33 mins. ago
አዲስ አበባ ፡ የኤምኤምኤ እና የቦክስ ስፖርት ውድድር ሊካሄድ ነው
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት የንክኪ ስፖርት ሁነቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነው የኢትዮ ፋይት ናይት የውድድር መድረክ ይፋ ሆኗል::
ዝግጅቱ የአዲስ አበባ ኪክ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ነሀሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (Aug 29/2026) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል::
በዚህ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ላይ በድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገራችንን ወክለው ደግሞ ቢኒያም ሽብሬ፣ ክብሮም ንጉሴ እና አገረሰላም አርባን ጨምሮ በርካታ ስፖርተኞች ወደ መድረኩ ይወርዳሉ::
በጠቅላላው ከ6 እስከ 8 የሚደርሱ ብርቱ ፍልሚያዎች የሚስተናገዱ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የተመረጡት በውድድር ታሪካቸው፣ በዓለም አቀፍ ልምዳቸው፣ በአካል ብቃት ጥንካሬያቸው እና ማራኪ ትዕይንት ማሳየት በሚችሉበት ብቃታቸው ላይ ተመስርቶ ነው::
አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ህግ መሰረት አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ፣ የክብደት ልኬትና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደቶችን ያጠናቀቁ ሲሆን ዝርዝር የክብደት መጠናቸውና ዜግነታቸው በቅርቡ ይፋ ይደረጋል::
ይህንን ታሪካዊ ፍልሚያ ለመታደም ከ8,000 እስከ 10,000 የሚደርሱ የስፖርት አፍቃሪዎች በአዳራሹ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አዘጋጆቹ የአፍሪካንና የሀገራችንን ስፖርታዊ አቅም ለዓለም የሚያስተዋውቅ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ፍጹም ሙያዊ ብቃት የተላበሰ ዝግጅት ለማቅረብ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል::
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ የንክኪ ስፖርቶችን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ አትሌቶች ሙያዊ መድረክ መፍጠር፣ ወጣቶችን ማነሳሳት፣ ስፖርታዊ ቱሪዝምን በአዲስ አበባና በኢትዮጵያ ማስፋፋት እንዲሁም ሀገራችንን የዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዕከል ማድረግ ነው::
ዝግጅቱ የሚስተናገድበት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር (AICC) ዘመናዊ የዲጂታል ምስልና የድምፅ መገልገያ መሳሪያዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለታዳሚው ምቹ መዝናኛን ለመፍጠር ተመራጭ አድርጎታል::
ገራሚ ኢቨንትስ የዝግጅቱን አጠቃላይ የፕሮዳክሽን ስራ በማስተናገድ ከባለቤቶቹ ጋር በጋራ የሚሰራ ሲሆን ለአትሌቶች ስልጠና፣ ለደህንነት፣ ለቦታ ዝግጅትና ለሎጂስቲክስ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሷል::
ይህንን ውድድር በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማዘጋጀት የታቀደ በመሆኑ፣ የዝግጅቱን ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በስፖንሰርሺፕ፣ በሚዲያ ሽፋን፣ በዲጂታል ግብይትና በቪአይፒ ተሳትፎ ላይ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል::
የመግቢያ ትኬት ዋጋንና የስርጭት ሽፋንን በተመለከተ ከሚዲያ አጋሮች ጋር ውይይት እየተደረገ ሲሆን የቴሌቪዥንና የዲጂታል ቀጥታ ስርጭት መረጃዎች በቅርቡ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል::
#mma #boxing #ethiofightnight #sportstourism #aicc #ethiopianathletes #geramievents #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት የንክኪ ስፖርት ሁነቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነው የኢትዮ ፋይት ናይት የውድድር መድረክ ይፋ ሆኗል::
ዝግጅቱ የአዲስ አበባ ኪክ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ነሀሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (Aug 29/2026) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል::
በዚህ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ላይ በድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገራችንን ወክለው ደግሞ ቢኒያም ሽብሬ፣ ክብሮም ንጉሴ እና አገረሰላም አርባን ጨምሮ በርካታ ስፖርተኞች ወደ መድረኩ ይወርዳሉ::
በጠቅላላው ከ6 እስከ 8 የሚደርሱ ብርቱ ፍልሚያዎች የሚስተናገዱ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የተመረጡት በውድድር ታሪካቸው፣ በዓለም አቀፍ ልምዳቸው፣ በአካል ብቃት ጥንካሬያቸው እና ማራኪ ትዕይንት ማሳየት በሚችሉበት ብቃታቸው ላይ ተመስርቶ ነው::
አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ህግ መሰረት አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ፣ የክብደት ልኬትና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደቶችን ያጠናቀቁ ሲሆን ዝርዝር የክብደት መጠናቸውና ዜግነታቸው በቅርቡ ይፋ ይደረጋል::
ይህንን ታሪካዊ ፍልሚያ ለመታደም ከ8,000 እስከ 10,000 የሚደርሱ የስፖርት አፍቃሪዎች በአዳራሹ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አዘጋጆቹ የአፍሪካንና የሀገራችንን ስፖርታዊ አቅም ለዓለም የሚያስተዋውቅ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ፍጹም ሙያዊ ብቃት የተላበሰ ዝግጅት ለማቅረብ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል::
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ የንክኪ ስፖርቶችን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ አትሌቶች ሙያዊ መድረክ መፍጠር፣ ወጣቶችን ማነሳሳት፣ ስፖርታዊ ቱሪዝምን በአዲስ አበባና በኢትዮጵያ ማስፋፋት እንዲሁም ሀገራችንን የዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዕከል ማድረግ ነው::
ዝግጅቱ የሚስተናገድበት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር (AICC) ዘመናዊ የዲጂታል ምስልና የድምፅ መገልገያ መሳሪያዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለታዳሚው ምቹ መዝናኛን ለመፍጠር ተመራጭ አድርጎታል::
ገራሚ ኢቨንትስ የዝግጅቱን አጠቃላይ የፕሮዳክሽን ስራ በማስተናገድ ከባለቤቶቹ ጋር በጋራ የሚሰራ ሲሆን ለአትሌቶች ስልጠና፣ ለደህንነት፣ ለቦታ ዝግጅትና ለሎጂስቲክስ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሷል::
ይህንን ውድድር በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማዘጋጀት የታቀደ በመሆኑ፣ የዝግጅቱን ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በስፖንሰርሺፕ፣ በሚዲያ ሽፋን፣ በዲጂታል ግብይትና በቪአይፒ ተሳትፎ ላይ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል::
የመግቢያ ትኬት ዋጋንና የስርጭት ሽፋንን በተመለከተ ከሚዲያ አጋሮች ጋር ውይይት እየተደረገ ሲሆን የቴሌቪዥንና የዲጂታል ቀጥታ ስርጭት መረጃዎች በቅርቡ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል::
#mma #boxing #ethiofightnight #sportstourism #aicc #ethiopianathletes #geramievents #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 hours ago
የአለልኝ አዘነ ገዳዮች ተብለው የ16 እና 15 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ግለሰቦች፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲለቀቁ ተወሰነ።"
የአለልኝ አዘነ ጉዳይ፡ የይግባኝ ሰሚው ችሎት ውሳኔ ቤተሰቡን ለከፍተኛ ሀዘን እና ድንጋጤ ዳርጓል
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ማህበረሰብን በከፍተኛ ሁኔታ ያሳዘነው እና የብዙ ኢትዮጵያውያንን ልብ ሰርስሮ የገባው የሟች አለልኝ አዘነ የፍትሕ ሂደት፣ አሁን ላይ አሳዛኝ እና አነጋጋሪ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ባለፈው ጊዜ በግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በቅደም ተከተል 16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወ/ሮ አደይ ጌታቸው እና ሉንጎ ሉቃስ፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲሰናበቱ መወሰኑን የሟች ቤተሰቦች አረጋግጠዋል።
ይህ ውሳኔ ቤተሰቡን ከዚህ ቀደም ከነበሩበት ሀዘን ባሻገር፣ ለከፍተኛ የስነ-ልቦና ቀውስ እና ብስጭት ዳርጓቸዋል። የቤተሰብ አባላት እንደገለጹት፣ ወንጀሉ ተፈጽሞ፣ ጥፋተኞች ተለይተውና በፍርድ ቤት ውሳኔ ተላልፎባቸው የነበረ ቢሆንም፣ በይግባኝ ሰበብ እንዲህ በነፃ መለቀቃቸው ተቀባይነት የሌለው እና የፍትሕ ሥርዓቱን የሚያጠይቅ ሆኖ አግኝተውታል።
በችሎቱ ውሎ ወቅት የነበረው ውጥረት፣ የቤተሰቡ ለቅሶ እና ሰቆቃ፣ እንዲሁም በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የነበራቸው የመጨረሻ ተስፋ መሟጠጡ መላውን የፍትህ ናፋቂ ማህበረሰብ በእጅጉ አሳዝኗል።
ቤተሰቡ እንደገለጸው፣ ድርጊቱ የተፈጸመበት ቦታ እርባምንጭ ሆኖ ሳለ፣ የፍርድ ሂደቱ ወደ ወላይታ ሶዶ ተዛውሮ የወሰደው ቅርፅና ውጤት ለቤተሰቡ ድርብ ስቃይ ሆኗል።
ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ የፍትሕ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክርክር ሊያስነሳ እንደሚችል እየተነገረ ነው። በተለይም የወንጀል ድርጊት ተረጋግጦ በነበረበት መዝገብ ላይ እንዲህ ያለ የይግባኝ ውሳኔ መሰጠቱ፣ በፍትሕ ተቋማት ላይ ያለው የመተማመን ቀውስ እንዲባባስ ማድረጉ አልቀረም።
የሕግ ባለሙያዎች እንደሚናገሩት፣ ጉዳዩ በሰብአዊ መብት እና በሕግ የበላይነት መርህ መሠረት በሰፊው ሊጤን የሚገባው ሆኗል።
የሟች ቤተሰብ አባላት በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ይገኛሉ፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናቸው እንዲቆም እና የፍትሕ ጥያቄውን እንዲያቀናጅ ጥሪ አቅርበዋል።
Via ጉርሻ
የአለልኝ አዘነ ጉዳይ፡ የይግባኝ ሰሚው ችሎት ውሳኔ ቤተሰቡን ለከፍተኛ ሀዘን እና ድንጋጤ ዳርጓል
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ማህበረሰብን በከፍተኛ ሁኔታ ያሳዘነው እና የብዙ ኢትዮጵያውያንን ልብ ሰርስሮ የገባው የሟች አለልኝ አዘነ የፍትሕ ሂደት፣ አሁን ላይ አሳዛኝ እና አነጋጋሪ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ባለፈው ጊዜ በግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በቅደም ተከተል 16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወ/ሮ አደይ ጌታቸው እና ሉንጎ ሉቃስ፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲሰናበቱ መወሰኑን የሟች ቤተሰቦች አረጋግጠዋል።
ይህ ውሳኔ ቤተሰቡን ከዚህ ቀደም ከነበሩበት ሀዘን ባሻገር፣ ለከፍተኛ የስነ-ልቦና ቀውስ እና ብስጭት ዳርጓቸዋል። የቤተሰብ አባላት እንደገለጹት፣ ወንጀሉ ተፈጽሞ፣ ጥፋተኞች ተለይተውና በፍርድ ቤት ውሳኔ ተላልፎባቸው የነበረ ቢሆንም፣ በይግባኝ ሰበብ እንዲህ በነፃ መለቀቃቸው ተቀባይነት የሌለው እና የፍትሕ ሥርዓቱን የሚያጠይቅ ሆኖ አግኝተውታል።
በችሎቱ ውሎ ወቅት የነበረው ውጥረት፣ የቤተሰቡ ለቅሶ እና ሰቆቃ፣ እንዲሁም በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የነበራቸው የመጨረሻ ተስፋ መሟጠጡ መላውን የፍትህ ናፋቂ ማህበረሰብ በእጅጉ አሳዝኗል።
ቤተሰቡ እንደገለጸው፣ ድርጊቱ የተፈጸመበት ቦታ እርባምንጭ ሆኖ ሳለ፣ የፍርድ ሂደቱ ወደ ወላይታ ሶዶ ተዛውሮ የወሰደው ቅርፅና ውጤት ለቤተሰቡ ድርብ ስቃይ ሆኗል።
ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ የፍትሕ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክርክር ሊያስነሳ እንደሚችል እየተነገረ ነው። በተለይም የወንጀል ድርጊት ተረጋግጦ በነበረበት መዝገብ ላይ እንዲህ ያለ የይግባኝ ውሳኔ መሰጠቱ፣ በፍትሕ ተቋማት ላይ ያለው የመተማመን ቀውስ እንዲባባስ ማድረጉ አልቀረም።
የሕግ ባለሙያዎች እንደሚናገሩት፣ ጉዳዩ በሰብአዊ መብት እና በሕግ የበላይነት መርህ መሠረት በሰፊው ሊጤን የሚገባው ሆኗል።
የሟች ቤተሰብ አባላት በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ይገኛሉ፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናቸው እንዲቆም እና የፍትሕ ጥያቄውን እንዲያቀናጅ ጥሪ አቅርበዋል።
Via ጉርሻ
4 hours ago
በትግራይ የተከናወነው ፍፁም ህገወጥና እውቅና የሌለው ድርጊት ነው፦ ጄኔራል ሳሞራ የኑስ
የቀድሞው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ የኑስ በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ የፖለቲካና የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ቃለ መጠይቅ አድርገዋል፡፡
ጄኔራሉ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) የትግርኛ ክፍል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በክልሉ በህወሓትና “በአቶ መለስ ዜናዊ ስም ተገን” በማድረግ የሚከናወኑ እንቅስቃሴዎች ሊቆሙ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
በትግራይ ክልል የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር አፍርሶ “የራስ አስተዳደር አዋቀርኩ” የሚለውን አካሄድ የተቃወሙት ጄኔራል ሳሞራ፣ ድርጊቱ ፍጹም ሕገ-ወጥና እውቅና የሌለው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ይህ ቡድን በአክሱም ከተማ ተሰብስቦ ያደረገውን ውሳኔ “ሕጋዊነት የጎደለው መንግሥት ምስረታ” ሲሉ የገለጹት ጄኔራሉ፣ መጀመሪያ በአቶ ጌታቸው ረዳ በመቀጠልም በሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ የሚመሩትን ጊዜያዊ አስተዳደሮች ሥራቸውን እንዳይሠሩና ሕዝቡን ወደ ምርጫ እንዳይወስዱ እንቅፋት ሲፈጠርባቸው መቆየቱንና በመጨረሻም ማኅተምና የአሠራር መሣሪያዎችን በመቀማት የማባረር ተግባር መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡
የክልሉ ፖለቲከኞች ዋና ዓላማ ሥልጣን ብቻ መሆኑንና ይህንን ሥልጣን የሚፈልጉት ከተጠያቂነት ለማምለጥ እንደሆነ የገለጹት ጄኔራሉ፣ የፌዴራል መንግሥት ጉዳዩን በትዕግሥትና በሰላማዊ መንገድ እየያዘበት ያለውን አካሄድ አድንቀዋል፡፡
የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተፈረመበት ወቅት የትግራይ ሕዝብ ከፍተኛ ደስታውን የገለጸ ቢሆንም፣ በክልሉ ያሉት ፖለቲከኞች ግን ወደ ሥልጣን ሽሚያ ማምራታቸውን ጄኔራሉ ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በክልሉ እየተካሄደ ስላለው “የወጣቶች አፈሳ” ሲያብራሩም፣ ድርጊቱ ከሻዕቢያን የድሮ የትግል ስትራቴጂ የተቀዳ መሆኑንና ሻዕቢያ ኢትዮጵያን የማተራመስ ስትራቴጂውን እንዳልቀየረ ገልጸዋል፡፡
ከፌዴራል መንግሥት በጀት እየወሰዱ መንግሥትን “ጠላት” ብሎ መፈረጅ ስህተት መሆኑን የጠቀሱት ጄኔራል ሳሞራ፣ የክልሉ አመራሮች “ከምርጫ በኋላ መንግሥት ይወጋናል” የሚል ፕሮፓጋንዳ ለወጣቶች አፈሳ እየተጠቀሙበት እንደሚገኝና በአንጻሩ መንግሥት ጉዳዩን በጦርነት ለመፍታት ፍላጎት እንደሌለው ገልጸዋል፡፡
ጄኔራል ሳሞራ ለትግራይ ሕዝብና ለወላጆች ባቀረቡት ጥሪም የወላጆች ስጋት የሆነውን የወጣቶች አፈሳ ለመግታት ወላጆች ተደራጅተው ሊቃወሙትና “ልጆቻችንን አንሰጥም” ብለው ሊታገሉ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ምርጫ በተካሄደበት በዚህ ወቅት የትግራይ ሕዝብ እንዳይመርጥ መከልከል እንደሌለበትና በመረጠው መሪ የመተዳደር መብቱ ሊከበርለት እንደሚገባ በመግለጽ የሕዝቡ ዋና ዋስትና እራሱ ሕዝቡ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
EBC
የቀድሞው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ የኑስ በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ የፖለቲካና የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ቃለ መጠይቅ አድርገዋል፡፡
ጄኔራሉ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) የትግርኛ ክፍል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በክልሉ በህወሓትና “በአቶ መለስ ዜናዊ ስም ተገን” በማድረግ የሚከናወኑ እንቅስቃሴዎች ሊቆሙ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
በትግራይ ክልል የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር አፍርሶ “የራስ አስተዳደር አዋቀርኩ” የሚለውን አካሄድ የተቃወሙት ጄኔራል ሳሞራ፣ ድርጊቱ ፍጹም ሕገ-ወጥና እውቅና የሌለው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ይህ ቡድን በአክሱም ከተማ ተሰብስቦ ያደረገውን ውሳኔ “ሕጋዊነት የጎደለው መንግሥት ምስረታ” ሲሉ የገለጹት ጄኔራሉ፣ መጀመሪያ በአቶ ጌታቸው ረዳ በመቀጠልም በሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ የሚመሩትን ጊዜያዊ አስተዳደሮች ሥራቸውን እንዳይሠሩና ሕዝቡን ወደ ምርጫ እንዳይወስዱ እንቅፋት ሲፈጠርባቸው መቆየቱንና በመጨረሻም ማኅተምና የአሠራር መሣሪያዎችን በመቀማት የማባረር ተግባር መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡
የክልሉ ፖለቲከኞች ዋና ዓላማ ሥልጣን ብቻ መሆኑንና ይህንን ሥልጣን የሚፈልጉት ከተጠያቂነት ለማምለጥ እንደሆነ የገለጹት ጄኔራሉ፣ የፌዴራል መንግሥት ጉዳዩን በትዕግሥትና በሰላማዊ መንገድ እየያዘበት ያለውን አካሄድ አድንቀዋል፡፡
የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተፈረመበት ወቅት የትግራይ ሕዝብ ከፍተኛ ደስታውን የገለጸ ቢሆንም፣ በክልሉ ያሉት ፖለቲከኞች ግን ወደ ሥልጣን ሽሚያ ማምራታቸውን ጄኔራሉ ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በክልሉ እየተካሄደ ስላለው “የወጣቶች አፈሳ” ሲያብራሩም፣ ድርጊቱ ከሻዕቢያን የድሮ የትግል ስትራቴጂ የተቀዳ መሆኑንና ሻዕቢያ ኢትዮጵያን የማተራመስ ስትራቴጂውን እንዳልቀየረ ገልጸዋል፡፡
ከፌዴራል መንግሥት በጀት እየወሰዱ መንግሥትን “ጠላት” ብሎ መፈረጅ ስህተት መሆኑን የጠቀሱት ጄኔራል ሳሞራ፣ የክልሉ አመራሮች “ከምርጫ በኋላ መንግሥት ይወጋናል” የሚል ፕሮፓጋንዳ ለወጣቶች አፈሳ እየተጠቀሙበት እንደሚገኝና በአንጻሩ መንግሥት ጉዳዩን በጦርነት ለመፍታት ፍላጎት እንደሌለው ገልጸዋል፡፡
ጄኔራል ሳሞራ ለትግራይ ሕዝብና ለወላጆች ባቀረቡት ጥሪም የወላጆች ስጋት የሆነውን የወጣቶች አፈሳ ለመግታት ወላጆች ተደራጅተው ሊቃወሙትና “ልጆቻችንን አንሰጥም” ብለው ሊታገሉ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ምርጫ በተካሄደበት በዚህ ወቅት የትግራይ ሕዝብ እንዳይመርጥ መከልከል እንደሌለበትና በመረጠው መሪ የመተዳደር መብቱ ሊከበርለት እንደሚገባ በመግለጽ የሕዝቡ ዋና ዋስትና እራሱ ሕዝቡ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
EBC
7 hours ago
ህወሃት ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባ ጠየቀ
#fastmereja I የሕዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ (ህወሃት) ከፍተኛ አመራር የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የፌደራል መንግስቱ በይፋ ማፍረሱንና ክልሉን በከበባ ውስጥ ማድረጉን በመጥቀስ፣ አዲስ ሊቀሰቀስ የሚችለውን አስከፊ ጦርነት ለመግታት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባ ጥሪ አቀረበ።
በትግራይ ክልል ያለውን የፖለቲካ የሥልጣን ክፍተት ለመሙላትና ተቋማዊ ቀጣይነትን ለማረጋገጥ ከ1 ሚሊዮን በላይ የክልሉ ነዋሪዎች የተሳተፉበት ሰፊ ውይይት መደረጉን የገለጸው የህወሃት መግለጫ፣ በዚህም መሠረት በ2012 ዓ.ም የተመረጠው የትግራይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወደ ሉዓላዊ ሥልጣኑ እንዲመለስ መወሰኑን ይፋ አድርጓል። ምክር ቤቱ ወደ ሥራው ሲመለስ አካታች የሆነ የሕግ አስፈጻሚና የዳኝነት መዋቅር እንደሚያዋቅር የተገለጸ ሲሆን፣ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች በካቢኔው ውስጥ የ33 በመቶ (አንድ ሶስተኛ) የሥልጣን ድርሻ እንዲኖራቸው ጥሪ መቅረቡም ገልጿል።
በትግራይ ክልል ያለው ሰብአዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አሁንም እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆኑን የጠቀሰው ይኸው አለም አቀፍ ጥሪ፣ የፌደራል መንግስቱ በነዳጅ እና በንግድ ዕቃዎች ላይ የጣለው እገዳ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን ሙሉ በሙሉ ማሽመድመዱንና ከፍተኛ የዋጋ ንረትን ማስከተሉን ያብራራል። ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በትግራይ ድንበሮች ዙሪያ መጠነ-ሰፊ ወታደራዊ ዝግጅትና ከበባ እያደረገ እንደሚገኝ በመግለጽ፣ ይህ ድርጊት በሕዝቡ ላይ ከፍተኛ የስነ-ልቦና እና የማኅበራዊ ጫና እየፈጠረ መሆኑን ይከሳል።
በተመሳሳይ በምዕራብ ትግራይ የሚገኙ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዳይመለሱ በፌደራል መንግስቱና በአጋሮቹ በኩል እንቅፋት እየተፈጠረባቸው መሆኑንና ዓለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶችም ድጋፋቸውን እያቋረጡ መምጣታቸውን ሰነዱ ያስረዳል።
የቀጣናው የፖለቲካ አቅጣጫ ወደ ግትርነት፣ ወታደራዊ ኃይል አማራጭነትና አንድ ወገንተኝነት እያዘገመ በመሆኑ አዲስ ጦርነት የመቀስቀስ ስጋቱ ከአሁን በኋላ ግምታዊ ሳይሆን በተጨባጭ ከደጃፍ ላይ የደረሰ መሆኑን ሰነዱ ያስጠነቅቃል። ይህ ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ሳይወሰን መላውን የአፍሪካ ቀንድ (Horn of Africa) ቀጣና ክፉኛ ሊያናጋ እንደሚችል በማመልከት፣ የጋራ ሰላምን ለማውረድ አሁንም ቢሆን የትግራይ መስተዳድር እና ህወሃት ለውይይት ዝግጁ መሆናቸውን በመግለጽ፣ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሁለቱንም ወገኖች ወደ ድርድር ጠረጴዛ ለማምጣት ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖውን እንዲጠቀም ጥሪ አቅርቧል።
#fastmereja I የሕዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ (ህወሃት) ከፍተኛ አመራር የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የፌደራል መንግስቱ በይፋ ማፍረሱንና ክልሉን በከበባ ውስጥ ማድረጉን በመጥቀስ፣ አዲስ ሊቀሰቀስ የሚችለውን አስከፊ ጦርነት ለመግታት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባ ጥሪ አቀረበ።
በትግራይ ክልል ያለውን የፖለቲካ የሥልጣን ክፍተት ለመሙላትና ተቋማዊ ቀጣይነትን ለማረጋገጥ ከ1 ሚሊዮን በላይ የክልሉ ነዋሪዎች የተሳተፉበት ሰፊ ውይይት መደረጉን የገለጸው የህወሃት መግለጫ፣ በዚህም መሠረት በ2012 ዓ.ም የተመረጠው የትግራይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወደ ሉዓላዊ ሥልጣኑ እንዲመለስ መወሰኑን ይፋ አድርጓል። ምክር ቤቱ ወደ ሥራው ሲመለስ አካታች የሆነ የሕግ አስፈጻሚና የዳኝነት መዋቅር እንደሚያዋቅር የተገለጸ ሲሆን፣ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች በካቢኔው ውስጥ የ33 በመቶ (አንድ ሶስተኛ) የሥልጣን ድርሻ እንዲኖራቸው ጥሪ መቅረቡም ገልጿል።
በትግራይ ክልል ያለው ሰብአዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አሁንም እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆኑን የጠቀሰው ይኸው አለም አቀፍ ጥሪ፣ የፌደራል መንግስቱ በነዳጅ እና በንግድ ዕቃዎች ላይ የጣለው እገዳ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን ሙሉ በሙሉ ማሽመድመዱንና ከፍተኛ የዋጋ ንረትን ማስከተሉን ያብራራል። ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በትግራይ ድንበሮች ዙሪያ መጠነ-ሰፊ ወታደራዊ ዝግጅትና ከበባ እያደረገ እንደሚገኝ በመግለጽ፣ ይህ ድርጊት በሕዝቡ ላይ ከፍተኛ የስነ-ልቦና እና የማኅበራዊ ጫና እየፈጠረ መሆኑን ይከሳል።
በተመሳሳይ በምዕራብ ትግራይ የሚገኙ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዳይመለሱ በፌደራል መንግስቱና በአጋሮቹ በኩል እንቅፋት እየተፈጠረባቸው መሆኑንና ዓለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶችም ድጋፋቸውን እያቋረጡ መምጣታቸውን ሰነዱ ያስረዳል።
የቀጣናው የፖለቲካ አቅጣጫ ወደ ግትርነት፣ ወታደራዊ ኃይል አማራጭነትና አንድ ወገንተኝነት እያዘገመ በመሆኑ አዲስ ጦርነት የመቀስቀስ ስጋቱ ከአሁን በኋላ ግምታዊ ሳይሆን በተጨባጭ ከደጃፍ ላይ የደረሰ መሆኑን ሰነዱ ያስጠነቅቃል። ይህ ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ሳይወሰን መላውን የአፍሪካ ቀንድ (Horn of Africa) ቀጣና ክፉኛ ሊያናጋ እንደሚችል በማመልከት፣ የጋራ ሰላምን ለማውረድ አሁንም ቢሆን የትግራይ መስተዳድር እና ህወሃት ለውይይት ዝግጁ መሆናቸውን በመግለጽ፣ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሁለቱንም ወገኖች ወደ ድርድር ጠረጴዛ ለማምጣት ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖውን እንዲጠቀም ጥሪ አቅርቧል።
8 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) እስራኤል እና ሊባኖስ በዋሽንግተን ባደረጉት ውይይት በቅድመ ሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የተኩስ አቁም ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ መስማማታቸው ከተገለጸ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ፣ ሐሙስ ጠዋት የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ ላይ ጥቃት መፈጸሙን የሀገሪቱ መንግሥታዊ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
የሊባኖስ ብሔራዊ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቀው፣ የእስራኤል ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) በበርካታ የደቡብ ሊባኖስ አካባቢዎች በሚገኙ መንገዶች ላይ ጥቃት አድርሰዋል፤ ከጥቃቶቹ ቢያንስ አንደኛው በሰው ህይወት እና አካል ላይ ጉዳት ማድረሱንም አክሎ ገልጿል።
በዋሽንግተን ይፋ የተደረገው ይህ ስምምነት፣ የተኩስ አቁሙ ተግባራዊ የሚሆነው "የሂዝቦላህ ተኩስ ሙሉ በሙሉ ሲቆም እና ሁሉም የሂዝቦላህ ታጣቂዎች ከሊታኒ ወንዝ በስተደቡብ ካሉ አካባቢዎች ለቀው ሲወጡ" ብቻ መሆኑን ያብራራል።
እነዚህ የጸጥታ ቀጠናዎች እንዴት እንደሚቋቋሙ እና ተግባራዊ እንደሚሆኑ እስካሁን በግልጽ የታወቀ ነገር ባይኖርም፣ ስምምነቱ የሊባኖስ ጦር በእነዚህ አካባቢዎች ላይ ሙሉ ቁጥጥር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
የሊባኖስ ብሔራዊ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቀው፣ የእስራኤል ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) በበርካታ የደቡብ ሊባኖስ አካባቢዎች በሚገኙ መንገዶች ላይ ጥቃት አድርሰዋል፤ ከጥቃቶቹ ቢያንስ አንደኛው በሰው ህይወት እና አካል ላይ ጉዳት ማድረሱንም አክሎ ገልጿል።
በዋሽንግተን ይፋ የተደረገው ይህ ስምምነት፣ የተኩስ አቁሙ ተግባራዊ የሚሆነው "የሂዝቦላህ ተኩስ ሙሉ በሙሉ ሲቆም እና ሁሉም የሂዝቦላህ ታጣቂዎች ከሊታኒ ወንዝ በስተደቡብ ካሉ አካባቢዎች ለቀው ሲወጡ" ብቻ መሆኑን ያብራራል።
እነዚህ የጸጥታ ቀጠናዎች እንዴት እንደሚቋቋሙ እና ተግባራዊ እንደሚሆኑ እስካሁን በግልጽ የታወቀ ነገር ባይኖርም፣ ስምምነቱ የሊባኖስ ጦር በእነዚህ አካባቢዎች ላይ ሙሉ ቁጥጥር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
Sponsored by
Surafel
9 hours ago
የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ በንጹሃን ላይ የተፈጸመውን ግድያና ቃጠሎ አወገዘ
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ ዞን አሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ፣ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ እና የአብያተ ክርስቲያናት ቃጠሎ በጽኑ ማውገዙን አስታወቀ።
ጉባኤው በጥቃቱ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጾ፣ ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።
ቀደም ሲል ተመሳሳይ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ጥበቃ እንዲደረግ መጠየቁን ያስታወሰው ጉባኤው፣ አሁንም ችግሩ ባለመቀረፉ ተጨማሪ ጉዳት መድረሱ ሃዘኑን እጥፍ ድርብ እንዳደረገው ገልጿል።
በመሆኑም መንግሥት የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ ተቀዳሚ ኃላፊነቱን እንዲወጣ፣ ለተፈናቀሉና ስጋት ላለባቸው ዜጎች አስተማማኝ ጥበቃ እንዲያደርግ እንዲሁም ወንጀለኞችን በአፋጣኝ ለፍርድ እንዲያቀርብ በጥብቅ አሳስቧል።
አባል ተቋማት ድርጊቱን በአንድነት እንዲያወግዙና የአካባቢው ማህበረሰብም በጋራ እንዲተጋገዝ ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ ዞን አሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ፣ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ እና የአብያተ ክርስቲያናት ቃጠሎ በጽኑ ማውገዙን አስታወቀ።
ጉባኤው በጥቃቱ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጾ፣ ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።
ቀደም ሲል ተመሳሳይ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ጥበቃ እንዲደረግ መጠየቁን ያስታወሰው ጉባኤው፣ አሁንም ችግሩ ባለመቀረፉ ተጨማሪ ጉዳት መድረሱ ሃዘኑን እጥፍ ድርብ እንዳደረገው ገልጿል።
በመሆኑም መንግሥት የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ ተቀዳሚ ኃላፊነቱን እንዲወጣ፣ ለተፈናቀሉና ስጋት ላለባቸው ዜጎች አስተማማኝ ጥበቃ እንዲያደርግ እንዲሁም ወንጀለኞችን በአፋጣኝ ለፍርድ እንዲያቀርብ በጥብቅ አሳስቧል።
አባል ተቋማት ድርጊቱን በአንድነት እንዲያወግዙና የአካባቢው ማህበረሰብም በጋራ እንዲተጋገዝ ጥሪ አቅርቧል።
10 hours ago
ሕወሃት አዲስ አውዳሚ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አስቸኳይ ጥሪ አቀረበ።
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
11 hours ago
ማስታወቂያ
"ለ60 ዓመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ" የቤተሰብ፣ የአንድነት ሩጫ!
የኮሜርሺያል ኖሚኒስ ቤተሰቦች፣ ክቡራን ደንበኞቻችን እና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት "ለ60 ዓመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ" የጎዳና ላይ ሩጫ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
60 ዓመታትን በታማኝነት ያገለገለው ኮሜርሺያል ኖሚኒስ፣ በደንበኞቹ፣ በእህት ተቋማቱ ፣ በሰራተኞቹ እና በመላው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማህበረሰብ መካከል ይበልጥ መቀራረብን ለመፍጠር እና ቤተሰባዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚረዳው የ5 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ እንድትሳተፉ በአክብሮት ጋብዘንዎታል።
የመሮጫ ቲ-ሸርቶቹን በኮሜርሺያል ኖሚኒስ ዋና መስሪያ ቤት እና ቅርንጫፎች ያገኛሉ።
ለተጨማሪ መረጃ በ6630 ነጻ የስልክ ጥሪ ወይም በ 0932151385 እና በ0904032498 ደውለው ማግኘት ይችላሉ
"ለ60 ዓመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ" የቤተሰብ፣ የአንድነት ሩጫ!
የኮሜርሺያል ኖሚኒስ ቤተሰቦች፣ ክቡራን ደንበኞቻችን እና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት "ለ60 ዓመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ" የጎዳና ላይ ሩጫ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
60 ዓመታትን በታማኝነት ያገለገለው ኮሜርሺያል ኖሚኒስ፣ በደንበኞቹ፣ በእህት ተቋማቱ ፣ በሰራተኞቹ እና በመላው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማህበረሰብ መካከል ይበልጥ መቀራረብን ለመፍጠር እና ቤተሰባዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚረዳው የ5 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ እንድትሳተፉ በአክብሮት ጋብዘንዎታል።
የመሮጫ ቲ-ሸርቶቹን በኮሜርሺያል ኖሚኒስ ዋና መስሪያ ቤት እና ቅርንጫፎች ያገኛሉ።
ለተጨማሪ መረጃ በ6630 ነጻ የስልክ ጥሪ ወይም በ 0932151385 እና በ0904032498 ደውለው ማግኘት ይችላሉ
17 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአዲስ አበባ የተጠራው የሱዳን ፖለቲካ ሀይሎች ስብሰባ ውዝግብ ፈጠረ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ከዛሬ አንስቶ ለሚቀጥሉት ቀናት የሚካሄደው የሱዳን ፖለቲካ ሀይሎች ውይይት ከጅምሩ ውዝግብ ተፈጥሮበታል፡፡ ስብሰባው የተጠራው አምስትዮሽ ሀይሎች ማለትም በአፍሪካ ህብረት፣ በኢጋድ፣ በተመድ፣ በአውሮፓ ህብረትና በአረብ ሊግ አማካኝነት ነው፡፡
የስብሰባው ዋነኛ አላማም ባለፈው ወር በበርሊን በተከናወነው 3ተኛው የሱዳን አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ያልተሳተፉ የፖለቲካ ሀይሎችን አገናኝቶ እንዲወያዩ ማድረግ ነው፡፡ በስብሰባው ላይ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚሳተፉ አስቀድመው ገልፀው የነበረ ቢሆንም በመጨረሻ ሰአት ግን ራሳቸውን ማግለላቸውን የገለፁ ፓርቲዎች እንዳሉ ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡ በተለይም ‹‹ሶሙድ›› በሚል የሚጠራው የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ያቀፈው ግንባር ክፍፍል መፍጠሩን አስረድቷል፡፡
በቀድሞው የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ የሚመራው ሶሙድ ውስጥ ከተጠቃለሉት ፓርቲዎች መካከል የተወሰኑት አዲስ አበባ ሲገቡ የተወሰኑት ደግሞ መቅረታቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡ በዚህ ስብሰባ ላይ የመሀመድ ዳጋሎ ፈጥኖ ደራሽ ሀይል አጋር የሆኑ ፓርቲዎች እየተሳተፉ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው በሌተና ጄኔራል አልብሩሀን የሚመራው መንግስት ጥሪ ቢደርሰውም ለመሳተፍ ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን ገልጿል፡፡ አምስቱ ቀጣናዊና አለም አቀፍ ድርጅቶች ያዘጋጁት ይህ ስብሰባ በሁለት የተከፈለ ሲሆን ዛሬ የተጀመረው አንደኛው ክፍል ነው፡፡ በቀጣይነት ማለትም ከጁላይ 8 እስከ 9 ሌላ የሱዳን ፖለቲካ ሀይሎችን ያሳተፈ ስብሰባ እንደሚደረግም ዘገባው አስታውቋል፡፡
የስብሰባው ዋነኛ አላማም ባለፈው ወር በበርሊን በተከናወነው 3ተኛው የሱዳን አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ያልተሳተፉ የፖለቲካ ሀይሎችን አገናኝቶ እንዲወያዩ ማድረግ ነው፡፡ በስብሰባው ላይ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚሳተፉ አስቀድመው ገልፀው የነበረ ቢሆንም በመጨረሻ ሰአት ግን ራሳቸውን ማግለላቸውን የገለፁ ፓርቲዎች እንዳሉ ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡ በተለይም ‹‹ሶሙድ›› በሚል የሚጠራው የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ያቀፈው ግንባር ክፍፍል መፍጠሩን አስረድቷል፡፡
በቀድሞው የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ የሚመራው ሶሙድ ውስጥ ከተጠቃለሉት ፓርቲዎች መካከል የተወሰኑት አዲስ አበባ ሲገቡ የተወሰኑት ደግሞ መቅረታቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡ በዚህ ስብሰባ ላይ የመሀመድ ዳጋሎ ፈጥኖ ደራሽ ሀይል አጋር የሆኑ ፓርቲዎች እየተሳተፉ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው በሌተና ጄኔራል አልብሩሀን የሚመራው መንግስት ጥሪ ቢደርሰውም ለመሳተፍ ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን ገልጿል፡፡ አምስቱ ቀጣናዊና አለም አቀፍ ድርጅቶች ያዘጋጁት ይህ ስብሰባ በሁለት የተከፈለ ሲሆን ዛሬ የተጀመረው አንደኛው ክፍል ነው፡፡ በቀጣይነት ማለትም ከጁላይ 8 እስከ 9 ሌላ የሱዳን ፖለቲካ ሀይሎችን ያሳተፈ ስብሰባ እንደሚደረግም ዘገባው አስታውቋል፡፡
21 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ታዋቂው የእስልምና ሃይማኖት መምህር ኡስታዝ ያሲን ኑሩ በምስራቅ አርሲ ዞን በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ጥቃት አጥብቀው በማውገዝ የተሰማቸውን ጥልቅ እና መሪር ሐዘን ገልጸዋል። ኡስታዙ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት "ምነው የተከበረው የሰው ልጅ ህይወት እንዲህ ረከሰ?" በማለት በመገረም፣ ድርጊቱን የዜጎችን ነፍስ ለርካሽ ዓለማዊ ግብ ማሳኪያነት ለመጠቀም የሚደረግ "ሀገር አጥፊ" ተግባር ሲሉ በጽኑ ኮንነውታል።
የብዝሃ ሃይማኖት እና ብሔር ብሔረሰቦች እናት የሆነችውን ሀገራችንን ሰላም ለማናጋት፣ እንዲሁም ለዘመናት የተገነባውን የሕዝቦች የጠበቀ ትስስር ለመበጠስ ያሰፈሰፉ ኃይሎች የሚያደርጉትን ጥፋት ያወገዙት ኡስታዝ ያሲን፤ የሚመለከተው የመንግሥት አካል አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል። የሚመለከታቸው አካላት ይህንን የሀገር ዕድገት የሚገታ እኩይ ተግባር በማስቆም፣ የዜጎችን በሰላም ወጥቶ የመግባት ሰብዓዊ መብት ማረጋገጥ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ዜጎች በሰላም ወጥተው ስለመግባታቸው መተማመኛ የሌላቸውን ሀገር ወደፊት የመራመድ እና የማደግ ዕድሏ የመነመነ መሆኑን ያስገነዘቡት ኡስታዙ፣ "ስለ ሀገሬ ያገባኛል፣ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ 'ሀይ' ሊል ይገባል" ሲሉ ሁሉም ዜጋ የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
"እንዲህ ዓይነቱን አስነዋሪ ድርጊት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በሕዝቦች መካከል አለመተማመንን የሚዘሩ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የጉዳዩን አደገኛነት ተገንዝበው ቆም ብለው እንዲያስቡ እና ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ኡዝታዙ አበክረው መክረዋል።
ፈጣሪ የተበዳዮችን እምባ እንዲያብስ፣ ለበዳዮችም የእጃቸውን እንዲሰጣቸው እና በሀገሪቱ ፍትሕን እንዲያሰፍን ጸሎት በማድረግ መልእክታቸውን አጠቃልለዋል።
የብዝሃ ሃይማኖት እና ብሔር ብሔረሰቦች እናት የሆነችውን ሀገራችንን ሰላም ለማናጋት፣ እንዲሁም ለዘመናት የተገነባውን የሕዝቦች የጠበቀ ትስስር ለመበጠስ ያሰፈሰፉ ኃይሎች የሚያደርጉትን ጥፋት ያወገዙት ኡስታዝ ያሲን፤ የሚመለከተው የመንግሥት አካል አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል። የሚመለከታቸው አካላት ይህንን የሀገር ዕድገት የሚገታ እኩይ ተግባር በማስቆም፣ የዜጎችን በሰላም ወጥቶ የመግባት ሰብዓዊ መብት ማረጋገጥ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ዜጎች በሰላም ወጥተው ስለመግባታቸው መተማመኛ የሌላቸውን ሀገር ወደፊት የመራመድ እና የማደግ ዕድሏ የመነመነ መሆኑን ያስገነዘቡት ኡስታዙ፣ "ስለ ሀገሬ ያገባኛል፣ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ 'ሀይ' ሊል ይገባል" ሲሉ ሁሉም ዜጋ የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
"እንዲህ ዓይነቱን አስነዋሪ ድርጊት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በሕዝቦች መካከል አለመተማመንን የሚዘሩ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የጉዳዩን አደገኛነት ተገንዝበው ቆም ብለው እንዲያስቡ እና ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ኡዝታዙ አበክረው መክረዋል።
ፈጣሪ የተበዳዮችን እምባ እንዲያብስ፣ ለበዳዮችም የእጃቸውን እንዲሰጣቸው እና በሀገሪቱ ፍትሕን እንዲያሰፍን ጸሎት በማድረግ መልእክታቸውን አጠቃልለዋል።
1 day ago
ወደ ኢትዮጵያ የሚደረግ የድምፅ ጥሪ ከመቼውም ጊዜ በላይ ቀላልና ኪስ የማይጎዳ ሆኗል!!
ኢትዮኮል:-
📞 ማንኛውንም የሞባይል ወይም የመደበኛ ስልክ ላይ መደወል ያስችላል
💰 በታላቅ ቅናሽ በደቂቃ ከ$0.1 ጀምሮ
🔄 ወደ ኢትዮጵያ መደወል ብቻ ሳይሆን፣ ጥሪዎችን በገዙት ጥቅል መነሻነት በነፃ መቀበል ይችላሉ።
አገልግሎቱ የጀመረባቸው አገራት:-
🇺🇸 አሜሪካ 🇨🇦 ካናዳ 🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
መተግበሪያውን ያውርዱ:
App store: https://bit.ly/42Zg6jx
Play store: https://bit.ly/4u12uPu
ከአኗኗርዎ ጋር የሚስማማውን ዕለታዊ፣ ሳምንታዊ ወይም የ15 ቀናት የድምፅ ጥቅሎችን መርጠው ይጠቀሙ።
#ethiocall #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ኢትዮኮል:-
📞 ማንኛውንም የሞባይል ወይም የመደበኛ ስልክ ላይ መደወል ያስችላል
💰 በታላቅ ቅናሽ በደቂቃ ከ$0.1 ጀምሮ
🔄 ወደ ኢትዮጵያ መደወል ብቻ ሳይሆን፣ ጥሪዎችን በገዙት ጥቅል መነሻነት በነፃ መቀበል ይችላሉ።
አገልግሎቱ የጀመረባቸው አገራት:-
🇺🇸 አሜሪካ 🇨🇦 ካናዳ 🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
መተግበሪያውን ያውርዱ:
App store: https://bit.ly/42Zg6jx
Play store: https://bit.ly/4u12uPu
ከአኗኗርዎ ጋር የሚስማማውን ዕለታዊ፣ ሳምንታዊ ወይም የ15 ቀናት የድምፅ ጥቅሎችን መርጠው ይጠቀሙ።
#ethiocall #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
1 day ago
ሁለተኛው የኢትዮጵያ እና ፊንላንድ የፖለቲካ ምክክር በአዲስ አበባ ተካሄደ
*********************
ሁለተኛው የኢትዮጵያ እና ፊንላንድ የፖለቲካ ምክክር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን በምክክሩ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ በትምህርት እና በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ሰፊ ግምገማ ተደርጓል።
ምክክሩን በጋራ የመሩት አምባሳደር መለስ ዓለም እና የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን የሁለቱን ሀገራት የቆየ ግንኙነት እና አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በዚሁ ወቅት ማብራሪያ የሰጡት አምባሳደር መለስ ዓለም በኢትዮጵያ ስላለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ስለ 7ኛው አጠቃላይ ምርጫ፣ ስለ ብሔራዊ ምክክር ሂደት እና ስለ ፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ለፊንላንድ ልዑካን ገልጸዋል።
አምባሳደሩ የፊንላንድ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂ እና በግብርና ማቀነባበሪያ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጥሪ በማቅረብ ንግድን ለማሳደግ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ምክር ቤቶች በቅርበት እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን በበኩላቸው፣ በአዲስ አበባ እየታየ ያለውን ፈጣን የልማት ለውጥ አድንቀዋል።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ለሀገራቸው ቁልፍ አጋር መሆኗን ገልጸው፣ ፊንላንድ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ተናግረዋል።
በተለይም በዲጂታላይዜሽን፣ በከፍተኛ ትምህርት፣ በሜትሮሎጂ እና በአስተማሪዎች ሥልጠና ዙሪያ የሚደረገው ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀው፣ መሰል መደበኛ ውይይቶችን አጠናክሮ ለመቀጠል መስማማታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #finland #ethiopiafinlandconsultation #addisababa
*********************
ሁለተኛው የኢትዮጵያ እና ፊንላንድ የፖለቲካ ምክክር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን በምክክሩ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ በትምህርት እና በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ሰፊ ግምገማ ተደርጓል።
ምክክሩን በጋራ የመሩት አምባሳደር መለስ ዓለም እና የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን የሁለቱን ሀገራት የቆየ ግንኙነት እና አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በዚሁ ወቅት ማብራሪያ የሰጡት አምባሳደር መለስ ዓለም በኢትዮጵያ ስላለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ስለ 7ኛው አጠቃላይ ምርጫ፣ ስለ ብሔራዊ ምክክር ሂደት እና ስለ ፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ለፊንላንድ ልዑካን ገልጸዋል።
አምባሳደሩ የፊንላንድ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂ እና በግብርና ማቀነባበሪያ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጥሪ በማቅረብ ንግድን ለማሳደግ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ምክር ቤቶች በቅርበት እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን በበኩላቸው፣ በአዲስ አበባ እየታየ ያለውን ፈጣን የልማት ለውጥ አድንቀዋል።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ለሀገራቸው ቁልፍ አጋር መሆኗን ገልጸው፣ ፊንላንድ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ተናግረዋል።
በተለይም በዲጂታላይዜሽን፣ በከፍተኛ ትምህርት፣ በሜትሮሎጂ እና በአስተማሪዎች ሥልጠና ዙሪያ የሚደረገው ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀው፣ መሰል መደበኛ ውይይቶችን አጠናክሮ ለመቀጠል መስማማታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #finland #ethiopiafinlandconsultation #addisababa
Sponsored by
Surafel
1 day ago
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት መልእክት አስተላለፉ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ ::
"በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን::"
Seledadotio
Seledadotio
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ ::
"በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን::"
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
የምርጫ ቦርድ ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም አካል ራሱን አሸናፊ አድርጎ ከመግለጽ ይቆጠብ":-ኢሰመጉ‼️
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ባወጣው የምርጫ መታዘብ ቅድመ መግለጫ ላይ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጥብቅ ማሳሰቢያ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም ግለሰብ፣ የፖለቲካ ድርጅት ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ጊዜያዊ ውጤት በማጋራት ማኅበረሰቡን ከማደናገር እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
የምልከታ ስፋት፦ኢሰመጉ ባሰማራቸው 433 ታዛቢዎች አማካኝነት ከ800 በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን ተከታትሏል።
⚠️ የተስተዋሉ ዋና ዋና ተግዳሮቶች፦
* የአዲሱ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥልት መጀመሩ የሚበረታታ ቢሆንም፣ የአስፈጻሚዎች ሥልጠና ማነስ ለመራጮች መጨናነቅና ለሰዓት መራዘም ምክንያት ሆኗል።
* በበርካታ አካባቢዎች የትራንስፖርት መቋረጥ፣ በአዲስ አበባ የሰልፍ አስተባባሪዎች ማነስ እና በመራጮች ላይ የደረሰ የእንግልት ሰዓት።
* በሐዋሳና አካባቢው በሚገኙ ውስን ጣቢያዎች የምርጫ አስፈጻሚዎች በሚስጥራዊ ድምፅ መስጫ ቦታ በመግባት የሥነ-ልቦና ጫና ማድረጋቸው እና ያልተመረጡ ወረቀቶችን ወደ ሳጥን ማስገባት የመሳሰሉ የነፃነት መብትን የገደቡ ክስተቶች መታየታቸው።
✅ በበጎ ጎን የተነሱ ነጥቦች፦
* የመራጮች ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ በቂ የቁሳቁስ አቅርቦት እና በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች የጎላ የጸጥታ መደፍረስ ሳይኖር ሂደቱ መጠናቀቁ።
"ኢሰመጉ ምርጫ ቦርድ በአንጻራዊነት ስኬታማና ሰላማዊ ምርጫ ማከናወኑን በመግለጽ ዕውቅና የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይ ግን የተስተዋሉ ችግሮችን በዝርዝር ለይቶ እንዲያርም ጥሪ አቅርቧል።"
Seledadotio
Seledadotio
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ባወጣው የምርጫ መታዘብ ቅድመ መግለጫ ላይ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጥብቅ ማሳሰቢያ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም ግለሰብ፣ የፖለቲካ ድርጅት ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ጊዜያዊ ውጤት በማጋራት ማኅበረሰቡን ከማደናገር እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
የምልከታ ስፋት፦ኢሰመጉ ባሰማራቸው 433 ታዛቢዎች አማካኝነት ከ800 በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን ተከታትሏል።
⚠️ የተስተዋሉ ዋና ዋና ተግዳሮቶች፦
* የአዲሱ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥልት መጀመሩ የሚበረታታ ቢሆንም፣ የአስፈጻሚዎች ሥልጠና ማነስ ለመራጮች መጨናነቅና ለሰዓት መራዘም ምክንያት ሆኗል።
* በበርካታ አካባቢዎች የትራንስፖርት መቋረጥ፣ በአዲስ አበባ የሰልፍ አስተባባሪዎች ማነስ እና በመራጮች ላይ የደረሰ የእንግልት ሰዓት።
* በሐዋሳና አካባቢው በሚገኙ ውስን ጣቢያዎች የምርጫ አስፈጻሚዎች በሚስጥራዊ ድምፅ መስጫ ቦታ በመግባት የሥነ-ልቦና ጫና ማድረጋቸው እና ያልተመረጡ ወረቀቶችን ወደ ሳጥን ማስገባት የመሳሰሉ የነፃነት መብትን የገደቡ ክስተቶች መታየታቸው።
✅ በበጎ ጎን የተነሱ ነጥቦች፦
* የመራጮች ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ በቂ የቁሳቁስ አቅርቦት እና በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች የጎላ የጸጥታ መደፍረስ ሳይኖር ሂደቱ መጠናቀቁ።
"ኢሰመጉ ምርጫ ቦርድ በአንጻራዊነት ስኬታማና ሰላማዊ ምርጫ ማከናወኑን በመግለጽ ዕውቅና የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይ ግን የተስተዋሉ ችግሮችን በዝርዝር ለይቶ እንዲያርም ጥሪ አቅርቧል።"
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
እጅግ በጣም ልብ ይሰብራል
የሚካኤል ወዳጆች የት ናችሁ
ይህ የምትመለከቱት በሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት ስር ያለው የሞዬ አማንጉልት አጣራ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለ20 ዓመት በመጋረጃ ውስጥ ተከልሎ በመቃብር ቤት ውስጥ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት ግን አባቶች በጠና እየታመሙ የድረሱልን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች የት አላችሁ እጃችሁን ዘርጉልን እያሉ እየተማፀኑ ይገኛሉ እንደምትመለከቱት ዙርያውን ክፍት ስለሆነ መቅደሱ የእንስሳ መራቢያ ሆኖ አባቶች ክፉኛ ችግር ውስጥ እየከተታቸው ይገኛል ስለሆነም ኦርቶዶክሳዊያን የሆንን ሁላችን ከ200 ብር ጀምሮ ለሚካኤል ቤተክርስቲያን ማሰሪያ ለንዋየተ ቅድሳት ማሟያ የሚሆነውን አስራታችሁንም በማውጣት ካላችሁ ላይ በመስጠት አሰሩልን ተራዱን ድረሱልን እያሉ ይገኛሉ
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቁጥር
1000392881879
የሞዬ አማንጉልት አጣራ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን 🙏✨
📞 ለበለጠ መረጃ
0952530207
(እባክዎን የክርስትና ስምዎን በቴሌግራም ወይም በዋትሳፕ በዚሁ ስልክ ይላኩላቸው በፀሎት ያስቧችኋል)
ሼር (Share) በማድረግ ድምፅ ሁኑልኝ! 🙏⛪
1 day ago
"እስከ መቼ?"
📌ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
📌ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
Sponsored by
Surafel
1 day ago
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
1 day ago
(ከተዋሕዶ ወርልድ) የአርሲ ተራሮች ለዘመናት የሰላም፣ የግብርና እና የአብሮነት ምልክት ሆነው ኖረዋል። የጠዋቱ ጸሐይ ሲወጣ የከብቶች ጩኸት፣ የእረኞች ዜማ እና የቤተ ክርስቲያን የደወል ድምፅ ተቀናጅተው መንፈስን የሚያድስ ተስፋን ይሰጡ ነበር። ዛሬ ግን... ዛሬ ከእነዚህ ተራሮች ጀርባ የሚወጣው ጭስ የዕጣን አይደለም፤ የቃጠሎ ነው። ዛሬ የሚሰማው ድምፅ የዝማሬ ሳይሆን የእንባ እና የዋይታ ነው። ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሺርካ እና በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ላይ ያንዣበበው የሞት ጥላ፣ ንጹሐንን በግፍ ቀጥፏል፤ ታሪካዊ መቅደሶችንም ወደ አመድነት ቀይሯል።
ይህ የተዋህዶ ወርልድ ትንታኔ የቁጥሮች ድምር አይደለም፤ የ13 የከበሩ የሰው ልጆች ሕይወት መነጠቅ፣ የ101 ዓመት ታሪክ መቃጠል፣ እና የ280 ዜጎች በባዶ እጅ መሰደድ ታሪክ እንጂ። ይህ፣ ሃይማኖት እና ማንነትን መሠረት አድርጎ የሚፈጸም አክራሪነት የሰውን ልጅ ምን ያህል ወደ አውሬነት እንደሚቀይረው የሚያሳይ የዘመናችን ህያው ማሳያ ነው።
የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንን እናስበው። ለ101 ዓመታት ሙሉ፣ አባቶች እና እናቶች በደጃፉ ተንበርክከው ፈጣሪያቸውን ተማጽነዋል። በዚያ መቅደስ ውስጥ ስንቱ ተጠምቋል? ስንቱ ተክሊል አስሯል? ስንቱስ በጸሎት ተጽናንቷል? ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ የቆመው ይህ የጸጋ ቤት፣ የበርካታ ትውልዶች የእምነት ማህደር ነበር። ነገር ግን፣ ጥላቻ ታሪክን አያውቅም፤ ክፋት ቅድስናን አይረዳም። በአንድ ጀንበር፣ ያ ሁሉ ታሪክ፣ ያ ሁሉ የእንጨት ጠረንና የዕጣን መዓዛ፣ በጭካኔ እሳት ተበላ።
በሌላ በኩል ደግሞ የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ዕጣ ፈንታ ሌላ ልብ ሰባሪ ትዕይንት ነበር። ታጣቂዎች መቅደሱን ሲዘርፉ፣ አማኞች የራሳቸውን ሕይወት እና ንብረት ለማዳን አልተጣደፉም። ይልቁንም፣ መኖሪያ ቤታቸው እያዩት በእሳት ሲጋይ፣ የዕድሜ ልክ ጥሪታቸው፣ ከብቶቻቸውና ማሳቸው ሲዘረፍ፣ እነርሱ ግን ከሁሉ የሚያስበልጡትን የቤተ ክርስቲያኑን ጽላት (ታቦት) በደረታቸው አቅፈው በጨለማ ወደማያውቁት ስደት መጓዝን መረጡ።
ይህ ትዕይንት ወደ ኋላ መለስ ብለን የመጽሐፍ ቅዱስን ታሪክ እንድናስታውስ ያደርገናል። እስራኤላውያን ታቦተ ጽዮንን ተሸክመው በበረሃ እንደተጓዙት ሁሉ፣ የአርሲ ምእመናንም አምላካቸውን በደረታቸው አቅፈው መከራውን ተቀበሉ።
ሞት በቁጥር ሲገለጽ ስሜት አይሰጥም፤ ነገር ግን እያንዳንዱ ቁጥር ከጀርባው ቤተሰብ፣ ተስፋ እና ህልም አለው። በአጠቃላይ 13 ንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን በግፍ ተገድለዋል።
የ80 ዓመቱን አቶ አማረ በላይነህን እንመልከት። እኚህ አረጋዊ በህይወት ዘመናቸው ስንት መንግስታትን አይተዋል? ስንት የሀገር መከራን አሳልፈዋል? በስተእርጅናቸው ዘመን ክፋት አላርፍ ብሎ አስጨናቂ ሞትን አመጣባቸው። የ70 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ የሆኑት አቶ ደምረው አበራ፣ አቶ ሐይሉ ንጉሴ እና አቶ ሰሙ አባይነህም እንዲሁ የዚህ ጭካኔ ሰለባ ሆነዋል። እነዚህ አባቶች ለሀገር ምርቃት እንጂ መርገም ያልነበሩ፣ በእምነታቸው ጸንተው የኖሩ የሰላም ሰዎች ነበሩ።
እንደነ እሸቴ ዳመና (42 ዓመት) እና አበባየሁ ዳኜ (42 ዓመት) ያሉ የጎልማሳነት ዘመናቸው ላይ የነበሩ አባወራዎች ሲገደሉ፣ ከጀርባቸው ስንት ቤተሰብ በትነው እንደሄዱ ማሰብ ያሳምማል። ገና ለሀገር እና ለወገን ይደርሳሉ የተባሉ ወጣቶችም የዚህ ጽዋ ቀማሾች ሆነዋል። ተሬ ደሴ (የ25 ዓመት ወጣት)፣ ገነነ ጥላሁን እና ሙርቴሳ ጥላሁን በሺርካ ወረዳ ሕልማቸው ተጨናግፎ፣ ደማቸው በመሬት ላይ ፈሷል።
አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ፣ አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል፣ ከፈለኝ ልክየለው... እነዚህ ስሞች ዝም ብለው በወረቀት ላይ የሰፈሩ አይደሉም። እነዚህ አባቶች ያሏቸው፣ እናቶች ያሳደጓቸው፣ ልጆች የሚጠብቋቸው ነፍሶች ነበሩ። በሃይማኖታቸው ምክንያት ብቻ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።
ይህ ዓይነቱ እምነትን መሠረት ያደረገ መከራ፣ በዓለማችን ታሪክ አዲስ አይደለም። የሰው ልጅ በፈጣሪው በማመኑ ብቻ የተከፈለው ዋጋ ብዙ ነው።
ወደ ሩቅ ጎረቤት ሀገር ግብጽ ስንሄድ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ለዘመናት በእምነታቸው ምክንያት ከፍተኛ ዋጋ ሲከፍሉ ኖረዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2015 በሊቢያ የባህር ዳርቻ አይ ኤስ በተባለው አሸባሪ ቡድን የታረዱት 21 የግብጽ ኮፕቲክ ክርስቲያኖችን ዓለም መቼም አይረሳም። ቢላዋ በአንገታቸው ላይ ሲያርፍ እንኳን የፈጣሪያቸውን ስም እየጠሩ በድፍረት ሰማዕትነትን ተቀብለዋል። የአርሲዎቹም ሰማዕታት ከዚሁ የጽናት መንገድ የወጡ አይደሉም። ኢትዮጵያውያንም በተመሳሳይ በሊቢያ እንዲሁ።
ወደ ምዕራብ አፍሪካ ስናቀና ደግሞ ናይጄሪያ እናገኛለን። በቦኮሃራም እና በአክራሪ የፉላኒ ታጣቂዎች አማካኝነት በሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍል በሺዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች አብያተ ክርስቲያናቶቻቸው ተቃጥለውባቸው፣ መንደራቸው ወድሞ በግፍ ተጨፍጭፈዋል።
የአርሜንያ የዘር ማጥፋት ታሪክም ሌላው ትልቅ ትምህርት ነው። በ1915 በኦቶማን ኢምፓየር ዘመን፣ ከአንድ ሚሊዮን በላይ አርመናውያን በክርስትና እምነታቸው እና በማንነታቸው ምክንያት ብቻ በግፍ ተጨፍጭፈዋል፣ በበረሃም ተሰደው አልቀዋል። ነገር ግን ዛሬ አርሜንያውያን ከየትኛውም ጊዜ በላይ አብበው፣ እምነታቸውንም አጽንተው ይገኛሉ። ጥይት እና እሳት ስጋን ሊገድል ይችላል፣ እምነትን እና መንፈስን ግን መቼም ሊያጠፋ አይችልም።
ታዋቂው የጥንት ቤተ ክርስቲያን ጸሐፊ ቴርቱሊያን እንዳለው፡-
"የሰማዕታት ደም የቤተ ክርስቲያን ዘር ነው።"
በአርሲ ተራሮች ላይ የፈሰሰው የነ አቶ አማረ፣ የነ ወጣት ተሬ ደሴ ደም በከንቱ አይቀርም። የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደሚያስተምረን፣ መከራ በበዛ ቁጥር፣ መቅደሶች በነደዱ ቁጥር፣ የእምነት ስር ይበልጥ ይጠልቃል እንጂ አይደርቅም።
በእንደዚህ ዓይነት ጥልቅ ሀዘን እና የሰብአዊነት ውድቀት ውስጥ ስናልፍ፣ የሰው ልጅ ታሪክ ካፈራቸው ታላላቅ መሪዎች እና ፈላስፎች የምንማረው ብዙ ነገር አለ። ጭካኔን በጭካኔ መመለስ የትም አያደርስም።
የሰብአዊ መብት ታጋዩ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር (የተናገረው ኃያል ቃል በዚህ ጊዜ ትዝ ይለናል፡-
"ጨለማ ጨለማን ሊያባርር አይችልም፤ ይህንን ማድረግ የሚችለው ብርሃን ብቻ ነው። ጥላቻ ጥላቻን ሊያጠፋ አይችልም፤ ይህንን ማድረግ የሚችለው ፍቅር ብቻ ነው።"
በአርሲ የተፈጸመው ድርጊት የጨለማ እና የጥላቻ ፍሬ ነው። ነገር ግን የተፈናቀሉት ምዕመናን ጽላቱን አቅፈው መውጣታቸው፣ ብርሃንን እና ፍቅርን ምርጫቸው እንዳደረጉ ያሳያል።
የሰላም ኖቤል ሽልማት አሸናፊው እና የሆሎኮስት (የአይሁዳውያን ጭፍጨፋ) ተራፊው ኤሊ ዊሰል ስለ ግፍ ዝምታ ሲናገር፡-
"ዝምታ ሁልጊዜም የሚጠቅመው አጥቂውን እንጂ ተጠቂውን አይደለም። ገለልተኝነት የሚረዳው ጨቋኙን እንጂ ተጨቋኙን አይደለም።" ብሎ ነበር።
ስለሆነም የነዚህን ንጹሐን መገደል፣ የ101 ዓመት ታሪካዊ ቅርስ መቃጠል፣ እና የ280 ሰዎች መፈናቀል እንደ ቀላል ዜና አልፈነው ልንሄድ አይገባም። ህመማቸውን ልንጋራ፣ ድምጻቸው ልንሆን ይገባል።
ታላቁ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ደግሞ ስለ መጽናት እንዲህ ይላሉ፡-
"ትልቁ የህይወት ክብር ያለው ፈጽሞ ባለመውደቅ ውስጥ ሳይሆን፣ በወደቅን ቁጥር ተመልሶ በመነሳት ውስጥ ነው።"
ኦርቶዶክሳውያኑ ዛሬ ቤታቸው ፈርሶ፣ ዘመዶቻቸው ተገድለውባቸው ሜዳ ላይ ወድቀው ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን እምነታቸው እስካለ ድረስ፣ ነገ ከአመዱ ላይ ተመልሰው ይነሳሉ።
በአሰኮ ወረዳ ብቻ ከ280 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተፈናቅለዋል። መፈናቀል ማለት መጓዝ ብቻ አይደለም። መፈናቀል ማለት ትዝታን፣ ልፋትን፣ የልጅነት የቦረቁበትን አፈር፣ እና የዘመዶችን መቃብር ትቶ መሄድ ማለት ነው። እነዚህ ሰዎች አሁን ያሉት ሜዳ ላይ ነው። የለበሱት ልብስ ብቻ ነው ያላቸው። የሌሊቱ ብርድ ሲቆራርጣቸው፣ የጠዋቱ ጸሐይ ሲያቃጥላቸው፣ የልጆቻቸው ርሃብ አንጀታቸውን ሲበላው... ያላቸው ብቸኛ መጽናኛ በደረታቸው ያቀፉት እምነታቸው ብቻ ነው።
"ስለ አንተ ሁልጊዜም ተገድለናል እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል" (መዝሙር 43:22)። የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሀዘን መግለጫቸውን የጀመሩት በዚህ የዳዊት መዝሙር ነበር። ይህ ቃል የዛሬን ብቻ ሳይሆን የዘመናትን የክርስቲያኖችን ህይወት የሚገልጽ ነው።
በእርግጥም እንደ በግ ለመታረድ የተሰለፉት እነዚህ ወገኖች ጥፋታቸው ምንድን ነው? ከማንም ጋር ያልተጣሉ፣ የፖለቲካ አጀንዳ የሌላቸው፣ ኑሯቸውን ለማሸነፍ መሬት የሚጭሩ ምስኪን ገበሬዎች ነበሩ። ነገር ግን በአክራሪነት የታወረው አእምሮ ይህንን ሊረዳ አይችልም።
እሳት ሁሉንም ነገር ያወድማል፤ መጽሐፍትን ያቃጥላል፣ ግድግዳን ያፈርሳል፣ ስጋን ያጠፋል። ነገር ግን እሳት እምነትን ሊያቃጥል አይችልም። የ101 ዓመቱ የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ዛሬ በአካላዊ ገጽታው ባይኖርም፣ ያ መቅደስ የሰራው መንፈሳዊ ህንጻ ግን አሁንም በምዕመናኑ ልብ ውስጥ ጸንቶ ይገኛል።
የ13ቱ ሰማዕታት ነፍስ በሰላም ታርፋለች፤ ደማቸው ግን ለትውልድ የሚተላለፍ የጽናት ትምህርት ሆኖ ይኖራል። የተሰደዱት ወገኖቻችን ዛሬ ሜዳ ላይ ቢሆኑም፣ የታሪክ ጌታ የሆነው አምላክ ነገን አዲስ አድርጎ ይሰራላቸዋል። የጥላቻ ኃይሎች በክፋታቸው መቅደሱን አፍርሰውታል፤ ሆኖም እውነተኛዋ ቤተ ክርስቲያን የድንጋይ እና የእንጨት ክምር ሳትሆን፣ ያቺ በስደት መሃልም ጽላቷን አቅፋ የምትጓዘዋ የሰው ልጅ ልብ ናት።
እስከዚያው ግን እንደ አቡነ ኤልሳዕ ጸሎት፤ ፈጣሪ የሞቱትን ነፍስ በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍ፣ የተፈናቀሉትን፣ የተራቡትን እና የተራቆቱትን ደግሞ በምህረት እጁ ይጎብኝ፣ ያጽናናም። ከጭስ እና ከአመድ በስተጀርባ፣ ብርሃን አለና።
ይህ የተዋህዶ ወርልድ ትንታኔ የቁጥሮች ድምር አይደለም፤ የ13 የከበሩ የሰው ልጆች ሕይወት መነጠቅ፣ የ101 ዓመት ታሪክ መቃጠል፣ እና የ280 ዜጎች በባዶ እጅ መሰደድ ታሪክ እንጂ። ይህ፣ ሃይማኖት እና ማንነትን መሠረት አድርጎ የሚፈጸም አክራሪነት የሰውን ልጅ ምን ያህል ወደ አውሬነት እንደሚቀይረው የሚያሳይ የዘመናችን ህያው ማሳያ ነው።
የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንን እናስበው። ለ101 ዓመታት ሙሉ፣ አባቶች እና እናቶች በደጃፉ ተንበርክከው ፈጣሪያቸውን ተማጽነዋል። በዚያ መቅደስ ውስጥ ስንቱ ተጠምቋል? ስንቱ ተክሊል አስሯል? ስንቱስ በጸሎት ተጽናንቷል? ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ የቆመው ይህ የጸጋ ቤት፣ የበርካታ ትውልዶች የእምነት ማህደር ነበር። ነገር ግን፣ ጥላቻ ታሪክን አያውቅም፤ ክፋት ቅድስናን አይረዳም። በአንድ ጀንበር፣ ያ ሁሉ ታሪክ፣ ያ ሁሉ የእንጨት ጠረንና የዕጣን መዓዛ፣ በጭካኔ እሳት ተበላ።
በሌላ በኩል ደግሞ የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ዕጣ ፈንታ ሌላ ልብ ሰባሪ ትዕይንት ነበር። ታጣቂዎች መቅደሱን ሲዘርፉ፣ አማኞች የራሳቸውን ሕይወት እና ንብረት ለማዳን አልተጣደፉም። ይልቁንም፣ መኖሪያ ቤታቸው እያዩት በእሳት ሲጋይ፣ የዕድሜ ልክ ጥሪታቸው፣ ከብቶቻቸውና ማሳቸው ሲዘረፍ፣ እነርሱ ግን ከሁሉ የሚያስበልጡትን የቤተ ክርስቲያኑን ጽላት (ታቦት) በደረታቸው አቅፈው በጨለማ ወደማያውቁት ስደት መጓዝን መረጡ።
ይህ ትዕይንት ወደ ኋላ መለስ ብለን የመጽሐፍ ቅዱስን ታሪክ እንድናስታውስ ያደርገናል። እስራኤላውያን ታቦተ ጽዮንን ተሸክመው በበረሃ እንደተጓዙት ሁሉ፣ የአርሲ ምእመናንም አምላካቸውን በደረታቸው አቅፈው መከራውን ተቀበሉ።
ሞት በቁጥር ሲገለጽ ስሜት አይሰጥም፤ ነገር ግን እያንዳንዱ ቁጥር ከጀርባው ቤተሰብ፣ ተስፋ እና ህልም አለው። በአጠቃላይ 13 ንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን በግፍ ተገድለዋል።
የ80 ዓመቱን አቶ አማረ በላይነህን እንመልከት። እኚህ አረጋዊ በህይወት ዘመናቸው ስንት መንግስታትን አይተዋል? ስንት የሀገር መከራን አሳልፈዋል? በስተእርጅናቸው ዘመን ክፋት አላርፍ ብሎ አስጨናቂ ሞትን አመጣባቸው። የ70 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ የሆኑት አቶ ደምረው አበራ፣ አቶ ሐይሉ ንጉሴ እና አቶ ሰሙ አባይነህም እንዲሁ የዚህ ጭካኔ ሰለባ ሆነዋል። እነዚህ አባቶች ለሀገር ምርቃት እንጂ መርገም ያልነበሩ፣ በእምነታቸው ጸንተው የኖሩ የሰላም ሰዎች ነበሩ።
እንደነ እሸቴ ዳመና (42 ዓመት) እና አበባየሁ ዳኜ (42 ዓመት) ያሉ የጎልማሳነት ዘመናቸው ላይ የነበሩ አባወራዎች ሲገደሉ፣ ከጀርባቸው ስንት ቤተሰብ በትነው እንደሄዱ ማሰብ ያሳምማል። ገና ለሀገር እና ለወገን ይደርሳሉ የተባሉ ወጣቶችም የዚህ ጽዋ ቀማሾች ሆነዋል። ተሬ ደሴ (የ25 ዓመት ወጣት)፣ ገነነ ጥላሁን እና ሙርቴሳ ጥላሁን በሺርካ ወረዳ ሕልማቸው ተጨናግፎ፣ ደማቸው በመሬት ላይ ፈሷል።
አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ፣ አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል፣ ከፈለኝ ልክየለው... እነዚህ ስሞች ዝም ብለው በወረቀት ላይ የሰፈሩ አይደሉም። እነዚህ አባቶች ያሏቸው፣ እናቶች ያሳደጓቸው፣ ልጆች የሚጠብቋቸው ነፍሶች ነበሩ። በሃይማኖታቸው ምክንያት ብቻ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።
ይህ ዓይነቱ እምነትን መሠረት ያደረገ መከራ፣ በዓለማችን ታሪክ አዲስ አይደለም። የሰው ልጅ በፈጣሪው በማመኑ ብቻ የተከፈለው ዋጋ ብዙ ነው።
ወደ ሩቅ ጎረቤት ሀገር ግብጽ ስንሄድ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ለዘመናት በእምነታቸው ምክንያት ከፍተኛ ዋጋ ሲከፍሉ ኖረዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2015 በሊቢያ የባህር ዳርቻ አይ ኤስ በተባለው አሸባሪ ቡድን የታረዱት 21 የግብጽ ኮፕቲክ ክርስቲያኖችን ዓለም መቼም አይረሳም። ቢላዋ በአንገታቸው ላይ ሲያርፍ እንኳን የፈጣሪያቸውን ስም እየጠሩ በድፍረት ሰማዕትነትን ተቀብለዋል። የአርሲዎቹም ሰማዕታት ከዚሁ የጽናት መንገድ የወጡ አይደሉም። ኢትዮጵያውያንም በተመሳሳይ በሊቢያ እንዲሁ።
ወደ ምዕራብ አፍሪካ ስናቀና ደግሞ ናይጄሪያ እናገኛለን። በቦኮሃራም እና በአክራሪ የፉላኒ ታጣቂዎች አማካኝነት በሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍል በሺዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች አብያተ ክርስቲያናቶቻቸው ተቃጥለውባቸው፣ መንደራቸው ወድሞ በግፍ ተጨፍጭፈዋል።
የአርሜንያ የዘር ማጥፋት ታሪክም ሌላው ትልቅ ትምህርት ነው። በ1915 በኦቶማን ኢምፓየር ዘመን፣ ከአንድ ሚሊዮን በላይ አርመናውያን በክርስትና እምነታቸው እና በማንነታቸው ምክንያት ብቻ በግፍ ተጨፍጭፈዋል፣ በበረሃም ተሰደው አልቀዋል። ነገር ግን ዛሬ አርሜንያውያን ከየትኛውም ጊዜ በላይ አብበው፣ እምነታቸውንም አጽንተው ይገኛሉ። ጥይት እና እሳት ስጋን ሊገድል ይችላል፣ እምነትን እና መንፈስን ግን መቼም ሊያጠፋ አይችልም።
ታዋቂው የጥንት ቤተ ክርስቲያን ጸሐፊ ቴርቱሊያን እንዳለው፡-
"የሰማዕታት ደም የቤተ ክርስቲያን ዘር ነው።"
በአርሲ ተራሮች ላይ የፈሰሰው የነ አቶ አማረ፣ የነ ወጣት ተሬ ደሴ ደም በከንቱ አይቀርም። የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደሚያስተምረን፣ መከራ በበዛ ቁጥር፣ መቅደሶች በነደዱ ቁጥር፣ የእምነት ስር ይበልጥ ይጠልቃል እንጂ አይደርቅም።
በእንደዚህ ዓይነት ጥልቅ ሀዘን እና የሰብአዊነት ውድቀት ውስጥ ስናልፍ፣ የሰው ልጅ ታሪክ ካፈራቸው ታላላቅ መሪዎች እና ፈላስፎች የምንማረው ብዙ ነገር አለ። ጭካኔን በጭካኔ መመለስ የትም አያደርስም።
የሰብአዊ መብት ታጋዩ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር (የተናገረው ኃያል ቃል በዚህ ጊዜ ትዝ ይለናል፡-
"ጨለማ ጨለማን ሊያባርር አይችልም፤ ይህንን ማድረግ የሚችለው ብርሃን ብቻ ነው። ጥላቻ ጥላቻን ሊያጠፋ አይችልም፤ ይህንን ማድረግ የሚችለው ፍቅር ብቻ ነው።"
በአርሲ የተፈጸመው ድርጊት የጨለማ እና የጥላቻ ፍሬ ነው። ነገር ግን የተፈናቀሉት ምዕመናን ጽላቱን አቅፈው መውጣታቸው፣ ብርሃንን እና ፍቅርን ምርጫቸው እንዳደረጉ ያሳያል።
የሰላም ኖቤል ሽልማት አሸናፊው እና የሆሎኮስት (የአይሁዳውያን ጭፍጨፋ) ተራፊው ኤሊ ዊሰል ስለ ግፍ ዝምታ ሲናገር፡-
"ዝምታ ሁልጊዜም የሚጠቅመው አጥቂውን እንጂ ተጠቂውን አይደለም። ገለልተኝነት የሚረዳው ጨቋኙን እንጂ ተጨቋኙን አይደለም።" ብሎ ነበር።
ስለሆነም የነዚህን ንጹሐን መገደል፣ የ101 ዓመት ታሪካዊ ቅርስ መቃጠል፣ እና የ280 ሰዎች መፈናቀል እንደ ቀላል ዜና አልፈነው ልንሄድ አይገባም። ህመማቸውን ልንጋራ፣ ድምጻቸው ልንሆን ይገባል።
ታላቁ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ደግሞ ስለ መጽናት እንዲህ ይላሉ፡-
"ትልቁ የህይወት ክብር ያለው ፈጽሞ ባለመውደቅ ውስጥ ሳይሆን፣ በወደቅን ቁጥር ተመልሶ በመነሳት ውስጥ ነው።"
ኦርቶዶክሳውያኑ ዛሬ ቤታቸው ፈርሶ፣ ዘመዶቻቸው ተገድለውባቸው ሜዳ ላይ ወድቀው ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን እምነታቸው እስካለ ድረስ፣ ነገ ከአመዱ ላይ ተመልሰው ይነሳሉ።
በአሰኮ ወረዳ ብቻ ከ280 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተፈናቅለዋል። መፈናቀል ማለት መጓዝ ብቻ አይደለም። መፈናቀል ማለት ትዝታን፣ ልፋትን፣ የልጅነት የቦረቁበትን አፈር፣ እና የዘመዶችን መቃብር ትቶ መሄድ ማለት ነው። እነዚህ ሰዎች አሁን ያሉት ሜዳ ላይ ነው። የለበሱት ልብስ ብቻ ነው ያላቸው። የሌሊቱ ብርድ ሲቆራርጣቸው፣ የጠዋቱ ጸሐይ ሲያቃጥላቸው፣ የልጆቻቸው ርሃብ አንጀታቸውን ሲበላው... ያላቸው ብቸኛ መጽናኛ በደረታቸው ያቀፉት እምነታቸው ብቻ ነው።
"ስለ አንተ ሁልጊዜም ተገድለናል እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል" (መዝሙር 43:22)። የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሀዘን መግለጫቸውን የጀመሩት በዚህ የዳዊት መዝሙር ነበር። ይህ ቃል የዛሬን ብቻ ሳይሆን የዘመናትን የክርስቲያኖችን ህይወት የሚገልጽ ነው።
በእርግጥም እንደ በግ ለመታረድ የተሰለፉት እነዚህ ወገኖች ጥፋታቸው ምንድን ነው? ከማንም ጋር ያልተጣሉ፣ የፖለቲካ አጀንዳ የሌላቸው፣ ኑሯቸውን ለማሸነፍ መሬት የሚጭሩ ምስኪን ገበሬዎች ነበሩ። ነገር ግን በአክራሪነት የታወረው አእምሮ ይህንን ሊረዳ አይችልም።
እሳት ሁሉንም ነገር ያወድማል፤ መጽሐፍትን ያቃጥላል፣ ግድግዳን ያፈርሳል፣ ስጋን ያጠፋል። ነገር ግን እሳት እምነትን ሊያቃጥል አይችልም። የ101 ዓመቱ የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ዛሬ በአካላዊ ገጽታው ባይኖርም፣ ያ መቅደስ የሰራው መንፈሳዊ ህንጻ ግን አሁንም በምዕመናኑ ልብ ውስጥ ጸንቶ ይገኛል።
የ13ቱ ሰማዕታት ነፍስ በሰላም ታርፋለች፤ ደማቸው ግን ለትውልድ የሚተላለፍ የጽናት ትምህርት ሆኖ ይኖራል። የተሰደዱት ወገኖቻችን ዛሬ ሜዳ ላይ ቢሆኑም፣ የታሪክ ጌታ የሆነው አምላክ ነገን አዲስ አድርጎ ይሰራላቸዋል። የጥላቻ ኃይሎች በክፋታቸው መቅደሱን አፍርሰውታል፤ ሆኖም እውነተኛዋ ቤተ ክርስቲያን የድንጋይ እና የእንጨት ክምር ሳትሆን፣ ያቺ በስደት መሃልም ጽላቷን አቅፋ የምትጓዘዋ የሰው ልጅ ልብ ናት።
እስከዚያው ግን እንደ አቡነ ኤልሳዕ ጸሎት፤ ፈጣሪ የሞቱትን ነፍስ በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍ፣ የተፈናቀሉትን፣ የተራቡትን እና የተራቆቱትን ደግሞ በምህረት እጁ ይጎብኝ፣ ያጽናናም። ከጭስ እና ከአመድ በስተጀርባ፣ ብርሃን አለና።
2 days ago
በአዲስ አበባ ስታዲየም :
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።
በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።
በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።
ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።
የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።
በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።
በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።
ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።
የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 days ago
በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል የተካሄደው የቁጣ ስልክ ጥሪ
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
2 days ago
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ በሰጡት መግለጫ ምን ምን ጉዳዮችን አነሱ?
**********************
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፣ ከድምፅ መስጫ ቀን በኋላ ያለውን አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ሁኔታና ቀጣይ ሥራዎችን አስመልክተው በሰጡት ማጠቃለያ መግለጫ በርካታ ዋና ዋና ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡ ሰብሳቢዋ በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
የድምፅ አሰጣጥ እና የቆጠራ ሂደት ወቅታዊ ሁኔታ፦ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን የተከናወነው የድምፅ መስጠት ሂደት በአብዛኛው በጥሩ ሁኔታ መከናወኑን የገለጹት ሰብሳቢዋ፣ የተወሰኑ ክልሎች በሰዓቱ አጠናቀው ወዲያውኑ ወደ ቆጠራ መግባታቸውንና አንዳንዶቹ ደግሞ ቆጠራውን አሳድረው ማከናወናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በተለየ ሁኔታ በአዲስ አበባ በነበረው ረጅም ሰልፍ ምክንያት ቦርዱ እስከ ሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ የጊዜ ማራዘሚያ ማድረጉንና በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ እንዲሁም በሲዳማ፣ በጋምቤላ፣ በአማራ እና በሶማሌ ክልሎች የሚገኙ የተወሰኑ ምርጫ ጣቢያዎች አሁንም በድምፅ ቆጠራ ሥራ ላይ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡
የመዘግየት ችግሮች እና የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች፦ በአዲስ አበባ የተስተዋለውን የሰልፍ መርዘምና የመዘግየት ችግር ለመፍታት ቦርዱ በርካታ ከፍተኛ ባለሙያዎችንና ኤክስፐርቶችን ወደ ጣቢያዎች መድቦ እንደነበር ሰብሳቢዋ አስታውቀዋል፡፡
ለመዘግየቱ እንደ ምክንያት ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች በመራጮች መዝገብ ላይ ስም የመፈለግ ሂደት መርዘም እና በአንዳንድ ጣቢያዎች የዕጩዎች ቁጥር እስከ 123 መድረሱ መራጮች በምስጢር ድምፅ መስጫ ክፍል ውስጥ የሚወስዱትን ደቂቃ ማርዘሙን ነው፡፡
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ቦርዱ ተጨማሪ የድምፅ መስጫ ሳጥኖችንና ቡዞችን ወደ ጣቢያዎች ልኮ መፍትሔ ለመስጠት መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ቅሬታዎችን ማስተናገድና የተወሰዱ የቅጣት እርምጃዎች፦ ቦርዱ በሕግ ክፍል፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች የሥራ ክፍል፣ በ6412 የጥሪ ማዕከልና ከታዛቢዎች በሚደርሱት ጥቆማዎች መሠረት የርምትና የማጣራት እርምጃዎችን ሲወስድ መቆየቱን ሜላትወርቅ ኃይሉ ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ አንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች መግባት የሌለባቸው ሰዎች ስለመታየታቸው የቀረቡ ጥቆማዎችን ቦርዱ በሞኒተሪንግ ቡድን አጣርቶ እውነት ሆነው በተገኙት ላይ እርምጃ መውሰዱንና ሕግና ደንብ ጥሰው የተገኙ የምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችን ማሰናበቱን አረጋግጠዋል፡፡
የውጤት አሰጣጥ እና የማረጋገጥ ቀጣይ ሥራዎች፦ በአሁኑ ወቅት የምርጫ ውጤታቸው በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ተደምሮ ያለቀላቸው ውጤቶች በየጣቢያዎቹ ተለጥፈው ለሕዝብ ይፋ መደረጋቸውን የጠቀሱት ሰብሳቢዋ፣ ቀጥሎም ውጤቶቹ ወደ ምርጫ ክልል ሄደው የማዳመር ሥራ እንደሚሠራ አስረድተዋል፡፡
በመጨረሻም ውጤቶቹ ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት የማረጋገጫ ማዕከል ከመጡ በኋላ፣ ከተመዘገበው የመራጭ ቁጥር አንጻር ዋጋ ያላቸው እና የሌላቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ተለይተው የማረጋገጥ ሥራው በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ቦርዱ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡
#ኢትዮጵያ_መርጣለች #ኢትዮጵያ_አሸንፋለች
**********************
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፣ ከድምፅ መስጫ ቀን በኋላ ያለውን አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ሁኔታና ቀጣይ ሥራዎችን አስመልክተው በሰጡት ማጠቃለያ መግለጫ በርካታ ዋና ዋና ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡ ሰብሳቢዋ በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
የድምፅ አሰጣጥ እና የቆጠራ ሂደት ወቅታዊ ሁኔታ፦ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን የተከናወነው የድምፅ መስጠት ሂደት በአብዛኛው በጥሩ ሁኔታ መከናወኑን የገለጹት ሰብሳቢዋ፣ የተወሰኑ ክልሎች በሰዓቱ አጠናቀው ወዲያውኑ ወደ ቆጠራ መግባታቸውንና አንዳንዶቹ ደግሞ ቆጠራውን አሳድረው ማከናወናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በተለየ ሁኔታ በአዲስ አበባ በነበረው ረጅም ሰልፍ ምክንያት ቦርዱ እስከ ሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ የጊዜ ማራዘሚያ ማድረጉንና በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ እንዲሁም በሲዳማ፣ በጋምቤላ፣ በአማራ እና በሶማሌ ክልሎች የሚገኙ የተወሰኑ ምርጫ ጣቢያዎች አሁንም በድምፅ ቆጠራ ሥራ ላይ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡
የመዘግየት ችግሮች እና የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች፦ በአዲስ አበባ የተስተዋለውን የሰልፍ መርዘምና የመዘግየት ችግር ለመፍታት ቦርዱ በርካታ ከፍተኛ ባለሙያዎችንና ኤክስፐርቶችን ወደ ጣቢያዎች መድቦ እንደነበር ሰብሳቢዋ አስታውቀዋል፡፡
ለመዘግየቱ እንደ ምክንያት ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች በመራጮች መዝገብ ላይ ስም የመፈለግ ሂደት መርዘም እና በአንዳንድ ጣቢያዎች የዕጩዎች ቁጥር እስከ 123 መድረሱ መራጮች በምስጢር ድምፅ መስጫ ክፍል ውስጥ የሚወስዱትን ደቂቃ ማርዘሙን ነው፡፡
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ቦርዱ ተጨማሪ የድምፅ መስጫ ሳጥኖችንና ቡዞችን ወደ ጣቢያዎች ልኮ መፍትሔ ለመስጠት መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ቅሬታዎችን ማስተናገድና የተወሰዱ የቅጣት እርምጃዎች፦ ቦርዱ በሕግ ክፍል፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች የሥራ ክፍል፣ በ6412 የጥሪ ማዕከልና ከታዛቢዎች በሚደርሱት ጥቆማዎች መሠረት የርምትና የማጣራት እርምጃዎችን ሲወስድ መቆየቱን ሜላትወርቅ ኃይሉ ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ አንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች መግባት የሌለባቸው ሰዎች ስለመታየታቸው የቀረቡ ጥቆማዎችን ቦርዱ በሞኒተሪንግ ቡድን አጣርቶ እውነት ሆነው በተገኙት ላይ እርምጃ መውሰዱንና ሕግና ደንብ ጥሰው የተገኙ የምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችን ማሰናበቱን አረጋግጠዋል፡፡
የውጤት አሰጣጥ እና የማረጋገጥ ቀጣይ ሥራዎች፦ በአሁኑ ወቅት የምርጫ ውጤታቸው በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ተደምሮ ያለቀላቸው ውጤቶች በየጣቢያዎቹ ተለጥፈው ለሕዝብ ይፋ መደረጋቸውን የጠቀሱት ሰብሳቢዋ፣ ቀጥሎም ውጤቶቹ ወደ ምርጫ ክልል ሄደው የማዳመር ሥራ እንደሚሠራ አስረድተዋል፡፡
በመጨረሻም ውጤቶቹ ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት የማረጋገጫ ማዕከል ከመጡ በኋላ፣ ከተመዘገበው የመራጭ ቁጥር አንጻር ዋጋ ያላቸው እና የሌላቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ተለይተው የማረጋገጥ ሥራው በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ቦርዱ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡
#ኢትዮጵያ_መርጣለች #ኢትዮጵያ_አሸንፋለች
2 days ago
ምርጫው የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ነው፦ የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
#ethiopia | የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ምርጫው ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ግልጽነት እና ፍትሐዊነት የተንጸባረቀበት፣ በመራጩ ሕዝብና በተፎካካሪ ፓርቲዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅቡልነት ያገኘ መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው እንዳመለከተው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ምርጫ መንግሥት በከተማዋ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሌላኛው ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ አልፏል።
ከእነዚህም መካከል እንደ ትልቅ ጅምር የሚወሰደው የዲጂታል የእጩዎች ምዝገባ ሒደት አላስፈላጊ መጉላላትን የቀነሰ እና የእጩዎችን መረጃ እና ደኅንነት ያረጋገጠ የአሰራ ግልፅነትን የፈጠረ መሆኑ በምርጫው ሂደት ከታዩ ዐበይት አዎንታዊ ሁነቶች መካከል እንደሆነ ተመላክቷል።
በምርጫው ዕለት መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ያለምንም ቀስቃሽ በነቂስ በመውጣት ድምፅ መስጠታቸውን የገለጸው ምክር ቤቱ፣ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና አረጋውያን ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ሂደቱን ይበልጥ እንዳደመቀው አብራርቷል።
ከምርጫ ጣቢያዎች የሚመጡ የአሠራር ችግሮችን በጋራ በመገምገም፣ ከምርጫ ቦርድ እና ከከተማው አመራሮች ጋር በቀጥታ በመነጋገር አፋጣኝ የእርምት እርምጃ መወሰዱ በፓርቲዎች እና በአስፈፃሚ አካላት መካከል መተማመንን ማጎልበቱ ተገልጿል።
በተጨማሪም የከተማዋ የጸጥታ አካላት ያለምንም ወገንተኝነት፣ ፍጹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ የምርጫ ጣቢያዎችን እና የመራጩን ሕዝብ ደኅንነት በመጠበቅ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።
በሂደቱም ምንም ዓይነት የጸጥታ መደፍረስም ሆነ የምርጫ ሕግ መጣስ ሳይኖር መጠናቀቁ የከተማዋን ነዋሪዎችና የጸጥታ አካላት ከፍተኛ የበስለት ደረጃ ያሳየ "የአዲስ አበባ ሞዴል" መሆኑ ተነግሯል።
የድምፅ መስጠት ሂደቱ በስኬት ተጠናቅቆ ወደ ቀጣዩ የድምፅ ቆጠራ እና ውጤት ማደራጀት ምዕራፍ መሸጋገሩን የጠቀሰው ምክር ቤቱ፤ የምርጫ ቦርድ ሕጋዊ አሠራርን መሠረት አድርጎ የከተማውን ውጤት በኦፊሴላዊ መልኩ እስኪገልጽ ድረስ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ደጋፊዎች ፍጹም በሆነ ትዕግሥት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiaprevails #peace #ምርጫ
#ethiopia | የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ምርጫው ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ግልጽነት እና ፍትሐዊነት የተንጸባረቀበት፣ በመራጩ ሕዝብና በተፎካካሪ ፓርቲዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅቡልነት ያገኘ መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው እንዳመለከተው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ምርጫ መንግሥት በከተማዋ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሌላኛው ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ አልፏል።
ከእነዚህም መካከል እንደ ትልቅ ጅምር የሚወሰደው የዲጂታል የእጩዎች ምዝገባ ሒደት አላስፈላጊ መጉላላትን የቀነሰ እና የእጩዎችን መረጃ እና ደኅንነት ያረጋገጠ የአሰራ ግልፅነትን የፈጠረ መሆኑ በምርጫው ሂደት ከታዩ ዐበይት አዎንታዊ ሁነቶች መካከል እንደሆነ ተመላክቷል።
በምርጫው ዕለት መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ያለምንም ቀስቃሽ በነቂስ በመውጣት ድምፅ መስጠታቸውን የገለጸው ምክር ቤቱ፣ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና አረጋውያን ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ሂደቱን ይበልጥ እንዳደመቀው አብራርቷል።
ከምርጫ ጣቢያዎች የሚመጡ የአሠራር ችግሮችን በጋራ በመገምገም፣ ከምርጫ ቦርድ እና ከከተማው አመራሮች ጋር በቀጥታ በመነጋገር አፋጣኝ የእርምት እርምጃ መወሰዱ በፓርቲዎች እና በአስፈፃሚ አካላት መካከል መተማመንን ማጎልበቱ ተገልጿል።
በተጨማሪም የከተማዋ የጸጥታ አካላት ያለምንም ወገንተኝነት፣ ፍጹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ የምርጫ ጣቢያዎችን እና የመራጩን ሕዝብ ደኅንነት በመጠበቅ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።
በሂደቱም ምንም ዓይነት የጸጥታ መደፍረስም ሆነ የምርጫ ሕግ መጣስ ሳይኖር መጠናቀቁ የከተማዋን ነዋሪዎችና የጸጥታ አካላት ከፍተኛ የበስለት ደረጃ ያሳየ "የአዲስ አበባ ሞዴል" መሆኑ ተነግሯል።
የድምፅ መስጠት ሂደቱ በስኬት ተጠናቅቆ ወደ ቀጣዩ የድምፅ ቆጠራ እና ውጤት ማደራጀት ምዕራፍ መሸጋገሩን የጠቀሰው ምክር ቤቱ፤ የምርጫ ቦርድ ሕጋዊ አሠራርን መሠረት አድርጎ የከተማውን ውጤት በኦፊሴላዊ መልኩ እስኪገልጽ ድረስ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ደጋፊዎች ፍጹም በሆነ ትዕግሥት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiaprevails #peace #ምርጫ
2 days ago
የእንጦጦ-ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ተመረቀ
#fastmereja | የፊታችን ማክሰኞ፣ ሰኔ 2 ቀን 2026 ዓ.ም፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተከናወነው የእንጦጦ-ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ተመርቆ ለሕዝብ ክፍት ሆኗል። ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተመርቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት፤ ከዚህ ቀደም ለሰው ኑሮ ምቹ ያልሆነ፣ የተጎሳቆለ እና ለአደጋ የተጋለጠ የነበረው የእንጦጦ እስከ ቀጨኔ ያለው አካባቢ፣ አሁን ላይ ወደ ቀድሞ ተፈጥሯዊ ይዘቱ ተመልሶ ውብ እና ማራኪ ገጽታን ተላብሷል። ይህ ፕሮጀክት የከተማዋን "ሳምባ" በሆነው ደን ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ ታሪክ እና የስራ ባህል የሚያንጸባርቁ ቅርሶችና ሐውልቶች ተካተውበታል።
የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ይዘቶች፦
ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 597 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፣ 9.6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የወንዝ ዳርቻን ይሸፍናል።
15 ሄክታር መሬት በአረንጓዴ ተሸፍኗል። በውስጡም 210 ቀፎ ዘመናዊ ንብ እርባታ፣ የአበባ ጋርደን እና የእጽዋት ጋርደን የተካተቱበት ነው።
የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፦
6.4 ኪሎ ሜትር የተሽከርካሪ መንገድ።
8 ኪሎ ሜትር የሳይክል መንገድ።
22 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ።
4 ኪሎ ሜትር የሃይኪንግ መንገድ።
39 ቼክ ዳሞች የተገነቡ ሲሆን፣ ሁለት አዳዲስ ድልድዮች እና ሶስት ነባር ድልድዮችም እድሳት ተደርጎላቸዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ይህንን ለብዙኃን አገልግሎት እንዲሰጥ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባውን የከተማ መናፈሻ፣ የከተማው ነዋሪ እንዲጠቀምበት እና እንዲንከባከበው ጥሪ አቅርቧል። ፕሮጀክቱ ለመዝናኛ፣ ለንግድ እና ለተለያዩ ማህበራዊ ኩነቶች ምቹ ሆኖ የተዘጋጀ መሆኑም ተገልጿል።
#fastmereja | የፊታችን ማክሰኞ፣ ሰኔ 2 ቀን 2026 ዓ.ም፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተከናወነው የእንጦጦ-ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ተመርቆ ለሕዝብ ክፍት ሆኗል። ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተመርቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት፤ ከዚህ ቀደም ለሰው ኑሮ ምቹ ያልሆነ፣ የተጎሳቆለ እና ለአደጋ የተጋለጠ የነበረው የእንጦጦ እስከ ቀጨኔ ያለው አካባቢ፣ አሁን ላይ ወደ ቀድሞ ተፈጥሯዊ ይዘቱ ተመልሶ ውብ እና ማራኪ ገጽታን ተላብሷል። ይህ ፕሮጀክት የከተማዋን "ሳምባ" በሆነው ደን ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ ታሪክ እና የስራ ባህል የሚያንጸባርቁ ቅርሶችና ሐውልቶች ተካተውበታል።
የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ይዘቶች፦
ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 597 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፣ 9.6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የወንዝ ዳርቻን ይሸፍናል።
15 ሄክታር መሬት በአረንጓዴ ተሸፍኗል። በውስጡም 210 ቀፎ ዘመናዊ ንብ እርባታ፣ የአበባ ጋርደን እና የእጽዋት ጋርደን የተካተቱበት ነው።
የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፦
6.4 ኪሎ ሜትር የተሽከርካሪ መንገድ።
8 ኪሎ ሜትር የሳይክል መንገድ።
22 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ።
4 ኪሎ ሜትር የሃይኪንግ መንገድ።
39 ቼክ ዳሞች የተገነቡ ሲሆን፣ ሁለት አዳዲስ ድልድዮች እና ሶስት ነባር ድልድዮችም እድሳት ተደርጎላቸዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ይህንን ለብዙኃን አገልግሎት እንዲሰጥ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባውን የከተማ መናፈሻ፣ የከተማው ነዋሪ እንዲጠቀምበት እና እንዲንከባከበው ጥሪ አቅርቧል። ፕሮጀክቱ ለመዝናኛ፣ ለንግድ እና ለተለያዩ ማህበራዊ ኩነቶች ምቹ ሆኖ የተዘጋጀ መሆኑም ተገልጿል።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
🚨 "እባካችሁ ድምፅ ሁኑን!" — ከምስራቅ አርሲ ጫካዎች የተሰማ የድረሱልን ጥሪ!
መላው አገር በምርጫው ትኩረት በተጠመደበት በዚህ ወቅት፣ በምስራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ጥቃት እየተፈጸመ ይገኛል።
📌 እስካሁን የደረሰው ጉዳት፦
የሕይወት መጥፋት፦ከ37 በላይ ንጹሐን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።
የንብረት ውድመት፦234 መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል።
የሃይማኖት ተቋማት፦ታሪካዊው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል እና የኩፍቴና መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል።
⚠️ ወቅታዊ ሁኔታ፦
ጥቃቱ አሁንም በተለያዩ ቀበሌዎች (ዘዲቡ፣ እሬቻ ሚካኤል፣ ሱንቴ ማርያም...) የቀጠለ ሲሆን፣ አቅመ-ቢስ እናቶችና ሕፃናት ሕይወታቸውን ለማዳን ንብረታቸውን ጥለው በጫካዎች ውስጥ ተደብቀው ይገኛሉ።
🙏 ነፍስ ይማር!
መላው አገር በምርጫው ትኩረት በተጠመደበት በዚህ ወቅት፣ በምስራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ጥቃት እየተፈጸመ ይገኛል።
📌 እስካሁን የደረሰው ጉዳት፦
የሕይወት መጥፋት፦ከ37 በላይ ንጹሐን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።
የንብረት ውድመት፦234 መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል።
የሃይማኖት ተቋማት፦ታሪካዊው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል እና የኩፍቴና መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል።
⚠️ ወቅታዊ ሁኔታ፦
ጥቃቱ አሁንም በተለያዩ ቀበሌዎች (ዘዲቡ፣ እሬቻ ሚካኤል፣ ሱንቴ ማርያም...) የቀጠለ ሲሆን፣ አቅመ-ቢስ እናቶችና ሕፃናት ሕይወታቸውን ለማዳን ንብረታቸውን ጥለው በጫካዎች ውስጥ ተደብቀው ይገኛሉ።
🙏 ነፍስ ይማር!
2 days ago
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት ተጠናቅቋል - የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የምርጫ ኮማንድ ፖስት
********************
የድምፅ መስጫ ሂደቱ እስከ ከሌሊቱ 7፡00 ሰዓት ሲከናወን ቆይቷል።
በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምጽ የመስጠት ሂደት ፍጹም ሠላማዊ እና ስኬታማ ሆኖ መጠናቀቁን በአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የተደራጀው የምርጫ ኮማንድ ፖስት አስታውቋል።
በትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን፣ ግንቦት 24 ቀንም ሆነ ሌሊት ምንም አይነት ወንጀል አለመፈጸሙ ተገልጿል።
ድምጽ የመስጠት ሥርዓቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ መራጩ ሕዝብ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ዕጩዎች እና ታዛቢዎች ላበረከቱት አስተዋጽኦ እና ኃላፊነታቸውን በተገቢው ለተወጡ መላው የጸጥታ አካላት ኮማንድ ፖስቱ ምስጋናውን አቅርቧል።
የድምጽ አሰጣጡ ከተጠናቀቀበት ሰዓት ጀምሮ ድምጽ ቆጠራው መቀጠሉንም ኮማንድ ፖስቱ አስታውቋል።
ድህረ ምርጫ ያለው ሂደት በተመሳሳይ በስኬት እንዲከናወን ባለ ድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የተደራጀው የምርጫ ኮማንድ ፖስት ጥሪውን አቅርቧል።
********************
የድምፅ መስጫ ሂደቱ እስከ ከሌሊቱ 7፡00 ሰዓት ሲከናወን ቆይቷል።
በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምጽ የመስጠት ሂደት ፍጹም ሠላማዊ እና ስኬታማ ሆኖ መጠናቀቁን በአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የተደራጀው የምርጫ ኮማንድ ፖስት አስታውቋል።
በትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን፣ ግንቦት 24 ቀንም ሆነ ሌሊት ምንም አይነት ወንጀል አለመፈጸሙ ተገልጿል።
ድምጽ የመስጠት ሥርዓቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ መራጩ ሕዝብ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ዕጩዎች እና ታዛቢዎች ላበረከቱት አስተዋጽኦ እና ኃላፊነታቸውን በተገቢው ለተወጡ መላው የጸጥታ አካላት ኮማንድ ፖስቱ ምስጋናውን አቅርቧል።
የድምጽ አሰጣጡ ከተጠናቀቀበት ሰዓት ጀምሮ ድምጽ ቆጠራው መቀጠሉንም ኮማንድ ፖስቱ አስታውቋል።
ድህረ ምርጫ ያለው ሂደት በተመሳሳይ በስኬት እንዲከናወን ባለ ድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የተደራጀው የምርጫ ኮማንድ ፖስት ጥሪውን አቅርቧል።
2 days ago
ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡
ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡
ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
2 days ago
ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች! - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
***********************
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችውን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት። ለሀገራቸው የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች። ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል። ዛሬ የተደገመውም ይኸው ነው።
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች። ለዚህ ደግሞ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር።
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል። እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈው ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው።
ምርጫው እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተው ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም። ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል። ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃው ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫውን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች።
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ግንቦት 25 2018፣ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ
#ebc #ethiopia #gcs
***********************
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችውን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት። ለሀገራቸው የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች። ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል። ዛሬ የተደገመውም ይኸው ነው።
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች። ለዚህ ደግሞ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር።
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል። እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈው ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው።
ምርጫው እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተው ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም። ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል። ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃው ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫውን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች።
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ግንቦት 25 2018፣ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ
#ebc #ethiopia #gcs
Sponsored by
Surafel
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሱማሊያ አለም አቀፍ አጋሮች መንግስትና ተቃዋሚዎች በምርጫ ዙሪያ ንግግራቸውን እንዲቀጥሉ አሳሰቡ፡፡ በሱማሊያ ውስጥ የተፈጠረውን ፖለቲካዊ ውጥረት ተከትሎ አለም አቀፍ አጋሮች የፌዴራል መንግስቱና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ውይይታቸውን በመቀጠል የምርጫ ፍኖተ ካርታ እንዲያወጡ አሳሰቡ፡፡
ዩናይትድ ኪንግደም፣ የተመድ የሽግግር ተልእኮ ለሱማሊያ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ስዊድን፣ ስዊዘርላንድና ኖርዌይ ዛሬ ባወጡት የጋራ መግለጫ ‹‹በዚህ ወሳኝ ፖለቲካዊ ወቅት የሱማሊያ መሪዎች ለአገራቸው ብሄራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሁሉም አካላት በተቻለ ፍጥነት ውይይታቸውን ቀጥለው ለሱማሊያ ህዝብ ጥቅም ሲሉ በምርጫ ፍኖተ ካርታ ላይ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጥሪያችንን እናቀርባለን›› ያለው መግለጫቸው ሁሉም ውጥረትን ከሚያባብስ ድርጊት እንዲቆጠቡም አሳስቧል፡፡
በሱማሊያዊያን በሚመራው ውይይት ላይ ድጋፍ እንዲሰጡ ከተጠየቁ ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጿል፡፡ ይህ መግለጫ ሊወጣ የቻለው የሱማሊያ ፌዴራል መንግስትና ተቃዋሚ ፓርቲዎች በህገ መንግስት ለውጥና ፖለቲካዊ ሽግግር ዙሪያ ያደረጉት ውይይት ያለ ስምምነት መበተኑን ተከትሎ ነው፡፡
ዩናይትድ ኪንግደም፣ የተመድ የሽግግር ተልእኮ ለሱማሊያ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ስዊድን፣ ስዊዘርላንድና ኖርዌይ ዛሬ ባወጡት የጋራ መግለጫ ‹‹በዚህ ወሳኝ ፖለቲካዊ ወቅት የሱማሊያ መሪዎች ለአገራቸው ብሄራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሁሉም አካላት በተቻለ ፍጥነት ውይይታቸውን ቀጥለው ለሱማሊያ ህዝብ ጥቅም ሲሉ በምርጫ ፍኖተ ካርታ ላይ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጥሪያችንን እናቀርባለን›› ያለው መግለጫቸው ሁሉም ውጥረትን ከሚያባብስ ድርጊት እንዲቆጠቡም አሳስቧል፡፡
በሱማሊያዊያን በሚመራው ውይይት ላይ ድጋፍ እንዲሰጡ ከተጠየቁ ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጿል፡፡ ይህ መግለጫ ሊወጣ የቻለው የሱማሊያ ፌዴራል መንግስትና ተቃዋሚ ፓርቲዎች በህገ መንግስት ለውጥና ፖለቲካዊ ሽግግር ዙሪያ ያደረጉት ውይይት ያለ ስምምነት መበተኑን ተከትሎ ነው፡፡
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በዛሬው ዕለት በመላው ሀገሪቱ እየተካሄደ ባለው የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሒደት ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባወጡት ይፋዊ መልዕክት የኢትዮጵያን ሕዝብ "አስደናቂም ተአምረኛም" ሲሉ በከፍተኛ ደረጃ አድንቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ መልዕክታቸው፣ ሕዝቡ በዘንድሮው ምርጫ የሀገር ወዳድነት እና የወል መሻቱን የመጠበቅ አቅሙን ዳግም ለዓለም ማሳየቱን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መራጩ ሕዝብ የገጠሙትን በርካታ የተፈጥሮ፣ የማኅበራዊ እና የጸጥታ ፈተናዎች ተቋቁሞ ድምፁን በመስጠቱ ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበውለታል። በምስጋና መልዕክታቸው ላይም መራጩ ዜጋ ያሳለፋቸውን ውጣ ውረዶች በዝርዝር አስቀምጠዋል። በዚህም መሠረት ዜጎች የሌሊቱን ብርድና ጨለማ ሳይፈሩ፣ እንዲሁም የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ሳይበግራቸው በምርጫ ጣቢያዎች መገኘታቸውን አድንቀዋል።
ከዚህም ባሻገር መራጮች ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶችን ወደ ጎን በመተው በምርጫው መሳተፋቸውን፣ ረጃጅም ሰልፎች ሳያታክቷቸው፣ እንዲሁም የአካል ጉዳት፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ሳይገድባቸው ድምፃቸውን መስጠታቸውን በከፍተኛ አክብሮት አውስተዋል። የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጆቻቸውን አዝለው ድምፅ የሰጡ እናቶችን ትጋት ያወደሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ከምንም በላይ ደግሞ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸውን ዜጎች ጽናት የዴሞክራሲ እውነተኛ ማሳያ መሆኑን አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ይህ ሕዝብ በውጣ ውረዶች መካከል ያሳየው ጽናት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ታላቅ መስዋዕትነት መሆኑን አጽንዖት ሰጥተዋል። አያይዘውም በመጪው አምስት ዓመት ሥልጣን ለሚይዙ እና የሕዝብ ውክልና ለሚያገኙ አካላት ጥብቅ አደራ አስተላልፈዋል።
"ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በምርጫው አሸንፈው ኃላፊነት ለሚቀበሉ ተመራጮች፣ ያከበራቸውን ሕዝብ አክብረው፣ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ይህንን ሁሉ ዋጋ የከፈለውን ዜጋ በንጽሕና እና በታማኝነት እንዲያገለግሉ ጥሪያቸውን በማቅረብ መልዕክታቸውን ደምድመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መራጩ ሕዝብ የገጠሙትን በርካታ የተፈጥሮ፣ የማኅበራዊ እና የጸጥታ ፈተናዎች ተቋቁሞ ድምፁን በመስጠቱ ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበውለታል። በምስጋና መልዕክታቸው ላይም መራጩ ዜጋ ያሳለፋቸውን ውጣ ውረዶች በዝርዝር አስቀምጠዋል። በዚህም መሠረት ዜጎች የሌሊቱን ብርድና ጨለማ ሳይፈሩ፣ እንዲሁም የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ሳይበግራቸው በምርጫ ጣቢያዎች መገኘታቸውን አድንቀዋል።
ከዚህም ባሻገር መራጮች ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶችን ወደ ጎን በመተው በምርጫው መሳተፋቸውን፣ ረጃጅም ሰልፎች ሳያታክቷቸው፣ እንዲሁም የአካል ጉዳት፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ሳይገድባቸው ድምፃቸውን መስጠታቸውን በከፍተኛ አክብሮት አውስተዋል። የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጆቻቸውን አዝለው ድምፅ የሰጡ እናቶችን ትጋት ያወደሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ከምንም በላይ ደግሞ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸውን ዜጎች ጽናት የዴሞክራሲ እውነተኛ ማሳያ መሆኑን አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ይህ ሕዝብ በውጣ ውረዶች መካከል ያሳየው ጽናት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ታላቅ መስዋዕትነት መሆኑን አጽንዖት ሰጥተዋል። አያይዘውም በመጪው አምስት ዓመት ሥልጣን ለሚይዙ እና የሕዝብ ውክልና ለሚያገኙ አካላት ጥብቅ አደራ አስተላልፈዋል።
"ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በምርጫው አሸንፈው ኃላፊነት ለሚቀበሉ ተመራጮች፣ ያከበራቸውን ሕዝብ አክብረው፣ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ይህንን ሁሉ ዋጋ የከፈለውን ዜጋ በንጽሕና እና በታማኝነት እንዲያገለግሉ ጥሪያቸውን በማቅረብ መልዕክታቸውን ደምድመዋል።
3 days ago
ሳውዲ አረቢያ በእስራኤል የተፈጸመውን የሊባኖስ ወታደራዊ ወረራ ኮነነች
#ethiopia | እስራኤል በሊባኖስ ላይ የከፈተችውን ወታደራዊ ጥቃት ሳውዲ አረቢያ አጥብቃ ያወገዘች ሲሆን የእስራኤል ጦር የሊባኖስን ድንበር ጥሶ መግባቱንና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት መጣሱን በፍጹም እንደማትቀበለው የሳውዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተጀመረውን ወረራ ለማስቆም እንዲሁም የእስራኤል ወታደራዊ ኃይል በሊባኖስ መሬት ላይ የሚያደርገውን መስፋፋት እንዲያበቃ የድርሻውን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪም የሊባኖስን ሉዓላዊ ፖለቲካዊ መብትና የህዝቧን ሰላም ማስከበር ከዓለም አቀፍ ስምምነቶች አንጻር ወሳኝ መሆኑን ሳውዲ አረቢያ በአጽንኦት ገልጻለች።
የሊባኖስ መንግስት በመላው የአገሪቱ ክልሎች ላይ ሙሉ ስልጣኑን እና ቁጥጥሩን መዘርጋት እንዲችል የጣኢፍ ስምምነት መከበር እንዳለበትም ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል።
በመጨረሻም ማንኛውም ዓይነት የጦር መሳሪያ በመንግስትና በህጋዊ የጸጥታ ተቋማት ቁጥጥር ስር ብቻ እንዲሆን የሊባኖስ ባለስልጣናት ያስተላለፉትን ውሳኔ ወደ ተግባር መለወጥ እንደሚገባ የሳውዲ መንግስት አመልክቷል።
ይህ ተግባር በሊባኖስ ምድር ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
#saudiarabia #israel #lebanon #middleeast #news #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | እስራኤል በሊባኖስ ላይ የከፈተችውን ወታደራዊ ጥቃት ሳውዲ አረቢያ አጥብቃ ያወገዘች ሲሆን የእስራኤል ጦር የሊባኖስን ድንበር ጥሶ መግባቱንና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት መጣሱን በፍጹም እንደማትቀበለው የሳውዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተጀመረውን ወረራ ለማስቆም እንዲሁም የእስራኤል ወታደራዊ ኃይል በሊባኖስ መሬት ላይ የሚያደርገውን መስፋፋት እንዲያበቃ የድርሻውን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪም የሊባኖስን ሉዓላዊ ፖለቲካዊ መብትና የህዝቧን ሰላም ማስከበር ከዓለም አቀፍ ስምምነቶች አንጻር ወሳኝ መሆኑን ሳውዲ አረቢያ በአጽንኦት ገልጻለች።
የሊባኖስ መንግስት በመላው የአገሪቱ ክልሎች ላይ ሙሉ ስልጣኑን እና ቁጥጥሩን መዘርጋት እንዲችል የጣኢፍ ስምምነት መከበር እንዳለበትም ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል።
በመጨረሻም ማንኛውም ዓይነት የጦር መሳሪያ በመንግስትና በህጋዊ የጸጥታ ተቋማት ቁጥጥር ስር ብቻ እንዲሆን የሊባኖስ ባለስልጣናት ያስተላለፉትን ውሳኔ ወደ ተግባር መለወጥ እንደሚገባ የሳውዲ መንግስት አመልክቷል።
ይህ ተግባር በሊባኖስ ምድር ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
#saudiarabia #israel #lebanon #middleeast #news #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa