18 days ago
ኢትዮጵያን በልባቸው ያነገቡት የቱሪዝም አምባሳደር፤ ከአዲስ አበባ እስከ አሜሪካ የምግብ ትራክ
#ethiopia | ታላላቅ ታሪኮች ብዙ ጊዜ የሚጀምሩት ባልታሰቡ አጋጣሚዎች ነው። የአቶ አበራ ዋሲሁን የሕይወት ጉዞም እንዲሁ ነበር።
በ12 ዓመታቸው በአዲስ አበባ ተክለሃይማኖት አካባቢ መንገድ የጠፉ ሁለት ጣሊያናውያን ቱሪስቶችን በመርዳት እና የኢትዮጵያን ታሪክ በማስተዋወቅ የመጀመሪያውን የአስጎብኚነት ጉዞ ጀመሩ።
በዚያን ቀን የተቀበሉት 20 ብር ሽልማት ከገንዘብ በላይ የሀገር ፍቅርና የቱሪዝም አገልግሎት መንፈስን በልባቸው አስርጎ አስቀመጠ።
ከዚያ ጀምሮ ለአራት አስርት ዓመታት በቱሪዝም ዘርፍ ያሳለፉት ጉዞ በብዙ ስኬቶች የተሞላ ነው። ከአስጎብኚነትና ከሹፌርነት ተነስተው የራሳቸውን "አበራ አስጎብኚ ድርጅት" በመመስረት የኢትዮጵያን ታሪክ፣ ባህልና ተፈጥሯዊ ውበት ለዓለም ማስተዋወቅ ችለዋል።
ለቢቢሲ ጋዜጠኞች፣ ለአውሮፓ ኅብረትና ለአፍሪካ ኅብረት ምርጫ ታዛቢዎች ያበረከቱት አገልግሎትም በሙያቸው ያላቸውን ብቃት ያሳያል።
በ2012 በአሜሪካ "Ethio USA Tours" የተሰኘውን ድርጅታቸውን በመመስረት የኢትዮጵያን ታሪክና የቱሪዝም ሀብት ለዓለም አቀፍ ተጓዦች ማስተዋወቅ ቀጠሉ። ኮቪድ-19 የቱሪዝም ዘርፉን ቢያዳክምም፣ የሀገር ማስተዋወቅ ተልዕኳቸው አልቆመም።
በአዲስ አቅጣጫ "MULU FEST LLC" የተሰኘ የምግብ ትራክ በመጀመር በዋሽንግተን ዲሲ፣ ቨርጂኒያና ሜሪላንድ የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግብ፣ ባህልና እንግዳ ተቀባይነት ለብዙዎች እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
ከአዲስ አበባ ጎዳናዎች የጀመረው ሕልማቸው ዛሬ በዓለም ሌላ ጫፍ የኢትዮጵያን ስም በክብር እያስጠራ ይገኛል። አቶ አበራ ዋሲሁን በሥራቸው የኢትዮጵያ ባህል፣ ቱሪዝምና ምግብ እውነተኛ አምባሳደሮች መሆን የቻሉ ተምሳሌት ናቸው።
#ethiopia #tourism #culture #ethiopiancuisine #ethiopiantourism #diaspora #getutemesgen #ኢትዮጵያ #ቱሪዝም #ባህል #አበራዋሲሁን #ጌጡተመስገን
#ethiopia | ታላላቅ ታሪኮች ብዙ ጊዜ የሚጀምሩት ባልታሰቡ አጋጣሚዎች ነው። የአቶ አበራ ዋሲሁን የሕይወት ጉዞም እንዲሁ ነበር።
በ12 ዓመታቸው በአዲስ አበባ ተክለሃይማኖት አካባቢ መንገድ የጠፉ ሁለት ጣሊያናውያን ቱሪስቶችን በመርዳት እና የኢትዮጵያን ታሪክ በማስተዋወቅ የመጀመሪያውን የአስጎብኚነት ጉዞ ጀመሩ።
በዚያን ቀን የተቀበሉት 20 ብር ሽልማት ከገንዘብ በላይ የሀገር ፍቅርና የቱሪዝም አገልግሎት መንፈስን በልባቸው አስርጎ አስቀመጠ።
ከዚያ ጀምሮ ለአራት አስርት ዓመታት በቱሪዝም ዘርፍ ያሳለፉት ጉዞ በብዙ ስኬቶች የተሞላ ነው። ከአስጎብኚነትና ከሹፌርነት ተነስተው የራሳቸውን "አበራ አስጎብኚ ድርጅት" በመመስረት የኢትዮጵያን ታሪክ፣ ባህልና ተፈጥሯዊ ውበት ለዓለም ማስተዋወቅ ችለዋል።
ለቢቢሲ ጋዜጠኞች፣ ለአውሮፓ ኅብረትና ለአፍሪካ ኅብረት ምርጫ ታዛቢዎች ያበረከቱት አገልግሎትም በሙያቸው ያላቸውን ብቃት ያሳያል።
በ2012 በአሜሪካ "Ethio USA Tours" የተሰኘውን ድርጅታቸውን በመመስረት የኢትዮጵያን ታሪክና የቱሪዝም ሀብት ለዓለም አቀፍ ተጓዦች ማስተዋወቅ ቀጠሉ። ኮቪድ-19 የቱሪዝም ዘርፉን ቢያዳክምም፣ የሀገር ማስተዋወቅ ተልዕኳቸው አልቆመም።
በአዲስ አቅጣጫ "MULU FEST LLC" የተሰኘ የምግብ ትራክ በመጀመር በዋሽንግተን ዲሲ፣ ቨርጂኒያና ሜሪላንድ የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግብ፣ ባህልና እንግዳ ተቀባይነት ለብዙዎች እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
ከአዲስ አበባ ጎዳናዎች የጀመረው ሕልማቸው ዛሬ በዓለም ሌላ ጫፍ የኢትዮጵያን ስም በክብር እያስጠራ ይገኛል። አቶ አበራ ዋሲሁን በሥራቸው የኢትዮጵያ ባህል፣ ቱሪዝምና ምግብ እውነተኛ አምባሳደሮች መሆን የቻሉ ተምሳሌት ናቸው።
#ethiopia #tourism #culture #ethiopiancuisine #ethiopiantourism #diaspora #getutemesgen #ኢትዮጵያ #ቱሪዝም #ባህል #አበራዋሲሁን #ጌጡተመስገን
1 month ago
ኢትዮጵያን ያላትን የቱሪዝም ጸጋ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማስተዋወቅ የጋዜጠኞች ድርሻ የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
#ethiopia | የኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን ማስተዋወቅ እና የጎብኚዎችን ቀልብ በመሳብ የቱሪዝም ዘርፉን ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ ሞተር ማድረግ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑ ተገለጸ።
ይህንን ግብ ከዳር ለማድረስም መገናኛ ብዙኃን በየአካባቢው የሚገኙ ጸጋዎችን ፈጠራ በታከለበትና ማራኪ በሆነ አቀራረብ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የማቅረብ ኃላፊነት እንዳለባቸው ተጠቁሟል።
በቱሪዝም ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አለማየሁ ጌታቸው እንደገለጹት፣ አገሪቱ ያሏትን እምቅ የቱሪዝም ሀብቶች በተሳለጠ መንገድ ለማስተዋወቅ የሚዲያው ሚና ወደር የለውም ብለዋል።
በቅርቡ የተመሰረተው የቱሪዝም ዘርፍ የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ፎረም ዋነኛ ዓላማም ይኸው ገጽታን የመገንባት፣ የማስተዋወቅ እና የሽያጭ ሥራን በተናበበ መልኩ ለመምራት ነው። ሚዲያው የሰዎችን ቀልብ በሚስብ አግባብ መረጃዎችን ሲያቀርብ፣ ሰዎች እንዲጓጉ፣ እንዲመኙ እና የጉዞ ዕቅድ አውጥተው በጀት እንዲመድቡ ከፍተኛ መነሳሳትን ይፈጥራል ብለዋል።
አቶ አለማየሁ እንደገለጹት፣ ማስተዋወቅ የቱሪዝም ስኬት ቁልፍ መሣሪያ ነው። ጎብኚዎች ወደ ስፍራዎቹ መጥተው ማኅበረሰቡ በጥሩ ሁኔታ ሲያስተናግዳቸውና የተደሰቱበትን የጉዞ ልምዳቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲያጋሩ የቱሪስቶች ፍሰት በሶስት እና አራት እጥፍ ይጨምራል ብለዋል።
በመላ አገሪቱ ከስምንት መቶ በላይ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎች ተለይተው እያንዳንዱ ወረዳ እና ዞን የየራሱን መዳረሻዎች እንዲያለማ አቅጣጫ ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል።
መገናኛ ብዙኃን እነዚህን መረጃዎች ከሚኒስቴሩ "ላንድ ኦፍ ኦሪጂን" (Land of Origins)፣ ከ"ማይስ" (MICE)፣ እንዲሁም ከክልል የቱሪዝም ፕላትፎርሞች በተለያዩ ቋንቋዎች በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ይሁንና ጋዜጠኞች ጥሬ መረጃዎችን ከማሰራጨት ባለፈ መዳረሻዎቹን በአካል በመጎብኘትና በማጣጣም ስሜትን የሚስቡና ሕያው የሆኑ ዘገባዎችን ለተመልካች ማድረስ እንደሚገባቸው አቶ አለማየሁ በማሳሰብ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen
#ethiopia #ethiopiantourism #landoforigins
#miceethiopia
#ethiopia | የኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን ማስተዋወቅ እና የጎብኚዎችን ቀልብ በመሳብ የቱሪዝም ዘርፉን ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ ሞተር ማድረግ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑ ተገለጸ።
ይህንን ግብ ከዳር ለማድረስም መገናኛ ብዙኃን በየአካባቢው የሚገኙ ጸጋዎችን ፈጠራ በታከለበትና ማራኪ በሆነ አቀራረብ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የማቅረብ ኃላፊነት እንዳለባቸው ተጠቁሟል።
በቱሪዝም ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አለማየሁ ጌታቸው እንደገለጹት፣ አገሪቱ ያሏትን እምቅ የቱሪዝም ሀብቶች በተሳለጠ መንገድ ለማስተዋወቅ የሚዲያው ሚና ወደር የለውም ብለዋል።
በቅርቡ የተመሰረተው የቱሪዝም ዘርፍ የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ፎረም ዋነኛ ዓላማም ይኸው ገጽታን የመገንባት፣ የማስተዋወቅ እና የሽያጭ ሥራን በተናበበ መልኩ ለመምራት ነው። ሚዲያው የሰዎችን ቀልብ በሚስብ አግባብ መረጃዎችን ሲያቀርብ፣ ሰዎች እንዲጓጉ፣ እንዲመኙ እና የጉዞ ዕቅድ አውጥተው በጀት እንዲመድቡ ከፍተኛ መነሳሳትን ይፈጥራል ብለዋል።
አቶ አለማየሁ እንደገለጹት፣ ማስተዋወቅ የቱሪዝም ስኬት ቁልፍ መሣሪያ ነው። ጎብኚዎች ወደ ስፍራዎቹ መጥተው ማኅበረሰቡ በጥሩ ሁኔታ ሲያስተናግዳቸውና የተደሰቱበትን የጉዞ ልምዳቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲያጋሩ የቱሪስቶች ፍሰት በሶስት እና አራት እጥፍ ይጨምራል ብለዋል።
በመላ አገሪቱ ከስምንት መቶ በላይ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎች ተለይተው እያንዳንዱ ወረዳ እና ዞን የየራሱን መዳረሻዎች እንዲያለማ አቅጣጫ ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል።
መገናኛ ብዙኃን እነዚህን መረጃዎች ከሚኒስቴሩ "ላንድ ኦፍ ኦሪጂን" (Land of Origins)፣ ከ"ማይስ" (MICE)፣ እንዲሁም ከክልል የቱሪዝም ፕላትፎርሞች በተለያዩ ቋንቋዎች በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ይሁንና ጋዜጠኞች ጥሬ መረጃዎችን ከማሰራጨት ባለፈ መዳረሻዎቹን በአካል በመጎብኘትና በማጣጣም ስሜትን የሚስቡና ሕያው የሆኑ ዘገባዎችን ለተመልካች ማድረስ እንደሚገባቸው አቶ አለማየሁ በማሳሰብ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen
#ethiopia #ethiopiantourism #landoforigins
#miceethiopia
2 months ago
በአዲስ አበባ ስታዲየም :
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።
በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።
በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።
ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።
የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።
በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።
በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።
ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።
የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ኢትዮጵያ እንዴት የዓለም ተጽዕኖ ፈጣሪዎችና የሀያላን ሀገራት ማዕከል ሆነች? #ethiopia #dylanpage #visitethiopia #ishowspeedethiopia #ethiopiantourism #landoforigins #addisababacorridor
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ከአይሾ ስፒድ እስከ ዲላን ፔጅ
***
ኢትዮጵያ እንዴት የዓለም ተጽዕኖ ፈጣሪዎችና የሀያላን ሀገራት ማዕከል ሆነች?
#ethiopia #dylanpage #addisababa #visitethiopia #gerd #ishowspeedethiopia #ethiopiantourism #landoforigins #addisababacorridor
3 months ago
ከአቧራ ወደ ዐሻራ፤ ከቅርስ ወደ ቁርስ
*************
በቅርብ ዓመታት ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍን ከተራ የኢኮኖሚ ምንጭነት ባለፈ ለሀገር ግንባታ፣ ለሰላም፣ ለብዝኃነትና ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት መገንቢያ ስትራቴጂካዊ መሣሪያ አድርጋ በመውሰድ ላይ ትገኛለች።
ሀገራችን በታሪክ፣ በባሕልና በተፈጥሮ ያላትን እምቅ ባለጠግነት ለመጠቀም ቱሪዝምን ዋነኛ የኢኮኖሚ ምሰሶ ያደረገች ሲሆን፣ ይህም መዋቅራዊ ለውጥ ለማምጣት፣ ገቢን ለማሳደግና ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር መሠረት ሆኗል።
መንግሥት የመንግሥትና የግል ዘርፍ ቅንጅትን ሚዛናዊ በሆነ መንገድ በመምራት፣ ቱሪዝም የጋራ ታሪክን የሚያሳይና ብሔራዊ ማንነትን የሚያጠናክር የጋራ መድረክ እንዲሆን እያደረገ ነው።
ይህን ዘርፍ ለማሳደግ ለ16 ዓመታት ሳይሻሻል የቆየው የቱሪዝም ፖሊሲ በአዲስ መልክ ተሻሽሎ በሚኒስቴር ደረጃ እንዲደራጅ መደረጉ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን አሳድጎታል።
በተጨማሪም የስብሰባ፣ የጉዞ፣ የኮንፍረንስና የኤግዚቢሽን (MICE) ስትራቴጂዎች ተቀርጸው ወደ ተግባር የገቡ ሲሆን፣ የአሠራር ሥርዓቱን ለማዘመን የኢ-ቪዛና የዲጂታል አሠራሮች ተዘርግተው የቱሪስት ፍሰቱን አቀላጥፈዋል።
እንደ “ገበታ ለሀገር”፣ “ገበታ ለሸገር” እና “ኮሪደር ልማት” ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች የተፈጥሮ ሀብትን ከልማት ጋር በማስተሳሰር ለሀገር ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
እነዚህ ተቋማዊ ጥረቶች እንደ እንጦጦ፣ ወንጪ፣ ሃላላ ኬላ እና ኮይሻ ያሉ መዳረሻዎችን ወደ ሥራ በማስገባት የቱሪስቶች ቁጥር ከ781 ሺህ ወደ 1.3 ሚሊዮን እንዲያድግ ማድረጉን የቱሪዝም ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
ይህም የውጭ ምንዛሪ ገቢን በከፍተኛ መጠን ከማሳደጉም በላይ በሆቴልና በአስጎብኚ ዘርፎች ለሺዎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል። ኢትዮጵያ በዓለም ቱሪዝም ድርጅት እንድትሸለም ከማድረጉም ባሻገር፣ በአንድ ዓመት ውስጥ ሦስት አዳዲስ ቅርሶችን በዩኔስኮ በማስመዝገብ የታሪክ ክብረ-ወሰን እንድታስመዘግብ አስችሏታል።
ኢትዮጵያን የአፍሪካ ዋናና በዓለም የተመረጠች መዳረሻ በማድረግ የቱሪስት ፍሰቱን እስከ 7.3 ሚሊዮን ለማድረስ ሰፊ ራዕይ ተቀምጧል።
ይህንን ለማሳካት አዳዲስ የኢኮ-ቱሪዝም መዳረሻዎችን ማስፋፋት፣ የታሪካዊ ቅርሶች ጥገናን ማዘመን፣ የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን ማበረታታትና የመሠረተ ልማት አውታሮችን ማሻሻል በትኩረት እየተከናወነ ነው።
በቀጣይም ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም አገልግሎቱን ማዘመንና በሚሊዮኖች የሚቆጠር ተጨማሪ የሥራ ዕድል መፍጠር የመንግሥት ዋነኛ ትኩረት ሲሆን፣ ይህም ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ዕድገትና ለዜጎች የኑሮ ደረጃ መሻሻል ጉልህ ሚና ይኖረዋል።
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopiantourism #landoforigins #visitethiopia #miceethiopia
*************
በቅርብ ዓመታት ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍን ከተራ የኢኮኖሚ ምንጭነት ባለፈ ለሀገር ግንባታ፣ ለሰላም፣ ለብዝኃነትና ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት መገንቢያ ስትራቴጂካዊ መሣሪያ አድርጋ በመውሰድ ላይ ትገኛለች።
ሀገራችን በታሪክ፣ በባሕልና በተፈጥሮ ያላትን እምቅ ባለጠግነት ለመጠቀም ቱሪዝምን ዋነኛ የኢኮኖሚ ምሰሶ ያደረገች ሲሆን፣ ይህም መዋቅራዊ ለውጥ ለማምጣት፣ ገቢን ለማሳደግና ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር መሠረት ሆኗል።
መንግሥት የመንግሥትና የግል ዘርፍ ቅንጅትን ሚዛናዊ በሆነ መንገድ በመምራት፣ ቱሪዝም የጋራ ታሪክን የሚያሳይና ብሔራዊ ማንነትን የሚያጠናክር የጋራ መድረክ እንዲሆን እያደረገ ነው።
ይህን ዘርፍ ለማሳደግ ለ16 ዓመታት ሳይሻሻል የቆየው የቱሪዝም ፖሊሲ በአዲስ መልክ ተሻሽሎ በሚኒስቴር ደረጃ እንዲደራጅ መደረጉ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን አሳድጎታል።
በተጨማሪም የስብሰባ፣ የጉዞ፣ የኮንፍረንስና የኤግዚቢሽን (MICE) ስትራቴጂዎች ተቀርጸው ወደ ተግባር የገቡ ሲሆን፣ የአሠራር ሥርዓቱን ለማዘመን የኢ-ቪዛና የዲጂታል አሠራሮች ተዘርግተው የቱሪስት ፍሰቱን አቀላጥፈዋል።
እንደ “ገበታ ለሀገር”፣ “ገበታ ለሸገር” እና “ኮሪደር ልማት” ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች የተፈጥሮ ሀብትን ከልማት ጋር በማስተሳሰር ለሀገር ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
እነዚህ ተቋማዊ ጥረቶች እንደ እንጦጦ፣ ወንጪ፣ ሃላላ ኬላ እና ኮይሻ ያሉ መዳረሻዎችን ወደ ሥራ በማስገባት የቱሪስቶች ቁጥር ከ781 ሺህ ወደ 1.3 ሚሊዮን እንዲያድግ ማድረጉን የቱሪዝም ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
ይህም የውጭ ምንዛሪ ገቢን በከፍተኛ መጠን ከማሳደጉም በላይ በሆቴልና በአስጎብኚ ዘርፎች ለሺዎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል። ኢትዮጵያ በዓለም ቱሪዝም ድርጅት እንድትሸለም ከማድረጉም ባሻገር፣ በአንድ ዓመት ውስጥ ሦስት አዳዲስ ቅርሶችን በዩኔስኮ በማስመዝገብ የታሪክ ክብረ-ወሰን እንድታስመዘግብ አስችሏታል።
ኢትዮጵያን የአፍሪካ ዋናና በዓለም የተመረጠች መዳረሻ በማድረግ የቱሪስት ፍሰቱን እስከ 7.3 ሚሊዮን ለማድረስ ሰፊ ራዕይ ተቀምጧል።
ይህንን ለማሳካት አዳዲስ የኢኮ-ቱሪዝም መዳረሻዎችን ማስፋፋት፣ የታሪካዊ ቅርሶች ጥገናን ማዘመን፣ የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን ማበረታታትና የመሠረተ ልማት አውታሮችን ማሻሻል በትኩረት እየተከናወነ ነው።
በቀጣይም ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም አገልግሎቱን ማዘመንና በሚሊዮኖች የሚቆጠር ተጨማሪ የሥራ ዕድል መፍጠር የመንግሥት ዋነኛ ትኩረት ሲሆን፣ ይህም ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ዕድገትና ለዜጎች የኑሮ ደረጃ መሻሻል ጉልህ ሚና ይኖረዋል።
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopiantourism #landoforigins #visitethiopia #miceethiopia
4 months ago
የኢትዮጵያ ገጽታ በታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አማካኝነት ለዓለም ሊተዋወቅ ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ባህላዊ ውበቶች፣ ታሪካዊ ቅርሶች እንዲሁም የዘመነ የአኗኗር ዘይቤን በዲጂታል አማራጮች ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ያለመ ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል።
"ኢንፍሉዌንሰር ቱር 2026" የተሰኘው ይህ መርሃ ግብር በአገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ ታዋቂ የሶሻል ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን በማሳተፍ የሀገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ ለማነቃቃት የታለመ ንቅናቄ ነው።
ይህ ታላቅ ጉዞ ታዋቂ ግለሰቦች በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በመዘዋወር ከማህበረሰቡ ጋር እንዲገናኙና ያዩትን ተጨባጭ እውነት በከፍተኛ ጥራት ለተከታዮቻቸው እንዲያጋሩ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
ፕሮጀክቱ በዋናነት የቱሪስት መዳረሻዎችን ከማስተዋወቅ ባለፈ፣ የወጣቶችን ተሳትፎ የሚያሳድጉ የዩኒቨርሲቲ ጉብኝቶችን፣ ማህበረሰብ ተኮር የበጎ አድራጎት ተግባራትን እና የስፖርት እንቅስቃሴዎችን ያካትታል።
በተጨማሪም በየክልሉ የሚገኙ አዳዲስ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ከታዋቂዎቹ ጋር ተቀናጅተው እንዲሰሩ በማድረግ የዘርፉን ዕድገት ለማፋጠን ታቅዷል።
መርሃ ግብሩን በበላይነት የሚመራው ኤን ዜድ ኮሙኒኬሽን ሲሆን፣ ድርጅቱ የኢንፍሉዌንሰሮችን አስተዳደር፣ የዘመቻ አፈጻጸምና አጋርነት ስራዎችን በኃላፊነት ያከናውናል ተብሏል።
በፕሮጀክቱ ላይ የሚሳተፉ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የኢትዮጵያን ማንነት ያለ ምንም ክፍያ በፈቃደኝነት ለማስተዋወቅ የተስማሙ ሲሆን፣ ይህ ተግባራቸው ለሀገራዊ ኩራትና ለዓለም አቀፍ እውቅና ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል።
ፕሮጀክቱ ከሚዲያ ተቋማት፣ ከንግድ ድርጅቶችና ከከተማ መስተዳድሮች ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አዘጋጁ ኤን ዜድ ኮሙኒኬሽንስ በሰጠው መግለጫ አስተዋውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #influencertour2026 #visitethiopia #digitalmarketing #ethiopiantourism #contentcreators #africarising #landoforigins #influencermarketing #azcommunication
#ethiopia | የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ባህላዊ ውበቶች፣ ታሪካዊ ቅርሶች እንዲሁም የዘመነ የአኗኗር ዘይቤን በዲጂታል አማራጮች ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ያለመ ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል።
"ኢንፍሉዌንሰር ቱር 2026" የተሰኘው ይህ መርሃ ግብር በአገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ ታዋቂ የሶሻል ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን በማሳተፍ የሀገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ ለማነቃቃት የታለመ ንቅናቄ ነው።
ይህ ታላቅ ጉዞ ታዋቂ ግለሰቦች በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በመዘዋወር ከማህበረሰቡ ጋር እንዲገናኙና ያዩትን ተጨባጭ እውነት በከፍተኛ ጥራት ለተከታዮቻቸው እንዲያጋሩ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
ፕሮጀክቱ በዋናነት የቱሪስት መዳረሻዎችን ከማስተዋወቅ ባለፈ፣ የወጣቶችን ተሳትፎ የሚያሳድጉ የዩኒቨርሲቲ ጉብኝቶችን፣ ማህበረሰብ ተኮር የበጎ አድራጎት ተግባራትን እና የስፖርት እንቅስቃሴዎችን ያካትታል።
በተጨማሪም በየክልሉ የሚገኙ አዳዲስ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ከታዋቂዎቹ ጋር ተቀናጅተው እንዲሰሩ በማድረግ የዘርፉን ዕድገት ለማፋጠን ታቅዷል።
መርሃ ግብሩን በበላይነት የሚመራው ኤን ዜድ ኮሙኒኬሽን ሲሆን፣ ድርጅቱ የኢንፍሉዌንሰሮችን አስተዳደር፣ የዘመቻ አፈጻጸምና አጋርነት ስራዎችን በኃላፊነት ያከናውናል ተብሏል።
በፕሮጀክቱ ላይ የሚሳተፉ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የኢትዮጵያን ማንነት ያለ ምንም ክፍያ በፈቃደኝነት ለማስተዋወቅ የተስማሙ ሲሆን፣ ይህ ተግባራቸው ለሀገራዊ ኩራትና ለዓለም አቀፍ እውቅና ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል።
ፕሮጀክቱ ከሚዲያ ተቋማት፣ ከንግድ ድርጅቶችና ከከተማ መስተዳድሮች ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አዘጋጁ ኤን ዜድ ኮሙኒኬሽንስ በሰጠው መግለጫ አስተዋውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #influencertour2026 #visitethiopia #digitalmarketing #ethiopiantourism #contentcreators #africarising #landoforigins #influencermarketing #azcommunication
Comments