Logo
Getu Temesgen
አንቸሎቲ፦ “ዛሬ ማሸነፍ ይገባን ነበር”
#ethiopia | የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ ቡድናቸው ከ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር መሰናበቱን ተከትሎ ከፍተኛ ሐዘን እንደተሰማቸው ገልጸዋል።

አንቸሎቲ ከጨዋታው በኋላ ለመገናኛ ብዙኃን ሲናገሩ፣ “ሁላችንም በጣም አዝነናል። ቡድኑ ድንቅ የዓለም ዋንጫ ባያሳልፍም ጥሩ ውድድር አድርጓል” ብለዋል።

አሰልጣኙ በዕለቱ በተደረገው ጨዋታ ብራዚል ድል ይገባት እንደነበር በመግለጽ፣ “ዛሬ ማሸነፍ ይገባን ነበር። እንደዚህ ያለ ሽንፈት ሲያጋጥም ይህንን እንደ አዲስ ጉዞና አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ መመልከት አለብን” ሲሉ ተናግረዋል።

ብራዚል በ16 ቡድኖች ዙር በኖርዌይ 2 ለ1 ተሸንፋ ከውድድሩ ስትሰናበት፣ ኖርዌይ ደግሞ ወደ ሩብ ፍጻሜ ማለፏን አረጋግጣለች።

1 month ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.