2 hours ago
ኢትዮጵያ እየተጠናቀቀ ባለው 2018 ዓ.ም ከ124 በላይ ዓለም አቀፍ ሜዳሊያዎች መገኘታቸውን ተገለጸ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ እይታን በመፍጠር፣ ህጋዊና መዋቅራዊ ማዕቀፎችን በማጠናከር እንዲሁም በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ የ2018 በጀት ዓመት አመርቂና ስኬታማ ጊዜ የነበረ መሆኑ ተገለጸ።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚያካሄደው የባህል፣ ጥበባትና ስፖርት ጥናትና ምርምር ጉባኤ እንዲሁም ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ ላይ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ መክዩ መሀመድ እንደገለጹት፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ የታቀዱ ግቦችን በጋራ ለመገምገም እና ከክልል እስከ ፌደራል ያሉ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
አክለውም ዘንድሮ የስፖርት ልማት ስራዎች በተሻለ መንገድ የተፈጸሙበትና በአጠቃላይ የስፖርት ዘመን ተብሎ ሊወሰድ የሚችልበት የስኬት ዓመት እንደነበር ጠቁመዋል።
የስፖርት ቤተሰቡ በተደጋጋሚ ያነሳቸው የነበሩ ህጋዊና አሰራር ነክ ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትር ድኤታው፣ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትና ምሁራንን ያሳተፈ አዲስ የስፖርት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁንና አዋጁም ወደ ትግበራ መግባቱን አስረድተዋል።
ይህ አዲስ ፖሊሲ የመንግስትን አመራር ሰጪነት፣ ከ139 ሺህ በላይ የሚሆኑ ህዝባዊ አደረጃጀቶችንና ማህበራትን አቅጣጫ፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚያፋጥነው የግል ባለሀብቶች ተሳትፎን በግልጽ የለየ አዲስ እይታ ይዞ መምጣቱንም አብራርተዋል።
ስፖርት ከሜዳ ውድድር ባለፈ የህዝቦች ወንድማማችነትን የሚገነባ፣ ሰላምና አንድነትን የሚያጠናክር ትልቅ የሀገር ልማት መሳሪያ መሆኑን የገለጹት አቶ መክዩ መሀመድ፣ በዚህ ዓመት በተካሄዱ 420 የክልል አቀፍ እና 118 ሀገር አቀፍ ውድድሮች ከአስር ሺዎች በላይ ስፖርተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። እነዚህ መድረኮች የወጡ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ሰላምን በመገንባትና ህዝቦችን በማቀራረብ ረገድ የጎላ ሚና እንደነበራቸው አብራርተዋል።
ህብረተሰቡን ንቁና ስፖርትን ባህል ያደረገ ለማድረግ በተሰራው ስራ የስፖርት አዘዋታሪው ህዝብ ቁጥር 24 በመቶ ወይም 32 ሚሊዮን ማድረስ መቻሉን ሚኒስትር ድኤታው ጠቁመዋል። ከዚህ በተጨማሪ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ ከ45 ሺህ በላይ የስፖርት ፋሲሊቲዎች መገንባታቸውንና እነዚህንም በቴክኖሎጂ ዘመናዊ የማድረግ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በአለም አቀፍና ቀጠናዊ ውድድሮች የሀገሪቱን ስም የሚያስጠሩ አሸናፊ ብሄራዊ ቡድኖችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አትሌቶቻችን ከ124 በላይ ሜዳሊያዎችን ማስመዝገባቸውን አቶ መክዩ መሀመድ አበክረው ገልጸዋል።
በተለይም በታዳጊዎች ልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ45 ሺህ በላይ ታዳጊዎች በማሰልጠኛ ማዕከላት ውስጥ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የስፖርት ቱሪዝምን ለማበራታት በተደረገው ጥረት ከ29 በላይ ዓለም አቀፍ ውድድሮችና ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ መካሄዳቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች ግንባታም ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ስፖርት ለሀገር ጂዲፒ እና ለስራ እድል ፈጠራ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የተጀመሩ ጥናቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።
በመጨረሻም፣ በአዲሱ ፖሊሲ የባህል ስፖርት ልዩ ትኩረት ማግኘቱንና በቀጣይ ዓመት ኢትዮጵያ የአፍሪካ የባህል ስፖርት ፌስቲቫልን በበላይነት እንደምታዘጋጅ አቶ መክዩ መሀመድ ገልጸው፤ ላመጣው ስኬት ለስፖርት ቤተሰቡና ለመገናኛ ብዙሃን አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopiansports #ethiopiasportpolicy #sportsdevelopment #ethiopia#youthinsports #sportinspiration
#ethiopia | በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ እይታን በመፍጠር፣ ህጋዊና መዋቅራዊ ማዕቀፎችን በማጠናከር እንዲሁም በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ የ2018 በጀት ዓመት አመርቂና ስኬታማ ጊዜ የነበረ መሆኑ ተገለጸ።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚያካሄደው የባህል፣ ጥበባትና ስፖርት ጥናትና ምርምር ጉባኤ እንዲሁም ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ ላይ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ መክዩ መሀመድ እንደገለጹት፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ የታቀዱ ግቦችን በጋራ ለመገምገም እና ከክልል እስከ ፌደራል ያሉ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
አክለውም ዘንድሮ የስፖርት ልማት ስራዎች በተሻለ መንገድ የተፈጸሙበትና በአጠቃላይ የስፖርት ዘመን ተብሎ ሊወሰድ የሚችልበት የስኬት ዓመት እንደነበር ጠቁመዋል።
የስፖርት ቤተሰቡ በተደጋጋሚ ያነሳቸው የነበሩ ህጋዊና አሰራር ነክ ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትር ድኤታው፣ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትና ምሁራንን ያሳተፈ አዲስ የስፖርት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁንና አዋጁም ወደ ትግበራ መግባቱን አስረድተዋል።
ይህ አዲስ ፖሊሲ የመንግስትን አመራር ሰጪነት፣ ከ139 ሺህ በላይ የሚሆኑ ህዝባዊ አደረጃጀቶችንና ማህበራትን አቅጣጫ፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚያፋጥነው የግል ባለሀብቶች ተሳትፎን በግልጽ የለየ አዲስ እይታ ይዞ መምጣቱንም አብራርተዋል።
ስፖርት ከሜዳ ውድድር ባለፈ የህዝቦች ወንድማማችነትን የሚገነባ፣ ሰላምና አንድነትን የሚያጠናክር ትልቅ የሀገር ልማት መሳሪያ መሆኑን የገለጹት አቶ መክዩ መሀመድ፣ በዚህ ዓመት በተካሄዱ 420 የክልል አቀፍ እና 118 ሀገር አቀፍ ውድድሮች ከአስር ሺዎች በላይ ስፖርተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። እነዚህ መድረኮች የወጡ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ሰላምን በመገንባትና ህዝቦችን በማቀራረብ ረገድ የጎላ ሚና እንደነበራቸው አብራርተዋል።
ህብረተሰቡን ንቁና ስፖርትን ባህል ያደረገ ለማድረግ በተሰራው ስራ የስፖርት አዘዋታሪው ህዝብ ቁጥር 24 በመቶ ወይም 32 ሚሊዮን ማድረስ መቻሉን ሚኒስትር ድኤታው ጠቁመዋል። ከዚህ በተጨማሪ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ ከ45 ሺህ በላይ የስፖርት ፋሲሊቲዎች መገንባታቸውንና እነዚህንም በቴክኖሎጂ ዘመናዊ የማድረግ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በአለም አቀፍና ቀጠናዊ ውድድሮች የሀገሪቱን ስም የሚያስጠሩ አሸናፊ ብሄራዊ ቡድኖችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አትሌቶቻችን ከ124 በላይ ሜዳሊያዎችን ማስመዝገባቸውን አቶ መክዩ መሀመድ አበክረው ገልጸዋል።
በተለይም በታዳጊዎች ልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ45 ሺህ በላይ ታዳጊዎች በማሰልጠኛ ማዕከላት ውስጥ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የስፖርት ቱሪዝምን ለማበራታት በተደረገው ጥረት ከ29 በላይ ዓለም አቀፍ ውድድሮችና ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ መካሄዳቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች ግንባታም ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ስፖርት ለሀገር ጂዲፒ እና ለስራ እድል ፈጠራ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የተጀመሩ ጥናቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።
በመጨረሻም፣ በአዲሱ ፖሊሲ የባህል ስፖርት ልዩ ትኩረት ማግኘቱንና በቀጣይ ዓመት ኢትዮጵያ የአፍሪካ የባህል ስፖርት ፌስቲቫልን በበላይነት እንደምታዘጋጅ አቶ መክዩ መሀመድ ገልጸው፤ ላመጣው ስኬት ለስፖርት ቤተሰቡና ለመገናኛ ብዙሃን አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopiansports #ethiopiasportpolicy #sportsdevelopment #ethiopia#youthinsports #sportinspiration
11 hours ago
ቱሪዝም - የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጫ አንዱ መሳሪያ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ውስጥ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የቱሪዝም ዘርፉ ከዋና ዋናዎቹ የክፍለ ኢኮኖሚው ምሰሶዎች ዝርዝር በመግባቱ ለዘርፉ በርካታ መሰረተ ልማቶች ተሰርተዋል፡፡
ኢትዮጵያም ለሌሎችም የሚተርፍ ገቢን መፍጠር የሚያስችል እምቅ የቱሪዝም ሃብት ቢኖራትም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ አልተጠቀመችበትም ነበር።
ዘርፉ እንዲያንሰራራ ፖሊሲ የማውጣት፣ ተቋማትን የማዋቀር፣ አዳዲስ ልማቶችን የማከናወን ሥራ ተከናውኗል፡፡
ከለውጡ ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ቅርሶችን ከመጠገን ባለፈ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተገንብተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ እመርታ በማሳየት የሀገሪቱ ዋና የኢኮኖሚ ምንጭ እየሆነ መጥቷል።
የመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ከነበረበት መዘናጋት በማውጣት የሀገሪቱን ብልጽግና ከሚያረጋግጡ ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
መንግሥት ዘርፉን እንደ አንድ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ምሰሶ አድርጎ በመቅረጽ፣ አዳዲስ ግዙፍ መዳረሻዎችን በመገንባት እና ነባር የባህል፣ የታሪክና የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
ቱሪዝምን ከተፈጥሮ ጥበቃ እና ከማህበረሰብ ልማት ጋር ያቀናጁ የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶችን መቅረጽና መተግበር ነው።
በርካታ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን በመሳብ ለሀገሪቱ ገቢና የስራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
ለዘርፉ እድገት መንግሥት በሰጠው ትኩረት አዳዲስ መዳረሻዎችና መሠረተ ልማቶች ተገንብተዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ እና በሌሎችም የሀገሪቱ ከተሞች የተከናወኑት የኮሪደር ልማቶች የከተሞችን ውበት በማጎልበት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ቱሪዝሙን ማነቃቃት ተችሏል፡፡
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የፋሲለደስ ግንብ እና የጁገል ግንብ የመሳሰሉ አንጋፋ ቅርሶችን የመጠበቅና የዕድሳት ሥራዎች በስፋት ተግባራዊ ተደርገዋል፡፡
ከውጭ ጎብኚዎች ባለፈ፣ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ከፍተኛ እድገት እያሳየ ሲሆን፤ ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁና እንዲጎበኙ በማድረግ፤ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን አጠናክሯል።
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ የሀገሪቱን አወንታዊ ገጽታ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቅ ረገድ የማይተካ ሚና አለው።
የቱሪዝም መዳረሻዎችን በዘመናዊ መንገድ የማልማትና አገልግሎቶችን የማዘመን ሥራዎችም በስፋት እየተሰሩ ነው፡፡
ኢኮኖሚው በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት መደረጉ በቱሪዝም ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ይበልጥ መጠቀም የሚያስችል ዕድል ፈጥሯል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ውስጥ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የቱሪዝም ዘርፉ ከዋና ዋናዎቹ የክፍለ ኢኮኖሚው ምሰሶዎች ዝርዝር በመግባቱ ለዘርፉ በርካታ መሰረተ ልማቶች ተሰርተዋል፡፡
ኢትዮጵያም ለሌሎችም የሚተርፍ ገቢን መፍጠር የሚያስችል እምቅ የቱሪዝም ሃብት ቢኖራትም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ አልተጠቀመችበትም ነበር።
ዘርፉ እንዲያንሰራራ ፖሊሲ የማውጣት፣ ተቋማትን የማዋቀር፣ አዳዲስ ልማቶችን የማከናወን ሥራ ተከናውኗል፡፡
ከለውጡ ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ቅርሶችን ከመጠገን ባለፈ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተገንብተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ እመርታ በማሳየት የሀገሪቱ ዋና የኢኮኖሚ ምንጭ እየሆነ መጥቷል።
የመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ከነበረበት መዘናጋት በማውጣት የሀገሪቱን ብልጽግና ከሚያረጋግጡ ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
መንግሥት ዘርፉን እንደ አንድ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ምሰሶ አድርጎ በመቅረጽ፣ አዳዲስ ግዙፍ መዳረሻዎችን በመገንባት እና ነባር የባህል፣ የታሪክና የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
ቱሪዝምን ከተፈጥሮ ጥበቃ እና ከማህበረሰብ ልማት ጋር ያቀናጁ የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶችን መቅረጽና መተግበር ነው።
በርካታ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን በመሳብ ለሀገሪቱ ገቢና የስራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
ለዘርፉ እድገት መንግሥት በሰጠው ትኩረት አዳዲስ መዳረሻዎችና መሠረተ ልማቶች ተገንብተዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ እና በሌሎችም የሀገሪቱ ከተሞች የተከናወኑት የኮሪደር ልማቶች የከተሞችን ውበት በማጎልበት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ቱሪዝሙን ማነቃቃት ተችሏል፡፡
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የፋሲለደስ ግንብ እና የጁገል ግንብ የመሳሰሉ አንጋፋ ቅርሶችን የመጠበቅና የዕድሳት ሥራዎች በስፋት ተግባራዊ ተደርገዋል፡፡
ከውጭ ጎብኚዎች ባለፈ፣ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ከፍተኛ እድገት እያሳየ ሲሆን፤ ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁና እንዲጎበኙ በማድረግ፤ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን አጠናክሯል።
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ የሀገሪቱን አወንታዊ ገጽታ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቅ ረገድ የማይተካ ሚና አለው።
የቱሪዝም መዳረሻዎችን በዘመናዊ መንገድ የማልማትና አገልግሎቶችን የማዘመን ሥራዎችም በስፋት እየተሰሩ ነው፡፡
ኢኮኖሚው በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት መደረጉ በቱሪዝም ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ይበልጥ መጠቀም የሚያስችል ዕድል ፈጥሯል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
18 hours ago
የኢትዮጵያ አስደናቂ የብዝሃ ኢኮኖሚና እምቅ የቱሪዝም አቅም በሲኤንኤን (CNN) ዕይታ
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
2 days ago
805.3 ሚሊዮን ችግኞች በአንድ ጀምበር፤ የኢትዮጵያውያን ተአምራዊ ውሎ
*********************
ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በአንድ ልብ እና በአንድ መንፈስ በመንቀሳቀስ በአንድ ጀምበር 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ፅፈዋል።
ኢትዮጵያውያን የዕድሜ ልዩነት ሳይበግራቸው ከሕፃናት እስከ አዛውንት ከአካል ጉዳተኞች እስከ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች በጋራ በመሆን አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። ይህ የነቃ ተሳትፎም የማህበረሰቡን አንድነትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ነው።
ይህ መርሃ ግብር ልጆችን በማሳተፍ ስለ አካባቢ ጥበቃ አስፈላጊነት በተግባር የሚማሩበት ልዩ መድረክ ሆኗል። ህፃናት ከወዲሁ የችግኝ እንክብካቤን እንደ ባህል እንዲለምዱና የነገዋን አረንጓዴ አገር የመረከብ ሃላፊነታቸውን ገና በሕፃንነታቸው እንዲረዱ ያግዛል።
በተጨማሪም ሀገራዊ አንድነትን በተግባር ከመግለጹ በላይ ለአየር ንብረት ለውጥ አሳሳቢ ፈተናዎች ምላሽ ለመስጠትና የኢትዮጵያን የመጻኢ ዘመን ዕጣ ፈንታ በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ያለመ ንቅናቄ ነው።
ይህ የተቀናጀ ሀገራዊ ርብርብ የትናንቱ የአድዋ ድል የነፃነት አርበኝነት በተፈጥሮ ጥበቃ የሚደገምበት የዘመናችን የጀግንነት ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል።
ቀደምት አባቶች በአድዋ ተራሮች ላይ ልዩነቶቻቸውን አክስመው ለሀገር ነፃነት እንደቆሙ ሁሉ የዛሬው ትውልድም ድህነትንና የተፈጥሮ መራቆትን ለማሸነፍ ዕውቀቱን ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።
የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ የአፈር መሸርሸርና የጎርፍ አደጋዎች እንዲቀንሱ እንዲሁም የከርሰ ምድር ውሃ እንዲበለጽግ በማድረግ ረገድ ትልቁን ድርሻ ታበረክታለች።
ከአካባቢ ጥበቃ ፋይዳው ባሻገር መርሐ ግብሩ የሀገሪቱን ምጣኔ ሀብት የሚያነቃቃ ታላቅ ዕድል ፈጥሯል። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወጣቶች በችግኝ ማፍላት በጉድጓድ ዝግጅትና በተከላ ሥራዎች በመሰማራት ሰፊ የሥራ ዕድል ያገኙ ሲሆን በተለይም እንደ ቡና፣ አቮካዶና ማንጎ ያሉ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ተክሎች ትኩረት ማግኘታቸው ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሠረት ጥሏል።
በተጨማሪም ይህ ሀገራዊ ጥረት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት መዛባትን ለመቋቋም የሚረዳና ኢትዮጵያ ለዓለም አረንጓዴ ልማት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሕያው ውርስ ነው።
ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በቅድመ ዝግጅት ከተያዘው እቅድ በላይ በመፈጸም በዛሬዉ ዕለት ብቻ 805.3 ሚሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን 26.2 ሚሊየን ሰዎች ተሳትፈዋል በዚህም 291.4 ሺህ ሄክታር መሬት መሸፈን ተችሏል በዚህም ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው አገራዊ የችግኝ ተከላ ዘመቻ የህዝባችንን የተቀናጀ የተቀናጀ ጥረት እና ለአካባቢ ጥበቃ ያለውን ቁርጠኝነት በአለም አቀፍ ደረጃ ታላቅ ሁነት ሆኖ አልፏል።
በዘንድሮው አመት እስካሁን ባለው ጊዜ ከ6.5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸው የተገለጸ ሲሆን የተያዘውን አጠቃላይ እቅድ ለማጠናቀቅ ቀሪ የሆኑት 1.5 ቢሊዮን ችግኞች ደግሞ በሚቀጥሉት ወራት ተተክለው የሚጠናቀቁ ይሆናል።
የዚህ ታሪካዊ ዘመቻ እውነተኛ ስኬት የሚለካው በተከላው ሂደት ብቻ ሳይሆን ከተከላ በኋላ በሚደረግ ቀጣይነት ያለው እንክብካቤና ጥበቃ በመሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ የተከላቸውን ችግኞች ተንከባክቦ ለፍሬ የማብቃት አደራ አለበት።
በብሌን ደምበሎ
*********************
ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በአንድ ልብ እና በአንድ መንፈስ በመንቀሳቀስ በአንድ ጀምበር 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ፅፈዋል።
ኢትዮጵያውያን የዕድሜ ልዩነት ሳይበግራቸው ከሕፃናት እስከ አዛውንት ከአካል ጉዳተኞች እስከ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች በጋራ በመሆን አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። ይህ የነቃ ተሳትፎም የማህበረሰቡን አንድነትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ነው።
ይህ መርሃ ግብር ልጆችን በማሳተፍ ስለ አካባቢ ጥበቃ አስፈላጊነት በተግባር የሚማሩበት ልዩ መድረክ ሆኗል። ህፃናት ከወዲሁ የችግኝ እንክብካቤን እንደ ባህል እንዲለምዱና የነገዋን አረንጓዴ አገር የመረከብ ሃላፊነታቸውን ገና በሕፃንነታቸው እንዲረዱ ያግዛል።
በተጨማሪም ሀገራዊ አንድነትን በተግባር ከመግለጹ በላይ ለአየር ንብረት ለውጥ አሳሳቢ ፈተናዎች ምላሽ ለመስጠትና የኢትዮጵያን የመጻኢ ዘመን ዕጣ ፈንታ በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ያለመ ንቅናቄ ነው።
ይህ የተቀናጀ ሀገራዊ ርብርብ የትናንቱ የአድዋ ድል የነፃነት አርበኝነት በተፈጥሮ ጥበቃ የሚደገምበት የዘመናችን የጀግንነት ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል።
ቀደምት አባቶች በአድዋ ተራሮች ላይ ልዩነቶቻቸውን አክስመው ለሀገር ነፃነት እንደቆሙ ሁሉ የዛሬው ትውልድም ድህነትንና የተፈጥሮ መራቆትን ለማሸነፍ ዕውቀቱን ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።
የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ የአፈር መሸርሸርና የጎርፍ አደጋዎች እንዲቀንሱ እንዲሁም የከርሰ ምድር ውሃ እንዲበለጽግ በማድረግ ረገድ ትልቁን ድርሻ ታበረክታለች።
ከአካባቢ ጥበቃ ፋይዳው ባሻገር መርሐ ግብሩ የሀገሪቱን ምጣኔ ሀብት የሚያነቃቃ ታላቅ ዕድል ፈጥሯል። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወጣቶች በችግኝ ማፍላት በጉድጓድ ዝግጅትና በተከላ ሥራዎች በመሰማራት ሰፊ የሥራ ዕድል ያገኙ ሲሆን በተለይም እንደ ቡና፣ አቮካዶና ማንጎ ያሉ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ተክሎች ትኩረት ማግኘታቸው ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሠረት ጥሏል።
በተጨማሪም ይህ ሀገራዊ ጥረት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት መዛባትን ለመቋቋም የሚረዳና ኢትዮጵያ ለዓለም አረንጓዴ ልማት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሕያው ውርስ ነው።
ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በቅድመ ዝግጅት ከተያዘው እቅድ በላይ በመፈጸም በዛሬዉ ዕለት ብቻ 805.3 ሚሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን 26.2 ሚሊየን ሰዎች ተሳትፈዋል በዚህም 291.4 ሺህ ሄክታር መሬት መሸፈን ተችሏል በዚህም ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው አገራዊ የችግኝ ተከላ ዘመቻ የህዝባችንን የተቀናጀ የተቀናጀ ጥረት እና ለአካባቢ ጥበቃ ያለውን ቁርጠኝነት በአለም አቀፍ ደረጃ ታላቅ ሁነት ሆኖ አልፏል።
በዘንድሮው አመት እስካሁን ባለው ጊዜ ከ6.5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸው የተገለጸ ሲሆን የተያዘውን አጠቃላይ እቅድ ለማጠናቀቅ ቀሪ የሆኑት 1.5 ቢሊዮን ችግኞች ደግሞ በሚቀጥሉት ወራት ተተክለው የሚጠናቀቁ ይሆናል።
የዚህ ታሪካዊ ዘመቻ እውነተኛ ስኬት የሚለካው በተከላው ሂደት ብቻ ሳይሆን ከተከላ በኋላ በሚደረግ ቀጣይነት ያለው እንክብካቤና ጥበቃ በመሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ የተከላቸውን ችግኞች ተንከባክቦ ለፍሬ የማብቃት አደራ አለበት።
በብሌን ደምበሎ
3 days ago
የውኃ ሉዓላዊነታችን በተግባር፡ ከ18 ዓመታት የእንቅልፍ ዘመን የነቃው የመገጭ ግድብ
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በአማራ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ከእነዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን የረዥም ዘመን የመጠጥ ውኃ ጥያቄ የሚመልሰው እና ሰፊ የመስኖ ልማት አቅም ያለው የመገጭ ግድብ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡
ግንባታው በ2001 ዓ.ም. የተጀመረው ይህ ግድብ፣ ላለፉት 18 ዓመታት የመልካም አስተዳደር እና የፕሮጀክት አመራር ድክመት ተጓትቶ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ በ2017 በጀት ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥተኛ አመራር፣ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ የነበረው ተቋራጭ ከፕሮጀክቱ እንዲወጣ ተደርጎ ሥራው ለሀገር በቀል ተቋራጭ ተሰጥቷል፡፡
የውጭ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተጋብዘው የመሬት መንሸራተት ችግሩ በጥናት እንዲፈታ መደረጉ፣ እንዲሁም ሥራው በቀን እና በሌሊት ፈረቃ እንዲከናወን መወሰኑ ፕሮጀክቱን ከእንቅልፉ ቀስቅሶ ወደ ጤናማ እና ፈጣን የአፈጻጸም ምዕራፍ አሸጋግሮታል፡፡
በዚህም የግንባታው ወሳኝ ምዕራፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በቅርቡ ለፍሬ እንደሚበቃ ይጠበቃል፡፡
የመገጭ ግድብ ከግንባታ ባለፈ የኢትዮጵያውያን የልማት ፅናት ማሳያ ነው፡፡ አጠቃላይ የውኃ መያዝ አቅሙ 185 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 116 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የሚሆነው ለመስኖ ልማት የሚውል ነው፡፡
ይህም 17 ሺህ ሔክታር መሬትን በመስኖ በማልማት የጎንደር ከተማን እንዲሁም የምሥራቅ እና የምዕራብ ደምቢያ አካባቢ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ክልሉ ያለውን ሰፊ የውኃ እና የመሬት ሀብት አቀናጅቶ ለመጠቀም እየተገነቡ ካሉ ሰፋፊ የመስኖ አውታሮች አንዱ የሆነው ይህ ፕሮጀክት፣ የሀገራችን የግብርና ትራንስፎርሜሽን እና የምግብ ዋስትና ራዕይ በጉልህ የሚያሳካ የዘመን ትሩፋት ነው፡፡
ይህ የኢትዮጵያ የማይቆም የልማት እርምጃ እንደተለመደው የግብፅ ሚዲያዎችን ሰላም ነስቷል፡፡
የመገጭ ግድብ በጣና ሐይቅ ገባር ወንዝ ላይ የሚገነባ መካከለኛ ፕሮጀክት ቢሆንም፣ የግብፅ ሚዲያዎች ፕሮጀክቱን በተመለከተ ሰሞኑን እያስተጋቡት ያለው ጩኸት ሀገሪቱ ከያዘችው የቆየ እና ራስ ወዳድ የውኃ ፖሊሲ የሚመነጭ ነው፡፡
ግብፅ ኢትዮጵያ የውኃ ሀብቷን እንዳትጠቀም የማስፈራራት ፖሊሲን ብትከተልም፣ ኢትዮጵያ ግን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ አጠናቅቃ ልማቷን የሚያፋጥኑ እንደ መገጭ ያሉ ግድቦችን መቀጠ "ኢትዮጵያ አትጨበጥም" የሚል ድንጋጤ ፈጥሮባቸዋል፡፡
ግብፅ አሁንም ጊዜ ያለፈባቸውን የቅኝ ግዛት ውሎች እያነሳች የትኛውም የኢትዮጵያ ልማት ግብርናዋን እንደሚጎዳ በማስመሰል ከእውነት የራቀ ኢ-ፍትሐዊ ትርክት ታራምዳለች፡፡
ኢትዮጵያ ግን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውኃ አጠቃቀም መርህን (CFA) በመከተል ሕዝቧን ለመመገብ የገዛ ሀብቷን የማልማት ተፈጥሯዊና ሕጋዊ መብቷን እያስከበረች ትገኛለች፡፡
ከዚህም ባሻገር እንደ መገጭ ባሉ የኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ግድብ መሥራት የውኃ ትነትን እጅግ የሚቀንስ መሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ማንንም የማይጎዳ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ማረጋገጫ ነው፡፡
እውነታው ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ምዕራፍ ከትላንቱ በእጅጉ የተለየ መሆኑ ነው፡፡ ሀገራችን የዜጎቿን ሕይወት ለመለወጥ እና ከድህነት ለመውጣት የምታደርገውን የልማት ጉዞ በማንኛውም የውጭ ኃይል እጅ ጥምዘዛ የማታቆምበት ታሪካዊ ከፍታ ላይ ትገኛለች፡፡
የመገጭ ግድብም ሆነ ሌሎች በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የዚሁ ሉዓላዊ መብት አካል ናቸው፡፡
ማንም ይጩህ ማን፣ ኢትዮጵያ በራሷ ሀብት፣ በራሷ አቅም እና በራሷ ጊዜ የጀመረቻቸውን የልማት ሥራዎች ከዳር በማድረስ ታሪኳን በአዲስ መልክ መጻፏን አጠናክራ ትቀጥላለች፡፡
መንግሥትም በቀጣይ የመገጭ ግድብ ቀሪ ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎችን በማጠናከር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የዲፕሎማሲ ሥራውን በማስፋት የኢትዮጵያን ብልጽግና ያረጋግጣል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #megechdam #nile #development #amhararegion
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በአማራ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ከእነዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን የረዥም ዘመን የመጠጥ ውኃ ጥያቄ የሚመልሰው እና ሰፊ የመስኖ ልማት አቅም ያለው የመገጭ ግድብ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡
ግንባታው በ2001 ዓ.ም. የተጀመረው ይህ ግድብ፣ ላለፉት 18 ዓመታት የመልካም አስተዳደር እና የፕሮጀክት አመራር ድክመት ተጓትቶ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ በ2017 በጀት ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥተኛ አመራር፣ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ የነበረው ተቋራጭ ከፕሮጀክቱ እንዲወጣ ተደርጎ ሥራው ለሀገር በቀል ተቋራጭ ተሰጥቷል፡፡
የውጭ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተጋብዘው የመሬት መንሸራተት ችግሩ በጥናት እንዲፈታ መደረጉ፣ እንዲሁም ሥራው በቀን እና በሌሊት ፈረቃ እንዲከናወን መወሰኑ ፕሮጀክቱን ከእንቅልፉ ቀስቅሶ ወደ ጤናማ እና ፈጣን የአፈጻጸም ምዕራፍ አሸጋግሮታል፡፡
በዚህም የግንባታው ወሳኝ ምዕራፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በቅርቡ ለፍሬ እንደሚበቃ ይጠበቃል፡፡
የመገጭ ግድብ ከግንባታ ባለፈ የኢትዮጵያውያን የልማት ፅናት ማሳያ ነው፡፡ አጠቃላይ የውኃ መያዝ አቅሙ 185 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 116 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የሚሆነው ለመስኖ ልማት የሚውል ነው፡፡
ይህም 17 ሺህ ሔክታር መሬትን በመስኖ በማልማት የጎንደር ከተማን እንዲሁም የምሥራቅ እና የምዕራብ ደምቢያ አካባቢ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ክልሉ ያለውን ሰፊ የውኃ እና የመሬት ሀብት አቀናጅቶ ለመጠቀም እየተገነቡ ካሉ ሰፋፊ የመስኖ አውታሮች አንዱ የሆነው ይህ ፕሮጀክት፣ የሀገራችን የግብርና ትራንስፎርሜሽን እና የምግብ ዋስትና ራዕይ በጉልህ የሚያሳካ የዘመን ትሩፋት ነው፡፡
ይህ የኢትዮጵያ የማይቆም የልማት እርምጃ እንደተለመደው የግብፅ ሚዲያዎችን ሰላም ነስቷል፡፡
የመገጭ ግድብ በጣና ሐይቅ ገባር ወንዝ ላይ የሚገነባ መካከለኛ ፕሮጀክት ቢሆንም፣ የግብፅ ሚዲያዎች ፕሮጀክቱን በተመለከተ ሰሞኑን እያስተጋቡት ያለው ጩኸት ሀገሪቱ ከያዘችው የቆየ እና ራስ ወዳድ የውኃ ፖሊሲ የሚመነጭ ነው፡፡
ግብፅ ኢትዮጵያ የውኃ ሀብቷን እንዳትጠቀም የማስፈራራት ፖሊሲን ብትከተልም፣ ኢትዮጵያ ግን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ አጠናቅቃ ልማቷን የሚያፋጥኑ እንደ መገጭ ያሉ ግድቦችን መቀጠ "ኢትዮጵያ አትጨበጥም" የሚል ድንጋጤ ፈጥሮባቸዋል፡፡
ግብፅ አሁንም ጊዜ ያለፈባቸውን የቅኝ ግዛት ውሎች እያነሳች የትኛውም የኢትዮጵያ ልማት ግብርናዋን እንደሚጎዳ በማስመሰል ከእውነት የራቀ ኢ-ፍትሐዊ ትርክት ታራምዳለች፡፡
ኢትዮጵያ ግን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውኃ አጠቃቀም መርህን (CFA) በመከተል ሕዝቧን ለመመገብ የገዛ ሀብቷን የማልማት ተፈጥሯዊና ሕጋዊ መብቷን እያስከበረች ትገኛለች፡፡
ከዚህም ባሻገር እንደ መገጭ ባሉ የኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ግድብ መሥራት የውኃ ትነትን እጅግ የሚቀንስ መሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ማንንም የማይጎዳ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ማረጋገጫ ነው፡፡
እውነታው ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ምዕራፍ ከትላንቱ በእጅጉ የተለየ መሆኑ ነው፡፡ ሀገራችን የዜጎቿን ሕይወት ለመለወጥ እና ከድህነት ለመውጣት የምታደርገውን የልማት ጉዞ በማንኛውም የውጭ ኃይል እጅ ጥምዘዛ የማታቆምበት ታሪካዊ ከፍታ ላይ ትገኛለች፡፡
የመገጭ ግድብም ሆነ ሌሎች በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የዚሁ ሉዓላዊ መብት አካል ናቸው፡፡
ማንም ይጩህ ማን፣ ኢትዮጵያ በራሷ ሀብት፣ በራሷ አቅም እና በራሷ ጊዜ የጀመረቻቸውን የልማት ሥራዎች ከዳር በማድረስ ታሪኳን በአዲስ መልክ መጻፏን አጠናክራ ትቀጥላለች፡፡
መንግሥትም በቀጣይ የመገጭ ግድብ ቀሪ ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎችን በማጠናከር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የዲፕሎማሲ ሥራውን በማስፋት የኢትዮጵያን ብልጽግና ያረጋግጣል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #megechdam #nile #development #amhararegion
Sponsored by
Surafel
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሽራሮ አቅራቢያ ዳግም ውጊያ ማገርሸቱን ተከትሎ፣ በፌደራል መንግስቱ እና በትግራይ ኃይሎች መካከል የተደረገውን የሶስት ዓመት የሰላም ስምምነት ክፉኛ የጣሰ ከባድ ክስተት ተፈጥሯል።
በመቀሌ የሚገኘው የትግራይ ክልላዊ መንግስት ባወጣው መግለጫ፣ የፌደራል መንግስት ኃይሎች ቅዳሜ ንጋት ላይ ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ ከሸራሮ አቅጣጫ ጥቃት መክፈታቸውን አስታውቋል። በጦርነቱ ወቅት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን የመሩት ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ በበኩላቸው፣ ግጭት መፈጠሩን አረጋግጠው፤ ነገር ግን ጥቃቱን የጀመሩት በህወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የሚመሩ ኃይሎች መሆናቸውን በመግለጽ ከሰዋል። ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው "ጦርነት ይብቃ! ልዩነቶቻችንን በውይይት እንፍታ" ሲሉ አሳስበዋል።
ይህ ግጭት የተከሰተው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እ.ኤ.አ. በ2018 ወደ ስልጣን ከመምጣታቸው በፊት ለሶስት አስርት ዓመታት ኢትዮጵያን ያስተዳደረው ህወሓት እና አዲስ አበባ ላለፉት ወራት እያሽቆለቆለ የመጣውን ግንኙነት ተከትሎ ነው። ሁለቱም ወገኖች የ2022ቱን (የ2015 ዓ.ም) የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ድንጋጌዎችን ተግባራዊ አላደረጉም በሚል እርስ በእርስ ሲወነጃጀሉ ቆይተዋል።
የትግራይ ባለስልጣናት ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በክልሉ ላይ የረጅም ጊዜ እገዳ እና የድሮን ጥቃት ዘመቻ ሲያካሂድ መቆየቱን እና ይህ አሁን ወደ ሙሉ ጦርነት ማደጉን ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት የትግራይ ኃይሎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ እና የሀይማኖት ተቋማት "ለሀገር ጥፋት እምቢ" በሚል መሪ ቃል ለብሔራዊ ህልውና ትግል እንዲዘጋጁ ጥሪ አቅርቧል።
በሌላ በኩል የቀድሞው የህወሓት ቃል አቀባይ እና የአሁኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ዶክተር ደብረፅዮን በኤርትራ እና በአማራ ታጣቂዎች ላይ ተማምነው በጉልበት ወደ ስልጣን ለመመለስ እየሞከሩ ነው ሲሉ በመክሰስ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች እርሳቸውን (ደብረፅዮንን) እንዲተዉ አሳስበዋል። እ.ኤ.አ. በ2022 ለህወሓት እና ለፌደራል መንግስቱ የፕሪቶሪያውን ስምምነት የፈረሙት አቶ ጌታቸው እና የደህንነት ሹሙ አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ባለፈው ሰኔ ወር በአልጀዚራ ላይ በጋራ ባወጡት ጽሁፍ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።
በኦስሎ ኒው ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ተንታኝ የሆኑት ቸቲል ትሮንቮል ለአልጀዚራ እንደተናገሩት፣ ይህ ውጊያ ከ2022ቱ የሰላም ስምምነት ወዲህ የታየ "እጅግ አሳሳቢው ክስተት" ነው። ስምምነቱ ጦርነቱን ቢያስቆምም፣ በመቀሌ እና አዲስ አበባ መካከል ያለውን "የግጭቱን መሰረታዊ ምክንያቶች" ሳይፈታ ማለፉን አክለዋል። ለዚህ ግጭት መነሻ በሆኑት ቀናት ውስጥ፣ የኢትዮጵያ መንግስት መገናኛ ብዙሃን ዶክተር ደብረፅዮንን በስማቸው ጠቅሰው ትግራውያንን ለጦርነት እየቀሰቀሱ ነው የሚል የክስ ዘመቻ ሲያካሂዱ ነበር።
ከሁለት ዓመታት በፊት ተጀምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈውን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው ስምምነት፣ የትጥቅ አፈታት እና የህወሓትን ህጋዊ ሰውነት በተመለከቱ ጥልቅ ጉዳዮች ላይ እልባት ሳይሰጥ ቆይቷል። ይህንም ተከትሎ አሜሪካ ባለፈው ሰኔ ወር ሰላምን ያደናቅፋሉ ባላቸው የህወሓት "አክራሪዎች" ላይ የቪዛ ማዕቀብ የጣለች ሲሆን፣ ህወሓትም እርምጃው ያልተሟላ እና ሚዛናዊ ያልሆነ መረጃ ላይ የተመሰረተ ነው ሲል ተችቶታል።
የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ስምምነቱን ለማትረፍ ወደ መቀሌ ቢያቀኑም፣ በሀምሌ ወር አጋማሽ ህወሓት የፕሪቶሪያው ስምምነት "በተግባር ሞቷል" ሲል አውጇል። የቀጠናው ተንታኝ ፋይሰል ሮብሌ ይህ የውጊያ ጅማሮ አሜሪካ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ያደረገችው ጥረት አለመሳካቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። አክለውም "ጠንካራ ዓለም አቀፍ ጣልቃ ገብነት ከሌለ፣ ወደ እጅግ የሰፋ ጦርነት ልናመራ እንችላለን" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በመቀሌ የሚገኘው የትግራይ ክልላዊ መንግስት ባወጣው መግለጫ፣ የፌደራል መንግስት ኃይሎች ቅዳሜ ንጋት ላይ ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ ከሸራሮ አቅጣጫ ጥቃት መክፈታቸውን አስታውቋል። በጦርነቱ ወቅት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን የመሩት ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ በበኩላቸው፣ ግጭት መፈጠሩን አረጋግጠው፤ ነገር ግን ጥቃቱን የጀመሩት በህወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የሚመሩ ኃይሎች መሆናቸውን በመግለጽ ከሰዋል። ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው "ጦርነት ይብቃ! ልዩነቶቻችንን በውይይት እንፍታ" ሲሉ አሳስበዋል።
ይህ ግጭት የተከሰተው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እ.ኤ.አ. በ2018 ወደ ስልጣን ከመምጣታቸው በፊት ለሶስት አስርት ዓመታት ኢትዮጵያን ያስተዳደረው ህወሓት እና አዲስ አበባ ላለፉት ወራት እያሽቆለቆለ የመጣውን ግንኙነት ተከትሎ ነው። ሁለቱም ወገኖች የ2022ቱን (የ2015 ዓ.ም) የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ድንጋጌዎችን ተግባራዊ አላደረጉም በሚል እርስ በእርስ ሲወነጃጀሉ ቆይተዋል።
የትግራይ ባለስልጣናት ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በክልሉ ላይ የረጅም ጊዜ እገዳ እና የድሮን ጥቃት ዘመቻ ሲያካሂድ መቆየቱን እና ይህ አሁን ወደ ሙሉ ጦርነት ማደጉን ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት የትግራይ ኃይሎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ እና የሀይማኖት ተቋማት "ለሀገር ጥፋት እምቢ" በሚል መሪ ቃል ለብሔራዊ ህልውና ትግል እንዲዘጋጁ ጥሪ አቅርቧል።
በሌላ በኩል የቀድሞው የህወሓት ቃል አቀባይ እና የአሁኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ዶክተር ደብረፅዮን በኤርትራ እና በአማራ ታጣቂዎች ላይ ተማምነው በጉልበት ወደ ስልጣን ለመመለስ እየሞከሩ ነው ሲሉ በመክሰስ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች እርሳቸውን (ደብረፅዮንን) እንዲተዉ አሳስበዋል። እ.ኤ.አ. በ2022 ለህወሓት እና ለፌደራል መንግስቱ የፕሪቶሪያውን ስምምነት የፈረሙት አቶ ጌታቸው እና የደህንነት ሹሙ አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ባለፈው ሰኔ ወር በአልጀዚራ ላይ በጋራ ባወጡት ጽሁፍ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።
በኦስሎ ኒው ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ተንታኝ የሆኑት ቸቲል ትሮንቮል ለአልጀዚራ እንደተናገሩት፣ ይህ ውጊያ ከ2022ቱ የሰላም ስምምነት ወዲህ የታየ "እጅግ አሳሳቢው ክስተት" ነው። ስምምነቱ ጦርነቱን ቢያስቆምም፣ በመቀሌ እና አዲስ አበባ መካከል ያለውን "የግጭቱን መሰረታዊ ምክንያቶች" ሳይፈታ ማለፉን አክለዋል። ለዚህ ግጭት መነሻ በሆኑት ቀናት ውስጥ፣ የኢትዮጵያ መንግስት መገናኛ ብዙሃን ዶክተር ደብረፅዮንን በስማቸው ጠቅሰው ትግራውያንን ለጦርነት እየቀሰቀሱ ነው የሚል የክስ ዘመቻ ሲያካሂዱ ነበር።
ከሁለት ዓመታት በፊት ተጀምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈውን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው ስምምነት፣ የትጥቅ አፈታት እና የህወሓትን ህጋዊ ሰውነት በተመለከቱ ጥልቅ ጉዳዮች ላይ እልባት ሳይሰጥ ቆይቷል። ይህንም ተከትሎ አሜሪካ ባለፈው ሰኔ ወር ሰላምን ያደናቅፋሉ ባላቸው የህወሓት "አክራሪዎች" ላይ የቪዛ ማዕቀብ የጣለች ሲሆን፣ ህወሓትም እርምጃው ያልተሟላ እና ሚዛናዊ ያልሆነ መረጃ ላይ የተመሰረተ ነው ሲል ተችቶታል።
የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ስምምነቱን ለማትረፍ ወደ መቀሌ ቢያቀኑም፣ በሀምሌ ወር አጋማሽ ህወሓት የፕሪቶሪያው ስምምነት "በተግባር ሞቷል" ሲል አውጇል። የቀጠናው ተንታኝ ፋይሰል ሮብሌ ይህ የውጊያ ጅማሮ አሜሪካ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ያደረገችው ጥረት አለመሳካቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። አክለውም "ጠንካራ ዓለም አቀፍ ጣልቃ ገብነት ከሌለ፣ ወደ እጅግ የሰፋ ጦርነት ልናመራ እንችላለን" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
5 days ago
የሀገራዊ ለውጥ ጉዞ የአንድ ሰሞን ድግስ ሳይሆን ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ ሂደት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*********************
የሀገራዊ ለውጥ ጉዞ የአንድ ሰሞን ድግስ ሳይሆን ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ ሂደት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ዜጎች ለወቅታዊ ፈተናዎች እጅ ሳይሰጡ ለሀገር ዘላቂ ጥቅም በጽናት ሊቆሙ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ እና የዘመኑን የመረጃ ፍሰት በአግባቡ መገንዘብ እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።
ከጥቂት ዓመታት በፊት መረጃ በዋናነት በብሔራዊ መገናኛ ብዙኃን ብቻ ይገኝ የነበረ መሆኑን አስታውሰው፣ አሁን ላይ ግን የኢንተርኔትና የዳታ ስርጭት በመስፋፋቱ እንዲሁም በርካታ ትንታኔ ሰጪዎች በመፈጠራቸው ወቅቱን በጥንቃቄ መረዳት ወሳኝ መሆኑን አመላክተዋል።
ለውጥ በአጭር ጊዜ የሚጠናቀቅ ባለመሆኑ ዜጎች ራሳቸውን እያስተማሩ እና ከሁኔታዎች ጋር እያስማሙ መጓዝ እንዳለባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ መክረዋል።
ጫናን መቋቋም አቅቷቸው ለጊዜያዊ ችግሮች ሸብረክ የሚሉ አካላት እንዳሉ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ ለርካሽ እና ጊዜያዊ ነገር ሲባል ከትልቅ ሀገራዊ ቁም ነገር መጉደል እንደማይገባ በአጽንኦት ተናግረዋል።
ሁሉም አካል ታሪክ መሥራት በሚያስችል ሁኔታ ላይ ማተኮር እንዳለበት፣ ይህ ካልተቻለ ደግሞ ቢያንስ ከታሪክ ቀኝ መቆም እንጂ በአቋም መዋዠቅ የሀገርን ጥቅም አደጋ ላይ መጣል እንደማይገባ አስገንዝበዋል።
እውነታው በሂደት እና በተጨባጭ ሥራዎች እየተገለጠ እንደሚመጣም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pmabiyahmed #nationalinterest #ebc
*********************
የሀገራዊ ለውጥ ጉዞ የአንድ ሰሞን ድግስ ሳይሆን ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ ሂደት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ዜጎች ለወቅታዊ ፈተናዎች እጅ ሳይሰጡ ለሀገር ዘላቂ ጥቅም በጽናት ሊቆሙ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ እና የዘመኑን የመረጃ ፍሰት በአግባቡ መገንዘብ እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።
ከጥቂት ዓመታት በፊት መረጃ በዋናነት በብሔራዊ መገናኛ ብዙኃን ብቻ ይገኝ የነበረ መሆኑን አስታውሰው፣ አሁን ላይ ግን የኢንተርኔትና የዳታ ስርጭት በመስፋፋቱ እንዲሁም በርካታ ትንታኔ ሰጪዎች በመፈጠራቸው ወቅቱን በጥንቃቄ መረዳት ወሳኝ መሆኑን አመላክተዋል።
ለውጥ በአጭር ጊዜ የሚጠናቀቅ ባለመሆኑ ዜጎች ራሳቸውን እያስተማሩ እና ከሁኔታዎች ጋር እያስማሙ መጓዝ እንዳለባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ መክረዋል።
ጫናን መቋቋም አቅቷቸው ለጊዜያዊ ችግሮች ሸብረክ የሚሉ አካላት እንዳሉ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ ለርካሽ እና ጊዜያዊ ነገር ሲባል ከትልቅ ሀገራዊ ቁም ነገር መጉደል እንደማይገባ በአጽንኦት ተናግረዋል።
ሁሉም አካል ታሪክ መሥራት በሚያስችል ሁኔታ ላይ ማተኮር እንዳለበት፣ ይህ ካልተቻለ ደግሞ ቢያንስ ከታሪክ ቀኝ መቆም እንጂ በአቋም መዋዠቅ የሀገርን ጥቅም አደጋ ላይ መጣል እንደማይገባ አስገንዝበዋል።
እውነታው በሂደት እና በተጨባጭ ሥራዎች እየተገለጠ እንደሚመጣም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pmabiyahmed #nationalinterest #ebc
5 days ago
ዜና እረፍት | ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ – የምሕረት፣ የጀግንነትና የአገር አገልግሎት ተምሳሌት አረፈች
#ethiopia | የኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹ ፕሮፌሽናል ነርሶች መካከል አንዷ፣ የኮሪያ ጦርነት ዘማች፣ የቀይ መስቀል በጎ ፈቃደኛ እና ዓለም አቀፍ የነርስነት ክብር ተሸላሚ የነበሩት መቶ አለቃ ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ በ96 ዓመታቸው አርፈዋል።
ሲስተር ብርቅነሽ በአዲስ አበባ ከአቶ ከበደ ዘውገ እና ከወ/ሮ አልመዝ የግሉ ተወለዱ። ወላጆቻቸውን በለጋ ዕድሜያቸው በሞት ካጡ በኋላ፣ በአያታቸው ወ/ሮ ላቀች ጻታ እጅ አደጉ። የአባታቸው የአርበኝነት ታሪክ በመታሰቡ፣ በእቴጌ መነን የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት በነጻ እንዲማሩ እድል አግኝተዋል።
በኋላም በወቅቱ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሆስፒታል (አሁን የካቲት 12 መታሰቢያ ሆስፒታል) በነበረው የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የነርሶች ትምህርት ቤት ተምረው፣ ከሀገሪቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ፕሮፌሽናል ነርሶች መካከል በክብር ተመርቀዋል።
በ1943 ዓ.ም. ከሦስተኛው ቃኘው ሻለቃ ጋር ወደ ኮሪያ በማቅናት፣ ከሁለት ጥቁር አፍሪካዊ ሴት ነርሶች አንዷ ሆነው ታሪክ ሠርተዋል። ከሲስተር አስቴር አያና ጋር በመሆን የኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹ የቀይ መስቀል ዘማቾች በመሆን በተባበሩት መንግሥታት ሥር በኮሪያ ጦርነት ውስጥ ለወታደሮች ሕክምና እና ሰብዓዊ አገልግሎት ሰጥተዋል። ከሕክምና ሥራቸው በተጨማሪ ለኢትዮጵያውያን ወታደሮች የትርጉም አገልግሎትም አበርክተዋል።
ከኮሪያ በኋላ በጃፓን ወታደራዊ ሆስፒታል እንዲሁም በኢትዮጵያ በክብር ዘበኛ ሆስፒታል፣ በጳውሎስ ሆስፒታል፣ በድሬዳዋና በአዲስ አበባ በሚገኙ የጤና ተቋማት ለብዙ ዓመታት በታማኝነት አገልግለዋል።
ለሰብዓዊ አገልግሎታቸው ዓለም አቀፍ ዕውቅና በማግኘት፣ በነርስነት ሙያ ከፍተኛ ክብር የሆነውን Florence Nightingale Award የተሸለሙ ጥቂት አፍሪካውያን ሴቶች መካከል አንዷ ሆነዋል።
የአገር አገልግሎታቸውን ለማክበር፣ እናት ባንክ በቦሌ ቡልቡላ የሚገኘውን አንድ ቅርንጫፍ በስማቸው ሰይሟል፤ ይህም ለሀገር ያበረከቱትን የማይረሳ አስተዋፅኦ የሚያሳይ የክብር ምልክት ነው።
መቶ አለቃ ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በ96 ዓመታቸው አርፈዋል። ከባለቤታቸው ከጄኔራል ደስታ ገመዳ ጋር ያፈሯቸውን አራት ልጆችና ስምንት የልጅ ልጆች ትተው አልፈዋል።
ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ በጀግንነታቸው፣ በሰብዓዊነታቸው እና ለሀገራቸው ባበረከቱት አገልግሎት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ለዘላለም የሚታወሱ ባለውለታ ሆነው ይኖራሉ።
ነፍሳቸውን በሰላም ያሳርፍ።
#tizbit Assefa
#ethiopia | የኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹ ፕሮፌሽናል ነርሶች መካከል አንዷ፣ የኮሪያ ጦርነት ዘማች፣ የቀይ መስቀል በጎ ፈቃደኛ እና ዓለም አቀፍ የነርስነት ክብር ተሸላሚ የነበሩት መቶ አለቃ ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ በ96 ዓመታቸው አርፈዋል።
ሲስተር ብርቅነሽ በአዲስ አበባ ከአቶ ከበደ ዘውገ እና ከወ/ሮ አልመዝ የግሉ ተወለዱ። ወላጆቻቸውን በለጋ ዕድሜያቸው በሞት ካጡ በኋላ፣ በአያታቸው ወ/ሮ ላቀች ጻታ እጅ አደጉ። የአባታቸው የአርበኝነት ታሪክ በመታሰቡ፣ በእቴጌ መነን የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት በነጻ እንዲማሩ እድል አግኝተዋል።
በኋላም በወቅቱ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሆስፒታል (አሁን የካቲት 12 መታሰቢያ ሆስፒታል) በነበረው የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የነርሶች ትምህርት ቤት ተምረው፣ ከሀገሪቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ፕሮፌሽናል ነርሶች መካከል በክብር ተመርቀዋል።
በ1943 ዓ.ም. ከሦስተኛው ቃኘው ሻለቃ ጋር ወደ ኮሪያ በማቅናት፣ ከሁለት ጥቁር አፍሪካዊ ሴት ነርሶች አንዷ ሆነው ታሪክ ሠርተዋል። ከሲስተር አስቴር አያና ጋር በመሆን የኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹ የቀይ መስቀል ዘማቾች በመሆን በተባበሩት መንግሥታት ሥር በኮሪያ ጦርነት ውስጥ ለወታደሮች ሕክምና እና ሰብዓዊ አገልግሎት ሰጥተዋል። ከሕክምና ሥራቸው በተጨማሪ ለኢትዮጵያውያን ወታደሮች የትርጉም አገልግሎትም አበርክተዋል።
ከኮሪያ በኋላ በጃፓን ወታደራዊ ሆስፒታል እንዲሁም በኢትዮጵያ በክብር ዘበኛ ሆስፒታል፣ በጳውሎስ ሆስፒታል፣ በድሬዳዋና በአዲስ አበባ በሚገኙ የጤና ተቋማት ለብዙ ዓመታት በታማኝነት አገልግለዋል።
ለሰብዓዊ አገልግሎታቸው ዓለም አቀፍ ዕውቅና በማግኘት፣ በነርስነት ሙያ ከፍተኛ ክብር የሆነውን Florence Nightingale Award የተሸለሙ ጥቂት አፍሪካውያን ሴቶች መካከል አንዷ ሆነዋል።
የአገር አገልግሎታቸውን ለማክበር፣ እናት ባንክ በቦሌ ቡልቡላ የሚገኘውን አንድ ቅርንጫፍ በስማቸው ሰይሟል፤ ይህም ለሀገር ያበረከቱትን የማይረሳ አስተዋፅኦ የሚያሳይ የክብር ምልክት ነው።
መቶ አለቃ ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በ96 ዓመታቸው አርፈዋል። ከባለቤታቸው ከጄኔራል ደስታ ገመዳ ጋር ያፈሯቸውን አራት ልጆችና ስምንት የልጅ ልጆች ትተው አልፈዋል።
ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ በጀግንነታቸው፣ በሰብዓዊነታቸው እና ለሀገራቸው ባበረከቱት አገልግሎት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ለዘላለም የሚታወሱ ባለውለታ ሆነው ይኖራሉ።
ነፍሳቸውን በሰላም ያሳርፍ።
#tizbit Assefa
7 days ago
የትግራይ ወጣቶች እውነተኛ ፍላጎት ሰላም ነው - የምክክር ጉባኤ ተሳታፊው ወጣት
************************************
ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ፣ የቆዩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ያለመ ታሪካዊ መድረክ ነው።
የትግራይ ክልልን በመወከል በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው እየተሳተፈ ያለው ወጣት፣ በክልሉ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በማንሳት የክልሉ ወጣቶች ዋና ፍላጎት ሰላም መሆኑን ይናገራል።
በምክክር ጉባኤ ተሳትፎው ለሀገር ግንባታ ይጠቅማል የሚለውን ሀሳብ በነጻነት እያቀረበ እንደሚገኝ ወጣቱ ገልጿል።
ጦርነት በትግራይም ሆነ በሌሎች የሀገራችን አካባቢዎች የወጣቶችን ሕይወት ከመቅጠፍ እና ማኅበራዊ ውድቀትን ከማስከተል ውጭ ያተረፈው ነገር እንደሌለ ጠቅሷል።
ተምረው ሀገር ሊገነቡ፣ ሥራ ፈጥረው ራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን ሊረዱ የሚችሉ ወጣቶች የጦርነት ሰለባ መሆናቸው ሀገርን ለከፍተኛ ማኅበራዊ ቀውስ እንደሚዳርግ አንስቷል።
የትግራይ ወጣቶችን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ሲናገርም፣ ወጣቱ ወደ ጦርነት አውድማ እየገባ ያለው በገዛ ፍላጎቱ ሳይሆን በግዳጅና በአፈሳ እንደሆነ ገልጿል።
የክልሉ ወጣቶች እውነተኛ ፍላጎት ሰላም፣ ትምህርት፣ የሥራ ዕድል እና የተረጋጋ ሕይወት እንጂ ወደ አላስፈላጊ ውጊያ መግባት አለመሆኑን የገለጸው ተመካካሪው፣ ሀሳባቸውን በነጻነት የሚገልጹበት እና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በራሳቸው የሚወስኑበት ምህዳር ሊመቻችላቸው እንደሚገባ ጠቁሟል።
በፖለቲካው ምህዳር ሰፊ ልዩነት ቢኖርም እንኳ ይህን ልዩነት በጠብመንጃ ሳይሆን በውይይት ጠረጴዛ ዙሪያ በመቀመጥ እያጠበቡ መሄድ እንደሚቻል ተሳታፊው አስምሮበታል።
ይህ ዓይነቱ ችግሮችን እና ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ በምክክር እና በሀሳብ የበላይነት የመፍታት ባህል በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካም ሊጎለብት እንደሚገባ ተናግሯል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #nationaldialogue #tigray #youth #peace #ebc
************************************
ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ፣ የቆዩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ያለመ ታሪካዊ መድረክ ነው።
የትግራይ ክልልን በመወከል በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው እየተሳተፈ ያለው ወጣት፣ በክልሉ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በማንሳት የክልሉ ወጣቶች ዋና ፍላጎት ሰላም መሆኑን ይናገራል።
በምክክር ጉባኤ ተሳትፎው ለሀገር ግንባታ ይጠቅማል የሚለውን ሀሳብ በነጻነት እያቀረበ እንደሚገኝ ወጣቱ ገልጿል።
ጦርነት በትግራይም ሆነ በሌሎች የሀገራችን አካባቢዎች የወጣቶችን ሕይወት ከመቅጠፍ እና ማኅበራዊ ውድቀትን ከማስከተል ውጭ ያተረፈው ነገር እንደሌለ ጠቅሷል።
ተምረው ሀገር ሊገነቡ፣ ሥራ ፈጥረው ራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን ሊረዱ የሚችሉ ወጣቶች የጦርነት ሰለባ መሆናቸው ሀገርን ለከፍተኛ ማኅበራዊ ቀውስ እንደሚዳርግ አንስቷል።
የትግራይ ወጣቶችን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ሲናገርም፣ ወጣቱ ወደ ጦርነት አውድማ እየገባ ያለው በገዛ ፍላጎቱ ሳይሆን በግዳጅና በአፈሳ እንደሆነ ገልጿል።
የክልሉ ወጣቶች እውነተኛ ፍላጎት ሰላም፣ ትምህርት፣ የሥራ ዕድል እና የተረጋጋ ሕይወት እንጂ ወደ አላስፈላጊ ውጊያ መግባት አለመሆኑን የገለጸው ተመካካሪው፣ ሀሳባቸውን በነጻነት የሚገልጹበት እና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በራሳቸው የሚወስኑበት ምህዳር ሊመቻችላቸው እንደሚገባ ጠቁሟል።
በፖለቲካው ምህዳር ሰፊ ልዩነት ቢኖርም እንኳ ይህን ልዩነት በጠብመንጃ ሳይሆን በውይይት ጠረጴዛ ዙሪያ በመቀመጥ እያጠበቡ መሄድ እንደሚቻል ተሳታፊው አስምሮበታል።
ይህ ዓይነቱ ችግሮችን እና ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ በምክክር እና በሀሳብ የበላይነት የመፍታት ባህል በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካም ሊጎለብት እንደሚገባ ተናግሯል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #nationaldialogue #tigray #youth #peace #ebc
8 days ago
ለሀገር ዕድገትና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት የጸና አገራዊ ቁርጠኝነት!
ኩባንያችን የኢትዮጵያን የዲጂታልና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን በግንባር ቀደምትነት እየመራ፣ ለሀገር ግንባታና ለዜጎች ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያደርገውን የማይተካ አገራዊ አስተዋፅኦ በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት በ2018 በጀት ዓመት ብቻ 73.5 ቢሊዮን ብር ታክስ ገቢ በማድረግ የሀገር ግንባታ ምሰሶነቱን ያስመሰከረ ሲሆን፣ ይህም ተቋማችን ያስገባቸውን አጠቃላይ የታክስ መጠን 244.5 ቢሊዮን ብር አድርሶታል። ከዚህ ቀደምም ኩባንያችን ለተከታታይ 5 ዓመታት የሀገሪቱ ግንባር ቀደም የፕላቲኒየም ግብር ከፋይና ልዩ ሽልማት ባለቤት መሆኑ ይታወሳል።
ከታማኝ ግብር ከፋይነቱ በተጨማሪ፣ ተቋማችን ከውድ ደንበኞቹ ጋር በመተባበር 2.4 ቢሊዮን ብር ለብሔራዊ አደጋ ማገገሚያ ፈንድ በማሰባሰብ፣ በችግር ጊዜ ለወገን አለኝታነቱን በተግባር ዳግመኛ አስመስክሯል። ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ እየተወጣ የሚገኘው ኩባንያችን፣ ለ44,757 ዜጎች ቀጥተኛ የቋሚና የውል ሥራ ዕድል በመፍጠር የበርካታ ቤተሰቦችን ኑሮ መደገፍ ችሏል።
በተጨማሪም ኩባንያችን 519,810 የምርትና አገልግሎት አከፋፋዮችንና የቴሌብር ወኪሎችን፣ 2,205 የሀገር ውስጥ አቅራቢዎችን፣ 1,213 የተጨማሪ እሴት አገልግሎት አጋሮችን፣ 138 የፍራንቻይዝ አጋሮችንና 693 ዓለም አቀፍ አጋሮችን በማቀፍ ከ2 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድልና የገቢ ምንጭ የሚፈጥር ግዙፍ የኢኮኖሚ ሥነ-ምህዳር መገንባት ችሏል።
በቀጣይም ኩባንያችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ፈጠራን ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ጋር በማቀናጀት፣ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ የማፋጠን፣ የሥራ ዕድል የመፍጠርና የታማኝ ግብር ከፋይነት አገራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ መወጣቱን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/45k6Gjw
#ethiotelecom
ኩባንያችን የኢትዮጵያን የዲጂታልና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን በግንባር ቀደምትነት እየመራ፣ ለሀገር ግንባታና ለዜጎች ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያደርገውን የማይተካ አገራዊ አስተዋፅኦ በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት በ2018 በጀት ዓመት ብቻ 73.5 ቢሊዮን ብር ታክስ ገቢ በማድረግ የሀገር ግንባታ ምሰሶነቱን ያስመሰከረ ሲሆን፣ ይህም ተቋማችን ያስገባቸውን አጠቃላይ የታክስ መጠን 244.5 ቢሊዮን ብር አድርሶታል። ከዚህ ቀደምም ኩባንያችን ለተከታታይ 5 ዓመታት የሀገሪቱ ግንባር ቀደም የፕላቲኒየም ግብር ከፋይና ልዩ ሽልማት ባለቤት መሆኑ ይታወሳል።
ከታማኝ ግብር ከፋይነቱ በተጨማሪ፣ ተቋማችን ከውድ ደንበኞቹ ጋር በመተባበር 2.4 ቢሊዮን ብር ለብሔራዊ አደጋ ማገገሚያ ፈንድ በማሰባሰብ፣ በችግር ጊዜ ለወገን አለኝታነቱን በተግባር ዳግመኛ አስመስክሯል። ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ እየተወጣ የሚገኘው ኩባንያችን፣ ለ44,757 ዜጎች ቀጥተኛ የቋሚና የውል ሥራ ዕድል በመፍጠር የበርካታ ቤተሰቦችን ኑሮ መደገፍ ችሏል።
በተጨማሪም ኩባንያችን 519,810 የምርትና አገልግሎት አከፋፋዮችንና የቴሌብር ወኪሎችን፣ 2,205 የሀገር ውስጥ አቅራቢዎችን፣ 1,213 የተጨማሪ እሴት አገልግሎት አጋሮችን፣ 138 የፍራንቻይዝ አጋሮችንና 693 ዓለም አቀፍ አጋሮችን በማቀፍ ከ2 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድልና የገቢ ምንጭ የሚፈጥር ግዙፍ የኢኮኖሚ ሥነ-ምህዳር መገንባት ችሏል።
በቀጣይም ኩባንያችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ፈጠራን ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ጋር በማቀናጀት፣ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ የማፋጠን፣ የሥራ ዕድል የመፍጠርና የታማኝ ግብር ከፋይነት አገራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ መወጣቱን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/45k6Gjw
#ethiotelecom
8 days ago
ለሀገር ዕድገትና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት የጸና አገራዊ ቁርጠኝነት!
ኩባንያችን የኢትዮጵያን የዲጂታልና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን በግንባር ቀደምትነት እየመራ፣ ለሀገር ግንባታና ለዜጎች ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያደርገውን የማይተካ አገራዊ አስተዋፅኦ በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት በ2018 በጀት ዓመት ብቻ 73.5 ቢሊዮን ብር ታክስ ገቢ በማድረግ የሀገር ግንባታ ምሰሶነቱን ያስመሰከረ ሲሆን፣ ይህም ተቋማችን ያስገባቸውን አጠቃላይ የታክስ መጠን 244.5 ቢሊዮን ብር አድርሶታል። ከዚህ ቀደምም ኩባንያችን ለተከታታይ 5 ዓመታት የሀገሪቱ ግንባር ቀደም የፕላቲኒየም ግብር ከፋይና ልዩ ሽልማት ባለቤት መሆኑ ይታወሳል።
ከታማኝ ግብር ከፋይነቱ በተጨማሪ፣ ተቋማችን ከውድ ደንበኞቹ ጋር በመተባበር 2.4 ቢሊዮን ብር ለብሔራዊ አደጋ ማገገሚያ ፈንድ በማሰባሰብ፣ በችግር ጊዜ ለወገን አለኝታነቱን በተግባር ዳግመኛ አስመስክሯል። ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ እየተወጣ የሚገኘው ኩባንያችን፣ ለ44,757 ዜጎች ቀጥተኛ የቋሚና የውል ሥራ ዕድል በመፍጠር የበርካታ ቤተሰቦችን ኑሮ መደገፍ ችሏል።
በተጨማሪም ኩባንያችን 519,810 የምርትና አገልግሎት አከፋፋዮችንና የቴሌብር ወኪሎችን፣ 2,205 የሀገር ውስጥ አቅራቢዎችን፣ 1,213 የተጨማሪ እሴት አገልግሎት አጋሮችን፣ 138 የፍራንቻይዝ አጋሮችንና 693 ዓለም አቀፍ አጋሮችን በማቀፍ ከ2 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድልና የገቢ ምንጭ የሚፈጥር ግዙፍ የኢኮኖሚ ሥነ-ምህዳር መገንባት ችሏል።
በቀጣይም ኩባንያችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ፈጠራን ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ጋር በማቀናጀት፣ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ የማፋጠን፣ የሥራ ዕድል የመፍጠርና የታማኝ ግብር ከፋይነት አገራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ መወጣቱን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/45k6Gjw
#ethiotelecom
ኩባንያችን የኢትዮጵያን የዲጂታልና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን በግንባር ቀደምትነት እየመራ፣ ለሀገር ግንባታና ለዜጎች ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያደርገውን የማይተካ አገራዊ አስተዋፅኦ በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት በ2018 በጀት ዓመት ብቻ 73.5 ቢሊዮን ብር ታክስ ገቢ በማድረግ የሀገር ግንባታ ምሰሶነቱን ያስመሰከረ ሲሆን፣ ይህም ተቋማችን ያስገባቸውን አጠቃላይ የታክስ መጠን 244.5 ቢሊዮን ብር አድርሶታል። ከዚህ ቀደምም ኩባንያችን ለተከታታይ 5 ዓመታት የሀገሪቱ ግንባር ቀደም የፕላቲኒየም ግብር ከፋይና ልዩ ሽልማት ባለቤት መሆኑ ይታወሳል።
ከታማኝ ግብር ከፋይነቱ በተጨማሪ፣ ተቋማችን ከውድ ደንበኞቹ ጋር በመተባበር 2.4 ቢሊዮን ብር ለብሔራዊ አደጋ ማገገሚያ ፈንድ በማሰባሰብ፣ በችግር ጊዜ ለወገን አለኝታነቱን በተግባር ዳግመኛ አስመስክሯል። ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ እየተወጣ የሚገኘው ኩባንያችን፣ ለ44,757 ዜጎች ቀጥተኛ የቋሚና የውል ሥራ ዕድል በመፍጠር የበርካታ ቤተሰቦችን ኑሮ መደገፍ ችሏል።
በተጨማሪም ኩባንያችን 519,810 የምርትና አገልግሎት አከፋፋዮችንና የቴሌብር ወኪሎችን፣ 2,205 የሀገር ውስጥ አቅራቢዎችን፣ 1,213 የተጨማሪ እሴት አገልግሎት አጋሮችን፣ 138 የፍራንቻይዝ አጋሮችንና 693 ዓለም አቀፍ አጋሮችን በማቀፍ ከ2 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድልና የገቢ ምንጭ የሚፈጥር ግዙፍ የኢኮኖሚ ሥነ-ምህዳር መገንባት ችሏል።
በቀጣይም ኩባንያችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ፈጠራን ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ጋር በማቀናጀት፣ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ የማፋጠን፣ የሥራ ዕድል የመፍጠርና የታማኝ ግብር ከፋይነት አገራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ መወጣቱን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/45k6Gjw
#ethiotelecom
8 days ago
u134du122c u12a8u1293u134du122d - u12a8u1243u120d u12a5u1235u12a8 u1270u130du1263u122d
#ethiopia #u1308u1260u1273_u1208u1275u12cdu120du12f5 #u1308u1260u1273_u1208u1200u1308u122d #pmabiyahmed ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ፍሬ ከናፍር - ከቃል እስከ ተግባር
#ethiopia #ገበታ_ለትውልድ #ገበታ_ለሀገር #pmabiyahmed
Sponsored by
Surafel
8 days ago
📌 ታላቅ የመጽሐፍ ምረቃ እና የውይይት መድረክ ጥሪ!
የአገራችንን ሰሜናዊ ክፍል ውስብስብ የጂኦ-ፖለቲካዊ ተለዋዋጭነት፣ የማንነት ጥያቄዎችን እና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ደህንነት በምሁራዊ መንገድ የሚተነትነው አዲሱ መጽሐፍ ይመረቃል።
በደራሲ ዶ/ር ቹቹ አለባቸዉ አበበ የተጻፈው "የተከዜ ፖለቲካ፡ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደህንነት" የተሰኘው መጽሐፍ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ በክብር ተጋብዘዋል።
መጽሐፉ ወቅታዊ የሆኑ የድንበር፣ የዜግነት እና የብሔር ፖለቲካ መገለጫዎችን በማንሳት፣ ለሀገር ሉዓላዊነት እና ለሰላም ግንባታ ሂደት የሚረዱ ወሳኝ የፖለቲካ እና የስትራቴጂካዊ ደህንነት ትንታኔዎችን ያቀርባል።
📅 የምረቃ ፕሮግራሙ ዝርዝር፦
ቀን፦ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም.
ቦታ፦ 4 ኪሎ፣ ኢክላስ ሕንጻ (ዋሊያ መጽሐፍት)
ሰዓት፦ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ
በዕለቱ በታዋቂ ምሁራን የሚደረግ የመጽሐፍ ዳሰሳና ጥልቅ የፓናል ውይይት ይኖራል!
🚨 በአዳራሹ ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ!
ለምረቃው ስነ-ስርዓት ቦታዎን ቀድመው ለመያዝ እና ለመመዝገብ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ፦
👉 https://readersget.com/eve...
ዕውቀት ለለውጥ!
ዶ/ር ቹቹ አለባቸዉ አበበ
#የተከዜ_ፖለቲካ #የመጽሐፍ_ምረቃ #ዶር_ቹቹ_አለባቸዉ #ኢትዮጵያ #ብሔራዊ_ደህንነት #ዋሊያ_መጽሐፍት #readersget
የአገራችንን ሰሜናዊ ክፍል ውስብስብ የጂኦ-ፖለቲካዊ ተለዋዋጭነት፣ የማንነት ጥያቄዎችን እና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ደህንነት በምሁራዊ መንገድ የሚተነትነው አዲሱ መጽሐፍ ይመረቃል።
በደራሲ ዶ/ር ቹቹ አለባቸዉ አበበ የተጻፈው "የተከዜ ፖለቲካ፡ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደህንነት" የተሰኘው መጽሐፍ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ በክብር ተጋብዘዋል።
መጽሐፉ ወቅታዊ የሆኑ የድንበር፣ የዜግነት እና የብሔር ፖለቲካ መገለጫዎችን በማንሳት፣ ለሀገር ሉዓላዊነት እና ለሰላም ግንባታ ሂደት የሚረዱ ወሳኝ የፖለቲካ እና የስትራቴጂካዊ ደህንነት ትንታኔዎችን ያቀርባል።
📅 የምረቃ ፕሮግራሙ ዝርዝር፦
ቀን፦ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም.
ቦታ፦ 4 ኪሎ፣ ኢክላስ ሕንጻ (ዋሊያ መጽሐፍት)
ሰዓት፦ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ
በዕለቱ በታዋቂ ምሁራን የሚደረግ የመጽሐፍ ዳሰሳና ጥልቅ የፓናል ውይይት ይኖራል!
🚨 በአዳራሹ ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ!
ለምረቃው ስነ-ስርዓት ቦታዎን ቀድመው ለመያዝ እና ለመመዝገብ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ፦
👉 https://readersget.com/eve...
ዕውቀት ለለውጥ!
ዶ/ር ቹቹ አለባቸዉ አበበ
#የተከዜ_ፖለቲካ #የመጽሐፍ_ምረቃ #ዶር_ቹቹ_አለባቸዉ #ኢትዮጵያ #ብሔራዊ_ደህንነት #ዋሊያ_መጽሐፍት #readersget
9 days ago
ስብራቱ የተጠገነው የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት ዓመታት የትምህርት ዘርፉን ጥራት እና ተደራሽነት ችግሮች ለመቅረፍ በተከናወኑ ተግባራት ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ተመዝግበዋል፡፡
የትምህርት ጥራት ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት በእውቀት እና በአዕምሮ የዳበረ የሰው ሃይል ለመፍጠር፣ ለኢኮኖሚ እድገት እና ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡
በሀገራችን ለበርካታ ዓመታት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሥራዎች እየተሰሩ ቢሆንም የተደረጉ ጥረቶች በሚፈለገው ልክ ውጤት አላመጡም፡፡
በዚህም ባለፉት ዓመታት በትምህርት ዘርፉ በተስተዋሉ ችግሮች ሳቢያ በእውቀትና በክህሎት የዳበረ የሰው ሀይል በማፍራት ረገድ ክፍተቶች ሲስተዋሉ ነበር፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በአንድ ወቅት÷ በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት ችግር ውስጥ ነጠላ ምክንያቶች የሉም፤ ችግሮቹ ዘርፈ ብዙ በመሆናቸው ሁለንተናዊ መፍትሄ ይሻሉ ሲሉ ገልፀዋል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ዓለማየሁ ተ/ማሪያም (ፕ/ር) በበኩላቸው÷ትምህርት ሲባል ክፍል ቆጥሮ መጨረስ ወይም ዲግሪ መጫን ሳይሆን ጥራት ያለውን የትምህርት ሥርዓት ዘርግቶ ተግባራዊ ማድረግና የሥነ ምግባር እና የእውቀት ለውጥ ማምጣት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የችግሩን ግዝፈት የተረዳው የመደመር መንግሥት በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ በትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት ዙሪያ በርካታ የማሻሻያ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡
ለአብነትም ተማሪዎች ከመሰረታቸው ጀምሮ የዳበረ ክህሎት እንዲኖራቸው ለማድረግ መንግሥት ደረጃቸውን የጠበቁ የቅድመ መደበኛ እና መደበኛ ትምህርት ቤቶች ግንባታን እያስፋፋ ይገኛል፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦች ልጆቻቸው ከትምህርት ገበታ እንዳይቀሩ ለማድረግ የተጀመረው የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት አካል ነው፡፡
የትምህርት ኢንቨስትመንትን የማስፋፋት፣ ሥርዓተ ትምህርቱን የማሻሻል፣የመምህራንን አቅምና ብቃት የማሳደግ ሥራዎች በትኩረት እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አካዳሚያዊ ነጻነታቸው ተጠብቆ እንዲሠሩ፣ በአስተዳደር እና በሰው ኃይል ልማታቸው የተሻሉ እንዲሆኑ መንግሥት በርካታ ድጋፎችን አድርጓል፡፡
በተመሳሳይ የቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ኢኮኖሚው የሚፈልጋቸውን፣ እጃቸው የሰላ፣ የተግባቦት አቅማቸው የዳበረ እና ምርታማነትን የሚያረጋግጡ ባለሙያዎችን እንዲያፈሩ ለማደረግ መንግሥት የሚያደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
በዚህም ከኩረጃ ነጻ የሆነ፣በራሱ የሚተማመን፣ ለችግሮች መፍትሔ መስጠት የሚችል ትውልድ ከማፍራት በተጨማሪ ጥራት ያለው ትምህርት ተደራሽ ማድረግ ተችሏል፡፡
በሚኪያስ አየለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት ዓመታት የትምህርት ዘርፉን ጥራት እና ተደራሽነት ችግሮች ለመቅረፍ በተከናወኑ ተግባራት ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ተመዝግበዋል፡፡
የትምህርት ጥራት ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት በእውቀት እና በአዕምሮ የዳበረ የሰው ሃይል ለመፍጠር፣ ለኢኮኖሚ እድገት እና ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡
በሀገራችን ለበርካታ ዓመታት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሥራዎች እየተሰሩ ቢሆንም የተደረጉ ጥረቶች በሚፈለገው ልክ ውጤት አላመጡም፡፡
በዚህም ባለፉት ዓመታት በትምህርት ዘርፉ በተስተዋሉ ችግሮች ሳቢያ በእውቀትና በክህሎት የዳበረ የሰው ሀይል በማፍራት ረገድ ክፍተቶች ሲስተዋሉ ነበር፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በአንድ ወቅት÷ በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት ችግር ውስጥ ነጠላ ምክንያቶች የሉም፤ ችግሮቹ ዘርፈ ብዙ በመሆናቸው ሁለንተናዊ መፍትሄ ይሻሉ ሲሉ ገልፀዋል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ዓለማየሁ ተ/ማሪያም (ፕ/ር) በበኩላቸው÷ትምህርት ሲባል ክፍል ቆጥሮ መጨረስ ወይም ዲግሪ መጫን ሳይሆን ጥራት ያለውን የትምህርት ሥርዓት ዘርግቶ ተግባራዊ ማድረግና የሥነ ምግባር እና የእውቀት ለውጥ ማምጣት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የችግሩን ግዝፈት የተረዳው የመደመር መንግሥት በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ በትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት ዙሪያ በርካታ የማሻሻያ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡
ለአብነትም ተማሪዎች ከመሰረታቸው ጀምሮ የዳበረ ክህሎት እንዲኖራቸው ለማድረግ መንግሥት ደረጃቸውን የጠበቁ የቅድመ መደበኛ እና መደበኛ ትምህርት ቤቶች ግንባታን እያስፋፋ ይገኛል፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦች ልጆቻቸው ከትምህርት ገበታ እንዳይቀሩ ለማድረግ የተጀመረው የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት አካል ነው፡፡
የትምህርት ኢንቨስትመንትን የማስፋፋት፣ ሥርዓተ ትምህርቱን የማሻሻል፣የመምህራንን አቅምና ብቃት የማሳደግ ሥራዎች በትኩረት እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አካዳሚያዊ ነጻነታቸው ተጠብቆ እንዲሠሩ፣ በአስተዳደር እና በሰው ኃይል ልማታቸው የተሻሉ እንዲሆኑ መንግሥት በርካታ ድጋፎችን አድርጓል፡፡
በተመሳሳይ የቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ኢኮኖሚው የሚፈልጋቸውን፣ እጃቸው የሰላ፣ የተግባቦት አቅማቸው የዳበረ እና ምርታማነትን የሚያረጋግጡ ባለሙያዎችን እንዲያፈሩ ለማደረግ መንግሥት የሚያደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
በዚህም ከኩረጃ ነጻ የሆነ፣በራሱ የሚተማመን፣ ለችግሮች መፍትሔ መስጠት የሚችል ትውልድ ከማፍራት በተጨማሪ ጥራት ያለው ትምህርት ተደራሽ ማድረግ ተችሏል፡፡
በሚኪያስ አየለ
9 days ago
ለመጪው ትውልድ የተተከለ ተስፋ፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ጉዞ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለብዙ ዓመታት ከፍተኛ የመሬት መሸርሸር ተደጋጋሚ ድርቅ እና የደን ሽፋን መሳሳት ለኢትዮጵያ ሥነ ምህዳራዊ ሚዛን እና የግብርና ምርታማነት ትልቅ አደጋ ደቅነው ቆይተዋል።
አሁን ግን የአረንጓዴ ልማትና የደን ሽፋን ንቅናቄ መልክዓ ምድርን እየለወጠ፤ በመላ ሀገሪቱ በተደረገ ስልታዊ አመራር ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ታሪኳን በአዲስ መልክ እየጻፈች ትገኛለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እየተመራች ሀገሪቱ በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ እጅግ ግዙፍ ከሆኑት ተፈጥሮ ተኮር መፍትሔዎች አንዱን እየተገበረች ትገኛለች::
ይህም በሚሊየን የሚቆጠር ሄክታር መሬት በማንሰራራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሲሆን ÷ ወደ አረንጓዴ መሪነት የሚያሸጋግረው የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የአካባቢ ጥበቃ ግብ ግልጽ እና ለውጥ አምጪ ነው፡፡
እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ማሳደግ እና ከ54 ሚሊየን ሄክታር በላይ የተበላሸ መሬት እንዲያገግም በማድረግና የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤን ለሀገራዊ ብልጽግና፣ ለአየር ንብረት ደህንነት እና ለግብርና መነቃቃት መሠረታዊ ለውጥ ተደርጎ ይወሰዳል።
ከደን ልማት አጀንዳው ስልታዊ ማዕቀፎች አንዱ በሆነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም በየዓመቱ በክረምት ወቅት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማንቀሳቀስ በመላ ሀገሪቱ በቢሊየን የሚቆጠሩ ችግኞችን በስኬት መተከል ተችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለሀገር በቀል ዛፎች ቅድሚያ መስጠት በችግኝ ጣቢያዎች ምርት ላይ ትልቅ ትኩረት አግኝቷል፡፡
ለተስማሚ ሥነ ምህዳር በየዓመቱ ከሚተከሉት ችግኞች የሀገር በቀል ዛፎች የአካባቢውን አየር ንብረት ለማሻሻል፣ የመሬት መሸርሸርን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ውኃ ተፋሰሶችን ለመጠበቅ ታስበው የተመረጡ ናቸው።
መንግሥት የፍራፍሬ ችግኞች እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ እና የእንስሳት መኖ እፅዋትን በስፋት እንዲተከሉ በማበረታታት እና አርሶ አደሮችን ከንግድ ሰንሰለቶች ጋር በማገናኘት ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ እንዲሁም የቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ወጪ ንግድን እንዲፋጠን በማድረግ ላይ ነው።
በደን መልሶ ማልማት በበጎ ፈቃድ የተከናወኑ በገንዘብ የማይለኩ አካባቢያዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡
በከፍተኛ ቦታዎች ላይ የተካሄደው ደን ልማት የከርሰ-ምድር ውኃ ክምችትን ያሻሻለ ሲሆን÷ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ላይ የሚያርፈውን የደለል ክምችት ቀንሶታል።
በቁልቁለታማና ኮረብታ ቦታዎች ላይ የተሰሩ እርከኖች እና የተተከሉ ዛፎች ለም አፈር እንዳይሸረሸር በመከላከል ለምግብ ምርት የሚሆን ለም መሬት እንዲጠበቅ ማድረግ አስችሏል።
በደን ልማት መነሻነት የማህበር እና የግል ችግኝ ጣቢያዎች መስፋፋት በተለይም ለወጣቶች ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን የፈጠረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ የደን ልማት ጥረቶች የተባበሩት መንግሥታት የሥነ ምህዳር ማገገሚያ አስር ዓመት፣ የቦን ፈተና እና ሀገራዊ የካርቦን ቅነሳ ቃልኪዳኖችን ጨምሮ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በቀጥታ የሚጣጣሙ ናቸው።
በሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ የበረሃማነትን ሒደት መመለስ እንደሚቻል በማስመስከር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ለዓለም አርአያ ሆና እያገለገለች ነው።
ይህ ዓለም አቀፍ መሪነት ያለው የደን ልማት እና የቀጣይ መንገድ የመደመር መንግሥት ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ሀገር ለማስረከብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በምሕረት ደምሴ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለብዙ ዓመታት ከፍተኛ የመሬት መሸርሸር ተደጋጋሚ ድርቅ እና የደን ሽፋን መሳሳት ለኢትዮጵያ ሥነ ምህዳራዊ ሚዛን እና የግብርና ምርታማነት ትልቅ አደጋ ደቅነው ቆይተዋል።
አሁን ግን የአረንጓዴ ልማትና የደን ሽፋን ንቅናቄ መልክዓ ምድርን እየለወጠ፤ በመላ ሀገሪቱ በተደረገ ስልታዊ አመራር ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ታሪኳን በአዲስ መልክ እየጻፈች ትገኛለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እየተመራች ሀገሪቱ በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ እጅግ ግዙፍ ከሆኑት ተፈጥሮ ተኮር መፍትሔዎች አንዱን እየተገበረች ትገኛለች::
ይህም በሚሊየን የሚቆጠር ሄክታር መሬት በማንሰራራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሲሆን ÷ ወደ አረንጓዴ መሪነት የሚያሸጋግረው የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የአካባቢ ጥበቃ ግብ ግልጽ እና ለውጥ አምጪ ነው፡፡
እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ማሳደግ እና ከ54 ሚሊየን ሄክታር በላይ የተበላሸ መሬት እንዲያገግም በማድረግና የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤን ለሀገራዊ ብልጽግና፣ ለአየር ንብረት ደህንነት እና ለግብርና መነቃቃት መሠረታዊ ለውጥ ተደርጎ ይወሰዳል።
ከደን ልማት አጀንዳው ስልታዊ ማዕቀፎች አንዱ በሆነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም በየዓመቱ በክረምት ወቅት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማንቀሳቀስ በመላ ሀገሪቱ በቢሊየን የሚቆጠሩ ችግኞችን በስኬት መተከል ተችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለሀገር በቀል ዛፎች ቅድሚያ መስጠት በችግኝ ጣቢያዎች ምርት ላይ ትልቅ ትኩረት አግኝቷል፡፡
ለተስማሚ ሥነ ምህዳር በየዓመቱ ከሚተከሉት ችግኞች የሀገር በቀል ዛፎች የአካባቢውን አየር ንብረት ለማሻሻል፣ የመሬት መሸርሸርን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ውኃ ተፋሰሶችን ለመጠበቅ ታስበው የተመረጡ ናቸው።
መንግሥት የፍራፍሬ ችግኞች እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ እና የእንስሳት መኖ እፅዋትን በስፋት እንዲተከሉ በማበረታታት እና አርሶ አደሮችን ከንግድ ሰንሰለቶች ጋር በማገናኘት ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ እንዲሁም የቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ወጪ ንግድን እንዲፋጠን በማድረግ ላይ ነው።
በደን መልሶ ማልማት በበጎ ፈቃድ የተከናወኑ በገንዘብ የማይለኩ አካባቢያዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡
በከፍተኛ ቦታዎች ላይ የተካሄደው ደን ልማት የከርሰ-ምድር ውኃ ክምችትን ያሻሻለ ሲሆን÷ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ላይ የሚያርፈውን የደለል ክምችት ቀንሶታል።
በቁልቁለታማና ኮረብታ ቦታዎች ላይ የተሰሩ እርከኖች እና የተተከሉ ዛፎች ለም አፈር እንዳይሸረሸር በመከላከል ለምግብ ምርት የሚሆን ለም መሬት እንዲጠበቅ ማድረግ አስችሏል።
በደን ልማት መነሻነት የማህበር እና የግል ችግኝ ጣቢያዎች መስፋፋት በተለይም ለወጣቶች ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን የፈጠረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ የደን ልማት ጥረቶች የተባበሩት መንግሥታት የሥነ ምህዳር ማገገሚያ አስር ዓመት፣ የቦን ፈተና እና ሀገራዊ የካርቦን ቅነሳ ቃልኪዳኖችን ጨምሮ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በቀጥታ የሚጣጣሙ ናቸው።
በሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ የበረሃማነትን ሒደት መመለስ እንደሚቻል በማስመስከር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ለዓለም አርአያ ሆና እያገለገለች ነው።
ይህ ዓለም አቀፍ መሪነት ያለው የደን ልማት እና የቀጣይ መንገድ የመደመር መንግሥት ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ሀገር ለማስረከብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በምሕረት ደምሴ
9 days ago
u12a2u1275u12eeu1335u12eb u12e8u1271u122au12ddu121d u12d8u122du134fu1295 u12a5u1295u12f4u1275 u12a5u12e8u1240u12e8u1228u127d u1290u12cd? | u1308u1260u1273 u1208u1200u1308u122d u12a5u1293 u12a0u12f3u12f2u1236u1279 u12e8u1271u122au1235u1275 u1218u12f3u1228u123bu12ceu127d
#ethiopia #tourismethiopia #landoforigins ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፏን እንዴት እየቀየረች ነው? | ገበታ ለሀገር እና አዳዲሶቹ የቱሪስት መዳረሻዎች
#ethiopia #tourismethiopia #landoforigins
Sponsored by
Surafel
9 days ago
ቱሪዝም፦ የመደመር እሳቤ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ኢኮኖሚ ሞተርነት የለወጠበት ተጨባጭ ማሳያ
***************************
ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የታሪክ፣ የተፈጥሮ፣ የመልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ እነዚህን ጸጋዎች አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ለዘመናት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ተጨባጭ አስተዋጽኦ ሳያበረክቱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህንን የአስተሳሰብ አጥር በመስበር፣ የሀገራችንን እውነተኛ አቅም ወደ መግለጥ ተሸጋግረዋል።
ይህ ስኬት የመጣው የመንግሥትን፣ የግሉን ዘርፍ፣ የማኅበረሰቡን እና የተፈጥሮን አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ከሚመራው የመደመር ፍልስፍና ነው። ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲወዱ እና እንዲኮሩባት የተደረገው ብሔራዊ ጥሪ ቱሪዝምን ከተለመደው የታሪክ ጥበቃ አልፎ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት አሸጋግሮታል።
በቱሪዝም ዘርፍ የታየው ይህ ሥር ነቀል ለውጥ የመጣው ታዲያ ፈጣን እና ፈጠራ በተሞላበት የፕሮጀክት አመራር የተመራ ሥልታዊ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ በ2011 ዓ.ም አዲስ አበባን ለማስዋብ ከተጀመረው እና እንጦጦ እንዲሁም ሸገር ፓርኮችን እውን ካደረገው "ገበታ ለሸገር" መርሐ ግብር ጅማሮውን አድርጓል።
የዚህ ፕሮጀክት መሳካት በ2012 ዓ.ም ልማቱን ወደ ክልሎች በማስፋፋት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የተፈጥሮ መዳረሻዎችን በከፍተኛ ጥራት ያለማውን "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ወልዷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ ስምንት አዳዲስ መዳረሻዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለማው "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ሀገራዊ የቱሪዝም ገጽታን በመሠረታዊነት እየቀየረ ይገኛል።
የእነዚህን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዳረሻዎች አስተዳደር ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለተመረጡ ባለሀብቶች መሰጠቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ ሥልታዊ ድልድይ ሆኗል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች የተገነቡት ፕሮጀክቶች የመደመር እሳቤን በተግባር የሚያሳዩ ተጨባጭ የልማት ዕንቁዎች ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋፋት እና ከአባያ እንዲሁም ጫሞ ሐይቆች ተፈጥሯዊ ውበት ጋር በመዋሃድ ለአካባቢው ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት 13.3 ሔክታር ላይ ያረፈ ዘመናዊ መገልገያዎችን እና የሔሊኮፕተር ማረፊያን ያካተተ ሲሆን፣ የሰሜኑን የሀገራችን የቱሪስት መስመር የሚያስተሳስር ወሳኝ ማዕከል ሆኗል።
በአፋር ክልል የተገነባው የኒዒን ሌ ፓልም ስፕሪንግ ሎጅ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ጋር ባለው ቅርበት የተፈጥሮ ፍል ውኃን እና ሐይቅን በማቀናጀት የቱሪዝም አቅምን እያጎላ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በበካ የቡና እርሻ አጠገብ ሙሉ በሙሉ ከአካባቢው የተገኙ የተፈጥሮ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የተገነባ የዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ነው። በዚሁ ክልል የሚገኘው የሀላላ ኬላ ሪዞርትም በጊቤ ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቅ ዳርቻ የተገነባ ሌላው አስደናቂ ማሳያ ነው።
እነዚህ ታላላቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዕይታ የቱሪዝምን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባዙ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁሳቁሶች እና በኢትዮጵያውያን አቅም መገንባታቸው በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረውን የግብይት ዝውውር በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከያዘችው ግብ ጋር በቀጥታ የሚጣጣም ሲሆን፣ ዘንድሮ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ5.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የዚህ የመደመር ቀመር ተግባራዊ ስኬት ነው።
የገበታ መርሐ ግብሮች ከተለመደው የቢሮክራሲ አሠራር ወጥተው በፈጠራ የታገዘ የፕሮጀክት አመራርን በማሳየት፣ የኢትዮጵያን የተዳፈነ ጸጋ ወደ ተግባራዊ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ የተጀመረው ጉዞ ስኬታማ ማሳያዎች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tourism #medemer #gebetainitiatives #economicgrowth #landoforigins
***************************
ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የታሪክ፣ የተፈጥሮ፣ የመልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ እነዚህን ጸጋዎች አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ለዘመናት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ተጨባጭ አስተዋጽኦ ሳያበረክቱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህንን የአስተሳሰብ አጥር በመስበር፣ የሀገራችንን እውነተኛ አቅም ወደ መግለጥ ተሸጋግረዋል።
ይህ ስኬት የመጣው የመንግሥትን፣ የግሉን ዘርፍ፣ የማኅበረሰቡን እና የተፈጥሮን አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ከሚመራው የመደመር ፍልስፍና ነው። ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲወዱ እና እንዲኮሩባት የተደረገው ብሔራዊ ጥሪ ቱሪዝምን ከተለመደው የታሪክ ጥበቃ አልፎ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት አሸጋግሮታል።
በቱሪዝም ዘርፍ የታየው ይህ ሥር ነቀል ለውጥ የመጣው ታዲያ ፈጣን እና ፈጠራ በተሞላበት የፕሮጀክት አመራር የተመራ ሥልታዊ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ በ2011 ዓ.ም አዲስ አበባን ለማስዋብ ከተጀመረው እና እንጦጦ እንዲሁም ሸገር ፓርኮችን እውን ካደረገው "ገበታ ለሸገር" መርሐ ግብር ጅማሮውን አድርጓል።
የዚህ ፕሮጀክት መሳካት በ2012 ዓ.ም ልማቱን ወደ ክልሎች በማስፋፋት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የተፈጥሮ መዳረሻዎችን በከፍተኛ ጥራት ያለማውን "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ወልዷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ ስምንት አዳዲስ መዳረሻዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለማው "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ሀገራዊ የቱሪዝም ገጽታን በመሠረታዊነት እየቀየረ ይገኛል።
የእነዚህን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዳረሻዎች አስተዳደር ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለተመረጡ ባለሀብቶች መሰጠቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ ሥልታዊ ድልድይ ሆኗል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች የተገነቡት ፕሮጀክቶች የመደመር እሳቤን በተግባር የሚያሳዩ ተጨባጭ የልማት ዕንቁዎች ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋፋት እና ከአባያ እንዲሁም ጫሞ ሐይቆች ተፈጥሯዊ ውበት ጋር በመዋሃድ ለአካባቢው ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት 13.3 ሔክታር ላይ ያረፈ ዘመናዊ መገልገያዎችን እና የሔሊኮፕተር ማረፊያን ያካተተ ሲሆን፣ የሰሜኑን የሀገራችን የቱሪስት መስመር የሚያስተሳስር ወሳኝ ማዕከል ሆኗል።
በአፋር ክልል የተገነባው የኒዒን ሌ ፓልም ስፕሪንግ ሎጅ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ጋር ባለው ቅርበት የተፈጥሮ ፍል ውኃን እና ሐይቅን በማቀናጀት የቱሪዝም አቅምን እያጎላ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በበካ የቡና እርሻ አጠገብ ሙሉ በሙሉ ከአካባቢው የተገኙ የተፈጥሮ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የተገነባ የዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ነው። በዚሁ ክልል የሚገኘው የሀላላ ኬላ ሪዞርትም በጊቤ ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቅ ዳርቻ የተገነባ ሌላው አስደናቂ ማሳያ ነው።
እነዚህ ታላላቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዕይታ የቱሪዝምን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባዙ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁሳቁሶች እና በኢትዮጵያውያን አቅም መገንባታቸው በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረውን የግብይት ዝውውር በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከያዘችው ግብ ጋር በቀጥታ የሚጣጣም ሲሆን፣ ዘንድሮ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ5.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የዚህ የመደመር ቀመር ተግባራዊ ስኬት ነው።
የገበታ መርሐ ግብሮች ከተለመደው የቢሮክራሲ አሠራር ወጥተው በፈጠራ የታገዘ የፕሮጀክት አመራርን በማሳየት፣ የኢትዮጵያን የተዳፈነ ጸጋ ወደ ተግባራዊ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ የተጀመረው ጉዞ ስኬታማ ማሳያዎች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tourism #medemer #gebetainitiatives #economicgrowth #landoforigins
10 days ago
አድማስ ዩኒቨርሲቲ ከ5,000 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ!
#fastmereja :-አድማስ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ በርቀት እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ መርሃ-ግብሮች ያሰለጠናቸውን ከ5,000 በላይ ተማሪዎች በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
ከተመራቂዎቹ መካከል 73.16 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ሲሆኑ ይህም ተቋሙ ለሴቶች የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ እያደረገ ያለውን አዎንታዊ አስተዋጽኦ የሚያሳይ መሆኑ ተመልክቷል።
በዕለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት አምባሳደር ዶ/ር የሺመብራት መርሻ ካሳ፣ የዩኒቨርሲቲው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ይብራህ ግርማይ፣ የሠኔት አባላት፣ መምህራንና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተቋሙ ላለፉት 27 ዓመታት ከ100,000 በላይ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ለሀገር ልማት ማበቃቱን የገለፀ ሲሆን ከአንድ አነስተኛ የማሰልጠኛ ማዕከል የተነሳው አድማስ ዩኒቨርሲቲ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገር ውስጥ 10 ካምፓሶችንና በርካታ የርቀት ማዕከላትን የከፈተ እና በሶማሊላንድና በፑንትላንድም ተመራጭ ተቋም ሆኖ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ነዉ የተገለፀዉ።
አድማስ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ጥራትና በስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ምዘናዎች በርካታ አገር አቀፍ ዕውቅናዎችን ያገኘ ሲሆን፣ በቅርቡም በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የዳግም ምዝገባ መስፈርትን ካሟሉ ጥቂት የግል ተቋማት አንዱ መሆኑ ተገልጿል።
ከመማር ማስተማሩ ጎን ለጎን ተቋሙ 18ኛውን ዓመታዊ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በመጪው ጳጉሜ ወር እንደሚያካሂድ ተገልፆ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የነፃ ትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) ለማህበረሰቡ መስጠቱ ተገልጿል።
በመጨረሻም፣ ሁለተኛና ሦስተኛ ዲግሪያቸውን ለመቀጠል ለሚፈልጉ ተመራቂዎች ለሚጠብቃቸው ሀገርአቀፍ የመግቢያ ፈተና ዩኒቨርሲቲው ነፃ የማጠናከሪያ ድጋፍ እንደሚሰጥ የገለጹት ፕሬዚደንቱ፣ ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው መልካም የምረቃ በዓል እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።
#fastmereja :-አድማስ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ በርቀት እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ መርሃ-ግብሮች ያሰለጠናቸውን ከ5,000 በላይ ተማሪዎች በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
ከተመራቂዎቹ መካከል 73.16 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ሲሆኑ ይህም ተቋሙ ለሴቶች የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ እያደረገ ያለውን አዎንታዊ አስተዋጽኦ የሚያሳይ መሆኑ ተመልክቷል።
በዕለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት አምባሳደር ዶ/ር የሺመብራት መርሻ ካሳ፣ የዩኒቨርሲቲው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ይብራህ ግርማይ፣ የሠኔት አባላት፣ መምህራንና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተቋሙ ላለፉት 27 ዓመታት ከ100,000 በላይ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ለሀገር ልማት ማበቃቱን የገለፀ ሲሆን ከአንድ አነስተኛ የማሰልጠኛ ማዕከል የተነሳው አድማስ ዩኒቨርሲቲ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገር ውስጥ 10 ካምፓሶችንና በርካታ የርቀት ማዕከላትን የከፈተ እና በሶማሊላንድና በፑንትላንድም ተመራጭ ተቋም ሆኖ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ነዉ የተገለፀዉ።
አድማስ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ጥራትና በስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ምዘናዎች በርካታ አገር አቀፍ ዕውቅናዎችን ያገኘ ሲሆን፣ በቅርቡም በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የዳግም ምዝገባ መስፈርትን ካሟሉ ጥቂት የግል ተቋማት አንዱ መሆኑ ተገልጿል።
ከመማር ማስተማሩ ጎን ለጎን ተቋሙ 18ኛውን ዓመታዊ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በመጪው ጳጉሜ ወር እንደሚያካሂድ ተገልፆ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የነፃ ትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) ለማህበረሰቡ መስጠቱ ተገልጿል።
በመጨረሻም፣ ሁለተኛና ሦስተኛ ዲግሪያቸውን ለመቀጠል ለሚፈልጉ ተመራቂዎች ለሚጠብቃቸው ሀገርአቀፍ የመግቢያ ፈተና ዩኒቨርሲቲው ነፃ የማጠናከሪያ ድጋፍ እንደሚሰጥ የገለጹት ፕሬዚደንቱ፣ ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው መልካም የምረቃ በዓል እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።
11 days ago
በሰው ህይወት ማዳን የሚለካው ደም ልገሳ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የክረምቱ ወራት ወጣቶችና ተማሪዎች እንዲሁም የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች እረፍት ላይ የሚገኙበት ወቅት በመሆኑ በርካታ ማህበረሰቡን የሚጠቅሙ የበጎ አድራጎት ስራዎች ይከናወናሉ፡፡
ከዚህም መካከል በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ በመሰማራት የሰው ህይወትን ለመታደግ የሚያስችለው የደም ልገሳ ነው፡፡ ደም ልገሳ በበጎ ፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ለሰዎች የመድረስ እና የመደጋገፍ ሂደት ነው፡፡
በጤና ተቋማት ለበርካታ ጊዜያት የደም እጥረት እያጋጠመው እንደሆነ ይናገራል፤ በመሆኑም በማንኛውም ሰዓት በመሄድ ከሚለገሰው በተጨማሪ ማህበረሰቡን ለማነቃቃት የሚጠቅሙ የደም ልገሳ መርሀ ግብሮችን ያዘጋጃል፡፡
ቀደም ባሉት ጊዜያት ሰዎች ደም መለገስን ከእምነት ጋር የሚጋጭ ነገር አድርገው በማሰብ፣ ራሳቸውን ከሂደቱ ያገልሉ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን የተለያዩ ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎች በመሰራታቸው የበጎ ፈቃድ ደም ለጋሾች መጠን እያደገ መጥቷል፡፡
የሰው ልጅ ተፈጥሮው ደግነት እንደሆነ ይታመናል፤ ተጋግዞና ተደግፎ በጋራ በመቆም ሀገር መገንባትን ይዞ የሚነሳው የመደመር ፍልስፍና መከፋፈልና በጋራ አለመቆም ለሀገር እንደማይበጅ በማስቀመጥ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህል ማዳበር እንዳለብን ይጠቁማል፡፡
ሰዎች በአካባቢው ባለ ማህበረሰብ ይቀረፃሉ፣ ለነገሮች ያለንን እይታ፣ በጎ ነገር ማድረግን ለማህበረሰብ መቆምን ከምንኖርበት አካባቢ እንማራለን። ኢትዮጵያውያን ባህላችንና የአኗኗር ስርአታችን አብሮነትን የተደገፈ ነው፡፡
የመተጋገዝ፣ የመረዳዳት ብሎም ችግሮችን በጋራ የመፍታት ልምዱ አለን።
አባቶቻችን እንዳሳዩን የኢኮኖሚ ችግሮችን ተሰብስቦ እቁብ በመጣል፣ የሀዘንና የደስታ ጊዜዎችን በምንኖርበት አካባቢ ዕድርና ማህበር በመመስረት መረዳዳትን ባህል አድርገን ዘልቀናል፡፡
ዛሬም የተለመደው የመተጋገዝ ባህላችንን መሰረት አድርገን ደም ስንለግስ ለታመመ ለመድረስ፣ በወሊድ ጊዜ ደም የሚፈሳቸው እናቶችን እንዲሁም ሌሎች በደም እጥረት የተነሳ ህይወታቸውን የሚያጡ ሰዎችን ለመታደግ እንደሆነ በማመን ነው፡፡
ባለፉት ዓመታት የመደመር መንግሥት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተቋማዊ ቁመና ይዞ በጋ ከክረምት እንዲተገበር እያደረገ ሲሆን፤ በመላ ሀገሪቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ተሳትፎ ያደርጋሉ።
በዚህም በቢሊየን ብሮች የሚገመቱ አገልግሎቶች ለህብረተሰቡ ይሰጣል።
ከአገልግሎቶቹ መካከል በገንዘብ ሳይሆን በሰው ህይወት ማዳን የሚገመተው የደም ልገሳ ዋናው ተግባር ነው።
በቤተልሔም ግርማ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የክረምቱ ወራት ወጣቶችና ተማሪዎች እንዲሁም የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች እረፍት ላይ የሚገኙበት ወቅት በመሆኑ በርካታ ማህበረሰቡን የሚጠቅሙ የበጎ አድራጎት ስራዎች ይከናወናሉ፡፡
ከዚህም መካከል በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ በመሰማራት የሰው ህይወትን ለመታደግ የሚያስችለው የደም ልገሳ ነው፡፡ ደም ልገሳ በበጎ ፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ለሰዎች የመድረስ እና የመደጋገፍ ሂደት ነው፡፡
በጤና ተቋማት ለበርካታ ጊዜያት የደም እጥረት እያጋጠመው እንደሆነ ይናገራል፤ በመሆኑም በማንኛውም ሰዓት በመሄድ ከሚለገሰው በተጨማሪ ማህበረሰቡን ለማነቃቃት የሚጠቅሙ የደም ልገሳ መርሀ ግብሮችን ያዘጋጃል፡፡
ቀደም ባሉት ጊዜያት ሰዎች ደም መለገስን ከእምነት ጋር የሚጋጭ ነገር አድርገው በማሰብ፣ ራሳቸውን ከሂደቱ ያገልሉ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን የተለያዩ ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎች በመሰራታቸው የበጎ ፈቃድ ደም ለጋሾች መጠን እያደገ መጥቷል፡፡
የሰው ልጅ ተፈጥሮው ደግነት እንደሆነ ይታመናል፤ ተጋግዞና ተደግፎ በጋራ በመቆም ሀገር መገንባትን ይዞ የሚነሳው የመደመር ፍልስፍና መከፋፈልና በጋራ አለመቆም ለሀገር እንደማይበጅ በማስቀመጥ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህል ማዳበር እንዳለብን ይጠቁማል፡፡
ሰዎች በአካባቢው ባለ ማህበረሰብ ይቀረፃሉ፣ ለነገሮች ያለንን እይታ፣ በጎ ነገር ማድረግን ለማህበረሰብ መቆምን ከምንኖርበት አካባቢ እንማራለን። ኢትዮጵያውያን ባህላችንና የአኗኗር ስርአታችን አብሮነትን የተደገፈ ነው፡፡
የመተጋገዝ፣ የመረዳዳት ብሎም ችግሮችን በጋራ የመፍታት ልምዱ አለን።
አባቶቻችን እንዳሳዩን የኢኮኖሚ ችግሮችን ተሰብስቦ እቁብ በመጣል፣ የሀዘንና የደስታ ጊዜዎችን በምንኖርበት አካባቢ ዕድርና ማህበር በመመስረት መረዳዳትን ባህል አድርገን ዘልቀናል፡፡
ዛሬም የተለመደው የመተጋገዝ ባህላችንን መሰረት አድርገን ደም ስንለግስ ለታመመ ለመድረስ፣ በወሊድ ጊዜ ደም የሚፈሳቸው እናቶችን እንዲሁም ሌሎች በደም እጥረት የተነሳ ህይወታቸውን የሚያጡ ሰዎችን ለመታደግ እንደሆነ በማመን ነው፡፡
ባለፉት ዓመታት የመደመር መንግሥት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተቋማዊ ቁመና ይዞ በጋ ከክረምት እንዲተገበር እያደረገ ሲሆን፤ በመላ ሀገሪቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ተሳትፎ ያደርጋሉ።
በዚህም በቢሊየን ብሮች የሚገመቱ አገልግሎቶች ለህብረተሰቡ ይሰጣል።
ከአገልግሎቶቹ መካከል በገንዘብ ሳይሆን በሰው ህይወት ማዳን የሚገመተው የደም ልገሳ ዋናው ተግባር ነው።
በቤተልሔም ግርማ
11 days ago
ከችርቻሮ የሱቅ ስራ የተነሳው ጊፍት ትሬዲንግ 35ኛ አመቱን አከበረ
#ethiopia | በኢትዮጵያ በገቢና ወጪ ንግድ ዘርፍ አንጋፋ ከሆኑ ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ጊፍት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ የተመሰረተበትን 35ኛ ዓመት የምስረታ ኢዮቤልዩ በዓል በዛሬዉ እለት አክብሯል።
በንግድ ማህበረሰቡ፣ በመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና በድርጅቱ አመራሮች በተገኙበት በዚህ መርሃ-ግብር ላይ ኩባንያው ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ከግማሽ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ያቀረበ ሲሆን፣ በቀጣይም ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሸጋገር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል።
ድርጅቱ ይፋ ባደረገው እቅድ መሠረት በአዳማ እና ሞጆ ከተሞች መካከል በሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ፍሪ ዞን ውስጥ 7,527.54 ካሬ ሜትር ቦታ መረከቡን ገልፀዉ ቦታው ከጅቡቲ ኮሪደር እና ከሞጆ ደረቅ ወደብ አቅራቢያ የሚገኝ በመሆኑ፣ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴውን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳልጠው የተገለጸ ሲሆን፤ የአካባቢው የዲዛይን ስራ ተጠናቆ ወደ ግንባታ ምዕራፍ መሸጋገሩ ተመልክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ኩባንያው እሴት በተጨመረባቸው የግብርና ምርቶች ዘርፍ መሰማራት የጀመረ ሲሆን፣ በተለይም በድፍድፍ የአቮካዶ ዘይት ማምረት እና በከባድ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች አስመጪነት ዘርፍ ለመግባት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።
የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን ለማሳደግ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በቤንች ሸኮ ዞን የጥቁር አዝሙድ እርሻ መጀመሩን የጠቆመው ጊፍት ትሬዲንግ፤ በቀጣይ ስድስት ወራት ውስጥ 300 ሄክታርየቡና እርሻ መሬት ተረክቦ ወደ ምርት እንደሚገባ አስታውቋል።
ከ50 ዓመታት በፊት በመርካቶ በታዋቂው የቢዝነስ ሰው በአቶ ገብረኢየሱስ ኢጋታ ሲማ በትንሽ የችርቻሮ ሱቅ የተጀመረው ይህ የንግድ እንቅስቃሴ፣ በ1980ዎቹ መጀመሪያ ወደ ገቢና ወጪ ንግድ በማደግ ለዛሬው ግዙፉ ጊፍት ቢዝነስ ግሩፕ (ጊፍት ሪል እስቴት፣ ጊፍት ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ብረታ ብረት፣ ጊፍት ፕሮፐርቲ እና ጊፍት ቱር ኤንድ ትራቭል) መፈጠር መሰረት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም B-29 የልብስ ሳሙና፣ የሮድ ስቶን የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ የጂንዳል ቆርቆሮዎች፣ የብረትና የኬሚካል ምርቶችን ጨምሮ በርካታ ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ በማስተዋወቅ ረገድ ኩባንያው የነበረው ሚና ከፍተኛ እንደነበር ተገልጿል።
ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2030 በኢትዮጵያ በቡና፣ ቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ እና ቅመማ ቅመም ላኪነት ከግንባርቀደም 5 ኩባንያዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #gifttradingrealstate #construction #technology
#ethiopia | በኢትዮጵያ በገቢና ወጪ ንግድ ዘርፍ አንጋፋ ከሆኑ ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ጊፍት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ የተመሰረተበትን 35ኛ ዓመት የምስረታ ኢዮቤልዩ በዓል በዛሬዉ እለት አክብሯል።
በንግድ ማህበረሰቡ፣ በመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና በድርጅቱ አመራሮች በተገኙበት በዚህ መርሃ-ግብር ላይ ኩባንያው ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ከግማሽ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ያቀረበ ሲሆን፣ በቀጣይም ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሸጋገር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል።
ድርጅቱ ይፋ ባደረገው እቅድ መሠረት በአዳማ እና ሞጆ ከተሞች መካከል በሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ፍሪ ዞን ውስጥ 7,527.54 ካሬ ሜትር ቦታ መረከቡን ገልፀዉ ቦታው ከጅቡቲ ኮሪደር እና ከሞጆ ደረቅ ወደብ አቅራቢያ የሚገኝ በመሆኑ፣ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴውን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳልጠው የተገለጸ ሲሆን፤ የአካባቢው የዲዛይን ስራ ተጠናቆ ወደ ግንባታ ምዕራፍ መሸጋገሩ ተመልክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ኩባንያው እሴት በተጨመረባቸው የግብርና ምርቶች ዘርፍ መሰማራት የጀመረ ሲሆን፣ በተለይም በድፍድፍ የአቮካዶ ዘይት ማምረት እና በከባድ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች አስመጪነት ዘርፍ ለመግባት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።
የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን ለማሳደግ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በቤንች ሸኮ ዞን የጥቁር አዝሙድ እርሻ መጀመሩን የጠቆመው ጊፍት ትሬዲንግ፤ በቀጣይ ስድስት ወራት ውስጥ 300 ሄክታርየቡና እርሻ መሬት ተረክቦ ወደ ምርት እንደሚገባ አስታውቋል።
ከ50 ዓመታት በፊት በመርካቶ በታዋቂው የቢዝነስ ሰው በአቶ ገብረኢየሱስ ኢጋታ ሲማ በትንሽ የችርቻሮ ሱቅ የተጀመረው ይህ የንግድ እንቅስቃሴ፣ በ1980ዎቹ መጀመሪያ ወደ ገቢና ወጪ ንግድ በማደግ ለዛሬው ግዙፉ ጊፍት ቢዝነስ ግሩፕ (ጊፍት ሪል እስቴት፣ ጊፍት ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ብረታ ብረት፣ ጊፍት ፕሮፐርቲ እና ጊፍት ቱር ኤንድ ትራቭል) መፈጠር መሰረት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም B-29 የልብስ ሳሙና፣ የሮድ ስቶን የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ የጂንዳል ቆርቆሮዎች፣ የብረትና የኬሚካል ምርቶችን ጨምሮ በርካታ ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ በማስተዋወቅ ረገድ ኩባንያው የነበረው ሚና ከፍተኛ እንደነበር ተገልጿል።
ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2030 በኢትዮጵያ በቡና፣ ቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ እና ቅመማ ቅመም ላኪነት ከግንባርቀደም 5 ኩባንያዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #gifttradingrealstate #construction #technology
11 days ago
ጊፍት ትሬዲንግ 35ኛ ዓመት የምስረታ ኢዮቤልዩውን አከበረ!
#fastmereja :- በኢትዮጵያ በገቢና ወጪ ንግድ ዘርፍ አንጋፋ ከሆኑ ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ጊፍት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ የተመሰረተበትን 35ኛ ዓመት የምስረታ ኢዮቤልዩ በዓል በዛሬዉ እለት አክብሯል።
በንግድ ማህበረሰቡ፣ በመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና በድርጅቱ አመራሮች በተገኙበት በዚህ መርሃ-ግብር ላይ ኩባንያው ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ከግማሽ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ያቀረበ ሲሆን፣ በቀጣይም ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሸጋገር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል።
ድርጅቱ ይፋ ባደረገው እቅድ መሠረት በአዳማ እና ሞጆ ከተሞች መካከል በሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ፍሪ ዞን ውስጥ 7,527.54 ካሬ ሜትር ቦታ መረከቡን ገልፀዉ ቦታው ከጅቡቲ ኮሪደር እና ከሞጆ ደረቅ ወደብ አቅራቢያ የሚገኝ በመሆኑ፣ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴውን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳልጠው የተገለጸ ሲሆን፤ የአካባቢው የዲዛይን ስራ ተጠናቆ ወደ ግንባታ ምዕራፍ መሸጋገሩ ተመልክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ኩባንያው እሴት በተጨመረባቸው የግብርና ምርቶች ዘርፍ መሰማራት የጀመረ ሲሆን፣ በተለይም በድፍድፍ የአቮካዶ ዘይት ማምረት እና በከባድ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች አስመጪነት ዘርፍ ለመግባት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።
የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን ለማሳደግ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በቤንች ሸኮ ዞን የጥቁር አዝሙድ እርሻ መጀመሩን የጠቆመው ጊፍት ትሬዲንግ፤ በቀጣይ ስድስት ወራት ውስጥ 300 ሄክታርየቡና እርሻ መሬት ተረክቦ ወደ ምርት እንደሚገባ አስታውቋል።
ከ50 ዓመታት በፊት በመርካቶ በታዋቂው የቢዝነስ ሰው በአቶ ገብረኢየሱስ ኢጋታ ሲማ በትንሽ የችርቻሮ ሱቅ የተጀመረው ይህ የንግድ እንቅስቃሴ፣ በ1980ዎቹ መጀመሪያ ወደ ገቢና ወጪ ንግድ በማደግ ለዛሬው ግዙፉ ጊፍት ቢዝነስ ግሩፕ (ጊፍት ሪል እስቴት፣ ጊፍት ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ብረታ ብረት፣ ጊፍት ፕሮፐርቲ እና ጊፍት ቱር ኤንድ ትራቭል) መፈጠር መሰረት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም B-29 የልብስ ሳሙና፣ የሮድ ስቶን የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ የጂንዳል ቆርቆሮዎች፣ የብረትና የኬሚካል ምርቶችን ጨምሮ በርካታ ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ በማስተዋወቅ ረገድ ኩባንያው የነበረው ሚና ከፍተኛ እንደነበር ተገልጿል።
ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2030 በኢትዮጵያ በቡና፣ ቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ እና ቅመማ ቅመም ላኪነት ከግንባርቀደም 5 ኩባንያዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
#fastmereja :- በኢትዮጵያ በገቢና ወጪ ንግድ ዘርፍ አንጋፋ ከሆኑ ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ጊፍት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ የተመሰረተበትን 35ኛ ዓመት የምስረታ ኢዮቤልዩ በዓል በዛሬዉ እለት አክብሯል።
በንግድ ማህበረሰቡ፣ በመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና በድርጅቱ አመራሮች በተገኙበት በዚህ መርሃ-ግብር ላይ ኩባንያው ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ከግማሽ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ያቀረበ ሲሆን፣ በቀጣይም ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሸጋገር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል።
ድርጅቱ ይፋ ባደረገው እቅድ መሠረት በአዳማ እና ሞጆ ከተሞች መካከል በሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ፍሪ ዞን ውስጥ 7,527.54 ካሬ ሜትር ቦታ መረከቡን ገልፀዉ ቦታው ከጅቡቲ ኮሪደር እና ከሞጆ ደረቅ ወደብ አቅራቢያ የሚገኝ በመሆኑ፣ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴውን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳልጠው የተገለጸ ሲሆን፤ የአካባቢው የዲዛይን ስራ ተጠናቆ ወደ ግንባታ ምዕራፍ መሸጋገሩ ተመልክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ኩባንያው እሴት በተጨመረባቸው የግብርና ምርቶች ዘርፍ መሰማራት የጀመረ ሲሆን፣ በተለይም በድፍድፍ የአቮካዶ ዘይት ማምረት እና በከባድ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች አስመጪነት ዘርፍ ለመግባት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።
የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን ለማሳደግ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በቤንች ሸኮ ዞን የጥቁር አዝሙድ እርሻ መጀመሩን የጠቆመው ጊፍት ትሬዲንግ፤ በቀጣይ ስድስት ወራት ውስጥ 300 ሄክታርየቡና እርሻ መሬት ተረክቦ ወደ ምርት እንደሚገባ አስታውቋል።
ከ50 ዓመታት በፊት በመርካቶ በታዋቂው የቢዝነስ ሰው በአቶ ገብረኢየሱስ ኢጋታ ሲማ በትንሽ የችርቻሮ ሱቅ የተጀመረው ይህ የንግድ እንቅስቃሴ፣ በ1980ዎቹ መጀመሪያ ወደ ገቢና ወጪ ንግድ በማደግ ለዛሬው ግዙፉ ጊፍት ቢዝነስ ግሩፕ (ጊፍት ሪል እስቴት፣ ጊፍት ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ብረታ ብረት፣ ጊፍት ፕሮፐርቲ እና ጊፍት ቱር ኤንድ ትራቭል) መፈጠር መሰረት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም B-29 የልብስ ሳሙና፣ የሮድ ስቶን የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ የጂንዳል ቆርቆሮዎች፣ የብረትና የኬሚካል ምርቶችን ጨምሮ በርካታ ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ በማስተዋወቅ ረገድ ኩባንያው የነበረው ሚና ከፍተኛ እንደነበር ተገልጿል።
ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2030 በኢትዮጵያ በቡና፣ ቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ እና ቅመማ ቅመም ላኪነት ከግንባርቀደም 5 ኩባንያዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
11 days ago
የአንጋፋ ጋዜጠኞች በልሁ ተረፈ እና አዲስዓለም ሓድጉ የምስጋናና የዕውቅና ፕሮግራም ተካሄደ
#ethiopia | የአንጋፋ ጋዜጠኞች በልሁ ተረፈ እና አዲስዓለም ሓድጉ የምስጋናና የዕውቅና ፕሮግራም በዛሬው ዕለት በወመዘክር መርስኤ ሀዘን አዳራሽ ተካሂዷል።
በፕሮግራሙ ላይ ጋዜጠኞች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ እንዲሁም ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ እንግዶች ተገኝተው ለሁለቱ አንጋፋ ጋዜጠኞች ክብርና እውቅና ሰጥተዋል።
ጋዜጠኛ በልሁ ተረፈ እና ጋዜጠኛ አዲስዓለም ሓድጉ ከ37 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ የሚዲያ ዘርፍ በትጋት በማገልገል ለሙያው እና ለሀገር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ አንጋፋ ጋዜጠኞች ናቸው።
ፕሮግራሙ ለረጅም ዓመታት ያበረከቱትን ሙያዊ አስተዋፅኦ በማክበርና በማመስገን የተዘጋጀ ሲሆን፣ የሙያ ጓደኞቻቸውና አድናቂዎቻቸውም የምስጋና መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።
#ethiopia | የአንጋፋ ጋዜጠኞች በልሁ ተረፈ እና አዲስዓለም ሓድጉ የምስጋናና የዕውቅና ፕሮግራም በዛሬው ዕለት በወመዘክር መርስኤ ሀዘን አዳራሽ ተካሂዷል።
በፕሮግራሙ ላይ ጋዜጠኞች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ እንዲሁም ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ እንግዶች ተገኝተው ለሁለቱ አንጋፋ ጋዜጠኞች ክብርና እውቅና ሰጥተዋል።
ጋዜጠኛ በልሁ ተረፈ እና ጋዜጠኛ አዲስዓለም ሓድጉ ከ37 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ የሚዲያ ዘርፍ በትጋት በማገልገል ለሙያው እና ለሀገር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ አንጋፋ ጋዜጠኞች ናቸው።
ፕሮግራሙ ለረጅም ዓመታት ያበረከቱትን ሙያዊ አስተዋፅኦ በማክበርና በማመስገን የተዘጋጀ ሲሆን፣ የሙያ ጓደኞቻቸውና አድናቂዎቻቸውም የምስጋና መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።
Sponsored by
Surafel
11 days ago
ክንዱ የማይታጠፈው የጀግኖች አምባ!
****************
እስቲ ለአፍታ ቆም ብለን እናስብ፤ የዛሬዋ ኢትዮጵያ የጸጥታና የሉዓላዊነት ምሽግ ምን ያህል ጠንካራ ነው? የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዛሬ የተረከበውን ሀገራዊ አደራ ታሪክን በሚቀይር የልህቀት ከፍታ ላይ አድርሶታል።
እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ በልዩ የሀገር ፍቅር ስሜት እና በጽኑ ኩራት የሚያስደምመው ይህ ተቋም፣ በጥልቅ ሪፎርም ዳግም የተወለደ የሉዓላዊነታችን ሕያው ምሽግ ነው። ሠራዊታችን ዛሬ በተግባር ያረጋገጠው አቅም የውጊያ ክህሎትን ማሳደግ ብቻ አይደለም።
ከዚያም በዘለለ፤ ጦርነትን ቀድሞ የማስቀረት፣ የጥፋት ሥጋትን ገና በእንጭጩ የማምከን እና በማያዳግም የቅድመ መከላከል (Deterrence) ሳይንሳዊ ስትራቴጂ ጠላትን የማንበርከክ እጅግ የላቀ አቅም ነው።
ጠላት ክፉ አስቦት ወደ ኋላ በድንጋጤ እንዲያፈገፍግ የሚያደርገው ይህ ዘመኑን የሚዋጅ ወታደራዊ ጥበብ፣ ኢትዮጵያን የማትደፈር የብረት አጥር አድርጓታል።
በምድር ላይ ከሚታየው አንበሳ መሰል የውጊያ ጀግንነት፣ በአየር ላይ ካለው ንስራዊ የበላይነት፣ እንዲሁም ከሁለት አሥርት ዓመታት በኋላ ዳግም ተቋቁሞ የቀይ ባሕርን ቀጣና በንቃት ከሚቃኘው የባሕር ኃይላችን ልዕልና ጀርባ ያለው ትልቁ ምሥጢር፤ በቴክኖሎጂ የታጀበው ታሪካዊ የተቋም ሪፎርም ነው።
በተለይም ዘመናዊ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን (UAVs)፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን እና ዘመን አመጣሽ የጦር ቴክኖሎጂዎችን በላቀ የሳይበር አቅም በማዋሃድ የገነባው የኤሮስፔስ ልዕልና፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ቀጣናዊ አስፈሪ ኃይል አድርጓታል።
የዘመኑ ሳይንስ በከፍተኛ ደረጃ ያስታጠቃቸው፣ በሥነ ልቦና የገዘፉት የሠራዊቱ አባላት፣ ኢትዮጵያን በላቀ የውጊያ ጥበብ የሚጠብቁ የብረት ካስማዎች ናቸው።
ይህ ታሪካዊና እጅግ ስኬታማ ሪፎርም "ሀገር አስቀድም፣ ራስ አስቀጣይና ብቃት ያለው ተቋም ፍጠር" በሚል የጠለቀ ፖለቲካዊና ተቋማዊ ፍልስፍና የተመራ ነው። መከላከያችን ዛሬ የጦርነት ጋሻችን ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የልማት አቅም፣ የሰላም ኢንጂን እና የሽግግሩ ዘመን ታማኝ ዋልታ ነው።
ሠራዊቱ የፈጠረው ቴክኖሎጂያዊ እና ሳይንሳዊ ብቃት ለሀገር የልማት ጉዞ፣ ለመሠረተ ልማት ደኅንነት እና ለኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነታችን ጥበቃ ትልቅ ትሩፋት እያበረከተ ይገኛል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የነገዋን፣ በለጽጋና ተከብራ የምትኖረውን ጠንካራ ኢትዮጵያ እውን የሚያደርግ የኩራታችን ምንጭ ነው።
ኢትዮጵያ የቱንም ያህል ውጫዊና ውስጣዊ ፈተና ቢገጥማት፣ ይህ በቴክኖሎጂ የረቀቀ፣ በሳይንስ የላቀ፣ ጦርነትን አስቀድሞ በማምከን ዘላቂ ሰላምን የሚያጸና አሸናፊ ኃይል እስካላት ድረስ፣ የማትበገር የነጻነት አምባ ሆና ለዘላለም ትቀጥላለች! ክብራችን፣ ጋሻችን፣ እና የዘመኑ የቴክኖሎጂ ምሽጋችን ለሆነው ጀግናው ሠራዊታችን ማለቂያ የሌለው ክብር ይገባል!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #endf #sovereignty #militarycapability
****************
እስቲ ለአፍታ ቆም ብለን እናስብ፤ የዛሬዋ ኢትዮጵያ የጸጥታና የሉዓላዊነት ምሽግ ምን ያህል ጠንካራ ነው? የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዛሬ የተረከበውን ሀገራዊ አደራ ታሪክን በሚቀይር የልህቀት ከፍታ ላይ አድርሶታል።
እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ በልዩ የሀገር ፍቅር ስሜት እና በጽኑ ኩራት የሚያስደምመው ይህ ተቋም፣ በጥልቅ ሪፎርም ዳግም የተወለደ የሉዓላዊነታችን ሕያው ምሽግ ነው። ሠራዊታችን ዛሬ በተግባር ያረጋገጠው አቅም የውጊያ ክህሎትን ማሳደግ ብቻ አይደለም።
ከዚያም በዘለለ፤ ጦርነትን ቀድሞ የማስቀረት፣ የጥፋት ሥጋትን ገና በእንጭጩ የማምከን እና በማያዳግም የቅድመ መከላከል (Deterrence) ሳይንሳዊ ስትራቴጂ ጠላትን የማንበርከክ እጅግ የላቀ አቅም ነው።
ጠላት ክፉ አስቦት ወደ ኋላ በድንጋጤ እንዲያፈገፍግ የሚያደርገው ይህ ዘመኑን የሚዋጅ ወታደራዊ ጥበብ፣ ኢትዮጵያን የማትደፈር የብረት አጥር አድርጓታል።
በምድር ላይ ከሚታየው አንበሳ መሰል የውጊያ ጀግንነት፣ በአየር ላይ ካለው ንስራዊ የበላይነት፣ እንዲሁም ከሁለት አሥርት ዓመታት በኋላ ዳግም ተቋቁሞ የቀይ ባሕርን ቀጣና በንቃት ከሚቃኘው የባሕር ኃይላችን ልዕልና ጀርባ ያለው ትልቁ ምሥጢር፤ በቴክኖሎጂ የታጀበው ታሪካዊ የተቋም ሪፎርም ነው።
በተለይም ዘመናዊ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን (UAVs)፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን እና ዘመን አመጣሽ የጦር ቴክኖሎጂዎችን በላቀ የሳይበር አቅም በማዋሃድ የገነባው የኤሮስፔስ ልዕልና፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ቀጣናዊ አስፈሪ ኃይል አድርጓታል።
የዘመኑ ሳይንስ በከፍተኛ ደረጃ ያስታጠቃቸው፣ በሥነ ልቦና የገዘፉት የሠራዊቱ አባላት፣ ኢትዮጵያን በላቀ የውጊያ ጥበብ የሚጠብቁ የብረት ካስማዎች ናቸው።
ይህ ታሪካዊና እጅግ ስኬታማ ሪፎርም "ሀገር አስቀድም፣ ራስ አስቀጣይና ብቃት ያለው ተቋም ፍጠር" በሚል የጠለቀ ፖለቲካዊና ተቋማዊ ፍልስፍና የተመራ ነው። መከላከያችን ዛሬ የጦርነት ጋሻችን ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የልማት አቅም፣ የሰላም ኢንጂን እና የሽግግሩ ዘመን ታማኝ ዋልታ ነው።
ሠራዊቱ የፈጠረው ቴክኖሎጂያዊ እና ሳይንሳዊ ብቃት ለሀገር የልማት ጉዞ፣ ለመሠረተ ልማት ደኅንነት እና ለኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነታችን ጥበቃ ትልቅ ትሩፋት እያበረከተ ይገኛል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የነገዋን፣ በለጽጋና ተከብራ የምትኖረውን ጠንካራ ኢትዮጵያ እውን የሚያደርግ የኩራታችን ምንጭ ነው።
ኢትዮጵያ የቱንም ያህል ውጫዊና ውስጣዊ ፈተና ቢገጥማት፣ ይህ በቴክኖሎጂ የረቀቀ፣ በሳይንስ የላቀ፣ ጦርነትን አስቀድሞ በማምከን ዘላቂ ሰላምን የሚያጸና አሸናፊ ኃይል እስካላት ድረስ፣ የማትበገር የነጻነት አምባ ሆና ለዘላለም ትቀጥላለች! ክብራችን፣ ጋሻችን፣ እና የዘመኑ የቴክኖሎጂ ምሽጋችን ለሆነው ጀግናው ሠራዊታችን ማለቂያ የሌለው ክብር ይገባል!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #endf #sovereignty #militarycapability
12 days ago
አማራጭ የሌለው ዘላቂ የመፍትሔ መንገድ
ኢትዮጵያ የረጅም ዘመናት ታሪክን፣ አያሌ የዳበሩ እሴቶችን፣ የባህል ብዝሃነትን እና የተፈጥሮ ጸጋዎችን አቅፋ የያዘች ሀገር ናት።
ሆኖም ላለፉት አስርት ዓመታት ፖለቲካዊ፣ ብሔራዊ እና አስተዳደራዊ አለመግባባቶች ምክንያት ያደረጉ ከፍተኛ ፈተናዎች ሲያጋጥሟት ቆይተዋል።
በእነዚህ ሀገራዊ ተግዳሮቶች ምክንያት የተከሰቱ ግጭቶች ደግሞ የበርካታ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት ደርሷል፤ የህዝቦች አብሮ የመኖር እሴትም ተፈትኗል።
ለችግሮቹ መፍትሔ ለመሻት በሚደረገው ጥረት ለሀገር የትኛው መንገድ ይበጃል የሚለው ጥያቄ የብዙዎች የሁልጊዜ ጥያቄ ነው።
በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ልዩነቶችንና ቅሬታዎችን በኃይልና በመሳሪያ አማራጭ ለመፍታት የተሄደባቸው መንገዶች ሁሉ ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት አለመቻላቸውን ታሪክ ይመሰክራል።
ኃይልን ወይም የመሳሪያ አማራጭን መጠቀም የሰብአዊና ቁሳዊ ሀብት ውድመት፣ የበቀልና የጽንፈኝነት ዑደት፣ የዴሞክራሲ ባህል መሸርሸር፣ ምጣኔ ሀብታዊ መዛባት እና የመሳሰሉትን ዋና ዋና ጉዳቶች ያስከትላል፡፡
ስለሆነም፣ ኃይልን እንደ መፍትሔ አማራጭ መውሰድ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና ዴሞክራሲ ለማምጣት ፍጹም የማይበጅና ሀገርን ወደባሰ ውድመት ያስገባል።
በኢትዮጵያ ከሳምንት በፊት የተጀመረውና እስከ አሁንም ድረስ በመካሄድ ላይ ያለው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ፣ ሀገራችንን ካለችበት ውስብስብ ችግር ለማውጣትና ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተዘጋጀ ታሪካዊ ዕድል ነው።
ምክክሩ ለዘላቂ ሰላም መሠረት በመጣል፣ ለብሔራዊ መግባባትና አንድነት ግንባታ፣ ለልማትና ምጣኔ ሀብት ዕድገት መንገድ በመክፈት እንዲሁም የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በማጠናከር ረገድ የጎላ ፋይዳ አለው።
የምክክር ባህል የዴሞክራሲ ዋና አምድ በመሆኑ ተቃራኒ ሃሳቦችን ማዳመጥ፣ መከባበርና በውይይት መፍትሔ መፈለግ ሲለመድ ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ተቋማት ለመፍጠር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፤ የሕግ የበላይነትም ለማስፈን ከፍ ያለ ሚና ይጫወታል።
ስለሆነም ሀገራችን ካለችበት ውስብስብ የታሪክ ምዕራፍ አኳያ፣ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ የጀመረው አካታች የሀገራዊ ምክክር ሂደት እጅግ ወሳኝ እና አማራጭ የሌለው የመፍትሔ መንገድ ነው።
በሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ የተፋጠነ ልማትና እውነተኛ ዴሞክራሲ እውን ማድረግ የሚቻለው በአሁኑ ወቅት የተጀመረውን ሀገራዊ ምክክር በቅንነት፣ በቁርጠኝነት እና በሙሉ አቅም መደገፍና በመተግበር ይገባል።
ለስኬቱ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን፣ ተቋማት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና የሚዲያ አካላት በትብብር መስራት አለባቸው።
በአመለወርቅ ደምሰው
ኢትዮጵያ የረጅም ዘመናት ታሪክን፣ አያሌ የዳበሩ እሴቶችን፣ የባህል ብዝሃነትን እና የተፈጥሮ ጸጋዎችን አቅፋ የያዘች ሀገር ናት።
ሆኖም ላለፉት አስርት ዓመታት ፖለቲካዊ፣ ብሔራዊ እና አስተዳደራዊ አለመግባባቶች ምክንያት ያደረጉ ከፍተኛ ፈተናዎች ሲያጋጥሟት ቆይተዋል።
በእነዚህ ሀገራዊ ተግዳሮቶች ምክንያት የተከሰቱ ግጭቶች ደግሞ የበርካታ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት ደርሷል፤ የህዝቦች አብሮ የመኖር እሴትም ተፈትኗል።
ለችግሮቹ መፍትሔ ለመሻት በሚደረገው ጥረት ለሀገር የትኛው መንገድ ይበጃል የሚለው ጥያቄ የብዙዎች የሁልጊዜ ጥያቄ ነው።
በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ልዩነቶችንና ቅሬታዎችን በኃይልና በመሳሪያ አማራጭ ለመፍታት የተሄደባቸው መንገዶች ሁሉ ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት አለመቻላቸውን ታሪክ ይመሰክራል።
ኃይልን ወይም የመሳሪያ አማራጭን መጠቀም የሰብአዊና ቁሳዊ ሀብት ውድመት፣ የበቀልና የጽንፈኝነት ዑደት፣ የዴሞክራሲ ባህል መሸርሸር፣ ምጣኔ ሀብታዊ መዛባት እና የመሳሰሉትን ዋና ዋና ጉዳቶች ያስከትላል፡፡
ስለሆነም፣ ኃይልን እንደ መፍትሔ አማራጭ መውሰድ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና ዴሞክራሲ ለማምጣት ፍጹም የማይበጅና ሀገርን ወደባሰ ውድመት ያስገባል።
በኢትዮጵያ ከሳምንት በፊት የተጀመረውና እስከ አሁንም ድረስ በመካሄድ ላይ ያለው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ፣ ሀገራችንን ካለችበት ውስብስብ ችግር ለማውጣትና ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተዘጋጀ ታሪካዊ ዕድል ነው።
ምክክሩ ለዘላቂ ሰላም መሠረት በመጣል፣ ለብሔራዊ መግባባትና አንድነት ግንባታ፣ ለልማትና ምጣኔ ሀብት ዕድገት መንገድ በመክፈት እንዲሁም የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በማጠናከር ረገድ የጎላ ፋይዳ አለው።
የምክክር ባህል የዴሞክራሲ ዋና አምድ በመሆኑ ተቃራኒ ሃሳቦችን ማዳመጥ፣ መከባበርና በውይይት መፍትሔ መፈለግ ሲለመድ ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ተቋማት ለመፍጠር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፤ የሕግ የበላይነትም ለማስፈን ከፍ ያለ ሚና ይጫወታል።
ስለሆነም ሀገራችን ካለችበት ውስብስብ የታሪክ ምዕራፍ አኳያ፣ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ የጀመረው አካታች የሀገራዊ ምክክር ሂደት እጅግ ወሳኝ እና አማራጭ የሌለው የመፍትሔ መንገድ ነው።
በሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ የተፋጠነ ልማትና እውነተኛ ዴሞክራሲ እውን ማድረግ የሚቻለው በአሁኑ ወቅት የተጀመረውን ሀገራዊ ምክክር በቅንነት፣ በቁርጠኝነት እና በሙሉ አቅም መደገፍና በመተግበር ይገባል።
ለስኬቱ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን፣ ተቋማት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና የሚዲያ አካላት በትብብር መስራት አለባቸው።
በአመለወርቅ ደምሰው
12 days ago
በአንድ ጥያቄ ውስጥ የተደበቀው የኢትዮጵያ የአብሮነት ፍልስፍና
**********************
"እንዴት ሰንብታችኋል?" የሚለው ለኢትዮጵያውያን ከሰላምታ በላይ ትርጉም ያለው ቃል ነው። በዚህ ጥያቄ ውስጥ "ደህና ነህ?" የሚል ብቻ ሳይሆን፣ "ምን አጋጠመህ? እንዴት አለፍክ? ምን ልረዳህ?" የሚል የመተሳሰብ፣ የመደማመጥ እና የአብሮነት መንፈስ ተደብቆ ይገኛል።
በኢትዮጵያ ማኅበራዊ እሴት ውስጥ ጥያቄ ማለት መረጃ መፈለግ ብቻ አይደለም። ሰውን ማስታወስ፣ ሁኔታውን መረዳት፣ ችግሩን መስማት እና አብሮ መፍትሔ መፈለግም ጭምር ነው። ይህም የማኅበረሰባችንን የአብሮነት መሠረት ያንጸባርቃል።
እንዲሁ የሀገር ጉዳዮችም በአንድ ወገን ውሳኔ ሳይሆን፣ እርስ በርስ በመጠያየቅ፣ በመደማመጥ፣ በመከባበር እና በጋራ መፍትሔ በመፈለግ ዘላቂ መልስ ያገኛሉ። ስለዚህ የምክክር መንፈስ በውይይት አዳራሾች ብቻ የሚወለድ ሳይሆን፣ በየቤታችን፣ በየመንደራችንና በየዕለቱ በምንለው "እንዴት ሰንብታችኋል?" ውስጥ ለዘመናት ሲኖር የቆየ ማኅበራዊ እሴት ነው።
ከሐምሌ 8 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መድረክም ይህ የመደማመጥ መንፈስ በሰፊው ታይቷል። ከተለያዩ ክልሎች፣ ማኅበረሰቦች እና ሙያዎች የመጡ ተመካካሪዎች ሐሳባቸውን በመግለጽና ሌሎችን በማዳመጥ የጋራ መፍትሔ የሚፈለግበት መድረክ መፍጠር ተችሏል።
በዚሁም የሀገራዊ ምክክር መንፈስ ለኢትዮጵያ እንግዳ የሆነ አዲስ ሐሳብ ሳይሆን፣ በማኅበራዊ ባህላችን ውስጥ ለዘመናት የቆየ የመደማመጥና የመተሳሰብ እሴት ዘመናዊ መገለጫ ነው።
ይህ የተጻፈ ሕግ አልነበረም፤ ግን ከብዙ ሕጎች በላይ ሰዎችን ያስተሳሰረ የማኅበረሰብ ሥርዓት ነበር። የኢትዮጵያ ባህል ከሽማግሌ ሥርዓት እስከ ዕርቅ፣ ከጎረቤት መተጋገዝ እስከ ቤተሰብ ውይይት መጀመሪያ መጠየቅን፣ ማዳመጥን እና መረዳዳትን ያስቀድማል።
ዛሬም ኢትዮጵያ የምትፈልገው ይህንኑ መንፈስ ነው። መጀመሪያ መጠየቅ፣ ከዚያ ማዳመጥ፣ ከዚያ መረዳት፣ በመጨረሻም አብሮ መፍትሔ መፈለግ ለሀገር እድገት በአንድ ላይ መቆምን ያረጋግጣል።
የአንድ ሕዝብ የመተሳሰብና የመደማመጥ መጀመሪያ የሆነው የአብሮነት መሠረት ከተለያዩ የሐሳብ ልዩነቶች የሚመጣ ምክክር ነው።
ከሁሉም በላይ ደግሞ በኢትዮጵያውያን ዕለታዊ ሕይወት ውስጥ ለዘመናት የተገነባ የመተሳሰብና የምክክር ባህል ምልክት ነው።
ከብዙ ሺህ ቃላት በፊት አንድ ጥያቄ ነበር። ‘እንዴት ሰንብታችኋል?' የሚለው ጥያቄ! የኢትዮጵያውያንን የመተሳሰብ እና የመደማመጥ ባህልን በሚያሳይ አንድ ምሳሌ ነው።
በልዩ እሸቱ
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogue #culturalvalue #nationbuilding
**********************
"እንዴት ሰንብታችኋል?" የሚለው ለኢትዮጵያውያን ከሰላምታ በላይ ትርጉም ያለው ቃል ነው። በዚህ ጥያቄ ውስጥ "ደህና ነህ?" የሚል ብቻ ሳይሆን፣ "ምን አጋጠመህ? እንዴት አለፍክ? ምን ልረዳህ?" የሚል የመተሳሰብ፣ የመደማመጥ እና የአብሮነት መንፈስ ተደብቆ ይገኛል።
በኢትዮጵያ ማኅበራዊ እሴት ውስጥ ጥያቄ ማለት መረጃ መፈለግ ብቻ አይደለም። ሰውን ማስታወስ፣ ሁኔታውን መረዳት፣ ችግሩን መስማት እና አብሮ መፍትሔ መፈለግም ጭምር ነው። ይህም የማኅበረሰባችንን የአብሮነት መሠረት ያንጸባርቃል።
እንዲሁ የሀገር ጉዳዮችም በአንድ ወገን ውሳኔ ሳይሆን፣ እርስ በርስ በመጠያየቅ፣ በመደማመጥ፣ በመከባበር እና በጋራ መፍትሔ በመፈለግ ዘላቂ መልስ ያገኛሉ። ስለዚህ የምክክር መንፈስ በውይይት አዳራሾች ብቻ የሚወለድ ሳይሆን፣ በየቤታችን፣ በየመንደራችንና በየዕለቱ በምንለው "እንዴት ሰንብታችኋል?" ውስጥ ለዘመናት ሲኖር የቆየ ማኅበራዊ እሴት ነው።
ከሐምሌ 8 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መድረክም ይህ የመደማመጥ መንፈስ በሰፊው ታይቷል። ከተለያዩ ክልሎች፣ ማኅበረሰቦች እና ሙያዎች የመጡ ተመካካሪዎች ሐሳባቸውን በመግለጽና ሌሎችን በማዳመጥ የጋራ መፍትሔ የሚፈለግበት መድረክ መፍጠር ተችሏል።
በዚሁም የሀገራዊ ምክክር መንፈስ ለኢትዮጵያ እንግዳ የሆነ አዲስ ሐሳብ ሳይሆን፣ በማኅበራዊ ባህላችን ውስጥ ለዘመናት የቆየ የመደማመጥና የመተሳሰብ እሴት ዘመናዊ መገለጫ ነው።
ይህ የተጻፈ ሕግ አልነበረም፤ ግን ከብዙ ሕጎች በላይ ሰዎችን ያስተሳሰረ የማኅበረሰብ ሥርዓት ነበር። የኢትዮጵያ ባህል ከሽማግሌ ሥርዓት እስከ ዕርቅ፣ ከጎረቤት መተጋገዝ እስከ ቤተሰብ ውይይት መጀመሪያ መጠየቅን፣ ማዳመጥን እና መረዳዳትን ያስቀድማል።
ዛሬም ኢትዮጵያ የምትፈልገው ይህንኑ መንፈስ ነው። መጀመሪያ መጠየቅ፣ ከዚያ ማዳመጥ፣ ከዚያ መረዳት፣ በመጨረሻም አብሮ መፍትሔ መፈለግ ለሀገር እድገት በአንድ ላይ መቆምን ያረጋግጣል።
የአንድ ሕዝብ የመተሳሰብና የመደማመጥ መጀመሪያ የሆነው የአብሮነት መሠረት ከተለያዩ የሐሳብ ልዩነቶች የሚመጣ ምክክር ነው።
ከሁሉም በላይ ደግሞ በኢትዮጵያውያን ዕለታዊ ሕይወት ውስጥ ለዘመናት የተገነባ የመተሳሰብና የምክክር ባህል ምልክት ነው።
ከብዙ ሺህ ቃላት በፊት አንድ ጥያቄ ነበር። ‘እንዴት ሰንብታችኋል?' የሚለው ጥያቄ! የኢትዮጵያውያንን የመተሳሰብ እና የመደማመጥ ባህልን በሚያሳይ አንድ ምሳሌ ነው።
በልዩ እሸቱ
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogue #culturalvalue #nationbuilding
12 days ago
🏢አንድ ሕንፃ የሚታየው በውጫዊ ቅርጹ ብቻ አይደለም፤ ከጀርባው ያሉ ታላላቅ ራዕዮች፣ የተወሰዱ ውሳኔዎች፣ የተከፈሉ መስዋዕቶች እና ለዓመታት የተደረገ ትጋት ጭምር ነው።
ከኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹ ዘመናዊ የግንባታ ታሪኮች ጀምሮ እስከ ዛሬ የከተሞቻችንን ገጽታ የቀየሩ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ድረስ፤ ሕልምን ወደ እውነት የቀየሩ፣ የመኖሪያ ምቾት የፈጠሩ እና ለሀገር እድገት አሻራቸውን ያሳረፉ አልሚ ድርጅቶች ክብር ይገባቸዋል።
እነዚህ ታሪኮች መታወስ አለባቸው፤ እነዚህ ስኬቶች በሀገራዊ መድረክ መመስከር ይገባቸዋል።
🏆 2ኛው ኢትዮ ሪል እስቴት አዋርድ
በሪል እስቴት ዘርፍ ላይ በትጋት፣ በፈጠራ እና በልዩ አስተዋጽኦ የሚሰሩ ተቋማትን በሚያከብር ታላቅ ሀገራዊ መድረክ ተመልሷል።
የማህበረሰብንና ሀገርን ፍላጎት ያሟላችሁ ቤት አልሚዎች ድርጅትዎን በዚህ ታላቅ ሀገራዊ እውቅና ላይ ያሳትፉ።
ለተጨማሪ መረጃና የተሳትፎ ሁኔታዎች፦
📞 በ09 11-62-88-59 ሀሎ ይበሉን።
2ኛው ኢትዮ ሪል እስቴት አዋርድ
የማይዝሉ ክንዶች ከፍ ከፍ ይላሉ!!
ከኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹ ዘመናዊ የግንባታ ታሪኮች ጀምሮ እስከ ዛሬ የከተሞቻችንን ገጽታ የቀየሩ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ድረስ፤ ሕልምን ወደ እውነት የቀየሩ፣ የመኖሪያ ምቾት የፈጠሩ እና ለሀገር እድገት አሻራቸውን ያሳረፉ አልሚ ድርጅቶች ክብር ይገባቸዋል።
እነዚህ ታሪኮች መታወስ አለባቸው፤ እነዚህ ስኬቶች በሀገራዊ መድረክ መመስከር ይገባቸዋል።
🏆 2ኛው ኢትዮ ሪል እስቴት አዋርድ
በሪል እስቴት ዘርፍ ላይ በትጋት፣ በፈጠራ እና በልዩ አስተዋጽኦ የሚሰሩ ተቋማትን በሚያከብር ታላቅ ሀገራዊ መድረክ ተመልሷል።
የማህበረሰብንና ሀገርን ፍላጎት ያሟላችሁ ቤት አልሚዎች ድርጅትዎን በዚህ ታላቅ ሀገራዊ እውቅና ላይ ያሳትፉ።
ለተጨማሪ መረጃና የተሳትፎ ሁኔታዎች፦
📞 በ09 11-62-88-59 ሀሎ ይበሉን።
2ኛው ኢትዮ ሪል እስቴት አዋርድ
የማይዝሉ ክንዶች ከፍ ከፍ ይላሉ!!
Sponsored by
Surafel
12 days ago
ኩባንያችን የኢትዮጵያን የዲጂታልና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን በግንባር ቀደምትነት እየመራ፣ ለሀገር ግንባታና ለዜጎች ሁለንተናዊ እድገት የሚያደርገውን የማይተካ አገራዊ አስተዋፅኦ በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት በ2018 በጀት ዓመት ብቻ 73.5 ቢሊዮን ብር ታክስ ገቢ በማድረግ የሀገር ግንባታ ምሰሶነቱን ያስመሰከረ ሲሆን፣ ይህም ተቋማችን ያስገባቸውን አጠቃላይ የታክስ መጠን ወደ 244.5 ቢሊዮን ብር አድርሶታል። ኩባንያችን ከዚህ ቀደምም ለተከታታይ አምስት ዓመታት የሀገራችን ግንባር ቀደም የ"ፕላቲኒየም ግብር ከፋይና ልዩ" ሽልማት ባለቤት መሆኑ ይታወሳል።
ከቀዳሚ ግብር ከፋይነቱ በተጨማሪ፣ ተቋማችን ከውድ ደንበኞቹ ጋር በመተባበር 2.4 ቢሊዮን ብር ለብሔራዊ አደጋ ማገገሚያ ፈንድ በማሰባሰብ፣ በችግር ጊዜ ለወገን አለኝታነቱን በተግባር ዳግመኛ አስመስክሯል፤ ለ44,757 ዜጎች ቀጥተኛ የቋሚና የኮንትራት ሥራ ዕድል በመፍጠር ዜጎችን ኑሮ መደገፍ ችሏል።
ከዚህም ባለፈ ኩባንያችን 519,810 የምርትና አገልግሎት አከፋፋዮችንና የቴሌብር ወኪሎችን፣ 2,205 የሀገር ውስጥ አቅራቢዎችን፣ 1,213 የተጨማሪ እሴት አገልግሎት (VAS) አጋሮችን፣ 138 የፍራንቻይዝ አጋሮችን እና 693 ዓለም አቀፍ አጋሮችን በማቀፍ ከ2 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድልና የገቢ ምንጭ የሚፈጥር ግዙፍ የኢኮኖሚ ሥነ-ምህዳር መገንባት ችሏል።
ኩባንያችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ፈጠራን ከማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ጋር በማቀናጀት፣ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ የማፋጠን፣ የሥራ ዕድል የመፍጠር እና የቀዳሚ ግብር ከፋይነት አገራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ መወጣቱን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ለተጨማሪ፡ https://bit.ly/45k6Gjw
በዚሁ መሠረት በ2018 በጀት ዓመት ብቻ 73.5 ቢሊዮን ብር ታክስ ገቢ በማድረግ የሀገር ግንባታ ምሰሶነቱን ያስመሰከረ ሲሆን፣ ይህም ተቋማችን ያስገባቸውን አጠቃላይ የታክስ መጠን ወደ 244.5 ቢሊዮን ብር አድርሶታል። ኩባንያችን ከዚህ ቀደምም ለተከታታይ አምስት ዓመታት የሀገራችን ግንባር ቀደም የ"ፕላቲኒየም ግብር ከፋይና ልዩ" ሽልማት ባለቤት መሆኑ ይታወሳል።
ከቀዳሚ ግብር ከፋይነቱ በተጨማሪ፣ ተቋማችን ከውድ ደንበኞቹ ጋር በመተባበር 2.4 ቢሊዮን ብር ለብሔራዊ አደጋ ማገገሚያ ፈንድ በማሰባሰብ፣ በችግር ጊዜ ለወገን አለኝታነቱን በተግባር ዳግመኛ አስመስክሯል፤ ለ44,757 ዜጎች ቀጥተኛ የቋሚና የኮንትራት ሥራ ዕድል በመፍጠር ዜጎችን ኑሮ መደገፍ ችሏል።
ከዚህም ባለፈ ኩባንያችን 519,810 የምርትና አገልግሎት አከፋፋዮችንና የቴሌብር ወኪሎችን፣ 2,205 የሀገር ውስጥ አቅራቢዎችን፣ 1,213 የተጨማሪ እሴት አገልግሎት (VAS) አጋሮችን፣ 138 የፍራንቻይዝ አጋሮችን እና 693 ዓለም አቀፍ አጋሮችን በማቀፍ ከ2 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድልና የገቢ ምንጭ የሚፈጥር ግዙፍ የኢኮኖሚ ሥነ-ምህዳር መገንባት ችሏል።
ኩባንያችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ፈጠራን ከማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ጋር በማቀናጀት፣ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ የማፋጠን፣ የሥራ ዕድል የመፍጠር እና የቀዳሚ ግብር ከፋይነት አገራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ መወጣቱን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ለተጨማሪ፡ https://bit.ly/45k6Gjw
13 days ago
“በጋና አክራ ከተማ የሚገኘውን ታሪካዊውን የክዋሜ ንክሩማህ መታሰቢያ ፓርክን ጎብኝተናል” - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
*********************
“በጋና አክራ ከተማ የሚገኘውን ታሪካዊውን የክዋሜ ንክሩማህ መታሰቢያ ፓርክን ጎብኝተናል፤ በሐውልታቸው ሥርም የአበባ ጉንጉን አኑረናል” ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ስፍራው የጋና የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት እና የፓን-አፍሪካኒዝም አቀንቃኝ የዶክተር ክዋሜ ንክሩማህ እንዲሁም የባለቤታቸው የፋቲያ ንክሩማህ መካነ መቃብርና ታሪካዊ ሙዚየምን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል።
ጋናውያን ለአፍሪካ ነፃነትና አንድነት አቀንቃኙ መሪያቸው ግዙፍ ሐውልት መታሰቢያ መገንባታቸው የቀደሙትን ማክበር ለትውልድና ለሀገር ግንባታ ያለውን ሚና ያሳያል ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባጋሩት መልዕክት።
ዶ/ር ክዋሜ ንክሩማህ ለጋና ነፃነት ብቻ ሳይሆን፣ ሙሉ አፍሪካ ከቅኝ ግዛት ነፃ እንድትወጣ የነበራቸው ራዕይ ዛሬም ድረስ ለትውልዱ ትልቅ የብርታት ምንጭ ነውም ብለዋል።
በተለይም ከኢትዮጵያ ጋር የነበራቸው ጥብቅ ወዳጅነት እና ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ አፍሪካ ኅብረት) መመስረት ያበረከቱት አስተዋጽኦ ሁልጊዜም በክብር የሚታወስ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
*********************
“በጋና አክራ ከተማ የሚገኘውን ታሪካዊውን የክዋሜ ንክሩማህ መታሰቢያ ፓርክን ጎብኝተናል፤ በሐውልታቸው ሥርም የአበባ ጉንጉን አኑረናል” ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ስፍራው የጋና የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት እና የፓን-አፍሪካኒዝም አቀንቃኝ የዶክተር ክዋሜ ንክሩማህ እንዲሁም የባለቤታቸው የፋቲያ ንክሩማህ መካነ መቃብርና ታሪካዊ ሙዚየምን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል።
ጋናውያን ለአፍሪካ ነፃነትና አንድነት አቀንቃኙ መሪያቸው ግዙፍ ሐውልት መታሰቢያ መገንባታቸው የቀደሙትን ማክበር ለትውልድና ለሀገር ግንባታ ያለውን ሚና ያሳያል ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባጋሩት መልዕክት።
ዶ/ር ክዋሜ ንክሩማህ ለጋና ነፃነት ብቻ ሳይሆን፣ ሙሉ አፍሪካ ከቅኝ ግዛት ነፃ እንድትወጣ የነበራቸው ራዕይ ዛሬም ድረስ ለትውልዱ ትልቅ የብርታት ምንጭ ነውም ብለዋል።
በተለይም ከኢትዮጵያ ጋር የነበራቸው ጥብቅ ወዳጅነት እና ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ አፍሪካ ኅብረት) መመስረት ያበረከቱት አስተዋጽኦ ሁልጊዜም በክብር የሚታወስ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
13 days ago
"ዘርፉ ሙሉ በሙሉ የህዝብ አመኔታ እንዲያገኝ ነው የምንሰራው"
#ethiopia | በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ዘርፍ የህዝብን አመኔታ በመገንባት፣ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ኢንቨስተሮች ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ ሁለት ስትራቴጂያዊ የመግባቢያ ሰነዶች ዛሬ በይፋ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር (EREDA) እና ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ሲሆኑ፣ ትብብሩ በዘርፉ የተከማቹ የፖሊሲ፣ የፋይናንስ፣ የኢንቨስትመንት እና የትስስር ክፍተቶችን በመቅረፍ ዘርፉን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚያግዝ ተገልጿል።
በስምምነቱ መሠረት የሪል ስቴት አልሚዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የፖሊሲ አውጪዎችና የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች በአንድ መድረክ በማገናኘት እስካሁን በዘርፉ የታየውን የተቆራረጠ የሥራ አሰራር ለማስቀረት ይሰራል።
እንደ መነሻ ሁለቱ ተቋማት በቅርቡ በሚካሄዱ ዓመታዊ የሪል ስቴት ጉባኤዎችና የኤክስፖ መድረኮች ላይ በጋራ በመሳተፍ የኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማጠናከር ተስማምተዋል።
ተቋማቱ በጋራ ባወጡት መግለጫ፣ ትብብሩ በግልጽ የኃላፊነት ክፍፍል፣ የሥራ ጊዜ ሰሌዳ እና የሚጠበቁ ውጤቶች ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ዘርፉን በሳይንሳዊና በተጠያቂነት መርህ ለመምራት ያግዛል ብለዋል።
በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ሚካኤል ጆርጅ፣ "ዘርፉ ሙሉ በሙሉ የህዝብ አመኔታ እንዲያገኝ ነው የምንሰራው" ሲሉ ገልጸዋል። እንደ እሳቸው ገለጻ፣ ሙያዊ መመዘኛዎችን ማስከበር፣ ግልጽነትን ማጠናከር እና የባለድርሻ አካላትን ትብብር ማሳደግ የማህበሩ ዋና ትኩረቶች ናቸው።
ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ በበኩሉ ዓለም አቀፍ ኢንቨስተሮችን በመሳብ፣ አዳዲስ የንግድ ትስስሮችን በመፍጠር እና የኢትዮጵያን የሪል ስቴት ዘርፍ ከአህጉራዊ ገበያ ጋር በማስተሳሰር የድርሻውን እንደሚወጣ ተገልጿል።
ተፈራራሚዎቹ እንደገለጹት፣ ይህ ስምምነት በዘርፉ የሚታዩትን የመሠረተ ልማት፣ የፋይናንስ አቅርቦትና የኢንቨስትመንት ችግሮች ለመቅረፍ ወሳኝ መሠረት እንደሚሆን እና የኢትዮጵያን የቤት ልማት ከአህጉራዊና ከዓለም አቀፍ የንግድ ትስስሮች ጋር ለማቀናጀት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
ፎቶ፦ ከበደ መክብብ
#ethiopia #getutemesgen #getunews
#ethiopia | በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ዘርፍ የህዝብን አመኔታ በመገንባት፣ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ኢንቨስተሮች ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ ሁለት ስትራቴጂያዊ የመግባቢያ ሰነዶች ዛሬ በይፋ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር (EREDA) እና ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ሲሆኑ፣ ትብብሩ በዘርፉ የተከማቹ የፖሊሲ፣ የፋይናንስ፣ የኢንቨስትመንት እና የትስስር ክፍተቶችን በመቅረፍ ዘርፉን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚያግዝ ተገልጿል።
በስምምነቱ መሠረት የሪል ስቴት አልሚዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የፖሊሲ አውጪዎችና የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች በአንድ መድረክ በማገናኘት እስካሁን በዘርፉ የታየውን የተቆራረጠ የሥራ አሰራር ለማስቀረት ይሰራል።
እንደ መነሻ ሁለቱ ተቋማት በቅርቡ በሚካሄዱ ዓመታዊ የሪል ስቴት ጉባኤዎችና የኤክስፖ መድረኮች ላይ በጋራ በመሳተፍ የኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማጠናከር ተስማምተዋል።
ተቋማቱ በጋራ ባወጡት መግለጫ፣ ትብብሩ በግልጽ የኃላፊነት ክፍፍል፣ የሥራ ጊዜ ሰሌዳ እና የሚጠበቁ ውጤቶች ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ዘርፉን በሳይንሳዊና በተጠያቂነት መርህ ለመምራት ያግዛል ብለዋል።
በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ሚካኤል ጆርጅ፣ "ዘርፉ ሙሉ በሙሉ የህዝብ አመኔታ እንዲያገኝ ነው የምንሰራው" ሲሉ ገልጸዋል። እንደ እሳቸው ገለጻ፣ ሙያዊ መመዘኛዎችን ማስከበር፣ ግልጽነትን ማጠናከር እና የባለድርሻ አካላትን ትብብር ማሳደግ የማህበሩ ዋና ትኩረቶች ናቸው።
ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ በበኩሉ ዓለም አቀፍ ኢንቨስተሮችን በመሳብ፣ አዳዲስ የንግድ ትስስሮችን በመፍጠር እና የኢትዮጵያን የሪል ስቴት ዘርፍ ከአህጉራዊ ገበያ ጋር በማስተሳሰር የድርሻውን እንደሚወጣ ተገልጿል።
ተፈራራሚዎቹ እንደገለጹት፣ ይህ ስምምነት በዘርፉ የሚታዩትን የመሠረተ ልማት፣ የፋይናንስ አቅርቦትና የኢንቨስትመንት ችግሮች ለመቅረፍ ወሳኝ መሠረት እንደሚሆን እና የኢትዮጵያን የቤት ልማት ከአህጉራዊና ከዓለም አቀፍ የንግድ ትስስሮች ጋር ለማቀናጀት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
ፎቶ፦ ከበደ መክብብ
#ethiopia #getutemesgen #getunews
14 days ago
ከምርታማነት እስከ ሥራ ፈጠራ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ተዝቆ የማያልቅ የተፈጥሮ ጸጋን ታድላለች፡፡ ለግብርና የሚስማማ ዓየር ንብረት፣ ዓመቱን ሙሉ የሚፈስሱ ወንዞች፣ ሊታረስ የሚችል ሰፊ ለም መሬት እንዲሁም ለእንስሳት እርባታ የሚስማማ አየር ሁኔታ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በተለይም ለምግብነት የሚውሉ የእንስሳትና የእጽዋት ሀብቶቿ በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጠቃሽ አድርጓታል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ማክሮ ኢኮኖሚዋን ለማረጋጋት እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በርካታ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ቀርጻ ስትተገብር ቆይታለች፡፡
በመደመር መንግሥት ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው እንደ አረንጓዴ አሻራ፣ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና የግብርና ሜካናይዜሽን፣ የሌማት ትሩፋት፣ ገበታ ለሀገር፣ የ5 ሚሊየን ኮደርስ እና የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የሌማት ትሩፋቱ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር የስራ እድል ፈጠራን ያበረታታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከወጪ ንግድ የሚገኝ ገቢን የሚያሳድግ እና ከውጭ የምናስገባቸውን የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ይተካል።
ለእንስሳት ተዋጽኦ ምርት እና ምርታማነት እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት ደግሞ በዘመናዊ መንገድ የተደራጁ የወተት ላሞች ማዕከላትን በመፍጠር የነፍስ ወከፍ የወተት አቅርቦትን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጓል።
በተለያዩ አካባቢዎችም ወተት አምራች አርሶ አደሮች በማህበር በመደራጀት እና ምርታቸውን የሚሸጡበት የገበያ ትስስርን በመፍጠር ተጠቃሚነታቸውን አረጋግጠዋል። ይህም ቀደም ሲል ይስተዋል የነበረውን የወተት ምርት አቅርቦት እጥረት ለመፍታት ያስቻለ ውጤት አምጥቷል።
በመሆኑም መርሐ ግብሩ መተግበር ከጀመረ ወዲህ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የተመጣጠነ የምግብ ስርዓት እንዲኖር እያደረገ ነው፡፡
የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል እና የድህነት ቅነሳ ስትራቴጂዋን ለማገዝ የያዘችው ትክክለኛ እና ስኬታማ መንገድ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ ባለፉት ዓመታት የተሰሩ ስራዎች በራስ አቅም መለወጥ እንደሚቻል ያሳዩ እና የዜጎችን አምራችነት ያረጋጋጡ ናቸው፡፡
እነዚህ ስኬቶች ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ ያስቀመጠችውን ግብ ለማፋጠን ትልቅ አቅም ይፈጥራሉ፡፡ በምግብም ራስን መቻል ከሀገር ሉዓላዊነትና ክብር ጋር ጥብቅ ቁርኝት አለው፡፡
በትዕግስት ግዛቸው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ተዝቆ የማያልቅ የተፈጥሮ ጸጋን ታድላለች፡፡ ለግብርና የሚስማማ ዓየር ንብረት፣ ዓመቱን ሙሉ የሚፈስሱ ወንዞች፣ ሊታረስ የሚችል ሰፊ ለም መሬት እንዲሁም ለእንስሳት እርባታ የሚስማማ አየር ሁኔታ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በተለይም ለምግብነት የሚውሉ የእንስሳትና የእጽዋት ሀብቶቿ በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጠቃሽ አድርጓታል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ማክሮ ኢኮኖሚዋን ለማረጋጋት እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በርካታ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ቀርጻ ስትተገብር ቆይታለች፡፡
በመደመር መንግሥት ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው እንደ አረንጓዴ አሻራ፣ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና የግብርና ሜካናይዜሽን፣ የሌማት ትሩፋት፣ ገበታ ለሀገር፣ የ5 ሚሊየን ኮደርስ እና የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የሌማት ትሩፋቱ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር የስራ እድል ፈጠራን ያበረታታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከወጪ ንግድ የሚገኝ ገቢን የሚያሳድግ እና ከውጭ የምናስገባቸውን የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ይተካል።
ለእንስሳት ተዋጽኦ ምርት እና ምርታማነት እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት ደግሞ በዘመናዊ መንገድ የተደራጁ የወተት ላሞች ማዕከላትን በመፍጠር የነፍስ ወከፍ የወተት አቅርቦትን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጓል።
በተለያዩ አካባቢዎችም ወተት አምራች አርሶ አደሮች በማህበር በመደራጀት እና ምርታቸውን የሚሸጡበት የገበያ ትስስርን በመፍጠር ተጠቃሚነታቸውን አረጋግጠዋል። ይህም ቀደም ሲል ይስተዋል የነበረውን የወተት ምርት አቅርቦት እጥረት ለመፍታት ያስቻለ ውጤት አምጥቷል።
በመሆኑም መርሐ ግብሩ መተግበር ከጀመረ ወዲህ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የተመጣጠነ የምግብ ስርዓት እንዲኖር እያደረገ ነው፡፡
የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል እና የድህነት ቅነሳ ስትራቴጂዋን ለማገዝ የያዘችው ትክክለኛ እና ስኬታማ መንገድ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ ባለፉት ዓመታት የተሰሩ ስራዎች በራስ አቅም መለወጥ እንደሚቻል ያሳዩ እና የዜጎችን አምራችነት ያረጋጋጡ ናቸው፡፡
እነዚህ ስኬቶች ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ ያስቀመጠችውን ግብ ለማፋጠን ትልቅ አቅም ይፈጥራሉ፡፡ በምግብም ራስን መቻል ከሀገር ሉዓላዊነትና ክብር ጋር ጥብቅ ቁርኝት አለው፡፡
በትዕግስት ግዛቸው
Sponsored by
Surafel
Comments