11 days ago
"ሰላም ፋስት መረጃዎች ይህ ምስል እና ቪዲዮ በርካቶች "የአርሲ ኦርቶዶክሶች" ተብሎ እየተሰራጨ ይገኛል ነገሩ ግን አርሲ አይደለም በአማራ ክልል ማኖ ቀጨኔ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያ የአከባቢው ገበሬ አዲስ ላሰራው ቤተክርስቲያን በከተማ የተሰሩ የቤተክርስቲያን ንዋይተ ቅድሳትን ይዞ ወደ አዲሱ ቤተ ክርስቲያን ሲሄድ የሚያሳይ ምስል ነው።
በቪዲዮ ላይ የሚያውቁን የከተማ ሰዎች እየደወሉ ምን ሆናችሁ ነው? በማለት እየተጨነቁ ስለሆነ እኛ ጋር ሰላም መሆናችን የሚዘዋወረው ፎቶ እና ቪዲዮ ለአዲሱ ቤተክርስቲያን መሆኑን አሳውቁልን። በአርሲ የተፈጸመውን ተግባር ሙሉ በሙሉ እናወግዛለን።"
በቪዲዮ ላይ የሚያውቁን የከተማ ሰዎች እየደወሉ ምን ሆናችሁ ነው? በማለት እየተጨነቁ ስለሆነ እኛ ጋር ሰላም መሆናችን የሚዘዋወረው ፎቶ እና ቪዲዮ ለአዲሱ ቤተክርስቲያን መሆኑን አሳውቁልን። በአርሲ የተፈጸመውን ተግባር ሙሉ በሙሉ እናወግዛለን።"
15 days ago
ዛሬ የዌብሳይት ዲዛይነሮች ቀን ነው። ዓለማችን ወደ ዲጅታል እየተቀየረች ባለችበት በዚህ ወቅት ድርጅታችሁ እና ቢዝነሳናችሁ መዘመን ግድ ነው።
ሱራፌል ተፈሪ ይባል በጣም ጎበዝ የሆነ የዌብሳይት ዲዛይነር ነው። የፋስት መረጃን ጨምሮ በርካታ ሚዲያዎችን ድረ ገጽ ዲዛይን የሰራው ይህ ጎበዝ ወጣት ነው። "Yene IT solution" የተሰኘ ተቋሙ ምርጥ ምርጥ ድረ ገጾችን ከAI ጋር አስተሳስሮ ይሰራል።
ሱራፌልን ለማግኘት
+25193333-2325
itsolutionyenevibe.com
ሱራፌል ተፈሪ ይባል በጣም ጎበዝ የሆነ የዌብሳይት ዲዛይነር ነው። የፋስት መረጃን ጨምሮ በርካታ ሚዲያዎችን ድረ ገጽ ዲዛይን የሰራው ይህ ጎበዝ ወጣት ነው። "Yene IT solution" የተሰኘ ተቋሙ ምርጥ ምርጥ ድረ ገጾችን ከAI ጋር አስተሳስሮ ይሰራል።
ሱራፌልን ለማግኘት
+25193333-2325
itsolutionyenevibe.com
1 month ago
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ባለውለታ የአትሌት የብርጓል መለሰ ድንገተኛ እረፍት
#fastmereja I በተለያዩ ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ውድድሮች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ስታደርግ የቆየችው ዝነኛው አትሌት የብርጓል መለሰ፣ ለመጪው የካናዳው ኦታዋ ማራቶን ዝግጅት ላይ እያለች ዛሬ ጠዋት በድንገት ህይወቷ አልፏል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በጀግናዋ አትሌት ድንገተኛ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል።
አትሌት የብርጓል መለሰ በስፖርታዊ ጨዋታዋ ለአፍሪካ እና ለዓለም አቀፍ መድረኮች አዲስ አልነበረችም። እ.ኤ.አ በ2015 በኮንጎ ብራዛቪል በተካሄደው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች በግማሽ ማራቶን የነሐስ ሜዳሊያ በማሸነፍ ሀገሯን አስከብራለች። በታዋቂው የቺካጎ ማራቶን የብር ሜዳሊያ ባለቤት ከመሆኗም ባሻገር፣ በሻንጋይ፣ ፕራግ እና ሂውስተን ማራቶኖች ላይ የድል አክሊልን ተቀዳጅታለች። በተጨማሪም በፓሪስ ግማሽ ማራቶን ለሁለት ጊዜያት እና በሊዝበን ግማሽ ማራቶን አሸናፊ በመሆን ስሟ በደመቀ ሁኔታ የሚነሳ ብርቱ አትሌት ነበረች።
ለተሳትፎ በዝግጅት ላይ በነበረችበት ወቅት የተሰማው ይህ አስደንጋጭ ዜና በመላው ስፖርት አፍቃሪ ዘንድ ታላቅ ሀዘንን ፈጥሯል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአትሌቷ ቤተሰቦች፣ ወዳጆች እና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መፅናናትን ተመኝቷል።
የ"ፋስት መረጃ" ዝግጅት ክፍልም በጀግናዋ አትሌት ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቿ መፅናናትን ይመኛል።
#fastmereja I በተለያዩ ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ውድድሮች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ስታደርግ የቆየችው ዝነኛው አትሌት የብርጓል መለሰ፣ ለመጪው የካናዳው ኦታዋ ማራቶን ዝግጅት ላይ እያለች ዛሬ ጠዋት በድንገት ህይወቷ አልፏል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በጀግናዋ አትሌት ድንገተኛ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል።
አትሌት የብርጓል መለሰ በስፖርታዊ ጨዋታዋ ለአፍሪካ እና ለዓለም አቀፍ መድረኮች አዲስ አልነበረችም። እ.ኤ.አ በ2015 በኮንጎ ብራዛቪል በተካሄደው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች በግማሽ ማራቶን የነሐስ ሜዳሊያ በማሸነፍ ሀገሯን አስከብራለች። በታዋቂው የቺካጎ ማራቶን የብር ሜዳሊያ ባለቤት ከመሆኗም ባሻገር፣ በሻንጋይ፣ ፕራግ እና ሂውስተን ማራቶኖች ላይ የድል አክሊልን ተቀዳጅታለች። በተጨማሪም በፓሪስ ግማሽ ማራቶን ለሁለት ጊዜያት እና በሊዝበን ግማሽ ማራቶን አሸናፊ በመሆን ስሟ በደመቀ ሁኔታ የሚነሳ ብርቱ አትሌት ነበረች።
ለተሳትፎ በዝግጅት ላይ በነበረችበት ወቅት የተሰማው ይህ አስደንጋጭ ዜና በመላው ስፖርት አፍቃሪ ዘንድ ታላቅ ሀዘንን ፈጥሯል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአትሌቷ ቤተሰቦች፣ ወዳጆች እና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መፅናናትን ተመኝቷል።
የ"ፋስት መረጃ" ዝግጅት ክፍልም በጀግናዋ አትሌት ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቿ መፅናናትን ይመኛል።
1 month ago
ዲኬ ሆልዲንግስ የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ የውጭ ምንዛሬን እያዳነ መሆኑን ገለጸ
#fastmereja I በአራተኛው ዙር "የኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ የተሳተፈው ዲኬ ሆልዲንግስ (DK Holdings)፣ ትራክተሮችንና የግብርና መሣሪያዎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የውጭ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ መተካት መቻሉን አስታወቀ። ኩባንያው በአሁኑ ወቅት ምርቶቹን እስከ 70 በመቶ የሚደርስ የሀገር ውስጥ ግብዓት በመጠቀም እያመረተ ይገኛል።
የኩባንያው ተወካይ አቶ ታረቀኝ ይልማ ለፋስት መረጃ እንደገለጹት፣ ድርጅቱ በግብርናው ዘርፍ ያለውን የቴክኖሎጂ ክፍተት ለመሙላት ሚዛን አማን ላይ ግዙፍ የትራክተር ማምረቻ ፋብሪካ እየገነባ ነው። ከትራክተር ባሻገር እንደ ማረሻ፣ መከትከቻ፣ የበቆሎ መፈልፈያ እና መውቂያ ያሉ የግብርና መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎችና ማሽነሪዎች እያመረተ ለገበሬው እያቀረበ ይገኛል።
ኩባንያው የኤሌክትሪክ ፍጆታን የሚቆጥቡና የክልሎችን ባህላዊ እሴት የሚያንፀባርቁ "ስማርት ፖሎችን" (ዘመናዊ የጎዳና መብራት ምሶሶዎች) በማምረት በጎንደር፣ በሚዛንና በቢሾፍቱ ከተሞች ተግባራዊ አድርጓል።
ቀደም ሲል 100 ፐርሰንት ከውጭ ይገቡ የነበሩ ትራንስፎርመሮችን የሀገሪቱን የጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ በሀገር ውስጥ እያመረተ ነው። ለከተማ ውበትና ለጽዳት አገልግሎት የሚውሉ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ጋንዳዎችን በስፋት እያቀረበ ይገኛል።
ዲኬ ሆልዲንግስ እነዚህን ምርቶች በሀገር ውስጥ ማምረቱ በከፍተኛ ዶላር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም የኢንዱስትሪ ማሽኖችን የመገጣጠም እና የመተከል ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
#fastmereja I በአራተኛው ዙር "የኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ የተሳተፈው ዲኬ ሆልዲንግስ (DK Holdings)፣ ትራክተሮችንና የግብርና መሣሪያዎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የውጭ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ መተካት መቻሉን አስታወቀ። ኩባንያው በአሁኑ ወቅት ምርቶቹን እስከ 70 በመቶ የሚደርስ የሀገር ውስጥ ግብዓት በመጠቀም እያመረተ ይገኛል።
የኩባንያው ተወካይ አቶ ታረቀኝ ይልማ ለፋስት መረጃ እንደገለጹት፣ ድርጅቱ በግብርናው ዘርፍ ያለውን የቴክኖሎጂ ክፍተት ለመሙላት ሚዛን አማን ላይ ግዙፍ የትራክተር ማምረቻ ፋብሪካ እየገነባ ነው። ከትራክተር ባሻገር እንደ ማረሻ፣ መከትከቻ፣ የበቆሎ መፈልፈያ እና መውቂያ ያሉ የግብርና መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎችና ማሽነሪዎች እያመረተ ለገበሬው እያቀረበ ይገኛል።
ኩባንያው የኤሌክትሪክ ፍጆታን የሚቆጥቡና የክልሎችን ባህላዊ እሴት የሚያንፀባርቁ "ስማርት ፖሎችን" (ዘመናዊ የጎዳና መብራት ምሶሶዎች) በማምረት በጎንደር፣ በሚዛንና በቢሾፍቱ ከተሞች ተግባራዊ አድርጓል።
ቀደም ሲል 100 ፐርሰንት ከውጭ ይገቡ የነበሩ ትራንስፎርመሮችን የሀገሪቱን የጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ በሀገር ውስጥ እያመረተ ነው። ለከተማ ውበትና ለጽዳት አገልግሎት የሚውሉ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ጋንዳዎችን በስፋት እያቀረበ ይገኛል።
ዲኬ ሆልዲንግስ እነዚህን ምርቶች በሀገር ውስጥ ማምረቱ በከፍተኛ ዶላር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም የኢንዱስትሪ ማሽኖችን የመገጣጠም እና የመተከል ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
2 months ago
በአሶሳ ዞን በደረሰ የባስ መገልበጥ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ
#fastmereja I በአሶሳ ዞን በመንጌ ወረዳ በደረሰ አስከፊ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ፣ በ24 ተሳፋሪዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደረሰ።
አደጋው የደረሰው ዛሬ ሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ገደማ ሲሆን፣ መነሻውን በሆሞሻ ወረዳ ፆሬ 6ኛ ካምፕ መገንጠያ አድርጎ ወደ ሽርቆሌ ወረዳ ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 - 01220 ቤ.ጉ የሆነ የሕዝብ ማመላለሻ ባስ በመንጌ ወረዳ "አቧራ ቀበሌ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ቁልቁለት ላይ ሲደርስ ተገልብጧል።
እንደ አሶሳ ዞን ፖሊስ መምሪያ መረጃ ከሆነ፣ የአደጋው መንስኤ በዝርዝር እየተጣራ ቢሆንም በቅድመ ምርመራ ግን ተሽከርካሪው ከልክ በላይ ጭነት ጭኖ ይጓዝ እንደነበር ታውቋል። ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች ወደ ሕክምና ተቋማት ተወስደው እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
ፖሊስ አሽከርካሪዎች የትራፊክ ሕግን በማክበርና የጭነት ልክን በመጠበቅ የዜጎችን ሕይወት እንዲታደጉ ጥሪ አቅርቧል። የ"ፋስት መረጃ" ዝግጅት ክፍል በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦች መጽናናትን ይመኛል።
#fastmereja I በአሶሳ ዞን በመንጌ ወረዳ በደረሰ አስከፊ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ፣ በ24 ተሳፋሪዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደረሰ።
አደጋው የደረሰው ዛሬ ሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ገደማ ሲሆን፣ መነሻውን በሆሞሻ ወረዳ ፆሬ 6ኛ ካምፕ መገንጠያ አድርጎ ወደ ሽርቆሌ ወረዳ ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 - 01220 ቤ.ጉ የሆነ የሕዝብ ማመላለሻ ባስ በመንጌ ወረዳ "አቧራ ቀበሌ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ቁልቁለት ላይ ሲደርስ ተገልብጧል።
እንደ አሶሳ ዞን ፖሊስ መምሪያ መረጃ ከሆነ፣ የአደጋው መንስኤ በዝርዝር እየተጣራ ቢሆንም በቅድመ ምርመራ ግን ተሽከርካሪው ከልክ በላይ ጭነት ጭኖ ይጓዝ እንደነበር ታውቋል። ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች ወደ ሕክምና ተቋማት ተወስደው እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
ፖሊስ አሽከርካሪዎች የትራፊክ ሕግን በማክበርና የጭነት ልክን በመጠበቅ የዜጎችን ሕይወት እንዲታደጉ ጥሪ አቅርቧል። የ"ፋስት መረጃ" ዝግጅት ክፍል በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦች መጽናናትን ይመኛል።
2 months ago
አንጋፋው የጤና ባለሙያ ላይ የተፈጸመው ድብደባ
#fastmereja I በባሌ ዞን ሮቤ ከተማ መናኸሪያ ውስጥ የ35 ዓመታት የሥራ ልምድ ያላቸው አንጋፋ የጤና ባለሙያ የደረሰባቸው የመንጋ ድብደባ ህዝቡን አስቆጥቷል። ግለሰቡ ለረጅም ዓመታት በጤናው ዘርፍ ሀገራቸውን ሲያገለግሉ የቆዩና በአሁኑ ወቅት የጡረታ ሰነዶቻቸውን እያስተካከሉ የሚገኙ አባት መሆናቸው ታውቋል።
ተጎጂው አቶ ዋቆ ከዲር ይባላሉ። ግለሰቡ በጤናው ዘርፍ ለ35 ዓመታት ያህል በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ማለትም በቄለም ወለጋ ሆስፒታል፣ በጎባ ሆስፒታል፣ በጊኒር ሆስፒታል፣ በራይቱ ጤና ጣቢያ ሲያገለግሉ የቆዩ ባለሙያ ናቸው።
አቶ ዋቆ አገልግሎታቸውን አጠናቅቀው የጡረታ መብታቸውን ለማስከበር ሰነዶቻቸውን በማደራጀት ላይ በነበሩበት ወቅት፣ በሮቤ ከተማ መነኸሪያ ውስጥ ማንነታቸው ባልታወቁ ግለሰቦች አማካኝነት (ቪዲዮ በፋስት መረጃ ቴሌግራም ላይ አለ) ድብደባ ተፈጽሞባቸዋል።
እንደ ቤተሰብ አባላትና የቅርብ ወዳጆቻቸው ገለጻ፣ አቶ ዋቆ በ2009 ዓ.ም ከሶማሌ ክልል ጋር በነበረው የድንበር ግጭት ወቅት ዛሬ ደጋፊ ሊሆኑ የሚችሉ ልጆቻቸውን በሞት ያጡ አባት ናቸው። ይህን መሰል በሀገር ባለውለታ ላይ የተፈጸመ ግፍ በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል።
ቪዲዮ 📍https://t.me/fastmereja
#fastmereja I በባሌ ዞን ሮቤ ከተማ መናኸሪያ ውስጥ የ35 ዓመታት የሥራ ልምድ ያላቸው አንጋፋ የጤና ባለሙያ የደረሰባቸው የመንጋ ድብደባ ህዝቡን አስቆጥቷል። ግለሰቡ ለረጅም ዓመታት በጤናው ዘርፍ ሀገራቸውን ሲያገለግሉ የቆዩና በአሁኑ ወቅት የጡረታ ሰነዶቻቸውን እያስተካከሉ የሚገኙ አባት መሆናቸው ታውቋል።
ተጎጂው አቶ ዋቆ ከዲር ይባላሉ። ግለሰቡ በጤናው ዘርፍ ለ35 ዓመታት ያህል በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ማለትም በቄለም ወለጋ ሆስፒታል፣ በጎባ ሆስፒታል፣ በጊኒር ሆስፒታል፣ በራይቱ ጤና ጣቢያ ሲያገለግሉ የቆዩ ባለሙያ ናቸው።
አቶ ዋቆ አገልግሎታቸውን አጠናቅቀው የጡረታ መብታቸውን ለማስከበር ሰነዶቻቸውን በማደራጀት ላይ በነበሩበት ወቅት፣ በሮቤ ከተማ መነኸሪያ ውስጥ ማንነታቸው ባልታወቁ ግለሰቦች አማካኝነት (ቪዲዮ በፋስት መረጃ ቴሌግራም ላይ አለ) ድብደባ ተፈጽሞባቸዋል።
እንደ ቤተሰብ አባላትና የቅርብ ወዳጆቻቸው ገለጻ፣ አቶ ዋቆ በ2009 ዓ.ም ከሶማሌ ክልል ጋር በነበረው የድንበር ግጭት ወቅት ዛሬ ደጋፊ ሊሆኑ የሚችሉ ልጆቻቸውን በሞት ያጡ አባት ናቸው። ይህን መሰል በሀገር ባለውለታ ላይ የተፈጸመ ግፍ በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል።
ቪዲዮ 📍https://t.me/fastmereja
2 months ago
በትራፊክ አደጋ ጉዳት ደርሶባት የነበረችው ህፃን ሔርማ ስንታየሁ ህይወቷ አለፈ
#fastmereja I በተባበሩት አደባባይ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ምክንያት በፅኑ ቆስላ በህክምና ስትረዳ የቆየችው ህፃን ሔርማ ስንታየሁ (እኩቹ) በዛሬው እለት ህይወቷ ማለፉ ተረጋገጠ። የህፃኗ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ሚያዝያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሰዓሊተ ምህረት ማርያም ካቴድራል ተፈጽሟል።
መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም በደረሰው በዚሁ የትራፊክ አደጋ፣ የአንድ ሰው ህይወት ወዲያውኑ ማለፉንና ሶስት ሰዎች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው እንደነበር ፖሊስ መግለጹ ይታወሳል። ህፃን ሔርማ በደረሰባት ከባድ ጉዳት ላለፉት ቀናት በህክምና ስትረዳ ብትቆይም፣ ጥረቱ ሳይሳካ ቀርቶ ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
"ፋስት መረጃ" ለቤተሰቦቿ እና ለወዳጅ ዘመዶቿ መጽናናትን ይመኛል።
#fastmereja I በተባበሩት አደባባይ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ምክንያት በፅኑ ቆስላ በህክምና ስትረዳ የቆየችው ህፃን ሔርማ ስንታየሁ (እኩቹ) በዛሬው እለት ህይወቷ ማለፉ ተረጋገጠ። የህፃኗ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ሚያዝያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሰዓሊተ ምህረት ማርያም ካቴድራል ተፈጽሟል።
መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም በደረሰው በዚሁ የትራፊክ አደጋ፣ የአንድ ሰው ህይወት ወዲያውኑ ማለፉንና ሶስት ሰዎች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው እንደነበር ፖሊስ መግለጹ ይታወሳል። ህፃን ሔርማ በደረሰባት ከባድ ጉዳት ላለፉት ቀናት በህክምና ስትረዳ ብትቆይም፣ ጥረቱ ሳይሳካ ቀርቶ ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
"ፋስት መረጃ" ለቤተሰቦቿ እና ለወዳጅ ዘመዶቿ መጽናናትን ይመኛል።
2 months ago
ሰብአዊነት በማደያ ሰልፍ
#fastmereja I በቀናት የነዳጅ ጥበቃ ሰልፍ ለተሰላቹ ሹፌሮች "ሲርለና" የተባለ በጎ አድራጎት ድርጅት ምግብና መጠጥ በማቅረብ አጋርነቱን አሳየ። ድርጅቱ በነዳጅ ማደያዎች አካባቢ ሌሊትና ቀን ለሚሰቃዩ አሽከርካሪዎች የሞራል ስንቅ ሆኗል።
ባለፉት ቀናት በነዳጅ እጥረት ምክንያት በርካታ አሽከርካሪዎች መኪናቸውን በማደያዎች ሰልፍ ላይ አቁመው አስቸጋሪ ሁኔታዎችን እያለፉ ይገኛሉ። ይህንን የተመለከተው ሲርለና በጎ አድራጎት ድርጅት፣ አባላቱን በማሰማራት ምግብ፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ፣ ቡና እና ሻይ በማቅረብ ሹፌሮችን "አይዟችሁ" ብሏል።
ይህ በጎ ተግባር በሹፌሮች ዘንድ ትልቅ ደስታን የፈጠረ ሲሆን፣ "በዚህ አስቸጋሪ ወቅት እንዲህ ያለ አጋርነት ማየት ትልቅ የሞራል ጥንካሬ ይሰጠናል" ሲሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ድርጅቱ ያከናወነው ይህ ተግባር በችግር ወቅት መረዳዳትን የሚያሳይ እና "ይበል" የሚያሰኝ አርአያነት ያለው ስራ ሆኖ ተመዝግቧል። የ"ፋስት መረጃ" ዝግጅት ክፍልም እንዲህ ያሉ በጎ አድራጊዎችን ማበረታታት ለህብረተሰቡ አጋርነት ወሳኝ መሆኑን ያምናል።
#fastmereja I በቀናት የነዳጅ ጥበቃ ሰልፍ ለተሰላቹ ሹፌሮች "ሲርለና" የተባለ በጎ አድራጎት ድርጅት ምግብና መጠጥ በማቅረብ አጋርነቱን አሳየ። ድርጅቱ በነዳጅ ማደያዎች አካባቢ ሌሊትና ቀን ለሚሰቃዩ አሽከርካሪዎች የሞራል ስንቅ ሆኗል።
ባለፉት ቀናት በነዳጅ እጥረት ምክንያት በርካታ አሽከርካሪዎች መኪናቸውን በማደያዎች ሰልፍ ላይ አቁመው አስቸጋሪ ሁኔታዎችን እያለፉ ይገኛሉ። ይህንን የተመለከተው ሲርለና በጎ አድራጎት ድርጅት፣ አባላቱን በማሰማራት ምግብ፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ፣ ቡና እና ሻይ በማቅረብ ሹፌሮችን "አይዟችሁ" ብሏል።
ይህ በጎ ተግባር በሹፌሮች ዘንድ ትልቅ ደስታን የፈጠረ ሲሆን፣ "በዚህ አስቸጋሪ ወቅት እንዲህ ያለ አጋርነት ማየት ትልቅ የሞራል ጥንካሬ ይሰጠናል" ሲሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ድርጅቱ ያከናወነው ይህ ተግባር በችግር ወቅት መረዳዳትን የሚያሳይ እና "ይበል" የሚያሰኝ አርአያነት ያለው ስራ ሆኖ ተመዝግቧል። የ"ፋስት መረጃ" ዝግጅት ክፍልም እንዲህ ያሉ በጎ አድራጊዎችን ማበረታታት ለህብረተሰቡ አጋርነት ወሳኝ መሆኑን ያምናል።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ሚሊዮን ድሪባ ይባላል ልክ የዛሬ አመት በአዲስ አበባ ጡት ማስያዣ በማድረግ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች እየቀረጸ በቲክቶክ በሚለቃቸው ቪዲዮዎች በአዲስ አበባ ፖሊስ ተይዞ ክስ እንደተመሰረተበት በፋስት መረጃ ተዘግቦ ነበር።
ከስህተቱ ያልተማረው ወጣት ሚሊዮን ድሪባ ከሀገር በመውጣት በስደት ኑሮውን የጀመረ ቢሆንም በቲክቶክ የሚለቀውን ቪዲዮ ግን አላቆመም ነበር በተለይ በእስልምና እና በኦርቶዶክስ እምነት ላይ በሚያስተላልፋቸው የጥላቻ ንግግሮች እና ድርጊቶች በርካቶችን ሲያስቆጣ ነበር። የእስልምና እምነት ተከታዮች ባደረጉት ክትትል የሚኖርበት አድራሻ በማግኘት በኬኒያ ይዘው ለፖሊስ አሳልፈው በመስጠት በስደት በሚኖርበት ሀገር ክስ መስርተውበታል።
ሚሊዮን በተያዘበት ወቅት በማልቀስ ይቅርታ እጠይቃለሁ ተውኝ በማለት ቢያለቅስም ለፖሊስ አሳልፈው ሰጥተውታል።
ቪዲዮን በቴሌግራም ገጻችን ያገኙታል
📌 https://t.me/fastmereja
📌 https://t.me/fastmereja
ከስህተቱ ያልተማረው ወጣት ሚሊዮን ድሪባ ከሀገር በመውጣት በስደት ኑሮውን የጀመረ ቢሆንም በቲክቶክ የሚለቀውን ቪዲዮ ግን አላቆመም ነበር በተለይ በእስልምና እና በኦርቶዶክስ እምነት ላይ በሚያስተላልፋቸው የጥላቻ ንግግሮች እና ድርጊቶች በርካቶችን ሲያስቆጣ ነበር። የእስልምና እምነት ተከታዮች ባደረጉት ክትትል የሚኖርበት አድራሻ በማግኘት በኬኒያ ይዘው ለፖሊስ አሳልፈው በመስጠት በስደት በሚኖርበት ሀገር ክስ መስርተውበታል።
ሚሊዮን በተያዘበት ወቅት በማልቀስ ይቅርታ እጠይቃለሁ ተውኝ በማለት ቢያለቅስም ለፖሊስ አሳልፈው ሰጥተውታል።
ቪዲዮን በቴሌግራም ገጻችን ያገኙታል
📌 https://t.me/fastmereja
📌 https://t.me/fastmereja
3 months ago
የሜትር ታክሲ ድርጅቶች "የቴክኖሎጂ አውታር ወይንስ የገንዘብ መሰብሰቢያ?" ከአሽከርካሪዎች የቀረበ ከባድ ወቀሳ
በፋስት መረጃ ሪፖርተር #fastmereja I በኢትዮጵያ የትራንስፖርት ዘርፍ ውስጥ አብዮት የፈጠሩት የሜትር ታክሲ ድርጅቶች፣ በአሁኑ ወቅት በአሽከርካሪዎችና በባለንብረቶች ዘንድ "ቸልተኞች" የሚል ስያሜ እየተሰጣቸው ነው። ድርጅቶቹ ከእያንዳንዱ ጉዞ ኮሚሽን ከመሰብሰብ ባለፈ፣ አሽከርካሪው በየመንገዱ ለሚገጥሙት መዋቅራዊ ችግሮች ድምጽ ለመሆን ፍቃደኛ አይደሉም የሚሉ ቅሬታዎች በዝርዝር እየቀረቡ ነው።
📍የመቆሚያና የመጫኛ ቦታ እጥረት
አሽከርካሪዎች ከሚያነሱት ዋነኛ ችግር አንዱ ተሳፋሪ ለመጫንና ለማውረድ፣ እንዲሁም ትዕዛዝ እስኪመጣ ቆመው የሚጠብቁበት ቦታ አለመኖሩ ነው።
ድርጅቶቹ በሺዎች የሚቆጠሩ መኪኖችን ወደ ስራ ቢያሰማሩም፣ እነዚህ መኪኖች የት ቆመው ትዕዛዝ እንደሚጠብቁ ከአስተዳደሩ ጋር ተነጋግረው መፍትሄ አላመጡም።
ተሳፋሪ ለመጫን ለአፍታ የቆመ አሽከርካሪ በትራፊክ ፖሊሶች "ህገ-ወጥ ማቆም" ተብሎ ለከፍተኛ ቅጣት ይዳረጋል። ድርጅቶቹ ግን ይህንን የአሰራር ችግር ለመፍታት ከመንግስት ጋር ድርድር ሲያደርጉ አይታዩም።
📍የበዙ ቅጣቶችና የአሽከርካሪው መከላከል አቅም ማጣት
በአሁኑ ወቅት የትራፊክ ቅጣቶች ከመጠን በላይ መጨመራቸው ይታወቃል። አሽከርካሪዎች እንደሚሉት፦
"ተሳፋሪው በፈለገበት ቦታ ቁም ይላል፤ እምቢ ካልን መጥፎ ደረጃ (Rating) ይሰጡናል። ከቆምን ደግሞ ፖሊስ ይቀጣናል።"
ድርጅቶቹ አሽከርካሪዎቻቸው በስራ ላይ እያሉ ለሚገጥማቸው አድሏዊ ቅጣት የህግ ከለላ ወይም ድምጽ የመሆን ዝንባሌ የላቸውም።
📍"የሚቆጥረው አይቆጥርም" የቴክኖሎጂ ስህተቶችና የታሪፍ ኢ-ፍትሃዊነት
ሌላው አሳሳቢ ቅሬታ በድርጅቶቹ መተግበሪያ (App) ላይ የሚታየው የርቀትና የዋጋ ስሌት አለመጣጣም ነው።
መተግበሪያዎቹ ብዙ ጊዜ የሚሰላው በኪሎሜትር እንጂ በትራፊክ መጨናነቅ ውስጥ ለሚባክነው ጊዜ እና ርቀት ተገቢውን ክፍያ አያካትቱም።
"አፕሊኬሽኑ የሚቆጥረው ርቀትና መኪናው በትክክል የሄደበት ርቀት አይጣጣምም፤ በዚህም የተነሳ አሽከርካሪው የሚገባውን ክፍያ አያገኝም" ሲሉ ቅሬታቸውን ይገልጻሉ።
📍የታክስ ጫና እና የኮሚሽን ግትርነት
የነዳጅ ዋጋ በየጊዜው ቢጨምርም፣ ድርጅቶቹ የሚወስዱት የኮሚሽን መቶኛ ግን ዝቅ እንዲል አይደረግም።
ባለንብረቶች እንደሚሉት ድርጅቶቹ ከመንግስት ጋር ተነጋግረው ለአሽከርካሪዎች የነዳጅ ድጎማ ወይም የቀለለ የታክስ ስርዓት እንዲዘረጋ ግፊት ማድረግ ሲገባቸው፣ ትኩረታቸው ኮሚሽን መሰብሰብ ላይ ብቻ ሆኗል።
📍ማጠቃለያ
አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች ድርጅቶቹን "ፕላትፎርሙን ብቻ ዘርግቶ ገንዘብ መሰብሰብ እንጂ ለአሽከርካሪው መብትና ለስራው ምቹ ሁኔታ መፈጠር ግድ የማይላቸው ከሆነ፣ ዘርፉ ወደ ቀውስ ሊያመራ ይችላል" ሲሉ የዘርፉ ተዋንያን ያስጠነቅቃሉ።
በፋስት መረጃ ሪፖርተር #fastmereja I በኢትዮጵያ የትራንስፖርት ዘርፍ ውስጥ አብዮት የፈጠሩት የሜትር ታክሲ ድርጅቶች፣ በአሁኑ ወቅት በአሽከርካሪዎችና በባለንብረቶች ዘንድ "ቸልተኞች" የሚል ስያሜ እየተሰጣቸው ነው። ድርጅቶቹ ከእያንዳንዱ ጉዞ ኮሚሽን ከመሰብሰብ ባለፈ፣ አሽከርካሪው በየመንገዱ ለሚገጥሙት መዋቅራዊ ችግሮች ድምጽ ለመሆን ፍቃደኛ አይደሉም የሚሉ ቅሬታዎች በዝርዝር እየቀረቡ ነው።
📍የመቆሚያና የመጫኛ ቦታ እጥረት
አሽከርካሪዎች ከሚያነሱት ዋነኛ ችግር አንዱ ተሳፋሪ ለመጫንና ለማውረድ፣ እንዲሁም ትዕዛዝ እስኪመጣ ቆመው የሚጠብቁበት ቦታ አለመኖሩ ነው።
ድርጅቶቹ በሺዎች የሚቆጠሩ መኪኖችን ወደ ስራ ቢያሰማሩም፣ እነዚህ መኪኖች የት ቆመው ትዕዛዝ እንደሚጠብቁ ከአስተዳደሩ ጋር ተነጋግረው መፍትሄ አላመጡም።
ተሳፋሪ ለመጫን ለአፍታ የቆመ አሽከርካሪ በትራፊክ ፖሊሶች "ህገ-ወጥ ማቆም" ተብሎ ለከፍተኛ ቅጣት ይዳረጋል። ድርጅቶቹ ግን ይህንን የአሰራር ችግር ለመፍታት ከመንግስት ጋር ድርድር ሲያደርጉ አይታዩም።
📍የበዙ ቅጣቶችና የአሽከርካሪው መከላከል አቅም ማጣት
በአሁኑ ወቅት የትራፊክ ቅጣቶች ከመጠን በላይ መጨመራቸው ይታወቃል። አሽከርካሪዎች እንደሚሉት፦
"ተሳፋሪው በፈለገበት ቦታ ቁም ይላል፤ እምቢ ካልን መጥፎ ደረጃ (Rating) ይሰጡናል። ከቆምን ደግሞ ፖሊስ ይቀጣናል።"
ድርጅቶቹ አሽከርካሪዎቻቸው በስራ ላይ እያሉ ለሚገጥማቸው አድሏዊ ቅጣት የህግ ከለላ ወይም ድምጽ የመሆን ዝንባሌ የላቸውም።
📍"የሚቆጥረው አይቆጥርም" የቴክኖሎጂ ስህተቶችና የታሪፍ ኢ-ፍትሃዊነት
ሌላው አሳሳቢ ቅሬታ በድርጅቶቹ መተግበሪያ (App) ላይ የሚታየው የርቀትና የዋጋ ስሌት አለመጣጣም ነው።
መተግበሪያዎቹ ብዙ ጊዜ የሚሰላው በኪሎሜትር እንጂ በትራፊክ መጨናነቅ ውስጥ ለሚባክነው ጊዜ እና ርቀት ተገቢውን ክፍያ አያካትቱም።
"አፕሊኬሽኑ የሚቆጥረው ርቀትና መኪናው በትክክል የሄደበት ርቀት አይጣጣምም፤ በዚህም የተነሳ አሽከርካሪው የሚገባውን ክፍያ አያገኝም" ሲሉ ቅሬታቸውን ይገልጻሉ።
📍የታክስ ጫና እና የኮሚሽን ግትርነት
የነዳጅ ዋጋ በየጊዜው ቢጨምርም፣ ድርጅቶቹ የሚወስዱት የኮሚሽን መቶኛ ግን ዝቅ እንዲል አይደረግም።
ባለንብረቶች እንደሚሉት ድርጅቶቹ ከመንግስት ጋር ተነጋግረው ለአሽከርካሪዎች የነዳጅ ድጎማ ወይም የቀለለ የታክስ ስርዓት እንዲዘረጋ ግፊት ማድረግ ሲገባቸው፣ ትኩረታቸው ኮሚሽን መሰብሰብ ላይ ብቻ ሆኗል።
📍ማጠቃለያ
አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች ድርጅቶቹን "ፕላትፎርሙን ብቻ ዘርግቶ ገንዘብ መሰብሰብ እንጂ ለአሽከርካሪው መብትና ለስራው ምቹ ሁኔታ መፈጠር ግድ የማይላቸው ከሆነ፣ ዘርፉ ወደ ቀውስ ሊያመራ ይችላል" ሲሉ የዘርፉ ተዋንያን ያስጠነቅቃሉ።
4 months ago
"እንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አድዋ የኢትዮጵያውያን የአንድነት ማህተም፣ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ፋና ነው። አባቶቻችንና እናቶቻችን በደማቸው የጻፉት ታሪክ ዛሬም ለእኛ ኩራታችን ነው! ድል ለኢትዮጵያ!"
ፋስት መረጃ
ፋስት መረጃ
4 months ago
በእስልምና ላይ የጥላቻ ንግግር ያሰራጨው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
#fastmereja I በፌስቡክ ገጹ ላይ የእስልምና ሃይማኖትን ክብር የሚነኩ ምስሎችንና የጥላቻ ንግግሮችን ሲያሰራጭ የነበረው ደሳለኝ በቀለ ጃላታ የተባለ ተከሳሽ፣ በ8 ወር እስራት እንዲቀጣ ተወሰነበት።
ተከሳሹ በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም በግል የፌስቡክ ገጹ ላይ የእስልምና ሃይማኖት የሆኑትን ቆብና ጀለቢያ የለበሰ፣ ነገር ግን አካላዊ ቅርጹ የተዛባ (እጅና እግሩ የተገላቢጦሽ የሆነ) ምስል በመልቀቅ "የእስልምና ሃይማኖት ያለበትን ሁኔታ በምስል ስንገልጽ" የሚል ጽሁፍ አጅቦታል። በተጨማሪም "እግዚአብሔር ሆይ! ይህን የጠመመ ሰው አቅናው" የሚሉ መልዕክቶችን አብሮ ሲያሰራጭ እንደነበር የሳቺ ወረዳ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል።
ተከሳሹ ድርጊቱን መፈጸሙን አምኖ፣ "ድርጊቱን የፈጸምኩት አብዱልቃሲም የተባለ ሰው የኔን ሃይማኖት (ክርስትናን) ዝቅ አድርጎ በመጻፉ በንዴት ተገፋፍቼ ነው" በማለት ስህተቱን አምኗል።
ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ የጥላቻ ንግግርና የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ መጣሱን አረጋግጧል።
በኦሮሚያ ክልል ኢሉ አባቦር ዞን የሳቺ ወረዳ ፍርድ ቤት ተከሳሹ ጥፋተኛ መሆኑን አምኖ ቀደምት የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን እንደ ማቅለያ በመያዝ፣ ሌሎች መሰል ድርጊት ከሚፈጽሙ ሰዎች እንዲማሩበት በሚል የ8 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ እንደወሰነበት ፋስት መረጃ ሰምቷል።
#ችሎት
#fastmereja I በፌስቡክ ገጹ ላይ የእስልምና ሃይማኖትን ክብር የሚነኩ ምስሎችንና የጥላቻ ንግግሮችን ሲያሰራጭ የነበረው ደሳለኝ በቀለ ጃላታ የተባለ ተከሳሽ፣ በ8 ወር እስራት እንዲቀጣ ተወሰነበት።
ተከሳሹ በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም በግል የፌስቡክ ገጹ ላይ የእስልምና ሃይማኖት የሆኑትን ቆብና ጀለቢያ የለበሰ፣ ነገር ግን አካላዊ ቅርጹ የተዛባ (እጅና እግሩ የተገላቢጦሽ የሆነ) ምስል በመልቀቅ "የእስልምና ሃይማኖት ያለበትን ሁኔታ በምስል ስንገልጽ" የሚል ጽሁፍ አጅቦታል። በተጨማሪም "እግዚአብሔር ሆይ! ይህን የጠመመ ሰው አቅናው" የሚሉ መልዕክቶችን አብሮ ሲያሰራጭ እንደነበር የሳቺ ወረዳ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል።
ተከሳሹ ድርጊቱን መፈጸሙን አምኖ፣ "ድርጊቱን የፈጸምኩት አብዱልቃሲም የተባለ ሰው የኔን ሃይማኖት (ክርስትናን) ዝቅ አድርጎ በመጻፉ በንዴት ተገፋፍቼ ነው" በማለት ስህተቱን አምኗል።
ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ የጥላቻ ንግግርና የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ መጣሱን አረጋግጧል።
በኦሮሚያ ክልል ኢሉ አባቦር ዞን የሳቺ ወረዳ ፍርድ ቤት ተከሳሹ ጥፋተኛ መሆኑን አምኖ ቀደምት የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን እንደ ማቅለያ በመያዝ፣ ሌሎች መሰል ድርጊት ከሚፈጽሙ ሰዎች እንዲማሩበት በሚል የ8 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ እንደወሰነበት ፋስት መረጃ ሰምቷል።
#ችሎት
4 months ago
የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪው መንሱር ጀማል ወደ ኢትዮጵያ ተመልሻለሁ አለ።
ባለፉት ወራት ኑሮውን በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አድርጎ የቆየው ታዋቂው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ መንሱር ጀማል፣ ዛሬ ረቡዕ የካቲት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን አስታውቋል።
መንሱር ጀማል ወደ አዲስ አበባ መግባቱን ለፋስት መረጃ አረጋግጧል። በቡርኪና ፋሶ በቆየባቸው ጊዜያት በተለያዩ የቢዝነስ ጉዳዮች እያስጨረሰ እንደቆየ ተናግሯል።
ባለፉት ወራት ኑሮውን በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አድርጎ የቆየው ታዋቂው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ መንሱር ጀማል፣ ዛሬ ረቡዕ የካቲት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን አስታውቋል።
መንሱር ጀማል ወደ አዲስ አበባ መግባቱን ለፋስት መረጃ አረጋግጧል። በቡርኪና ፋሶ በቆየባቸው ጊዜያት በተለያዩ የቢዝነስ ጉዳዮች እያስጨረሰ እንደቆየ ተናግሯል።
4 months ago
አዋሽ ኢንሹራንስ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የጉዞ ጤና ኢንሹራንስ አገልግሎት ጀመሩ
📅 የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም
📍 አዲስ አበባ
አዋሽ ኢንሹራንስ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር መንገደኞች በጉዟቸው ወቅት ለሚያጋጥሟቸው ያልተጠበቁ የጤና እክሎች ዋስትና የሚሰጥ ዘመናዊ የጉዞ ጤና ኢንሹራንስ አገልግሎት በይፋ ማስጀመሩን አስታወቀ።
መንገደኞች የአየር መንገዱን የሞባይል መተግበሪያ (Mobile App) በመጠቀም ብቻ አገልግሎቱን በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
በጉዞ ወቅት ለሚከሰቱ ድንገተኛ የጤና እክሎች እና ሌሎች ተያያዥ ችግሮች አስተማማኝ የኢንሹራንስ ሽፋን ይሰጣል።
የሁለቱን ግዙፍ ተቋማት ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እና የደንበኞችን ምቾት ለማረጋገጥ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
አዋሽ ኢንሹራንስ እስከ ታህሳስ 2025 (እ.ኤ.አ) ድረስ አጠቃላይ ሀብቱ ከ13 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ገልጿል።
#fastmereja | #ፋስት_መረጃ #ቢዝነስ መረጃ
📅 የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም
📍 አዲስ አበባ
አዋሽ ኢንሹራንስ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር መንገደኞች በጉዟቸው ወቅት ለሚያጋጥሟቸው ያልተጠበቁ የጤና እክሎች ዋስትና የሚሰጥ ዘመናዊ የጉዞ ጤና ኢንሹራንስ አገልግሎት በይፋ ማስጀመሩን አስታወቀ።
መንገደኞች የአየር መንገዱን የሞባይል መተግበሪያ (Mobile App) በመጠቀም ብቻ አገልግሎቱን በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
በጉዞ ወቅት ለሚከሰቱ ድንገተኛ የጤና እክሎች እና ሌሎች ተያያዥ ችግሮች አስተማማኝ የኢንሹራንስ ሽፋን ይሰጣል።
የሁለቱን ግዙፍ ተቋማት ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እና የደንበኞችን ምቾት ለማረጋገጥ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
አዋሽ ኢንሹራንስ እስከ ታህሳስ 2025 (እ.ኤ.አ) ድረስ አጠቃላይ ሀብቱ ከ13 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ገልጿል።
#fastmereja | #ፋስት_መረጃ #ቢዝነስ መረጃ
Sponsored by
Surafel
4 months ago
ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ በ2.8 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክቶችን ይፋ አደረገ
---------------------------------------
📅 የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም
📍 አዲስ አበባ
ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ በስዊዘርላንድ መንግስት ድጋፍ የሚተገበሩና ከ2.8 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበላቸው ስድስት ፕሮጀክቶችን በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምሯል።
በሲዳማ ክልል (አለታወንዶ እና ይርጋለም) እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል (ያቤሎ) የሚተገበሩ ስድስት አዳዲስ የቤተሰብ እና የማህበረሰብ ማጠናከሪያ ፕሮጀክቶች ይፋ ሆነዋል።
ቀደም ሲል በሐረር፣ በጅጅጋ እና በጎዴ ሲተገበሩ የነበሩ ሶስት ፕሮጀክቶችም በዚሁ በጀት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።
ከእነዚህ በተጨማሪ በሶማሌ ክልል (ቀብሪ ደሃር) እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል (ሆሳዕና) ላይ ከ251 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበላቸው ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች እየተተገበሩ ይገኛሉ ተብሏል።
ፕሮጀክቶቹ በሚቀጥሉት ከሶስት እስከ አራት ዓመታት ውስጥ ተግባራዊ የሚሆኑ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ከ420,000 በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ።
ዋና ዓላማውም ለህጻናትና ወጣቶች ሁለንተናዊ እድገት ምቹ የሆነ አካባቢ መፍጠር፣ ቤተሰቦችን በኢኮኖሚ ማጠናከር እና የህጻናት ጥበቃ ስርዓቶችን ማጎልበት እንደሆነ ተነግሯል።
የኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች የኢትዮጵያ እና የደቡብ ሱዳን ብሄራዊ ዳይሬክተር አቶ ሳህለማርያም አበበ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ቤተሰብንና ማህበረሰብን ማጠናከር፣ እንዲሁም የህጻናትና ወጣቶችን ደህንነት ማረጋገጥ አማራጭ የሌለው ግዴታ መሆኑን አምኖ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
በስካይላይት ሆቴል በተካሄደው የፕሮጀክቶቹ ማስጀመሪያ ስነ-ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የክልል ተወካዮች፣ የኤምባሲ ዲፕሎማቶች እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተገኝቷል።
#fastmereja | #ፋስት_መረጃ
---------------------------------------
📅 የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም
📍 አዲስ አበባ
ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ በስዊዘርላንድ መንግስት ድጋፍ የሚተገበሩና ከ2.8 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበላቸው ስድስት ፕሮጀክቶችን በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምሯል።
በሲዳማ ክልል (አለታወንዶ እና ይርጋለም) እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል (ያቤሎ) የሚተገበሩ ስድስት አዳዲስ የቤተሰብ እና የማህበረሰብ ማጠናከሪያ ፕሮጀክቶች ይፋ ሆነዋል።
ቀደም ሲል በሐረር፣ በጅጅጋ እና በጎዴ ሲተገበሩ የነበሩ ሶስት ፕሮጀክቶችም በዚሁ በጀት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።
ከእነዚህ በተጨማሪ በሶማሌ ክልል (ቀብሪ ደሃር) እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል (ሆሳዕና) ላይ ከ251 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበላቸው ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች እየተተገበሩ ይገኛሉ ተብሏል።
ፕሮጀክቶቹ በሚቀጥሉት ከሶስት እስከ አራት ዓመታት ውስጥ ተግባራዊ የሚሆኑ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ከ420,000 በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ።
ዋና ዓላማውም ለህጻናትና ወጣቶች ሁለንተናዊ እድገት ምቹ የሆነ አካባቢ መፍጠር፣ ቤተሰቦችን በኢኮኖሚ ማጠናከር እና የህጻናት ጥበቃ ስርዓቶችን ማጎልበት እንደሆነ ተነግሯል።
የኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች የኢትዮጵያ እና የደቡብ ሱዳን ብሄራዊ ዳይሬክተር አቶ ሳህለማርያም አበበ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ቤተሰብንና ማህበረሰብን ማጠናከር፣ እንዲሁም የህጻናትና ወጣቶችን ደህንነት ማረጋገጥ አማራጭ የሌለው ግዴታ መሆኑን አምኖ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
በስካይላይት ሆቴል በተካሄደው የፕሮጀክቶቹ ማስጀመሪያ ስነ-ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የክልል ተወካዮች፣ የኤምባሲ ዲፕሎማቶች እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተገኝቷል።
#fastmereja | #ፋስት_መረጃ
4 months ago
"በስሜት ተገፋፍቶ መናገር ቡድኑን ይጎዳል" ሚኬል አርቴታ
#fastmereja | ሚኬል አርቴታ ነጥብ ከጣሉ በኋላ ስላለው ስሜትና ቀጣይ እርምጃዎች የሚከተለውን ብሏል፦ "አሁን ስሜት ውስጥ በሆንንበት ሰዓት ቡድኑን ሊጎዱ የሚችሉ ነገሮችን መናገር በጣም ቀላል ነው። ሁሉም ተጫዋች የተቻለውን ለማድረግ እንደሚጥር ጥርጥር የለውም፤ ስለዚህ በዚህ ሰዓት የተሳሳተ ንግግር ማድረግ ሊወሰድ የሚችል መጥፎ ውሳኔ ነው" ብሏል።
"ዛሬ በሚፈለገው ደረጃም ሆነ ፉክክር ውስጥ አልነበርንም። በዚህ የሊግ ደረጃ ደግሞ ከሚፈለገው የብቃት ደረጃ በታች ከሆንክ የሚመጣውን ውጤት መቀበል አለብህ" ሲል ገልጿል።
"በሊጉ አሁን ያለንበት ደረጃ ላይ መገኘትን ደስ የሚል የሚያደርገው እንዲህ ያሉ የፈተና ጊዜያትን ማለፍ ነው። በፕሪምየር ሊግ ወደ የትኛውም ሜዳ ሄደህ ያለ ምንም ፈተናና መከራ ታሸንፋለህ ብለህ ካሰብክ፣ ያ ከእውነታው የራቀ ነው" ሲል አክሏል።
#ፋስት_መረጃ #ስፖርት
#fastmereja | ሚኬል አርቴታ ነጥብ ከጣሉ በኋላ ስላለው ስሜትና ቀጣይ እርምጃዎች የሚከተለውን ብሏል፦ "አሁን ስሜት ውስጥ በሆንንበት ሰዓት ቡድኑን ሊጎዱ የሚችሉ ነገሮችን መናገር በጣም ቀላል ነው። ሁሉም ተጫዋች የተቻለውን ለማድረግ እንደሚጥር ጥርጥር የለውም፤ ስለዚህ በዚህ ሰዓት የተሳሳተ ንግግር ማድረግ ሊወሰድ የሚችል መጥፎ ውሳኔ ነው" ብሏል።
"ዛሬ በሚፈለገው ደረጃም ሆነ ፉክክር ውስጥ አልነበርንም። በዚህ የሊግ ደረጃ ደግሞ ከሚፈለገው የብቃት ደረጃ በታች ከሆንክ የሚመጣውን ውጤት መቀበል አለብህ" ሲል ገልጿል።
"በሊጉ አሁን ያለንበት ደረጃ ላይ መገኘትን ደስ የሚል የሚያደርገው እንዲህ ያሉ የፈተና ጊዜያትን ማለፍ ነው። በፕሪምየር ሊግ ወደ የትኛውም ሜዳ ሄደህ ያለ ምንም ፈተናና መከራ ታሸንፋለህ ብለህ ካሰብክ፣ ያ ከእውነታው የራቀ ነው" ሲል አክሏል።
#ፋስት_መረጃ #ስፖርት
4 months ago
2ኛው የኢትዮጵያ የቡና ባህል ቀን ፌስቲቫል በአድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል!
📅 የካቲት 10 ቀን 2018 ዓ.ም
📍 አዲስ አበባ
ዋርካ ኮፊ ኃ/የተ/የግ/ማህበር "የቡና ባህላችን ለሀገራዊ አንድነታችንና ለኢኮኖሚ እድገታችን" በሚል መሪ ቃል 2ኛውን የኢትዮጵያ የቡና ባህል ቀን ፌስቲቫል የፊታችን የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በድምቀት እንደሚከበር ተገለፀ።
ይህ ፌስቲቫል ዝም ብሎ የቡና መጠጫ ፕሮግራም ብቻ ሳይሆን የሀገር ኩራት የሆነውን የቡና ባህላችንን በዓለም አቀፉ የቅርስ ተቋም (UNESCO) እንዲመዘገብ የሚደረግበት ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ መሆን ተገልጿል።
በእለቱ የአስራ አንዱም ክልሎች ውብ የቡና ባህል አልባሳት እና የቁሳቁስ አውደ-ርዕይ፣በእናቶቻችን እጅ የሚፈሉ ጣፋጭ ቡናዎችና የባህል የቡና ቁርሶች፣የስዕል ኤግዚቢሽን፣ የእደ ጥበብ ስራዎች ባዛርና ልዩ ልዩ ጌሞች እንዲሁም ስለ ቡና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ከባለሙያዎች ጋር የፓናል ዉይይት እንደሚኖር ነዉ የተገለፀዉ።
በእለቱም ከ2500-3000 የከተማዋ ነዋሪዎችና የዉጭ ሀገር ጎብኚዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በፌስቲቫሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የክልል ተወካዮች፣ ዲፕሎማቶች፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ የኤምባሲ አምባሳደሮች፣ የቅርስ ጥበቃ ባለሙያዎች እንዲሁም የቡና ላኪዎችና ተመራማሪዎች ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል።
እንዲሁም በዛሬዉ መርሀ-ግብር ዋርካ ኮፊ ኃ/የተ/የግ/ማ እና የኢትዮጵያ ኤክስፖርት ማርኬት (EEM) በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸዉን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
#fastmereja | #ፋስት_መረጃ
----------------------------
ፈጣን • ታማኝ • ተደራሽ
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ቤተሰብ ይሁኑ፦
🔘 ቴሌግራም፦ https://t.me/fastmereja
📅 የካቲት 10 ቀን 2018 ዓ.ም
📍 አዲስ አበባ
ዋርካ ኮፊ ኃ/የተ/የግ/ማህበር "የቡና ባህላችን ለሀገራዊ አንድነታችንና ለኢኮኖሚ እድገታችን" በሚል መሪ ቃል 2ኛውን የኢትዮጵያ የቡና ባህል ቀን ፌስቲቫል የፊታችን የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በድምቀት እንደሚከበር ተገለፀ።
ይህ ፌስቲቫል ዝም ብሎ የቡና መጠጫ ፕሮግራም ብቻ ሳይሆን የሀገር ኩራት የሆነውን የቡና ባህላችንን በዓለም አቀፉ የቅርስ ተቋም (UNESCO) እንዲመዘገብ የሚደረግበት ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ መሆን ተገልጿል።
በእለቱ የአስራ አንዱም ክልሎች ውብ የቡና ባህል አልባሳት እና የቁሳቁስ አውደ-ርዕይ፣በእናቶቻችን እጅ የሚፈሉ ጣፋጭ ቡናዎችና የባህል የቡና ቁርሶች፣የስዕል ኤግዚቢሽን፣ የእደ ጥበብ ስራዎች ባዛርና ልዩ ልዩ ጌሞች እንዲሁም ስለ ቡና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ከባለሙያዎች ጋር የፓናል ዉይይት እንደሚኖር ነዉ የተገለፀዉ።
በእለቱም ከ2500-3000 የከተማዋ ነዋሪዎችና የዉጭ ሀገር ጎብኚዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በፌስቲቫሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የክልል ተወካዮች፣ ዲፕሎማቶች፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ የኤምባሲ አምባሳደሮች፣ የቅርስ ጥበቃ ባለሙያዎች እንዲሁም የቡና ላኪዎችና ተመራማሪዎች ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል።
እንዲሁም በዛሬዉ መርሀ-ግብር ዋርካ ኮፊ ኃ/የተ/የግ/ማ እና የኢትዮጵያ ኤክስፖርት ማርኬት (EEM) በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸዉን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
#fastmereja | #ፋስት_መረጃ
----------------------------
ፈጣን • ታማኝ • ተደራሽ
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ቤተሰብ ይሁኑ፦
🔘 ቴሌግራም፦ https://t.me/fastmereja
4 months ago
🧧 祝大家 2026 马年快乐!🧧
全球数十亿人正在欢庆中国农历新年。速报 向在埃塞俄比亚生活的中国同胞、合作伙伴及所有朋友致以最亲切的节日问候。
根据中国传统历法,2026 年是马年。马象征着力量、速度、活力与成功。正如奔腾的骏马,我们祝愿大家在新的一年里勇往直前,事业腾飞!
🧧 እንኳን ለ2026 የቻይና የፈረስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! 🐎
#fastmereja
በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ የዓለማችን ሕዝቦች የሚያከብሩት የቻይና አዲስ ዓመት (Lunar New Year) ዛሬ በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል። ፋስት መረጃ በኢትዮጵያ ለሚኖሩ የቻይናውያን ማህበረሰብ፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸውና ለወዳጆቻቸው በሙሉ ልባዊ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
እንደ ቻይናውያን የዘመን አቆጣጠር 2026 የፈረስ ዓመት ነው። በቻይና ባህል ፈረስ የጥንካሬ፣ የፍጥነት፣ የነፃነት እና የድል ተምሳሌት ተደርጎ ይታመናል። ልክ እንደ ሚጋልብ ፈረስ፣ አዲሱ ዓመት ለሁላችንም ወደፊት የምንገሰግስበትና ስኬትን የምናጭድበት እንዲሆን እንመኛለን።
全球数十亿人正在欢庆中国农历新年。速报 向在埃塞俄比亚生活的中国同胞、合作伙伴及所有朋友致以最亲切的节日问候。
根据中国传统历法,2026 年是马年。马象征着力量、速度、活力与成功。正如奔腾的骏马,我们祝愿大家在新的一年里勇往直前,事业腾飞!
🧧 እንኳን ለ2026 የቻይና የፈረስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! 🐎
#fastmereja
በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ የዓለማችን ሕዝቦች የሚያከብሩት የቻይና አዲስ ዓመት (Lunar New Year) ዛሬ በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል። ፋስት መረጃ በኢትዮጵያ ለሚኖሩ የቻይናውያን ማህበረሰብ፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸውና ለወዳጆቻቸው በሙሉ ልባዊ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
እንደ ቻይናውያን የዘመን አቆጣጠር 2026 የፈረስ ዓመት ነው። በቻይና ባህል ፈረስ የጥንካሬ፣ የፍጥነት፣ የነፃነት እና የድል ተምሳሌት ተደርጎ ይታመናል። ልክ እንደ ሚጋልብ ፈረስ፣ አዲሱ ዓመት ለሁላችንም ወደፊት የምንገሰግስበትና ስኬትን የምናጭድበት እንዲሆን እንመኛለን።
4 months ago
ህወሓት የኢትዮጵያ መንግስት "ለሌላ ዙር ደማዊ ጦርነት እየተዘጋጀ ነው" ሲል ከሰሰ
#fastmereja I ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ባወጣው ሳምንታዊ መግለጫ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት መሰረት ወደ ድርድር ከመግባት ይልቅ መጠነ-ሰፊ ወታደራዊ ዝግጅት በማድረግ ወደ አዲስ ጦርነት እያመራ መሆኑን አስታወቀ። ፋስት መረጃ ከመግለጫው እንደተመለከተው፣ ድርጅቱ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የጦርነት ደመናውን ለመግታት በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባ ጥሪ አቅርቧል።
ህወሓት በመግለጫው እንዳመለከተው፣ የኢትዮጵያ መንግስት በአሁኑ ወቅት ግዙፍ የጦር መሳሪያና የሰራዊት ክምችት ወደ ትግራይ አቅጣጫ እያስጠጋ ይገኛል። ይህ እንቅስቃሴ "ሌላ ዙር ደማዊ ጦርነት ለመክፈት የታለመ ነው" ሲል ድርጅቱ የገለጸ ሲሆን፣ ባለፈው ሳምንት በሰላማዊ ሰዎችና በሰራዊቱ ላይ የተፈጸሙ የአየርና የምድር ጥቃቶች ለዚህ ማሳያ መሆናቸውን ጠቁሟል።
ድርጅቱ በመግለጫው ካሰፈራቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል የኢትዮጵያ መንግስት ባደራጃቸው ታጣቂዎች አማካኝነት 40 በመቶ የሚሆነውን የትግራይ ህገ-መንግስታዊ መሬት ወሮ በመያዙ፣ ህዝቡ በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ለሞትና ለስቃይ መዳረጉን ገልጿል።
ህወሓት ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ልዩነቶች በውይይት እንዲፈቱ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱንና አሁንም ፍላጎቱ ወደ ጦርነት መግባት ሳይሆን የፕሪቶርያው ስምምነት ወደ ዘላቂ ሰላም እንዲሸጋገር መሆኑን ገልጿል።
ማህበረሰቡ እስካሁን ለቀረቡ የሰላም ጥሪዎች "ጆሮ ዳባ ልበስ" ማለቱን የጠቀሰው መግለጫው፤ ሰሞኑን በተባበሩት መንግስታት፣ በአፍሪካ ህብረትና በአሜሪካ በኩል የወጡ መግለጫዎች ጥሩ ጅምር ቢሆኑም፣ አሁን ካለው ስጋት አንጻር ግን "ተጨባጭ እርምጃ" እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
በመጨረሻም ህወሓት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ወታደራዊ ዝግጅቱን በአስቸኳይ አቁሞ ወደ ሰላማዊ ድርድር እንዲመለስ ሲል በመግለጫው ገልጿል።
#fastmereja I ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ባወጣው ሳምንታዊ መግለጫ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት መሰረት ወደ ድርድር ከመግባት ይልቅ መጠነ-ሰፊ ወታደራዊ ዝግጅት በማድረግ ወደ አዲስ ጦርነት እያመራ መሆኑን አስታወቀ። ፋስት መረጃ ከመግለጫው እንደተመለከተው፣ ድርጅቱ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የጦርነት ደመናውን ለመግታት በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባ ጥሪ አቅርቧል።
ህወሓት በመግለጫው እንዳመለከተው፣ የኢትዮጵያ መንግስት በአሁኑ ወቅት ግዙፍ የጦር መሳሪያና የሰራዊት ክምችት ወደ ትግራይ አቅጣጫ እያስጠጋ ይገኛል። ይህ እንቅስቃሴ "ሌላ ዙር ደማዊ ጦርነት ለመክፈት የታለመ ነው" ሲል ድርጅቱ የገለጸ ሲሆን፣ ባለፈው ሳምንት በሰላማዊ ሰዎችና በሰራዊቱ ላይ የተፈጸሙ የአየርና የምድር ጥቃቶች ለዚህ ማሳያ መሆናቸውን ጠቁሟል።
ድርጅቱ በመግለጫው ካሰፈራቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል የኢትዮጵያ መንግስት ባደራጃቸው ታጣቂዎች አማካኝነት 40 በመቶ የሚሆነውን የትግራይ ህገ-መንግስታዊ መሬት ወሮ በመያዙ፣ ህዝቡ በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ለሞትና ለስቃይ መዳረጉን ገልጿል።
ህወሓት ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ልዩነቶች በውይይት እንዲፈቱ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱንና አሁንም ፍላጎቱ ወደ ጦርነት መግባት ሳይሆን የፕሪቶርያው ስምምነት ወደ ዘላቂ ሰላም እንዲሸጋገር መሆኑን ገልጿል።
ማህበረሰቡ እስካሁን ለቀረቡ የሰላም ጥሪዎች "ጆሮ ዳባ ልበስ" ማለቱን የጠቀሰው መግለጫው፤ ሰሞኑን በተባበሩት መንግስታት፣ በአፍሪካ ህብረትና በአሜሪካ በኩል የወጡ መግለጫዎች ጥሩ ጅምር ቢሆኑም፣ አሁን ካለው ስጋት አንጻር ግን "ተጨባጭ እርምጃ" እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
በመጨረሻም ህወሓት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ወታደራዊ ዝግጅቱን በአስቸኳይ አቁሞ ወደ ሰላማዊ ድርድር እንዲመለስ ሲል በመግለጫው ገልጿል።
5 months ago
አረቄ ቤት እና ቢንጎ ቤት እንዲዘጋ ህዝቡ ጠየቀ
l በሲዳማ ክልል ሆኮ ወረዳ የግርጃ ከተማ ወጣቶች የአረቄ መጠጥና የቢንጎ ቁማር ቤቶች የብዙ ወንድሞቻችን ህይወት ችግር ውስጥ ከቷል ብዙ ወንድሞቻችን በሞትም አጥተናል ስለዚህ በከተማችን ውስጥ የምገኙ አረቄ ቤቶችንና የቢንጎ ቁማር ቤቶች ይዘጉልን በማለት ድምፃቸውን አሰምቷል።
መረጃውን የፋስት መረጃ ነዉ
seledadotio
seledadotio
l በሲዳማ ክልል ሆኮ ወረዳ የግርጃ ከተማ ወጣቶች የአረቄ መጠጥና የቢንጎ ቁማር ቤቶች የብዙ ወንድሞቻችን ህይወት ችግር ውስጥ ከቷል ብዙ ወንድሞቻችን በሞትም አጥተናል ስለዚህ በከተማችን ውስጥ የምገኙ አረቄ ቤቶችንና የቢንጎ ቁማር ቤቶች ይዘጉልን በማለት ድምፃቸውን አሰምቷል።
መረጃውን የፋስት መረጃ ነዉ
seledadotio
seledadotio
5 months ago
አረቄ ቤት እና ቢንጎ ቤት እንዲዘጋ ህዝቡ ጠየቀ
FastMereja.com l በሲዳማ ክልል ሆኮ ወረዳ የግርጃ ከተማ ወጣቶች የአረቄ መጠጥና የቢንጎ ቁማር ቤቶች የብዙ ወንድሞቻችን ህይወት ችግር ውስጥ ከቷል ብዙ ወንድሞቻችን በሞትም አጥተናል ስለዚህ በከተማችን ውስጥ የምገኙ አረቄ ቤቶችንና የቢንጎ ቁማር ቤቶች ይዘጉልን በማለት ድምፃቸውን አሰምቷል።
ፍሬዘር ግማ መረጃውን ለፋስት መረጃ ያደረሰው
FastMereja.com l በሲዳማ ክልል ሆኮ ወረዳ የግርጃ ከተማ ወጣቶች የአረቄ መጠጥና የቢንጎ ቁማር ቤቶች የብዙ ወንድሞቻችን ህይወት ችግር ውስጥ ከቷል ብዙ ወንድሞቻችን በሞትም አጥተናል ስለዚህ በከተማችን ውስጥ የምገኙ አረቄ ቤቶችንና የቢንጎ ቁማር ቤቶች ይዘጉልን በማለት ድምፃቸውን አሰምቷል።
ፍሬዘር ግማ መረጃውን ለፋስት መረጃ ያደረሰው
5 months ago
መንታ ወንድማማቾችን በአንድ ጊዜ የምታፈቅረው ወጣት አነጋጋሪ ሆናለች
#fastmereja I በታይላንድ አንዲት ወጣት ሁለት ተመሳሳይ መንታ ወንድማማቾችን በአንድ ጊዜ በማፍቀርና በአንድ ጣራ ሥር አብራቸው በመኖር ላይ መሆኗን ይፋ ማድረጓ በዓለም አቀፍ ደረጃ የማኅበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኗል። ኦዲቲ ሴንተራል የተባለው የዜና ምንጭ እንደዘገበውና ፋስት መረጃ እንደተመለከተው፣ የ24 ዓመቷ ኖንግ ፋህ ይህን ያልተለመደ የፍቅር ግንኙነት የጀመረችው ሲንግ እና ሱዌ ከተባሉ መንታ ወንድማማቾች ጋር በአንድ ምግብ ቤት ውስጥ ከተዋወቁ በኋላ ነው።
መጀመሪያ ላይ ከሁለቱ አንዱን እንድትመርጥ በጓደኞቿ ግፊት ይደረግባት የነበረ ቢሆንም፣ እሷ ግን ለሁለቱም እኩል ፍቅር እንዳላት ተረድታለች። ፋስት መረጃ ከኦዲቲ ሴንተራል ዘገባ እንደተረዳው፣ ወንድማማቾቹም ሁኔታውን በጸጋ በመቀበል ሦስቱም በአንድ ቤት ውስጥ በፍቅር ለመኖር መስማማታቸውን ገልጸዋል።
ይህ ግንኙነት ከፍቅር ባለፈ በጋራ የገንዘብ አያያዝም የታጀበ ነው። ወንድማማቾቹ በግብርና ሥራ የሚተዳደሩ ሲሆን፣ ፋህ ደግሞ የቤቱን ፋይናንስና የሁለቱንም ወንድማማቾች የባንክ ሂሳብ በበላይነት ታስተዳድራለች። ወጣቷ በመካከላቸው ምንም ዓይነት የቅናት መንፈስ እንደሌለና ሦስቱም በአንድ ትልቅ አልጋ ላይ አብረው እንደሚተኙ ለሚዲያዎች በግልጽ ተናግራለች።
ምንም እንኳ ጉዳዩ በማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ የሥነ-ምግባር ክርክር ቢያስነሳም፣ የወጣቷና የወንድማማቾቹ ቤተሰቦች ግንኙነታቸውን አውቀውና ተቀብለው አብረው እንዲኖሩ ፈቅደውላቸዋል። በታይላንድ ሚዲያዎች ከፍተኛ ሽፋን ያገኘው ይህ ታሪክ፣ በሰዎች ዘንድ "የዘመኑ አስገራሚ የፍቅር ታሪክ" በሚል እየተነገረ ይገኛል።
#fastmereja I በታይላንድ አንዲት ወጣት ሁለት ተመሳሳይ መንታ ወንድማማቾችን በአንድ ጊዜ በማፍቀርና በአንድ ጣራ ሥር አብራቸው በመኖር ላይ መሆኗን ይፋ ማድረጓ በዓለም አቀፍ ደረጃ የማኅበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኗል። ኦዲቲ ሴንተራል የተባለው የዜና ምንጭ እንደዘገበውና ፋስት መረጃ እንደተመለከተው፣ የ24 ዓመቷ ኖንግ ፋህ ይህን ያልተለመደ የፍቅር ግንኙነት የጀመረችው ሲንግ እና ሱዌ ከተባሉ መንታ ወንድማማቾች ጋር በአንድ ምግብ ቤት ውስጥ ከተዋወቁ በኋላ ነው።
መጀመሪያ ላይ ከሁለቱ አንዱን እንድትመርጥ በጓደኞቿ ግፊት ይደረግባት የነበረ ቢሆንም፣ እሷ ግን ለሁለቱም እኩል ፍቅር እንዳላት ተረድታለች። ፋስት መረጃ ከኦዲቲ ሴንተራል ዘገባ እንደተረዳው፣ ወንድማማቾቹም ሁኔታውን በጸጋ በመቀበል ሦስቱም በአንድ ቤት ውስጥ በፍቅር ለመኖር መስማማታቸውን ገልጸዋል።
ይህ ግንኙነት ከፍቅር ባለፈ በጋራ የገንዘብ አያያዝም የታጀበ ነው። ወንድማማቾቹ በግብርና ሥራ የሚተዳደሩ ሲሆን፣ ፋህ ደግሞ የቤቱን ፋይናንስና የሁለቱንም ወንድማማቾች የባንክ ሂሳብ በበላይነት ታስተዳድራለች። ወጣቷ በመካከላቸው ምንም ዓይነት የቅናት መንፈስ እንደሌለና ሦስቱም በአንድ ትልቅ አልጋ ላይ አብረው እንደሚተኙ ለሚዲያዎች በግልጽ ተናግራለች።
ምንም እንኳ ጉዳዩ በማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ የሥነ-ምግባር ክርክር ቢያስነሳም፣ የወጣቷና የወንድማማቾቹ ቤተሰቦች ግንኙነታቸውን አውቀውና ተቀብለው አብረው እንዲኖሩ ፈቅደውላቸዋል። በታይላንድ ሚዲያዎች ከፍተኛ ሽፋን ያገኘው ይህ ታሪክ፣ በሰዎች ዘንድ "የዘመኑ አስገራሚ የፍቅር ታሪክ" በሚል እየተነገረ ይገኛል።
Sponsored by
Surafel
5 months ago
የአዲስ አበባ የሜትር ታክሲዎች፦ በታክስና በገቢ መሃል የቆመው "የመቆሚያ" ፈተና
#fastmereja I በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ፣ የትራንስፖርት ዘርፉን ለማዘመንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ ወደ ሥራ የገቡት የሜትር ታክሲዎች፣ በአሁኑ ወቅት ከከፍተኛ የመቆሚያ ቦታ እጥረት ጋር እየታገሉ ይገኛሉ። የፋስት መረጃ ዘጋቢ እንደዘገበው፤ አገልግሎት ሰጪዎቹ መንግሥት የሚፈልግባቸውን ግብርና ልዩ ልዩ ክፍያዎች በአግባቡ ቢወጡም፣ በምላሹ ግን በከተማዋ የንግድ ማዕከላትና ሰው በሚበዛባቸው አካባቢዎች በነፃነት ቆመው ተሳፋሪ የሚጠብቁበት ቦታ በማጣታቸው ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገዋል።
1. የችግሩ ምንጭና መገለጫዎች
የሜትር ታክሲዎች እንደ ታክሲ (ሰማያዊና ነጭ) በተወሰነ መስመር ብቻ የሚመላለሱ ሳይሆኑ፣ ጥሪ በሚደረግላቸው ቦታ ሁሉ ተገኝተው አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው። ሆኖም የሚከተሉት ችግሮች ተግዳሮት ሆነውባቸዋል፦
የማቆሚያ ቦታዎች እጥረት፦ በከተማዋ ሰፊ የግንባታ ስራዎችና የመንገድ ማስፋፊያዎች በሚካሄዱባቸው አካባቢዎች ለሜትር ታክሲዎች የሚሆን የተለየ ማቆሚያ አልተዘጋጀም።
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ያለው ግጭት፦ አሽከርካሪዎች ተሳፋሪ ለመጠበቅ መንገድ ዳር ሲቆሙ በየትራፊክ ፖሊሶችና በመንገድ ደህንነት ተቆጣጣሪዎች ለከፍተኛ ቅጣትና ለሰሌዳ መፈታት ይጋለጣሉ።
ከሆቴሎችና የንግድ ማዕከላት ጋር ያለው አለመግባባት፦ ትልልቅ ሆቴሎችና የገበያ አዳራሾች ለራሳቸው ደንበኞች ብቻ ቦታውን ስለሚይዙ፣ የሜትር ታክሲዎች በነዚህ ቦታዎች አካባቢ መጠጋት እንኳን እንደማይችሉ ይገልጻሉ።
2. የአሽከርካሪዎች ብሶት
ብዙዎቹ አሽከርካሪዎች እንደሚገልጹት፣ ስራው አትራፊ የሚሆነው ሰው ባለበት አካባቢ ቆሞ በመጠበቅ እንጂ ዝም ብሎ ከተማዋን በማሽከርከር (Cruising) አይደለም። "ነዳጅ እየተወደደ ባለበት ሁኔታ ደንበኛ ፍለጋ ከተማዋን ማዞር ኪሳራ ነው" ይላሉ።
ዘጋቢያችን ያነጋገራቸውና ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ አሽከርካሪ እንደሚከተለው ብለዋል፦
"እኛ የንግድ ፈቃድ አውጥተን፣ ግብር እየከፈልን የምንሰራ ነን። ነገር ግን ቆመን ተሳፋሪ የምንጠብቅበት ቦታ ስለሌለን፣ በየደቂቃው ከትራፊክ ፖሊሶች ጋር እንጋጫለን። መቆሚያ ማጣት ማለት ለእኛ ሥራ ማጣት ማለት ነው።"
3. የኢኮኖሚና የማህበራዊ ተፅዕኖው
ይህ ችግር በአሽከርካሪዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በከተማዋ ኢኮኖሚ ላይም ተፅዕኖ አለው፦
የአገልግሎት ጥራት መውረድ፦ ታክሲዎች ራቅ ያሉ ቦታዎች ላይ ለመቆም በመገደዳቸው፣ ደንበኞች ጥሪ ሲያደርጉ ታክሲው እስኪመጣ ረጅም ጊዜ እንዲጠብቁ ያደርጋቸዋል።
የነዳጅ ብክነትና የትራፊክ መጨናነቅ፦ ቋሚ መቆሚያ የሌላቸው ታክሲዎች ደንበኛ ፍለጋ መንገዶችን እያጨናነቁ ለመዞር ይገደዳሉ፣ ይህም ከፍተኛ የነዳጅ ብክነትን ያስከትላል።
የገቢ መቀነስ፦ አሽከርካሪዎች አብዛኛውን ጊዜያቸውን ለቅጣት ስለሚያሳልፉ፣ ያገኙት ገቢ ለቤት ኪራይና ለቤተሰብ ማስተዳደሪያ ሳይበቃቸው ይቀራል።
4. መፍትሔ የሚሹ ነጥቦች
አገልግሎት ሰጪዎቹና የዘርፉ ባለሙያዎች የሚከተሉትን የመፍትሔ ሃሳቦች ያነሳሉ፦
ተለይተው የታወቁ ማቆሚያዎች (Dedicated Zones)፦ በከተማዋ ዋና ዋና የንግድ አካባቢዎችና በሆቴሎች አቅራቢያ ለሜትር ታክሲዎች ብቻ የሚውሉ የመቆሚያ ቦታዎች መመደብ።
የዲጂታል መተግበሪያዎችንና መቆሚያዎችን ማቀናጀት፦ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አሽከርካሪዎች በአቅራቢያቸው ወዳለ ክፍት ማቆሚያ የሚመሩበትን አሰራር መዘርጋት።
ከባለድርሻ አካላት ጋር መነጋገር፦ የትራንስፖርት ቢሮ፣ የትራፊክ ማኔጅመንት እና የሜትር ታክሲ የሚሰጡ ድርጅቶች በጋራ በመቀመጥ የአሰራር መመሪያዎችን ማሻሻል።
ማጠቃለያ
የአዲስ አበባ ሜትር ታክሲዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለብዙ ሺህ ወጣቶች የሥራ ዕድል የፈጠሩ ናቸው። በመሆኑም እነዚህ ግብር ከፋይ ዜጎች በሥራቸው ላይ የሚገጥማቸውን የመቆሚያ ቦታ ችግር መፍታት፣ የከተማዋን የትራንስፖርት ሥርዓት ከማዘመን ባለፈ ፍትሃዊ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ዘጋቢያችን ዘገባውን ያጠናቅቃል።
#fastmereja I በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ፣ የትራንስፖርት ዘርፉን ለማዘመንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ ወደ ሥራ የገቡት የሜትር ታክሲዎች፣ በአሁኑ ወቅት ከከፍተኛ የመቆሚያ ቦታ እጥረት ጋር እየታገሉ ይገኛሉ። የፋስት መረጃ ዘጋቢ እንደዘገበው፤ አገልግሎት ሰጪዎቹ መንግሥት የሚፈልግባቸውን ግብርና ልዩ ልዩ ክፍያዎች በአግባቡ ቢወጡም፣ በምላሹ ግን በከተማዋ የንግድ ማዕከላትና ሰው በሚበዛባቸው አካባቢዎች በነፃነት ቆመው ተሳፋሪ የሚጠብቁበት ቦታ በማጣታቸው ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገዋል።
1. የችግሩ ምንጭና መገለጫዎች
የሜትር ታክሲዎች እንደ ታክሲ (ሰማያዊና ነጭ) በተወሰነ መስመር ብቻ የሚመላለሱ ሳይሆኑ፣ ጥሪ በሚደረግላቸው ቦታ ሁሉ ተገኝተው አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው። ሆኖም የሚከተሉት ችግሮች ተግዳሮት ሆነውባቸዋል፦
የማቆሚያ ቦታዎች እጥረት፦ በከተማዋ ሰፊ የግንባታ ስራዎችና የመንገድ ማስፋፊያዎች በሚካሄዱባቸው አካባቢዎች ለሜትር ታክሲዎች የሚሆን የተለየ ማቆሚያ አልተዘጋጀም።
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ያለው ግጭት፦ አሽከርካሪዎች ተሳፋሪ ለመጠበቅ መንገድ ዳር ሲቆሙ በየትራፊክ ፖሊሶችና በመንገድ ደህንነት ተቆጣጣሪዎች ለከፍተኛ ቅጣትና ለሰሌዳ መፈታት ይጋለጣሉ።
ከሆቴሎችና የንግድ ማዕከላት ጋር ያለው አለመግባባት፦ ትልልቅ ሆቴሎችና የገበያ አዳራሾች ለራሳቸው ደንበኞች ብቻ ቦታውን ስለሚይዙ፣ የሜትር ታክሲዎች በነዚህ ቦታዎች አካባቢ መጠጋት እንኳን እንደማይችሉ ይገልጻሉ።
2. የአሽከርካሪዎች ብሶት
ብዙዎቹ አሽከርካሪዎች እንደሚገልጹት፣ ስራው አትራፊ የሚሆነው ሰው ባለበት አካባቢ ቆሞ በመጠበቅ እንጂ ዝም ብሎ ከተማዋን በማሽከርከር (Cruising) አይደለም። "ነዳጅ እየተወደደ ባለበት ሁኔታ ደንበኛ ፍለጋ ከተማዋን ማዞር ኪሳራ ነው" ይላሉ።
ዘጋቢያችን ያነጋገራቸውና ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ አሽከርካሪ እንደሚከተለው ብለዋል፦
"እኛ የንግድ ፈቃድ አውጥተን፣ ግብር እየከፈልን የምንሰራ ነን። ነገር ግን ቆመን ተሳፋሪ የምንጠብቅበት ቦታ ስለሌለን፣ በየደቂቃው ከትራፊክ ፖሊሶች ጋር እንጋጫለን። መቆሚያ ማጣት ማለት ለእኛ ሥራ ማጣት ማለት ነው።"
3. የኢኮኖሚና የማህበራዊ ተፅዕኖው
ይህ ችግር በአሽከርካሪዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በከተማዋ ኢኮኖሚ ላይም ተፅዕኖ አለው፦
የአገልግሎት ጥራት መውረድ፦ ታክሲዎች ራቅ ያሉ ቦታዎች ላይ ለመቆም በመገደዳቸው፣ ደንበኞች ጥሪ ሲያደርጉ ታክሲው እስኪመጣ ረጅም ጊዜ እንዲጠብቁ ያደርጋቸዋል።
የነዳጅ ብክነትና የትራፊክ መጨናነቅ፦ ቋሚ መቆሚያ የሌላቸው ታክሲዎች ደንበኛ ፍለጋ መንገዶችን እያጨናነቁ ለመዞር ይገደዳሉ፣ ይህም ከፍተኛ የነዳጅ ብክነትን ያስከትላል።
የገቢ መቀነስ፦ አሽከርካሪዎች አብዛኛውን ጊዜያቸውን ለቅጣት ስለሚያሳልፉ፣ ያገኙት ገቢ ለቤት ኪራይና ለቤተሰብ ማስተዳደሪያ ሳይበቃቸው ይቀራል።
4. መፍትሔ የሚሹ ነጥቦች
አገልግሎት ሰጪዎቹና የዘርፉ ባለሙያዎች የሚከተሉትን የመፍትሔ ሃሳቦች ያነሳሉ፦
ተለይተው የታወቁ ማቆሚያዎች (Dedicated Zones)፦ በከተማዋ ዋና ዋና የንግድ አካባቢዎችና በሆቴሎች አቅራቢያ ለሜትር ታክሲዎች ብቻ የሚውሉ የመቆሚያ ቦታዎች መመደብ።
የዲጂታል መተግበሪያዎችንና መቆሚያዎችን ማቀናጀት፦ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አሽከርካሪዎች በአቅራቢያቸው ወዳለ ክፍት ማቆሚያ የሚመሩበትን አሰራር መዘርጋት።
ከባለድርሻ አካላት ጋር መነጋገር፦ የትራንስፖርት ቢሮ፣ የትራፊክ ማኔጅመንት እና የሜትር ታክሲ የሚሰጡ ድርጅቶች በጋራ በመቀመጥ የአሰራር መመሪያዎችን ማሻሻል።
ማጠቃለያ
የአዲስ አበባ ሜትር ታክሲዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለብዙ ሺህ ወጣቶች የሥራ ዕድል የፈጠሩ ናቸው። በመሆኑም እነዚህ ግብር ከፋይ ዜጎች በሥራቸው ላይ የሚገጥማቸውን የመቆሚያ ቦታ ችግር መፍታት፣ የከተማዋን የትራንስፖርት ሥርዓት ከማዘመን ባለፈ ፍትሃዊ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ዘጋቢያችን ዘገባውን ያጠናቅቃል።
5 months ago
ስለ ማስተር አብነት ከበደ የጤና ሁኔታና እየተሰራጩ ስላሉ የሀሰት መረጃዎች የተሰጠ ማብራሪያ
#fastmereja I በአሁኑ ወቅት በህክምና ላይ የሚገኙት ታዋቂው የማህበራዊ ሚዲያ በጎ ፣ድራጊ ማስተር አብነት ከበደን ስም በመጠቀም፣ የተሳሳቱ መረጃዎችና የማጭበርበር ድርጊቶች እየተፈጸሙ መሆኑ ተገለጸ። ማስተር አብነት ለፋስት መረጃ በላከው ልዩ መግለጫ፣ ህዝብ ከእነዚህ መሰል ድርጊቶች ራሱን እንዲጠብቅ አሳስቧል።
የማጭበርበር ሙከራዎችና የAI ቴክኖሎጂ ስጋት
ማስተር አብነት በህክምና ላይ መሆኑን ተገን በማድረግ፣ በተለያዩ የሀሰት (Fake) አካውንቶች እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ተቀናብረው የሚወጡ ምስሎች፣ ጽሁፎችና ተንቀሳቃሽ ምስሎች በስፋት እየተሰራጩ መሆኑ ተረጋግጧል።
ከዚህም ባለፈ አጭበርባሪዎች በውስጥ መስመር (Inbox) የድምጽና የጽሁፍ መልዕክቶችን በመላክ፣ “ለህክምና ድጋፍ” በሚል ስም የደጋግ ሰዎችን ገንዘብ ለመዝረፍ ሙከራ እያደረጉ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል።
መግለጫው በግልጽ እንደሚያስረዳው፦
📌 ለማስተር አብነት ከበደ ህክምና የሚውል ምንም ዓይነት የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ እየተከናወነ አይደለም።
📌 በማንኛውም መንገድ በስሙ የሚጠየቅ የገንዘብ ድጋፍ ሙሉ በሙሉ ሀሰተኛ እና ለማጭበርበር የታለመ ነው።
በማስተር አብነት ስም የተከፈቱ በርካታ የሀሰት ገጾች ቢኖሩም፣ ተከታዮች መረጃ እንዲቀበሉ የተፈቀደላቸው በሚከተሉት ትክክለኛ ገጾቹ ብቻ መሆኑ ታውቋል፦
Facebook: ከ1.9 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሉት ገጽ።
TikTok: ከ5.7 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሉት ገጽ።
በመጨረሻም፣ ህዝባችን እና የሚዲያ ተከታዮች ካልተረጋገጡና ከተቀናበሩ የሀሰት መረጃዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ፣ እንዲሁም መረጃዎችን ከታመኑ ምንጮች ብቻ እንዲከታተሉ ጥብቅ መልዕክት ተላልፏል።
#fastmereja I በአሁኑ ወቅት በህክምና ላይ የሚገኙት ታዋቂው የማህበራዊ ሚዲያ በጎ ፣ድራጊ ማስተር አብነት ከበደን ስም በመጠቀም፣ የተሳሳቱ መረጃዎችና የማጭበርበር ድርጊቶች እየተፈጸሙ መሆኑ ተገለጸ። ማስተር አብነት ለፋስት መረጃ በላከው ልዩ መግለጫ፣ ህዝብ ከእነዚህ መሰል ድርጊቶች ራሱን እንዲጠብቅ አሳስቧል።
የማጭበርበር ሙከራዎችና የAI ቴክኖሎጂ ስጋት
ማስተር አብነት በህክምና ላይ መሆኑን ተገን በማድረግ፣ በተለያዩ የሀሰት (Fake) አካውንቶች እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ተቀናብረው የሚወጡ ምስሎች፣ ጽሁፎችና ተንቀሳቃሽ ምስሎች በስፋት እየተሰራጩ መሆኑ ተረጋግጧል።
ከዚህም ባለፈ አጭበርባሪዎች በውስጥ መስመር (Inbox) የድምጽና የጽሁፍ መልዕክቶችን በመላክ፣ “ለህክምና ድጋፍ” በሚል ስም የደጋግ ሰዎችን ገንዘብ ለመዝረፍ ሙከራ እያደረጉ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል።
መግለጫው በግልጽ እንደሚያስረዳው፦
📌 ለማስተር አብነት ከበደ ህክምና የሚውል ምንም ዓይነት የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ እየተከናወነ አይደለም።
📌 በማንኛውም መንገድ በስሙ የሚጠየቅ የገንዘብ ድጋፍ ሙሉ በሙሉ ሀሰተኛ እና ለማጭበርበር የታለመ ነው።
በማስተር አብነት ስም የተከፈቱ በርካታ የሀሰት ገጾች ቢኖሩም፣ ተከታዮች መረጃ እንዲቀበሉ የተፈቀደላቸው በሚከተሉት ትክክለኛ ገጾቹ ብቻ መሆኑ ታውቋል፦
Facebook: ከ1.9 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሉት ገጽ።
TikTok: ከ5.7 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሉት ገጽ።
በመጨረሻም፣ ህዝባችን እና የሚዲያ ተከታዮች ካልተረጋገጡና ከተቀናበሩ የሀሰት መረጃዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ፣ እንዲሁም መረጃዎችን ከታመኑ ምንጮች ብቻ እንዲከታተሉ ጥብቅ መልዕክት ተላልፏል።
5 months ago
መልካም ልደት ለመሰረት መብራቴ! 🎂🎈
በተሰጥኦዋ ልባችንን የገዛች፣ በስብዕናዋ አርአያ የሆነችው ተወዳጇ አርቲስት መሰረት መብራቴ ልደቷ ነው።
መሰረት በኢትዮጵያ የፊልም እና የድራማ ታሪክ ውስጥ የማይረሱ ገጸ-ባህሪያትን በመላበስ፣ በብዙ ሚሊዮኖች ዘንድ ተወዳጅነትን አትርፋለች። ከጥበብ ስራዎቿ ባሻገር በበጎ አድራጎት ስራዎቿና ለሃገር ባላት ፍቅር የምትታወቀው መሰረት፤ ዛሬም ድረስ የጥበብ ስራዎቿና ውበቷ እንደደመቁ አሉ።
ፋስት መረጃ ለመሰረት መብራቴ ረጅም እድሜ፣ ጤና እና ተጨማሪ የጥበብ ስኬቶችን ይመኛል!
#meseretmebrate #happybirthday #fastmereja #ethiopianartist #ፋስትመረጃ #መሰረትመብራቴ
በተሰጥኦዋ ልባችንን የገዛች፣ በስብዕናዋ አርአያ የሆነችው ተወዳጇ አርቲስት መሰረት መብራቴ ልደቷ ነው።
መሰረት በኢትዮጵያ የፊልም እና የድራማ ታሪክ ውስጥ የማይረሱ ገጸ-ባህሪያትን በመላበስ፣ በብዙ ሚሊዮኖች ዘንድ ተወዳጅነትን አትርፋለች። ከጥበብ ስራዎቿ ባሻገር በበጎ አድራጎት ስራዎቿና ለሃገር ባላት ፍቅር የምትታወቀው መሰረት፤ ዛሬም ድረስ የጥበብ ስራዎቿና ውበቷ እንደደመቁ አሉ።
ፋስት መረጃ ለመሰረት መብራቴ ረጅም እድሜ፣ ጤና እና ተጨማሪ የጥበብ ስኬቶችን ይመኛል!
#meseretmebrate #happybirthday #fastmereja #ethiopianartist #ፋስትመረጃ #መሰረትመብራቴ
5 months ago
ድምጻዊ አንዱአለም ጎሳ በባለቤቱ ህልፈት ዙሪያ የተሰነዘሩበትን ውንጀላዎች አስተባበለ
#fastmereja I ድምጻዊ አንዱአለም ጎሳ ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያና በተለያዩ ወገኖች በባለቤቱ በቀነኒ አዱኛ ህልፈት ዙሪያ እየተሰነዘሩበት ባሉ ትችቶችና ጥርጣሬዎች ላይ ምላሽ ሰጠ።
ድምጻዊው ዛሬ በአፋን ኦሮሞ ባወጣው የቪዲዮ መግለጫ፣ ክስተቱ የተፈጸመበትን ሁኔታና ከዚያ በፊት የነበሩ ጉዳዮችን በዝርዝር አብራርቷል በፋስት መረጃ በአማርኛ እንደሚከተለው ይቀርባል።
አንዱአለም በመግለጫው ላይ እንደተናገረው፣ ባለቤቱ ቀነኒ አዱኛ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ራሷን የማጥፋት ሙከራ ታደርግ እንደነበር ገልጿል። ይህንንም አስቸጋሪ ሁኔታ ለቤተሰቦቿ በተደጋጋሚ እንዳሳወቀና አባቷ ጉዳዩን እንደሚያውቁ ተናግሯል።
ባለቤቱ ህይወቷ ባለፈበት ዕለት ስለነበረው ሁኔታ ድምጻዊው የሚከተሉትን ነጥቦች አቅርቧል፦
በዕለቱ አብረው እንደነበሩና በተለይ ሃኪም ቤት የእርግዝና ምርመራ ስታደርግ፣ የልደት ፎቶ ልትነሳ ስትሄድም አድራሻት ስትጨርሺ ደውይልኝ ብያት ነው የሄድኩት ማታም አብረው ተኝተው እንደነበር ገልጿል።
ማታ አብረው ተኝተው ስለ ውሎ ስጠይቃት ከጎኑ ተነስታ መሄዷንና ስትቆይበት ተነስቶ ሲፈልጋት የኩሽናው በር በውስጥ በኩል ተቆልፎ እንዳገኘው ተናግሯል።
በሩ በላይ በኩል ክፍት ስለነበር ዘሎ ሲገባ "ላርጎ" (የጽዳት ፈሳሽ) ስትጠጣ ማየቱንና "ለምን እንዲህ ታደርጊያለሽ?" ብሎ ሊያረጋጋትና ሊያወራት መሞከሩን ገልጿል።
ድምጻዊው እንዲህ ያለውን ድርጊት የማታቆም ከሆነ ለቤተሰቦቿ ነግሮ እንደሚለያዩ ቢነግራትም፣ እሷ ግን "ይስፋልህ" በማለት በድንገት ሮጣ መዝለሏን አስረድቷል። ሊይዛት ቢሞክርም ሳይሳካለት ቀርቶ መውደቋን ገልጿል።
ድምጻዊ አንዱአለም ጎሳ በማጠቃለያው ላይ "በምንም ተአምር እሷን አልገደልኳትም" በማለት የቀረበበትን የወንጀል ክስ አጥብቆ አስተባብሏል።
ሽማግሌዎችንም የላኩት ከቤተሰብ ጋር ያለው ግኑኝነት እንዲቀጥል በማሰብ እንጂ ካሳ ለመክፈል የሚባለውን ነገር አላውቅም ብሏል።
#fastmereja I ድምጻዊ አንዱአለም ጎሳ ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያና በተለያዩ ወገኖች በባለቤቱ በቀነኒ አዱኛ ህልፈት ዙሪያ እየተሰነዘሩበት ባሉ ትችቶችና ጥርጣሬዎች ላይ ምላሽ ሰጠ።
ድምጻዊው ዛሬ በአፋን ኦሮሞ ባወጣው የቪዲዮ መግለጫ፣ ክስተቱ የተፈጸመበትን ሁኔታና ከዚያ በፊት የነበሩ ጉዳዮችን በዝርዝር አብራርቷል በፋስት መረጃ በአማርኛ እንደሚከተለው ይቀርባል።
አንዱአለም በመግለጫው ላይ እንደተናገረው፣ ባለቤቱ ቀነኒ አዱኛ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ራሷን የማጥፋት ሙከራ ታደርግ እንደነበር ገልጿል። ይህንንም አስቸጋሪ ሁኔታ ለቤተሰቦቿ በተደጋጋሚ እንዳሳወቀና አባቷ ጉዳዩን እንደሚያውቁ ተናግሯል።
ባለቤቱ ህይወቷ ባለፈበት ዕለት ስለነበረው ሁኔታ ድምጻዊው የሚከተሉትን ነጥቦች አቅርቧል፦
በዕለቱ አብረው እንደነበሩና በተለይ ሃኪም ቤት የእርግዝና ምርመራ ስታደርግ፣ የልደት ፎቶ ልትነሳ ስትሄድም አድራሻት ስትጨርሺ ደውይልኝ ብያት ነው የሄድኩት ማታም አብረው ተኝተው እንደነበር ገልጿል።
ማታ አብረው ተኝተው ስለ ውሎ ስጠይቃት ከጎኑ ተነስታ መሄዷንና ስትቆይበት ተነስቶ ሲፈልጋት የኩሽናው በር በውስጥ በኩል ተቆልፎ እንዳገኘው ተናግሯል።
በሩ በላይ በኩል ክፍት ስለነበር ዘሎ ሲገባ "ላርጎ" (የጽዳት ፈሳሽ) ስትጠጣ ማየቱንና "ለምን እንዲህ ታደርጊያለሽ?" ብሎ ሊያረጋጋትና ሊያወራት መሞከሩን ገልጿል።
ድምጻዊው እንዲህ ያለውን ድርጊት የማታቆም ከሆነ ለቤተሰቦቿ ነግሮ እንደሚለያዩ ቢነግራትም፣ እሷ ግን "ይስፋልህ" በማለት በድንገት ሮጣ መዝለሏን አስረድቷል። ሊይዛት ቢሞክርም ሳይሳካለት ቀርቶ መውደቋን ገልጿል።
ድምጻዊ አንዱአለም ጎሳ በማጠቃለያው ላይ "በምንም ተአምር እሷን አልገደልኳትም" በማለት የቀረበበትን የወንጀል ክስ አጥብቆ አስተባብሏል።
ሽማግሌዎችንም የላኩት ከቤተሰብ ጋር ያለው ግኑኝነት እንዲቀጥል በማሰብ እንጂ ካሳ ለመክፈል የሚባለውን ነገር አላውቅም ብሏል።
Sponsored by
Surafel
6 months ago
🎂 መልካም ልደት ለቤተሳይዳ ሲሳይ!
ለፋስት መረጃ (Fast Mereja) ገጽ ወሳኝ ተሳታፊና ንቁ ቤተሰብ ለሆንሽው ለተከበርሽው ቤተሳይዳ ሲሳይ፤
በዛሬው ዕለት የሚከበረው የልደት ቀንሽን ምክንያት በማድረግ፣ የፋስት መረጃ አባላትና ወዳጆችሽ በሙሉ የተሰማንን ደስታ እንገልጻለን። ላበረከትሽው ቀና ተሳትፎና ላለሽ መልካም ስብዕና ትልቅ አክብሮት አለን።
አዲሱ ዓመት፦
🔥 የሰላም፣ የጤና እና የደስታ፤
🔥 ስኬትና ብርሃን የሚበዛበት፤
🔥 ሕልሞችሽ ሁሉ እውን የሚሆኑበት እንዲሆንልሽ ከልብ እንመኛለን!
መልካም ልደት! 🎈✨
ለፋስት መረጃ (Fast Mereja) ገጽ ወሳኝ ተሳታፊና ንቁ ቤተሰብ ለሆንሽው ለተከበርሽው ቤተሳይዳ ሲሳይ፤
በዛሬው ዕለት የሚከበረው የልደት ቀንሽን ምክንያት በማድረግ፣ የፋስት መረጃ አባላትና ወዳጆችሽ በሙሉ የተሰማንን ደስታ እንገልጻለን። ላበረከትሽው ቀና ተሳትፎና ላለሽ መልካም ስብዕና ትልቅ አክብሮት አለን።
አዲሱ ዓመት፦
🔥 የሰላም፣ የጤና እና የደስታ፤
🔥 ስኬትና ብርሃን የሚበዛበት፤
🔥 ሕልሞችሽ ሁሉ እውን የሚሆኑበት እንዲሆንልሽ ከልብ እንመኛለን!
መልካም ልደት! 🎈✨
6 months ago
35ተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር በሞሮኮ 24 ሀገራት 6 ምድቦች 52 ጨዋታዎች!
ምድብ 1. ሞሮኮ 🇲🇦, ማሊ 🇲🇱, ዛምቢያ 🇿🇲, ኮሞሮስ 🇰🇲
ሞሮኮ በ 2030 የዓለም ዋንጫን በማዘጋጀት በአፍሪካ ሁለተኛዋ ሀገር ለመሆን እየተዘጋጀች ነው:: ጥራታቸውን የጠበቁ መሰረተ ልማቶች ላይ ኢንቨስት እያደረገች ነው:: ከዚያም በላይ ደግሞ ቶፕ ክላስ ቡድን መገንባት:: ለዚያም ነው በዚህ የአፍሪካ ዋንጫ ከ favorite ቡድኖች አንዷ ሆና ግምት የተሰጣት:: ዋና አሰልጣኙ Walid Regragui በቡድኑ አስደናቂ የሚባል ትራክ ሪከርድ አለው:: የሞሮኮ ቡድን በ elite-level ያሉ ተጫዋቾችን የያዘ ስብስብ ነው::
በዚህ ምድብ ሌላኛዋ ሀገር ማሊ ናት:: የማሊ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ Tom Saintfiet , እኚህ ሰው በኢትዮጵያ ብ.ቡድን ነበሩ (July 2011-Oct 2011)
13 የተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖችን የማሰልጠን ልምድ , ከ underdogs ቡድኖች ጋር ኦቨርአቺቭ የማድረግ ስምና ዝና :: የማሊ ቡድን ወጣት ባለተሰጥኦ ተጫዋቾች ያሉት ነው::
ዛምቢያ ከቀድሞው አሰልጣኟ ጋር ተለያይታለች, ከቶርናመንቱ ሁለት ወራት በፊት (የቀድሞው የቼልሲ አሰልጣኝ Avram Grant) ታድያ ረዳታቸው የነበረው Moses Sichone የዋና አሰልጣኝነት ሚናውን ተረክቧል:: የ 2012 ቻምፒየኖቹ በ2025 በዚህስ ውድድር?
ኮሞሮስ ዝቅተኛ ግምት ከሚሰጣቸው ሀገራት ናት, በውድድሩ ከሚሳተፉ ሃገራት አነስተኛ የህዝብ ቁጥር ያላት:: በጣልያናዊው አሰልጣኝ Stefano Cusin ትመራለች::
ምድብ 2. ግብጽ 🇪🇬 , ደቡብ አፍሪካ 🇿🇦 , አንጎላ 🇦🇴 , ዚምባብዌ 🇿🇼
በአፍሪካ ዋንጫ በጣም ስኬታማዋ ሀገር ግብጽ, 7 ዋንጫዎች:: ይሁን እንጂ በቅርብ ዓመታት የዋንጫ ድርቅ መቷታል ከ 2010 በሗላ ዋንጫ አላሸነፈችም:: ሞሃመድ ሳላህ የመጀመሪያ International title ለማሳካት:: ይህ ቡድን ሌሎችም የሚጠበቁ ተጫዋቾች አሉት ኦማር ማርሙሽ እና ሞስታፋ ሞሃመድ:: በተጫዋችነትም በአሰልጣኝነትም ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር ልምድ ያለው ሆሳም ሀሳን በውድድሩ ይጠበቃል::
ደቡብ አፍሪካ ስድስት በአውሮፓ የሚጫወቱ ሁለት ደግሞ በሳውዲ አራቢያ የሚጫወቱ እና ሌሎች ከዚያው ከሀገር ውስጥ የተሰባሰቡ:: ይህ ቡድን በ Hugo Broos ስር በታክቲካል ኢንተለጀንሱ ይታወቃል:: ምርጥ ፐርፎርማንስ እንደሚያሳይ እና ለየትኛውም ቡድን ከባድ ተጋጣሚ እንደሚሆን ይጠበቃል::
አንጎላ በቅርብ ዓመታት በተከታታይ ኦቨርአቺቨር ሆናለች:: ስብስቧ የወጣት እና ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች ውህድ ነው:: ፈረንሳዊው አሰልጣኝ Patrice Beaumelle ቡድኑን ረዘም ላለ ጊዜ ይዘውት ከቆዩት Pedro Gonçalves ኅላፊነቱን ተረክበዋል::
ዚምባብዌ ከወር በፊት ነው አዲስ አሰልጣኝ የሾመችው Mario Marinică . የዎልቭሱ አማካይ Marshall Munetsi ከጉዳቱ አገግሞ ይህንን ስብስብ ተቀላቅሏል::
ምድብ 3. ናይጄሪያ 🇳🇬 , ቱኒዚያ 🇹🇳 , ዩጋንዳ(ኡጋንዳ) 🇺🇬 , ታንዛኒያ 🇹🇿
ያለፈው ውድድር የፍጻሜ ተፋላሚ , ለዓለም ዋንጫ ውድድር ማለፍ ያልቻለችው ሀገር ከዚህ የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ብዙ ትጠብቃለች, ቁጭትም አለ:: ማጥቃት ላይ ቅንጦት ያለው ቡድን Victor Osimhen እና Lookman በስብስቧ አሉ:: Tolu Arokodare እና Victor Boniface በዚህ ስብስብ ውስጥ አልተካተቱም:: በዚህ ቡድን ፈተናው የሚድፊልዱን ሚዛን መፈለግ ነው:: Eric Chelle አይቮሪ ኮስት ተወልዶ ለማሊ የተጫወተው ይህ ሰው ናይጄሪያን በዋና አሰልጣኝነት ይመራል::
ቱኒዚያ የ Sami Trabelsi ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ በ 10 ጨዋታዎች ክሊን ሺት የጠበቀ , ማንም ሊገጥመው የማይፈልገው ግን ደግሞ በማጥቃት ደካማ:: ይህ ቡድን ከፊት መስመር ተጫዋቾች ድጋፍ ይፈልጋል::
ዩጋንዳ (ኡጋንዳ) አሰልጣኝ Paul Put ለተጫዋቾች ጥሪ ያቀረቡት ከሁልም ዓለማት ነው:: ከ USL ቻምፒየንሺፕ አሜሪካ, Thailand, Tanzania, Rwanda, Romania , Czechia እና ከእንግሊዝ 3ተኛ ቲር Burton Albion. ልዩ ልዩ ዓይነት ተጫዋቾችን የያዘውን ስብስብ እንደ ቡድን ፎርም ማድረግ ለአሰልጣኙ ከባድ ስራ::
ታንዛኒያ ካለፉት አራት የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ለሶስተኛ ጊዜ ስትሳተፍ ነው:: በሚቀጥለውም ስለመሳተፏ ዋስትና አላት, ከኬንያ እና ዩጋንዳ (ኡጋንዳ) ጋር በጋራ ውድድሩን ስለምታዘጋጅ:: የአዲሱ አሰልጣኝ (አርጀንቲናዊው Miguel Gamondi) ቀዳሚ ዋና ነገር ቡድኑን የጨዋታዎች አሸናፊ ማድረግ ነው:: እኚህ አሰልጣኝ ያለፉትን 25 ዓመታት በአህጉሪቱ አሳልፈዋል, የተለያዩ ክለቦችን በማሰልጠን, ብሔራዊ ቡድን ሲይዙ ግን የመጀመሪያቸው ነው::
ምድብ 4. ሴኔጋል 🇸🇳 , ዲ.ኮንጎ 🇨🇩, ቤኒን 🇧🇯 , ቦትስዋና 🇧🇼
የ 2021 የአፍሪካ ዋንጫ ቻምፒየን ሴኔጋል ለአሰልጣኟ Pape Thaiw የመጀመሪያው ሜጀር ቶርናመንት ነው:: ሴኔጋል ባለፉት 23 competitive ጨዋታዎች አልተሸነፈችም, በጣም ጥሩ ስብስብ አላት::
ዲ.ኮንጎ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የነበራት ደካማ ብቃት በዚህም ውድድር ዝቅተኛ ግምት እንዲሰጣት ያደርጋል:: ቁልፍ የፊት መስመር ተጫዋቿ Yoane Wissa በስብስቡ የለም::
ቤኒን ባለፉት ሁለት ውድድሮች ካለመሳተፍ በሗላ ተመልሳለች, ለአራተኛ ጊዜ በውድድሩ ትካፈላለች: ጀርመናዊው አሰልጣኝ Gernot Rohr በዉድድሩ የቡድኑን የመሸነፍ ታሪክ ወደ አሸናፊነት የመቀየር ዕድል አላቸው::
ቦትስዋና በዚህ ውድድር ዝቅተኛ ግምት የተሰጠው ቡድን የያዘች ሀገር:: ለሁለተኛ ጊዜ በውድድሩ ትሳተፋለች::
ምድብ 5. አልጄሪያ 🇩🇿 , ቡርኪና ፋሶ 🇧🇫, ኢኳቶሪያል ጊኒ 🇬🇶, ሱዳን 🇸🇩
አልጄሪያ በውድድሩ ዋነኛ የዋንጫ ተፎካካሪ ነገር ግን የምድብ ጨዋታዎች ላይ መበርታት , ከምድብ ማለፍ ይቀድማል:: Vladimir Petković ቡድኑን በጥሩ ስኬት ይዘውታል, እውነተኛ ፈተናቸው ግን የሚጀምረው አሁን ነው:: የቡድኑን መከላከል ማጠንከር ከአጥቂ ተጫዋቾች ምርጣቸውን ማውጣት::
ቡርኪና ፋሶ Brama Traoré በብሔራዊ ቡድኑ ዙሪያ ቆይቷል ረዳት አሰልጣኝ እና የታዳጊዎች አሰልጣኝ ሆኖ, አሁን ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በዋና አሰልጣኝነት:: ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች አሉት Bertrand Traoré, Edmond Tapsoba, እና Hervè Koffi ወጣቶቹን Dango Ouattara እና Cyriaque Irié ጨምሮ::
ኢኳቶሪያል ጊኒ ያለፈው የአፍሪካ ዋንጫ ሰርፕራይዚንግ ቡድን የፍጻሜ ተፋላሚዎች ከነበሩት ናይጄሪያ እና አይቮሪ ኮስትም በላይ ምድቡን በበላይነት:: አሁንም ጥራት እና ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች በስብስቧ ይዛለች::
ሱዳን ባለፋት አስር ዓመታት ለሁለተኛ ጊዜ , ከ 1976 ጀምሮ ለአራተኛ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ ውድድር:: Kwesi Appiah ሱዳን አቅሟን እንድትጠቀም ያስቻለ አሰልጣኝ ነው:: ሱዳን እዚህ ስኬት ላይ የደረሰችው በጦርነት ውስጥ አልፋ ነው እናም በሜዳ ላይ እያንዳንዱ ጨዋታ ከእግር ኳስም በላይ ትርጉም አለው::
ምድብ 6. አይቮሪ ኮስት 🇨🇮 , ካሜሩን 🇨🇲 , ጋቦን 🇬🇦, ሞዛምቢክ 🇲🇿
Defending champion አይቮሪ ኮስት ለሶስተኛ ጊዜ ዋንጫውን ስታሸንፍ በውድድሩ ታሪክ አስገራሚ ክስተቶች ነበሩ:: በምድብ ጨዋታ ሁለቱን ተሸንፋ, በውድድሩ መሀል የአሰልጣኝ ለውጥ አድርጋ, በጥሎ ማለፍ ውጤቶችን ቀልብሳ ድል በማድረግ:: አሰልጣኙ Emerse Faé ተስፋ አለው በስብስቡ ምርጫ ላይም ቦልድ ውሳኔዎችንም አሳልፏል Nicolas Pépé እና Simon Adingra በመተው ወጣቶቹ Yan Diomande እና Bazoumana Touré ተካተዋል:: ልምድ እና ጥራት ያላቸው ተጫዋቾች ያሉት ብርቱ የtitle defence ስብስብ::
ካሜሩን የአምስት ጊዜ የዋንጫው ባለክብር አሁን ላይ ግን የእግር ኳስ አመራሯ ችግር ውስጥ የተጠመደ የተወሳሰበ ነው ብጥብጥ, ሁከት ያለበት:: ያልተረጋጋ! ለውድድሩ ሁለት የተለያየ ስብስብ ያላት አንደኛው የእግር ኳስ ማህበሩን እና አዲስ የተቀጠረውን አሰልጣኝ David Pagouን ወክሎ , ሌላኛው ደግሞ በቡድኑ አሰልጣኝነት ውል ካለው ከ Marc Brys ወገን:: የችግሩ ምንጭ የ Brys እና የ FA ፕሬዝዳንቱ Samuel Etò ግጭት ነው::
ጋቦን ባለፈው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር አልነበረችም አሁን ተመልሳለች::
ሞዛምቢክ በውድድሩ ላይ ለስድስተኛ ጊዜ ትሳተፋለች , በጨዋታ የመጀመሪያ አሸናፊነት ለማግኘት:: የአሰልጣኙ Chiquinho Conde ስብስብ ያልተቀየረ, አብሮ የቆየ ነው:: የ 42 ዓመቱ Domingues ጨዋታ የሚያደርግ ከሆነ በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ በእድሜ ትልቁ outfield player ይሆናል::
ሰላም ጎሳዬ ለፋስት መረጃ
ምድብ 1. ሞሮኮ 🇲🇦, ማሊ 🇲🇱, ዛምቢያ 🇿🇲, ኮሞሮስ 🇰🇲
ሞሮኮ በ 2030 የዓለም ዋንጫን በማዘጋጀት በአፍሪካ ሁለተኛዋ ሀገር ለመሆን እየተዘጋጀች ነው:: ጥራታቸውን የጠበቁ መሰረተ ልማቶች ላይ ኢንቨስት እያደረገች ነው:: ከዚያም በላይ ደግሞ ቶፕ ክላስ ቡድን መገንባት:: ለዚያም ነው በዚህ የአፍሪካ ዋንጫ ከ favorite ቡድኖች አንዷ ሆና ግምት የተሰጣት:: ዋና አሰልጣኙ Walid Regragui በቡድኑ አስደናቂ የሚባል ትራክ ሪከርድ አለው:: የሞሮኮ ቡድን በ elite-level ያሉ ተጫዋቾችን የያዘ ስብስብ ነው::
በዚህ ምድብ ሌላኛዋ ሀገር ማሊ ናት:: የማሊ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ Tom Saintfiet , እኚህ ሰው በኢትዮጵያ ብ.ቡድን ነበሩ (July 2011-Oct 2011)
13 የተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖችን የማሰልጠን ልምድ , ከ underdogs ቡድኖች ጋር ኦቨርአቺቭ የማድረግ ስምና ዝና :: የማሊ ቡድን ወጣት ባለተሰጥኦ ተጫዋቾች ያሉት ነው::
ዛምቢያ ከቀድሞው አሰልጣኟ ጋር ተለያይታለች, ከቶርናመንቱ ሁለት ወራት በፊት (የቀድሞው የቼልሲ አሰልጣኝ Avram Grant) ታድያ ረዳታቸው የነበረው Moses Sichone የዋና አሰልጣኝነት ሚናውን ተረክቧል:: የ 2012 ቻምፒየኖቹ በ2025 በዚህስ ውድድር?
ኮሞሮስ ዝቅተኛ ግምት ከሚሰጣቸው ሀገራት ናት, በውድድሩ ከሚሳተፉ ሃገራት አነስተኛ የህዝብ ቁጥር ያላት:: በጣልያናዊው አሰልጣኝ Stefano Cusin ትመራለች::
ምድብ 2. ግብጽ 🇪🇬 , ደቡብ አፍሪካ 🇿🇦 , አንጎላ 🇦🇴 , ዚምባብዌ 🇿🇼
በአፍሪካ ዋንጫ በጣም ስኬታማዋ ሀገር ግብጽ, 7 ዋንጫዎች:: ይሁን እንጂ በቅርብ ዓመታት የዋንጫ ድርቅ መቷታል ከ 2010 በሗላ ዋንጫ አላሸነፈችም:: ሞሃመድ ሳላህ የመጀመሪያ International title ለማሳካት:: ይህ ቡድን ሌሎችም የሚጠበቁ ተጫዋቾች አሉት ኦማር ማርሙሽ እና ሞስታፋ ሞሃመድ:: በተጫዋችነትም በአሰልጣኝነትም ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር ልምድ ያለው ሆሳም ሀሳን በውድድሩ ይጠበቃል::
ደቡብ አፍሪካ ስድስት በአውሮፓ የሚጫወቱ ሁለት ደግሞ በሳውዲ አራቢያ የሚጫወቱ እና ሌሎች ከዚያው ከሀገር ውስጥ የተሰባሰቡ:: ይህ ቡድን በ Hugo Broos ስር በታክቲካል ኢንተለጀንሱ ይታወቃል:: ምርጥ ፐርፎርማንስ እንደሚያሳይ እና ለየትኛውም ቡድን ከባድ ተጋጣሚ እንደሚሆን ይጠበቃል::
አንጎላ በቅርብ ዓመታት በተከታታይ ኦቨርአቺቨር ሆናለች:: ስብስቧ የወጣት እና ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች ውህድ ነው:: ፈረንሳዊው አሰልጣኝ Patrice Beaumelle ቡድኑን ረዘም ላለ ጊዜ ይዘውት ከቆዩት Pedro Gonçalves ኅላፊነቱን ተረክበዋል::
ዚምባብዌ ከወር በፊት ነው አዲስ አሰልጣኝ የሾመችው Mario Marinică . የዎልቭሱ አማካይ Marshall Munetsi ከጉዳቱ አገግሞ ይህንን ስብስብ ተቀላቅሏል::
ምድብ 3. ናይጄሪያ 🇳🇬 , ቱኒዚያ 🇹🇳 , ዩጋንዳ(ኡጋንዳ) 🇺🇬 , ታንዛኒያ 🇹🇿
ያለፈው ውድድር የፍጻሜ ተፋላሚ , ለዓለም ዋንጫ ውድድር ማለፍ ያልቻለችው ሀገር ከዚህ የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ብዙ ትጠብቃለች, ቁጭትም አለ:: ማጥቃት ላይ ቅንጦት ያለው ቡድን Victor Osimhen እና Lookman በስብስቧ አሉ:: Tolu Arokodare እና Victor Boniface በዚህ ስብስብ ውስጥ አልተካተቱም:: በዚህ ቡድን ፈተናው የሚድፊልዱን ሚዛን መፈለግ ነው:: Eric Chelle አይቮሪ ኮስት ተወልዶ ለማሊ የተጫወተው ይህ ሰው ናይጄሪያን በዋና አሰልጣኝነት ይመራል::
ቱኒዚያ የ Sami Trabelsi ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ በ 10 ጨዋታዎች ክሊን ሺት የጠበቀ , ማንም ሊገጥመው የማይፈልገው ግን ደግሞ በማጥቃት ደካማ:: ይህ ቡድን ከፊት መስመር ተጫዋቾች ድጋፍ ይፈልጋል::
ዩጋንዳ (ኡጋንዳ) አሰልጣኝ Paul Put ለተጫዋቾች ጥሪ ያቀረቡት ከሁልም ዓለማት ነው:: ከ USL ቻምፒየንሺፕ አሜሪካ, Thailand, Tanzania, Rwanda, Romania , Czechia እና ከእንግሊዝ 3ተኛ ቲር Burton Albion. ልዩ ልዩ ዓይነት ተጫዋቾችን የያዘውን ስብስብ እንደ ቡድን ፎርም ማድረግ ለአሰልጣኙ ከባድ ስራ::
ታንዛኒያ ካለፉት አራት የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ለሶስተኛ ጊዜ ስትሳተፍ ነው:: በሚቀጥለውም ስለመሳተፏ ዋስትና አላት, ከኬንያ እና ዩጋንዳ (ኡጋንዳ) ጋር በጋራ ውድድሩን ስለምታዘጋጅ:: የአዲሱ አሰልጣኝ (አርጀንቲናዊው Miguel Gamondi) ቀዳሚ ዋና ነገር ቡድኑን የጨዋታዎች አሸናፊ ማድረግ ነው:: እኚህ አሰልጣኝ ያለፉትን 25 ዓመታት በአህጉሪቱ አሳልፈዋል, የተለያዩ ክለቦችን በማሰልጠን, ብሔራዊ ቡድን ሲይዙ ግን የመጀመሪያቸው ነው::
ምድብ 4. ሴኔጋል 🇸🇳 , ዲ.ኮንጎ 🇨🇩, ቤኒን 🇧🇯 , ቦትስዋና 🇧🇼
የ 2021 የአፍሪካ ዋንጫ ቻምፒየን ሴኔጋል ለአሰልጣኟ Pape Thaiw የመጀመሪያው ሜጀር ቶርናመንት ነው:: ሴኔጋል ባለፉት 23 competitive ጨዋታዎች አልተሸነፈችም, በጣም ጥሩ ስብስብ አላት::
ዲ.ኮንጎ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የነበራት ደካማ ብቃት በዚህም ውድድር ዝቅተኛ ግምት እንዲሰጣት ያደርጋል:: ቁልፍ የፊት መስመር ተጫዋቿ Yoane Wissa በስብስቡ የለም::
ቤኒን ባለፉት ሁለት ውድድሮች ካለመሳተፍ በሗላ ተመልሳለች, ለአራተኛ ጊዜ በውድድሩ ትካፈላለች: ጀርመናዊው አሰልጣኝ Gernot Rohr በዉድድሩ የቡድኑን የመሸነፍ ታሪክ ወደ አሸናፊነት የመቀየር ዕድል አላቸው::
ቦትስዋና በዚህ ውድድር ዝቅተኛ ግምት የተሰጠው ቡድን የያዘች ሀገር:: ለሁለተኛ ጊዜ በውድድሩ ትሳተፋለች::
ምድብ 5. አልጄሪያ 🇩🇿 , ቡርኪና ፋሶ 🇧🇫, ኢኳቶሪያል ጊኒ 🇬🇶, ሱዳን 🇸🇩
አልጄሪያ በውድድሩ ዋነኛ የዋንጫ ተፎካካሪ ነገር ግን የምድብ ጨዋታዎች ላይ መበርታት , ከምድብ ማለፍ ይቀድማል:: Vladimir Petković ቡድኑን በጥሩ ስኬት ይዘውታል, እውነተኛ ፈተናቸው ግን የሚጀምረው አሁን ነው:: የቡድኑን መከላከል ማጠንከር ከአጥቂ ተጫዋቾች ምርጣቸውን ማውጣት::
ቡርኪና ፋሶ Brama Traoré በብሔራዊ ቡድኑ ዙሪያ ቆይቷል ረዳት አሰልጣኝ እና የታዳጊዎች አሰልጣኝ ሆኖ, አሁን ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በዋና አሰልጣኝነት:: ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች አሉት Bertrand Traoré, Edmond Tapsoba, እና Hervè Koffi ወጣቶቹን Dango Ouattara እና Cyriaque Irié ጨምሮ::
ኢኳቶሪያል ጊኒ ያለፈው የአፍሪካ ዋንጫ ሰርፕራይዚንግ ቡድን የፍጻሜ ተፋላሚዎች ከነበሩት ናይጄሪያ እና አይቮሪ ኮስትም በላይ ምድቡን በበላይነት:: አሁንም ጥራት እና ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች በስብስቧ ይዛለች::
ሱዳን ባለፋት አስር ዓመታት ለሁለተኛ ጊዜ , ከ 1976 ጀምሮ ለአራተኛ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ ውድድር:: Kwesi Appiah ሱዳን አቅሟን እንድትጠቀም ያስቻለ አሰልጣኝ ነው:: ሱዳን እዚህ ስኬት ላይ የደረሰችው በጦርነት ውስጥ አልፋ ነው እናም በሜዳ ላይ እያንዳንዱ ጨዋታ ከእግር ኳስም በላይ ትርጉም አለው::
ምድብ 6. አይቮሪ ኮስት 🇨🇮 , ካሜሩን 🇨🇲 , ጋቦን 🇬🇦, ሞዛምቢክ 🇲🇿
Defending champion አይቮሪ ኮስት ለሶስተኛ ጊዜ ዋንጫውን ስታሸንፍ በውድድሩ ታሪክ አስገራሚ ክስተቶች ነበሩ:: በምድብ ጨዋታ ሁለቱን ተሸንፋ, በውድድሩ መሀል የአሰልጣኝ ለውጥ አድርጋ, በጥሎ ማለፍ ውጤቶችን ቀልብሳ ድል በማድረግ:: አሰልጣኙ Emerse Faé ተስፋ አለው በስብስቡ ምርጫ ላይም ቦልድ ውሳኔዎችንም አሳልፏል Nicolas Pépé እና Simon Adingra በመተው ወጣቶቹ Yan Diomande እና Bazoumana Touré ተካተዋል:: ልምድ እና ጥራት ያላቸው ተጫዋቾች ያሉት ብርቱ የtitle defence ስብስብ::
ካሜሩን የአምስት ጊዜ የዋንጫው ባለክብር አሁን ላይ ግን የእግር ኳስ አመራሯ ችግር ውስጥ የተጠመደ የተወሳሰበ ነው ብጥብጥ, ሁከት ያለበት:: ያልተረጋጋ! ለውድድሩ ሁለት የተለያየ ስብስብ ያላት አንደኛው የእግር ኳስ ማህበሩን እና አዲስ የተቀጠረውን አሰልጣኝ David Pagouን ወክሎ , ሌላኛው ደግሞ በቡድኑ አሰልጣኝነት ውል ካለው ከ Marc Brys ወገን:: የችግሩ ምንጭ የ Brys እና የ FA ፕሬዝዳንቱ Samuel Etò ግጭት ነው::
ጋቦን ባለፈው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር አልነበረችም አሁን ተመልሳለች::
ሞዛምቢክ በውድድሩ ላይ ለስድስተኛ ጊዜ ትሳተፋለች , በጨዋታ የመጀመሪያ አሸናፊነት ለማግኘት:: የአሰልጣኙ Chiquinho Conde ስብስብ ያልተቀየረ, አብሮ የቆየ ነው:: የ 42 ዓመቱ Domingues ጨዋታ የሚያደርግ ከሆነ በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ በእድሜ ትልቁ outfield player ይሆናል::
ሰላም ጎሳዬ ለፋስት መረጃ
6 months ago
አፋን ኦሮሞ ትችላላችሁ እንዴ?
ፋስት መረጃ በአማርኛ ከሚያቀርበው መረጃዎች በተጨማሪ በአፋን ኦሮሞ እና በእንግሊዘኛ መረጃዎችን ለእናንተ ያደርሳል። አፋን ኦሮሞ የምትችሉ ከታች ያለውን ሊንክ በመክፈት ፎሎ ማድረግ ትችላላችሁ!
https://www.facebook.com/s...
ፋስት መረጃ በአማርኛ ከሚያቀርበው መረጃዎች በተጨማሪ በአፋን ኦሮሞ እና በእንግሊዘኛ መረጃዎችን ለእናንተ ያደርሳል። አፋን ኦሮሞ የምትችሉ ከታች ያለውን ሊንክ በመክፈት ፎሎ ማድረግ ትችላላችሁ!
https://www.facebook.com/s...
6 months ago
እንግሊዘኛ ትችላላችሁ?
ፋስት መረጃ በአማርኛ ከሚያቀርበው መረጃዎች በተጨማሪ በአፋን ኦሮሞ እና በእንግሊዘኛ መረጃዎችን ለእናንተ ያደርሳል። እንግሊዘኛ የምትችሉ ከታች ያለውን ሊንክ በመክፈት ፎሎ ማድረግ ትችላላችሁ!
https://www.facebook.com/s...
ፋስት መረጃ በአማርኛ ከሚያቀርበው መረጃዎች በተጨማሪ በአፋን ኦሮሞ እና በእንግሊዘኛ መረጃዎችን ለእናንተ ያደርሳል። እንግሊዘኛ የምትችሉ ከታች ያለውን ሊንክ በመክፈት ፎሎ ማድረግ ትችላላችሁ!
https://www.facebook.com/s...
Sponsored by
Surafel
Comments