2 months ago
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰብዓዊ መብቶችን ባከበረ መልኩ የተካሄደ ነው - የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት
*****************
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰብዓዊ መብቶችን ባከበረ መልኩ በስኬት የተካሄደና የሰከነ የፖለቲካ ፉክክር የታየበት መሆኑን የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ገለጸ።
የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ዳይሬክተር መስዑድ ገበየሁ እንደገለጹት፤ የዘንድሮው ምርጫ ሂደት ከሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አንጻር በጥሩ ሁኔታ የተከናወነና ስኬታማ ነበር።
አቶ መስዑድ እንዳሉት፣ በዘንድሮው ምርጫ ዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን አሳይተዋል።
በምርጫው የፉክክር ሂደት፣ ፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ ሃሳባቸውን ለህዝብ ሲያቀርቡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ የነበራቸው መናበብ አስደማሚ እንደነበር መታዘባቸውን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
ይህም ፖለቲካ ፓርቲዎች የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅሞች መከበር የሰከነ የፖለቲካ ምኅዳር በመፍጠር እየተሳተፉ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ አክለዋል።
በምርጫው ወቅት የተስተዋለው የምርጫ ጣቢያዎች አሠራርም ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ዜጎችን የመምረጥ መብት ያረጋገጠ ነበር ብለዋል።
በተለይ ለአካል ጉዳተኞች፣ መስማት ለተሳናቸው፣ ለነፍሰ ጡሮችና ጨቅላ ሕፃናት ለያዙ ወላጆች ምቹ ምኅዳር ተፈጥሮ እንደነበር በአብነት መጥቀሳቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
#ethiopia #democracy #government #humanrights #ethiopiaprevails #ebc
*****************
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰብዓዊ መብቶችን ባከበረ መልኩ በስኬት የተካሄደና የሰከነ የፖለቲካ ፉክክር የታየበት መሆኑን የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ገለጸ።
የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ዳይሬክተር መስዑድ ገበየሁ እንደገለጹት፤ የዘንድሮው ምርጫ ሂደት ከሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አንጻር በጥሩ ሁኔታ የተከናወነና ስኬታማ ነበር።
አቶ መስዑድ እንዳሉት፣ በዘንድሮው ምርጫ ዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን አሳይተዋል።
በምርጫው የፉክክር ሂደት፣ ፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ ሃሳባቸውን ለህዝብ ሲያቀርቡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ የነበራቸው መናበብ አስደማሚ እንደነበር መታዘባቸውን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
ይህም ፖለቲካ ፓርቲዎች የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅሞች መከበር የሰከነ የፖለቲካ ምኅዳር በመፍጠር እየተሳተፉ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ አክለዋል።
በምርጫው ወቅት የተስተዋለው የምርጫ ጣቢያዎች አሠራርም ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ዜጎችን የመምረጥ መብት ያረጋገጠ ነበር ብለዋል።
በተለይ ለአካል ጉዳተኞች፣ መስማት ለተሳናቸው፣ ለነፍሰ ጡሮችና ጨቅላ ሕፃናት ለያዙ ወላጆች ምቹ ምኅዳር ተፈጥሮ እንደነበር በአብነት መጥቀሳቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
#ethiopia #democracy #government #humanrights #ethiopiaprevails #ebc
2 months ago
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የአማራ ክልል ሕዝብ እና አመራሩ ወደ አዲስ የመንቃት ምዕራፍ የተሻገሩበት የልዩ ዘመን መክፈቻ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
*******************
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ የከፍተኛ አመራሮች የግምገማ መድረክ መካሄዱን እና በመድረኩ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም እና ስትራቴጂካዊ ውጤቶች በጥልቀት መገምገሙን ገልጸዋል።
ይህ ምርጫ የክልሉ ሕዝብ እና አመራር ከጠላት መጠነ ሰፊ ሴራዎች ከፍ ብለው በመራመድ፣ ለክልሉ ዘላቂ ልማት እና ሰላም በጠራ መስመር እና በማይናወጥ አንድነት በመቆም የማይሻር ገድል የፈጸሙበት ነው ብለዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ “ሕዝባችን በዚህ ምርጫ ያሳየው ወደር የለሽ የሰላም ቁርጠኝነት እና የዴሞክራሲ ብስለት፤ በክልሉ ላይ በባዕዳን እና በባንዳዎች የተጋረጡ የጥፋት ማነቆዎችን ሙሉ በሙሉ እንዲቀለበሱ አስችሏል” ሲሉ ገልጸዋል።
በቀጣይም የክልሉን እምቅ አቅም ለመጠቀም ሰላምን በዘላቂነት ማጽናት፣ መልካም አስተዳደርን ማስፈን እና የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች በቁርጠኝነት መመለስ ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ በግምገማው የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን አረጋግጠዋል።
#ethiopia #ebc #ethiopiaprevails
*******************
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ የከፍተኛ አመራሮች የግምገማ መድረክ መካሄዱን እና በመድረኩ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም እና ስትራቴጂካዊ ውጤቶች በጥልቀት መገምገሙን ገልጸዋል።
ይህ ምርጫ የክልሉ ሕዝብ እና አመራር ከጠላት መጠነ ሰፊ ሴራዎች ከፍ ብለው በመራመድ፣ ለክልሉ ዘላቂ ልማት እና ሰላም በጠራ መስመር እና በማይናወጥ አንድነት በመቆም የማይሻር ገድል የፈጸሙበት ነው ብለዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ “ሕዝባችን በዚህ ምርጫ ያሳየው ወደር የለሽ የሰላም ቁርጠኝነት እና የዴሞክራሲ ብስለት፤ በክልሉ ላይ በባዕዳን እና በባንዳዎች የተጋረጡ የጥፋት ማነቆዎችን ሙሉ በሙሉ እንዲቀለበሱ አስችሏል” ሲሉ ገልጸዋል።
በቀጣይም የክልሉን እምቅ አቅም ለመጠቀም ሰላምን በዘላቂነት ማጽናት፣ መልካም አስተዳደርን ማስፈን እና የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች በቁርጠኝነት መመለስ ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ በግምገማው የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን አረጋግጠዋል።
#ethiopia #ebc #ethiopiaprevails
2 months ago
ምርጫው የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ነው፦ የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
#ethiopia | የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ምርጫው ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ግልጽነት እና ፍትሐዊነት የተንጸባረቀበት፣ በመራጩ ሕዝብና በተፎካካሪ ፓርቲዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅቡልነት ያገኘ መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው እንዳመለከተው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ምርጫ መንግሥት በከተማዋ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሌላኛው ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ አልፏል።
ከእነዚህም መካከል እንደ ትልቅ ጅምር የሚወሰደው የዲጂታል የእጩዎች ምዝገባ ሒደት አላስፈላጊ መጉላላትን የቀነሰ እና የእጩዎችን መረጃ እና ደኅንነት ያረጋገጠ የአሰራ ግልፅነትን የፈጠረ መሆኑ በምርጫው ሂደት ከታዩ ዐበይት አዎንታዊ ሁነቶች መካከል እንደሆነ ተመላክቷል።
በምርጫው ዕለት መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ያለምንም ቀስቃሽ በነቂስ በመውጣት ድምፅ መስጠታቸውን የገለጸው ምክር ቤቱ፣ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና አረጋውያን ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ሂደቱን ይበልጥ እንዳደመቀው አብራርቷል።
ከምርጫ ጣቢያዎች የሚመጡ የአሠራር ችግሮችን በጋራ በመገምገም፣ ከምርጫ ቦርድ እና ከከተማው አመራሮች ጋር በቀጥታ በመነጋገር አፋጣኝ የእርምት እርምጃ መወሰዱ በፓርቲዎች እና በአስፈፃሚ አካላት መካከል መተማመንን ማጎልበቱ ተገልጿል።
በተጨማሪም የከተማዋ የጸጥታ አካላት ያለምንም ወገንተኝነት፣ ፍጹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ የምርጫ ጣቢያዎችን እና የመራጩን ሕዝብ ደኅንነት በመጠበቅ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።
በሂደቱም ምንም ዓይነት የጸጥታ መደፍረስም ሆነ የምርጫ ሕግ መጣስ ሳይኖር መጠናቀቁ የከተማዋን ነዋሪዎችና የጸጥታ አካላት ከፍተኛ የበስለት ደረጃ ያሳየ "የአዲስ አበባ ሞዴል" መሆኑ ተነግሯል።
የድምፅ መስጠት ሂደቱ በስኬት ተጠናቅቆ ወደ ቀጣዩ የድምፅ ቆጠራ እና ውጤት ማደራጀት ምዕራፍ መሸጋገሩን የጠቀሰው ምክር ቤቱ፤ የምርጫ ቦርድ ሕጋዊ አሠራርን መሠረት አድርጎ የከተማውን ውጤት በኦፊሴላዊ መልኩ እስኪገልጽ ድረስ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ደጋፊዎች ፍጹም በሆነ ትዕግሥት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiaprevails #peace #ምርጫ
#ethiopia | የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ምርጫው ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ግልጽነት እና ፍትሐዊነት የተንጸባረቀበት፣ በመራጩ ሕዝብና በተፎካካሪ ፓርቲዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅቡልነት ያገኘ መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው እንዳመለከተው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ምርጫ መንግሥት በከተማዋ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሌላኛው ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ አልፏል።
ከእነዚህም መካከል እንደ ትልቅ ጅምር የሚወሰደው የዲጂታል የእጩዎች ምዝገባ ሒደት አላስፈላጊ መጉላላትን የቀነሰ እና የእጩዎችን መረጃ እና ደኅንነት ያረጋገጠ የአሰራ ግልፅነትን የፈጠረ መሆኑ በምርጫው ሂደት ከታዩ ዐበይት አዎንታዊ ሁነቶች መካከል እንደሆነ ተመላክቷል።
በምርጫው ዕለት መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ያለምንም ቀስቃሽ በነቂስ በመውጣት ድምፅ መስጠታቸውን የገለጸው ምክር ቤቱ፣ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና አረጋውያን ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ሂደቱን ይበልጥ እንዳደመቀው አብራርቷል።
ከምርጫ ጣቢያዎች የሚመጡ የአሠራር ችግሮችን በጋራ በመገምገም፣ ከምርጫ ቦርድ እና ከከተማው አመራሮች ጋር በቀጥታ በመነጋገር አፋጣኝ የእርምት እርምጃ መወሰዱ በፓርቲዎች እና በአስፈፃሚ አካላት መካከል መተማመንን ማጎልበቱ ተገልጿል።
በተጨማሪም የከተማዋ የጸጥታ አካላት ያለምንም ወገንተኝነት፣ ፍጹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ የምርጫ ጣቢያዎችን እና የመራጩን ሕዝብ ደኅንነት በመጠበቅ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።
በሂደቱም ምንም ዓይነት የጸጥታ መደፍረስም ሆነ የምርጫ ሕግ መጣስ ሳይኖር መጠናቀቁ የከተማዋን ነዋሪዎችና የጸጥታ አካላት ከፍተኛ የበስለት ደረጃ ያሳየ "የአዲስ አበባ ሞዴል" መሆኑ ተነግሯል።
የድምፅ መስጠት ሂደቱ በስኬት ተጠናቅቆ ወደ ቀጣዩ የድምፅ ቆጠራ እና ውጤት ማደራጀት ምዕራፍ መሸጋገሩን የጠቀሰው ምክር ቤቱ፤ የምርጫ ቦርድ ሕጋዊ አሠራርን መሠረት አድርጎ የከተማውን ውጤት በኦፊሴላዊ መልኩ እስኪገልጽ ድረስ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ደጋፊዎች ፍጹም በሆነ ትዕግሥት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiaprevails #peace #ምርጫ
2 months ago
"ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅ እና ሊገመግም የሚችል ማን ነው?"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያውያንን ፅናት፣ ሀገር ወዳድነት እና ለሀገረ-መንግሥት ግንባታ ያለችውን ቁርጠኝነት የገለጹበት መልዕክት።
#ebc #ethiopia #pmabiyahmed #ethiopiaprevails
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያውያንን ፅናት፣ ሀገር ወዳድነት እና ለሀገረ-መንግሥት ግንባታ ያለችውን ቁርጠኝነት የገለጹበት መልዕክት።
#ebc #ethiopia #pmabiyahmed #ethiopiaprevails
Comments