4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ ድምጽ የነበረው ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ተከትሎ ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በይፋዊ የትስስር ገጹ ገልጿል።
ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ በመልዕክቱ፣ "በተወዳጅ እና በልዩ የዜማ ስልቱ ስንወደው በነበረው ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ህልፈት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽኩ፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለመላው የኪነጥበብ ማህበረሰብ መጽናናትን እመኛለሁ" ብሏል።
ቴዲ አፍሮ አክሎም ሰማኸኝ በለው የባህል ሙዚቃውን በአንቱታ ያገለገለ እና በኪነጥበቡ ዓለም ትልቅ አሻራ ጥሎ ያለፈ ሰው መሆኑን በማውሳት፣ "ነፍሱ በገነት ትረፍ፤ ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር፤ ፍቅር ያሸንፋል" በማለት መልእክቱን አጠናቋል።
የድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ህልፈት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ኢንዱስትሪ በታላቅ ሐዘን ውስጥ የጣለ ክስተት ሆኗል። አርቲስቱ በተለይም በባህል ሙዚቃው ዘርፍ የነበረው የላቀ አስተዋጽኦ ለዘመናት በኪነጥበብ አፍቃሪዎች ዘንድ ሲዘከር የሚኖር ነው። የድምጻዊውን ማለፍ አስመልክቶ ቴዲ አፍሮን ጨምሮ በርካታ የሙያ ባልደረቦቹ እና አድናቂዎቹ የህመም እና የሀዘን መግለጫዎችን በመላክ ላይ ይገኛሉ።
ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ በመልዕክቱ፣ "በተወዳጅ እና በልዩ የዜማ ስልቱ ስንወደው በነበረው ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ህልፈት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽኩ፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለመላው የኪነጥበብ ማህበረሰብ መጽናናትን እመኛለሁ" ብሏል።
ቴዲ አፍሮ አክሎም ሰማኸኝ በለው የባህል ሙዚቃውን በአንቱታ ያገለገለ እና በኪነጥበቡ ዓለም ትልቅ አሻራ ጥሎ ያለፈ ሰው መሆኑን በማውሳት፣ "ነፍሱ በገነት ትረፍ፤ ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር፤ ፍቅር ያሸንፋል" በማለት መልእክቱን አጠናቋል።
የድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ህልፈት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ኢንዱስትሪ በታላቅ ሐዘን ውስጥ የጣለ ክስተት ሆኗል። አርቲስቱ በተለይም በባህል ሙዚቃው ዘርፍ የነበረው የላቀ አስተዋጽኦ ለዘመናት በኪነጥበብ አፍቃሪዎች ዘንድ ሲዘከር የሚኖር ነው። የድምጻዊውን ማለፍ አስመልክቶ ቴዲ አፍሮን ጨምሮ በርካታ የሙያ ባልደረቦቹ እና አድናቂዎቹ የህመም እና የሀዘን መግለጫዎችን በመላክ ላይ ይገኛሉ።
9 days ago
በትውልድ አከባቢው ምሳሌ የነበረው ሃኪም ራሱን አጠፋ
በሲዳማ ክልል ከኩታዮ ቀበሌ ፈልቆ፣ በኦሳ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ብርሃኑን ማብራት የጀመረው ድንቅ ኮከብ፤ የማትሪክ ውጤቱን ሰቅሎ ለአካባቢው አይንና ኩራት የሆነው ወጣት ምሳሌ ቡዙነህ በድንገት ተለየን።
በአርሲ ዩኒቨርስቲ የሕክምና ትምህርት ክፍልን በመቀላቀል በማዕረግ (With Distinction) የተመረቀ የነገ ትልቅ ተስፋ የነበረው ባለሙያ ነበር።
ለቤተሰቦቹ ብቸኛ ወንድ ልጅ በመሆኑ ከምንም በላይ የሚሳሱለት፣ በአካባቢው ታላላቅ ልጆች ዘንድ "ተከታያችን" ተብሎ ትልቅ ተስፋ የተጣለበት፣ ታናናሾቹም እንደ ስሙ 'ምሳሌ' አድርገው የሚያዩት እጅግ ትሁት እና ከተባለው በላይ Excellent ልጅ ነበረ።
በቅርቡ በሞጆ አካባቢ በሚገኝ የሕክምና ተቋም ውስጥ በሙያው ማኅበረሰቡን ማገልገል ጀምሮ እንደነበር ሰምተን ሳይጠገብ፣ ትናንትና አመሻሽ ግን ሕይወት አዳኝ በነበሩት በእነዚያ ጎበዝ እጆቹ በራሱ ላይ ጨክኖ ሕይወቱን ማጥፋቱን ስንሰማ ልባችን በሐዘን ተሰበረ። ኦሳ መብራቷን አጥታለች፤ ሎካም የነገ ተስፋዋን ተነጥቃለች።
የውድ ልጃችን ሃኪም ምሳሌ ቡዙነህ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በነገው ዕለት በተወለደበት በኩታዮ ቀበሌ ልዩ ስሙ 'ባዲቻ' በሚባለው ቦታ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ይፈጸማል።
ለተከበሩ ቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለጠቅላላው የኦሳ፣ የኩታዮ እና የሎካ ማኅበረሰብ ጥልቅ መጽናናትን እንመኛለን።
ነፍስህን በአጸደ ገነት ያኑራት ምሳሌ! 🕊️🕯️
Via: ምሳሌ ፈንታ
በሲዳማ ክልል ከኩታዮ ቀበሌ ፈልቆ፣ በኦሳ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ብርሃኑን ማብራት የጀመረው ድንቅ ኮከብ፤ የማትሪክ ውጤቱን ሰቅሎ ለአካባቢው አይንና ኩራት የሆነው ወጣት ምሳሌ ቡዙነህ በድንገት ተለየን።
በአርሲ ዩኒቨርስቲ የሕክምና ትምህርት ክፍልን በመቀላቀል በማዕረግ (With Distinction) የተመረቀ የነገ ትልቅ ተስፋ የነበረው ባለሙያ ነበር።
ለቤተሰቦቹ ብቸኛ ወንድ ልጅ በመሆኑ ከምንም በላይ የሚሳሱለት፣ በአካባቢው ታላላቅ ልጆች ዘንድ "ተከታያችን" ተብሎ ትልቅ ተስፋ የተጣለበት፣ ታናናሾቹም እንደ ስሙ 'ምሳሌ' አድርገው የሚያዩት እጅግ ትሁት እና ከተባለው በላይ Excellent ልጅ ነበረ።
በቅርቡ በሞጆ አካባቢ በሚገኝ የሕክምና ተቋም ውስጥ በሙያው ማኅበረሰቡን ማገልገል ጀምሮ እንደነበር ሰምተን ሳይጠገብ፣ ትናንትና አመሻሽ ግን ሕይወት አዳኝ በነበሩት በእነዚያ ጎበዝ እጆቹ በራሱ ላይ ጨክኖ ሕይወቱን ማጥፋቱን ስንሰማ ልባችን በሐዘን ተሰበረ። ኦሳ መብራቷን አጥታለች፤ ሎካም የነገ ተስፋዋን ተነጥቃለች።
የውድ ልጃችን ሃኪም ምሳሌ ቡዙነህ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በነገው ዕለት በተወለደበት በኩታዮ ቀበሌ ልዩ ስሙ 'ባዲቻ' በሚባለው ቦታ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ይፈጸማል።
ለተከበሩ ቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለጠቅላላው የኦሳ፣ የኩታዮ እና የሎካ ማኅበረሰብ ጥልቅ መጽናናትን እንመኛለን።
ነፍስህን በአጸደ ገነት ያኑራት ምሳሌ! 🕊️🕯️
Via: ምሳሌ ፈንታ
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ታዋቂው የእስልምና ሃይማኖት መምህር ኡስታዝ ያሲን ኑሩ በምስራቅ አርሲ ዞን በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ጥቃት አጥብቀው በማውገዝ የተሰማቸውን ጥልቅ እና መሪር ሐዘን ገልጸዋል። ኡስታዙ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት "ምነው የተከበረው የሰው ልጅ ህይወት እንዲህ ረከሰ?" በማለት በመገረም፣ ድርጊቱን የዜጎችን ነፍስ ለርካሽ ዓለማዊ ግብ ማሳኪያነት ለመጠቀም የሚደረግ "ሀገር አጥፊ" ተግባር ሲሉ በጽኑ ኮንነውታል።
የብዝሃ ሃይማኖት እና ብሔር ብሔረሰቦች እናት የሆነችውን ሀገራችንን ሰላም ለማናጋት፣ እንዲሁም ለዘመናት የተገነባውን የሕዝቦች የጠበቀ ትስስር ለመበጠስ ያሰፈሰፉ ኃይሎች የሚያደርጉትን ጥፋት ያወገዙት ኡስታዝ ያሲን፤ የሚመለከተው የመንግሥት አካል አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል። የሚመለከታቸው አካላት ይህንን የሀገር ዕድገት የሚገታ እኩይ ተግባር በማስቆም፣ የዜጎችን በሰላም ወጥቶ የመግባት ሰብዓዊ መብት ማረጋገጥ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ዜጎች በሰላም ወጥተው ስለመግባታቸው መተማመኛ የሌላቸውን ሀገር ወደፊት የመራመድ እና የማደግ ዕድሏ የመነመነ መሆኑን ያስገነዘቡት ኡስታዙ፣ "ስለ ሀገሬ ያገባኛል፣ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ 'ሀይ' ሊል ይገባል" ሲሉ ሁሉም ዜጋ የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
"እንዲህ ዓይነቱን አስነዋሪ ድርጊት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በሕዝቦች መካከል አለመተማመንን የሚዘሩ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የጉዳዩን አደገኛነት ተገንዝበው ቆም ብለው እንዲያስቡ እና ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ኡዝታዙ አበክረው መክረዋል።
ፈጣሪ የተበዳዮችን እምባ እንዲያብስ፣ ለበዳዮችም የእጃቸውን እንዲሰጣቸው እና በሀገሪቱ ፍትሕን እንዲያሰፍን ጸሎት በማድረግ መልእክታቸውን አጠቃልለዋል።
የብዝሃ ሃይማኖት እና ብሔር ብሔረሰቦች እናት የሆነችውን ሀገራችንን ሰላም ለማናጋት፣ እንዲሁም ለዘመናት የተገነባውን የሕዝቦች የጠበቀ ትስስር ለመበጠስ ያሰፈሰፉ ኃይሎች የሚያደርጉትን ጥፋት ያወገዙት ኡስታዝ ያሲን፤ የሚመለከተው የመንግሥት አካል አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል። የሚመለከታቸው አካላት ይህንን የሀገር ዕድገት የሚገታ እኩይ ተግባር በማስቆም፣ የዜጎችን በሰላም ወጥቶ የመግባት ሰብዓዊ መብት ማረጋገጥ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ዜጎች በሰላም ወጥተው ስለመግባታቸው መተማመኛ የሌላቸውን ሀገር ወደፊት የመራመድ እና የማደግ ዕድሏ የመነመነ መሆኑን ያስገነዘቡት ኡስታዙ፣ "ስለ ሀገሬ ያገባኛል፣ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ 'ሀይ' ሊል ይገባል" ሲሉ ሁሉም ዜጋ የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
"እንዲህ ዓይነቱን አስነዋሪ ድርጊት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በሕዝቦች መካከል አለመተማመንን የሚዘሩ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የጉዳዩን አደገኛነት ተገንዝበው ቆም ብለው እንዲያስቡ እና ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ኡዝታዙ አበክረው መክረዋል።
ፈጣሪ የተበዳዮችን እምባ እንዲያብስ፣ ለበዳዮችም የእጃቸውን እንዲሰጣቸው እና በሀገሪቱ ፍትሕን እንዲያሰፍን ጸሎት በማድረግ መልእክታቸውን አጠቃልለዋል።
16 days ago
ምነው የተከበረው የሰው ልጅ ህይዋት እንዲህ እረከሰ ?!!!
ደመ*ና—ደም መና!!
በምስራቅ አርሲ በውድ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ጥቃት በመስማቴ የተሰማኝን ጥልቅና መሪር ሐዘን ለመግለፅ እወዳለሁ።
የብዝኃ ኃይማኖትና ብሔር ብሔረሰቦች እናት የሆነችውን ሀገራችንን ሰላም ለማናጋት፤ ለዘመናት የተገነባውን የሕዝቦች የእርስ በርስ የጠበቀ ትስስር ለመበጠስ፤ ብሎም የዜጎችን ነፍስ ለርካሽ ዓለማዊ ግባቸው ማሳኪያ ለመጠቀም ያሰፈሰፉ እኩያን በተደጋጋሚ እየፈፀሙት ያለውን ሀገር አጥፊ ድርጊት አጥብቄ እኮንናለሁ። አወግዛለሁም።
የሰውን ልጅ ክቡር ህይዎት የሚያጠፉና የሃገራችን ኢትዮጵያን ዕድገት የሚገታ እኩይ ተግባር ላይ ተሰማርተው በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እየፈፀሙት ያለውን መጠነ ሰፊ ጥፋት የሚመለከተው አካል አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ የዜጎችን በሰላም ወጥቶ የመግባት ሰብዓዊ መብት ማረጋገጥ ይገባዋል።
በሰላም ወጥተው ስለመግባታቸው መተማመኛ የሌላቸውን ዜጎች ያቀፈች ሀገር ወደፊት የመራመድ ዕድሏ የቀጨጨ፣ የማደግ ተስፋዋ የመነመነ ነውና ስለ ሀገሬ ያገባኛል፣ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ ‹ሀይ› ሊል ይገባል።
ከምንም በላይ ደሞ መሰል አስነዋሪ ድርጊቶችን እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም በሕዝቦች መካከል አለመተማመንን የሚዘሩ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የጉዳዩን አደገኛነት ከግምት በማስገባት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ቆም ብለው እንዲያስቡ አበክሬ ለመግለፅ እወዳለሁ።
አላህ የተበዳዮችን እምባ እንዲያብስ፤ ለበዳዮችም የእጃቸውን እንዲሰጣቸውና ፍትሕን እንዲያሰፍንልን የበረታ ዱዓዬ ነው።
ሰላም ለሀገራችን!
(ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ል)
ኡስታዝ ያሲን ኑሩ
ደመ*ና—ደም መና!!
በምስራቅ አርሲ በውድ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ጥቃት በመስማቴ የተሰማኝን ጥልቅና መሪር ሐዘን ለመግለፅ እወዳለሁ።
የብዝኃ ኃይማኖትና ብሔር ብሔረሰቦች እናት የሆነችውን ሀገራችንን ሰላም ለማናጋት፤ ለዘመናት የተገነባውን የሕዝቦች የእርስ በርስ የጠበቀ ትስስር ለመበጠስ፤ ብሎም የዜጎችን ነፍስ ለርካሽ ዓለማዊ ግባቸው ማሳኪያ ለመጠቀም ያሰፈሰፉ እኩያን በተደጋጋሚ እየፈፀሙት ያለውን ሀገር አጥፊ ድርጊት አጥብቄ እኮንናለሁ። አወግዛለሁም።
የሰውን ልጅ ክቡር ህይዎት የሚያጠፉና የሃገራችን ኢትዮጵያን ዕድገት የሚገታ እኩይ ተግባር ላይ ተሰማርተው በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እየፈፀሙት ያለውን መጠነ ሰፊ ጥፋት የሚመለከተው አካል አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ የዜጎችን በሰላም ወጥቶ የመግባት ሰብዓዊ መብት ማረጋገጥ ይገባዋል።
በሰላም ወጥተው ስለመግባታቸው መተማመኛ የሌላቸውን ዜጎች ያቀፈች ሀገር ወደፊት የመራመድ ዕድሏ የቀጨጨ፣ የማደግ ተስፋዋ የመነመነ ነውና ስለ ሀገሬ ያገባኛል፣ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ ‹ሀይ› ሊል ይገባል።
ከምንም በላይ ደሞ መሰል አስነዋሪ ድርጊቶችን እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም በሕዝቦች መካከል አለመተማመንን የሚዘሩ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የጉዳዩን አደገኛነት ከግምት በማስገባት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ቆም ብለው እንዲያስቡ አበክሬ ለመግለፅ እወዳለሁ።
አላህ የተበዳዮችን እምባ እንዲያብስ፤ ለበዳዮችም የእጃቸውን እንዲሰጣቸውና ፍትሕን እንዲያሰፍንልን የበረታ ዱዓዬ ነው።
ሰላም ለሀገራችን!
(ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ል)
ኡስታዝ ያሲን ኑሩ
Sponsored by
Surafel
16 days ago
ሰላም! እንደምን አደራችሁ?
ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራቸውን መንግሥት ለመምረጥ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 ቀን ከማለዳ ጀምሮ እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
ዜጎች በየአካባቢው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት÷ ኢትዮጵያውያን ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ለሀገረ መንግሥት ምስረታ ያላቸውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩበት ሆኖ አልፏል።
በሚሊየን የሚቆጠሩ መራጮች በነቂስ ወጥተው ዝናብና ጸሐይን እንዲሁም ከተለያዩ አካላት የሚነዙ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችንና ዛቻዎችን ሳያዳምጡ በረጃጅም ሰልፎች ተሰልፈው ውሳኔያቸውን አስተላልፈዋል።
በሕመም አልጋ ላይ የነበሩ ከሕመማቸው ጋር እየታገሉ፣ ሐዘን የገጠማቸውም ከሐዘናቸው ተነስተው በመውጣት ለነጋቸው የሚበጀውን ድምፅ የሰጡበት ዕለት ነው ግንቦት 24።
በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ ለመሳተፍ በሚያስችል ዕድሜ ላይ የሚገኙ ከ54 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተመዝግበው ከ10 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎችና 80 የግል ዕጩዎች በተወዳደሩበት ምርጫ ድምጻቸውን በመስጠት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል።
የምርጫውን ግልጽነት፣ አሳታፊነትና ተዓማኒነት ከፍ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን÷ ከእነዚህም መካከል ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ሚና ያላቸውና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ ያገኙ 68 የመገናኛ ብዙኃን ተሰማርተዋል፤ ከእነዚህ ውስጥ 12ቱ የውጭ መገናኛ ብዙኃን ናቸው።
በተጨማሪም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድምፅ አሰጣጥና የውጤት ቆጠራ ሂደቱን በቅርበት ለመከታተል ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን በየምርጫ ጣቢያዎቹ መድበዋል።
በሌላ በኩል የኬንያ ቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራውና 59 አባላትን የያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እንዲሁም 26 አባላትን ያሰማራው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመሰማራት ሂደቱን በንቃት ታዝበዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ÷ የምርጫው ድምፅ የመስጠት ሂደት በስኬት መጠናቀቁንና በየምርጫ ጣቢያዎቹ የምርጫ ውጤቶችን ለሕዝብ የመለጠፍ ሥራዎች በይፋ መከናወናቸውን አረጋግጠዋል።
ይህም ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል ለመወሰን መካሪና ገሳጭ እንደማያስፈልጋት በድጋሚ ያሳየበት ነው።
በድምፅ መስጫው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመራጩ ሕዝብ በላይ የተመራጮች ጉዳይና ኃላፊነት ይበልጥ እንደሚያሳስባቸው መግለጻቸው ይታወሳል።
በመሆኑም ሕዝብ ያሳየውን ፅኑ እምነትና የዴሞክራሲ ፍላጎት ሳይሸረሽር፣ በታማኝነትና በንጹሕ ልብ ማገልገል የነገው መንግሥት ቀዳሚ የቤት ሥራ እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንዖት ሰጥተዋል።
የሕዝቡን ሕይወት የሚነካና የሀገሪቱን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን እውነተኛ ለውጥ ማምጣት የሚቻለውም ተመራጮች የተጣለባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት በትክክል ተረድተው ሲሰናዱ ብቻ በመሆኑ የኢትዮጵያ ቀጣይ አምስት ዓመታት ጉዞ በዚሁ የተመራጮች የዝግጁነት ሚዛን ላይ የሚያርፍ ይሆናል።
ኢትዮጵያ መርጣለች፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!!
ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራቸውን መንግሥት ለመምረጥ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 ቀን ከማለዳ ጀምሮ እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
ዜጎች በየአካባቢው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት÷ ኢትዮጵያውያን ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ለሀገረ መንግሥት ምስረታ ያላቸውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩበት ሆኖ አልፏል።
በሚሊየን የሚቆጠሩ መራጮች በነቂስ ወጥተው ዝናብና ጸሐይን እንዲሁም ከተለያዩ አካላት የሚነዙ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችንና ዛቻዎችን ሳያዳምጡ በረጃጅም ሰልፎች ተሰልፈው ውሳኔያቸውን አስተላልፈዋል።
በሕመም አልጋ ላይ የነበሩ ከሕመማቸው ጋር እየታገሉ፣ ሐዘን የገጠማቸውም ከሐዘናቸው ተነስተው በመውጣት ለነጋቸው የሚበጀውን ድምፅ የሰጡበት ዕለት ነው ግንቦት 24።
በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ ለመሳተፍ በሚያስችል ዕድሜ ላይ የሚገኙ ከ54 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተመዝግበው ከ10 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎችና 80 የግል ዕጩዎች በተወዳደሩበት ምርጫ ድምጻቸውን በመስጠት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል።
የምርጫውን ግልጽነት፣ አሳታፊነትና ተዓማኒነት ከፍ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን÷ ከእነዚህም መካከል ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ሚና ያላቸውና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ ያገኙ 68 የመገናኛ ብዙኃን ተሰማርተዋል፤ ከእነዚህ ውስጥ 12ቱ የውጭ መገናኛ ብዙኃን ናቸው።
በተጨማሪም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድምፅ አሰጣጥና የውጤት ቆጠራ ሂደቱን በቅርበት ለመከታተል ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን በየምርጫ ጣቢያዎቹ መድበዋል።
በሌላ በኩል የኬንያ ቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራውና 59 አባላትን የያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እንዲሁም 26 አባላትን ያሰማራው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመሰማራት ሂደቱን በንቃት ታዝበዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ÷ የምርጫው ድምፅ የመስጠት ሂደት በስኬት መጠናቀቁንና በየምርጫ ጣቢያዎቹ የምርጫ ውጤቶችን ለሕዝብ የመለጠፍ ሥራዎች በይፋ መከናወናቸውን አረጋግጠዋል።
ይህም ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል ለመወሰን መካሪና ገሳጭ እንደማያስፈልጋት በድጋሚ ያሳየበት ነው።
በድምፅ መስጫው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመራጩ ሕዝብ በላይ የተመራጮች ጉዳይና ኃላፊነት ይበልጥ እንደሚያሳስባቸው መግለጻቸው ይታወሳል።
በመሆኑም ሕዝብ ያሳየውን ፅኑ እምነትና የዴሞክራሲ ፍላጎት ሳይሸረሽር፣ በታማኝነትና በንጹሕ ልብ ማገልገል የነገው መንግሥት ቀዳሚ የቤት ሥራ እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንዖት ሰጥተዋል።
የሕዝቡን ሕይወት የሚነካና የሀገሪቱን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን እውነተኛ ለውጥ ማምጣት የሚቻለውም ተመራጮች የተጣለባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት በትክክል ተረድተው ሲሰናዱ ብቻ በመሆኑ የኢትዮጵያ ቀጣይ አምስት ዓመታት ጉዞ በዚሁ የተመራጮች የዝግጁነት ሚዛን ላይ የሚያርፍ ይሆናል።
ኢትዮጵያ መርጣለች፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!!
17 days ago
በአርሲ ሀገረ ስብከት በደረሰ ጥቃት የ13 ሰዎች ሕይወት አለፈ የአንድ ክፍለ ዘመን ዕድሜ ያለው ቤተ ክርስቲያንም ወደመ
የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚዲያን ጠቅሶ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ጥቃቱ የተፈጸመው ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአሰኮ፣ በሺርካ እና በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ላይ ነው። በጥቃቱ ሳቢያ የ101 ዓመት ዕድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት የፈረሰ ሲሆን፣ በካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይ ደግሞ ከፍተኛ ዘረፋ ተፈጽሟል። በዚህም ምክንያት ምእመናን የቤተ ክርስቲያኑን ጽላት ይዘው ለመሰደድ ተገድደዋል።
ብፁዕነታቸው እንደገለጹት፣ በጥቃቱ ሳቢያ በአሰኮ ወረዳ ብቻ ከ280 በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ የነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶች ተቃጥለዋል፤ ከብቶቻቸውና ንብረቶቻቸውም ተዘርፈዋል።
"ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በማንነታቸውና በሃይማኖታቸው ብቻ እየተለዩ ጥቃት ደርሶባቸዋል" ያሉት ሊቀ ጳጳሱ፣ ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎች ይዘውት የሸሹት እምነታቸውን ብቻ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት ሜዳ ላይ ወድቀው ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን ጠቁመዋል።
በተፈጸመው በዚህ ጥቃት ሕይወታቸውን ያጡት 13ቱ ሰዎች ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦
1. አቶ ደምረው አበራ (የ70 ዓመት)
2. አቶ ከፈለኝ ልክየለው (የ56 ዓመት)
3. አቶ ሐይሉ ንጉሴ (የ70 ዓመት)
4. አቶ እሸቴ ዳመና (የ42 ዓመት)
5. አቶ አበባየሁ ዳኜ (የ42 ዓመት)
6. አቶ ሰሙ አባይነህ (የ70 ዓመት)
7. ስማቸው ያልተጠቀሰ 1 የአካባቢው ሚሊሻ
8. አቶ አማረ በላይነህ (የ80 ዓመት)
9. ተሬ ደሴ (የ25 ዓመት)
10. ወጣት ገነነ ጥላሁን (በሺርካ ወረዳ)
11. ሙርቴሳ ጥላሁን (በሺርካ ወረዳ)
12. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ (በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ)
13. አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል (በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ)
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በተፈጸመው አረመኔያዊ ድርጊት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ፣ "የሞቱትን ወገኖቻችንን እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን፤ ያዘኑትን እና በሜዳ ላይ ወድቀው የሚገኙትን የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን እግዚአብሔር ያጽናናልን" ሲሉ የጸሎትና የማጽናኛ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚዲያን ጠቅሶ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ጥቃቱ የተፈጸመው ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአሰኮ፣ በሺርካ እና በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ላይ ነው። በጥቃቱ ሳቢያ የ101 ዓመት ዕድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት የፈረሰ ሲሆን፣ በካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይ ደግሞ ከፍተኛ ዘረፋ ተፈጽሟል። በዚህም ምክንያት ምእመናን የቤተ ክርስቲያኑን ጽላት ይዘው ለመሰደድ ተገድደዋል።
ብፁዕነታቸው እንደገለጹት፣ በጥቃቱ ሳቢያ በአሰኮ ወረዳ ብቻ ከ280 በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ የነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶች ተቃጥለዋል፤ ከብቶቻቸውና ንብረቶቻቸውም ተዘርፈዋል።
"ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በማንነታቸውና በሃይማኖታቸው ብቻ እየተለዩ ጥቃት ደርሶባቸዋል" ያሉት ሊቀ ጳጳሱ፣ ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎች ይዘውት የሸሹት እምነታቸውን ብቻ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት ሜዳ ላይ ወድቀው ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን ጠቁመዋል።
በተፈጸመው በዚህ ጥቃት ሕይወታቸውን ያጡት 13ቱ ሰዎች ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦
1. አቶ ደምረው አበራ (የ70 ዓመት)
2. አቶ ከፈለኝ ልክየለው (የ56 ዓመት)
3. አቶ ሐይሉ ንጉሴ (የ70 ዓመት)
4. አቶ እሸቴ ዳመና (የ42 ዓመት)
5. አቶ አበባየሁ ዳኜ (የ42 ዓመት)
6. አቶ ሰሙ አባይነህ (የ70 ዓመት)
7. ስማቸው ያልተጠቀሰ 1 የአካባቢው ሚሊሻ
8. አቶ አማረ በላይነህ (የ80 ዓመት)
9. ተሬ ደሴ (የ25 ዓመት)
10. ወጣት ገነነ ጥላሁን (በሺርካ ወረዳ)
11. ሙርቴሳ ጥላሁን (በሺርካ ወረዳ)
12. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ (በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ)
13. አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል (በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ)
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በተፈጸመው አረመኔያዊ ድርጊት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ፣ "የሞቱትን ወገኖቻችንን እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን፤ ያዘኑትን እና በሜዳ ላይ ወድቀው የሚገኙትን የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን እግዚአብሔር ያጽናናልን" ሲሉ የጸሎትና የማጽናኛ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
17 days ago
የሀዘን መግለጫ
እስመ በእንቲአከ ይቀትሉነ ኩሎ አሚረ::
ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ መዝ 43:22
"ስለ አንተ ሁልጊዜም ተገድለናል እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል። መዝ 43:22
Waa'ee Keetif Yeroo Hunda Duuna, Akka Hoolota qalamaniis Taane. Far 43:22
ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ:ም ጀምሮ በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ ወረዳ; በሺርካ ወረዳና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 13 ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ
የ101 ዓመት እድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።
የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል።
የተገደሉ ሰዎች ስም ዝርዝርም
1. አቶ ደምረው አበራ የ70 ዓመት
2. ከፈለኝ ልክየለው የ56ዓመት
3. ሐይሉ ንጉሴ የ70 ዓመት
4. እሸቴ ዳመና የ42 ዓመት
5. አበባየሁ ዳኜ የ42 ዓመት
6. ሰሙ አባይነህ የ70 ዓመት
7. 1 ሚሊሻ
8. አማረ በላይነህ የ80 ዓመት
9. ተሬ ደሴ የ25 ዓመት
10. ወጣት ገነነ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ
11. ሙርቴሳ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ
12. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ
13. አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ
በአጠቃላይ የ13 ሰዎች ህይወት አልፈዋል።
በተጨማሪ በአሰኮ ወረዳ ከ280 ሰው በላይ ተፈናቅለዋል::
በመሆኑም ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በሃይማኖታቸው ብቻ ቤታቸው እየተለየ ተቃጥሏል፤ ንብረታቸውና ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል። ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎችም ይዘውት የሸሹት እምነታቸውንና ማንነታቸውን ብቻ በመሆኑ አሁን ላይ ሜዳ ላይ ወድቀው ይገኛሉ
ስለዚህ በተፈጸመው ጥቃት የተሰማነን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን የሞቱትን ወገኖቻችን (ልጆቻችን) እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን ይማርልን (በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን) የዘኑትን እና የተፈናቀሉትን ወገኖቻችን(ልጆቻችን)
እግዚአብሔር ያጽናናልን።
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል።
© Arsi Diocese Public Relations Department
© Biyya Lallaba Arsiitti Kutaa Sab-Qunnamtii
© የአርሲ ሀገረ ስብከት ህዝብ ግንኙነት ክፍል
© የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚድያ Miidiyaa Biyya Lallaba Arsii ...✍️
👉 Liinkii Gadii Kana Hordofuudhan Gara Chaanaaliiwwan Miidiyaa Keenyatti Dabalamaa
👉 ከታች ያሉትን ሊንክ በመጫን ወደ ቻናሎቻችን ተቀላቀሉ
👉 FACEBOOK👇👇👇👇👇ፌስቡክ
https://www.facebook.com/s...
👉 TIKTOK👇👇👇👇👇ቲክቶት
tiktok.com/miidiyaa.ku.la.arsii
WhatsApp 👇👇👇👇👇ዋትሳፕ
https://whatsapp.com/chann...
Inistagram👇👇👇👇👇ኢንስታግራም
https://www.instagram.com/...
Telegram Chanal 👇👇👇👇👇ቴሌግራም
https://t.me/Arsi21
Telegram Group👇👇👇የግሩፕ ቴሌግራም
https://t.me/+do8_6-C5_ek4...
Telegram Cominicate
BIYYALALLABAARSII
IMO👇👇👇👇👇ኢሞ
https://call.imo.im/BiyyaL...
እስመ በእንቲአከ ይቀትሉነ ኩሎ አሚረ::
ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ መዝ 43:22
"ስለ አንተ ሁልጊዜም ተገድለናል እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል። መዝ 43:22
Waa'ee Keetif Yeroo Hunda Duuna, Akka Hoolota qalamaniis Taane. Far 43:22
ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ:ም ጀምሮ በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ ወረዳ; በሺርካ ወረዳና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 13 ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ
የ101 ዓመት እድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።
የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል።
የተገደሉ ሰዎች ስም ዝርዝርም
1. አቶ ደምረው አበራ የ70 ዓመት
2. ከፈለኝ ልክየለው የ56ዓመት
3. ሐይሉ ንጉሴ የ70 ዓመት
4. እሸቴ ዳመና የ42 ዓመት
5. አበባየሁ ዳኜ የ42 ዓመት
6. ሰሙ አባይነህ የ70 ዓመት
7. 1 ሚሊሻ
8. አማረ በላይነህ የ80 ዓመት
9. ተሬ ደሴ የ25 ዓመት
10. ወጣት ገነነ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ
11. ሙርቴሳ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ
12. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ
13. አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ
በአጠቃላይ የ13 ሰዎች ህይወት አልፈዋል።
በተጨማሪ በአሰኮ ወረዳ ከ280 ሰው በላይ ተፈናቅለዋል::
በመሆኑም ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በሃይማኖታቸው ብቻ ቤታቸው እየተለየ ተቃጥሏል፤ ንብረታቸውና ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል። ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎችም ይዘውት የሸሹት እምነታቸውንና ማንነታቸውን ብቻ በመሆኑ አሁን ላይ ሜዳ ላይ ወድቀው ይገኛሉ
ስለዚህ በተፈጸመው ጥቃት የተሰማነን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን የሞቱትን ወገኖቻችን (ልጆቻችን) እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን ይማርልን (በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን) የዘኑትን እና የተፈናቀሉትን ወገኖቻችን(ልጆቻችን)
እግዚአብሔር ያጽናናልን።
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል።
© Arsi Diocese Public Relations Department
© Biyya Lallaba Arsiitti Kutaa Sab-Qunnamtii
© የአርሲ ሀገረ ስብከት ህዝብ ግንኙነት ክፍል
© የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚድያ Miidiyaa Biyya Lallaba Arsii ...✍️
👉 Liinkii Gadii Kana Hordofuudhan Gara Chaanaaliiwwan Miidiyaa Keenyatti Dabalamaa
👉 ከታች ያሉትን ሊንክ በመጫን ወደ ቻናሎቻችን ተቀላቀሉ
👉 FACEBOOK👇👇👇👇👇ፌስቡክ
https://www.facebook.com/s...
👉 TIKTOK👇👇👇👇👇ቲክቶት
tiktok.com/miidiyaa.ku.la.arsii
WhatsApp 👇👇👇👇👇ዋትሳፕ
https://whatsapp.com/chann...
Inistagram👇👇👇👇👇ኢንስታግራም
https://www.instagram.com/...
Telegram Chanal 👇👇👇👇👇ቴሌግራም
https://t.me/Arsi21
Telegram Group👇👇👇የግሩፕ ቴሌግራም
https://t.me/+do8_6-C5_ek4...
Telegram Cominicate
BIYYALALLABAARSII
IMO👇👇👇👇👇ኢሞ
https://call.imo.im/BiyyaL...
26 days ago
አብረን ከርመን አብረን ሳንሆን ቀረን!
ፋናን እንደተቀላቀልኩ አንድ ሳምንት የተሻገረኝ አይመስለኝም። በወቅቱ 7ኛ ፎቅ ላይ ከነበረው የጋዜጠኞች መሥሪያ (Workstation) እና መሰባሰቢያ ቦታ ተቀምጦ የነበረ አንድ ባለ ጆሮ-ገብ ድምፅ ከወትሮ በተለየ ስሜት ውስጥ ሆኖ ወደ ተቀመጠበት እንድጠጋው በእጁ አመለከተኝ። እዚያ ተቋም ስንገናኝ ለሁለተኛ ጊዜ ቢሆንም፣ ሰላምታውና አቀባበሉ ለከረመ ወዳጅ ይመስል ነበር።
የግራ እጁን ሁለት ጣቶች አገጩ ላይ ጭኖ፣ በቀኝ እጁ ከደረቱ ትይዩ ካስቀመጠው ወፍራም የግል ኮምፒውተር (PC) “መለስተኛ ሳጥን ብንለው😂” ውስጥ ፋይል መበርበር ጀመረ። “ይሄ ልጅ ከተዋወቅን ገና ሁለተኛ ሰላምታ ስሰጠው ነው፤ ምን ይዞብኝ ይሆን?” ብዬ ሳስብ፣ ከመቅጽበት የሆነ ፎቶ አወጣና፣ “ይሄ ልጅ አንተ ነህ አይደል?” አለኝ።
ፎቶውን ሳይ እራሴን ለመካድ ዳዳኝ። ለካስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ እያለን፣ እነሱ ከአ/አ ዩኒቨርሲቲ ለትምህርታዊ ጉዞ ወደ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በመጡ ጊዜ፣ የJOCOSA ፕሬዝዳንት ስለነበርኩ አቀባበልና ግብዣ (የውሃ😂) አድርጌላቸው ነበር። በዚያ ጊዜ ያስቀረነውን ፎቶ ነው መዞ ያሳየኝ። እኔ ግን በፍጹም አላስታወስኩትም ነበር። የተማሪነት ጊዜው አዳነ ከጋዜጠኛው አዳነ ጋር የተራራቁ ናቸው።
ከአዴ ጋር የጓደኝነት ውላችን ከዚያች ቀን የጀመረ ይመስለኛል። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ደስ የሚል ቤተሰባዊ ጓደኝነት ፈጥረን ኖረናል። በእኔ ወሳኝ ደስታና ሐዘን ውስጥ እሱ አለ፤ እኔም በተመሳሳይ።
እኔ ባለቤቴን ሳጭ፣ ሽምግልና ከሄዱት ውስጥ አዴ አንዱ ነው። ሳገባም ሚዜዬ ነበር። በተቃራኒው፣ እሱ “እጮኛውን ታገቢኛለሽ?” ሲል ከተገኙት ጥቂት ወዳጆቹ መካከል እኔ ነበርኩ። ሽምግልና ከሄዱት ታላላቅ ሰዎች መካከልም ተገኝቻለሁ።ይሄን ጋብቻ በህግ ለማፅናት ቀበሌ ተገኝተው የጋብቻ ውል(80) ሲፈራረሙም አንዱ እማኝ ነበርኩ።
ይህን ሂደት በታላቅ ሥርዓት ለመቋጨትና ለሰርጉ ሲሰናዳም፣ ሚዜው ሆኜ ከአጠገቡ ለመቆም እኔ ብቻ ሳልሆን፣ ውድ ባለቤቴም የእሱ ባለቤት ሚዜ ሆና የማይረሳውን ቀን በጋራ ለማሳለፍ አቅደን፣ ልብስ ተለክተን፣ መኪና ተከራይተን ዝግጁ ብንሆንም፣ ሰርጉ ሳምንት ሲቀረው በሥራ ምክንያት ከአገር መውጣት ግዴታ ሆነብኝ።
ከዓመታት በፊት ማግባቱን ሲወስንና ሲያሳውቀኝ፣ ቀን ቆጥረን የጋብቻ እቅድ አውጥተን፣ እንደ ወንድም ቀኑን በጋራ ናፍቀን እንደከረምን ሰዎች፣ በዚህ ውብ ቀን አጠገቡ አለመቆም የሚፈጥረው ስሜት ከባድ ቢሆንም፣ መልካም ምኞትን ከማስፈር ውጪ ሌላ አማራጭ የለም።
አዴ እና B2 መልካም ጋብቻ እንዲሆንላችሁ ከውዷ ባለቤቴ ጋር እንመኝላችኋለን።
Haikemikael_Debisa
ፋናን እንደተቀላቀልኩ አንድ ሳምንት የተሻገረኝ አይመስለኝም። በወቅቱ 7ኛ ፎቅ ላይ ከነበረው የጋዜጠኞች መሥሪያ (Workstation) እና መሰባሰቢያ ቦታ ተቀምጦ የነበረ አንድ ባለ ጆሮ-ገብ ድምፅ ከወትሮ በተለየ ስሜት ውስጥ ሆኖ ወደ ተቀመጠበት እንድጠጋው በእጁ አመለከተኝ። እዚያ ተቋም ስንገናኝ ለሁለተኛ ጊዜ ቢሆንም፣ ሰላምታውና አቀባበሉ ለከረመ ወዳጅ ይመስል ነበር።
የግራ እጁን ሁለት ጣቶች አገጩ ላይ ጭኖ፣ በቀኝ እጁ ከደረቱ ትይዩ ካስቀመጠው ወፍራም የግል ኮምፒውተር (PC) “መለስተኛ ሳጥን ብንለው😂” ውስጥ ፋይል መበርበር ጀመረ። “ይሄ ልጅ ከተዋወቅን ገና ሁለተኛ ሰላምታ ስሰጠው ነው፤ ምን ይዞብኝ ይሆን?” ብዬ ሳስብ፣ ከመቅጽበት የሆነ ፎቶ አወጣና፣ “ይሄ ልጅ አንተ ነህ አይደል?” አለኝ።
ፎቶውን ሳይ እራሴን ለመካድ ዳዳኝ። ለካስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ እያለን፣ እነሱ ከአ/አ ዩኒቨርሲቲ ለትምህርታዊ ጉዞ ወደ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በመጡ ጊዜ፣ የJOCOSA ፕሬዝዳንት ስለነበርኩ አቀባበልና ግብዣ (የውሃ😂) አድርጌላቸው ነበር። በዚያ ጊዜ ያስቀረነውን ፎቶ ነው መዞ ያሳየኝ። እኔ ግን በፍጹም አላስታወስኩትም ነበር። የተማሪነት ጊዜው አዳነ ከጋዜጠኛው አዳነ ጋር የተራራቁ ናቸው።
ከአዴ ጋር የጓደኝነት ውላችን ከዚያች ቀን የጀመረ ይመስለኛል። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ደስ የሚል ቤተሰባዊ ጓደኝነት ፈጥረን ኖረናል። በእኔ ወሳኝ ደስታና ሐዘን ውስጥ እሱ አለ፤ እኔም በተመሳሳይ።
እኔ ባለቤቴን ሳጭ፣ ሽምግልና ከሄዱት ውስጥ አዴ አንዱ ነው። ሳገባም ሚዜዬ ነበር። በተቃራኒው፣ እሱ “እጮኛውን ታገቢኛለሽ?” ሲል ከተገኙት ጥቂት ወዳጆቹ መካከል እኔ ነበርኩ። ሽምግልና ከሄዱት ታላላቅ ሰዎች መካከልም ተገኝቻለሁ።ይሄን ጋብቻ በህግ ለማፅናት ቀበሌ ተገኝተው የጋብቻ ውል(80) ሲፈራረሙም አንዱ እማኝ ነበርኩ።
ይህን ሂደት በታላቅ ሥርዓት ለመቋጨትና ለሰርጉ ሲሰናዳም፣ ሚዜው ሆኜ ከአጠገቡ ለመቆም እኔ ብቻ ሳልሆን፣ ውድ ባለቤቴም የእሱ ባለቤት ሚዜ ሆና የማይረሳውን ቀን በጋራ ለማሳለፍ አቅደን፣ ልብስ ተለክተን፣ መኪና ተከራይተን ዝግጁ ብንሆንም፣ ሰርጉ ሳምንት ሲቀረው በሥራ ምክንያት ከአገር መውጣት ግዴታ ሆነብኝ።
ከዓመታት በፊት ማግባቱን ሲወስንና ሲያሳውቀኝ፣ ቀን ቆጥረን የጋብቻ እቅድ አውጥተን፣ እንደ ወንድም ቀኑን በጋራ ናፍቀን እንደከረምን ሰዎች፣ በዚህ ውብ ቀን አጠገቡ አለመቆም የሚፈጥረው ስሜት ከባድ ቢሆንም፣ መልካም ምኞትን ከማስፈር ውጪ ሌላ አማራጭ የለም።
አዴ እና B2 መልካም ጋብቻ እንዲሆንላችሁ ከውዷ ባለቤቴ ጋር እንመኝላችኋለን።
Haikemikael_Debisa
1 month ago
እናት እና ልጅን ጨምሮ ከ30 በላይ ሰዎች የተገደሉበት የመተከል ጥቃት
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማክሰኞ ግንቦት 4/2018 ዓ.ም. በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ከ30 ሰዎች በላይ መገደላቸውን የሟች ቤተሰቦች እና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ።
ይህ በርካታ ሰዎች የተገደሉበት እና ጉዳት የደረሰባቸው ጥቃት የተፈጸመው ከክልሉ ዋና ከተማ አሶሳ መንገደኞችን ባሳፈሩ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ላይ ነው።
በጥቃቱ እስከ 35 የሚሆኑ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸው፣ ከ50 በላይ ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን እንዲሁም ተሽከርካሪዎች መቃጠላቸውን የሆስፒታል ምንጮች እና የሟች ቤተሰቦች ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ከአካባቢው ተመርጠው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር መብራቱ ዓለሙ ጥቃቱን በቅርብ ጊዜ ከተፈፀሙ ሁሉ "አስከፊው ነው" ብለውታል።
ጥቃቱ የተፈጸመው ወደ መተከል ዞን ዋና ከተማ ግልገል በለስ እየተጓዙ በነበሩ አራት ተሽከርካሪዎች ላይ በዳንጉር እና ጉባ ወረዳዎች መካከል ላይ አይሲድ ቀበሌ ወይም አፍሪካ እርሻ ልማት በተባለ ስፍራ ላይ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።
በ20ዎቹ መጨረሻ የምትገኘው እናት ፀሐይነሽ ሳዑዲ አረቢያ ለስምንት ዓመታት ሠርታ የተለመለሰች እና በንግድ ሥራ ላይ የተሰማራች የአሶሳ ከተማ ነዋሪ፤ ህመም ላይ የነበሩ እናቷን ለመጠየቅ ሕጻን ልጇን ይዛ ወደ ቡለን ወረዳ እየተጓዘች በነበረችበት ጊዜ ታጣቂዎቹ በፈጸሙት ጥቃት ከነ ልጇ ከተገደሉት ውስጥ ናቸው።
ሚስቱ እና ልጁ በታጣቂዎች የተገደሉበት ባለቤቷ በከፍተኛ ሐዘን ምክንያት በመረበሹ ራሱን እና ሌሎችን እንዳይጎዳ በሚል "ታስሮ" እንደሚገኝ የቤተሰብ አባሉ ተናግረዋል።
seledadotio
seledadotio
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማክሰኞ ግንቦት 4/2018 ዓ.ም. በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ከ30 ሰዎች በላይ መገደላቸውን የሟች ቤተሰቦች እና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ።
ይህ በርካታ ሰዎች የተገደሉበት እና ጉዳት የደረሰባቸው ጥቃት የተፈጸመው ከክልሉ ዋና ከተማ አሶሳ መንገደኞችን ባሳፈሩ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ላይ ነው።
በጥቃቱ እስከ 35 የሚሆኑ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸው፣ ከ50 በላይ ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን እንዲሁም ተሽከርካሪዎች መቃጠላቸውን የሆስፒታል ምንጮች እና የሟች ቤተሰቦች ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ከአካባቢው ተመርጠው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር መብራቱ ዓለሙ ጥቃቱን በቅርብ ጊዜ ከተፈፀሙ ሁሉ "አስከፊው ነው" ብለውታል።
ጥቃቱ የተፈጸመው ወደ መተከል ዞን ዋና ከተማ ግልገል በለስ እየተጓዙ በነበሩ አራት ተሽከርካሪዎች ላይ በዳንጉር እና ጉባ ወረዳዎች መካከል ላይ አይሲድ ቀበሌ ወይም አፍሪካ እርሻ ልማት በተባለ ስፍራ ላይ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።
በ20ዎቹ መጨረሻ የምትገኘው እናት ፀሐይነሽ ሳዑዲ አረቢያ ለስምንት ዓመታት ሠርታ የተለመለሰች እና በንግድ ሥራ ላይ የተሰማራች የአሶሳ ከተማ ነዋሪ፤ ህመም ላይ የነበሩ እናቷን ለመጠየቅ ሕጻን ልጇን ይዛ ወደ ቡለን ወረዳ እየተጓዘች በነበረችበት ጊዜ ታጣቂዎቹ በፈጸሙት ጥቃት ከነ ልጇ ከተገደሉት ውስጥ ናቸው።
ሚስቱ እና ልጁ በታጣቂዎች የተገደሉበት ባለቤቷ በከፍተኛ ሐዘን ምክንያት በመረበሹ ራሱን እና ሌሎችን እንዳይጎዳ በሚል "ታስሮ" እንደሚገኝ የቤተሰብ አባሉ ተናግረዋል።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የጀግናዋ አትሌት ሻምበል ባሻ የብርጓል መለሰ የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈጸመ
#ethiopia | በበርካታ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ስታደርግ የቆየችው ዝነኛዋ አትሌት ሻምበል ባሻ የብርጓል መለሰ የቀብር ሥነ ሥርዓት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በክብር ተፈጽሟል።
በመጋቢት ወር 1982 ዓ.ም በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የተወለደችው አትሌቷ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሩጫው ዓለም በመግባት ስኬታማ ጉዞ ስታደርግ ቆይታለች።
በ2003 ዓ.ም የመከላከያ መቻል ስፖርት ክለብን በመቀላቀል በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ በ10 ኪሎ ሜትር፣ በሀገር አቋራጭ እንዲሁም በማራቶን ውድድሮች በርካታ ድሎችን ለሀገሯና ለክለቧ አስመዝግባለች።
አትሌት የብርጓል መለሰ እ.ኤ.አ በ2015 በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የነሐስ ሜዳሊያ፣ በ2013 በዓለም ሀገር አቋራጭ ውድድር የብር ሜዳሊያ እንዲሁም በሂውስተን፣ በሻንጋይ፣ በፕራግ እና በሊዝበን ማራቶኖች አንደኛ በመውጣት ታላቅ ውጤት ያስመዘገበች ጀግና ነበረች።
አትሌቷ በካናዳ ለሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ዝግጅት እያደረገች በነበረበት ወቅት በደረሰባት ድንገተኛ የጤና እክል ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
በዛሬው የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች፣ የጦር ኃይሎች መኮንኖች፣ አትሌቶችና ቤተሰቦቿ በተገኙበት በመከላከያ የክብር ዘብ የታጀበ ሽኝት ተደርጎላታል።
አትሌት የብርጓል በትዳር አጋሯ አትሌት ወሰን ዘለቀና በሁለት ሕፃናት ልጆቿ እንዲሁም በሥራ ባልደረቦቿ ዘንድ በትሕትናዋና በአርአያነቷ የምትታወስ ታላቅ ስፖርተኛ ነበረች።
Getu Temesgen ( ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ በጀግናዋ አትሌት ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን ለቤተሰቦ፤ ለአድናቂዎቿ መጽናናትን እንመኛለን።
#athletics #ethiopianathletes #yebrgualmelese #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በበርካታ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ስታደርግ የቆየችው ዝነኛዋ አትሌት ሻምበል ባሻ የብርጓል መለሰ የቀብር ሥነ ሥርዓት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በክብር ተፈጽሟል።
በመጋቢት ወር 1982 ዓ.ም በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የተወለደችው አትሌቷ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሩጫው ዓለም በመግባት ስኬታማ ጉዞ ስታደርግ ቆይታለች።
በ2003 ዓ.ም የመከላከያ መቻል ስፖርት ክለብን በመቀላቀል በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ በ10 ኪሎ ሜትር፣ በሀገር አቋራጭ እንዲሁም በማራቶን ውድድሮች በርካታ ድሎችን ለሀገሯና ለክለቧ አስመዝግባለች።
አትሌት የብርጓል መለሰ እ.ኤ.አ በ2015 በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የነሐስ ሜዳሊያ፣ በ2013 በዓለም ሀገር አቋራጭ ውድድር የብር ሜዳሊያ እንዲሁም በሂውስተን፣ በሻንጋይ፣ በፕራግ እና በሊዝበን ማራቶኖች አንደኛ በመውጣት ታላቅ ውጤት ያስመዘገበች ጀግና ነበረች።
አትሌቷ በካናዳ ለሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ዝግጅት እያደረገች በነበረበት ወቅት በደረሰባት ድንገተኛ የጤና እክል ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
በዛሬው የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች፣ የጦር ኃይሎች መኮንኖች፣ አትሌቶችና ቤተሰቦቿ በተገኙበት በመከላከያ የክብር ዘብ የታጀበ ሽኝት ተደርጎላታል።
አትሌት የብርጓል በትዳር አጋሯ አትሌት ወሰን ዘለቀና በሁለት ሕፃናት ልጆቿ እንዲሁም በሥራ ባልደረቦቿ ዘንድ በትሕትናዋና በአርአያነቷ የምትታወስ ታላቅ ስፖርተኛ ነበረች።
Getu Temesgen ( ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ በጀግናዋ አትሌት ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን ለቤተሰቦ፤ ለአድናቂዎቿ መጽናናትን እንመኛለን።
#athletics #ethiopianathletes #yebrgualmelese #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
አትሌት የብርጓል መለሰ በድንገተኛ አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች
****************
ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ውድድሮች ስታስጠራ የቆየችው አትሌት የብርጓል መለሰ በዛሬው ዕለት በደረሰባት ድንገተኛ አደጋ በ36 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
አትሌቷ ዛሬ ማለዳ በጃን ሜዳ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ልምምድ ላይ ሳለች በድንገት የመውደቅ አደጋ ደርሶባት ወደ ጤና ተቋም ብትወሰድም ሕይወቷን ማትረፍ ሳይቻል ቀርቷል።
ሚያዝያ 1982 ዓ.ም የተወለደችው አትሌት የብርጓል መለሰ፤ ከ2003 ዓ.ም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና አንስታ በበርካታ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ስኬታማ ውጤቶችን አስመዝግባለች።
በተለይም በሂዩስተን፣ በፕራግ እና በሻንጋይ ማራቶን በተለያዩ ዓመታት በቀዳሚነት ያጠናቀቀች ሲሆን፣ እ.ኤ.አ በ2018 የሻንጋይ ማራቶንን ስታሸንፍም የስፍራውን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ነበር።
በፓሪስ ግማሽ ማራቶን ሁለት ጊዜ፣ በፖርቹጋል ግማሽ ማራቶን ደግሞ አንድ ጊዜ ባለድል ለመሆን የበቃችው የብርጓል፤ በ2015 ኮንጎ ብራዛቪል ላይ በተካሄደው ውድድር ኢትዮጵያን ወክላ የነሐስ ሜዳሊያ አስመዝግባለች።
በዚሁ ዓመት በቺካጎ ማራቶን ደግሞ ሁለተኛ ደረጃን በማግኘት በ"ማራቶን ሜጀርስ" ስሟን አስጠርታለች።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌቷ ሕልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ፤ ለቤተሰቦቿ፣ ለወዳጅ ዘመዶቿ፣ ለአድናቂዎቿ እንዲሁም ለመላው የስፖርት ቤተሰብ መጽናናትን ተመኝቷል።
#ethiopianbroadcastingcorporation #yebrgualmelese #ethiopianathletics #marathon
****************
ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ውድድሮች ስታስጠራ የቆየችው አትሌት የብርጓል መለሰ በዛሬው ዕለት በደረሰባት ድንገተኛ አደጋ በ36 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
አትሌቷ ዛሬ ማለዳ በጃን ሜዳ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ልምምድ ላይ ሳለች በድንገት የመውደቅ አደጋ ደርሶባት ወደ ጤና ተቋም ብትወሰድም ሕይወቷን ማትረፍ ሳይቻል ቀርቷል።
ሚያዝያ 1982 ዓ.ም የተወለደችው አትሌት የብርጓል መለሰ፤ ከ2003 ዓ.ም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና አንስታ በበርካታ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ስኬታማ ውጤቶችን አስመዝግባለች።
በተለይም በሂዩስተን፣ በፕራግ እና በሻንጋይ ማራቶን በተለያዩ ዓመታት በቀዳሚነት ያጠናቀቀች ሲሆን፣ እ.ኤ.አ በ2018 የሻንጋይ ማራቶንን ስታሸንፍም የስፍራውን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ነበር።
በፓሪስ ግማሽ ማራቶን ሁለት ጊዜ፣ በፖርቹጋል ግማሽ ማራቶን ደግሞ አንድ ጊዜ ባለድል ለመሆን የበቃችው የብርጓል፤ በ2015 ኮንጎ ብራዛቪል ላይ በተካሄደው ውድድር ኢትዮጵያን ወክላ የነሐስ ሜዳሊያ አስመዝግባለች።
በዚሁ ዓመት በቺካጎ ማራቶን ደግሞ ሁለተኛ ደረጃን በማግኘት በ"ማራቶን ሜጀርስ" ስሟን አስጠርታለች።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌቷ ሕልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ፤ ለቤተሰቦቿ፣ ለወዳጅ ዘመዶቿ፣ ለአድናቂዎቿ እንዲሁም ለመላው የስፖርት ቤተሰብ መጽናናትን ተመኝቷል።
#ethiopianbroadcastingcorporation #yebrgualmelese #ethiopianathletics #marathon
2 months ago
"በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
2 months ago
ለአምስት ተከታታይ ቀናት ከሥራ የቀረ ሠራተኛ ያለ ማስጠንቀቂያ ከሥራ እንደሚሰናበት በሰበር ችሎት የተሰጠው የሕግ ትርጓሜ፣ በአዋጁ ላይ ያለውን ግልጽ አሠራር መሠረት ያደረገ መሆኑ ተገለጸ
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) እንዳስታወቀው፣ በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ እንዲሁም በኅብረት ስምምነት ከተቀመጡት የፈቃድ ዓይነቶች ውጭ ለ5 ተከታታይ ቀናት ከሥራ የቀረ ሠራተኛ ከሥራ እንደሚሰናበት በግልጽ ተቀምጧል።
የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ የሰበር ችሎት በጉዳዩ ላይ የሰጠው ትርጓሜ አዲስ ሕግ ሳይሆን በአዋጁ ላይ ያለውን አሠራር የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ ከተፈቀዱ ሕጋዊ ፈቃዶች ውጭ አንድ ሠራተኛ በራሱ ምክንያት ለ5 ተከታታይ ቀናት ከሥራ ከቀረ አሠሪው ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሚችል አዋጁ በግልጽ ያስቀምጣል ብለዋል። ሰበር ችሎትም ሕጉን ሲተረጉም አዲስ ነገር ሳይሆን በአዋጅና በኅብረት ስምምነት ያለውን አሠራር በመከተል መሆኑን ጠቁመዋል።
ይሁን እንጂ እርምጃው በሚወሰድበት ወቅት በሕግ የተፈቀዱ እንደ ሐዘን፣ የወሊድ እና የሕክምና ፈቃድ የመሳሰሉትን አካቶ መሆን እንደሌለበትና ይህ ካልሆነ ግን አሠራሩ ስህተት እንደሚሆን ገልጸዋል።
የአሠሪና ሠራተኛ ደንቦችና መመሪያዎች ሲወጡ በሦስትዮሽ ውይይት እንደሚወሰኑና በአፈጻጸም ላይ የሚታዩ ክፍተቶችም በዚህ መንገድ እንዲፈቱ እንደሚሠራ ተመልክቷል።
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከሰሞኑ በሰጠው ውሳኔ፣ ከልዩ ልዩ ፈቃዶች ውጭ አንድ ሠራተኛ ለ5 ተከታታይ የሥራ ቀናትና ከዚያ በላይ ከሥራ ከቀረ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ውሉን ማቋረጥ እንደሚቻል መግለጹ ይታወሳል።
seledadotio
seledadotio
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) እንዳስታወቀው፣ በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ እንዲሁም በኅብረት ስምምነት ከተቀመጡት የፈቃድ ዓይነቶች ውጭ ለ5 ተከታታይ ቀናት ከሥራ የቀረ ሠራተኛ ከሥራ እንደሚሰናበት በግልጽ ተቀምጧል።
የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ የሰበር ችሎት በጉዳዩ ላይ የሰጠው ትርጓሜ አዲስ ሕግ ሳይሆን በአዋጁ ላይ ያለውን አሠራር የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ ከተፈቀዱ ሕጋዊ ፈቃዶች ውጭ አንድ ሠራተኛ በራሱ ምክንያት ለ5 ተከታታይ ቀናት ከሥራ ከቀረ አሠሪው ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሚችል አዋጁ በግልጽ ያስቀምጣል ብለዋል። ሰበር ችሎትም ሕጉን ሲተረጉም አዲስ ነገር ሳይሆን በአዋጅና በኅብረት ስምምነት ያለውን አሠራር በመከተል መሆኑን ጠቁመዋል።
ይሁን እንጂ እርምጃው በሚወሰድበት ወቅት በሕግ የተፈቀዱ እንደ ሐዘን፣ የወሊድ እና የሕክምና ፈቃድ የመሳሰሉትን አካቶ መሆን እንደሌለበትና ይህ ካልሆነ ግን አሠራሩ ስህተት እንደሚሆን ገልጸዋል።
የአሠሪና ሠራተኛ ደንቦችና መመሪያዎች ሲወጡ በሦስትዮሽ ውይይት እንደሚወሰኑና በአፈጻጸም ላይ የሚታዩ ክፍተቶችም በዚህ መንገድ እንዲፈቱ እንደሚሠራ ተመልክቷል።
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከሰሞኑ በሰጠው ውሳኔ፣ ከልዩ ልዩ ፈቃዶች ውጭ አንድ ሠራተኛ ለ5 ተከታታይ የሥራ ቀናትና ከዚያ በላይ ከሥራ ከቀረ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ውሉን ማቋረጥ እንደሚቻል መግለጹ ይታወሳል።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
Abebe Tilahun culture & Sport:
ለፈረንጅ ሚስቶች የቆመች ሐውልት‼️
የመጽሐፉ ርዕስ፦ የፈረንጅ ሚስት
ደራሲት፦ እስከዳር ግርማይ
የገጽ ብዛት ፦ 119
የመጽሐፉ ዋጋ ፦ 150 ብር
እትም፦ 3ኛ /2017 ዓ.ም
ዘውግ፦ ግለ ማስታወሻ (Memoir)+
አርታኢያን፦ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል እና አርቲስት አዜብ ወርቁ
👉መንደርደሪያ
ካርል ሮጀርስ (Carl Rogers) የተባለው ታዋቂው አሜሪካዊ የሥነ-ልቦና ባለሙያ "On Becoming a Person" በተሰኘ መጽሐፉ ላይ በሰዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት በማጥናት እንዲህ ይላል። “What is most personal is most universal.” ፦ “እጅግ ሲበዛ ግላዊ የሆነው ነገር፣ እጅግ ሲበዛ ዓለማቀፋዊ ነው።”
ግለ-ማስታወሻ (Memoir)፤ ከሕይወት ውስጥ አንድን ወሳኝ ክስተት፣ ስሜት ወይም ጭብጥ (Theme) መርጦ ይተነትናል። ትኩረቱ "ከገጠመኝ ነገር ምን ተማርኩ? ምን ተሰማኝ?" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር ግለ-ማስታወሻ ከታሪክ ይልቅ ትርጓሜና ስሜት ላይ ያተኩራል።
አንድ ሰው ለብቻው የሚሰማው፣ ለሌላ ሰው ለመናገር የሚፈራው ወይም "እኔ ብቻ ነኝ እንዲህ የሚሰማኝ" ብሎ የሚያስበው የግል ስሜት (ለምሳሌ፦ የፍርሃት፣ የብቸኝነት ስሜት፣ ወይም የናፍቆት፣ የመበሳጨትና የመብከንከን ስሜት) በሚገርም ሁኔታ ሌሎች ሰዎችም በውስጣቸው የሚሰማቸው ነው።
ስለሆነም ጸሐፊዋ እስከዳር ስለ ራሷና በዙሪያዋ ስላሉ ተመሳሳይ ሰዎች እጅግ ጥብቅና ግላዊ የሆኑ ጉዳዮችን በሐቀኝነት ስትናገር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በታሪኳ ውስጥ የራሳቸውን ስሜት አግኝተውታል። የሥነ-ልቦና ጠበብት አንድ ሰው ወደ ራሱ ማንነት (Inner self) በጥልቀት በወረደ ቁጥር፣ ከግል ማንነቱ ባለፈ የሰው ልጅን የጋራ ማንነት (Collective Human Experience) ያገኛል ብለው ያምናሉና በፈረንጅ ሚስት የሆነውም ይሄው ነው።
ሌላኛው ጄምስ ጆይስ (James Joyce)የተባለ ምሁር "በተለየው (in the particular) ውስጥ ሁልጊዜም ዓለማቀፋዊውን (the universal) ነገር እናገኛለን።" በማለት በሥነ-ጽሑፍ ሥራዎቹ የግል ተሞክሮን ማዕከል ማድረጉን ገልጿል። እንዲሁም ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን (Ralph Waldo Emerson) "በገዛ ልብህ ውስጥ የምታምነው እውነት ለሁሉም ሰዎች እውነት ነው።" በሚል ሀሳብ ተመሳሳይ ፍልስፍናን አራምዷል።
በአጠቃላይ አባባሉ "የሰው ልጅ ስሜትና ተፈጥሮ በየትኛውም ቦታ አንድ ነው" የሚለውን መሠረታዊ እውነት የሚያሳይ ነው። የፈረንጅ ሚስት የሚለው ግለ-ማስታወሻ በራስ ሕይወት መስኮትነት ዓለምን የማሳያ ጥበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ጸሐፊዋ በራሷ ሕይወት ውስጥ ያለውን ትርጉም ስትፈልግ፣ አንባቢው ደግሞ በጸሐፊው ታሪክ ውስጥ የራሱንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ያያል፣ ይታዘባል።
የፈረንጅ ሚስት
👉ግላዊና ዓለማቀፋዊ ሀሳብ፤ ጸሐፊዋ ስለ ራሷ ብቻ ስታወራ ለአንባቢው አሰልቺ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በግል ሕይወቷ በፈረንጅ ሚስትነቷ፣ በኢትዮጵያዊነቷ፣ የደረሰባትን ሐዘን፣ ፍቅር፣ ክህደት ወይም መገለል በሐቀኝነት ስለገለጠችው፣ አንባቢያን በራሳቸው ሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት አጋጥሟቸው ስለሚያውቅ ከጸሐፊዋ ጋር፣ እንደግል በሀሳብ፣ እንደማኅበረሰብ በአባልነት ይቆራኛሉ።
ሰው ወደ ራሱ ውስጠት በጥልቀት በቆፈረ ቁጥር፣ የሁሉንም ሰው የጋራ ምንጭ ያገኛል። የራስን እውነተኛ ስሜት፣ ስቃይ እና ደስታ መፈለግ እና እዚያ ጥልቀት ላይ ሲደርሱ የምናገኘው ራስን ብቻ ሳይሆን መላውን የሰው ልጅ የሚያገናኘውን የጋራ ክር ነው። ለዚህ ነው ግላዊ ማስታወሻዎች (Memoirs) በሚገባ ተቆፍረው ሲጻፉ ዓለምን ሁሉ የመንካት አቅም የሚኖራቸው።
በሥነ-ጽሑፍ እና በፈጠራ ድርሰት ዓለም ውስጥ በስፋት የምትታወቀው አሜሪካዊት ጸሐፊ ማያ አንጄሉ (Maya Angelou) “In the particular is contained the universal.” ፦ በተለየው/በግል ታሪክ ውስጥ፣ ዓለማቀፋዊው እውነት ይገኛል። ብላለች ።
ይህች የፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ከኢትዮጵያዊ ወንድ ውጭ ላገባችሁ ቀወል ስም የፈረንጅ ሚስት ለምትባሉ ሁሉ ሴቶች የቆመች ቅልብጭ ያለች ሐውልት ናት።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ውስጥ ፤
ሐቀኝነት (Honesty)አለ፦ ግለ-ማስታወሻ ጸሐፊዋ ራሷን ብቻ ያሞግሰችበት ሳይሆን፣ ድክመትና ስህተቶችንም ጭምር የገለጥችበት መጽሐፍ ነው። ሐቀኝነት ከሌለ አንባቢው በታሪኩ አይመሰጥም።
የራስ መተማመኗን ፈረንጅ የማግባት ውጤት ሲያደርጉት፤ ሐበሻ ብታገባ ኖሮ በዚህ የራስ መተማመኗ ድሮ እንደሚፈታት ሲያሙላት በስላቅ ሐቋን ትጠይቃለች።
"እውነት የሀገሬ ሴቶች ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና በራሳችሁ
የምትተማመኑ ከሆናችሁ ትዳራችሁ አይጸናም?
ደመወዛችሁ ከባለቤታችሁ ደመወዝ ሲበልጥ፣ ሥልጣናችሁ ከትዳራችሁ በላይ ሲገዝፍ ትፋታላችሁ?
ወይስ ትዳራችሁን መርጣችሁ፣ የመጣላችሁን ዕድል አሳልፋችሁ ለወንድ እና ላላገቡ ሴቶች ትሰጣላችሁ?
የሀገሬ ወንዶችስ? በሥራ፣ በደመወዝ ወይም በሥልጣን የምትበልጣችሁን ሴት ማግባት ትፈራላችሁ እንዴ?"
መልስ አትፈልግም።
ይልቁንስ ደራሲዋ ጥያቄዎቹን የምታቀርበው ምላሽ ፈልጋ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡን በመስታወት ፊት አቁማ ራሱን እንዲታዘብ ለማድረግ ነው።
ጭብጥ (Theme)አለ፦ ታሪኳ የሚሽከረከርበት አንድ ማዕከላዊ እውነት አለው ። ማዕከላዊ እውነቷ በማኅበረሰባችን ዘንድ ለፈረንጅ ሚስት ያለውን ስሁት አመለካከት ማረም፣ እውነቷንና ጽናቷን በመግለጽ ማንነቷን ማሳየት ነው። ለእያንዳንዱ ገጠመኟ በተግባር የተፈጸመ ምሳሌ ያልደበዘዘ ትውስታ ተቀምጧል ።
በማኅበረሰባችን ዘንድ የፈረንጅ ሚስትን ከሚያራክስበት ዝቅጠታዊ ልማድ የባሰ የሀብታም ቅምጥን የሚያሞግስበትና የሚያከብርበት የስብእና ንጥፈት እንዴት እንዳብከነከናት በሚቆጠቁጥ መልኩ የማዕከላዊ ጭብጡ ማጠንጠኛ ሆኗል ።
ደሞ ለምን ፈረንጅ አገባሽ ? እያሉ የጅል ጥያቄ ለሚጠይቁ አድርቅ ጋዜጠኞች ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ በጥያቄያቸው እንዲያፍሩ የምታደርግበት ጥበብ የፈረንጁ ባሏ ምክርና የጭብጧ ማጠናከሪያ ነበር።
"ባለቤቴ ሁል ጊዜ የማይደረስ ጥያቄ ለሚጠይቅሽ ሰው፤ የጠየቀሽን ጥያቄ መልሰሽ ራሱን ጠይቂው። መልሱ ካላጠገበሽ ምን ማለትህ ነው? ብለሽ ይበልጥ እንዲያብራራልሽ እንደገና ጠይቂው። ስህተቱን
እስኪረዳው ተፋተኚው። እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ከአምስት
ጥያቄዎች በላይ መመለስ አይችሉም፤ የሚለኝን ሳስበው ተግባራዊ እያደረግኩ።" ትለናለች። (ገጽ34)
ጥበባዊ አቀራረብ አለ፦ ምንም እንኳን እውነተኛ ታሪክ ቢሆንም፣ እንደ ልብ-ወለድ (Fiction) የታሪክ አወቃቀር፣ ገጸ-ባህሪያት አሳሳል እና የቃላት ምርጫ (Imagery) ተጠቀማለች። እንደ ገጸ ባሕርይ ራሷን እና በዙሪያዋ ያሉ ተመሳሳይ ሕይወት የሚጋሩ ወዳጆቿን፣ ቤተሰቦቿን እና በመንገዷ የገጠሟትን አካታለች። የታሪክ አወቃቀሩ ከአንዱ የሕይወት ገጠመኝ ወደ ሌላኛው የሕይወት ገጠመኝ እየተሻገረች፣ በትውስታ እያጀበች በምሳሌ አዋቅራ የልቧን እውነት የሕይወቷን ትርክት ቀንጭባ አቅርባዋለች።
የቃላት አመራረጧ ትኩሳቷን በመግለጥ እንደ እሳት የሚጋረፉ ፣ ስታዝን የሚለዝቡ፣ ስትቆጣ የሚንጣጡ ቃላት ናቸው።
ለምሳሌ የሀብታም ቅምጥን የገለጠችበትን ቃላት ተመልከቱ፦ "የሀብታም ቅምጥ የከተማው ሁሉ ወንድ የሚመኛት፣ ያሳደጓት የሰፈር ጎረምሶች ዓይናቸው እያየ ለባለጸጋ አሳልፈው በመስጠታቸው የሚቆጩባት፣ ዘመድ አዝማዶቿ የእሷ ስኬት የልጆቻቸው ባለመሆኑ የሚቀኑባት፣ የሰፈሩ ሰዎች ለአቅመ ሔዋን ላልደረሱ ልጆቻቸው "አርአያነቷን" እንዲከተሉ ጀብዳቸውን የሚነግሩላት፤ በየቦታው ትንሽዬ "ፈጣሪ" ሆና ብዙ "ደቀ መዛሙርት" ያፈራች ሴት ናት።" (ገጽ 27)
ውስጣዊ ሙግት (Internal Dialogue/ አለ፦ በሆነባት በተደረገባት ነገር ብቻ ሳይሆን፤ የወጣችበት ማኅበረሰብ ግንዛቤ ባለበት ቆሞ መቅረት ጭምር ሲያብሰከስካት ፤ እንደግል መብቷን፣ እንደማኅበረሰብ ውበቷን ስትገፈፍ የምትናገራቸው ቃላት የውስጧን መብከንከን ይገልጻሉ።
"የማዝነው፤ ማኅበረሰባችን በየመንገዱ መሰደቧን እንዳላየ እንዳልሰማ ሆኖ ስለሚያልፋት ብቻ አይደለም ። ከሐበሻ ወንድ ወጭ ሲሆን በፍቅር የማትወድቅ፣ ከሀገሯ ቋንቋ በቀር የፍቅር ቃላት የማትሰማ፣ ጠረን ለምዳ የማትሸነፍ ናት፤ ብለው በመወሰናቸውና የስሜት ሕዋሳቷ ለሌላ ሀገር ዜጋም ቢሆን እንደሚሠሩ ባለማወቃቸውም እንጂ!" (ገጽ16)
"ውጭ ሀገር ስንኖር አለመከበራችን በምንም መልኩ ልክ አይደለም፤ በሰው ሀገር ስንከፋ የሚሰማን ስሜት ፣ ከራሳችን ሀገር ከሚደርስብን የጥቃት ስሜት ጋር ካነጻጸርነው ግን፣ የሕመሙ ክብደት በሰው ሀገር
ሲሆን ይቀንሳል።
ሀገር ያስከፋን ጊዜ ግን ወዴት አቤት ይባላል? የራስ ሕዝብስ ለማን ይከሰሳል?" እያለች ምሯን ትናገራለች።
እናቴ አሳዛኝና አንጀት ቆራጭ ነገሮች ሲገጥሟት፦ "ከቀላድም ባይረዝም ከመጫኛም ባይበልጥ፤
አንጀት ያልቅ የለም ወይ ሲቆረጥ ሲቆረጥ።" ትላለች ።
የማኅበረሰባዊ መገፋት አንጀት ይቆርጣል ፤ አይመልሰኝ አሰኝቶ ድንጋይ ያስወረውራል። በጊዜ ሊታረም ከዘመኑ ጋርም ሊዘምን የሚገባ እንጅ የምናጌጥበት ነውር መሆን የለበትም ።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ
ደራሲዋ እስከዳር ግርማይና መሰል የፈረንጅ ሚስቶች ያለፈና ያለን ቁስል በቃላት አስጊጣ በመግለጧ ግላዊ እፎይታ ፣ ሕሊናዊ ፈውስ አግኝተውበታል፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።
በመሰል ፈተና ውስጥ ያሉ ሰዎች የግለ ማስታወሻዎቹን ሂደትና መፍትሔ አይተው ተስፋ የሚሰጥ ትምህርት ያገኛሉ። በማኅበረሰባዊ ሂሷም ብዙዎች ራሳቸውን እንዲታዘቡ ራሳቸውን እንዲመረምሩና እንዲታረሙ ኮርኩራለች።
እስከዳር በራሷ የተወሰነ ዘመንና ማኅበረሰብ ውስጥ ለፈረንጅ ሚስት የነበረን አመለካከት ለትውልድ በማስተላለፍ የታሪክ ምስክር በመሆን፤ ለፈረንጅ ሚስቶች ሐውልት አቁማለች።
ማጠቃለያ
ደራሲ እስከዳር ግርማይ በመጽሐፏ ውስጥ 'የፈረንጅ ሚስት' የሚለውን ስም ከስድብነት ወደ ማንነት (Identity)፣ ከማንነትም ወደ ተጋድሎ (Resistance) ቀይራዋለች። ይህ መጽሐፍ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነትን እና የዘመናዊነትን (Modernity) ግጭት፣ እንዲሁም የሴትነትን ነፃነት የሚፈትን፣ ማኅበረሰባዊ ሕጸፅን ነቅሶ የሚያሳይ መስታወት ነው።
👉እስከዬ አሁንም ያላወጣሽው ብዙ ግላዊ "የመሬማውያን ጉዳይ" አለና በጥልቀት ቆፍረሽ ታወጭው ዘንድ አደራ እላለሁ 🙏
👉የፈረንጅ ሚስት በዶክመንተሪ ቢዘጋጅ ደግሞ ከንባብ የራቀውና የስድብ መጋዘን ከሆነው የማኅበረሰብ ክፍል ውስጥ በእጁ ላይ ገብተሽ ትነግሪዋለሽ። የፈረንጅ ሚስት ማለት በምን የሕይወት ሸለቆ ውስጥ አልፋ ምርጫዋን የምታስከብር እንደሆነች ታሳያቸዋለሽ።
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
ለፈረንጅ ሚስቶች የቆመች ሐውልት‼️
የመጽሐፉ ርዕስ፦ የፈረንጅ ሚስት
ደራሲት፦ እስከዳር ግርማይ
የገጽ ብዛት ፦ 119
የመጽሐፉ ዋጋ ፦ 150 ብር
እትም፦ 3ኛ /2017 ዓ.ም
ዘውግ፦ ግለ ማስታወሻ (Memoir)+
አርታኢያን፦ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል እና አርቲስት አዜብ ወርቁ
👉መንደርደሪያ
ካርል ሮጀርስ (Carl Rogers) የተባለው ታዋቂው አሜሪካዊ የሥነ-ልቦና ባለሙያ "On Becoming a Person" በተሰኘ መጽሐፉ ላይ በሰዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት በማጥናት እንዲህ ይላል። “What is most personal is most universal.” ፦ “እጅግ ሲበዛ ግላዊ የሆነው ነገር፣ እጅግ ሲበዛ ዓለማቀፋዊ ነው።”
ግለ-ማስታወሻ (Memoir)፤ ከሕይወት ውስጥ አንድን ወሳኝ ክስተት፣ ስሜት ወይም ጭብጥ (Theme) መርጦ ይተነትናል። ትኩረቱ "ከገጠመኝ ነገር ምን ተማርኩ? ምን ተሰማኝ?" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር ግለ-ማስታወሻ ከታሪክ ይልቅ ትርጓሜና ስሜት ላይ ያተኩራል።
አንድ ሰው ለብቻው የሚሰማው፣ ለሌላ ሰው ለመናገር የሚፈራው ወይም "እኔ ብቻ ነኝ እንዲህ የሚሰማኝ" ብሎ የሚያስበው የግል ስሜት (ለምሳሌ፦ የፍርሃት፣ የብቸኝነት ስሜት፣ ወይም የናፍቆት፣ የመበሳጨትና የመብከንከን ስሜት) በሚገርም ሁኔታ ሌሎች ሰዎችም በውስጣቸው የሚሰማቸው ነው።
ስለሆነም ጸሐፊዋ እስከዳር ስለ ራሷና በዙሪያዋ ስላሉ ተመሳሳይ ሰዎች እጅግ ጥብቅና ግላዊ የሆኑ ጉዳዮችን በሐቀኝነት ስትናገር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በታሪኳ ውስጥ የራሳቸውን ስሜት አግኝተውታል። የሥነ-ልቦና ጠበብት አንድ ሰው ወደ ራሱ ማንነት (Inner self) በጥልቀት በወረደ ቁጥር፣ ከግል ማንነቱ ባለፈ የሰው ልጅን የጋራ ማንነት (Collective Human Experience) ያገኛል ብለው ያምናሉና በፈረንጅ ሚስት የሆነውም ይሄው ነው።
ሌላኛው ጄምስ ጆይስ (James Joyce)የተባለ ምሁር "በተለየው (in the particular) ውስጥ ሁልጊዜም ዓለማቀፋዊውን (the universal) ነገር እናገኛለን።" በማለት በሥነ-ጽሑፍ ሥራዎቹ የግል ተሞክሮን ማዕከል ማድረጉን ገልጿል። እንዲሁም ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን (Ralph Waldo Emerson) "በገዛ ልብህ ውስጥ የምታምነው እውነት ለሁሉም ሰዎች እውነት ነው።" በሚል ሀሳብ ተመሳሳይ ፍልስፍናን አራምዷል።
በአጠቃላይ አባባሉ "የሰው ልጅ ስሜትና ተፈጥሮ በየትኛውም ቦታ አንድ ነው" የሚለውን መሠረታዊ እውነት የሚያሳይ ነው። የፈረንጅ ሚስት የሚለው ግለ-ማስታወሻ በራስ ሕይወት መስኮትነት ዓለምን የማሳያ ጥበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ጸሐፊዋ በራሷ ሕይወት ውስጥ ያለውን ትርጉም ስትፈልግ፣ አንባቢው ደግሞ በጸሐፊው ታሪክ ውስጥ የራሱንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ያያል፣ ይታዘባል።
የፈረንጅ ሚስት
👉ግላዊና ዓለማቀፋዊ ሀሳብ፤ ጸሐፊዋ ስለ ራሷ ብቻ ስታወራ ለአንባቢው አሰልቺ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በግል ሕይወቷ በፈረንጅ ሚስትነቷ፣ በኢትዮጵያዊነቷ፣ የደረሰባትን ሐዘን፣ ፍቅር፣ ክህደት ወይም መገለል በሐቀኝነት ስለገለጠችው፣ አንባቢያን በራሳቸው ሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት አጋጥሟቸው ስለሚያውቅ ከጸሐፊዋ ጋር፣ እንደግል በሀሳብ፣ እንደማኅበረሰብ በአባልነት ይቆራኛሉ።
ሰው ወደ ራሱ ውስጠት በጥልቀት በቆፈረ ቁጥር፣ የሁሉንም ሰው የጋራ ምንጭ ያገኛል። የራስን እውነተኛ ስሜት፣ ስቃይ እና ደስታ መፈለግ እና እዚያ ጥልቀት ላይ ሲደርሱ የምናገኘው ራስን ብቻ ሳይሆን መላውን የሰው ልጅ የሚያገናኘውን የጋራ ክር ነው። ለዚህ ነው ግላዊ ማስታወሻዎች (Memoirs) በሚገባ ተቆፍረው ሲጻፉ ዓለምን ሁሉ የመንካት አቅም የሚኖራቸው።
በሥነ-ጽሑፍ እና በፈጠራ ድርሰት ዓለም ውስጥ በስፋት የምትታወቀው አሜሪካዊት ጸሐፊ ማያ አንጄሉ (Maya Angelou) “In the particular is contained the universal.” ፦ በተለየው/በግል ታሪክ ውስጥ፣ ዓለማቀፋዊው እውነት ይገኛል። ብላለች ።
ይህች የፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ከኢትዮጵያዊ ወንድ ውጭ ላገባችሁ ቀወል ስም የፈረንጅ ሚስት ለምትባሉ ሁሉ ሴቶች የቆመች ቅልብጭ ያለች ሐውልት ናት።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ውስጥ ፤
ሐቀኝነት (Honesty)አለ፦ ግለ-ማስታወሻ ጸሐፊዋ ራሷን ብቻ ያሞግሰችበት ሳይሆን፣ ድክመትና ስህተቶችንም ጭምር የገለጥችበት መጽሐፍ ነው። ሐቀኝነት ከሌለ አንባቢው በታሪኩ አይመሰጥም።
የራስ መተማመኗን ፈረንጅ የማግባት ውጤት ሲያደርጉት፤ ሐበሻ ብታገባ ኖሮ በዚህ የራስ መተማመኗ ድሮ እንደሚፈታት ሲያሙላት በስላቅ ሐቋን ትጠይቃለች።
"እውነት የሀገሬ ሴቶች ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና በራሳችሁ
የምትተማመኑ ከሆናችሁ ትዳራችሁ አይጸናም?
ደመወዛችሁ ከባለቤታችሁ ደመወዝ ሲበልጥ፣ ሥልጣናችሁ ከትዳራችሁ በላይ ሲገዝፍ ትፋታላችሁ?
ወይስ ትዳራችሁን መርጣችሁ፣ የመጣላችሁን ዕድል አሳልፋችሁ ለወንድ እና ላላገቡ ሴቶች ትሰጣላችሁ?
የሀገሬ ወንዶችስ? በሥራ፣ በደመወዝ ወይም በሥልጣን የምትበልጣችሁን ሴት ማግባት ትፈራላችሁ እንዴ?"
መልስ አትፈልግም።
ይልቁንስ ደራሲዋ ጥያቄዎቹን የምታቀርበው ምላሽ ፈልጋ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡን በመስታወት ፊት አቁማ ራሱን እንዲታዘብ ለማድረግ ነው።
ጭብጥ (Theme)አለ፦ ታሪኳ የሚሽከረከርበት አንድ ማዕከላዊ እውነት አለው ። ማዕከላዊ እውነቷ በማኅበረሰባችን ዘንድ ለፈረንጅ ሚስት ያለውን ስሁት አመለካከት ማረም፣ እውነቷንና ጽናቷን በመግለጽ ማንነቷን ማሳየት ነው። ለእያንዳንዱ ገጠመኟ በተግባር የተፈጸመ ምሳሌ ያልደበዘዘ ትውስታ ተቀምጧል ።
በማኅበረሰባችን ዘንድ የፈረንጅ ሚስትን ከሚያራክስበት ዝቅጠታዊ ልማድ የባሰ የሀብታም ቅምጥን የሚያሞግስበትና የሚያከብርበት የስብእና ንጥፈት እንዴት እንዳብከነከናት በሚቆጠቁጥ መልኩ የማዕከላዊ ጭብጡ ማጠንጠኛ ሆኗል ።
ደሞ ለምን ፈረንጅ አገባሽ ? እያሉ የጅል ጥያቄ ለሚጠይቁ አድርቅ ጋዜጠኞች ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ በጥያቄያቸው እንዲያፍሩ የምታደርግበት ጥበብ የፈረንጁ ባሏ ምክርና የጭብጧ ማጠናከሪያ ነበር።
"ባለቤቴ ሁል ጊዜ የማይደረስ ጥያቄ ለሚጠይቅሽ ሰው፤ የጠየቀሽን ጥያቄ መልሰሽ ራሱን ጠይቂው። መልሱ ካላጠገበሽ ምን ማለትህ ነው? ብለሽ ይበልጥ እንዲያብራራልሽ እንደገና ጠይቂው። ስህተቱን
እስኪረዳው ተፋተኚው። እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ከአምስት
ጥያቄዎች በላይ መመለስ አይችሉም፤ የሚለኝን ሳስበው ተግባራዊ እያደረግኩ።" ትለናለች። (ገጽ34)
ጥበባዊ አቀራረብ አለ፦ ምንም እንኳን እውነተኛ ታሪክ ቢሆንም፣ እንደ ልብ-ወለድ (Fiction) የታሪክ አወቃቀር፣ ገጸ-ባህሪያት አሳሳል እና የቃላት ምርጫ (Imagery) ተጠቀማለች። እንደ ገጸ ባሕርይ ራሷን እና በዙሪያዋ ያሉ ተመሳሳይ ሕይወት የሚጋሩ ወዳጆቿን፣ ቤተሰቦቿን እና በመንገዷ የገጠሟትን አካታለች። የታሪክ አወቃቀሩ ከአንዱ የሕይወት ገጠመኝ ወደ ሌላኛው የሕይወት ገጠመኝ እየተሻገረች፣ በትውስታ እያጀበች በምሳሌ አዋቅራ የልቧን እውነት የሕይወቷን ትርክት ቀንጭባ አቅርባዋለች።
የቃላት አመራረጧ ትኩሳቷን በመግለጥ እንደ እሳት የሚጋረፉ ፣ ስታዝን የሚለዝቡ፣ ስትቆጣ የሚንጣጡ ቃላት ናቸው።
ለምሳሌ የሀብታም ቅምጥን የገለጠችበትን ቃላት ተመልከቱ፦ "የሀብታም ቅምጥ የከተማው ሁሉ ወንድ የሚመኛት፣ ያሳደጓት የሰፈር ጎረምሶች ዓይናቸው እያየ ለባለጸጋ አሳልፈው በመስጠታቸው የሚቆጩባት፣ ዘመድ አዝማዶቿ የእሷ ስኬት የልጆቻቸው ባለመሆኑ የሚቀኑባት፣ የሰፈሩ ሰዎች ለአቅመ ሔዋን ላልደረሱ ልጆቻቸው "አርአያነቷን" እንዲከተሉ ጀብዳቸውን የሚነግሩላት፤ በየቦታው ትንሽዬ "ፈጣሪ" ሆና ብዙ "ደቀ መዛሙርት" ያፈራች ሴት ናት።" (ገጽ 27)
ውስጣዊ ሙግት (Internal Dialogue/ አለ፦ በሆነባት በተደረገባት ነገር ብቻ ሳይሆን፤ የወጣችበት ማኅበረሰብ ግንዛቤ ባለበት ቆሞ መቅረት ጭምር ሲያብሰከስካት ፤ እንደግል መብቷን፣ እንደማኅበረሰብ ውበቷን ስትገፈፍ የምትናገራቸው ቃላት የውስጧን መብከንከን ይገልጻሉ።
"የማዝነው፤ ማኅበረሰባችን በየመንገዱ መሰደቧን እንዳላየ እንዳልሰማ ሆኖ ስለሚያልፋት ብቻ አይደለም ። ከሐበሻ ወንድ ወጭ ሲሆን በፍቅር የማትወድቅ፣ ከሀገሯ ቋንቋ በቀር የፍቅር ቃላት የማትሰማ፣ ጠረን ለምዳ የማትሸነፍ ናት፤ ብለው በመወሰናቸውና የስሜት ሕዋሳቷ ለሌላ ሀገር ዜጋም ቢሆን እንደሚሠሩ ባለማወቃቸውም እንጂ!" (ገጽ16)
"ውጭ ሀገር ስንኖር አለመከበራችን በምንም መልኩ ልክ አይደለም፤ በሰው ሀገር ስንከፋ የሚሰማን ስሜት ፣ ከራሳችን ሀገር ከሚደርስብን የጥቃት ስሜት ጋር ካነጻጸርነው ግን፣ የሕመሙ ክብደት በሰው ሀገር
ሲሆን ይቀንሳል።
ሀገር ያስከፋን ጊዜ ግን ወዴት አቤት ይባላል? የራስ ሕዝብስ ለማን ይከሰሳል?" እያለች ምሯን ትናገራለች።
እናቴ አሳዛኝና አንጀት ቆራጭ ነገሮች ሲገጥሟት፦ "ከቀላድም ባይረዝም ከመጫኛም ባይበልጥ፤
አንጀት ያልቅ የለም ወይ ሲቆረጥ ሲቆረጥ።" ትላለች ።
የማኅበረሰባዊ መገፋት አንጀት ይቆርጣል ፤ አይመልሰኝ አሰኝቶ ድንጋይ ያስወረውራል። በጊዜ ሊታረም ከዘመኑ ጋርም ሊዘምን የሚገባ እንጅ የምናጌጥበት ነውር መሆን የለበትም ።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ
ደራሲዋ እስከዳር ግርማይና መሰል የፈረንጅ ሚስቶች ያለፈና ያለን ቁስል በቃላት አስጊጣ በመግለጧ ግላዊ እፎይታ ፣ ሕሊናዊ ፈውስ አግኝተውበታል፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።
በመሰል ፈተና ውስጥ ያሉ ሰዎች የግለ ማስታወሻዎቹን ሂደትና መፍትሔ አይተው ተስፋ የሚሰጥ ትምህርት ያገኛሉ። በማኅበረሰባዊ ሂሷም ብዙዎች ራሳቸውን እንዲታዘቡ ራሳቸውን እንዲመረምሩና እንዲታረሙ ኮርኩራለች።
እስከዳር በራሷ የተወሰነ ዘመንና ማኅበረሰብ ውስጥ ለፈረንጅ ሚስት የነበረን አመለካከት ለትውልድ በማስተላለፍ የታሪክ ምስክር በመሆን፤ ለፈረንጅ ሚስቶች ሐውልት አቁማለች።
ማጠቃለያ
ደራሲ እስከዳር ግርማይ በመጽሐፏ ውስጥ 'የፈረንጅ ሚስት' የሚለውን ስም ከስድብነት ወደ ማንነት (Identity)፣ ከማንነትም ወደ ተጋድሎ (Resistance) ቀይራዋለች። ይህ መጽሐፍ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነትን እና የዘመናዊነትን (Modernity) ግጭት፣ እንዲሁም የሴትነትን ነፃነት የሚፈትን፣ ማኅበረሰባዊ ሕጸፅን ነቅሶ የሚያሳይ መስታወት ነው።
👉እስከዬ አሁንም ያላወጣሽው ብዙ ግላዊ "የመሬማውያን ጉዳይ" አለና በጥልቀት ቆፍረሽ ታወጭው ዘንድ አደራ እላለሁ 🙏
👉የፈረንጅ ሚስት በዶክመንተሪ ቢዘጋጅ ደግሞ ከንባብ የራቀውና የስድብ መጋዘን ከሆነው የማኅበረሰብ ክፍል ውስጥ በእጁ ላይ ገብተሽ ትነግሪዋለሽ። የፈረንጅ ሚስት ማለት በምን የሕይወት ሸለቆ ውስጥ አልፋ ምርጫዋን የምታስከብር እንደሆነች ታሳያቸዋለሽ።
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
2 months ago
በአፋር ወደ መቐለ ሲጓዝ የነበረ ሾፌር የገደሉት አንዱ ሲያዝ አንዱ እየተፈለገ ነው።
#fastmereja I በአፋር ክልል ኤሬብቲ ወረዳ ልዩ ስሙ "ሔርቶ በህሪ" በተባለ አካባቢ፣ ከጅቡቲ ወደ መቐለ ሲጓዝ የነበረ አሽከርካሪ በታጠቁ ግለሰቦች በተከፈተበት ተኩስ ሕይወቱ ማለፉን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ። ጥቃቱን ከፈጸሙት ሁለት ግለሰቦች መካከል አንዱ ቆስሎ በቁጥጥር ሥር ሲውል፣ ሁለተኛው ተጠርጣሪ ወደ ጫካ በመግባቱ ፍለጋ እየተካሄደበት ይገኛል።
ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ገደማ፣ አሽከርካሪ አቶ ጥጋቡ ለገሰ ተሰማ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮ3-A35438/94911 ኢት የሆነ ከባድ መኪና በመንዳት ከጅቡቲ-ሰርዶ መንገድ ወደ መቐለ በመጓዝ ላይ ነበሩ። ተሽከርካሪው አፍዴራ ሲረባን አልፎ ኤሬብቲ ወረዳ ሲደርስ፣ ሁለት የታጠቁ ግለሰቦች መኪናውን በማስቆም በአሽከርካሪው ላይ ጥቃት መፈጸማቸው ተረጋግጧል።
በደረሰው ጥቆማ መሠረት የጸጥታ አካላት በፍጥነት ቦታው ላይ የደረሱ ሲሆን፣ አንደኛው ተጠርጣሪ በግራ እግሩ ላይ በደረሰበት የተኩስ ቁስል ምክንያት በቁጥጥር ሥር ውሏል። ሁለተኛው ግለሰብ የፖሊስ ተሽከርካሪን ከርቀት በማየቱ ወደ ጫካ ውስጥ በመግባት ለጊዜው የተሰወረ ቢሆንም፣ የፖሊስ አባላትና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል አሁንም በጫካው ውስጥ መጠነ ሰፊ አሰሳ እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል።
የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በክልሉ ያልተለመደ ያለውን ይህን አስነዋሪ ድርጊት በማውገዝ፣ ለተፈጠረው ክስተት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ በክልሉ ስም ይቅርታ ጠይቋል። ፖሊስ በቁጥጥር ሥር የዋለው ተጠርጣሪ በሕግ እንደሚጠየቅና ያመለጠውን ግለሰብ በአጭር ጊዜ ውስጥ አድኖ ለሕግ ለማቅረብ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጧል።
#fastmereja I በአፋር ክልል ኤሬብቲ ወረዳ ልዩ ስሙ "ሔርቶ በህሪ" በተባለ አካባቢ፣ ከጅቡቲ ወደ መቐለ ሲጓዝ የነበረ አሽከርካሪ በታጠቁ ግለሰቦች በተከፈተበት ተኩስ ሕይወቱ ማለፉን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ። ጥቃቱን ከፈጸሙት ሁለት ግለሰቦች መካከል አንዱ ቆስሎ በቁጥጥር ሥር ሲውል፣ ሁለተኛው ተጠርጣሪ ወደ ጫካ በመግባቱ ፍለጋ እየተካሄደበት ይገኛል።
ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ገደማ፣ አሽከርካሪ አቶ ጥጋቡ ለገሰ ተሰማ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮ3-A35438/94911 ኢት የሆነ ከባድ መኪና በመንዳት ከጅቡቲ-ሰርዶ መንገድ ወደ መቐለ በመጓዝ ላይ ነበሩ። ተሽከርካሪው አፍዴራ ሲረባን አልፎ ኤሬብቲ ወረዳ ሲደርስ፣ ሁለት የታጠቁ ግለሰቦች መኪናውን በማስቆም በአሽከርካሪው ላይ ጥቃት መፈጸማቸው ተረጋግጧል።
በደረሰው ጥቆማ መሠረት የጸጥታ አካላት በፍጥነት ቦታው ላይ የደረሱ ሲሆን፣ አንደኛው ተጠርጣሪ በግራ እግሩ ላይ በደረሰበት የተኩስ ቁስል ምክንያት በቁጥጥር ሥር ውሏል። ሁለተኛው ግለሰብ የፖሊስ ተሽከርካሪን ከርቀት በማየቱ ወደ ጫካ ውስጥ በመግባት ለጊዜው የተሰወረ ቢሆንም፣ የፖሊስ አባላትና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል አሁንም በጫካው ውስጥ መጠነ ሰፊ አሰሳ እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል።
የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በክልሉ ያልተለመደ ያለውን ይህን አስነዋሪ ድርጊት በማውገዝ፣ ለተፈጠረው ክስተት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ በክልሉ ስም ይቅርታ ጠይቋል። ፖሊስ በቁጥጥር ሥር የዋለው ተጠርጣሪ በሕግ እንደሚጠየቅና ያመለጠውን ግለሰብ በአጭር ጊዜ ውስጥ አድኖ ለሕግ ለማቅረብ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጧል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
በግፍ ለተገደለው ወጣት ተመስገን ዳንኤል ፍትህ ይስፈን!
ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ማለዳ 2:00 አካባቢ የአቢሲኒያ ባንክ ባልደረባ የሆነው ወጣት ተመስገን ዳንኤል ወደ ሥራ ገበታው እየተሰማራ ባለበት ወቅት በአሰቃቂ ሁኔታ ሕይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።
ወጣቱ በሽጉጥና በሳንጃ ተወግቶ ለሞት የተዳረገው በአደባባይ እርዳታ እየጠየቀ ቢሆንም፣ በስፍራው የነበረው ማኅበረሰብ በድንጋጤና በዝምታ በመመልከቱ ተገቢውን ድጋፍ ሳያገኝ ነፍሱ እንድታልፍ ተገዷል።
ይህ ዘግናኝ ድርጊት መነሻው ቂም በቀል እንደሆነ በማኅበረሰቡ ዘንድ በስፊው እየተነገረ ይገኛል።
ሟች ተመስገን በቅርቡ በትዳር ከታሰረችው ባለቤቱ ጋር የነበረውን ግንኙነት ያልተቀበለውና ለዓመታት የቀድሞ ፍቅረኛዋ እንደነበር የሚነገርለት ግለሰብ፣ ይህንን አሰቃቂ ጥቃት እንደፈጸመበት መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የአንድ ንጹህ ሰው ሕይወት በዚህ መልኩ በአደባባይ መቀጠፉ እጅግ የሚያሳዝንና የሕግ የበላይነትን የሚፈታተን ተግባር ነው።
በመሆኑም ይህንን ኢ-ሰብአዊ ወንጀል የፈጸሙ አካላት በአስቸኳይ ለሕግ እንዲቀርቡና ለሟች ተመስገን ዳንኤል የሚገባው ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ እናቀርባለን።
የሕግ አስከባሪ አካላት ጉዳዩን በጥልቀት በመመርመር የንጹሃንን ደም በከንቱ የሚያፈሱ ወንጀለኞች ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
በቅርቡ ትዳር መሥርታ የሐዘን ማቅ ለለበሰችው ባለቤቱ፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለሥራ ባልደረቦቹ በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።gursha
ፍትህ ለተመስገን ዳንኤል!
Seledadotio
Seledadotio
ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ማለዳ 2:00 አካባቢ የአቢሲኒያ ባንክ ባልደረባ የሆነው ወጣት ተመስገን ዳንኤል ወደ ሥራ ገበታው እየተሰማራ ባለበት ወቅት በአሰቃቂ ሁኔታ ሕይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።
ወጣቱ በሽጉጥና በሳንጃ ተወግቶ ለሞት የተዳረገው በአደባባይ እርዳታ እየጠየቀ ቢሆንም፣ በስፍራው የነበረው ማኅበረሰብ በድንጋጤና በዝምታ በመመልከቱ ተገቢውን ድጋፍ ሳያገኝ ነፍሱ እንድታልፍ ተገዷል።
ይህ ዘግናኝ ድርጊት መነሻው ቂም በቀል እንደሆነ በማኅበረሰቡ ዘንድ በስፊው እየተነገረ ይገኛል።
ሟች ተመስገን በቅርቡ በትዳር ከታሰረችው ባለቤቱ ጋር የነበረውን ግንኙነት ያልተቀበለውና ለዓመታት የቀድሞ ፍቅረኛዋ እንደነበር የሚነገርለት ግለሰብ፣ ይህንን አሰቃቂ ጥቃት እንደፈጸመበት መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የአንድ ንጹህ ሰው ሕይወት በዚህ መልኩ በአደባባይ መቀጠፉ እጅግ የሚያሳዝንና የሕግ የበላይነትን የሚፈታተን ተግባር ነው።
በመሆኑም ይህንን ኢ-ሰብአዊ ወንጀል የፈጸሙ አካላት በአስቸኳይ ለሕግ እንዲቀርቡና ለሟች ተመስገን ዳንኤል የሚገባው ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ እናቀርባለን።
የሕግ አስከባሪ አካላት ጉዳዩን በጥልቀት በመመርመር የንጹሃንን ደም በከንቱ የሚያፈሱ ወንጀለኞች ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
በቅርቡ ትዳር መሥርታ የሐዘን ማቅ ለለበሰችው ባለቤቱ፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለሥራ ባልደረቦቹ በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።gursha
ፍትህ ለተመስገን ዳንኤል!
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
የቀድሞው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ወ/ሮ ገበያነሽ ነጋሽ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
#fastmereja I የቀድሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አማካሪ የነበሩት ወ/ሮ ገበያነሽ ነጋሽ ባጋጠማቸው ድንገተኛ ሕመም በ46 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው ዛሬ ሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በትውልድ ቦታቸው በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ይፈጸማል።
ወ/ሮ ገበያነሽ ነጋሽ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ ለ11 ዓመታት (ከ2003 እስከ 2014 ዓ.ም) ወረዳቸውን በመወከልና በተለያዩ ቋሚ ኮሚቴዎች ውስጥ አባል በመሆን አገልግለዋል። ከመስከረም 2014 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማካሪነት ሲሰሩ ቆይተዋል።
ከባለቤታቸው ከዶ/ር ሀብቴ ጅፋር ጋር ትዳር መስርተው የአንድ ወንድና የአንድ ሴት ልጅ እናት ነበሩ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በወ/ሮ ገበያነሽ ነጋሽ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።
ሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም
#fastmereja I የቀድሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አማካሪ የነበሩት ወ/ሮ ገበያነሽ ነጋሽ ባጋጠማቸው ድንገተኛ ሕመም በ46 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው ዛሬ ሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በትውልድ ቦታቸው በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ይፈጸማል።
ወ/ሮ ገበያነሽ ነጋሽ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ ለ11 ዓመታት (ከ2003 እስከ 2014 ዓ.ም) ወረዳቸውን በመወከልና በተለያዩ ቋሚ ኮሚቴዎች ውስጥ አባል በመሆን አገልግለዋል። ከመስከረም 2014 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማካሪነት ሲሰሩ ቆይተዋል።
ከባለቤታቸው ከዶ/ር ሀብቴ ጅፋር ጋር ትዳር መስርተው የአንድ ወንድና የአንድ ሴት ልጅ እናት ነበሩ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በወ/ሮ ገበያነሽ ነጋሽ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።
ሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም
2 months ago
በመስቀሉ ሰላም አደረገ - ቄጤማ ይዘን የምስራች እንባባላለን🙏
አዳም ከ5500 ዘመን በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው ባለው ቃል መሠረት ዘመን እየቆጠረ ቀኑን ሲጠብቅ ቆየ፡፡ በዕለተ አርብ ልክ ክርስቶስ ነብሱን ከስጋው ሲለይ፣ አዳም እንደ ተስፋ ቃሉ ይመጣልና በፀሎት እናስታውሰው ብሎ ልክ 11:00 ላይ በሲኦል ያሉትን ነብሳት “ተንስኡ ለጸሎት ለጸሎት ተነሱ” አላቸው፡፡ እነርሱም “እግዚኦ ተሰሀለነ፣ አቤቱ ይቅር በለን” ብለው መለሱ፡፡ ወዲያው ጌታችን “ሰላም ለኩልክሙ፣ ሰላም ለሁላችሁ ይሁን” አላቸው፡፡ እነርሱም “ምስለ መንፈስከ፣ እንደ ቃልህ ይደረግልን” አሉት፡፡ ሲኦል ባዶ ሆነች፣ ነፍሳትን ሁሉ ነጻ አወጣ፡፡ በማግስቱ ልዩዋ ቅዳሜ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቃብር ያሳለፋት፣ የምትጾም ከመጾም አልፋ የሚከፈልባት ነችና ቀዳም ሥዑር ትባላለች፡፡ ለምለም ቅዳሜ፣ ቅዱስ ቅዳሜም ትባላለች፡፡
እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና ወዳጆቹ ሐዋርያት ትንሣኤውን እስኪያዩ በሐዘን፣ በጾም፣ በጸሎት ቆይተዋልና እኛም በአክፍሎት፣ በጾም እናሳልፋታለን። በቀዳም ሥዑር ሌሊት ሥርዓቱ የሚጀመረው በመኀልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምንባብ ነው፡፡ ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጠዋት ላይ አቡን መዋሥዕት ውዳሴ ማርያም ዜማ ይደረሳል፡፡ ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጨሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡ ነፍሳት ከሲኦል ወጡ፡፡ የገነት በር ተከፈተልን፣ ርስተ መንግስተ ሰማያት ተመለሰልን፤ አባታችን አዳምም ከፈጣሪው ጋር ታረቀልን በማለት “በመስቀሉ ሰላመ አደረገ” እያልን የተድላ፣ የደስታ ምልክት የሆነ ልምላሜ ያለውን ቄጤማ ይዘን የምስራች እንባባላለን፡፡
በኖኅ ጊዜም ርግብ “የጥፋት ውኃ ጎደለ፣ አለቀ እያለች “የወይራ ዝንጣፊ” ይዛ ኖኅን አብስራዋለች፡፡ ርግብ የካህናት፣ ኖኅ የምእመናን፣ ኖኅ እጁን ዘርግቶ ርግብን እንደተቀበላት ካህናትም በየመንደሩ እየዞሩ “ክርስቶስ ተመረመረ፤ ዲያብሎስ ታሰረ” በማለት ቄጤማ ሲያድሉ፤ ምእመናንም እጃቸውን ዘርግተው መቀበላቸው የዚህ ምሳሌ ነው፡፡ ስለዚህ አሁንም ቢገኝ የወይራ ልምላሜ፣ ቢታጣ ቄጠማ እየታደልን የምሥራች መባባላችን ነፍሳት ከሲኦል ለመውጣታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ይህን የድኅነታችንን ብስራት በደስታ የሚቀበሉት ገዳማውያን የማዳኑን ሥራ፣ ፍቅሩን ዘወትር ለማሰብ ዓለምን ትተው ወጥተዋልና ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
አዳም ከ5500 ዘመን በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው ባለው ቃል መሠረት ዘመን እየቆጠረ ቀኑን ሲጠብቅ ቆየ፡፡ በዕለተ አርብ ልክ ክርስቶስ ነብሱን ከስጋው ሲለይ፣ አዳም እንደ ተስፋ ቃሉ ይመጣልና በፀሎት እናስታውሰው ብሎ ልክ 11:00 ላይ በሲኦል ያሉትን ነብሳት “ተንስኡ ለጸሎት ለጸሎት ተነሱ” አላቸው፡፡ እነርሱም “እግዚኦ ተሰሀለነ፣ አቤቱ ይቅር በለን” ብለው መለሱ፡፡ ወዲያው ጌታችን “ሰላም ለኩልክሙ፣ ሰላም ለሁላችሁ ይሁን” አላቸው፡፡ እነርሱም “ምስለ መንፈስከ፣ እንደ ቃልህ ይደረግልን” አሉት፡፡ ሲኦል ባዶ ሆነች፣ ነፍሳትን ሁሉ ነጻ አወጣ፡፡ በማግስቱ ልዩዋ ቅዳሜ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቃብር ያሳለፋት፣ የምትጾም ከመጾም አልፋ የሚከፈልባት ነችና ቀዳም ሥዑር ትባላለች፡፡ ለምለም ቅዳሜ፣ ቅዱስ ቅዳሜም ትባላለች፡፡
እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና ወዳጆቹ ሐዋርያት ትንሣኤውን እስኪያዩ በሐዘን፣ በጾም፣ በጸሎት ቆይተዋልና እኛም በአክፍሎት፣ በጾም እናሳልፋታለን። በቀዳም ሥዑር ሌሊት ሥርዓቱ የሚጀመረው በመኀልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምንባብ ነው፡፡ ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጠዋት ላይ አቡን መዋሥዕት ውዳሴ ማርያም ዜማ ይደረሳል፡፡ ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጨሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡ ነፍሳት ከሲኦል ወጡ፡፡ የገነት በር ተከፈተልን፣ ርስተ መንግስተ ሰማያት ተመለሰልን፤ አባታችን አዳምም ከፈጣሪው ጋር ታረቀልን በማለት “በመስቀሉ ሰላመ አደረገ” እያልን የተድላ፣ የደስታ ምልክት የሆነ ልምላሜ ያለውን ቄጤማ ይዘን የምስራች እንባባላለን፡፡
በኖኅ ጊዜም ርግብ “የጥፋት ውኃ ጎደለ፣ አለቀ እያለች “የወይራ ዝንጣፊ” ይዛ ኖኅን አብስራዋለች፡፡ ርግብ የካህናት፣ ኖኅ የምእመናን፣ ኖኅ እጁን ዘርግቶ ርግብን እንደተቀበላት ካህናትም በየመንደሩ እየዞሩ “ክርስቶስ ተመረመረ፤ ዲያብሎስ ታሰረ” በማለት ቄጤማ ሲያድሉ፤ ምእመናንም እጃቸውን ዘርግተው መቀበላቸው የዚህ ምሳሌ ነው፡፡ ስለዚህ አሁንም ቢገኝ የወይራ ልምላሜ፣ ቢታጣ ቄጠማ እየታደልን የምሥራች መባባላችን ነፍሳት ከሲኦል ለመውጣታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ይህን የድኅነታችንን ብስራት በደስታ የሚቀበሉት ገዳማውያን የማዳኑን ሥራ፣ ፍቅሩን ዘወትር ለማሰብ ዓለምን ትተው ወጥተዋልና ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
2 months ago
"ሰው ሳላደርግሽ ስለሞተሽብኝ አዝናለሁ"
#fastmereja I በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ፣ የድሉ ባለቤትና የጨዋታው ኮከብ የሆነው አጥቂው ፍፁም ጥላሁን ድሉን ከሦስት ዓመት በፊት ለሞተችው እናቱ በመስጠት በስሜት ተሞልቶ በእንባ ታጅቦ ምስክርነቱን ሰጥቷል።
ለቅዱስ ጊዮርጊስ የድል ግብ በማስቆጠር የጨዋታው ኮከብ ተብሎ የተመረጠው ፍፁም ጥላሁን፣ ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በሜዳው ውስጥ በሰጠው ቃለ መጠይቅ መላውን ስፖርት አፍቃሪ ያስለቀሰ ንግግር አድርጓል።
አጥቂው የነገው ቀን እናቱ ካረፈች ሦስተኛ ዓመቷ መሆኑን ገልጾ፣ በህይወት እያለች ካሰበው ደረጃ ላይ ሊያደርሳት ባለመቻሉ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጿል። "እናቴን እወዳታለሁ፤ ነፍሴን ለእርሷ መቀየር ብችል እቀይራት ነበር" ያለው ፍፁም፣ እናቱ በህይወት ዘመኗ ብዙ መከራና ችግር እንዳሳለፈች እንዲሁም "እንደ ሰው ሳይደላት" ማለፏ የሁልጊዜ ቁጭቱ መሆኑን በለቅሶ ተናግሯል።
ተጫዋቹ ጨምሮም "ሰው ሳላደርግሽ ስለሞተሽብኝ አዝናለሁ፣ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው" በማለት ለቤተሰቦቹና ለሟች እናቱ ያለውን ጥልቅ ፍቅር ተናግሯል።
#fastmereja I በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ፣ የድሉ ባለቤትና የጨዋታው ኮከብ የሆነው አጥቂው ፍፁም ጥላሁን ድሉን ከሦስት ዓመት በፊት ለሞተችው እናቱ በመስጠት በስሜት ተሞልቶ በእንባ ታጅቦ ምስክርነቱን ሰጥቷል።
ለቅዱስ ጊዮርጊስ የድል ግብ በማስቆጠር የጨዋታው ኮከብ ተብሎ የተመረጠው ፍፁም ጥላሁን፣ ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በሜዳው ውስጥ በሰጠው ቃለ መጠይቅ መላውን ስፖርት አፍቃሪ ያስለቀሰ ንግግር አድርጓል።
አጥቂው የነገው ቀን እናቱ ካረፈች ሦስተኛ ዓመቷ መሆኑን ገልጾ፣ በህይወት እያለች ካሰበው ደረጃ ላይ ሊያደርሳት ባለመቻሉ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጿል። "እናቴን እወዳታለሁ፤ ነፍሴን ለእርሷ መቀየር ብችል እቀይራት ነበር" ያለው ፍፁም፣ እናቱ በህይወት ዘመኗ ብዙ መከራና ችግር እንዳሳለፈች እንዲሁም "እንደ ሰው ሳይደላት" ማለፏ የሁልጊዜ ቁጭቱ መሆኑን በለቅሶ ተናግሯል።
ተጫዋቹ ጨምሮም "ሰው ሳላደርግሽ ስለሞተሽብኝ አዝናለሁ፣ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው" በማለት ለቤተሰቦቹና ለሟች እናቱ ያለውን ጥልቅ ፍቅር ተናግሯል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የአፋልጉኝ ተማጽኖ
#ethiopia | እህታችን ቀለሟ ገ/ሥላሴ ትባላለች። የአይምሮ ህመምተኛ ነች።
መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከእንጦጦ ኪዳነምህረት ጸበል ቦታ ጠፍታ እስካሁን አልተመለሰችም።
በመጥፋቷም መላው ቤተሰቧ ተጨንቀዋል፤ ወላጅ እናቷም በከባድ ሐዘን ላይ ይገኛሉ።
ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ትብብራችሁን በእግዚአብሔር ስም እንማጸናለን።
ያያችሁ ወይም ያለችበትን የምታውቁ ጥቆማ እንድትሰጡን እንጠይቃለን!
ጥቆማ ለመስጠት፦
📞 0901257258
📞 0912883788
📞 0922837097
📞 0913043972
📞 0911952553
ወረታውን እግዚአብሔር አምላክ ይክፈላችሁ!
እባካችሁ ይህንን መረጃ Share በማድረግ ለቤተሰቦቿ እንድረስላቸው።
#getu #afalgun #entotokidanemihret #missingperson #addisababa #ethiopia #urgentsearch #helpfindher #አፋልጉኝ #እንጦጦኪዳነምህረት #አዲስአበባ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | እህታችን ቀለሟ ገ/ሥላሴ ትባላለች። የአይምሮ ህመምተኛ ነች።
መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከእንጦጦ ኪዳነምህረት ጸበል ቦታ ጠፍታ እስካሁን አልተመለሰችም።
በመጥፋቷም መላው ቤተሰቧ ተጨንቀዋል፤ ወላጅ እናቷም በከባድ ሐዘን ላይ ይገኛሉ።
ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ትብብራችሁን በእግዚአብሔር ስም እንማጸናለን።
ያያችሁ ወይም ያለችበትን የምታውቁ ጥቆማ እንድትሰጡን እንጠይቃለን!
ጥቆማ ለመስጠት፦
📞 0901257258
📞 0912883788
📞 0922837097
📞 0913043972
📞 0911952553
ወረታውን እግዚአብሔር አምላክ ይክፈላችሁ!
እባካችሁ ይህንን መረጃ Share በማድረግ ለቤተሰቦቿ እንድረስላቸው።
#getu #afalgun #entotokidanemihret #missingperson #addisababa #ethiopia #urgentsearch #helpfindher #አፋልጉኝ #እንጦጦኪዳነምህረት #አዲስአበባ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
ጣሊያን የቤት እንስሳ ለሞተበት ሠራተኛ ሶስት ቀን የሐዘን ፈቃድ ልትሰጥ ነው
#ethiopia | በጣሊያን ሀገር የቤት እንስሳ ለሞተባቸው ወይም ለታመሙባቸው ሠራተኞች የሚከፈልበት የሥራ ፈቃድ እንዲሰጥ የሚጠይቅ አዲስ የሕግ ረቂቅ ቀረበ።
ይህ ተነሳሽነት በጣሊያን የሚገኙ የቤት እንስሳት እንደ ቤተሰብ አባል የሚታዩበትን ማህበራዊ እውነታ መሠረት ያደረገ ነው።
ረቂቁ አንድ የቤት እንስሳ (ውሻ ወይም ድመት) ሲሞት ሠራተኛው ለሦስት ቀናት የሚከፈልበት የሐዘን ፈቃድ እንዲያገኝ ይጠይቃል።
ለቤት እንስሳት ድንገተኛ ሕክምና በዓመት ስምንት ሰዓታት ከሥራ ገበታ የመቅረት መብት እንዲኖር ረቂቁ ይደነግጋል።
56% የሚሆኑ የጣሊያን ቤተሰቦች የቤት እንስሳ ያላቸው ሲሆን፣ የእንስሳቱ መታመም ወይም መሞት በሠራተኛው የሥነ-ልቦና እና የሥራ ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ጥናቶች ያመለክታሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ላ_ሪፐብሊካ #internationalbusiness #italy #fidelpost #economynews #internetsafety
#ethiopia | በጣሊያን ሀገር የቤት እንስሳ ለሞተባቸው ወይም ለታመሙባቸው ሠራተኞች የሚከፈልበት የሥራ ፈቃድ እንዲሰጥ የሚጠይቅ አዲስ የሕግ ረቂቅ ቀረበ።
ይህ ተነሳሽነት በጣሊያን የሚገኙ የቤት እንስሳት እንደ ቤተሰብ አባል የሚታዩበትን ማህበራዊ እውነታ መሠረት ያደረገ ነው።
ረቂቁ አንድ የቤት እንስሳ (ውሻ ወይም ድመት) ሲሞት ሠራተኛው ለሦስት ቀናት የሚከፈልበት የሐዘን ፈቃድ እንዲያገኝ ይጠይቃል።
ለቤት እንስሳት ድንገተኛ ሕክምና በዓመት ስምንት ሰዓታት ከሥራ ገበታ የመቅረት መብት እንዲኖር ረቂቁ ይደነግጋል።
56% የሚሆኑ የጣሊያን ቤተሰቦች የቤት እንስሳ ያላቸው ሲሆን፣ የእንስሳቱ መታመም ወይም መሞት በሠራተኛው የሥነ-ልቦና እና የሥራ ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ጥናቶች ያመለክታሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ላ_ሪፐብሊካ #internationalbusiness #italy #fidelpost #economynews #internetsafety
3 months ago
ጣሊያን የቤት እንስሳ ለሞተበት ሠራተኛ ሶስት ቀን የሐዘን ፈቃድ ልትሰጥ ነው
በጣሊያን ሀገር የቤት እንስሳ ለሞተባቸው ወይም ለታመሙባቸው ሠራተኞች የሚከፈልበት የሥራ ፈቃድ እንዲሰጥ የሚጠይቅ አዲስ የሕግ ረቂቅ ቀረበ።
ይህ ተነሳሽነት በጣሊያን የሚገኙ የቤት እንስሳት እንደ ቤተሰብ አባል የሚታዩበትን ማህበራዊ እውነታ መሠረት ያደረገ ነው።
ረቂቁ አንድ የቤት እንስሳ (ውሻ ወይም ድመት) ሲሞት ሠራተኛው ለሦስት ቀናት የሚከፈልበት የሐዘን ፈቃድ እንዲያገኝ ይጠይቃል።
ለቤት እንስሳት ድንገተኛ ሕክምና በዓመት ስምንት ሰዓታት ከሥራ ገበታ የመቅረት መብት እንዲኖር ረቂቁ ይደነግጋል።
56% የሚሆኑ የጣሊያን ቤተሰቦች የቤት እንስሳ ያላቸው ሲሆን፣ የእንስሳቱ መታመም ወይም መሞት በሠራተኛው የሥነ-ልቦና እና የሥራ ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ጥናቶች ያመለክታሉ።
ምንጭ: ላ ሪፐብሊካ
seledadotio
seledadotio
በጣሊያን ሀገር የቤት እንስሳ ለሞተባቸው ወይም ለታመሙባቸው ሠራተኞች የሚከፈልበት የሥራ ፈቃድ እንዲሰጥ የሚጠይቅ አዲስ የሕግ ረቂቅ ቀረበ።
ይህ ተነሳሽነት በጣሊያን የሚገኙ የቤት እንስሳት እንደ ቤተሰብ አባል የሚታዩበትን ማህበራዊ እውነታ መሠረት ያደረገ ነው።
ረቂቁ አንድ የቤት እንስሳ (ውሻ ወይም ድመት) ሲሞት ሠራተኛው ለሦስት ቀናት የሚከፈልበት የሐዘን ፈቃድ እንዲያገኝ ይጠይቃል።
ለቤት እንስሳት ድንገተኛ ሕክምና በዓመት ስምንት ሰዓታት ከሥራ ገበታ የመቅረት መብት እንዲኖር ረቂቁ ይደነግጋል።
56% የሚሆኑ የጣሊያን ቤተሰቦች የቤት እንስሳ ያላቸው ሲሆን፣ የእንስሳቱ መታመም ወይም መሞት በሠራተኛው የሥነ-ልቦና እና የሥራ ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ጥናቶች ያመለክታሉ።
ምንጭ: ላ ሪፐብሊካ
seledadotio
seledadotio
3 months ago
ጣሊያን የቤት እንስሳ ለሞተበት ሠራተኛ ሶስት ቀን የሐዘን ፈቃድ ልትሰጥ ነው
በጣሊያን ሀገር የቤት እንስሳ ለሞተባቸው ወይም ለታመሙባቸው ሠራተኞች የሚከፈልበት የሥራ ፈቃድ እንዲሰጥ የሚጠይቅ አዲስ የሕግ ረቂቅ ቀረበ።
ይህ ተነሳሽነት በጣሊያን የሚገኙ የቤት እንስሳት እንደ ቤተሰብ አባል የሚታዩበትን ማህበራዊ እውነታ መሠረት ያደረገ ነው።
ረቂቁ አንድ የቤት እንስሳ (ውሻ ወይም ድመት) ሲሞት ሠራተኛው ለሦስት ቀናት የሚከፈልበት የሐዘን ፈቃድ እንዲያገኝ ይጠይቃል።
ለቤት እንስሳት ድንገተኛ ሕክምና በዓመት ስምንት ሰዓታት ከሥራ ገበታ የመቅረት መብት እንዲኖር ረቂቁ ይደነግጋል።
56% የሚሆኑ የጣሊያን ቤተሰቦች የቤት እንስሳ ያላቸው ሲሆን፣ የእንስሳቱ መታመም ወይም መሞት በሠራተኛው የሥነ-ልቦና እና የሥራ ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ጥናቶች ያመለክታሉ።
ምንጭ: ላ ሪፐብሊካ
በጣሊያን ሀገር የቤት እንስሳ ለሞተባቸው ወይም ለታመሙባቸው ሠራተኞች የሚከፈልበት የሥራ ፈቃድ እንዲሰጥ የሚጠይቅ አዲስ የሕግ ረቂቅ ቀረበ።
ይህ ተነሳሽነት በጣሊያን የሚገኙ የቤት እንስሳት እንደ ቤተሰብ አባል የሚታዩበትን ማህበራዊ እውነታ መሠረት ያደረገ ነው።
ረቂቁ አንድ የቤት እንስሳ (ውሻ ወይም ድመት) ሲሞት ሠራተኛው ለሦስት ቀናት የሚከፈልበት የሐዘን ፈቃድ እንዲያገኝ ይጠይቃል።
ለቤት እንስሳት ድንገተኛ ሕክምና በዓመት ስምንት ሰዓታት ከሥራ ገበታ የመቅረት መብት እንዲኖር ረቂቁ ይደነግጋል።
56% የሚሆኑ የጣሊያን ቤተሰቦች የቤት እንስሳ ያላቸው ሲሆን፣ የእንስሳቱ መታመም ወይም መሞት በሠራተኛው የሥነ-ልቦና እና የሥራ ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ጥናቶች ያመለክታሉ።
ምንጭ: ላ ሪፐብሊካ
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ቀብር
#ethiopia | የአዲስ አውቶሞቲቭ የሬዲዮ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (EBC) አንጋፋ የዜና አንባቢ የጋዜጠኛ ሰለሞን ጥዑመልሳን እናት ወይዘሮ ቀኑብሽ አባማነው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።
የቀብር ሥነ-ሥርዓት መረጃ፦
ረቡዕ መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም.
በፈረንሳይ ለጋሲዮን ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ከቀኑ 8:30 ይፈጸማል።
ለጋዜጠኛ ሰለሞን ጥዑመልሳን፣ ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።
ለሟች እናታችንም
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑርልን።
#getu #ethiopia #solomontiumelsan #ebc #addisautomotive #condolences #restinpeace #addisababa #ሐዘን #ቀብር #ሰለሞንጥዑመልሳን #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | የአዲስ አውቶሞቲቭ የሬዲዮ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (EBC) አንጋፋ የዜና አንባቢ የጋዜጠኛ ሰለሞን ጥዑመልሳን እናት ወይዘሮ ቀኑብሽ አባማነው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።
የቀብር ሥነ-ሥርዓት መረጃ፦
ረቡዕ መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም.
በፈረንሳይ ለጋሲዮን ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ከቀኑ 8:30 ይፈጸማል።
ለጋዜጠኛ ሰለሞን ጥዑመልሳን፣ ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።
ለሟች እናታችንም
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑርልን።
#getu #ethiopia #solomontiumelsan #ebc #addisautomotive #condolences #restinpeace #addisababa #ሐዘን #ቀብር #ሰለሞንጥዑመልሳን #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
መሪር ሐዘን በኢትዮጵያ ሲኒማ
የ"አሸንጌ" ፊልም ዳይሬክተር ጳውሎስ ረጋሳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
#ethiopia | የኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ አንዱን ድንቅ ባለሙያውን አጥቷል።
በፊልም ዳይሬክተርነቱ፣ በሙዚቃ ቀማሪነቱና በፖስት ፕሮዳክሽን (Post-production) ሊቅነቱ የሚታወቀው ጳውሎስ ረጋሳ ዛሬ፣ ቅዳሜ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ጳውሎስ በተለይ "አሸንጌ" የተሰኘውን ድንቅ ፊልም ለታዳሚ በማቅረብ የሚታወስ ባለሙያ ነው።
ለብዙ የዘርፉ ባለሙያዎች የሲኒማ ጥበብ መምህር፣ በተግሳጽና በምክር ያሳደገ ታላቅ ወንድም እንዲሁም ነገሩ ሁሉ ፊት ለፊት የሆነ እውነተኛ ባለሙያ ነበር።
ከዳይሬክተርነት ባለፈ በሙዚቃ ቅንብርና በፊልም ቴክኒክ ሥራዎች ላይ የነበረው ተሰጥኦ ለኢትዮጵያ ሲኒማ ዕድገት ትልቅ አሻራ ጥሎ አልፏል።
ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጆቹና ለመላው የኪነጥበብ ቤተሰብ መጽናናትን እንመኛለን።
የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ፦
መቼ እንደሚከናወን አስከሬኑ ከሕንድ ሲመጣ የምናሳውቅ ይሆናል።
የጥበብ ሰው ጳውሎስ ረጋሳ ነፍስ ይማር!
#getu #ethiopia #cinema #filmmaking #ashengefilm #paulosregassa #art #tribute #ኢትዮጵያ #ሲኒማ #ጳውሎስረጋሳ #አሸንጌ #ሐዘን #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የ"አሸንጌ" ፊልም ዳይሬክተር ጳውሎስ ረጋሳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
#ethiopia | የኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ አንዱን ድንቅ ባለሙያውን አጥቷል።
በፊልም ዳይሬክተርነቱ፣ በሙዚቃ ቀማሪነቱና በፖስት ፕሮዳክሽን (Post-production) ሊቅነቱ የሚታወቀው ጳውሎስ ረጋሳ ዛሬ፣ ቅዳሜ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ጳውሎስ በተለይ "አሸንጌ" የተሰኘውን ድንቅ ፊልም ለታዳሚ በማቅረብ የሚታወስ ባለሙያ ነው።
ለብዙ የዘርፉ ባለሙያዎች የሲኒማ ጥበብ መምህር፣ በተግሳጽና በምክር ያሳደገ ታላቅ ወንድም እንዲሁም ነገሩ ሁሉ ፊት ለፊት የሆነ እውነተኛ ባለሙያ ነበር።
ከዳይሬክተርነት ባለፈ በሙዚቃ ቅንብርና በፊልም ቴክኒክ ሥራዎች ላይ የነበረው ተሰጥኦ ለኢትዮጵያ ሲኒማ ዕድገት ትልቅ አሻራ ጥሎ አልፏል።
ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጆቹና ለመላው የኪነጥበብ ቤተሰብ መጽናናትን እንመኛለን።
የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ፦
መቼ እንደሚከናወን አስከሬኑ ከሕንድ ሲመጣ የምናሳውቅ ይሆናል።
የጥበብ ሰው ጳውሎስ ረጋሳ ነፍስ ይማር!
#getu #ethiopia #cinema #filmmaking #ashengefilm #paulosregassa #art #tribute #ኢትዮጵያ #ሲኒማ #ጳውሎስረጋሳ #አሸንጌ #ሐዘን #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
የሞተ አንጎል የተደበቀ ግድያን እንዴት ደረሰበት ? የ12 ዓመታት አስፈሪ ምስጢር የአስክሬን ምርመራ አመለካከትን ቀየረ
በእንግሊዝ በተፈጥሮ ምክንያት እንደሞተች ተገምታ የነበረች አንዲት ሴት፣ ለአንጎል ህክምና ምርምር በለገሰችው የአካል ክፍል አማካኝነት ተገድላ እንደነበር ታወቀ።
በ2010 እ.ኤ.አ. የትምህርት ቤት ፀሐፊ የነበረችው የ47 አመቷ ዳያን ስቱዋርት በቤቷ ውስጥ ህይወቷ አልፎ ተገኘ። ባለቤቷ ኢያን ስቱዋርት ለድንገተኛ አደጋ እርዳታ ደውሎ ዳያን በአትክልት ስፍራው ውስጥ በሚጥል በሽታ እንደወደቀች ተናገረ።
ዳያን የመጨረሻው የሚጥል በሽታ ህመም ያጋጠማት ከ18 ዓመታት በፊት ቢሆንም፣ በወቅቱ በዚሁ በሽታ ምክንያት እንደሞተች ተገምቶ ነበር። የዳያን አስክሬን እንዲቃጠል ቢደረግም፣ አንጎሏ ግን ለሳይንሳዊ ምርምር እንዲለገስ ተደርጎ ነበር።
ዳያን ከሞተች ከአንድ ዓመት በኋላ፣ ኢያን በሐዘንተኞች መርጃ ቡድን ውስጥ ሄለን ቤይሊ የተባለች የ51 አመት ዝነኛ የልጆች መጽሐፍ ደራሲን አገኘ።
ሁለቱ ተቀራርበው በአንድ ላይ መኖር የጀመሩ ሲሆን ቤትም ገዙ። ነገር ግን የሄለን መጨረሻ እንደ መጀመሪያዋ ሚስቱ እንደ ዳያን ሆነ፤ ኢያን አንቆ ገደላት።
የአስክሬን ምርመራ ውጤቱን ለወጠው
ኢያን የሄለንን አስክሬን በቤቱ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ውስጥ ደበቀው። አስክሬኑ ከሦስት ወራት በኋላ ተገኘ። ኢያን በሄለን ግድያ በቁጥጥር ስር ሲውል፣ ፖሊስ የቀድሞ ሚስቱን የዳያንን ሞት በድጋሚ መመርመር ጀመረ።
በምርምር ማዕከል ተጠብቆ የቆየው የዳያን አንጎል በባለሙያዎች በጥልቀት ተመረመረ። ባለሙያዎቹም ሞቷ በሚጥል በሽታ ሳይሆን በኦክስጅን እጥረት ምክንያት የመጣ የአንጎል ጉዳት መሆኑን ደረሱበት።
በ2022 እ.ኤ.አ. የተጠናቀቀው ምርመራ ኢያን ስቱዋርት በዳያንም ግድያ ጥፋተኛ መሆኑን አረጋገጠ። ኢያን ግድያዎቹን የፈጸመው የኢንሹራንስ ክፍያ ገንዘብ ለማግኘት እንደሆነ ይታመናል። በአሁኑ ወቅት የዕድሜ ልክ እስራት እየፈረደበት ይገኛል።
ባለሙያዎች እንደሚናገሩት ከሆነ ከዚህ ክስተት በኋላ የአንጎል ምርመራ አሠራር ሥርዓት ተለውጧል።
ምንጮች: Sky News፣The Guardian፣ እና BBC News
በእንግሊዝ በተፈጥሮ ምክንያት እንደሞተች ተገምታ የነበረች አንዲት ሴት፣ ለአንጎል ህክምና ምርምር በለገሰችው የአካል ክፍል አማካኝነት ተገድላ እንደነበር ታወቀ።
በ2010 እ.ኤ.አ. የትምህርት ቤት ፀሐፊ የነበረችው የ47 አመቷ ዳያን ስቱዋርት በቤቷ ውስጥ ህይወቷ አልፎ ተገኘ። ባለቤቷ ኢያን ስቱዋርት ለድንገተኛ አደጋ እርዳታ ደውሎ ዳያን በአትክልት ስፍራው ውስጥ በሚጥል በሽታ እንደወደቀች ተናገረ።
ዳያን የመጨረሻው የሚጥል በሽታ ህመም ያጋጠማት ከ18 ዓመታት በፊት ቢሆንም፣ በወቅቱ በዚሁ በሽታ ምክንያት እንደሞተች ተገምቶ ነበር። የዳያን አስክሬን እንዲቃጠል ቢደረግም፣ አንጎሏ ግን ለሳይንሳዊ ምርምር እንዲለገስ ተደርጎ ነበር።
ዳያን ከሞተች ከአንድ ዓመት በኋላ፣ ኢያን በሐዘንተኞች መርጃ ቡድን ውስጥ ሄለን ቤይሊ የተባለች የ51 አመት ዝነኛ የልጆች መጽሐፍ ደራሲን አገኘ።
ሁለቱ ተቀራርበው በአንድ ላይ መኖር የጀመሩ ሲሆን ቤትም ገዙ። ነገር ግን የሄለን መጨረሻ እንደ መጀመሪያዋ ሚስቱ እንደ ዳያን ሆነ፤ ኢያን አንቆ ገደላት።
የአስክሬን ምርመራ ውጤቱን ለወጠው
ኢያን የሄለንን አስክሬን በቤቱ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ውስጥ ደበቀው። አስክሬኑ ከሦስት ወራት በኋላ ተገኘ። ኢያን በሄለን ግድያ በቁጥጥር ስር ሲውል፣ ፖሊስ የቀድሞ ሚስቱን የዳያንን ሞት በድጋሚ መመርመር ጀመረ።
በምርምር ማዕከል ተጠብቆ የቆየው የዳያን አንጎል በባለሙያዎች በጥልቀት ተመረመረ። ባለሙያዎቹም ሞቷ በሚጥል በሽታ ሳይሆን በኦክስጅን እጥረት ምክንያት የመጣ የአንጎል ጉዳት መሆኑን ደረሱበት።
በ2022 እ.ኤ.አ. የተጠናቀቀው ምርመራ ኢያን ስቱዋርት በዳያንም ግድያ ጥፋተኛ መሆኑን አረጋገጠ። ኢያን ግድያዎቹን የፈጸመው የኢንሹራንስ ክፍያ ገንዘብ ለማግኘት እንደሆነ ይታመናል። በአሁኑ ወቅት የዕድሜ ልክ እስራት እየፈረደበት ይገኛል።
ባለሙያዎች እንደሚናገሩት ከሆነ ከዚህ ክስተት በኋላ የአንጎል ምርመራ አሠራር ሥርዓት ተለውጧል።
ምንጮች: Sky News፣The Guardian፣ እና BBC News
3 months ago
ድጋፋ ቀጥሏል !!!
በጋሞ ዞን በደረሰው ድንገተኛ አደጋ ለተጎዱ ወገኖቻችን የ150,000 ሺህ ብር(አናያር ትሬዲንግ ,አግሮ ማይን , እሺ ሚዲያ እና ኮምኒኬሽን) የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።
የድጋፍ ገንዘብ ርክክቡን ያከናወኑት ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳና ልዑካቸው ባስተላለፉት መልዕክትበአደጋው ምክንያት ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸው መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢንስትራክተር ነፃነት ይህ ድጋፍ የመጀመሪያ ዙር መሆኑንና በቀጣይም አጋርነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ድጋፉን የተረከቡት የጋሞ አባቶችና የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ በበኩላቸው፤ ተቋማቱ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ላሳየው ወንድማዊ አጋርነትና ላደረጉት ድጋፍ በዞኑ ሕዝብና በመንግሥት ስም ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል ከጉዳቱ ክብደት የተነሳ ሌሎች ወገኖችም እገዛቸውን እንዲቀጥሉ አሳስበዋል ።
የጋሞ ዞን አደጋ ስጋት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር CBE፦ 1000321312865
በጋሞ ዞን በደረሰው ድንገተኛ አደጋ ለተጎዱ ወገኖቻችን የ150,000 ሺህ ብር(አናያር ትሬዲንግ ,አግሮ ማይን , እሺ ሚዲያ እና ኮምኒኬሽን) የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።
የድጋፍ ገንዘብ ርክክቡን ያከናወኑት ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳና ልዑካቸው ባስተላለፉት መልዕክትበአደጋው ምክንያት ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸው መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢንስትራክተር ነፃነት ይህ ድጋፍ የመጀመሪያ ዙር መሆኑንና በቀጣይም አጋርነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ድጋፉን የተረከቡት የጋሞ አባቶችና የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ በበኩላቸው፤ ተቋማቱ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ላሳየው ወንድማዊ አጋርነትና ላደረጉት ድጋፍ በዞኑ ሕዝብና በመንግሥት ስም ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል ከጉዳቱ ክብደት የተነሳ ሌሎች ወገኖችም እገዛቸውን እንዲቀጥሉ አሳስበዋል ።
የጋሞ ዞን አደጋ ስጋት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር CBE፦ 1000321312865
3 months ago
አራት የቤተሰብ አባላትን የቀማው የመሬት ናዳ ያልሰበረው ታላቅ ስብዕና እና ጽናት
#fastmereja I መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ የደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋው በተከሰተበት ወቅት፣ አቶ ዳመነ ሌሎች ተጎጂዎችን ለማዳን በፍጥነት ወደ ስፍራው ቢያቀኑም፤ በዚያው ቅጽበት ግን ባለቤታቸውን፣ ልጃቸውን፣ የልጃቸውን ሚስትና የልጅ ልጃቸውን በአደጋው ማጣታቸውን ይገልጻሉ።
በደቂቃዎች ልዩነት አራት የቤተሰብ አባላትን በዓይናቸው እያዩ የማጣት ከባድ ፈተና የገጠማቸው እኚህ አባት፤ በአካባቢው በነበረው አስቸጋሪ መልክዓ ምድር ምክንያትም የቤተሰቦቻቸውን አስክሬን ለማግኘት ለአራት ቀናት በመከራ ውስጥ ለመቆየት ተገደዋል።
ይሁን እንጂ ይህ መሪር ሐዘን የአቶ ዳመነን ታላቅ ስብዕና ሊሰብረው አልቻለም። እንዲያውም ከራሳቸው ሐዘን በላይ ለተጎዳው ማኅበረሰባቸው መቆምን መርጠዋል።
የቀበሌው ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ዳመነ፣ ለሌሎች ተጎጂዎች የመጽናኛ ተምሳሌት በመሆን ሕዝቡ ከደረሰበት ድንጋጤ ወጥቶ ወደ መደበኛ የልማት ሥራው እንዲመለስ በትጋት እያስተማሩ ይገኛሉ።
የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ዳመነ፣ ለተጎጂዎች እየተደረገ ያለው ሰብዓዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
አያይዘውም አካባቢው ለተፈጥሮ አደጋ ተጋላጭ በመሆኑ፣ መሰል ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ አማራጭ የመፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አሳስበዋል ሲል ኢቢሲ ነው የዘገበው።
#fastmereja I መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ የደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋው በተከሰተበት ወቅት፣ አቶ ዳመነ ሌሎች ተጎጂዎችን ለማዳን በፍጥነት ወደ ስፍራው ቢያቀኑም፤ በዚያው ቅጽበት ግን ባለቤታቸውን፣ ልጃቸውን፣ የልጃቸውን ሚስትና የልጅ ልጃቸውን በአደጋው ማጣታቸውን ይገልጻሉ።
በደቂቃዎች ልዩነት አራት የቤተሰብ አባላትን በዓይናቸው እያዩ የማጣት ከባድ ፈተና የገጠማቸው እኚህ አባት፤ በአካባቢው በነበረው አስቸጋሪ መልክዓ ምድር ምክንያትም የቤተሰቦቻቸውን አስክሬን ለማግኘት ለአራት ቀናት በመከራ ውስጥ ለመቆየት ተገደዋል።
ይሁን እንጂ ይህ መሪር ሐዘን የአቶ ዳመነን ታላቅ ስብዕና ሊሰብረው አልቻለም። እንዲያውም ከራሳቸው ሐዘን በላይ ለተጎዳው ማኅበረሰባቸው መቆምን መርጠዋል።
የቀበሌው ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ዳመነ፣ ለሌሎች ተጎጂዎች የመጽናኛ ተምሳሌት በመሆን ሕዝቡ ከደረሰበት ድንጋጤ ወጥቶ ወደ መደበኛ የልማት ሥራው እንዲመለስ በትጋት እያስተማሩ ይገኛሉ።
የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ዳመነ፣ ለተጎጂዎች እየተደረገ ያለው ሰብዓዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
አያይዘውም አካባቢው ለተፈጥሮ አደጋ ተጋላጭ በመሆኑ፣ መሰል ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ አማራጭ የመፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አሳስበዋል ሲል ኢቢሲ ነው የዘገበው።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የአርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ ወላጅ እናት ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
#ethiopia | ታዋቂው አርቲስት፣ ዳይሬክተርና የሠራዊት ፍቅሬ ፕሮሞሽን ባለቤት ሠራዊት ፍቅሬ ወላጅ እናት ወይዘሮ በለጥሻቸው ማመጫ በተወለዱ በ89 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
የቀብ
የወይዘሮ በለጥሻቸው ማመጫ ሥርዓተ ቀብር ነገ ማክሰኞ መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በየካ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ ይፈጸማል።
ለሟች ቤተሰቦች ሐዘን መድረስ ለሚፈልጉ ወዳጅ ዘመዶች በሙሉ፣ መኖሪያ ቤታቸው ካዛንችስ ከእንደራሴ ሆቴል በስተጀርባ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽንስ በወይዘሮ በለጥሻቸው ሕልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ፣ ለአርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ፣ ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ በሙሉ መጽናናትን ይመኛል።
ፈጣሪ የሟቹን ነፍስ በአጸደ ገነት ያኑር።
#ሠራዊትፍቅሬ #ሐዘን #ኢትዮጵያ #አዲስአበባ #ካዛንችስ #አርቲስትሠራዊትፍቅሬ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ታዋቂው አርቲስት፣ ዳይሬክተርና የሠራዊት ፍቅሬ ፕሮሞሽን ባለቤት ሠራዊት ፍቅሬ ወላጅ እናት ወይዘሮ በለጥሻቸው ማመጫ በተወለዱ በ89 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
የቀብ
የወይዘሮ በለጥሻቸው ማመጫ ሥርዓተ ቀብር ነገ ማክሰኞ መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በየካ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ ይፈጸማል።
ለሟች ቤተሰቦች ሐዘን መድረስ ለሚፈልጉ ወዳጅ ዘመዶች በሙሉ፣ መኖሪያ ቤታቸው ካዛንችስ ከእንደራሴ ሆቴል በስተጀርባ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽንስ በወይዘሮ በለጥሻቸው ሕልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ፣ ለአርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ፣ ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ በሙሉ መጽናናትን ይመኛል።
ፈጣሪ የሟቹን ነፍስ በአጸደ ገነት ያኑር።
#ሠራዊትፍቅሬ #ሐዘን #ኢትዮጵያ #አዲስአበባ #ካዛንችስ #አርቲስትሠራዊትፍቅሬ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጋሞ ዞን በደረሰው አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገለጹ
#ethiopia | የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በደረሰው አስከፊ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ የሐዘን መግለጫ መልዕክታቸውን ለኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶች መጽናናትን የተመኙ ሲሆን፣ ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎችም በፍጥነት እንዲያገግሙ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
ስለ አደጋው አጠቃላይ መረጃ
በጋሞ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የካቲት 30 እና መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለው የጎርፍ እና የመሬት ናዳ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ይታወሳል። የዞኑ መረጃ እንደሚያመለክተው፦
* አደጋው በተለያዩ ወረዳዎች የተከሰተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተጎዱ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።
ይህ የሩሲያ ፕሬዚዳንት መግለጫ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነትና በአስቸጋሪ ወቅት የሚታይ አጋርነትን የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጋሞ_ዞን #የመሬት_መንሸራተት #የሐዘን_መግለጫ #ቭላድሚር_ፑቲን #ኢትዮጵያ #ሩሲያ #ተፈጥሮ_አደጋ
#ethiopia | የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በደረሰው አስከፊ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ የሐዘን መግለጫ መልዕክታቸውን ለኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶች መጽናናትን የተመኙ ሲሆን፣ ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎችም በፍጥነት እንዲያገግሙ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
ስለ አደጋው አጠቃላይ መረጃ
በጋሞ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የካቲት 30 እና መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለው የጎርፍ እና የመሬት ናዳ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ይታወሳል። የዞኑ መረጃ እንደሚያመለክተው፦
* አደጋው በተለያዩ ወረዳዎች የተከሰተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተጎዱ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።
ይህ የሩሲያ ፕሬዚዳንት መግለጫ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነትና በአስቸጋሪ ወቅት የሚታይ አጋርነትን የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጋሞ_ዞን #የመሬት_መንሸራተት #የሐዘን_መግለጫ #ቭላድሚር_ፑቲን #ኢትዮጵያ #ሩሲያ #ተፈጥሮ_አደጋ
Comments