5 days ago
የዲያስፖራ የባንክ ሂሳብ እገዳን ለማንሳት የተዘጋጀ አዲስ መመሪያ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ቁጥርን ከባንክ ሂሳብ ጋር ባለማያያዝ ምክንያት የታገዱ የዲያስፖራ ደንበኞችን ሂሳብ በጊዜያዊነት ለመክፈት የሚያስችሉ አማራጭ መንገዶችን ይፋ አደረገ።
ባንኩ ይህንን ያስታወቀው ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ለኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት በጻፈው ይፋዊ ደብዳቤ ነው።
በመመሪያው መሰረት፣ ሂሳብ በከፈቱበት ወቅት የመኖሪያ አድራሻቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ ማድረጋቸውን በባንኩ የመረጃ ቋት ላይ ያስመዘገቡ ደንበኞች ሂሳባቸው አልታገደም።
ሆኖም አድራሻቸውን ያላስመዘገቡና ሂሳባቸው የታገደባቸው ደንበኞች፣ የፋይዳ መታወቂያ ማቅረብ ባይችሉም እንኳ በውጭ ሀገር መኖራቸውን የሚያረጋግጡ ተለዋጭ ማስረጃዎችን በማቅረብ እገዳውን ማንሳት ይችላሉ።
ደንበኞች እገዳውን ለማንሳት የሚከተሉትን ማስረጃዎች ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፦
👉የውጭ ሀገር የመኖሪያ ፈቃድ (Residence Permit/ID)፣ የትምህርት ወይም የህክምና ማስረጃ።
👉በህጋዊ አካል የተረጋገጠ እና በውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚገልጽ የውክልና ማስረጃ (በወኪሎቻቸው በኩል)።
👉ለዲፕሎማቶች የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ መታወቂያ።
👉በውጭ ሀገር በሚገኝ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ጽሕፈት ቤት በኩል በቀጥታ በኢሜል የሚላክ ማረጋገጫ።
የዲያስፖራ ደንበኞች እነዚህን ማስረጃዎች ሂሳባቸው ለተከፈተበት የባንክ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ኢሜል ወይም በዋናው መስሪያ ቤት ለሚገኘው የዲያስፖራ ባንኪንግ ክፍል (DiasporaBankingcbe.com.et) በመላክ እገዳው በጊዜያዊነት እንዲነሳላቸው ማድረግ ይችላሉ።
በሌላ በኩል፣ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ዜጎች እዚያው ባሉበት ቦታ የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ማካሄድ የሚችሉ በመሆኑ፣ ይህ ጊዜያዊ መመሪያ እንደማይመለከታቸው ባንኩ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ቁጥርን ከባንክ ሂሳብ ጋር ባለማያያዝ ምክንያት የታገዱ የዲያስፖራ ደንበኞችን ሂሳብ በጊዜያዊነት ለመክፈት የሚያስችሉ አማራጭ መንገዶችን ይፋ አደረገ።
ባንኩ ይህንን ያስታወቀው ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ለኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት በጻፈው ይፋዊ ደብዳቤ ነው።
በመመሪያው መሰረት፣ ሂሳብ በከፈቱበት ወቅት የመኖሪያ አድራሻቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ ማድረጋቸውን በባንኩ የመረጃ ቋት ላይ ያስመዘገቡ ደንበኞች ሂሳባቸው አልታገደም።
ሆኖም አድራሻቸውን ያላስመዘገቡና ሂሳባቸው የታገደባቸው ደንበኞች፣ የፋይዳ መታወቂያ ማቅረብ ባይችሉም እንኳ በውጭ ሀገር መኖራቸውን የሚያረጋግጡ ተለዋጭ ማስረጃዎችን በማቅረብ እገዳውን ማንሳት ይችላሉ።
ደንበኞች እገዳውን ለማንሳት የሚከተሉትን ማስረጃዎች ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፦
👉የውጭ ሀገር የመኖሪያ ፈቃድ (Residence Permit/ID)፣ የትምህርት ወይም የህክምና ማስረጃ።
👉በህጋዊ አካል የተረጋገጠ እና በውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚገልጽ የውክልና ማስረጃ (በወኪሎቻቸው በኩል)።
👉ለዲፕሎማቶች የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ መታወቂያ።
👉በውጭ ሀገር በሚገኝ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ጽሕፈት ቤት በኩል በቀጥታ በኢሜል የሚላክ ማረጋገጫ።
የዲያስፖራ ደንበኞች እነዚህን ማስረጃዎች ሂሳባቸው ለተከፈተበት የባንክ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ኢሜል ወይም በዋናው መስሪያ ቤት ለሚገኘው የዲያስፖራ ባንኪንግ ክፍል (DiasporaBankingcbe.com.et) በመላክ እገዳው በጊዜያዊነት እንዲነሳላቸው ማድረግ ይችላሉ።
በሌላ በኩል፣ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ዜጎች እዚያው ባሉበት ቦታ የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ማካሄድ የሚችሉ በመሆኑ፣ ይህ ጊዜያዊ መመሪያ እንደማይመለከታቸው ባንኩ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
14 days ago
የሩሲያው በሮኬቶቿ የንግድ ማስታወቂያ መለጠፍ ጀመረች
#ethiopia | በከፍተኛ ወጪ እና በረጅም ጊዜ ዝግጅት የሚከናወኑት የሕዋ ሮኬት መንኮራኩር ሂደቶች፣ አሁን ላይ የቢሊዮን ዶላር የንግድ ማስታወቂያ መድረክ እየሆኑ መጥተዋል። የሩሲያ ብሔራዊ ስፔስ ኤጀንሲ (ሮስኮስሞስ) ገቢውን ለማሳደግና ግዙፍ የሕዋ ወጪዎቹን ለማቅለል፣ በሕዋ ሮኬቶቹ ላይ የንግድ ማስታወቂያዎችን ማሳየት መጀመሩ ተሰምቷል።
ባለፈው ዓመት በሩሲያ ፓርላማ በፀደቀው አዲስ ረቂቅ ሕግ መሠረት፣ ስፔስ ኤጀንሲው የታዋቂ የንግድ ምልክት አርማዎችን (Logos) እና መፈክሮችን በሮኬቶች ላይ በመለጠፍ ገቢ እንዲሰበስብ ሙሉ ፈቃድ ተሰጥቶታል። ይህንን ተከትሎም ኤጀንሲው የሀገሪቱን ግዙፍ የፋይናንስ ተቋም ፒኤስቢ ባንክ (PSB Bank) እና የታወቀውን የቡና መሸጫ ሰንሰለት ኮፌማኒያን (Kofemanija) ጨምሮ ለበርካታ ሀገራዊ ብራንዶች የመጀመሪያውን የማስታወቂያ ስራ በተግባር አሳይቷል።
እንደ ኦዲቲ ሴንትራል ዘገባ ከሆነ፣ ማስታወቂያዎቹ በይፋ መታየት ከጀመሩበት ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ ኤጀንሲው ከግል ኩባንያዎች በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ሩብል (የሩሲያ ገንዘብ) ገቢ ማጋበስ ችሏል።
በሕዋ ሮኬት ላይ ማስታወቂያ ማስነገር እንደ ተራ የጎዳና ላይ ቢልቦርድ ቀላል አይደለም።
የማስታወቂያው ዋጋ የሚሰላው ልዩ ቀመርን በመጠቀም ሲሆን፣ የሚከተሉትን ነጥቦች ግምት ውስጥ ያስገባል፡
-የማስታወቂያው አጠቃላይ ስፋት
-በሮኬቱ አካል ላይ የሚይዘው የገጽታ መጠን
-ማስታወቂያው በሮኬቱ ላይ የሚቆይበት ጊዜ
የሮኬት መንኮራኩር ሂደት በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የሳይንስና የቴክኖሎጂ አፍቃሪያን በቀጥታ ስርጭት የሚከታተሉት ታላቅ ክስተት በመሆኑ፣ ለትልልቅ ኩባንያዎች አይነተኛ የገበያ መድረክ ሆኗል።
የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ፣ ኤጀንሲው ከዓመቱ መጀመሪያ ጀምሮ ከታዋቂው የባይኮኑር የሕዋ ጣቢያ (Baikonur Cosmodrome) የማስታወቂያ አርማዎችን ያዘሉ አራት ሮኬቶችን በተሳካ ሁኔታ አስወንጭፏል።
ይህ አካሄድ የሕዋ ምርምር ድርጅቶች ከመንግስት በጀት ጥገኝነት ወጥተው የራሳቸውን ወጪ በራሳቸው የንግድ ፈጠራ ለመሸፈን ለሚያደርጉት ጥረት ትልቅ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የሕዋምርምር #ሩሲያ #ሮስኮስሞስ #የንግድማስታወቂያ #ቴክኖሎጂ #ሮኬት #ባይኮኑር #ኢኮኖሚ #ሳይንስ
#ethiopia | በከፍተኛ ወጪ እና በረጅም ጊዜ ዝግጅት የሚከናወኑት የሕዋ ሮኬት መንኮራኩር ሂደቶች፣ አሁን ላይ የቢሊዮን ዶላር የንግድ ማስታወቂያ መድረክ እየሆኑ መጥተዋል። የሩሲያ ብሔራዊ ስፔስ ኤጀንሲ (ሮስኮስሞስ) ገቢውን ለማሳደግና ግዙፍ የሕዋ ወጪዎቹን ለማቅለል፣ በሕዋ ሮኬቶቹ ላይ የንግድ ማስታወቂያዎችን ማሳየት መጀመሩ ተሰምቷል።
ባለፈው ዓመት በሩሲያ ፓርላማ በፀደቀው አዲስ ረቂቅ ሕግ መሠረት፣ ስፔስ ኤጀንሲው የታዋቂ የንግድ ምልክት አርማዎችን (Logos) እና መፈክሮችን በሮኬቶች ላይ በመለጠፍ ገቢ እንዲሰበስብ ሙሉ ፈቃድ ተሰጥቶታል። ይህንን ተከትሎም ኤጀንሲው የሀገሪቱን ግዙፍ የፋይናንስ ተቋም ፒኤስቢ ባንክ (PSB Bank) እና የታወቀውን የቡና መሸጫ ሰንሰለት ኮፌማኒያን (Kofemanija) ጨምሮ ለበርካታ ሀገራዊ ብራንዶች የመጀመሪያውን የማስታወቂያ ስራ በተግባር አሳይቷል።
እንደ ኦዲቲ ሴንትራል ዘገባ ከሆነ፣ ማስታወቂያዎቹ በይፋ መታየት ከጀመሩበት ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ ኤጀንሲው ከግል ኩባንያዎች በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ሩብል (የሩሲያ ገንዘብ) ገቢ ማጋበስ ችሏል።
በሕዋ ሮኬት ላይ ማስታወቂያ ማስነገር እንደ ተራ የጎዳና ላይ ቢልቦርድ ቀላል አይደለም።
የማስታወቂያው ዋጋ የሚሰላው ልዩ ቀመርን በመጠቀም ሲሆን፣ የሚከተሉትን ነጥቦች ግምት ውስጥ ያስገባል፡
-የማስታወቂያው አጠቃላይ ስፋት
-በሮኬቱ አካል ላይ የሚይዘው የገጽታ መጠን
-ማስታወቂያው በሮኬቱ ላይ የሚቆይበት ጊዜ
የሮኬት መንኮራኩር ሂደት በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የሳይንስና የቴክኖሎጂ አፍቃሪያን በቀጥታ ስርጭት የሚከታተሉት ታላቅ ክስተት በመሆኑ፣ ለትልልቅ ኩባንያዎች አይነተኛ የገበያ መድረክ ሆኗል።
የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ፣ ኤጀንሲው ከዓመቱ መጀመሪያ ጀምሮ ከታዋቂው የባይኮኑር የሕዋ ጣቢያ (Baikonur Cosmodrome) የማስታወቂያ አርማዎችን ያዘሉ አራት ሮኬቶችን በተሳካ ሁኔታ አስወንጭፏል።
ይህ አካሄድ የሕዋ ምርምር ድርጅቶች ከመንግስት በጀት ጥገኝነት ወጥተው የራሳቸውን ወጪ በራሳቸው የንግድ ፈጠራ ለመሸፈን ለሚያደርጉት ጥረት ትልቅ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የሕዋምርምር #ሩሲያ #ሮስኮስሞስ #የንግድማስታወቂያ #ቴክኖሎጂ #ሮኬት #ባይኮኑር #ኢኮኖሚ #ሳይንስ
16 days ago
Ethio telecom and the African Development Bank (AfDB) Review Strategic Partnership to Accelerate Ethiopia’s Digital Transformation and Next Horizon Strategy
Ethio telecom CEO, Frehiwot Tamru, held a high-level strategic engagement with Excellency Mr. Solomon Quaynor S, Vice President of the African Development Bank, together with senior AfDB management, to review the ongoing partnership and collaborative engagements aimed at supporting the execution of Ethio telecom’s transformative “Next Horizon: Digital & Beyond 2028” strategy and Ethiopia’s broader digital transformation journey.
During the meeting, both institutions assessed the strong progress of their ongoing strategic engagements and financing discussions designed to accelerate the expansion and modernization of Ethiopia’s digital and telecom infrastructure, strengthen digital platforms and ecosystems, and expand inclusive access to innovative digital services that empower millions of citizens, businesses, and institutions across the country.
The CEO briefed the AfDB leadership on the significant progress being achieved under the “Next Horizon: Digital & Beyond 2028” strategy, highlighting Ethio telecom’s continued growth and advancement across all major business and transformation pillars. She emphasized the company’s successful evolution from a traditional telecom operator into a leading digital solutions and platform provider, supported by continuous investments in advanced telecom infrastructure, cloud services, AI-enabled technologies, fintech ecosystems, and digital platforms.
The discussion further highlighted Ethio telecom’s rapidly expanding “Beyond Connectivity” ecosystem, including strategic digital platforms such as telebirr, Zemen GEBEYA, and znexus, which are increasingly contributing to financial inclusion, digital commerce, entrepreneurship, innovation, and socio-economic empowerment. The CEO also outlined the company’s ongoing investments in next-generation digital infrastructure, including 4G and 5G expansion, rural connectivity, cloud and AI capabilities, green and energy-efficient infrastructure, and cross-border initiatives such as the Horizon Fiber project, which collectively reinforce Ethiopia’s growing role in the regional digital economy.
Vice President Solomon Quaynor and the AfDB senior management acknowledged Ethio telecom’s remarkable transformation journey and operational progress, noting the company’s growing relevance as one of Africa’s leading digital transformation success stories. They reaffirmed AfDB’s commitment to strengthening strategic collaboration and exploring sustainable financing frameworks that support large-scale digital infrastructure development, digital inclusion, innovation, and long-term economic growth.
The engagement also reflected the shared commitment of both institutions toward advancing continental priorities, including Africa’s digital transformation agenda, regional digital integration, and the broader vision of a connected and inclusive African digital economy.
At the conclusion of the meeting, Ethio telecom and the African Development Bank reaffirmed their mutual commitment to expediting ongoing collaborative initiatives, deepening their long-term strategic partnership, and accelerating investments that will continue to digitally transform Ethiopia, empower millions of lives, and contribute to sustainable and inclusive growth across the continent.
#ethiotelecom #afdb #digitalafrica #nexthorizon2028 #telebirr #digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu
Ethio telecom CEO, Frehiwot Tamru, held a high-level strategic engagement with Excellency Mr. Solomon Quaynor S, Vice President of the African Development Bank, together with senior AfDB management, to review the ongoing partnership and collaborative engagements aimed at supporting the execution of Ethio telecom’s transformative “Next Horizon: Digital & Beyond 2028” strategy and Ethiopia’s broader digital transformation journey.
During the meeting, both institutions assessed the strong progress of their ongoing strategic engagements and financing discussions designed to accelerate the expansion and modernization of Ethiopia’s digital and telecom infrastructure, strengthen digital platforms and ecosystems, and expand inclusive access to innovative digital services that empower millions of citizens, businesses, and institutions across the country.
The CEO briefed the AfDB leadership on the significant progress being achieved under the “Next Horizon: Digital & Beyond 2028” strategy, highlighting Ethio telecom’s continued growth and advancement across all major business and transformation pillars. She emphasized the company’s successful evolution from a traditional telecom operator into a leading digital solutions and platform provider, supported by continuous investments in advanced telecom infrastructure, cloud services, AI-enabled technologies, fintech ecosystems, and digital platforms.
The discussion further highlighted Ethio telecom’s rapidly expanding “Beyond Connectivity” ecosystem, including strategic digital platforms such as telebirr, Zemen GEBEYA, and znexus, which are increasingly contributing to financial inclusion, digital commerce, entrepreneurship, innovation, and socio-economic empowerment. The CEO also outlined the company’s ongoing investments in next-generation digital infrastructure, including 4G and 5G expansion, rural connectivity, cloud and AI capabilities, green and energy-efficient infrastructure, and cross-border initiatives such as the Horizon Fiber project, which collectively reinforce Ethiopia’s growing role in the regional digital economy.
Vice President Solomon Quaynor and the AfDB senior management acknowledged Ethio telecom’s remarkable transformation journey and operational progress, noting the company’s growing relevance as one of Africa’s leading digital transformation success stories. They reaffirmed AfDB’s commitment to strengthening strategic collaboration and exploring sustainable financing frameworks that support large-scale digital infrastructure development, digital inclusion, innovation, and long-term economic growth.
The engagement also reflected the shared commitment of both institutions toward advancing continental priorities, including Africa’s digital transformation agenda, regional digital integration, and the broader vision of a connected and inclusive African digital economy.
At the conclusion of the meeting, Ethio telecom and the African Development Bank reaffirmed their mutual commitment to expediting ongoing collaborative initiatives, deepening their long-term strategic partnership, and accelerating investments that will continue to digitally transform Ethiopia, empower millions of lives, and contribute to sustainable and inclusive growth across the continent.
#ethiotelecom #afdb #digitalafrica #nexthorizon2028 #telebirr #digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu
1 month ago
Ethiopian Airlines’ 80th anniversary celebration continued today, 30 April, 2026, dedicate to highlighting customers’ experience.
The event had been filled with insightful panel discussions with Her Excellency Dr. Fitsum Assefa Minister of Planning and Development, His Excellency Ahmed Shide Minister of Finance, and His Excellency Dr. Eyob Tekalegn Governor of the National Bank of Ethiopia taking part.
For the second part of the panel discussion the airline’s platinum members came together with CEOs of local banks and Visa Head of East Africa and Country Manager Ethiopia taking part.
The event had been filled with insightful panel discussions with Her Excellency Dr. Fitsum Assefa Minister of Planning and Development, His Excellency Ahmed Shide Minister of Finance, and His Excellency Dr. Eyob Tekalegn Governor of the National Bank of Ethiopia taking part.
For the second part of the panel discussion the airline’s platinum members came together with CEOs of local banks and Visa Head of East Africa and Country Manager Ethiopia taking part.
1 month ago
የአዋሽ መገበያያ ድህረ-ገጽ (Merchant Portal)
============
ነጋዴዎች ሆይ፣ ባሉበት ቦታ ሆነው ንግድዎን ዛሬውኑ ያዘምኑ!
ከክፍያ እስከ ሪፖርት ሁሉንም በአንድ ቦታ ያግኙ!
ፈጣን፣ ዘመናዊ እና ውጤታማ መፍትሄዎች ከአዋሽ ባንክ ጋር!
ወደ ድህረ-ገፁ ለመግባት የሚከተለውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://awashpay.awashbank...
መተግበሪያውን ለማውረድ https://onelink.to/j7fnbz ይጫኑ!
Daldaltoonni, bakka jirtanii har'uma daldala keessan ammayyeessaa!
Kaffaltii daldalaa irraa kaasee hanga gabaasa nagaheetti waan hunda bakka tokkotti argadhaa!
Tajaajila saffisaa, ammayyaa fi gahumsa qabu Baankii Awaash waliin!
Gara marsariitii seenuuf geessituu itti aanu fayyadamaa
https://awashpay.awashbank...
Tajaajilicha karaa appilikeeshinii AwaashBirr-Pro https://onelink.to/j7fnbz buufadhaa. #awashbank #merchant #portal #ethiopia #nurturingliketheriver
============
ነጋዴዎች ሆይ፣ ባሉበት ቦታ ሆነው ንግድዎን ዛሬውኑ ያዘምኑ!
ከክፍያ እስከ ሪፖርት ሁሉንም በአንድ ቦታ ያግኙ!
ፈጣን፣ ዘመናዊ እና ውጤታማ መፍትሄዎች ከአዋሽ ባንክ ጋር!
ወደ ድህረ-ገፁ ለመግባት የሚከተለውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://awashpay.awashbank...
መተግበሪያውን ለማውረድ https://onelink.to/j7fnbz ይጫኑ!
Daldaltoonni, bakka jirtanii har'uma daldala keessan ammayyeessaa!
Kaffaltii daldalaa irraa kaasee hanga gabaasa nagaheetti waan hunda bakka tokkotti argadhaa!
Tajaajila saffisaa, ammayyaa fi gahumsa qabu Baankii Awaash waliin!
Gara marsariitii seenuuf geessituu itti aanu fayyadamaa
https://awashpay.awashbank...
Tajaajilicha karaa appilikeeshinii AwaashBirr-Pro https://onelink.to/j7fnbz buufadhaa. #awashbank #merchant #portal #ethiopia #nurturingliketheriver
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የሕይወት አድን ጥሪ
ለመምህር ዘመነ በጋራ እንድረስላቸው
#ethiopia | ቃለ እግዚአብሔርን ሲያስተምሩና ሲመክሩ የኖሩት ታላቁ አባት መልዓከ ብርሃን መምህር ዘመነ፣ በአሁኑ ወቅት በጠና የልብ ሕመም ምክንያት በከባድ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።
ሐኪሞች ሕይወታቸውን ለማዳን በአፋጣኝ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker) መለወጥ እንዳለባቸው ወስነዋል።
አስፈላጊው መሣሪያ፦ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker)።
የሚያስፈልገው ገንዘብ፦
500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ብር።
ይህ የሕክምና ወጪ ከመምህራችን አቅም በላይ በመሆኑ የእያንዳንዳችንን ርብርብ ይሻል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
1000502420384
ዓባይ ባንክ (Abay Bank)
9250885
የምትሰጡት ሳንቲም ሳይሆን የሰው ሕይወት ነው!
እንዲሉ፣ ዛሬ የምናደርገው ጥቂት እርዳታ ለታላቁ አባት የሕይወት ተስፋ ይሆናል።
እባክዎ ይህ መልእክት ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ይተባበሩን።
#getu #ethiopia #healthalert #saveteacherzemene #heartsurgery #pacemaker #charityethiopia #communitysupport #addisababa #churchteachers #መምህርዘመነ #የልብሕክምና #የሕይወትአድንጥሪ #እርዳታ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ለመምህር ዘመነ በጋራ እንድረስላቸው
#ethiopia | ቃለ እግዚአብሔርን ሲያስተምሩና ሲመክሩ የኖሩት ታላቁ አባት መልዓከ ብርሃን መምህር ዘመነ፣ በአሁኑ ወቅት በጠና የልብ ሕመም ምክንያት በከባድ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።
ሐኪሞች ሕይወታቸውን ለማዳን በአፋጣኝ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker) መለወጥ እንዳለባቸው ወስነዋል።
አስፈላጊው መሣሪያ፦ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker)።
የሚያስፈልገው ገንዘብ፦
500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ብር።
ይህ የሕክምና ወጪ ከመምህራችን አቅም በላይ በመሆኑ የእያንዳንዳችንን ርብርብ ይሻል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
1000502420384
ዓባይ ባንክ (Abay Bank)
9250885
የምትሰጡት ሳንቲም ሳይሆን የሰው ሕይወት ነው!
እንዲሉ፣ ዛሬ የምናደርገው ጥቂት እርዳታ ለታላቁ አባት የሕይወት ተስፋ ይሆናል።
እባክዎ ይህ መልእክት ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ይተባበሩን።
#getu #ethiopia #healthalert #saveteacherzemene #heartsurgery #pacemaker #charityethiopia #communitysupport #addisababa #churchteachers #መምህርዘመነ #የልብሕክምና #የሕይወትአድንጥሪ #እርዳታ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
እናት ባንክ የሴቶች የፋይናንስ ተጠቃሚነት ለማሳደግ 'የሥርዓተ ፆታ ቦንድ' ሊጀመር ነው!
#fastmereja :እናት ባንክ የሴት አመራሮችን ክህሎትና ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ "High Level Women Leadership" የተሰኘ የፓናል ውይይት በዲሊዮፖል ሆቴል አካሄደ።
የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ አስቴር ሰለሞን በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት፤ ባንኩ ባለፉት 13 ዓመታት የሴት ሰራተኞችን አቅም በማሳደግና ወደ አመራር በማምጣት የደንበኞችን አገልግሎት ማሻሻል መቻሉን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅትም የባንኩን እድገት ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት ውስጥ ሴት ሰራተኞች ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት እናት ባንክ ካሉት ከ2,000 በላይ ሰራተኞች መካከል 952ቱ ሴቶች ሲሆኑ፣ ከ11 የቦርድ አባላት መካከል 7ቱ ሴቶች መሆናቸዉ የተገለፀ ሲሆን በተጨማሪም በከፍተኛ የሥራ ካውንስል ውስጥ የሴቶች ድርሻ 44 በመቶ መድረሱ የባንኩን አካታችነት እንደሚያሳይ ተገልጿል።
ባንኩ ላሳየው ተከታታይነት ያለው የሴቶች ተሳትፎ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና በዓለም ባንክ የጋራ ምዘና (Gender Scorecard) "ፈር ቀዳጅ ባንክ"(The First and Only Transformational Bank) የሚል እውቅና ማግኘቱም በዝግጅቱ ላይ ይፋ ሆኗል።
ይህ እውቅና የተሰጠው ባንኩ በፋይናንስ አካታችነት፣ በሴቶች የሥራ ዕድገትና ለሴቶች ተብለው በተቀረጹ የብድርና ቁጠባ አገልግሎቶች ባከናወነው ውጤታማ ተግባር መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
በቀጣይነትም በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚተገበረውንና የሴቶችን የፋይናንስ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል የተባለለትን የሥርዓተ ፆታ ቦንድ (Gender Bond) ወደ አገልግሎት ለማስገባት ዝግጅት መጠናቀቁ ተገልጿል።
በመድረኩ ላይ ዶ/ር ተዋበች ቢሻው፣ ወ/ሮ ናስሪን መሐመድ እና ዶ/ር ገመቹ ዋቅቶላ የካበተ የሥራና የሕይወት ተሞክሮአቸውን ለታዳሚዎች አጋርተዋል።
እናት ባንክ በአሁኑ ወቅት በመላ ሀገሪቱ 222 ቅርንጫፎችን በመክፈትና የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎቱን በማስፋፋት ተደራሽነቱን እያሳደገ ይገኛል።
#fastmereja :እናት ባንክ የሴት አመራሮችን ክህሎትና ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ "High Level Women Leadership" የተሰኘ የፓናል ውይይት በዲሊዮፖል ሆቴል አካሄደ።
የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ አስቴር ሰለሞን በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት፤ ባንኩ ባለፉት 13 ዓመታት የሴት ሰራተኞችን አቅም በማሳደግና ወደ አመራር በማምጣት የደንበኞችን አገልግሎት ማሻሻል መቻሉን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅትም የባንኩን እድገት ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት ውስጥ ሴት ሰራተኞች ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት እናት ባንክ ካሉት ከ2,000 በላይ ሰራተኞች መካከል 952ቱ ሴቶች ሲሆኑ፣ ከ11 የቦርድ አባላት መካከል 7ቱ ሴቶች መሆናቸዉ የተገለፀ ሲሆን በተጨማሪም በከፍተኛ የሥራ ካውንስል ውስጥ የሴቶች ድርሻ 44 በመቶ መድረሱ የባንኩን አካታችነት እንደሚያሳይ ተገልጿል።
ባንኩ ላሳየው ተከታታይነት ያለው የሴቶች ተሳትፎ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና በዓለም ባንክ የጋራ ምዘና (Gender Scorecard) "ፈር ቀዳጅ ባንክ"(The First and Only Transformational Bank) የሚል እውቅና ማግኘቱም በዝግጅቱ ላይ ይፋ ሆኗል።
ይህ እውቅና የተሰጠው ባንኩ በፋይናንስ አካታችነት፣ በሴቶች የሥራ ዕድገትና ለሴቶች ተብለው በተቀረጹ የብድርና ቁጠባ አገልግሎቶች ባከናወነው ውጤታማ ተግባር መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
በቀጣይነትም በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚተገበረውንና የሴቶችን የፋይናንስ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል የተባለለትን የሥርዓተ ፆታ ቦንድ (Gender Bond) ወደ አገልግሎት ለማስገባት ዝግጅት መጠናቀቁ ተገልጿል።
በመድረኩ ላይ ዶ/ር ተዋበች ቢሻው፣ ወ/ሮ ናስሪን መሐመድ እና ዶ/ር ገመቹ ዋቅቶላ የካበተ የሥራና የሕይወት ተሞክሮአቸውን ለታዳሚዎች አጋርተዋል።
እናት ባንክ በአሁኑ ወቅት በመላ ሀገሪቱ 222 ቅርንጫፎችን በመክፈትና የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎቱን በማስፋፋት ተደራሽነቱን እያሳደገ ይገኛል።
3 months ago
በኮሪደር ልማት ስም ከሚነግዱና ደንበኞችን ከሚያጭበረብረው "የየአብ መስታወት ስራ" (Yeab Glass) ራሳችሁን ጠብቁ!
በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት ምክንያት በርካታ ነዋሪዎችና የንግድ ተቋማት የህንፃዎቻቸውን የፊት ለፊት ገጽታ በመስታወት ስራ እያዘመኑ መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ደንበኞችን የሚያጭበረብሩና የመንግስትን ታክስ የሚሰውሩ ድርጅቶች መበራከታቸው አሳሳቢ ሆኗል።
በቦሌ ቡልቡላ ስታዲየም ፊት ለፊት የሚገኘው "የየአብ መስታወት ስራ" (Yeab Glass) የተባለው ድርጅት በደንበኞች ላይ እያደረሰ ያለው በደል ለዚህ ማሳያ ነው።
የተፈጸሙ ዋና ዋና ጥሰቶች፦
* የገንዘብ ማጭበርበር፦ ለህንፃ በር መስታወት ስራ 110,000 (አንድ መቶ አስር ሺህ) ብር ሙሉ ክፍያ ተቀብሎ፣ በ15 ቀን ውስጥ አጠናቅቃለሁ ብሎ የተስማማውን ስራ ከ2 ወር በላይ አጓትቷል።
* ጥራት የጎደለው ስራ፦ ከብዙ እንግልት በኋላ ተገጥሞ ያለቀው ስራ የተሰበረ መስታወት ሲሆን፣ እስካሁንም ለበሩ ቁልፍ ሳይገጥም ደንበኛውን ለከፍተኛ ስጋትና እንግልት ዳርጓል።
* የታክስ ስወራ፦ ለተከፈለው 110 ሺህ ብር ህጋዊ የቫት (VAT) ደረሰኝ ለመስጠት ፍቃደኛ ባለመሆን የመንግስትን ታክስ እየሰወረ ይገኛል።
🔥ለገቢዎች ቢሮ የቀረበ ጥቆማ፦
ይህ ድርጅት ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚፈጽመውን የታክስ ስወራ የሚመለከተው የገቢዎች ባለስልጣን ጥብቅ ክትትል እንዲያደርግበት እናሳስባለን። ለክፍያው ማስረጃ የሚሆን የባንክ የክፍያ ስሊፕ (Bank Slip) በእጃችን የሚገኝ በመሆኑ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ እንጠይቃለን።
ማሳሰቢያ፦
ህዝባችን በዚህ ድርጅት እንዳይታለልና ገንዘቡን ለከንቱ ብክነት እንዳይዳርግ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን። "የየአብ መስታወት ስራ" (Yeab Glass) ላይ የሚሰሩ ሰራተኞችና ባለቤቶች ደንበኛን ማክበርና የገቡትን ቃል መፈጸም ሲገባቸው አሳሳች ስራ እየሰሩ በመሆኑ ህዝብ ሊያውቃቸው ይገባል።
በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት ምክንያት በርካታ ነዋሪዎችና የንግድ ተቋማት የህንፃዎቻቸውን የፊት ለፊት ገጽታ በመስታወት ስራ እያዘመኑ መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ደንበኞችን የሚያጭበረብሩና የመንግስትን ታክስ የሚሰውሩ ድርጅቶች መበራከታቸው አሳሳቢ ሆኗል።
በቦሌ ቡልቡላ ስታዲየም ፊት ለፊት የሚገኘው "የየአብ መስታወት ስራ" (Yeab Glass) የተባለው ድርጅት በደንበኞች ላይ እያደረሰ ያለው በደል ለዚህ ማሳያ ነው።
የተፈጸሙ ዋና ዋና ጥሰቶች፦
* የገንዘብ ማጭበርበር፦ ለህንፃ በር መስታወት ስራ 110,000 (አንድ መቶ አስር ሺህ) ብር ሙሉ ክፍያ ተቀብሎ፣ በ15 ቀን ውስጥ አጠናቅቃለሁ ብሎ የተስማማውን ስራ ከ2 ወር በላይ አጓትቷል።
* ጥራት የጎደለው ስራ፦ ከብዙ እንግልት በኋላ ተገጥሞ ያለቀው ስራ የተሰበረ መስታወት ሲሆን፣ እስካሁንም ለበሩ ቁልፍ ሳይገጥም ደንበኛውን ለከፍተኛ ስጋትና እንግልት ዳርጓል።
* የታክስ ስወራ፦ ለተከፈለው 110 ሺህ ብር ህጋዊ የቫት (VAT) ደረሰኝ ለመስጠት ፍቃደኛ ባለመሆን የመንግስትን ታክስ እየሰወረ ይገኛል።
🔥ለገቢዎች ቢሮ የቀረበ ጥቆማ፦
ይህ ድርጅት ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚፈጽመውን የታክስ ስወራ የሚመለከተው የገቢዎች ባለስልጣን ጥብቅ ክትትል እንዲያደርግበት እናሳስባለን። ለክፍያው ማስረጃ የሚሆን የባንክ የክፍያ ስሊፕ (Bank Slip) በእጃችን የሚገኝ በመሆኑ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ እንጠይቃለን።
ማሳሰቢያ፦
ህዝባችን በዚህ ድርጅት እንዳይታለልና ገንዘቡን ለከንቱ ብክነት እንዳይዳርግ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን። "የየአብ መስታወት ስራ" (Yeab Glass) ላይ የሚሰሩ ሰራተኞችና ባለቤቶች ደንበኛን ማክበርና የገቡትን ቃል መፈጸም ሲገባቸው አሳሳች ስራ እየሰሩ በመሆኑ ህዝብ ሊያውቃቸው ይገባል።
3 months ago
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ተግዳሮቶች እና የመፍትሄ ጥቆማዎች: ከመንግስት የፋይናንስ ጥገኝነት እስከ ተጫዋቾች ደሞዝ ቀውስ
ክፍል 3
በዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ ለመሠረት ሚድያ
#ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስን መሰረታዊ ማነቆዎች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች የምንፈትሽበትን ይህንን ተከታታይ የጥናት ፅሁፍ በትኩረት እየተከታተላችሁ ስለሆነ ከልብ እናመሰግናለን።
በክፍል አንድ ጽሁፍ የክለቦቻችንን የመንግስታት የፋይናንስ ጥገኝነት፣ የመንግስት እጅ ያለበትን የአመራር አደረጃጀት እና ደካማ ተቋማዊ ቁመና መዳሰሳችን አይዘነጋም። ባለፈው በቀረበው የክፍል ሁለት ጽሁፍ ደግሞ፣ ወደ ክለቦቹ የውስጥ አሰራር በማተኮር ሶስት ወሳኝ ችግሮችን ተመልክተናል፣ እኝህም፦ በሰለጠነ የሰው ሃይል አለመመራታቸው፣ በክለቦች ውስጥ በጉልህ የሚታየው የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነትና ተጠያቂነት መጥፋት፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚፈታተነው የበጀት ዕቅድ እና አጠቃቀም ጉድለት ነበሩ።
እነዚህ እስካሁን የተመለከትናቸው ስድስት አንኳር ነጥቦች፣ የእግር ኳሳችንን የችግር ስረ-መሰረት በተወሰነ መጠን አሳይተውናል። በዛሬው የክፍል ሦስት ተከታታይ ፅሁፍ፣ የክለቦቻችንን ዕጣ ፈንታ እየወሰኑ ያሉ ተጨማሪ ተግዳሮቶች ተዳሰዋል። እስካሁን ስድስት መሰረታዊ ችግሮችን በዝርዝር የዳሰስን በመሆኑ፣ የዛሬውን ትንታኔያችንን የምንጀምረው በጥናቱ ከተለዩት ማነቆዎች መካከል ሰባተኛው ከሆነው (የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር) ተግዳሮት በመነሳት ይሆናል።
የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር
የተጫዋቾች የክፍያ አስተዳደር፣ ከበጀት ዕቅድ እና አጠቃቀም ጉድለት ጋር በተሳሰረ፣ በጥናቱ ተሳታፊዎች በስፋት እና በተደጋጋሚ የተነሳ የሊጉ ፈታኝ ነባራዊ ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል። የተጫዋቾች ክፍያ፣ ክለቦች ከሚመድቡት በጀት የአንበሳውን ድርሻ የያዘ ቢሆንም፣ የአገሪቷ እግር ኳስ ከደረሰበት ደረጃ ጋር ሲነጻጸር ወጪው እና በብሔራዊ ደረጃ ያለው ውጤት መካከል ከፍተኛ ክፍተት መታየቱ ጉዳዩ ላይ ጥያቄ እንደሚያስነሳ ነው።
የተጫዋቾች ደሞዝ ድርድር፣ የተጫዋቾች ደሞዝ አከፋፈል፣ የተጫዋቾች ዝውውር፣ የፊርማ ክፍያ፣ የማበረታቻ ክፍያ፣ ወዘተ በአግባቡ የሚተገበርበት መመሪያ አለመኖሩ እና የአሰራር ስርዓት አለመዘርጋቱ በዘልማዳዊ አሰራር ክፍያዎች እንደሚስተናገዱ የጥናቱ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።
ክለቦች፣ በየአመቱ ያላቸውን በጀት አስቀድሞ ማወቅ፣ ምን ያህል ተጫዋች ማምጣት እንዳለባቸው መተንበይ፣ እንዲሁም ተጫዋቾችን ሲቀጥሩ በምን አይነት መንገድ እንደሚያተርፏቸው፣ በምን ያህል መንገድ ክለቦቻቸውን እንደሚታደጓቸው፣ እና ሌሎች ተመሳሳይ በጥንቃቄ መያዝ ያለባቸው ጉዳዮችን በአግባቡ ሳይስተናገዱ እንደሚሰራ የጥናቱ ተሳታፊዎች በተደጋጋሚ ጠቁመዋል።
አብዛኞቹ ተሳታፊዎች፣ የተጨዋቾች ክፍያ የክለቦችን እውነተኛ አቅም ያላመጣጠነ ፣ ወጥ ያልሆነ የገበያ ዋጋ የሚታይበት፣ እና ከሃገራችን የኢኮኖሚ እድገት ጋር ያልተጣጣመ ነው ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል።
በመሆኑም፣ የአገራችንን እግር ኳስ እየበረዙ ካሉ ነባራዊ ሁኔታዎች መካከል የተጫዋቾች ደሞዝ አስተዳደር ቅድሚያ ትኩረት ሊቸረው የሚገባ ሆኖ ተነስቷል። ብዙዎች የጥናቱ ተሳታፊዎች፣ ተጫዋቾች ጥሩ ክፍያ ሊያገኙ ይገባል የሚል እምነት ያላቸው ሲሆን፣ ስጋታቸው በመሰረተ ልማቱ እና በደሞዝ ክፍያው መጠን መካካል ሚዛኑን ያልጠበቀ አካሄድ መኖሩ እንደሆነ እይታቸውን አጋርተዋል። በተለይም፣ የተደራጀ እንደ ቢሮ፣ ባለሞያ፣ እና ድርጅታዊ መዋቅር ሳይኖራቸው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለተጫዋች የመክፈሉ ባህል ብዙዎቹ ተሳታፊዎችን ግር ያሰኘ አሰራር መሆኑን ገልጸዋል።
የተጫዋቾች ደሞዝ መናር ጀርባ የተሳሰሩ ነባራዊ ሁኔታዎች መኖራቸውን ተሳታፊዎች ያነሱ ሲሆን በተደጋጋሚ ከተነሱት ነጥቦች መካከል፦ ክለቦች ዋንጫ ላይ ያተኩረ ግብ ሰንቀው የሚንቀሳቀሱ መሆኑ፣ የደሞዙ የገንዘብ ምንጭ በጥረት ከተሰባሰበ ገቢ ሳይሆን ከመንግስት ካዘና መሆኑ፣ የስምምነት ፊርማዎች በአንድ አመት የመገደብ ባህል መለመዱ፣ የሚሉ ይገኙበታል። ለደሞዝ የሚውለው ገንዘብ ምንጩ የመንግስት ካዘና መሆኑ ለክፍያው መናር እንደምክንያት እንደሚጠቀስም የጥናቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።
የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር ዙሪያ በተጠቀሱት እክሎች የተነሳ የተለያዩ መስተጓጉሎች በሊጉ ውድድሮች ላይ መድረሱን እንዲሁም ለደሞዝ የሚወጣውን ገንዘብ የሚመጥን ጥልቅ ምዘና በተጫዋቾቹ ዙሪያ አለመተግበሩን የጥናቱ ተሳታፊዎች ጠቁመዋል። የብዙዎቹን ምልከታ በሚገልጽ መልኩ የተጫዋቾች ኤጀንት የሆኑ አንድ ተሳታፊ የሚከተለውን አጋርተዋል፦
"ክለቦች፣ እጅ ጠብቀው የሚኖሩ ሆነው፣ ለመክፈል ቃል የሚገቡት ግን ከአቅማቸው በላይ ነው። በገንዘብ አቅም ምክኒያት፣ ፎርፌ የተሰጠበት፣ የውድድር ዓመቱን ከ23 ዓመት በታች ባለው ቡድኑ የተጨረሰበት አጋጣሚ አለ። መክፈል አቅቷቸው ደግሞ፣ ክርክር፣ ሸንጎ፣ ፍርድ ቤት የሚሄዱ አሉ። ሲቀጥሩ እንኳን ተጫዋቾቹን ጥልቅ በሆነ የቴክኒክ አናልስስ /ትንተና/ እና የሃኪም የአካል ብቃት ፍተሻ ማድረግ አልተለመደም። ‘ልመነው እስኪ’ በሚል በባለፈው አመት ፐርፎርማንስ ነው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለተጫዋች ደሞዝ የሚያፈሰው" ብለዋል
የተጫዋቾች ደሞዝን በሚመለከት በተሳታፊዎቹ በስፋት የተነሱ ነጥቦችን አንድ ፌዴሬሽኑን ወክለው በጥናቱ ከተካፈሉ ተሳታፊ በሚከተለው እይታቸው ያንጸባርቁታል።
"በተጫዋቾች ክፍያ ዙሪያ ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ለማስፈን ተጫዋቾቹ የሚከፍሉትን ታክስ ለሊጉ ሊያቀርቡ ይገባል። ለተጫዋቾች የሚቀርበው የማበረታቻ ክፍያ … ሊጤን ይገባል። የማበረታቻው ልዩነት፣ 3 ሺህ የሚቀርብለት ተጫዋች 25 ሺህ ከሚቀርበለት ተጫዋች ጋር የመደራደር ክፍተትን የሚፈጥር መሆን የለበትም።
ክለቦች በመሰረት ልማት ግንባታ እንዲሰማሩ እየተጠበቀ፣ በአሁኑ ወቅት ገቢያው የሚመራውን የደሞዝ ክፍያ እንዲቋቋሙ መጠበቅ አግባብ አይደለም። እነ ጨርቃጨርቅ፣ ምድር ባቡር፣ ሙገር ሲሚንቶ ያሉ ከለባት የመለማመጃ ቦታ እና የማረፊያ ቦታ ነበራቸው። ነገር ግን ቋሚ እሴቶች ላይ እየሰሩ በአንድ በኩል፣ እየናረ የመጣውን የተጫዋቾች ደሞዝ በሌላ በኩል ሊቋቋሙት አልቻሉም። ነገር ግን እነሱ የሰሩት ቋሚ ሃብት ለሌሎች ይተርፋል። ይህ የሚያሳይህ፣ ጤነኛ ያለሆነ የተጫዋቾች ክፍያ እንዳለ እና ለስፖርቱ እድገት ለሚተጋ፣ ያለው ሲስተም የማይመች መሆኑን ነው" ብለዋል
ምክረ- ሃሳብ፦ ለአገራችን እግር ኳስ ገጽታ እና ለሌሎች ራሳቸውን በአግባቡ ለሚያስተዳድሩ ጥቂት ክለቦች ስኬት፣ የተጫዋቾች የደሞዝ ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ላይ ሁለት አማራጭ መንገድ በምክረ ሃሳብነት ቀርቧል (እዚህ ጋር፣ ዝርዝር የመፍትሄ ሃሳቡ በዋናው ጥናት የቀረበ እና በዚህ ጽሁፍ ለአንባቢያን ባጠረ መልኩ የመፍትሄ ሃሳቡ የቀረበ መሆኑን መግለጽ ይጋባል)፦ አማራጭ አንድ፦ የአንድ የውድድር ዘመን የበጀት አመትን የፋይናንስ ዝርዝር እቅድ ከደብዳቤ ጋር አያይዞ ማቅረብ።
ይህም በአንድ ውድድር ዘመን ሊፈጠሩ ለሚችሉ ክፍተቶች ቀጥተኛ ተጠያቂነትን ያመጣል፤ አማራጭ ሁለት፦ አንድ ክለብ፣ የባንክ ሂሳብ መዝገቡን /bank book or bank statement/ ከዝርዝር የአመቱ የበጀት እቅድ ጋር አያይዞ ማቅረብ። የባንክ ሂሳብ መዝገብ ውስጥ ተቀምጦ የሚታየው የገንዘብ መጠን በአመቱ በጀት ውስጥ ከተጠቀሰው የወጪ መጠን መብለጥ ወይም እኩል መሆን አለበት። ሁለቱም የአማራጭ መንገዶችን በመተግበር ሂደት ውስጥ፣ ለአላማው መተግበር የሚቀርቡ ሰነዶች በሊጉ እና በክለቦች መካከል ብቻ በሚስጥር የሚቀመጡ መሆናቸውን ሊጉ የማስተማመኛ ደብዳቤ ሊያቀርብ ይገባል። ክለቦች ወደ ውድድር ለመግባትም ሊቀላቀሉ የሚቸሉት ከሚያሟሏቸው አመታዊ መስፈርቶች መካከል አንዱ ይህ ይሆናል።
ከዚህ በፊት አንደተጠቆመውም ተጫዋቾች የደሞዝ ታክስ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ሊጠየቅ ይገባል። ይህ ሪፖርት እና ሌሎች ለአላማው መተግበር በማንኛወም አካል የሚቀርቡ ሰነዶች በሊጉ እና በአቅራቢው መካከል ብቻ በሚስጥር የሚቀመጡ መሆናቸውን ሊጉ የማስተማመኛ ሰነድ ሊያቀርብ ይገባል።
ይህ አሰራር ከሚያስገኘው የአሰራር ግልጽነት እና ተጠያቂነት ባሻገር የክለቦችን እውነተኛ የመክፈል አቅምን ማመላከት ያስችላል፤ ተጫዋቾች የተስማሙበትን ደሞዝ (እና በወቅቱ) እንዲያገኙ ዋስትና ይሰጣል፤ በአንድ የውድድር ዘመን ውድድራቸውን የጀመሩ ክለቦች ውድድራቸውን እንደሚጨርሱ ለሊጉ ማስተማመኛ መስጫ አንድ መንገድ ሆኖ ያገለግላል። ለዚሁም የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ማውጣት የግድ ይላል።
ይህም ከሚያካትታቸው መካካል በበርካታ አገራት እንደሚከናወነው፣ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት ክለባት የውድድር ዘመናቸውን የሚያስጨርሳቸውን ገንዘብ በአካውንታቸው መኖሩን ማሳየት መቻል አለባቸው። በተያያዘም፣ ዲሲፕሊን እና ፐርፎርማንስ ጋር የተያያዘ የውል ማቋረጥ መስፈርቶች በግልጽ ሊቀረጹ ይገባል። በተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ውስጥ ከሚካተቱ ቁልፍ ነጥቦች መካከል የፊርማ፣ የማበረታቻ፣ የመደጎሚያ ክፍያዎች ይገኙበታል። ይህ አሰራር በአውሮፓ እና አሜሪካ ያሉ ሊጎች ዘንድ የተለመደ አሰራር ሲሆን፣ በዋናነት ክፍያዎች ሊያስከትሉት የሚችሉትን የፋይናንስ ቀውስ አስቀድሞ ለመቋቋም ያስችላል።
የገቢ ምንጮችን ማስፋፋት
የገቢ ምንጮች ማስፋፋትን በሚመለከት በተደጋጋሚ ከተነሱት ርዕሰ ጉዳዮች መካከል እግር ኳሱ ያለበት አንዱ ፈታኝ ነባራዊ ሁኔታ እንደሆነ ተመልክቷል። በተለይ፣ ክለቦች እግር ኳሱን እንደቢዝነስ የሚያዩበት አሰራር ያልተለመደ መሆኑን እና በጉዳዩ ላይ የአስተሳሰብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ በብዛት ተነስቷል።
የቡድን አርማ የያዙ ቁሳቁሶች ሽያጭ፣ የሚዲያ መብት ሽያጭ፣ ስፖንሰርሺፕ (የቡድን፣ የመለያ፣ የስም መጠሪያ)፣ የተጫዋቾች ግብይት፣ የተለያዩ የትኬት ሽያጮች፣ የስታዲየም ውስጥ አገልግሎቶች ሽያጭ፣ ወዘተ ያሉ የገቢ ምንጮችን ወደ ገንዘብ የመቀየር አሰራር በክለቦች ዘንድ መዳበር የሚገባው ነው።
በተለይ፣ ሌሎች አገሮች ከእነዚህ የገቢ ምንጮች የሚያሰባስቡት የገንዘብ መጠን ሲቃኝ፣ በአገራችን እየባከነ ያለ ሰፊ ሃብት መኖሩን ያመለክታል። በተለይ፣ ክለቦች የአካባቢያዊ መንግስት በጀት ጥገኛ መሆናቸው፣ በፈጠራ ላይ የታገዙ ዘዴዎችን ተጠቅመው ገቢ የማሰባሰብ ተነሳሽነታቸው ላይ የራሱን አሉታዊ ተጸዕኖ እንዳሳደረ ጠቁመዋል።
ክለቦች ተጨማሪ የገቢ ማስገኛ አማራጮችን በመፍጠር፣ የመንግስት በጀትን ደረጃ በደረጃ ወደ መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያውሉበትን መንገድ የመቅረጽ ቀጣይ ሃላፊነት የሊጉ እንዲሆንም ተሳታፊዎች በአጽዕኖት ጠይቀዋል። በርዕሰ ጉዳዩ ዙሪያ በርካታ ነገር ግን ተመሳሳይነት ያላቸው እይታዎች የተጋሩ ሲሆን፣ የብዙዎቹን አተያየት በሚወክል መንገድ፣ የክለብ አስተዳደር የሆኑ ተሳታፊ የሚከተለውን አካፍለዋል፦
“ክለቦች የራሳቸውን የገቢ ምንጭ አስፍተው መንቀሳቀሳቸው፣ መንግስትን ራሱን ቀጣዩን በጀት ለመልቀቅ የሚያበረታታ ይሆናል። ለምሳሌ፣ የሶስት ዓመት ስፖንሰር ብትፈራረም ለክለቡ ገቢ ነው፣ የክለቡ ባለቤት ለሆነው የከተማው መንግሰት ደግሞ የሶስት አመት ዕዳም፣ ሃላፊነትም ነው። እና፣ ገቢን ማሳደግ የተሳሰረ ጠቀሜታ አለው" ብለዋል።
ገቢ የማመንጨት ልምድን በሚመለከት የብዙ ተሳታፊዎችን ምልከታ፣ አንድ ደጋፊ የጥናቱ ተሳታፊ እንደሚከተለው አጋርተዋል፦
"እየባክኑ ያሉ ብዙ የገቢ ዕድሎች አሉ። ለምሳሌ፣ ‘ስንቱ ክለብ ነው በሚጫወትበት ሰዓት ስፖንሰሮቹን እያሰተዋወቀ ያለው?’ ስቴዲየሙም፣ የቲቪ ስክሪኑም እኮ ባዶ ነው። ገንዘቡ አነሰም በዛ፣ በስርጭት ወቅት የሚታይ ነገር የለም። ይህም ማለት መገኘት የሚችል ሃብት እየባከነ ነው።" ብለዋል
ገቢን በማሳደግ ዙሪያ፣ የተጫዋቾች ዝውውር እና የዝውውር ገቢያ ባህል ሊዳብር እንደሚገባው ተሳታፊዎች አንስተዋል። በገቢ ማሰባሰብ ዙሪያ ያሉ ማነቆዎች ለረጅም ጊዜ የተንከባለሉ የጥልቅ እና ውስብስብ ችግሮች ውጤት መሆናቸውን ተሳታፊዎች አንስተው፣ በጉዳዩ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ሁለገብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።
ምክረ ሃሳብ፦ ክለቦች የገቢ ማስፋፊያ ቢያንስ የሶስት አመት እቅዳቸውን እንዲያቀርቡ ሊጠየቅ ይገባል። አሰራሩን ለማዳበር፣ የአለፈውን አመት ዕቅድ ያሳኩ ክለባት የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት በተያዘው አመት ማጠናቀቂያ ላይ እንዲቀርብላቸው ይመከራል።
የገቢ ምንጮች አስተዳደርን በሚመለከት የስፖርት ቢዝነስ ማናጀመንት ስልጠና ለክለቦች አመራሮች ሊሠጣቸው ይገባል። ክለቦች ሊሰማሩባቸው የሚችሉባቸው መስኮች በሶስት ይከፈላሉ፦ ቀጥተኛ፣ ተዛማጅ እና አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች ወይም መንገዶች ናቸው።
ሀ) ክለቦች ቀጥተኛ የገቢ ምንጫቸውን ከስፖንሰርሺፕ፣ ከአካባቢያዊ የመገናኛ ብዙሃን የመብት ሽያጭ፣ የንግድ ምልክት ከያዙ ቁሳቁሶች የመብት ሽያጭ፣ ከስቴዲየም ትኬት፣ ከስታዲየም ውስጥ የእንግዳ መስተንግዶ ሽያጭ፣ ከተጫዋቾች ሽያጭና ከመሳሰሉት ማግኘት ይችላሉ።
ለ) ተዛማጅ የገቢ ምንጫቸውን ለማግኘት ደግሞ የሆቴል፣ የሬስቶራንት፣ የትጥቅ ማምረቻ ፣ የትራንስፖርት ንግድ፣ እና የኢነርጂ ምግብ እና መጠጥ አማራጮችን መጠቀም ይችላሉ ። የተዛማጅ ምንጮች፣ በአብዛኛው ወጪ የሚቀንሱ ሲሆኑ፣ በጊዜ ሂደት ወደ ገቢ ማመንጨት ሊደራጁ ይችላሉ። እኝህን የገቢ ምንጮች ተግባራዊ ለማድረግ፣ ክለቦች በሊዝ በመከራየት ሊያከናወኑ ይቻላሉ።
ሐ) አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች ከሚያካትታቸው መካከል ደግሞ ካፌ፣ ባዛር፣ ኮንሰርት፣ ብዙሃኑን ያሳተፈ ሩጫ፣ የመሳሰሉት ይገኙበታል።
ተዛማጅ እና አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች በባለቤትነት፣ በግዥ እና በሊዝ ወይም በኮንትራት ኪራይ ሊከናወኑ ይችላሉ።
ክለቦች በተለያዩ የንግድ ስራዎች በነጻነት እንዲሰማሩ፣ ወደ ህዝብነት ተለውጠው የንግድ ፈቃድ አውጥተው የሚንቀሳቀሱበት አሰራር ሊዘረጋ ይገባል።
የኢትዮጵያ ክለቦች ችግሮች ዘርፈ ብዙ ነው። ጽሁፉ በተከታታይ ክፍሎች የተሰናዳ ሲሆን አራተኛውን እና የመጨረሻውን የጥናቱ ግምገማ በቅርቡ እናቀርባለን
ስለ ፀሀፊው፦
ዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ በአሜሪካ ሜሪላንድ ታውሰን ዩኒቨርስቲ የስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ፕሮፌሰርና ተመራማሪ እንዲሁም በጀርመን ሙኒክ ቢዝነስ ስኩል የ5 ዶክትሬት ተማሪዎች አማካሪ ናቸው።
ዶ/ር ጋሻው በስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ዙሪያ በርካታ መፅሀፍትን የፃፉ አለም አቀፍ ተቋማትን የሚያማክሩና የሚያስተምሩ ምሁር ናቸው። እስካሁን 10 መፅሀፍትን አሳትመዋል። በስፖርት ማኔጅመንት ላይ ያተኮሩ ከ100 በላይ የሳይንሳዊ ምርምር የህትመት ውጤቶችን ለአንባቢዎች አቅርበዋል።
ክፍል 3
በዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ ለመሠረት ሚድያ
#ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስን መሰረታዊ ማነቆዎች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች የምንፈትሽበትን ይህንን ተከታታይ የጥናት ፅሁፍ በትኩረት እየተከታተላችሁ ስለሆነ ከልብ እናመሰግናለን።
በክፍል አንድ ጽሁፍ የክለቦቻችንን የመንግስታት የፋይናንስ ጥገኝነት፣ የመንግስት እጅ ያለበትን የአመራር አደረጃጀት እና ደካማ ተቋማዊ ቁመና መዳሰሳችን አይዘነጋም። ባለፈው በቀረበው የክፍል ሁለት ጽሁፍ ደግሞ፣ ወደ ክለቦቹ የውስጥ አሰራር በማተኮር ሶስት ወሳኝ ችግሮችን ተመልክተናል፣ እኝህም፦ በሰለጠነ የሰው ሃይል አለመመራታቸው፣ በክለቦች ውስጥ በጉልህ የሚታየው የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነትና ተጠያቂነት መጥፋት፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚፈታተነው የበጀት ዕቅድ እና አጠቃቀም ጉድለት ነበሩ።
እነዚህ እስካሁን የተመለከትናቸው ስድስት አንኳር ነጥቦች፣ የእግር ኳሳችንን የችግር ስረ-መሰረት በተወሰነ መጠን አሳይተውናል። በዛሬው የክፍል ሦስት ተከታታይ ፅሁፍ፣ የክለቦቻችንን ዕጣ ፈንታ እየወሰኑ ያሉ ተጨማሪ ተግዳሮቶች ተዳሰዋል። እስካሁን ስድስት መሰረታዊ ችግሮችን በዝርዝር የዳሰስን በመሆኑ፣ የዛሬውን ትንታኔያችንን የምንጀምረው በጥናቱ ከተለዩት ማነቆዎች መካከል ሰባተኛው ከሆነው (የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር) ተግዳሮት በመነሳት ይሆናል።
የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር
የተጫዋቾች የክፍያ አስተዳደር፣ ከበጀት ዕቅድ እና አጠቃቀም ጉድለት ጋር በተሳሰረ፣ በጥናቱ ተሳታፊዎች በስፋት እና በተደጋጋሚ የተነሳ የሊጉ ፈታኝ ነባራዊ ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል። የተጫዋቾች ክፍያ፣ ክለቦች ከሚመድቡት በጀት የአንበሳውን ድርሻ የያዘ ቢሆንም፣ የአገሪቷ እግር ኳስ ከደረሰበት ደረጃ ጋር ሲነጻጸር ወጪው እና በብሔራዊ ደረጃ ያለው ውጤት መካከል ከፍተኛ ክፍተት መታየቱ ጉዳዩ ላይ ጥያቄ እንደሚያስነሳ ነው።
የተጫዋቾች ደሞዝ ድርድር፣ የተጫዋቾች ደሞዝ አከፋፈል፣ የተጫዋቾች ዝውውር፣ የፊርማ ክፍያ፣ የማበረታቻ ክፍያ፣ ወዘተ በአግባቡ የሚተገበርበት መመሪያ አለመኖሩ እና የአሰራር ስርዓት አለመዘርጋቱ በዘልማዳዊ አሰራር ክፍያዎች እንደሚስተናገዱ የጥናቱ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።
ክለቦች፣ በየአመቱ ያላቸውን በጀት አስቀድሞ ማወቅ፣ ምን ያህል ተጫዋች ማምጣት እንዳለባቸው መተንበይ፣ እንዲሁም ተጫዋቾችን ሲቀጥሩ በምን አይነት መንገድ እንደሚያተርፏቸው፣ በምን ያህል መንገድ ክለቦቻቸውን እንደሚታደጓቸው፣ እና ሌሎች ተመሳሳይ በጥንቃቄ መያዝ ያለባቸው ጉዳዮችን በአግባቡ ሳይስተናገዱ እንደሚሰራ የጥናቱ ተሳታፊዎች በተደጋጋሚ ጠቁመዋል።
አብዛኞቹ ተሳታፊዎች፣ የተጨዋቾች ክፍያ የክለቦችን እውነተኛ አቅም ያላመጣጠነ ፣ ወጥ ያልሆነ የገበያ ዋጋ የሚታይበት፣ እና ከሃገራችን የኢኮኖሚ እድገት ጋር ያልተጣጣመ ነው ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል።
በመሆኑም፣ የአገራችንን እግር ኳስ እየበረዙ ካሉ ነባራዊ ሁኔታዎች መካከል የተጫዋቾች ደሞዝ አስተዳደር ቅድሚያ ትኩረት ሊቸረው የሚገባ ሆኖ ተነስቷል። ብዙዎች የጥናቱ ተሳታፊዎች፣ ተጫዋቾች ጥሩ ክፍያ ሊያገኙ ይገባል የሚል እምነት ያላቸው ሲሆን፣ ስጋታቸው በመሰረተ ልማቱ እና በደሞዝ ክፍያው መጠን መካካል ሚዛኑን ያልጠበቀ አካሄድ መኖሩ እንደሆነ እይታቸውን አጋርተዋል። በተለይም፣ የተደራጀ እንደ ቢሮ፣ ባለሞያ፣ እና ድርጅታዊ መዋቅር ሳይኖራቸው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለተጫዋች የመክፈሉ ባህል ብዙዎቹ ተሳታፊዎችን ግር ያሰኘ አሰራር መሆኑን ገልጸዋል።
የተጫዋቾች ደሞዝ መናር ጀርባ የተሳሰሩ ነባራዊ ሁኔታዎች መኖራቸውን ተሳታፊዎች ያነሱ ሲሆን በተደጋጋሚ ከተነሱት ነጥቦች መካከል፦ ክለቦች ዋንጫ ላይ ያተኩረ ግብ ሰንቀው የሚንቀሳቀሱ መሆኑ፣ የደሞዙ የገንዘብ ምንጭ በጥረት ከተሰባሰበ ገቢ ሳይሆን ከመንግስት ካዘና መሆኑ፣ የስምምነት ፊርማዎች በአንድ አመት የመገደብ ባህል መለመዱ፣ የሚሉ ይገኙበታል። ለደሞዝ የሚውለው ገንዘብ ምንጩ የመንግስት ካዘና መሆኑ ለክፍያው መናር እንደምክንያት እንደሚጠቀስም የጥናቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።
የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር ዙሪያ በተጠቀሱት እክሎች የተነሳ የተለያዩ መስተጓጉሎች በሊጉ ውድድሮች ላይ መድረሱን እንዲሁም ለደሞዝ የሚወጣውን ገንዘብ የሚመጥን ጥልቅ ምዘና በተጫዋቾቹ ዙሪያ አለመተግበሩን የጥናቱ ተሳታፊዎች ጠቁመዋል። የብዙዎቹን ምልከታ በሚገልጽ መልኩ የተጫዋቾች ኤጀንት የሆኑ አንድ ተሳታፊ የሚከተለውን አጋርተዋል፦
"ክለቦች፣ እጅ ጠብቀው የሚኖሩ ሆነው፣ ለመክፈል ቃል የሚገቡት ግን ከአቅማቸው በላይ ነው። በገንዘብ አቅም ምክኒያት፣ ፎርፌ የተሰጠበት፣ የውድድር ዓመቱን ከ23 ዓመት በታች ባለው ቡድኑ የተጨረሰበት አጋጣሚ አለ። መክፈል አቅቷቸው ደግሞ፣ ክርክር፣ ሸንጎ፣ ፍርድ ቤት የሚሄዱ አሉ። ሲቀጥሩ እንኳን ተጫዋቾቹን ጥልቅ በሆነ የቴክኒክ አናልስስ /ትንተና/ እና የሃኪም የአካል ብቃት ፍተሻ ማድረግ አልተለመደም። ‘ልመነው እስኪ’ በሚል በባለፈው አመት ፐርፎርማንስ ነው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለተጫዋች ደሞዝ የሚያፈሰው" ብለዋል
የተጫዋቾች ደሞዝን በሚመለከት በተሳታፊዎቹ በስፋት የተነሱ ነጥቦችን አንድ ፌዴሬሽኑን ወክለው በጥናቱ ከተካፈሉ ተሳታፊ በሚከተለው እይታቸው ያንጸባርቁታል።
"በተጫዋቾች ክፍያ ዙሪያ ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ለማስፈን ተጫዋቾቹ የሚከፍሉትን ታክስ ለሊጉ ሊያቀርቡ ይገባል። ለተጫዋቾች የሚቀርበው የማበረታቻ ክፍያ … ሊጤን ይገባል። የማበረታቻው ልዩነት፣ 3 ሺህ የሚቀርብለት ተጫዋች 25 ሺህ ከሚቀርበለት ተጫዋች ጋር የመደራደር ክፍተትን የሚፈጥር መሆን የለበትም።
ክለቦች በመሰረት ልማት ግንባታ እንዲሰማሩ እየተጠበቀ፣ በአሁኑ ወቅት ገቢያው የሚመራውን የደሞዝ ክፍያ እንዲቋቋሙ መጠበቅ አግባብ አይደለም። እነ ጨርቃጨርቅ፣ ምድር ባቡር፣ ሙገር ሲሚንቶ ያሉ ከለባት የመለማመጃ ቦታ እና የማረፊያ ቦታ ነበራቸው። ነገር ግን ቋሚ እሴቶች ላይ እየሰሩ በአንድ በኩል፣ እየናረ የመጣውን የተጫዋቾች ደሞዝ በሌላ በኩል ሊቋቋሙት አልቻሉም። ነገር ግን እነሱ የሰሩት ቋሚ ሃብት ለሌሎች ይተርፋል። ይህ የሚያሳይህ፣ ጤነኛ ያለሆነ የተጫዋቾች ክፍያ እንዳለ እና ለስፖርቱ እድገት ለሚተጋ፣ ያለው ሲስተም የማይመች መሆኑን ነው" ብለዋል
ምክረ- ሃሳብ፦ ለአገራችን እግር ኳስ ገጽታ እና ለሌሎች ራሳቸውን በአግባቡ ለሚያስተዳድሩ ጥቂት ክለቦች ስኬት፣ የተጫዋቾች የደሞዝ ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ላይ ሁለት አማራጭ መንገድ በምክረ ሃሳብነት ቀርቧል (እዚህ ጋር፣ ዝርዝር የመፍትሄ ሃሳቡ በዋናው ጥናት የቀረበ እና በዚህ ጽሁፍ ለአንባቢያን ባጠረ መልኩ የመፍትሄ ሃሳቡ የቀረበ መሆኑን መግለጽ ይጋባል)፦ አማራጭ አንድ፦ የአንድ የውድድር ዘመን የበጀት አመትን የፋይናንስ ዝርዝር እቅድ ከደብዳቤ ጋር አያይዞ ማቅረብ።
ይህም በአንድ ውድድር ዘመን ሊፈጠሩ ለሚችሉ ክፍተቶች ቀጥተኛ ተጠያቂነትን ያመጣል፤ አማራጭ ሁለት፦ አንድ ክለብ፣ የባንክ ሂሳብ መዝገቡን /bank book or bank statement/ ከዝርዝር የአመቱ የበጀት እቅድ ጋር አያይዞ ማቅረብ። የባንክ ሂሳብ መዝገብ ውስጥ ተቀምጦ የሚታየው የገንዘብ መጠን በአመቱ በጀት ውስጥ ከተጠቀሰው የወጪ መጠን መብለጥ ወይም እኩል መሆን አለበት። ሁለቱም የአማራጭ መንገዶችን በመተግበር ሂደት ውስጥ፣ ለአላማው መተግበር የሚቀርቡ ሰነዶች በሊጉ እና በክለቦች መካከል ብቻ በሚስጥር የሚቀመጡ መሆናቸውን ሊጉ የማስተማመኛ ደብዳቤ ሊያቀርብ ይገባል። ክለቦች ወደ ውድድር ለመግባትም ሊቀላቀሉ የሚቸሉት ከሚያሟሏቸው አመታዊ መስፈርቶች መካከል አንዱ ይህ ይሆናል።
ከዚህ በፊት አንደተጠቆመውም ተጫዋቾች የደሞዝ ታክስ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ሊጠየቅ ይገባል። ይህ ሪፖርት እና ሌሎች ለአላማው መተግበር በማንኛወም አካል የሚቀርቡ ሰነዶች በሊጉ እና በአቅራቢው መካከል ብቻ በሚስጥር የሚቀመጡ መሆናቸውን ሊጉ የማስተማመኛ ሰነድ ሊያቀርብ ይገባል።
ይህ አሰራር ከሚያስገኘው የአሰራር ግልጽነት እና ተጠያቂነት ባሻገር የክለቦችን እውነተኛ የመክፈል አቅምን ማመላከት ያስችላል፤ ተጫዋቾች የተስማሙበትን ደሞዝ (እና በወቅቱ) እንዲያገኙ ዋስትና ይሰጣል፤ በአንድ የውድድር ዘመን ውድድራቸውን የጀመሩ ክለቦች ውድድራቸውን እንደሚጨርሱ ለሊጉ ማስተማመኛ መስጫ አንድ መንገድ ሆኖ ያገለግላል። ለዚሁም የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ማውጣት የግድ ይላል።
ይህም ከሚያካትታቸው መካካል በበርካታ አገራት እንደሚከናወነው፣ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት ክለባት የውድድር ዘመናቸውን የሚያስጨርሳቸውን ገንዘብ በአካውንታቸው መኖሩን ማሳየት መቻል አለባቸው። በተያያዘም፣ ዲሲፕሊን እና ፐርፎርማንስ ጋር የተያያዘ የውል ማቋረጥ መስፈርቶች በግልጽ ሊቀረጹ ይገባል። በተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ውስጥ ከሚካተቱ ቁልፍ ነጥቦች መካከል የፊርማ፣ የማበረታቻ፣ የመደጎሚያ ክፍያዎች ይገኙበታል። ይህ አሰራር በአውሮፓ እና አሜሪካ ያሉ ሊጎች ዘንድ የተለመደ አሰራር ሲሆን፣ በዋናነት ክፍያዎች ሊያስከትሉት የሚችሉትን የፋይናንስ ቀውስ አስቀድሞ ለመቋቋም ያስችላል።
የገቢ ምንጮችን ማስፋፋት
የገቢ ምንጮች ማስፋፋትን በሚመለከት በተደጋጋሚ ከተነሱት ርዕሰ ጉዳዮች መካከል እግር ኳሱ ያለበት አንዱ ፈታኝ ነባራዊ ሁኔታ እንደሆነ ተመልክቷል። በተለይ፣ ክለቦች እግር ኳሱን እንደቢዝነስ የሚያዩበት አሰራር ያልተለመደ መሆኑን እና በጉዳዩ ላይ የአስተሳሰብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ በብዛት ተነስቷል።
የቡድን አርማ የያዙ ቁሳቁሶች ሽያጭ፣ የሚዲያ መብት ሽያጭ፣ ስፖንሰርሺፕ (የቡድን፣ የመለያ፣ የስም መጠሪያ)፣ የተጫዋቾች ግብይት፣ የተለያዩ የትኬት ሽያጮች፣ የስታዲየም ውስጥ አገልግሎቶች ሽያጭ፣ ወዘተ ያሉ የገቢ ምንጮችን ወደ ገንዘብ የመቀየር አሰራር በክለቦች ዘንድ መዳበር የሚገባው ነው።
በተለይ፣ ሌሎች አገሮች ከእነዚህ የገቢ ምንጮች የሚያሰባስቡት የገንዘብ መጠን ሲቃኝ፣ በአገራችን እየባከነ ያለ ሰፊ ሃብት መኖሩን ያመለክታል። በተለይ፣ ክለቦች የአካባቢያዊ መንግስት በጀት ጥገኛ መሆናቸው፣ በፈጠራ ላይ የታገዙ ዘዴዎችን ተጠቅመው ገቢ የማሰባሰብ ተነሳሽነታቸው ላይ የራሱን አሉታዊ ተጸዕኖ እንዳሳደረ ጠቁመዋል።
ክለቦች ተጨማሪ የገቢ ማስገኛ አማራጮችን በመፍጠር፣ የመንግስት በጀትን ደረጃ በደረጃ ወደ መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያውሉበትን መንገድ የመቅረጽ ቀጣይ ሃላፊነት የሊጉ እንዲሆንም ተሳታፊዎች በአጽዕኖት ጠይቀዋል። በርዕሰ ጉዳዩ ዙሪያ በርካታ ነገር ግን ተመሳሳይነት ያላቸው እይታዎች የተጋሩ ሲሆን፣ የብዙዎቹን አተያየት በሚወክል መንገድ፣ የክለብ አስተዳደር የሆኑ ተሳታፊ የሚከተለውን አካፍለዋል፦
“ክለቦች የራሳቸውን የገቢ ምንጭ አስፍተው መንቀሳቀሳቸው፣ መንግስትን ራሱን ቀጣዩን በጀት ለመልቀቅ የሚያበረታታ ይሆናል። ለምሳሌ፣ የሶስት ዓመት ስፖንሰር ብትፈራረም ለክለቡ ገቢ ነው፣ የክለቡ ባለቤት ለሆነው የከተማው መንግሰት ደግሞ የሶስት አመት ዕዳም፣ ሃላፊነትም ነው። እና፣ ገቢን ማሳደግ የተሳሰረ ጠቀሜታ አለው" ብለዋል።
ገቢ የማመንጨት ልምድን በሚመለከት የብዙ ተሳታፊዎችን ምልከታ፣ አንድ ደጋፊ የጥናቱ ተሳታፊ እንደሚከተለው አጋርተዋል፦
"እየባክኑ ያሉ ብዙ የገቢ ዕድሎች አሉ። ለምሳሌ፣ ‘ስንቱ ክለብ ነው በሚጫወትበት ሰዓት ስፖንሰሮቹን እያሰተዋወቀ ያለው?’ ስቴዲየሙም፣ የቲቪ ስክሪኑም እኮ ባዶ ነው። ገንዘቡ አነሰም በዛ፣ በስርጭት ወቅት የሚታይ ነገር የለም። ይህም ማለት መገኘት የሚችል ሃብት እየባከነ ነው።" ብለዋል
ገቢን በማሳደግ ዙሪያ፣ የተጫዋቾች ዝውውር እና የዝውውር ገቢያ ባህል ሊዳብር እንደሚገባው ተሳታፊዎች አንስተዋል። በገቢ ማሰባሰብ ዙሪያ ያሉ ማነቆዎች ለረጅም ጊዜ የተንከባለሉ የጥልቅ እና ውስብስብ ችግሮች ውጤት መሆናቸውን ተሳታፊዎች አንስተው፣ በጉዳዩ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ሁለገብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።
ምክረ ሃሳብ፦ ክለቦች የገቢ ማስፋፊያ ቢያንስ የሶስት አመት እቅዳቸውን እንዲያቀርቡ ሊጠየቅ ይገባል። አሰራሩን ለማዳበር፣ የአለፈውን አመት ዕቅድ ያሳኩ ክለባት የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት በተያዘው አመት ማጠናቀቂያ ላይ እንዲቀርብላቸው ይመከራል።
የገቢ ምንጮች አስተዳደርን በሚመለከት የስፖርት ቢዝነስ ማናጀመንት ስልጠና ለክለቦች አመራሮች ሊሠጣቸው ይገባል። ክለቦች ሊሰማሩባቸው የሚችሉባቸው መስኮች በሶስት ይከፈላሉ፦ ቀጥተኛ፣ ተዛማጅ እና አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች ወይም መንገዶች ናቸው።
ሀ) ክለቦች ቀጥተኛ የገቢ ምንጫቸውን ከስፖንሰርሺፕ፣ ከአካባቢያዊ የመገናኛ ብዙሃን የመብት ሽያጭ፣ የንግድ ምልክት ከያዙ ቁሳቁሶች የመብት ሽያጭ፣ ከስቴዲየም ትኬት፣ ከስታዲየም ውስጥ የእንግዳ መስተንግዶ ሽያጭ፣ ከተጫዋቾች ሽያጭና ከመሳሰሉት ማግኘት ይችላሉ።
ለ) ተዛማጅ የገቢ ምንጫቸውን ለማግኘት ደግሞ የሆቴል፣ የሬስቶራንት፣ የትጥቅ ማምረቻ ፣ የትራንስፖርት ንግድ፣ እና የኢነርጂ ምግብ እና መጠጥ አማራጮችን መጠቀም ይችላሉ ። የተዛማጅ ምንጮች፣ በአብዛኛው ወጪ የሚቀንሱ ሲሆኑ፣ በጊዜ ሂደት ወደ ገቢ ማመንጨት ሊደራጁ ይችላሉ። እኝህን የገቢ ምንጮች ተግባራዊ ለማድረግ፣ ክለቦች በሊዝ በመከራየት ሊያከናወኑ ይቻላሉ።
ሐ) አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች ከሚያካትታቸው መካከል ደግሞ ካፌ፣ ባዛር፣ ኮንሰርት፣ ብዙሃኑን ያሳተፈ ሩጫ፣ የመሳሰሉት ይገኙበታል።
ተዛማጅ እና አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች በባለቤትነት፣ በግዥ እና በሊዝ ወይም በኮንትራት ኪራይ ሊከናወኑ ይችላሉ።
ክለቦች በተለያዩ የንግድ ስራዎች በነጻነት እንዲሰማሩ፣ ወደ ህዝብነት ተለውጠው የንግድ ፈቃድ አውጥተው የሚንቀሳቀሱበት አሰራር ሊዘረጋ ይገባል።
የኢትዮጵያ ክለቦች ችግሮች ዘርፈ ብዙ ነው። ጽሁፉ በተከታታይ ክፍሎች የተሰናዳ ሲሆን አራተኛውን እና የመጨረሻውን የጥናቱ ግምገማ በቅርቡ እናቀርባለን
ስለ ፀሀፊው፦
ዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ በአሜሪካ ሜሪላንድ ታውሰን ዩኒቨርስቲ የስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ፕሮፌሰርና ተመራማሪ እንዲሁም በጀርመን ሙኒክ ቢዝነስ ስኩል የ5 ዶክትሬት ተማሪዎች አማካሪ ናቸው።
ዶ/ር ጋሻው በስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ዙሪያ በርካታ መፅሀፍትን የፃፉ አለም አቀፍ ተቋማትን የሚያማክሩና የሚያስተምሩ ምሁር ናቸው። እስካሁን 10 መፅሀፍትን አሳትመዋል። በስፖርት ማኔጅመንት ላይ ያተኮሩ ከ100 በላይ የሳይንሳዊ ምርምር የህትመት ውጤቶችን ለአንባቢዎች አቅርበዋል።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የኬንያው ግዙፍ ባንክ ኬሲቢ (KCB) በኢትዮጵያ የሚገዛውን ባንክ መለየቱን አስታወቀ
#ethiopia | በሀብት መጠኑ በምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ከሆኑ የፋይናንስ ተቋማት አንዱ የሆነው ኬሲቢ ግሩፕ (KCB Group)፣ ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት ሲያደርገው የነበረው ዝግጅት መጠናቀቁን ገለጸ። ባንኩ በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ውስጥ ድርሻ የሚገዛበትን አንድ የሀገር ውስጥ ባንክ መለየቱንም በይፋ አስታውቋል።
ወደ ኢትዮጵያ ገበያ የመግቢያ ስትራቴጂ
ኬሲቢ ግሩፕ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ የአገናኝ ቢሮ (Representative Office) ከፍቶ ሲንቀሳቀስ የቆየ ቢሆንም፣ አሁን ግን የኢትዮጵያ መንግሥት የባንክ ዘርፉን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጉን ተከትሎ በባለቤትነት ለመሳተፍ ወስኗል።
* ግዥው፦ ባንኩ የትኛውን የሀገር ውስጥ ባንክ እንደሚገዛ በስም ባይገልጽም፣ ሂደቱ ግን የተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁሟል።
* ዓላማው፦ የኬንያ ባንኮች ያላቸውን ሰፊ ልምድና የቴክኖሎጂ አቅም በመጠቀም በኢትዮጵያ ያለውን ሰፊ የፋይናንስ ፍላጎት ለመጠቀም ያለመ ነው።
በምሥራቅ አፍሪካ ያለው ተጽዕኖ
ይህ የኬሲቢ ውሳኔ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ያለውን ፉክክር ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋግረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ቀደም ሲል ሌላኛው የኬንያ ግዙፍ ባንክ ኤኩይቲ ባንክ (Equity Bank) ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ፍላጎት ማሳየቱ የሚታወስ ሲሆን፣ የኬሲቢ ቀዳሚ መሆን ግን በገበያው ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል።
📉 የገበያው አንድምታ
የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸው፦
* ለሀገር ውስጥ ባንኮች ከፍተኛ የውድድር መንፈስ ይፈጥራል።
* አዳዲስ የፋይናንስ ቴክኖሎጂዎችና የብድር አቅርቦቶች እንዲስፋፉ ይረዳል።
* የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ፍሰትን ያሳድጋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ኢትዮጵያ #ባንክ #ኬሲቢ #ኢኮኖሚ #ኬንያ #ኢንቨስትመንት #ethiopia #banking #kcb #kenya #businessnews
#ethiopia | በሀብት መጠኑ በምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ከሆኑ የፋይናንስ ተቋማት አንዱ የሆነው ኬሲቢ ግሩፕ (KCB Group)፣ ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት ሲያደርገው የነበረው ዝግጅት መጠናቀቁን ገለጸ። ባንኩ በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ውስጥ ድርሻ የሚገዛበትን አንድ የሀገር ውስጥ ባንክ መለየቱንም በይፋ አስታውቋል።
ወደ ኢትዮጵያ ገበያ የመግቢያ ስትራቴጂ
ኬሲቢ ግሩፕ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ የአገናኝ ቢሮ (Representative Office) ከፍቶ ሲንቀሳቀስ የቆየ ቢሆንም፣ አሁን ግን የኢትዮጵያ መንግሥት የባንክ ዘርፉን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጉን ተከትሎ በባለቤትነት ለመሳተፍ ወስኗል።
* ግዥው፦ ባንኩ የትኛውን የሀገር ውስጥ ባንክ እንደሚገዛ በስም ባይገልጽም፣ ሂደቱ ግን የተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁሟል።
* ዓላማው፦ የኬንያ ባንኮች ያላቸውን ሰፊ ልምድና የቴክኖሎጂ አቅም በመጠቀም በኢትዮጵያ ያለውን ሰፊ የፋይናንስ ፍላጎት ለመጠቀም ያለመ ነው።
በምሥራቅ አፍሪካ ያለው ተጽዕኖ
ይህ የኬሲቢ ውሳኔ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ያለውን ፉክክር ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋግረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ቀደም ሲል ሌላኛው የኬንያ ግዙፍ ባንክ ኤኩይቲ ባንክ (Equity Bank) ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ፍላጎት ማሳየቱ የሚታወስ ሲሆን፣ የኬሲቢ ቀዳሚ መሆን ግን በገበያው ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል።
📉 የገበያው አንድምታ
የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸው፦
* ለሀገር ውስጥ ባንኮች ከፍተኛ የውድድር መንፈስ ይፈጥራል።
* አዳዲስ የፋይናንስ ቴክኖሎጂዎችና የብድር አቅርቦቶች እንዲስፋፉ ይረዳል።
* የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ፍሰትን ያሳድጋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ኢትዮጵያ #ባንክ #ኬሲቢ #ኢኮኖሚ #ኬንያ #ኢንቨስትመንት #ethiopia #banking #kcb #kenya #businessnews
3 months ago
የእርዳታ ተማጽኖ
#ethiopia | ለወጣቷ ሰብለ አሰፋ የህይወት አድን ጥሪ
ከካንሰር ጋር የምታደርገውን ትግል እንድታሸንፍ እንርዳት
#ethiopia | የደቡብ ጎንደር የወረታ ከተማ ተወላጅ የሆነችው የ21 ዓመቷ ወጣት ሰብለ አሰፋ፣ የትዳር ህይወቷን በደስታ ጀምራ ነበር።
ነገር ግን ይህ የደስታ ጊዜዋ ብዙም ሳይቆይ በአስደንጋጭ የጤና እክል ተተካ። መጀመሪያ ላይ የእርግዝና ምልክት መስሏት የነበረው ድካምና የትንፋሽ መቆራረጥ፣ ምርመራ ሲደረግላት ግን "አኪውት ማይሎብላስቲክ ሌውኬሚያ" (Acute Myeloblastic Leukemia) የተሰኘ ፈጣንና አስከፊ የደም ካንሰር መሆኑ ታወቀ።
ሰብለ ካንሰሩ ሲታወቅባት የ24 ሳምንት ነፍሰ ጡር ነበረች።
ዶክተሮች ካንሰሩን እያከሙ ፅንሱን ለማዳን ጥረት ቢያደርጉም፣ በህመሙ መፅናት ምክንያት ልጇ በማህፀን ውስጥ ሊሞት ችሏል።
በጥቂት ወራት ውስጥ የትዳር ደስታዋን፣ ልጇን እና ጤናዋን ያጣችው ሰብለ፣ አሁን ከሞት ጋር ብርቱ ትግል እያደረገች ትገኛለች።
በደጋፊዎች እርዳታ ወደ ህንድ ሀገር ለህክምና ያመራችው ሰብለ፣ ባለፉት ሦስት ወራት ሁለት ዙር የኬሞቴራፒ ህክምና ብታደርግም ካንሰሩ ሊጠፋላት አልቻለም።
አሁን ዶክተሮች ብቸኛው የህይወት ማዳኛ አማራጭ "የአጥንት መቅኒ ንቅለ ተከላ" (Bone Marrow Transplant) መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን የህይወት አድን ህክምና ለማድረግ እና ሌሎች ተያያዥ ወጪዎችን ለመሸፈን 20,000 የአሜሪካ ዶላር በአስቸኳይ ያስፈልጋታል።
ሰብለ ገና 21 ዓመቷ ነው፤ መኖር ትፈልጋለች። ይህንን የገንዘብ አቅም ብቻዋን መቋቋም ስለማትችል ሁላችንም ከጎኗ እንቁም።
(የጎፈንድሚ (GoFundMe) ሊንክ : https://gofund.me/905858c8...
CBE: 1000220940121
Abay Bank: 2081011096364019
Telebirr: 0918094300
Tewodros Wondimu
ሰብለና ቤተሰቦቿ ይህንን አስቸጋሪ ጊዜ እንዲያልፉ በጸሎታችሁ አስቧቸው።
ለሰብለ የምናደርገው እያንዳንዷ በጎነት ለህይወቷ ትልቅ ተስፋ ናት። ዛሬ ለወገን ደራሽ እንሁን።
#ሰብለአሰፋ #ለወገንደራሽ #ኢትዮጵያ #የደምካንሰር #እርዳታ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ለወጣቷ ሰብለ አሰፋ የህይወት አድን ጥሪ
ከካንሰር ጋር የምታደርገውን ትግል እንድታሸንፍ እንርዳት
#ethiopia | የደቡብ ጎንደር የወረታ ከተማ ተወላጅ የሆነችው የ21 ዓመቷ ወጣት ሰብለ አሰፋ፣ የትዳር ህይወቷን በደስታ ጀምራ ነበር።
ነገር ግን ይህ የደስታ ጊዜዋ ብዙም ሳይቆይ በአስደንጋጭ የጤና እክል ተተካ። መጀመሪያ ላይ የእርግዝና ምልክት መስሏት የነበረው ድካምና የትንፋሽ መቆራረጥ፣ ምርመራ ሲደረግላት ግን "አኪውት ማይሎብላስቲክ ሌውኬሚያ" (Acute Myeloblastic Leukemia) የተሰኘ ፈጣንና አስከፊ የደም ካንሰር መሆኑ ታወቀ።
ሰብለ ካንሰሩ ሲታወቅባት የ24 ሳምንት ነፍሰ ጡር ነበረች።
ዶክተሮች ካንሰሩን እያከሙ ፅንሱን ለማዳን ጥረት ቢያደርጉም፣ በህመሙ መፅናት ምክንያት ልጇ በማህፀን ውስጥ ሊሞት ችሏል።
በጥቂት ወራት ውስጥ የትዳር ደስታዋን፣ ልጇን እና ጤናዋን ያጣችው ሰብለ፣ አሁን ከሞት ጋር ብርቱ ትግል እያደረገች ትገኛለች።
በደጋፊዎች እርዳታ ወደ ህንድ ሀገር ለህክምና ያመራችው ሰብለ፣ ባለፉት ሦስት ወራት ሁለት ዙር የኬሞቴራፒ ህክምና ብታደርግም ካንሰሩ ሊጠፋላት አልቻለም።
አሁን ዶክተሮች ብቸኛው የህይወት ማዳኛ አማራጭ "የአጥንት መቅኒ ንቅለ ተከላ" (Bone Marrow Transplant) መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን የህይወት አድን ህክምና ለማድረግ እና ሌሎች ተያያዥ ወጪዎችን ለመሸፈን 20,000 የአሜሪካ ዶላር በአስቸኳይ ያስፈልጋታል።
ሰብለ ገና 21 ዓመቷ ነው፤ መኖር ትፈልጋለች። ይህንን የገንዘብ አቅም ብቻዋን መቋቋም ስለማትችል ሁላችንም ከጎኗ እንቁም።
(የጎፈንድሚ (GoFundMe) ሊንክ : https://gofund.me/905858c8...
CBE: 1000220940121
Abay Bank: 2081011096364019
Telebirr: 0918094300
Tewodros Wondimu
ሰብለና ቤተሰቦቿ ይህንን አስቸጋሪ ጊዜ እንዲያልፉ በጸሎታችሁ አስቧቸው።
ለሰብለ የምናደርገው እያንዳንዷ በጎነት ለህይወቷ ትልቅ ተስፋ ናት። ዛሬ ለወገን ደራሽ እንሁን።
#ሰብለአሰፋ #ለወገንደራሽ #ኢትዮጵያ #የደምካንሰር #እርዳታ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
በዴንማርክ የሚገኝ የወንድ የዘር ፍሬ ባንክ በለጋሾች ላይ የIQ ምርመራ እንዲደረግ መመሪያ አወጣ
በዴንማርክ የሚገኝ አንድ ታዋቂ የወንድ የዘር ፍሬ ባንክ (Sperm Bank) ሊለግሱ የሚመጡ ወንዶች የላቀ የማሰብ ችሎታ ወይም IQ ምርመራ እንዲያደርጉ የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ ማውጣቱን አስታወቀ።
በመመሪያው መሠረት በፈተናው ላይ ከ85 ነጥብ በታች የሚያስመዘግቡ አመልካቾች ለጋሽ መሆን አይችሉም።
ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ለተለያዩ የዓለም ክፍሎች የዘር ፍሬ የሚያከፋፍለው ‘ዶነር ኔትወርክ’ (Donor Network) የተባለ ድርጅት ነው።
ዴንማርክ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ መጠን ያለው የወንድ የዘር ፍሬ ለተለያዩ ሀገራት የፅንስ ሕክምና ክሊኒኮች በመላክ ቀዳሚዋ ሀገር መሆኗ ይታወቃል።
የኩባንያው ተወካዮች እንደሚሉት ከሆነ፣ ይህ የምርመራ ሂደት ደንበኞቻቸው የሚጠብቁትን የጥራት ደረጃ ለማሟላት ታስቦ የተዘጋጀ ነው። አብዛኛውን ጊዜ ለጋሾች የሕክምና ታሪካቸው፣ የስነ-ልቦና ግምገማቸው እና የግል ስብዕናቸው በዝርዝር ተጠንቶ ለተረካቢዎች የሚቀርብ ቢሆንም፣ አሁን የIQ ምርመራው መታከሉ ሂደቱን ይበልጥ የተሟላ ያደርገዋል።
ይሁን እንጂ ይህ አዲስ አሰራር በስነ-ምግባር እና በሕክምና ባለሙያዎች ዘንድ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።
ተቺዎች እንደሚሉት ከሆነ፣ አንድ ሰው በፈተና የሚያመጣው ውጤት ለወደፊት ልጅ ጥሩ ወላጅ የመሆን ብቃቱን ወይም የልጁን የተፈጥሮ ተሰጥኦ በትክክል ሊያሳይ አይችልም።
ይህ ጉዳይ በዘር ምርጫ (Genetic Selection) እና በመራቢያ ቴክኖሎጂ ዙሪያ ያሉ ሰፋ ያሉ የሞራል እና የሳይንስ ጥያቄዎችን ዳግም የቀሰቀሰ ሲሆን፣ በዘርፉ ያሉ ፖሊሲዎች ወደፊትም አከራካሪነታቸው እንደሚቀጥል ተመልክቷል።
seledadotio
seledadotio
በዴንማርክ የሚገኝ አንድ ታዋቂ የወንድ የዘር ፍሬ ባንክ (Sperm Bank) ሊለግሱ የሚመጡ ወንዶች የላቀ የማሰብ ችሎታ ወይም IQ ምርመራ እንዲያደርጉ የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ ማውጣቱን አስታወቀ።
በመመሪያው መሠረት በፈተናው ላይ ከ85 ነጥብ በታች የሚያስመዘግቡ አመልካቾች ለጋሽ መሆን አይችሉም።
ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ለተለያዩ የዓለም ክፍሎች የዘር ፍሬ የሚያከፋፍለው ‘ዶነር ኔትወርክ’ (Donor Network) የተባለ ድርጅት ነው።
ዴንማርክ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ መጠን ያለው የወንድ የዘር ፍሬ ለተለያዩ ሀገራት የፅንስ ሕክምና ክሊኒኮች በመላክ ቀዳሚዋ ሀገር መሆኗ ይታወቃል።
የኩባንያው ተወካዮች እንደሚሉት ከሆነ፣ ይህ የምርመራ ሂደት ደንበኞቻቸው የሚጠብቁትን የጥራት ደረጃ ለማሟላት ታስቦ የተዘጋጀ ነው። አብዛኛውን ጊዜ ለጋሾች የሕክምና ታሪካቸው፣ የስነ-ልቦና ግምገማቸው እና የግል ስብዕናቸው በዝርዝር ተጠንቶ ለተረካቢዎች የሚቀርብ ቢሆንም፣ አሁን የIQ ምርመራው መታከሉ ሂደቱን ይበልጥ የተሟላ ያደርገዋል።
ይሁን እንጂ ይህ አዲስ አሰራር በስነ-ምግባር እና በሕክምና ባለሙያዎች ዘንድ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።
ተቺዎች እንደሚሉት ከሆነ፣ አንድ ሰው በፈተና የሚያመጣው ውጤት ለወደፊት ልጅ ጥሩ ወላጅ የመሆን ብቃቱን ወይም የልጁን የተፈጥሮ ተሰጥኦ በትክክል ሊያሳይ አይችልም።
ይህ ጉዳይ በዘር ምርጫ (Genetic Selection) እና በመራቢያ ቴክኖሎጂ ዙሪያ ያሉ ሰፋ ያሉ የሞራል እና የሳይንስ ጥያቄዎችን ዳግም የቀሰቀሰ ሲሆን፣ በዘርፉ ያሉ ፖሊሲዎች ወደፊትም አከራካሪነታቸው እንደሚቀጥል ተመልክቷል።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
አስቸኳይ የሕይወት አድን ጥሪ
የአንዲት እናትን ሕይወት እንታደግ
#ethiopia | ባለ ትዳርና የአንዲት ሴት ልጅ እናት የሆነችው ወይዘሮ መቅደስ ሰለሞን፣ በደረሰባት ጽኑ የልብ ሕመም ምክንያት ሕይወቷ አደጋ ላይ ወድቋል። ቀደም ሲል ቤተሰቦቿ ያላቸውን ጥሪት በማሟጠጥ ሕንድ አገር ድረስ ሄዳ የታከመች ቢሆንም፣ አሁን ግን የልቧ ቱቦ በመጥበቡ ምክንያት በአፋጣኝ ሌላ ቀዶ ጥገና እንዲደረግላት በታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ጥገና ማዕከል ተወስኖባታል።
ለዚህ ሕክምና ከ 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር በላይ ያስፈልጋል። ባለቤቷ አቶ ወንድማገኝ ጌታቸው በአንድ የግል ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ በሚያገኘው አነስተኛ ገቢ ይህን ከፍተኛ ወጪ መሸፈን በፍጹም የማይቻል ሆኖባቸዋል።
"ሰማይ ተደፍቶብናል" የሚሉት ቤተሰቦቿ፣ የወገን ያለህ እያሉ ይማጸናሉ።
ይህች እናት ወደ ልጇና ወደ ባለቤቷ በጤና ተመልሳ እንድትቀላቀል፣ እኛ ወገኖቿ በአቅማችን ያለውን ድጋፍ እንድናደርግላት በፈጣሪ ስም ጥሪ ቀርቧል። ዛሬ የምናደርገው ጥቂት እርዳታ የአንዲትን እናት ሕይወት ይታደጋል።
ድጋፍ ለማድረግ (በባንክ አካውንቶቻቸው)፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000361917468
አዋሽ ባንክ (Awash Bank)፦ 01349432281700
ስም፦ መቅደስ ሰለሞን / ወንድማገኝ ጌታቸው
ስልክ ቁጥሮች፦
📞 0911 74 72 53
📞 0966 98 44 11
የሰጠ አይጎድልበትም! እባክዎን ይህንን መረጃ Share በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ ይተባበሩን።
#የእርዳታጥሪ #መቅደስሰለሞን #የልብሕክምና #ኢትዮጵያ #savemekdes #medicalhelp #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
የአንዲት እናትን ሕይወት እንታደግ
#ethiopia | ባለ ትዳርና የአንዲት ሴት ልጅ እናት የሆነችው ወይዘሮ መቅደስ ሰለሞን፣ በደረሰባት ጽኑ የልብ ሕመም ምክንያት ሕይወቷ አደጋ ላይ ወድቋል። ቀደም ሲል ቤተሰቦቿ ያላቸውን ጥሪት በማሟጠጥ ሕንድ አገር ድረስ ሄዳ የታከመች ቢሆንም፣ አሁን ግን የልቧ ቱቦ በመጥበቡ ምክንያት በአፋጣኝ ሌላ ቀዶ ጥገና እንዲደረግላት በታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ጥገና ማዕከል ተወስኖባታል።
ለዚህ ሕክምና ከ 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር በላይ ያስፈልጋል። ባለቤቷ አቶ ወንድማገኝ ጌታቸው በአንድ የግል ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ በሚያገኘው አነስተኛ ገቢ ይህን ከፍተኛ ወጪ መሸፈን በፍጹም የማይቻል ሆኖባቸዋል።
"ሰማይ ተደፍቶብናል" የሚሉት ቤተሰቦቿ፣ የወገን ያለህ እያሉ ይማጸናሉ።
ይህች እናት ወደ ልጇና ወደ ባለቤቷ በጤና ተመልሳ እንድትቀላቀል፣ እኛ ወገኖቿ በአቅማችን ያለውን ድጋፍ እንድናደርግላት በፈጣሪ ስም ጥሪ ቀርቧል። ዛሬ የምናደርገው ጥቂት እርዳታ የአንዲትን እናት ሕይወት ይታደጋል።
ድጋፍ ለማድረግ (በባንክ አካውንቶቻቸው)፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000361917468
አዋሽ ባንክ (Awash Bank)፦ 01349432281700
ስም፦ መቅደስ ሰለሞን / ወንድማገኝ ጌታቸው
ስልክ ቁጥሮች፦
📞 0911 74 72 53
📞 0966 98 44 11
የሰጠ አይጎድልበትም! እባክዎን ይህንን መረጃ Share በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ ይተባበሩን።
#የእርዳታጥሪ #መቅደስሰለሞን #የልብሕክምና #ኢትዮጵያ #savemekdes #medicalhelp #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
3 months ago
ዳሽን ባንክ ለደንበኞቹ የኢፍጣር መርሃ ግብር አዘጋጀ
#ethiopia | ዳሽን ባንክ የረመዳን ወርን ምክንያት በማድረግ ለደንበኞቹ ያዘጋጀውን ልዩ የኢፍጣር መርሃ ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል አካሄደ።
መርሃ ግብሩ ባንኩ ያለውን ማህበራዊ ተሳትፎ ለማሳደግና ከደንበኞቹ ጋር ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በዝግጅቱ ላይ የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ዓለሙ ባደረጉት ንግግር፤ ለባንኩ ደንበኞችና ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አቶ አስፋው አክለውም ዳሽን ባንክ ከደንበኞች እሴትና የፋይናንስ ፍላጎት ጋር የሚጣጣሙ፣ የሸሪዓ መርሆዎችን ያከበሩ የባንክ አገልግሎቶችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ማህበራዊ ኃላፊነትና ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት
ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት (ሸሪካ) ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ባለው ቁርጠኝነት መሰረት ባለፈው ዓመት ካከናወናቸው ተግባራት መካከል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፦
ከደንበኞች በአደራ መልክ የሰበሰበውን ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ለ31 አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ማከፋፈሉ፤
በሶማሌ ክልል ለሚገኙ ስራ ፈጣሪዎች ከወለድ ነፃ በሆነ መንገድ የ100 ሚሊዮን ብር ተዘዋዋሪ ብድር ማቅረቡ።
ዳሽን ባንክ በአሁኑ ወቅት ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የኢንተረስት ፍሪ (ከወለድ ነፃ) አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች እንዳሉት የገለጸ ሲሆን፣ ይህም ባንኩ ያለውን ሁሉን አቀፍነትና የጋራ ተጠቃሚነት ባህል እንደሚያሳይ ተጠቁሟል።
ባንኩ በዘርፉ ባሳየው ጥንካሬ በ2023 በዱባይ በተካሄደው 9ኛው የኢስላሚክ ሪቴል ባንክ ሽልማት ላይ "በኢትዮጵያ ጠንካራው የኢስላሚክ የችርቻሮ ባንክ መስኮት" (The Strongest Islamic Retail Banking Window in Ethiopia) የሚል እውቅና ማግኘቱም ይታወሳል።
በተጨማሪም ዳሽን ባንክ ዓለም አቀፍ የእስልምና ፋይናንስ ተቋማትን የሂሳብ አያያዝ፣ የኦዲትና የሸሪዓ መስፈርቶችን የሚያወጣው AAOIFI (The Accounting and Auditing Organization for Islamic Financial Institutions) አባል የሆነ ብቸኛው የኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋም ነው።
#dashenbank #iftarprogram #islamicbanking #shariacompliant #ethiopianbanking #ramadankareem #financialinclusion
#ethiopia | ዳሽን ባንክ የረመዳን ወርን ምክንያት በማድረግ ለደንበኞቹ ያዘጋጀውን ልዩ የኢፍጣር መርሃ ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል አካሄደ።
መርሃ ግብሩ ባንኩ ያለውን ማህበራዊ ተሳትፎ ለማሳደግና ከደንበኞቹ ጋር ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በዝግጅቱ ላይ የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ዓለሙ ባደረጉት ንግግር፤ ለባንኩ ደንበኞችና ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አቶ አስፋው አክለውም ዳሽን ባንክ ከደንበኞች እሴትና የፋይናንስ ፍላጎት ጋር የሚጣጣሙ፣ የሸሪዓ መርሆዎችን ያከበሩ የባንክ አገልግሎቶችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ማህበራዊ ኃላፊነትና ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት
ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት (ሸሪካ) ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ባለው ቁርጠኝነት መሰረት ባለፈው ዓመት ካከናወናቸው ተግባራት መካከል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፦
ከደንበኞች በአደራ መልክ የሰበሰበውን ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ለ31 አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ማከፋፈሉ፤
በሶማሌ ክልል ለሚገኙ ስራ ፈጣሪዎች ከወለድ ነፃ በሆነ መንገድ የ100 ሚሊዮን ብር ተዘዋዋሪ ብድር ማቅረቡ።
ዳሽን ባንክ በአሁኑ ወቅት ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የኢንተረስት ፍሪ (ከወለድ ነፃ) አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች እንዳሉት የገለጸ ሲሆን፣ ይህም ባንኩ ያለውን ሁሉን አቀፍነትና የጋራ ተጠቃሚነት ባህል እንደሚያሳይ ተጠቁሟል።
ባንኩ በዘርፉ ባሳየው ጥንካሬ በ2023 በዱባይ በተካሄደው 9ኛው የኢስላሚክ ሪቴል ባንክ ሽልማት ላይ "በኢትዮጵያ ጠንካራው የኢስላሚክ የችርቻሮ ባንክ መስኮት" (The Strongest Islamic Retail Banking Window in Ethiopia) የሚል እውቅና ማግኘቱም ይታወሳል።
በተጨማሪም ዳሽን ባንክ ዓለም አቀፍ የእስልምና ፋይናንስ ተቋማትን የሂሳብ አያያዝ፣ የኦዲትና የሸሪዓ መስፈርቶችን የሚያወጣው AAOIFI (The Accounting and Auditing Organization for Islamic Financial Institutions) አባል የሆነ ብቸኛው የኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋም ነው።
#dashenbank #iftarprogram #islamicbanking #shariacompliant #ethiopianbanking #ramadankareem #financialinclusion
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ዳሸን ባንክ በሸራተን አዲስ የኢፍጣር መርሃ ግብር አካሄደ
ዳሸን ባንክ የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ ለደንበኞቹ፣ ለሀይማኖት አባቶችና ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች በሸራተን አዲስ ሆቴል ደማቅ የኢፍጣር መርሃ ግብር ዛሬ አከናውኗል።
ይህ መርሃ ግብር ባንኩ ካሉት ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የ"ሸሪክ" (ከወለድ ነፃ) አገልግሎት ተጠቃሚዎች ጋር ያለውን ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከርና የአብሮነት እሴትን ለማጎልበት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
በዝግጅቱ ላይ የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች እንደገለጹት፣ ዳሸን ባንክ የፋይናንስ ተቋም ብቻ ሳይሆን የማህበረሰቡ እሴትና እምነት ጠባቂ በመሆን አገልገሎቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ ላይ ይገኛል።
የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው አለሙ በዝግጅቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ዳሸን ባንክ የደንበኞቹን የፋይናንስ ፍላጎት ከሸሪዓ መርሆዎች ጋር በማጣጣም ረገድ ትልቅ ስኬት ማስመዝገቡን ገልጸዋል።
ባንኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ባለው ጽኑ አቋም፣ ባለፈው በጀት ዓመት ብቻ ከደንበኞቹ በአደራ መልክ የሰበሰበውን ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ለ131 አገር በቀል የግብረ-ሰናይ ድርጅቶች መለገሱ የዚሁ ቁርጠኝነት አካል መሆኑን አብራርተዋል።
ይህ ልገሳ በተለይ ረመዳንን የመሰሉ የለጋስነት ወቅቶች ላይ ባንኩ ለማህበረሰቡ ደህንነት የሚሰጠውን ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ገልፀው ይህም በኢትዮጵያ የባንክ ታሪክ ውስጥ ተዘዋዋሪ ብድርንና የሰብአዊ ድጋፍን በማጣመር ረገድ አዲስ ምዕራፍ ከፋች ነው ብለዋል።
በተለይ በሱማሌ ክልል ለሚገኙ ሴት ስራ ፈጣሪዎች የቀረበው የ100 ሚሊዮን ብር ከወለድ ነፃ ተዘዋዋሪ ብድር፣ ዳሸን ባንክ በኢኮኖሚ ዝቅተኛ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማብቃት ያለውን ራዕይ የሚያንጸባርቅ እንደሆነ በመርሃ ግብሩ ላይ ተጠቅሷል።
ይህ ተግባር ባንኩ ከትርፍ ባለፈ ለሀገር ግንባታና ለሴቶች ተጠቃሚነት የሚሰጠውን ስፍራ የሚያሳይ ሲሆን፣ የሸሪዓን መርህ ተከትሎ የሚሰጥ የፋይናንስ ድጋፍ እንዴት ማህበረሰባዊ ለውጥ እንደሚያመጣ ማሳያ ነው ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል።
ይህ የብድር አገልግሎት በክልሉ የሚገኙ ሴቶች የንግድ ስራዎቻቸውን እንዲያስፋፉና ራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም በዝግጅቱ ላይ ተገልጿል።
ዳሸን ባንክ እ.ኤ.አ በ2023 በባህሬን ማናማ በተካሄደው 9ኛው የኢስላሚክ ሪቴል ባንክ ሽልማት ላይ "The Strongest Islamic Retail Banking Window in Ethiopia" በሚል እውቅና ማግኘቱ ይታወሳል።
ዳሸን ባንክ የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ ለደንበኞቹ፣ ለሀይማኖት አባቶችና ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች በሸራተን አዲስ ሆቴል ደማቅ የኢፍጣር መርሃ ግብር ዛሬ አከናውኗል።
ይህ መርሃ ግብር ባንኩ ካሉት ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የ"ሸሪክ" (ከወለድ ነፃ) አገልግሎት ተጠቃሚዎች ጋር ያለውን ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከርና የአብሮነት እሴትን ለማጎልበት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
በዝግጅቱ ላይ የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች እንደገለጹት፣ ዳሸን ባንክ የፋይናንስ ተቋም ብቻ ሳይሆን የማህበረሰቡ እሴትና እምነት ጠባቂ በመሆን አገልገሎቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ ላይ ይገኛል።
የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው አለሙ በዝግጅቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ዳሸን ባንክ የደንበኞቹን የፋይናንስ ፍላጎት ከሸሪዓ መርሆዎች ጋር በማጣጣም ረገድ ትልቅ ስኬት ማስመዝገቡን ገልጸዋል።
ባንኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ባለው ጽኑ አቋም፣ ባለፈው በጀት ዓመት ብቻ ከደንበኞቹ በአደራ መልክ የሰበሰበውን ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ለ131 አገር በቀል የግብረ-ሰናይ ድርጅቶች መለገሱ የዚሁ ቁርጠኝነት አካል መሆኑን አብራርተዋል።
ይህ ልገሳ በተለይ ረመዳንን የመሰሉ የለጋስነት ወቅቶች ላይ ባንኩ ለማህበረሰቡ ደህንነት የሚሰጠውን ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ገልፀው ይህም በኢትዮጵያ የባንክ ታሪክ ውስጥ ተዘዋዋሪ ብድርንና የሰብአዊ ድጋፍን በማጣመር ረገድ አዲስ ምዕራፍ ከፋች ነው ብለዋል።
በተለይ በሱማሌ ክልል ለሚገኙ ሴት ስራ ፈጣሪዎች የቀረበው የ100 ሚሊዮን ብር ከወለድ ነፃ ተዘዋዋሪ ብድር፣ ዳሸን ባንክ በኢኮኖሚ ዝቅተኛ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማብቃት ያለውን ራዕይ የሚያንጸባርቅ እንደሆነ በመርሃ ግብሩ ላይ ተጠቅሷል።
ይህ ተግባር ባንኩ ከትርፍ ባለፈ ለሀገር ግንባታና ለሴቶች ተጠቃሚነት የሚሰጠውን ስፍራ የሚያሳይ ሲሆን፣ የሸሪዓን መርህ ተከትሎ የሚሰጥ የፋይናንስ ድጋፍ እንዴት ማህበረሰባዊ ለውጥ እንደሚያመጣ ማሳያ ነው ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል።
ይህ የብድር አገልግሎት በክልሉ የሚገኙ ሴቶች የንግድ ስራዎቻቸውን እንዲያስፋፉና ራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም በዝግጅቱ ላይ ተገልጿል።
ዳሸን ባንክ እ.ኤ.አ በ2023 በባህሬን ማናማ በተካሄደው 9ኛው የኢስላሚክ ሪቴል ባንክ ሽልማት ላይ "The Strongest Islamic Retail Banking Window in Ethiopia" በሚል እውቅና ማግኘቱ ይታወሳል።
3 months ago
የካፒታል ገበያ እና መዋለ ንዋይ ሰነድ
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
የኢትዮጲያ ካፒታል አዋጅ ቁጥር 1248/13
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | የካፒታል ገበያ በኢትዮጵያ በህግ ማእቀፍ ተደግፎ የመዋለ ሰነዶችን ሽያጭ በማሳደግ ረገድ ሀገራችን የካፒታል አዋጅ ቁጥር 1248/13 አውጥቶ በስራ ላይ መዋሉ የእነዚህ ሰነዶችን ሽያጭ ገበያ በመፍጠር ኢንቨስተሮችን ከመሳብ ፣ የንግድ ማህበራትን፣ባንኮችን ከማሳደግ፣ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት ከፍ ከማድረግ አንጻር ዘርፈ ብዙ የተሳለጠ የንግድ ትስስር የሚፈጥር ሲሆን በዚህ ጽሁፍ ከህግ ጋር ተያይዞ ያለውን ይዘት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ለመስጠት ይህን ጽሁፍ ወደ እናንተ አቅርበናል።
1. የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪካዊ ዳራ
ኢትዮጵያ ብዙ የህግ ታሪክ ስለ ካፒታል ገበያ እንደሌሎች ሀገራት እንደሌላት የተለያዩ ስለካፒታል ገበያ የተመለከቱ የኢትዮጵያን ታሪክ መመልከት የሚቻል ነው። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪካዊ ዳራን ስናጤን በአጼ ዘመነ መንግስት እ.ኤ.አ በ1867 ዓ.ም በአጼ ሚኒሊክ ዘመነ መንግስት የኢትዮ ጅቡቲን ሀዲድ ለመዘርጋት የ40 ሚሊዮን ፍራንክ አክስዮን በፈረንሳይ ሀገር መሸጣቸው ታሪክ ያወሳል።በእሳቸው ዘመን የተቋቋመው የመጀመርያው ባንክ፣ አቢሲኒያ ባንክ ሲመሠረት አክሲዮኖቹ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ኒውዮርክ፣ ፓሪስ፣ ለንደንና ቪየና እንደተሸጡ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡
እ.ኤ.አ. በ1956 የኢትዮጵያ የቄራዎች ድርጅት ለሕዝብ ሽያጭ የወጣ ሲሆን፣ እሱን ተከትሎ እ.ኤ.አ. ከ1957 እስከ 1963 ባለው ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ ጠርሙስ ፋብሪካ (Ethiopian Bottling Company)፣ ኢንዶ-ኢትዮጵያን ጨርቃ ጨርቅ፣ ኤችቪኤ ኢትዮጵያ፣ ሳባ ጠጅ፣ ተንዳሆ ተክልና የአዲስ አበባ ባንክ ለሕዝብ ሽያጭ መውጣታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተጨማሪ እ.ኤ.አ. በ1959 ወንጂ ስኳር ፋብሪካ ለሕዝብ ሽያጭ የቀረበ ድርጅት መሆኑንና በወቅቱ በሦስት ወራት ውስጥ ከአክሲዮን ሽያጭ 2.5 ሚሊዮን ዶላር መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን፣ ኤችቪኤ የተባለው የሆላንድ ኩባንያ አብዛኛውን አክሲዮን መግዛቱ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ሕዝቡም ቀላል ሊባል በማይችል መልኩ በግብይት መሳተፉንና ድርሻ መግዛቱን ጄዲቮን ፒስኬ የተባለ ጸሐፊ፣ «አክሲዮንና የአክሲዮን ግብይት በአዲስ አበባ» በሚለው መጽሐፉ ከትቦት ይገኛል።
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በ1960 ዓ.ም. በኢትዮጵያ መንግሥት ባንክ (State Bank of Ethiopia) ውስጥ የአክሲዮን ግብይት መምርያ መቋቋሙ የአክሲዮን ግብይቱን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡ ይህንን መምርያ ማደራጀት የአክሲዮን ገበያን ለማስፋፋት በመንግሥት የተወሰደ የመጀመርያው ተቋማዊ አደረጃጀት ዕርምጃ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በወቅቱ የተለያዩ ኢንቨስተሮችን በግብይት በማሳተፍና ዋጋ እንዲሰጡ በማድረግ፣ እንዲሁም በተለያዩ መንገዶች ዋጋ እንዲወሰን ይደረግ ነበር፡፡
እ.ኤ.አ. በ1965 የአክሲዮን ግብይት እያደገ በመሄዱ፣ የሕዝብን እምነት በማግኘቱ፣ ኢኮኖሚውም ዕድገት በማሳየቱ፣ አዳዲስ ኀይለስላሴ ዘመነመንግስት የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ ኖሮት የተለያዩ አስፈጻሚ ተቋሟት የማቋቋም የማደራጀት እና የመነቃቃት ስራዎች ተሞክረዋል። ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለመገንባት በተደረገው ህዝባዊ ንቅናቄም ብዙ የቦንድ ሽያጭ ለዜጎች፣ ሀገር በቀል ድርጅቶች ፣ ለትውልደ ኢትዮጲያን ፣ ዲያስፖራ ለሌሎችም ተሳታፊ አካላት ተሽጦ በብዙ ቢሊዮን ብር ተሰብስቦ ታላቁን ህዳሴ ግድብ ተገንብቷል።
ይህ ህጉ ከመውጣቱ በፊት ባልተማከለ አሰራር የተፈጸመ ቢሆንም የካፒታል ገበያ ስረአት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል። ከዚህም ባለፈ የገበያ መር ስረአት የሚደግፍ ሲሆን ለነጋዴዎች፣ለባለሀብቶች፣ ለሀገር እድገት መንሰራራት፣ለአለምአቀፍ የገበያ ትስስር፣ለዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ፣ለአጠቃላይ የገበያ እድገት እንቅስቃሴ ከፍተኛ በርን የከፈተ ሲሆን እኝህን መሪዎችንና እና ተባባሪዎቻቸውን አለማመስገን ንፉግነት መሆኑ ያነበበኩት እና ለመመረቂያ ጽሁፌ ያጠናውት " The Challenges and Opportunities of the capital market proclamation implementation " ማለትም በአማረኛ ለማስገንዘብ ያህል "የካፒታል ገበያ አዋጅ አፈጻጸም ተግዳሮት እና መጻኢ እድል" በሚል በአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ የታተመው ጹሁፍ ምስክር ይሆኑኛል።
ይሁን እንጂ የደርግ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ የሶሻሊስት ስረአት መንግስትን ባህርይ ያለው መሆኑን ተከትሎ የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ እንዳይኖረው እንዲሁም የገበያ መር ስረአትን የማይከተል በመሆኑ የካፒታል ገበያ ቦታ እንዳይኖረው አድርጎት አሁን ግን ጊዜው ደርስ የህግ ማእቀፍ እንዲኖረው ተደርጓል።
2. አሁን ላይ የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ ምን ይመስላል?
አሁን ባለንበት የኢፊድሪ ህገመንግስት ዲሞክርያሲያዊ እና ገበያ መር ስረአትን ፈቃጅ ሲሆን ይህን ተከትሎም ለሀገር እድገት የሚበጁ የንግድ ስረአታችንን የሚያዘምኑ ከአለም የገበያ ስረአት ጋር እኩል የሚሄዱ ህጎች እየወጡ የሚገኙ ሲሆን አንዱም የኢትዮጲያ ካፒታል ገበያ አዋጅ ቀጥር 1248/13 ነው።በዚህ አዋጅ አንቀጽ 3 ላይ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የተቋቋመ ሲሆን ይህን ተከትሎም የተለያዩ ደንብ እና መመሪያዎች በመውጣት ላይም ይገኛሉ።
ይህ ለሀገራችን እድገት እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ሌሎች ህጎችም ሊደግፉ እና ተጣጥመው ሊተገበሩ የሚገባ በመሆኑ የብሔራዊ ባንክ አዋጅ፣የንግድ ባንክ አዋጅ፣ የኢፊድሪ ንግድ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 ሌሎች የፋይናንስ እና የንግድ ተቋማት ህጎች በመውጣት በመሻሻል ላይ ይገኛሉ። በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 ስር የሚታቀፉ ወይም የታቀፉ ዘርፈ ብዙ ተቋማት የሚገኙ ሲሆኑ ዋናው ጉዳይ ግን የሙአለ ንዋይ ሰነድ ገበያን ተፈጻሚ የሚያደርጉ ናቸው።
የሙአለ ሰነድ ገበያ በዋናነት ለመጥቀስ ያህል በአዋጁ አንቀጽ 31 መሠረት የሚመሰረት ሲሆን ይህን በተመለከተ የኢፊድሪ መንግስትም ስራ መጀመሩን አብስሯል። ይህ ዋናው የአዋጁ መቋቋም መሠረታዊ አላማ ነው። ሌላው የመወእለ ሰነዶች አስቀማጭ ክፍያ አጣሪ ፈጻሚ ኩባንያ በአዋጁ የህግ እውቅና የተሰጠው ሲሆን ይህ ግብይት የሚፈጸምባቸውን ሰነዶች ክፍያ አፈጻጸም ከእዳና ከተለያዩ ክፍያዎች ነጻ ስለመሆኑ በማጣራት ሰነዶችን በመለየት የሚያስቀምጥ ነው። በዚህ ረገድ ብሔራዊ ባንክም ስልጣን የተሰጠበት አግባብ በአዋጁ ላይ ተዘርዝሮ የተቀመጠ ነው። የመንግስት መዋአለ ሰነዶችን በተመለከተ ሰነዶችን የማስቀመጥ የማስተዳደር ስልጣን ተሰጥቶታል።
3. .ሙአለ ንዋይ ሰነዶች ምንድን ናቸው?
የሰነደ ሙዓለ ንዋይ (Securities) ማለት በገንዘብ ሊተመን የሚችል ባለቤትነትን የሚገልጽ ሰነድ ማለት ሲሆን ሊሸጥ፣ ሊለወጥ ወይም በዋስትና ሊሰጥ የሚችል መብት የሚያቋቁም ሰነድ ነው፡፡ በእኛ አገር የሚታወቁት የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ዓይነቶች አክሲዮን፣ ቦንድና የግምጃ ቤት ሰነድ ናቸው፡፡ ባደጉት አገሮች የተለያዩ ዓይነት የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ይገበያያሉ፡፡ እነዚህም አክሲዮኖችን (Shares)፣ የዕዳ ሰነዶችን (Debt Instruments)፣ ብድሮችን (Loans)፣ ቦንዶችንና ሌሎች ወደ ኩባንያ ካፒታልነት ሊቀየሩ የሚችሉ ስምምነቶችን ያካትታል፡፡ በተጨማሪም ሁሉም በመንግሥት ወይም በመንግሥት የልማት ድርጅቶች የወጡና
ለግብይት የሚውሉ የሕዝብ የብድር ሰነደ ሙዓለ ንዋዮችን፣ ለወደፊት የሚፈጸሙ የውል ዓይነቶችን (Futures)፣ ያለ ግዴታ የመግዛት ወይም የመሸጥ መብት ለገዥው የሚሰጡ ሰነዶችን (Options)፣ ተዛማጅን (Derivatives) እና በጋራ የኢንቨስትመንት ፈንድ ውስጥ ያለ የድርሻ ክፍልፋይ (Units in a Collective Investment Scheme) ይይዛል፡፡
እነዚህንና ሌሎች የካፒታል ገበያ ሰነዶችን በአገራችን በተማከለ ገበያ ለማገበያየት እንዲያመች እንደ ሌሎቹ አገሮች የራሱ የሆነ ሒደትን መዘርጋት፣ መደገፍ፣ መቆጣጠር ብሎም መከታተል የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የካፒታል ገበያ አዋጅ ወጥቶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 አንቀጽ 2(62) መሠረት ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ማለት ከላይ በሌሎች አገሮች ግብይት ይደረግባቸዋል የተባሉትን ሰነዶች ጨምሮ፣ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ናቸው ብሎ የሚወስናቸውን ማናቸውም በግብይት የድርሻ ባለቤትነትን የሚያረጋግጡና በባለሥልጣኑ ፈቃድ መሠረት የሚተላለፉ ሰነዶችን ይጨምራል፡፡
4. የሙአለ ሰነዶች ገበያ መመዝገብ እና መሠረዝ
ሌላው ደግሞ በዚህ መግቢያ መነሳት ያለበት ነጥብ በሙአለ ሰነዶች ገበያ የሚመዘገቡ ሰነዶች ሲሆኑ በዚህ የሚሳተፉ ተቋማት አስፈላጊውን መሥፈርት አሟልተው በጥንቃቄ ተመርምረው የሚመዘገቡ ናቸው። እነዚህም የተመዘገቡ ኩባንያዎች listing companies ሲባሉ ነገር ግን በተለያየ ምክንያት በግብይት ሂደት ውስጥ መረጃ በማሳሳት ገብተው ወይም ወንጀል ፈጽመው ወይም ግዴታቸውን ሳይወጡ ቀርተው እንደሆነ ከገበያው የሚሰረዙበት ስረአት በህጉ የተቀመጡ ሲሆን ከገበያው የተሰረዙ ኩባንያዎች/delisting campany/በመባል ይታወቃሉ። እነዚህን የካፒታል ገበያ አላማ ከዳር ለማድረስ መንግስት በራሱ ብቻ የሚከውነው ሳይሆን ለተለያዩ አገልግሎት ብቁ ለሆኑ የግል አግልግሎት ሰጪዎች ብቁ ሆነው ከተገኙ ፍቃድ በሚሰጥበት አግባብ የሚጠበቅባቸውን መስፈርት የሚያሟሉ ከሆነ ፍቃድ ተሰጥቶአቸው የሚሰሩበት አግባብ እንዳለ በአዋጁ አንቀጹ 55 ላይ በዝርዝር ተቀምጧል።
5. የኢትዮጲያ ካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት
ሌላው ትኩረት የምናደርግበት በአዋጁ አንቀጽ 64 መሠረት የተቋቋመ ሲሆን ይህም የካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት ነው። ይህ ፍርድ ቤት ሙእለ ሰነዶች ግብይት ላይ አስመልክቶ በዚህ አዋጅ ሽፋን ስር በሚወድቁ አጠቃላይ ተግባራት ላይ በባለስልጣኑ ውሳኔዎች ላይ በሚሰጡ በሚተላለፉ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ ቅሬታ ያለው ወገን ክስ አቅርቦ የሚታይበት ሲሆን በዚህ ፍርድ ቤት የሚሰጡ ውሳኔች ላይ ቅር የተሰኘ ወገን በመሠረታዊ የህግ ስህተት ላይ ብቻ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ የሚጠየቅበት ይሆናል። ይህ ማለት የፍሬ ነገር ክርክር ጉዳዮች በተመለከተ የክርክር ሂደት እዚሁ የካፒታል አስተዳደር ፍርድ ቤት የሚያልቅ በመሆኑ ጥንቃቄ ሊደረግ የሚገባው ነው።
በዚህ ካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት የሚሾሙ ዳኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሆን በዚህ ዘርፍ የተለየ በእውቀት በልምድ በስልጠና በሀገር ወጭም ጭምር የዳበሩ ልዩ እውቀትና ልምድ ያላቸው ሊሆኑ ይገባል። ይህ ካልሆነ ከፈጣን እና ፍትሀዊ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር በቶሎ ውሳኔ የማይሰጥበት ከሆነ በዚህ ዘርፍ ለሚሳተፉ ኢንቨስተሮች፣ተቋማት ለሙአለ ሰነድ ግብይት ስራ ዘርፍ እና ኢትዮጲያ ሀገራችን ለጀመረችው የዚህ የካፒታል ገበያ እድገት ጎታች ሊሆን ስለሚችል ይህ ኢንቨስተሮችን የሚያርቅ ተስፋ የሚያስቆርጥ ይልቁንም የማይስተማምን ተገማችነትን የሚያሳጣ መሆን የለበትም ። ከዚህ አንጻር የፍርድ ቤቱ ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች፣በወንጀል ጉዳይ ደግሞ መርማሪዎች፣አቃቢ ህጎች በተለየ እውቀት ፣ ልምድ፣ ስልጠና የዳበሩ ሊሆኑ ያስፈልጋል። ይህም ማለት ዳኞችን በዋናነት ጨምሮ ስለ ሙአለ ንዋይ ሰነዶ ምንነት፣ባህርይ፣ግብይት፣ ህግና መመሪያዎቻቸውን በዚህ ዘርፍ የሚሳተፋትን ኩባንያ፣ኢንቨስተሮችን፣ፍቃድ የተሰጣቸውን አገልግሎት ተቋማትን በተሳታፊ ኩባንያ ውስጥ ያሉ ሰራተኞች መብትና ግዴታዎችን የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ስልጣኑንና ተግባሩን ኀላፊነቱን ተጠያቂነቱን በዚህ ዘርፍ ስር የሚገኙ ሰራተኞችን መብት ግዴታ አሰራሮቻቸውን ማወቁ ለዚህ ለሚመለከተው ፍርድ ቤት ፍትህ አሰጣጥ እጅግ ጠቃሚ ነው።
6. ሲጠቃለል
ይህን አዋጅ ባቀፈው ህግጋት እና አላማ ልክ ተፈጻሚ ለማድረግ ያሉን መልካም አጋጣሚዎች እንደ ሀገር ምን ምን እንደሆኑ መታየቱ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። የዚህን አዋጅ ተፈጻሚነት ከዳር ከማድረስ አንጻር በሚደረገው ከፍተኛ ትንቅንቅ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮች ምን ምን ናቸው ለእነዚህስ መሠረታዊ የሚሆን መፍቴዎች ምንድን ናቸው በሚሉ በዝርዝር አስፈላጊ በሚባሉ ነጥቦች ላይ መሠረታዊ ትንተና ሊሰጥበት የሚገባ ሲሆን የሌሎች ሀገረች ልምድና ተሞክሮ ጭምር የመፍትሄ አካል ሆኖ መወሰዱ ወሳኝ ነገር ነው።
በአጠቃላይ የካፒታል ገበያ ህግ ለሀገራችን እጅግ ጠቃሚ ከመሆነ የተነሳ ከ19ኛ ክ/ዘመን ወዲህ ጀምሮ ባለተማከለ የገበያ አሰራር የሙአለ ሰነድ ሽያጮች ይከናወኑ እንደነበሩ እና በዚህ ለሀገራችን እድገት ወሰኝ የነበረ ሲሆን ይህንና አለምአቀፍ ልምዶች ህጎች ትስስሮች በመረዳት በተማከለ የካፒታል ገበያ ስረአት ውስጥ በመጓዝ ሀገርን እና ዜጎችን በኢኮኖሚ እድገት ከፍ ለማድረግ የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 ይህንንም ተከትሎ ሌሎች ሊያሰሩ የሚችሉ ደንቦችን መመሪያዎችን በማውጣት ላይ የሚገኝ ሲሆን ከዚህ በፊት የነበሩ የንግድ የባንክ፣የፋይናንስ ህጎች በመሻሻል ላይ ይገኛሉ።
መንግስትም ይህን የሚመጥን በህግ ማእቀፉ እንደተቀመጠው በቴክኖሎጂ የታገዙ ተቋማትን መገንባት የሚገባ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የሰው ሀይል ማብቃትም በተመለከተ ትኩረት ሊወሰድበት የሚገባው ነው። ማህበረሰቡ ኢንቨስተሩ ኩባንያውም በዚህ ልክ እንዲነቃቃ አስፈላጊውን ግንዛቤ ሊሰጠው ያስፈልጋል። የካፒታል ገበያ ባለስልጣኑም በአዋጁ የተሰጠውን ትልቅ ኀላፊነት ለመወጣት አስፈላጊውን ዝግጅት ሊወስድ የሚገባ ሲሆን በግብይት ሂደት ተሳታፊ የሆኑ ቅን ባለሀብቶችን መብት ጥበቃ ሊያደርግ የሚያስፈልግ ሲሆን አጭበርባሪዎችን ለአሰራር እንቅፋት የሚፈጥሩትን በመለየት እንዲታረሙ ከማድረግ አንጻር ተገቢውን ጥረት ሊያደርግ የሚገባው ነው። ይህ ሲሆን የካፒታል ገበያ አዋጅ 1248/13 ተፈጻሚ በማድረግ ለሀገራችን ትልቅ የኢኮኖሚ ፋይዳ ያለው ስለመሆኑ አያጠያይቅም።
ማጣቀሻዎች/References/
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1/1987
2. የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13
3. Fantahun Delelew, Challenge and opportunities of the implementation of capital proclamation 1248/13,Addisababa University
(የካፒታል አዋጁ አፈጻጸም ተግዳሮት እና መጻኢ እድል)
4. የብሔራዊ ባንክ አዋጅ ቁጥር 1359/17
5. ስለ ባንክ ስራዎች አዋጅ ቁጥር 1360/17
https://www.facebook.com
https://t.me/Fantahunlawye...
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
የኢትዮጲያ ካፒታል አዋጅ ቁጥር 1248/13
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | የካፒታል ገበያ በኢትዮጵያ በህግ ማእቀፍ ተደግፎ የመዋለ ሰነዶችን ሽያጭ በማሳደግ ረገድ ሀገራችን የካፒታል አዋጅ ቁጥር 1248/13 አውጥቶ በስራ ላይ መዋሉ የእነዚህ ሰነዶችን ሽያጭ ገበያ በመፍጠር ኢንቨስተሮችን ከመሳብ ፣ የንግድ ማህበራትን፣ባንኮችን ከማሳደግ፣ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት ከፍ ከማድረግ አንጻር ዘርፈ ብዙ የተሳለጠ የንግድ ትስስር የሚፈጥር ሲሆን በዚህ ጽሁፍ ከህግ ጋር ተያይዞ ያለውን ይዘት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ለመስጠት ይህን ጽሁፍ ወደ እናንተ አቅርበናል።
1. የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪካዊ ዳራ
ኢትዮጵያ ብዙ የህግ ታሪክ ስለ ካፒታል ገበያ እንደሌሎች ሀገራት እንደሌላት የተለያዩ ስለካፒታል ገበያ የተመለከቱ የኢትዮጵያን ታሪክ መመልከት የሚቻል ነው። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪካዊ ዳራን ስናጤን በአጼ ዘመነ መንግስት እ.ኤ.አ በ1867 ዓ.ም በአጼ ሚኒሊክ ዘመነ መንግስት የኢትዮ ጅቡቲን ሀዲድ ለመዘርጋት የ40 ሚሊዮን ፍራንክ አክስዮን በፈረንሳይ ሀገር መሸጣቸው ታሪክ ያወሳል።በእሳቸው ዘመን የተቋቋመው የመጀመርያው ባንክ፣ አቢሲኒያ ባንክ ሲመሠረት አክሲዮኖቹ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ኒውዮርክ፣ ፓሪስ፣ ለንደንና ቪየና እንደተሸጡ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡
እ.ኤ.አ. በ1956 የኢትዮጵያ የቄራዎች ድርጅት ለሕዝብ ሽያጭ የወጣ ሲሆን፣ እሱን ተከትሎ እ.ኤ.አ. ከ1957 እስከ 1963 ባለው ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ ጠርሙስ ፋብሪካ (Ethiopian Bottling Company)፣ ኢንዶ-ኢትዮጵያን ጨርቃ ጨርቅ፣ ኤችቪኤ ኢትዮጵያ፣ ሳባ ጠጅ፣ ተንዳሆ ተክልና የአዲስ አበባ ባንክ ለሕዝብ ሽያጭ መውጣታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተጨማሪ እ.ኤ.አ. በ1959 ወንጂ ስኳር ፋብሪካ ለሕዝብ ሽያጭ የቀረበ ድርጅት መሆኑንና በወቅቱ በሦስት ወራት ውስጥ ከአክሲዮን ሽያጭ 2.5 ሚሊዮን ዶላር መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን፣ ኤችቪኤ የተባለው የሆላንድ ኩባንያ አብዛኛውን አክሲዮን መግዛቱ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ሕዝቡም ቀላል ሊባል በማይችል መልኩ በግብይት መሳተፉንና ድርሻ መግዛቱን ጄዲቮን ፒስኬ የተባለ ጸሐፊ፣ «አክሲዮንና የአክሲዮን ግብይት በአዲስ አበባ» በሚለው መጽሐፉ ከትቦት ይገኛል።
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በ1960 ዓ.ም. በኢትዮጵያ መንግሥት ባንክ (State Bank of Ethiopia) ውስጥ የአክሲዮን ግብይት መምርያ መቋቋሙ የአክሲዮን ግብይቱን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡ ይህንን መምርያ ማደራጀት የአክሲዮን ገበያን ለማስፋፋት በመንግሥት የተወሰደ የመጀመርያው ተቋማዊ አደረጃጀት ዕርምጃ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በወቅቱ የተለያዩ ኢንቨስተሮችን በግብይት በማሳተፍና ዋጋ እንዲሰጡ በማድረግ፣ እንዲሁም በተለያዩ መንገዶች ዋጋ እንዲወሰን ይደረግ ነበር፡፡
እ.ኤ.አ. በ1965 የአክሲዮን ግብይት እያደገ በመሄዱ፣ የሕዝብን እምነት በማግኘቱ፣ ኢኮኖሚውም ዕድገት በማሳየቱ፣ አዳዲስ ኀይለስላሴ ዘመነመንግስት የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ ኖሮት የተለያዩ አስፈጻሚ ተቋሟት የማቋቋም የማደራጀት እና የመነቃቃት ስራዎች ተሞክረዋል። ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለመገንባት በተደረገው ህዝባዊ ንቅናቄም ብዙ የቦንድ ሽያጭ ለዜጎች፣ ሀገር በቀል ድርጅቶች ፣ ለትውልደ ኢትዮጲያን ፣ ዲያስፖራ ለሌሎችም ተሳታፊ አካላት ተሽጦ በብዙ ቢሊዮን ብር ተሰብስቦ ታላቁን ህዳሴ ግድብ ተገንብቷል።
ይህ ህጉ ከመውጣቱ በፊት ባልተማከለ አሰራር የተፈጸመ ቢሆንም የካፒታል ገበያ ስረአት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል። ከዚህም ባለፈ የገበያ መር ስረአት የሚደግፍ ሲሆን ለነጋዴዎች፣ለባለሀብቶች፣ ለሀገር እድገት መንሰራራት፣ለአለምአቀፍ የገበያ ትስስር፣ለዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ፣ለአጠቃላይ የገበያ እድገት እንቅስቃሴ ከፍተኛ በርን የከፈተ ሲሆን እኝህን መሪዎችንና እና ተባባሪዎቻቸውን አለማመስገን ንፉግነት መሆኑ ያነበበኩት እና ለመመረቂያ ጽሁፌ ያጠናውት " The Challenges and Opportunities of the capital market proclamation implementation " ማለትም በአማረኛ ለማስገንዘብ ያህል "የካፒታል ገበያ አዋጅ አፈጻጸም ተግዳሮት እና መጻኢ እድል" በሚል በአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ የታተመው ጹሁፍ ምስክር ይሆኑኛል።
ይሁን እንጂ የደርግ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ የሶሻሊስት ስረአት መንግስትን ባህርይ ያለው መሆኑን ተከትሎ የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ እንዳይኖረው እንዲሁም የገበያ መር ስረአትን የማይከተል በመሆኑ የካፒታል ገበያ ቦታ እንዳይኖረው አድርጎት አሁን ግን ጊዜው ደርስ የህግ ማእቀፍ እንዲኖረው ተደርጓል።
2. አሁን ላይ የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ ምን ይመስላል?
አሁን ባለንበት የኢፊድሪ ህገመንግስት ዲሞክርያሲያዊ እና ገበያ መር ስረአትን ፈቃጅ ሲሆን ይህን ተከትሎም ለሀገር እድገት የሚበጁ የንግድ ስረአታችንን የሚያዘምኑ ከአለም የገበያ ስረአት ጋር እኩል የሚሄዱ ህጎች እየወጡ የሚገኙ ሲሆን አንዱም የኢትዮጲያ ካፒታል ገበያ አዋጅ ቀጥር 1248/13 ነው።በዚህ አዋጅ አንቀጽ 3 ላይ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የተቋቋመ ሲሆን ይህን ተከትሎም የተለያዩ ደንብ እና መመሪያዎች በመውጣት ላይም ይገኛሉ።
ይህ ለሀገራችን እድገት እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ሌሎች ህጎችም ሊደግፉ እና ተጣጥመው ሊተገበሩ የሚገባ በመሆኑ የብሔራዊ ባንክ አዋጅ፣የንግድ ባንክ አዋጅ፣ የኢፊድሪ ንግድ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 ሌሎች የፋይናንስ እና የንግድ ተቋማት ህጎች በመውጣት በመሻሻል ላይ ይገኛሉ። በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 ስር የሚታቀፉ ወይም የታቀፉ ዘርፈ ብዙ ተቋማት የሚገኙ ሲሆኑ ዋናው ጉዳይ ግን የሙአለ ንዋይ ሰነድ ገበያን ተፈጻሚ የሚያደርጉ ናቸው።
የሙአለ ሰነድ ገበያ በዋናነት ለመጥቀስ ያህል በአዋጁ አንቀጽ 31 መሠረት የሚመሰረት ሲሆን ይህን በተመለከተ የኢፊድሪ መንግስትም ስራ መጀመሩን አብስሯል። ይህ ዋናው የአዋጁ መቋቋም መሠረታዊ አላማ ነው። ሌላው የመወእለ ሰነዶች አስቀማጭ ክፍያ አጣሪ ፈጻሚ ኩባንያ በአዋጁ የህግ እውቅና የተሰጠው ሲሆን ይህ ግብይት የሚፈጸምባቸውን ሰነዶች ክፍያ አፈጻጸም ከእዳና ከተለያዩ ክፍያዎች ነጻ ስለመሆኑ በማጣራት ሰነዶችን በመለየት የሚያስቀምጥ ነው። በዚህ ረገድ ብሔራዊ ባንክም ስልጣን የተሰጠበት አግባብ በአዋጁ ላይ ተዘርዝሮ የተቀመጠ ነው። የመንግስት መዋአለ ሰነዶችን በተመለከተ ሰነዶችን የማስቀመጥ የማስተዳደር ስልጣን ተሰጥቶታል።
3. .ሙአለ ንዋይ ሰነዶች ምንድን ናቸው?
የሰነደ ሙዓለ ንዋይ (Securities) ማለት በገንዘብ ሊተመን የሚችል ባለቤትነትን የሚገልጽ ሰነድ ማለት ሲሆን ሊሸጥ፣ ሊለወጥ ወይም በዋስትና ሊሰጥ የሚችል መብት የሚያቋቁም ሰነድ ነው፡፡ በእኛ አገር የሚታወቁት የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ዓይነቶች አክሲዮን፣ ቦንድና የግምጃ ቤት ሰነድ ናቸው፡፡ ባደጉት አገሮች የተለያዩ ዓይነት የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ይገበያያሉ፡፡ እነዚህም አክሲዮኖችን (Shares)፣ የዕዳ ሰነዶችን (Debt Instruments)፣ ብድሮችን (Loans)፣ ቦንዶችንና ሌሎች ወደ ኩባንያ ካፒታልነት ሊቀየሩ የሚችሉ ስምምነቶችን ያካትታል፡፡ በተጨማሪም ሁሉም በመንግሥት ወይም በመንግሥት የልማት ድርጅቶች የወጡና
ለግብይት የሚውሉ የሕዝብ የብድር ሰነደ ሙዓለ ንዋዮችን፣ ለወደፊት የሚፈጸሙ የውል ዓይነቶችን (Futures)፣ ያለ ግዴታ የመግዛት ወይም የመሸጥ መብት ለገዥው የሚሰጡ ሰነዶችን (Options)፣ ተዛማጅን (Derivatives) እና በጋራ የኢንቨስትመንት ፈንድ ውስጥ ያለ የድርሻ ክፍልፋይ (Units in a Collective Investment Scheme) ይይዛል፡፡
እነዚህንና ሌሎች የካፒታል ገበያ ሰነዶችን በአገራችን በተማከለ ገበያ ለማገበያየት እንዲያመች እንደ ሌሎቹ አገሮች የራሱ የሆነ ሒደትን መዘርጋት፣ መደገፍ፣ መቆጣጠር ብሎም መከታተል የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የካፒታል ገበያ አዋጅ ወጥቶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 አንቀጽ 2(62) መሠረት ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ማለት ከላይ በሌሎች አገሮች ግብይት ይደረግባቸዋል የተባሉትን ሰነዶች ጨምሮ፣ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ናቸው ብሎ የሚወስናቸውን ማናቸውም በግብይት የድርሻ ባለቤትነትን የሚያረጋግጡና በባለሥልጣኑ ፈቃድ መሠረት የሚተላለፉ ሰነዶችን ይጨምራል፡፡
4. የሙአለ ሰነዶች ገበያ መመዝገብ እና መሠረዝ
ሌላው ደግሞ በዚህ መግቢያ መነሳት ያለበት ነጥብ በሙአለ ሰነዶች ገበያ የሚመዘገቡ ሰነዶች ሲሆኑ በዚህ የሚሳተፉ ተቋማት አስፈላጊውን መሥፈርት አሟልተው በጥንቃቄ ተመርምረው የሚመዘገቡ ናቸው። እነዚህም የተመዘገቡ ኩባንያዎች listing companies ሲባሉ ነገር ግን በተለያየ ምክንያት በግብይት ሂደት ውስጥ መረጃ በማሳሳት ገብተው ወይም ወንጀል ፈጽመው ወይም ግዴታቸውን ሳይወጡ ቀርተው እንደሆነ ከገበያው የሚሰረዙበት ስረአት በህጉ የተቀመጡ ሲሆን ከገበያው የተሰረዙ ኩባንያዎች/delisting campany/በመባል ይታወቃሉ። እነዚህን የካፒታል ገበያ አላማ ከዳር ለማድረስ መንግስት በራሱ ብቻ የሚከውነው ሳይሆን ለተለያዩ አገልግሎት ብቁ ለሆኑ የግል አግልግሎት ሰጪዎች ብቁ ሆነው ከተገኙ ፍቃድ በሚሰጥበት አግባብ የሚጠበቅባቸውን መስፈርት የሚያሟሉ ከሆነ ፍቃድ ተሰጥቶአቸው የሚሰሩበት አግባብ እንዳለ በአዋጁ አንቀጹ 55 ላይ በዝርዝር ተቀምጧል።
5. የኢትዮጲያ ካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት
ሌላው ትኩረት የምናደርግበት በአዋጁ አንቀጽ 64 መሠረት የተቋቋመ ሲሆን ይህም የካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት ነው። ይህ ፍርድ ቤት ሙእለ ሰነዶች ግብይት ላይ አስመልክቶ በዚህ አዋጅ ሽፋን ስር በሚወድቁ አጠቃላይ ተግባራት ላይ በባለስልጣኑ ውሳኔዎች ላይ በሚሰጡ በሚተላለፉ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ ቅሬታ ያለው ወገን ክስ አቅርቦ የሚታይበት ሲሆን በዚህ ፍርድ ቤት የሚሰጡ ውሳኔች ላይ ቅር የተሰኘ ወገን በመሠረታዊ የህግ ስህተት ላይ ብቻ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ የሚጠየቅበት ይሆናል። ይህ ማለት የፍሬ ነገር ክርክር ጉዳዮች በተመለከተ የክርክር ሂደት እዚሁ የካፒታል አስተዳደር ፍርድ ቤት የሚያልቅ በመሆኑ ጥንቃቄ ሊደረግ የሚገባው ነው።
በዚህ ካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት የሚሾሙ ዳኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሆን በዚህ ዘርፍ የተለየ በእውቀት በልምድ በስልጠና በሀገር ወጭም ጭምር የዳበሩ ልዩ እውቀትና ልምድ ያላቸው ሊሆኑ ይገባል። ይህ ካልሆነ ከፈጣን እና ፍትሀዊ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር በቶሎ ውሳኔ የማይሰጥበት ከሆነ በዚህ ዘርፍ ለሚሳተፉ ኢንቨስተሮች፣ተቋማት ለሙአለ ሰነድ ግብይት ስራ ዘርፍ እና ኢትዮጲያ ሀገራችን ለጀመረችው የዚህ የካፒታል ገበያ እድገት ጎታች ሊሆን ስለሚችል ይህ ኢንቨስተሮችን የሚያርቅ ተስፋ የሚያስቆርጥ ይልቁንም የማይስተማምን ተገማችነትን የሚያሳጣ መሆን የለበትም ። ከዚህ አንጻር የፍርድ ቤቱ ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች፣በወንጀል ጉዳይ ደግሞ መርማሪዎች፣አቃቢ ህጎች በተለየ እውቀት ፣ ልምድ፣ ስልጠና የዳበሩ ሊሆኑ ያስፈልጋል። ይህም ማለት ዳኞችን በዋናነት ጨምሮ ስለ ሙአለ ንዋይ ሰነዶ ምንነት፣ባህርይ፣ግብይት፣ ህግና መመሪያዎቻቸውን በዚህ ዘርፍ የሚሳተፋትን ኩባንያ፣ኢንቨስተሮችን፣ፍቃድ የተሰጣቸውን አገልግሎት ተቋማትን በተሳታፊ ኩባንያ ውስጥ ያሉ ሰራተኞች መብትና ግዴታዎችን የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ስልጣኑንና ተግባሩን ኀላፊነቱን ተጠያቂነቱን በዚህ ዘርፍ ስር የሚገኙ ሰራተኞችን መብት ግዴታ አሰራሮቻቸውን ማወቁ ለዚህ ለሚመለከተው ፍርድ ቤት ፍትህ አሰጣጥ እጅግ ጠቃሚ ነው።
6. ሲጠቃለል
ይህን አዋጅ ባቀፈው ህግጋት እና አላማ ልክ ተፈጻሚ ለማድረግ ያሉን መልካም አጋጣሚዎች እንደ ሀገር ምን ምን እንደሆኑ መታየቱ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። የዚህን አዋጅ ተፈጻሚነት ከዳር ከማድረስ አንጻር በሚደረገው ከፍተኛ ትንቅንቅ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮች ምን ምን ናቸው ለእነዚህስ መሠረታዊ የሚሆን መፍቴዎች ምንድን ናቸው በሚሉ በዝርዝር አስፈላጊ በሚባሉ ነጥቦች ላይ መሠረታዊ ትንተና ሊሰጥበት የሚገባ ሲሆን የሌሎች ሀገረች ልምድና ተሞክሮ ጭምር የመፍትሄ አካል ሆኖ መወሰዱ ወሳኝ ነገር ነው።
በአጠቃላይ የካፒታል ገበያ ህግ ለሀገራችን እጅግ ጠቃሚ ከመሆነ የተነሳ ከ19ኛ ክ/ዘመን ወዲህ ጀምሮ ባለተማከለ የገበያ አሰራር የሙአለ ሰነድ ሽያጮች ይከናወኑ እንደነበሩ እና በዚህ ለሀገራችን እድገት ወሰኝ የነበረ ሲሆን ይህንና አለምአቀፍ ልምዶች ህጎች ትስስሮች በመረዳት በተማከለ የካፒታል ገበያ ስረአት ውስጥ በመጓዝ ሀገርን እና ዜጎችን በኢኮኖሚ እድገት ከፍ ለማድረግ የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 ይህንንም ተከትሎ ሌሎች ሊያሰሩ የሚችሉ ደንቦችን መመሪያዎችን በማውጣት ላይ የሚገኝ ሲሆን ከዚህ በፊት የነበሩ የንግድ የባንክ፣የፋይናንስ ህጎች በመሻሻል ላይ ይገኛሉ።
መንግስትም ይህን የሚመጥን በህግ ማእቀፉ እንደተቀመጠው በቴክኖሎጂ የታገዙ ተቋማትን መገንባት የሚገባ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የሰው ሀይል ማብቃትም በተመለከተ ትኩረት ሊወሰድበት የሚገባው ነው። ማህበረሰቡ ኢንቨስተሩ ኩባንያውም በዚህ ልክ እንዲነቃቃ አስፈላጊውን ግንዛቤ ሊሰጠው ያስፈልጋል። የካፒታል ገበያ ባለስልጣኑም በአዋጁ የተሰጠውን ትልቅ ኀላፊነት ለመወጣት አስፈላጊውን ዝግጅት ሊወስድ የሚገባ ሲሆን በግብይት ሂደት ተሳታፊ የሆኑ ቅን ባለሀብቶችን መብት ጥበቃ ሊያደርግ የሚያስፈልግ ሲሆን አጭበርባሪዎችን ለአሰራር እንቅፋት የሚፈጥሩትን በመለየት እንዲታረሙ ከማድረግ አንጻር ተገቢውን ጥረት ሊያደርግ የሚገባው ነው። ይህ ሲሆን የካፒታል ገበያ አዋጅ 1248/13 ተፈጻሚ በማድረግ ለሀገራችን ትልቅ የኢኮኖሚ ፋይዳ ያለው ስለመሆኑ አያጠያይቅም።
ማጣቀሻዎች/References/
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1/1987
2. የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13
3. Fantahun Delelew, Challenge and opportunities of the implementation of capital proclamation 1248/13,Addisababa University
(የካፒታል አዋጁ አፈጻጸም ተግዳሮት እና መጻኢ እድል)
4. የብሔራዊ ባንክ አዋጅ ቁጥር 1359/17
5. ስለ ባንክ ስራዎች አዋጅ ቁጥር 1360/17
https://www.facebook.com
https://t.me/Fantahunlawye...
4 months ago
🚗 የቤትና የመኪና ባለቤት መሆን አሁን ቀላል ነው
ሆራይዘን በታላቅ ሽልማቶች ሥራ ጀመረ! 🏠✨
#ethiopia | "ይቆጥቡ ይሸለሙ!" በሚል መሪ ቃል በፋይናንሱ ዘርፍ አዲስ ተስፋ ይዞ የመጣው ሆራይዘን የገንዘብ ብድርና ቁጠባ የኅብረት ሥራ ማኀበር፣ 3ኛ ቅርንጫፉን በአዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ ከፍቷል።
ለምን ሆራይዘንን ይመርጣሉ?
🏆 የሆራይዘን ሽልማቶች፦
ተቋሙ ሥራውን በይፋ ሲጀምር የቤት እና የመኪና ሽልማቶችን አዘጋጅቶ መጥቷል።
💻 የሆራይዘን የቴክኖሎጂ መሪነት፦
በኢትዮጵያ በብድርና ቁጠባ ተቋማት የመጀመርያ የሆነው እጅግ ዘመናዊ የሆነ የራሱ ቴክኖሎጂ In house Developed Cor banking system ይዞ በኢትዮጵያ የብርድና ቁጠባ ተቋም ኢንዱስትሪ መዝለቁን አቶ ሀበን ኪሮስ አስታውቀዋል።
150 የሚሆኑ መሥራች አባላት ይዞ ሥራውን ጀምሯል።
💰 የሆራይዘን ሰፊ የብድር አማራጭ፦
* ለመንግስት ሰራተኞች፦
እስከ 500,000 ብር ያለ ዋስትና (በጠለፋ ዋስትና)።
ለሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች፦
እስከ 10 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ብድር እንደሚሰጥ የሆራይዘን የገንዘብ ብድርና ቁጠባ የኅብረት ሥራ ማኀበር ጊዚያዊ አስተባባሪ አቶ ዳዊት ገብሩ አስታውቀዋል።
⏳የሆራይዘን ፈጣን አገልግሎት፦
የተበታተነ የህዝብ ሀብትን በመሰብሰብ፣ አባላት ከአንድ ወር ቆጣቢነት በኋላ ብድር ማግኘት የሚችሉበትን ስርአት ዘርግቷል።
ሆራይዘን የገንዘብ ብድርና ቁጠባ የኅብረት ሥራ ማኀበር
የቁጠባ አይነቶች፦
መደበኛ፣ የኢንቨስትመንት፣ የሴቶች፣ የልጆች፣ የቤት፣ የመኪና፣ የህክምና እና የግብርና ቁጠባዎችን ያካትታል።
ተቋሙ ከአዶ Fertility Center፣ ከአብሪ ሞተርስ (Abri Motors) እና ከአፍሮ ኢንቨስትመንት ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሷል።
ከአዶ Fertility Center የሼር ሽያጭ 10 ሚሊዮን ደርሷል።
ከAbri Motors በኢትዮዽያ የመጀመርያዉ በነፃ የመኪና መሸጫ E-commerce በመጠቀም እና በመሸጥ የመኪና ብድር በራሳቸዉ ዝግ አካዉንት ያከናውናሉ።
ሆራይዘን የገንዘብ ብድርና ቁጠባ የኅብረት ሥራ ማኀበር
ከአፍሮ ኢንቨስትመንት የብራንዲንግ ስምምነት በማድግ መሥራት መጀመሩን አብስሯል።
መላው ኢትዮጵያውያን እና ዳያስፖራዎች የዚህ ታላቅ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተቋሙ የቦርድ ሊቀ መንበር ወ/ሮ አብርኸት አየለ ጥሪ አቅርበዋል።
በሆራይዘን እጅዎ ላይ ባለ አፕ ይቆጥቡ ይሸለሙ
አድራሻ፣
ቦሌ ሰንቸሪ ሞል ዩጎ ቸርች አጠገብ
ስልክ ቁጥር
0905311308 /0904209768 ይደውሉልን
የነገውን ብሩህ ተስፋ ዛሬ በሆራይዘን ይጀምሩ! 🚀
#horizonsacco #ethiopiafinance #savingandcredit #addisababa #businessethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
ሆራይዘን በታላቅ ሽልማቶች ሥራ ጀመረ! 🏠✨
#ethiopia | "ይቆጥቡ ይሸለሙ!" በሚል መሪ ቃል በፋይናንሱ ዘርፍ አዲስ ተስፋ ይዞ የመጣው ሆራይዘን የገንዘብ ብድርና ቁጠባ የኅብረት ሥራ ማኀበር፣ 3ኛ ቅርንጫፉን በአዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ ከፍቷል።
ለምን ሆራይዘንን ይመርጣሉ?
🏆 የሆራይዘን ሽልማቶች፦
ተቋሙ ሥራውን በይፋ ሲጀምር የቤት እና የመኪና ሽልማቶችን አዘጋጅቶ መጥቷል።
💻 የሆራይዘን የቴክኖሎጂ መሪነት፦
በኢትዮጵያ በብድርና ቁጠባ ተቋማት የመጀመርያ የሆነው እጅግ ዘመናዊ የሆነ የራሱ ቴክኖሎጂ In house Developed Cor banking system ይዞ በኢትዮጵያ የብርድና ቁጠባ ተቋም ኢንዱስትሪ መዝለቁን አቶ ሀበን ኪሮስ አስታውቀዋል።
150 የሚሆኑ መሥራች አባላት ይዞ ሥራውን ጀምሯል።
💰 የሆራይዘን ሰፊ የብድር አማራጭ፦
* ለመንግስት ሰራተኞች፦
እስከ 500,000 ብር ያለ ዋስትና (በጠለፋ ዋስትና)።
ለሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች፦
እስከ 10 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ብድር እንደሚሰጥ የሆራይዘን የገንዘብ ብድርና ቁጠባ የኅብረት ሥራ ማኀበር ጊዚያዊ አስተባባሪ አቶ ዳዊት ገብሩ አስታውቀዋል።
⏳የሆራይዘን ፈጣን አገልግሎት፦
የተበታተነ የህዝብ ሀብትን በመሰብሰብ፣ አባላት ከአንድ ወር ቆጣቢነት በኋላ ብድር ማግኘት የሚችሉበትን ስርአት ዘርግቷል።
ሆራይዘን የገንዘብ ብድርና ቁጠባ የኅብረት ሥራ ማኀበር
የቁጠባ አይነቶች፦
መደበኛ፣ የኢንቨስትመንት፣ የሴቶች፣ የልጆች፣ የቤት፣ የመኪና፣ የህክምና እና የግብርና ቁጠባዎችን ያካትታል።
ተቋሙ ከአዶ Fertility Center፣ ከአብሪ ሞተርስ (Abri Motors) እና ከአፍሮ ኢንቨስትመንት ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሷል።
ከአዶ Fertility Center የሼር ሽያጭ 10 ሚሊዮን ደርሷል።
ከAbri Motors በኢትዮዽያ የመጀመርያዉ በነፃ የመኪና መሸጫ E-commerce በመጠቀም እና በመሸጥ የመኪና ብድር በራሳቸዉ ዝግ አካዉንት ያከናውናሉ።
ሆራይዘን የገንዘብ ብድርና ቁጠባ የኅብረት ሥራ ማኀበር
ከአፍሮ ኢንቨስትመንት የብራንዲንግ ስምምነት በማድግ መሥራት መጀመሩን አብስሯል።
መላው ኢትዮጵያውያን እና ዳያስፖራዎች የዚህ ታላቅ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተቋሙ የቦርድ ሊቀ መንበር ወ/ሮ አብርኸት አየለ ጥሪ አቅርበዋል።
በሆራይዘን እጅዎ ላይ ባለ አፕ ይቆጥቡ ይሸለሙ
አድራሻ፣
ቦሌ ሰንቸሪ ሞል ዩጎ ቸርች አጠገብ
ስልክ ቁጥር
0905311308 /0904209768 ይደውሉልን
የነገውን ብሩህ ተስፋ ዛሬ በሆራይዘን ይጀምሩ! 🚀
#horizonsacco #ethiopiafinance #savingandcredit #addisababa #businessethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ባለሙያዎችን ወደ ውሳኔ ሰጪነት አመጣ፦ የፖሊሲ ነፃነት ወይስ የሉዓላዊነት ስጋት?
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በአዲሱ አዋጁ መሠረት፣ በገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው (MPC) ውስጥ ሁለት ታዋቂ የውጭ ሀገር የኢኮኖሚክስ ባለሙያዎችን መሾሙን አስታውቋል። ይህ እርምጃ በኢትዮጵያ የባንክ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ተደርጎ ተወስዷል።
ሳይንሳዊ ውሳኔ፦ የፖሊሲ ውሳኔዎች ከፖለቲካ ተጽዕኖ ነፃ ሆነው በማስረጃ እና በሳይንሳዊ ትንተና ላይ እንዲመሰረቱ ያደርጋል።
ዓለም አቀፍ ተቀባይነት፦ እንደ እንግሊዝ ማዕከላዊ ባንክ (Bank of England) ያሉ ተቋማት ልምድን በመቀመር፣ ለዓለም አቀፍ አበዳሪዎችና ባለሀብቶች ባንኩ ነፃ መሆኑን ያሳያል።
የሃሳብ ብዝሃነት፦ በውሳኔ አሰጣጥ ወቅት አንድ አይነት አስተሳሰብን (Groupthink) በመቀነስ፣ አማራጭ የኢኮኖሚ መፍትሄዎችን ያመነጫል።
እነዚህ ባለሙያዎች የሚቀላቀሉት የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (MPC)፣ በሀገሪቱ ያለውን የወለድ መጠን የመወሰን፣ የገንዘብ ስርጭትን የመቆጣጠር እና የዋጋ ግሽበትን የማረጋጋት ከፍተኛ ስልጣን ያለው አካል ነው።
ይህም ባንኩ ከመንግስት ካዝና ጠባቂነት ወጥቶ፣ ገለልተኛ የኢኮኖሚ ተዋናይ እንዲሆን ለጀመረው ማሻሻያ ትልቅ እገዛ ያደርጋል።
⚖️አዎንታዊ ጎኑ፦
ባንኩ "የማኔጂመንት ጥራት" (Institutional Quality) እንዲኖረውና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ገበያ አመኔታ እንዲያገኝ ያደርጋል። ይህም የውጭ ኢንቨስትመንት እንዲሳብ በር ይከፍታል።
ሊታሰቡ የሚገቡ ስጋቶች፦
የሀገር በቀል እውቀት ክፍተት፦ የውጭ ባለሙያዎቹ የኢትዮጵያን ተጨባጭ መዋቅራዊ ችግሮች (ለምሳሌ የጥቁር ገበያ ባህሪ እና የማህበረሰቡን የፍጆታ ዘይቤ) በውል ካልተረዱ፣ የሚያመጧቸው መፍትሄዎች "ንድፈ-ሃሳባዊ" ብቻ ሊሆኑ ይችላሉ።
የሉዓላዊነት ጥያቄ፦ የሀገሪቱን ቁልፍ የኢኮኖሚ ውሳኔዎች ለውጭ ዜጎች አሳልፎ መስጠት፣ በፖለቲካዊ ረገድ "የውጭ ተጽዕኖ" የሚል ትችት ሊያስነሳ ይችላል።
🎯 ዋና ዓላማው፦ የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር እና አገሪቱ የጀመረችውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በስኬት ማጠናቀቅ ነው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በአዲሱ አዋጁ መሠረት፣ በገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው (MPC) ውስጥ ሁለት ታዋቂ የውጭ ሀገር የኢኮኖሚክስ ባለሙያዎችን መሾሙን አስታውቋል። ይህ እርምጃ በኢትዮጵያ የባንክ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ተደርጎ ተወስዷል።
ሳይንሳዊ ውሳኔ፦ የፖሊሲ ውሳኔዎች ከፖለቲካ ተጽዕኖ ነፃ ሆነው በማስረጃ እና በሳይንሳዊ ትንተና ላይ እንዲመሰረቱ ያደርጋል።
ዓለም አቀፍ ተቀባይነት፦ እንደ እንግሊዝ ማዕከላዊ ባንክ (Bank of England) ያሉ ተቋማት ልምድን በመቀመር፣ ለዓለም አቀፍ አበዳሪዎችና ባለሀብቶች ባንኩ ነፃ መሆኑን ያሳያል።
የሃሳብ ብዝሃነት፦ በውሳኔ አሰጣጥ ወቅት አንድ አይነት አስተሳሰብን (Groupthink) በመቀነስ፣ አማራጭ የኢኮኖሚ መፍትሄዎችን ያመነጫል።
እነዚህ ባለሙያዎች የሚቀላቀሉት የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (MPC)፣ በሀገሪቱ ያለውን የወለድ መጠን የመወሰን፣ የገንዘብ ስርጭትን የመቆጣጠር እና የዋጋ ግሽበትን የማረጋጋት ከፍተኛ ስልጣን ያለው አካል ነው።
ይህም ባንኩ ከመንግስት ካዝና ጠባቂነት ወጥቶ፣ ገለልተኛ የኢኮኖሚ ተዋናይ እንዲሆን ለጀመረው ማሻሻያ ትልቅ እገዛ ያደርጋል።
⚖️አዎንታዊ ጎኑ፦
ባንኩ "የማኔጂመንት ጥራት" (Institutional Quality) እንዲኖረውና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ገበያ አመኔታ እንዲያገኝ ያደርጋል። ይህም የውጭ ኢንቨስትመንት እንዲሳብ በር ይከፍታል።
ሊታሰቡ የሚገቡ ስጋቶች፦
የሀገር በቀል እውቀት ክፍተት፦ የውጭ ባለሙያዎቹ የኢትዮጵያን ተጨባጭ መዋቅራዊ ችግሮች (ለምሳሌ የጥቁር ገበያ ባህሪ እና የማህበረሰቡን የፍጆታ ዘይቤ) በውል ካልተረዱ፣ የሚያመጧቸው መፍትሄዎች "ንድፈ-ሃሳባዊ" ብቻ ሊሆኑ ይችላሉ።
የሉዓላዊነት ጥያቄ፦ የሀገሪቱን ቁልፍ የኢኮኖሚ ውሳኔዎች ለውጭ ዜጎች አሳልፎ መስጠት፣ በፖለቲካዊ ረገድ "የውጭ ተጽዕኖ" የሚል ትችት ሊያስነሳ ይችላል።
🎯 ዋና ዓላማው፦ የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር እና አገሪቱ የጀመረችውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በስኬት ማጠናቀቅ ነው።
4 months ago
የጄፍሪ ኤፕስታይን የሀብት ምስጢር፡- መምህሩ እንዴት ሚሊየነር ሆነ?
በኒውዮርክ ኮኒ አይላንድ በሚገኝ ተራ የሰራተኛ መደብ ቤተሰብ ውስጥ ያደገው ጄፍሪ ኤፕስታይን፣ ገና በወጣትነቱ ያልተገራ ምኞትና ልዩ የማሳመን ችሎታ ነበረው። ምንም እንኳን የዩኒቨርሲቲ ዲግሪ ባይኖረውም፣ በዳልተን የግል ትምህርት ቤት ውስጥ የፊዚክስና የሒሳብ መምህር ሆኖ ተቀጠረ። ይህ ትምህርት ቤት የኒውዮርክ ባለጸጎች ልጆች የሚማሩበት በመሆኑ፣ ኤፕስታይን ወደ ኃያላኑ ዓለም ለመግባት የመጀመሪያውን በር እንዲያንኳኳ ረዳው።
የቤር ስተርንስ ዘመን እና የውሸት መሰላል
በፈረንጆቹ 1970ዎቹ መገባደጃ ላይ፣ ኤፕስታይን በአንድ ተማሪው ወላጅ አማካኝነት በታዋቂው የኢንቨስትመንት ባንክ ቤር ስተርንስ ውስጥ ሥራ አገኘ። እዚህ ጋር ነበር "የፋይናንስ ሊቅ" የሚለውን ጭንብል መልበስ የጀመረው። በዎል ስትሪት የንግድ ልውውጥ ዓለም ውስጥ በፍጥነት በመገስገስ በ1980 የኩባንያው አጋር ለመሆን በቃ። ሆኖም ይህ ስኬት ብዙም አልዘለቀም፤ በባንኩ ውስጥ በነበረው የሥነ-ምግባር ጉድለት ምክንያት ከስራው ተባረረ።
ነገር ግን ኤፕስታይን መውደቅን ወደ ዕድል የመለወጥ ሰይጣናዊ ችሎታ ነበረው። ከባንኩ ከወጣ በኋላ የራሱን የማማከር ስራ የጀመረ ቢሆንም፣ ዋናው የገቢ ምንጩ ግን ጨለማ የተሞላበት ነበር። ስቴፈን ሆፈንበርግ የተባለው የ"ታወርስ ፋይናንሺያል" ዳይሬክተር በኋላ ላይ እንደመሰከረው፣ ኤፕስታይን በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ የተበላበት የ"ፖንዚ ስኪም" (Ponzi scheme) ዋና አርክቴክት ነበር። ሆፈንበርግ ወደ እስር ቤት ሲወርድ፣ ኤፕስታይን ግን በሚገርም ሁኔታ ሳይከሰስ አመለጠ።
የቢሊየነሩ "ጥላ"፡ ሌስ ዌክስነር
የኤፕስታይን የሀብት ማማ የተገነባው በቪክቶሪያ ሲክሬት መስራች በቢሊየነሩ ሌስ ዌክስነር ጀርባ ላይ ነው። በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ ኤፕስታይን የዌክስነር የቅርብ ወዳጅና የፋይናንስ አማካሪ ሆነ። ዌክስነር ለኤፕስታይን የሰጠው ስልጣን በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ነበር፤ የባንክ ሂሳቦቹን፣ ንብረቶቹንና የግል ድርጅቶቹን ሙሉ በሙሉ እንዲያስተዳድር "Power of Attorney" ሰጠው።
ይህ ግንኙነት ኤፕስታይንን ከምንም ተነስቶ ወደ ታላላቅ የቅንጦት ቤቶች፣ የግል አውሮፕላኖችና ወደማይነጥፍ የገንዘብ ምንጭ አሸጋገረው። ኤፕስታይን በዌክስነር ስም ንብረቶችን እየገዛ በዝቅተኛ ዋጋ ለራሱ ያዛውር ነበር። በኒውዮርክ የሚገኘው ታዋቂው ግዙፍ መኖሪያ ቤቱና "ሎሊታ ኤክስፕረስ" ተብሎ የሚጠራው የግል አውሮፕላኑ የተገኙት በዚህ ማጭበርበር እንደሆነ ይታመናል።
ዌክስነር በኋላ ላይ ኤፕስታይን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እንደሰረቀበት ቢናገርም፣ በሁለቱ መካከል የነበረው ምስጢራዊ ትስስር ግን እስከ መጨረሻው ድረስ ጥያቄ ምልክት ሆኖ ቆይቷል።
የጥቁር መዝገብና የኃይል አውታር
የኤፕስታይን ሀብት ከገንዘብ በላይ ነበር—እሱ የሰዎችን ምስጢር ይሰበስብ ነበር። በዓለም ዙሪያ ያሉ ፖለቲከኞችን፣ ሳይንቲስቶችን፣ የንጉሳዊ ቤተሰብ አባላትንና ታዋቂ ሰዎችን ወደ ግል ደሴቱና መኖሪያ ቤቶቹ ይጋብዝ ነበር። እዚያ በሚደረጉት ህገ-ወጥ ድርጊቶችና የህጻናት ዝውውሮች ውስጥ እነዚህን ኃያላን ሰዎች በማሳተፍ "ጥቁር መዝገብ" (Blackmail) እንደያዘባቸው በሰፊው ይታመናል።
ይህ የጥቁር መዝገብ ስልጣን ኤፕስታይንን የማይነካ አደረገው። በ2008 በሕፃናት ላይ በፈጸመው አስከፊ ወንጀል ተከሶ እንኳን፣ ከአቃቤ ሕግ ጋር ባደረገው "የምስጢር ስምምነት" ምክንያት በጣም ቀላል ቅጣት ብቻ ተቀብሎ ወጣ። ጄፒ ሞርጋን (JPMorgan Chase) እና ዶቼ ባንክ (Deutsche Bank) የመሳሰሉ ግዙፍ የገንዘብ ተቋማት፣ ኤፕስታይን ወንጀለኛ መሆኑ እየታወቀ እንኳን ለዓመታት የገንዘብ ዝውውሩን አስተናግደውለታል።
ውድቀትና አሳዛኝ ፍጻሜ
የኤፕስታይን የውሸት ዓለም በሐምሌ 2019 ፈረሰ። በሕፃናት ዝውውርና ወሲባዊ ጥቃት ተከሶ በቁጥጥር ስር ዋለ። በዚህ ጊዜ ግን የጥቁር መዝገቡም ሆነ የገንዘብ ክምችቱ ሊያድኑት አልቻሉም። ነሐሴ 2019 በኒውዮርክ በሚገኝ ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግበት እስር ቤት ውስጥ በሞት ተገኘ። ይፋዊው ሪፖርት "ራሱን አጠፋ" ቢልም፣ ብዙዎች ግን "ከጀርባ ያሉት ኃያላን ሰዎች ምስጢራቸውን ለመጠበቅ ገድለውታል" ብለው ያምናሉ።
ኤፕስታይን ሲሞት ሀብቱ 577 ሚሊዮን ዶላር ይገመት ነበር። ሆኖም ይህ ሀብት በብልህ የኢንቨስትመንት ስራ ሳይሆን በስርቆት፣ በማጭበርበር፣ በሰዎች ስቃይና በክህደት የተገነባ ነበር። ዛሬ ያ ንብረት ለተበዳዮች ካሳና ለሕግ ወጪዎች እየዋለ ይገኛል።
የጄፍሪ ኤፕስታይን ታሪክ የገንዘብ ስኬት ታሪክ አይደለም፤ ይልቁንም የሞራል ዝቅጠትና የስርዓት ጉድለት ታሪክ ነው። አንድ መምህር የዓለምን ኃያላን መረብ ውስጥ አስገብቶ ሲያሾፍባቸው መኖሩ፣ በዓለማችን ላይ ያለው የፍትህና የፋይናንስ ስርዓት ምን ያህል ክፍተት እንዳለበት ማሳያ ነው። ኤፕስታይን የገነባው ግዙፍ ግዛት ዛሬ የለም፤ የተረፈው ግን በብዙ ወጣት ሴቶች ሕይወት ላይ የተከለከለ ጠባሳና በታሪክ የማይፋቅ ጥቁር ነጥብ ብቻ ነው።
በኒውዮርክ ኮኒ አይላንድ በሚገኝ ተራ የሰራተኛ መደብ ቤተሰብ ውስጥ ያደገው ጄፍሪ ኤፕስታይን፣ ገና በወጣትነቱ ያልተገራ ምኞትና ልዩ የማሳመን ችሎታ ነበረው። ምንም እንኳን የዩኒቨርሲቲ ዲግሪ ባይኖረውም፣ በዳልተን የግል ትምህርት ቤት ውስጥ የፊዚክስና የሒሳብ መምህር ሆኖ ተቀጠረ። ይህ ትምህርት ቤት የኒውዮርክ ባለጸጎች ልጆች የሚማሩበት በመሆኑ፣ ኤፕስታይን ወደ ኃያላኑ ዓለም ለመግባት የመጀመሪያውን በር እንዲያንኳኳ ረዳው።
የቤር ስተርንስ ዘመን እና የውሸት መሰላል
በፈረንጆቹ 1970ዎቹ መገባደጃ ላይ፣ ኤፕስታይን በአንድ ተማሪው ወላጅ አማካኝነት በታዋቂው የኢንቨስትመንት ባንክ ቤር ስተርንስ ውስጥ ሥራ አገኘ። እዚህ ጋር ነበር "የፋይናንስ ሊቅ" የሚለውን ጭንብል መልበስ የጀመረው። በዎል ስትሪት የንግድ ልውውጥ ዓለም ውስጥ በፍጥነት በመገስገስ በ1980 የኩባንያው አጋር ለመሆን በቃ። ሆኖም ይህ ስኬት ብዙም አልዘለቀም፤ በባንኩ ውስጥ በነበረው የሥነ-ምግባር ጉድለት ምክንያት ከስራው ተባረረ።
ነገር ግን ኤፕስታይን መውደቅን ወደ ዕድል የመለወጥ ሰይጣናዊ ችሎታ ነበረው። ከባንኩ ከወጣ በኋላ የራሱን የማማከር ስራ የጀመረ ቢሆንም፣ ዋናው የገቢ ምንጩ ግን ጨለማ የተሞላበት ነበር። ስቴፈን ሆፈንበርግ የተባለው የ"ታወርስ ፋይናንሺያል" ዳይሬክተር በኋላ ላይ እንደመሰከረው፣ ኤፕስታይን በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ የተበላበት የ"ፖንዚ ስኪም" (Ponzi scheme) ዋና አርክቴክት ነበር። ሆፈንበርግ ወደ እስር ቤት ሲወርድ፣ ኤፕስታይን ግን በሚገርም ሁኔታ ሳይከሰስ አመለጠ።
የቢሊየነሩ "ጥላ"፡ ሌስ ዌክስነር
የኤፕስታይን የሀብት ማማ የተገነባው በቪክቶሪያ ሲክሬት መስራች በቢሊየነሩ ሌስ ዌክስነር ጀርባ ላይ ነው። በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ ኤፕስታይን የዌክስነር የቅርብ ወዳጅና የፋይናንስ አማካሪ ሆነ። ዌክስነር ለኤፕስታይን የሰጠው ስልጣን በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ነበር፤ የባንክ ሂሳቦቹን፣ ንብረቶቹንና የግል ድርጅቶቹን ሙሉ በሙሉ እንዲያስተዳድር "Power of Attorney" ሰጠው።
ይህ ግንኙነት ኤፕስታይንን ከምንም ተነስቶ ወደ ታላላቅ የቅንጦት ቤቶች፣ የግል አውሮፕላኖችና ወደማይነጥፍ የገንዘብ ምንጭ አሸጋገረው። ኤፕስታይን በዌክስነር ስም ንብረቶችን እየገዛ በዝቅተኛ ዋጋ ለራሱ ያዛውር ነበር። በኒውዮርክ የሚገኘው ታዋቂው ግዙፍ መኖሪያ ቤቱና "ሎሊታ ኤክስፕረስ" ተብሎ የሚጠራው የግል አውሮፕላኑ የተገኙት በዚህ ማጭበርበር እንደሆነ ይታመናል።
ዌክስነር በኋላ ላይ ኤፕስታይን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እንደሰረቀበት ቢናገርም፣ በሁለቱ መካከል የነበረው ምስጢራዊ ትስስር ግን እስከ መጨረሻው ድረስ ጥያቄ ምልክት ሆኖ ቆይቷል።
የጥቁር መዝገብና የኃይል አውታር
የኤፕስታይን ሀብት ከገንዘብ በላይ ነበር—እሱ የሰዎችን ምስጢር ይሰበስብ ነበር። በዓለም ዙሪያ ያሉ ፖለቲከኞችን፣ ሳይንቲስቶችን፣ የንጉሳዊ ቤተሰብ አባላትንና ታዋቂ ሰዎችን ወደ ግል ደሴቱና መኖሪያ ቤቶቹ ይጋብዝ ነበር። እዚያ በሚደረጉት ህገ-ወጥ ድርጊቶችና የህጻናት ዝውውሮች ውስጥ እነዚህን ኃያላን ሰዎች በማሳተፍ "ጥቁር መዝገብ" (Blackmail) እንደያዘባቸው በሰፊው ይታመናል።
ይህ የጥቁር መዝገብ ስልጣን ኤፕስታይንን የማይነካ አደረገው። በ2008 በሕፃናት ላይ በፈጸመው አስከፊ ወንጀል ተከሶ እንኳን፣ ከአቃቤ ሕግ ጋር ባደረገው "የምስጢር ስምምነት" ምክንያት በጣም ቀላል ቅጣት ብቻ ተቀብሎ ወጣ። ጄፒ ሞርጋን (JPMorgan Chase) እና ዶቼ ባንክ (Deutsche Bank) የመሳሰሉ ግዙፍ የገንዘብ ተቋማት፣ ኤፕስታይን ወንጀለኛ መሆኑ እየታወቀ እንኳን ለዓመታት የገንዘብ ዝውውሩን አስተናግደውለታል።
ውድቀትና አሳዛኝ ፍጻሜ
የኤፕስታይን የውሸት ዓለም በሐምሌ 2019 ፈረሰ። በሕፃናት ዝውውርና ወሲባዊ ጥቃት ተከሶ በቁጥጥር ስር ዋለ። በዚህ ጊዜ ግን የጥቁር መዝገቡም ሆነ የገንዘብ ክምችቱ ሊያድኑት አልቻሉም። ነሐሴ 2019 በኒውዮርክ በሚገኝ ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግበት እስር ቤት ውስጥ በሞት ተገኘ። ይፋዊው ሪፖርት "ራሱን አጠፋ" ቢልም፣ ብዙዎች ግን "ከጀርባ ያሉት ኃያላን ሰዎች ምስጢራቸውን ለመጠበቅ ገድለውታል" ብለው ያምናሉ።
ኤፕስታይን ሲሞት ሀብቱ 577 ሚሊዮን ዶላር ይገመት ነበር። ሆኖም ይህ ሀብት በብልህ የኢንቨስትመንት ስራ ሳይሆን በስርቆት፣ በማጭበርበር፣ በሰዎች ስቃይና በክህደት የተገነባ ነበር። ዛሬ ያ ንብረት ለተበዳዮች ካሳና ለሕግ ወጪዎች እየዋለ ይገኛል።
የጄፍሪ ኤፕስታይን ታሪክ የገንዘብ ስኬት ታሪክ አይደለም፤ ይልቁንም የሞራል ዝቅጠትና የስርዓት ጉድለት ታሪክ ነው። አንድ መምህር የዓለምን ኃያላን መረብ ውስጥ አስገብቶ ሲያሾፍባቸው መኖሩ፣ በዓለማችን ላይ ያለው የፍትህና የፋይናንስ ስርዓት ምን ያህል ክፍተት እንዳለበት ማሳያ ነው። ኤፕስታይን የገነባው ግዙፍ ግዛት ዛሬ የለም፤ የተረፈው ግን በብዙ ወጣት ሴቶች ሕይወት ላይ የተከለከለ ጠባሳና በታሪክ የማይፋቅ ጥቁር ነጥብ ብቻ ነው።
4 months ago
የዶላር ዳግም ልደት ወይስ የኢኮኖሚ ቁማር? የኢትዮጵያ “ቢግ ባንግ” ሪፎርም እና የነፃ ገበያ መገፋፋት
1. የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ያደረገው የውጭ ምንዛሪ መመሪያ፣ ዝም ብሎ የቴክኒክ ሰነድ አይደለም፤ ይልቁንም ላለፉት 50 ዓመታት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ደም ስር አንቆ የያዘውን “የቁጥጥር ሰንሰለት” የሚበጣጥስ መጥረቢያ ነው። ይህ 19 ነጥቦችን የያዘው አዋጅ፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ አድርጋው የማታውቀውን የኢኮኖሚ “ቢግ ባንግ” (Big Bang) ሽግግር መጀመሯን ያበስራል። በኢኮኖሚ ፈላስፎች መነጽር ሲታይ፣ ይህ እርምጃ አዳም ስሚዝ “የማይታየው እጅ” (Invisible Hand) ብሎ የጠራውን ገበያ መር ስርዓት በኢትዮጵያ ምድር ለመትከል የተደረገ ደፋር ሙከራ ነው።
2. የዚህ ሪፎርም ዋነኛው መነሻ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር የተደረሰው የ 3.4 ቢሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት ቢሆንም፣ ውስጣዊ ፍላጎቱ ግን የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ረሃብ በዘላቂነት መፍታት ነው። ቀደም ሲል በኦፊሴላዊው የምንዛሪ ዋጋ እና በጥቁር ገበያው መካከል የነበረው ልዩነት (Premium) ከ 100% በላይ ማደጉ፣ ምርት ወደ ውጭ የሚላክበትን ሳይሆን ዶላር የሚሸሸግበትን ኢኮኖሚ ፈጥሮ ነበር። አዲሱ መመሪያ ይህንን “የጥላ ኢኮኖሚ” አፍርሶ፣ ዶላርን ከጓዳ ወደ ባንክ አደባባይ ለማውጣት የታለመ ነው።
3. የአገልግሎት ላኪዎች 100% ገቢያቸውን እንዲይዙ መፈቀዱ (አንቀጽ 1)፣ ከቲዮሪ አንጻር “የባለቤትነት መብት” (Property Rights) ማረጋገጫ ነው። ጆን ሎክ እንደሚለው፣ አንድ ሰው በጥረቱ ያገኘውን ሀብት የመጠቀም ሙሉ መብት ሊኖረው ይገባል። መንግስት ቀደም ሲል ከላኪዎች ላይ ይነጥቅ የነበረውን 50% እና ከዚያ በላይ ድርሻ መተዉ፣ ላኪዎች ይበልጥ እንዲያመርቱ ትልቅ ማበረታቻ (Incentive) ይፈጥራል። ይህ ደግሞ በረዥም ጊዜ የሀገሪቱን የወጪ ንግድ ገቢ በቢሊዮን ዶላሮች እንደሚያሳድገው ይጠበቃል።
4. ግለሰቦች ለቤተሰቦቻቸው እስከ 3,000 ዶላር እንዲልኩ መፈቀዱ (አንቀጽ 8)፣ የመንግስትን የቁጥጥር ስፋት (State Scope) በእጅጉ ይቀንሳል። ይህ እርምጃ ሚልተን ፍሪድማን “Capitalism and Freedom” በሚለው መጽሐፉ የጠቀሰውን የግል ኢኮኖሚ ነፃነት የሚያንፀባርቅ ነው። ዜጎች በገዛ ገንዘባቸው የልጆቻቸውን ትምህርትና ህክምና እንዲከፍሉ መፈቀዱ፣ በህዝብና በመንግስት መካከል ለዘመናት ተሸርሽሮ የነበረውን ማህበራዊ ውል (Social Contract) መልሶ የማደስ አቅም አለው።
5. ዳታዎች እንደሚያሳዩት፣ ኢትዮጵያ በየአመቱ ከዳያስፖራ የምታገኘው ሬሚታንስ (Remittance) ከ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ቢሆንም፣ ከግማሽ በላይ የሚሆነው በህገ-ወጥ መንገድ ይዘዋወር ነበር። አዲሱ መመሪያ ዶላርን ያለ ሰነድ መመንዘር መፍቀዱ (አንቀጽ 7)፣ ይህን በጥቁር ገበያ የሚመላለሰውን ቢሊዮን ዶላር ወደ ህጋዊው ስርዓት የሚመልስ “መግነጢሳዊ ኃይል” ነው። ይህ የገንዘብ ፍሰት ወደ ባንኮች ሲገባ፣ ባንኮች ለኢንዱስትሪው የሚሰጡት የብድር አቅም (Liquidity) በእጥፍ ሊያድግ ይችላል።
6. የውጭ ኢንቨስተሮች ትርፋቸውን ያለ ገደብ እንዲያወጡ መፈቀዱ (አንቀጽ 16) ግን የሁለት ስለት ቢላዋ ነው። ለዴቪድ ሪካርዶ የንግድ ቲዮሪ ተከታዮች፣ ይህ እርምጃ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን (FDI) የሚስብ ማር ነው። ሆኖም፣ እንደ ጆሴፍ ስቲግሊዝ ያሉ ሊቃውንት “የካፒታል ሽሽት” (Capital Flight) ስጋትን ያነሳሉ። በሀገር ውስጥ የፖለቲካ አለመረጋጋት ቢከሰት፣ ኢንቨስተሮች ያላቸውን ዶላር ይዘው በአንድ ጀምበር ቢወጡ፣ የኢትዮጵያ የውጭ መጠባበቂያ ክምችት (Foreign Reserve) ድንገት ሊሟጠጥ ይችላል።
7. የባንኮች ራስ-ገዝነት (Autonomy) መጨመር ሌላው የዚህ ሪፎርም ምሰሶ ነው። ባንኮች የፎርዋርድ ግብይት (Forward Transaction) እንዲያካሂዱ መፈቀዱ (አንቀጽ 9)፣ ነጋዴዎች ለወደፊት ግዢዎቻቸው የምንዛሪ ዋጋን ቀድመው እንዲቆልፉ (Hedging) ይረዳቸዋል። ይህ በንግድ ዓለም ውስጥ ያለውን እርግጠኛ አለመሆን (Uncertainty) በመቀነስ፣ የዋጋ ግሽበትን ለማረጋጋት የሚረዳ ዘመናዊ የፋይናንስ መሳሪያ ነው።
8. ይሁን እንጂ፣ ባንኮች ከካፒታላቸው 10% ዋስትና እንዲሰጡ መፈቀዱ (አንቀጽ 14) ልብ አንጠልጣይ አደጋ አለው። የኢትዮጵያ ባንኮች በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ቀውስ የመመታት ልምድ የላቸውም። ባንኮች የገቡት ዋስትና ተቀባይነት አጥቶ ወይም ብድሩ ሳይከፈል ቢቀር፣ የሀገር ውስጥ ባንኮች መክሰር (Bank Failure) ደረጃ ሊደርሱ ይችላሉ። ይህ ደግሞ በዜጎች ቁጠባ ላይ ትልቅ አደጋ ስለሚደቅን፣ የብሔራዊ ባንክ የቁጥጥር ዓይን (Supervision) እጅግ ንቁ መሆን አለበት።
9. የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ጥሬ ገንዘብ የመያዝ አቅማቸው ወደ 25% ማደጉ (አንቀጽ 18)፣ የገበያውን የዶላር ዝውውር (Circulation) ያቀልጠዋል። ይህ እርምጃ የጥቁር ገበያ ደላሎችን ከስራ የሚያስወጣ ቢሆንም፣ አዲሶቹ የፍቃድ ባለቤቶች ራሳቸው ወደ “ህጋዊ ደላላነት” እንዳይቀየሩ ጥብቅ ኦዲት ይፈልጋል። የገንዘብ ማጠብ (Money Laundering) ወንጀሎችን ለመከላከል የዲጂታል ክትትል ስርዓት የግድ ይላል።
10. የቬትናምን ተሞክሮ ብንመለከት፣ ሀገሪቱ በ 1980 ዎቹ መጨረሻ መሰል እርምጃ ስትወስድ፣ በአምራች ዘርፉ ላይ ትልቅ ስራ ሰርታ ነበር። ኢትዮጵያ ግን አሁንም 80% የምትጠቀመውን ሸቀጥ ከውጭ ታስገባለች። ዶላር በነፃነት መዘዋወሩ ብቻውን ለውጥ አያመጣም፤ የምርት አብዮት ካልታከለበት፣ ነፃ ገበያው የውጭ ሀገራት ምርቶች መጣያ (Dumping ground) የመሆን አደጋ አለው።
11. የዋጋ ግሽበት (Inflation) የዚህ ሪፎርም ትልቁ ጠላት ነው። የምንዛሪ ዋጋው ለገበያ ሲተው፣ የብር ዋጋ መውደቁ አይቀሬ ነው። ይህ ደግሞ የመድኃኒት፣ የነዳጅ እና የፋብሪካ ጥሬ እቃዎች ዋጋን ሊያስንረው ይችላል። ኬይንስ እንደሚለው፣ በመካከለኛ ጊዜ ኢኮኖሚው ቢረጋጋም፣ “በመጨረሻ ሁላችንም እንሞታለን”። ስለዚህ ዝቅተኛው ማህበረሰብ በዚህ የሽግግር ወቅት በኑሮ ውድነት እንዳይቀጠቀጥ መንግስት የማህበራዊ ድጋፍ መረቦችን ማጠናከር አለበት።
12. 100 ዶላር የነበረው የሂሳብ መክፈቻ መቅረት (አንቀጽ 5)፣ ለድሃው ዜጋ የተሰጠ የኢኮኖሚ “ዲሞክራሲ” ነው። ይህም የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን (Financial Inclusion) በመጨመር፣ ህዝቡ በዶላር እንዲቆጥብና የሀገር ውስጥ ካፒታል እንዲያድግ ያደርጋል። ይህ የባህሪ ለውጥ (Behavioral Change) በረዥም ጊዜ የሀገሪቱን የቁጠባ ባህል ይቀይረዋል።
13. ድርጅቶች ከሀገር ውጭ መዋእለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ መፈቀዱ (አንቀጽ 6) ግን እጅግ አነጋጋሪ ነው። ኢትዮጵያ ራሷ የካፒታል እጥረት ባለባት ሁኔታ፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ዶላር ይዘው ወደ ውጭ እንዲወጡ መፈቀዱ በምን ስሌት እንደመጣ ግልጽ አይደለም። ይህ ነጥብ ባለሀብቶች ሀብታቸውን ወደ አስተማማኝ ሀገራት እንዲያሸሹ (Flight to Safety) በር ሊከፍት ይችላል።
1. የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ያደረገው የውጭ ምንዛሪ መመሪያ፣ ዝም ብሎ የቴክኒክ ሰነድ አይደለም፤ ይልቁንም ላለፉት 50 ዓመታት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ደም ስር አንቆ የያዘውን “የቁጥጥር ሰንሰለት” የሚበጣጥስ መጥረቢያ ነው። ይህ 19 ነጥቦችን የያዘው አዋጅ፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ አድርጋው የማታውቀውን የኢኮኖሚ “ቢግ ባንግ” (Big Bang) ሽግግር መጀመሯን ያበስራል። በኢኮኖሚ ፈላስፎች መነጽር ሲታይ፣ ይህ እርምጃ አዳም ስሚዝ “የማይታየው እጅ” (Invisible Hand) ብሎ የጠራውን ገበያ መር ስርዓት በኢትዮጵያ ምድር ለመትከል የተደረገ ደፋር ሙከራ ነው።
2. የዚህ ሪፎርም ዋነኛው መነሻ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር የተደረሰው የ 3.4 ቢሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት ቢሆንም፣ ውስጣዊ ፍላጎቱ ግን የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ረሃብ በዘላቂነት መፍታት ነው። ቀደም ሲል በኦፊሴላዊው የምንዛሪ ዋጋ እና በጥቁር ገበያው መካከል የነበረው ልዩነት (Premium) ከ 100% በላይ ማደጉ፣ ምርት ወደ ውጭ የሚላክበትን ሳይሆን ዶላር የሚሸሸግበትን ኢኮኖሚ ፈጥሮ ነበር። አዲሱ መመሪያ ይህንን “የጥላ ኢኮኖሚ” አፍርሶ፣ ዶላርን ከጓዳ ወደ ባንክ አደባባይ ለማውጣት የታለመ ነው።
3. የአገልግሎት ላኪዎች 100% ገቢያቸውን እንዲይዙ መፈቀዱ (አንቀጽ 1)፣ ከቲዮሪ አንጻር “የባለቤትነት መብት” (Property Rights) ማረጋገጫ ነው። ጆን ሎክ እንደሚለው፣ አንድ ሰው በጥረቱ ያገኘውን ሀብት የመጠቀም ሙሉ መብት ሊኖረው ይገባል። መንግስት ቀደም ሲል ከላኪዎች ላይ ይነጥቅ የነበረውን 50% እና ከዚያ በላይ ድርሻ መተዉ፣ ላኪዎች ይበልጥ እንዲያመርቱ ትልቅ ማበረታቻ (Incentive) ይፈጥራል። ይህ ደግሞ በረዥም ጊዜ የሀገሪቱን የወጪ ንግድ ገቢ በቢሊዮን ዶላሮች እንደሚያሳድገው ይጠበቃል።
4. ግለሰቦች ለቤተሰቦቻቸው እስከ 3,000 ዶላር እንዲልኩ መፈቀዱ (አንቀጽ 8)፣ የመንግስትን የቁጥጥር ስፋት (State Scope) በእጅጉ ይቀንሳል። ይህ እርምጃ ሚልተን ፍሪድማን “Capitalism and Freedom” በሚለው መጽሐፉ የጠቀሰውን የግል ኢኮኖሚ ነፃነት የሚያንፀባርቅ ነው። ዜጎች በገዛ ገንዘባቸው የልጆቻቸውን ትምህርትና ህክምና እንዲከፍሉ መፈቀዱ፣ በህዝብና በመንግስት መካከል ለዘመናት ተሸርሽሮ የነበረውን ማህበራዊ ውል (Social Contract) መልሶ የማደስ አቅም አለው።
5. ዳታዎች እንደሚያሳዩት፣ ኢትዮጵያ በየአመቱ ከዳያስፖራ የምታገኘው ሬሚታንስ (Remittance) ከ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ቢሆንም፣ ከግማሽ በላይ የሚሆነው በህገ-ወጥ መንገድ ይዘዋወር ነበር። አዲሱ መመሪያ ዶላርን ያለ ሰነድ መመንዘር መፍቀዱ (አንቀጽ 7)፣ ይህን በጥቁር ገበያ የሚመላለሰውን ቢሊዮን ዶላር ወደ ህጋዊው ስርዓት የሚመልስ “መግነጢሳዊ ኃይል” ነው። ይህ የገንዘብ ፍሰት ወደ ባንኮች ሲገባ፣ ባንኮች ለኢንዱስትሪው የሚሰጡት የብድር አቅም (Liquidity) በእጥፍ ሊያድግ ይችላል።
6. የውጭ ኢንቨስተሮች ትርፋቸውን ያለ ገደብ እንዲያወጡ መፈቀዱ (አንቀጽ 16) ግን የሁለት ስለት ቢላዋ ነው። ለዴቪድ ሪካርዶ የንግድ ቲዮሪ ተከታዮች፣ ይህ እርምጃ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን (FDI) የሚስብ ማር ነው። ሆኖም፣ እንደ ጆሴፍ ስቲግሊዝ ያሉ ሊቃውንት “የካፒታል ሽሽት” (Capital Flight) ስጋትን ያነሳሉ። በሀገር ውስጥ የፖለቲካ አለመረጋጋት ቢከሰት፣ ኢንቨስተሮች ያላቸውን ዶላር ይዘው በአንድ ጀምበር ቢወጡ፣ የኢትዮጵያ የውጭ መጠባበቂያ ክምችት (Foreign Reserve) ድንገት ሊሟጠጥ ይችላል።
7. የባንኮች ራስ-ገዝነት (Autonomy) መጨመር ሌላው የዚህ ሪፎርም ምሰሶ ነው። ባንኮች የፎርዋርድ ግብይት (Forward Transaction) እንዲያካሂዱ መፈቀዱ (አንቀጽ 9)፣ ነጋዴዎች ለወደፊት ግዢዎቻቸው የምንዛሪ ዋጋን ቀድመው እንዲቆልፉ (Hedging) ይረዳቸዋል። ይህ በንግድ ዓለም ውስጥ ያለውን እርግጠኛ አለመሆን (Uncertainty) በመቀነስ፣ የዋጋ ግሽበትን ለማረጋጋት የሚረዳ ዘመናዊ የፋይናንስ መሳሪያ ነው።
8. ይሁን እንጂ፣ ባንኮች ከካፒታላቸው 10% ዋስትና እንዲሰጡ መፈቀዱ (አንቀጽ 14) ልብ አንጠልጣይ አደጋ አለው። የኢትዮጵያ ባንኮች በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ቀውስ የመመታት ልምድ የላቸውም። ባንኮች የገቡት ዋስትና ተቀባይነት አጥቶ ወይም ብድሩ ሳይከፈል ቢቀር፣ የሀገር ውስጥ ባንኮች መክሰር (Bank Failure) ደረጃ ሊደርሱ ይችላሉ። ይህ ደግሞ በዜጎች ቁጠባ ላይ ትልቅ አደጋ ስለሚደቅን፣ የብሔራዊ ባንክ የቁጥጥር ዓይን (Supervision) እጅግ ንቁ መሆን አለበት።
9. የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ጥሬ ገንዘብ የመያዝ አቅማቸው ወደ 25% ማደጉ (አንቀጽ 18)፣ የገበያውን የዶላር ዝውውር (Circulation) ያቀልጠዋል። ይህ እርምጃ የጥቁር ገበያ ደላሎችን ከስራ የሚያስወጣ ቢሆንም፣ አዲሶቹ የፍቃድ ባለቤቶች ራሳቸው ወደ “ህጋዊ ደላላነት” እንዳይቀየሩ ጥብቅ ኦዲት ይፈልጋል። የገንዘብ ማጠብ (Money Laundering) ወንጀሎችን ለመከላከል የዲጂታል ክትትል ስርዓት የግድ ይላል።
10. የቬትናምን ተሞክሮ ብንመለከት፣ ሀገሪቱ በ 1980 ዎቹ መጨረሻ መሰል እርምጃ ስትወስድ፣ በአምራች ዘርፉ ላይ ትልቅ ስራ ሰርታ ነበር። ኢትዮጵያ ግን አሁንም 80% የምትጠቀመውን ሸቀጥ ከውጭ ታስገባለች። ዶላር በነፃነት መዘዋወሩ ብቻውን ለውጥ አያመጣም፤ የምርት አብዮት ካልታከለበት፣ ነፃ ገበያው የውጭ ሀገራት ምርቶች መጣያ (Dumping ground) የመሆን አደጋ አለው።
11. የዋጋ ግሽበት (Inflation) የዚህ ሪፎርም ትልቁ ጠላት ነው። የምንዛሪ ዋጋው ለገበያ ሲተው፣ የብር ዋጋ መውደቁ አይቀሬ ነው። ይህ ደግሞ የመድኃኒት፣ የነዳጅ እና የፋብሪካ ጥሬ እቃዎች ዋጋን ሊያስንረው ይችላል። ኬይንስ እንደሚለው፣ በመካከለኛ ጊዜ ኢኮኖሚው ቢረጋጋም፣ “በመጨረሻ ሁላችንም እንሞታለን”። ስለዚህ ዝቅተኛው ማህበረሰብ በዚህ የሽግግር ወቅት በኑሮ ውድነት እንዳይቀጠቀጥ መንግስት የማህበራዊ ድጋፍ መረቦችን ማጠናከር አለበት።
12. 100 ዶላር የነበረው የሂሳብ መክፈቻ መቅረት (አንቀጽ 5)፣ ለድሃው ዜጋ የተሰጠ የኢኮኖሚ “ዲሞክራሲ” ነው። ይህም የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን (Financial Inclusion) በመጨመር፣ ህዝቡ በዶላር እንዲቆጥብና የሀገር ውስጥ ካፒታል እንዲያድግ ያደርጋል። ይህ የባህሪ ለውጥ (Behavioral Change) በረዥም ጊዜ የሀገሪቱን የቁጠባ ባህል ይቀይረዋል።
13. ድርጅቶች ከሀገር ውጭ መዋእለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ መፈቀዱ (አንቀጽ 6) ግን እጅግ አነጋጋሪ ነው። ኢትዮጵያ ራሷ የካፒታል እጥረት ባለባት ሁኔታ፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ዶላር ይዘው ወደ ውጭ እንዲወጡ መፈቀዱ በምን ስሌት እንደመጣ ግልጽ አይደለም። ይህ ነጥብ ባለሀብቶች ሀብታቸውን ወደ አስተማማኝ ሀገራት እንዲያሸሹ (Flight to Safety) በር ሊከፍት ይችላል።
Sponsored by
Surafel
4 months ago
በውጭ ምንዛሪ መመሪያዎች ላይ ማሻሻያ ተደረገ‼️
የተሰጠው መግለጫ ከስር ቀርቧል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሟላ የማክሮኢኮኖሚ ሪፎርም መደረግ ከጀመረበት ሀምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ፤ የውጭ ምንዛሪ ገበያን ለማጎልበት የሚያስችሉ የተለያዩ የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያዎችን ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በአሁኑ ወቅትም የውጭ ምንዛሪ ገበያን የበለጠ ለማጎልበት በማሰብ በውጭ ምንዛሪ መመሪያ ላይ የሚከተሉትን ማሻሻያዎች ማድረጉን ያሳውቃል፡፡
1. የአገልግሎት ላኪዎች ከወጪ ንግድ የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሪ ሙሉ በሙሉ በሪቴንሽን ሂሳባቸው ያለ ምንም የጊዜ ገደብ እንዲይዙ ተፈቅዷል፡፡
2. ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ ላላቸው ደንበኞቻቸው ለውጭ ሀገር ክፍያ የኤሌክትሮኒክ ግብይትን ጨምሮ የሚያገለግል ዓለምአቀፍ ካርድ ማዘጋጀት እንዲችሉ ተፈቅዷል፡፡
3. ማንኛውም የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ ያለው የባንክ ደንበኛ ሕጋዊ ስነዱን ሂሳብ ለከፈተበት ባንክበማቅረብ፤ የውጭ ምንዛሪ ሂሳቡን በመጠቀም ለትዳር አጋሩና ለልጆቹ የትምህርት፤የህክምናና የጉዞ ወጪ ክፍያ ማድረግ ይችላል፡፡
4. ማንኛውም ለትርፍ የተቋቋመ ድርጅት የውጭ ምንዛሪ ምንጩ ከወጪ ንግድ የሚገኝን የውጭምንዛሪ ሳይጨምር በእርዳታ/ስጦታ አለያም ከሌላ የውጭ ምንዛሪ ምንጭ የተገኘ መሆኑ ከተረጋገጠ የተንቀሳቃሽ፣ የቁጠባና የጊዜ ገደብ የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ መክፈት ይችላል፡፡
5. ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ቀደም ሲል የውጭ ምንዛሪ የቁጠባ ሂሳብ ለመክፈት ይጠየቁት የነበረው አነስተኛ 100 የአሜሪካ ዶላር እንዲቀር ተደርጓል፡፡
6. ድርጅቶች የመዋእለ ነዋያቸውን ሁኔታ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እያስመረመሩ ከሀገር ውጭበሌላ ሀገር መዋእለ ነዋያቸውን ፈሰስ ማድረግ እንዲችሉ ተፈቅዷል፡፡
7. ማንኛውም ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ የሆነ ግለሰብ ወደ ሀገር ይዞት የተመለሰውን የትኛውንም ያህል መጠን ያለው የውጭ ምንዛሪ ያለ ጉምሩክ ሰነድ በባንኮችና ሕጋዊ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ቢሮዎች በኩል ወደ ብር መመንዘር አለያም ወደ የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ በማስገባት ተቀማጭማድረግ ይችላል፡፡
8. ኢትዮጵያውያን ሕጋዊ ሰነድ ለባኮች በማቅረብ መጠኑ ከ3,000 የአሜሪካ ዶላር ያልበለጠ የውጭምንዛሪ ከሀገር ውጭ ለሚኖሩ ዘመዶቻቸው እገዛ እንዲውል ከሀገር ወደ ውጭ ማስተላለፍ የሚችሉበት ሥርዓት ተፈቅዷል፡፡
9. ባንኮች የፎርዋርድ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ያለ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማረጋገጫ ማካሄድ እንዲችሉ ተፈቅዷል፡፡
10. የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስተሮች፣ ኤምባሲዎችና በሀገር ውስጥ የሚሰሩ ዓለምአቀፍ ተቋማት የተራድኦ ድርጅቶችን ጨምሮ ያለ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማረጋገጫ በባንኮች የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ መክፈት ይችላሉ፡፡
11. ድርጅቶች ወደ ሀገር ውስጥ የሚያመጡት የውጭ ብድር (በገንዘብና በዓይነት) እና የስፕላዬርብድርን የማጽደቅ ሥራ የውጭ ምንዛሪ መመሪያ መስፈርቶችን በተከተለ መልኩ ሙሉ በሙሉ በባንኮች እንዲከናወን ተፈቅዷል፡፡
12. ማንኛውም በወጪ ንግድ ላይ የተሰማራ ላኪ ድርጅት ከማንኛውም የውጭ አካል የቅድመ ክፍያ ስምምነት ላይ በመድረስ እና በሁለቱ ወገኖች የተደረሰውን የስምምነት ሰነድ ለላኪው ድርጅት ደንበኛ ባንክ በማቅረብ የቅድመ ክፍያ ማከናወን ይችላል፡፡
13. በተጨማሪም የውጭ ምንዛሪ ገቢ ለወደፊት የወጪ ንግድ ክፍያ እንደ ቅድመ ክፍያ የሚቆጠረው (ሀ) ስምምነቱ ገዥውን ለማመላከት ታስቦ “ቅድመ ክፍያው ለወደፊት ወጪ ወይም ገቢ ንግድ የሚውል" ወይ (ለ) ወደፊት ወደ ውጭ የሚላኩ ሸቀጦችን ከዘረዘረ ወይም የደረሰኝ ቁጥሩ ከተጠቀሰ አለያም የግብይት የውል ስምምነት ሰነድ ቁጥር በሚላከው የውጭ ምንዛሪ ደረሰኝ ላይ ከተጠቀሰ ይሆናል፡፡
14. ባንኮች ከካፒታላቸው ከ10 በመቶ ያልበለጠ ለግሉ ዘርፍ የውጭ ሀገር ብድር ዋስትና መስጠት እንዲችሉ ተፈቅዷል፡፡
15. ባንኮች የውጭ ተቋም በሚሰጠው የማረጋገጫ ደብዳቤ እና ደንበኛው በሚያቀርበው ጥያቄ ላይበመመርኮዝ በአንድ ጉዳይ ከ20,000 የአሜሪካ ዶላር ወይም ከተመጣጣኝ የሌላ ሀገር ገንዘብ ያልበለጠ የውጭ ምንዛሪ ለህክምናና ለትምህርት ያለ ቪዛ እና የአውሮፕላን ትኬት ቅድመ ክፍያ ማከናወን ይችላሉ፡፡
16. ያለምንም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማረጋገጫ የውጭ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ መመሪያ መሰረት አስፈላጊውን ሰነድ ለባንካቸው በማቅረብ እንዲሁም ባንኮች በመመሪያው መሰረት የቀረበው ሰነድ መሟላቱን በማረጋገጥ በትርፍ ክፍፍል መልክያገኙትን የውጭ ምንዛሪ ከሀገር ማስወጣት እንዲችሉ ተፈቅዷል፡፡
17. የውጭ ምንዛሪ ግብይት ቢሮዎችን የገንዘብ ፍሰትና ካፒታል የበለጠ ለማጎልበት በማሰብ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በፈቃድ አሰጣጥ ወቅት የሚይዘውን ተቀማጭ ገንዘብ፤ (አንድ ዓመት እና ከዚያ በላይ በሥራ ላይ ለሆኑ ቢሮዎች 30 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ቢያንስ ለስድስት ወራት በሥራ ላይ ላሉ ቢሮዎች 15 ሚሊዮን ብር) ተመላሽ ያደርጋል፡፡
18. የውጭ ምንዛሪ ግብይት ቢሮዎች በእጃቸው የሚይዙት ጥሬ የውጭ ምንዛሪ ገንዘብ ቀደም ሲል ከነበረው የካፒታላቸው 10 በመቶ ወደ 25 በመቶ ተሻሽሏል፡፡ ከዚህ በላይ የሆነ ትርፍ የውጭምንዛሪ ገንዘብ ለባንኮች መሸጥ አለበት፡፡
19. ሁሉም የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች አስፈላጊውን ሰነድ በመጠየቅ ለቪዛ፣ ለጋስፖርትና ለፈቃድ እድሳት ጥሬ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ እንዲያከናውኑ ተፈቅዷል፡፡
Via National Bank of Ethiopia
seledadotio
seledadotio
የተሰጠው መግለጫ ከስር ቀርቧል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሟላ የማክሮኢኮኖሚ ሪፎርም መደረግ ከጀመረበት ሀምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ፤ የውጭ ምንዛሪ ገበያን ለማጎልበት የሚያስችሉ የተለያዩ የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያዎችን ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በአሁኑ ወቅትም የውጭ ምንዛሪ ገበያን የበለጠ ለማጎልበት በማሰብ በውጭ ምንዛሪ መመሪያ ላይ የሚከተሉትን ማሻሻያዎች ማድረጉን ያሳውቃል፡፡
1. የአገልግሎት ላኪዎች ከወጪ ንግድ የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሪ ሙሉ በሙሉ በሪቴንሽን ሂሳባቸው ያለ ምንም የጊዜ ገደብ እንዲይዙ ተፈቅዷል፡፡
2. ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ ላላቸው ደንበኞቻቸው ለውጭ ሀገር ክፍያ የኤሌክትሮኒክ ግብይትን ጨምሮ የሚያገለግል ዓለምአቀፍ ካርድ ማዘጋጀት እንዲችሉ ተፈቅዷል፡፡
3. ማንኛውም የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ ያለው የባንክ ደንበኛ ሕጋዊ ስነዱን ሂሳብ ለከፈተበት ባንክበማቅረብ፤ የውጭ ምንዛሪ ሂሳቡን በመጠቀም ለትዳር አጋሩና ለልጆቹ የትምህርት፤የህክምናና የጉዞ ወጪ ክፍያ ማድረግ ይችላል፡፡
4. ማንኛውም ለትርፍ የተቋቋመ ድርጅት የውጭ ምንዛሪ ምንጩ ከወጪ ንግድ የሚገኝን የውጭምንዛሪ ሳይጨምር በእርዳታ/ስጦታ አለያም ከሌላ የውጭ ምንዛሪ ምንጭ የተገኘ መሆኑ ከተረጋገጠ የተንቀሳቃሽ፣ የቁጠባና የጊዜ ገደብ የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ መክፈት ይችላል፡፡
5. ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ቀደም ሲል የውጭ ምንዛሪ የቁጠባ ሂሳብ ለመክፈት ይጠየቁት የነበረው አነስተኛ 100 የአሜሪካ ዶላር እንዲቀር ተደርጓል፡፡
6. ድርጅቶች የመዋእለ ነዋያቸውን ሁኔታ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እያስመረመሩ ከሀገር ውጭበሌላ ሀገር መዋእለ ነዋያቸውን ፈሰስ ማድረግ እንዲችሉ ተፈቅዷል፡፡
7. ማንኛውም ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ የሆነ ግለሰብ ወደ ሀገር ይዞት የተመለሰውን የትኛውንም ያህል መጠን ያለው የውጭ ምንዛሪ ያለ ጉምሩክ ሰነድ በባንኮችና ሕጋዊ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ቢሮዎች በኩል ወደ ብር መመንዘር አለያም ወደ የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ በማስገባት ተቀማጭማድረግ ይችላል፡፡
8. ኢትዮጵያውያን ሕጋዊ ሰነድ ለባኮች በማቅረብ መጠኑ ከ3,000 የአሜሪካ ዶላር ያልበለጠ የውጭምንዛሪ ከሀገር ውጭ ለሚኖሩ ዘመዶቻቸው እገዛ እንዲውል ከሀገር ወደ ውጭ ማስተላለፍ የሚችሉበት ሥርዓት ተፈቅዷል፡፡
9. ባንኮች የፎርዋርድ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ያለ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማረጋገጫ ማካሄድ እንዲችሉ ተፈቅዷል፡፡
10. የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስተሮች፣ ኤምባሲዎችና በሀገር ውስጥ የሚሰሩ ዓለምአቀፍ ተቋማት የተራድኦ ድርጅቶችን ጨምሮ ያለ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማረጋገጫ በባንኮች የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ መክፈት ይችላሉ፡፡
11. ድርጅቶች ወደ ሀገር ውስጥ የሚያመጡት የውጭ ብድር (በገንዘብና በዓይነት) እና የስፕላዬርብድርን የማጽደቅ ሥራ የውጭ ምንዛሪ መመሪያ መስፈርቶችን በተከተለ መልኩ ሙሉ በሙሉ በባንኮች እንዲከናወን ተፈቅዷል፡፡
12. ማንኛውም በወጪ ንግድ ላይ የተሰማራ ላኪ ድርጅት ከማንኛውም የውጭ አካል የቅድመ ክፍያ ስምምነት ላይ በመድረስ እና በሁለቱ ወገኖች የተደረሰውን የስምምነት ሰነድ ለላኪው ድርጅት ደንበኛ ባንክ በማቅረብ የቅድመ ክፍያ ማከናወን ይችላል፡፡
13. በተጨማሪም የውጭ ምንዛሪ ገቢ ለወደፊት የወጪ ንግድ ክፍያ እንደ ቅድመ ክፍያ የሚቆጠረው (ሀ) ስምምነቱ ገዥውን ለማመላከት ታስቦ “ቅድመ ክፍያው ለወደፊት ወጪ ወይም ገቢ ንግድ የሚውል" ወይ (ለ) ወደፊት ወደ ውጭ የሚላኩ ሸቀጦችን ከዘረዘረ ወይም የደረሰኝ ቁጥሩ ከተጠቀሰ አለያም የግብይት የውል ስምምነት ሰነድ ቁጥር በሚላከው የውጭ ምንዛሪ ደረሰኝ ላይ ከተጠቀሰ ይሆናል፡፡
14. ባንኮች ከካፒታላቸው ከ10 በመቶ ያልበለጠ ለግሉ ዘርፍ የውጭ ሀገር ብድር ዋስትና መስጠት እንዲችሉ ተፈቅዷል፡፡
15. ባንኮች የውጭ ተቋም በሚሰጠው የማረጋገጫ ደብዳቤ እና ደንበኛው በሚያቀርበው ጥያቄ ላይበመመርኮዝ በአንድ ጉዳይ ከ20,000 የአሜሪካ ዶላር ወይም ከተመጣጣኝ የሌላ ሀገር ገንዘብ ያልበለጠ የውጭ ምንዛሪ ለህክምናና ለትምህርት ያለ ቪዛ እና የአውሮፕላን ትኬት ቅድመ ክፍያ ማከናወን ይችላሉ፡፡
16. ያለምንም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማረጋገጫ የውጭ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ መመሪያ መሰረት አስፈላጊውን ሰነድ ለባንካቸው በማቅረብ እንዲሁም ባንኮች በመመሪያው መሰረት የቀረበው ሰነድ መሟላቱን በማረጋገጥ በትርፍ ክፍፍል መልክያገኙትን የውጭ ምንዛሪ ከሀገር ማስወጣት እንዲችሉ ተፈቅዷል፡፡
17. የውጭ ምንዛሪ ግብይት ቢሮዎችን የገንዘብ ፍሰትና ካፒታል የበለጠ ለማጎልበት በማሰብ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በፈቃድ አሰጣጥ ወቅት የሚይዘውን ተቀማጭ ገንዘብ፤ (አንድ ዓመት እና ከዚያ በላይ በሥራ ላይ ለሆኑ ቢሮዎች 30 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ቢያንስ ለስድስት ወራት በሥራ ላይ ላሉ ቢሮዎች 15 ሚሊዮን ብር) ተመላሽ ያደርጋል፡፡
18. የውጭ ምንዛሪ ግብይት ቢሮዎች በእጃቸው የሚይዙት ጥሬ የውጭ ምንዛሪ ገንዘብ ቀደም ሲል ከነበረው የካፒታላቸው 10 በመቶ ወደ 25 በመቶ ተሻሽሏል፡፡ ከዚህ በላይ የሆነ ትርፍ የውጭምንዛሪ ገንዘብ ለባንኮች መሸጥ አለበት፡፡
19. ሁሉም የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች አስፈላጊውን ሰነድ በመጠየቅ ለቪዛ፣ ለጋስፖርትና ለፈቃድ እድሳት ጥሬ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ እንዲያከናውኑ ተፈቅዷል፡፡
Via National Bank of Ethiopia
seledadotio
seledadotio
4 months ago
🚀 የደቡብ አፍሪካው የፋይናንስ ግዙፍ "አብሳ" ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት አይኑን ጥሏል!
— በ78 ቢሊዮን ዶላር ሀብቱ የሚታወቀው አብሳ፣ የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለመቀላቀል የመንግሥትን "አረንጓዴ መብራት" እየጠበቀ ነው —
በአፍሪካ ካሉ ግዙፍ ባንኮች አንዱ የሆነው አብሳ ግሩፕ (Absa Group)፣ በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ውስጥ በባለቤትነት ለመሳተፍ ያለውን ዝግጁነት በድጋሚ አረጋገጠ። ባንኩ በቅርቡ የወጣውን የውጭ ባንኮች መግቢያ መመሪያ ቢያደንቅም፣ ይበልጥ "ተለዋዋጭ" የሆኑ ተጨማሪ ማሻሻያዎች እንዲደረጉ ይፈልጋል።
📊 አብሳ ግሩፕ በቁጥር፦ ለምን ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ ትልቅ ዜና ሆነ?
አብሳ ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባቱ የፋይናንስ ዘርፉን ሊያነቃቃ ይችላል ተብሎ የሚጠበቀው በሚከተሉት ምክንያቶች ነው፦
ግዙፍ የሀብት አቅም፦ በአሁኑ ወቅት የባንኩ ጠቅላላ የሀብት መጠን (Total Assets) ከ 1.5 ትሪሊዮን የደቡብ አፍሪካ ራንድ (በግምት 78 ቢሊዮን ዶላር) በላይ ነው።
አህጉራዊ ተደራሽነት፦ በ12 የአፍሪካ አገራት (ኬንያ፣ ጋና፣ ቦትስዋና፣ ሞሪሸስ...) ከ 12 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች አሉት።
የቴክኖሎጂ አቅም፦ ባንኩ በዲጂታል ባንኪንግ እና በኢንቨስትመንት ዘርፍ በአፍሪካ ቀዳሚ ከሚባሉት አንዱ ነው።
🔍 የአብሳ የኢትዮጵያ "ስትራቴጂ" ምንድነው?
እንደ ዘ ኢስት አፍሪካን ዘገባ፣ አብሳ ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት የሚከተሉትን ስልቶች ይከተላል ተብሎ ይጠበቃል፦
የባንክ ድርሻ መግዛት (Acquisition)፦ ባንኩ አዲስ ቅርንጫፍ ከመክፈት ይልቅ፣ አትራፊ የሆኑ የኢትዮጵያ የግል ባንኮችን ድርሻ (Share) በመግዛት በሽርክና መስራት ይመርጣል።
የድርጅቶች ባንኪንግ (Corporate Banking)፦ ባንኩ በዋናነት ትኩረት የሚያደርገው ግዙፍ ፕሮጀክቶች፣ ማኑፋክቸሪንግ እና የንግድ ፋይናንስ ላይ ነው።
የፖሊሲ ማሻሻያ ጥያቄ፦ ባንኩ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር እና የትርፍ አወጣጥ (Profit Repatriation) ላይ መንግስት ተጨማሪ ማሻሻያዎችን እንዲያደርግ ፍላጎት አለው።
⚔️ የውጭ ባንኮች "ፉክክር" በኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ባንኮች እስከ 40% ድረስ በሀገር ውስጥ ባንኮች ላይ ድርሻ እንዲኖራቸው መፍቀዱን ተከትሎ፣ አብሳ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ደጅ እየጠኑ ነው፦
🇰🇪 KCB እና Equity Bank (ኬንያ)፦ አስቀድመው ቢሮ በመክፈት ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል።
🇪🇬 Standard Chartered እና EFG Hermes፦ ገበያውን ለማጥናት ከፍተኛ ፍላጎት አሳይተዋል።
🇿🇦 Standard Bank፦ የአብሳ ዋነኛ ተፎካካሪ ሲሆን፣ እሱም ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት እንቅስቃሴ ጀምሯል።
💡 ለኢትዮጵያውያን ምን ትርጉም አለው?
👉አብሳን የመሰሉ ግዙፍ ባንኮች መግባት፦
ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የብድር አቅርቦት ይጨምራል።
👉የአገልግሎት ጥራት እና የዲጂታል ክፍያ ስርአትን ያዘምናል።
👉የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰትን (FDI) ያሳድጋል።
— በ78 ቢሊዮን ዶላር ሀብቱ የሚታወቀው አብሳ፣ የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለመቀላቀል የመንግሥትን "አረንጓዴ መብራት" እየጠበቀ ነው —
በአፍሪካ ካሉ ግዙፍ ባንኮች አንዱ የሆነው አብሳ ግሩፕ (Absa Group)፣ በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ውስጥ በባለቤትነት ለመሳተፍ ያለውን ዝግጁነት በድጋሚ አረጋገጠ። ባንኩ በቅርቡ የወጣውን የውጭ ባንኮች መግቢያ መመሪያ ቢያደንቅም፣ ይበልጥ "ተለዋዋጭ" የሆኑ ተጨማሪ ማሻሻያዎች እንዲደረጉ ይፈልጋል።
📊 አብሳ ግሩፕ በቁጥር፦ ለምን ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ ትልቅ ዜና ሆነ?
አብሳ ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባቱ የፋይናንስ ዘርፉን ሊያነቃቃ ይችላል ተብሎ የሚጠበቀው በሚከተሉት ምክንያቶች ነው፦
ግዙፍ የሀብት አቅም፦ በአሁኑ ወቅት የባንኩ ጠቅላላ የሀብት መጠን (Total Assets) ከ 1.5 ትሪሊዮን የደቡብ አፍሪካ ራንድ (በግምት 78 ቢሊዮን ዶላር) በላይ ነው።
አህጉራዊ ተደራሽነት፦ በ12 የአፍሪካ አገራት (ኬንያ፣ ጋና፣ ቦትስዋና፣ ሞሪሸስ...) ከ 12 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች አሉት።
የቴክኖሎጂ አቅም፦ ባንኩ በዲጂታል ባንኪንግ እና በኢንቨስትመንት ዘርፍ በአፍሪካ ቀዳሚ ከሚባሉት አንዱ ነው።
🔍 የአብሳ የኢትዮጵያ "ስትራቴጂ" ምንድነው?
እንደ ዘ ኢስት አፍሪካን ዘገባ፣ አብሳ ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት የሚከተሉትን ስልቶች ይከተላል ተብሎ ይጠበቃል፦
የባንክ ድርሻ መግዛት (Acquisition)፦ ባንኩ አዲስ ቅርንጫፍ ከመክፈት ይልቅ፣ አትራፊ የሆኑ የኢትዮጵያ የግል ባንኮችን ድርሻ (Share) በመግዛት በሽርክና መስራት ይመርጣል።
የድርጅቶች ባንኪንግ (Corporate Banking)፦ ባንኩ በዋናነት ትኩረት የሚያደርገው ግዙፍ ፕሮጀክቶች፣ ማኑፋክቸሪንግ እና የንግድ ፋይናንስ ላይ ነው።
የፖሊሲ ማሻሻያ ጥያቄ፦ ባንኩ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር እና የትርፍ አወጣጥ (Profit Repatriation) ላይ መንግስት ተጨማሪ ማሻሻያዎችን እንዲያደርግ ፍላጎት አለው።
⚔️ የውጭ ባንኮች "ፉክክር" በኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ባንኮች እስከ 40% ድረስ በሀገር ውስጥ ባንኮች ላይ ድርሻ እንዲኖራቸው መፍቀዱን ተከትሎ፣ አብሳ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ደጅ እየጠኑ ነው፦
🇰🇪 KCB እና Equity Bank (ኬንያ)፦ አስቀድመው ቢሮ በመክፈት ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል።
🇪🇬 Standard Chartered እና EFG Hermes፦ ገበያውን ለማጥናት ከፍተኛ ፍላጎት አሳይተዋል።
🇿🇦 Standard Bank፦ የአብሳ ዋነኛ ተፎካካሪ ሲሆን፣ እሱም ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት እንቅስቃሴ ጀምሯል።
💡 ለኢትዮጵያውያን ምን ትርጉም አለው?
👉አብሳን የመሰሉ ግዙፍ ባንኮች መግባት፦
ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የብድር አቅርቦት ይጨምራል።
👉የአገልግሎት ጥራት እና የዲጂታል ክፍያ ስርአትን ያዘምናል።
👉የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰትን (FDI) ያሳድጋል።
4 months ago
⚖️ የኢትዮጵያ የዩሮቦንድ እዳ ክርክር ወደ ለንደን ፍርድ ቤት ሊያመራ ነው፡ ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ምን አንድምታ አለው?
ኢትዮጵያ ያለባትን የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ እዳ ለማሻሻል ከግል አበዳሪዎች ጋር ስታደርግ የነበረው ድርድር ባለመሳካቱ፣ ጉዳዩ ወደ ለንደን ፍርድ ቤት ሊያመራ መሆኑ ተሰምቷል።
ይህ ክርክር አገሪቱ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የብድር ሽግሽግ ሂደት ሊያጓትት ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
ዋናው የክርክር ነጥብ ምንድነው?
የኢትዮጵያ መንግሥት እና የግል አበዳሪዎች በጥር ወር መጀመሪያ ላይ የ15% ቅናሽ (Haircut) የሚያካትት ስምምነት ላይ ደርሰው የነበረ ቢሆንም፣ የፓሪስ ክለብን ጨምሮ የመንግሥት አበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) ስምምነቱን ውድቅ አድርጎታል።
ምክንያቱ፦ "የአበዳሪዎች እኩልነት" (Comparability of Treatment) የሚባለውን መርህ ይጥሳል። የመንግሥት አበዳሪዎች እንደሚሉት፣ የቀረበው ስምምነት ለግል አበዳሪዎች ከእነሱ በበለጠ የተሻለ ጥቅም ይሰጣል።
የቦንድ ባለቤቶች ምላሽ፦ የግል አበዳሪዎቹ በበኩላቸው "መንግሥት በቅን ልቦና አልተደራደረም" በሚል ጉዳዩን ወደ ለንደን ፍርድ ቤት እንደሚወስዱት አስታውቀዋል።
📊 የኢትዮጵያ እዳ በቁጥር (እስከ ሰኔ 2024 የነበረው መረጃ)
የኢትዮጵያ አጠቃላይ የውጭ እዳ 28.9 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን፣ ስብጥሩም የሚከተለው ነው፦
ባለብዙ ወገን አበዳሪዎች (World Bank, IMF ወዘተ)፦ 52%
የመንግሥት የሁለትዮሽ አበዳሪዎች (ቻይና፣ ፈረንሳይ ወዘተ)፦ 28%
የግል አበዳሪዎች (ዩሮቦንድን ጨምሮ)፦ 20%
የሌሎች አገራት ተሞክሮ፡ ዛምቢያ እና ስሪላንካ
ኢትዮጵያ አሁን የገጠማት ፈተና ከዚህ ቀደም ሌሎች አገራት ካለፉበት ሂደት ጋር ይመሳሰላል፦
የዛምቢያ ተሞክሮ ፦ ዛምቢያ እዳዋን ለማሽጋሸግ ለሦስት ዓመታት ያህል ስትታገል ቆይታለች። ልክ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ፣ በግል አበዳሪዎች እና በመንግሥት አበዳሪዎች (በተለይ ቻይና) መካከል በነበረው "እኩልነት" ክርክር ምክንያት ሂደቱ ተጓትቶ ነበር። ዛምቢያ ስምምነት ላይ የደረሰችው የግል አበዳሪዎች የአገሪቱ ኢኮኖሚ ሲያድግ ተጨማሪ ክፍያ የሚያገኙበትን (Value Recovery Instrument) መካኒዝም ካካተቱ በኋላ ነው።
የስሪላንካ ተሞክሮ ፦ ስሪላንካ በG20 የጋራ ማዕቀፍ (Common Framework) ውስጥ ባለመሆኗ በራሷ ድርድር ስታደርግ ቆይታለች። ይሁን እንጂ የግል አበዳሪዎች በፍርድ ቤት ክስ መመስረታቸው አገሪቱ ከአይ ኤም ኤፍ (IMF) የምታገኘው የገንዘብ ድጋፍ እንዲዘገይ አድርጎባታል።
⚠️ ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎች
የIMF ድጋፍ መጓተት፦ በፍርድ ቤት የሚደረግ ረጅም ክርክር አይ ኤም ኤፍ ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ (EFF) ቀጣይ ምዕራፎች ሊያስተጓጉል ይችላል።
የገበያ መገለል፦ ክርክሩ እስካልተፈታ ድረስ ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ገበያ ተመልሳ ተጨማሪ ብድር ለማግኘት ትቸገራለች።
የበጀት ጫና፦ ለትምህርት፣ ለጤና እና ለልማት መዋል ያለበት የውጭ ምንዛሬ ለእዳ ክፍያ እንዲውል ጫና ሊፈጥር ይችላል።
ኢትዮጵያ ያለባትን የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ እዳ ለማሻሻል ከግል አበዳሪዎች ጋር ስታደርግ የነበረው ድርድር ባለመሳካቱ፣ ጉዳዩ ወደ ለንደን ፍርድ ቤት ሊያመራ መሆኑ ተሰምቷል።
ይህ ክርክር አገሪቱ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የብድር ሽግሽግ ሂደት ሊያጓትት ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
ዋናው የክርክር ነጥብ ምንድነው?
የኢትዮጵያ መንግሥት እና የግል አበዳሪዎች በጥር ወር መጀመሪያ ላይ የ15% ቅናሽ (Haircut) የሚያካትት ስምምነት ላይ ደርሰው የነበረ ቢሆንም፣ የፓሪስ ክለብን ጨምሮ የመንግሥት አበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) ስምምነቱን ውድቅ አድርጎታል።
ምክንያቱ፦ "የአበዳሪዎች እኩልነት" (Comparability of Treatment) የሚባለውን መርህ ይጥሳል። የመንግሥት አበዳሪዎች እንደሚሉት፣ የቀረበው ስምምነት ለግል አበዳሪዎች ከእነሱ በበለጠ የተሻለ ጥቅም ይሰጣል።
የቦንድ ባለቤቶች ምላሽ፦ የግል አበዳሪዎቹ በበኩላቸው "መንግሥት በቅን ልቦና አልተደራደረም" በሚል ጉዳዩን ወደ ለንደን ፍርድ ቤት እንደሚወስዱት አስታውቀዋል።
📊 የኢትዮጵያ እዳ በቁጥር (እስከ ሰኔ 2024 የነበረው መረጃ)
የኢትዮጵያ አጠቃላይ የውጭ እዳ 28.9 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን፣ ስብጥሩም የሚከተለው ነው፦
ባለብዙ ወገን አበዳሪዎች (World Bank, IMF ወዘተ)፦ 52%
የመንግሥት የሁለትዮሽ አበዳሪዎች (ቻይና፣ ፈረንሳይ ወዘተ)፦ 28%
የግል አበዳሪዎች (ዩሮቦንድን ጨምሮ)፦ 20%
የሌሎች አገራት ተሞክሮ፡ ዛምቢያ እና ስሪላንካ
ኢትዮጵያ አሁን የገጠማት ፈተና ከዚህ ቀደም ሌሎች አገራት ካለፉበት ሂደት ጋር ይመሳሰላል፦
የዛምቢያ ተሞክሮ ፦ ዛምቢያ እዳዋን ለማሽጋሸግ ለሦስት ዓመታት ያህል ስትታገል ቆይታለች። ልክ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ፣ በግል አበዳሪዎች እና በመንግሥት አበዳሪዎች (በተለይ ቻይና) መካከል በነበረው "እኩልነት" ክርክር ምክንያት ሂደቱ ተጓትቶ ነበር። ዛምቢያ ስምምነት ላይ የደረሰችው የግል አበዳሪዎች የአገሪቱ ኢኮኖሚ ሲያድግ ተጨማሪ ክፍያ የሚያገኙበትን (Value Recovery Instrument) መካኒዝም ካካተቱ በኋላ ነው።
የስሪላንካ ተሞክሮ ፦ ስሪላንካ በG20 የጋራ ማዕቀፍ (Common Framework) ውስጥ ባለመሆኗ በራሷ ድርድር ስታደርግ ቆይታለች። ይሁን እንጂ የግል አበዳሪዎች በፍርድ ቤት ክስ መመስረታቸው አገሪቱ ከአይ ኤም ኤፍ (IMF) የምታገኘው የገንዘብ ድጋፍ እንዲዘገይ አድርጎባታል።
⚠️ ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎች
የIMF ድጋፍ መጓተት፦ በፍርድ ቤት የሚደረግ ረጅም ክርክር አይ ኤም ኤፍ ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ (EFF) ቀጣይ ምዕራፎች ሊያስተጓጉል ይችላል።
የገበያ መገለል፦ ክርክሩ እስካልተፈታ ድረስ ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ገበያ ተመልሳ ተጨማሪ ብድር ለማግኘት ትቸገራለች።
የበጀት ጫና፦ ለትምህርት፣ ለጤና እና ለልማት መዋል ያለበት የውጭ ምንዛሬ ለእዳ ክፍያ እንዲውል ጫና ሊፈጥር ይችላል።
4 months ago
ታላቅ የቤተክርስቲያን የገቢ ማሰባሰቢያ ጥሪ
ለተከበራችሁ የገናናው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች በሙሉ
በሰሜን ሸዋ ስላሴ ሀገረ ስብከት በአለልቱ ወረዳ ቤ/ክህነት ሥር የሚገኘው የአለልቱ ዘራማ ቅዱስ ገብርኤል ህንፃ ቤ/ክርስቲያን ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምስራቅ በደብረብርሃን መውጫ መንገድ በ57 ኪ.ሜትር በዋናው አስፋልት ላይ ይገኛል።
ይህ የቅዱስ ገብርኤል ፅላት ከተለያዩ ንዋየ ቅዱሳት ጋር ግንቦት 24 ቀን 2007 ዓ.ም. ለ300 ዓመታት ተሰውሮ ከነበረበት አለት ድንጋይ ሥር ጊዜው ሲደርስ ወጥቶ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን እየተፈፀመበትና ፀበሉም ተአምራትን እየሠራ ይገኛል፡፡ ይህ ህንፃ ቤ/ክርስቲያን በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብፅዑ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ መልካም ፈቃድ ግንቦት 9 ቀን 2009 ዓ.ም. የመሰረት ድንጋይ ከተጣለ በኋላ በቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች ከየአቅየጫው የሚገኙት ምእመናን በቁሳቁስና በጥሬ ገንዘብ ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ለሁለት ተከታታይ ዓመታት በተደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ ባዛር በማዘጋጀት በተገኘው ገቢ በከፍተኛ ፍጥነት ህንፃው ለፍፃሜ እየተቃረበ ይገኛል፡፡ በዚህ መልኩ አስተዋፅኦ ላደረጋችሁልን የቤ/ክርስቲያናችን ልጆች ሁሉ ምስጋናችንን በእግዚአብሔር ስም እናቀርባለን።
በእግዚአብሔር አጋዥነት እኛው የጀመርነውን እኛው ጨርሰን ለአገልግሎት ለማብቃት ለመጨረሻ ጊዜ ከጥር 30 ቀን እስከ የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚቆይ ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ባዛር አዘጋጀተን የጀመርነውን እንጨርሰዋለን እግዚአብሔር ቢረዳን በማለት የቀረንን የውስጥና የውጭ ሥራዎች በርብርብ ለመጨረስ በዚህ ኘሮግራም ላይ የገንዘብ እና የቁሳቁስ ድጋፍ ልክ እንደ ትላንቱ ለማድረግ እርስዎም ቤተሰብዎን ወዳጅ ዘመድዎንና ሌሎችንም ምእመናን በማስተባበር የበኩልዎን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱልን በማለት አክብሮታዊ ጥሪያችንን በገናናው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ስም እናቀርባለን።
👉 Commercial Bank of Ethiopia - 1000153993002
👉 Awash Bank - 01321117226200
👉 Coffee Bank - 5559501001063
👉 Dashen Bank - 5811797956011
ለተከበራችሁ የገናናው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች በሙሉ
በሰሜን ሸዋ ስላሴ ሀገረ ስብከት በአለልቱ ወረዳ ቤ/ክህነት ሥር የሚገኘው የአለልቱ ዘራማ ቅዱስ ገብርኤል ህንፃ ቤ/ክርስቲያን ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምስራቅ በደብረብርሃን መውጫ መንገድ በ57 ኪ.ሜትር በዋናው አስፋልት ላይ ይገኛል።
ይህ የቅዱስ ገብርኤል ፅላት ከተለያዩ ንዋየ ቅዱሳት ጋር ግንቦት 24 ቀን 2007 ዓ.ም. ለ300 ዓመታት ተሰውሮ ከነበረበት አለት ድንጋይ ሥር ጊዜው ሲደርስ ወጥቶ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን እየተፈፀመበትና ፀበሉም ተአምራትን እየሠራ ይገኛል፡፡ ይህ ህንፃ ቤ/ክርስቲያን በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብፅዑ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ መልካም ፈቃድ ግንቦት 9 ቀን 2009 ዓ.ም. የመሰረት ድንጋይ ከተጣለ በኋላ በቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች ከየአቅየጫው የሚገኙት ምእመናን በቁሳቁስና በጥሬ ገንዘብ ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ለሁለት ተከታታይ ዓመታት በተደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ ባዛር በማዘጋጀት በተገኘው ገቢ በከፍተኛ ፍጥነት ህንፃው ለፍፃሜ እየተቃረበ ይገኛል፡፡ በዚህ መልኩ አስተዋፅኦ ላደረጋችሁልን የቤ/ክርስቲያናችን ልጆች ሁሉ ምስጋናችንን በእግዚአብሔር ስም እናቀርባለን።
በእግዚአብሔር አጋዥነት እኛው የጀመርነውን እኛው ጨርሰን ለአገልግሎት ለማብቃት ለመጨረሻ ጊዜ ከጥር 30 ቀን እስከ የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚቆይ ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ባዛር አዘጋጀተን የጀመርነውን እንጨርሰዋለን እግዚአብሔር ቢረዳን በማለት የቀረንን የውስጥና የውጭ ሥራዎች በርብርብ ለመጨረስ በዚህ ኘሮግራም ላይ የገንዘብ እና የቁሳቁስ ድጋፍ ልክ እንደ ትላንቱ ለማድረግ እርስዎም ቤተሰብዎን ወዳጅ ዘመድዎንና ሌሎችንም ምእመናን በማስተባበር የበኩልዎን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱልን በማለት አክብሮታዊ ጥሪያችንን በገናናው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ስም እናቀርባለን።
👉 Commercial Bank of Ethiopia - 1000153993002
👉 Awash Bank - 01321117226200
👉 Coffee Bank - 5559501001063
👉 Dashen Bank - 5811797956011
4 months ago
ሒሳብ ቁጥርዎን ከፋይዳ ጋር ያስተሳስሩ!
ውድ ደንበኞቻችን !
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሰጠው አቅጣጫ መሠረት፤ ሁሉም የባንክ ደንበኞች ሒሳባቸውን በቀጣይነት ለማንቀሳቀስ የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥራቸውን ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ስለገለጸ፤ እርስዎም ባሉበት ሆነው ይህንን ሊንክ በመጠቀም https://verifayda.ahaduban... ወይም አቅራቢያዎ ወደሚገኝ የባንካችን ቅርንጫፍ ጎራ በማለት ባለ 16 አኃዝ ልዩ ቁጥር (FCN) እንዲሰጡ በአክብሮት እንጠይቃለን ፡፡
አሐዱ፡ ባንክ አ.ማ
ውድ ደንበኞቻችን !
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሰጠው አቅጣጫ መሠረት፤ ሁሉም የባንክ ደንበኞች ሒሳባቸውን በቀጣይነት ለማንቀሳቀስ የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥራቸውን ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ስለገለጸ፤ እርስዎም ባሉበት ሆነው ይህንን ሊንክ በመጠቀም https://verifayda.ahaduban... ወይም አቅራቢያዎ ወደሚገኝ የባንካችን ቅርንጫፍ ጎራ በማለት ባለ 16 አኃዝ ልዩ ቁጥር (FCN) እንዲሰጡ በአክብሮት እንጠይቃለን ፡፡
አሐዱ፡ ባንክ አ.ማ
4 months ago
የአቢሲኒያ ባንክ አዲስ የአክሲዮን ሽያጭ ይፋ አደረገ!
የአቢሲኒያ ባንክ ነባር ባለአክሲዮኖች በሙሉ!
የአቢሲኒያ ባንክ (Bank of Abyssinia S.C) ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ባገኘው ፈቃድ መሰረት ለነባር ባለአክሲዮኖች 3,125,000 አዳዲስ ተራ አክሲዮኖችን ለሽያጭ ማቅረቡን በደስታ ያበስራል።
ቁልፍ መረጃዎች፡
💰 የአንድ አክሲዮን ዋጋ፦ 1,600 ብር
📅 የሽያጭ ጊዜ፦ ከጥር 22 ቀን 2018 እስከ የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
⚖️ የአከፋፈል ሁኔታ፦ አክሲዮኖቹ የሚከፋፈሉት እንደ ነባር የባለቤትነት ድርሻ (Pro rata basis) ይሆናል።
ለመግዛት ምን ያስፈልጋል?
ባለአክሲዮኖች በካፒታል ገበያ ባለስልጣን ፈቃድ ያላቸውን የኢንቨስትመንት ደላሎች (Investment Brokers) ዘንድ በመቅረብ የንግድ አካውንት መክፈትና የግዢ ትዕዛዝ መስጠት ይኖርባቸዋል።
አስፈላጊ ሰነዶች፦
ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ ቁጥር)
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN
የኢሜል አድራሻ (Email)
በወኪል ለሚፈጽሙ ደግሞ ሕጋዊ የውክልና ስልጣን ማስረጃ
ማሳሰቢያ፦ ኢንቨስት ከማድረግዎ በፊት የባንኩን "Prospectus" (መረጃ መግለጫ) ሙሉ በሙሉ እንዲያነቡና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የፋይናንስ ባለሙያዎችን እንዲያማክሩ ይመከራል።
ለበለጠ መረጃ፦
📍 ለገሃር በሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት በአካል በመቅረብ ወይም በሚከተሉት ስልኮች ይደውሉ፡
📞 +251-115-526314 | 0974-506535 | 0911-373294 | 0937-439882
የአቢሲኒያ ባንክ ነባር ባለአክሲዮኖች በሙሉ!
የአቢሲኒያ ባንክ (Bank of Abyssinia S.C) ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ባገኘው ፈቃድ መሰረት ለነባር ባለአክሲዮኖች 3,125,000 አዳዲስ ተራ አክሲዮኖችን ለሽያጭ ማቅረቡን በደስታ ያበስራል።
ቁልፍ መረጃዎች፡
💰 የአንድ አክሲዮን ዋጋ፦ 1,600 ብር
📅 የሽያጭ ጊዜ፦ ከጥር 22 ቀን 2018 እስከ የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
⚖️ የአከፋፈል ሁኔታ፦ አክሲዮኖቹ የሚከፋፈሉት እንደ ነባር የባለቤትነት ድርሻ (Pro rata basis) ይሆናል።
ለመግዛት ምን ያስፈልጋል?
ባለአክሲዮኖች በካፒታል ገበያ ባለስልጣን ፈቃድ ያላቸውን የኢንቨስትመንት ደላሎች (Investment Brokers) ዘንድ በመቅረብ የንግድ አካውንት መክፈትና የግዢ ትዕዛዝ መስጠት ይኖርባቸዋል።
አስፈላጊ ሰነዶች፦
ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ ቁጥር)
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN
የኢሜል አድራሻ (Email)
በወኪል ለሚፈጽሙ ደግሞ ሕጋዊ የውክልና ስልጣን ማስረጃ
ማሳሰቢያ፦ ኢንቨስት ከማድረግዎ በፊት የባንኩን "Prospectus" (መረጃ መግለጫ) ሙሉ በሙሉ እንዲያነቡና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የፋይናንስ ባለሙያዎችን እንዲያማክሩ ይመከራል።
ለበለጠ መረጃ፦
📍 ለገሃር በሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት በአካል በመቅረብ ወይም በሚከተሉት ስልኮች ይደውሉ፡
📞 +251-115-526314 | 0974-506535 | 0911-373294 | 0937-439882
Sponsored by
Surafel
4 months ago
የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ገበያ ወደ አዲስ ምዕራፍ፡ ባንኮች በዲጂታል መድረክ እርስ በእርስ መገበያየት ጀመሩ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የፋይናንስ ታሪክ የሚቀይር "የባንክ ለባንክ የውጭ ምንዛሬ ግብይት" በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሥርዓት (Automated Trading Platform) መጀመሩን በይፋ አበሰረ።
ይህ አሠራር ባንኮች ያላቸውን ትርፍ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ላለባቸው ባንኮች በገበያ ዋጋ የሚሸጡበት ግልጽ መድረክ ነው።
🌍 የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ምን ያስተምረናል?
ኢትዮጵያ አሁን የጀመረችው ይህ ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ ስኬታማ በሆኑ ሀገራት የተሞከረና ውጤታማነቱ የተረጋገጠ ነው።
ቬትናም : እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ ተመሳሳይ የኢንተርባንክ (Interbank) ገበያ በመጀመሯ፣ በሀገሪቱ የነበረውን ጥቁር ገበያ በእጅጉ መቀነስ ችላለች። ይህም የውጭ ኢንቨስተሮች በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ላይ እምነት እንዲኖራቸው አድርጓል።
ግብፅ : እ.ኤ.አ በ2016 የውጭ ምንዛሬ ተመንን ለገበያ ክፍት ካደረገች በኋላ፣ የባንክ ለባንክ ግብይቱን በማጠናከሯ በባንኮች ውስጥ ያለውን የውጭ ምንዛሬ ፈሳሽነት (Liquidity) በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ችላለች።
ናይጄሪያ : ምንም እንኳን ተግዳሮቶች ቢገጥሟትም፣ የዲጂታል ግብይት ሥርዓቱን በማዘመኗ የውጭ ምንዛሬ ተመን ግልጽ በሆነ መንገድ በየቀኑ እንዲታወቅና ግምታዊ ግብይት (Speculation) እንዲቀንስ ረድቷታል።
💎 የአዲሱ ሥርዓት ልዩ ባህሪያት
"ሪል ታይም" ግብይት፦ በኢትዮጵያ ሰኩሪቲስ ኤክስቼንጅ (ESX) በኩል የሚመራው ይሄው መድረክ፣ ባንኮች በሰከንዶች ውስጥ የዋጋ ማቅረቢያና ሽያጭ እንዲያከናውኑ ያስችላቸዋል።
የመረጃ እኩልነት፦ ቀደም ሲል የነበረውን "መረጃ ያለው ብቻ ያተርፋል" የሚለውን አሠራር በማስቀረት፣ ሁሉም ባንኮች የገበያውን እንቅስቃሴ በእኩልነት እንዲያዩ ያደርጋል።
ጥብቅ ቁጥጥር፦ ብሔራዊ ባንክ በዳሽቦርዱ በኩል እያንዳንዱን ግብይት በቀጥታ ይከታተላል፤ ይህም ሕገ-ወጥ አሠራሮችንና የዋጋ መዛባትን ይከላከላል።
🎤 የባንኩ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ምን አሉ?
"ዛሬ የተጀመረው የቴክኖሎጂ ሥርዓት የፋይናንስ ዘርፋችንን ለማዘመን የወሰድነው ትልቁ እርምጃ ነው። ይህም ግልጽነትን በማስፈን፣ ትክክለኛ የገበያ ዋጋ እንዲወጣ በማድረግ እና ለጠቅላላው ኢኮኖሚ መረጋጋት የጀርባ አጥንት ይሆናል።"
📌 ለምን ይጠቅመናል?
ይህ ሥርዓት ተግባራዊ መሆኑ የውጭ ምንዛሬ በአንድ ባንክ ብቻ ታጥሮ እንዳይቀር ያደርጋል። አንድ ባንክ ምንዛሬ ሲያጥረው ሌላው ካለው እንዲገዛ በማስቻሉ፣ ለገቢ ምርቶች (እንደ መድኃኒትና ነዳጅ) የሚፈለገው የውጭ ምንዛሬ ፍሰት እንዲቀላጠፍ ይረዳል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የፋይናንስ ታሪክ የሚቀይር "የባንክ ለባንክ የውጭ ምንዛሬ ግብይት" በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሥርዓት (Automated Trading Platform) መጀመሩን በይፋ አበሰረ።
ይህ አሠራር ባንኮች ያላቸውን ትርፍ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ላለባቸው ባንኮች በገበያ ዋጋ የሚሸጡበት ግልጽ መድረክ ነው።
🌍 የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ምን ያስተምረናል?
ኢትዮጵያ አሁን የጀመረችው ይህ ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ ስኬታማ በሆኑ ሀገራት የተሞከረና ውጤታማነቱ የተረጋገጠ ነው።
ቬትናም : እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ ተመሳሳይ የኢንተርባንክ (Interbank) ገበያ በመጀመሯ፣ በሀገሪቱ የነበረውን ጥቁር ገበያ በእጅጉ መቀነስ ችላለች። ይህም የውጭ ኢንቨስተሮች በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ላይ እምነት እንዲኖራቸው አድርጓል።
ግብፅ : እ.ኤ.አ በ2016 የውጭ ምንዛሬ ተመንን ለገበያ ክፍት ካደረገች በኋላ፣ የባንክ ለባንክ ግብይቱን በማጠናከሯ በባንኮች ውስጥ ያለውን የውጭ ምንዛሬ ፈሳሽነት (Liquidity) በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ችላለች።
ናይጄሪያ : ምንም እንኳን ተግዳሮቶች ቢገጥሟትም፣ የዲጂታል ግብይት ሥርዓቱን በማዘመኗ የውጭ ምንዛሬ ተመን ግልጽ በሆነ መንገድ በየቀኑ እንዲታወቅና ግምታዊ ግብይት (Speculation) እንዲቀንስ ረድቷታል።
💎 የአዲሱ ሥርዓት ልዩ ባህሪያት
"ሪል ታይም" ግብይት፦ በኢትዮጵያ ሰኩሪቲስ ኤክስቼንጅ (ESX) በኩል የሚመራው ይሄው መድረክ፣ ባንኮች በሰከንዶች ውስጥ የዋጋ ማቅረቢያና ሽያጭ እንዲያከናውኑ ያስችላቸዋል።
የመረጃ እኩልነት፦ ቀደም ሲል የነበረውን "መረጃ ያለው ብቻ ያተርፋል" የሚለውን አሠራር በማስቀረት፣ ሁሉም ባንኮች የገበያውን እንቅስቃሴ በእኩልነት እንዲያዩ ያደርጋል።
ጥብቅ ቁጥጥር፦ ብሔራዊ ባንክ በዳሽቦርዱ በኩል እያንዳንዱን ግብይት በቀጥታ ይከታተላል፤ ይህም ሕገ-ወጥ አሠራሮችንና የዋጋ መዛባትን ይከላከላል።
🎤 የባንኩ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ምን አሉ?
"ዛሬ የተጀመረው የቴክኖሎጂ ሥርዓት የፋይናንስ ዘርፋችንን ለማዘመን የወሰድነው ትልቁ እርምጃ ነው። ይህም ግልጽነትን በማስፈን፣ ትክክለኛ የገበያ ዋጋ እንዲወጣ በማድረግ እና ለጠቅላላው ኢኮኖሚ መረጋጋት የጀርባ አጥንት ይሆናል።"
📌 ለምን ይጠቅመናል?
ይህ ሥርዓት ተግባራዊ መሆኑ የውጭ ምንዛሬ በአንድ ባንክ ብቻ ታጥሮ እንዳይቀር ያደርጋል። አንድ ባንክ ምንዛሬ ሲያጥረው ሌላው ካለው እንዲገዛ በማስቻሉ፣ ለገቢ ምርቶች (እንደ መድኃኒትና ነዳጅ) የሚፈለገው የውጭ ምንዛሬ ፍሰት እንዲቀላጠፍ ይረዳል።
5 months ago
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ!
🏆የጥምቀት ትዝታዎን በፎቶ ሲያስቀሩ ወይም የበዓሉን ድባብ የሚያሳይ ፎቶ ሲያነሱ፤ አሐዱ፡ባንክ ሊሸልምዎ ተሰናድቷል፡፡
የሚከተሉትን ቀላል የውድድር መስፈርቶች በማሟላት፤ ራስዎን ለሽልማት እጩ ያድርጉ!
👉መጀመሪያ የአሐዱ:ባንክን ማኅበራዊ ገጾችን ይቀላቀሉ፤
Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube
👉በራስዎ የፌስቡክ ገጽ ባንካችንን ታግ በማድረግ የሚወዳደሩበትን ፎቶ ይለጥፉ፤
👉ፎቶዎን በገጽዎ ላይ ሲለጥፉ፤ እነኚህን ሀሽ ታጎች (#ahadubank #አሐዱባንክ ) ይጠቀሙ፤
👉የለጠፉትን ፎቶ ሊንክ በዚህ የአሐዱ ባንክ ቴሌግራም https://t.me/ahadubanket ገጽ ይላኩ፤
👉ውድድሩ ከጥር 10 -15/2018 ዓ. ም ከቀኑ 8፡00 ድረስ ይቆያል፤
👉በተጠቀሱት ቀናት ውስጥ ከፍተኛውን ላይክ ያገኙ ሦስት ፎቶዎችን እንደ ደረጃቸው ብር 10,000፣ 7,000 እና 3,000 ይሸለማሉ፤
ይበሉ! የጥምቀት በዓልዎን ያክብሩ፣ ትዝታዎን በፎቶ ያስቀሩ፣ ይወዳደሩ፣ ይሸለሙ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ!
መልካም በዓል!
አሐዱ፡ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች
🏆የጥምቀት ትዝታዎን በፎቶ ሲያስቀሩ ወይም የበዓሉን ድባብ የሚያሳይ ፎቶ ሲያነሱ፤ አሐዱ፡ባንክ ሊሸልምዎ ተሰናድቷል፡፡
የሚከተሉትን ቀላል የውድድር መስፈርቶች በማሟላት፤ ራስዎን ለሽልማት እጩ ያድርጉ!
👉መጀመሪያ የአሐዱ:ባንክን ማኅበራዊ ገጾችን ይቀላቀሉ፤
Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube
👉በራስዎ የፌስቡክ ገጽ ባንካችንን ታግ በማድረግ የሚወዳደሩበትን ፎቶ ይለጥፉ፤
👉ፎቶዎን በገጽዎ ላይ ሲለጥፉ፤ እነኚህን ሀሽ ታጎች (#ahadubank #አሐዱባንክ ) ይጠቀሙ፤
👉የለጠፉትን ፎቶ ሊንክ በዚህ የአሐዱ ባንክ ቴሌግራም https://t.me/ahadubanket ገጽ ይላኩ፤
👉ውድድሩ ከጥር 10 -15/2018 ዓ. ም ከቀኑ 8፡00 ድረስ ይቆያል፤
👉በተጠቀሱት ቀናት ውስጥ ከፍተኛውን ላይክ ያገኙ ሦስት ፎቶዎችን እንደ ደረጃቸው ብር 10,000፣ 7,000 እና 3,000 ይሸለማሉ፤
ይበሉ! የጥምቀት በዓልዎን ያክብሩ፣ ትዝታዎን በፎቶ ያስቀሩ፣ ይወዳደሩ፣ ይሸለሙ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ!
መልካም በዓል!
አሐዱ፡ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች
5 months ago
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ!
🏆የጥምቀት ትዝታዎን በፎቶ ሲያስቀሩ ወይም የበዓሉን ድባብ የሚያሳይ ፎቶ ሲያነሱ፤ አሐዱ፡ባንክ ሊሸልምዎ ተሰናድቷል፡፡
የሚከተሉትን ቀላል የውድድር መስፈርቶች በማሟላት፤ ራስዎን ለሽልማት እጩ ያድርጉ!
👉መጀመሪያ የአሐዱ:ባንክን ማኅበራዊ ገጾችን ይቀላቀሉ፤
Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube
👉በራስዎ የፌስቡክ ገጽ ባንካችንን ታግ በማድረግ የሚወዳደሩበትን ፎቶ ይለጥፉ፤
👉ፎቶዎን በገጽዎ ላይ ሲለጥፉ፤ እነኚህን ሀሽ ታጎች (#ahadubank #አሐዱባንክ ) ይጠቀሙ፤
👉የለጠፉትን ፎቶ ሊንክ በዚህ የአሐዱ ባንክ ቴሌግራም https://t.me/ahadubanket ገጽ ይላኩ፤
👉ውድድሩ ከጥር 10 -15/2018 ዓ. ም ከቀኑ 8፡00 ድረስ ይቆያል፤
👉በተጠቀሱት ቀናት ውስጥ ከፍተኛውን ላይክ ያገኙ ሦስት ፎቶዎችን እንደ ደረጃቸው ብር 10,000፣ 7,000 እና 3,000 ይሸለማሉ፤
ይበሉ! የጥምቀት በዓልዎን ያክብሩ፣ ትዝታዎን በፎቶ ያስቀሩ፣ ይወዳደሩ፣ ይሸለሙ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ!
መልካም በዓል!
አሐዱ፡ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች
🏆የጥምቀት ትዝታዎን በፎቶ ሲያስቀሩ ወይም የበዓሉን ድባብ የሚያሳይ ፎቶ ሲያነሱ፤ አሐዱ፡ባንክ ሊሸልምዎ ተሰናድቷል፡፡
የሚከተሉትን ቀላል የውድድር መስፈርቶች በማሟላት፤ ራስዎን ለሽልማት እጩ ያድርጉ!
👉መጀመሪያ የአሐዱ:ባንክን ማኅበራዊ ገጾችን ይቀላቀሉ፤
Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube
👉በራስዎ የፌስቡክ ገጽ ባንካችንን ታግ በማድረግ የሚወዳደሩበትን ፎቶ ይለጥፉ፤
👉ፎቶዎን በገጽዎ ላይ ሲለጥፉ፤ እነኚህን ሀሽ ታጎች (#ahadubank #አሐዱባንክ ) ይጠቀሙ፤
👉የለጠፉትን ፎቶ ሊንክ በዚህ የአሐዱ ባንክ ቴሌግራም https://t.me/ahadubanket ገጽ ይላኩ፤
👉ውድድሩ ከጥር 10 -15/2018 ዓ. ም ከቀኑ 8፡00 ድረስ ይቆያል፤
👉በተጠቀሱት ቀናት ውስጥ ከፍተኛውን ላይክ ያገኙ ሦስት ፎቶዎችን እንደ ደረጃቸው ብር 10,000፣ 7,000 እና 3,000 ይሸለማሉ፤
ይበሉ! የጥምቀት በዓልዎን ያክብሩ፣ ትዝታዎን በፎቶ ያስቀሩ፣ ይወዳደሩ፣ ይሸለሙ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ!
መልካም በዓል!
አሐዱ፡ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች
5 months ago
🚨 አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ ለቤት ተመዝጋቢዎች፡ ከቤት ሳትወጡ መረጃችሁን አረጋግጡ!
በአዲስ አበባ የ20/80 እና 40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም ተመዝጋቢዎች የሆናችሁ ዜጎች፣ ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች ሳቢያ ለከፍተኛ እንግልትና ለተጨማሪ ወጪ እየተዳረጉ መሆኑ ታውቋል።
ቢሮው ያስተላለፋቸው ተጨማሪ ማብራሪያዎችና መረጃዎች፦
📍 የአካል መገኘት አያስፈልግም፦ "ምዝገባችሁን አክቲቭ አድርጉ" በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሐሰት ሲሆን፣ ለዚህ ጉዳይ ወደ ቢሮው በአካል መምጣትና መሰለፍ በፍጹም አያስፈልግም።
💻 አገልግሎቱ በድረ-ገጽ ብቻ፦ ማንኛውም ተመዝጋቢ የቆጠባ ሂሳብ ቁጥሩን ብቻ በመጠቀም http://aahdab.et/saving በተባለው የቢሮው ድረ-ገጽ ላይ መረጃውን ማረጋገጥ ይችላል።
⏰ የጊዜ ገደብ የለም፦ መረጃን የማረጋገጡ ሂደት በማንኛውም ሰዓትና ቀን የሚሰራ በመሆኑ፣ "ጊዜው ሳያልፍባችሁ" በሚሉ አስፈሪ መልዕክቶች አትደናገጡ።
⚠️ ከደላሎች ተጠንቀቁ፦ "ጉዳያችሁን እናስፈጽማለን" ወይም "ስማችሁን ወደ ቅድሚያ ዝርዝር እናስገባለን" የሚሉ ግለሰቦች ሊያጭበረብሯችሁ ስለሚችሉ መረጃችሁን ለማንም አሳልፋችሁ አትስጡ።
📱 ይፋዊ የመረጃ ምንጮችን ብቻ ተከተሉ፦ ከቢሮው የፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ቲክቶክና ዩቲዩብ ገጾች ውጪ የሚለቀቁ መረጃዎች ተዓማኒነት የሌላቸው መሆኑን ይረዱ።
ምን ማድረግ ይኖርብዎታል?
የቆጠባ ሂሳብ ቁጥርዎን (Bank Account) መያዝ።
ወደ ድረ-ገጹ http://aahdab.et/saving መግባት።
መረጃዎን ካረጋገጡ በኋላ ለሚመጣው ማንኛውም ጥሪ ይፋዊ መግለጫዎችን መጠበቅ።
በአዲስ አበባ የ20/80 እና 40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም ተመዝጋቢዎች የሆናችሁ ዜጎች፣ ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች ሳቢያ ለከፍተኛ እንግልትና ለተጨማሪ ወጪ እየተዳረጉ መሆኑ ታውቋል።
ቢሮው ያስተላለፋቸው ተጨማሪ ማብራሪያዎችና መረጃዎች፦
📍 የአካል መገኘት አያስፈልግም፦ "ምዝገባችሁን አክቲቭ አድርጉ" በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሐሰት ሲሆን፣ ለዚህ ጉዳይ ወደ ቢሮው በአካል መምጣትና መሰለፍ በፍጹም አያስፈልግም።
💻 አገልግሎቱ በድረ-ገጽ ብቻ፦ ማንኛውም ተመዝጋቢ የቆጠባ ሂሳብ ቁጥሩን ብቻ በመጠቀም http://aahdab.et/saving በተባለው የቢሮው ድረ-ገጽ ላይ መረጃውን ማረጋገጥ ይችላል።
⏰ የጊዜ ገደብ የለም፦ መረጃን የማረጋገጡ ሂደት በማንኛውም ሰዓትና ቀን የሚሰራ በመሆኑ፣ "ጊዜው ሳያልፍባችሁ" በሚሉ አስፈሪ መልዕክቶች አትደናገጡ።
⚠️ ከደላሎች ተጠንቀቁ፦ "ጉዳያችሁን እናስፈጽማለን" ወይም "ስማችሁን ወደ ቅድሚያ ዝርዝር እናስገባለን" የሚሉ ግለሰቦች ሊያጭበረብሯችሁ ስለሚችሉ መረጃችሁን ለማንም አሳልፋችሁ አትስጡ።
📱 ይፋዊ የመረጃ ምንጮችን ብቻ ተከተሉ፦ ከቢሮው የፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ቲክቶክና ዩቲዩብ ገጾች ውጪ የሚለቀቁ መረጃዎች ተዓማኒነት የሌላቸው መሆኑን ይረዱ።
ምን ማድረግ ይኖርብዎታል?
የቆጠባ ሂሳብ ቁጥርዎን (Bank Account) መያዝ።
ወደ ድረ-ገጹ http://aahdab.et/saving መግባት።
መረጃዎን ካረጋገጡ በኋላ ለሚመጣው ማንኛውም ጥሪ ይፋዊ መግለጫዎችን መጠበቅ።