ተጠብቋል። እስካሁን ያ ቀን አልመጣም።
በእርግጥ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ በተቆጠሩ ግቦች ከሊዮኔል ሜሲ እና ከኢራናዊው ዓሊ ዳይ በእጅጉ ርቋል። በዚህ በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ደግሞ በመድረኩ ከተሳተፉ አንጋፋ ተጫዋቾች አንዱ ሆኖ ወደ አሜሪካ ምድር ሲዘልቅ ብዙ ጥበቃዎች ነበሩ። እነዛ ጥበቃዎች ግን በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ያለግብ ሲለያዩ ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገቡ ያደረገ ሆነ። በርከት ያሉ ትችቶች እርሱም ሆነ የቡድን አጋሮቹ ላይ መሰንዘራቸው አልቀረም።
ቀን ጠብቆ በአሉታ ለተቹትም፣ በበጎ ለጠበቁትም ምላሽ ሰጥቷል። ኡዝቤኪስታንን 5 ለ 0 በረቱበት ጨዋታ ከመረብ ያሳረፋቸው እነዚያ ሁለት ግቦች ትችቶቹን አቅጣጫ ማስቀየሪያ ብቻ አልሆኑም። አዳዲስ ክብረ ወሰኖችንም አስከትለዋል።
ሮናልዶ ከካሜሩናዊው ሮጀር ሚላ በመቀጠል በመድረኩ ግብ ያስቆጠረ አንጋፋ ተጫዋች ተሰኝቷል፤ ከ2006 የጀርመን ዓለም ዋንጫ እስከ 23ኛው የአሜሪካ ምድር ዓለም ዋንጫ በተሳተፈባቸው 6 ውድድሮች በሁሉም ግብ በማስቆጠር ደግሞ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል።
በጨዋታ ዘመኑ ያስቆጠራቸው ግቦችም 975 ደርሰዋል። በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ደግሞ 145ኛ ግቡን በማስቆጠር ከተከታዩ ሊዮኔል ሜሲ ጋር ያለውን ልዩነት ወደ 23 አስፍቷል።
በጨለማ ከመሰለው አስቸጋሪ ሳምንት በኋላ፣ ትችት ከበረከተባቸው ሰሞናት በኋላ “ተመልሰናል” ብሏል ሮናልዶ። በግል የሚመዘገቡ ክብረ ወሰኖች መልካም ቢሆኑም፤ ቀዳሚ ግቡ ግን ቡድኑን መርዳትና ለአሸናፊነት ማብቃት መሆኑን ነው የገለፀው።
ያ መንገድ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ዛሬም ቀጥሏል። እንደ ትላንቱ ባይሰላም ለተባለው ሁሉ ተግባራዊ ምላሽ እየሰጠ አለ። የትችት ወጀብ ሳይገታው፣ የዕድሜ መግፋትም ሳይረታው እንደ ጥንቱ ስል ባይሆንም አለሁ እያለ ነው።
ዋይኒ ሩኒ የተናገው ይህን በሚገባ ይገልፃል።ሮናልዶ ትችትን ማስተናገድ፣ ለትችቱም አስፈላጊውን ተግባራዊ ምለሽ መስጠት በእግር ኳስ ዘመኑ ሁሉ የተጓዘበት እውነት ነው።
“ትዝታ አያረጅም” ሲባል በጎም ይሁን መጥፎ በአዕምሮ ጓዳ ደጋግሞ ስለሚመላለስ ነው። ሮናልዶ ግን ያለፈ ትዝታ፤ ያላለፈ ዛሬ ነው።
እነዚያ በፅናት የተጓዘባቸው ውጤታማ ዓመታት፣ ያንን የሊዝበን ሰታዲየም እንባ ይገልፃሉ። ያ የእልህ እና የቁጭት እንባ፤ ከዓመታት በኋላ ዛሬም ትኩስ ነው፣ አልቀዘቀዘም!
በእድሪስ አህመድ
Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት #sports #ronaldo #football
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የታሂት ቾንግ የእግር ኳስ ህይወት ጉዞ "በጽናት መታገል እና ወደ ማንነት መመለስ" ለሚለው እጅግ አበረታች የሆነ ህያው ምስክር ነው። የህይወት መንገድ ሁልጊዜ ቀጥ ያለ መስመር አይደለም፤ ውጣ ውረዶች እና ያልተጠበቁ ምዕራፎች አሉት። የቾንግ ታሪክም የሚያስተምረን ይህንን ነው።
በኔዘርላንዱ ፌይኑርድ የጀመረው የልጅነት ህልሙ፣ ገና በ16 ዓመቱ ወደ ታላቁ ማንቸስተር ዩናይትድ አካዳሚ ሲቀላቀል እውን የሆነ ይመስል ነበር። በዚያም የክለቡን ታላላቅ የወጣት ተጫዋቾች ሽልማቶችን ጠቅልሎ በመውሰድ በብዙዎች ዘንድ ትልቅ ተስፋ ተጣለበት። እ.ኤ.አ በ2019 ደግሞ በኤፍ ኤ ካፕ የመጀመሪያውን ፕሮፌሽናል ጨዋታ በማድረግ ህልሙን አኖረ።
ነገር ግን በእግር ኳስ ዓለም ውስጥ ያለው እውነታ ሁልጊዜ እንደታሰበው አይሄድም። ታሂት የቋሚነት ቦታ ለማግኘት ባደረገው ትግል በውሰት ከሀገር ሀገር ተንከራትቷል፤ ወደ ጀርመኑ ቨርደር ብሬመን፣ ወደ ቤልጅየሙ ክለብ ብሩጅ፣ እንዲሁም ወደ እንግሊዙ በርሚንግሀም ሲቲ። ብዙዎች "ህልሙ እዚህ ላይ አከተመ" ብለው ሲያስቡ፣ እሱ ግን ተስፋ አልቆረጠም። በየሄደበት ቦታ ሁሉ ራሱን እያሻሻለ፣ ከውድቀት እየተማረ ጉዞውን ቀጠለ። በበርሚንግሀም ቋሚ ኮንትራት ፈርሞ፣ ቀጥሎም ወደ ሉተን ታውን አድጎ፣ አሁን ደግሞ በ2025 ሼፊልድ ዩናይትድን ተቀላቅሎ ጠንካራ ተጫዋች መሆኑን እያስመሰከረ ይገኛል። ከምቾት ቀጣና ወጥቶ መስራት እና አለመሰላቸት የት እንደሚያደርስ አሳይቷል።
ከሁሉም በላይ ግን የታሂት ቾንግ ታሪክ ልብ የሚነካው በብሔራዊ ቡድን ምርጫው ላይ ነው!
ታሂት ከ15 እስከ 21 ዓመት በታች ባሉ የኔዘርላንድስ (ሆላንድ) ብሔራዊ ቡድኖች ውስጥ ከ40 ጊዜ በላይ ተሰልፎ ተጫውቷል። በታላቋ ኔዘርላንድስ ዋናው ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የመጫወት እድል እና ከፍ ያለ ስም የማግኘት በር ከፊቱ ተከፍቶ ነበር። እሱ ግን በ2025 የልቡን ጥሪ አዳመጠ። በዓለም ካርታ ላይ ጣት ለምታክል እና በዓለም ዋንጫ ታሪክ ከታዩ ሀገራት ሁሉ እጅግ ትንሿ ለሆነችው የትውልድ ሀረጉ ኩራሳዎ ለመጫወት ወሰነ!
ይህ ውሳኔ ትልቅ ትምህርት አለው። ስኬት ማለት ሁልጊዜ በታላላቅ መድረኮች ላይ መታየት ብቻ አይደለም፤ ስኬት ማለት ማንነትን አለመዘንጋት፣ ህዝብህ እና የዘር ሐረግህን በትንሹም ቢሆን ስትጠቅመው ማየት፣ እንዲሁም ለምትወደው ነገር በልበ ሙሉነት መቆም ጭምር ነው። ታሂት ቾንግ ትልቅ ስም እና ዝና ከሚያስገኝለት የኔዘርላንድስ ማሊያ ይልቅ፣ የኩራሳዎን ማሊያ ለብሶ ለሀገሩ ታሪክ መስራትን መረጠ።
የታሂት ቾንግ ጉዞ የሚነግረን አንድ ትልቅ እውነት አለ፦ "ምንም ያህል ተሰጥኦ ቢኖረን፣ ፈተናዎች ሲገጥሙን በጽናት ማለፍ አለብን፤ ከየት እንደመጣን እና ማንነታችንን ደግሞ መቼም ቢሆን መርሳት የለብንም!"
በኔዘርላንዱ ፌይኑርድ የጀመረው የልጅነት ህልሙ፣ ገና በ16 ዓመቱ ወደ ታላቁ ማንቸስተር ዩናይትድ አካዳሚ ሲቀላቀል እውን የሆነ ይመስል ነበር። በዚያም የክለቡን ታላላቅ የወጣት ተጫዋቾች ሽልማቶችን ጠቅልሎ በመውሰድ በብዙዎች ዘንድ ትልቅ ተስፋ ተጣለበት። እ.ኤ.አ በ2019 ደግሞ በኤፍ ኤ ካፕ የመጀመሪያውን ፕሮፌሽናል ጨዋታ በማድረግ ህልሙን አኖረ።
ነገር ግን በእግር ኳስ ዓለም ውስጥ ያለው እውነታ ሁልጊዜ እንደታሰበው አይሄድም። ታሂት የቋሚነት ቦታ ለማግኘት ባደረገው ትግል በውሰት ከሀገር ሀገር ተንከራትቷል፤ ወደ ጀርመኑ ቨርደር ብሬመን፣ ወደ ቤልጅየሙ ክለብ ብሩጅ፣ እንዲሁም ወደ እንግሊዙ በርሚንግሀም ሲቲ። ብዙዎች "ህልሙ እዚህ ላይ አከተመ" ብለው ሲያስቡ፣ እሱ ግን ተስፋ አልቆረጠም። በየሄደበት ቦታ ሁሉ ራሱን እያሻሻለ፣ ከውድቀት እየተማረ ጉዞውን ቀጠለ። በበርሚንግሀም ቋሚ ኮንትራት ፈርሞ፣ ቀጥሎም ወደ ሉተን ታውን አድጎ፣ አሁን ደግሞ በ2025 ሼፊልድ ዩናይትድን ተቀላቅሎ ጠንካራ ተጫዋች መሆኑን እያስመሰከረ ይገኛል። ከምቾት ቀጣና ወጥቶ መስራት እና አለመሰላቸት የት እንደሚያደርስ አሳይቷል።
ከሁሉም በላይ ግን የታሂት ቾንግ ታሪክ ልብ የሚነካው በብሔራዊ ቡድን ምርጫው ላይ ነው!
ታሂት ከ15 እስከ 21 ዓመት በታች ባሉ የኔዘርላንድስ (ሆላንድ) ብሔራዊ ቡድኖች ውስጥ ከ40 ጊዜ በላይ ተሰልፎ ተጫውቷል። በታላቋ ኔዘርላንድስ ዋናው ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የመጫወት እድል እና ከፍ ያለ ስም የማግኘት በር ከፊቱ ተከፍቶ ነበር። እሱ ግን በ2025 የልቡን ጥሪ አዳመጠ። በዓለም ካርታ ላይ ጣት ለምታክል እና በዓለም ዋንጫ ታሪክ ከታዩ ሀገራት ሁሉ እጅግ ትንሿ ለሆነችው የትውልድ ሀረጉ ኩራሳዎ ለመጫወት ወሰነ!
ይህ ውሳኔ ትልቅ ትምህርት አለው። ስኬት ማለት ሁልጊዜ በታላላቅ መድረኮች ላይ መታየት ብቻ አይደለም፤ ስኬት ማለት ማንነትን አለመዘንጋት፣ ህዝብህ እና የዘር ሐረግህን በትንሹም ቢሆን ስትጠቅመው ማየት፣ እንዲሁም ለምትወደው ነገር በልበ ሙሉነት መቆም ጭምር ነው። ታሂት ቾንግ ትልቅ ስም እና ዝና ከሚያስገኝለት የኔዘርላንድስ ማሊያ ይልቅ፣ የኩራሳዎን ማሊያ ለብሶ ለሀገሩ ታሪክ መስራትን መረጠ።
የታሂት ቾንግ ጉዞ የሚነግረን አንድ ትልቅ እውነት አለ፦ "ምንም ያህል ተሰጥኦ ቢኖረን፣ ፈተናዎች ሲገጥሙን በጽናት ማለፍ አለብን፤ ከየት እንደመጣን እና ማንነታችንን ደግሞ መቼም ቢሆን መርሳት የለብንም!"
2 months ago
ብርቱካናማዎቹ ስዊድንን በጎል ናዳ አጥለቀለቁ
* ብሪያን ብሮቢ ከታላላቆቹ ተርታ ተሰለፈ!
#ethiopia | በዓለም ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታ የኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን (ብርቱካናማዎቹ) የስዊድንን አቻቸውን 5 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት በመርታት ድንቅ ድል አስመዝግበዋል። ይህ በጎል የተባረከ ድል የሮናልድ ኮማንን (ኪዩመን) ስብስብ በ4 ነጥብ የምድቡ መሪ አድርጎታል።
የጎል ማዕበል እና የጋክፖ ድምቀት
በጨዋታው ላይ የሊቨርፑሉ ኮከብ አጥቂ ኮዲ ጋክፖ እና ወጣቱ ብሪያን ብሮቢ እያንዳንዳቸው 2 ጎሎችን በማስቆጠር የቡድናቸውን የድል ጉዞ መርተዋል። ቀሪዋን አንድ ጎል ክሪሰንሲዮ ሰመርቪል ከመረብ ጋር ሲያገናኝ፣ ለስዊድን ብቸኛዋን ማስተካከያ ጎል ያስቆጠረው የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ፣ የወቅቱ የኖቲንግሃም ፎረስት አጥቂ አንቶኒ ኤላንጋ ነው።
ብሪያን ብሮቢ በታሪክ ማህደር ውስጥ
ይህ ጨዋታ ለኔዘርላንዱ አጥቂ ብሪያን ብሮቢ ልዩ የታሪክ ምዕራፍ የከፈተ ሆኗል። በጨዋታው መጀመሪያ በ12ኛው እና በ16ኛው ደቂቃ ላይ (በ4 ደቂቃዎች ልዩነት ውስጥ) ተከታታይ ጎሎችን በማስቆጠር፣ በዓለም ዋንጫ ታሪክ በፈጣን ሰዓት ተከታታይ ጎል ካስቆጠሩት ታላላቅ የዓለም እግር ኳስ አፈ ታሪኮች ጋር ስሙን በወርቅ ቀለም አጽፏል።
ብሮቢ በዚህ ስኬቱ የብራዚሉን ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ፣ የጀርመኑን ሉካስ ፖዶልስኪ እና የእንግሊዙን ጋሪ ሊንከር ታሪክ ለመጋራት በቅቷል።
በዚህ ድል ማግስት ብርቱካናማዎቹ ምድባቸውን በ4 ነጥብ እየመሩ ወደ ቀጣዩ ደረጃ ለማለፍ ሰፊ ዕድል የፈጠሩ ሲሆን፣ ስዊድናውያን ግን በቀጣይ ጨዋታቸው ታድገው ለመቅረብ ከፍተኛ የቤት ሥራ ይጠብቃቸዋል።
* ብሪያን ብሮቢ ከታላላቆቹ ተርታ ተሰለፈ!
#ethiopia | በዓለም ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታ የኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን (ብርቱካናማዎቹ) የስዊድንን አቻቸውን 5 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት በመርታት ድንቅ ድል አስመዝግበዋል። ይህ በጎል የተባረከ ድል የሮናልድ ኮማንን (ኪዩመን) ስብስብ በ4 ነጥብ የምድቡ መሪ አድርጎታል።
የጎል ማዕበል እና የጋክፖ ድምቀት
በጨዋታው ላይ የሊቨርፑሉ ኮከብ አጥቂ ኮዲ ጋክፖ እና ወጣቱ ብሪያን ብሮቢ እያንዳንዳቸው 2 ጎሎችን በማስቆጠር የቡድናቸውን የድል ጉዞ መርተዋል። ቀሪዋን አንድ ጎል ክሪሰንሲዮ ሰመርቪል ከመረብ ጋር ሲያገናኝ፣ ለስዊድን ብቸኛዋን ማስተካከያ ጎል ያስቆጠረው የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ፣ የወቅቱ የኖቲንግሃም ፎረስት አጥቂ አንቶኒ ኤላንጋ ነው።
ብሪያን ብሮቢ በታሪክ ማህደር ውስጥ
ይህ ጨዋታ ለኔዘርላንዱ አጥቂ ብሪያን ብሮቢ ልዩ የታሪክ ምዕራፍ የከፈተ ሆኗል። በጨዋታው መጀመሪያ በ12ኛው እና በ16ኛው ደቂቃ ላይ (በ4 ደቂቃዎች ልዩነት ውስጥ) ተከታታይ ጎሎችን በማስቆጠር፣ በዓለም ዋንጫ ታሪክ በፈጣን ሰዓት ተከታታይ ጎል ካስቆጠሩት ታላላቅ የዓለም እግር ኳስ አፈ ታሪኮች ጋር ስሙን በወርቅ ቀለም አጽፏል።
ብሮቢ በዚህ ስኬቱ የብራዚሉን ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ፣ የጀርመኑን ሉካስ ፖዶልስኪ እና የእንግሊዙን ጋሪ ሊንከር ታሪክ ለመጋራት በቅቷል።
በዚህ ድል ማግስት ብርቱካናማዎቹ ምድባቸውን በ4 ነጥብ እየመሩ ወደ ቀጣዩ ደረጃ ለማለፍ ሰፊ ዕድል የፈጠሩ ሲሆን፣ ስዊድናውያን ግን በቀጣይ ጨዋታቸው ታድገው ለመቅረብ ከፍተኛ የቤት ሥራ ይጠብቃቸዋል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
አማድ ዲያሎ ባለፈው ዲሴምበር 15 ለማንቸስተር ዩናይትድ ለመጨረሻ ጊዜ ግብ ካስቆጠረ ወዲህ፣ ለአይቮሪ ኮስት አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ከእነዚህም ግቦች ውስጥ ሦስቱ በአፍሪካ ዋንጫ የተቆጠሩ ሲሆኑ፣ በፈረንሳይ ላይ ያስቆጠራት የማሸነፊያ ጎል እና አሁን ደግሞ ያስቆጠራት የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ጎሉ ይገኙበታል።
2 months ago
ማንቸስተር ዩናይትድ ከጄደን ሳንቾ ጋር ተለያየ
#ethiopia | ማንቸስተር ዩናይትድ በዚህ ወር ውሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ጄደን ሳንቾ ከክለቡ መልቀቁን አረጋግጧል።
የ26 ዓመቱ የፊት መስመር ተጫዋች በ2021 ከቦሩሲያ ዶርትሙንድ በ85 ሚሊዮን ዩሮ ማንቸስተር ዩናይትድን ከተቀላቀለ በኋላ፣ ወጥነት የሌላቸው አምስት ዓመታትን አሳልፎ ክለቡን ተሰናብቷል።
ከነሐሴ 2024 ጀምሮ ለዩናይትድ ምንም ጨዋታ ያላደረገው ሳንቾ፣ ያለፉትን ሁለት የውድድር ዘመናት በቼልሲ እና በአስቶን ቪላ በውሰት አሳልፏል።
ሳንቾ በማንቸስተር ዩናይትድ ቆይታው 83 ጨዋታዎችን አድርጎ 12 ግቦችን ሲያስቆጥር፤ 6 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።
በውድድር ዘመኑ ሳንቾ አስቶን ቪላ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን እንዲያሸንፍ ቢረዳም በሁሉም ውድድሮች ግን ማስቆጠር የቻለው አንድ ግብ ብቻ ነው።
እንደ ዘ አትሌቲክ ዘገባ የቀድሞ ክለቡ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ተጫዋቹን ወደ ጀርመን ለመመለስ ፍላጎት ማሳየቱ ታውቋል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በተጨማሪም ታይሬል ማላሲያ እና ካሴሚሮ የውል ስምምነታቸው ሲያልቅ ክለቡን እንደሚለቁ አረጋግጧል።
የሳንቾ ከክለቡ መሰናበት በማንቸስተር ዩናይትድ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ውስጥ እጅግ ውድ ነገር ግን ስኬታማ ካልሆኑ የዝውውር ታሪኮች መካከል የአንዱ ማብቂያ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopianbroadcastingcorporation #sport #now #football
#ethiopia | ማንቸስተር ዩናይትድ በዚህ ወር ውሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ጄደን ሳንቾ ከክለቡ መልቀቁን አረጋግጧል።
የ26 ዓመቱ የፊት መስመር ተጫዋች በ2021 ከቦሩሲያ ዶርትሙንድ በ85 ሚሊዮን ዩሮ ማንቸስተር ዩናይትድን ከተቀላቀለ በኋላ፣ ወጥነት የሌላቸው አምስት ዓመታትን አሳልፎ ክለቡን ተሰናብቷል።
ከነሐሴ 2024 ጀምሮ ለዩናይትድ ምንም ጨዋታ ያላደረገው ሳንቾ፣ ያለፉትን ሁለት የውድድር ዘመናት በቼልሲ እና በአስቶን ቪላ በውሰት አሳልፏል።
ሳንቾ በማንቸስተር ዩናይትድ ቆይታው 83 ጨዋታዎችን አድርጎ 12 ግቦችን ሲያስቆጥር፤ 6 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።
በውድድር ዘመኑ ሳንቾ አስቶን ቪላ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን እንዲያሸንፍ ቢረዳም በሁሉም ውድድሮች ግን ማስቆጠር የቻለው አንድ ግብ ብቻ ነው።
እንደ ዘ አትሌቲክ ዘገባ የቀድሞ ክለቡ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ተጫዋቹን ወደ ጀርመን ለመመለስ ፍላጎት ማሳየቱ ታውቋል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በተጨማሪም ታይሬል ማላሲያ እና ካሴሚሮ የውል ስምምነታቸው ሲያልቅ ክለቡን እንደሚለቁ አረጋግጧል።
የሳንቾ ከክለቡ መሰናበት በማንቸስተር ዩናይትድ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ውስጥ እጅግ ውድ ነገር ግን ስኬታማ ካልሆኑ የዝውውር ታሪኮች መካከል የአንዱ ማብቂያ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopianbroadcastingcorporation #sport #now #football
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ቀያይ ሰይጣኖቹ ለፕሪሚየር ሊጉ ባስገቡት የዘንድሮ የተጫዋቾች ዝርዝር መሰረት በኦልድ ትራፎርድ ግርማ ሞገስ ነበራቸው የተባሉ ተጫዋቾች የማንቸስተር ቆይታቸው ማብቃቱ በይፋ ተረጋግጧል። ከነዚህም መካከል ዋነኛው እንግሊዛዊው የክንፍ ተጫዋች ጃዶን ሳንቾ ነው። ማንቸስተር ዩናይትድ ከ73 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ ካዝናውን አራቁቶ ያመጣው ይህ ኮከብ፣ ከክለቡ ጋር የነበረው ቆይታ እጅግ አሳዛኝ እና ኪሳራ የበዛበት ሆኖ አልፏል። አቋሙን ማግኘት ተስኖት ከቀድሞ አሰልጣኞች ጋር ጭምር እሰጥ አገባ ውስጥ ገብቶ የነበረው ሳንቾ.. በመጨረሻም የክለቡን በር ለዘለቄታው ዘግቶ ወጥቷል። ከእሱ ጋርም ብራዚላዊው አንጋፋ አማካይ ካሴሚሮ እና ታይረል ማላሲያ ስንብታቸው ተረጋግጧል።
ማንቸስተር ዩናይትድ ባወጣው ይፋዊ የመሰናበቻ መግለጫ "ጃዶን ሳንቾ በ2021 ወደ ኦልድ ትራፎርድ ከመጣ በኋላ የ2023ቱን የካራባኦ ካፕ ካነሳው ስብስብ አንዱ ነበር። ወደ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ በውሰት ከመመለሱ፣ እንዲሁም በቼልሲ እና አስቶን ቪላ ጊዜያዊ ቆይታዎችን ከማድረጉ በፊት ለክለቡ 83 ጨዋታዎችን አድርጓል። ክለባችን ካሴሚሮ፣ ታይረል እና ጃዶን ላበረከቱት አስተዋጽኦ እያመሰገነ፣ ለቀጣይ የእግር ኳስ ህይወታቸው መልካሙን ሁሉ ይመኛል" ብሏል።
የማንቸስተር ዩናይትድ ማልያ ከብዶት የታየው የ26 ዓመቱ አጥቂ፣ በአምስት ዓመት የዩናይትድ ቆይታው በሁሉም ውድድሮች ማግባት የቻለው 12 ጎሎችን እና 6 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ማቀበል ብቻ ነው። ይህ ደካማ አቋሙ የቀድሞ የክለቡን ተጫዋቾች ሳይቀር አበሳጭቷል። በተለይም ሉዊስ ሳሃ፣ ሳንቾን "በማንቸስተር ዩናይትድ ታሪክ እጅግ አሳዛኙ ፈራሚ" ሲል ከባድ ትችት ሰንዝሮበታል።
ሳሃ በቁጭት ስሜት ሲናገር... "ከመምጣቱ በፊት በቦሩሲያ ዶርትሙንድ ያሳየው አስገራሚ ብቃት እና የነበረው ተሰጥኦ ታላቅ ተስፋ ሰጥቶን ነበር፤ እንግሊዝ መጥቶ ያ ሁሉ መጥፋቱ ግን እንቆቅልሽ ሆኖብኛል። እኔ እግር ኳስ ተጫዋች በመሆኔ እድለኛ ነበርኩ፣ ግን በጉዳት ብዙ ጊዜ አሳልፌያለሁ። በእሱ ዕድሜ እና ተሰጥኦ የሱን ያህል ጨዋታዎችን መጫወት ብችል ምንኛ መታደል ነበር... አስገራሚ ነገሮችን ማድረግ የሚችል ልጅ ነው፤ ነገር ግን ይህ ሁሉ ችሎታው እና የተሰለፈባቸው ጨዋታዎች ሲባክኑ ማየት በእጅጉ ያሳዝናል" ብሏል።
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቢቸገርም በጀርመን ምድር ግን ሳንቾ አሁንም ትልቅ ከበሬታ እና ስም አለው። መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ፣ ተጫዋቹ ከ2021 ጀምሮ የጠፋበትን የእግር ኳስ ህይወቱን ዳግም ለማንሰራራት ለሶስተኛ ጊዜ ወደ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ለማምራት በሩን ክፍት አድርጓል። የክለቡ ዋና አሰልጣኝ ኒኮ ኮቫችም ለዚህ ዝውውር አረንጓዴ መብራት አብርተዋል እየተባለ ይገኛል።
ሳንቾ የህይወቱን ምርጥ ጊዜ ያሳለፈው በዚሁ በሲግናል ኢዱና ፓርክ ሲሆን.. በመጀመሪያ ቆይታው በ137 ጨዋታዎች በ114 ጎሎች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ ነበረው። በ2024 በውሰት ተመልሶ ክለቡን እስከ ዌምብሌዩ የሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ማድረሱም አይዘነጋም። ወደ ቡንደስሊጋው መመለሱ፣ ከ2021 ጀምሮ ለተለየው የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ዳግም እንዲጠራ የሚያስችለውን መተማመን ሊሰጠው ይችላል።
የፋይናንስ መዛግብቱን ለማስተካከል እና አዲስ ጠንካራ ስብስብ ለመገንባት ቆርጦ የተነሳው ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮቹን እያጸዳ ይገኛል። ከሳንቾ በተጨማሪ አንጋፋው ብራዚላዊ አማካይ ካሴሚሮ እና የግራ መስመር ተከላካዩ ታይረል ማላሲያ በኮንትራት መጠናቀቅ ምክንያት ተሰናብተዋል። ከሪያል ማድሪድ መጥቶ በአራት የውድድር ዘመናት ቆይታው የካራባኦ ካፕ እና የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫዎችን ያነሳው ካሴሚሮ፤ እንዲሁም ከ2022 የፌይኖርድ ዝውውሩ በኋላ በጉዳት እየታመሰ 50 ጨዋታዎችን ብቻ ማድረግ የቻለው ማላሲያ የክለቡን በር ዘግተው ወጥተዋል።
አዲሱ የማንቸስተር ዩናይትድ የስፖርት አመራር እነዚህን ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ ተጫዋቾች ማሰናበቱ፣ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት አዳዲስ እና ወጣት ደም ለማስገባት በደመወዝ በጀቱ ላይ ሰፊ የፋይናንስ ነጻነትን ፈጥሮለታል። አሁን የሁሉም አይን ዩናይትድ ይህንን ክፍተት በማን እንደሚተካው ላይ አርፏል!
ማንቸስተር ዩናይትድ ባወጣው ይፋዊ የመሰናበቻ መግለጫ "ጃዶን ሳንቾ በ2021 ወደ ኦልድ ትራፎርድ ከመጣ በኋላ የ2023ቱን የካራባኦ ካፕ ካነሳው ስብስብ አንዱ ነበር። ወደ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ በውሰት ከመመለሱ፣ እንዲሁም በቼልሲ እና አስቶን ቪላ ጊዜያዊ ቆይታዎችን ከማድረጉ በፊት ለክለቡ 83 ጨዋታዎችን አድርጓል። ክለባችን ካሴሚሮ፣ ታይረል እና ጃዶን ላበረከቱት አስተዋጽኦ እያመሰገነ፣ ለቀጣይ የእግር ኳስ ህይወታቸው መልካሙን ሁሉ ይመኛል" ብሏል።
የማንቸስተር ዩናይትድ ማልያ ከብዶት የታየው የ26 ዓመቱ አጥቂ፣ በአምስት ዓመት የዩናይትድ ቆይታው በሁሉም ውድድሮች ማግባት የቻለው 12 ጎሎችን እና 6 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ማቀበል ብቻ ነው። ይህ ደካማ አቋሙ የቀድሞ የክለቡን ተጫዋቾች ሳይቀር አበሳጭቷል። በተለይም ሉዊስ ሳሃ፣ ሳንቾን "በማንቸስተር ዩናይትድ ታሪክ እጅግ አሳዛኙ ፈራሚ" ሲል ከባድ ትችት ሰንዝሮበታል።
ሳሃ በቁጭት ስሜት ሲናገር... "ከመምጣቱ በፊት በቦሩሲያ ዶርትሙንድ ያሳየው አስገራሚ ብቃት እና የነበረው ተሰጥኦ ታላቅ ተስፋ ሰጥቶን ነበር፤ እንግሊዝ መጥቶ ያ ሁሉ መጥፋቱ ግን እንቆቅልሽ ሆኖብኛል። እኔ እግር ኳስ ተጫዋች በመሆኔ እድለኛ ነበርኩ፣ ግን በጉዳት ብዙ ጊዜ አሳልፌያለሁ። በእሱ ዕድሜ እና ተሰጥኦ የሱን ያህል ጨዋታዎችን መጫወት ብችል ምንኛ መታደል ነበር... አስገራሚ ነገሮችን ማድረግ የሚችል ልጅ ነው፤ ነገር ግን ይህ ሁሉ ችሎታው እና የተሰለፈባቸው ጨዋታዎች ሲባክኑ ማየት በእጅጉ ያሳዝናል" ብሏል።
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቢቸገርም በጀርመን ምድር ግን ሳንቾ አሁንም ትልቅ ከበሬታ እና ስም አለው። መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ፣ ተጫዋቹ ከ2021 ጀምሮ የጠፋበትን የእግር ኳስ ህይወቱን ዳግም ለማንሰራራት ለሶስተኛ ጊዜ ወደ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ለማምራት በሩን ክፍት አድርጓል። የክለቡ ዋና አሰልጣኝ ኒኮ ኮቫችም ለዚህ ዝውውር አረንጓዴ መብራት አብርተዋል እየተባለ ይገኛል።
ሳንቾ የህይወቱን ምርጥ ጊዜ ያሳለፈው በዚሁ በሲግናል ኢዱና ፓርክ ሲሆን.. በመጀመሪያ ቆይታው በ137 ጨዋታዎች በ114 ጎሎች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ ነበረው። በ2024 በውሰት ተመልሶ ክለቡን እስከ ዌምብሌዩ የሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ማድረሱም አይዘነጋም። ወደ ቡንደስሊጋው መመለሱ፣ ከ2021 ጀምሮ ለተለየው የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ዳግም እንዲጠራ የሚያስችለውን መተማመን ሊሰጠው ይችላል።
የፋይናንስ መዛግብቱን ለማስተካከል እና አዲስ ጠንካራ ስብስብ ለመገንባት ቆርጦ የተነሳው ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮቹን እያጸዳ ይገኛል። ከሳንቾ በተጨማሪ አንጋፋው ብራዚላዊ አማካይ ካሴሚሮ እና የግራ መስመር ተከላካዩ ታይረል ማላሲያ በኮንትራት መጠናቀቅ ምክንያት ተሰናብተዋል። ከሪያል ማድሪድ መጥቶ በአራት የውድድር ዘመናት ቆይታው የካራባኦ ካፕ እና የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫዎችን ያነሳው ካሴሚሮ፤ እንዲሁም ከ2022 የፌይኖርድ ዝውውሩ በኋላ በጉዳት እየታመሰ 50 ጨዋታዎችን ብቻ ማድረግ የቻለው ማላሲያ የክለቡን በር ዘግተው ወጥተዋል።
አዲሱ የማንቸስተር ዩናይትድ የስፖርት አመራር እነዚህን ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ ተጫዋቾች ማሰናበቱ፣ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት አዳዲስ እና ወጣት ደም ለማስገባት በደመወዝ በጀቱ ላይ ሰፊ የፋይናንስ ነጻነትን ፈጥሮለታል። አሁን የሁሉም አይን ዩናይትድ ይህንን ክፍተት በማን እንደሚተካው ላይ አርፏል!
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ማንቸስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን አማካይ ኤደርሰንን ከአታላንታ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሱ ተረጋገጠ። ለሳምንታት የዘለቀው ድርድር በተሳካ ሁኔታ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ዩናይትድ ለ26 ዓመቱ ተጫዋች 40.5 ሚሊዮን ዩሮ ቋሚ ክፍያ እና 4.5 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ማበረታቻዎችን በማካተት በድምሩ የ45 ሚሊዮን ዩሮ ጥቅል ለአታላንታ ለመክፈል ተስማምቷል። ይህ ዝውውር በመጪው የውድድር ዘመን የክለቡ አሰልጣኝ ለሆኑት ማይክል ካሪክ የክረምቱ የመጀመሪያው ፈራሚ ያደርገዋል።
ኤደርሰን በኦልድ ትራፎርድ እስከ ሰኔ 2030 ድረስ የሚያቆየውን የአራት ዓመት ኮንትራት ለመፈረም በግል ጥቅማጥቅሞች ላይ የተስማማ ሲሆን፣ ውሉን ለተጨማሪ 12 ወራት የማራዘም አማራጭም በስምምነቱ ውስጥ ተካቷል። ተጫዋቹ የህክምና ምርመራውን ካጠናቀቀ በኋላ በሀምሌ ወር መጀመሪያ ላይ ዝውውሩ በይፋ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።
ኤደርሰን በ2027 ነፃ ወኪል የመሆን ዕድል ስለነበረው፣ ሌሎች ታላላቅ ክለቦች ቢፈልጉትም ቅድሚያ ለዩናይትድ በመስጠቱ ክለቡ ከዚህ ቀደም በገበያው ይገመት ከነበረው ዋጋ በጣም ባነሰ መልኩ ሊያገኘው ችሏል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በ2026-27 የውድድር ዘመን በቻምፒየንስ ሊግ የሚሳተፍ በመሆኑ፣ እንዲሁም ካሴሚሮ ክለቡን መልቀቁን ተከትሎ ክፍት የሆነውን የአማካይ ክፍል ለማጠናከር ይህ ዝውውር ወሳኝ ጅምር ሆኖለታል። በቀጣይም በዚሁ የሜዳ ክፍል ላይ ተጨማሪ ተጫዋቾችን ያመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የስፖርት ተንታኞች ማርክ ኬሪ እና ላውሪ ዊትዌል እንዳስነበቡት፣ኤደርሰን በሜዳ ላይ ልክ እንደ "ፓክ-ማን" የጨዋታ አደጋዎችን በማጽዳት፣ ኳሶችን በማቋረጥ እና መልሶ በመቀማት ከፍተኛ ብቃት ያለው ተጫዋች ነው። ኳስን በመቆጣጠር እና አጫጭር ኳሶችን በማቀበል ከሀገሩ ልጅ ካሴሚሮ የተሻለ ብቃት እንዳለው የሚነገርለት ሲሆን፣ ኳስን ወደ ፊት ይዘው ለሚሮጡ አጥቂዎችም ጥሩ አቀባይ ነው። በሁለቱም የግብ ክልሎች መካከል እየተመላለሰ የሚጫወተው ይህ ብራዚላዊ አሰልጣኞች እጅግ የሚወዱት ዓይነት ተጫዋች ነው። ሁልጊዜ የዜና ርዕስ ባይሆንም፣ በሜዳ ላይ ለሚኖረው የቡድን ስብስብ ወሳኝ ሞተር በመሆን የቡድን አጋሮቹ በሙሉ አቅማቸው እንዲጫወቱ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ኤደርሰን በኦልድ ትራፎርድ እስከ ሰኔ 2030 ድረስ የሚያቆየውን የአራት ዓመት ኮንትራት ለመፈረም በግል ጥቅማጥቅሞች ላይ የተስማማ ሲሆን፣ ውሉን ለተጨማሪ 12 ወራት የማራዘም አማራጭም በስምምነቱ ውስጥ ተካቷል። ተጫዋቹ የህክምና ምርመራውን ካጠናቀቀ በኋላ በሀምሌ ወር መጀመሪያ ላይ ዝውውሩ በይፋ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።
ኤደርሰን በ2027 ነፃ ወኪል የመሆን ዕድል ስለነበረው፣ ሌሎች ታላላቅ ክለቦች ቢፈልጉትም ቅድሚያ ለዩናይትድ በመስጠቱ ክለቡ ከዚህ ቀደም በገበያው ይገመት ከነበረው ዋጋ በጣም ባነሰ መልኩ ሊያገኘው ችሏል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በ2026-27 የውድድር ዘመን በቻምፒየንስ ሊግ የሚሳተፍ በመሆኑ፣ እንዲሁም ካሴሚሮ ክለቡን መልቀቁን ተከትሎ ክፍት የሆነውን የአማካይ ክፍል ለማጠናከር ይህ ዝውውር ወሳኝ ጅምር ሆኖለታል። በቀጣይም በዚሁ የሜዳ ክፍል ላይ ተጨማሪ ተጫዋቾችን ያመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የስፖርት ተንታኞች ማርክ ኬሪ እና ላውሪ ዊትዌል እንዳስነበቡት፣ኤደርሰን በሜዳ ላይ ልክ እንደ "ፓክ-ማን" የጨዋታ አደጋዎችን በማጽዳት፣ ኳሶችን በማቋረጥ እና መልሶ በመቀማት ከፍተኛ ብቃት ያለው ተጫዋች ነው። ኳስን በመቆጣጠር እና አጫጭር ኳሶችን በማቀበል ከሀገሩ ልጅ ካሴሚሮ የተሻለ ብቃት እንዳለው የሚነገርለት ሲሆን፣ ኳስን ወደ ፊት ይዘው ለሚሮጡ አጥቂዎችም ጥሩ አቀባይ ነው። በሁለቱም የግብ ክልሎች መካከል እየተመላለሰ የሚጫወተው ይህ ብራዚላዊ አሰልጣኞች እጅግ የሚወዱት ዓይነት ተጫዋች ነው። ሁልጊዜ የዜና ርዕስ ባይሆንም፣ በሜዳ ላይ ለሚኖረው የቡድን ስብስብ ወሳኝ ሞተር በመሆን የቡድን አጋሮቹ በሙሉ አቅማቸው እንዲጫወቱ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ብሩኖ ፈርናንዴዝን በኦልድ ትራፎርድ ለማቆየት አዲስ ውይይት ተጀምሯል
#ethiopia | ማንቸስተር ዩናይትድ የቡድኑን መሪ እና ቁልፍ ተጫዋች ብሩኖ ፈርናንዴዝን በክለቡ ለማቆየት አዲስ የኮንትራት ስምምነት ላይ የውስጥ ውይይት መጀመሩ ተሰማ።
ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ ፋብሪዚዮ ሮማኖ እንደዘገበው ከሆነ፣ ዩናይትድ በዚህ የክረምት የዝውውር መስኮት ፖርቹጋላዊውን አማካይ አሳልፎ የመስጠት ምንም ዓይነት ፍላጎት የለውም። ከበስተጀርባ እየተካሄደ ባለው በዚህ ንግግር ላይ የክለቡ ባለቤቶች፣ የአስተዳደር አባላት፣ የአሰልጣኝ ስታፍ እና የቡድን አጋሮቹ ተጫዋቹን በኦልድ ትራፎርድ ለማቆየት ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
በዚህ የውድድር ዘመን ለዩናይትድ እጅግ አስደናቂ ብቃቱን ያሳየው ፈርናንዴዝ፣ በፕሪሚየር ሊጉ ላይ 21 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማሳለፍና በአጠቃላይ 30 የጎል አስተዋፅዖዎችን በማስመዝገብ የቡድኑ የማጥቃት መስመር የጀርባ አጥንት መሆኑን በድጋሚ አስመስክሯል።
ከአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች እና ከሳውዲ አረቢያ የሚቀርቡለትን ፈታኝ ጥያቄዎች ለመከላከል የቆረጠው ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ከካፒቴኑ ጋር የሚያደርገውን ንግግር በሂደት ላይ ያለ ስራ ("work in progress") በሚል በንቃት እየገፋበት ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#manchesterunited #brunofernandes #fabrizioromano #mufc #premierleague #transfernews #oldtrafford #የስፖርትዜና
#ethiopia | ማንቸስተር ዩናይትድ የቡድኑን መሪ እና ቁልፍ ተጫዋች ብሩኖ ፈርናንዴዝን በክለቡ ለማቆየት አዲስ የኮንትራት ስምምነት ላይ የውስጥ ውይይት መጀመሩ ተሰማ።
ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ ፋብሪዚዮ ሮማኖ እንደዘገበው ከሆነ፣ ዩናይትድ በዚህ የክረምት የዝውውር መስኮት ፖርቹጋላዊውን አማካይ አሳልፎ የመስጠት ምንም ዓይነት ፍላጎት የለውም። ከበስተጀርባ እየተካሄደ ባለው በዚህ ንግግር ላይ የክለቡ ባለቤቶች፣ የአስተዳደር አባላት፣ የአሰልጣኝ ስታፍ እና የቡድን አጋሮቹ ተጫዋቹን በኦልድ ትራፎርድ ለማቆየት ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
በዚህ የውድድር ዘመን ለዩናይትድ እጅግ አስደናቂ ብቃቱን ያሳየው ፈርናንዴዝ፣ በፕሪሚየር ሊጉ ላይ 21 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማሳለፍና በአጠቃላይ 30 የጎል አስተዋፅዖዎችን በማስመዝገብ የቡድኑ የማጥቃት መስመር የጀርባ አጥንት መሆኑን በድጋሚ አስመስክሯል።
ከአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች እና ከሳውዲ አረቢያ የሚቀርቡለትን ፈታኝ ጥያቄዎች ለመከላከል የቆረጠው ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ከካፒቴኑ ጋር የሚያደርገውን ንግግር በሂደት ላይ ያለ ስራ ("work in progress") በሚል በንቃት እየገፋበት ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#manchesterunited #brunofernandes #fabrizioromano #mufc #premierleague #transfernews #oldtrafford #የስፖርትዜና
2 months ago
ብሩኖ ፈርናንዴዝ 21 ለግብ የሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል አዲስ ሪከርድ ሰበረ
#ethiopia | ብሩኖ ፈርናንዴዝ በቴሪ ሄነሪ እና በኬቨን ዴብሩይነ ተይዞ የነበረውን ለግብ ኳስ አመቻችቶ የማቀበል ሪከርድ ሰበረ።
በሊጉ የመጨረሻ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናይትድ ከብራይተን ጋር እያደረጉት ባለው ጨዋታ 33ኛው ደቂቃ ላይ ፓትሪክ ዶርጉ ላስቆጠረው ግብ ኳስ አመቻችቶ በማቀበሉ ሪከርዱን ሊሰብር ችሏል።
የማንችስተር ዩናይትዱ አማካይ ብሩኖ ፈርናንዴዝ በዚህ ዓመት በሊጉ 21 ለግብ የሆነ ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ብሩኖ ፈርናንዴዝ በቴሪ ሄነሪ እና በኬቨን ዴብሩይነ ተይዞ የነበረውን ለግብ ኳስ አመቻችቶ የማቀበል ሪከርድ ሰበረ።
በሊጉ የመጨረሻ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናይትድ ከብራይተን ጋር እያደረጉት ባለው ጨዋታ 33ኛው ደቂቃ ላይ ፓትሪክ ዶርጉ ላስቆጠረው ግብ ኳስ አመቻችቶ በማቀበሉ ሪከርዱን ሊሰብር ችሏል።
የማንችስተር ዩናይትዱ አማካይ ብሩኖ ፈርናንዴዝ በዚህ ዓመት በሊጉ 21 ለግብ የሆነ ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 months ago
ሻምፒዮኑ አርሰናል ሲያሸንፍ፣ ዌስትሀም ወረደ ቶተንሀም ተረፈ
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመድፈኞቹ የዋንጫ ጥማት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተቋጭቷል።
አርሰናል በ38ኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታው ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን የክብር አክሊል ይረከባል።
በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ገብርኤል ጀሱስ ያስቆጠራት ግብ የድሉን መንገድ የጠረገች ሲሆን፤ ቡድኑ እስከ ጨዋታው ፍጻሜ ድረስ ብቃቱን በማስመስከር የለንደን ጎዳናዎችን በደስታ እና በእልልታ እንዲሞሉ አድርጓል።
በሌሎች የዛሬው የመጨረሻ ሳምንት መርሃ ግብሮች ማንቸስተር ሲቲ በአስቶን ቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሲሸነፍ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ረቷል።
ዌስትሃም ሊድስን በ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም ወደታችኛው ሊግ ወርዷል።
ቶተንሃም ኤቨርተንን 1 ለ 0 አሸንፎ በሊጉ መቆየት ችሏል።
በሌላ በኩል ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር 1 ለ 1፣ ፉልሃም ኒውካስትልን 2 ለ 0፣ ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ ያልተጠበቀ ውጤት አስመዝግቧል።
በርንሌይ ከዎልቭስ እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት የውድድር ዘመኑን አጠናቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመድፈኞቹ የዋንጫ ጥማት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተቋጭቷል።
አርሰናል በ38ኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታው ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን የክብር አክሊል ይረከባል።
በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ገብርኤል ጀሱስ ያስቆጠራት ግብ የድሉን መንገድ የጠረገች ሲሆን፤ ቡድኑ እስከ ጨዋታው ፍጻሜ ድረስ ብቃቱን በማስመስከር የለንደን ጎዳናዎችን በደስታ እና በእልልታ እንዲሞሉ አድርጓል።
በሌሎች የዛሬው የመጨረሻ ሳምንት መርሃ ግብሮች ማንቸስተር ሲቲ በአስቶን ቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሲሸነፍ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ረቷል።
ዌስትሃም ሊድስን በ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም ወደታችኛው ሊግ ወርዷል።
ቶተንሃም ኤቨርተንን 1 ለ 0 አሸንፎ በሊጉ መቆየት ችሏል።
በሌላ በኩል ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር 1 ለ 1፣ ፉልሃም ኒውካስትልን 2 ለ 0፣ ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ ያልተጠበቀ ውጤት አስመዝግቧል።
በርንሌይ ከዎልቭስ እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት የውድድር ዘመኑን አጠናቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የሳዑዲ አረቢያ እግር ኳስን በዓለም መድረክ ላይ ላስተዋወቀው የሊጉ "ፖስተር ቦይ" ከዚህ የተሻለ የድል ምስል ሊኖር አይችልም፦ ክርስቲያኖ ሮናልዶ የሳዑዲ ፕሮ ሊግን ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ላይ ከፍ አድርጎ አነሳው!
አል-ናስር በታህሳስ 2022 የማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ተከትሎ ይህንን ሜጋ ስታር ወደ ሪያድ ሲያመጣው፣ ዓለምን ማስደንገጥ እና ሀገሪቱን ወደ ዓለም አቀፉ የስፖርት መድረክ ማሸጋገር ዋነኛ ዓላማው ነበር። ይሁን እንጂ፣ ከሦስት ዓመታት በላይ ቆይታ በኋላ፣ ይህ የ41 ዓመቱ የእግር ኳስ ጠበብት አንድም ትልቅ የሀገር ውስጥ ዋንጫ አለማንሳቱ ብዙዎችን ሲያስገርም ቆይቷል።
የረዥም ጊዜ ጥበቃው ግን ሐሙስ ምሽት ማብቂያ አግኝቷል። በውድድር ዘመኑ የመጨረሻ ቀን፣ አል-ናስር ዳማክን 4ለ1 በረመረመበት አጓጊ ጨዋታ ላይ ሮናልዶ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር፣ የዘመናት ባላንጣ የሆነውን አል-ሂላልን በመርታት ክለቡ ከ2019 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የሻምፒዮንነት ክብሩን እንዲቀዳጅ አስችሎታል።
በቅርቡ በሳዑዲ ፕሮ ሊግ 100ኛ ግቡን ያስቆጠረው ሮናልዶ፣ በሁሉም ውድድሮች ለአል-ናስር 129 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል። ይህ ዋንጫ ግን፣ እሱ በዋናነት እንዲያነሳው የተፈረመበት ትልቁ የክብር አክሊል ነበር።
ሮናልዶ ከሦስት ዓመት ተኩል በፊት ወደ ሳዑዲ ካመራ በኋላ ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል። የእሱ መምጣት እንደ ካሪም ቤንዜማ፣ ንጎሎ ካንቴ፣ ሪያድ ማህሬዝ፣ ሳዲዮ ማኔ፣ ኔይማር እና ሌሎችም ታላላቅ ከዋክብት ወደ 'ታላላቆቹ አራት' ክለቦች (በሪያድ አል-ሂላል እና አል-ናስር፣ በጅዳ አል-አህሊ እና አል-ኢትሃድ) እንዲጎርፉ መንገድ ጠርጓል።
በ2023 ክረምት ላይ እነዚህ አራት ክለቦች በሀገሪቱ የህዝብ ኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) ስር የገቡ ሲሆን፣ በሚያዝያ 2026 ግን የ70 በመቶ የአል-ሂላል ድርሻ በልዑል አልዋሊድ ቢን ታላል ለሚመራው 'ኪንግደም ሆልዲንግ ኩባንያ' መሸጡ ይታወሳል።
ይህኛው የውድድር ዘመን ግን ከሁሉም የተለየ እና እጅግ አጓጊ ነበር። ለተወሰነ ጊዜ አራት ቡድኖች በዋንጫ ፉክክሩ ውስጥ ነበሩ። በአይቫን ቶኒ ግቦች የታገዘው አል-አህሊ፣ እና በሳዑዲው የነዳጅ ግዙፍ ኩባንያ አራምኮ የሚደገፈውና በብሬንዳን ሮጀርስ የሚሰለጥነው አል-ቃድሲያህ በመጨረሻዎቹ ሳምንታት ከፉክክሩ ርቀዋል።
ፉክክሩ በአል-ናስር እና በአል-ሂላል መካከል ብቻ ተወስኖ የቀጠለ ሲሆን፣ ሜይ 12 የተካሄደው የሁለቱ ክለቦች ትልቁ ፍጥጫ የሊጉን አቅጣጫ የወሰነ ነበር። ከ180 በላይ ሀገራት የተላለፈው ይህ ታሪካዊ ጨዋታ፣ አስገራሚ ፍጻሜ ነበረው። አል-ናስር 1ለ0 እየመራ ጨዋታው 97ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስ፣ ቢጫ የለበሱ ደጋፊዎች ድሉን ማክበር ጀምረው ነበር። ነገር ግን በመጨረሻዋ ሰከንድ ላይ ግብ ጠባቂው ቤንቶ በቀላሉ ሊይዛት የሚገባትን ኳስ አምልጦት በራሱ ላይ ባስቆጠረው ግብ ጨዋታው 1ለ1 ተጠናቀቀ። የዋንጫው ፉክክር ህያው ሆኖ ቢቀጥልም፣ ሐሙስ ዕለት ግን አል-ናስር ስራውን በተጨባጭ አጠናቋል።
ይህ ድል ለአል-ናስር 11ኛው የሊግ ዋንጫ ሲሆን፣ ለክርስቲያኖ ሮናልዶ ደግሞ በእንግሊዝ (ማንቸስተር ዩናይትድ)፣ በስፔን (ሪያል ማድሪድ) እና በጣሊያን (ጁቬንቱስ) ካነሳቸው ዋንጫዎች በመቀጠል 8ኛው የሊግ ሻምፒዮንነት ሆኖ ተመዝግቧል።
"በሪያድ ያሉ ባለስልጣናት የአል-ናስርን ድል የሮናልዶን ዝውውር እና ክለቡን በPIF ስር ለማቆየት የተደረገውን ውሳኔ ትክክለኛነት እንደሚያረጋግጥ አድርገው ይመለከቱታል" ሲሉ በፓሪስ ኢምሊዮን ቢዝነስ ስር የአፍሮ-ዩራሲያ ስፖርት ፕሮፌሰር የሆኑት ሳይመን ቻድዊክ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ይህ የሊግ ድል የመጣው፣ ቅዳሜ ዕለት የእስያ ዩሮፓ ሊግ አቻ በሆነው 'ኤኤፍሲ ቻምፒየንስ ሊግ 2' ፍጻሜ ላይ አል-ናስር ባልተጠበቀ ሁኔታ በጃፓኑ ጋምባ ኦሳካ ከተሸነፈ በኋላ በመሆኑ፣ ለሮናልዶ ትልቅ እፎይታን ሰጥቶታል።
የዘንድሮው የውድድር ዘመን ከውዝግብ የጸዳ አልነበረም። በየካቲት ወር ሮናልዶ በሁለት የሊግ ጨዋታዎች ላይ ያልተሰለፈ ሲሆን፣ ይህ የሆነው PIF ክለቡን የሚያስተዳድርበት መንገድ ከአል-ሂላል ጋር ሲነጻጸር ፍትሃዊ አይደለም በሚል ቅሬታ እንደሆነ ተዘግቧል። በሌላ በኩል ደግሞ ሊጉ ሮናልዶን ይደግፋል የሚሉ ወገኖች አልጠፉም። የአል-አህሊው አይቫን ቶኒ እና ብራዚላዊው ጋሌኖ ሊጉ ለሮናልዶ እና ለአል-ናስር ያደላል ሲሉ ከከሰሱት መካከል ይገኛሉ።
ሮናልዶ ለዚህ በሰጠው ምላሽ፡ "ይህ ለሊጉ ጥሩ አይመስለኝም። ሁሉም ያማርራል። ይህ እግር ኳስ እንጂ ጦርነት አይደለም... ግን ሁሉም ነገር አይፈቀድም። ብዙ፣ ብዙ መጥፎ ነገሮችን ስላየሁ በውድድር ዘመኑ መጨረሻ ላይ እናገራለሁ። ብዙ ተጫዋቾች በኢንስታግራም እና ፌስቡክ ላይ ስለ ዳኞች፣ ስለ ሊጉ እና ስለ ፕሮጀክቱ ቅሬታ ያሰማሉ። ይህ ጥሩ አይደለም፤ የሊጉም ዓላማ ይህ አይደለም" በማለት ተችቷል።
በአጠቃላይ የሳዑዲ አረቢያ የስፖርት ፕሮጀክት በቅርቡ ጥያቄ ውስጥ ወድቋል። ሚያዝያ ላይ PIF የሊቭ ጎልፍ የገንዘብ ድጋፍን እንደሚያቋርጥ ሲያሳውቅ፣ በጥር ወር ደግሞ ሀገሪቱ ልታስተናግደው የነበረው የ2029 የክረምት የእስያ ጨዋታዎች ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል። የሴቶች ቴኒስ የፍጻሜ ውድድርም ከሳዑዲ እንደሚወጣ ተዘግቧል።
በእግር ኳሱም ቢሆን ሚዲያው በታላላቅ ተጫዋቾች ዝውውር ወሬ ይሞላበት የነበረው ጊዜ ያለፈ ይመስላል። አሁንም ቢሆን አል-ቃድሲያህ ጣሊያናዊውን ማቴዎ ሬቴጉዊን በ57 ሚሊዮን ፓውንድ፣ አል-ሂላል ደግሞ ዳርዊን ኑኔዝን በ46 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረማቸው ትልቅ እርምጃ ቢሆንም፣ ከ2023ቱ የዝውውር ማዕበል ጋር ሲነጻጸር አሁን ትኩረቱ ዳግም ሊሸጡ በሚችሉ ወጣት ተጫዋቾች ላይ ሆኗል። ይሁን እንጂ፣ ሊቨርፑልን የሚለቀቀውን ሞሀመድ ሳላህን የመሰለ አንጋፋ ኮከብ ለማምጣት አሁንም በጀቱ ክፍት መሆኑ ይነገራል።
የሮናልዶ የሊግ ሻምፒዮንነት የሳዑዲ ክለቦች በአንድ የዝውውር መስኮት 700 ሚሊዮን ፓውንድ ያፈሱበት "ያለፈው ወርቃማ ዘመን የመጨረሻው የድል ጩኸት" ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ቀጣዩ የሳዑዲ እግር ኳስ እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል የጊዜ ጉዳይ ቢሆንም፣ ለአሁኑ ግን የሪያድ ቢጫ ለባሾች እና የዓለም አቀፉ የሮናልዶ ደጋፊዎች በደስታ ማዕበል ውስጥ እየዋኙ ይገኛሉ።
አል-ናስር በታህሳስ 2022 የማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ተከትሎ ይህንን ሜጋ ስታር ወደ ሪያድ ሲያመጣው፣ ዓለምን ማስደንገጥ እና ሀገሪቱን ወደ ዓለም አቀፉ የስፖርት መድረክ ማሸጋገር ዋነኛ ዓላማው ነበር። ይሁን እንጂ፣ ከሦስት ዓመታት በላይ ቆይታ በኋላ፣ ይህ የ41 ዓመቱ የእግር ኳስ ጠበብት አንድም ትልቅ የሀገር ውስጥ ዋንጫ አለማንሳቱ ብዙዎችን ሲያስገርም ቆይቷል።
የረዥም ጊዜ ጥበቃው ግን ሐሙስ ምሽት ማብቂያ አግኝቷል። በውድድር ዘመኑ የመጨረሻ ቀን፣ አል-ናስር ዳማክን 4ለ1 በረመረመበት አጓጊ ጨዋታ ላይ ሮናልዶ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር፣ የዘመናት ባላንጣ የሆነውን አል-ሂላልን በመርታት ክለቡ ከ2019 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የሻምፒዮንነት ክብሩን እንዲቀዳጅ አስችሎታል።
በቅርቡ በሳዑዲ ፕሮ ሊግ 100ኛ ግቡን ያስቆጠረው ሮናልዶ፣ በሁሉም ውድድሮች ለአል-ናስር 129 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል። ይህ ዋንጫ ግን፣ እሱ በዋናነት እንዲያነሳው የተፈረመበት ትልቁ የክብር አክሊል ነበር።
ሮናልዶ ከሦስት ዓመት ተኩል በፊት ወደ ሳዑዲ ካመራ በኋላ ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል። የእሱ መምጣት እንደ ካሪም ቤንዜማ፣ ንጎሎ ካንቴ፣ ሪያድ ማህሬዝ፣ ሳዲዮ ማኔ፣ ኔይማር እና ሌሎችም ታላላቅ ከዋክብት ወደ 'ታላላቆቹ አራት' ክለቦች (በሪያድ አል-ሂላል እና አል-ናስር፣ በጅዳ አል-አህሊ እና አል-ኢትሃድ) እንዲጎርፉ መንገድ ጠርጓል።
በ2023 ክረምት ላይ እነዚህ አራት ክለቦች በሀገሪቱ የህዝብ ኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) ስር የገቡ ሲሆን፣ በሚያዝያ 2026 ግን የ70 በመቶ የአል-ሂላል ድርሻ በልዑል አልዋሊድ ቢን ታላል ለሚመራው 'ኪንግደም ሆልዲንግ ኩባንያ' መሸጡ ይታወሳል።
ይህኛው የውድድር ዘመን ግን ከሁሉም የተለየ እና እጅግ አጓጊ ነበር። ለተወሰነ ጊዜ አራት ቡድኖች በዋንጫ ፉክክሩ ውስጥ ነበሩ። በአይቫን ቶኒ ግቦች የታገዘው አል-አህሊ፣ እና በሳዑዲው የነዳጅ ግዙፍ ኩባንያ አራምኮ የሚደገፈውና በብሬንዳን ሮጀርስ የሚሰለጥነው አል-ቃድሲያህ በመጨረሻዎቹ ሳምንታት ከፉክክሩ ርቀዋል።
ፉክክሩ በአል-ናስር እና በአል-ሂላል መካከል ብቻ ተወስኖ የቀጠለ ሲሆን፣ ሜይ 12 የተካሄደው የሁለቱ ክለቦች ትልቁ ፍጥጫ የሊጉን አቅጣጫ የወሰነ ነበር። ከ180 በላይ ሀገራት የተላለፈው ይህ ታሪካዊ ጨዋታ፣ አስገራሚ ፍጻሜ ነበረው። አል-ናስር 1ለ0 እየመራ ጨዋታው 97ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስ፣ ቢጫ የለበሱ ደጋፊዎች ድሉን ማክበር ጀምረው ነበር። ነገር ግን በመጨረሻዋ ሰከንድ ላይ ግብ ጠባቂው ቤንቶ በቀላሉ ሊይዛት የሚገባትን ኳስ አምልጦት በራሱ ላይ ባስቆጠረው ግብ ጨዋታው 1ለ1 ተጠናቀቀ። የዋንጫው ፉክክር ህያው ሆኖ ቢቀጥልም፣ ሐሙስ ዕለት ግን አል-ናስር ስራውን በተጨባጭ አጠናቋል።
ይህ ድል ለአል-ናስር 11ኛው የሊግ ዋንጫ ሲሆን፣ ለክርስቲያኖ ሮናልዶ ደግሞ በእንግሊዝ (ማንቸስተር ዩናይትድ)፣ በስፔን (ሪያል ማድሪድ) እና በጣሊያን (ጁቬንቱስ) ካነሳቸው ዋንጫዎች በመቀጠል 8ኛው የሊግ ሻምፒዮንነት ሆኖ ተመዝግቧል።
"በሪያድ ያሉ ባለስልጣናት የአል-ናስርን ድል የሮናልዶን ዝውውር እና ክለቡን በPIF ስር ለማቆየት የተደረገውን ውሳኔ ትክክለኛነት እንደሚያረጋግጥ አድርገው ይመለከቱታል" ሲሉ በፓሪስ ኢምሊዮን ቢዝነስ ስር የአፍሮ-ዩራሲያ ስፖርት ፕሮፌሰር የሆኑት ሳይመን ቻድዊክ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ይህ የሊግ ድል የመጣው፣ ቅዳሜ ዕለት የእስያ ዩሮፓ ሊግ አቻ በሆነው 'ኤኤፍሲ ቻምፒየንስ ሊግ 2' ፍጻሜ ላይ አል-ናስር ባልተጠበቀ ሁኔታ በጃፓኑ ጋምባ ኦሳካ ከተሸነፈ በኋላ በመሆኑ፣ ለሮናልዶ ትልቅ እፎይታን ሰጥቶታል።
የዘንድሮው የውድድር ዘመን ከውዝግብ የጸዳ አልነበረም። በየካቲት ወር ሮናልዶ በሁለት የሊግ ጨዋታዎች ላይ ያልተሰለፈ ሲሆን፣ ይህ የሆነው PIF ክለቡን የሚያስተዳድርበት መንገድ ከአል-ሂላል ጋር ሲነጻጸር ፍትሃዊ አይደለም በሚል ቅሬታ እንደሆነ ተዘግቧል። በሌላ በኩል ደግሞ ሊጉ ሮናልዶን ይደግፋል የሚሉ ወገኖች አልጠፉም። የአል-አህሊው አይቫን ቶኒ እና ብራዚላዊው ጋሌኖ ሊጉ ለሮናልዶ እና ለአል-ናስር ያደላል ሲሉ ከከሰሱት መካከል ይገኛሉ።
ሮናልዶ ለዚህ በሰጠው ምላሽ፡ "ይህ ለሊጉ ጥሩ አይመስለኝም። ሁሉም ያማርራል። ይህ እግር ኳስ እንጂ ጦርነት አይደለም... ግን ሁሉም ነገር አይፈቀድም። ብዙ፣ ብዙ መጥፎ ነገሮችን ስላየሁ በውድድር ዘመኑ መጨረሻ ላይ እናገራለሁ። ብዙ ተጫዋቾች በኢንስታግራም እና ፌስቡክ ላይ ስለ ዳኞች፣ ስለ ሊጉ እና ስለ ፕሮጀክቱ ቅሬታ ያሰማሉ። ይህ ጥሩ አይደለም፤ የሊጉም ዓላማ ይህ አይደለም" በማለት ተችቷል።
በአጠቃላይ የሳዑዲ አረቢያ የስፖርት ፕሮጀክት በቅርቡ ጥያቄ ውስጥ ወድቋል። ሚያዝያ ላይ PIF የሊቭ ጎልፍ የገንዘብ ድጋፍን እንደሚያቋርጥ ሲያሳውቅ፣ በጥር ወር ደግሞ ሀገሪቱ ልታስተናግደው የነበረው የ2029 የክረምት የእስያ ጨዋታዎች ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል። የሴቶች ቴኒስ የፍጻሜ ውድድርም ከሳዑዲ እንደሚወጣ ተዘግቧል።
በእግር ኳሱም ቢሆን ሚዲያው በታላላቅ ተጫዋቾች ዝውውር ወሬ ይሞላበት የነበረው ጊዜ ያለፈ ይመስላል። አሁንም ቢሆን አል-ቃድሲያህ ጣሊያናዊውን ማቴዎ ሬቴጉዊን በ57 ሚሊዮን ፓውንድ፣ አል-ሂላል ደግሞ ዳርዊን ኑኔዝን በ46 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረማቸው ትልቅ እርምጃ ቢሆንም፣ ከ2023ቱ የዝውውር ማዕበል ጋር ሲነጻጸር አሁን ትኩረቱ ዳግም ሊሸጡ በሚችሉ ወጣት ተጫዋቾች ላይ ሆኗል። ይሁን እንጂ፣ ሊቨርፑልን የሚለቀቀውን ሞሀመድ ሳላህን የመሰለ አንጋፋ ኮከብ ለማምጣት አሁንም በጀቱ ክፍት መሆኑ ይነገራል።
የሮናልዶ የሊግ ሻምፒዮንነት የሳዑዲ ክለቦች በአንድ የዝውውር መስኮት 700 ሚሊዮን ፓውንድ ያፈሱበት "ያለፈው ወርቃማ ዘመን የመጨረሻው የድል ጩኸት" ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ቀጣዩ የሳዑዲ እግር ኳስ እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል የጊዜ ጉዳይ ቢሆንም፣ ለአሁኑ ግን የሪያድ ቢጫ ለባሾች እና የዓለም አቀፉ የሮናልዶ ደጋፊዎች በደስታ ማዕበል ውስጥ እየዋኙ ይገኛሉ።
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) እስኪ ያንተን የሰዓት እጅ ወደኋላ አሽከርክረው፤ አርሰን ቬንገር በስታዲየሙ መሀል ቆመው፣ ቲየሪ ኦነሪ መረቡን ሲቀደው፣ ፓትሪክ ቪዬራ መሀል ሜዳውን ሲገዛው እና ያ የማይበገረው የ"ኢንቪንሲብልስ" ስብስብ ወርቃማውን ዋንጫ ወደ ሰማይ ሲሰቅለው የነበረው ያ ድንቅ ዘመን! ያኔ 2003/04 ላይ ነበር። ከዚያ በኋላ ግን በመድፈኞቹ ቤት ዘመኑ የረሃብ፣ የናፍቆት እና የእንባ ሆነ። ያ ሁሉ ስቃይ፣ ያ ሁሉ መከራ ግን ዛሬ ማክሰኞ ምሽት አበቃለት!
ትዕይንቱ የተደገሰው በለንደን ሳይሆን በቪታሊቲ ስታዲየም ነበር። ማንቸስተር ሲቲ ዋንጫውን ከአርሰናል እጅ ለመንጠቅ የመጨረሻ የተስፋ ፍርሃቱን ይዞ ወደ ቦርማውዝ አቅንቶ ነበር። ሆኖም ግን የፔፕ ጋርዲዮላ ማሽን በቦርማውዝ ብረት ለበስ መከላከያ ፊት ተሰባበረ። ጨዋታው 1 ለ 1 በሆነ እኩል ውጤት ፍጻሜውን ሲያገኝ፣ ሰማያዊዎቹ የለንደኑን ንጉሥ ማሳደድ የማይችሉበት የነጥብ እርቀት ላይ መውደቃቸውን አረጋገጡ። በዚያችው ቅጽበት የለንደን ሰማይ በቀይና በነጭ ርችቶች ደመቀ፤ አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንግሊሽ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን መሆኑ በይፋ ታወጀ!
ይህ ዋንጫ ዝም ብሎ የመጣ አልነበረም። ለአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እና ለልጆቹ ፍጹም የእሳት እራት የመሆን ያህል ከባድ ፈተና የተሻገሩበት ነው። በዘንድሮው የውድድር ዘመን አብዛኛውን ጊዜ የሊጉን አናት ተቆጣጥረውት የነበረ ቢሆንም፣ በሚያዝያ ወር ግን ያ የለመዱት የፍርሃት ጥላ ዳግም አጥልቶባቸው ነበር። ማንቸስተር ሲቲ እንደ ከርከሮ ከበስተጀርባቸው ይተነፍስባቸው ጀመር። ይባስ ብሎ በኢቲሃድ ስታዲየም 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በሲቲ ሲሸነፉ፣ ብዙዎች "ታሪኩ ተደገመ፣ አርሰናል ዘንድሮም ዋንጫውን አሳልፎ ሰጠ" ብለው ፈርደውባቸው ነበር።
ነገር ግን የዘንድሮው ስብስብ የተለየ ብረት የተገነባ ነበር! ከተሸነፉበት ማግስት ጀምሮ እንደ ቆሰለ አንበሳ አገገሙ፤ አንዳችም ነጥብ ሳይጥሉ እስከ መጨረሻው ተዋጉ። ያንን የጋርዲዮላን አስፈሪ ሰራዊት አስከብበው በመያዝ፣ ከስድስት ዓመታት የዋንጫ ድርቅ በኋላ የክለቡን ታላቅ ታሪክ መልሰው ጻፉት። ይህ ድል ለአርሰናል በታሪኩ 14ኛው የሊግ ዋንጫው ሲሆን፣ ለአርቴታ ደግሞ በኤምሬትስ ስታዲየም ሁለተኛው ትልቅ የስኬት ማማው ነው።
አሁን መድፈኞቹ በ37 ጨዋታዎች 82 ነጥብ ሰብስበው የሊጉን አክሊል ደፍተዋል። ሰንጠረዡ እንደሚያሳየው ሲቲ በ78 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ እና አስቶን ቪላ ደግሞ ተከታዮቹን የቻምፒዮንስ ሊግ ቦታዎች ይዘዋል። አርሰናል ይህንን ታላቅ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ እሁድ ዕለት በሴልኸርስት ፓርክ ከክሪስታል ፓላስ ጋር ከሚያደርገው የዓመቱ የመጨረሻ ጨዋታ በኋላ በይፋ ርክክብ ያደርጋል።
ነገር ግን ታሪኩ በዚህ አያበቃም! ለሰሜን ለንደኑ ክለብ ከፊት ለፊቱ ሌላ ታላቅ የክብር ማዕድ ተደግሶለታል። መድፈኞቹ በክለቡ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ለመጨበጥ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም (ማለትም ቅዳሜ ሜይ 30) በቡዳፔስት ከፈረንሳዩ ሀብታም ክለብ ፒኤስጂ ጋር ለፍጻሜ ይፋለማሉ።
አርሰናል አሁን አምኗል፤ ደጋፊዎቹም በደስታ ሰክረዋል። የ22 ዓመታት የበርሃ ጉዞ አብቅቶ፣ መድፈኞቹ ወደ ተስፋይቱ ምድር በክብር ገብተዋል!
ሊሊ ሞገስ - የዘ-ሐበሻ ስፖርት አዘጋጅ
ትዕይንቱ የተደገሰው በለንደን ሳይሆን በቪታሊቲ ስታዲየም ነበር። ማንቸስተር ሲቲ ዋንጫውን ከአርሰናል እጅ ለመንጠቅ የመጨረሻ የተስፋ ፍርሃቱን ይዞ ወደ ቦርማውዝ አቅንቶ ነበር። ሆኖም ግን የፔፕ ጋርዲዮላ ማሽን በቦርማውዝ ብረት ለበስ መከላከያ ፊት ተሰባበረ። ጨዋታው 1 ለ 1 በሆነ እኩል ውጤት ፍጻሜውን ሲያገኝ፣ ሰማያዊዎቹ የለንደኑን ንጉሥ ማሳደድ የማይችሉበት የነጥብ እርቀት ላይ መውደቃቸውን አረጋገጡ። በዚያችው ቅጽበት የለንደን ሰማይ በቀይና በነጭ ርችቶች ደመቀ፤ አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንግሊሽ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን መሆኑ በይፋ ታወጀ!
ይህ ዋንጫ ዝም ብሎ የመጣ አልነበረም። ለአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እና ለልጆቹ ፍጹም የእሳት እራት የመሆን ያህል ከባድ ፈተና የተሻገሩበት ነው። በዘንድሮው የውድድር ዘመን አብዛኛውን ጊዜ የሊጉን አናት ተቆጣጥረውት የነበረ ቢሆንም፣ በሚያዝያ ወር ግን ያ የለመዱት የፍርሃት ጥላ ዳግም አጥልቶባቸው ነበር። ማንቸስተር ሲቲ እንደ ከርከሮ ከበስተጀርባቸው ይተነፍስባቸው ጀመር። ይባስ ብሎ በኢቲሃድ ስታዲየም 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በሲቲ ሲሸነፉ፣ ብዙዎች "ታሪኩ ተደገመ፣ አርሰናል ዘንድሮም ዋንጫውን አሳልፎ ሰጠ" ብለው ፈርደውባቸው ነበር።
ነገር ግን የዘንድሮው ስብስብ የተለየ ብረት የተገነባ ነበር! ከተሸነፉበት ማግስት ጀምሮ እንደ ቆሰለ አንበሳ አገገሙ፤ አንዳችም ነጥብ ሳይጥሉ እስከ መጨረሻው ተዋጉ። ያንን የጋርዲዮላን አስፈሪ ሰራዊት አስከብበው በመያዝ፣ ከስድስት ዓመታት የዋንጫ ድርቅ በኋላ የክለቡን ታላቅ ታሪክ መልሰው ጻፉት። ይህ ድል ለአርሰናል በታሪኩ 14ኛው የሊግ ዋንጫው ሲሆን፣ ለአርቴታ ደግሞ በኤምሬትስ ስታዲየም ሁለተኛው ትልቅ የስኬት ማማው ነው።
አሁን መድፈኞቹ በ37 ጨዋታዎች 82 ነጥብ ሰብስበው የሊጉን አክሊል ደፍተዋል። ሰንጠረዡ እንደሚያሳየው ሲቲ በ78 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ እና አስቶን ቪላ ደግሞ ተከታዮቹን የቻምፒዮንስ ሊግ ቦታዎች ይዘዋል። አርሰናል ይህንን ታላቅ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ እሁድ ዕለት በሴልኸርስት ፓርክ ከክሪስታል ፓላስ ጋር ከሚያደርገው የዓመቱ የመጨረሻ ጨዋታ በኋላ በይፋ ርክክብ ያደርጋል።
ነገር ግን ታሪኩ በዚህ አያበቃም! ለሰሜን ለንደኑ ክለብ ከፊት ለፊቱ ሌላ ታላቅ የክብር ማዕድ ተደግሶለታል። መድፈኞቹ በክለቡ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ለመጨበጥ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም (ማለትም ቅዳሜ ሜይ 30) በቡዳፔስት ከፈረንሳዩ ሀብታም ክለብ ፒኤስጂ ጋር ለፍጻሜ ይፋለማሉ።
አርሰናል አሁን አምኗል፤ ደጋፊዎቹም በደስታ ሰክረዋል። የ22 ዓመታት የበርሃ ጉዞ አብቅቶ፣ መድፈኞቹ ወደ ተስፋይቱ ምድር በክብር ገብተዋል!
ሊሊ ሞገስ - የዘ-ሐበሻ ስፖርት አዘጋጅ
Sponsored by
Surafel
3 months ago
"አርሰናሎች የዛሬውን ምሽት ማሸነፍ ከሚገባቸው በላይ ራሳቸው አክብደውታል። ጨዋታውን በፍጥነትም ሆነ በሚፈለገው የቁጭት ስሜት አልተጫወቱትም። ዝም ብለው በራሳቸው ምቾት ተዘናግተው ነው ያመሹት።"
ጋሪ ኔቪል (የቀድሞው ማንቸስተር ዩናይትድ ተከላካይ፣ በስካይ ስፖርትስ ላይ ሲናገር የሰማነው)
ጋሪ ኔቪል (የቀድሞው ማንቸስተር ዩናይትድ ተከላካይ፣ በስካይ ስፖርትስ ላይ ሲናገር የሰማነው)
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ማንቸስተር ዩናይትድ በሜዳው ኦልድ ትራፎርድ ኖቲንግሀም ፎረስትን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በዘንድሮው የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዓመት ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁን አረጋግጧል። ይህ ማራኪ ድል አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ በሜዳቸው ካደረጓቸው ዘጠኝ ጨዋታዎች ለስምንተኛ ጊዜ ያሸነፉበት አስደናቂ ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል።
በዚህ አጓጊ ጨዋታ ላይ የብሩኖ ፈርናንዴዝ እና የካሴሚሮ ጉዳይ የብዙዎችን ቀልብ የሳበ ትልቅ ክስተት ነበር። ብሩኖ ፈርናንዴዝ ለብራያን እምቤውሞ የዩናይትድን ሶስተኛ ግብ አመቻችቶ በማቀበል በውድድር ዓመቱ 20ኛውን 'አሲስት' በማድረግ የፕሪሚየር ሊጉን ታሪካዊ ክብረወሰን ከኬቪን ደብሩይነ እና ቲየሪ ኦንሪ ጋር በጋራ መያዝ ችሏል። የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ ተከላካይ ጋሪ ኔቭል ይህንን ድንቅ ክስተት በማድነቅ ስታዲየሙ በብሩኖ ስም ሲናወጥ እንደነበር አጋርቷል። በሌላ በኩል ደግሞ ብራዚላዊው አማካይ ካሴሚሮ በ81ኛው ደቂቃ በሚሰን ማውንት ተቀይሮ ሲወጣ ከስታዲየሙ ሞቅ ያለ አሸኛኘት እና ክብር ተችሮታል፤ ከሁለት ዓመት በፊት ያልታሰበው የካሴሚሮ የማንቸስተር ዩናይትድ ቆይታም በዚህ መልኩ እጅግ በሚያምር ስንብት ተቋጭቷል።
የጨዋታው ዋነኛ መነጋገሪያ እና አወዛጋቢ ጉዳይ ግን በ55ኛው ደቂቃ ላይ ማቲየስ ኩኛ ዩናይትድን 2 ለ 1 መሪ ያደረገበት ግብ ነው። ኳሷ ወደ ግብነት ከመቀየሯ በፊት በብራያን እምቤውሞ እጅ መንካቷን ተከትሎ የቫር (VAR) ዳኛው ማት ዶኖሁ፣ ዋናው ዳኛ ማይክል ሳልስበሪ ውሳኔያቸውን በስክሪን እንዲያዩ ቢጋብዙም፣ ዳኛው ግን "የእጅ ንክኪው ያልታሰበ ነው" በማለት የመጀመሪያ ውሳኔያቸውን አጽንተው ግቡን አጽድቀውታል። የፕሪሚየር ሊጉ የቀድሞ ረዳት ዳኛ ዳረን ካን በሰጡት አስተያየት፣ ዳኛው በውሳኔያቸው መጽናታቸው (በዘንድሮው የውድድር ዓመት ለ4ኛ ጊዜ ብቻ የተፈጠረ) የሚደነቅ ቢሆንም፣ ኳሷ እጅን ነክታ ለግብ መነሻ ስትሆን የኳስ ቤተሰቡ ጥፋት ሊሰጥ ይገባል የሚል ጠንካራ እምነት እንዳለው በቢቢሲ ስፖርት ላይ አብራርተዋል።
ጨዋታው ልክ እንደ ቅርጫት ኳስ ከአንዱ የግብ ክልል ወደ ሌላኛው የግብ ክልል በፍጥነት ሲመላለስ የነበረበት እና ኖቲንግሀም ፎረስትም እጅግ አደገኛ ሆኖ የታየበት ማራኪ ፍልሚያ ነበር።
በዚህ አጓጊ ጨዋታ ላይ የብሩኖ ፈርናንዴዝ እና የካሴሚሮ ጉዳይ የብዙዎችን ቀልብ የሳበ ትልቅ ክስተት ነበር። ብሩኖ ፈርናንዴዝ ለብራያን እምቤውሞ የዩናይትድን ሶስተኛ ግብ አመቻችቶ በማቀበል በውድድር ዓመቱ 20ኛውን 'አሲስት' በማድረግ የፕሪሚየር ሊጉን ታሪካዊ ክብረወሰን ከኬቪን ደብሩይነ እና ቲየሪ ኦንሪ ጋር በጋራ መያዝ ችሏል። የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ ተከላካይ ጋሪ ኔቭል ይህንን ድንቅ ክስተት በማድነቅ ስታዲየሙ በብሩኖ ስም ሲናወጥ እንደነበር አጋርቷል። በሌላ በኩል ደግሞ ብራዚላዊው አማካይ ካሴሚሮ በ81ኛው ደቂቃ በሚሰን ማውንት ተቀይሮ ሲወጣ ከስታዲየሙ ሞቅ ያለ አሸኛኘት እና ክብር ተችሮታል፤ ከሁለት ዓመት በፊት ያልታሰበው የካሴሚሮ የማንቸስተር ዩናይትድ ቆይታም በዚህ መልኩ እጅግ በሚያምር ስንብት ተቋጭቷል።
የጨዋታው ዋነኛ መነጋገሪያ እና አወዛጋቢ ጉዳይ ግን በ55ኛው ደቂቃ ላይ ማቲየስ ኩኛ ዩናይትድን 2 ለ 1 መሪ ያደረገበት ግብ ነው። ኳሷ ወደ ግብነት ከመቀየሯ በፊት በብራያን እምቤውሞ እጅ መንካቷን ተከትሎ የቫር (VAR) ዳኛው ማት ዶኖሁ፣ ዋናው ዳኛ ማይክል ሳልስበሪ ውሳኔያቸውን በስክሪን እንዲያዩ ቢጋብዙም፣ ዳኛው ግን "የእጅ ንክኪው ያልታሰበ ነው" በማለት የመጀመሪያ ውሳኔያቸውን አጽንተው ግቡን አጽድቀውታል። የፕሪሚየር ሊጉ የቀድሞ ረዳት ዳኛ ዳረን ካን በሰጡት አስተያየት፣ ዳኛው በውሳኔያቸው መጽናታቸው (በዘንድሮው የውድድር ዓመት ለ4ኛ ጊዜ ብቻ የተፈጠረ) የሚደነቅ ቢሆንም፣ ኳሷ እጅን ነክታ ለግብ መነሻ ስትሆን የኳስ ቤተሰቡ ጥፋት ሊሰጥ ይገባል የሚል ጠንካራ እምነት እንዳለው በቢቢሲ ስፖርት ላይ አብራርተዋል።
ጨዋታው ልክ እንደ ቅርጫት ኳስ ከአንዱ የግብ ክልል ወደ ሌላኛው የግብ ክልል በፍጥነት ሲመላለስ የነበረበት እና ኖቲንግሀም ፎረስትም እጅግ አደገኛ ሆኖ የታየበት ማራኪ ፍልሚያ ነበር።
3 months ago
ማንቸስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን በመርታት የዋንጫ ተፎካካሪነቱን አጠናከረ
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቸስተር ሲቲ በገዛ ሜዳው ኢቲሃድ ስታዲየም ብሬንትፎርድን አስተናግዶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ጨዋታው እስከ 60ኛው ደቂቃ ድረስ ያለምንም ግብ ቢቀጥልም በሁለተኛው አጋማሽ የሲቲ አጥቂዎች ባሳዩት ድንቅ ብቃት ድል ቀንቷቸዋል።
ለውሃ ሰማያዊዎቹ ግቦቹን ጄረሚ ዶኩ፣ አርሊንግ ሃላንድ እና ኦማር ማርሙሽ ከመረብ አሳርፈዋል።
ይህንን ውጤት ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ በሊጉ 22ኛ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን ወደ 74 ከፍ አድርጓል።
ይህም ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ብቻ ዝቅ እንዲል አድርጎታል።
ኖርዌያዊው የግብ ማሽን አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 25 በማድረስ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በበላይነት እየመራ ይገኛል።
በሌላ በኩል በሊጉ መሪነት ላይ የሚገኘው አርሰናል ነገ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ብሬንትፎርድ በበኩሉ በዚህ የውድድር ዓመት የ13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደ ሲሆን በ51 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በተያያዘ ዜና ማንቸስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል በሳምንቱ መርሃ ግብራቸው ነጥብ መጋራታቸው ታውቋል።
#manchestercity #premierleague #footballnews #mancity #haaland #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቸስተር ሲቲ በገዛ ሜዳው ኢቲሃድ ስታዲየም ብሬንትፎርድን አስተናግዶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ጨዋታው እስከ 60ኛው ደቂቃ ድረስ ያለምንም ግብ ቢቀጥልም በሁለተኛው አጋማሽ የሲቲ አጥቂዎች ባሳዩት ድንቅ ብቃት ድል ቀንቷቸዋል።
ለውሃ ሰማያዊዎቹ ግቦቹን ጄረሚ ዶኩ፣ አርሊንግ ሃላንድ እና ኦማር ማርሙሽ ከመረብ አሳርፈዋል።
ይህንን ውጤት ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ በሊጉ 22ኛ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን ወደ 74 ከፍ አድርጓል።
ይህም ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ብቻ ዝቅ እንዲል አድርጎታል።
ኖርዌያዊው የግብ ማሽን አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 25 በማድረስ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በበላይነት እየመራ ይገኛል።
በሌላ በኩል በሊጉ መሪነት ላይ የሚገኘው አርሰናል ነገ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ብሬንትፎርድ በበኩሉ በዚህ የውድድር ዓመት የ13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደ ሲሆን በ51 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በተያያዘ ዜና ማንቸስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል በሳምንቱ መርሃ ግብራቸው ነጥብ መጋራታቸው ታውቋል።
#manchestercity #premierleague #footballnews #mancity #haaland #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
ቡሩኖ ፈርናንዴዝ
#ethiopia | የእግር ኳስ ፀሀፊዎች ማህበር ብሩኖ ፈርናንዴዝን የአመቱ የፕሪሜር ሊግ ምርጥ ተጫዋች ብሎ መርጧል።
የማንቸስተር ዩናይትድ አንበል ብሩኖ ፈርናንዴዝ በእንግሊዝ የእግር ኳስ ጸሐፊዎች ማህበር (FWA) የዓመቱ ምርጥ ወንድ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ።
ፖርቹጋላዊው አማካይ በዚህ የውድድር ዘመን ለቀይ ሰይጣኖቹ በሁሉም ውድድሮች ባደረጋቸው 34 ጨዋታዎች 8 ግቦችን ከመረብ ሲያሳርፍ፣ 20 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን (አሲስት) አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።
ፈርናንዴዝ ቡድኑ በጊዜያዊ አሰልጣኙ ማይክል ካሪክ ስር ላሳየው የተሻሻለ አቋም ቁልፍ ሚና መጫወቱ ተገልጿል።
ምንም እንኳን ማንቸስተር ዩናይትድ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የውድድር ዘመኑን ያለ ዋንጫ የሚያጠናቅቅ ቢሆንም፣ በፕሪምየር ሊጉ በሶስተኛ ደረጃ ላይ በመገኘት የቻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን ለማረጋገጥ ተቃርቧል።
ብሩኖ ፈርናንዴዝ እ.ኤ.አ. በ2010 ይህንን ሽልማት ካሸነፈው ዋይን ሩኒ በኋላ የFWA የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ክብርን የተቀዳጀ የመጀመሪያው የዩናይትድ ተጫዋች ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | የእግር ኳስ ፀሀፊዎች ማህበር ብሩኖ ፈርናንዴዝን የአመቱ የፕሪሜር ሊግ ምርጥ ተጫዋች ብሎ መርጧል።
የማንቸስተር ዩናይትድ አንበል ብሩኖ ፈርናንዴዝ በእንግሊዝ የእግር ኳስ ጸሐፊዎች ማህበር (FWA) የዓመቱ ምርጥ ወንድ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ።
ፖርቹጋላዊው አማካይ በዚህ የውድድር ዘመን ለቀይ ሰይጣኖቹ በሁሉም ውድድሮች ባደረጋቸው 34 ጨዋታዎች 8 ግቦችን ከመረብ ሲያሳርፍ፣ 20 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን (አሲስት) አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።
ፈርናንዴዝ ቡድኑ በጊዜያዊ አሰልጣኙ ማይክል ካሪክ ስር ላሳየው የተሻሻለ አቋም ቁልፍ ሚና መጫወቱ ተገልጿል።
ምንም እንኳን ማንቸስተር ዩናይትድ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የውድድር ዘመኑን ያለ ዋንጫ የሚያጠናቅቅ ቢሆንም፣ በፕሪምየር ሊጉ በሶስተኛ ደረጃ ላይ በመገኘት የቻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን ለማረጋገጥ ተቃርቧል።
ብሩኖ ፈርናንዴዝ እ.ኤ.አ. በ2010 ይህንን ሽልማት ካሸነፈው ዋይን ሩኒ በኋላ የFWA የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ክብርን የተቀዳጀ የመጀመሪያው የዩናይትድ ተጫዋች ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
Comments