2 hours ago
ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል በዓመት ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ህክምና መስጠቱን ገለጸ
ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሰረተ በአጭር ጊዜ ወደውጭ ሀገር በሚወስዱ የህክምና ጥገኝነትን በመቀየር፣ በሀገር ውስጥ ዘመናዊ ህክምና መስጠት የሚያስችል አገልግሎት መዘርጋቱን አስታወቀ።
ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ሆስፒታሉ በመሥራቹና ባለራዕዩ ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ እየተመራ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለታካሚዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም በያዝነው 2018 ዓ.ም ብቻ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከ4 ሺ 500 በላይ የቀዶ ህክምናዎችን በማካሄድ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።
ሆስፒታሉ እነዚህን ሀገር በቀል አቅሞች በመገንባቱ ቀደም ሲል ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ይሄዱ የነበሩ ታካሚዎችን ቁጥር በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር የታካሚዎችን ችግር መቅረፍ ችሏል።
በመግለጫው ወቅት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የአጠቃላይ እና ደረት አካባቢ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ተባባሪ ኘሮፌሰር ስዩም ካሣ መርኔ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በኢንተርቬንሽናል ካርዲዮሎጂ መስክ ያለ ኦፕሬሽን በደም ስሮች በኩል በሚደረግ ህክምና ጨምሮ በአዋቂና በልጆች የልብ ሕክምና በአጠቃላይ ከ735 በላይ ታካሚዎችን መታደግ ችሏል። አክለውም ይህ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ ሌሊትና ቀን ሳይቋረጥ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከውጭ ሀገር በሚመጡ ጊዜያዊ ዘመቻዎች ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን አሰራር መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በመታገዝ ወደውጪ ሀገር የሚያስኬዱ በተለይ የልብ ሕክምናዎችን 90 በመቶ በሆስፒታሉ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።
እንደ ዶክተር ስዩም ገለጻ፣ ሆስፒታሉ በኒውሮሰርጀሪ፣ በኦፕን ካርዲያክ፣ በአጥንትና ስፓይን፣ በኩላሊት፣ በሳምባ፣ የአንጎል፣ የዳሌና የጉልበት ቅየራ እንዲሁም በሚኒማሊ ኢንቬሲቭ (ላፓሮስኮፒክና ቶራኮስኮፒክ) እና ከ46 በላይ ሰብስፔሻሊቲ ህክምና ዘርፎች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ የሬዲዮሎጂ ክፍሉም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የህክምና ምርመራ ጥራቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሆስፒታሉ የውስጥ ደዌና የአዋቂዎች ኢንተርቬንሽናል የልብ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ከፈለኝ ደጀኔ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከተሰሩት 321 የሕፃናት የልብ ህክምናዎች መከናወናቸውን ጠቁመው 90 የሚጠጋ ድንገተኛ የልብ ደምስር መዘጋት አደጋ ያጋጠማቸውና ታካሚዎች በ24 ሰዓት ድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ህይወታቸው መታደግ ተችላል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ ቁጥራቸው ከ90 በላይ የሚኾኑ የውጭ ሀገር ዜጎችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል።
የሆስፒታሉ የቺፍ ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፣ የአንገትና ጭንቅላት ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተር መለስ ገበየሁ እንደገለጹት ደግሞ፣ ተቋሙ ከንግድ ዓላማው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል። በሆስፒታሉ ባለቤትና ዋና ስራአስፈጻሚ አቶ ብርሃን ተድላ አማካይነት በተቋቋመው "Heart to Heart Children's Aid" የተሰኘ ፋውንዴሽን በኩል ትልቅ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ በመጨረሻም ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደሥራ መግባቱና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መድረስ የቻለው በተቋሙ መስራችና ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ የቅርብ ጠንካራ አመራርና ክትትል፣ በሰራተኞችና ባለሙያዎች ትጋት መኾኑን በመጥቀስ ምስጋና አቅርበዋል።
ሆስፒታሉ ለ 333 ጊዜያዊና ቋሚ ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲኾን ከእነዚህ መካከል 86 ያህሉ ሰብስፔሻስት ሐኪሞች መኾናቸው ተነግሯል።
ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሰረተ በአጭር ጊዜ ወደውጭ ሀገር በሚወስዱ የህክምና ጥገኝነትን በመቀየር፣ በሀገር ውስጥ ዘመናዊ ህክምና መስጠት የሚያስችል አገልግሎት መዘርጋቱን አስታወቀ።
ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ሆስፒታሉ በመሥራቹና ባለራዕዩ ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ እየተመራ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለታካሚዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም በያዝነው 2018 ዓ.ም ብቻ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከ4 ሺ 500 በላይ የቀዶ ህክምናዎችን በማካሄድ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።
ሆስፒታሉ እነዚህን ሀገር በቀል አቅሞች በመገንባቱ ቀደም ሲል ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ይሄዱ የነበሩ ታካሚዎችን ቁጥር በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር የታካሚዎችን ችግር መቅረፍ ችሏል።
በመግለጫው ወቅት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የአጠቃላይ እና ደረት አካባቢ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ተባባሪ ኘሮፌሰር ስዩም ካሣ መርኔ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በኢንተርቬንሽናል ካርዲዮሎጂ መስክ ያለ ኦፕሬሽን በደም ስሮች በኩል በሚደረግ ህክምና ጨምሮ በአዋቂና በልጆች የልብ ሕክምና በአጠቃላይ ከ735 በላይ ታካሚዎችን መታደግ ችሏል። አክለውም ይህ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ ሌሊትና ቀን ሳይቋረጥ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከውጭ ሀገር በሚመጡ ጊዜያዊ ዘመቻዎች ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን አሰራር መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በመታገዝ ወደውጪ ሀገር የሚያስኬዱ በተለይ የልብ ሕክምናዎችን 90 በመቶ በሆስፒታሉ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።
እንደ ዶክተር ስዩም ገለጻ፣ ሆስፒታሉ በኒውሮሰርጀሪ፣ በኦፕን ካርዲያክ፣ በአጥንትና ስፓይን፣ በኩላሊት፣ በሳምባ፣ የአንጎል፣ የዳሌና የጉልበት ቅየራ እንዲሁም በሚኒማሊ ኢንቬሲቭ (ላፓሮስኮፒክና ቶራኮስኮፒክ) እና ከ46 በላይ ሰብስፔሻሊቲ ህክምና ዘርፎች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ የሬዲዮሎጂ ክፍሉም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የህክምና ምርመራ ጥራቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሆስፒታሉ የውስጥ ደዌና የአዋቂዎች ኢንተርቬንሽናል የልብ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ከፈለኝ ደጀኔ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከተሰሩት 321 የሕፃናት የልብ ህክምናዎች መከናወናቸውን ጠቁመው 90 የሚጠጋ ድንገተኛ የልብ ደምስር መዘጋት አደጋ ያጋጠማቸውና ታካሚዎች በ24 ሰዓት ድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ህይወታቸው መታደግ ተችላል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ ቁጥራቸው ከ90 በላይ የሚኾኑ የውጭ ሀገር ዜጎችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል።
የሆስፒታሉ የቺፍ ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፣ የአንገትና ጭንቅላት ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተር መለስ ገበየሁ እንደገለጹት ደግሞ፣ ተቋሙ ከንግድ ዓላማው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል። በሆስፒታሉ ባለቤትና ዋና ስራአስፈጻሚ አቶ ብርሃን ተድላ አማካይነት በተቋቋመው "Heart to Heart Children's Aid" የተሰኘ ፋውንዴሽን በኩል ትልቅ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ በመጨረሻም ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደሥራ መግባቱና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መድረስ የቻለው በተቋሙ መስራችና ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ የቅርብ ጠንካራ አመራርና ክትትል፣ በሰራተኞችና ባለሙያዎች ትጋት መኾኑን በመጥቀስ ምስጋና አቅርበዋል።
ሆስፒታሉ ለ 333 ጊዜያዊና ቋሚ ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲኾን ከእነዚህ መካከል 86 ያህሉ ሰብስፔሻስት ሐኪሞች መኾናቸው ተነግሯል።
2 hours ago
የጨጓራ ህመም ተገቢዉን ህክምና ካላገኘ የምግብ መተላለፊያ ቱቦን በመዝጋት ለከፋ የጤና ችግር ሊያጋልጥ ይችላል ተባለ
የጨጓራ ህመምን በቤት ዉስጥ በተለያዩ መንገዶች ማከም አንዱ አማራጭ ቢሆንም ደረጃዉ ከፍ ሳይል ተገቢዉን የህክምና አገልግሎት ካላገኘ ለከፋ የጤና ችግር እንደሚያጋልጥ ተገልጿል።የጨጓራ ህመም ተገቢዉን የህክምና እርዳታ ካላገኘ እና ወደ መጨረሻዉ ደረጃ ከፍ ካለ ቁስለቱ እስከ መድማት ደርሶ ደም ማስመለስን ሊያስከትል ይችላል ።
የጨጓራ ቁስለት በከፍተኛ ደረጃ ተባብሶ የጨጓራ ግድግዳን ሙሉ በሙሉ በመብሳት ቀዳዳ በሚፈጥርበት ወቅት በሆድ ዕቃ ውስጥ ከባድ ኢንፌክሽንን ስለሚያስከትል አስቸኳይ የሕክምና እርዳታ ማግኘት ተገቢ ነዉ ተብሏል ።በተጨማሪም ጨጓራ ከትንሹ አንጀት ጋር የሚገናኝበት ቦታ ላይ በተደጋጋሚ ጉዳት ሲደርስበት ቦታዉ ይጠብና የምግብ መተላለፊያ ቱቦን በመዝጋት ለከፋ የጤና ችግር ስለሚያጋልጥ ተገቢዉን የህክምና እገዛ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የዉስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር አምደመስቀል መርሻ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል ።
የህክምና ባለሙያው አክለዉም በአንዳንድ ሰዎች ላይ በጨጓራ ባክቴሪያ አማካኝነት ወደ ካንሰር የመቀየር ዕድል ሊኖረዉ እንደሚችል አስገንዝበዋል።ለህመም ማስታገሻ ተብለዉ የሚወሰዱ እንደ አይቡፕሮፌን እና አስፕሪን ያሉ መድሃኒቶች ለረጅም ጊዜ የሚወሰዱ ከሆነ ለጨጓራ ቁስለት ሊያጋልጡ ይችላሉ በማለት የህክምና ባለሙያው ጨምረው ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የጨጓራ ህመምን በቤት ዉስጥ በተለያዩ መንገዶች ማከም አንዱ አማራጭ ቢሆንም ደረጃዉ ከፍ ሳይል ተገቢዉን የህክምና አገልግሎት ካላገኘ ለከፋ የጤና ችግር እንደሚያጋልጥ ተገልጿል።የጨጓራ ህመም ተገቢዉን የህክምና እርዳታ ካላገኘ እና ወደ መጨረሻዉ ደረጃ ከፍ ካለ ቁስለቱ እስከ መድማት ደርሶ ደም ማስመለስን ሊያስከትል ይችላል ።
የጨጓራ ቁስለት በከፍተኛ ደረጃ ተባብሶ የጨጓራ ግድግዳን ሙሉ በሙሉ በመብሳት ቀዳዳ በሚፈጥርበት ወቅት በሆድ ዕቃ ውስጥ ከባድ ኢንፌክሽንን ስለሚያስከትል አስቸኳይ የሕክምና እርዳታ ማግኘት ተገቢ ነዉ ተብሏል ።በተጨማሪም ጨጓራ ከትንሹ አንጀት ጋር የሚገናኝበት ቦታ ላይ በተደጋጋሚ ጉዳት ሲደርስበት ቦታዉ ይጠብና የምግብ መተላለፊያ ቱቦን በመዝጋት ለከፋ የጤና ችግር ስለሚያጋልጥ ተገቢዉን የህክምና እገዛ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የዉስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር አምደመስቀል መርሻ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል ።
የህክምና ባለሙያው አክለዉም በአንዳንድ ሰዎች ላይ በጨጓራ ባክቴሪያ አማካኝነት ወደ ካንሰር የመቀየር ዕድል ሊኖረዉ እንደሚችል አስገንዝበዋል።ለህመም ማስታገሻ ተብለዉ የሚወሰዱ እንደ አይቡፕሮፌን እና አስፕሪን ያሉ መድሃኒቶች ለረጅም ጊዜ የሚወሰዱ ከሆነ ለጨጓራ ቁስለት ሊያጋልጡ ይችላሉ በማለት የህክምና ባለሙያው ጨምረው ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
14 hours ago
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ለመቄዶንያ ከ4.6 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አበረከተ
#ethiopia | አዲስ አበባ | ኢትዮጵያ – የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የመስሪያ ቤቱን ማኔጅመንት፣ ሰራተኞች እና ታራሚዎች በማስተባበር ለመቄዶንያ አረጋውያንና ህጻናት መረዳጃ ማህበር ከ4.6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አበርክቷል።
ኮሚሽኑ ቀደም ሲል በገባው ቃል መሰረት በየዓመቱ ሐምሌ 28 መቄዶንያን የመጎብኘት ልማዱን በመቀጠል፣ በዚህ ዓመትም 547 ሺህ 65 ብር ጥሬ ገንዘብ እና ከ4.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለማህበሩ አስረክቧል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ዋና ኮሚሽነር የኑስ ሙሉ፣ መቄዶንያ ለሚያከናውነው ሰብዓዊ አገልግሎት በኮሚሽኑ ስም ያላቸውን አክብሮትና ምስጋና ገልጸዋል።
በጉብኝቱ ወቅት የኮሚሽኑ የህክምና ልዑካን ቡድን ከ770 ሺህ ብር በላይ የሚገመቱ የህክምና ቁሳቁሶችን በማበርከት ብቻ ሳይሆን፣ ለማህበሩ ተገልጋዮች የህክምና አገልግሎትም ሰጥቷል።
በተጨማሪም በኮሚሽኑ ስር የሚገኙ ታራሚዎች በእጃቸው ያመረቷቸውን የተለያዩ ቁሳቁሶች በስጦታ በማበርከት ከመልካም ምኞት መልዕክታቸው ጋር ለማህበሩ አስረክበዋል።
የመቄዶንያ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር ዶ/ር ቢንያም በለጠ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣ የማህበሩ ተገልጋይ አረጋውያንም በተደረገላቸው ጉብኝትና ድጋፍ ያላቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ጌጡ ተመስገን
#ethiopia #federalprisoncommission #macedonia #charitysupport #givingback #humanitarianassociation #getutemesgen #ጌጡተመስገን
#ethiopia | አዲስ አበባ | ኢትዮጵያ – የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የመስሪያ ቤቱን ማኔጅመንት፣ ሰራተኞች እና ታራሚዎች በማስተባበር ለመቄዶንያ አረጋውያንና ህጻናት መረዳጃ ማህበር ከ4.6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አበርክቷል።
ኮሚሽኑ ቀደም ሲል በገባው ቃል መሰረት በየዓመቱ ሐምሌ 28 መቄዶንያን የመጎብኘት ልማዱን በመቀጠል፣ በዚህ ዓመትም 547 ሺህ 65 ብር ጥሬ ገንዘብ እና ከ4.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለማህበሩ አስረክቧል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ዋና ኮሚሽነር የኑስ ሙሉ፣ መቄዶንያ ለሚያከናውነው ሰብዓዊ አገልግሎት በኮሚሽኑ ስም ያላቸውን አክብሮትና ምስጋና ገልጸዋል።
በጉብኝቱ ወቅት የኮሚሽኑ የህክምና ልዑካን ቡድን ከ770 ሺህ ብር በላይ የሚገመቱ የህክምና ቁሳቁሶችን በማበርከት ብቻ ሳይሆን፣ ለማህበሩ ተገልጋዮች የህክምና አገልግሎትም ሰጥቷል።
በተጨማሪም በኮሚሽኑ ስር የሚገኙ ታራሚዎች በእጃቸው ያመረቷቸውን የተለያዩ ቁሳቁሶች በስጦታ በማበርከት ከመልካም ምኞት መልዕክታቸው ጋር ለማህበሩ አስረክበዋል።
የመቄዶንያ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር ዶ/ር ቢንያም በለጠ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣ የማህበሩ ተገልጋይ አረጋውያንም በተደረገላቸው ጉብኝትና ድጋፍ ያላቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ጌጡ ተመስገን
#ethiopia #federalprisoncommission #macedonia #charitysupport #givingback #humanitarianassociation #getutemesgen #ጌጡተመስገን
15 hours ago
ይህን እሽግ እንደተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ ወንጀል ነው!
#ethiopia | በከባድ የምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናትን ሕይወት ለማዳን የሚሰጠው አጣዳፊ የምግብ መድኃኒት (RUTF) ወይ በተለምዶ ስሙ ፕላምፕሌት በገበያ ላይ ለንግድ መቅረቡና ለክብደት መጨመሪያ መዋሉ ከፍተኛ የሞራልና የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ወንጀል መሆኑ ተገለጸ።
በሞት አፋፍ ላይ የሚገኙ ሕፃናትን ለማዳን በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀውን ይህን ሕይወት አድን እሽግ እንደ ተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ በእርግጥም ህክምናው ለሚገባቸው ሕፃናት የሚደርሰውን እርዳታ በመንጠቅ ሕይወታቸውን ለሞት አደጋ የሚያጋልጥ ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ይህ ምርት በካሎሪ፣ በቅባትና በቫይታሚኖች እጅግ የበለፀገ በመሆኑ ጤናማ ሰዎች ሳያስፈልጋቸው ሲመገቡት ለከፍተኛ የኩላሊትና የጉበት ጫና፣ ለደም ስኳርና ቅባት መዛባት እንዲሁም ለቫይታሚን መርዝነት ያጋልጣቸዋል።
በመሆኑም በነፃ ወይም በሕክምና ተቋማት በኩል ለተቸገሩ ሕፃናት የተላከን እርዳታ መሸጥም ሆነ መግዛት በሕግ የሚያስጠይቅ ወንጀል በመሆኑ፣ ሕይወት አድን መድኃኒቶች የንግድ ዕቃ አለመሆናቸውን ተረድቶ ኅብረተሰቡ ከዚህ ድርጊት ሊቆጠብ እንደሚገባ መልእክት ተላልፏል።
(via ጤና)
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በከባድ የምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናትን ሕይወት ለማዳን የሚሰጠው አጣዳፊ የምግብ መድኃኒት (RUTF) ወይ በተለምዶ ስሙ ፕላምፕሌት በገበያ ላይ ለንግድ መቅረቡና ለክብደት መጨመሪያ መዋሉ ከፍተኛ የሞራልና የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ወንጀል መሆኑ ተገለጸ።
በሞት አፋፍ ላይ የሚገኙ ሕፃናትን ለማዳን በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀውን ይህን ሕይወት አድን እሽግ እንደ ተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ በእርግጥም ህክምናው ለሚገባቸው ሕፃናት የሚደርሰውን እርዳታ በመንጠቅ ሕይወታቸውን ለሞት አደጋ የሚያጋልጥ ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ይህ ምርት በካሎሪ፣ በቅባትና በቫይታሚኖች እጅግ የበለፀገ በመሆኑ ጤናማ ሰዎች ሳያስፈልጋቸው ሲመገቡት ለከፍተኛ የኩላሊትና የጉበት ጫና፣ ለደም ስኳርና ቅባት መዛባት እንዲሁም ለቫይታሚን መርዝነት ያጋልጣቸዋል።
በመሆኑም በነፃ ወይም በሕክምና ተቋማት በኩል ለተቸገሩ ሕፃናት የተላከን እርዳታ መሸጥም ሆነ መግዛት በሕግ የሚያስጠይቅ ወንጀል በመሆኑ፣ ሕይወት አድን መድኃኒቶች የንግድ ዕቃ አለመሆናቸውን ተረድቶ ኅብረተሰቡ ከዚህ ድርጊት ሊቆጠብ እንደሚገባ መልእክት ተላልፏል።
(via ጤና)
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
16 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሱማሊላንድ ፕሬዝደንት የኩላሊት ዲያሊሲስ አገልግሎት በነፃ እንዲሰጥ ትእዛዝ ሰጡ፡፡ የሱማሊላንድ ፕሬዝደንት አብዱራህማን መሀመድ ኢሮ በአገራቸው ውስጥ በነፃ የኩላሊት ዲያሊሲስ አገልግሎት እንዲሰጥ ትእዛዝ ማስተላፋቸውን ሂራን ኒውስ ዘገበ፡፡
እንደዘገባው ይህንን ትእዛዝ ለመስጠት የተገደዱት ህሙማን በቂ አገልግሎት ባለመኖሩ ለከፍተኛ ወጪ እየተዳረጉ መሆናቸውን በመግለፃቸው ነው፡፡ ትላንት ከሱማሊላንድ ፕሬዝደንት ፅህፈት ቤት የወጣው መመሪያ የአገሪቱ ጤና ሚኒስትር በአስቸኳይ 12 የዲያሊሲስ ማሽኖችን እንዲገዛና በሀርጌሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የሚሰጠውን ይህንን ህክምና እንዲያሰፋ ትእዛዝ ማስተላለፉን ዘገባው አስረድቷል፡፡ ይህ የፕሬዝደንቱ መመሪያ ማንኛውም የኩላሊት ህመም ህክምና ዲያሊሲስን ጨምሮ በነፃ እንዲሰጥም የሚገልፅ ነው፡፡
ፕሬዝደንቱ ይህንን መመሪያ ከመስጠታቸው ከጥቂት ቀናት በፊት በሀርጌሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ተገኝተው ጉብኝት በማድረግ ከህሙማን፣ ከአስተዳደሩና ከዶክተሮች ጋር ውይይት አድርገው ነበር፡፡ ለዚህ ጉብኝት መሰረት የሆናቸው ደግሞ ባለፈው ሳምንት በርካታ የኩላሊት ህሙማን በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው እንደሆነ ከዘገባው ላይ ተመልክተናል፡፡
እንደዘገባው ይህንን ትእዛዝ ለመስጠት የተገደዱት ህሙማን በቂ አገልግሎት ባለመኖሩ ለከፍተኛ ወጪ እየተዳረጉ መሆናቸውን በመግለፃቸው ነው፡፡ ትላንት ከሱማሊላንድ ፕሬዝደንት ፅህፈት ቤት የወጣው መመሪያ የአገሪቱ ጤና ሚኒስትር በአስቸኳይ 12 የዲያሊሲስ ማሽኖችን እንዲገዛና በሀርጌሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የሚሰጠውን ይህንን ህክምና እንዲያሰፋ ትእዛዝ ማስተላለፉን ዘገባው አስረድቷል፡፡ ይህ የፕሬዝደንቱ መመሪያ ማንኛውም የኩላሊት ህመም ህክምና ዲያሊሲስን ጨምሮ በነፃ እንዲሰጥም የሚገልፅ ነው፡፡
ፕሬዝደንቱ ይህንን መመሪያ ከመስጠታቸው ከጥቂት ቀናት በፊት በሀርጌሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ተገኝተው ጉብኝት በማድረግ ከህሙማን፣ ከአስተዳደሩና ከዶክተሮች ጋር ውይይት አድርገው ነበር፡፡ ለዚህ ጉብኝት መሰረት የሆናቸው ደግሞ ባለፈው ሳምንት በርካታ የኩላሊት ህሙማን በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው እንደሆነ ከዘገባው ላይ ተመልክተናል፡፡
19 hours ago
“ከምኩራቡ በስተጀርባ”፡ የቤተ-እስራኤላውያንን ስውር ታሪክ የሚያወሳው አዲስ መጽሐፍ ተመረቀ
የቤተ-እስራኤላውያንን ህይወት እና ስውር ታሪክ የሚያወሳው “ከምኩራቡ በስተጀርባ” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በስቴይ ኢዚ ፕላዛ በድምቀት ተመርቋል።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች” እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል። በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል። በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው። መጽሐፉ እንደ «ፈ ላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስ ድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል። እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል። ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
የቤተ-እስራኤላውያንን ህይወት እና ስውር ታሪክ የሚያወሳው “ከምኩራቡ በስተጀርባ” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በስቴይ ኢዚ ፕላዛ በድምቀት ተመርቋል።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች” እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል። በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል። በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው። መጽሐፉ እንደ «ፈ ላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስ ድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል። እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል። ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
19 hours ago
ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የባለቤቷን ህመም (FTD) ለመከታተል የሚያስችል ህግ እንዲፀድቅ ግፊት አደረገች
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
19 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ሰኞ ዕለት በአማራ ክልል በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ የመሬት መንሸራተት የ14 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ በሰባት ሰዎች ላይ ደግሞ ጉዳት ደርሷል። የፍለጋ እና የነፍስ አድን ስራው አሁንም ቀጥሎ ባለበት በዚህ ወቅት፣ እስካሁን የገቡበት ያልታወቁ እና በፍርስራሹ ስር የተቀበሩ በርካታ ሰዎች እንዳሉ ተነግሯል።
አደጋው የተከሰተው በፃድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ሲሆን፣ በወቅቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ለፀበል እና ለመንፈሳዊ ፈውስ በስፍራው ተሰብስበው ነበር። የሀገረ ስብከቱ ዋና ስራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ነቃ ጥበብ አባቡ ለአሶሼትድ ፕሬስ እንደተናገሩት፣ "አደጋው የተከሰተው ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ገደማ ሲሆን፣ ከሟቾቹ መካከል አብዛኞቹ ፀበል ለመጠመቅ የተሰበሰቡ ነበሩ።" ስራ አስኪያጁ አክለውም፣ "ከሟቾቹ መካከል አስራ አንዱ በገዳሙ ውስጥ የተቀበሩ ሲሆን፣ የሌሎቹ አስከሬን ወደ ትውልድ ስፍራቸው ተልኳል፤ ይሁን እንጂ የአንዳንዶቹን ሟቾች ማንነት ለመለየት አስቸጋሪ ሆኗል" ብለዋል።
ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ከገዳሙ 70 ኪሎ ሜትር (43 ማይል) ርቀት ላይ ወደምትገኘው የሰሜን ሸዋ አስተዳደር ዞን ዋና ከተማ ደብረ ብርሃን ለህክምና ተወስደዋል። የመሬት መንሸራተቱ የተከሰተው ከተራራ አጠገብ በመሆኑ፣ ግዙፍ አለቶች ተገንጥለው በምዕመናኑ ላይ መውደቃቸው አደጋውን ይበልጥ አባብሶታል። የአካባቢው አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ የፍለጋ እና አድን ስራዎችን ለማገዝ የአካባቢው የአደጋ መከላከል ጽህፈት ቤት ባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው መሰማራቱን አስታውቋል።
በኢትዮጵያ ከሰኔ እስከ መስከረም በሚዘልቀው የክረምት ወቅት ከባድ ዝናብ የሚያስከትለው የመሬት መንሸራተት እና ጎርፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተለመደ መጥቷል። በሐምሌ 2024 በደቡብ ኢትዮጵያ በጣለ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ አሳዛኝ የመሬት መንሸራተት ቢያንስ 257 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል። ከዚህ ቀደምም በዚህ ዓመት መጀመሪያ አካባቢ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ ጋሞ ውስጥ በተከሰተ ተመሳሳይ የመሬት መንሸራተት ከ100 በላይ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።
በአፍሪካ ቀንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዙ የከፋ የአየር ፀባይ ክስተቶች በከፍተኛ ሁኔታ እየተጠቃች ትገኛለች። በተለይም በገጠራማ አካባቢዎች ያለው ደካማ መሰረተ ልማት፣ በርካታ ማህበረሰቦችን ለጎርፍ፣ ለመሬት መንሸራተት እና ተደጋጋሚ ድርቅ በቀላሉ ተጋላጭ እንዲሆኑ ያደረጋቸው ሲሆን፣ ለእንደዚህ አይነት አደጋዎች ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅማቸውም እጅግ ውስን ሆኖ ቆይቷል።
አደጋው የተከሰተው በፃድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ሲሆን፣ በወቅቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ለፀበል እና ለመንፈሳዊ ፈውስ በስፍራው ተሰብስበው ነበር። የሀገረ ስብከቱ ዋና ስራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ነቃ ጥበብ አባቡ ለአሶሼትድ ፕሬስ እንደተናገሩት፣ "አደጋው የተከሰተው ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ገደማ ሲሆን፣ ከሟቾቹ መካከል አብዛኞቹ ፀበል ለመጠመቅ የተሰበሰቡ ነበሩ።" ስራ አስኪያጁ አክለውም፣ "ከሟቾቹ መካከል አስራ አንዱ በገዳሙ ውስጥ የተቀበሩ ሲሆን፣ የሌሎቹ አስከሬን ወደ ትውልድ ስፍራቸው ተልኳል፤ ይሁን እንጂ የአንዳንዶቹን ሟቾች ማንነት ለመለየት አስቸጋሪ ሆኗል" ብለዋል።
ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ከገዳሙ 70 ኪሎ ሜትር (43 ማይል) ርቀት ላይ ወደምትገኘው የሰሜን ሸዋ አስተዳደር ዞን ዋና ከተማ ደብረ ብርሃን ለህክምና ተወስደዋል። የመሬት መንሸራተቱ የተከሰተው ከተራራ አጠገብ በመሆኑ፣ ግዙፍ አለቶች ተገንጥለው በምዕመናኑ ላይ መውደቃቸው አደጋውን ይበልጥ አባብሶታል። የአካባቢው አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ የፍለጋ እና አድን ስራዎችን ለማገዝ የአካባቢው የአደጋ መከላከል ጽህፈት ቤት ባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው መሰማራቱን አስታውቋል።
በኢትዮጵያ ከሰኔ እስከ መስከረም በሚዘልቀው የክረምት ወቅት ከባድ ዝናብ የሚያስከትለው የመሬት መንሸራተት እና ጎርፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተለመደ መጥቷል። በሐምሌ 2024 በደቡብ ኢትዮጵያ በጣለ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ አሳዛኝ የመሬት መንሸራተት ቢያንስ 257 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል። ከዚህ ቀደምም በዚህ ዓመት መጀመሪያ አካባቢ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ ጋሞ ውስጥ በተከሰተ ተመሳሳይ የመሬት መንሸራተት ከ100 በላይ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።
በአፍሪካ ቀንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዙ የከፋ የአየር ፀባይ ክስተቶች በከፍተኛ ሁኔታ እየተጠቃች ትገኛለች። በተለይም በገጠራማ አካባቢዎች ያለው ደካማ መሰረተ ልማት፣ በርካታ ማህበረሰቦችን ለጎርፍ፣ ለመሬት መንሸራተት እና ተደጋጋሚ ድርቅ በቀላሉ ተጋላጭ እንዲሆኑ ያደረጋቸው ሲሆን፣ ለእንደዚህ አይነት አደጋዎች ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅማቸውም እጅግ ውስን ሆኖ ቆይቷል።
20 hours ago
ከምኩራቡ በስተጀርባ
#ethiopia | የቤተ እስራኤላዊያንን ስውር ታሪክ የሚያወሳው መጽሐፍ ተመረቀ።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች”እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል።
በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል።
በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው።
መጽሐፉ እንደ «ፈላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል።
እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል።
ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews
#ethiopia | የቤተ እስራኤላዊያንን ስውር ታሪክ የሚያወሳው መጽሐፍ ተመረቀ።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች”እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል።
በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል።
በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው።
መጽሐፉ እንደ «ፈላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል።
እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል።
ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews
Sponsored by
Surafel
1 day ago
አሳዛኝ ታሪክ- የፔቲዲን ሱስ
#ethiopia | ዶክተር ካሳ አደጋ ያጋጥመውና የእጁ አጥንት ይሰበራል። ወደ ድንገተኛ ክፍል ሲሄድ ለህመም ማስታገሻ ፔቲዲን የተባለውን መርፌ ይወጉታል። የስብራቱ ህመም ይጠፋና የደስታ ስሜት ይሰማዋል። ከስብራቱ ቢያገግምም ለህመም ማስታገሻ የወሰደው ፔቲዲን ሱስ ሆኖበት በየቀኑ ብዙ ብልቃጦች ራሱን ይወጋል።
ፔቲዲን የሚፃፈው በልዩ የመድሀኒት ማዘዣ ነው። ዶክተር ካሳ ጓደኞቹ እንዲፅፉለት ይጠይቃቸዋል። መጀመሪያ ላይ ይፅፉለት ነበር። በኋላ ግን የሚወስደው መጠን ከፍ ስላለ "አንፅፍም!" ብለው ከለከሉት። አንዳንድ ባልደረቦቹ ግን እያዘኑለት ይፅፉለታል። የሚወስደው መድሀኒት መጠን ከፍ ሲል ልዩ የመድሀኒት ማዘዣውን ይዞ እራሱ እየፃፈ መግዛት ጀመረ። መድሀኒቱ ውድ ስለሆነ ዶክተር ካሳ አብዛኛው ደሞዙን በመድሀኒት ግዢ ነው የሚያጠፋው። ከባልደረቦቹም በተለያየ ጊዜ ብሮች ተበድሯል።
ዶክተር ካሳ ሱሱን ለማቆም ሞክሮ ያውቃል። ነገር ግን ሳይወስድ ሲቀር ላብበላብ ይሆናል። ተረጋግቶ መስራት አይችልም። ይቅበጠበጣል። መድሀኒቱን ባለመውሰዱ የሚሰማውን ምቾት የሚነሳ ስሜት ለማጥፋት ውሳኔውን ሽሮ ፔቲዲን ይወጋል።
አንድ ቀን ዶክተር ካሳ ሆስፒታሉ የሰጠው ቤት ውስጥ ራሱን ስቶ ተዘርሮ ወድቋል። ክፍሉ ውስጥ የፔቲዲን ብልቃጦች አሉ። መርፌና ሲሪንጅ አጠገቡ አለ....
ዶክተር ካሳ ልቦለዳዊ ስም ይሆን እንጂ ተመሳሳይ የፔቲዲን ሱስ ውስጥ ያሉ ብዙ ሰዎች አሉ። አብዛኞቹ ደግሞ የጤና ባለሞያዎች ናቸው። ነርሶች፣ የሰመመን ባለሞያዎች፣ ሀኪሞች፣ የፋርማሲ ባለምያዎች...። ህክምና ሞያ ውስጥ ጥቂት አመታት ያሳለፍን ሰዎች በዚህ ሱስ የሚቸገር የምናውቀው ሰው ወይም ወዳጅ አለን።
በሱስ የሚቸገሩ ሰዎች ላይ ፍረጃ ከማድረግ ይልቅ ሞያዊ እገዛ እንዲያገኙ ብናደርግ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮች እንዳይከሰቱ ማድረግ እንችላለን። ሱስ ህክምና ያለው የአእምሮ ህመም ነው።
እኔ የምወደውን ሰው በፔቲዲን ሱስ ምክኒያት አጥቻለሁ። ይመለከተኛል። ሌሎች ሰዎች ተመሳሳይ ነገር ውስጥ እንዳያልፉና ተገቢውን የአእምሮ ህክምና እንዲያገኙ የምችለውን ያህል ግንዛቤ ለመፍጠር እጥራለሁ።
ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!
ዶ/ር ዮናስ ላቀው
#ethiopia | ዶክተር ካሳ አደጋ ያጋጥመውና የእጁ አጥንት ይሰበራል። ወደ ድንገተኛ ክፍል ሲሄድ ለህመም ማስታገሻ ፔቲዲን የተባለውን መርፌ ይወጉታል። የስብራቱ ህመም ይጠፋና የደስታ ስሜት ይሰማዋል። ከስብራቱ ቢያገግምም ለህመም ማስታገሻ የወሰደው ፔቲዲን ሱስ ሆኖበት በየቀኑ ብዙ ብልቃጦች ራሱን ይወጋል።
ፔቲዲን የሚፃፈው በልዩ የመድሀኒት ማዘዣ ነው። ዶክተር ካሳ ጓደኞቹ እንዲፅፉለት ይጠይቃቸዋል። መጀመሪያ ላይ ይፅፉለት ነበር። በኋላ ግን የሚወስደው መጠን ከፍ ስላለ "አንፅፍም!" ብለው ከለከሉት። አንዳንድ ባልደረቦቹ ግን እያዘኑለት ይፅፉለታል። የሚወስደው መድሀኒት መጠን ከፍ ሲል ልዩ የመድሀኒት ማዘዣውን ይዞ እራሱ እየፃፈ መግዛት ጀመረ። መድሀኒቱ ውድ ስለሆነ ዶክተር ካሳ አብዛኛው ደሞዙን በመድሀኒት ግዢ ነው የሚያጠፋው። ከባልደረቦቹም በተለያየ ጊዜ ብሮች ተበድሯል።
ዶክተር ካሳ ሱሱን ለማቆም ሞክሮ ያውቃል። ነገር ግን ሳይወስድ ሲቀር ላብበላብ ይሆናል። ተረጋግቶ መስራት አይችልም። ይቅበጠበጣል። መድሀኒቱን ባለመውሰዱ የሚሰማውን ምቾት የሚነሳ ስሜት ለማጥፋት ውሳኔውን ሽሮ ፔቲዲን ይወጋል።
አንድ ቀን ዶክተር ካሳ ሆስፒታሉ የሰጠው ቤት ውስጥ ራሱን ስቶ ተዘርሮ ወድቋል። ክፍሉ ውስጥ የፔቲዲን ብልቃጦች አሉ። መርፌና ሲሪንጅ አጠገቡ አለ....
ዶክተር ካሳ ልቦለዳዊ ስም ይሆን እንጂ ተመሳሳይ የፔቲዲን ሱስ ውስጥ ያሉ ብዙ ሰዎች አሉ። አብዛኞቹ ደግሞ የጤና ባለሞያዎች ናቸው። ነርሶች፣ የሰመመን ባለሞያዎች፣ ሀኪሞች፣ የፋርማሲ ባለምያዎች...። ህክምና ሞያ ውስጥ ጥቂት አመታት ያሳለፍን ሰዎች በዚህ ሱስ የሚቸገር የምናውቀው ሰው ወይም ወዳጅ አለን።
በሱስ የሚቸገሩ ሰዎች ላይ ፍረጃ ከማድረግ ይልቅ ሞያዊ እገዛ እንዲያገኙ ብናደርግ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮች እንዳይከሰቱ ማድረግ እንችላለን። ሱስ ህክምና ያለው የአእምሮ ህመም ነው።
እኔ የምወደውን ሰው በፔቲዲን ሱስ ምክኒያት አጥቻለሁ። ይመለከተኛል። ሌሎች ሰዎች ተመሳሳይ ነገር ውስጥ እንዳያልፉና ተገቢውን የአእምሮ ህክምና እንዲያገኙ የምችለውን ያህል ግንዛቤ ለመፍጠር እጥራለሁ።
ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!
ዶ/ር ዮናስ ላቀው
2 days ago
በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ያጣሉ
#ethiopia | በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸውን እንደሚያጡ መረጃዎች ጠቁመዋል።
የሞት ምጣኔ በሀገራት መካከል በከፍተኛ ሁኔታ የሚለያይ ሲሆን ዋና ዋና ምክንያቶቹ የዕድሜ ስብጥር የአረጋውያን ቁጥር መብዛት ደካማ የጤና ስርዓት ጦርነትና ግጭት ዋነኞቹ ናቸው።
ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት እንደ ድህነት ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎች ለሞት ምጣኔው ከፍተኛ መሆን እንደምክንያትነት ይጠቀሳሉ።
በተጨማሪም በሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ በቂ የህክምና አቅርቦት አለመኖር ተላላፊ በሽታዎች እና የእናቶችና ህፃናት ሞት ምጣኔ ከፍተኛ መሆን ዋና ምክንያቶች ናቸው።
በጦርነት ውስጥ ባሉ ሀገራት የሰው ህይወት ማጣት እና የጤና ተቋማት መውደም የሞት ምጣኔውን ከፍተኛ አድርጎታል።
በምስራቅ አውሮፓ እንደ ቡልጋሪያ እና ላቲቪያ ያለው የሞት ምጣኔ በቁጥር ከፍ ብሎ የሚታየው አረጋውያን በመብዛታቸው ምክንያት ነው ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldpopulation #deathrate #europe #africa
#ethiopia | በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸውን እንደሚያጡ መረጃዎች ጠቁመዋል።
የሞት ምጣኔ በሀገራት መካከል በከፍተኛ ሁኔታ የሚለያይ ሲሆን ዋና ዋና ምክንያቶቹ የዕድሜ ስብጥር የአረጋውያን ቁጥር መብዛት ደካማ የጤና ስርዓት ጦርነትና ግጭት ዋነኞቹ ናቸው።
ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት እንደ ድህነት ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎች ለሞት ምጣኔው ከፍተኛ መሆን እንደምክንያትነት ይጠቀሳሉ።
በተጨማሪም በሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ በቂ የህክምና አቅርቦት አለመኖር ተላላፊ በሽታዎች እና የእናቶችና ህፃናት ሞት ምጣኔ ከፍተኛ መሆን ዋና ምክንያቶች ናቸው።
በጦርነት ውስጥ ባሉ ሀገራት የሰው ህይወት ማጣት እና የጤና ተቋማት መውደም የሞት ምጣኔውን ከፍተኛ አድርጎታል።
በምስራቅ አውሮፓ እንደ ቡልጋሪያ እና ላቲቪያ ያለው የሞት ምጣኔ በቁጥር ከፍ ብሎ የሚታየው አረጋውያን በመብዛታቸው ምክንያት ነው ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldpopulation #deathrate #europe #africa
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ባለፈው ሳምንት በሌክ ታሆ ውስጥ ሰጥሞ ህይወቱ ያለፈው ኢትዮጵያዊው የአማዞን ሶፍትዌር መሃንዲስ ጓደኞች፣ በህይወቱ የመጨረሻ ደቂቃዎች ውስጥ በትክክል ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ የአይን እማኞች መረጃ በመስጠት እንዲተባበሯቸው ጥሪ አቀረቡ።
የ32 ዓመቱ የኦስቲን ቴክሳስ ነዋሪ የሆነው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ያደሳ እምሩ አጋ፣ ጁላይ 27 ቀን በኔቫዳ የባህር ዳርቻ በሚገኘው ሳንድ ሀርበር አቅራቢያ ውሃ ውስጥ እያለ ራሱን ስቶ ነበር። በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ወደ ዳርቻው ያወጡት ሲሆን፣ ፖሊሶች እና የህክምና ባለሙያዎች ህይወቱን ለመታደግ ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል።
የዋሾ ካውንቲ ፖሊስ ሞቱን እንደ ድንገተኛ የውሃ ውስጥ የመስመጥ አደጋ እየመረመረው ይገኛል። ሆኖም የካውንቲው የህክምና መርማሪ የመጨረሻውን የሞት ምክንያት እስካሁን ይፋ ስላላደረገ፣ የያደሳ ጓደኞች እና ዘመዶች በውሃው ውስጥ በትክክል ምን እንደተፈጠረ ግልጽ የሆነ መረጃ ለማግኘት እየጣሩ ነው።
በሬዲት ላይ ራሱን የሟች የቅርብ ጓደኛ መሆኑን የገለጸ ግለሰብ፣ በዚያ ምሽት ሳንድ ሀርበር የነበረ ማንኛውም ሰው ፎቶግራፎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም በአካል የተመለከተውን መረጃ እንዲያካፍል ጠይቋል።
እንደ ጸሃፊው ገለጻ ያደሳ ጀምበር ልትጠልቅ ስትል ከሌሎች ጋር እየዋኘ እንደነበር እና ከዚያም ከውሃው ውስጥ የድረሱልኝ ጩኸት እንደተሰማ የአይን እማኞች ተናግረዋል። ሁለት ጓደኞቹ እሱን ለማዳን ሲሞክሩ እንደተቸገሩ እና በፓድል ቦርድ ላይ የነበሩ ሰዎች ሶስቱንም ዋናተኞች ወደ ዳርቻው ለማውጣት እንደረዱ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ደግሞ የያደሳ የሊንክድኢን ፕሮፋይል ፎቶግራፍ ታችኛው ግራ ጥግ ላይ በትንሽ ፊደላት "አዝናለሁ !!!!!" (I am Sorry !!!!!) የሚል ጽሑፍ መገኘቱ ብዙዎችን አነጋግሯል። ይህ ጽሑፍ የሚታየው ምስሉ ሲጎላ ብቻ መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ እንቆቅልሽ አድርጎታል።
ለሟች መታሰቢያ የተከፈተው የገንዘብ ማሰባሰቢያ ገጽ (GoFundMe) እንዳስነበበው፣ ያደሳ ከቤተክርስቲያን ኮንፈረንስ እየተመለሰ በሌክ ታሆ ከጓደኞቹ ጋር ጊዜ እያሳለፈ በነበረበት ወቅት አደጋው ያጋጠመው እጅግ መንፈሳዊ ወጣት ነበር። በደግነቱ፣ በሞቅታው እና በለጋስነቱ የሚታወቅ መሆኑን የገለጸው ማሰባሰቢያው፣ የሚሰበሰበው ገንዘብ ለቀብር ስነ-ስርዓት እና አስከሬኑን ወደ ሀገሩ ኢትዮጵያ ለመመለስ እንደሚውል አስታውቋል።
የ32 ዓመቱ የኦስቲን ቴክሳስ ነዋሪ የሆነው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ያደሳ እምሩ አጋ፣ ጁላይ 27 ቀን በኔቫዳ የባህር ዳርቻ በሚገኘው ሳንድ ሀርበር አቅራቢያ ውሃ ውስጥ እያለ ራሱን ስቶ ነበር። በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ወደ ዳርቻው ያወጡት ሲሆን፣ ፖሊሶች እና የህክምና ባለሙያዎች ህይወቱን ለመታደግ ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል።
የዋሾ ካውንቲ ፖሊስ ሞቱን እንደ ድንገተኛ የውሃ ውስጥ የመስመጥ አደጋ እየመረመረው ይገኛል። ሆኖም የካውንቲው የህክምና መርማሪ የመጨረሻውን የሞት ምክንያት እስካሁን ይፋ ስላላደረገ፣ የያደሳ ጓደኞች እና ዘመዶች በውሃው ውስጥ በትክክል ምን እንደተፈጠረ ግልጽ የሆነ መረጃ ለማግኘት እየጣሩ ነው።
በሬዲት ላይ ራሱን የሟች የቅርብ ጓደኛ መሆኑን የገለጸ ግለሰብ፣ በዚያ ምሽት ሳንድ ሀርበር የነበረ ማንኛውም ሰው ፎቶግራፎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም በአካል የተመለከተውን መረጃ እንዲያካፍል ጠይቋል።
እንደ ጸሃፊው ገለጻ ያደሳ ጀምበር ልትጠልቅ ስትል ከሌሎች ጋር እየዋኘ እንደነበር እና ከዚያም ከውሃው ውስጥ የድረሱልኝ ጩኸት እንደተሰማ የአይን እማኞች ተናግረዋል። ሁለት ጓደኞቹ እሱን ለማዳን ሲሞክሩ እንደተቸገሩ እና በፓድል ቦርድ ላይ የነበሩ ሰዎች ሶስቱንም ዋናተኞች ወደ ዳርቻው ለማውጣት እንደረዱ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ደግሞ የያደሳ የሊንክድኢን ፕሮፋይል ፎቶግራፍ ታችኛው ግራ ጥግ ላይ በትንሽ ፊደላት "አዝናለሁ !!!!!" (I am Sorry !!!!!) የሚል ጽሑፍ መገኘቱ ብዙዎችን አነጋግሯል። ይህ ጽሑፍ የሚታየው ምስሉ ሲጎላ ብቻ መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ እንቆቅልሽ አድርጎታል።
ለሟች መታሰቢያ የተከፈተው የገንዘብ ማሰባሰቢያ ገጽ (GoFundMe) እንዳስነበበው፣ ያደሳ ከቤተክርስቲያን ኮንፈረንስ እየተመለሰ በሌክ ታሆ ከጓደኞቹ ጋር ጊዜ እያሳለፈ በነበረበት ወቅት አደጋው ያጋጠመው እጅግ መንፈሳዊ ወጣት ነበር። በደግነቱ፣ በሞቅታው እና በለጋስነቱ የሚታወቅ መሆኑን የገለጸው ማሰባሰቢያው፣ የሚሰበሰበው ገንዘብ ለቀብር ስነ-ስርዓት እና አስከሬኑን ወደ ሀገሩ ኢትዮጵያ ለመመለስ እንደሚውል አስታውቋል።
2 days ago
ከሞጃና ወደራ ወረዳ አስተዳደር ምክርቤት የተሰጠ የሀዘን መግለጫ
በታላቋ ገዳም በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ድንገት በተከሰተ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰው ሕይወት አለፈ።
በመሬት መንሸራተቱ የ14 ምዕመናን ሂወት ሲያልፍ በ5 ሰው ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በ2 ሰዎች ላይ መለስተኛ ጉዳት በመድረሱ የወረዳዉ አስተዳደር ምክርቤት መሪር ኀዘኑን ገልፆል ።
የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ የማነብርሀን ተስፈ ጨምሮ የወረዳ አስተባባሪ አመራርና የፀጥታ አመራሩ እቦታዉ ላይ በመገኘት ነፍስ በማዳን እርብርቡ ላይ ሁለተናዊ ድጋፍ አድርገዋል።
የህክምና ባለሙያዎች የአካባቢዉ ማህበረሰብ በቦታዉ ላይ በመገኘት የተጎዱ ወገኖችን የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ብርቱ ትግል አድርገዋል።
ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ በስፍራው የተገኙ ሲሆን ለሞቱ ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት ለተጎዱት ጸሎት ላዘኑ ወገኖቻችን የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ።
በታላቋ ገዳም በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ድንገት በተከሰተ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰው ሕይወት አለፈ።
በመሬት መንሸራተቱ የ14 ምዕመናን ሂወት ሲያልፍ በ5 ሰው ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በ2 ሰዎች ላይ መለስተኛ ጉዳት በመድረሱ የወረዳዉ አስተዳደር ምክርቤት መሪር ኀዘኑን ገልፆል ።
የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ የማነብርሀን ተስፈ ጨምሮ የወረዳ አስተባባሪ አመራርና የፀጥታ አመራሩ እቦታዉ ላይ በመገኘት ነፍስ በማዳን እርብርቡ ላይ ሁለተናዊ ድጋፍ አድርገዋል።
የህክምና ባለሙያዎች የአካባቢዉ ማህበረሰብ በቦታዉ ላይ በመገኘት የተጎዱ ወገኖችን የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ብርቱ ትግል አድርገዋል።
ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ በስፍራው የተገኙ ሲሆን ለሞቱ ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት ለተጎዱት ጸሎት ላዘኑ ወገኖቻችን የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ።
2 days ago
ትርፍ አንጀት ምንድን ነው?
በተለምዶ ትርፍ አንጀት እየተባለ የሚጠራው ችግር የሚከሰተው አፔንዲክስ (ትርፍ አንጀት) ሚባለው ትንሽ የአንጀት አካል ሲያብጥ ወይም ሲቆጣ ነው። ይህ ችግር በፍጥነት ካልታከሙ ሊፈነዳ እና አደገኛ ኢንፌክሽን ሊያስከትል ይችላል።
የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ምንድን ነው?
የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ትርፍ አንጀት ለማስወገድ የሚደረግ ቀዶ ጥገና ሲሆን ለትርፍ አንጀት ችግር በጣም የተለመደው ሕክምና ነው። ቀዶ ሕክምናው በክፍት (open) መንገድ ወይም በላፓሮስኮፒ ሊሰራ ይችላል።
🚨 የትርፍ አንጀት አደገኛ ምልክቶች፡
👉 ከታች በቀኝ በኩል ባለው የሆድ ክፍል ላይ ድንገተኛ እና ከባድ ህመም ፣
🔹ማቅለሽለሽ እና ማስታወክ ፣
🔹ትኩሳት እና ብርድ ብርድ ማለት፣
🔹 የምግብ ፍላጎት ማጣት እና
🔹 በእንቅስቃሴ የሚባባስ ህመም ሲኖር በፍጥነት ወደ ህክምና መሄድ ያስፈልጋል።
✨ የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ለምን ያስፈልጋል?
✅ ትርፍ አንጀት እንዳይፈነዳ እና
✅ ከባድ ኢንፌክሽን እንዳይፈጠር እንዲሁም
✅ በፍጥነት ለማገገም ይህ ቀዶ ህክምና ያስፈልጋል።
ከቀዶ ጥገናው በኋላ ምን ማድረግ ያስፈልጋል?
🔹 በቀላሉ ሊፈጩ የሚችሉ ምግቦችን መመገብ፣
🔹 ረጋ ያለ እንቅስቃሴ ማድረግ፣
🔹 እረፍት ማድረግ እና
🔹 ውሃ በደንብ መጠጣት ቶሎ ለማገገም ይረዳል።
Seledadotio
Seledadotio
በተለምዶ ትርፍ አንጀት እየተባለ የሚጠራው ችግር የሚከሰተው አፔንዲክስ (ትርፍ አንጀት) ሚባለው ትንሽ የአንጀት አካል ሲያብጥ ወይም ሲቆጣ ነው። ይህ ችግር በፍጥነት ካልታከሙ ሊፈነዳ እና አደገኛ ኢንፌክሽን ሊያስከትል ይችላል።
የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ምንድን ነው?
የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ትርፍ አንጀት ለማስወገድ የሚደረግ ቀዶ ጥገና ሲሆን ለትርፍ አንጀት ችግር በጣም የተለመደው ሕክምና ነው። ቀዶ ሕክምናው በክፍት (open) መንገድ ወይም በላፓሮስኮፒ ሊሰራ ይችላል።
🚨 የትርፍ አንጀት አደገኛ ምልክቶች፡
👉 ከታች በቀኝ በኩል ባለው የሆድ ክፍል ላይ ድንገተኛ እና ከባድ ህመም ፣
🔹ማቅለሽለሽ እና ማስታወክ ፣
🔹ትኩሳት እና ብርድ ብርድ ማለት፣
🔹 የምግብ ፍላጎት ማጣት እና
🔹 በእንቅስቃሴ የሚባባስ ህመም ሲኖር በፍጥነት ወደ ህክምና መሄድ ያስፈልጋል።
✨ የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ለምን ያስፈልጋል?
✅ ትርፍ አንጀት እንዳይፈነዳ እና
✅ ከባድ ኢንፌክሽን እንዳይፈጠር እንዲሁም
✅ በፍጥነት ለማገገም ይህ ቀዶ ህክምና ያስፈልጋል።
ከቀዶ ጥገናው በኋላ ምን ማድረግ ያስፈልጋል?
🔹 በቀላሉ ሊፈጩ የሚችሉ ምግቦችን መመገብ፣
🔹 ረጋ ያለ እንቅስቃሴ ማድረግ፣
🔹 እረፍት ማድረግ እና
🔹 ውሃ በደንብ መጠጣት ቶሎ ለማገገም ይረዳል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
የጤናው ዘርፍ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአፍሪካ ህብረት መረጃ እንደሚያመለክተው ቢያንስ 600,000 ሰዎችን ከገደለው ጦርነት ከአራት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ፣ የፌደራል መንግስት ሰራዊት እና የትግራይ ኃይሎች በሰሜን ትግራይ ድንበር አካባቢ ለወራት ኃይል ሲያከማቹ መቆየታቸው ዳግም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚለውን ስጋት አባብሶታል። በዚህም መሰረት በድንበር አካባቢ የተቀሰቀሰውን ውጊያ በመሸሽ በመቶዎች የሚቆጠሩ ከሰሜን ትግራይ ክልል የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ ወደ ጎረቤት ሱዳን መግባታቸውን የሱዳን የጸጥታ እና የህክምና ምንጮች ለኤኤፍፒ ተናግረዋል። ይህ የስደተኞች ፍሰት የተከሰተው ሱዳን ራሷ ከሚያዝያ 2023 ጀምሮ በሱዳን ጦር እና በፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) መካከል በሚካሄድ አውዳሚ ጦርነት ውስጥ ባለችበት ወቅት ነው።
አንድ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባል እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ ጦር እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ከባድ የጦር መሳሪያዎች እና ድሮኖች የታከሉበት ውጊያ በምዕራብ ትግራይ፣ ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ሸረሪና በተባለችው አካባቢ ቅዳሜ ማለዳ ላይ የተቀሰቀሰ ሲሆን፣ እስከ እሁድ ንጋት 11፡00 ሰዓት (5:00 am) ድረስ ቀጥሎ ነበር። ቅዳሜ ዕለት ህወሓት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስትን ሰፋፊ የእግረኛ ጦር ጥቃቶችን ፈጽሞብኛል ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ ባለስልጣናት ለዚህ ክስ ወዲያውኑ የሰጡት ምላሽ የለም። ኤኤፍፒ የህወሓትን ክሶች በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥም ሆነ በሸረሪና ውጊያ ውስጥ የተሳተፉትን ኃይሎች በግልጽ መለየት አለመቻሉን ዘግቧል።
በድንበር ከተማዋ ሀምዳይት የሚገኝ አንድ የሱዳን የጸጥታ ምንጭ፣ ከትግራይ ወደ ሱዳን ከገቡት ሰዎች መካከል የቆሰሉ ተዋጊዎች እንደሚገኙበት ገልጿል። በድንበር ጤና ጣቢያ የሚገኝ የህክምና ምንጭ እንዳስታወቀው፣ የቆሰሉት ሰዎች የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ ከተደረገላቸው በኋላ በ2020-2022 በነበረው የትግራይ ጦርነት የተፈናቀሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደሚገኙበት እና 15 ኪሎ ሜትር ሱዳን ውስጥ ወደሚገኘው አል-ሀሻባ ተዛውረዋል። በሱዳን በኩል የሚገኙ የድንበር አካባቢ ነዋሪዎች በውጊያው ወቅት ከባድ ፍንዳታዎች እና ተከታታይ የተኩስ ልውውጦች ሲሰሙ እንደነበር ዘግበዋል።
ከድንበሩ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዋድ አል-ሁለይዋ የተባለች መንደር ነዋሪ የሆነ የዓይን እማኝ፣ ቅዳሜ ማለዳ ላይ ሶስት ኃይለኛ ፍንዳታዎችን መስማቱን ተናግሯል። እማኙ አክሎም፣ ከቀኑ 10፡30 ገደማ ላይ ከባድ የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር እና በአቅራቢያው የምትገኘው የአል-ቁዳይማ መንደር ነዋሪዎች የሰቲት ወንዝን አቋርጠው መሸሻቸውን አስረድቷል። በሀምዳይት የሚገኝ ሌላ የዓይን እማኝ በበኩሉ፣ ቅዳሜን ሙሉ ፍንዳታዎች ይሰሙ እንደነበር እና ከሀምዳይት በስተደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ አውሮፕላኖች ሲበሩ መመልከቱን ገልጿል።
ይህ የሰሞኑ ግጭት የተከሰተው በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው ግንኙነት ሻክሮ በሚገኝበት ወቅት መሆኑ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ባለፈው ግንቦት ወር ኢትዮጵያ የሱዳን ጦር ከህወሓት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ቅጥረኞች ይደግፋል ስትል የከሰሰች ሲሆን፣ ሱዳን በበኩሏ ኢትዮጵያ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጋር በመቀናጀት ከግዛቷ የድሮን ጥቃቶች እንዲፈጸሙ ፈቅዳለች የሚል ክስ አቅርባለች። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቀረበባትን ክስ ብታስተባብልም፣ የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) ዋነኛ ደጋፊ ናት ተብላ ትከሰሳለች።
አንድ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባል እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ ጦር እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ከባድ የጦር መሳሪያዎች እና ድሮኖች የታከሉበት ውጊያ በምዕራብ ትግራይ፣ ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ሸረሪና በተባለችው አካባቢ ቅዳሜ ማለዳ ላይ የተቀሰቀሰ ሲሆን፣ እስከ እሁድ ንጋት 11፡00 ሰዓት (5:00 am) ድረስ ቀጥሎ ነበር። ቅዳሜ ዕለት ህወሓት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስትን ሰፋፊ የእግረኛ ጦር ጥቃቶችን ፈጽሞብኛል ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ ባለስልጣናት ለዚህ ክስ ወዲያውኑ የሰጡት ምላሽ የለም። ኤኤፍፒ የህወሓትን ክሶች በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥም ሆነ በሸረሪና ውጊያ ውስጥ የተሳተፉትን ኃይሎች በግልጽ መለየት አለመቻሉን ዘግቧል።
በድንበር ከተማዋ ሀምዳይት የሚገኝ አንድ የሱዳን የጸጥታ ምንጭ፣ ከትግራይ ወደ ሱዳን ከገቡት ሰዎች መካከል የቆሰሉ ተዋጊዎች እንደሚገኙበት ገልጿል። በድንበር ጤና ጣቢያ የሚገኝ የህክምና ምንጭ እንዳስታወቀው፣ የቆሰሉት ሰዎች የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ ከተደረገላቸው በኋላ በ2020-2022 በነበረው የትግራይ ጦርነት የተፈናቀሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደሚገኙበት እና 15 ኪሎ ሜትር ሱዳን ውስጥ ወደሚገኘው አል-ሀሻባ ተዛውረዋል። በሱዳን በኩል የሚገኙ የድንበር አካባቢ ነዋሪዎች በውጊያው ወቅት ከባድ ፍንዳታዎች እና ተከታታይ የተኩስ ልውውጦች ሲሰሙ እንደነበር ዘግበዋል።
ከድንበሩ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዋድ አል-ሁለይዋ የተባለች መንደር ነዋሪ የሆነ የዓይን እማኝ፣ ቅዳሜ ማለዳ ላይ ሶስት ኃይለኛ ፍንዳታዎችን መስማቱን ተናግሯል። እማኙ አክሎም፣ ከቀኑ 10፡30 ገደማ ላይ ከባድ የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር እና በአቅራቢያው የምትገኘው የአል-ቁዳይማ መንደር ነዋሪዎች የሰቲት ወንዝን አቋርጠው መሸሻቸውን አስረድቷል። በሀምዳይት የሚገኝ ሌላ የዓይን እማኝ በበኩሉ፣ ቅዳሜን ሙሉ ፍንዳታዎች ይሰሙ እንደነበር እና ከሀምዳይት በስተደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ አውሮፕላኖች ሲበሩ መመልከቱን ገልጿል።
ይህ የሰሞኑ ግጭት የተከሰተው በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው ግንኙነት ሻክሮ በሚገኝበት ወቅት መሆኑ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ባለፈው ግንቦት ወር ኢትዮጵያ የሱዳን ጦር ከህወሓት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ቅጥረኞች ይደግፋል ስትል የከሰሰች ሲሆን፣ ሱዳን በበኩሏ ኢትዮጵያ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጋር በመቀናጀት ከግዛቷ የድሮን ጥቃቶች እንዲፈጸሙ ፈቅዳለች የሚል ክስ አቅርባለች። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቀረበባትን ክስ ብታስተባብልም፣ የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) ዋነኛ ደጋፊ ናት ተብላ ትከሰሳለች።
3 days ago
ኢትዮጵያ ሆይ ! - ስደተኛው ልጅሽ ከ27 ዓመታት በኋላ መጥቷል! - ደስ ይበልሽ!"
· አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ፦ የሰዎች ህመም የሚሰማቸው፣ ተስፋን በተግባር የሚተረጉሙት ስራ ፈጣሪ
“Life’s most persistent and urgent question is, 'What are you doing for others?'”
(የህይወት ዘወተር እና አጣዳፊው ጥያቄ፦ ‘ለሌሎች ሰዎች ምን እያደረግክ ነው?’ የሚለው ነው።)
— ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር
በማህበረሰብ ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶችን አይቶ ከመቆጨት ይልቅ የመፍትሔ አካል ለመሆን መነሳት የትልልቅ ሰዎች መለያ ባህሪይ ነው። በትውልደ ኢትዮጵያዊው ስራ ፈጣሪ አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ዘንድም የሚታየው ይህ ህያው እውነት ነው፤ ጥበብን፣ የበጎ አድራጎት መንፈስን እና ዘመናዊ የህክምና አገልግሎትን በማስተሳሰር በሀገራችን ልዩ የለውጥ አሻራ በማስቀመጥ ላይ ይገኛሉ።
የተድላ አምቡላንስ መወለድ፦
የህይወት አድን አገልግሎት ራዕይ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በሀገራችን በህክምና ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትልቅ ክፍተት በጥናት በመረዳት ነው "ተድላ አምቡላንስን" ወደ ስራ ያስገቡት። በተለይም አካል ጉዳተኞች፣ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት (ኦቲዝም) ያለባቸው፣ የዳያሊሲስ ህመምተኞች እና አረጋውያን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ የሚያጋጥማቸውን የእንቅስቃሴ እና የትራንስፖርት እንግልት በመመልከት፣ ደረጃውን የጠበቀና ዘመናዊ የድንገተኛ እና ድንገተኛ ያልሆነ የህክምና መጓጓዣ አገልግሎት እንዲመሰረት አድርገዋል።
ድርጅቱ ከንግድ ስራ በላይ የማህበረሰብ አለኝታነትን መርሁ በማድረግ፦
· ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ያቀረበ፣
· በገንዘብም ሆነ በአገልግሎት ደረጃ አቅም የሌላቸውን ለመደገፍ የተጋ፣
· ለሁሉ አቀፍ ተደራሽነትና ለዜጎች ክብር የቆመ ተቋም ሆኖ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።
“The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others.”
(ራስህን ለማግኘት የሚቻለው የተሻለው መንገድ በሌሎች አገልግሎት ውስጥ ራስህን ስትሰጥ ነው።)
— ማሃትማ ጋንዲ
“ማንም የላት”፦
ጥበብ ለሰብአዊነት እና ለማህበራዊ ንቅናቄ
አቶ ሳሚ ከስራ ፈጣሪነታቸው ባሻገር፣ ጥበብ ለማህበራዊ ለውጥ ያላትን ትልቅ ሀይል በመረዳት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ “ማንም የላት” የተሰኘውን ታሪካዊ የኅብረት ዜማ ፕሮዲዩስ አድርገዋል።
ይህ ስራ በግጥም ናትናኤል ግርማቸው፣ በዜማ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ በቅንብር ታምሩ አማረ (ቶሚ) እንዲሁም በዳይሬክቲንግ ነፃዓለም አብዲ የተቃኘ ሲሆን፤ ድምፃውያን ማስተዋል እያዩ፣ ሄዋን ገብረወልድ፣ ሀና ግርማ እና አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) ድምፃቸውን ሰጥተውበታል። ከ50 በላይ የሙያ አጋሮች የተሳተፉበት ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ ህብረተሰቡን ስሜታዊ ጉዳት ውስጥ ሳይከት በደማቅ ቅንብር የችግሩን አሳሳቢነትና የለውጥ አስፈላጊነት ያሳያል።
አካል ጉዳተኝነት የችግር ምንጭ ሳይሆን፣ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እና የትራንስፖርት እጥረት ዋናው ክፍተት መሆኑን ማሳወቅ ነው። “ማንም የላት” የሚለውን ስሜት “እኛ አለንላት!”በሚል አዎንታዊ ምላሽ ለመተካት ያለመ ማህበራዊ ንቅናቄ ነው።
አቶ ሳሚ ካህሳይ እና ድርጅታቸው ተድላ አምቡላንስ ቃላቸውን በተግባር በማስመስከር፤ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ በተደረገ ስነ-ስርዓት፦የሙዚቃ ቪዲዮውን ገቢ፦ በሰይፉ ኦን ኢቢኤስ (Seifu on EBS) የዩቲዩብ ቻናል ተለቆ የሚሰበሰበው ሙሉ ገቢ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማዕከል እንዲሆን አስረክበው ነበር።
በርካታ ዊልቸሮች፣ ዘይት፣ ላርጎ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለመቄዶንያ መስራች ለዶ/ር ቢንያም በለጠ በአካል አስረክበዋል።
ተድላ አምቡላንስ ለማንኛውም ሰዓት ለመቄዶንያ ማዕከል ነፃ የአምቡላንስ አገልግሎት ለመስጠት በይፋ ቃል ገብተዋል።
የአቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ህልም በዋና ከተማው አዲስ አበባ ብቻ የተገደበ አይደለም። በክልሎች፣ በገጠራማ አካባቢዎች እና ክፍለ ሀገራት የሚኖሩ፣ አማራጭ ያጡ ዜጎች ዘንድ ይሄው ዘመናዊና የተከበረ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲደርስ ከመንግስት እና ከተለያዩ አካላት ጋር በትስስር ለመስራት አቅደዋል።
“No one has ever become poor by giving.”
(መስጠት ማንም ሰው ደሃ አያደርግም።)
— አን ፍራንክ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ በስራ ፈጠራቸው ሀገራዊ ክፍተትን የደፈኑ፣ በጥበብ ስራቸው የማህበረሰብ ህሊናን ያነቁ፣ በበጎ አድራጎታቸው ደግሞ የብዙዎችን እምባ ያበሱ የዘመናችን አርአያ ናቸው።
ተድላ አምቡላንስ “ሕይወትን ለማስቀጠል እየመጣን ነው!” በሚለው መሪ ቃሉ፣ የብዙዎችን ህይወት የመታደግ እና ተስፋ የመንዛት ታላቅ ሀገራዊ አገልግሎቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።
መደምደሚያ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ከ 27 ዓመታት ሰድት በኋላ አገር ቤት መጥተዋል። የእናት ሀገር ኢትዮጵያ ጥሪ ተቀብለው "እናቴ፤ ኢትዮጵያ ሆይ ! - ስደተኛው ልጅሽ ከ27 ዓመታት በኋላ መጥቷል! - ደስ ይበልሽ!"
የሀገር ጥሪን የመለሰ የዲያስፖራ ተሳትፎ፦ ህልምን በሀገር ላይ መተርጎም እንደነሳሚ ነው።
“Ask not what your country can do for you — ask what you can do for your country.”*
(ሀገሬ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን፣ እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ ብለህ ጠይቅ።)
— ጆን ኤፍ. ኬኔዲ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በምዕራቡ ዓለም (በአሜሪካ) ያካበቱትን የሙያ ልምድ፣ እውቀትና ሀብት ይዘው ወደ ሀገራቸው በመመለስ በህክምናና በትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩት በምክንያት ነው። መንግስትና የሀገር ጥሪ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያቀረቡትን ጥሪ መሰረት በማድረግ፣ በውጭ ሀገር ያዩትን ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥና ህልማቸውን በሀገራቸው ምድር ላይ ተግባራዊ አድርገዋል።
ይህ እርምጃቸው ክፍተቶችን በመሙላት ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተ ሲሆን፤ ሌሎች በውጭ ሀገር የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንም በየተሰማሩበት የሙያ ዘርፍ መጥተው ሀገራቸውንና ህዝባቸውን እንዲያገለግሉ ትልቅ ማነቃቂያና መንገድ ጠራጊ አርአያ የሚሆን ነው።
እናንት ያገሬ ልጆች
ግልጽነት ለዘላለም ይኑር!
መሥራት ጀግንነት ነው፤ ማድነቅ ደግሞ ጀግንነት ነው!
ለሥራቸው፤ ለሰበአዊነታቸው እጅ እንነሳለን!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
"ሕይወትን ማዳን፤ የመጀመሪያ ቅድሚያችን!"
– ተድላ አንቡላንስ
📞 ለአስቸኳይ ጥሪዎች 24 ሰዓት፣ 7 ቀናት ዝግጁ
☎️ +251 985 585 888
📞 8558
የማኅበራዊ ሚዲያ ሊንኮች ናቸው - ይከተሉን፦
Facebook: fb.com/Tedlaambulance
Instagram: instagram.com/tedlaambulance
Telegram: t.me/tedlaambulanceservice
TikTok: tiktok.com/tedlaambulance
· አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ፦ የሰዎች ህመም የሚሰማቸው፣ ተስፋን በተግባር የሚተረጉሙት ስራ ፈጣሪ
“Life’s most persistent and urgent question is, 'What are you doing for others?'”
(የህይወት ዘወተር እና አጣዳፊው ጥያቄ፦ ‘ለሌሎች ሰዎች ምን እያደረግክ ነው?’ የሚለው ነው።)
— ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር
በማህበረሰብ ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶችን አይቶ ከመቆጨት ይልቅ የመፍትሔ አካል ለመሆን መነሳት የትልልቅ ሰዎች መለያ ባህሪይ ነው። በትውልደ ኢትዮጵያዊው ስራ ፈጣሪ አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ዘንድም የሚታየው ይህ ህያው እውነት ነው፤ ጥበብን፣ የበጎ አድራጎት መንፈስን እና ዘመናዊ የህክምና አገልግሎትን በማስተሳሰር በሀገራችን ልዩ የለውጥ አሻራ በማስቀመጥ ላይ ይገኛሉ።
የተድላ አምቡላንስ መወለድ፦
የህይወት አድን አገልግሎት ራዕይ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በሀገራችን በህክምና ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትልቅ ክፍተት በጥናት በመረዳት ነው "ተድላ አምቡላንስን" ወደ ስራ ያስገቡት። በተለይም አካል ጉዳተኞች፣ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት (ኦቲዝም) ያለባቸው፣ የዳያሊሲስ ህመምተኞች እና አረጋውያን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ የሚያጋጥማቸውን የእንቅስቃሴ እና የትራንስፖርት እንግልት በመመልከት፣ ደረጃውን የጠበቀና ዘመናዊ የድንገተኛ እና ድንገተኛ ያልሆነ የህክምና መጓጓዣ አገልግሎት እንዲመሰረት አድርገዋል።
ድርጅቱ ከንግድ ስራ በላይ የማህበረሰብ አለኝታነትን መርሁ በማድረግ፦
· ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ያቀረበ፣
· በገንዘብም ሆነ በአገልግሎት ደረጃ አቅም የሌላቸውን ለመደገፍ የተጋ፣
· ለሁሉ አቀፍ ተደራሽነትና ለዜጎች ክብር የቆመ ተቋም ሆኖ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።
“The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others.”
(ራስህን ለማግኘት የሚቻለው የተሻለው መንገድ በሌሎች አገልግሎት ውስጥ ራስህን ስትሰጥ ነው።)
— ማሃትማ ጋንዲ
“ማንም የላት”፦
ጥበብ ለሰብአዊነት እና ለማህበራዊ ንቅናቄ
አቶ ሳሚ ከስራ ፈጣሪነታቸው ባሻገር፣ ጥበብ ለማህበራዊ ለውጥ ያላትን ትልቅ ሀይል በመረዳት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ “ማንም የላት” የተሰኘውን ታሪካዊ የኅብረት ዜማ ፕሮዲዩስ አድርገዋል።
ይህ ስራ በግጥም ናትናኤል ግርማቸው፣ በዜማ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ በቅንብር ታምሩ አማረ (ቶሚ) እንዲሁም በዳይሬክቲንግ ነፃዓለም አብዲ የተቃኘ ሲሆን፤ ድምፃውያን ማስተዋል እያዩ፣ ሄዋን ገብረወልድ፣ ሀና ግርማ እና አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) ድምፃቸውን ሰጥተውበታል። ከ50 በላይ የሙያ አጋሮች የተሳተፉበት ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ ህብረተሰቡን ስሜታዊ ጉዳት ውስጥ ሳይከት በደማቅ ቅንብር የችግሩን አሳሳቢነትና የለውጥ አስፈላጊነት ያሳያል።
አካል ጉዳተኝነት የችግር ምንጭ ሳይሆን፣ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እና የትራንስፖርት እጥረት ዋናው ክፍተት መሆኑን ማሳወቅ ነው። “ማንም የላት” የሚለውን ስሜት “እኛ አለንላት!”በሚል አዎንታዊ ምላሽ ለመተካት ያለመ ማህበራዊ ንቅናቄ ነው።
አቶ ሳሚ ካህሳይ እና ድርጅታቸው ተድላ አምቡላንስ ቃላቸውን በተግባር በማስመስከር፤ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ በተደረገ ስነ-ስርዓት፦የሙዚቃ ቪዲዮውን ገቢ፦ በሰይፉ ኦን ኢቢኤስ (Seifu on EBS) የዩቲዩብ ቻናል ተለቆ የሚሰበሰበው ሙሉ ገቢ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማዕከል እንዲሆን አስረክበው ነበር።
በርካታ ዊልቸሮች፣ ዘይት፣ ላርጎ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለመቄዶንያ መስራች ለዶ/ር ቢንያም በለጠ በአካል አስረክበዋል።
ተድላ አምቡላንስ ለማንኛውም ሰዓት ለመቄዶንያ ማዕከል ነፃ የአምቡላንስ አገልግሎት ለመስጠት በይፋ ቃል ገብተዋል።
የአቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ህልም በዋና ከተማው አዲስ አበባ ብቻ የተገደበ አይደለም። በክልሎች፣ በገጠራማ አካባቢዎች እና ክፍለ ሀገራት የሚኖሩ፣ አማራጭ ያጡ ዜጎች ዘንድ ይሄው ዘመናዊና የተከበረ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲደርስ ከመንግስት እና ከተለያዩ አካላት ጋር በትስስር ለመስራት አቅደዋል።
“No one has ever become poor by giving.”
(መስጠት ማንም ሰው ደሃ አያደርግም።)
— አን ፍራንክ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ በስራ ፈጠራቸው ሀገራዊ ክፍተትን የደፈኑ፣ በጥበብ ስራቸው የማህበረሰብ ህሊናን ያነቁ፣ በበጎ አድራጎታቸው ደግሞ የብዙዎችን እምባ ያበሱ የዘመናችን አርአያ ናቸው።
ተድላ አምቡላንስ “ሕይወትን ለማስቀጠል እየመጣን ነው!” በሚለው መሪ ቃሉ፣ የብዙዎችን ህይወት የመታደግ እና ተስፋ የመንዛት ታላቅ ሀገራዊ አገልግሎቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።
መደምደሚያ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ከ 27 ዓመታት ሰድት በኋላ አገር ቤት መጥተዋል። የእናት ሀገር ኢትዮጵያ ጥሪ ተቀብለው "እናቴ፤ ኢትዮጵያ ሆይ ! - ስደተኛው ልጅሽ ከ27 ዓመታት በኋላ መጥቷል! - ደስ ይበልሽ!"
የሀገር ጥሪን የመለሰ የዲያስፖራ ተሳትፎ፦ ህልምን በሀገር ላይ መተርጎም እንደነሳሚ ነው።
“Ask not what your country can do for you — ask what you can do for your country.”*
(ሀገሬ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን፣ እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ ብለህ ጠይቅ።)
— ጆን ኤፍ. ኬኔዲ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በምዕራቡ ዓለም (በአሜሪካ) ያካበቱትን የሙያ ልምድ፣ እውቀትና ሀብት ይዘው ወደ ሀገራቸው በመመለስ በህክምናና በትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩት በምክንያት ነው። መንግስትና የሀገር ጥሪ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያቀረቡትን ጥሪ መሰረት በማድረግ፣ በውጭ ሀገር ያዩትን ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥና ህልማቸውን በሀገራቸው ምድር ላይ ተግባራዊ አድርገዋል።
ይህ እርምጃቸው ክፍተቶችን በመሙላት ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተ ሲሆን፤ ሌሎች በውጭ ሀገር የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንም በየተሰማሩበት የሙያ ዘርፍ መጥተው ሀገራቸውንና ህዝባቸውን እንዲያገለግሉ ትልቅ ማነቃቂያና መንገድ ጠራጊ አርአያ የሚሆን ነው።
እናንት ያገሬ ልጆች
ግልጽነት ለዘላለም ይኑር!
መሥራት ጀግንነት ነው፤ ማድነቅ ደግሞ ጀግንነት ነው!
ለሥራቸው፤ ለሰበአዊነታቸው እጅ እንነሳለን!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
"ሕይወትን ማዳን፤ የመጀመሪያ ቅድሚያችን!"
– ተድላ አንቡላንስ
📞 ለአስቸኳይ ጥሪዎች 24 ሰዓት፣ 7 ቀናት ዝግጁ
☎️ +251 985 585 888
📞 8558
የማኅበራዊ ሚዲያ ሊንኮች ናቸው - ይከተሉን፦
Facebook: fb.com/Tedlaambulance
Instagram: instagram.com/tedlaambulance
Telegram: t.me/tedlaambulanceservice
TikTok: tiktok.com/tedlaambulance
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት ኦስቲን ከተማ በታዋቂው የአማዞን ኩባንያ ውስጥ በሶፍትዌር ኢንጂነርነት ሲሰራ የነበረው (ከዚህ ቀደም በኢንሳ ሰርቷል) ኢትዮጵያዊው ወጣት ያዴሳ እምሩ አጋ በኔቫዳ ግዛት በሚገኘው ታዋቂው 'ሌክ ታሆ' ሐይቅ ውስጥ ሰምጦ አሳዛኝ ህልፈተ ህይወት እንዳጋጠመው ትናንት በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን ይታወሳል። የካሊፎርኒያ ጋዜጦች ዛሬ ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘው ወጥተዋል። የሰላሳ ሁለት ዓመቱ ወጣት ያዴሳ ወደ ስፍራው ያቀናው ከቅርብ ጓደኞቹ ጋር በመሆን መንፈሳዊ የቤተክርስቲያን ኮንፈረንስ ላይ ለመካፈል እንደነበር የቅርብ ሰዎቹ እና ቤተሰቦቹ በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ሆነው ገልጸዋል።
አደጋው የደረሰው ሰኞ ምሽት አካባቢ ሲሆን፣ የዋሾ ካውንቲ የሸሪፍ ጽህፈት ቤት ፖሊሶች እንደገለጹት ወጣቱ ድንጋያማ ወደሆኑት የሐይቁ ክፍሎች እየዋኘ ከሄደ በኋላ በድንገት ከውሃው ወለል በታች ጠፍቶ ሊሰምጥ ችሏል። በአካባቢው የነበሩ ሰዎች በፍጥነት ወደ ውሃው በመግባት ያዴሳን አውጥተው የመጀመሪያ እርዳታ (CPR) ያደረጉለት ቢሆንም፣ እንዲሁም የድንገተኛ አደጋ ህክምና ባለሙያዎች ቦታው ላይ ደርሰው ህይወቱን ለመታደግ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርጉም በዚያው በስፍራው ህይወቱ ሊያልፍ መቻሉን ፖሊስ አረጋግጧል።
የያዴሳ ጓደኞች፣ ቤተሰቦች እና የቤተክርስቲያን አባላት ለቀብር ማስፈጸሚያ የሚሆን የገንዘብ ማሰባሰቢያ ያዘጋጁ ሲሆን፣ ወጣቱ እጅግ ትሁት፣ ፊቱ ሁልጊዜ በፈገግታ የተሞላ እና ለሰዎች አሳቢ እንደነበር መሰክረውለታል። እምነቱ በህይወቱ ውስጥ ትልቁን ስፍራ እንደሚይዝና ተፈጥሮን ማድነቅ እንዲሁም መጎብኘት ይወድ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት አስከሬኑን ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ለመላክ እና በአሜሪካም ሆነ በሀገር ቤት ለሚደረገው የቀብር ስነ-ስርዓት የሚወጣውን ወጪ ለመሸፈን ማህበረሰቡ ርብርብ እያደረገ ይገኛል። ቀጣሪው የአማዞን ኩባንያም የተወሰነውን ወጪ ለመሸፈን ከቤተሰቦቹ ጋር አብሮ እየሰራ መሆኑ ታውቋል።
የአካባቢው ፖሊስ አደጋውን ድንገተኛ የመስመጥ አደጋ ብሎ የመዘገበው ቢሆንም፣ የዋሾ ካውንቲ የህክምና መርማሪዎች ቢሮ ምርመራው ገና ስላላለቀ ትክክለኛውን የሞት መንስኤ ይፋ አለማድረጉን አሳውቋል። የባለሙያዎቹ ሪፖርት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለመውጣት ከአስር እስከ አስራ ሁለት ሳምንታት ሊፈጅ እንደሚችል ተገልጿል። ይህ አሳዛኝ ክስተት የተፈጠረው፣ በዚሁ ተመሳሳይ ሐይቅ ውስጥ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሌላ ሰው በውሃ ውስጥ አደጋ አጋጥሞት ህይወቱ ማለፉ ከተሰማ በኋላ መሆኑ ታውቋል።
የጎ ፈንድ ሚ ሊንኩን ኮመንት ላይ አስቀምጠናል።
አደጋው የደረሰው ሰኞ ምሽት አካባቢ ሲሆን፣ የዋሾ ካውንቲ የሸሪፍ ጽህፈት ቤት ፖሊሶች እንደገለጹት ወጣቱ ድንጋያማ ወደሆኑት የሐይቁ ክፍሎች እየዋኘ ከሄደ በኋላ በድንገት ከውሃው ወለል በታች ጠፍቶ ሊሰምጥ ችሏል። በአካባቢው የነበሩ ሰዎች በፍጥነት ወደ ውሃው በመግባት ያዴሳን አውጥተው የመጀመሪያ እርዳታ (CPR) ያደረጉለት ቢሆንም፣ እንዲሁም የድንገተኛ አደጋ ህክምና ባለሙያዎች ቦታው ላይ ደርሰው ህይወቱን ለመታደግ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርጉም በዚያው በስፍራው ህይወቱ ሊያልፍ መቻሉን ፖሊስ አረጋግጧል።
የያዴሳ ጓደኞች፣ ቤተሰቦች እና የቤተክርስቲያን አባላት ለቀብር ማስፈጸሚያ የሚሆን የገንዘብ ማሰባሰቢያ ያዘጋጁ ሲሆን፣ ወጣቱ እጅግ ትሁት፣ ፊቱ ሁልጊዜ በፈገግታ የተሞላ እና ለሰዎች አሳቢ እንደነበር መሰክረውለታል። እምነቱ በህይወቱ ውስጥ ትልቁን ስፍራ እንደሚይዝና ተፈጥሮን ማድነቅ እንዲሁም መጎብኘት ይወድ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት አስከሬኑን ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ለመላክ እና በአሜሪካም ሆነ በሀገር ቤት ለሚደረገው የቀብር ስነ-ስርዓት የሚወጣውን ወጪ ለመሸፈን ማህበረሰቡ ርብርብ እያደረገ ይገኛል። ቀጣሪው የአማዞን ኩባንያም የተወሰነውን ወጪ ለመሸፈን ከቤተሰቦቹ ጋር አብሮ እየሰራ መሆኑ ታውቋል።
የአካባቢው ፖሊስ አደጋውን ድንገተኛ የመስመጥ አደጋ ብሎ የመዘገበው ቢሆንም፣ የዋሾ ካውንቲ የህክምና መርማሪዎች ቢሮ ምርመራው ገና ስላላለቀ ትክክለኛውን የሞት መንስኤ ይፋ አለማድረጉን አሳውቋል። የባለሙያዎቹ ሪፖርት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለመውጣት ከአስር እስከ አስራ ሁለት ሳምንታት ሊፈጅ እንደሚችል ተገልጿል። ይህ አሳዛኝ ክስተት የተፈጠረው፣ በዚሁ ተመሳሳይ ሐይቅ ውስጥ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሌላ ሰው በውሃ ውስጥ አደጋ አጋጥሞት ህይወቱ ማለፉ ከተሰማ በኋላ መሆኑ ታውቋል።
የጎ ፈንድ ሚ ሊንኩን ኮመንት ላይ አስቀምጠናል።
Sponsored by
Surafel
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በዚህ ክረምት... ጥቂት የአሜሪካ የሃይማኖት አባቶች (ረቢዎች) በኢትዮጵያ የሚገኙትን ቀሪ የአይሁድ ማህበረሰቦችን ለመጎብኘት ለአንድ ሳምንት ያህል በሀገሪቱ ቆይታ አድርገዋል። ከጎብኚዎቹ አንዱ ያጋሩት እማኝነት እንደሚያሳየው፣ ጉዞው ዓይን ገላጭ እና የህይወት አመለካከትን የሚቀይር ነበር። ከከባድ ድህነት ጋር የሚኖረው ይህ ማህበረሰብ፣ ልብ በሚነካ ደግነት፣ ጥልቅ ሃይማኖታዊ ትጋት እና ጠንካራ ተስፋ የታጀበ መሆኑን ጎብኚዎቹ መስክረዋል።
ጎብኚዎቹ በተለይ 14,000 የሚጠጉ የአይሁድ ማህበረሰብ አባላት በሚገኙባት እና በከፍተኛ ድህነት ውስጥ በምትገኘው ጎንደር ያሳለፉት የሁለት ቀናት ቆይታ እጅግ ጥልቅ ስሜት የፈጠረባቸው መሆኑን ገልጸዋል። ማህበረሰቡ የሚኖርባቸው ቤቶች ከጭቃ እና ከእንጨት የተሰሩ፣ አንዲት አልጋ ብቻ የምትገኝባቸው ጠባብ ክፍሎች ቢሆኑም፤ በርካታ የቤተሰብ አባላትን አቅፈው ይዘዋል። የመብራት መቆራረጥ በብዛት ቢኖርም ቀኑን ሙሉ አገልግሎት የሚሰጠውን ነጻ የጤና ጣቢያቸውን፣ እንዲሁም ምንም ዓይነት የኤሌክትሪክ ብርሃን በሌለበት፣ ወለሉ አፈር በሆነ እና በድንኳን በተከበበ ጠባብ ክፍል ውስጥ ልጆቻቸው በከፍተኛ ትጋት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ መመልከታቸውን አሜሪካዊው ረቢ አስረድተዋል።
በአንድ ጊዜ ከ1,000 በላይ ምዕመናን ተራ በተራ በሚገቡበት ምኩራብ (የአይሁዶች ጸሎት ቤት) ውስጥ የሚደረገው ጸሎት እጅግ አስደናቂ እንደነበር ተገልጿል። በጸሎቱ ወቅት ምዕመናኑ ምንም ዓይነት ድምጽ ሳያወጡ፣ 'ሀዛን' (የጸሎት መሪው) በአማርኛ እና በዕብራይስጥ ቋንቋዎች የሚያሰማውን ጸሎት በከፍተኛ ትኩረት ያዳምጣሉ። ለሙሉ ማህበረሰቡ ጥቂት የጸሎት መጽሐፍት (Siddurim) ብቻ ቢኖሩም፣ ጸሎተኞቹ በሙሉ በእጃቸው አንድ ነገር አጥብቀው ይዘው ነበር። ከአንድ ሰዓት ተኩል የጸሎት መርሃ-ግብር በኋላ፣ በእጃቸው የያዙት ምን እንደሆነ ሲጠየቁ፣ ወደ እስራኤል ያቀኑ እና የተራራቋቸውን የቤተሰቦቻቸውን ፎቶግራፎች አሳዩአቸው። ከእነዚህ ቤተሰቦቻቸው መካከል አንዳንዶቹ በእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ውስጥ እያገለገሉ ህይወታቸው ያለፈ ናቸው።
እነዚህ ማህበረሰቦች ከከባድ ድህነት ጋር ቢታገሉም፣ ጎብኚዎቹ "ምን እንድናደርግላችሁ ትፈልጋላችሁ?" ብለው ሲጠይቋቸው የመጀመሪያ ምርጫቸው ገንዘብ አልነበረም። ከዚህ ይልቅ የሃይማኖት ትምህርት ድጋፍ (እንደ ሜዙዛ አጻጻፍ እና የኮሸር እርድ ያሉ) እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል። ማህበረሰቡ ባለው ጥቂት ነገር የመስጠት ባህሉ የዳበረ ነው። በማህበረሰቡ አባላት የተዘጋጁ ምግቦችን በነጻ የሚያከፋፍሉበትን ማዕከል የጎበኙት አሜሪካውያኑ፣ ማህበረሰቡ ራሱ የሰራቸውን ውብ ሻርፖች በስጦታ ሲበረከትላቸው በደስታ አጨብጭበዋል። ይሁን እንጂ፣ የነዋሪዎቹ ትልቁ እና ዋነኛው ህልም፣ በከፍተኛ ናፍቆት ወደ እስራኤል (Aliyah) መጓዝ ነው።
ማህበረሰቡን የሚረዳው 'የኢትዮጵያ አይሁዶችን የመታደግ ትግል' (SSEJ) የተሰኘው ተቋም፣ እጅግ ውስብስብ እና ከባድ የሆኑ የግብዓት ድልድል ውሳኔዎችን ለማሳለፍ ይገደዳል። ለምሳሌ እናቶች የልጆቻቸውን ጨርቅ ዳይፐር አጥበው ለመጠቀም ሳሙና አጥብቀው ቢለምኑም፣ ሳሙና ከተገዛ በምግብ እጥረት ለሚሰቃዩ ልጆች የሚሆን የምግብ በጀት ይቀንሳል። በሌላ በኩል በህጻናት ሞት መብዛት ምክንያት አዲስ የመቃብር ቦታ ቢያስፈልጋቸውም፣ ይህንን ለማድረግ ግን አቅሙን ያልቻለውን የጤና ክሊኒክ ማስፋፊያ በጀት መሰረዝን ይጠይቃል። በዚህም የተነሳ ክሊኒኩ በአሁኑ ሰዓት ህክምና መስጠት የሚችለው ከ18 ዓመት በታች እና ከ50 ዓመት በላይ ለሆኑት ብቻ ሆኗል። ቀደም ሲል ከ5 ዓመት በታች ያሉ ህጻናትን ይመግቡ የነበረ ሲሆን፣ አሁን ባለው የበጀት እጥረት መመገብ የሚችሉት ከ3 ዓመት በታች ያሉትን ብቻ ነው።
ከእነዚህ የዕለት ተዕለት ፈተናዎች እና የኢኮኖሚ እጥረቶች በተጨማሪ፣ ማህበረሰቡ በዓለም አቀፉ የአይሁድ ሚዲያ ሽፋን ያላገኙ ተደጋጋሚ የእገታ ወንጀሎች ሰለባ መሆኑም ተጠቁሟል። የልዑካን ቡድኑ ከእስራኤል አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ንጉሴ ጋር ያደረጉት ውይይት የችግሩን ስፋት ይበልጥ እንዲገነዘቡ ያደረጋቸው ሲሆን፤ በአሜሪካውያኑ ረቢዎች እይታ፣ ይህ ጉብኝት የኢትዮጵያ አይሁዶች ያላቸውን አስገራሚ ጥንካሬ፣ ደግነት እና ጽናት ያሳየ የማይረሳ የህይወት ተሞክሮ ሆኖ አልፏል።
ጎብኚዎቹ በተለይ 14,000 የሚጠጉ የአይሁድ ማህበረሰብ አባላት በሚገኙባት እና በከፍተኛ ድህነት ውስጥ በምትገኘው ጎንደር ያሳለፉት የሁለት ቀናት ቆይታ እጅግ ጥልቅ ስሜት የፈጠረባቸው መሆኑን ገልጸዋል። ማህበረሰቡ የሚኖርባቸው ቤቶች ከጭቃ እና ከእንጨት የተሰሩ፣ አንዲት አልጋ ብቻ የምትገኝባቸው ጠባብ ክፍሎች ቢሆኑም፤ በርካታ የቤተሰብ አባላትን አቅፈው ይዘዋል። የመብራት መቆራረጥ በብዛት ቢኖርም ቀኑን ሙሉ አገልግሎት የሚሰጠውን ነጻ የጤና ጣቢያቸውን፣ እንዲሁም ምንም ዓይነት የኤሌክትሪክ ብርሃን በሌለበት፣ ወለሉ አፈር በሆነ እና በድንኳን በተከበበ ጠባብ ክፍል ውስጥ ልጆቻቸው በከፍተኛ ትጋት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ መመልከታቸውን አሜሪካዊው ረቢ አስረድተዋል።
በአንድ ጊዜ ከ1,000 በላይ ምዕመናን ተራ በተራ በሚገቡበት ምኩራብ (የአይሁዶች ጸሎት ቤት) ውስጥ የሚደረገው ጸሎት እጅግ አስደናቂ እንደነበር ተገልጿል። በጸሎቱ ወቅት ምዕመናኑ ምንም ዓይነት ድምጽ ሳያወጡ፣ 'ሀዛን' (የጸሎት መሪው) በአማርኛ እና በዕብራይስጥ ቋንቋዎች የሚያሰማውን ጸሎት በከፍተኛ ትኩረት ያዳምጣሉ። ለሙሉ ማህበረሰቡ ጥቂት የጸሎት መጽሐፍት (Siddurim) ብቻ ቢኖሩም፣ ጸሎተኞቹ በሙሉ በእጃቸው አንድ ነገር አጥብቀው ይዘው ነበር። ከአንድ ሰዓት ተኩል የጸሎት መርሃ-ግብር በኋላ፣ በእጃቸው የያዙት ምን እንደሆነ ሲጠየቁ፣ ወደ እስራኤል ያቀኑ እና የተራራቋቸውን የቤተሰቦቻቸውን ፎቶግራፎች አሳዩአቸው። ከእነዚህ ቤተሰቦቻቸው መካከል አንዳንዶቹ በእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ውስጥ እያገለገሉ ህይወታቸው ያለፈ ናቸው።
እነዚህ ማህበረሰቦች ከከባድ ድህነት ጋር ቢታገሉም፣ ጎብኚዎቹ "ምን እንድናደርግላችሁ ትፈልጋላችሁ?" ብለው ሲጠይቋቸው የመጀመሪያ ምርጫቸው ገንዘብ አልነበረም። ከዚህ ይልቅ የሃይማኖት ትምህርት ድጋፍ (እንደ ሜዙዛ አጻጻፍ እና የኮሸር እርድ ያሉ) እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል። ማህበረሰቡ ባለው ጥቂት ነገር የመስጠት ባህሉ የዳበረ ነው። በማህበረሰቡ አባላት የተዘጋጁ ምግቦችን በነጻ የሚያከፋፍሉበትን ማዕከል የጎበኙት አሜሪካውያኑ፣ ማህበረሰቡ ራሱ የሰራቸውን ውብ ሻርፖች በስጦታ ሲበረከትላቸው በደስታ አጨብጭበዋል። ይሁን እንጂ፣ የነዋሪዎቹ ትልቁ እና ዋነኛው ህልም፣ በከፍተኛ ናፍቆት ወደ እስራኤል (Aliyah) መጓዝ ነው።
ማህበረሰቡን የሚረዳው 'የኢትዮጵያ አይሁዶችን የመታደግ ትግል' (SSEJ) የተሰኘው ተቋም፣ እጅግ ውስብስብ እና ከባድ የሆኑ የግብዓት ድልድል ውሳኔዎችን ለማሳለፍ ይገደዳል። ለምሳሌ እናቶች የልጆቻቸውን ጨርቅ ዳይፐር አጥበው ለመጠቀም ሳሙና አጥብቀው ቢለምኑም፣ ሳሙና ከተገዛ በምግብ እጥረት ለሚሰቃዩ ልጆች የሚሆን የምግብ በጀት ይቀንሳል። በሌላ በኩል በህጻናት ሞት መብዛት ምክንያት አዲስ የመቃብር ቦታ ቢያስፈልጋቸውም፣ ይህንን ለማድረግ ግን አቅሙን ያልቻለውን የጤና ክሊኒክ ማስፋፊያ በጀት መሰረዝን ይጠይቃል። በዚህም የተነሳ ክሊኒኩ በአሁኑ ሰዓት ህክምና መስጠት የሚችለው ከ18 ዓመት በታች እና ከ50 ዓመት በላይ ለሆኑት ብቻ ሆኗል። ቀደም ሲል ከ5 ዓመት በታች ያሉ ህጻናትን ይመግቡ የነበረ ሲሆን፣ አሁን ባለው የበጀት እጥረት መመገብ የሚችሉት ከ3 ዓመት በታች ያሉትን ብቻ ነው።
ከእነዚህ የዕለት ተዕለት ፈተናዎች እና የኢኮኖሚ እጥረቶች በተጨማሪ፣ ማህበረሰቡ በዓለም አቀፉ የአይሁድ ሚዲያ ሽፋን ያላገኙ ተደጋጋሚ የእገታ ወንጀሎች ሰለባ መሆኑም ተጠቁሟል። የልዑካን ቡድኑ ከእስራኤል አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ንጉሴ ጋር ያደረጉት ውይይት የችግሩን ስፋት ይበልጥ እንዲገነዘቡ ያደረጋቸው ሲሆን፤ በአሜሪካውያኑ ረቢዎች እይታ፣ ይህ ጉብኝት የኢትዮጵያ አይሁዶች ያላቸውን አስገራሚ ጥንካሬ፣ ደግነት እና ጽናት ያሳየ የማይረሳ የህይወት ተሞክሮ ሆኖ አልፏል።
6 days ago
6 ነጥብ 4 ኪ.ግ የምትመዝን ህጻን ተወለደች
በቤንች ሸኮ ዞን አንዲት እናት 6 ነጥብ 4 ኪ.ግ የምትመዝን ህጻን በሰላም ተገላግላለች።
በዞኑ የአማን ሻሸቃ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ ሳይሉሽ ባህሩ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች በተደረገላት ክትትል ህጻኑን በቀዶ ህክምና መገላገሏን በሆስፒታሉ የማህጸንና ጽንስ ስፔሻሊስቱ ዶ/ር ቹቹ አረጋ ገልጸዋል።
ወ/ሮ ሳይሉሽ ባህሩ በተመሳሳይ ከ6 ዓመት በፊት 2ኛ ልጇን ስትወልድ 5 ኪ.ግ መሆኑንና በቀዶ ጥገና ህክምና እንደተገላገለች ገልጻለች።
Seledadotio
Seledadotio
በቤንች ሸኮ ዞን አንዲት እናት 6 ነጥብ 4 ኪ.ግ የምትመዝን ህጻን በሰላም ተገላግላለች።
በዞኑ የአማን ሻሸቃ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ ሳይሉሽ ባህሩ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች በተደረገላት ክትትል ህጻኑን በቀዶ ህክምና መገላገሏን በሆስፒታሉ የማህጸንና ጽንስ ስፔሻሊስቱ ዶ/ር ቹቹ አረጋ ገልጸዋል።
ወ/ሮ ሳይሉሽ ባህሩ በተመሳሳይ ከ6 ዓመት በፊት 2ኛ ልጇን ስትወልድ 5 ኪ.ግ መሆኑንና በቀዶ ጥገና ህክምና እንደተገላገለች ገልጻለች።
Seledadotio
Seledadotio
6 days ago
የሞተው ሕያው የሆነበት ማሩ ከዋሻ የሚፈስበት አስደናቂው ስፍራ
♦️ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም
#ethiopia | በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ምስራቅ በለሳ ወረዳ፣ ጎጋ ቀበሌ የሚገኘው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም፤ የቀደመ ታሪኩን ፣ የተፈጥሮ ግርማውንና ታአምራት በአንድ ላይ የያዘ ድንቅ መንፈሳዊ ስፍራ ነው።
አባቶች እንደሚያስረዱት የስፍራው የቀደመ መጠሪያ "ዛጅር ማኤል" ይሰኝ ነበር። ይህ ስም "ዛጅር" ማለት ውሃ በደረቅ አለት ላይ ፈንጥቆ የሚወጣበትን አቅጣጫ ሲያመላክት፣ "ማ" ዋሻውን፣ "ኤል" ደግሞ የሰማይ አምላክን በመወከል እግዚአብሔር በድንቅ ሁኔታ በደረቅ አለት ላይ ውሃ የፈነጠቀበት ስፍራ መሆኑን ይናገራሉ።
የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የስብከተ ወንጌል ኃላፊ እና ጸኃፊ አባ ብርሃነ ሠላም እንደሚገልጹት፣ የቦታው ተአምራዊ ጉዞ በይፋ ጎልቶ መታየት የጀመረው በ2013 ዓ.ም የጸበል አገልግሎት ሲጀመር ነው።
በተለይም የስፍራውን ስም ከአዲሱ ስያሜ ጋር ያያዘው ታዓምር በዚሁ ዘመን ተከስቷል። ከገዳሙ 12 ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ በምትገኘው ዙ ሐሙሲት ከተማ አቅራቢያ የምትኖር አንዲት ሴት በጽኑ ታማ ወደ ህክምና ከተወሰደች በኋላ በቃሬዛ ላይ እያለች ህይወቷ ያልፋል።
በወቅቱ የጸበሉ አስተዳዳሪ የነበሩት አባት እና ሌሎች ካህናት አስከሬኑን ይዘው በመንገድ ላይ ሳሉ የእግዚአብሔርን ኃይል በማመን ቅዱስ ጸበሉን አፍሰው ረጩባት። በዚያው ቅጽበት የሞተችው ሴት ትንፋሽ ተመልሶላት ተነሳች፤ ሙሉ ፈውስ አግኝታም ድንቅ ምስክርነቷን ሰጠች።
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ጸበሉ "ሙት አንሳ" የሚለውን ስያሜ አገኘ። በኋላም ከዋሻው በላይ ከሚንጠበጠበው ማር ጋር ተያይዞ "ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል እና ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም" ተብሎ መጠራት ጀመረ።
የገዳሙ መነኮሳት እንደሚናገሩት በዋሻው ጣሪያ ላይ ለዘመናት ሳይቆረጥ የቆየ ልዩ ማር ይገኛል። ይህ ማር በተለያዩ ጊዜያት በራዕይ "ተቆርጦ ለምእመናን ፈውስ ይሁን" የሚል መልእክት ይሰጥ የነበረ ቢሆንም፣ የቦታው ገደላማና አስፈሪ አቀማመጥ ማንም እንዲደፍረው አላደረገም።
ቆየት ብሎ መነኮሳቱ በጸሎትና በምህላ ሲገቡ ንቡ ቦታውን ለቆ ይወጣል። ማሩ አሁን ላይ እየተቆረጠ ለበርካታ ድውያናትና ምእመናን ዘላቂ ፈውስን በመስጠት ላይ ይገኛል።
ዛሬ ለቁጥር በርካታ የሆኑ መነኮሳት የሚኖሩበት ይህ ታላቅ ገዳም የተመሰረተው በአንድ አባት መንፈሳዊ ታዛዥነትና ጽናት ነው። አባ ብርሃነ ሠላም እንደሚያስረዱት፣ በ2009 ዓመተ ምህረት ግንቦት 21 ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ አባ ብርሃነ ማርያም ከድዊ አንሳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም ተነስተው ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄዱ በፊታቸው የተለየ ብርሃን እየመራቸው
ቦታው ይደርሳሉ።
ያን ብርሃን እየተከተሉ የሶስት ሰዓት መንገድ በእግር ተጉዘው አሁን ገዳሙ በሚገኝበት ስፍራ ሲደርሱ ብርሃኑ ተሰወረባቸው። በወቅቱ ምንም ዓይነት መኖሪያ ቤትና መጠለያ በሌለበት፣ የክረምቱ ዝናብና ቅዝቃዜ በበዛበት ወቅት አባታችን በእርጥብ ዋሻ ውስጥ ማደር ጀመሩ።
እግዚአብሔርም በቸርነቱ የሚያድሩበትን ስፍራ ደረቅ በማድረግ ጠበቃቸው፤ የዕለት ምግባቸውንም የአካባቢው ህዝብና ጸበልተኞች እያመጡ ያቀርቡላቸው ነበር።
የአባታችንን ትምህርትና ተአምራዊ ፈውሱን ያዩ በርካታ መንፈሳውያን ልጆች በየጊዜው ወደ ስፍራው በመምጣታቸው የምናኔ ሀሳብ በብዙዎች ህሊና ውስጥ ሰረፀ። አባ ብርሃነ ሠላም አያይዘው እንደሚገልጹት፣ በ2011 ዓመተ ምህረት በአካባቢው ሰበካ ጉባኤ ድጋፍ የተገዙ በሬዎችን በመጠቀም መሬት ማረስና የጋራ ኑሮ ተጀመረ። በ2013 ዓመተ ምህረት የመነኮሳቱ ቁጥር ከመቶ በላይ በመድረሱ የአካባቢው ህዝብና ካህናት ተመካክረው ቦታ በመስጠታቸው ትንሽ መቃኞ ተሠርቶ ታቦተ ሚካኤል ገባ።
በመጨረሻም በ2014 ዓመተ ምህረት መስከረም 29 ቀን በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቡጽዕ አቡነ ዮሐንስ አባታዊ ቡራኬና ውሳኔ ገዳም የመሆን ሙሉ ክብሩንና ስያሜውን አገኘ።
ይህን መንፈሳዊና ታሪካዊ ገዳም የሚገኘው ከአዲስ አበባ
በሰሜን አቅጣጫ 667 ኪሎ ሜትር፣ ከባህርዳር ከተማ 183 ኪሎ ሜትር፣ ከዞኑ ጎንደር ከተማ በአዲስ ዘመን - እብናት -ጎሃላ 192 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ከጎንደር ማክሰኚት- አረባያ -ጎሃላ 119 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም፤ በአባቶችና በእናቶች ጸሎትና በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ እስከ ዛሬ የቆየ፣ ለትውልድ የሚተርፍ ታላቅ መንፈሳዊ አደራ ነው።
ይህ ገዳም ከተመሠረተበት ጊዜ አንሥቶ በርካታ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ዛሬ ላይ ደርሷል። ከሰሞኑን በገዳሙና በአካባቢው በመዘዋወር እየተከናወኑ ያሉትን የልማት ሥራዎች ተመልክተናል፤ የተመለከትነውንም በተከታታይ ክፍሎች እናቀርብላችኋለን።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#mutansa #ethiopianmonastery #gondarethiopia #ethiopianorthodox #spiritualjourney
♦️ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም
#ethiopia | በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ምስራቅ በለሳ ወረዳ፣ ጎጋ ቀበሌ የሚገኘው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም፤ የቀደመ ታሪኩን ፣ የተፈጥሮ ግርማውንና ታአምራት በአንድ ላይ የያዘ ድንቅ መንፈሳዊ ስፍራ ነው።
አባቶች እንደሚያስረዱት የስፍራው የቀደመ መጠሪያ "ዛጅር ማኤል" ይሰኝ ነበር። ይህ ስም "ዛጅር" ማለት ውሃ በደረቅ አለት ላይ ፈንጥቆ የሚወጣበትን አቅጣጫ ሲያመላክት፣ "ማ" ዋሻውን፣ "ኤል" ደግሞ የሰማይ አምላክን በመወከል እግዚአብሔር በድንቅ ሁኔታ በደረቅ አለት ላይ ውሃ የፈነጠቀበት ስፍራ መሆኑን ይናገራሉ።
የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የስብከተ ወንጌል ኃላፊ እና ጸኃፊ አባ ብርሃነ ሠላም እንደሚገልጹት፣ የቦታው ተአምራዊ ጉዞ በይፋ ጎልቶ መታየት የጀመረው በ2013 ዓ.ም የጸበል አገልግሎት ሲጀመር ነው።
በተለይም የስፍራውን ስም ከአዲሱ ስያሜ ጋር ያያዘው ታዓምር በዚሁ ዘመን ተከስቷል። ከገዳሙ 12 ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ በምትገኘው ዙ ሐሙሲት ከተማ አቅራቢያ የምትኖር አንዲት ሴት በጽኑ ታማ ወደ ህክምና ከተወሰደች በኋላ በቃሬዛ ላይ እያለች ህይወቷ ያልፋል።
በወቅቱ የጸበሉ አስተዳዳሪ የነበሩት አባት እና ሌሎች ካህናት አስከሬኑን ይዘው በመንገድ ላይ ሳሉ የእግዚአብሔርን ኃይል በማመን ቅዱስ ጸበሉን አፍሰው ረጩባት። በዚያው ቅጽበት የሞተችው ሴት ትንፋሽ ተመልሶላት ተነሳች፤ ሙሉ ፈውስ አግኝታም ድንቅ ምስክርነቷን ሰጠች።
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ጸበሉ "ሙት አንሳ" የሚለውን ስያሜ አገኘ። በኋላም ከዋሻው በላይ ከሚንጠበጠበው ማር ጋር ተያይዞ "ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል እና ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም" ተብሎ መጠራት ጀመረ።
የገዳሙ መነኮሳት እንደሚናገሩት በዋሻው ጣሪያ ላይ ለዘመናት ሳይቆረጥ የቆየ ልዩ ማር ይገኛል። ይህ ማር በተለያዩ ጊዜያት በራዕይ "ተቆርጦ ለምእመናን ፈውስ ይሁን" የሚል መልእክት ይሰጥ የነበረ ቢሆንም፣ የቦታው ገደላማና አስፈሪ አቀማመጥ ማንም እንዲደፍረው አላደረገም።
ቆየት ብሎ መነኮሳቱ በጸሎትና በምህላ ሲገቡ ንቡ ቦታውን ለቆ ይወጣል። ማሩ አሁን ላይ እየተቆረጠ ለበርካታ ድውያናትና ምእመናን ዘላቂ ፈውስን በመስጠት ላይ ይገኛል።
ዛሬ ለቁጥር በርካታ የሆኑ መነኮሳት የሚኖሩበት ይህ ታላቅ ገዳም የተመሰረተው በአንድ አባት መንፈሳዊ ታዛዥነትና ጽናት ነው። አባ ብርሃነ ሠላም እንደሚያስረዱት፣ በ2009 ዓመተ ምህረት ግንቦት 21 ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ አባ ብርሃነ ማርያም ከድዊ አንሳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም ተነስተው ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄዱ በፊታቸው የተለየ ብርሃን እየመራቸው
ቦታው ይደርሳሉ።
ያን ብርሃን እየተከተሉ የሶስት ሰዓት መንገድ በእግር ተጉዘው አሁን ገዳሙ በሚገኝበት ስፍራ ሲደርሱ ብርሃኑ ተሰወረባቸው። በወቅቱ ምንም ዓይነት መኖሪያ ቤትና መጠለያ በሌለበት፣ የክረምቱ ዝናብና ቅዝቃዜ በበዛበት ወቅት አባታችን በእርጥብ ዋሻ ውስጥ ማደር ጀመሩ።
እግዚአብሔርም በቸርነቱ የሚያድሩበትን ስፍራ ደረቅ በማድረግ ጠበቃቸው፤ የዕለት ምግባቸውንም የአካባቢው ህዝብና ጸበልተኞች እያመጡ ያቀርቡላቸው ነበር።
የአባታችንን ትምህርትና ተአምራዊ ፈውሱን ያዩ በርካታ መንፈሳውያን ልጆች በየጊዜው ወደ ስፍራው በመምጣታቸው የምናኔ ሀሳብ በብዙዎች ህሊና ውስጥ ሰረፀ። አባ ብርሃነ ሠላም አያይዘው እንደሚገልጹት፣ በ2011 ዓመተ ምህረት በአካባቢው ሰበካ ጉባኤ ድጋፍ የተገዙ በሬዎችን በመጠቀም መሬት ማረስና የጋራ ኑሮ ተጀመረ። በ2013 ዓመተ ምህረት የመነኮሳቱ ቁጥር ከመቶ በላይ በመድረሱ የአካባቢው ህዝብና ካህናት ተመካክረው ቦታ በመስጠታቸው ትንሽ መቃኞ ተሠርቶ ታቦተ ሚካኤል ገባ።
በመጨረሻም በ2014 ዓመተ ምህረት መስከረም 29 ቀን በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቡጽዕ አቡነ ዮሐንስ አባታዊ ቡራኬና ውሳኔ ገዳም የመሆን ሙሉ ክብሩንና ስያሜውን አገኘ።
ይህን መንፈሳዊና ታሪካዊ ገዳም የሚገኘው ከአዲስ አበባ
በሰሜን አቅጣጫ 667 ኪሎ ሜትር፣ ከባህርዳር ከተማ 183 ኪሎ ሜትር፣ ከዞኑ ጎንደር ከተማ በአዲስ ዘመን - እብናት -ጎሃላ 192 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ከጎንደር ማክሰኚት- አረባያ -ጎሃላ 119 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም፤ በአባቶችና በእናቶች ጸሎትና በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ እስከ ዛሬ የቆየ፣ ለትውልድ የሚተርፍ ታላቅ መንፈሳዊ አደራ ነው።
ይህ ገዳም ከተመሠረተበት ጊዜ አንሥቶ በርካታ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ዛሬ ላይ ደርሷል። ከሰሞኑን በገዳሙና በአካባቢው በመዘዋወር እየተከናወኑ ያሉትን የልማት ሥራዎች ተመልክተናል፤ የተመለከትነውንም በተከታታይ ክፍሎች እናቀርብላችኋለን።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#mutansa #ethiopianmonastery #gondarethiopia #ethiopianorthodox #spiritualjourney
7 days ago
ብቸኝነት ያለባቸው ሰዎች ለከባድ የልብ በሽታ የመጋለጥ ዕድላቸው በ19 በመቶ እንደሚጨምር በአዲስ ጥናት ተመላከተ
ብቸኝነት የአእምሮ ጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የልብን መዋቅር በቀጥታ በመጉዳት ለከፋ የጤና ችግር የሚያጋልጥ አሳሳቢ ችግር መሆኑን በአሜሪካ የልብ ማህበር (AHA) ይፋ የተደረገ አንድ አዲስ ጥናት አመላክቷል።
ጥናቱ እንዳመለከተው፣ ብቸኝነት የሰውነትን የጭንቀት መጠንን በመጨመር የጭንቀት ሆርሞኖች (እንደ ኮርቲሶል ያሉ) በሰውነታችን ውስጥ እንዲጨምሩ ያደርጋል።
ይህ ከብቸኝነት የሚመነጭ ስነ-ልቦናዊ እና ማህበራዊ ጭንቀት ደግሞ፣ በጊዜ ሂደት የልብ ቫልቭን (Heart Valve) በመጉዳት ለከፋ የልብ ጤና መቃወስ እንደሚያጋልጥ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የተመራው ይህ የጥናት ቡድንአረጋግጧል።
በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ሀኪም የሆኑት ዶክተር ክሪስታል ዋይሊ ሴኔ እንዳሉት፤ “የህክምና ባለሙያዎች ታካሚዎቻቸውን ስለ ማህበራዊ ግንኙነቶቻቸው ሊጠይቋቸው ይገባል፤ ይህን አለማድረግ ታካሚዎችን ለከፋ የልብ ጤና እክል አልፎ ተርፎም ለሞት ሊያጋልጣቸው ይችላል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በተጨማሪም ብቸኛ የሆኑ ሰዎች ሲጋራ ማጨስን፣ ከመጠን በላይ አልኮል መጠጣትን እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግን የመሳሰሉ ጤናማ ያልሆኑ የአኗኗር ዘይቤዎችን በብዛት ስለሚከተሉ፣ ይህ ልምምድ ለልብ እና የደም ስር ጉዳት መፋጠን ተጨማሪ ምክንያት መሆኑ ተጠቁሟል።
የአሜሪካ ዋና የቀዶ ጥገና ሀኪም በፈረጆቹ 2023 ብቸኝነትን "የህዝብ ጤና ወረርሽኝ" ሲሉ ያወጁት ሲሆን፤ ችግሩ ያለዕድሜ የመሞት አደጋን በ26 በመቶ ከፍ እንደሚያደርገውና ይህም በቀን 15 ሲጋራዎችን ከማጨስ ጋር እኩል የሚመዘን ጉዳት እንዳለው መግለጻቸው ይታወሳል።
ይህ የችግሩ አሳሳቢነት የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ከአንድ ዓመት በፊት ካወጣው ሪፖርት ያስታወቀ ሲሆን ፣ ድርጅቱ ብቸኝነትን በየዓመቱ ከ871ሺህ በላይ ሰዎችን ያለዕድሜ የሚቀጥፍ ዓለም አቀፍ የጤና ስጋት አድርጎ ፈርጆታል።
በተጨማሪም፤ ከልብ በሽታ፣ ስትሮክ እና ድብርት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ይህ አሳሳቢ ችግር በየሰዓቱ 100 ሰዎችን ለሞት እንደሚዳርግ መግለጹ አይዘነጋም።
በመሆኑም የህክምና ባለሙያዎች 'የብቸኝነት' እንደ አእምሮ ጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የልብ እና የደም ስር የጤና ስጋት በመሆኑ ተገቢውን ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በጥናቱ አጽኖት ተሰጥቷል።
Seledadotio
Seledadotio
ብቸኝነት የአእምሮ ጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የልብን መዋቅር በቀጥታ በመጉዳት ለከፋ የጤና ችግር የሚያጋልጥ አሳሳቢ ችግር መሆኑን በአሜሪካ የልብ ማህበር (AHA) ይፋ የተደረገ አንድ አዲስ ጥናት አመላክቷል።
ጥናቱ እንዳመለከተው፣ ብቸኝነት የሰውነትን የጭንቀት መጠንን በመጨመር የጭንቀት ሆርሞኖች (እንደ ኮርቲሶል ያሉ) በሰውነታችን ውስጥ እንዲጨምሩ ያደርጋል።
ይህ ከብቸኝነት የሚመነጭ ስነ-ልቦናዊ እና ማህበራዊ ጭንቀት ደግሞ፣ በጊዜ ሂደት የልብ ቫልቭን (Heart Valve) በመጉዳት ለከፋ የልብ ጤና መቃወስ እንደሚያጋልጥ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የተመራው ይህ የጥናት ቡድንአረጋግጧል።
በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ሀኪም የሆኑት ዶክተር ክሪስታል ዋይሊ ሴኔ እንዳሉት፤ “የህክምና ባለሙያዎች ታካሚዎቻቸውን ስለ ማህበራዊ ግንኙነቶቻቸው ሊጠይቋቸው ይገባል፤ ይህን አለማድረግ ታካሚዎችን ለከፋ የልብ ጤና እክል አልፎ ተርፎም ለሞት ሊያጋልጣቸው ይችላል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በተጨማሪም ብቸኛ የሆኑ ሰዎች ሲጋራ ማጨስን፣ ከመጠን በላይ አልኮል መጠጣትን እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግን የመሳሰሉ ጤናማ ያልሆኑ የአኗኗር ዘይቤዎችን በብዛት ስለሚከተሉ፣ ይህ ልምምድ ለልብ እና የደም ስር ጉዳት መፋጠን ተጨማሪ ምክንያት መሆኑ ተጠቁሟል።
የአሜሪካ ዋና የቀዶ ጥገና ሀኪም በፈረጆቹ 2023 ብቸኝነትን "የህዝብ ጤና ወረርሽኝ" ሲሉ ያወጁት ሲሆን፤ ችግሩ ያለዕድሜ የመሞት አደጋን በ26 በመቶ ከፍ እንደሚያደርገውና ይህም በቀን 15 ሲጋራዎችን ከማጨስ ጋር እኩል የሚመዘን ጉዳት እንዳለው መግለጻቸው ይታወሳል።
ይህ የችግሩ አሳሳቢነት የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ከአንድ ዓመት በፊት ካወጣው ሪፖርት ያስታወቀ ሲሆን ፣ ድርጅቱ ብቸኝነትን በየዓመቱ ከ871ሺህ በላይ ሰዎችን ያለዕድሜ የሚቀጥፍ ዓለም አቀፍ የጤና ስጋት አድርጎ ፈርጆታል።
በተጨማሪም፤ ከልብ በሽታ፣ ስትሮክ እና ድብርት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ይህ አሳሳቢ ችግር በየሰዓቱ 100 ሰዎችን ለሞት እንደሚዳርግ መግለጹ አይዘነጋም።
በመሆኑም የህክምና ባለሙያዎች 'የብቸኝነት' እንደ አእምሮ ጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የልብ እና የደም ስር የጤና ስጋት በመሆኑ ተገቢውን ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በጥናቱ አጽኖት ተሰጥቷል።
Seledadotio
Seledadotio
7 days ago
ከቁሉቢ ገብርኤል ንግስ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ የነበሩ ሁለት የአንድ ቤተሰብ አባላት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ
በኦሮሚያ ክልል አለልቱ አካባቢ በደረሰ አሳዛኝ የትራፊክ አደጋ ከቁሉቢ ገብርኤል ንግስ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ የነበሩ ሁለት የአንድ ቤተሰብ አባላት ሕይወት ወዲያውኑ ማለፉ ተሰምቷል። የአሌልቱ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር መርድ ሙሉጌታ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ሐምሌ 21ቀን 2018 ከቀኑ ስምንት ሰዓት አደጋው ደርሷል።
በሠሜን ሸዋ ዞን አለሊቱ ወረዳ ጮሌ ቀበሌ ውስጥ፣ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-A-27185 ኢቲ
ጠጠር የጫነ ሲኖትራክ ከባድ ተሽከርካሪ ሌላ ተሽከርካሪ በመደረብ ለማለፍ ሲሞክር፣ ከሚኒባስ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው አደጋው ደርሷል።
በሚኒባስ ተሽከርካሪው ውስጥ ይጓዙ የነበሩት የደብረ ብርሐን ከተማ አጂፕ አካባቢ ነዋሪዎችና የአንድ ቤተሰብ አባላት ሲሆኑ፣ የቁሉቢ ገብርኤል ንግስ አንግሠው ወደ ቤታቸው ሲጓዙ አደጋው እንዳጋጠማቸው ገልፀዋል።በዚሁ አደጋ ወዲያው ሑለት ሴቶች ሲሞቱ ፣በሚኒባሱ ሹፌር ና ሁለት ህፃናት ላይ ከባድ ጉዳት በሌሎች አራት ሠዎች ላይ ደግሞ ቀላል አደጋ ስለደረሰበቸው በህክምና ላይ ይገኛሉ።
በአንዳንድ የማሕበራዊ ሚዲያ የሟቾች ቁጥር አራት ተብሎ ቢገለፅም እስካሑን ድረስ የደረሣቸው መረጃ እንደሌለ ኢንስፔክተር መርድ ሙሉጌታ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በኦሮሚያ ክልል አለልቱ አካባቢ በደረሰ አሳዛኝ የትራፊክ አደጋ ከቁሉቢ ገብርኤል ንግስ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ የነበሩ ሁለት የአንድ ቤተሰብ አባላት ሕይወት ወዲያውኑ ማለፉ ተሰምቷል። የአሌልቱ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር መርድ ሙሉጌታ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ሐምሌ 21ቀን 2018 ከቀኑ ስምንት ሰዓት አደጋው ደርሷል።
በሠሜን ሸዋ ዞን አለሊቱ ወረዳ ጮሌ ቀበሌ ውስጥ፣ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-A-27185 ኢቲ
ጠጠር የጫነ ሲኖትራክ ከባድ ተሽከርካሪ ሌላ ተሽከርካሪ በመደረብ ለማለፍ ሲሞክር፣ ከሚኒባስ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው አደጋው ደርሷል።
በሚኒባስ ተሽከርካሪው ውስጥ ይጓዙ የነበሩት የደብረ ብርሐን ከተማ አጂፕ አካባቢ ነዋሪዎችና የአንድ ቤተሰብ አባላት ሲሆኑ፣ የቁሉቢ ገብርኤል ንግስ አንግሠው ወደ ቤታቸው ሲጓዙ አደጋው እንዳጋጠማቸው ገልፀዋል።በዚሁ አደጋ ወዲያው ሑለት ሴቶች ሲሞቱ ፣በሚኒባሱ ሹፌር ና ሁለት ህፃናት ላይ ከባድ ጉዳት በሌሎች አራት ሠዎች ላይ ደግሞ ቀላል አደጋ ስለደረሰበቸው በህክምና ላይ ይገኛሉ።
በአንዳንድ የማሕበራዊ ሚዲያ የሟቾች ቁጥር አራት ተብሎ ቢገለፅም እስካሑን ድረስ የደረሣቸው መረጃ እንደሌለ ኢንስፔክተር መርድ ሙሉጌታ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
8 days ago
የኢሰመጉ 158ኛ ልዩ መግለጫ፡
በምስራቅ አርሲ ዞን በሃይማኖትና ማንነት ላይ ያነጣጠሩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መቀጠላቸውን ኢሰመጉ ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ሐምሌ 2018 ዓ.ም ባወጣው 158ኛ ልዩ መግለጫው፣ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በሚገኙ በርካታ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ሃይማኖትንና ማንነትን መሰረት ያደረጉ ከባድ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መፈጸማቸውን ገለጸ።
ተቋሙ ከመጋቢት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው የምርመራ ወቅት በተሰበሰቡ አስረጂዎች፣ በዞኑ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች በዋናነት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ላይ ያነጣጠረ የግድያ፣ የአካል ጉዳት፣ የእገታ፣ የመፈናቀል እና የንብረት ውድመት ድርጊት መፈጸማቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል።
የጥቃቶቹ ስፋትና የደረሰው ጉዳትበኢሰመጉ የምርመራ ግኝት መሰረት በተጠቀሱት ዓመታት ውስጥ በምስራቅ አርሲ ዞን ወረዳዎች በግድያ ህይወታቸውን ያጡ ሰላማዊ ሰዎች ቁጥር የሚከተለውን ይመስላል፦
መርቲ ወረዳ፦ 117 ሰዎች
-ሽርካ ወረዳ፦ 116 ሰዎች
-ጀጁ ወረዳ፦ 101 ሰዎች
-ሮቤ ወረዳ፦ 47 ሰዎች
-ጉና ወረዳ፦ 26 ሰዎች (በአንድ ጉድጓድ የተቀበሩ 5 ሰዎችን ጨምሮ)
-ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ፦ 20 ሰዎች
-አሰኮ ወረዳ፦ 5 ንጹሃን ዜጎች እና
4 የመንግስት ሚሊሻዎች
አርሲ ሲሬ ወረዳ፦ 3 ሰዎች
በተጨማሪም በህጻናትና አረጋውያን ላይ የከፋ የአካል ጉዳት መድረሱን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ በጉና ወረዳ በፈጸመ ጥቃት የ4 እና የ8 ዓመት ህጻናት በጥይት መመታታቸውንና የአንዱ ህጻን እግር ሊቆረጥ መቻሉን በአብነት ጠቅሷል።
እገታ፣ መፈናቀል እና የንብረት ውድመት
ኢሰመጉ ባቀረበው ዝርዝር መረጃ መሰረት፦
እገታ፦
በሮቤ ወረዳ 156 ሰዎች፣
በጀጁ 182 ሰዎች፣
በምርቲ 29 ሰዎች እንዲሁም
በሽርካ 39 ሰዎች ታግተው ከፍተኛ የገንዘብ ransom የተጠየቀባቸው ሲሆን
በርካቶቹ በገንዘብ ቢለቀቁም የበርካታ ታጋቾች ያሉበት ሁኔታ እስካሁን አይታወቅም።
መፈናቀል፦
በጥቃቱ ስጋት ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፤ ከጀጁ ወረዳ 6,216፣ ከሽርካ 3,746፣ ከአሰኮ 2,133፣ ከሮቤ 1,270 እና ከመርቲ 1,036 ሰዎች ተፈናቅለው በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኛሉ።
የንብረት ውድመት፦
በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መዘረፋቸውንና መቃጠላቸውን (ለምሳሌ በ101 ዓመት ዕድሜ ያለው የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን)፣ ቤቶች መፍረሳቸውንና መቃጠላቸውን እንዲሁም በርካታ የጋማና የቀንድ ከብቶች መዘረፋቸውን ሰነዱ ያመላክታል።
የህግ ግዴታዎችና የኢሰመጉ ጥሪ
ኢሰመጉ ድርጊቶቹ በስልታዊና በተስፋፋ መልኩ በሲቪል ህዝብ ላይ የተፈጸሙ በመሆናቸው በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች (Crimes Against Humanity) ባህሪ ያላቸው መሆኑን በመጠቆም፣ የፌደራል እና የኦሮሚያ ክልል መንግስታት የሚከተሉትን እርምጃዎች እንዲወስዱ ጥሪ አቅርቧል፦
ተጠያቂነትን ማረጋገጥ፦ በጥቃቱ የተሳተፉ ታጣቂዎችንና ሀላፊነታቸውን ያልተወጡ የጸጥታና የአስተዳደር አካላትን በአስቸኳይ ለህግ ማቅረብ።
ሰብዓዊ እርዳታና መልሶ ማቋቋም፦ ለተፈናቀሉ ዜጎች ህክምና ማቅረብ እንዲሁም በይስሙላ ሳይሆን በዘላቂ ሰላም ወደ ቀያቸው የሚመለሱበትን መንገድ ማመቻቸት።
የፌደራል መንግስት ጣልቃ ገብነት፦ የክልሉ መንግስት የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ካልቻለ፣ በህግ በተደነገገው መሰረት (አዋጅ ቁጥር 359/2003) የፌደራል መንግስት ጣልቃ በመግባት የዜጎችን ህይወት እንዲታደግ።
በምስራቅ አርሲ ዞን በሃይማኖትና ማንነት ላይ ያነጣጠሩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መቀጠላቸውን ኢሰመጉ ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ሐምሌ 2018 ዓ.ም ባወጣው 158ኛ ልዩ መግለጫው፣ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በሚገኙ በርካታ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ሃይማኖትንና ማንነትን መሰረት ያደረጉ ከባድ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መፈጸማቸውን ገለጸ።
ተቋሙ ከመጋቢት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው የምርመራ ወቅት በተሰበሰቡ አስረጂዎች፣ በዞኑ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች በዋናነት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ላይ ያነጣጠረ የግድያ፣ የአካል ጉዳት፣ የእገታ፣ የመፈናቀል እና የንብረት ውድመት ድርጊት መፈጸማቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል።
የጥቃቶቹ ስፋትና የደረሰው ጉዳትበኢሰመጉ የምርመራ ግኝት መሰረት በተጠቀሱት ዓመታት ውስጥ በምስራቅ አርሲ ዞን ወረዳዎች በግድያ ህይወታቸውን ያጡ ሰላማዊ ሰዎች ቁጥር የሚከተለውን ይመስላል፦
መርቲ ወረዳ፦ 117 ሰዎች
-ሽርካ ወረዳ፦ 116 ሰዎች
-ጀጁ ወረዳ፦ 101 ሰዎች
-ሮቤ ወረዳ፦ 47 ሰዎች
-ጉና ወረዳ፦ 26 ሰዎች (በአንድ ጉድጓድ የተቀበሩ 5 ሰዎችን ጨምሮ)
-ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ፦ 20 ሰዎች
-አሰኮ ወረዳ፦ 5 ንጹሃን ዜጎች እና
4 የመንግስት ሚሊሻዎች
አርሲ ሲሬ ወረዳ፦ 3 ሰዎች
በተጨማሪም በህጻናትና አረጋውያን ላይ የከፋ የአካል ጉዳት መድረሱን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ በጉና ወረዳ በፈጸመ ጥቃት የ4 እና የ8 ዓመት ህጻናት በጥይት መመታታቸውንና የአንዱ ህጻን እግር ሊቆረጥ መቻሉን በአብነት ጠቅሷል።
እገታ፣ መፈናቀል እና የንብረት ውድመት
ኢሰመጉ ባቀረበው ዝርዝር መረጃ መሰረት፦
እገታ፦
በሮቤ ወረዳ 156 ሰዎች፣
በጀጁ 182 ሰዎች፣
በምርቲ 29 ሰዎች እንዲሁም
በሽርካ 39 ሰዎች ታግተው ከፍተኛ የገንዘብ ransom የተጠየቀባቸው ሲሆን
በርካቶቹ በገንዘብ ቢለቀቁም የበርካታ ታጋቾች ያሉበት ሁኔታ እስካሁን አይታወቅም።
መፈናቀል፦
በጥቃቱ ስጋት ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፤ ከጀጁ ወረዳ 6,216፣ ከሽርካ 3,746፣ ከአሰኮ 2,133፣ ከሮቤ 1,270 እና ከመርቲ 1,036 ሰዎች ተፈናቅለው በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኛሉ።
የንብረት ውድመት፦
በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መዘረፋቸውንና መቃጠላቸውን (ለምሳሌ በ101 ዓመት ዕድሜ ያለው የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን)፣ ቤቶች መፍረሳቸውንና መቃጠላቸውን እንዲሁም በርካታ የጋማና የቀንድ ከብቶች መዘረፋቸውን ሰነዱ ያመላክታል።
የህግ ግዴታዎችና የኢሰመጉ ጥሪ
ኢሰመጉ ድርጊቶቹ በስልታዊና በተስፋፋ መልኩ በሲቪል ህዝብ ላይ የተፈጸሙ በመሆናቸው በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች (Crimes Against Humanity) ባህሪ ያላቸው መሆኑን በመጠቆም፣ የፌደራል እና የኦሮሚያ ክልል መንግስታት የሚከተሉትን እርምጃዎች እንዲወስዱ ጥሪ አቅርቧል፦
ተጠያቂነትን ማረጋገጥ፦ በጥቃቱ የተሳተፉ ታጣቂዎችንና ሀላፊነታቸውን ያልተወጡ የጸጥታና የአስተዳደር አካላትን በአስቸኳይ ለህግ ማቅረብ።
ሰብዓዊ እርዳታና መልሶ ማቋቋም፦ ለተፈናቀሉ ዜጎች ህክምና ማቅረብ እንዲሁም በይስሙላ ሳይሆን በዘላቂ ሰላም ወደ ቀያቸው የሚመለሱበትን መንገድ ማመቻቸት።
የፌደራል መንግስት ጣልቃ ገብነት፦ የክልሉ መንግስት የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ካልቻለ፣ በህግ በተደነገገው መሰረት (አዋጅ ቁጥር 359/2003) የፌደራል መንግስት ጣልቃ በመግባት የዜጎችን ህይወት እንዲታደግ።
8 days ago
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የዶ/ር በርናንድ እና ሲ/ር እማዋይሽ ጅምር ሆስፒታል ለሕዝብ አገልግሎት እንዲውል ስምምነት አደረገ
#ethiopia | በጎንደር ከተማ የተጀመረው የዶክተር በርናንድ አንደርሰን እና የሲስተር እማዋይሽ ገሪማ መታሰቢያ ጅምር ሆስፒታል ለኢትዮጵያ ህዝብ የጤና አገልግሎትና የምርምር ማዕከል ሆኖ እንዲቀጥል ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከኑዛዜ ወራሾች እና ተጠቃሚዎች ጋር የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነት በ2008 ዓ.ም ተጀምሮ የነበረውን ሀገራዊ አላማ ከውልና ማስረጃ እንዲሁም ከእንደራሴው አቶ ዳዊት ደርበው ጋር በመተባበር ዳር ለማድረስ ያስቻለ ምዕራፍ መሆኑ ነው።
በተደረገው ስምምነት መሠረት ሆስፒታሉ የማይሸጥ፣ የማይለወጥ፣ ቅርጽና ይዘቱ ሳይለወጥ እንዲሁም ስመ ንብረቱ ወደ ሌላ ሶስተኛ ወገን ሳይተላለፍ የለጋሾቹ የዘላለም መታሰቢያ ሆኖ እንዲኖር ዋስትና ይሰጣል።
የተከናወነው ስምምነት መሠረት ዩኒቨርሲቲው ህንጻውን አጠናቆ ለህዝብ የህክምና አገልግሎት፣ ለትምህርት እና ለምርምር ማዋል የሚችለውን ጠንካራ መሰረት የጣለ ሲሆን፣ በኑዛዜው የተገለጹት ተጠቃሚዎች መብቶችም ሙሉ በሙሉ እንዲከበሩ ተደርጓል።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሥራት አፀደወይን ለጋሾቹ ለህዝብ ጥቅም የለገሱት ይህ በጎ አድራጎት ለወደፊቱ ትውልድ ትልቅ አርአያ የሚሆንና የሀገሪቱን የጤና ዘርፍ እንዲሁም የህክምና ቱሪዝም የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸዋል።
የወራሾችን በመወከል ንግግር ያደረጉት አቶ ዳዊት ደርበው እንደገለጹት፣ በዕለቱ የተገኙበት ዋና ምክንያት በሲስተር ማዋይሽ ገሪማ ኑዛዜ መሠረት የተጀመረውን ሆስፒታል አጠናቀው ወደ ተግባር ለማዋል እንደሆነ አስረድተዋል።
እርሳቸውም በኑዛዜው እንደራሴ በመሆን የተሰጣቸውን ሙሉ ስልጣን በመጠቀም ሥራውን ለማስፈጸም እንደተገኙ ገልጸው፣ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ሲስተር ማዋይሽ በህይወት በነበረችበት ጊዜ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር አድርጋው የነበረውን ውል እንደገና በማነቃቃት የጀመሩትን ሂደት ለማጠናቀቅ መሆኑን አብራርተዋል።
ስምምነቱ ከተጠናቀቀ በኋላም ተሳታፊዎች የዶክተር በርናንድ አንደርሰን እና የሲስተር እማዋይሽ ገሪማ መታሰቢያ ሙዚየምን እንዲሁም የሆስፒታሉን ጅምር ግንባታ በጋራ ጎብኝተዋል።
#gondaruniversity #drbernardandsisteremawesh #gondar #ethiopia #healthcare #medicalresearch #legacy #publichealth
#ethiopia | በጎንደር ከተማ የተጀመረው የዶክተር በርናንድ አንደርሰን እና የሲስተር እማዋይሽ ገሪማ መታሰቢያ ጅምር ሆስፒታል ለኢትዮጵያ ህዝብ የጤና አገልግሎትና የምርምር ማዕከል ሆኖ እንዲቀጥል ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከኑዛዜ ወራሾች እና ተጠቃሚዎች ጋር የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነት በ2008 ዓ.ም ተጀምሮ የነበረውን ሀገራዊ አላማ ከውልና ማስረጃ እንዲሁም ከእንደራሴው አቶ ዳዊት ደርበው ጋር በመተባበር ዳር ለማድረስ ያስቻለ ምዕራፍ መሆኑ ነው።
በተደረገው ስምምነት መሠረት ሆስፒታሉ የማይሸጥ፣ የማይለወጥ፣ ቅርጽና ይዘቱ ሳይለወጥ እንዲሁም ስመ ንብረቱ ወደ ሌላ ሶስተኛ ወገን ሳይተላለፍ የለጋሾቹ የዘላለም መታሰቢያ ሆኖ እንዲኖር ዋስትና ይሰጣል።
የተከናወነው ስምምነት መሠረት ዩኒቨርሲቲው ህንጻውን አጠናቆ ለህዝብ የህክምና አገልግሎት፣ ለትምህርት እና ለምርምር ማዋል የሚችለውን ጠንካራ መሰረት የጣለ ሲሆን፣ በኑዛዜው የተገለጹት ተጠቃሚዎች መብቶችም ሙሉ በሙሉ እንዲከበሩ ተደርጓል።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሥራት አፀደወይን ለጋሾቹ ለህዝብ ጥቅም የለገሱት ይህ በጎ አድራጎት ለወደፊቱ ትውልድ ትልቅ አርአያ የሚሆንና የሀገሪቱን የጤና ዘርፍ እንዲሁም የህክምና ቱሪዝም የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸዋል።
የወራሾችን በመወከል ንግግር ያደረጉት አቶ ዳዊት ደርበው እንደገለጹት፣ በዕለቱ የተገኙበት ዋና ምክንያት በሲስተር ማዋይሽ ገሪማ ኑዛዜ መሠረት የተጀመረውን ሆስፒታል አጠናቀው ወደ ተግባር ለማዋል እንደሆነ አስረድተዋል።
እርሳቸውም በኑዛዜው እንደራሴ በመሆን የተሰጣቸውን ሙሉ ስልጣን በመጠቀም ሥራውን ለማስፈጸም እንደተገኙ ገልጸው፣ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ሲስተር ማዋይሽ በህይወት በነበረችበት ጊዜ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር አድርጋው የነበረውን ውል እንደገና በማነቃቃት የጀመሩትን ሂደት ለማጠናቀቅ መሆኑን አብራርተዋል።
ስምምነቱ ከተጠናቀቀ በኋላም ተሳታፊዎች የዶክተር በርናንድ አንደርሰን እና የሲስተር እማዋይሽ ገሪማ መታሰቢያ ሙዚየምን እንዲሁም የሆስፒታሉን ጅምር ግንባታ በጋራ ጎብኝተዋል።
#gondaruniversity #drbernardandsisteremawesh #gondar #ethiopia #healthcare #medicalresearch #legacy #publichealth
Sponsored by
Surafel
9 days ago
Seattle Update: የአሜሪካ ባለስልጣናት እንዳስታወቁት፣ እሁድ ዕለት በሲያትል ሴንተር በተካሄደው የ'ባይት ኦፍ ሲያትል' የምግብ ፌስቲቫል ላይ በተከፈተ ተኩስ የሁለት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ ሌሎች አምስት ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል። የሲያትል ከተማ ከንቲባ ኬቲ ዊልሰን አንድ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጸዋል። ስለ ተጠርጣሪው ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ እስካሁን አልወጣም። የሲያትል ፖሊስ ዲፓርትመንት ጉዳዩን እያጣራ መሆኑን አስታውቋል።የሲያትል እሳት አደጋ መከላከያ ክፍል እንዳስታወቀው፣ የመጀመሪያ የህክምና እና አደጋ ጊዜ እርዳታ ሰጪዎች ከምሽቱ 12 ሰዓት (6 p.m.) ገደማ በኋላ ወዲያውኑ ወደ ስፍራው ተሰማርተዋል።
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በ 'JAMA Network Open' ጆርናል ላይ የታተመ አዲስ ጥናት እንዳመለከተው፣ ከህዳር 2020 እስከ ህዳር 2022 የነበረው የትግራይ ጦርነት በመቀሌ ከተማ በሚሰጠው የኤችአይቪ ምርመራ እና ህክምና ላይ ከፍተኛ መስተጓጎል ፈጥሯል። በመቀሌ በሚገኙ ሰባት የጤና ተቋማት ውስጥ የ20 ዓመታት መረጃን እና 13 ሺህ 478 የኤችአይቪ ምርመራዎችን በመጠቀም የተሰራው ይህ ጥናት አሳሳቢ ግኝቶችን አሳይቷል።
በጥናቱ መሰረት በጦርነቱ ወቅት አዳዲስ የኤችአይቪ ምርመራዎች፣ ታካሚዎችን ከህክምና ጋር የማገናኘት እና የፀረ-ኤችአይቪ ህክምና አጀማመር ከ29 እስከ 32 በመቶ የሚደርስ ቅናሽ አሳይተዋል። በዚህ የህክምና አገልግሎት መቋረጥ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዱት ሴቶች እንዲሁም ከ0 እስከ 24 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ወጣቶች እና ህፃናት መሆናቸው ተመላክቷል።
በተጨማሪም ከመንግስት ተቋማት ይልቅ መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች በሚተዳደሩ የጤና ተቋማት ታካሚ የሆኑ ዜጎች ከፍተኛውን የአገልግሎት መቋረጥ አስተናግደዋል።
ከጦርነቱ ማብቃት በኋላ በአማካይ የህክምና አገልግሎቱ ወደ ቀድሞው የጦርነት ቅድመ-ሁኔታ የመመለስ አዝማሚያ ቢያሳይም፣ በጦርነቱ ወቅት የተፈጠረውን ከፍተኛ ክፍተት ግን ከሁለት ዓመታት በኋላም ማካካስ አልተቻለም። በጥናቱ ማጠቃለያ እንደተጠቆመው፣ በግጭት ወቅት እና ከዚያም በኋላ የሚዘረጉ የኤችአይቪ የህክምና ፕሮግራሞች በተለይም ለሴቶች፣ ለወጣቶች እና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ለሚደገፉ ተቋማት ልዩ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል።
በጥናቱ መሰረት በጦርነቱ ወቅት አዳዲስ የኤችአይቪ ምርመራዎች፣ ታካሚዎችን ከህክምና ጋር የማገናኘት እና የፀረ-ኤችአይቪ ህክምና አጀማመር ከ29 እስከ 32 በመቶ የሚደርስ ቅናሽ አሳይተዋል። በዚህ የህክምና አገልግሎት መቋረጥ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዱት ሴቶች እንዲሁም ከ0 እስከ 24 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ወጣቶች እና ህፃናት መሆናቸው ተመላክቷል።
በተጨማሪም ከመንግስት ተቋማት ይልቅ መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች በሚተዳደሩ የጤና ተቋማት ታካሚ የሆኑ ዜጎች ከፍተኛውን የአገልግሎት መቋረጥ አስተናግደዋል።
ከጦርነቱ ማብቃት በኋላ በአማካይ የህክምና አገልግሎቱ ወደ ቀድሞው የጦርነት ቅድመ-ሁኔታ የመመለስ አዝማሚያ ቢያሳይም፣ በጦርነቱ ወቅት የተፈጠረውን ከፍተኛ ክፍተት ግን ከሁለት ዓመታት በኋላም ማካካስ አልተቻለም። በጥናቱ ማጠቃለያ እንደተጠቆመው፣ በግጭት ወቅት እና ከዚያም በኋላ የሚዘረጉ የኤችአይቪ የህክምና ፕሮግራሞች በተለይም ለሴቶች፣ ለወጣቶች እና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ለሚደገፉ ተቋማት ልዩ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል።
11 days ago
በህይወት እያሉ ተመሰገኑ
(በዕዝራ እጅጉ)
.የመዲናዋ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና እንዲያገኙ ወሰነ
#ethiopia | አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ ዛሬ ጋቢ በተደረበላቸው ዕለት ደስታቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር።
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት እነዚህ ጉምቱ ባለሙያዎች ከ 35 አመት በላይ በትጋት ያገለገሉ ሲሆን በሙያ አጋሮቻቸው ተከበው አድናቆት ሲቸራቸው ውለዋል።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም ከ 4 ሰዓት ጀምሮ በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በተደረገው መርሀ ግብር የሚድያ ባለሙያዎች እና ወዳጆቻቸው ተገኝተው እኛም አመስጋኞቻችሁ ነን በማለት ለመርሀ ግብሩ ድምቀት ሰጥተዋል።
ባለሙያዎቹን ለማመስገን ራሱን የቻለ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን ይህም ኮሚቴ ባለሙያዎቹ በዘለቄታዊነት የሚታገዙበት መንገድ ያመቻቸ ነው።
ለዝግጅቱ መሳካት በተከፈተው የwhat is up ገፅ ኮሚቴው ውስጥ ተግባራቸውን የተወጡት ጥላሁን ካሣ ፣ሀብታሙ ድረስ ፣ሰለሞን ሀይለኢየሱስ፣ዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)፣ አለም ታደሰ፣ሠናይት ሀይሌ፣እሸቱ ገለቱ፣ ጌጡ ተመስገን እና ግደይ ገብረ ሲሆኑ እነርሱም በዕለቱ እንደተናገሩት ሥራው በአጭር ጊዜ ታስቦ ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ለአንጋፋ ባለሙያዎቹ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና የሚያገኙበት መንገድ ያመቻቸ ሲሆን ይህ የመረዳዳት ባህል ወደፊትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተነግሯል።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
"ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን "የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች እንደነበሩ በዕለቱ ምስክርነት የሰጡ ባልደረቦቻቸው የተናገሩ ሲሆን የምስጋና ቀን መዘጋጀቱ አዲስ የሚመጣውንም ባለሙያ የሚያበረታታ ነው ሲሉ ሀሣብ ሰንዝረዋል።
በዕለቱ የሚድያ ሥራን ከ1950ዎቹ ጀምሮ ያስቃኘ አጭር የትዝታ ዘጋቢ ፊልም የቀረበ ሲሆን ተመስጋኞቹ ከዚህ ቀደም አየር ላይ ያዋሏቸው ሥራዎችም በዕለቱ ለታደሙት እንግዶች ቀርበዋል።
በባልደረቦቻቸው የምስጋና ዝግጅት የተደረገላቸው አዲስአለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ እንደዛሬ ደስ ብሎንም አያውቅ ፣ ይህን መርሀ ግብር በተሳካ መንገድ ዕውን እንዲሆን የጣራችሁ ሁሉ ፈጣሪ መንገዳችሁን ያቃና ሲሉ መርቀዋል።
የአዘጋጅ ኮሚቴው አባል እሸቱ ገለቱ እንዳለው በኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚሠሩ ባልደረቦች የመጠያየቅ ባህልን ከጀመሩ ሁለት አመት እንደሆናቸው ጠቅሰው ይህ የምስጋና መርሀ ግብር የዚያ መጠያየቅ አካል እንደሆነ ጠቁሟል።
ባለሙያዎች ጡረታ ሲወጡ የሚደገፉበት፣ በተለይም በኢኮኖሚ እገዛ የሚያገኙበት ስልት መነደፍ እንዳለበትም ጋዜጠኛ እሸቱ ጥቆማ ሰጥቷል። በተጨማሪም የጤና ሁኔታቸውን፣ የሚከታተሉበት መንገድ መፈጠር እንዳለበትም ተናግሯል።
ከጡረታ በኃላ ምክር በመስጠት ባለሙያዎቹ ልምዳቸውን ማጋራት አለባቸውም ብሏል።ይህንኑ ትልቅ ርዕይ ለማሳካት መንግሥትና የሚመለከታቸው የሚድያ ማህበራት ሊተባበሩ ይገባልም ሲል ሀሣብ አንስቷል።
የእለቱን የምስጋና መሰናዶ እንዲሳካ አቶ ሠርፀፍሬ ስብሓት አዳራሽ በመስጠት ፣ ጋዜጠኛ ማህደረ ታሪኩ ፕሮጀክተር በመለገስ እንዲሁም አልፋ ውሃ፣ ለታዳሚዎች የመስተንግዶ ውሃ በማቅረብ መርሀ ግብሩ የተሳካ እንዲሆን አድርገዋል።
(በዕዝራ እጅጉ)
.የመዲናዋ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና እንዲያገኙ ወሰነ
#ethiopia | አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ ዛሬ ጋቢ በተደረበላቸው ዕለት ደስታቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር።
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት እነዚህ ጉምቱ ባለሙያዎች ከ 35 አመት በላይ በትጋት ያገለገሉ ሲሆን በሙያ አጋሮቻቸው ተከበው አድናቆት ሲቸራቸው ውለዋል።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም ከ 4 ሰዓት ጀምሮ በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በተደረገው መርሀ ግብር የሚድያ ባለሙያዎች እና ወዳጆቻቸው ተገኝተው እኛም አመስጋኞቻችሁ ነን በማለት ለመርሀ ግብሩ ድምቀት ሰጥተዋል።
ባለሙያዎቹን ለማመስገን ራሱን የቻለ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን ይህም ኮሚቴ ባለሙያዎቹ በዘለቄታዊነት የሚታገዙበት መንገድ ያመቻቸ ነው።
ለዝግጅቱ መሳካት በተከፈተው የwhat is up ገፅ ኮሚቴው ውስጥ ተግባራቸውን የተወጡት ጥላሁን ካሣ ፣ሀብታሙ ድረስ ፣ሰለሞን ሀይለኢየሱስ፣ዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)፣ አለም ታደሰ፣ሠናይት ሀይሌ፣እሸቱ ገለቱ፣ ጌጡ ተመስገን እና ግደይ ገብረ ሲሆኑ እነርሱም በዕለቱ እንደተናገሩት ሥራው በአጭር ጊዜ ታስቦ ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ለአንጋፋ ባለሙያዎቹ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና የሚያገኙበት መንገድ ያመቻቸ ሲሆን ይህ የመረዳዳት ባህል ወደፊትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተነግሯል።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
"ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን "የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች እንደነበሩ በዕለቱ ምስክርነት የሰጡ ባልደረቦቻቸው የተናገሩ ሲሆን የምስጋና ቀን መዘጋጀቱ አዲስ የሚመጣውንም ባለሙያ የሚያበረታታ ነው ሲሉ ሀሣብ ሰንዝረዋል።
በዕለቱ የሚድያ ሥራን ከ1950ዎቹ ጀምሮ ያስቃኘ አጭር የትዝታ ዘጋቢ ፊልም የቀረበ ሲሆን ተመስጋኞቹ ከዚህ ቀደም አየር ላይ ያዋሏቸው ሥራዎችም በዕለቱ ለታደሙት እንግዶች ቀርበዋል።
በባልደረቦቻቸው የምስጋና ዝግጅት የተደረገላቸው አዲስአለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ እንደዛሬ ደስ ብሎንም አያውቅ ፣ ይህን መርሀ ግብር በተሳካ መንገድ ዕውን እንዲሆን የጣራችሁ ሁሉ ፈጣሪ መንገዳችሁን ያቃና ሲሉ መርቀዋል።
የአዘጋጅ ኮሚቴው አባል እሸቱ ገለቱ እንዳለው በኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚሠሩ ባልደረቦች የመጠያየቅ ባህልን ከጀመሩ ሁለት አመት እንደሆናቸው ጠቅሰው ይህ የምስጋና መርሀ ግብር የዚያ መጠያየቅ አካል እንደሆነ ጠቁሟል።
ባለሙያዎች ጡረታ ሲወጡ የሚደገፉበት፣ በተለይም በኢኮኖሚ እገዛ የሚያገኙበት ስልት መነደፍ እንዳለበትም ጋዜጠኛ እሸቱ ጥቆማ ሰጥቷል። በተጨማሪም የጤና ሁኔታቸውን፣ የሚከታተሉበት መንገድ መፈጠር እንዳለበትም ተናግሯል።
ከጡረታ በኃላ ምክር በመስጠት ባለሙያዎቹ ልምዳቸውን ማጋራት አለባቸውም ብሏል።ይህንኑ ትልቅ ርዕይ ለማሳካት መንግሥትና የሚመለከታቸው የሚድያ ማህበራት ሊተባበሩ ይገባልም ሲል ሀሣብ አንስቷል።
የእለቱን የምስጋና መሰናዶ እንዲሳካ አቶ ሠርፀፍሬ ስብሓት አዳራሽ በመስጠት ፣ ጋዜጠኛ ማህደረ ታሪኩ ፕሮጀክተር በመለገስ እንዲሁም አልፋ ውሃ፣ ለታዳሚዎች የመስተንግዶ ውሃ በማቅረብ መርሀ ግብሩ የተሳካ እንዲሆን አድርገዋል።
11 days ago
የበጎነት ዋጋ በቢሊዮኖች ሲሰላ፡ ያልተነካው የሀገር ውስጥ አቅም
*****************
(የዕለቱ መልዕክት)
ያለአንዳች ደመወዝ የሚሰራ፣ ነዳጅ የማይጠይቅ፣ ነገር ግን በቢሊዮኖች የሚቆጠር ሀብት በማዳን የሀገርን ሸክም የሚያቀል ግዙፍ የኢኮኖሚ ሞተር አለ ብንልዎስ? ይህ ከርህራሄና ከሰብዓዊነት ካባ ጀርባ የማክሮ ኢኮኖሚውን መዋቅር በፀጥታ እያንቀሳቀሰ የሚገኘው ‘የበጎ ፈቃድ አገልግሎት’ እውነተኛ ገፅታ ነው፡፡
የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ስናስብ፣ አእምሯችን ቀድሞ የሚስለው የበጎ አድራጎትን ሰብዓዊነት ቢሆንም በዘመናዊ የምጣኔ ሀብት እሳቤ ግን ይህ ዘርፍ በቀጥታ በሀገር ጠቅላላ ምርት (GDP) ውስጥ ያልተካተተ ግዙፍ "የህዝብ ካፒታል" ነው።
የዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት (ILO) እና የተባበሩት መንግስታት ሪፖርቶች እንደሚያረጋግጡት የበጎ ፈቃድ ዘርፍ መንግስታት ሊያወጡት የሚችሉትን በጀት የሚተካ እና በመንግስትና በግሉ ዘርፍ መካከል ያለውን ክፍተት የሚሞላ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ሞተር ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ለዚህ ጥልቅ እሳቤ ባዳ አይደለችም፤ ማህበረሰባችንን ለዘመናት አስተሳስረው ያቆዩት እንደ ደቦ፣ እድር እና እቁብ ያሉ ሀገር በቀል የትብብር ተቋማት የዚሁ ማህበራዊ ካፒታል መገለጫዎች ናቸው።
ኖርጂያን ‘ዱግናድ’ በሚሉት የትብብር ባህላቸው እንዲሁም አሜሪካና ካናዳ በቢሊዮን ዶላሮች በሚገመት የዜጎቻቸው ነፃ አገልግሎት የፈጠሩትን የኢኮኖሚ አቅም፣ እኛም ዛሬ በራሳችን ዐውድ እና ጥበብ በተግባር እያሳየነው እንገኛለን።
በተለይም ከ2010 ዓ.ም ወዲህ "የመደመር ትውልድ" በሚለው ሀገራዊ እሳቤ አማካኝነት ይህ ዘርፍ መሰረታዊ እና መዋቅራዊ ለውጥን አስተናግዷል።
ያለፈውን ስብራት የመጠገን፣ ያለውን የማፅናት እና የነገውን አቅም የመገንባት ጥልቅ ትልም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ውስጥ በተግባር ሲተረጎም በመንግስት አቅም ብቻ ሊሸፈን የማይችለውን ግዙፍ የልማት ክፍተት በመድፈን ተጨባጭ ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ ትርጉም አምጥቷል።
በየዓመቱ በአማካይ ከ20 እስከ 25 ሚሊዮን ዜጎች በሚሳተፉበት በዚህ ሀገራዊ ንቅናቄ የተገኙት ውጤቶች በገንዘብ ሲተመኑ ሀገርን የታደጉበት መጠን እጅግ አስገራሚ ነው። ለአብነት ያህል በክረምት ወራት በተከናወኑ የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳት ስራዎች ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የመንግስት የኮንስትራክሽን እና የማህበራዊ ዋስትና በጀት መታደግ ተችሏል።
ከዚህም ጋር ተያይዞ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በተተገበረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በዜጎች ነፃ ጉልበት በመትከልና በመንከባከብ በዋጋ ሊተመን የማይችል ግዙፍ ሀብት ተፈጥሯል።
ይህ መነቃቃት በጤናውና በትምህርት ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል፤ በየዓመቱ ከ300 ሺህ ዩኒት በላይ ደም በመለገስ የህክምና ግብዓት ወጪን ከማዳንም ባሻገር የበርካታ ዜጎች ህይወት የታደገ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደብተሮች፣ የማጠናከሪያ ትምህርቶች እና የቁሳቁስ ድጋፎች ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦችን ጫና በእጅጉ አቅልለዋል።
የዚህ ሁሉ ሀገራዊ ጥረት ትልቁ ድል፣ የበጎ ፈቃድ ስራ ከ"ክረምት የዘመቻ ስራነት" ተላቆ ዓመቱን ሙሉ የሚተገበር ተቋማዊ ባህል እና የኑሮ ዘይቤ መሆኑ ነው። ይህ ወደ ዘላቂነት የተደረገ ሽግግር ወጣቶች ቋሚ የስራ ልምድ፣ የጊዜ አጠቃቀም እና የአመራር ክህሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለስራ ገበያው ብቁ እያደረጋቸው ይገኛል።
ይህ ሂደት በተዘዋዋሪ የስራ አጥነትን ጫና ከማቃለሉም ባሻገር፣ አምራች ኢንዱስትሪዎች እና ተቋማት የሰለጠነ እና ስነ-ምግባር ያለው የሰው ኃይል በቀላሉ እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል። ከሚያመነጨው ቁሳዊ ትርፍ በዘለለም፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተለያየ ዳራ፣ ባህል እና እምነት ያላቸውን ዜጎች በአንድ የጋራ ዓላማ በማሰባሰብ "የእኔ" ከሚለው ጠባብ አስተሳሰብ ወደ "የእኛ" ሰፊ ሀገራዊ ማንነት እያሸጋገራቸው ይገኛል።
በዚህ የበጎነት መድረክ አዛውንቶች የህይወት ተሞክሯቸውን ሲያካፍሉ ወጣቱ ደግሞ ጉልበቱንና የዘመኑን እውቀት ይለግሳል፤ ይህ ውብ የትውልድ ቅብብሎሽ ማህበረሰባዊ መተማመንን በማሳደግ በፍትህና ፀጥታ ተቋማት ላይ ያለውን ጫና በእጅጉ ይቀንሳል።
ጠንካራ መተማመን እና ትስስር ያለው ማህበረሰብ ደግሞ ተፈጥሯዊም ሆነ ሰው ሰራሽ ቀውሶችን በጋራ የመቋቋም አቅሙ እጅግ የላቀ ነው።
የኢኮኖሚ እድገት ትክክለኛ ትርጉም እና ጣዕም የሚኖረውም የተሳሰረ እና አንዱ ለአንዱ የሚቆረቆር ጠንካራ ማህበረሰብ ሲኖር ነው። በገንዘብ ሲተመን በቢሊዮኖች የሚገመት ሀብት የፈጠረውን ይህን ግዙፍ ሀገራዊ ካፒታል ይበልጥ ለማሳደግ እና ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ ዘመኑ በሚጠይቀው የቴክኖሎጂ ስርአት መደገፍ የግድ ይላል።
በመሆኑም የሚመለከታቸው አካላት የምዝገባ እና የዕውቅና አሰጣጥ ስርአቱን በማዘመን፣ ይህ ያልተነካ የህዝብ ካፒታል በማክሮ ኢኮኖሚ እቅድ ውስጥ እንደ አንድ ራሱን የቻለ የሀብት ምንጭ ተደርጎ በይፋ ሊሰላ እና የበለጠ ሀገራዊ ትኩረት ሊያገኝ ይገባል
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*****************
(የዕለቱ መልዕክት)
ያለአንዳች ደመወዝ የሚሰራ፣ ነዳጅ የማይጠይቅ፣ ነገር ግን በቢሊዮኖች የሚቆጠር ሀብት በማዳን የሀገርን ሸክም የሚያቀል ግዙፍ የኢኮኖሚ ሞተር አለ ብንልዎስ? ይህ ከርህራሄና ከሰብዓዊነት ካባ ጀርባ የማክሮ ኢኮኖሚውን መዋቅር በፀጥታ እያንቀሳቀሰ የሚገኘው ‘የበጎ ፈቃድ አገልግሎት’ እውነተኛ ገፅታ ነው፡፡
የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ስናስብ፣ አእምሯችን ቀድሞ የሚስለው የበጎ አድራጎትን ሰብዓዊነት ቢሆንም በዘመናዊ የምጣኔ ሀብት እሳቤ ግን ይህ ዘርፍ በቀጥታ በሀገር ጠቅላላ ምርት (GDP) ውስጥ ያልተካተተ ግዙፍ "የህዝብ ካፒታል" ነው።
የዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት (ILO) እና የተባበሩት መንግስታት ሪፖርቶች እንደሚያረጋግጡት የበጎ ፈቃድ ዘርፍ መንግስታት ሊያወጡት የሚችሉትን በጀት የሚተካ እና በመንግስትና በግሉ ዘርፍ መካከል ያለውን ክፍተት የሚሞላ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ሞተር ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ለዚህ ጥልቅ እሳቤ ባዳ አይደለችም፤ ማህበረሰባችንን ለዘመናት አስተሳስረው ያቆዩት እንደ ደቦ፣ እድር እና እቁብ ያሉ ሀገር በቀል የትብብር ተቋማት የዚሁ ማህበራዊ ካፒታል መገለጫዎች ናቸው።
ኖርጂያን ‘ዱግናድ’ በሚሉት የትብብር ባህላቸው እንዲሁም አሜሪካና ካናዳ በቢሊዮን ዶላሮች በሚገመት የዜጎቻቸው ነፃ አገልግሎት የፈጠሩትን የኢኮኖሚ አቅም፣ እኛም ዛሬ በራሳችን ዐውድ እና ጥበብ በተግባር እያሳየነው እንገኛለን።
በተለይም ከ2010 ዓ.ም ወዲህ "የመደመር ትውልድ" በሚለው ሀገራዊ እሳቤ አማካኝነት ይህ ዘርፍ መሰረታዊ እና መዋቅራዊ ለውጥን አስተናግዷል።
ያለፈውን ስብራት የመጠገን፣ ያለውን የማፅናት እና የነገውን አቅም የመገንባት ጥልቅ ትልም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ውስጥ በተግባር ሲተረጎም በመንግስት አቅም ብቻ ሊሸፈን የማይችለውን ግዙፍ የልማት ክፍተት በመድፈን ተጨባጭ ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ ትርጉም አምጥቷል።
በየዓመቱ በአማካይ ከ20 እስከ 25 ሚሊዮን ዜጎች በሚሳተፉበት በዚህ ሀገራዊ ንቅናቄ የተገኙት ውጤቶች በገንዘብ ሲተመኑ ሀገርን የታደጉበት መጠን እጅግ አስገራሚ ነው። ለአብነት ያህል በክረምት ወራት በተከናወኑ የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳት ስራዎች ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የመንግስት የኮንስትራክሽን እና የማህበራዊ ዋስትና በጀት መታደግ ተችሏል።
ከዚህም ጋር ተያይዞ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በተተገበረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በዜጎች ነፃ ጉልበት በመትከልና በመንከባከብ በዋጋ ሊተመን የማይችል ግዙፍ ሀብት ተፈጥሯል።
ይህ መነቃቃት በጤናውና በትምህርት ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል፤ በየዓመቱ ከ300 ሺህ ዩኒት በላይ ደም በመለገስ የህክምና ግብዓት ወጪን ከማዳንም ባሻገር የበርካታ ዜጎች ህይወት የታደገ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደብተሮች፣ የማጠናከሪያ ትምህርቶች እና የቁሳቁስ ድጋፎች ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦችን ጫና በእጅጉ አቅልለዋል።
የዚህ ሁሉ ሀገራዊ ጥረት ትልቁ ድል፣ የበጎ ፈቃድ ስራ ከ"ክረምት የዘመቻ ስራነት" ተላቆ ዓመቱን ሙሉ የሚተገበር ተቋማዊ ባህል እና የኑሮ ዘይቤ መሆኑ ነው። ይህ ወደ ዘላቂነት የተደረገ ሽግግር ወጣቶች ቋሚ የስራ ልምድ፣ የጊዜ አጠቃቀም እና የአመራር ክህሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለስራ ገበያው ብቁ እያደረጋቸው ይገኛል።
ይህ ሂደት በተዘዋዋሪ የስራ አጥነትን ጫና ከማቃለሉም ባሻገር፣ አምራች ኢንዱስትሪዎች እና ተቋማት የሰለጠነ እና ስነ-ምግባር ያለው የሰው ኃይል በቀላሉ እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል። ከሚያመነጨው ቁሳዊ ትርፍ በዘለለም፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተለያየ ዳራ፣ ባህል እና እምነት ያላቸውን ዜጎች በአንድ የጋራ ዓላማ በማሰባሰብ "የእኔ" ከሚለው ጠባብ አስተሳሰብ ወደ "የእኛ" ሰፊ ሀገራዊ ማንነት እያሸጋገራቸው ይገኛል።
በዚህ የበጎነት መድረክ አዛውንቶች የህይወት ተሞክሯቸውን ሲያካፍሉ ወጣቱ ደግሞ ጉልበቱንና የዘመኑን እውቀት ይለግሳል፤ ይህ ውብ የትውልድ ቅብብሎሽ ማህበረሰባዊ መተማመንን በማሳደግ በፍትህና ፀጥታ ተቋማት ላይ ያለውን ጫና በእጅጉ ይቀንሳል።
ጠንካራ መተማመን እና ትስስር ያለው ማህበረሰብ ደግሞ ተፈጥሯዊም ሆነ ሰው ሰራሽ ቀውሶችን በጋራ የመቋቋም አቅሙ እጅግ የላቀ ነው።
የኢኮኖሚ እድገት ትክክለኛ ትርጉም እና ጣዕም የሚኖረውም የተሳሰረ እና አንዱ ለአንዱ የሚቆረቆር ጠንካራ ማህበረሰብ ሲኖር ነው። በገንዘብ ሲተመን በቢሊዮኖች የሚገመት ሀብት የፈጠረውን ይህን ግዙፍ ሀገራዊ ካፒታል ይበልጥ ለማሳደግ እና ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ ዘመኑ በሚጠይቀው የቴክኖሎጂ ስርአት መደገፍ የግድ ይላል።
በመሆኑም የሚመለከታቸው አካላት የምዝገባ እና የዕውቅና አሰጣጥ ስርአቱን በማዘመን፣ ይህ ያልተነካ የህዝብ ካፒታል በማክሮ ኢኮኖሚ እቅድ ውስጥ እንደ አንድ ራሱን የቻለ የሀብት ምንጭ ተደርጎ በይፋ ሊሰላ እና የበለጠ ሀገራዊ ትኩረት ሊያገኝ ይገባል
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
11 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ማሂ ኤል-ዲን ሳሌም፣ አሜሪካ፣ ብሪታንያ እና የአውሮፓ ኅብረት በሀገራቸው ላይ የጣሉት ማዕቀብ ግቡን የማያሳካ "የፖለቲካ መሣሪያ" መሆኑን ገለጹ። ሚኒስትሩ በወቅታዊ የሱዳን ጉዳዮች ላይ በሰጡት ሰፊ መግለጫ፣ በሱዳን ጦርነት ውስጥ የውጭ ኃይሎች እጅ እንዳለበት በተጨባጭ መረጋገጡን እና ከጦርነቱ በኋላ የሀገሪቱ ዲፕሎማሲ የተለየ መልክ እንደሚኖረው አስታውቀዋል።
አምባሳደር ማሂ ኤል-ዲን እንዳብራሩት፣ በሱዳን ጉዳይ የውጭ ሀገራት ጣልቃ ገብነት መኖሩን የሚነሱት ጉዳዮች ክስ ሳይሆኑ በተጨባጭ መረጃ የተረጋገጡ እውነታዎች ናቸው። ለአብነትም በአሜሪካ የሚገኘው የዬል ዩኒቨርሲቲ የሳተላይት መረጃዎችን በመጠቀም እንደ ኢትዮጵያ ባለ ቀጣና ውስጥ የጦር ካምፖች መቋቋማቸውን ማረጋገጡን፣ እንዲሁም እንደ ዋሽንግተን ፖስት ያሉ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጉዳዩን መዘገባቸውን አስታውሰዋል። ሚኒስትሩ አክለውም ኃይሎቹ እና ቅጥረኛ ተዋጊዎች ከቻድ፣ ከምስራቃዊ ሊቢያ (በሀፍታር ቡድን በኩል)፣ አልፎ ተርፎም ከኮሎምቢያ ሳይቀር ድንበር አቋርጠው ወደ ካርቱም እየገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በደቡብ ሱዳን በኩልም መንግሥት ቀጥተኛ ሚና ባይኖረውም፣ ሕገ-ወጦች እና አማፂያን በሌላ መንገድ ወደ ሱዳን እየገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምንም እንኳን አንዳንድ ጎረቤት ሀገራት ሚሊሺያዎችን እና ቅጥረኛ ተዋጊዎችን ቢያስተባብሩም፣ ሱዳን ግን ታሪክ ያላት፣ የጎለመሰች እና በመልካም ጉርብትና የምትታወቅ ሀገር በመሆኗ እስከ አሁን ድረስ ከእነዚህ ሀገራት የሚመጡ ስደተኞችን በክብር እያስተናገደች እንደምትገኝ አብራርተዋል። በሌላ በኩል፣ በሱዳን ላይ ለተቃጣው ፈተና ከጎናቸው ለቆሙት እንደ ኤርትራ እና ግብፅ ላሉ እህትማማች ሀገራት የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጦርነቱን ተከትሎ የሱዳን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚደረግ ያረጋገጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ ከጦርነቱ በኋላ የሱዳን ዲፕሎማሲ የተለየ መልክ እንደሚኖረው እና የሀገራትን አቋም በድጋሚ መገምገም ግድ እንደሚል ተናግረዋል። "ማነው ከእኛ ጋር የቆመው? ማነው ከዚህ ሚሊሺያ ጋር በመሆን በሱዳን ህዝብ ላይ የቆመው? የሚለውን ቅርብም ሆኑ ሩቅ ያሉ ሀገራትን አቋም መገምገም አለብን" ብለዋል።
የሱዳን ህዝብ በለጋስነቱና በመቻቻል የሚታወቅ፣ እንዲሁም በየትኛውም ሀገር ላይ ጥቃት ሰንዝሮ የማያውቅ ሰላማዊ ህዝብ መሆኑን በመጥቀስ፤ በአሁኑ ወቅት በማያሻማ መልኩ በህዝቡ ላይ የተከፈተበት ጦርነት ግን የሁሉንም ሱዳናዊ ህይወት፣ ዘመድ፣ ንብረት፣ ትምህርት እና የህክምና አገልግሎት ያመሰቃቀለ ዘግናኝ ጥቃት በመሆኑ፣ ከዚህ እውነታ አንፃር ሀገሪቱ የዲፕሎማሲ ግንኙነቷን እንደገና ማስተካከል እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አምባሳደር ማሂ ኤል-ዲን እንዳብራሩት፣ በሱዳን ጉዳይ የውጭ ሀገራት ጣልቃ ገብነት መኖሩን የሚነሱት ጉዳዮች ክስ ሳይሆኑ በተጨባጭ መረጃ የተረጋገጡ እውነታዎች ናቸው። ለአብነትም በአሜሪካ የሚገኘው የዬል ዩኒቨርሲቲ የሳተላይት መረጃዎችን በመጠቀም እንደ ኢትዮጵያ ባለ ቀጣና ውስጥ የጦር ካምፖች መቋቋማቸውን ማረጋገጡን፣ እንዲሁም እንደ ዋሽንግተን ፖስት ያሉ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጉዳዩን መዘገባቸውን አስታውሰዋል። ሚኒስትሩ አክለውም ኃይሎቹ እና ቅጥረኛ ተዋጊዎች ከቻድ፣ ከምስራቃዊ ሊቢያ (በሀፍታር ቡድን በኩል)፣ አልፎ ተርፎም ከኮሎምቢያ ሳይቀር ድንበር አቋርጠው ወደ ካርቱም እየገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በደቡብ ሱዳን በኩልም መንግሥት ቀጥተኛ ሚና ባይኖረውም፣ ሕገ-ወጦች እና አማፂያን በሌላ መንገድ ወደ ሱዳን እየገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምንም እንኳን አንዳንድ ጎረቤት ሀገራት ሚሊሺያዎችን እና ቅጥረኛ ተዋጊዎችን ቢያስተባብሩም፣ ሱዳን ግን ታሪክ ያላት፣ የጎለመሰች እና በመልካም ጉርብትና የምትታወቅ ሀገር በመሆኗ እስከ አሁን ድረስ ከእነዚህ ሀገራት የሚመጡ ስደተኞችን በክብር እያስተናገደች እንደምትገኝ አብራርተዋል። በሌላ በኩል፣ በሱዳን ላይ ለተቃጣው ፈተና ከጎናቸው ለቆሙት እንደ ኤርትራ እና ግብፅ ላሉ እህትማማች ሀገራት የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጦርነቱን ተከትሎ የሱዳን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚደረግ ያረጋገጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ ከጦርነቱ በኋላ የሱዳን ዲፕሎማሲ የተለየ መልክ እንደሚኖረው እና የሀገራትን አቋም በድጋሚ መገምገም ግድ እንደሚል ተናግረዋል። "ማነው ከእኛ ጋር የቆመው? ማነው ከዚህ ሚሊሺያ ጋር በመሆን በሱዳን ህዝብ ላይ የቆመው? የሚለውን ቅርብም ሆኑ ሩቅ ያሉ ሀገራትን አቋም መገምገም አለብን" ብለዋል።
የሱዳን ህዝብ በለጋስነቱና በመቻቻል የሚታወቅ፣ እንዲሁም በየትኛውም ሀገር ላይ ጥቃት ሰንዝሮ የማያውቅ ሰላማዊ ህዝብ መሆኑን በመጥቀስ፤ በአሁኑ ወቅት በማያሻማ መልኩ በህዝቡ ላይ የተከፈተበት ጦርነት ግን የሁሉንም ሱዳናዊ ህይወት፣ ዘመድ፣ ንብረት፣ ትምህርት እና የህክምና አገልግሎት ያመሰቃቀለ ዘግናኝ ጥቃት በመሆኑ፣ ከዚህ እውነታ አንፃር ሀገሪቱ የዲፕሎማሲ ግንኙነቷን እንደገና ማስተካከል እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
Sponsored by
Surafel
Comments