1 day ago
የከተማ አስተዳደሩ በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ የደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች እንዲበረታቱ ፣ የግብር ጫና እንዳይደርስባቸውና ትርፋማነታቸውን በማጎልበት ወደ ቀጣይ ደረጃ እንዲሸጋገሩ በቁርጠኛነት እየሰራ መሆኑን ቢሮው አስታወቀ ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በደረጃ ግብር ከፋዮች አከፋፈል ፣በሚነሱ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች አፈታት ዙሪያ ለሚዲያ ተቋማት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል ።
ቢሮው ባለፉት 2 አመታት ሰፋፊ የሪፎርም ተግባራት ማከናወኑን በጋዜጣዊ መግለጫው የተገለፀ ሲሆን የሪፎርም ተግባራቱ መሰረታዊ ዓላማዎችም ፍትሐዊ የግብር አሰባሰብ ስርዐት መዘርጋት ፣ የመልካም አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን መቅረፍ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች ጋር በተያያዘም አብዛኞቹ ግብር ከፋዮች በተቋሙ በተዘረጋ የኦንላይን የክፍያ ስርዓት መወጣታቸውና የተቀሩትም እየከፈሉ ናቸው ተብሏል፡፡
በተጨማሪም በከተማዋ በተለያዩ ንግዶች ፣ በኪራይና በራይድ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ 456 ሺህ 433 የደረጃ ግብር ከፋዮች የሚገኙ መሆናቸው የተጠቆመ ሲሆን ከእነዚህ ግብር ከፋዮች በአጠቃላይ 9.2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱ ተመላክቷል፡፡
ይህ ዓመታዊ የደረጃ ‹‹ለ›. ግብር ከፋዮች ገቢ በመንግስትና በግል ድርጅት ውስጥ ከሚገኙ ተቀጣሪ ደሞዝተኞች ዓመታዊ ደሞዝ ገቢ ግብር ጋር ሲነፃፀር በጣም አነስተኛ እንደሆነ ተገልጿል
ይህም በዋነኛነት ዐላማው የከተማ አስተዳደሩ በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች እንዲበረታቱ፣ የግብር ጫና እንዳይደርስባቸውና ትርፋማነታቸውን በማጎልበት ወደ ቀጣይ ደረጃ እንዲሸጋገሩ ካለው አቋምና ቁርጠኛነት የመነጨ መሆኑም ተብራርቷል፡፡
በመሆኑም እስከ ሀምሌ 25 ድረስ ዓመታዊ ግብራችሁን እንድትከፍሉ መልዕክት በስልካችሁ የተላከላችሁ ግብር ከፋዮች በሙሉ እስከ ሀምሌ 30/2018 ዓ.ም ድረስ የግብር ግዴታችሁን በኦንላይን በመክፈል ከቅጣትና ወለድ እራሳችሁን እንዲጠብቁ ጥሪ ተላልፏል፡፡
ይሁንና በተለያዩ ምክንያቶች ቴክስት ያልደረሳችሁ ግብር ከፋዮች እንዲሁም ከሀምሌ 25 በኃላ ቴክሰት( መልዕክት ) የተላከላችሁ ግብር ከፋዮች ወደ ቅጣት የማይገቡ በመሆኑ እስከ ነሀሴ 20/2018 ዓ.ም ዓመታዊ ግብራችውን መክፈል እንደሚችሉ በመግለፅ ቴክስት ያልተላከላቸው ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው በትዕግስት እንዲጠባበቁ ቢሮው ይገልፃል ፡፡
በተያያዘም ቴክስት (መልዕክት ) ከተላከለት በኃላ ‹‹ግብር በዛብኝ›› የሚል ቅሬታ ላለው ማንኛውም ግብር ከፋይ የቅሬታ አፈታት ስርዓት ተዘርግቶ ወደ ተግባር የተገባ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን ቅሬታ ያለው ግብር ከፋይ በወረዳ ደረጃ ቅሬታ አቅርቦ መረጃው ለክፍለ ከተማ ከተላከ በኃላ በክፍለ ከተማ በተደራጀ የቀን ገቢ ገማች አማካኝነት ድጋሚ የቀን ገቢ ግምት በማካሄድ ቅሬታዎች የሚፈቱበት አሰራር መዘርጋቱ ተገልፆል፡፡
ከቅድመ ታክስ ክፍያ ጋር በተያያዘ ለደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች በቴክስት የተላከ ዓመታዊ የግብር መጠንም ግብር ከፋዮች በቅድመ ታክስ የከፈሉትን የገንዘብ መጠን ተቀናሽ በማድረግ የተላከ እንደሆነም በጋዜጣዊ መግለጫው ተመላክቷል፡፡ በ2019 በጀት አመት እንደ ከተማ 502.27 ቢሊየን ፣ በገቢዎች ቢሮ 380 ቢሊየን ብር ገቢን በፍትሐዊነት ለመሠብሰብ መታቀዱም ተገልፆል፡፡
አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በደረጃ ግብር ከፋዮች አከፋፈል ፣በሚነሱ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች አፈታት ዙሪያ ለሚዲያ ተቋማት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል ።
ቢሮው ባለፉት 2 አመታት ሰፋፊ የሪፎርም ተግባራት ማከናወኑን በጋዜጣዊ መግለጫው የተገለፀ ሲሆን የሪፎርም ተግባራቱ መሰረታዊ ዓላማዎችም ፍትሐዊ የግብር አሰባሰብ ስርዐት መዘርጋት ፣ የመልካም አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን መቅረፍ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች ጋር በተያያዘም አብዛኞቹ ግብር ከፋዮች በተቋሙ በተዘረጋ የኦንላይን የክፍያ ስርዓት መወጣታቸውና የተቀሩትም እየከፈሉ ናቸው ተብሏል፡፡
በተጨማሪም በከተማዋ በተለያዩ ንግዶች ፣ በኪራይና በራይድ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ 456 ሺህ 433 የደረጃ ግብር ከፋዮች የሚገኙ መሆናቸው የተጠቆመ ሲሆን ከእነዚህ ግብር ከፋዮች በአጠቃላይ 9.2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱ ተመላክቷል፡፡
ይህ ዓመታዊ የደረጃ ‹‹ለ›. ግብር ከፋዮች ገቢ በመንግስትና በግል ድርጅት ውስጥ ከሚገኙ ተቀጣሪ ደሞዝተኞች ዓመታዊ ደሞዝ ገቢ ግብር ጋር ሲነፃፀር በጣም አነስተኛ እንደሆነ ተገልጿል
ይህም በዋነኛነት ዐላማው የከተማ አስተዳደሩ በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች እንዲበረታቱ፣ የግብር ጫና እንዳይደርስባቸውና ትርፋማነታቸውን በማጎልበት ወደ ቀጣይ ደረጃ እንዲሸጋገሩ ካለው አቋምና ቁርጠኛነት የመነጨ መሆኑም ተብራርቷል፡፡
በመሆኑም እስከ ሀምሌ 25 ድረስ ዓመታዊ ግብራችሁን እንድትከፍሉ መልዕክት በስልካችሁ የተላከላችሁ ግብር ከፋዮች በሙሉ እስከ ሀምሌ 30/2018 ዓ.ም ድረስ የግብር ግዴታችሁን በኦንላይን በመክፈል ከቅጣትና ወለድ እራሳችሁን እንዲጠብቁ ጥሪ ተላልፏል፡፡
ይሁንና በተለያዩ ምክንያቶች ቴክስት ያልደረሳችሁ ግብር ከፋዮች እንዲሁም ከሀምሌ 25 በኃላ ቴክሰት( መልዕክት ) የተላከላችሁ ግብር ከፋዮች ወደ ቅጣት የማይገቡ በመሆኑ እስከ ነሀሴ 20/2018 ዓ.ም ዓመታዊ ግብራችውን መክፈል እንደሚችሉ በመግለፅ ቴክስት ያልተላከላቸው ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው በትዕግስት እንዲጠባበቁ ቢሮው ይገልፃል ፡፡
በተያያዘም ቴክስት (መልዕክት ) ከተላከለት በኃላ ‹‹ግብር በዛብኝ›› የሚል ቅሬታ ላለው ማንኛውም ግብር ከፋይ የቅሬታ አፈታት ስርዓት ተዘርግቶ ወደ ተግባር የተገባ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን ቅሬታ ያለው ግብር ከፋይ በወረዳ ደረጃ ቅሬታ አቅርቦ መረጃው ለክፍለ ከተማ ከተላከ በኃላ በክፍለ ከተማ በተደራጀ የቀን ገቢ ገማች አማካኝነት ድጋሚ የቀን ገቢ ግምት በማካሄድ ቅሬታዎች የሚፈቱበት አሰራር መዘርጋቱ ተገልፆል፡፡
ከቅድመ ታክስ ክፍያ ጋር በተያያዘ ለደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች በቴክስት የተላከ ዓመታዊ የግብር መጠንም ግብር ከፋዮች በቅድመ ታክስ የከፈሉትን የገንዘብ መጠን ተቀናሽ በማድረግ የተላከ እንደሆነም በጋዜጣዊ መግለጫው ተመላክቷል፡፡ በ2019 በጀት አመት እንደ ከተማ 502.27 ቢሊየን ፣ በገቢዎች ቢሮ 380 ቢሊየን ብር ገቢን በፍትሐዊነት ለመሠብሰብ መታቀዱም ተገልፆል፡፡
አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
1 day ago
እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወርሐዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏
ገብርኤልና አባቱ ዘካርያስ ትንቢት የተናገሩለት፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ እግዚአብሔርን ያገለገለ፤ በፍጹም ልቡ ዓለምን የናቀ፤ ከተድላዋና ከደስታዋም የተለየ፤ አምላክን ለማጥመቅ የታደለ ሐዋርያ፣ መምህር፣ ሰማዕት፣ ባሕታዊ፣ ነቢይ፣ ጻድቅ ነው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቅዱስ፡፡ ዮሐንስ ማለት እግዚአብሔር ጸጋ ነው ማለት ነው፡፡ በሉቃስ 1÷14 እንደተጻፈው ቅዱስ ወንጌልም መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን ተድላና ደስታ ይለዋል፡፡ ወላጆቹ በእርሱ መወለድ ተደስተዋልና፡፡ በዚህ የወንጌል ክፍል ካህኑ ቅዱስ ዘካርያስና ሚስቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ሁሉ በመፈጸም ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ፡፡ ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ ይሰጣቸው ዘንድም እግዚአብሔርን ዘወትር ይማጸኑት ነበር፡፡ ካህኑ ዘካርያስ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ዕጣን በማሳረግ ላይ ሳለ የእግዚአብሔር መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ጸሎቱ እንደ ተሰማ ነገረው፡፡
ሚስቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ እንደምትወልድ፣ ስሙንም ዮሐንስ እንደሚለው፤ በመወለዱም ብዙዎች እንደሚደሰቱ፤ ልጁም በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ እንደሚኾን፤ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ እንደማይጠጣ፤ እንደዚሁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ እንደሚሞላበት ነገረው፡፡ ካህኑ ዘካርያስም መልአኩን “እኔ ሽማግሌ ነኝ፤ ሚስቴም አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ?” አለው፡፡ መልአኩም “እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፤ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፡፡ እነሆም በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ ይህ ነገር እስከሚኾን ቀን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ፤ መናገርም አትችልም” አለው፡፡ ከውጪ ቆመው ጸሎት ሲያደርጉ የነበሩት ሕዝብም ዘካርያስን ከቤተ መቅደስ እስኪወጣ ይጠብቁት ነበር፤ በመዘግየቱም ይደነቁ ነበር፡፡
ከቤተ መቅደስ በወጣም ጊዜ ሊያናግራቸው ባለመቻሉ ይጠቅሳቸው ነበር፡፡ በሁኔታውም በቤተ መቅደስ ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፡፡ እርሱም ድዳ ሆኖ ኖረ፡፡ የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሔደ፤ ከሁለት ቀን በኋላም አረጋዊቷ ቅድስት ኤልሳቤጥ ፀነሰች፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም በመካንነቷ ከሰዎች የሚደርስባት ሽሙጥ ተወግዷላታልና “እግዚአብሔር በዚህ ወራት ከሰው ስድቤን ያርቅ ዘንድ እንዲህ አደረገልኝ” ስትል ለአምስት ወራት ተሸሸገች፡፡ ጌታችን ሊወለድ ስድስት ወራት ሲቀረው፣ ሰኔ 30 ቀን ንዑድ፣ ክቡር የሆነው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ተወለደ፡፡ ዘመዶቹ ስሙን በአባቱ መጠርያ ዘካርያስ ሊሉት ቢወዱም እናቱ ግን “ዮሐንስ ይባል” አለች፡፡ የመልአኩን የብሥራት ቃል ባለመቀበሉ አንደበቱ ተይዞ የነበረው ካህኑ ዘካርያም ስሙ “ዮሐንስ” ይባል ብሎ ሲጽፍ አፉ ተከፈተ፤ አንደበቱም ተፈታ፡፡
በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶም “… አንተ ሕፃን ሆይ! የልዑል ነቢይ ትባላለህ፤ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሔዳለህና… ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል፤ እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል፤” በማለት የቅዱስ ዮሐንስን ነቢይነትና አጥማቂነት፣ እንደዚሁም የክርስቶስን የማዳን ትምህርት አብሣሪነት የሚመለከት ትንቢት አስቀድሞ ተናገሯል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ሰኔ 30 ቀን የተወለደበት፤ መስከረም 1 ቀን ቃል ኪዳን የተቀበለበት፤ መስከረም 2 ቀን በሰማዕትነት ያረፈበት፤ ጥር 11 ቀን ጌታችንን ያጠመቀበት፤ ሰኔ 2 ቀን ደግሞ ዐፅሙ የፈለሰበት በዓል በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ ይከበራል፡፡ የገዳማዊ ሕይወት ምሣሌ የሆነውን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ስናስብ ገዳማውያንን መደገፍ፣ በዓታቸውንም ማጽናት ይገባል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ገብርኤልና አባቱ ዘካርያስ ትንቢት የተናገሩለት፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ እግዚአብሔርን ያገለገለ፤ በፍጹም ልቡ ዓለምን የናቀ፤ ከተድላዋና ከደስታዋም የተለየ፤ አምላክን ለማጥመቅ የታደለ ሐዋርያ፣ መምህር፣ ሰማዕት፣ ባሕታዊ፣ ነቢይ፣ ጻድቅ ነው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቅዱስ፡፡ ዮሐንስ ማለት እግዚአብሔር ጸጋ ነው ማለት ነው፡፡ በሉቃስ 1÷14 እንደተጻፈው ቅዱስ ወንጌልም መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን ተድላና ደስታ ይለዋል፡፡ ወላጆቹ በእርሱ መወለድ ተደስተዋልና፡፡ በዚህ የወንጌል ክፍል ካህኑ ቅዱስ ዘካርያስና ሚስቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ሁሉ በመፈጸም ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ፡፡ ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ ይሰጣቸው ዘንድም እግዚአብሔርን ዘወትር ይማጸኑት ነበር፡፡ ካህኑ ዘካርያስ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ዕጣን በማሳረግ ላይ ሳለ የእግዚአብሔር መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ጸሎቱ እንደ ተሰማ ነገረው፡፡
ሚስቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ እንደምትወልድ፣ ስሙንም ዮሐንስ እንደሚለው፤ በመወለዱም ብዙዎች እንደሚደሰቱ፤ ልጁም በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ እንደሚኾን፤ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ እንደማይጠጣ፤ እንደዚሁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ እንደሚሞላበት ነገረው፡፡ ካህኑ ዘካርያስም መልአኩን “እኔ ሽማግሌ ነኝ፤ ሚስቴም አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ?” አለው፡፡ መልአኩም “እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፤ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፡፡ እነሆም በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ ይህ ነገር እስከሚኾን ቀን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ፤ መናገርም አትችልም” አለው፡፡ ከውጪ ቆመው ጸሎት ሲያደርጉ የነበሩት ሕዝብም ዘካርያስን ከቤተ መቅደስ እስኪወጣ ይጠብቁት ነበር፤ በመዘግየቱም ይደነቁ ነበር፡፡
ከቤተ መቅደስ በወጣም ጊዜ ሊያናግራቸው ባለመቻሉ ይጠቅሳቸው ነበር፡፡ በሁኔታውም በቤተ መቅደስ ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፡፡ እርሱም ድዳ ሆኖ ኖረ፡፡ የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሔደ፤ ከሁለት ቀን በኋላም አረጋዊቷ ቅድስት ኤልሳቤጥ ፀነሰች፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም በመካንነቷ ከሰዎች የሚደርስባት ሽሙጥ ተወግዷላታልና “እግዚአብሔር በዚህ ወራት ከሰው ስድቤን ያርቅ ዘንድ እንዲህ አደረገልኝ” ስትል ለአምስት ወራት ተሸሸገች፡፡ ጌታችን ሊወለድ ስድስት ወራት ሲቀረው፣ ሰኔ 30 ቀን ንዑድ፣ ክቡር የሆነው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ተወለደ፡፡ ዘመዶቹ ስሙን በአባቱ መጠርያ ዘካርያስ ሊሉት ቢወዱም እናቱ ግን “ዮሐንስ ይባል” አለች፡፡ የመልአኩን የብሥራት ቃል ባለመቀበሉ አንደበቱ ተይዞ የነበረው ካህኑ ዘካርያም ስሙ “ዮሐንስ” ይባል ብሎ ሲጽፍ አፉ ተከፈተ፤ አንደበቱም ተፈታ፡፡
በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶም “… አንተ ሕፃን ሆይ! የልዑል ነቢይ ትባላለህ፤ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሔዳለህና… ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል፤ እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል፤” በማለት የቅዱስ ዮሐንስን ነቢይነትና አጥማቂነት፣ እንደዚሁም የክርስቶስን የማዳን ትምህርት አብሣሪነት የሚመለከት ትንቢት አስቀድሞ ተናገሯል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ሰኔ 30 ቀን የተወለደበት፤ መስከረም 1 ቀን ቃል ኪዳን የተቀበለበት፤ መስከረም 2 ቀን በሰማዕትነት ያረፈበት፤ ጥር 11 ቀን ጌታችንን ያጠመቀበት፤ ሰኔ 2 ቀን ደግሞ ዐፅሙ የፈለሰበት በዓል በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ ይከበራል፡፡ የገዳማዊ ሕይወት ምሣሌ የሆነውን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ስናስብ ገዳማውያንን መደገፍ፣ በዓታቸውንም ማጽናት ይገባል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሚኒሶታ ጤና መምሪያ በግዛቲቱ በሚገኙ የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች ውስጥ ከሚቀርበው ሃላፒኖ የሚባለው የቃሪያ ዓይነት (የሜክሲኮ ቃሪያ) ጋር የተያያዘ የ'ሳልሞኔላ ጃቪያና' ወረርሽኝን እየመረመረ መሆኑን አስታወቀ። መምሪያው እስካሁን 110 የተረጋገጡ የሳልሞኔላ ታማሚዎች መመዝገባቸውን ገልጿል።
የጤና ባለስልጣናት ህመሙ ከተከሰተባቸው ሰዎች መካከል 84ቱን ያነጋገሩ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 75 በመቶ የሚሆኑት ከሰኔ 14 እስከ ሀምሌ 14 ባለው ጊዜ ውስጥ 'ቺፖትሌ' በተባለው ታዋቂ ምግብ ቤት የተመገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎች የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች መመገባቸውን ተናግረዋል። ወረርሽኙን ተከትሎ ቺፖትሌ በሚኒሶታ ከሚገኙ በርካታ ቅርንጫፎቹ ሃላፔኖ ቃሪያዎችን ማንሳቱን አስታውቋል።
የቺፖትሌ ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ፣ "ሊከሰት ስለሚችለው ወረርሽኝ እንደሰማን ወዲያውኑ የክትትል ስርዓታችንን በመጠቀም ሃላፔኖ ቃሪያው የተሰራጨባቸውን ምግብ ቤቶች ለይተናል፤ ለጥንቃቄ ሲባልም የተጠረጠሩትን ምርቶች ከምግብ ቤቶቻችን በማስወገድ ከሌሎች አምራቾች በተገኙ ቃሪያዎች ተክተናል" ብለዋል። በሚኒሶታ ጤና መምሪያ የምግብ ወለድ በሽታዎች ክፍል ከፍተኛ ኤፒዲሚዮሎጂስት ካርሎታ ሜዱስ በበኩላቸው፣ ቺፖትሌ ከምርመራው ጋር በተያያዘ መረጃዎችን ከመስጠት ጀምሮ የተጠረጠሩትን ቃሪያዎች ለማስወገድ የወሰደውን ፈጣን እርምጃ በማንሳት የተቋሙን ሙሉ ትብብር አድንቀዋል።
የጤና መምሪያው ወረርሽኙ አሁንም እንደቀጠለ ለማወቅ ጊዜው ገና መሆኑን ቢገልጽም፣ ቺፖትሌ በወሰደው ፈጣን እርምጃ ምክንያት በድርጅቱ ላይ ስጋት እንደሌለው አስታውቋል። ሆኖም የተበከለው ቃሪያ በሌሎች ምግብ ቤቶች አሁንም እየቀረበ ከሆነ ወረርሽኙ ሊቀጥል እንደሚችል እና በቀጣይ ቀናት ተጨማሪ ታማሚዎች ሊመዘገቡ እንደሚችሉ ስጋቱን አጋርቷል።
ወረርሽኙን በፍጥነት ለመቆጣጠር የታማሚዎች መረጃ እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ካርሎታ ሜዱስ፣ የጤና ባለሙያዎች ምርመራቸውን የሚያካሂዱት ጥቆማ በደረሳቸው ታማሚዎች ላይ በመደወል በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ለሚደረጉ የስልክ ጥሪዎች ምላሽ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የጤና ባለስልጣናት ህመሙ ከተከሰተባቸው ሰዎች መካከል 84ቱን ያነጋገሩ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 75 በመቶ የሚሆኑት ከሰኔ 14 እስከ ሀምሌ 14 ባለው ጊዜ ውስጥ 'ቺፖትሌ' በተባለው ታዋቂ ምግብ ቤት የተመገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎች የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች መመገባቸውን ተናግረዋል። ወረርሽኙን ተከትሎ ቺፖትሌ በሚኒሶታ ከሚገኙ በርካታ ቅርንጫፎቹ ሃላፔኖ ቃሪያዎችን ማንሳቱን አስታውቋል።
የቺፖትሌ ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ፣ "ሊከሰት ስለሚችለው ወረርሽኝ እንደሰማን ወዲያውኑ የክትትል ስርዓታችንን በመጠቀም ሃላፔኖ ቃሪያው የተሰራጨባቸውን ምግብ ቤቶች ለይተናል፤ ለጥንቃቄ ሲባልም የተጠረጠሩትን ምርቶች ከምግብ ቤቶቻችን በማስወገድ ከሌሎች አምራቾች በተገኙ ቃሪያዎች ተክተናል" ብለዋል። በሚኒሶታ ጤና መምሪያ የምግብ ወለድ በሽታዎች ክፍል ከፍተኛ ኤፒዲሚዮሎጂስት ካርሎታ ሜዱስ በበኩላቸው፣ ቺፖትሌ ከምርመራው ጋር በተያያዘ መረጃዎችን ከመስጠት ጀምሮ የተጠረጠሩትን ቃሪያዎች ለማስወገድ የወሰደውን ፈጣን እርምጃ በማንሳት የተቋሙን ሙሉ ትብብር አድንቀዋል።
የጤና መምሪያው ወረርሽኙ አሁንም እንደቀጠለ ለማወቅ ጊዜው ገና መሆኑን ቢገልጽም፣ ቺፖትሌ በወሰደው ፈጣን እርምጃ ምክንያት በድርጅቱ ላይ ስጋት እንደሌለው አስታውቋል። ሆኖም የተበከለው ቃሪያ በሌሎች ምግብ ቤቶች አሁንም እየቀረበ ከሆነ ወረርሽኙ ሊቀጥል እንደሚችል እና በቀጣይ ቀናት ተጨማሪ ታማሚዎች ሊመዘገቡ እንደሚችሉ ስጋቱን አጋርቷል።
ወረርሽኙን በፍጥነት ለመቆጣጠር የታማሚዎች መረጃ እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ካርሎታ ሜዱስ፣ የጤና ባለሙያዎች ምርመራቸውን የሚያካሂዱት ጥቆማ በደረሳቸው ታማሚዎች ላይ በመደወል በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ለሚደረጉ የስልክ ጥሪዎች ምላሽ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
Sponsored by
Surafel
3 days ago
“ከምኩራቡ በስተጀርባ”፡ የቤተ-እስራኤላውያንን ስውር ታሪክ የሚያወሳው አዲስ መጽሐፍ ተመረቀ
የቤተ-እስራኤላውያንን ህይወት እና ስውር ታሪክ የሚያወሳው “ከምኩራቡ በስተጀርባ” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በስቴይ ኢዚ ፕላዛ በድምቀት ተመርቋል።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች” እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል። በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል። በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው። መጽሐፉ እንደ «ፈ ላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስ ድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል። እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል። ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
የቤተ-እስራኤላውያንን ህይወት እና ስውር ታሪክ የሚያወሳው “ከምኩራቡ በስተጀርባ” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በስቴይ ኢዚ ፕላዛ በድምቀት ተመርቋል።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች” እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል። በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል። በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው። መጽሐፉ እንደ «ፈ ላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስ ድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል። እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል። ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
3 days ago
ከምኩራቡ በስተጀርባ
#ethiopia | የቤተ እስራኤላዊያንን ስውር ታሪክ የሚያወሳው መጽሐፍ ተመረቀ።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች”እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል።
በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል።
በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው።
መጽሐፉ እንደ «ፈላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል።
እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል።
ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews
#ethiopia | የቤተ እስራኤላዊያንን ስውር ታሪክ የሚያወሳው መጽሐፍ ተመረቀ።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች”እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል።
በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል።
በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው።
መጽሐፉ እንደ «ፈላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል።
እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል።
ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) አዲሱ የሱፐርማን ፊልም በጉጉት ሲጠበቅ የነበረ ሲሆን፣ የጄምስ ገን የዲሲ ኮሚክስ ዩኒቨርስ የመጀመሪያው ትልቅ የሲኒማ ፊልም በመሆኑ የተለየ ትኩረት ስቦለታል። በዚህ ፊልም ላይ ከተለመዱት የሱፐርማን ገጸ-ባህሪያት በተጨማሪ ሚስተር ቴሪፊክ የተባለው ገጸ-ባህሪ ተካቷል። ይህ ገጸ-ባህሪ ከፍተኛ የቴክኖሎጂ አቅም ያለው፣ ምጡቅ መሃንዲስ እና ሳይንቲስት፣ እንዲሁም በሰው ለሰው ውጊያ የተካነ ነው። ሚስተር ቴሪፊክን ወክሎ የሚጫወተው ኤዲ ጋቴጊ፣ ለረጅም ጊዜ በፊልም እና ቴሌቪዥን ኢንዱስትሪ ውስጥ የቆየ ቢሆንም፣ የፊቱ ገጽታ እንጂ ስሙ በብዙዎች ዘንድ በደንብ አይታወቅም።
የትውልደ ኬንያዊው አሜሪካዊ ተዋናይ የፊልም ህይወት በ2006 በ'ክራንክ' ፊልም ላይ በታክሲ ሹፌርነት የጀመረ ሲሆን፣ በመቀጠልም በ'ሀውስ'፣ 'ሲኤስአይ፡ ማያሚ' እና የመሳሰሉት የቴሌቪዥን ተከታታይ ፊልሞች ላይ ተሳትፏል። 'ሱፐርማን' ለጋቴጊ የመጀመሪያው የሱፐርሂሮ ፊልም አይደለም። ከዚህ ቀደም በ2011 በወጣው 'ኤክስ-ሜን፡ ፈርስት ክላስ' ፊልም ላይ 'ዳርዊን' የተባለውን ማናቸውንም አደጋዎች ተቋቁሞ በህይወት መቆየት የሚችል የ'ማርቨል' ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከታዋቂ ተዋንያን ጋር ተጫውቷል።
ጋቴጊ ከ'ኤክስ-ሜን' በፊት በታዋቂው የ'ትዋይላይት' ፊልም ላይ ሎረንት የተባለውን ቫምፓየር ሆኖ በመተወን ይታወቃል። ምንም እንኳን ገጸ-ባህሪው በፊልሙ ላይ ቢገደልም፣ ቫምፓየር ሆኖ የመተወን የረጅም ጊዜ ህልም እንደነበረው ተዋናዩ ይናገራል። ከዚህ በተጨማሪ በታዋቂው የ'ብላክሊስት' ተከታታይ ፊልም ላይ፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የጦር ወንጀል የፈጸመውን እና የሲአይኤ ሰላይ የነበረውን ማቲያስ ሰለሞን የተባለ አደገኛ ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከ20 በላይ ክፍሎች ላይ ተሳትፏል።
ተዋናዩ በ2016 በታየው 'ስታርትአፕ' ላይም ሮናልድ ዴሲ በተባለ ዋና ገጸ-ባህሪነት የተጫወተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በአፕል ቲቪ+ (Apple TV+) 'ፎር ኦል ማንካይንድ'በተሰኘው የሳይንስ ልብወለድ ተከታታይ ፊልም ላይ ዴቭ አዬሳ የተባለውን ታዋቂ መሃንዲስ፣ የኩባንያ መስራች እና ነጋዴ ወክሎ በመተወን ላይ ይገኛል። አሁን ደግሞ በ'ሱፐርማን' ፊልም ላይ በሚጫወተው የሚስተር ቴሪፊክ ሚና በድጋሚ የብዙዎችን ትኩረት ወደ ራሱ እየሳበ ይገኛል።
የትውልደ ኬንያዊው አሜሪካዊ ተዋናይ የፊልም ህይወት በ2006 በ'ክራንክ' ፊልም ላይ በታክሲ ሹፌርነት የጀመረ ሲሆን፣ በመቀጠልም በ'ሀውስ'፣ 'ሲኤስአይ፡ ማያሚ' እና የመሳሰሉት የቴሌቪዥን ተከታታይ ፊልሞች ላይ ተሳትፏል። 'ሱፐርማን' ለጋቴጊ የመጀመሪያው የሱፐርሂሮ ፊልም አይደለም። ከዚህ ቀደም በ2011 በወጣው 'ኤክስ-ሜን፡ ፈርስት ክላስ' ፊልም ላይ 'ዳርዊን' የተባለውን ማናቸውንም አደጋዎች ተቋቁሞ በህይወት መቆየት የሚችል የ'ማርቨል' ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከታዋቂ ተዋንያን ጋር ተጫውቷል።
ጋቴጊ ከ'ኤክስ-ሜን' በፊት በታዋቂው የ'ትዋይላይት' ፊልም ላይ ሎረንት የተባለውን ቫምፓየር ሆኖ በመተወን ይታወቃል። ምንም እንኳን ገጸ-ባህሪው በፊልሙ ላይ ቢገደልም፣ ቫምፓየር ሆኖ የመተወን የረጅም ጊዜ ህልም እንደነበረው ተዋናዩ ይናገራል። ከዚህ በተጨማሪ በታዋቂው የ'ብላክሊስት' ተከታታይ ፊልም ላይ፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የጦር ወንጀል የፈጸመውን እና የሲአይኤ ሰላይ የነበረውን ማቲያስ ሰለሞን የተባለ አደገኛ ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከ20 በላይ ክፍሎች ላይ ተሳትፏል።
ተዋናዩ በ2016 በታየው 'ስታርትአፕ' ላይም ሮናልድ ዴሲ በተባለ ዋና ገጸ-ባህሪነት የተጫወተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በአፕል ቲቪ+ (Apple TV+) 'ፎር ኦል ማንካይንድ'በተሰኘው የሳይንስ ልብወለድ ተከታታይ ፊልም ላይ ዴቭ አዬሳ የተባለውን ታዋቂ መሃንዲስ፣ የኩባንያ መስራች እና ነጋዴ ወክሎ በመተወን ላይ ይገኛል። አሁን ደግሞ በ'ሱፐርማን' ፊልም ላይ በሚጫወተው የሚስተር ቴሪፊክ ሚና በድጋሚ የብዙዎችን ትኩረት ወደ ራሱ እየሳበ ይገኛል።
5 days ago
ኢትዮጵያ ሆይ ! - ስደተኛው ልጅሽ ከ27 ዓመታት በኋላ መጥቷል! - ደስ ይበልሽ!"
· አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ፦ የሰዎች ህመም የሚሰማቸው፣ ተስፋን በተግባር የሚተረጉሙት ስራ ፈጣሪ
“Life’s most persistent and urgent question is, 'What are you doing for others?'”
(የህይወት ዘወተር እና አጣዳፊው ጥያቄ፦ ‘ለሌሎች ሰዎች ምን እያደረግክ ነው?’ የሚለው ነው።)
— ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር
በማህበረሰብ ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶችን አይቶ ከመቆጨት ይልቅ የመፍትሔ አካል ለመሆን መነሳት የትልልቅ ሰዎች መለያ ባህሪይ ነው። በትውልደ ኢትዮጵያዊው ስራ ፈጣሪ አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ዘንድም የሚታየው ይህ ህያው እውነት ነው፤ ጥበብን፣ የበጎ አድራጎት መንፈስን እና ዘመናዊ የህክምና አገልግሎትን በማስተሳሰር በሀገራችን ልዩ የለውጥ አሻራ በማስቀመጥ ላይ ይገኛሉ።
የተድላ አምቡላንስ መወለድ፦
የህይወት አድን አገልግሎት ራዕይ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በሀገራችን በህክምና ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትልቅ ክፍተት በጥናት በመረዳት ነው "ተድላ አምቡላንስን" ወደ ስራ ያስገቡት። በተለይም አካል ጉዳተኞች፣ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት (ኦቲዝም) ያለባቸው፣ የዳያሊሲስ ህመምተኞች እና አረጋውያን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ የሚያጋጥማቸውን የእንቅስቃሴ እና የትራንስፖርት እንግልት በመመልከት፣ ደረጃውን የጠበቀና ዘመናዊ የድንገተኛ እና ድንገተኛ ያልሆነ የህክምና መጓጓዣ አገልግሎት እንዲመሰረት አድርገዋል።
ድርጅቱ ከንግድ ስራ በላይ የማህበረሰብ አለኝታነትን መርሁ በማድረግ፦
· ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ያቀረበ፣
· በገንዘብም ሆነ በአገልግሎት ደረጃ አቅም የሌላቸውን ለመደገፍ የተጋ፣
· ለሁሉ አቀፍ ተደራሽነትና ለዜጎች ክብር የቆመ ተቋም ሆኖ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።
“The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others.”
(ራስህን ለማግኘት የሚቻለው የተሻለው መንገድ በሌሎች አገልግሎት ውስጥ ራስህን ስትሰጥ ነው።)
— ማሃትማ ጋንዲ
“ማንም የላት”፦
ጥበብ ለሰብአዊነት እና ለማህበራዊ ንቅናቄ
አቶ ሳሚ ከስራ ፈጣሪነታቸው ባሻገር፣ ጥበብ ለማህበራዊ ለውጥ ያላትን ትልቅ ሀይል በመረዳት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ “ማንም የላት” የተሰኘውን ታሪካዊ የኅብረት ዜማ ፕሮዲዩስ አድርገዋል።
ይህ ስራ በግጥም ናትናኤል ግርማቸው፣ በዜማ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ በቅንብር ታምሩ አማረ (ቶሚ) እንዲሁም በዳይሬክቲንግ ነፃዓለም አብዲ የተቃኘ ሲሆን፤ ድምፃውያን ማስተዋል እያዩ፣ ሄዋን ገብረወልድ፣ ሀና ግርማ እና አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) ድምፃቸውን ሰጥተውበታል። ከ50 በላይ የሙያ አጋሮች የተሳተፉበት ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ ህብረተሰቡን ስሜታዊ ጉዳት ውስጥ ሳይከት በደማቅ ቅንብር የችግሩን አሳሳቢነትና የለውጥ አስፈላጊነት ያሳያል።
አካል ጉዳተኝነት የችግር ምንጭ ሳይሆን፣ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እና የትራንስፖርት እጥረት ዋናው ክፍተት መሆኑን ማሳወቅ ነው። “ማንም የላት” የሚለውን ስሜት “እኛ አለንላት!”በሚል አዎንታዊ ምላሽ ለመተካት ያለመ ማህበራዊ ንቅናቄ ነው።
አቶ ሳሚ ካህሳይ እና ድርጅታቸው ተድላ አምቡላንስ ቃላቸውን በተግባር በማስመስከር፤ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ በተደረገ ስነ-ስርዓት፦የሙዚቃ ቪዲዮውን ገቢ፦ በሰይፉ ኦን ኢቢኤስ (Seifu on EBS) የዩቲዩብ ቻናል ተለቆ የሚሰበሰበው ሙሉ ገቢ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማዕከል እንዲሆን አስረክበው ነበር።
በርካታ ዊልቸሮች፣ ዘይት፣ ላርጎ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለመቄዶንያ መስራች ለዶ/ር ቢንያም በለጠ በአካል አስረክበዋል።
ተድላ አምቡላንስ ለማንኛውም ሰዓት ለመቄዶንያ ማዕከል ነፃ የአምቡላንስ አገልግሎት ለመስጠት በይፋ ቃል ገብተዋል።
የአቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ህልም በዋና ከተማው አዲስ አበባ ብቻ የተገደበ አይደለም። በክልሎች፣ በገጠራማ አካባቢዎች እና ክፍለ ሀገራት የሚኖሩ፣ አማራጭ ያጡ ዜጎች ዘንድ ይሄው ዘመናዊና የተከበረ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲደርስ ከመንግስት እና ከተለያዩ አካላት ጋር በትስስር ለመስራት አቅደዋል።
“No one has ever become poor by giving.”
(መስጠት ማንም ሰው ደሃ አያደርግም።)
— አን ፍራንክ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ በስራ ፈጠራቸው ሀገራዊ ክፍተትን የደፈኑ፣ በጥበብ ስራቸው የማህበረሰብ ህሊናን ያነቁ፣ በበጎ አድራጎታቸው ደግሞ የብዙዎችን እምባ ያበሱ የዘመናችን አርአያ ናቸው።
ተድላ አምቡላንስ “ሕይወትን ለማስቀጠል እየመጣን ነው!” በሚለው መሪ ቃሉ፣ የብዙዎችን ህይወት የመታደግ እና ተስፋ የመንዛት ታላቅ ሀገራዊ አገልግሎቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።
መደምደሚያ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ከ 27 ዓመታት ሰድት በኋላ አገር ቤት መጥተዋል። የእናት ሀገር ኢትዮጵያ ጥሪ ተቀብለው "እናቴ፤ ኢትዮጵያ ሆይ ! - ስደተኛው ልጅሽ ከ27 ዓመታት በኋላ መጥቷል! - ደስ ይበልሽ!"
የሀገር ጥሪን የመለሰ የዲያስፖራ ተሳትፎ፦ ህልምን በሀገር ላይ መተርጎም እንደነሳሚ ነው።
“Ask not what your country can do for you — ask what you can do for your country.”*
(ሀገሬ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን፣ እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ ብለህ ጠይቅ።)
— ጆን ኤፍ. ኬኔዲ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በምዕራቡ ዓለም (በአሜሪካ) ያካበቱትን የሙያ ልምድ፣ እውቀትና ሀብት ይዘው ወደ ሀገራቸው በመመለስ በህክምናና በትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩት በምክንያት ነው። መንግስትና የሀገር ጥሪ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያቀረቡትን ጥሪ መሰረት በማድረግ፣ በውጭ ሀገር ያዩትን ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥና ህልማቸውን በሀገራቸው ምድር ላይ ተግባራዊ አድርገዋል።
ይህ እርምጃቸው ክፍተቶችን በመሙላት ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተ ሲሆን፤ ሌሎች በውጭ ሀገር የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንም በየተሰማሩበት የሙያ ዘርፍ መጥተው ሀገራቸውንና ህዝባቸውን እንዲያገለግሉ ትልቅ ማነቃቂያና መንገድ ጠራጊ አርአያ የሚሆን ነው።
እናንት ያገሬ ልጆች
ግልጽነት ለዘላለም ይኑር!
መሥራት ጀግንነት ነው፤ ማድነቅ ደግሞ ጀግንነት ነው!
ለሥራቸው፤ ለሰበአዊነታቸው እጅ እንነሳለን!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
"ሕይወትን ማዳን፤ የመጀመሪያ ቅድሚያችን!"
– ተድላ አንቡላንስ
📞 ለአስቸኳይ ጥሪዎች 24 ሰዓት፣ 7 ቀናት ዝግጁ
☎️ +251 985 585 888
📞 8558
የማኅበራዊ ሚዲያ ሊንኮች ናቸው - ይከተሉን፦
Facebook: fb.com/Tedlaambulance
Instagram: instagram.com/tedlaambulance
Telegram: t.me/tedlaambulanceservice
TikTok: tiktok.com/tedlaambulance
· አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ፦ የሰዎች ህመም የሚሰማቸው፣ ተስፋን በተግባር የሚተረጉሙት ስራ ፈጣሪ
“Life’s most persistent and urgent question is, 'What are you doing for others?'”
(የህይወት ዘወተር እና አጣዳፊው ጥያቄ፦ ‘ለሌሎች ሰዎች ምን እያደረግክ ነው?’ የሚለው ነው።)
— ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር
በማህበረሰብ ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶችን አይቶ ከመቆጨት ይልቅ የመፍትሔ አካል ለመሆን መነሳት የትልልቅ ሰዎች መለያ ባህሪይ ነው። በትውልደ ኢትዮጵያዊው ስራ ፈጣሪ አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ዘንድም የሚታየው ይህ ህያው እውነት ነው፤ ጥበብን፣ የበጎ አድራጎት መንፈስን እና ዘመናዊ የህክምና አገልግሎትን በማስተሳሰር በሀገራችን ልዩ የለውጥ አሻራ በማስቀመጥ ላይ ይገኛሉ።
የተድላ አምቡላንስ መወለድ፦
የህይወት አድን አገልግሎት ራዕይ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በሀገራችን በህክምና ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትልቅ ክፍተት በጥናት በመረዳት ነው "ተድላ አምቡላንስን" ወደ ስራ ያስገቡት። በተለይም አካል ጉዳተኞች፣ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት (ኦቲዝም) ያለባቸው፣ የዳያሊሲስ ህመምተኞች እና አረጋውያን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ የሚያጋጥማቸውን የእንቅስቃሴ እና የትራንስፖርት እንግልት በመመልከት፣ ደረጃውን የጠበቀና ዘመናዊ የድንገተኛ እና ድንገተኛ ያልሆነ የህክምና መጓጓዣ አገልግሎት እንዲመሰረት አድርገዋል።
ድርጅቱ ከንግድ ስራ በላይ የማህበረሰብ አለኝታነትን መርሁ በማድረግ፦
· ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ያቀረበ፣
· በገንዘብም ሆነ በአገልግሎት ደረጃ አቅም የሌላቸውን ለመደገፍ የተጋ፣
· ለሁሉ አቀፍ ተደራሽነትና ለዜጎች ክብር የቆመ ተቋም ሆኖ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።
“The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others.”
(ራስህን ለማግኘት የሚቻለው የተሻለው መንገድ በሌሎች አገልግሎት ውስጥ ራስህን ስትሰጥ ነው።)
— ማሃትማ ጋንዲ
“ማንም የላት”፦
ጥበብ ለሰብአዊነት እና ለማህበራዊ ንቅናቄ
አቶ ሳሚ ከስራ ፈጣሪነታቸው ባሻገር፣ ጥበብ ለማህበራዊ ለውጥ ያላትን ትልቅ ሀይል በመረዳት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ “ማንም የላት” የተሰኘውን ታሪካዊ የኅብረት ዜማ ፕሮዲዩስ አድርገዋል።
ይህ ስራ በግጥም ናትናኤል ግርማቸው፣ በዜማ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ በቅንብር ታምሩ አማረ (ቶሚ) እንዲሁም በዳይሬክቲንግ ነፃዓለም አብዲ የተቃኘ ሲሆን፤ ድምፃውያን ማስተዋል እያዩ፣ ሄዋን ገብረወልድ፣ ሀና ግርማ እና አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) ድምፃቸውን ሰጥተውበታል። ከ50 በላይ የሙያ አጋሮች የተሳተፉበት ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ ህብረተሰቡን ስሜታዊ ጉዳት ውስጥ ሳይከት በደማቅ ቅንብር የችግሩን አሳሳቢነትና የለውጥ አስፈላጊነት ያሳያል።
አካል ጉዳተኝነት የችግር ምንጭ ሳይሆን፣ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እና የትራንስፖርት እጥረት ዋናው ክፍተት መሆኑን ማሳወቅ ነው። “ማንም የላት” የሚለውን ስሜት “እኛ አለንላት!”በሚል አዎንታዊ ምላሽ ለመተካት ያለመ ማህበራዊ ንቅናቄ ነው።
አቶ ሳሚ ካህሳይ እና ድርጅታቸው ተድላ አምቡላንስ ቃላቸውን በተግባር በማስመስከር፤ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ በተደረገ ስነ-ስርዓት፦የሙዚቃ ቪዲዮውን ገቢ፦ በሰይፉ ኦን ኢቢኤስ (Seifu on EBS) የዩቲዩብ ቻናል ተለቆ የሚሰበሰበው ሙሉ ገቢ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማዕከል እንዲሆን አስረክበው ነበር።
በርካታ ዊልቸሮች፣ ዘይት፣ ላርጎ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለመቄዶንያ መስራች ለዶ/ር ቢንያም በለጠ በአካል አስረክበዋል።
ተድላ አምቡላንስ ለማንኛውም ሰዓት ለመቄዶንያ ማዕከል ነፃ የአምቡላንስ አገልግሎት ለመስጠት በይፋ ቃል ገብተዋል።
የአቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ህልም በዋና ከተማው አዲስ አበባ ብቻ የተገደበ አይደለም። በክልሎች፣ በገጠራማ አካባቢዎች እና ክፍለ ሀገራት የሚኖሩ፣ አማራጭ ያጡ ዜጎች ዘንድ ይሄው ዘመናዊና የተከበረ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲደርስ ከመንግስት እና ከተለያዩ አካላት ጋር በትስስር ለመስራት አቅደዋል።
“No one has ever become poor by giving.”
(መስጠት ማንም ሰው ደሃ አያደርግም።)
— አን ፍራንክ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ በስራ ፈጠራቸው ሀገራዊ ክፍተትን የደፈኑ፣ በጥበብ ስራቸው የማህበረሰብ ህሊናን ያነቁ፣ በበጎ አድራጎታቸው ደግሞ የብዙዎችን እምባ ያበሱ የዘመናችን አርአያ ናቸው።
ተድላ አምቡላንስ “ሕይወትን ለማስቀጠል እየመጣን ነው!” በሚለው መሪ ቃሉ፣ የብዙዎችን ህይወት የመታደግ እና ተስፋ የመንዛት ታላቅ ሀገራዊ አገልግሎቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።
መደምደሚያ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ከ 27 ዓመታት ሰድት በኋላ አገር ቤት መጥተዋል። የእናት ሀገር ኢትዮጵያ ጥሪ ተቀብለው "እናቴ፤ ኢትዮጵያ ሆይ ! - ስደተኛው ልጅሽ ከ27 ዓመታት በኋላ መጥቷል! - ደስ ይበልሽ!"
የሀገር ጥሪን የመለሰ የዲያስፖራ ተሳትፎ፦ ህልምን በሀገር ላይ መተርጎም እንደነሳሚ ነው።
“Ask not what your country can do for you — ask what you can do for your country.”*
(ሀገሬ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን፣ እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ ብለህ ጠይቅ።)
— ጆን ኤፍ. ኬኔዲ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በምዕራቡ ዓለም (በአሜሪካ) ያካበቱትን የሙያ ልምድ፣ እውቀትና ሀብት ይዘው ወደ ሀገራቸው በመመለስ በህክምናና በትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩት በምክንያት ነው። መንግስትና የሀገር ጥሪ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያቀረቡትን ጥሪ መሰረት በማድረግ፣ በውጭ ሀገር ያዩትን ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥና ህልማቸውን በሀገራቸው ምድር ላይ ተግባራዊ አድርገዋል።
ይህ እርምጃቸው ክፍተቶችን በመሙላት ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተ ሲሆን፤ ሌሎች በውጭ ሀገር የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንም በየተሰማሩበት የሙያ ዘርፍ መጥተው ሀገራቸውንና ህዝባቸውን እንዲያገለግሉ ትልቅ ማነቃቂያና መንገድ ጠራጊ አርአያ የሚሆን ነው።
እናንት ያገሬ ልጆች
ግልጽነት ለዘላለም ይኑር!
መሥራት ጀግንነት ነው፤ ማድነቅ ደግሞ ጀግንነት ነው!
ለሥራቸው፤ ለሰበአዊነታቸው እጅ እንነሳለን!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
"ሕይወትን ማዳን፤ የመጀመሪያ ቅድሚያችን!"
– ተድላ አንቡላንስ
📞 ለአስቸኳይ ጥሪዎች 24 ሰዓት፣ 7 ቀናት ዝግጁ
☎️ +251 985 585 888
📞 8558
የማኅበራዊ ሚዲያ ሊንኮች ናቸው - ይከተሉን፦
Facebook: fb.com/Tedlaambulance
Instagram: instagram.com/tedlaambulance
Telegram: t.me/tedlaambulanceservice
TikTok: tiktok.com/tedlaambulance
8 days ago
ዘመን ወደኋላ አይቆጥርም፤ ትውልድም አይሸነፍም!
*****************
ሐሳብ ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ጥቅም ላይ ይውላል፣ ያረጃልም። ይህ የተፈጥሮ ዑደት ነው። በእርግጥ ዘመናትን የሚሻገሩ፣ የማያረጁ እና ሁልጊዜም ብሩህ ሆነው የሚኖሩ ጥልቅ ሐሳቦች አሉ። በተቃራኒው ደግሞ አንዳንዶቹ ሐሳቦች ገና ከጅምሩ ሲወለዱም የጨነገፉ ሆነው ይወለዳሉ።
ከዓለም ፍጥረት አንስቶ ጊዜ እና ዘመን ወደፊት ይገሰግሳል እንጂ፣ ለአፍታም ቢሆን ቆሞ አያውቅም፤ ፈጽሞም ወደኋላ ሊቆጥር አይችልም። ማንም ሰው ቢመኝ እና ቢጓጓ ወደነበረበት የልጅነት ዘመኑ መመለስ እንደማይችለው ሁሉ፣ ከዘመን ጋር መጣላትም ሆነ ታሪክን ወደኋላ መመለስ አይቻልም። በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ ማጠራቀም አይቻልም፤ አዲሱ ወይን ያረጀውን አቁማዳ ቀዶት ይፈሳልና። ያለፉ ትውልዶች እና ያረጁ ሐሳቦች ለጊዜው አጃቢ አግኝተው ጭብጨባ ቢቸራቸውም፣ የዘመኑን እውነት የታጠቀው አዲሱ ትውልድ እና አዲስ ሐሳብ ግን ውሎ አድሮ ማሸነፋቸው የማይቀር ተፈጥሯዊ ሀቅ ነው።
ህገወጡ የህወሓት ቡድን ግን፣ ከዚህ የተፈጥሮ እና የዘመን ህግ በተቃራኒ የሚቆም፣ እውነታውን የካደ ስብስብ ነው። ከግማሽ ፍለ ዘመን ጀምሮ የያዘውን እና ገና ሲወለድ የጨነገፈውን የጥፋት እሳቤ፣ ዛሬም በዚህ አዲስ የዕውቀት ዘመን አዲሱን ትውልድ ሊያሞኝበት እና ሊያታልልበት ይሞክራል። ከተፈጠረበት ጊዜ አንስቶ ይዞ ባመጣው ሐሳብ ላይ ምንም ዓይነት የሐሳብ ለውጥ፣ ማሻሻያም ሆነ የእድገት እርምጃ ማድረግ የማይችል ነው።
አንድ ጊዜ የገለበጠውን የሶሻሊስት ማኒፌስቶ ከትውልድ ወደ ትውልድ እያቀባበለ፣ ያንኑ ያረጀ የጥፋት ዜማ ከዘመን ዘመን እየደገመ የሚኖር የቅራኔ ስብስብ ነው። በየትኛውም ዘመን ቢሆን ከጠላት እና ወዳጅ የፈጠራ ትርክት ውጭ መቆም አይችልም። ሁልጊዜም ስጋትን፣ ግጭትን እና ደም መፋሰስን እንደ ዕድሜ ማራዘሚያ እና የኅልውና መቀጠያ አድርጎ የሚጠቀም፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ አንዲትም ስንዝር አዲስ ሐሳብ ያላሳደገ አፍራሽ ኃይል ነው።
ይህ ህገወጥ ቡድን የትግራይን ሕዝብ በጠላት እንደተከበበ አድርጎ በመሳል፣ "ተከበናል፤ ሁሉም ይጠላናል" በሚል የሀሰት ትርክት ጨምድዶ ለመግዛት የሚጥር፣ በልዩነትና ግጭት መሀል ትርፍ ለማስላት የሚሞክር አቅመ-ቢስ ነው። ዛሬ ላይ ከ50 ዓመታት በኋላ፣ ዓለም በሥልጣኔ፣ በቴክኖሎጂ እና በእውቀት ማማ ላይ በደረሰችበት በዚህ ዘመን፣ ይህ ቡድን ያንን ያረጀ እና የሻገተ ዜማውን ይዞ የዛሬውን ንቁ ትውልድ እገዛለሁ ብሎ ማሰብ፣ እጅግ ቀልበ-ቢስ እና በከፍተኛ የቅዠት ዓለም ውስጥ የሚኖር መሆኑን ያረጋግጣል።
የዚህ የጥፋት ዜማ ቁልፍ ማሳያዎች እጅግ ግልጽ እና ደጋግመው የሚታዩ ናቸው። ዘወትር ጠላትን መፍጠር እና በማያባራ የጦርነት አዙሪት ውስጥ ራሱን እንደ ብቸኛ "አዳኝ" እና "መልአክ" አድርጎ ለማቅረብ ይሞክራል። የትግራይን ሕዝብ መከታ አድርጎ በየመግለጫዎቹ ሌላውን ፋሺስት፣ አምባገነን እና ጨፍጫፊ እያለ ቢከስም፤ ከዚህ ሁሉ የውሸት ጭንብል ጀርባ ያለው እውነተኛ ማንነቱ ግን፣ በሕዝብ ስጋትና ሰቆቃ ውስጥ የራሱን ጠባብ የቡድን ጥቅም ማስጠበቅ፣ ግላዊ ፍላጎቱን ማርካት እና ሀብት መዝረፍ ብቻ ነው።
ለ50 ዓመታት ያልተቀየረው ሌላው የክፋት መገለጫው፣ ራሱንና የትግራይን ሕዝብ አጣብቆ ለማቅረብ የሚያደርገው እኩይ ጥረት ነው። "እኔን የነካ የትግራይን ሕዝብ ነካ" በሚል ማታለል፣ ለዘረፈው ሀብት፣ ለፈጸመው ወንጀል እና ለገባበት ታሪካዊ ዕዳ ሕዝቡ ተካፋይ እንዲሆን ያላክካል። ይህ ድርጊቱ፣ ቡድኑ ለትግራይ ሕዝብ ያለውን ጥልቅ ጥላቻ፣ ንቀት እና እኩይነት በተግባር የሚያሳይ ነው። ይህ ስብስብ ቋሚ መርህ የሌለው፣ አንደበቱ እና ተግባሩ የማይገናኝ ሙሉጭልጭ ነው። በአንድ በኩል ድሃውን የትግራይ ወጣት "ተዋጋልኝ፣ ተሰለፍልኝ" እያለ በአቋራጭ ወደ እሳት ይማግዳል፤ በሌላ በኩል ደግሞ የሕዝቡን አንጡራ ሀብት በኮንትሮባንድ እያሸሸ ካዝናውን ያደልባል።
አሁን ግን ጊዜው ተቀይሯል። የትግራይ ሕዝብም ሆነ ወጣቱ የቡድኑን እኩይነት ሙሉ በሙሉ ተረድቶ፣ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጋር በመተባበር ይህንን ዘመን ያለፈበትን የጥፋት ተሽከርካሪ ከጫንቃው ላይ እያወረደው ይገኛል። አዲሱ ትውልድ በሀሰተኛ ትርክት የሚሸነፍበት ዘመን አብቅቷል። የትግራይ ወጣት የቡድኑ ማታለያ ለዘለዓለም እንዲያበቃ ቆርጦ ተነስቷል፤ ምክንያቱም የትውልድ ዘመን ወደኋላ አይቆጥርም፤ ትውልድም ፈጽሞ አይሸነፍም!
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #newgenerations #tigray
*****************
ሐሳብ ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ጥቅም ላይ ይውላል፣ ያረጃልም። ይህ የተፈጥሮ ዑደት ነው። በእርግጥ ዘመናትን የሚሻገሩ፣ የማያረጁ እና ሁልጊዜም ብሩህ ሆነው የሚኖሩ ጥልቅ ሐሳቦች አሉ። በተቃራኒው ደግሞ አንዳንዶቹ ሐሳቦች ገና ከጅምሩ ሲወለዱም የጨነገፉ ሆነው ይወለዳሉ።
ከዓለም ፍጥረት አንስቶ ጊዜ እና ዘመን ወደፊት ይገሰግሳል እንጂ፣ ለአፍታም ቢሆን ቆሞ አያውቅም፤ ፈጽሞም ወደኋላ ሊቆጥር አይችልም። ማንም ሰው ቢመኝ እና ቢጓጓ ወደነበረበት የልጅነት ዘመኑ መመለስ እንደማይችለው ሁሉ፣ ከዘመን ጋር መጣላትም ሆነ ታሪክን ወደኋላ መመለስ አይቻልም። በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ ማጠራቀም አይቻልም፤ አዲሱ ወይን ያረጀውን አቁማዳ ቀዶት ይፈሳልና። ያለፉ ትውልዶች እና ያረጁ ሐሳቦች ለጊዜው አጃቢ አግኝተው ጭብጨባ ቢቸራቸውም፣ የዘመኑን እውነት የታጠቀው አዲሱ ትውልድ እና አዲስ ሐሳብ ግን ውሎ አድሮ ማሸነፋቸው የማይቀር ተፈጥሯዊ ሀቅ ነው።
ህገወጡ የህወሓት ቡድን ግን፣ ከዚህ የተፈጥሮ እና የዘመን ህግ በተቃራኒ የሚቆም፣ እውነታውን የካደ ስብስብ ነው። ከግማሽ ፍለ ዘመን ጀምሮ የያዘውን እና ገና ሲወለድ የጨነገፈውን የጥፋት እሳቤ፣ ዛሬም በዚህ አዲስ የዕውቀት ዘመን አዲሱን ትውልድ ሊያሞኝበት እና ሊያታልልበት ይሞክራል። ከተፈጠረበት ጊዜ አንስቶ ይዞ ባመጣው ሐሳብ ላይ ምንም ዓይነት የሐሳብ ለውጥ፣ ማሻሻያም ሆነ የእድገት እርምጃ ማድረግ የማይችል ነው።
አንድ ጊዜ የገለበጠውን የሶሻሊስት ማኒፌስቶ ከትውልድ ወደ ትውልድ እያቀባበለ፣ ያንኑ ያረጀ የጥፋት ዜማ ከዘመን ዘመን እየደገመ የሚኖር የቅራኔ ስብስብ ነው። በየትኛውም ዘመን ቢሆን ከጠላት እና ወዳጅ የፈጠራ ትርክት ውጭ መቆም አይችልም። ሁልጊዜም ስጋትን፣ ግጭትን እና ደም መፋሰስን እንደ ዕድሜ ማራዘሚያ እና የኅልውና መቀጠያ አድርጎ የሚጠቀም፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ አንዲትም ስንዝር አዲስ ሐሳብ ያላሳደገ አፍራሽ ኃይል ነው።
ይህ ህገወጥ ቡድን የትግራይን ሕዝብ በጠላት እንደተከበበ አድርጎ በመሳል፣ "ተከበናል፤ ሁሉም ይጠላናል" በሚል የሀሰት ትርክት ጨምድዶ ለመግዛት የሚጥር፣ በልዩነትና ግጭት መሀል ትርፍ ለማስላት የሚሞክር አቅመ-ቢስ ነው። ዛሬ ላይ ከ50 ዓመታት በኋላ፣ ዓለም በሥልጣኔ፣ በቴክኖሎጂ እና በእውቀት ማማ ላይ በደረሰችበት በዚህ ዘመን፣ ይህ ቡድን ያንን ያረጀ እና የሻገተ ዜማውን ይዞ የዛሬውን ንቁ ትውልድ እገዛለሁ ብሎ ማሰብ፣ እጅግ ቀልበ-ቢስ እና በከፍተኛ የቅዠት ዓለም ውስጥ የሚኖር መሆኑን ያረጋግጣል።
የዚህ የጥፋት ዜማ ቁልፍ ማሳያዎች እጅግ ግልጽ እና ደጋግመው የሚታዩ ናቸው። ዘወትር ጠላትን መፍጠር እና በማያባራ የጦርነት አዙሪት ውስጥ ራሱን እንደ ብቸኛ "አዳኝ" እና "መልአክ" አድርጎ ለማቅረብ ይሞክራል። የትግራይን ሕዝብ መከታ አድርጎ በየመግለጫዎቹ ሌላውን ፋሺስት፣ አምባገነን እና ጨፍጫፊ እያለ ቢከስም፤ ከዚህ ሁሉ የውሸት ጭንብል ጀርባ ያለው እውነተኛ ማንነቱ ግን፣ በሕዝብ ስጋትና ሰቆቃ ውስጥ የራሱን ጠባብ የቡድን ጥቅም ማስጠበቅ፣ ግላዊ ፍላጎቱን ማርካት እና ሀብት መዝረፍ ብቻ ነው።
ለ50 ዓመታት ያልተቀየረው ሌላው የክፋት መገለጫው፣ ራሱንና የትግራይን ሕዝብ አጣብቆ ለማቅረብ የሚያደርገው እኩይ ጥረት ነው። "እኔን የነካ የትግራይን ሕዝብ ነካ" በሚል ማታለል፣ ለዘረፈው ሀብት፣ ለፈጸመው ወንጀል እና ለገባበት ታሪካዊ ዕዳ ሕዝቡ ተካፋይ እንዲሆን ያላክካል። ይህ ድርጊቱ፣ ቡድኑ ለትግራይ ሕዝብ ያለውን ጥልቅ ጥላቻ፣ ንቀት እና እኩይነት በተግባር የሚያሳይ ነው። ይህ ስብስብ ቋሚ መርህ የሌለው፣ አንደበቱ እና ተግባሩ የማይገናኝ ሙሉጭልጭ ነው። በአንድ በኩል ድሃውን የትግራይ ወጣት "ተዋጋልኝ፣ ተሰለፍልኝ" እያለ በአቋራጭ ወደ እሳት ይማግዳል፤ በሌላ በኩል ደግሞ የሕዝቡን አንጡራ ሀብት በኮንትሮባንድ እያሸሸ ካዝናውን ያደልባል።
አሁን ግን ጊዜው ተቀይሯል። የትግራይ ሕዝብም ሆነ ወጣቱ የቡድኑን እኩይነት ሙሉ በሙሉ ተረድቶ፣ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጋር በመተባበር ይህንን ዘመን ያለፈበትን የጥፋት ተሽከርካሪ ከጫንቃው ላይ እያወረደው ይገኛል። አዲሱ ትውልድ በሀሰተኛ ትርክት የሚሸነፍበት ዘመን አብቅቷል። የትግራይ ወጣት የቡድኑ ማታለያ ለዘለዓለም እንዲያበቃ ቆርጦ ተነስቷል፤ ምክንያቱም የትውልድ ዘመን ወደኋላ አይቆጥርም፤ ትውልድም ፈጽሞ አይሸነፍም!
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #newgenerations #tigray
Sponsored by
Surafel
10 days ago
በሆነ በዘመን የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም!
የአህመድ ተሸመ (ዲንቢ) “ጊዜ አይሄድም”!
ተስፋዬ እሸቱ (ረ/ፕሮፌሰር)
#ethiopia | መቸም የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ድንቅ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፡፡ ለራሱ የሠራቸውን ዘግየት እናድርግና ለሌሎች የሙያ አጋሮቹ ሠርቶላቸው በብዙኋን አድማጮች ዘንድ ሰፊ ተቀባይነትን ያገኙትን የዜማ ድርሰቶቹን እንዘርዝር ብንል ጊዜም ሥፍራም አይበቃንም፡፡
እንደው ከግምታችን በላይ ስለሆነው ስለዲንቢ የላቀ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና መሠረታዊ ግንዛቤ ሊያስጨብጠን ቢችል ግን ጥቂቱን ብቻ ከዚህ እንደሚከተለው እዘረዝርላችኋለሁ፡—
ለአሊ ቢራና ሄለን በርሄ - “ሲያዴ”፤ ለፀሀዬ ዮሐንስ - “ማን ልበልሽ”፤ ለማዲንጎ አፈወርቅ - “ላላተርፍ”፤ ለብዙአየሁ ደምሴ - “የህልሜ ንግስት”፤ ለዘቢባ ግርማ - “ገራገር”፤ ለኢሳያስ ታምራት - “እያዳነ ያማል”፤ ለታረቀኝ ሙሉ - “ስሚያቸው”፤ ለሚኪያስ ቸርነት - “ግርማ ሞገሴ”፤ ለሃይማኖት ግርማ - “ከዚራ ቁ-2”፤ ለግርማ ተፈራ - “ልዩ”፤ ለሀመልማል አባተ - “ሀሴት”፤ እና የመሳሰሉቱን የአህመድ ዲንቢን የዜማ ፈጠራዎች ከብዙ በጥቂቱ ማስታወስ ይቻላል፡፡
አንዳንድ ሙዚቃዎች ለጆሮ ብቻ አይሰሩም፤ ለስሜት ይደርሳሉ፤ ዛሬ ተሰርተው ግን ትዝታችንን ይመልሱልናል፡፡
አንዳንድ ዜማዎች፣ በውስጣችን የተከረቸሙ የጊዜ በሮችን ያንኳኳሉ፤ ይከፍታሉምም፡፡ በሮቹ ሲከፈቱ ደግሞ የተዘነጉ ፊቶች፣ የተለየናቸው ጓደኞች፣ የተራመድንባቸውን ጎዳናዎች… ብቻ ምኑ ቅጡ ትላንታችንን እንደ መጽሀፍ ይገልጡልናል፡፡ በሆነ ዘመን የቀረውን ማንነታችንን እንደገና ይመልሱልናል።
አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ከ14 ዓመታት በኋላ በአዲስ አልበሙ ሲመለስ፣ እኔ የሰማሁት የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብን አይደለም። አንድ በሆነ ዘመን የነበረ የዜማ ሰዋሰውና በዚሁ ዜማ ምክንያት የተሰፋ፣ የምናፍቀውን ዘመን የመለሰልኝ ያህል ነው የተሰማኝ፡፡
ያ የኔ ዘመን የምለው “ዘጠናዎቹ”ን ነው፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሆኜ የገባሁት በ1997 ዓ.ም. ነው። አይ፣ ተማሪነት! እንዴት ያለ ጣፋጭ፣ እንዴት ያለ የማይደገም ዘመን ነበር! ያ ዘመን ለእኔ የወጣትነት ወርቃማ ጠዋት ነበር። ዓለምን እንደ አዲስ ማየት የጀመርኩበት፤ ከተማዋን፣ ሕይወትን፣ ፍቅርን፣ ሐሳብንና ነፃነትን ለመጀመሪያ ጊዜ በሙሉ ልብ ያጣጣምኩበት ዘመን ነበር።
ያ ዘመን ከጓደኞቸ ጋር እንደፈለግን የኖርንበት ዘመን ነበር። በአደባባይ የተከራከርንበት፣ አለምን የጠየቅንበት፣ መንግሥትን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቃወምንበት፣ ነፃነትን ያየንበት፣ ዜማን ያጣጣምንበት ወቅት ነበር። ያ ዘመን “ዘጠናዎቹ” ነበር፡፡
ያንን ዘመን ሁሌም እናፍቀዋለሁ፤ ምናልባትም የምናፍቀው ዘመኑን ራሱን አይደለም፤ በዚያ ዘመን ውስጥ የነበርነውን እሱን፣ እሷን፣እኔን፣እኛን ነው። እንደገና እንዲመጣም እመኛለሁ።
ማርሴል ፕሩስት የተባለ ፈረንሳያዊ የልብ ወለድ ጸሀፊና ሀያሲ ጥልቅ የሆነን ትዝታ አስበን ለማስታወስ በምናደርገው ጥረት አይመለስም፤ ነገር ግን የስሜት ሕዋሳችን በሚነካ አንድ ድንገተኛ ልምድ ሊቀሰቀስ ይችላል ይላል፡፡ ሙዚቃም ከእነዚህ የትዝታ ቀስቃሾች መካከል እጅግ ኃይለኛው ሳይሆን አይቀርም።
በዚህ ረገድ እንደ አህመድ ተሾመ ጥንቅቅ ተደርጎ የተሰራ ዜማ የተረሳ ግን ተደበቀ ስሜትን ይቀሰቅሳል፤ የጠፋ የሚመስለውን የዜማ ስልተ ምት ይመልሳል፤ በዘመን ጥላ ሥር ተደብቆ የኖረ ማንነት እንደገና ያነቃቃል።
በ1990ዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ የራሱ የሆነ የዜማ ሰዋሰው፣ ቀለምና የአወራረድ ለዛ ነበረው። ያ ዘመን ለእኔ ሙዚቃን ከመስማት ወደ ማዳመጥ የተሸጋገርኩበት ጊዜ ነው። ስለዚህ የዚያ ዘመን ዜማዎች በጆሮዬ ብቻ ተደምጠው አልቀሩም፤ በማንነቴ ውስጥ ህያው ናቸው።
እኔ የሙዚቃ ባለሙያ አይደለሁም፤ ሙዚቃን ግን በልቤ አዳምጠዋለሁ። በእኔ የዜማ አረዳድ፣ የዚያ ዘመን የዜማ አሠራሮች በቀላሉ የሚደገሙ አይደሉም። ምክንያቱም ዜማው የተፈጠረው በድምፅ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመኑ መንፈስም ጭምር ነው። ከዚያ በኋላ የመጡት ዘመናት የራሳቸውን የሙዚቃ ቋንቋ ፈጥረዋል።
ያው ዘመን ሲለወጥ የዜማ ሰዋሰውም የሚለወጥ ይመስለኛል፡፡ ይህም የሥነ ጥበብ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው፤ ዋናው ጉዳይ ግን በ1990ዎቹና ከዚያ በኋላ በመጡት ዜማዎች መካከል የተቋረጠ ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡ መቆራረጡ ለሙዚቃ ባለሙያዎች ትልቅ የጥናት ርዕስ የሚሆንም ነው፡፡
ታዲያ የአህመድ ተሾመ አዲስ አልበም፣ የ1990ዎቹን የዜማ መንፈስ አገኘሁበት፤ የቀድሞውን በቀጥታ ሳይደግም፣ ያንን ለዛ በአዲስ ስልተ ምት የቀነበበ ዜማ ሆኖ አዳመጥኩት። ጉዳዩን ሳይንቲፊካሊ መግለጽ ባልችልም ልቤ ግን አልበሙ በዚያን ጊዜና በዛሬው የሙዚቃ ዘመን መካከል የተዘረጋ የዜማ ድልድይ እንደሆነ ይነግረኛል።
በአጠቃላይ ለእኔ፣ የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ጊዜ አይሄድም አዲስ አልበም የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ካለፈ ጊዜና ትዝታ ጋር የተደረገ ውይይት ነው፤ ትናንትን ከዛሬ ጋር ያስታረቀ የዜማ ድልድይ ነው፤ በዘጠናዎቹ የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም ነው። ይመችሽ ዲንቢ!!
ካላመናችሁኝ ደግሞ ከአዲስ አልበሙ መካከል "ጊዜ አይሄድም"፣"አይሽና"፣ "ይረፍዳል" እና "ህልም ነው" አድመጣችሁ ፍረዱኝ፤ ካጠፋሁ እኔ ሳልሆን ዲንቢ ይቀጣል፡፡
የአህመድ ተሸመ (ዲንቢ) “ጊዜ አይሄድም”!
ተስፋዬ እሸቱ (ረ/ፕሮፌሰር)
#ethiopia | መቸም የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ድንቅ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፡፡ ለራሱ የሠራቸውን ዘግየት እናድርግና ለሌሎች የሙያ አጋሮቹ ሠርቶላቸው በብዙኋን አድማጮች ዘንድ ሰፊ ተቀባይነትን ያገኙትን የዜማ ድርሰቶቹን እንዘርዝር ብንል ጊዜም ሥፍራም አይበቃንም፡፡
እንደው ከግምታችን በላይ ስለሆነው ስለዲንቢ የላቀ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና መሠረታዊ ግንዛቤ ሊያስጨብጠን ቢችል ግን ጥቂቱን ብቻ ከዚህ እንደሚከተለው እዘረዝርላችኋለሁ፡—
ለአሊ ቢራና ሄለን በርሄ - “ሲያዴ”፤ ለፀሀዬ ዮሐንስ - “ማን ልበልሽ”፤ ለማዲንጎ አፈወርቅ - “ላላተርፍ”፤ ለብዙአየሁ ደምሴ - “የህልሜ ንግስት”፤ ለዘቢባ ግርማ - “ገራገር”፤ ለኢሳያስ ታምራት - “እያዳነ ያማል”፤ ለታረቀኝ ሙሉ - “ስሚያቸው”፤ ለሚኪያስ ቸርነት - “ግርማ ሞገሴ”፤ ለሃይማኖት ግርማ - “ከዚራ ቁ-2”፤ ለግርማ ተፈራ - “ልዩ”፤ ለሀመልማል አባተ - “ሀሴት”፤ እና የመሳሰሉቱን የአህመድ ዲንቢን የዜማ ፈጠራዎች ከብዙ በጥቂቱ ማስታወስ ይቻላል፡፡
አንዳንድ ሙዚቃዎች ለጆሮ ብቻ አይሰሩም፤ ለስሜት ይደርሳሉ፤ ዛሬ ተሰርተው ግን ትዝታችንን ይመልሱልናል፡፡
አንዳንድ ዜማዎች፣ በውስጣችን የተከረቸሙ የጊዜ በሮችን ያንኳኳሉ፤ ይከፍታሉምም፡፡ በሮቹ ሲከፈቱ ደግሞ የተዘነጉ ፊቶች፣ የተለየናቸው ጓደኞች፣ የተራመድንባቸውን ጎዳናዎች… ብቻ ምኑ ቅጡ ትላንታችንን እንደ መጽሀፍ ይገልጡልናል፡፡ በሆነ ዘመን የቀረውን ማንነታችንን እንደገና ይመልሱልናል።
አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ከ14 ዓመታት በኋላ በአዲስ አልበሙ ሲመለስ፣ እኔ የሰማሁት የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብን አይደለም። አንድ በሆነ ዘመን የነበረ የዜማ ሰዋሰውና በዚሁ ዜማ ምክንያት የተሰፋ፣ የምናፍቀውን ዘመን የመለሰልኝ ያህል ነው የተሰማኝ፡፡
ያ የኔ ዘመን የምለው “ዘጠናዎቹ”ን ነው፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሆኜ የገባሁት በ1997 ዓ.ም. ነው። አይ፣ ተማሪነት! እንዴት ያለ ጣፋጭ፣ እንዴት ያለ የማይደገም ዘመን ነበር! ያ ዘመን ለእኔ የወጣትነት ወርቃማ ጠዋት ነበር። ዓለምን እንደ አዲስ ማየት የጀመርኩበት፤ ከተማዋን፣ ሕይወትን፣ ፍቅርን፣ ሐሳብንና ነፃነትን ለመጀመሪያ ጊዜ በሙሉ ልብ ያጣጣምኩበት ዘመን ነበር።
ያ ዘመን ከጓደኞቸ ጋር እንደፈለግን የኖርንበት ዘመን ነበር። በአደባባይ የተከራከርንበት፣ አለምን የጠየቅንበት፣ መንግሥትን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቃወምንበት፣ ነፃነትን ያየንበት፣ ዜማን ያጣጣምንበት ወቅት ነበር። ያ ዘመን “ዘጠናዎቹ” ነበር፡፡
ያንን ዘመን ሁሌም እናፍቀዋለሁ፤ ምናልባትም የምናፍቀው ዘመኑን ራሱን አይደለም፤ በዚያ ዘመን ውስጥ የነበርነውን እሱን፣ እሷን፣እኔን፣እኛን ነው። እንደገና እንዲመጣም እመኛለሁ።
ማርሴል ፕሩስት የተባለ ፈረንሳያዊ የልብ ወለድ ጸሀፊና ሀያሲ ጥልቅ የሆነን ትዝታ አስበን ለማስታወስ በምናደርገው ጥረት አይመለስም፤ ነገር ግን የስሜት ሕዋሳችን በሚነካ አንድ ድንገተኛ ልምድ ሊቀሰቀስ ይችላል ይላል፡፡ ሙዚቃም ከእነዚህ የትዝታ ቀስቃሾች መካከል እጅግ ኃይለኛው ሳይሆን አይቀርም።
በዚህ ረገድ እንደ አህመድ ተሾመ ጥንቅቅ ተደርጎ የተሰራ ዜማ የተረሳ ግን ተደበቀ ስሜትን ይቀሰቅሳል፤ የጠፋ የሚመስለውን የዜማ ስልተ ምት ይመልሳል፤ በዘመን ጥላ ሥር ተደብቆ የኖረ ማንነት እንደገና ያነቃቃል።
በ1990ዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ የራሱ የሆነ የዜማ ሰዋሰው፣ ቀለምና የአወራረድ ለዛ ነበረው። ያ ዘመን ለእኔ ሙዚቃን ከመስማት ወደ ማዳመጥ የተሸጋገርኩበት ጊዜ ነው። ስለዚህ የዚያ ዘመን ዜማዎች በጆሮዬ ብቻ ተደምጠው አልቀሩም፤ በማንነቴ ውስጥ ህያው ናቸው።
እኔ የሙዚቃ ባለሙያ አይደለሁም፤ ሙዚቃን ግን በልቤ አዳምጠዋለሁ። በእኔ የዜማ አረዳድ፣ የዚያ ዘመን የዜማ አሠራሮች በቀላሉ የሚደገሙ አይደሉም። ምክንያቱም ዜማው የተፈጠረው በድምፅ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመኑ መንፈስም ጭምር ነው። ከዚያ በኋላ የመጡት ዘመናት የራሳቸውን የሙዚቃ ቋንቋ ፈጥረዋል።
ያው ዘመን ሲለወጥ የዜማ ሰዋሰውም የሚለወጥ ይመስለኛል፡፡ ይህም የሥነ ጥበብ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው፤ ዋናው ጉዳይ ግን በ1990ዎቹና ከዚያ በኋላ በመጡት ዜማዎች መካከል የተቋረጠ ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡ መቆራረጡ ለሙዚቃ ባለሙያዎች ትልቅ የጥናት ርዕስ የሚሆንም ነው፡፡
ታዲያ የአህመድ ተሾመ አዲስ አልበም፣ የ1990ዎቹን የዜማ መንፈስ አገኘሁበት፤ የቀድሞውን በቀጥታ ሳይደግም፣ ያንን ለዛ በአዲስ ስልተ ምት የቀነበበ ዜማ ሆኖ አዳመጥኩት። ጉዳዩን ሳይንቲፊካሊ መግለጽ ባልችልም ልቤ ግን አልበሙ በዚያን ጊዜና በዛሬው የሙዚቃ ዘመን መካከል የተዘረጋ የዜማ ድልድይ እንደሆነ ይነግረኛል።
በአጠቃላይ ለእኔ፣ የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ጊዜ አይሄድም አዲስ አልበም የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ካለፈ ጊዜና ትዝታ ጋር የተደረገ ውይይት ነው፤ ትናንትን ከዛሬ ጋር ያስታረቀ የዜማ ድልድይ ነው፤ በዘጠናዎቹ የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም ነው። ይመችሽ ዲንቢ!!
ካላመናችሁኝ ደግሞ ከአዲስ አልበሙ መካከል "ጊዜ አይሄድም"፣"አይሽና"፣ "ይረፍዳል" እና "ህልም ነው" አድመጣችሁ ፍረዱኝ፤ ካጠፋሁ እኔ ሳልሆን ዲንቢ ይቀጣል፡፡
10 days ago
#ቤተልሔም_ሸረፈዲን - " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ ያላት "
( የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ )
**********************************************
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
#በመጨረሻም ፦ ጽሑፉ ለፌስቡክ ረጅም ( አረፍ አረፍ እየተባለ ተነቦ የሚያልቅ ) ነው ። አጥሮ ሁሉም ጋ ከሚደርስ ረዝሞ የሚመለከታቸውና የሚያስፈልጋቸው ቢያነቡት መርጬ ነው ። ሆነ ብዬ ነው ማለት ነው ። ይሁን ። እንግዲህ እያረፋችሁም ፣ እያለፋችሁም አንብቡት ።
ለግጥምም ፣ ለዜማም አልፎ ሂያጅ ነኝ። ( በተለይ ) ለግጥም አልፎ ሂያጅ መሆኔ ያስቆጨኛል ። ግጥም ምኞቴ ነው ፤ ጉድለቴም ። ማንም እንደሚሰማውና እንደሚረዳው ነኝ ። አዚያዚያምን መረዳትም ላይ ጨዋ አላዋቂ ነኝ ። ቤተልሔም ሸረፈዲን " ደስተኛ " ብላ ስለሰየመችው አዲሱ አልበሟ የተሰማኝን ልላችሁ ነው ዳር ዳር የምለው ።
እኔ የምለው ፣ ቤተልሔም ሸረፈዲን ግን ስንት ዓመቷ ነው ? በቅርቡ ትንሽ ልጅ አልነበረችም እንዴ ? ከመቼው አደገች ? ከምኔው አብባ አፈራች ? አልበሟ በተለቀቀበት " ኩራ ስትሪም " ላይ ገጣሚው ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) እንደ ገጣሚነቱ ቃላት ቆጥቦና ሀሳቡን አስውቦ " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ አላት
" እንዳላት ሆና ነው የመጣችው ። የጥበብ ስራ አመዛኙን ሁለቱን ይፈልጋል ። እውቀትም ፣ ተሰጥዖም በዝቶ ኖሯቸው የትም ሳይደርሱ የቀሩ " እገሌ ፣ እገሌ " የምንላቸው ጥቂት የማይባሉ የጥበብ ሰዎች በየአልባሌው ወድቀው ቀርተዋል ። እስቲ እነዚህን ሰዎች አስቧቸው ። የህጻን ልብም ፣ የአዋቂ ጆሮም አታገኙባቸውም ።
10 ዘፈኖች የያዘው " ደስተኛ " አልበም ናትናኤል ግርማቸውና ታምሩ አማረ በጥምረት ፕሮዲዩስ ያደረጉት ነው ። ከጀርባቸው ደግሞ ከብዙ ጥበባትና የጥበብ ሰዎች ጀርባ ያለው ዘላለም ኩራባቸው " ኩራ ስትሪም " ን ይዞ አለ ። ቅንብሩን ፣ ሚክሲንግ እና አሬንጅመንቱን ታምሩ አማረ ፣ ግጥሞቹን ( በሙሉ ) ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) ፣ " ባለቤቴ " እና " እንዴት " ዜማዎችን ዮሴፍ በቀለ ( ጆ ) ፣ " አይታለፍም " ዜማ እሱባለው ይታየው ( የሺ ) ፣ የቀሪዎቹን 7 ስራዎች ዜማዎች በምህረተአብ ደስታ ሲፈጠሩ ከእነዚህ ውስጥ የእበሙ መጠሪያ የሆነው " ደስተኛ " ን ዜማ ናቲና ምህረተአብ በጋራ ሰርተዋቸዋል ።
በአሁኑ ጊዜ አንድ ነጠላ ዜማ መስራት የምረቃ ፕሮግራም ያዘጋጃል ፤ ወዳጅ ዘመድ ያጠራራል ፤ " ሰይፉ በኢቢኤስ " ላይ ያስቀርባል ፤ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ አላስቆም አላስቀምጥ ያስብላል ። አልበም መስራት ( አድማጭ ያልተቀበለውም ቢሆን እንኳ ) እንደ አራሷ ሴት " ምጡን ተዪው ፤ ልጁን እዪው " እየተባለና የስቃዩ ጊዜ እየተረሳ እንጂ ደጋግሞ በስሜት ሞቶ መነሳት ነው ። የሚያገጫጭ ፣ የሚያነጫንጭ ፣ የሚያቀያይምንና " ሁለተኛ ብንገናኝ ! " የሚያባብል ነው ። የምጡ ጊዜ አልፎ ልጁ ሲታይ እየተረሳ ነው አንዱ ሙዚቀኛ ከሌላው ጋር የኖረው ። ቤተልሔም መልካሞችና ህልም ያላቸው ሙያተኞች እጅ ላይ አሳርፏት እንጂ ጀምሮ አለመጨረስ ፣ ወድቆ አለመነሳትም አለ ። ገና በመጀመሪያው አልበም ፣ በትንሽ እድሜ ፣ በጀማሪነት አረዳድ እንዲህ ያለ ስኬታማ አልበም መስራት ደጋግሞ የማያጋጥም ነው ። ህብስት ጥሩነህ እነ አየለ ማሞ ( ማንዶሊን ) እና ታንጎ ሙዚቃ ቤትን እንዳገኘችው አይነት እድለኛነት ይጠይቃል ። የናቲ እና ታምሩ ጥምረት ደግሞ የእነ ኤሌክራትን እና አምባሰልን ዘመን ያስታውሰናል ።
ናቲ " ኩራ ስትሪም " ላይ 4 ዓመት ስላለፈው " ደስተኛ " አልበም ሲናገር " አልበሙን ጀምረነው ባልነው ጊዜ ያልጨረስነው እኛ በዚያ ውስጥ እየተሰራን ስለነበረ ነው " ይለዋል ። ፕሮዲዩሰሮቹ በምን በምን እንደተሰሩ አላውቅም ። ቤተልሔምን ግን በእርግጥም ሰርተዋታል ። አፈሩን ቆፍረውና አልመው ፣ አቡክተው ቤተልሔምን እንደ ውቡ ሸክላ አስጊጠው ሰርተዋታል ። እሷ እንደምትለውም ትንሿ ቤተልሔም " ከብዙ ልምምድ በኋላ የመጣ አልበም " ባለቤት እንትሆን አድርገዋታል ። ቤተልሔም ሸረፈዲን የተባለች ጥንቅቅ ፣ ጥፍጥ ያለ ስራ ያላት ድምጻዊትን ለዘመኑ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ( ? ) አበርክተዋል ። አሁን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ቤተልሔም ሸረፈዲን የምትባል ብስል ፣ ትክን ያለች ድምጻዊት አለችለት ። ቤተልሔም ስለ አዲሱ አልበሟ ለኩራ ስትሪም ስትናገር " ይሄን አልበም እንደ መጀመሪያም ፣ እንደ መጨረሻም ስራ አድርጌ ነው የማየው ። " ብላለች ።
ናትናኤል ግርማቸው ገጣሚነት ተሰጥቶታል ። ገጣሚነቱ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የሀሳብ ስፋት የታደለው ነው ። ናቲን በራሄል ጌቱ " ኢትዮጵያዬ " ነው ያወቅኩት ። የራሷን የራሄል ጌቱን " ያገሬ ሰው " ፣ በኋላም " ወረት " ን ሰርቶ አስደንቆኛል ። ናቲን በራሄል ጌቱ ( በስራዎቿ ) በኩል ነው ያገኘሁት ። ይህ ሰው ነው ደግሞ ከታምሩ አማረ ጋር ሆኖ ቤተልሔም ሸረፈዲንን ያገኛት ። ሁለቱ በፕሮዲዩሰርነት ባይከሰቱ ቤተልሔም ሸረፈዲን ቢያንስ በዚህ ጊዜ አትወለድም ። የጀርባ አቅሟን ባላውቅም የ10 ግጥም ፣ የ10 ዜማ ፣ የ10 ዜማዎች ቅንብር ፣ ሚክሲንግ እና ማስተሪንግ ክፍያን አትወጣውም ( ብዬ እገምታለሁ ) ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ዘላለም ኩራባቸውን አታገኘውም ። ዘላለም ኩራባቸው ወደ ሙዚቃ ማምረት ስራ ሲገባ ከገንዘብ የነፍስ ጥሪ ትርፉን አስቦ እንደሚሆን አምናለሁ ። ካሁን ቀደም በተናጠል ሲያደርግ የነበረውን ሙያውንና ሙያተኛውን እንደ ታላቅ ወንድም አጋር የመሆን ዝንባሌውን ተቋማዊ ቅርጽ ሰጥቶት መምጣቱ ይመስለኛል ። ቤተልሔም እድለኛ ናት ። እነ ንዋይ ደበበ ፣ ሀመልማል አባተ ፣ ጸሐዬ ዮሀንስ እና ዘመንኞቻቸው በመጡበት መንገድ ነው የመጣችው ። ሌላም እድለኛነት ( ከችሎታ ጋር ) አላት ።እነ ጠረፍ ካሳሁን ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ለምለም ኃ/ሚካኤል ፣ ዘቢባ ግርማ ተሰርተው የወጡበት " የኛ " ፕሮጀክት ፣ የእነ አይዳ አሸናፊ እጅም አርፎባታል ።
ከአስሩ የ " ደስተኛ " አልበም ስራዎች በተሸከመው ሀሳብ ( ለእኔ ) " ባለቤቴ " ን የሚያህልልኝ አላገኘሁም ። ለዚህ ዘፈን ከ " ባለቤቴ " ይልቅ " አትክልተኛው " ስምም ሆኖልኛል ። ምናልባት ግን " አትክልተኛው " ለዘፈን ርዕስነት ያንስ ( አይሆን ) እንደሆን አላውቅም ። ሙሉ ዘፈኑን ስንሰማው ገጸባሕሪዋ በምናቧ ከዋለለችለት የምናብ ባለቤቷ ይልቅ የሰው ያልሆነ ፣ ለሰው አዕምሮ " ሞኝ " የሚባል ፣ ለፍጽምና የቀረበ በዝናብም ፣ በጸሐይም ስራውን የማያስተጓጉል ፣ ብርሀን መርጦ የማይመጣ ፣ በጭለማ የማይሸሸግ ፣ የማግኘትም ፣ የማጣትም ጊዜ ወዳጅ ፣ እንደ አምላክ ያለ ብርቱ ሰው ነው ። ባለቤትነቱ ህልም ሲሆን ብርቱ አትክልተኝነቱ ግን እውን ነው ። ይህ ሰው ትትርናውና ቸርነቱ እንደ አምላክ ያለ ነው ። ከማንም ፣ ከምንም የማይጠብቅ ። መስጠት ብቻ የሆነ ። በአበቦቹ መሐል ብቻ አይደለም ያለው ። ልብ ባለበት ሁሉ ነው ።
" በዝናብ አካሉም በዶፉ እየረሰረሰ
የአትክልቶቹን ስር ሲያጠጣ የልምዱን ውሀ እያፈሰሰ
አሉት የማን ነው ጅል ያን አትክልተኛ
ሳቁበት እንደሞኝ ወይኔ
አላወቁም የእሱ ዝናብ መጣ ቀረ
ንፍገትን ለልቡ እንዳላስተማረ ።
*************************
አሰብኩት ከሆነ እንዲህ ለአትክልቱ
እንዴት መልካም ይሆን ለሚወዳት ሚስቱ "
ያለችውን ብርቱና ቸር ሰው ነው . . .
" ቢዘንብም ቢያካፋም ከጎኔ የማይጠፋ
እንደ ባለ አጸዱ ጽኑ ለመውደዱ
ሳላውቅህ ልንገርህ የነገ ውሀ አጣጬ
አርገኝ እንዳልከስም ፍቅርን ተጠምቼ "
እያለች ምኞቷን ፣ መሻቷን ፣ የወደፊት ህልሟን ትነግረናለች ። መልካምነት መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልንም ይፈልጋል ። ምርጥ ዘር ምርጥ አፈርንም ይፈልጋል ። በተዘራበት ሁሉ አይበቅልም ። እንደ እሷ የሚረዳ ካልተገኘ ሌሎቹ እንዳሉት " የማነው ሞኝ ? " ያስብላል ።
በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ የዚህ የወደድኩት ብርቱ አትክልተኛ ተቃራኒ ቢሆንም የእኔ ከ1ኛ - 3ኛ " ቻው ( ዎ ) " ነው ።
" አልነበረም ከዓይን የተሰወረ
መንገድህን ሳላየው መች ቀረ
ሰነባብቷል መንፈስህ ሸፍቷል
ልቤን ልብህ ቻው ካለው ቆይቷል ።
አልታወጀም እንጂ ፊትም የእኛ ነገር
የተለያየነው አብረን ሆነን ነበር ።
እንባዬ ተማጽኖህ እንዳያስታርቀን
ያለቀው ያኔ ነው ልብህ የሄደ ቀን ።
እያንዳንዱን ቀናት በእንባ እየሰፈርኩኝ
ቻው ስልህ ኖሬያለሁ እየሸራረፍኩኝ ።
ዛሬም ለበደልህ አረከኝ ጣል ጣል
ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል ። "
ይኽ መቸም በየፍቅር ጎጆው ፣ በየትዳር ማጀቱ ፣ በየጓደኝነቱና ወዳጅነቱ አደባባይ የሚታይ የወቅቱ እውነታ ነው ። በየግንኙነታችን " ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል " ። አብዛኛዎቻችን አንድ ላይ ቆመናል እንጂ አብረን አይደለንም ። " አንድ ላይ ብንሆንም ተለያይተናል " እንዳለው ድምጻዊው ። እግሮቻችን ብቻ አብረው ይጓዛሉ ፤ አካላችን አንድ ላይ ይታያል ፤ ነፍስ የሌለው ስጋ ነው ። አብረን ውለን እናድራለን ፤ በልባችን ግን ተለያይተናል ። አልታወቀን ይሆናል እንጂ እንደ ግልም ፣ እንደ ሀገርም እንዲህ ሆነናል ። ለዚህ ነው አሁን ያለንበት ላይ ያለነው ። ለዚህ ነው በየሰበቡ ሕይወት የሚታክተን ። ለዚህ ነው መኖር ትግል ፣ አብሮነት መተናነቅ የሚሆንብን ( የሆነብን ) ። የቤተልሔም ሸረፈዲን " ቻው " ለአንድ ተፈቃሪ ወንድ የተሰራም ቢሆን ሀሳቡ ግን እዚህ ድረስም የሚመጣ ነው ። ናቲ " ቃሉ ከዜማው ጋር ነው የመጣው " ያለውና ራሷን ድምጻዊቷን አስለቅሶ የተገለጠው " ቻው " ገና ብዙውን ልብ የሚነካ ስራ ይሆናል ።
" ልቤን " ን ላልወደው አስቤ ነበረ መሰለኝ ። የእድሜም ፣ የፍላጎትም ጉዳይ ሆኖ ፈጠን ላሉ ምቶች አልደነግጥ ሆኖ ይሆናል እንጂ ምን ሆኜ ነው ዜማው ፣ ምቱ ፣ በተለይ የድምጻዊቷ አዘፋፈን ከፍ ብሎ የታየበትን ይህን ስራ " ይቆየኝ " ያልኩት ? ባልወደውና ደጋግሜ ባልሰማው ይቆጨኝ ነበር ። ( ለነገሩ ካልወደድኩት ለምን ይቆጨኛል ? ) " ደስተኛ " ርዕስና ሀሳቡ ደስተኛ ካልሆነች ፣ " አልወድሽም " ከተባለችና ከተገፋች ገጸባህሪ የተገኘ ነው ። " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ትላለች ። " አልወድሽም " ተብላና " ብትጎዘጉዝ አበባ ዛሬ አይረባ " ያለች ሴት ራሷን ማታለል ሳይሆን " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ስትል ካዋጣትና ከተቻላት ያድርግላት ። ከእሷ እንባና የልብ ስብራት ምን ጉዳይ አለን ? ብቻ ከአፏ ሳይሆን ከልቧ ይሁን ።
" እንደ ውሀ መውረድ ፣ እንደ ጸሐይ መውጣት
እንደ ጊዜው መክነፍ ፣ እንደ አሸዋ መብዛት
እውነታ መሆኑን ቅንጣት ሳልጠረጥር
እኔስ አምነዋለሁ የልብህን ፍቅር "
ያለችበት " አካልዬ " ለረጋ ያለ ሙዚቃ አፍቃሪ ይሁነኝ ተብሎ የተቀመረ ስራ ነው ። በምርጤነት ከተቀበልኳቸው መካከል አንዱ ነው ።
አንደኛው ሙዚቃ አስተያየት መስጫ ውስጥ ገብቼ ሳነብ " የዚህ አልበም ትልቁ ችግሩ ውስጡ ያሉት ዘፈኖች 10 ብቻ መሆናቸው ነው " ሲል " አድናቆቱን " ገልጿል ። እኔም እንደዚያ ሆኖ ይሰማኛል ። ከአስሩ ሰባቱን ስራዎች በልዩ ሁኔታ ወድጃቸዋለሁ ። አንዱ የዋለልኩበትና ሁለቱ ደግሞ ልብ ያልሰጠኋቸው ናቸው ። ይህ በአንድ አለበም ውስጥ ከበቂ በላይ ስኬታማነት ነው ። ከብዙ ዓመት በኋላ ተሟልቶ ያገኙሁት ምርጤ ነው " ደስተኛ " አልበም ።
እዚህ አልበም ላይ ያለኝ አንድ ( ግላዊ ) ቅሬታ አስሩም ስራዎች የተቃራኒ ጾታ ፍቅር ላይ ብቻ ያተኮሩ መሆናቸው ነው ። እንዳይሆኑ የሚከለክል ደንብ የለም ። ፕሮዲዩሰሮቹ የቤተልሔምን እድሜና የፍቅር ጊዜዋን አስበው ያደረጉት ሊሆን ይችላል ። ያም ቢሆን በዚህ ውጥንቅጡ የወጣ የመከራ ጊዜ ፣ በብዙ ሰው ሰራሽና የአስተሳሰብ ሰንሰለት እግር ከወርች ታስረን መሔጃ ባጣንበት ዘመንና ሀገር ፣ ላለንበት ጊዜ ፣ ለስሜታችን ፣ ለህመማችን ፣ ለሰለለው ተስፋችን የሚሆን አንድ ስራ ልናጣ አይገባም ብዬ አስባለሁ ። ናቲና ምህረተአብ ለራሄል ጌቱ እንደሰጧት " ያገሬ ሰው " ያለ ስራ ቢመርቁልን እንዴት መልካም ነበረ ?
ከቀናት በፊት አስቴር አወቀ ( በድጋሚ ስራዎቿም ቢሆን ) በትንሿ ቤተልሔም ሸረፈዲን ላይ ተደርባ አልበሟን መልቀቋ አስፈርቶኝ ነበረ ። ይህን የመሰለ አልበም ፣ የ4 ዓመት የሚነገርና የማይነገር እልህ አስጨራሽ ድካም መና እንዳይቀር ሰግቼ ነበረ ። ስጋቴ ስጋት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ። ቤተልሔም የዋርካው ጥላ ሳያርፍባት አልፋለች ። ገና ገና ትቀጥላለች ፤ ትቀጣጠላለች ።
( የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ )
**********************************************
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
#በመጨረሻም ፦ ጽሑፉ ለፌስቡክ ረጅም ( አረፍ አረፍ እየተባለ ተነቦ የሚያልቅ ) ነው ። አጥሮ ሁሉም ጋ ከሚደርስ ረዝሞ የሚመለከታቸውና የሚያስፈልጋቸው ቢያነቡት መርጬ ነው ። ሆነ ብዬ ነው ማለት ነው ። ይሁን ። እንግዲህ እያረፋችሁም ፣ እያለፋችሁም አንብቡት ።
ለግጥምም ፣ ለዜማም አልፎ ሂያጅ ነኝ። ( በተለይ ) ለግጥም አልፎ ሂያጅ መሆኔ ያስቆጨኛል ። ግጥም ምኞቴ ነው ፤ ጉድለቴም ። ማንም እንደሚሰማውና እንደሚረዳው ነኝ ። አዚያዚያምን መረዳትም ላይ ጨዋ አላዋቂ ነኝ ። ቤተልሔም ሸረፈዲን " ደስተኛ " ብላ ስለሰየመችው አዲሱ አልበሟ የተሰማኝን ልላችሁ ነው ዳር ዳር የምለው ።
እኔ የምለው ፣ ቤተልሔም ሸረፈዲን ግን ስንት ዓመቷ ነው ? በቅርቡ ትንሽ ልጅ አልነበረችም እንዴ ? ከመቼው አደገች ? ከምኔው አብባ አፈራች ? አልበሟ በተለቀቀበት " ኩራ ስትሪም " ላይ ገጣሚው ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) እንደ ገጣሚነቱ ቃላት ቆጥቦና ሀሳቡን አስውቦ " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ አላት
" እንዳላት ሆና ነው የመጣችው ። የጥበብ ስራ አመዛኙን ሁለቱን ይፈልጋል ። እውቀትም ፣ ተሰጥዖም በዝቶ ኖሯቸው የትም ሳይደርሱ የቀሩ " እገሌ ፣ እገሌ " የምንላቸው ጥቂት የማይባሉ የጥበብ ሰዎች በየአልባሌው ወድቀው ቀርተዋል ። እስቲ እነዚህን ሰዎች አስቧቸው ። የህጻን ልብም ፣ የአዋቂ ጆሮም አታገኙባቸውም ።
10 ዘፈኖች የያዘው " ደስተኛ " አልበም ናትናኤል ግርማቸውና ታምሩ አማረ በጥምረት ፕሮዲዩስ ያደረጉት ነው ። ከጀርባቸው ደግሞ ከብዙ ጥበባትና የጥበብ ሰዎች ጀርባ ያለው ዘላለም ኩራባቸው " ኩራ ስትሪም " ን ይዞ አለ ። ቅንብሩን ፣ ሚክሲንግ እና አሬንጅመንቱን ታምሩ አማረ ፣ ግጥሞቹን ( በሙሉ ) ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) ፣ " ባለቤቴ " እና " እንዴት " ዜማዎችን ዮሴፍ በቀለ ( ጆ ) ፣ " አይታለፍም " ዜማ እሱባለው ይታየው ( የሺ ) ፣ የቀሪዎቹን 7 ስራዎች ዜማዎች በምህረተአብ ደስታ ሲፈጠሩ ከእነዚህ ውስጥ የእበሙ መጠሪያ የሆነው " ደስተኛ " ን ዜማ ናቲና ምህረተአብ በጋራ ሰርተዋቸዋል ።
በአሁኑ ጊዜ አንድ ነጠላ ዜማ መስራት የምረቃ ፕሮግራም ያዘጋጃል ፤ ወዳጅ ዘመድ ያጠራራል ፤ " ሰይፉ በኢቢኤስ " ላይ ያስቀርባል ፤ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ አላስቆም አላስቀምጥ ያስብላል ። አልበም መስራት ( አድማጭ ያልተቀበለውም ቢሆን እንኳ ) እንደ አራሷ ሴት " ምጡን ተዪው ፤ ልጁን እዪው " እየተባለና የስቃዩ ጊዜ እየተረሳ እንጂ ደጋግሞ በስሜት ሞቶ መነሳት ነው ። የሚያገጫጭ ፣ የሚያነጫንጭ ፣ የሚያቀያይምንና " ሁለተኛ ብንገናኝ ! " የሚያባብል ነው ። የምጡ ጊዜ አልፎ ልጁ ሲታይ እየተረሳ ነው አንዱ ሙዚቀኛ ከሌላው ጋር የኖረው ። ቤተልሔም መልካሞችና ህልም ያላቸው ሙያተኞች እጅ ላይ አሳርፏት እንጂ ጀምሮ አለመጨረስ ፣ ወድቆ አለመነሳትም አለ ። ገና በመጀመሪያው አልበም ፣ በትንሽ እድሜ ፣ በጀማሪነት አረዳድ እንዲህ ያለ ስኬታማ አልበም መስራት ደጋግሞ የማያጋጥም ነው ። ህብስት ጥሩነህ እነ አየለ ማሞ ( ማንዶሊን ) እና ታንጎ ሙዚቃ ቤትን እንዳገኘችው አይነት እድለኛነት ይጠይቃል ። የናቲ እና ታምሩ ጥምረት ደግሞ የእነ ኤሌክራትን እና አምባሰልን ዘመን ያስታውሰናል ።
ናቲ " ኩራ ስትሪም " ላይ 4 ዓመት ስላለፈው " ደስተኛ " አልበም ሲናገር " አልበሙን ጀምረነው ባልነው ጊዜ ያልጨረስነው እኛ በዚያ ውስጥ እየተሰራን ስለነበረ ነው " ይለዋል ። ፕሮዲዩሰሮቹ በምን በምን እንደተሰሩ አላውቅም ። ቤተልሔምን ግን በእርግጥም ሰርተዋታል ። አፈሩን ቆፍረውና አልመው ፣ አቡክተው ቤተልሔምን እንደ ውቡ ሸክላ አስጊጠው ሰርተዋታል ። እሷ እንደምትለውም ትንሿ ቤተልሔም " ከብዙ ልምምድ በኋላ የመጣ አልበም " ባለቤት እንትሆን አድርገዋታል ። ቤተልሔም ሸረፈዲን የተባለች ጥንቅቅ ፣ ጥፍጥ ያለ ስራ ያላት ድምጻዊትን ለዘመኑ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ( ? ) አበርክተዋል ። አሁን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ቤተልሔም ሸረፈዲን የምትባል ብስል ፣ ትክን ያለች ድምጻዊት አለችለት ። ቤተልሔም ስለ አዲሱ አልበሟ ለኩራ ስትሪም ስትናገር " ይሄን አልበም እንደ መጀመሪያም ፣ እንደ መጨረሻም ስራ አድርጌ ነው የማየው ። " ብላለች ።
ናትናኤል ግርማቸው ገጣሚነት ተሰጥቶታል ። ገጣሚነቱ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የሀሳብ ስፋት የታደለው ነው ። ናቲን በራሄል ጌቱ " ኢትዮጵያዬ " ነው ያወቅኩት ። የራሷን የራሄል ጌቱን " ያገሬ ሰው " ፣ በኋላም " ወረት " ን ሰርቶ አስደንቆኛል ። ናቲን በራሄል ጌቱ ( በስራዎቿ ) በኩል ነው ያገኘሁት ። ይህ ሰው ነው ደግሞ ከታምሩ አማረ ጋር ሆኖ ቤተልሔም ሸረፈዲንን ያገኛት ። ሁለቱ በፕሮዲዩሰርነት ባይከሰቱ ቤተልሔም ሸረፈዲን ቢያንስ በዚህ ጊዜ አትወለድም ። የጀርባ አቅሟን ባላውቅም የ10 ግጥም ፣ የ10 ዜማ ፣ የ10 ዜማዎች ቅንብር ፣ ሚክሲንግ እና ማስተሪንግ ክፍያን አትወጣውም ( ብዬ እገምታለሁ ) ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ዘላለም ኩራባቸውን አታገኘውም ። ዘላለም ኩራባቸው ወደ ሙዚቃ ማምረት ስራ ሲገባ ከገንዘብ የነፍስ ጥሪ ትርፉን አስቦ እንደሚሆን አምናለሁ ። ካሁን ቀደም በተናጠል ሲያደርግ የነበረውን ሙያውንና ሙያተኛውን እንደ ታላቅ ወንድም አጋር የመሆን ዝንባሌውን ተቋማዊ ቅርጽ ሰጥቶት መምጣቱ ይመስለኛል ። ቤተልሔም እድለኛ ናት ። እነ ንዋይ ደበበ ፣ ሀመልማል አባተ ፣ ጸሐዬ ዮሀንስ እና ዘመንኞቻቸው በመጡበት መንገድ ነው የመጣችው ። ሌላም እድለኛነት ( ከችሎታ ጋር ) አላት ።እነ ጠረፍ ካሳሁን ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ለምለም ኃ/ሚካኤል ፣ ዘቢባ ግርማ ተሰርተው የወጡበት " የኛ " ፕሮጀክት ፣ የእነ አይዳ አሸናፊ እጅም አርፎባታል ።
ከአስሩ የ " ደስተኛ " አልበም ስራዎች በተሸከመው ሀሳብ ( ለእኔ ) " ባለቤቴ " ን የሚያህልልኝ አላገኘሁም ። ለዚህ ዘፈን ከ " ባለቤቴ " ይልቅ " አትክልተኛው " ስምም ሆኖልኛል ። ምናልባት ግን " አትክልተኛው " ለዘፈን ርዕስነት ያንስ ( አይሆን ) እንደሆን አላውቅም ። ሙሉ ዘፈኑን ስንሰማው ገጸባሕሪዋ በምናቧ ከዋለለችለት የምናብ ባለቤቷ ይልቅ የሰው ያልሆነ ፣ ለሰው አዕምሮ " ሞኝ " የሚባል ፣ ለፍጽምና የቀረበ በዝናብም ፣ በጸሐይም ስራውን የማያስተጓጉል ፣ ብርሀን መርጦ የማይመጣ ፣ በጭለማ የማይሸሸግ ፣ የማግኘትም ፣ የማጣትም ጊዜ ወዳጅ ፣ እንደ አምላክ ያለ ብርቱ ሰው ነው ። ባለቤትነቱ ህልም ሲሆን ብርቱ አትክልተኝነቱ ግን እውን ነው ። ይህ ሰው ትትርናውና ቸርነቱ እንደ አምላክ ያለ ነው ። ከማንም ፣ ከምንም የማይጠብቅ ። መስጠት ብቻ የሆነ ። በአበቦቹ መሐል ብቻ አይደለም ያለው ። ልብ ባለበት ሁሉ ነው ።
" በዝናብ አካሉም በዶፉ እየረሰረሰ
የአትክልቶቹን ስር ሲያጠጣ የልምዱን ውሀ እያፈሰሰ
አሉት የማን ነው ጅል ያን አትክልተኛ
ሳቁበት እንደሞኝ ወይኔ
አላወቁም የእሱ ዝናብ መጣ ቀረ
ንፍገትን ለልቡ እንዳላስተማረ ።
*************************
አሰብኩት ከሆነ እንዲህ ለአትክልቱ
እንዴት መልካም ይሆን ለሚወዳት ሚስቱ "
ያለችውን ብርቱና ቸር ሰው ነው . . .
" ቢዘንብም ቢያካፋም ከጎኔ የማይጠፋ
እንደ ባለ አጸዱ ጽኑ ለመውደዱ
ሳላውቅህ ልንገርህ የነገ ውሀ አጣጬ
አርገኝ እንዳልከስም ፍቅርን ተጠምቼ "
እያለች ምኞቷን ፣ መሻቷን ፣ የወደፊት ህልሟን ትነግረናለች ። መልካምነት መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልንም ይፈልጋል ። ምርጥ ዘር ምርጥ አፈርንም ይፈልጋል ። በተዘራበት ሁሉ አይበቅልም ። እንደ እሷ የሚረዳ ካልተገኘ ሌሎቹ እንዳሉት " የማነው ሞኝ ? " ያስብላል ።
በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ የዚህ የወደድኩት ብርቱ አትክልተኛ ተቃራኒ ቢሆንም የእኔ ከ1ኛ - 3ኛ " ቻው ( ዎ ) " ነው ።
" አልነበረም ከዓይን የተሰወረ
መንገድህን ሳላየው መች ቀረ
ሰነባብቷል መንፈስህ ሸፍቷል
ልቤን ልብህ ቻው ካለው ቆይቷል ።
አልታወጀም እንጂ ፊትም የእኛ ነገር
የተለያየነው አብረን ሆነን ነበር ።
እንባዬ ተማጽኖህ እንዳያስታርቀን
ያለቀው ያኔ ነው ልብህ የሄደ ቀን ።
እያንዳንዱን ቀናት በእንባ እየሰፈርኩኝ
ቻው ስልህ ኖሬያለሁ እየሸራረፍኩኝ ።
ዛሬም ለበደልህ አረከኝ ጣል ጣል
ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል ። "
ይኽ መቸም በየፍቅር ጎጆው ፣ በየትዳር ማጀቱ ፣ በየጓደኝነቱና ወዳጅነቱ አደባባይ የሚታይ የወቅቱ እውነታ ነው ። በየግንኙነታችን " ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል " ። አብዛኛዎቻችን አንድ ላይ ቆመናል እንጂ አብረን አይደለንም ። " አንድ ላይ ብንሆንም ተለያይተናል " እንዳለው ድምጻዊው ። እግሮቻችን ብቻ አብረው ይጓዛሉ ፤ አካላችን አንድ ላይ ይታያል ፤ ነፍስ የሌለው ስጋ ነው ። አብረን ውለን እናድራለን ፤ በልባችን ግን ተለያይተናል ። አልታወቀን ይሆናል እንጂ እንደ ግልም ፣ እንደ ሀገርም እንዲህ ሆነናል ። ለዚህ ነው አሁን ያለንበት ላይ ያለነው ። ለዚህ ነው በየሰበቡ ሕይወት የሚታክተን ። ለዚህ ነው መኖር ትግል ፣ አብሮነት መተናነቅ የሚሆንብን ( የሆነብን ) ። የቤተልሔም ሸረፈዲን " ቻው " ለአንድ ተፈቃሪ ወንድ የተሰራም ቢሆን ሀሳቡ ግን እዚህ ድረስም የሚመጣ ነው ። ናቲ " ቃሉ ከዜማው ጋር ነው የመጣው " ያለውና ራሷን ድምጻዊቷን አስለቅሶ የተገለጠው " ቻው " ገና ብዙውን ልብ የሚነካ ስራ ይሆናል ።
" ልቤን " ን ላልወደው አስቤ ነበረ መሰለኝ ። የእድሜም ፣ የፍላጎትም ጉዳይ ሆኖ ፈጠን ላሉ ምቶች አልደነግጥ ሆኖ ይሆናል እንጂ ምን ሆኜ ነው ዜማው ፣ ምቱ ፣ በተለይ የድምጻዊቷ አዘፋፈን ከፍ ብሎ የታየበትን ይህን ስራ " ይቆየኝ " ያልኩት ? ባልወደውና ደጋግሜ ባልሰማው ይቆጨኝ ነበር ። ( ለነገሩ ካልወደድኩት ለምን ይቆጨኛል ? ) " ደስተኛ " ርዕስና ሀሳቡ ደስተኛ ካልሆነች ፣ " አልወድሽም " ከተባለችና ከተገፋች ገጸባህሪ የተገኘ ነው ። " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ትላለች ። " አልወድሽም " ተብላና " ብትጎዘጉዝ አበባ ዛሬ አይረባ " ያለች ሴት ራሷን ማታለል ሳይሆን " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ስትል ካዋጣትና ከተቻላት ያድርግላት ። ከእሷ እንባና የልብ ስብራት ምን ጉዳይ አለን ? ብቻ ከአፏ ሳይሆን ከልቧ ይሁን ።
" እንደ ውሀ መውረድ ፣ እንደ ጸሐይ መውጣት
እንደ ጊዜው መክነፍ ፣ እንደ አሸዋ መብዛት
እውነታ መሆኑን ቅንጣት ሳልጠረጥር
እኔስ አምነዋለሁ የልብህን ፍቅር "
ያለችበት " አካልዬ " ለረጋ ያለ ሙዚቃ አፍቃሪ ይሁነኝ ተብሎ የተቀመረ ስራ ነው ። በምርጤነት ከተቀበልኳቸው መካከል አንዱ ነው ።
አንደኛው ሙዚቃ አስተያየት መስጫ ውስጥ ገብቼ ሳነብ " የዚህ አልበም ትልቁ ችግሩ ውስጡ ያሉት ዘፈኖች 10 ብቻ መሆናቸው ነው " ሲል " አድናቆቱን " ገልጿል ። እኔም እንደዚያ ሆኖ ይሰማኛል ። ከአስሩ ሰባቱን ስራዎች በልዩ ሁኔታ ወድጃቸዋለሁ ። አንዱ የዋለልኩበትና ሁለቱ ደግሞ ልብ ያልሰጠኋቸው ናቸው ። ይህ በአንድ አለበም ውስጥ ከበቂ በላይ ስኬታማነት ነው ። ከብዙ ዓመት በኋላ ተሟልቶ ያገኙሁት ምርጤ ነው " ደስተኛ " አልበም ።
እዚህ አልበም ላይ ያለኝ አንድ ( ግላዊ ) ቅሬታ አስሩም ስራዎች የተቃራኒ ጾታ ፍቅር ላይ ብቻ ያተኮሩ መሆናቸው ነው ። እንዳይሆኑ የሚከለክል ደንብ የለም ። ፕሮዲዩሰሮቹ የቤተልሔምን እድሜና የፍቅር ጊዜዋን አስበው ያደረጉት ሊሆን ይችላል ። ያም ቢሆን በዚህ ውጥንቅጡ የወጣ የመከራ ጊዜ ፣ በብዙ ሰው ሰራሽና የአስተሳሰብ ሰንሰለት እግር ከወርች ታስረን መሔጃ ባጣንበት ዘመንና ሀገር ፣ ላለንበት ጊዜ ፣ ለስሜታችን ፣ ለህመማችን ፣ ለሰለለው ተስፋችን የሚሆን አንድ ስራ ልናጣ አይገባም ብዬ አስባለሁ ። ናቲና ምህረተአብ ለራሄል ጌቱ እንደሰጧት " ያገሬ ሰው " ያለ ስራ ቢመርቁልን እንዴት መልካም ነበረ ?
ከቀናት በፊት አስቴር አወቀ ( በድጋሚ ስራዎቿም ቢሆን ) በትንሿ ቤተልሔም ሸረፈዲን ላይ ተደርባ አልበሟን መልቀቋ አስፈርቶኝ ነበረ ። ይህን የመሰለ አልበም ፣ የ4 ዓመት የሚነገርና የማይነገር እልህ አስጨራሽ ድካም መና እንዳይቀር ሰግቼ ነበረ ። ስጋቴ ስጋት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ። ቤተልሔም የዋርካው ጥላ ሳያርፍባት አልፋለች ። ገና ገና ትቀጥላለች ፤ ትቀጣጠላለች ።
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ባለፈው ዓመት ታይቶ የነበረውን የዋጋ ማረጋጋት ሂደት በመቀልበስ፣ በ2026 የመጀመሪያ አጋማሽ በአፍሪካ ቀዳሚ የሚባሉ ኢኮኖሚዎች ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እያስተናገዱ መሆኑ ተገለጸ። ለዚህ የዋጋ ንረት ማገርሸት ዋነኛ ምክንያት የሆነው በመካከለኛው ምስራቅ (በተለይም በኢራን) ያለው ግጭት የዓለም የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋን ወደ 100 ዶላር እንዲጠጋ በማድረጉ ነው። አስር ዋና ዋና የአፍሪካ ኢኮኖሚዎችን ባካተተ ጥናት፣ ሁሉም ሀገራት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የዋጋ ግሽበት ጭማሪ አስመዝግበዋል። በዚህም ኢትዮጵያ በ4.1 በመቶ ጭማሪ ቀዳሚ ስትሆን፣ የሰኔ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቷ 13.9 በመቶ ደርሷል። የምግብ ዋጋ ንረቱም ወደ 15.1 በመቶ አሻቅቧል። ከኢትዮጵያ በመቀጠል ግብጽ፣ ኬንያ እና ጋና ከፍተኛ የዋጋ ንረት ያስመዘገቡ ሀገራት ሆነዋል።
ይህ ጂኦፖለቲካዊ ቀውስ የአፍሪካ ኢኮኖሚዎች ለውጫዊ የኃይል አቅርቦት እና የዋጋ መናወጥ ምን ያህል ተጋላጭ እንደሆኑ በድጋሚ ያጋለጠ ነው። የነዳጅ፣ የትራንስፖርት እና የምግብ ዋጋ መናር የሀገራቱን ማዕከላዊ ባንኮች የገንዘብ ፖሊሲያቸውን እንዲያጠብቁ (ለአብነት ያህል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወለድ መጠኑን ወደ 16 በመቶ እንዳሳደገው) ወይም የጀመሩትን የፖሊሲ ማላላት እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል። የዓለም ባንክ እንዳስጠነቀቀው፣ መንግስታት የተገደበ ሀብታቸውን ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመታደግ ካላዋሉ በስተቀር አሁን የተፈጠረው የማክሮ-ኢኮኖሚ ጫና አብዛኛውን ገቢውን ለምግብ እና ኢነርጂ በሚያውቀው ድሃው የህብረተሰብ ክፍል ላይ ከባድ ሸክም በመፍጠር ወደ ከፋ ማህበራዊ ቀውስ ሊያመራ ይችላል።
ይህ ጂኦፖለቲካዊ ቀውስ የአፍሪካ ኢኮኖሚዎች ለውጫዊ የኃይል አቅርቦት እና የዋጋ መናወጥ ምን ያህል ተጋላጭ እንደሆኑ በድጋሚ ያጋለጠ ነው። የነዳጅ፣ የትራንስፖርት እና የምግብ ዋጋ መናር የሀገራቱን ማዕከላዊ ባንኮች የገንዘብ ፖሊሲያቸውን እንዲያጠብቁ (ለአብነት ያህል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወለድ መጠኑን ወደ 16 በመቶ እንዳሳደገው) ወይም የጀመሩትን የፖሊሲ ማላላት እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል። የዓለም ባንክ እንዳስጠነቀቀው፣ መንግስታት የተገደበ ሀብታቸውን ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመታደግ ካላዋሉ በስተቀር አሁን የተፈጠረው የማክሮ-ኢኮኖሚ ጫና አብዛኛውን ገቢውን ለምግብ እና ኢነርጂ በሚያውቀው ድሃው የህብረተሰብ ክፍል ላይ ከባድ ሸክም በመፍጠር ወደ ከፋ ማህበራዊ ቀውስ ሊያመራ ይችላል።
13 days ago
"ታሪክ ይፈርዳል ሕዝብ ይመሰክራል እውነት ለዘላለም ይኖራል!"
#ethiopia | እኔ ለኢትዮጵያ የተወለድሁ በኢትዮጵያ ያደግሁ ለኢትዮጵያም ሕይወቴን ለመስጠት በቃልኪዳን የቆምኩ ኩሩ ወታደር ነበርኩ ።
ወታደርነት ዩኒፎርም መልበስ ወይም መሣሪያ መታጠቅ ብቻ አይደለም ። ወታደርነት ማለት የሀገርን ክብር በነፍስ መጠበቅ የሕዝብን ተስፋ በደም ማቆየት የነፃነትን አደራ በትውልድ ላይ ማስቀጠል ነው።
ወታደር ማለት ሀገር ነው።
ሀገር ደግሞ በካርታ ላይ የተሳለ ድንበር ወይም ዝም ያለ መሬት አይደለችም።
ሀገር ማለት የአባቶች አደራ የእናቶች እንባ የጀግኖች መስዋዕትነት የሕፃናት ፈገግታ የወጣቶች ሕልም የአረጋውያን ተስፋ እና የመጪው ትውልድ እጣ ፈንታ ናት።
ሀገር ማለት
• የሕዝቧ ዘላቂ ሰላምና ደህንነት
• የሕፃናት ያልተቋረጠ የነፃነት ሳቅ
• የእናቶች የልብ እፎይታ
• የወጣቶች ብሩህ ተስፋ
• በነፃነት የሚተነፈስ አየርና በፍትሕ የሚገነባ ነገ ናት።
እነዚህን ሁሉ ክቡር እሴቶች በደሙና በሕይወቱ ዋጋ የሚጠብቀው ወታደር ነው። ለእያንዳንዱ የሰላም ሰከንድ የማይታይ መስዋዕትነት አለ ከእያንዳንዱ የነፃነት ቀን ጀርባም የብዙ ጀግኖች ደምና ታሪክ ተጽፎበታል።
ዛሬም ሀገሬ ኢትዮጵያ በጠራችኝ ጊዜ ሁሉ ከፊት የመቆም ግዴታዬን እየተወጣሁ እገኛለሁ። በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ስለ ሰላም ስለ አብሮነት ስለ ሀገራችን ቀጣይነት ስለ ፍትሕና ልማት ስለ ትውልድ የሚተርፍ አንድነት ከወገኖቼ ጋር በኃላፊነትና በቅንነት እየተመካከርኩ ነው።
ዛሬ ሁላችንም በታሪክ ፊት ቆመናል።
በዚህ ወሳኝ ወቅት የምንናገረው ቃል የምንወስነው ውሳኔ የምንፈፅመው ተግባር በዘመናት መዝገብ ላይ ይቀረፃል።
ስለዚህ ከልዩነታችን በላይ የሚያስተሳስረንን ሀገራችንን እናስቀድማለን ።
ከጊዜያዊ ክርክር በላይ ዘላቂ ሰላምን እንመርጣለን ከመከፋፈል ይልቅ መተባበርን እናከብራለን።
የሕዝብን ተስፋ ለማደናቀፍ የመግባባትን መንፈስ ለማዳከም የሚሞክሩ ድምፆች ሊኖሩ ይችላሉ
ነገር ግን እውነት ከአሉባልታ ይበልጣል አንድነት ከመከፋፈል ይበረታል የሕዝብ ፍቅር ከጥላቻ ይልቃል።
እኛ ኢትዮጵያውያን ነን።
የልዩነታችን ውበት አንድነታችንን አያጠፋም ይልቁን ያጎለብተዋል።
ሰላምን በጽናት ፍትሕን በብልህነት ሀገርን በፍቅር እንገነባለን።
ለኢትዮጵያ የሕይወት ቃልኪዳን
"ሀገሬ ኢትዮጵያ ሆይ!
ለአንቺ የማልከፍለው ዋጋ የማልሰጥሽ ጥረት የማልከብርሽ ክብር የለም።
በጠራሽኝ ጊዜ ሁሉ በየትኛውም ስፍራና በየትኛውም ዘመን ለነፃነትሽ ለሰላምሽ ለአንድነትሽ እና ለክብርሽ እቆማለሁ።
ይህ የፖለቲካ ቃል አይደለም ።
የሕይወቴ ቃልኪዳን ነው።
ይህ የዛሬ ውሳኔ ብቻ አይደለም ። ለመጪው ትውልድ የተቀመጠ አደራ ነው።
አሉባልታ ይጠፋል
ውሸት ይደበዝዛል
ጊዜ ያልፋል
ነገር ግን የታሪክ እውነት የሕዝብ ፍቅር የሀገር ክብር እና የጀግኖች መስዋዕትነት ለዘላለም ይኖራሉ ።
ታሪክ በቃላት አይገነባም በመስዋዕትነት ይጻፋል።
ሀገር በምኞት አትፀናም በአንድነት ትቆማለች።
ሕዝብ በፍርሃት አያድግም በተስፋ ያብባል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር በልጆቿ ጥረት በልጆቿ አንድነት ለዘላለም ፀንታ ትኑር !
ለሐገሬና ለሕዝቤ የተገባ የሕይወት ቃልኪዳን ።
አለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ኢትዮጵያ)
#ethiopia | እኔ ለኢትዮጵያ የተወለድሁ በኢትዮጵያ ያደግሁ ለኢትዮጵያም ሕይወቴን ለመስጠት በቃልኪዳን የቆምኩ ኩሩ ወታደር ነበርኩ ።
ወታደርነት ዩኒፎርም መልበስ ወይም መሣሪያ መታጠቅ ብቻ አይደለም ። ወታደርነት ማለት የሀገርን ክብር በነፍስ መጠበቅ የሕዝብን ተስፋ በደም ማቆየት የነፃነትን አደራ በትውልድ ላይ ማስቀጠል ነው።
ወታደር ማለት ሀገር ነው።
ሀገር ደግሞ በካርታ ላይ የተሳለ ድንበር ወይም ዝም ያለ መሬት አይደለችም።
ሀገር ማለት የአባቶች አደራ የእናቶች እንባ የጀግኖች መስዋዕትነት የሕፃናት ፈገግታ የወጣቶች ሕልም የአረጋውያን ተስፋ እና የመጪው ትውልድ እጣ ፈንታ ናት።
ሀገር ማለት
• የሕዝቧ ዘላቂ ሰላምና ደህንነት
• የሕፃናት ያልተቋረጠ የነፃነት ሳቅ
• የእናቶች የልብ እፎይታ
• የወጣቶች ብሩህ ተስፋ
• በነፃነት የሚተነፈስ አየርና በፍትሕ የሚገነባ ነገ ናት።
እነዚህን ሁሉ ክቡር እሴቶች በደሙና በሕይወቱ ዋጋ የሚጠብቀው ወታደር ነው። ለእያንዳንዱ የሰላም ሰከንድ የማይታይ መስዋዕትነት አለ ከእያንዳንዱ የነፃነት ቀን ጀርባም የብዙ ጀግኖች ደምና ታሪክ ተጽፎበታል።
ዛሬም ሀገሬ ኢትዮጵያ በጠራችኝ ጊዜ ሁሉ ከፊት የመቆም ግዴታዬን እየተወጣሁ እገኛለሁ። በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ስለ ሰላም ስለ አብሮነት ስለ ሀገራችን ቀጣይነት ስለ ፍትሕና ልማት ስለ ትውልድ የሚተርፍ አንድነት ከወገኖቼ ጋር በኃላፊነትና በቅንነት እየተመካከርኩ ነው።
ዛሬ ሁላችንም በታሪክ ፊት ቆመናል።
በዚህ ወሳኝ ወቅት የምንናገረው ቃል የምንወስነው ውሳኔ የምንፈፅመው ተግባር በዘመናት መዝገብ ላይ ይቀረፃል።
ስለዚህ ከልዩነታችን በላይ የሚያስተሳስረንን ሀገራችንን እናስቀድማለን ።
ከጊዜያዊ ክርክር በላይ ዘላቂ ሰላምን እንመርጣለን ከመከፋፈል ይልቅ መተባበርን እናከብራለን።
የሕዝብን ተስፋ ለማደናቀፍ የመግባባትን መንፈስ ለማዳከም የሚሞክሩ ድምፆች ሊኖሩ ይችላሉ
ነገር ግን እውነት ከአሉባልታ ይበልጣል አንድነት ከመከፋፈል ይበረታል የሕዝብ ፍቅር ከጥላቻ ይልቃል።
እኛ ኢትዮጵያውያን ነን።
የልዩነታችን ውበት አንድነታችንን አያጠፋም ይልቁን ያጎለብተዋል።
ሰላምን በጽናት ፍትሕን በብልህነት ሀገርን በፍቅር እንገነባለን።
ለኢትዮጵያ የሕይወት ቃልኪዳን
"ሀገሬ ኢትዮጵያ ሆይ!
ለአንቺ የማልከፍለው ዋጋ የማልሰጥሽ ጥረት የማልከብርሽ ክብር የለም።
በጠራሽኝ ጊዜ ሁሉ በየትኛውም ስፍራና በየትኛውም ዘመን ለነፃነትሽ ለሰላምሽ ለአንድነትሽ እና ለክብርሽ እቆማለሁ።
ይህ የፖለቲካ ቃል አይደለም ።
የሕይወቴ ቃልኪዳን ነው።
ይህ የዛሬ ውሳኔ ብቻ አይደለም ። ለመጪው ትውልድ የተቀመጠ አደራ ነው።
አሉባልታ ይጠፋል
ውሸት ይደበዝዛል
ጊዜ ያልፋል
ነገር ግን የታሪክ እውነት የሕዝብ ፍቅር የሀገር ክብር እና የጀግኖች መስዋዕትነት ለዘላለም ይኖራሉ ።
ታሪክ በቃላት አይገነባም በመስዋዕትነት ይጻፋል።
ሀገር በምኞት አትፀናም በአንድነት ትቆማለች።
ሕዝብ በፍርሃት አያድግም በተስፋ ያብባል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር በልጆቿ ጥረት በልጆቿ አንድነት ለዘላለም ፀንታ ትኑር !
ለሐገሬና ለሕዝቤ የተገባ የሕይወት ቃልኪዳን ።
አለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ኢትዮጵያ)
Sponsored by
Surafel
14 days ago
በአንድ ጥያቄ ውስጥ የተደበቀው የኢትዮጵያ የአብሮነት ፍልስፍና
**********************
"እንዴት ሰንብታችኋል?" የሚለው ለኢትዮጵያውያን ከሰላምታ በላይ ትርጉም ያለው ቃል ነው። በዚህ ጥያቄ ውስጥ "ደህና ነህ?" የሚል ብቻ ሳይሆን፣ "ምን አጋጠመህ? እንዴት አለፍክ? ምን ልረዳህ?" የሚል የመተሳሰብ፣ የመደማመጥ እና የአብሮነት መንፈስ ተደብቆ ይገኛል።
በኢትዮጵያ ማኅበራዊ እሴት ውስጥ ጥያቄ ማለት መረጃ መፈለግ ብቻ አይደለም። ሰውን ማስታወስ፣ ሁኔታውን መረዳት፣ ችግሩን መስማት እና አብሮ መፍትሔ መፈለግም ጭምር ነው። ይህም የማኅበረሰባችንን የአብሮነት መሠረት ያንጸባርቃል።
እንዲሁ የሀገር ጉዳዮችም በአንድ ወገን ውሳኔ ሳይሆን፣ እርስ በርስ በመጠያየቅ፣ በመደማመጥ፣ በመከባበር እና በጋራ መፍትሔ በመፈለግ ዘላቂ መልስ ያገኛሉ። ስለዚህ የምክክር መንፈስ በውይይት አዳራሾች ብቻ የሚወለድ ሳይሆን፣ በየቤታችን፣ በየመንደራችንና በየዕለቱ በምንለው "እንዴት ሰንብታችኋል?" ውስጥ ለዘመናት ሲኖር የቆየ ማኅበራዊ እሴት ነው።
ከሐምሌ 8 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መድረክም ይህ የመደማመጥ መንፈስ በሰፊው ታይቷል። ከተለያዩ ክልሎች፣ ማኅበረሰቦች እና ሙያዎች የመጡ ተመካካሪዎች ሐሳባቸውን በመግለጽና ሌሎችን በማዳመጥ የጋራ መፍትሔ የሚፈለግበት መድረክ መፍጠር ተችሏል።
በዚሁም የሀገራዊ ምክክር መንፈስ ለኢትዮጵያ እንግዳ የሆነ አዲስ ሐሳብ ሳይሆን፣ በማኅበራዊ ባህላችን ውስጥ ለዘመናት የቆየ የመደማመጥና የመተሳሰብ እሴት ዘመናዊ መገለጫ ነው።
ይህ የተጻፈ ሕግ አልነበረም፤ ግን ከብዙ ሕጎች በላይ ሰዎችን ያስተሳሰረ የማኅበረሰብ ሥርዓት ነበር። የኢትዮጵያ ባህል ከሽማግሌ ሥርዓት እስከ ዕርቅ፣ ከጎረቤት መተጋገዝ እስከ ቤተሰብ ውይይት መጀመሪያ መጠየቅን፣ ማዳመጥን እና መረዳዳትን ያስቀድማል።
ዛሬም ኢትዮጵያ የምትፈልገው ይህንኑ መንፈስ ነው። መጀመሪያ መጠየቅ፣ ከዚያ ማዳመጥ፣ ከዚያ መረዳት፣ በመጨረሻም አብሮ መፍትሔ መፈለግ ለሀገር እድገት በአንድ ላይ መቆምን ያረጋግጣል።
የአንድ ሕዝብ የመተሳሰብና የመደማመጥ መጀመሪያ የሆነው የአብሮነት መሠረት ከተለያዩ የሐሳብ ልዩነቶች የሚመጣ ምክክር ነው።
ከሁሉም በላይ ደግሞ በኢትዮጵያውያን ዕለታዊ ሕይወት ውስጥ ለዘመናት የተገነባ የመተሳሰብና የምክክር ባህል ምልክት ነው።
ከብዙ ሺህ ቃላት በፊት አንድ ጥያቄ ነበር። ‘እንዴት ሰንብታችኋል?' የሚለው ጥያቄ! የኢትዮጵያውያንን የመተሳሰብ እና የመደማመጥ ባህልን በሚያሳይ አንድ ምሳሌ ነው።
በልዩ እሸቱ
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogue #culturalvalue #nationbuilding
**********************
"እንዴት ሰንብታችኋል?" የሚለው ለኢትዮጵያውያን ከሰላምታ በላይ ትርጉም ያለው ቃል ነው። በዚህ ጥያቄ ውስጥ "ደህና ነህ?" የሚል ብቻ ሳይሆን፣ "ምን አጋጠመህ? እንዴት አለፍክ? ምን ልረዳህ?" የሚል የመተሳሰብ፣ የመደማመጥ እና የአብሮነት መንፈስ ተደብቆ ይገኛል።
በኢትዮጵያ ማኅበራዊ እሴት ውስጥ ጥያቄ ማለት መረጃ መፈለግ ብቻ አይደለም። ሰውን ማስታወስ፣ ሁኔታውን መረዳት፣ ችግሩን መስማት እና አብሮ መፍትሔ መፈለግም ጭምር ነው። ይህም የማኅበረሰባችንን የአብሮነት መሠረት ያንጸባርቃል።
እንዲሁ የሀገር ጉዳዮችም በአንድ ወገን ውሳኔ ሳይሆን፣ እርስ በርስ በመጠያየቅ፣ በመደማመጥ፣ በመከባበር እና በጋራ መፍትሔ በመፈለግ ዘላቂ መልስ ያገኛሉ። ስለዚህ የምክክር መንፈስ በውይይት አዳራሾች ብቻ የሚወለድ ሳይሆን፣ በየቤታችን፣ በየመንደራችንና በየዕለቱ በምንለው "እንዴት ሰንብታችኋል?" ውስጥ ለዘመናት ሲኖር የቆየ ማኅበራዊ እሴት ነው።
ከሐምሌ 8 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መድረክም ይህ የመደማመጥ መንፈስ በሰፊው ታይቷል። ከተለያዩ ክልሎች፣ ማኅበረሰቦች እና ሙያዎች የመጡ ተመካካሪዎች ሐሳባቸውን በመግለጽና ሌሎችን በማዳመጥ የጋራ መፍትሔ የሚፈለግበት መድረክ መፍጠር ተችሏል።
በዚሁም የሀገራዊ ምክክር መንፈስ ለኢትዮጵያ እንግዳ የሆነ አዲስ ሐሳብ ሳይሆን፣ በማኅበራዊ ባህላችን ውስጥ ለዘመናት የቆየ የመደማመጥና የመተሳሰብ እሴት ዘመናዊ መገለጫ ነው።
ይህ የተጻፈ ሕግ አልነበረም፤ ግን ከብዙ ሕጎች በላይ ሰዎችን ያስተሳሰረ የማኅበረሰብ ሥርዓት ነበር። የኢትዮጵያ ባህል ከሽማግሌ ሥርዓት እስከ ዕርቅ፣ ከጎረቤት መተጋገዝ እስከ ቤተሰብ ውይይት መጀመሪያ መጠየቅን፣ ማዳመጥን እና መረዳዳትን ያስቀድማል።
ዛሬም ኢትዮጵያ የምትፈልገው ይህንኑ መንፈስ ነው። መጀመሪያ መጠየቅ፣ ከዚያ ማዳመጥ፣ ከዚያ መረዳት፣ በመጨረሻም አብሮ መፍትሔ መፈለግ ለሀገር እድገት በአንድ ላይ መቆምን ያረጋግጣል።
የአንድ ሕዝብ የመተሳሰብና የመደማመጥ መጀመሪያ የሆነው የአብሮነት መሠረት ከተለያዩ የሐሳብ ልዩነቶች የሚመጣ ምክክር ነው።
ከሁሉም በላይ ደግሞ በኢትዮጵያውያን ዕለታዊ ሕይወት ውስጥ ለዘመናት የተገነባ የመተሳሰብና የምክክር ባህል ምልክት ነው።
ከብዙ ሺህ ቃላት በፊት አንድ ጥያቄ ነበር። ‘እንዴት ሰንብታችኋል?' የሚለው ጥያቄ! የኢትዮጵያውያንን የመተሳሰብ እና የመደማመጥ ባህልን በሚያሳይ አንድ ምሳሌ ነው።
በልዩ እሸቱ
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogue #culturalvalue #nationbuilding
14 days ago
ከ700 በላይ የዓለም መሪዎችንና ፈጣሪዎችን የሚያሰባስበው ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው!
#fastmereja :- ታሪካዊው «የዓለም አቀፍ የሕዝቦች ጉባኤ አፍሪካ» (World Public Summit Africa) ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በዲፕሎማሲያዊቷ መዲና አዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የፈጠራ አውጪዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ የብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች እና የባህል መሪዎች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ይሳተፋሉ።
ጉባኤው በስፖርት አማካኝነት በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ከሚያቀራርበው የዓለም ዋንጫ ጋር በሚመሳሰል መልኩ፡ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አካላትን በማሰባሰብ በጋራ ሀሳብ የመለዋወጥ፣ ጠንካራ አጋርነቶችን የመፍጠር እና ለዓለማችን መሠረታዊ ኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊ፣ ማህበራዊ እና የልማት ጉዳዮች መፍትሔ የመፈለግ ዓላማን ማሰናዳቱን ተገልጿል።
ይህ ታላቅ መድረክ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ይህም አፍሪካ በዓለም አቀፍ የንግድ፣የፈጠራ፣ የዘላቂ ልማት፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ እና የሁለገብ ትብብር ውይይቶች ላይ ያላትን እየጎለበተ የመጣ ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅ እንደሆነ በመግለጫው ወቅት ተመላክቷል።
የጉባኤው ዋና ማዕከል ከሆኑት ዝግጅቶች አንዱ «አንድነት» (Unity) የተሰኘው ዓለም አቀፍ ዘመናዊ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን መሆኑን አዘጋጆቹ ጠቁመዋል።
ኤግዚቢሽኑ ከ16 የአፍሪካ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ካሜሩን፣ ኮንጎ ዲ/ሪ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ማዳጋስካር፣ ናሚቢያ፣ ናይጄሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሱዳን፣ ታንዛኒያ፣ ቱኒዚያ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ) የተጣጣሙ ታዋቂ አርቲስቶችን እንዲሁም የአፍሪካና የዳያስፖራውን ታሪካዊ ቁርኝት የሚያሳይ አፍሮ-ብራዚላዊ አርቲስትን ያሰባስባል።
በተጨማሪም «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሳይንሳዊ ጥናት የሚቀርብ ሲሆን፣ ጥናቱ ወንዙ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት (አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክ) እድገት ላይ ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ በስፋት እንደሚመረምር ነዉ የተገለፀዉ።
የጠቅላላው ምክር ቤት ሊቀመንበር አማካሪ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እንደገለፁት «አንድነት ማለት ወጥ መሆን ማለት አይደለም፤ ይልቁንም ለባህል ብዝሃነት ከሚሰጥ አክብሮት፣ ከእርስ በእርስ እምነት፣ ክፍትነት እና ለመደማመጥ ከሚኖር ፈቃደኝነት የሚወለድ መሆኑን ገልፀዉ ስለዚህም ጥበብ ልክ እንደ ስፖርት ሁሉ የሰው ልጅ የጋራ ቋንቋ እና የሕዝብ ዲፕሎማሲ መሣሪያ ነው። ቃላት ብቻቸውን ማሳካት በማይችሉበት ቦታ ሰዎችን ያቀራርባል።» ብለዋል።
የሰርቭ ግሎባል (Serve Global) ምክትል የሀገርውስጥ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ነጋሽ እንደገለፁት«ጉባኤው በንግድ ድርድር ላይ ሳይሆን አልሞ የተነሳና የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ ይጠርጋል።» ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ጉባኤ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል ዓለም አቀፍ የትብብር መድረክ አካል ሲሆን፣ ቀጣዩ ዓለም አቀፍ መድረክ በመስከረም ወር በሩሲያ ሞስኮ እንደሚካሄድ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እና ታሪኩ ነጋሽ ጨምረው አስታውቀዋል።
#fastmereja :- ታሪካዊው «የዓለም አቀፍ የሕዝቦች ጉባኤ አፍሪካ» (World Public Summit Africa) ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በዲፕሎማሲያዊቷ መዲና አዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የፈጠራ አውጪዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ የብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች እና የባህል መሪዎች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ይሳተፋሉ።
ጉባኤው በስፖርት አማካኝነት በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ከሚያቀራርበው የዓለም ዋንጫ ጋር በሚመሳሰል መልኩ፡ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አካላትን በማሰባሰብ በጋራ ሀሳብ የመለዋወጥ፣ ጠንካራ አጋርነቶችን የመፍጠር እና ለዓለማችን መሠረታዊ ኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊ፣ ማህበራዊ እና የልማት ጉዳዮች መፍትሔ የመፈለግ ዓላማን ማሰናዳቱን ተገልጿል።
ይህ ታላቅ መድረክ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ይህም አፍሪካ በዓለም አቀፍ የንግድ፣የፈጠራ፣ የዘላቂ ልማት፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ እና የሁለገብ ትብብር ውይይቶች ላይ ያላትን እየጎለበተ የመጣ ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅ እንደሆነ በመግለጫው ወቅት ተመላክቷል።
የጉባኤው ዋና ማዕከል ከሆኑት ዝግጅቶች አንዱ «አንድነት» (Unity) የተሰኘው ዓለም አቀፍ ዘመናዊ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን መሆኑን አዘጋጆቹ ጠቁመዋል።
ኤግዚቢሽኑ ከ16 የአፍሪካ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ካሜሩን፣ ኮንጎ ዲ/ሪ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ማዳጋስካር፣ ናሚቢያ፣ ናይጄሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሱዳን፣ ታንዛኒያ፣ ቱኒዚያ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ) የተጣጣሙ ታዋቂ አርቲስቶችን እንዲሁም የአፍሪካና የዳያስፖራውን ታሪካዊ ቁርኝት የሚያሳይ አፍሮ-ብራዚላዊ አርቲስትን ያሰባስባል።
በተጨማሪም «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሳይንሳዊ ጥናት የሚቀርብ ሲሆን፣ ጥናቱ ወንዙ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት (አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክ) እድገት ላይ ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ በስፋት እንደሚመረምር ነዉ የተገለፀዉ።
የጠቅላላው ምክር ቤት ሊቀመንበር አማካሪ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እንደገለፁት «አንድነት ማለት ወጥ መሆን ማለት አይደለም፤ ይልቁንም ለባህል ብዝሃነት ከሚሰጥ አክብሮት፣ ከእርስ በእርስ እምነት፣ ክፍትነት እና ለመደማመጥ ከሚኖር ፈቃደኝነት የሚወለድ መሆኑን ገልፀዉ ስለዚህም ጥበብ ልክ እንደ ስፖርት ሁሉ የሰው ልጅ የጋራ ቋንቋ እና የሕዝብ ዲፕሎማሲ መሣሪያ ነው። ቃላት ብቻቸውን ማሳካት በማይችሉበት ቦታ ሰዎችን ያቀራርባል።» ብለዋል።
የሰርቭ ግሎባል (Serve Global) ምክትል የሀገርውስጥ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ነጋሽ እንደገለፁት«ጉባኤው በንግድ ድርድር ላይ ሳይሆን አልሞ የተነሳና የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ ይጠርጋል።» ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ጉባኤ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል ዓለም አቀፍ የትብብር መድረክ አካል ሲሆን፣ ቀጣዩ ዓለም አቀፍ መድረክ በመስከረም ወር በሩሲያ ሞስኮ እንደሚካሄድ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እና ታሪኩ ነጋሽ ጨምረው አስታውቀዋል።
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የታወቁት የኢኮኖሚ ተንታኝ አቶ ክቡር ገና "Who Should Own Ethiopia’s Gold? The IMF’s Dangerous Advice" (የኢትዮጵያ ወርቅ የማን መሆን አለበት? የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት አደገኛ ምክር) በሚል ባወጡት አዲስ የሞጋች ሀሳብ ጽሑፍ፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከወርቅ ገበያ አሠራር በሂደት እንዲወጣ የሰጠውን ምክር በጥብቅ ተቃወሙ። ተንታኙ የብሔራዊ ባንክ ከወርቅ ገበያ መውጣት አገራዊ የኢኮኖሚ ልዑላኔንና የውጭ ምንዛሬ ማከማቸት አቅምን አደጋ ላይ የሚጥል አደገኛ አካሄድ እንደሆነ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በቅርቡ ባወጣው የብድር ክለሳ ሪፖርቱ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወርቅ ገበያ አሠራሩን ማሻሻልና በሂደት ከወርቅ ገበያ ገዢነት በሙሉ በመውጣት ቦታውን ለግል ንግድ ባንኮች መልቀቅ እንዳለበት አሳስቧል። አይ ኤም ኤፍ ይህን ያለው ማዕከላዊ ባንኮች መደበኛ የሸቀጥ ነጋዴ መሆን የለባቸውም በሚል የኢኮኖሚ ንድፈ-ሐሳብ መሠረት ቢሆንም፣ አቶ ክቡር ገና እንደሚሞግቱት ግን ይህ ምክር የበለጸጉና የዳበረ የፋይናንስ ሥርዓት ያላቸውን እንደ ስዊዘርላንድና ካናዳ ያሉ አገራትን ታሳቢ ያደረገ እንጂ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ውስጥ ለምትገኘው ኢትዮጵያ ፈጽሞ የማይሰራና አደገኛ ነው። ወርቅ ለኢትዮጵያ ተራ የንግድ ሸቀጥ ሳይሆን የአገሪቱን የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት የሚያጠናክር፣ አስፈላጊ የነዳጅና የመድኃኒት ግዢዎችን የሚሸፍን እና የአገሪቱን የፋይናንስ ሕልውና የሚያስጠብቅ ስልታዊ አገራዊ ሀብት ነው።
አይ ኤም ኤፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን በግል ንግድ ባንኮች ለመተካት የሚያቀርበው መሬት የማይነካ መላምት የግል ባንኮችን እና የብሔራዊ ባንክን መሠረታዊ ዓላማ ያላገናዘበ መሆኑንም ተንታኙ ያብራራሉ። የግል ንግድ ባንኮች የሚሰሩት ለባለአክሲዮኖቻቸው ትርፍ ለማብዛት ሲሆን፣ ቅድሚያ የሚሰጡትም ለወለድና ለአገልግሎት ክፍያ እንጂ ለአገራዊ የኢኮኖሚ ልማት አይደለም። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተቋቋመው የአገሪቱን ገንዘብ ዋጋ ለማስጠበቅ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ለማሳደግ እና የአገሪቱን የረጅም ጊዜ የልማት ፍላጎቶች ለማረጋገጥ በመሆኑ፣ የአገሪቱን ዋና የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ለግል ባንኮች አሳልፎ መስጠት አገራዊ የኢኮኖሚ ጥቅምንም አሳልፎ መስጠት ነው።
በተጨማሪም አይ ኤም ኤፍ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የወርቅ ዋጋ በላይ ጨምሮ ከአገር ውስጥ አምራቾች ወርቅ መግዛቱን እንደ ገበያ ማዛባት ቢነቅፈውም፣ አቶ ክቡር ገና ግን ይህ አሠራር ተግባራዊና አስፈላጊ መሆኑን ይሞግታሉ። ብሔራዊ ባንክ እየተወዳደረ ያለው ድበር ተሻጋሪ ከሆኑ የኮንትሮባንድ መረቦች ጋር በመሆኑ፣ ተጨማሪ ዋጋ ከፍሎ ወርቁን ወደ መደበኛው የሕግ አሠራር ማስገባት ካልቻለ አገሪቱ ወርቁንም፣ የውጭ ምንዛሬውንም ሆነ የታክስ ገቢዋን ሙሉ በሙሉ ታጣለች።
አቶ ክቡር ገና በጽሑፋቸው ማጠቃለያ ላይ እንዳሰመሩበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወርቅ ግዢ አሠራሩን ግልጽ ማድረግና ማዘመን አለበት እንጂ ከገበያው መውጣት የለበትም። ኢትዮጵያ አሁንም የውጭ ምንዛሬ እጥረት ያለባት፣ የኢንዱስትሪ ሽግግሯ ያልተጠናቀቀ እና የኢኮኖሚ ልዑላኔዋ በግንባታ ላይ ያለች አገር በመሆኗ፣ በዚህ ሁኔታ ውስጥ አገሪቱ ያላትን ብቸኛ ስልታዊ የወርቅ ሀብት ቁጥጥር አሳልፋ እንድትሰጥ የቀረበው የምክር ሀሳብ ልማታዊ ሳይሆን ወደኋላ ማፈግፈግ እንደሆነ በመግለጽ ደምድመዋል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በቅርቡ ባወጣው የብድር ክለሳ ሪፖርቱ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወርቅ ገበያ አሠራሩን ማሻሻልና በሂደት ከወርቅ ገበያ ገዢነት በሙሉ በመውጣት ቦታውን ለግል ንግድ ባንኮች መልቀቅ እንዳለበት አሳስቧል። አይ ኤም ኤፍ ይህን ያለው ማዕከላዊ ባንኮች መደበኛ የሸቀጥ ነጋዴ መሆን የለባቸውም በሚል የኢኮኖሚ ንድፈ-ሐሳብ መሠረት ቢሆንም፣ አቶ ክቡር ገና እንደሚሞግቱት ግን ይህ ምክር የበለጸጉና የዳበረ የፋይናንስ ሥርዓት ያላቸውን እንደ ስዊዘርላንድና ካናዳ ያሉ አገራትን ታሳቢ ያደረገ እንጂ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ውስጥ ለምትገኘው ኢትዮጵያ ፈጽሞ የማይሰራና አደገኛ ነው። ወርቅ ለኢትዮጵያ ተራ የንግድ ሸቀጥ ሳይሆን የአገሪቱን የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት የሚያጠናክር፣ አስፈላጊ የነዳጅና የመድኃኒት ግዢዎችን የሚሸፍን እና የአገሪቱን የፋይናንስ ሕልውና የሚያስጠብቅ ስልታዊ አገራዊ ሀብት ነው።
አይ ኤም ኤፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን በግል ንግድ ባንኮች ለመተካት የሚያቀርበው መሬት የማይነካ መላምት የግል ባንኮችን እና የብሔራዊ ባንክን መሠረታዊ ዓላማ ያላገናዘበ መሆኑንም ተንታኙ ያብራራሉ። የግል ንግድ ባንኮች የሚሰሩት ለባለአክሲዮኖቻቸው ትርፍ ለማብዛት ሲሆን፣ ቅድሚያ የሚሰጡትም ለወለድና ለአገልግሎት ክፍያ እንጂ ለአገራዊ የኢኮኖሚ ልማት አይደለም። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተቋቋመው የአገሪቱን ገንዘብ ዋጋ ለማስጠበቅ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ለማሳደግ እና የአገሪቱን የረጅም ጊዜ የልማት ፍላጎቶች ለማረጋገጥ በመሆኑ፣ የአገሪቱን ዋና የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ለግል ባንኮች አሳልፎ መስጠት አገራዊ የኢኮኖሚ ጥቅምንም አሳልፎ መስጠት ነው።
በተጨማሪም አይ ኤም ኤፍ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የወርቅ ዋጋ በላይ ጨምሮ ከአገር ውስጥ አምራቾች ወርቅ መግዛቱን እንደ ገበያ ማዛባት ቢነቅፈውም፣ አቶ ክቡር ገና ግን ይህ አሠራር ተግባራዊና አስፈላጊ መሆኑን ይሞግታሉ። ብሔራዊ ባንክ እየተወዳደረ ያለው ድበር ተሻጋሪ ከሆኑ የኮንትሮባንድ መረቦች ጋር በመሆኑ፣ ተጨማሪ ዋጋ ከፍሎ ወርቁን ወደ መደበኛው የሕግ አሠራር ማስገባት ካልቻለ አገሪቱ ወርቁንም፣ የውጭ ምንዛሬውንም ሆነ የታክስ ገቢዋን ሙሉ በሙሉ ታጣለች።
አቶ ክቡር ገና በጽሑፋቸው ማጠቃለያ ላይ እንዳሰመሩበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወርቅ ግዢ አሠራሩን ግልጽ ማድረግና ማዘመን አለበት እንጂ ከገበያው መውጣት የለበትም። ኢትዮጵያ አሁንም የውጭ ምንዛሬ እጥረት ያለባት፣ የኢንዱስትሪ ሽግግሯ ያልተጠናቀቀ እና የኢኮኖሚ ልዑላኔዋ በግንባታ ላይ ያለች አገር በመሆኗ፣ በዚህ ሁኔታ ውስጥ አገሪቱ ያላትን ብቸኛ ስልታዊ የወርቅ ሀብት ቁጥጥር አሳልፋ እንድትሰጥ የቀረበው የምክር ሀሳብ ልማታዊ ሳይሆን ወደኋላ ማፈግፈግ እንደሆነ በመግለጽ ደምድመዋል።
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) በሆሊውድ ዝነኛ የብሎክባስተር ፊልሞች "Godzilla vs. Kong" እና "Godzilla x Kong: The New Empire" ላይ “ጂያ” የተሰኘውን ቁልፍ ገጸ-ባህሪ በመወከል የምትታወቀው የ18 ዓመቷ መስማት የተሳናት ወጣት ተዋናይት ኬይሊ ሆትል ማክሰኞ ጠዋት በደረሰባት ድንገተኛ የመኪና አደጋ ሕይወቷ ማለፉን ፎክስ ኒውስ ዲጂታል አረጋግጧል።
የተዋናይቷ አባት ጆሹዋ ሆትል በሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ስለደረሰው አደጋ በሰጠውና በፌስቡክ በኩል ባስተላለፈው የ23 ደቂቃ የአሜሪካ የምልክት ቋንቋ (ASL) ቀጥታ ስርጭት መግለጫ፣ ልጁ ወደ ሆስፒታል በመጓዝ ላይ እያለች ልቧ መቆሙን በለቅሶ አስታውቋል። ከተከታታይ መስማት የተሳናቸው ትውልዶች በተገኘችውና የቨርጂኒያ ተወላጅ በሆነችው ኬይሊ ሆትል ሞት ሳቢያ መላው የሆሊውድ የኪነ-ጥበብ ማኅበረሰብ በከባድ ሐዘን ውስጥ ወድቋል።
ይህንን ልብ ሰባሪ ክስተት እና የተዋናይቷን አጭር የሕይወት ጉዞ በጥልቀት ስንመለከተው ኬይሊ በሆሊውድ ውስጥ በገንዘብና በጥቅም ብቻ በሚመራው የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ መስማት ለተሳናቸው አካላት እውነተኛና ተጨባጭ የውክልና መድረክ የፈጠረች ስልታዊ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆኗን ያሳያል። በ2021 ዓ.ም. “ጎድዚላ ቨርሰስ ኮንግ” በተሰኘው ታላቅ ፊልም ላይ ከግዙፉ “ኮንግ” ጋር ልዩ የልብ ትስስር ያላትን የጂያን ገጸ-ባህሪ ወክላ ስትወጣ፣ በሆሊውድ ታሪክ ውስጥ መስማት የተሳናቸው ተዋናዮች በትልልቅ የሳይንስ ልብወለድ ፊልሞች ላይ የመሪነት ሚና መጫወት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየች ድንቅ ተሰጥኦ ነበረች።
በ2024 ዓ.ም. በወጣው ሁለተኛው ፊልም ላይም የምልክት ቋንቋን በፊልሙ ውስጥ በስፋት በማስተዋወቅ የራሷን ደማቅ አሻራ አኑራለች።
በተጨማሪም፣ ኬይሊ ሆትል ወደ ትልቁ የፊልም ዓለም ከመግባቷ በፊትም ቢሆን በተለያዩ የንግድ ማስታወቂያዎችና የጥበቃ ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ መስማት ለተሳናቸው ማኅበረሰቦች እኩል ዕድል እንዲሰጥ ስትሟገት የቆየች የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ጭምር ነበረች። ምንም እንኳን ገና በለጋ ዕድሜዋ መክሰሟ እና በሲኒማው ዓለም የጀመረችው ደማቅ ጉዞ በአሰቃቂ የመኪና አደጋ በአጭር የተቀጨ ቢሆንም፣ በሆሊውድ ውስጥ ያሉ መስማት የተሳናቸው ወጣት ተዋናዮች የወደፊት ዕድል እንዲቀየርና ማግለል እንዲቆም ያደረገችው ተጋድሎ ግን ዘላቂ ውርስ ሆኖ የሚቀጥል መሆኑን የፊልም ኢንዱስትሪ ተንታኞች በጥብቅ ያመለክታሉ።
የተዋናይቷ አባት ጆሹዋ ሆትል በሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ስለደረሰው አደጋ በሰጠውና በፌስቡክ በኩል ባስተላለፈው የ23 ደቂቃ የአሜሪካ የምልክት ቋንቋ (ASL) ቀጥታ ስርጭት መግለጫ፣ ልጁ ወደ ሆስፒታል በመጓዝ ላይ እያለች ልቧ መቆሙን በለቅሶ አስታውቋል። ከተከታታይ መስማት የተሳናቸው ትውልዶች በተገኘችውና የቨርጂኒያ ተወላጅ በሆነችው ኬይሊ ሆትል ሞት ሳቢያ መላው የሆሊውድ የኪነ-ጥበብ ማኅበረሰብ በከባድ ሐዘን ውስጥ ወድቋል።
ይህንን ልብ ሰባሪ ክስተት እና የተዋናይቷን አጭር የሕይወት ጉዞ በጥልቀት ስንመለከተው ኬይሊ በሆሊውድ ውስጥ በገንዘብና በጥቅም ብቻ በሚመራው የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ መስማት ለተሳናቸው አካላት እውነተኛና ተጨባጭ የውክልና መድረክ የፈጠረች ስልታዊ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆኗን ያሳያል። በ2021 ዓ.ም. “ጎድዚላ ቨርሰስ ኮንግ” በተሰኘው ታላቅ ፊልም ላይ ከግዙፉ “ኮንግ” ጋር ልዩ የልብ ትስስር ያላትን የጂያን ገጸ-ባህሪ ወክላ ስትወጣ፣ በሆሊውድ ታሪክ ውስጥ መስማት የተሳናቸው ተዋናዮች በትልልቅ የሳይንስ ልብወለድ ፊልሞች ላይ የመሪነት ሚና መጫወት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየች ድንቅ ተሰጥኦ ነበረች።
በ2024 ዓ.ም. በወጣው ሁለተኛው ፊልም ላይም የምልክት ቋንቋን በፊልሙ ውስጥ በስፋት በማስተዋወቅ የራሷን ደማቅ አሻራ አኑራለች።
በተጨማሪም፣ ኬይሊ ሆትል ወደ ትልቁ የፊልም ዓለም ከመግባቷ በፊትም ቢሆን በተለያዩ የንግድ ማስታወቂያዎችና የጥበቃ ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ መስማት ለተሳናቸው ማኅበረሰቦች እኩል ዕድል እንዲሰጥ ስትሟገት የቆየች የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ጭምር ነበረች። ምንም እንኳን ገና በለጋ ዕድሜዋ መክሰሟ እና በሲኒማው ዓለም የጀመረችው ደማቅ ጉዞ በአሰቃቂ የመኪና አደጋ በአጭር የተቀጨ ቢሆንም፣ በሆሊውድ ውስጥ ያሉ መስማት የተሳናቸው ወጣት ተዋናዮች የወደፊት ዕድል እንዲቀየርና ማግለል እንዲቆም ያደረገችው ተጋድሎ ግን ዘላቂ ውርስ ሆኖ የሚቀጥል መሆኑን የፊልም ኢንዱስትሪ ተንታኞች በጥብቅ ያመለክታሉ።
18 days ago
ቅዱስ ሩፋኤል ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልለን፤ ምልጃ እና ረድኤቱም አይለየን🙏
ቊጥሩ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሲሆን፤ “ሩፋ” ማለት ሐኪም፤ ኤል ማለት እግዚአብሔር ማለት ሲኾን ሩፋኤል ማለት “እግዚአብሔር ሐኪሜ ነው” ማለት ነው፡፡
ቅዱስ ኤጲፋንዮስም በመጽሐፈ አክሲማሮስ “በራማ ሰማይ የሚገኘውን ሁለተኛውን ዐሥሩን ነገድ መናብርት ሲላቸው አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፤ እነዚህም ረቂቅ የሆነ የመብረቅ ጋሻ የእሳት ጦር ይዘው ከነፋስ ይልቅ የፈጠኑ ሲሆኑ በራማ በሁለተኛው ክፍል ላይ አስፍሯቸዋል፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል ነገደ መናብርት የሚባሉትን ራማ በሚባለው ሰማይ የሚኖሩትን ነገደ መላእክት የሚመራቸው ናቸው፡፡ አባ ጊዮርጊስም በሰዓታቱ “ጽርሐ አርያም አዳራሹ፤ የትጉሃን መኖሪያ ቦታው የሚኾን እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ ተብሎ በአንድነት በሦስትነት ይመሰገናል፤ ካህናተ ሰማይ በዙሪያው ይቆማሉ፤ በዙፋኑ ፊት እየሰገዱ አክሊሎቻቸውን ያወርዳሉ፤ እሳትነቱ በሚበርቅ፣ በሚል ጊዜ እንዳይመታቸው ይንቀጠቀጣሉ” ይላል፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል ከሚመራው ከዚህ ነገድ 24ቱ ካህናተ ሰማይ ወጥተዋል፡፡” ይለናል፡፡ በመጽሐፈ ሄኖክ 6÷3 ላይም “በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” ተብሏል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ባስልዮስም “በፊቱ የሚቆሙ የመላእክት ሰራዊትም ሁሉ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ የመላእክት አለቆችም ለማይታይ ለባለዚህ ስም ዘንበል ብለው ይሰግዳሉ፤ ዙፋኑን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ ዕጣንን የተመሉ የወርቅ ማዕጠንት በእጆቻቸው ያለ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ይኸውም የቅዱሳን ጸሎት ነው እስከ ዘላለሙ ሕያው በሆነው ፊት የሚቀበለው መሥዋዕት አድርገው ወደ ላይ ያሳርጋሉ” በማለት አስተምሯል፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል ፈታሔ ማኀፀን ወሰፋድል። መወለድ መንፈሳዊ። ወሐኪም ሰማያዊ ይባላል። የወላድ ማኀፀን እንዲፈታ በእግዚአብሔር ስለተሾመ አዋላጅ ብትኖርም ባትኖርም ቅዱስ ሩፋኤል በዚያ አይታጣም፡፡ በተለይ በባላገር ያሉ ሴቶች በምጥ ጊዜ ሁሉ መልክአ ሩፋኤል በአንገታቸው ያነግታሉ፣ ይጸልያሉ፣ የተጸለየበትንም ጸበል ይጠጣሉ፤ በፍጥነትም ይወልዳሉ። በየወሩ በ13 ቀን መታሰቢያ በዓሉ የሚከበር ሲሆን ጳጉሜ 3 ደግሞ ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል በረከትና ረድኤቱ አይለየን፤ ምልጃው ይጠብቀን፡፡ ገዳማውያንም ይህን ተራዳኢነቱን በመታመን ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሩታል፡፡ ገዳማቸውን በመደገፍና በዓታቸውን በማጽናት የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ቊጥሩ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሲሆን፤ “ሩፋ” ማለት ሐኪም፤ ኤል ማለት እግዚአብሔር ማለት ሲኾን ሩፋኤል ማለት “እግዚአብሔር ሐኪሜ ነው” ማለት ነው፡፡
ቅዱስ ኤጲፋንዮስም በመጽሐፈ አክሲማሮስ “በራማ ሰማይ የሚገኘውን ሁለተኛውን ዐሥሩን ነገድ መናብርት ሲላቸው አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፤ እነዚህም ረቂቅ የሆነ የመብረቅ ጋሻ የእሳት ጦር ይዘው ከነፋስ ይልቅ የፈጠኑ ሲሆኑ በራማ በሁለተኛው ክፍል ላይ አስፍሯቸዋል፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል ነገደ መናብርት የሚባሉትን ራማ በሚባለው ሰማይ የሚኖሩትን ነገደ መላእክት የሚመራቸው ናቸው፡፡ አባ ጊዮርጊስም በሰዓታቱ “ጽርሐ አርያም አዳራሹ፤ የትጉሃን መኖሪያ ቦታው የሚኾን እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ ተብሎ በአንድነት በሦስትነት ይመሰገናል፤ ካህናተ ሰማይ በዙሪያው ይቆማሉ፤ በዙፋኑ ፊት እየሰገዱ አክሊሎቻቸውን ያወርዳሉ፤ እሳትነቱ በሚበርቅ፣ በሚል ጊዜ እንዳይመታቸው ይንቀጠቀጣሉ” ይላል፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል ከሚመራው ከዚህ ነገድ 24ቱ ካህናተ ሰማይ ወጥተዋል፡፡” ይለናል፡፡ በመጽሐፈ ሄኖክ 6÷3 ላይም “በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” ተብሏል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ባስልዮስም “በፊቱ የሚቆሙ የመላእክት ሰራዊትም ሁሉ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ የመላእክት አለቆችም ለማይታይ ለባለዚህ ስም ዘንበል ብለው ይሰግዳሉ፤ ዙፋኑን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ ዕጣንን የተመሉ የወርቅ ማዕጠንት በእጆቻቸው ያለ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ይኸውም የቅዱሳን ጸሎት ነው እስከ ዘላለሙ ሕያው በሆነው ፊት የሚቀበለው መሥዋዕት አድርገው ወደ ላይ ያሳርጋሉ” በማለት አስተምሯል፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል ፈታሔ ማኀፀን ወሰፋድል። መወለድ መንፈሳዊ። ወሐኪም ሰማያዊ ይባላል። የወላድ ማኀፀን እንዲፈታ በእግዚአብሔር ስለተሾመ አዋላጅ ብትኖርም ባትኖርም ቅዱስ ሩፋኤል በዚያ አይታጣም፡፡ በተለይ በባላገር ያሉ ሴቶች በምጥ ጊዜ ሁሉ መልክአ ሩፋኤል በአንገታቸው ያነግታሉ፣ ይጸልያሉ፣ የተጸለየበትንም ጸበል ይጠጣሉ፤ በፍጥነትም ይወልዳሉ። በየወሩ በ13 ቀን መታሰቢያ በዓሉ የሚከበር ሲሆን ጳጉሜ 3 ደግሞ ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል በረከትና ረድኤቱ አይለየን፤ ምልጃው ይጠብቀን፡፡ ገዳማውያንም ይህን ተራዳኢነቱን በመታመን ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሩታል፡፡ ገዳማቸውን በመደገፍና በዓታቸውን በማጽናት የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
20 days ago
በኒው ዮርክ ታይምስ በምርጥ ሽያጭ የተመዘገበ መጽሐፍ!
#ethiopia | Speak በተሰኘው ታዋቂ ልብወለድ ወግ የተጻፈው ይህ ድንቅ የመጀመሪያ ልብወለድ፣ አንዲት ወጣት ከከባድ የጾታዊ ጥቃት በኋላ እንዴት የመቋቋም ኃይልን እንደምታገኝ የሚያስደንቅ ታሪክ ይነግራል።
ኤደን ሁልጊዜ ጥሩ ልጅ ሆና መኖርን ትወድ ነበር። ወደ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መግባቷም ያንን ባህሪዋን አልቀየረውም። ነገር ግን የወንድሟ የቅርብ ጓደኛ በጾታዊ ጥቃት ባደረሰባት ሌሊት፣ ሕይወቷ ፈጽሞ ተገልብጦ ይሄዳል።
ቀድሞ ቀላል የነበሩ ነገሮች ውስብስብ ይሆናሉ፤ የምትወዳቸውን ሰዎችና ነገሮች መጥላት ትጀምራለች። እውነት ብላ ያመነችው ሁሉ ውሸት ይመስላታል። ምንም ነገር ትርጉም አይሰጣትም። የደረሰባትን ለሌሎች መንገር እንዳለባት ብታውቅም፣ መናገር አትችልም። ስለዚህ ሁሉንም በውስጧ ትቀብራለች፤ ከዚያም ቀድሞ የነበረችውን ራሷንም ከዚያው ጋር ትቀብራለች።
መጽሐፉ በአራት ክፍሎች—የመጀመሪያ፣ የሁለተኛ፣ የሦስተኛ እና የአራተኛ ዓመት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት—ተከፍሎ የቀረበ ሲሆን፣ የጭንቀትና የስነልቦና ቁስሎች ምን ያህል ጥልቅ እንደሚሆኑ ያሳያል።
በተመሳሳይ ጊዜም አንዲት ወጣት በወጣትነት ዘመኗ የሚገጥሟትን ህመሞች፣ የመጀመሪያ ፍቅርና የመጀመሪያ ልብ ስብራት፣ የሚፈርሱና እንደገና የሚገነቡ ጓደኝነቶችን እየተሻገረች፣ በልቧ ውስጥ ተደብቆ የነበረውን የመትረፍና የመቋቋም አስደናቂ ኃይል እንዴት እንደምታገኘው በአስደናቂ ሁኔታ ያሳያል።
የመጽሐፍ ጀርባ ( book blurb )
በዚህ ምሽት፤ ቤተሰብ ተሰብስብን እያወጋን ነው። ይህንን መጽሐፍ ተስፈንጥራ የምታነብ ነፍስ የተመረጠች ናት።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | Speak በተሰኘው ታዋቂ ልብወለድ ወግ የተጻፈው ይህ ድንቅ የመጀመሪያ ልብወለድ፣ አንዲት ወጣት ከከባድ የጾታዊ ጥቃት በኋላ እንዴት የመቋቋም ኃይልን እንደምታገኝ የሚያስደንቅ ታሪክ ይነግራል።
ኤደን ሁልጊዜ ጥሩ ልጅ ሆና መኖርን ትወድ ነበር። ወደ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መግባቷም ያንን ባህሪዋን አልቀየረውም። ነገር ግን የወንድሟ የቅርብ ጓደኛ በጾታዊ ጥቃት ባደረሰባት ሌሊት፣ ሕይወቷ ፈጽሞ ተገልብጦ ይሄዳል።
ቀድሞ ቀላል የነበሩ ነገሮች ውስብስብ ይሆናሉ፤ የምትወዳቸውን ሰዎችና ነገሮች መጥላት ትጀምራለች። እውነት ብላ ያመነችው ሁሉ ውሸት ይመስላታል። ምንም ነገር ትርጉም አይሰጣትም። የደረሰባትን ለሌሎች መንገር እንዳለባት ብታውቅም፣ መናገር አትችልም። ስለዚህ ሁሉንም በውስጧ ትቀብራለች፤ ከዚያም ቀድሞ የነበረችውን ራሷንም ከዚያው ጋር ትቀብራለች።
መጽሐፉ በአራት ክፍሎች—የመጀመሪያ፣ የሁለተኛ፣ የሦስተኛ እና የአራተኛ ዓመት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት—ተከፍሎ የቀረበ ሲሆን፣ የጭንቀትና የስነልቦና ቁስሎች ምን ያህል ጥልቅ እንደሚሆኑ ያሳያል።
በተመሳሳይ ጊዜም አንዲት ወጣት በወጣትነት ዘመኗ የሚገጥሟትን ህመሞች፣ የመጀመሪያ ፍቅርና የመጀመሪያ ልብ ስብራት፣ የሚፈርሱና እንደገና የሚገነቡ ጓደኝነቶችን እየተሻገረች፣ በልቧ ውስጥ ተደብቆ የነበረውን የመትረፍና የመቋቋም አስደናቂ ኃይል እንዴት እንደምታገኘው በአስደናቂ ሁኔታ ያሳያል።
የመጽሐፍ ጀርባ ( book blurb )
በዚህ ምሽት፤ ቤተሰብ ተሰብስብን እያወጋን ነው። ይህንን መጽሐፍ ተስፈንጥራ የምታነብ ነፍስ የተመረጠች ናት።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ኢቦኒ መፅሄት ‹‹ልእልት ኤሊያና ሮዝ መኮንን አንድ አመት ሞላት›› ብሏል፡፡ በመፅሄቱ ዘገባ መሰረት ይህች ህፃን ዛሬ ጁላይ 17 ቀን የመጀመሪያ ልደቷን እያከበረች ትገኛለች፡፡ ህፃኗ የልእልት ኤድና ተፈሪ መኮንን እና ጀማል ሮቢንሰን ልጅ ናት፡፡ ይህም ማለት የኢትዮጵያ የመጨረሻው ንጉስ አፄ ሀይለስላሴ የልጅ ልጅ ልጅ ያደርጋታል፡፡ እናቷ ኤድና የልኡል ራስ ተፈሪ መኮንንና የልእልት አስቴር አብተው ልጅ ናት፡፡
ኤድና ለመፅሄቱ በሰጠችው መግለጫ ‹‹ልጄን ካየሁበት እለት አንስቶ ስሜቴን በቃላት ልገልፀው አልችልም፡፡ የእሷን መምጣት ለረጅም ጊዜ በፀሎት ስንጠባበቅ ነበር›› ያለች ሲሆን ያለፉትን 365 ቀናት መላ ቤተሰቡ ደስተኛ መሆኑን አስረድታለች፡፡ እንደገለፀችውም የኤሊያና ወደዚህ አለም መምጣት ከእሷ ህይወት ጋር ያመሳስለዋል፡፡ ምክንያቱም በወላጆቿ ውስጥ ብቸኛዋ ሴት በመሆኗ ስትወለድ ቤተሰቦቿ በጣም ደስተኛ ለመሆን ችለው ነበር፡፡
እንደዘገባው እናቷ ልእልት አስቴር ወደቤተሰቡ ለተቀላቀለችው የልጅ ልጃቸው ልደት ልዩ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ ይህ ስጦታም ኤድና በህፃንነቷ ስታደርጋቸው የነበሩት ልብሶች ናቸው፡፡ ኤድና ስትናገር ‹‹እናቴ እነዚህን በህፃንነቴ ሳደርጋቸው የነበሩትን ቀሚሶች የት እንዳስቀመጠቻቸው አላውቅም ነበር፡፡ እነዚህን ልብሶች አንዳንዶቹን በቪዲዮ አይቻቸዋለሁ፡፡ ነገር ግን አላስታውሳቸውም›› በማለት ገልፃ በእናቷ ‹‹ሰርፕራይዝ›› መደረጓን አስታውቃለች፡፡
ኤድና ለመፅሄቱ በሰጠችው መግለጫ ‹‹ልጄን ካየሁበት እለት አንስቶ ስሜቴን በቃላት ልገልፀው አልችልም፡፡ የእሷን መምጣት ለረጅም ጊዜ በፀሎት ስንጠባበቅ ነበር›› ያለች ሲሆን ያለፉትን 365 ቀናት መላ ቤተሰቡ ደስተኛ መሆኑን አስረድታለች፡፡ እንደገለፀችውም የኤሊያና ወደዚህ አለም መምጣት ከእሷ ህይወት ጋር ያመሳስለዋል፡፡ ምክንያቱም በወላጆቿ ውስጥ ብቸኛዋ ሴት በመሆኗ ስትወለድ ቤተሰቦቿ በጣም ደስተኛ ለመሆን ችለው ነበር፡፡
እንደዘገባው እናቷ ልእልት አስቴር ወደቤተሰቡ ለተቀላቀለችው የልጅ ልጃቸው ልደት ልዩ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ ይህ ስጦታም ኤድና በህፃንነቷ ስታደርጋቸው የነበሩት ልብሶች ናቸው፡፡ ኤድና ስትናገር ‹‹እናቴ እነዚህን በህፃንነቴ ሳደርጋቸው የነበሩትን ቀሚሶች የት እንዳስቀመጠቻቸው አላውቅም ነበር፡፡ እነዚህን ልብሶች አንዳንዶቹን በቪዲዮ አይቻቸዋለሁ፡፡ ነገር ግን አላስታውሳቸውም›› በማለት ገልፃ በእናቷ ‹‹ሰርፕራይዝ›› መደረጓን አስታውቃለች፡፡
22 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የዘመናችን ታላቁ የእግር ኳስ ጠበብት እና በባርሴሎና የቀኝ መስመር ላይ የክብሩ ወራሽ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው ድንቁ ወጣት... እሁድ ዕለት አርጀንቲና ከስፔን በሚያደርጉት የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት ይፋጠጣሉ። ሊዮኔል ሜሲ በ39 ዓመቱ፣ ላሚን ያማል ደግሞ ገና በ19 ዓመቱ በዚህ ታላቅ የእግር ኳስ መድረክ ላይ መገናኘታቸው፣ የሜሲን አስደናቂ ጽናት እና የያማልን ልዩ የተፈጥሮ ተሰጥኦ በግልጽ የሚያሳይ ነው።
ይሁን እንጂ የሁለቱ ተጫዋቾች መንገድ ሲገናኝ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ አይደለም። ጊዜው እ.ኤ.አ 2007 ነበር፤ የ20 ዓመቱ ወጣት ሊዮኔል ሜሲ በባርሴሎና ዋናው ቡድን ውስጥ ቋሚ ተሰላፊ መሆን በጀመረበት በዚያን ወቅት፣ ላሚን ያማል ገና የ5 ወር ጡት ጠባቂ ሕፃን ነበር። ይህን አስገራሚ ታሪካዊ አጋጣሚ በካሜራው ሌንስ ያስቀረው ፎቶግራፍ አንሺ ጆአን ሞንፎርት ነው። ፎቶግራፎቹ ከሁለት ዓመት በፊት ያማል ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር ዩሮ 2024ን ሲያነሳ፣ አባቱ «የሁለት ጀግኖች ጅማሮ» በሚል ጽሑፍ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እስካጋራው ጊዜ ድረስ ተዘንግተው ቆይተው ነበር። በምስሉ ላይ ፊቱ በፈገግታ የተሞላው ሜሲ፣ ከዓመታት በኋላ የእሱን የእግር ኳስ ፈለግ በጥብቅ የሚከተለውን አንድ ትንሽ ሕፃን በውሃ ገንዳ ውስጥ እያጠበና እያጫወተ ይታያል።
ፎቶግራፍ አንሺው ጆአን ሞንፎርትሲናገር "...ይህ እውነተኛ የዕጣ ፈንታ ተአምር ነው" ይለዋል። "ይህን ታሪክ ለፊልም ጽሑፍ ብታቀርበው እንኳን አሳማኝ አይሆንም። ከምትገምተው በላይ እጅግ ልዩ የሆነ ነገር ስታገኝ የሚሰማህ ስሜት ነው" በማለት ይገልጸዋል።
የፎቶግራፍ መነሳቱ መርሃ ግብር የተከናወነው በባርሴሎናው ካምፕ ኑ ስታዲየም የመልበሻ ክፍል ውስጥ ነበር። የያማል ቤተሰቦች በወቅቱ እዚያ ሊገኙ የቻሉት በእጣ አሸናፊነት ነው። ትውልደ ሞሮኳዊው አባቱ ሙኒር ናስራውይ እና ኢኳቶሪያል ጊኒያዊቷ እናቱ ሺላ ኢባና፣ በልጅነታቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ካታሎንያ ከመጡ በኋላ ነበር የተዋወቁት። ላሚን ያማል የመጀመሪያ ልጃቸው ሲሆን፣ እሱ በተወለደበት ወቅት የካታላኑ ስፖርት ጋዜጣ ከባርሴሎና ማሊያ ስፖንሰር ዩኒሴፍ (Unicef) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት የእጣ ውድድር ላይ ተሳትፈው አሸናፊ ሆኑ። የውድድሩ አሸናፊዎች ከባርሴሎና ዋናው ቡድን ተጫዋች ጋር የልጃቸውን ፎቶግራፍ በሙያዊ መንገድ የማንሳት ዕድል ያገኛሉ። የያማል ቤተሰቦች በዕለቱ ስታዲየም ሲደርሱ፣ በዕጣ ፈንታ ከሊዮኔል ሜሲ ጋር እንዲነሱ ተመደቡ።
ፎቶግራፍ አንሺው ሞንፎርት ያንን ቀን ሲያስታውስ፣ "ሜሲ በጣም አይን አፋር እና ዝምተኛ ልጅ ነው። ወደ መልበሻ ክፍሉ ገብቶ በድንገት ከዚህ ሕፃን ጋር ፎቶ መነሳት እንዳለበት ሲነገረው፣ ሕፃኑን ምን እንደሚያደርገው ግራ ገብቶት ፊቱ ተለዋውጦ ነበር" ይላል። "ለአንድ ወጣት ልጅ ከባድ ቢሆንም፣ ላሚን ግን በጣም ደስተኛ እና ፈገግታ የማያጣ ሕፃን ነበር። እናቱ ሺላም ታግዘን ነበር፤ በጣም ደሀ ቤተሰቦች ቢሆኑም አብሮ ለመስራት እጅግ ጥሩ ሰዎች ነበሩ። ሜሲ እንዲህ ባሉ ነገሮች ላይ ሁልጊዜም ፕሮፌሽናል ስለሆነ፣ ከሁኔታው ጋር ቶሎ ተላመደ።"
ላሚን ያማል ሰኞ ዕለት 19ኛ ዓመቱን ሲያከብር፣ አስገራሚ የእግር ኳስ ጉዞን አስመዝግቧል። ሜሲ 19 ዓመት ሲሞላው 11 የክለብ ግቦችን አስቆጥሮ አንድ የላሊጋ እና አንድ የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አሸንፎ ነበር። ያማል ግን በአንጻሩ 56 ግቦችን ከመረብ አሳርፎ፣ ሦስት የላሊጋ ዋንጫዎችን፣ አንድ የኮፓ ዴል ሬይ እና የዩሮ 2024 ዋንጫን ማንሳት ችሏል።
የሚገርመው ነገር «ያማል» የልጁ የአባት ስም ሳይሆን፣ ሁለተኛው መጠሪያ ስሙ መሆኑ ነው። ሙሉ ስሙ ላሚን ያማል ናስራውይ ኢባና ሲሆን፣ በማሊያው ጀርባ ላይ የሚጠቀመው የመጀመሪያዎቹን ሁለት ስሞቹን ነው። ይህ የሆነበት ምክንያት ደግሞ፣ እሱ በሚወለድበት ወቅት ቤተሰቡ በከፍተኛ የገንዘብ ችግር ውስጥ ወድቆ በነበረበት ሰዓት የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉላቸው ሁለት የቅርብ ወዳጆቻቸው ክብር ሲሉ አባቱ ቃል በገባው መሠረት የተሰየመ ነው።
በአረብኛ «ላሚን» ማለት ታማኝ ማለት ሲሆን፣ «ያማል» ደግሞ የጀማል ሌላኛው አጠራር ሆኖ ውበት ወይም ግርማ ሞገስ ማለት ነው። ያማል ባስቆጠራቸው ግቦች ላይ በጣቶቹ «3-0-4» የሚል ምልክት በማሳየት ደስታውን ይገልጻል፤ ይህ ደግሞ ያደገበትንና ከባርሴሎና 20 ማይል ርቃ የምትገኘውን የሮካፎንዳ ሰፈር የፖስታ ኮድ የሚያመላክት ነው። ያማል ስለ ቤተሰቦቹ ሲናገር... "ወላጆቼ ያደረጉልኝን ነገር እኔ ልጄ ላልሆነ ሰው ማድረግ አልችልም። ገንዘብ ከሌለህ ልጅህ እግር ኳስ እንዲጫወት መርዳት በጣም ከባድ ነው፤ ወላጆቼ ግን ይህን ሁሉ አሳክተዋል። ውለታቸውን መቼም ልመልስላቸው አልችልም" ብሏል።
ለካታላኑ እና የባርሴሎና ደጋፊ ለሆነው ፎቶግራፍ አንሺ ሞንፎርት፣ የሁለቱ ተጫዋቾች በዓለም ዋንጫ የፍጻሜ መድረክ ላይ መገናኘት ከሁለት አሥርት ዓመታት በፊት ለጀመረው ታሪክ ፍጹም ማሳረጊያ ነው። የ58 ዓመቱ ሞንፎርት፣ "የታሪካቸውን ዑደት እየዘጋን ይመስለኛል፤ አስደሳች ፍጻሜ ነው። እኔ የባርሴሎና ደጋፊ ነኝ፤ ለሜሲ የእግር ኳስ ህይወቱን ሁለተኛውን የዓለም ዋንጫ በማንሳት ቢያጠናቅቅ ፍጹም ይገባዋል እላለሁ። ላሚን ደግሞ ገና ወደፊት የዓለም ዋንጫን የሚያነሳበት ብዙ ጊዜ አለው። ነገር ግን ስፔን እና ላሚን አሁን በጥሩ ሞራል ላይ ይገኛሉ፤ ይህንን ዋንጫ ቢያነሳ ከሌሎች ክብሮቹ ሁሉ የላቀ ይሆናል። ስለዚህ ምርጫው ለእኔ በጣም ከባድ ነው፤ ልቤ ለሁለት እየተሰነጠቀ ነው" በማለት ስሜቱን ገልጿል።
ይሁን እንጂ የሁለቱ ተጫዋቾች መንገድ ሲገናኝ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ አይደለም። ጊዜው እ.ኤ.አ 2007 ነበር፤ የ20 ዓመቱ ወጣት ሊዮኔል ሜሲ በባርሴሎና ዋናው ቡድን ውስጥ ቋሚ ተሰላፊ መሆን በጀመረበት በዚያን ወቅት፣ ላሚን ያማል ገና የ5 ወር ጡት ጠባቂ ሕፃን ነበር። ይህን አስገራሚ ታሪካዊ አጋጣሚ በካሜራው ሌንስ ያስቀረው ፎቶግራፍ አንሺ ጆአን ሞንፎርት ነው። ፎቶግራፎቹ ከሁለት ዓመት በፊት ያማል ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር ዩሮ 2024ን ሲያነሳ፣ አባቱ «የሁለት ጀግኖች ጅማሮ» በሚል ጽሑፍ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እስካጋራው ጊዜ ድረስ ተዘንግተው ቆይተው ነበር። በምስሉ ላይ ፊቱ በፈገግታ የተሞላው ሜሲ፣ ከዓመታት በኋላ የእሱን የእግር ኳስ ፈለግ በጥብቅ የሚከተለውን አንድ ትንሽ ሕፃን በውሃ ገንዳ ውስጥ እያጠበና እያጫወተ ይታያል።
ፎቶግራፍ አንሺው ጆአን ሞንፎርትሲናገር "...ይህ እውነተኛ የዕጣ ፈንታ ተአምር ነው" ይለዋል። "ይህን ታሪክ ለፊልም ጽሑፍ ብታቀርበው እንኳን አሳማኝ አይሆንም። ከምትገምተው በላይ እጅግ ልዩ የሆነ ነገር ስታገኝ የሚሰማህ ስሜት ነው" በማለት ይገልጸዋል።
የፎቶግራፍ መነሳቱ መርሃ ግብር የተከናወነው በባርሴሎናው ካምፕ ኑ ስታዲየም የመልበሻ ክፍል ውስጥ ነበር። የያማል ቤተሰቦች በወቅቱ እዚያ ሊገኙ የቻሉት በእጣ አሸናፊነት ነው። ትውልደ ሞሮኳዊው አባቱ ሙኒር ናስራውይ እና ኢኳቶሪያል ጊኒያዊቷ እናቱ ሺላ ኢባና፣ በልጅነታቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ካታሎንያ ከመጡ በኋላ ነበር የተዋወቁት። ላሚን ያማል የመጀመሪያ ልጃቸው ሲሆን፣ እሱ በተወለደበት ወቅት የካታላኑ ስፖርት ጋዜጣ ከባርሴሎና ማሊያ ስፖንሰር ዩኒሴፍ (Unicef) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት የእጣ ውድድር ላይ ተሳትፈው አሸናፊ ሆኑ። የውድድሩ አሸናፊዎች ከባርሴሎና ዋናው ቡድን ተጫዋች ጋር የልጃቸውን ፎቶግራፍ በሙያዊ መንገድ የማንሳት ዕድል ያገኛሉ። የያማል ቤተሰቦች በዕለቱ ስታዲየም ሲደርሱ፣ በዕጣ ፈንታ ከሊዮኔል ሜሲ ጋር እንዲነሱ ተመደቡ።
ፎቶግራፍ አንሺው ሞንፎርት ያንን ቀን ሲያስታውስ፣ "ሜሲ በጣም አይን አፋር እና ዝምተኛ ልጅ ነው። ወደ መልበሻ ክፍሉ ገብቶ በድንገት ከዚህ ሕፃን ጋር ፎቶ መነሳት እንዳለበት ሲነገረው፣ ሕፃኑን ምን እንደሚያደርገው ግራ ገብቶት ፊቱ ተለዋውጦ ነበር" ይላል። "ለአንድ ወጣት ልጅ ከባድ ቢሆንም፣ ላሚን ግን በጣም ደስተኛ እና ፈገግታ የማያጣ ሕፃን ነበር። እናቱ ሺላም ታግዘን ነበር፤ በጣም ደሀ ቤተሰቦች ቢሆኑም አብሮ ለመስራት እጅግ ጥሩ ሰዎች ነበሩ። ሜሲ እንዲህ ባሉ ነገሮች ላይ ሁልጊዜም ፕሮፌሽናል ስለሆነ፣ ከሁኔታው ጋር ቶሎ ተላመደ።"
ላሚን ያማል ሰኞ ዕለት 19ኛ ዓመቱን ሲያከብር፣ አስገራሚ የእግር ኳስ ጉዞን አስመዝግቧል። ሜሲ 19 ዓመት ሲሞላው 11 የክለብ ግቦችን አስቆጥሮ አንድ የላሊጋ እና አንድ የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አሸንፎ ነበር። ያማል ግን በአንጻሩ 56 ግቦችን ከመረብ አሳርፎ፣ ሦስት የላሊጋ ዋንጫዎችን፣ አንድ የኮፓ ዴል ሬይ እና የዩሮ 2024 ዋንጫን ማንሳት ችሏል።
የሚገርመው ነገር «ያማል» የልጁ የአባት ስም ሳይሆን፣ ሁለተኛው መጠሪያ ስሙ መሆኑ ነው። ሙሉ ስሙ ላሚን ያማል ናስራውይ ኢባና ሲሆን፣ በማሊያው ጀርባ ላይ የሚጠቀመው የመጀመሪያዎቹን ሁለት ስሞቹን ነው። ይህ የሆነበት ምክንያት ደግሞ፣ እሱ በሚወለድበት ወቅት ቤተሰቡ በከፍተኛ የገንዘብ ችግር ውስጥ ወድቆ በነበረበት ሰዓት የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉላቸው ሁለት የቅርብ ወዳጆቻቸው ክብር ሲሉ አባቱ ቃል በገባው መሠረት የተሰየመ ነው።
በአረብኛ «ላሚን» ማለት ታማኝ ማለት ሲሆን፣ «ያማል» ደግሞ የጀማል ሌላኛው አጠራር ሆኖ ውበት ወይም ግርማ ሞገስ ማለት ነው። ያማል ባስቆጠራቸው ግቦች ላይ በጣቶቹ «3-0-4» የሚል ምልክት በማሳየት ደስታውን ይገልጻል፤ ይህ ደግሞ ያደገበትንና ከባርሴሎና 20 ማይል ርቃ የምትገኘውን የሮካፎንዳ ሰፈር የፖስታ ኮድ የሚያመላክት ነው። ያማል ስለ ቤተሰቦቹ ሲናገር... "ወላጆቼ ያደረጉልኝን ነገር እኔ ልጄ ላልሆነ ሰው ማድረግ አልችልም። ገንዘብ ከሌለህ ልጅህ እግር ኳስ እንዲጫወት መርዳት በጣም ከባድ ነው፤ ወላጆቼ ግን ይህን ሁሉ አሳክተዋል። ውለታቸውን መቼም ልመልስላቸው አልችልም" ብሏል።
ለካታላኑ እና የባርሴሎና ደጋፊ ለሆነው ፎቶግራፍ አንሺ ሞንፎርት፣ የሁለቱ ተጫዋቾች በዓለም ዋንጫ የፍጻሜ መድረክ ላይ መገናኘት ከሁለት አሥርት ዓመታት በፊት ለጀመረው ታሪክ ፍጹም ማሳረጊያ ነው። የ58 ዓመቱ ሞንፎርት፣ "የታሪካቸውን ዑደት እየዘጋን ይመስለኛል፤ አስደሳች ፍጻሜ ነው። እኔ የባርሴሎና ደጋፊ ነኝ፤ ለሜሲ የእግር ኳስ ህይወቱን ሁለተኛውን የዓለም ዋንጫ በማንሳት ቢያጠናቅቅ ፍጹም ይገባዋል እላለሁ። ላሚን ደግሞ ገና ወደፊት የዓለም ዋንጫን የሚያነሳበት ብዙ ጊዜ አለው። ነገር ግን ስፔን እና ላሚን አሁን በጥሩ ሞራል ላይ ይገኛሉ፤ ይህንን ዋንጫ ቢያነሳ ከሌሎች ክብሮቹ ሁሉ የላቀ ይሆናል። ስለዚህ ምርጫው ለእኔ በጣም ከባድ ነው፤ ልቤ ለሁለት እየተሰነጠቀ ነው" በማለት ስሜቱን ገልጿል።
Sponsored by
Surafel
22 days ago
የአጭር ጊዜ ቪዲዮዎች (TikTok እና Reels) ራስን የመቆጣጠር እና የዲሲፕሊን ክህሎትን የሚገነባውን የአንጎል ክፍል ስራ እንደሚያደናቅፉ አዲስ ጥናት አመለከተ
ተጠቃሚዎች በምስሎቹ ቢደሰቱም ባይደሰቱም፥ ቪዲዮዎቹ በአንጎል ላይ የሚያሳድሩት አሉታዊ ተፅዕኖ አይቀሬ መሆኑ ተረጋግጧል።
ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ እነዚህ ምስል-ወለድ ይዘቶች የተመልካቹን ቀልብ አንዴ ከሳቡ በኋላ ፈጣን የዶፓሚን ሆርሞን መለቀቅን ያስከትላሉ።
ይህም የአንጎልን የተፈጥሮ ውሳኔ ሰጪነት በማደንዘዝ፣ ከዕፅ ሱስ የጠነከረ ከፍተኛ የሱስ የመለከፍ አደጋ ይፈጥራል።
ይህ የፈጣን መዝናኛ አባዜ የሰውን ልጅ ወደ ማገናዘብ የማይችል “ዞምቢ” እየቀየረው መሆኑን ተመራማሪዎች አስጠንቅቀዋል።
ራስን የመግዛት አቅምን ለመጠበቅ ከማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም መገደብ ወሳኝ እንደሆነም ተመክሯል።
Seledadotio
Seledadotio
ተጠቃሚዎች በምስሎቹ ቢደሰቱም ባይደሰቱም፥ ቪዲዮዎቹ በአንጎል ላይ የሚያሳድሩት አሉታዊ ተፅዕኖ አይቀሬ መሆኑ ተረጋግጧል።
ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ እነዚህ ምስል-ወለድ ይዘቶች የተመልካቹን ቀልብ አንዴ ከሳቡ በኋላ ፈጣን የዶፓሚን ሆርሞን መለቀቅን ያስከትላሉ።
ይህም የአንጎልን የተፈጥሮ ውሳኔ ሰጪነት በማደንዘዝ፣ ከዕፅ ሱስ የጠነከረ ከፍተኛ የሱስ የመለከፍ አደጋ ይፈጥራል።
ይህ የፈጣን መዝናኛ አባዜ የሰውን ልጅ ወደ ማገናዘብ የማይችል “ዞምቢ” እየቀየረው መሆኑን ተመራማሪዎች አስጠንቅቀዋል።
ራስን የመግዛት አቅምን ለመጠበቅ ከማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም መገደብ ወሳኝ እንደሆነም ተመክሯል።
Seledadotio
Seledadotio
24 days ago
ዛሬ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ደማቅ ቀን ነው። አድማጮች በሙዚቃው የሚወዱት፣ ግጥምና ዜማውን በራሱ የሚቃኘው ተወዳጁ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የተወለደበት ቀን ነው።
የትውልድ እና እድገቱ አዲስ አበባ የሆነው ቴዲ፣ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትምህርቱን የተከታተለውም እዚሁ ከተማ ነው። ለሙዚቃ ባለው ከፍተኛ ፍቅር እና ባሳየው የፈጠራ ብቃት፣ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ስሙ በጉልህ እንዲሰፍር አድርጎታል።
"ፍቅር ያሸንፋል" በሚለው አባባሉ የሚታወቀውና በአድናቂዎቹ ዘንድ ትልቅ ስፍራ ያለው ቴዲ፣ ከውጫዊ ተጽዕኖዎች ይልቅ ትኩረቱን ሙዚቃው ላይ ብቻ በማድረግ ለሙዚቃው ኢንዱስትሪ ትልቅ አሻራ ጥሏል።
ዛሬ የተወለድክበት ቀን ነውና፣ ለቀጣይ የኪነ-ጥበብ ስራዎችህ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። እንኳን ተወለድክ!
የትውልድ እና እድገቱ አዲስ አበባ የሆነው ቴዲ፣ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትምህርቱን የተከታተለውም እዚሁ ከተማ ነው። ለሙዚቃ ባለው ከፍተኛ ፍቅር እና ባሳየው የፈጠራ ብቃት፣ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ስሙ በጉልህ እንዲሰፍር አድርጎታል።
"ፍቅር ያሸንፋል" በሚለው አባባሉ የሚታወቀውና በአድናቂዎቹ ዘንድ ትልቅ ስፍራ ያለው ቴዲ፣ ከውጫዊ ተጽዕኖዎች ይልቅ ትኩረቱን ሙዚቃው ላይ ብቻ በማድረግ ለሙዚቃው ኢንዱስትሪ ትልቅ አሻራ ጥሏል።
ዛሬ የተወለድክበት ቀን ነውና፣ ለቀጣይ የኪነ-ጥበብ ስራዎችህ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። እንኳን ተወለድክ!
24 days ago
📍በአዲሲቷ ፒያሳ አድዋ ፊትለፊት
👉ግንባታቸው 50% በላይ የተጠናቀቀ ዘመናዊ የንግድ ሱቆችን በመሃል ፒያሳ አደባባይ
👉 ከ 20 ካሬ ጀምሮ 2B+G+5 Mall
👉 ከ 1,400,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ ወይም 4,800,000 ጠቅላላ ክፍያ
👉 በ 4ቱም አቅጣጫ ዋናውን መንገድ መያዙ ለ ንግድ ተመራጭ ያደርገዋል
👉 እስከ 200,000 ብር የመከራየት አቅም ያላቸው
👉 የ ሱቅ ቁልፍ ብቻ በሚሸጥባት ፒያሳ ላይ ብቸኛው የ ግልዎን ሱቅ የሚያገኙበት አማራጭ በመሆኑ
........ ልብ ይበሉ
1. ቴምር ሪል እስቴት በ11 ዓመት 10ፕሮጀክት ጥንቅቅ አድርጎ ያስረከበ ግዙፍ ታማኝ ተቋም ነው
2. ምንም ዓይነት የዋጋ ግሽበት አይመለከተዎትም
3. ቀስ ብለው ካለ ምንም ወለድ ከፍለው ያጠናቀቃሉ
4. ያሉበት አገር በ DHL ልከን እናስፈርመዎታለን
5. ቀሪ ክፍያ በ ግንባታ ሂደት ብቻ ይከፍላሉ(ምቹ አከፋፈል አለን )
🧩 ሳርቤት እና ቡልጋሪ አፍሪካ ህብረት ዘመናዊ አፓርታማ ቤቶች አሉን
ዋና የሽያጭ ቢሮ በታች ባለው ስልክ ይደውሉልን
☎️ 09 10 79 83 53
09 08 77 00 77
ወይም በ WhatsApp ላይ ያዋሩን Https://Wa.me/+25191079835... #realestateagent #realestate #temerproperty #ethiopianrealestate
👉ግንባታቸው 50% በላይ የተጠናቀቀ ዘመናዊ የንግድ ሱቆችን በመሃል ፒያሳ አደባባይ
👉 ከ 20 ካሬ ጀምሮ 2B+G+5 Mall
👉 ከ 1,400,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ ወይም 4,800,000 ጠቅላላ ክፍያ
👉 በ 4ቱም አቅጣጫ ዋናውን መንገድ መያዙ ለ ንግድ ተመራጭ ያደርገዋል
👉 እስከ 200,000 ብር የመከራየት አቅም ያላቸው
👉 የ ሱቅ ቁልፍ ብቻ በሚሸጥባት ፒያሳ ላይ ብቸኛው የ ግልዎን ሱቅ የሚያገኙበት አማራጭ በመሆኑ
........ ልብ ይበሉ
1. ቴምር ሪል እስቴት በ11 ዓመት 10ፕሮጀክት ጥንቅቅ አድርጎ ያስረከበ ግዙፍ ታማኝ ተቋም ነው
2. ምንም ዓይነት የዋጋ ግሽበት አይመለከተዎትም
3. ቀስ ብለው ካለ ምንም ወለድ ከፍለው ያጠናቀቃሉ
4. ያሉበት አገር በ DHL ልከን እናስፈርመዎታለን
5. ቀሪ ክፍያ በ ግንባታ ሂደት ብቻ ይከፍላሉ(ምቹ አከፋፈል አለን )
🧩 ሳርቤት እና ቡልጋሪ አፍሪካ ህብረት ዘመናዊ አፓርታማ ቤቶች አሉን
ዋና የሽያጭ ቢሮ በታች ባለው ስልክ ይደውሉልን
☎️ 09 10 79 83 53
09 08 77 00 77
ወይም በ WhatsApp ላይ ያዋሩን Https://Wa.me/+25191079835... #realestateagent #realestate #temerproperty #ethiopianrealestate
24 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በንግድ ባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን ዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን አስታወቀ። ባንኩ ይህ እርምጃው ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ አቋሙን ማላላቱን እንደማያሳይና በወለድ ተመን ላይ ወደተመሰረተ ማዕቀፍ የተደረገ "የተሳካ ሽግግር" መሆኑን በመግለጫው ቢከራከርም፣ የብድር ገደቡ በአንዴ መነሳት በገበያው ውስጥ ያለውን የገንዘብ ዝውውር በማብዛት አሁን ያለውን አሳሳቢ የዋጋ ንረት ይበልጥ እንዳያባብሰው ስጋት ፈጥሯል።
ብሔራዊ ባንኩ ቀጥተኛ ያልሆኑ የፖሊሲ መሳሪያዎችን መተግበሩን እንደሚቀጥል በመግለጽ፣ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔውን ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ ከፍ ማድረጉን አስታውቋል። በተጓዳኝም ላኪዎችን ለማበረታታት እና የውጭ ምንዛሬ እጥረቱን ለማርገብ በሚመስል መልኩ፣ ባንኩ የሚቆርጠውን የውጭ ምንዛሬ ኮሚሽን ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ ዝቅ አድርጓል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ላኪዎች ከሚያገኙት የውጭ ምንዛሬ ገቢ ለብሔራዊ ባንክ በግዴታ እንዲሸጡ ተጥሎ የነበረው የ50 በመቶ ገደብ ወደ 30 በመቶ ዝቅ እንዲል ተወስኗል።
እነዚህ ተቃራኒ የሚመስሉ እርምጃዎች (በአንድ በኩል ወለድን መጨመር፣ በሌላ በኩል ደግሞ የብድር ጣሪያን ማንሳት እና የውጭ ምንዛሬ ቁጥጥርን ማላላት) ብሔራዊ ባንኩ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር እና አስከፊውን የውጭ ምንዛሬ ቀውስ ለመፍታት እያደረገ ያለውን መፍጨርጨር የሚያሳዩ ናቸው።
በተለይም የብድር ገደቡ መነሳት ባንኮች በነጻነት ብድር እንዲሰጡ የሚያስችል ቢሆንም፣ በ1 በመቶ ብቻ ያደገው የማሻሻያ የወለድ ምጣኔ፣ የብድር መለቀቁ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚያመጣውን የዋጋ ንረት ጫና አፍኖ ለመያዝ በቂ ነው ወይ? የሚለው የባንኩን አዲስ አቅጣጫ ጥያቄ ውስጥ የሚጥል ነው። የላኪዎች የውጭ ምንዛሬ ገቢ ግዴታ ወደ 30 በመቶ ዝቅ መደረጉም፣ መንግስት የውጭ ምንዛሬን በቀጥታ ከመቆጣጠር ይልቅ ገበያው ራሱን እንዲያስተካክል ለማድረግ የተገደደበትን ሁኔታ ያሳያል።
ብሔራዊ ባንኩ ቀጥተኛ ያልሆኑ የፖሊሲ መሳሪያዎችን መተግበሩን እንደሚቀጥል በመግለጽ፣ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔውን ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ ከፍ ማድረጉን አስታውቋል። በተጓዳኝም ላኪዎችን ለማበረታታት እና የውጭ ምንዛሬ እጥረቱን ለማርገብ በሚመስል መልኩ፣ ባንኩ የሚቆርጠውን የውጭ ምንዛሬ ኮሚሽን ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ ዝቅ አድርጓል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ላኪዎች ከሚያገኙት የውጭ ምንዛሬ ገቢ ለብሔራዊ ባንክ በግዴታ እንዲሸጡ ተጥሎ የነበረው የ50 በመቶ ገደብ ወደ 30 በመቶ ዝቅ እንዲል ተወስኗል።
እነዚህ ተቃራኒ የሚመስሉ እርምጃዎች (በአንድ በኩል ወለድን መጨመር፣ በሌላ በኩል ደግሞ የብድር ጣሪያን ማንሳት እና የውጭ ምንዛሬ ቁጥጥርን ማላላት) ብሔራዊ ባንኩ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር እና አስከፊውን የውጭ ምንዛሬ ቀውስ ለመፍታት እያደረገ ያለውን መፍጨርጨር የሚያሳዩ ናቸው።
በተለይም የብድር ገደቡ መነሳት ባንኮች በነጻነት ብድር እንዲሰጡ የሚያስችል ቢሆንም፣ በ1 በመቶ ብቻ ያደገው የማሻሻያ የወለድ ምጣኔ፣ የብድር መለቀቁ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚያመጣውን የዋጋ ንረት ጫና አፍኖ ለመያዝ በቂ ነው ወይ? የሚለው የባንኩን አዲስ አቅጣጫ ጥያቄ ውስጥ የሚጥል ነው። የላኪዎች የውጭ ምንዛሬ ገቢ ግዴታ ወደ 30 በመቶ ዝቅ መደረጉም፣ መንግስት የውጭ ምንዛሬን በቀጥታ ከመቆጣጠር ይልቅ ገበያው ራሱን እንዲያስተካክል ለማድረግ የተገደደበትን ሁኔታ ያሳያል።
25 days ago
የባንኮች የማበደር ገደብ ተነሳ‼
የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (ቁጥር 7) ስብሰባ ዋና ዋና ውሳኔዎችና የኢኮኖሚ አፈጻጸም አጭር መግለጫ:-
፩. ዋና ዋና የፖሊሲ ውሳኔዎች
📌የብድር ገደብ መነሳት፦ በባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብ (Credit Cap) ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል።
📌 የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ማሻሻያ፦ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ (Policy Rate) በ1.0 በመቶ ነጥብ ከፍ በማለት ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ እንዲያድግ ተደርጓል።
📌 የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ግዴታ (FX Surrender)፦ ላኪዎችና የውጭ ምንዛሬ አስገኚዎች ለባንኮች ገቢ የሚያደርጉት የውጭ ምንዛሬ ግዴታ ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ እንዲል ተወስኗል።
📌 የኮሚሽን ምጣኔ ቅነሳ፦ ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግዢ ጋር ተያይዞ የሚያስከፍሉት የኮሚሽን ምጣኔ ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል።
፪. የኢኮኖሚ አፈጻጸም ማጠቃለያ
📌 የኢኮኖሚ ዕድገት፦ በ2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድገት 9.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
📌የዋጋ ግሽበት፦ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም. ወደ 13.4 በመቶ ዝቅ ብሏል።
📌 የበጀት ጉድለት፦ የአገሪቱ የበጀት ጉድለት ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አንጻር ወደ 0.9 በመቶ ወርዷል።
📌 የውጭ ኢኮኖሚ ክምችት፦ አጠቃላይ የውጭ ክፍያ ሚዛን ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ማሻሻያው ከመደረጉ በፊት ከነበረው አንጻር በ20 እጥፍ አድጓል።
Seledadotio
Seledadotio
የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (ቁጥር 7) ስብሰባ ዋና ዋና ውሳኔዎችና የኢኮኖሚ አፈጻጸም አጭር መግለጫ:-
፩. ዋና ዋና የፖሊሲ ውሳኔዎች
📌የብድር ገደብ መነሳት፦ በባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብ (Credit Cap) ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል።
📌 የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ማሻሻያ፦ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ (Policy Rate) በ1.0 በመቶ ነጥብ ከፍ በማለት ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ እንዲያድግ ተደርጓል።
📌 የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ግዴታ (FX Surrender)፦ ላኪዎችና የውጭ ምንዛሬ አስገኚዎች ለባንኮች ገቢ የሚያደርጉት የውጭ ምንዛሬ ግዴታ ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ እንዲል ተወስኗል።
📌 የኮሚሽን ምጣኔ ቅነሳ፦ ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግዢ ጋር ተያይዞ የሚያስከፍሉት የኮሚሽን ምጣኔ ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል።
፪. የኢኮኖሚ አፈጻጸም ማጠቃለያ
📌 የኢኮኖሚ ዕድገት፦ በ2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድገት 9.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
📌የዋጋ ግሽበት፦ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም. ወደ 13.4 በመቶ ዝቅ ብሏል።
📌 የበጀት ጉድለት፦ የአገሪቱ የበጀት ጉድለት ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አንጻር ወደ 0.9 በመቶ ወርዷል።
📌 የውጭ ኢኮኖሚ ክምችት፦ አጠቃላይ የውጭ ክፍያ ሚዛን ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ማሻሻያው ከመደረጉ በፊት ከነበረው አንጻር በ20 እጥፍ አድጓል።
Seledadotio
Seledadotio
25 days ago
የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ጤናማ እና የተረጋጋ ሆኗል - የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ
***************
የኢትዮጵያ ባንክ ዘርፍ የተረጋጋ መሆኑን እንዲሁም የመሠረታዊ ገንዘብ ዕድገት መረጋጋት ማሳየቱን የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡
የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ በሀገራችን ያለው የመሠረታዊ ገንዘብ ዕድገት በከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
የወለድ በተመለከተ የአጭር ጊዜ የወለድ ተመኖች ከፍተኛ መሻሻል ማሳየታቸውን እና ከማስቀመጫ ወለድ ውጭ ያሉት በሙሉ ከዜሮ በላይ መሆናቸውን መግለጫው አትቷል፡፡
በግንቦት ወር 2018 የሁሉም የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነዶች አማካይ የወለድ ምጣኔ እና የ91 ቀን የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ አማካይ የወለድ ምጣኔ በቅደም ተከተል 12.3 እና 11 በመቶ በመሆን ካለፈው ዓመት ቅናሽ አሳይተዋል፡፡
ይሁን እንጂ በመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ ገበያ በተለይ በአጭር ጊዜ ሰነዶች ላይ ወደ 667.8 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ከፍተኛ የተጨማሪ ፍላጎት ተመዝግቧል፡፡
የኢንቨስትመንት ባንኮች ተሳትፎ መጨመር ገበያውን ይበልጥ እንዳሰፋው ነው ኮሚቴው በመግለጫው የጠቀሰው፡፡
ባንኮች እርስ በእርስ የሚበዳደሩበት የ7-ቀን የባንክ ለባንክ የገንዘብ ገበያ አማካይ የወለድ ምጣኔ በመጋቢት ወር 2018 ከነበረው 18.0 በመቶ ቅናሽ በማሳየት በግንቦት ወር 2018 ወደ 14.6 በመቶ ደርሷል፡፡
በዚህም የባንክ ለባንክ የገንዘብ ገበያ አጠቃላይ የግብይት መጠንም 3 ትሪሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡
በአጠቃላይ የባንክና የፋይናንስ ዘርፉ በቂ ካፒታል ያለው እና የተበላሸ ብድር መጠኑ ዝቅተኛ በመሆኑ ጤናማ እና የተረጋጋ ሆኖ መቀጠሉን ኮሚቴው አረጋግጧል፡፡
ለዚህ አዎንታዊ አፈፃፀም የአጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ ክምችት ማደግ እና የብድር ተመላሽ መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
የባንኮችን ጤናማነት በይበልጥ ከሚያሳዩት አንዱ የሆነው የግል ባንኮች የብድር እና የተቀማጭ ሂሳብ ምጣኔ በ2016 ከነበረው 90.3 በመቶ በ2018 ወደ 72.7 በመቶ ዝቅ ማለቱ፣ የባንኮች የገንዘብ አስተዳደር አቅም በከፍተኛ ሁኔታ መሻሻሉን እንደሚያሳይ በመግለጫው ተጠቁሟል፡፡
#ethiopia #ebc #nationalbankofethiopia #bankingsector #financialstability #monetarypolicy #economicgrowth #treasurybills
***************
የኢትዮጵያ ባንክ ዘርፍ የተረጋጋ መሆኑን እንዲሁም የመሠረታዊ ገንዘብ ዕድገት መረጋጋት ማሳየቱን የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡
የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ በሀገራችን ያለው የመሠረታዊ ገንዘብ ዕድገት በከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
የወለድ በተመለከተ የአጭር ጊዜ የወለድ ተመኖች ከፍተኛ መሻሻል ማሳየታቸውን እና ከማስቀመጫ ወለድ ውጭ ያሉት በሙሉ ከዜሮ በላይ መሆናቸውን መግለጫው አትቷል፡፡
በግንቦት ወር 2018 የሁሉም የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነዶች አማካይ የወለድ ምጣኔ እና የ91 ቀን የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ አማካይ የወለድ ምጣኔ በቅደም ተከተል 12.3 እና 11 በመቶ በመሆን ካለፈው ዓመት ቅናሽ አሳይተዋል፡፡
ይሁን እንጂ በመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ ገበያ በተለይ በአጭር ጊዜ ሰነዶች ላይ ወደ 667.8 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ከፍተኛ የተጨማሪ ፍላጎት ተመዝግቧል፡፡
የኢንቨስትመንት ባንኮች ተሳትፎ መጨመር ገበያውን ይበልጥ እንዳሰፋው ነው ኮሚቴው በመግለጫው የጠቀሰው፡፡
ባንኮች እርስ በእርስ የሚበዳደሩበት የ7-ቀን የባንክ ለባንክ የገንዘብ ገበያ አማካይ የወለድ ምጣኔ በመጋቢት ወር 2018 ከነበረው 18.0 በመቶ ቅናሽ በማሳየት በግንቦት ወር 2018 ወደ 14.6 በመቶ ደርሷል፡፡
በዚህም የባንክ ለባንክ የገንዘብ ገበያ አጠቃላይ የግብይት መጠንም 3 ትሪሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡
በአጠቃላይ የባንክና የፋይናንስ ዘርፉ በቂ ካፒታል ያለው እና የተበላሸ ብድር መጠኑ ዝቅተኛ በመሆኑ ጤናማ እና የተረጋጋ ሆኖ መቀጠሉን ኮሚቴው አረጋግጧል፡፡
ለዚህ አዎንታዊ አፈፃፀም የአጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ ክምችት ማደግ እና የብድር ተመላሽ መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
የባንኮችን ጤናማነት በይበልጥ ከሚያሳዩት አንዱ የሆነው የግል ባንኮች የብድር እና የተቀማጭ ሂሳብ ምጣኔ በ2016 ከነበረው 90.3 በመቶ በ2018 ወደ 72.7 በመቶ ዝቅ ማለቱ፣ የባንኮች የገንዘብ አስተዳደር አቅም በከፍተኛ ሁኔታ መሻሻሉን እንደሚያሳይ በመግለጫው ተጠቁሟል፡፡
#ethiopia #ebc #nationalbankofethiopia #bankingsector #financialstability #monetarypolicy #economicgrowth #treasurybills
Sponsored by
Surafel
25 days ago
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የብድር ጣሪያን ማንሳቱን አስታወቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ከዚህ ቀደም በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን ጊዜያዊ የብድር ጣሪያ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን ገልጿል። ይህ ውሳኔ ወደ ገበያ መር የገንዘብ ፖሊሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰደ እርምጃ መሆኑ ተጠቅሷል።
የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ባንኩ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔን በአንድ በመቶ ከፍ አድርጓል። በተጨማሪም የዋጋ ግሽበትን ለመከላከል የሚያስችል አዲስ የታለመ የመጠባበቂያ ግዴታ ማዕቀፍ አስተዋውቋል።
ከውጭ ንግድ ጋር በተያያዘም ባንኩ የውጭ ምንዛሪ ኮሚሽንን ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ ዝቅ አድርጓል። እንዲሁም ላኪዎች የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሪ ለባንክ የመሸጥ ግዴታ (Surrender requirement) ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ በማድረግ፣ የላኪዎችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግና የውጭ ምንዛሪ ገበያውን ለማጠናከር አቅዷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ከዚህ ቀደም በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን ጊዜያዊ የብድር ጣሪያ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን ገልጿል። ይህ ውሳኔ ወደ ገበያ መር የገንዘብ ፖሊሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰደ እርምጃ መሆኑ ተጠቅሷል።
የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ባንኩ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔን በአንድ በመቶ ከፍ አድርጓል። በተጨማሪም የዋጋ ግሽበትን ለመከላከል የሚያስችል አዲስ የታለመ የመጠባበቂያ ግዴታ ማዕቀፍ አስተዋውቋል።
ከውጭ ንግድ ጋር በተያያዘም ባንኩ የውጭ ምንዛሪ ኮሚሽንን ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ ዝቅ አድርጓል። እንዲሁም ላኪዎች የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሪ ለባንክ የመሸጥ ግዴታ (Surrender requirement) ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ በማድረግ፣ የላኪዎችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግና የውጭ ምንዛሪ ገበያውን ለማጠናከር አቅዷል።
25 days ago
"ባለፉት አምስት ዓመታት ከ98 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በዕጣ ለቆጣቢዎች ተላልፈዋል"— ከንቲባ አዳነች አቤቤ
26 ሺህ 563 የመንግስት ቤቶችም ለልማት ተነሺዎች እንዲተላለፉ ተደርጓል
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት በቤት ልማት ዘርፍ ያስመዘገባቸውን ውጤቶችና በቀጣይ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን አስመልክቶ የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለምክር ቤቱ ሰፊ ሪፖርት አቅርበዋል።
ከንቲባዋ በሪፖርታቸው እንዳመለከቱት፣ የቤት ጥያቄ መሰረታዊና አንገብጋቢ የሕዝብ ጥያቄ መሆኑን በመረዳት ባለፉት አምስት ዓመታት በመንግስት፣ በሪል እስቴት፣ በህብረት ስራ ማህበራትና በበጎ ፈቃደኞች አማካኝነት በጠቅላላው 496 ሺህ 971 ቤቶች ተገንብተዋል።
በተለይም ለቤት ፈላጊው ማህበረሰብ ትልቅ ተስፋ የሆነውን የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ በተመለከተ፣ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ98 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በዕጣ ለቆጣቢዎች ተላልፈዋል። ከዚህ በተጨማሪም 26 ሺህ 563 የመንግስት ቤቶች ለልማት ተነሺዎች እንዲተላለፉ ተደርጓል።
በአሁኑ ወቅትም የመንግስት ቤቶችን ጨምሮ በተለያዩ የግንባታ አማራጮች የ179 ሺህ 516 ቤቶች ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ከንቲባዋ ገልጸዋል። ከመንግስት በጀት ብቻ ለተገነቡ ቤቶች አፈጻጸሙ ከ40 በመቶ በላይ መድረሱንም ጠቁመዋል።
ከተማ አስተዳደሩ በቤት ልማት ዘርፍ የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በመቀነስ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱ በሪፖርቱ ተመላክቷል።
ከዚህ ቀደም ከ90 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሶ የነበረው የባንክ ብድርና ወለድ፣ በከፍተኛ ጥረት 62 ቢሊዮን ብር መክፈል በመቻሉ አሁን ላይ ቀሪው ዕዳ ወደ 37 ቢሊዮን ብር ዝቅ ማለቱን ከንቲባዋ አስረድተዋል።
ለዓለም አሰፋ
26 ሺህ 563 የመንግስት ቤቶችም ለልማት ተነሺዎች እንዲተላለፉ ተደርጓል
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት በቤት ልማት ዘርፍ ያስመዘገባቸውን ውጤቶችና በቀጣይ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን አስመልክቶ የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለምክር ቤቱ ሰፊ ሪፖርት አቅርበዋል።
ከንቲባዋ በሪፖርታቸው እንዳመለከቱት፣ የቤት ጥያቄ መሰረታዊና አንገብጋቢ የሕዝብ ጥያቄ መሆኑን በመረዳት ባለፉት አምስት ዓመታት በመንግስት፣ በሪል እስቴት፣ በህብረት ስራ ማህበራትና በበጎ ፈቃደኞች አማካኝነት በጠቅላላው 496 ሺህ 971 ቤቶች ተገንብተዋል።
በተለይም ለቤት ፈላጊው ማህበረሰብ ትልቅ ተስፋ የሆነውን የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ በተመለከተ፣ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ98 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በዕጣ ለቆጣቢዎች ተላልፈዋል። ከዚህ በተጨማሪም 26 ሺህ 563 የመንግስት ቤቶች ለልማት ተነሺዎች እንዲተላለፉ ተደርጓል።
በአሁኑ ወቅትም የመንግስት ቤቶችን ጨምሮ በተለያዩ የግንባታ አማራጮች የ179 ሺህ 516 ቤቶች ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ከንቲባዋ ገልጸዋል። ከመንግስት በጀት ብቻ ለተገነቡ ቤቶች አፈጻጸሙ ከ40 በመቶ በላይ መድረሱንም ጠቁመዋል።
ከተማ አስተዳደሩ በቤት ልማት ዘርፍ የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በመቀነስ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱ በሪፖርቱ ተመላክቷል።
ከዚህ ቀደም ከ90 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሶ የነበረው የባንክ ብድርና ወለድ፣ በከፍተኛ ጥረት 62 ቢሊዮን ብር መክፈል በመቻሉ አሁን ላይ ቀሪው ዕዳ ወደ 37 ቢሊዮን ብር ዝቅ ማለቱን ከንቲባዋ አስረድተዋል።
ለዓለም አሰፋ
27 days ago
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ለቀጣናዊ ሰላም
የአፍሪካ ቀንድ በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ላይ ባለው ስልታዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ሳቢያ ሁልጊዜም የጂኦፖለቲካ ፍላጎቶች መናኸሪያ ነው።
በዚህ ቀጣና ውስጥ ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ የባህር በር አልባ መሆኗ የራሷን የኢኮኖሚ እድገት ከመገደቡ ባለፈ በቀጣናው መረጋጋት ላይ የራሱ ተጽእኖ አለው።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የሀገሪቱን የልማት ጥያቄ ከመመለስ ባለፈ ለአጠቃላይ ቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ትስስር ሚናው ወሳኝ ነው።
የፖለቲካ ሳይንስ ሳይንሳዊ እውነታዎች እንደሚያሳዩት፣ ሀገራት በኢኮኖሚ እርስ በርስ የሚኖራቸው ትስስር በጠነከረ ቁጥር በመካከላቸው የመተማመንና የመተባበር መንፈስ በርትቶ የግጭት ዕድል በእጅጉ ይቀንሳል።
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ ቀጥተኛ የባህር በር ካላት የምርት ወጪዋ ይቀንሳል፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በሙሉ አቅማቸው ያመርታሉ፣ ሰፊ የሥራ ዕድልም ይፈጠራል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል እና የወደብ መዋቅር ሲኖራት፣ በቀጣናው የሚስተዋሉትን የባህር ላይ ወንብድና እና የሽብርተኝነት ስጋቶች ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመከላከል ሰፊ አቅም ይፈጥራል።
ይህ ደግሞ በኤደን ባህረ-ሰላጤ እና በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ህገ-ወጥ ስደት እና የወንጀል ተጋላጭነት ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዲፕሎማሲ እና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ካገኘ፣ በሀገሪቱ ላይ የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ መታፈን ያስወግዳል። ይህ ደግሞ ስጋት-ወለድ ለሆኑ ግጭቶች በር ይዘጋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋን የምታነሳው የዓለም አቀፍ የባህር ህግን እና የጋራ ልማት መርሆዎችን መሠረት አድርጋ ነው።
ይህ አካሄድ ከሃይል ይልቅ በድርድር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የዲፕሎማሲ ባህል በአፍሪካ ቀንድ እንዲዳብር መንገድ ከፍቷል።
በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ቀንድ የሰላም ዋስትና ነው።
በመሆኑም የባህር በር ጥያቄው መመለስ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያፋጥን እና ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍን ታሪካዊ እርምጃ ነው።
የአፍሪካ ቀንድ በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ላይ ባለው ስልታዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ሳቢያ ሁልጊዜም የጂኦፖለቲካ ፍላጎቶች መናኸሪያ ነው።
በዚህ ቀጣና ውስጥ ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ የባህር በር አልባ መሆኗ የራሷን የኢኮኖሚ እድገት ከመገደቡ ባለፈ በቀጣናው መረጋጋት ላይ የራሱ ተጽእኖ አለው።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የሀገሪቱን የልማት ጥያቄ ከመመለስ ባለፈ ለአጠቃላይ ቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ትስስር ሚናው ወሳኝ ነው።
የፖለቲካ ሳይንስ ሳይንሳዊ እውነታዎች እንደሚያሳዩት፣ ሀገራት በኢኮኖሚ እርስ በርስ የሚኖራቸው ትስስር በጠነከረ ቁጥር በመካከላቸው የመተማመንና የመተባበር መንፈስ በርትቶ የግጭት ዕድል በእጅጉ ይቀንሳል።
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ ቀጥተኛ የባህር በር ካላት የምርት ወጪዋ ይቀንሳል፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በሙሉ አቅማቸው ያመርታሉ፣ ሰፊ የሥራ ዕድልም ይፈጠራል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል እና የወደብ መዋቅር ሲኖራት፣ በቀጣናው የሚስተዋሉትን የባህር ላይ ወንብድና እና የሽብርተኝነት ስጋቶች ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመከላከል ሰፊ አቅም ይፈጥራል።
ይህ ደግሞ በኤደን ባህረ-ሰላጤ እና በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ህገ-ወጥ ስደት እና የወንጀል ተጋላጭነት ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዲፕሎማሲ እና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ካገኘ፣ በሀገሪቱ ላይ የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ መታፈን ያስወግዳል። ይህ ደግሞ ስጋት-ወለድ ለሆኑ ግጭቶች በር ይዘጋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋን የምታነሳው የዓለም አቀፍ የባህር ህግን እና የጋራ ልማት መርሆዎችን መሠረት አድርጋ ነው።
ይህ አካሄድ ከሃይል ይልቅ በድርድር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የዲፕሎማሲ ባህል በአፍሪካ ቀንድ እንዲዳብር መንገድ ከፍቷል።
በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ቀንድ የሰላም ዋስትና ነው።
በመሆኑም የባህር በር ጥያቄው መመለስ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያፋጥን እና ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍን ታሪካዊ እርምጃ ነው።
Sponsored by
Surafel
Comments