Logo
Getu Temesgen
ማንቸስተር ዩናይትድ ከጄደን ሳንቾ ጋር ተለያየ
#ethiopia | ማንቸስተር ዩናይትድ በዚህ ወር ውሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ጄደን ሳንቾ ከክለቡ መልቀቁን አረጋግጧል።

​የ26 ዓመቱ የፊት መስመር ተጫዋች በ2021 ከቦሩሲያ ዶርትሙንድ በ85 ሚሊዮን ዩሮ ማንቸስተር ዩናይትድን ከተቀላቀለ በኋላ፣ ወጥነት የሌላቸው አምስት ዓመታትን አሳልፎ ክለቡን ተሰናብቷል።

ከነሐሴ 2024 ጀምሮ ለዩናይትድ ምንም ጨዋታ ያላደረገው ሳንቾ፣ ያለፉትን ሁለት የውድድር ዘመናት በቼልሲ እና በአስቶን ቪላ በውሰት አሳልፏል።

ሳንቾ ​በማንቸስተር ዩናይትድ ቆይታው 83 ጨዋታዎችን አድርጎ 12 ግቦችን ሲያስቆጥር፤ 6 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።

​በውድድር ዘመኑ ሳንቾ አስቶን ቪላ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን እንዲያሸንፍ ቢረዳም በሁሉም ውድድሮች ግን ማስቆጠር የቻለው አንድ ግብ ብቻ ነው።

እንደ ዘ አትሌቲክ ዘገባ የቀድሞ ክለቡ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ተጫዋቹን ወደ ጀርመን ለመመለስ ፍላጎት ማሳየቱ ታውቋል።

​ማንቸስተር ዩናይትድ በተጨማሪም ታይሬል ማላሲያ እና ካሴሚሮ የውል ስምምነታቸው ሲያልቅ ክለቡን እንደሚለቁ አረጋግጧል።

​የሳንቾ ከክለቡ መሰናበት በማንቸስተር ዩናይትድ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ውስጥ እጅግ ውድ ነገር ግን ስኬታማ ካልሆኑ የዝውውር ታሪኮች መካከል የአንዱ ማብቂያ ሆኗል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopianbroadcastingcorporation #sport #now #football

11 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.