2 days ago
የጤናው ዘርፍ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
1 month ago
ብዙ እያተረፍንበት ያለው ጊዜያዊ ችግርን ተደጋገፎ የማለፍ ባህላችን
****************
"በብዙ መንገድ ምግብ ተርፎ በሚደፋባት ከተማ ውስጥ በቀን አንድ ጊዜ በተሟላ ሁኔታ ለመመገብ የሚቸገሩ ወገኖቻችንን ማየት የሁላችንም ሕመም እና ሁላችንም ልንወጣው የሚገባ ትልቅ ኃላፊነት ነው።"
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በየረር 30ኛውን የነዋሪዎች የምገባ ማዕከል በመረቁበት ወቅት የተናገሩት ይህ ሀሳብ በከተማዋ ውስጥ ማኅበራዊ ፍትሕን የማንገስን አስፈላጊነት በጉልህ ያሳያል።
ይህ ማዕከል በየረር የተገነባበት ዋናው ምክንያት በሸራተን ሆቴል ማስፋፊያ ልማት ከቂርቆስ አካባቢ ለተነሱ እንዲሁም ከካዛንቺስ ለተዛወሩ ቋሚ ገቢና መጠለያ ያልነበራቸው ዜጎች ድጋፍ ለመስጠት ነው።
"ሕጋዊ ቤት አልነበራችሁም ብለን ነዋሪዎቻችንን መተው ስለማንችል፣ ኃላፊነት ወስደን ያስገባናቸው በርካታ ሰዎች አሉ" በማለት ከንቲባዋ የመንግሥት ልማት ሰው-ተኮር መሆኑን አረጋግጠዋል።
የምገባ ማዕከላት መከፈት በተለይም በልማት ምክንያት ለተነሱና ቋሚ ገቢ ለሌላቸው ዜጎች ንጹሕና ትኩስ ምግብ በነፃ የሚያገኙበት የሕልውና ዋስትና ነው።
እያንዳንዱ ማዕከል አቅመ ደካሞችና አረጋውያን ሰብዓዊ ክብራቸው ተጠብቆ የሚመገቡበትና የሚገናኙበት ቋሚ ቤታቸው ከመሆኑም በላይ፣ ወደ ማዕከል መምጣት ለማይችሉ አቅመ ደካሞችም ምግቡ ወደ ቤታቸው የሚላክበት አሠራር የተመቻቸበት ጊዜያዊ ችግርን ተደጋግፎ የማለፊያ ትልቅ ድልድይ ሆኗል።
ይሁን እንጂ የዚህ ስትራቴጂ ዋና ግብ ዜጎችን ሁልጊዜ በማዕከሉ ላይ ጥገኛ ማድረግ ሳይሆን፣ የምግብ ዋስትናቸውን እያረጋገጡ ወደ ቋሚ የሥራ ዕድል ማሸጋገር ነው።
እስካሁን በተከፈቱት 29 የምገባ ማዕከላት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በሂደት ወደ ሥራ መግባታቸውና በ30ኛውም የየረር ማዕከልም በርካታ ነዋሪዎች ገና በምረቃው ዕለት በመጋቢነትና በአስተናጋጅነት መቀጠራቸው ለዚህ ማሳያ ነው።
በተጨማሪም በከተማዋ በሴፍቲኔት ተይዘው ከነበሩ መካከል ከ100 ሺህ በላይ ተጠቃሚዎች ራሳቸውን ችለው ዛሬ ላይ ሌሎችን መቅጠር መቻላቸው ከተማዋን ከድህነት ለማውጣት የተያዘው ሰው-ተኮር ልማት በተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ያረጋግጣል።
ይህ በከተማዋ የተጀመረው ጊዜያዊ ችግርን ተደጋገፎ የማለፍ ባህል የመንግሥት ሸክም ብቻ ሳይሆን ባለሀብቶችና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ከገቢያቸው ላይ ቀንሰው የሚሳተፉበት የማኅበራዊ ኃላፊነት ውጤት ነው።
ማዕከላቱ በዘላቂነት ጥራታቸውን ጠብቀው እንዲቀጥሉ ለማስቻል የምገባ ኤጀንሲው የቁሳቁስና የደረጃ ክትትል የሚያደርግ ሲሆን፣ ጉድለት በተገኘ ጊዜም ከመንግሥት በጀት እንደሚሟላ ታውቋል።
ከተማን በዘላቂነት ማበልጸግ የሚቻለው ሕንጻዎችን በመገንባት ብቻ ሳይሆን ሌት ተቀን ጠንክሮ በመሥራት፣ እርስ በርስ በመደጋገፍና ለአቅመ ደካማ ወገኖች በመትረፍ ጭምር መሆኑን የ30ኛው የምገባ ማዕከል መከፈት ትልቅ ማሳያ ነው።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #addisababa #communitysupport #socialjustice #ebc
****************
"በብዙ መንገድ ምግብ ተርፎ በሚደፋባት ከተማ ውስጥ በቀን አንድ ጊዜ በተሟላ ሁኔታ ለመመገብ የሚቸገሩ ወገኖቻችንን ማየት የሁላችንም ሕመም እና ሁላችንም ልንወጣው የሚገባ ትልቅ ኃላፊነት ነው።"
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በየረር 30ኛውን የነዋሪዎች የምገባ ማዕከል በመረቁበት ወቅት የተናገሩት ይህ ሀሳብ በከተማዋ ውስጥ ማኅበራዊ ፍትሕን የማንገስን አስፈላጊነት በጉልህ ያሳያል።
ይህ ማዕከል በየረር የተገነባበት ዋናው ምክንያት በሸራተን ሆቴል ማስፋፊያ ልማት ከቂርቆስ አካባቢ ለተነሱ እንዲሁም ከካዛንቺስ ለተዛወሩ ቋሚ ገቢና መጠለያ ያልነበራቸው ዜጎች ድጋፍ ለመስጠት ነው።
"ሕጋዊ ቤት አልነበራችሁም ብለን ነዋሪዎቻችንን መተው ስለማንችል፣ ኃላፊነት ወስደን ያስገባናቸው በርካታ ሰዎች አሉ" በማለት ከንቲባዋ የመንግሥት ልማት ሰው-ተኮር መሆኑን አረጋግጠዋል።
የምገባ ማዕከላት መከፈት በተለይም በልማት ምክንያት ለተነሱና ቋሚ ገቢ ለሌላቸው ዜጎች ንጹሕና ትኩስ ምግብ በነፃ የሚያገኙበት የሕልውና ዋስትና ነው።
እያንዳንዱ ማዕከል አቅመ ደካሞችና አረጋውያን ሰብዓዊ ክብራቸው ተጠብቆ የሚመገቡበትና የሚገናኙበት ቋሚ ቤታቸው ከመሆኑም በላይ፣ ወደ ማዕከል መምጣት ለማይችሉ አቅመ ደካሞችም ምግቡ ወደ ቤታቸው የሚላክበት አሠራር የተመቻቸበት ጊዜያዊ ችግርን ተደጋግፎ የማለፊያ ትልቅ ድልድይ ሆኗል።
ይሁን እንጂ የዚህ ስትራቴጂ ዋና ግብ ዜጎችን ሁልጊዜ በማዕከሉ ላይ ጥገኛ ማድረግ ሳይሆን፣ የምግብ ዋስትናቸውን እያረጋገጡ ወደ ቋሚ የሥራ ዕድል ማሸጋገር ነው።
እስካሁን በተከፈቱት 29 የምገባ ማዕከላት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በሂደት ወደ ሥራ መግባታቸውና በ30ኛውም የየረር ማዕከልም በርካታ ነዋሪዎች ገና በምረቃው ዕለት በመጋቢነትና በአስተናጋጅነት መቀጠራቸው ለዚህ ማሳያ ነው።
በተጨማሪም በከተማዋ በሴፍቲኔት ተይዘው ከነበሩ መካከል ከ100 ሺህ በላይ ተጠቃሚዎች ራሳቸውን ችለው ዛሬ ላይ ሌሎችን መቅጠር መቻላቸው ከተማዋን ከድህነት ለማውጣት የተያዘው ሰው-ተኮር ልማት በተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ያረጋግጣል።
ይህ በከተማዋ የተጀመረው ጊዜያዊ ችግርን ተደጋገፎ የማለፍ ባህል የመንግሥት ሸክም ብቻ ሳይሆን ባለሀብቶችና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ከገቢያቸው ላይ ቀንሰው የሚሳተፉበት የማኅበራዊ ኃላፊነት ውጤት ነው።
ማዕከላቱ በዘላቂነት ጥራታቸውን ጠብቀው እንዲቀጥሉ ለማስቻል የምገባ ኤጀንሲው የቁሳቁስና የደረጃ ክትትል የሚያደርግ ሲሆን፣ ጉድለት በተገኘ ጊዜም ከመንግሥት በጀት እንደሚሟላ ታውቋል።
ከተማን በዘላቂነት ማበልጸግ የሚቻለው ሕንጻዎችን በመገንባት ብቻ ሳይሆን ሌት ተቀን ጠንክሮ በመሥራት፣ እርስ በርስ በመደጋገፍና ለአቅመ ደካማ ወገኖች በመትረፍ ጭምር መሆኑን የ30ኛው የምገባ ማዕከል መከፈት ትልቅ ማሳያ ነው።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #addisababa #communitysupport #socialjustice #ebc
1 month ago
በጋምቤላ ክልል ከ200 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት
*********************
በጋምቤላ ክልል "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ-ግብር በይፋ ተጀምሯል።
በክልሉ ጋምቤላ ከተማን እና የኢታንግ ልዩ ወረዳን ጨምሮ በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች በሚከናወነው በዚህ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ ከ200 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ልዩ ልዩ የልማትና የድጋፍ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተገልጿል።
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ቱት ጆክ ዛሬ በከተማ አስተዳደሩ የሚገኑ የአቅመ-ደካማ ወገኖችን የቤት ዕድሳት በይፋ በማስጀመር የክረምቱን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ አስጀምረዋል።
ከንቲባው መርሃ-ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት፤ ወጣቶችንና በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር ረዳት የሌላቸውን አረጋውያን ቤቶች የመገንባትና የማደስ፣ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ፣ የአካባቢ ጽዳት፣ የደም ልገሳ እንዲሁም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፎችን የማበርከት ተግባራት በስፋት ይከናወናሉ።
የበጎ ፈቃደኝነት ተግባር የሁሉም ዜጋ ማኅበራዊ ኃላፊነት በመሆኑ፣ መላው የከተማዋ ነዋሪ በመርሃ-ግብሩ ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለበት አሳስበዋል።
አክለውም በጎነት የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህልን በማጎልበት የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያግዝ በመሆኑ፣ የሁሉም አካላት ቅንጅታዊ ተሳትፎ እንደሚያስፈልገው ከንቲባው ተናግረዋል።
በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የክረምት ወራት ከ90 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞችን በተለያዩ ዘርፎች በማሰማራት ከ218 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ ሰፊ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
በሚፍታህ አብዱልቃድር
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopia #gambella #voluntaryservice #communitysupport
*********************
በጋምቤላ ክልል "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ-ግብር በይፋ ተጀምሯል።
በክልሉ ጋምቤላ ከተማን እና የኢታንግ ልዩ ወረዳን ጨምሮ በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች በሚከናወነው በዚህ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ ከ200 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ልዩ ልዩ የልማትና የድጋፍ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተገልጿል።
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ቱት ጆክ ዛሬ በከተማ አስተዳደሩ የሚገኑ የአቅመ-ደካማ ወገኖችን የቤት ዕድሳት በይፋ በማስጀመር የክረምቱን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ አስጀምረዋል።
ከንቲባው መርሃ-ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት፤ ወጣቶችንና በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር ረዳት የሌላቸውን አረጋውያን ቤቶች የመገንባትና የማደስ፣ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ፣ የአካባቢ ጽዳት፣ የደም ልገሳ እንዲሁም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፎችን የማበርከት ተግባራት በስፋት ይከናወናሉ።
የበጎ ፈቃደኝነት ተግባር የሁሉም ዜጋ ማኅበራዊ ኃላፊነት በመሆኑ፣ መላው የከተማዋ ነዋሪ በመርሃ-ግብሩ ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለበት አሳስበዋል።
አክለውም በጎነት የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህልን በማጎልበት የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያግዝ በመሆኑ፣ የሁሉም አካላት ቅንጅታዊ ተሳትፎ እንደሚያስፈልገው ከንቲባው ተናግረዋል።
በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የክረምት ወራት ከ90 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞችን በተለያዩ ዘርፎች በማሰማራት ከ218 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ ሰፊ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
በሚፍታህ አብዱልቃድር
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopia #gambella #voluntaryservice #communitysupport
3 months ago
ኢትዮጵያዊ ባህላችንና እሴታችን
* ሃዘንተኛን ማጽናናትና መደገፍ
#ethiopia | የሟች ቤተሰቦችን የመደገፍና የማጽናናት ኢትዮጵያዊ እሴት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጠ
በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 በአንድ የፖሊስ አባል ህይወታቸው ያለፈው የአቶ ተገኝ ባልቻን ቤተሰቦች የአዲስ አበባ አስተዳደር እያጽናና እንደሚገኝ አስታውቋል።
አስተዳደሩ በገባው ቃል መሰረትም ለሟች ቤተሰቦች የመኖሪያ ቤትና የመስሪያ ቦታ ርክክብ አድርጓል።
በስነስርዓቱ ላይ የሟች ቤተሰቦችና የሀገር ሽማግሌዎች የተገኙ ሲሆን ቤተሰቦቹም አስተዳደሩ ከጎናቸው በመሆን ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
በወቅቱ የተገኙት የአዲስ አበባ ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ዶክተር ማሾ ኦላና እንደገለጹት አጋጣሚውን ለፖለቲካ ትርፍና ለተዛባ አጀንዳ ለመጠቀም የሚሞክሩ አካላት ከእውነታው የራቁ ናቸው ብለዋል።
የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በበኩላቸው መሰል ድንገተኛ ክስተቶችን በሀገር በቀል እሴቶች መፍታት እንደሚገባ ገልጸው በሰው መርዶ ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት መሞከር ከባህላችን ያፈነገጠ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል።
በመጨረሻም ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን በመመኘት ከህዝብ ጋር በልማትና በጸጥታ ጉዳዮች ላይ ተባብሮ የመስራቱ ተግባር እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
#gulele #addisababa #humanity #ethiopianvalues #communitysupport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
* ሃዘንተኛን ማጽናናትና መደገፍ
#ethiopia | የሟች ቤተሰቦችን የመደገፍና የማጽናናት ኢትዮጵያዊ እሴት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጠ
በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 በአንድ የፖሊስ አባል ህይወታቸው ያለፈው የአቶ ተገኝ ባልቻን ቤተሰቦች የአዲስ አበባ አስተዳደር እያጽናና እንደሚገኝ አስታውቋል።
አስተዳደሩ በገባው ቃል መሰረትም ለሟች ቤተሰቦች የመኖሪያ ቤትና የመስሪያ ቦታ ርክክብ አድርጓል።
በስነስርዓቱ ላይ የሟች ቤተሰቦችና የሀገር ሽማግሌዎች የተገኙ ሲሆን ቤተሰቦቹም አስተዳደሩ ከጎናቸው በመሆን ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
በወቅቱ የተገኙት የአዲስ አበባ ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ዶክተር ማሾ ኦላና እንደገለጹት አጋጣሚውን ለፖለቲካ ትርፍና ለተዛባ አጀንዳ ለመጠቀም የሚሞክሩ አካላት ከእውነታው የራቁ ናቸው ብለዋል።
የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በበኩላቸው መሰል ድንገተኛ ክስተቶችን በሀገር በቀል እሴቶች መፍታት እንደሚገባ ገልጸው በሰው መርዶ ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት መሞከር ከባህላችን ያፈነገጠ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል።
በመጨረሻም ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን በመመኘት ከህዝብ ጋር በልማትና በጸጥታ ጉዳዮች ላይ ተባብሮ የመስራቱ ተግባር እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
#gulele #addisababa #humanity #ethiopianvalues #communitysupport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 months ago
የማዕድ ማጋራት
አዋሽ ባንክ ለ5 ሺህ ወገኖች የበዓል ደስታን አበረከተ!
#ethiopia | አዋሽ ባንክ የ2018 ዓ.ም የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ “ክብራችን ወገናችን - ደስታችን ማካፈላችን” በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ ደማቅ የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር አከናውኗል።
የድጋፉ ዝርዝር፦
ተጠቃሚዎች፦ በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ከ5,000 በላይ አረጋውያንና አቅመ ደካማ ወገኖች።
የዓይነት ድጋፍ፦ ለእያንዳንዱ ተጠቃሚ 5 ሊትር ዘይት እና 25 ኪሎ ዱቄት ተበርክቷል።
ተጨማሪ፦ ከዓይነት ድጋፉ ባለፈ የአንድ ለአንድ የጥሬ ገንዘብ ስጦታም ተደርጓል።
የባንኩ ማህበራዊ አሻራ፦
አዋሽ ባንክ በ2024/25 የሒሳብ ዓመት ብቻ ለማኅበራዊ ኃላፊነት ተግባራት ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መድቦ በትምህርት፣ በጤና እና በቤት ግንባታ ዘርፎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ባንኩ አሁን ላይ ከ1005 በላይ ቅርንጫፎችና ከ16 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ያሉት ግዙፍ ተቋም ነው።
"የሰውን ልጅ መርዳት ለነፍስ እረፍት ነው!
ለአዋሽ ባንክ ምስጋና ይገባዋል።" 🙏
#getu #awashbank #csr #ethiopia #eastersharing #awashbank31years #socialresponsibility #addisababa #communitysupport #አዋሽባንክ #ማዕድማጋራት #ፋሲካ #ኢትዮጵያ #በጎነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
አዋሽ ባንክ ለ5 ሺህ ወገኖች የበዓል ደስታን አበረከተ!
#ethiopia | አዋሽ ባንክ የ2018 ዓ.ም የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ “ክብራችን ወገናችን - ደስታችን ማካፈላችን” በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ ደማቅ የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር አከናውኗል።
የድጋፉ ዝርዝር፦
ተጠቃሚዎች፦ በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ከ5,000 በላይ አረጋውያንና አቅመ ደካማ ወገኖች።
የዓይነት ድጋፍ፦ ለእያንዳንዱ ተጠቃሚ 5 ሊትር ዘይት እና 25 ኪሎ ዱቄት ተበርክቷል።
ተጨማሪ፦ ከዓይነት ድጋፉ ባለፈ የአንድ ለአንድ የጥሬ ገንዘብ ስጦታም ተደርጓል።
የባንኩ ማህበራዊ አሻራ፦
አዋሽ ባንክ በ2024/25 የሒሳብ ዓመት ብቻ ለማኅበራዊ ኃላፊነት ተግባራት ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መድቦ በትምህርት፣ በጤና እና በቤት ግንባታ ዘርፎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ባንኩ አሁን ላይ ከ1005 በላይ ቅርንጫፎችና ከ16 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ያሉት ግዙፍ ተቋም ነው።
"የሰውን ልጅ መርዳት ለነፍስ እረፍት ነው!
ለአዋሽ ባንክ ምስጋና ይገባዋል።" 🙏
#getu #awashbank #csr #ethiopia #eastersharing #awashbank31years #socialresponsibility #addisababa #communitysupport #አዋሽባንክ #ማዕድማጋራት #ፋሲካ #ኢትዮጵያ #በጎነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
Sponsored by
Surafel
4 months ago
የሕይወት አድን ጥሪ
ለመምህር ዘመነ በጋራ እንድረስላቸው
#ethiopia | ቃለ እግዚአብሔርን ሲያስተምሩና ሲመክሩ የኖሩት ታላቁ አባት መልዓከ ብርሃን መምህር ዘመነ፣ በአሁኑ ወቅት በጠና የልብ ሕመም ምክንያት በከባድ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።
ሐኪሞች ሕይወታቸውን ለማዳን በአፋጣኝ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker) መለወጥ እንዳለባቸው ወስነዋል።
አስፈላጊው መሣሪያ፦ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker)።
የሚያስፈልገው ገንዘብ፦
500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ብር።
ይህ የሕክምና ወጪ ከመምህራችን አቅም በላይ በመሆኑ የእያንዳንዳችንን ርብርብ ይሻል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
1000502420384
ዓባይ ባንክ (Abay Bank)
9250885
የምትሰጡት ሳንቲም ሳይሆን የሰው ሕይወት ነው!
እንዲሉ፣ ዛሬ የምናደርገው ጥቂት እርዳታ ለታላቁ አባት የሕይወት ተስፋ ይሆናል።
እባክዎ ይህ መልእክት ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ይተባበሩን።
#getu #ethiopia #healthalert #saveteacherzemene #heartsurgery #pacemaker #charityethiopia #communitysupport #addisababa #churchteachers #መምህርዘመነ #የልብሕክምና #የሕይወትአድንጥሪ #እርዳታ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ለመምህር ዘመነ በጋራ እንድረስላቸው
#ethiopia | ቃለ እግዚአብሔርን ሲያስተምሩና ሲመክሩ የኖሩት ታላቁ አባት መልዓከ ብርሃን መምህር ዘመነ፣ በአሁኑ ወቅት በጠና የልብ ሕመም ምክንያት በከባድ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።
ሐኪሞች ሕይወታቸውን ለማዳን በአፋጣኝ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker) መለወጥ እንዳለባቸው ወስነዋል።
አስፈላጊው መሣሪያ፦ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker)።
የሚያስፈልገው ገንዘብ፦
500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ብር።
ይህ የሕክምና ወጪ ከመምህራችን አቅም በላይ በመሆኑ የእያንዳንዳችንን ርብርብ ይሻል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
1000502420384
ዓባይ ባንክ (Abay Bank)
9250885
የምትሰጡት ሳንቲም ሳይሆን የሰው ሕይወት ነው!
እንዲሉ፣ ዛሬ የምናደርገው ጥቂት እርዳታ ለታላቁ አባት የሕይወት ተስፋ ይሆናል።
እባክዎ ይህ መልእክት ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ይተባበሩን።
#getu #ethiopia #healthalert #saveteacherzemene #heartsurgery #pacemaker #charityethiopia #communitysupport #addisababa #churchteachers #መምህርዘመነ #የልብሕክምና #የሕይወትአድንጥሪ #እርዳታ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
የሕይወት አድን ጥሪ
እህታችን መሠረት ፈንታቢልን (አስካለ ማርያምን) በጋራ እንታደጋት
ከ2010 ዓ.ም. ጀምሮ በኩላሊት ሕመም ስትሰቃይ የቆየችው እህታችን መሠረት ፈንታቢል፣ አሁን ላይ ሕይወቷን ለማዳን የእያንዳንዳችን የጋራ ርብርብ ያስፈልጋታል።
መሠረት በባህር ዳር፣ በጎንደርና በአዲስ አበባ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ለዓመታት ስትታከም ቆይታለች።
በ2015 ዓ.ም. አረጋዊ አባቷ ኩላሊታቸውን ቢሰጧትም፣ ከሁለት ቀን በኋላ ሳይሳካ ቀርቶ ኩላሊቱ ሥራ አቁሟል።
ከኩላሊቱ በተጨማሪ በ2017 ዓ.ም. የልብ ቧንቧ ጥበት አጋጥሟት የልብ ሕክምና አድርጋለች።
በአሁኑ ወቅት በየሳምንቱ ሦስት ጊዜ የዲያሊሲስ (Dialysis) ሕክምና እያደረገች ሲሆን፣ ይህ ሕክምና አጥንቷንና ሌላው ሰውነቷን እየጎዳው ይገኛል።
ልጆቿና ቤተሰቧ ካሉበት ጭንቀት እንዲገላገሉና መሠረት የተሻለ ሕክምና አግኝታ ወደ ጤናዋ እንድትመለስ የገንዘብ ድጋፍ ያስፈልጋታል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
1000706400544
አቢሲኒያ ባንክ (BoA)
230444447
https://gofund.me/0b08e84b...
ነገ በእኛም ላይ ምን እንደሚገጥመን አናውቅምና፣ ዛሬ ለወገን ደራሽ በመሆን እህታችንን እናሳክማት።
አቅማችሁ የፈቀደውን በመለገስና ይህንን መረጃ ለሌሎች በማጋራት (Share) እንተባበር።
#getu #ethiopia #healthalert #kidneyfailure #supportmeseret #addisababa #charityethiopia #communitysupport #savealife #እህታችንንእንታደጋት #የኩላሊትሕክምና #የሕይወትአድንጥሪ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
እህታችን መሠረት ፈንታቢልን (አስካለ ማርያምን) በጋራ እንታደጋት
ከ2010 ዓ.ም. ጀምሮ በኩላሊት ሕመም ስትሰቃይ የቆየችው እህታችን መሠረት ፈንታቢል፣ አሁን ላይ ሕይወቷን ለማዳን የእያንዳንዳችን የጋራ ርብርብ ያስፈልጋታል።
መሠረት በባህር ዳር፣ በጎንደርና በአዲስ አበባ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ለዓመታት ስትታከም ቆይታለች።
በ2015 ዓ.ም. አረጋዊ አባቷ ኩላሊታቸውን ቢሰጧትም፣ ከሁለት ቀን በኋላ ሳይሳካ ቀርቶ ኩላሊቱ ሥራ አቁሟል።
ከኩላሊቱ በተጨማሪ በ2017 ዓ.ም. የልብ ቧንቧ ጥበት አጋጥሟት የልብ ሕክምና አድርጋለች።
በአሁኑ ወቅት በየሳምንቱ ሦስት ጊዜ የዲያሊሲስ (Dialysis) ሕክምና እያደረገች ሲሆን፣ ይህ ሕክምና አጥንቷንና ሌላው ሰውነቷን እየጎዳው ይገኛል።
ልጆቿና ቤተሰቧ ካሉበት ጭንቀት እንዲገላገሉና መሠረት የተሻለ ሕክምና አግኝታ ወደ ጤናዋ እንድትመለስ የገንዘብ ድጋፍ ያስፈልጋታል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
1000706400544
አቢሲኒያ ባንክ (BoA)
230444447
https://gofund.me/0b08e84b...
ነገ በእኛም ላይ ምን እንደሚገጥመን አናውቅምና፣ ዛሬ ለወገን ደራሽ በመሆን እህታችንን እናሳክማት።
አቅማችሁ የፈቀደውን በመለገስና ይህንን መረጃ ለሌሎች በማጋራት (Share) እንተባበር።
#getu #ethiopia #healthalert #kidneyfailure #supportmeseret #addisababa #charityethiopia #communitysupport #savealife #እህታችንንእንታደጋት #የኩላሊትሕክምና #የሕይወትአድንጥሪ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
6 months ago
በሃዘን ለተጎዱ ቤተሰቦች እንድረስላቸው! 💔🙏
"ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፤ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ" (ሮሜ 12:15)
#ethiopia | በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ አካባቢ በሚገኘው የኮየ ፈንታ ደብረ ፀሐይ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን በበዓለ ጥምቀት ዕለት በአሳዛኝ የኤሌክትሪክ አደጋ አራት ወጣት አስተባባሪዎችን ማጣታችን ይታወሳል።
እነዚህ ወጣቶች በበዓሉ ድምቀት ሰረገላ በማዘጋጀት እና በማጓጓዝ ላይ እንዳሉ በኤሌክትሪክ ንኪኪ በተከሰተ አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ማህበረሰቡን በእጅጉ አሳዝኗል።
ይህ ክስተት የወጣቶቹን ቤተሰቦች ለከፍተኛ ችግር ዳርጓቸዋል። በተለይም፦
ከሟቾች መካከል የአቶ አበበ ተፈራ ባለቤት የ9 ወር ነፍሰ ጡር መሆናቸውና ልጆቻቸውም አሁን ካሉበት ቤት በኪራይ ምክንያት እንዲወጡ መደረጋቸው፤
የሟች አቶ ፍቃዱ ተክለየስ ቤተሰቦች የሚመገቡት የሌላቸው 5 ቤተሰቦች በችግር ላይ መውደቃቸው፤
ሌላኛው ሟች አቶ ሄሮጳ ማሞ የቤተሰቡ አስተዳዳሪና ብቸኛ ደጋፊ በመሆኑ ቤተሰቡ በከፍተኛ ሃዘንና ችግር ውስጥ መገኘቱ ሁኔታውን ይበልጥ አሳዛኝ ያደርገዋል።
ስለሆነም እነዚህን የተቸገሩ ቤተሰቦች ለመርዳት ከጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል።
ለተጎጂ ቤተሰቦች ተብሎ በተከፈተው የጋራ የባንክ አካውንት ድጋፍዎን ማድረግ ይችላሉ፦
💰 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000742754247
💰 አቢሲኒያ ባንክ፦ 249319147
የፊታችን ማክሰኞ የካቲት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በሚደረገው የቀጥታ ስርጭት ላይ በመሳተፍና ይህን መልዕክት ለሌሎች በማጋራት የድርሻዎን እንዲወጡ በትህትና እንጠይቃለን።
ፈጣሪ ለሟቾች መንግስተ ሰማያትን ያውርስልን፤ ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን ይስጥልን!
#emergencyappeal #charityethiopia #supportfamilies #humanitarianaid #eotc #communitysupport #ethiopiahelp
"ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፤ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ" (ሮሜ 12:15)
#ethiopia | በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ አካባቢ በሚገኘው የኮየ ፈንታ ደብረ ፀሐይ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን በበዓለ ጥምቀት ዕለት በአሳዛኝ የኤሌክትሪክ አደጋ አራት ወጣት አስተባባሪዎችን ማጣታችን ይታወሳል።
እነዚህ ወጣቶች በበዓሉ ድምቀት ሰረገላ በማዘጋጀት እና በማጓጓዝ ላይ እንዳሉ በኤሌክትሪክ ንኪኪ በተከሰተ አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ማህበረሰቡን በእጅጉ አሳዝኗል።
ይህ ክስተት የወጣቶቹን ቤተሰቦች ለከፍተኛ ችግር ዳርጓቸዋል። በተለይም፦
ከሟቾች መካከል የአቶ አበበ ተፈራ ባለቤት የ9 ወር ነፍሰ ጡር መሆናቸውና ልጆቻቸውም አሁን ካሉበት ቤት በኪራይ ምክንያት እንዲወጡ መደረጋቸው፤
የሟች አቶ ፍቃዱ ተክለየስ ቤተሰቦች የሚመገቡት የሌላቸው 5 ቤተሰቦች በችግር ላይ መውደቃቸው፤
ሌላኛው ሟች አቶ ሄሮጳ ማሞ የቤተሰቡ አስተዳዳሪና ብቸኛ ደጋፊ በመሆኑ ቤተሰቡ በከፍተኛ ሃዘንና ችግር ውስጥ መገኘቱ ሁኔታውን ይበልጥ አሳዛኝ ያደርገዋል።
ስለሆነም እነዚህን የተቸገሩ ቤተሰቦች ለመርዳት ከጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል።
ለተጎጂ ቤተሰቦች ተብሎ በተከፈተው የጋራ የባንክ አካውንት ድጋፍዎን ማድረግ ይችላሉ፦
💰 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000742754247
💰 አቢሲኒያ ባንክ፦ 249319147
የፊታችን ማክሰኞ የካቲት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በሚደረገው የቀጥታ ስርጭት ላይ በመሳተፍና ይህን መልዕክት ለሌሎች በማጋራት የድርሻዎን እንዲወጡ በትህትና እንጠይቃለን።
ፈጣሪ ለሟቾች መንግስተ ሰማያትን ያውርስልን፤ ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን ይስጥልን!
#emergencyappeal #charityethiopia #supportfamilies #humanitarianaid #eotc #communitysupport #ethiopiahelp
Comments