22 hours ago
የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ከኢራን ጋር በተደረሰው የኒውክሌር ስምምነት ዙሪያ ተግባራዊ እርምጃዎችን ለመውሰድ መዘጋጀቱን አስታወቀ
#ethiopia | የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር በተመለከተ ወደ ተጨባጭ ተግባር ለመሻገር ዝግጁ መሆናቸውን በይፋ ገልጸዋል።
ኢራን ከአሜሪካ ጋር በፈረመችው አዲስ የመግባቢያ ሰነድ አማካኝነት የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ላለማምረትም ሆነ በባለቤትነት ላለመያዝ ዳግም ቁርጠኝነቷን አረጋግጣለች።
ከዚህ በተጨማሪም ሁለቱ አገራት ኢራን አከማችታው በሚገኘው የበለጸገ ዩራኒየም ጉዳይ ላይ በጋራ ለመወያየት ተስማምተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ራፋኤል ግሮሲ ዛሬ ማለዳ በሰጡት መግለጫ ሊያጋጥሙ በሚችሉ የቴክኒክ ፈተናዎች ላይ ብቻ በማተኮር ጊዜን ማባከን ተገቢ እንዳልሆነ አሳስበዋል።
ሁሉም ወገኖች በቅን ልቦና ተሳትፎ በማድረግ ስምምነቱ ግቡን እንዲመታ ይፈልጋሉ በሚል እምነት ድርድሩን እንደሚመሩት የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ስምምነቱን መፈረማቸው ራሱ ሂደቱን በቁም ነገር ለመተግበር ፍላጎት እንዳላቸው የሚያሳይ ምልክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ኤጀንሲው ስለ ተወሰኑ ጉዳዮችና ፍተሻ ሊደረግባቸው ስለሚገቡ ስፍራዎች በቂና አስተማማኝ መረጃ እንዳለው የጠቀሱት ግሮሲ፣ ሆኖም ከሂደቱ ቀድሞ መደምደሚያ ላይ መድረስ ትክክል እንዳልሆነና በአሁኑ ወቅት በቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እጅግ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል።
#iran #nuclear #iaea #rafaelgrossi #worldnews #internationalrelations #usa #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር በተመለከተ ወደ ተጨባጭ ተግባር ለመሻገር ዝግጁ መሆናቸውን በይፋ ገልጸዋል።
ኢራን ከአሜሪካ ጋር በፈረመችው አዲስ የመግባቢያ ሰነድ አማካኝነት የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ላለማምረትም ሆነ በባለቤትነት ላለመያዝ ዳግም ቁርጠኝነቷን አረጋግጣለች።
ከዚህ በተጨማሪም ሁለቱ አገራት ኢራን አከማችታው በሚገኘው የበለጸገ ዩራኒየም ጉዳይ ላይ በጋራ ለመወያየት ተስማምተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ራፋኤል ግሮሲ ዛሬ ማለዳ በሰጡት መግለጫ ሊያጋጥሙ በሚችሉ የቴክኒክ ፈተናዎች ላይ ብቻ በማተኮር ጊዜን ማባከን ተገቢ እንዳልሆነ አሳስበዋል።
ሁሉም ወገኖች በቅን ልቦና ተሳትፎ በማድረግ ስምምነቱ ግቡን እንዲመታ ይፈልጋሉ በሚል እምነት ድርድሩን እንደሚመሩት የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ስምምነቱን መፈረማቸው ራሱ ሂደቱን በቁም ነገር ለመተግበር ፍላጎት እንዳላቸው የሚያሳይ ምልክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ኤጀንሲው ስለ ተወሰኑ ጉዳዮችና ፍተሻ ሊደረግባቸው ስለሚገቡ ስፍራዎች በቂና አስተማማኝ መረጃ እንዳለው የጠቀሱት ግሮሲ፣ ሆኖም ከሂደቱ ቀድሞ መደምደሚያ ላይ መድረስ ትክክል እንዳልሆነና በአሁኑ ወቅት በቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እጅግ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል።
#iran #nuclear #iaea #rafaelgrossi #worldnews #internationalrelations #usa #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋኢ፣ ሃገራቸው ከአሜሪካ ጋር የነበራትን የመግባቢያ ሰነድ (MoU) በኤሌክትሮኒክ መንገድ መፈራረሟን ለኢራን መገናኛ ብዙሃን አረጋግጠዋል። የሁለቱ ሃገራት ተደራዳሪ ቡድኖች በጄኔቫ ለመገናኘት ቀጠሮ የያዙ ቢሆንም፣ ሰነዱ በዲጂታል መንገድ መፈረሙ በስዊዘርላንድ የሚካሄድ ምንም አይነት አካላዊ የፊርማ ስነስርዓት እንደማይኖር ያሳያል።
በመጀመሪያው ስምምነት መሰረት አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችው የባህር ላይ እገዳ በ30 ቀናት ውስጥ የሚነሳ ሲሆን፣ ለዚህም በምላሹ ኢራን በሆርሙዝ ስትሬት ላይ የመተላለፊያ ፈቃድ ትሰጣለች ተብሎ ነበር።
ነገር ግን የእስራኤል መንግስት በዳሂየህ ላይ ያደረሰውን ጥቃት እና የኢራንን ተከታታይ ዛቻ ተከትሎ፣ ወዲያውኑ በተካሄደው ድርድር አሜሪካ ስምምነቱን በፍጥነት ተግባራዊ እንድታደርግ አድርጓታል። በዚህም መሰረት በአሁኑ ሰዓት የኢራን መርከቦች ያለምንም ማቋረጥ ወደቦችን እየገቡ እና እየወጡ ይገኛሉ። የሰነዱ መፈረምን ተከትሎም ኢራን በሰነዱ ላይ የተስማማችባቸውን የጋራ ግዴታዎች በይፋ መተግበር ትጀምራለች።
ለቴህራን፣ በሊባኖስ ያለውን ጦርነት ማቆም እና የተኩስ አቁም ስምምነት ማረጋገጥ ልክ እንደ ሀገር ውስጥ ፍላጎቷ እኩል ክብደት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። የመግባቢያ ሰነዱ የመጀመሪያ አንቀጽ ላይ የሊባኖስ ስም ሶስት ጊዜ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ይህም የሊባኖስን የግዛት አንድነት እና ብሔራዊ ሉዓላዊነት ማክበርን በግልጽ የሚያስገድድ ነው።
በዚህ የመጀመሪያ ደረጃ ላይ ኢራን ሆን ብላ ጦርነቱን በማቆም ላይ ብቻ ትኩረት ያደረገች ሲሆን፣ የኒውክሌር ጉዳይን ግን ለጊዜው ወደ ጎን ትታዋለች። የተፈረመው ሰነድ ወዲያውኑ ተግባራዊ የሚደረግ ጥብቅ የ60 ቀናት የጊዜ ገደብ ያስቀመጠ ሲሆን፣ ይህ ጊዜ በኒውክሌር ፕሮግራሙ እና ማዕቀቦችን በማንሳት ላይ ብቻ ለመደራደር የሚያገለግል ነው፤ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘም ሊራዘም የሚችልበት አማራጭ አለው።
በሌላ በኩል የኢራን የመከላከያ አቅም እና የሚሳኤል ፕሮግራሞች በምንም መልኩ ለድርድር እንደማይቀርቡ ተገልጿል። ቃል አቀባዩ ባጋኢ እንዳሉት "የሃገሪቱ ሚሳኤሎች ለመተኮስ ብቻ እንጂ ለድርድር የሚቀርቡ አይደሉም" በማለት፣ ቴህራን ስለ መከላከያ ሀብቷ ከማንኛውም አካል ጋር በምንም አይነት ሂደት እንደማትወያይ አረጋግጠዋል።
በመጀመሪያው ስምምነት መሰረት አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችው የባህር ላይ እገዳ በ30 ቀናት ውስጥ የሚነሳ ሲሆን፣ ለዚህም በምላሹ ኢራን በሆርሙዝ ስትሬት ላይ የመተላለፊያ ፈቃድ ትሰጣለች ተብሎ ነበር።
ነገር ግን የእስራኤል መንግስት በዳሂየህ ላይ ያደረሰውን ጥቃት እና የኢራንን ተከታታይ ዛቻ ተከትሎ፣ ወዲያውኑ በተካሄደው ድርድር አሜሪካ ስምምነቱን በፍጥነት ተግባራዊ እንድታደርግ አድርጓታል። በዚህም መሰረት በአሁኑ ሰዓት የኢራን መርከቦች ያለምንም ማቋረጥ ወደቦችን እየገቡ እና እየወጡ ይገኛሉ። የሰነዱ መፈረምን ተከትሎም ኢራን በሰነዱ ላይ የተስማማችባቸውን የጋራ ግዴታዎች በይፋ መተግበር ትጀምራለች።
ለቴህራን፣ በሊባኖስ ያለውን ጦርነት ማቆም እና የተኩስ አቁም ስምምነት ማረጋገጥ ልክ እንደ ሀገር ውስጥ ፍላጎቷ እኩል ክብደት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። የመግባቢያ ሰነዱ የመጀመሪያ አንቀጽ ላይ የሊባኖስ ስም ሶስት ጊዜ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ይህም የሊባኖስን የግዛት አንድነት እና ብሔራዊ ሉዓላዊነት ማክበርን በግልጽ የሚያስገድድ ነው።
በዚህ የመጀመሪያ ደረጃ ላይ ኢራን ሆን ብላ ጦርነቱን በማቆም ላይ ብቻ ትኩረት ያደረገች ሲሆን፣ የኒውክሌር ጉዳይን ግን ለጊዜው ወደ ጎን ትታዋለች። የተፈረመው ሰነድ ወዲያውኑ ተግባራዊ የሚደረግ ጥብቅ የ60 ቀናት የጊዜ ገደብ ያስቀመጠ ሲሆን፣ ይህ ጊዜ በኒውክሌር ፕሮግራሙ እና ማዕቀቦችን በማንሳት ላይ ብቻ ለመደራደር የሚያገለግል ነው፤ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘም ሊራዘም የሚችልበት አማራጭ አለው።
በሌላ በኩል የኢራን የመከላከያ አቅም እና የሚሳኤል ፕሮግራሞች በምንም መልኩ ለድርድር እንደማይቀርቡ ተገልጿል። ቃል አቀባዩ ባጋኢ እንዳሉት "የሃገሪቱ ሚሳኤሎች ለመተኮስ ብቻ እንጂ ለድርድር የሚቀርቡ አይደሉም" በማለት፣ ቴህራን ስለ መከላከያ ሀብቷ ከማንኛውም አካል ጋር በምንም አይነት ሂደት እንደማትወያይ አረጋግጠዋል።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በከቀናት በፊት ቅሬታቸውን ሲገልጹባቸው ወደ ነበሩት የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ትኩረታቸውን በማዞር ኔታንያሁ "ጥሩ ሰው" መሆናቸውን ቢገልጹም፣ ነገር ግን "አንዳንዴ ትንሽ ስሜታዊ ይሆናሉ" ሲሉ ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኔታንያሁ አሁን ከሚከተሉት መንገድ ይልቅ "ትንሽ ለዘብ ያለ አካሄድ" ቢጠቀሙ የተሻለ እንደሚሆን ጠቁመዋል። አክለውም፣ "ከሂዝቦላህ የሆነ ሰው ወደ አንድ ህንፃ በገባ ቁጥር፣ ህንፃውን ሙሉ በሙሉ ማፍረስ አይጠበቅብዎትም" በማለት የእስራኤልን ወታደራዊ እርምጃዎች በተዘዋዋሪ ተችተዋል።
አክለውም ትራምፕ በአሜሪካ እና ኢራን መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በንግግራቸው የዳሰሱ ሲሆን፣ እ.ኤ.አ. በ2020 የኢራኑ ከፍተኛ ጀነራል ቃሲም ሱሌማኒ የተገደሉበትን ጥቃት አስታውሰዋል።
ፕሬዝዳንቱ የኦባማ አስተዳደር ከኢራን ጋር ተፈራርሞት የነበረውን የኒውክሌር ስምምነትም በጽኑ ተችተዋል። ስምምነቱ ኢራን "ወደ ኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንድታመራ መንገድ የሚከፍት ነበር" በማለት የራሳቸውን አስተዳደር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ትክክለኛነት ሞግተዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኔታንያሁ አሁን ከሚከተሉት መንገድ ይልቅ "ትንሽ ለዘብ ያለ አካሄድ" ቢጠቀሙ የተሻለ እንደሚሆን ጠቁመዋል። አክለውም፣ "ከሂዝቦላህ የሆነ ሰው ወደ አንድ ህንፃ በገባ ቁጥር፣ ህንፃውን ሙሉ በሙሉ ማፍረስ አይጠበቅብዎትም" በማለት የእስራኤልን ወታደራዊ እርምጃዎች በተዘዋዋሪ ተችተዋል።
አክለውም ትራምፕ በአሜሪካ እና ኢራን መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በንግግራቸው የዳሰሱ ሲሆን፣ እ.ኤ.አ. በ2020 የኢራኑ ከፍተኛ ጀነራል ቃሲም ሱሌማኒ የተገደሉበትን ጥቃት አስታውሰዋል።
ፕሬዝዳንቱ የኦባማ አስተዳደር ከኢራን ጋር ተፈራርሞት የነበረውን የኒውክሌር ስምምነትም በጽኑ ተችተዋል። ስምምነቱ ኢራን "ወደ ኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንድታመራ መንገድ የሚከፍት ነበር" በማለት የራሳቸውን አስተዳደር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ትክክለኛነት ሞግተዋል።
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሄዝቦላህ የሚዲያ ግንኙነት ቢሮ ለሮይተርስ የዜና ወኪል እንደገለጸው ዋና ደጋፊው የሆነችው ኢራን በቀጣይ ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው የኒውክሌር ድርድር ምዕራፍ ላይ የእስራኤል ጦር ከሊባኖስ ለቆ እንዲወጣ ጥያቄ እንደምታቀርብ ማረጋገጫ ሰጥታዋለች።
ባለፈው አርብ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል የተፈረመውን የመግባቢያ ሰነድ ተከትሎ በሚቀጥለው ውይይት፣ የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ከሊባኖስ መውጣት የድርድሩ አንዱ ውጤት እንጂ ውይይቱን ለመቀጠል እንደ ቅድመ ሁኔታ እንደማይቀርብ የሄዝቦላህ ቡድን አብራርቷል።
ሄዝቦላህ ለሮይተርስ በሰጠው ጠንከር ያለ አስተያየት "እስራኤላውያን ጦራቸውን ከሊባኖስ ጠቅልለው እስካልወጡ ድረስ በኢራን እና በአሜሪካ መካከል ምንም ዓይነት የኒውክሌር ስምምነት አይኖርም" በማለት ጥብቅ አቋሙን አንጸባርቋል።
ባለፈው አርብ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል የተፈረመውን የመግባቢያ ሰነድ ተከትሎ በሚቀጥለው ውይይት፣ የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ከሊባኖስ መውጣት የድርድሩ አንዱ ውጤት እንጂ ውይይቱን ለመቀጠል እንደ ቅድመ ሁኔታ እንደማይቀርብ የሄዝቦላህ ቡድን አብራርቷል።
ሄዝቦላህ ለሮይተርስ በሰጠው ጠንከር ያለ አስተያየት "እስራኤላውያን ጦራቸውን ከሊባኖስ ጠቅልለው እስካልወጡ ድረስ በኢራን እና በአሜሪካ መካከል ምንም ዓይነት የኒውክሌር ስምምነት አይኖርም" በማለት ጥብቅ አቋሙን አንጸባርቋል።
4 days ago
ከስምምነት የደረሱባቸው ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው?
#ethiopia | አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም ከስምምነት የደረሱባቸው የመግባቢያ ነጥቦች ይፋ ሆኑ።
አሜሪካ እና ኢራን ከሦስት ወራት በላይ የዘለቀውን ጦርነት ለማስቆም የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታወቁ።
በመካከለኛው ምሥራቅ ብሎም በመላው ዓለም ከባድ ቀውስን አስከትሎ የቆየውን ጦርነት ለማስቆም ለወራት ሲደረግ የነበረው ድርድረ አርብ ዕለት ስዊትዘርላንድ ውስጥ በሚካሄድ የፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ይቋጫል ተብሏል።
አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱ እንዲቆም በደረሱት የመግባቢያ ስምምነት ላይ ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች ጦርነቱ እንደሚቆም እና የሆርሙዝ ወሽመጥ እንደሚከፈት ተዘግቧል።
የኢራን ብሔራዊ መገናኛ ብዙኃን በቴህራን እና ዋሺንግተን መካከል ጦርነቱን ለማስቆም ስምምነት በተደረሰበት የመግባቢያ ሰነድ ውስጥ የተካተቱ ነጥቦችን ይፋ አድረገዋል።
የመገናኛ ብዙኃኑ ባቀረቧቸው ዝርዝሮች ውስጥ የተካተቱት ነጥቦች በሁለቱም ወገን ማረጋገጫ አልተሰጠባቸውም።
ሜህር የዜና ወኪል ከዘረዘራቸው ነጥቦች መካከል፦
* በሁሉም ግንባሮች ሊባኖስን ጨምሮ በቋሚነት ተኩስ ይቆማል
* አሜሪካ በኢራን ውስጣዊ ጉዳይ ጣልቃ አትገባም
* በ30 ቀናት ውስጥ የአሜሪካ የባሕር ዕገዳ ይነሳል
* የአሜሪካ ጦር ከኢራን ለቅቆ ይወጣል
* የሆርሙዝ ወሽመጥ “በኢራናውያን ቁጥጥር” በ30 ቀናት ውስጥ ዳግም ይከፈታል
* አሜሪካ እና አጋሮቿ 300 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የመልሶ ግንባታ ዕቅድ ያቀርባሉ
* በኢራን የነዳጅ ዘይት እና ኢነርጂ ምርቶች ላይ የተጣለውን ማዕቀብ ማንሳት
* ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ላለማምረት ዳግም ታረጋግጣለች
አሜሪካ በቀጣናው ያላትን ጦር አትጨምርም እና አዲስ ማዕቀብም አትጥልም።
* ሜህር አክሎም የስምምነቱ መጨረሻ የኢራን እንዳይንቀሳቀሱ የታገዱ ግማሽ ሃብቷ እስኪለቀቅ፣ የኢራን ነዳጅ ዘይት ላይ የተጣለው ማዕቀብ እና የባሕር ላይ ዕገዳው እስኪነሳ ድረስ የመጨረሻው ድርድር አይጀመርም ሲል ዘግቧል።
እንዲሁም የመጨረሻው ስምምነት በተባበሩት መንግሥታት በፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ እንደሚጸድቅ ዘግቧል።
#አሜሪካ #ኢራን #ጦርነት #ስምምነት #bbc #ጌጡተመስገን #ሚዲያኮሚኒኬሽን #getutemsgen #mediacommunication
#ethiopia | አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም ከስምምነት የደረሱባቸው የመግባቢያ ነጥቦች ይፋ ሆኑ።
አሜሪካ እና ኢራን ከሦስት ወራት በላይ የዘለቀውን ጦርነት ለማስቆም የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታወቁ።
በመካከለኛው ምሥራቅ ብሎም በመላው ዓለም ከባድ ቀውስን አስከትሎ የቆየውን ጦርነት ለማስቆም ለወራት ሲደረግ የነበረው ድርድረ አርብ ዕለት ስዊትዘርላንድ ውስጥ በሚካሄድ የፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ይቋጫል ተብሏል።
አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱ እንዲቆም በደረሱት የመግባቢያ ስምምነት ላይ ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች ጦርነቱ እንደሚቆም እና የሆርሙዝ ወሽመጥ እንደሚከፈት ተዘግቧል።
የኢራን ብሔራዊ መገናኛ ብዙኃን በቴህራን እና ዋሺንግተን መካከል ጦርነቱን ለማስቆም ስምምነት በተደረሰበት የመግባቢያ ሰነድ ውስጥ የተካተቱ ነጥቦችን ይፋ አድረገዋል።
የመገናኛ ብዙኃኑ ባቀረቧቸው ዝርዝሮች ውስጥ የተካተቱት ነጥቦች በሁለቱም ወገን ማረጋገጫ አልተሰጠባቸውም።
ሜህር የዜና ወኪል ከዘረዘራቸው ነጥቦች መካከል፦
* በሁሉም ግንባሮች ሊባኖስን ጨምሮ በቋሚነት ተኩስ ይቆማል
* አሜሪካ በኢራን ውስጣዊ ጉዳይ ጣልቃ አትገባም
* በ30 ቀናት ውስጥ የአሜሪካ የባሕር ዕገዳ ይነሳል
* የአሜሪካ ጦር ከኢራን ለቅቆ ይወጣል
* የሆርሙዝ ወሽመጥ “በኢራናውያን ቁጥጥር” በ30 ቀናት ውስጥ ዳግም ይከፈታል
* አሜሪካ እና አጋሮቿ 300 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የመልሶ ግንባታ ዕቅድ ያቀርባሉ
* በኢራን የነዳጅ ዘይት እና ኢነርጂ ምርቶች ላይ የተጣለውን ማዕቀብ ማንሳት
* ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ላለማምረት ዳግም ታረጋግጣለች
አሜሪካ በቀጣናው ያላትን ጦር አትጨምርም እና አዲስ ማዕቀብም አትጥልም።
* ሜህር አክሎም የስምምነቱ መጨረሻ የኢራን እንዳይንቀሳቀሱ የታገዱ ግማሽ ሃብቷ እስኪለቀቅ፣ የኢራን ነዳጅ ዘይት ላይ የተጣለው ማዕቀብ እና የባሕር ላይ ዕገዳው እስኪነሳ ድረስ የመጨረሻው ድርድር አይጀመርም ሲል ዘግቧል።
እንዲሁም የመጨረሻው ስምምነት በተባበሩት መንግሥታት በፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ እንደሚጸድቅ ዘግቧል።
#አሜሪካ #ኢራን #ጦርነት #ስምምነት #bbc #ጌጡተመስገን #ሚዲያኮሚኒኬሽን #getutemsgen #mediacommunication
Sponsored by
Surafel
5 days ago
ጋዜጠኛ ያልተቀጠረለት ምስጥራዊው የሩሲያ የሬዲዮ ጣቢያ
#ethiopia | ሸገር የሬዲዮ ጣቢያን ካለ ዜና አልያ ካለ ፕሮግራም እና ሙዚቃ ውጭ እስቲ አስቡት? በዓለም ዙሪያ ያሉ የሬዲዮ መገናኛ አጥኚዎችን እና ተመራማሪዎችን ለበርካታ አስርት ዓመታት ሲያወዛግብ የቆየውና "ዘ ቡዘር" በመባል የሚታወቀው ምስጢራዊው የሩሲያ አጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ "ዩቪቢ-76" ፣ አሁንም ድረስ ትክክለኛ አላማው ሳይታወቅ ስርጭቱን እንደቀጠለ ነው።
በ4625 ኪሎ ኸርዝ (kHz) ሞገድ ላይ የሚሰራጨው ይህ ጣቢያ፣ በቀን ለ24 ሰዓታት አሰልቺ እና ተደጋጋሚ የሆነ የ"ቡዝ" ድምጽ ያሰማል። ጣቢያው ስርጭቱን ከጀመረበት ከ1970ዎቹ መገባደጃ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት ድምፁ ድንገት ተቋርጦ በሩሲያኛ ቋንቋ ቁጥሮችን፣ ስሞችን እና አጫጭር መልእክቶችን የሚያነቡ ሰዎች ድምፅ ይሰማል። ሆኖም ግን የመልእክቶቹ ትርጉምም ሆነ የጣቢያው ትክክለኛ አገልግሎት እስካሁን በውል አልታወቀም።
ስለ ጣቢያው ምንነት እና አላማ ከተለያዩ አካላት በርካታ መላምቶች ያሉ ሲሆን
በርካቶች ጣቢያው በዓለም ዙሪያ ለተሰማሩ የሩሲያ ሰላዮች ምስጢራዊ መልእክቶችን ለማስተላለፍ እና ለሩሲያ ጦር ሰራዊት በተለይም ለምዕራባዊው ወታደራዊ እዝ እና ለተለያዩ የጦር ሰፈሮች መገናኛነት እንደሚያገለግል በስፋት ይገመታል።
አንዳንዶች ደግሞ ይህ ጣቢያ ሩሲያ የኒውክሌር ጥቃት ቢሰነዘርባት እና ከፍተኛ አመራሮቿ ቢገደሉ፣ በራስ ሰር የኒውክሌር አፀፋዊ ጥቃት እንዲሰነዘር የሚያደርገው ስርዓት አካል ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ።
ምንም እንኳን ጣቢያው ከቦታ ቦታ ከሞስኮ አቅራቢያ ወደ ሴንት ፒተርስበርግ አካባቢ መቀየሩ ቢታወቅም፣ የሩሲያ መንግስት ስለ ጣቢያው ህልውናም ሆነ አላማ እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ የለም። በዘመናዊው የዲጂታል ኮሙኒኬሽን እና የሳተላይት መገናኛ ዘመን፣ ይህ አሮጌ የአጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ ያለማቋረጥ ስርጭቱን መቀጠሉ አሁንም ድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንቆቅልሽን እንደሆነ ቀጥሏል ቀጥሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ሸገር የሬዲዮ ጣቢያን ካለ ዜና አልያ ካለ ፕሮግራም እና ሙዚቃ ውጭ እስቲ አስቡት? በዓለም ዙሪያ ያሉ የሬዲዮ መገናኛ አጥኚዎችን እና ተመራማሪዎችን ለበርካታ አስርት ዓመታት ሲያወዛግብ የቆየውና "ዘ ቡዘር" በመባል የሚታወቀው ምስጢራዊው የሩሲያ አጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ "ዩቪቢ-76" ፣ አሁንም ድረስ ትክክለኛ አላማው ሳይታወቅ ስርጭቱን እንደቀጠለ ነው።
በ4625 ኪሎ ኸርዝ (kHz) ሞገድ ላይ የሚሰራጨው ይህ ጣቢያ፣ በቀን ለ24 ሰዓታት አሰልቺ እና ተደጋጋሚ የሆነ የ"ቡዝ" ድምጽ ያሰማል። ጣቢያው ስርጭቱን ከጀመረበት ከ1970ዎቹ መገባደጃ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት ድምፁ ድንገት ተቋርጦ በሩሲያኛ ቋንቋ ቁጥሮችን፣ ስሞችን እና አጫጭር መልእክቶችን የሚያነቡ ሰዎች ድምፅ ይሰማል። ሆኖም ግን የመልእክቶቹ ትርጉምም ሆነ የጣቢያው ትክክለኛ አገልግሎት እስካሁን በውል አልታወቀም።
ስለ ጣቢያው ምንነት እና አላማ ከተለያዩ አካላት በርካታ መላምቶች ያሉ ሲሆን
በርካቶች ጣቢያው በዓለም ዙሪያ ለተሰማሩ የሩሲያ ሰላዮች ምስጢራዊ መልእክቶችን ለማስተላለፍ እና ለሩሲያ ጦር ሰራዊት በተለይም ለምዕራባዊው ወታደራዊ እዝ እና ለተለያዩ የጦር ሰፈሮች መገናኛነት እንደሚያገለግል በስፋት ይገመታል።
አንዳንዶች ደግሞ ይህ ጣቢያ ሩሲያ የኒውክሌር ጥቃት ቢሰነዘርባት እና ከፍተኛ አመራሮቿ ቢገደሉ፣ በራስ ሰር የኒውክሌር አፀፋዊ ጥቃት እንዲሰነዘር የሚያደርገው ስርዓት አካል ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ።
ምንም እንኳን ጣቢያው ከቦታ ቦታ ከሞስኮ አቅራቢያ ወደ ሴንት ፒተርስበርግ አካባቢ መቀየሩ ቢታወቅም፣ የሩሲያ መንግስት ስለ ጣቢያው ህልውናም ሆነ አላማ እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ የለም። በዘመናዊው የዲጂታል ኮሙኒኬሽን እና የሳተላይት መገናኛ ዘመን፣ ይህ አሮጌ የአጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ ያለማቋረጥ ስርጭቱን መቀጠሉ አሁንም ድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንቆቅልሽን እንደሆነ ቀጥሏል ቀጥሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእስራኤል ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ያየር ላፒድ፣ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል እየተረቀቀ ባለው አዲስ ስምምነት ላይ ጠንካራ ትችት ሰንዝረዋል። ላፒድ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ ስምምነቱ የእስራኤልን የትኛውንም የጦርነት ግብ እንደማያሳካ አስጠንቅቀዋል። ምክንያታቸውንም ሲያብራሩ፣ "ስምምነቱ የኢራንን አገዛዝ በስልጣን ላይ እንዲቆይ የሚያደርግ... የሚሳኤል ፕሮግራሟን ሳይነካ የሚያስቀጥል፣ እንዲሁም የኒውክሌር ፕሮግራሟን ዳግም እንድትገነባ የሚያስችላት ነው" ብለዋል።
ተቃዋሚ መሪው ይህንን ክስተት የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ "ፍጹም ውድቀት" ሲሉ በጽኑ ኮንነውታል። ላፒድ አክለውም፣ አካሄዱ እስራኤልን በብሔራዊ ደህንነቷ ጉዳይ ከሌሎች ትዕዛዝ የምትቀበል "ጥገኛ አገር" እንድትሆን ያደርጋታል በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ በጦር ሜዳ የተገኙ ወታደራዊ ድሎችን ወደ ዘላቂ ስትራቴጂካዊ ስኬቶች የመቀየር ብቃት እንደሌላቸው አጥብቀው ተችተዋል።
ተቃዋሚ መሪው ይህንን ክስተት የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ "ፍጹም ውድቀት" ሲሉ በጽኑ ኮንነውታል። ላፒድ አክለውም፣ አካሄዱ እስራኤልን በብሔራዊ ደህንነቷ ጉዳይ ከሌሎች ትዕዛዝ የምትቀበል "ጥገኛ አገር" እንድትሆን ያደርጋታል በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ በጦር ሜዳ የተገኙ ወታደራዊ ድሎችን ወደ ዘላቂ ስትራቴጂካዊ ስኬቶች የመቀየር ብቃት እንደሌላቸው አጥብቀው ተችተዋል።
6 days ago
የአሜሪካ እና እስራዔል ፍላጎት ለየቅል ሆኗል
#ethiopia | የአሜሪካው ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ሀገራቸውና እስራኤል ከኢራን ጋር ስላለው ጦርነት ማጠቃለያ የተለያየ አቋም እንዳላቸው ይፋ አድርገዋል። እንደ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ገለጻ፣ ሁለቱ ሀገራት በብዙ ጉዳዮች ላይ አብረው ቢሰሩም ጦርነቱ እንዴት መቋጨት አለበት በሚለው ነጥብ ላይ ግን ፍላጎቶቻቸው ይለያያሉ።
ዋሺንግተን የኢራንን የኒውክሌር መርሐግብር በዘለቄታው የሚፈታና ሀገሪቱ የኒውክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት የሚያረጋግጥ የረጅም ጊዜ ስምምነት ላይ ለመድረስ እየሰራች መሆኑን ቫንስ ጠቁመዋል። ይህ ስምምነት በእስራኤል በኩል ተቀባይነት ሊኖረውም ላይኖረውም እንደሚችል የገለጹት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ጉዳዩ ግን የአሜሪካ መሠረታዊ ጥቅም በመሆኑ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትኩረት እንደሚገፉበት አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት አሜሪካና ኢራን የስምምነት “የመጨረሻው ጥረት” ላይ እንደሚገኙና በመጪዎቹ ሳምንታት ወይም ወራት ውስጥ ስምምነት ላይ ሊደርሱ እንደሚችሉ ተገልጿል። በዚህ የሰላም ጥረት ውስጥ ሁለቱን ሀገራት በማሸማገል ላይ የምትገኘው ፓኪስታን በበኩሏ፣ የመጨረሻው ግብ ላይ ለመድረስ የሁሉንም ወገኖች ከጥቃት መቆጠብ እንደሚያስፈልግ አሳስባለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #እስራኤል #ኢራን #ጄዲ_ቫንስ #ዶናልድ_ትራምፕ #የመካከለኛው_ምሥራቅ_ጦርነት #የኒውክሌር_ስምምነት
#ethiopia | የአሜሪካው ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ሀገራቸውና እስራኤል ከኢራን ጋር ስላለው ጦርነት ማጠቃለያ የተለያየ አቋም እንዳላቸው ይፋ አድርገዋል። እንደ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ገለጻ፣ ሁለቱ ሀገራት በብዙ ጉዳዮች ላይ አብረው ቢሰሩም ጦርነቱ እንዴት መቋጨት አለበት በሚለው ነጥብ ላይ ግን ፍላጎቶቻቸው ይለያያሉ።
ዋሺንግተን የኢራንን የኒውክሌር መርሐግብር በዘለቄታው የሚፈታና ሀገሪቱ የኒውክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት የሚያረጋግጥ የረጅም ጊዜ ስምምነት ላይ ለመድረስ እየሰራች መሆኑን ቫንስ ጠቁመዋል። ይህ ስምምነት በእስራኤል በኩል ተቀባይነት ሊኖረውም ላይኖረውም እንደሚችል የገለጹት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ጉዳዩ ግን የአሜሪካ መሠረታዊ ጥቅም በመሆኑ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትኩረት እንደሚገፉበት አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት አሜሪካና ኢራን የስምምነት “የመጨረሻው ጥረት” ላይ እንደሚገኙና በመጪዎቹ ሳምንታት ወይም ወራት ውስጥ ስምምነት ላይ ሊደርሱ እንደሚችሉ ተገልጿል። በዚህ የሰላም ጥረት ውስጥ ሁለቱን ሀገራት በማሸማገል ላይ የምትገኘው ፓኪስታን በበኩሏ፣ የመጨረሻው ግብ ላይ ለመድረስ የሁሉንም ወገኖች ከጥቃት መቆጠብ እንደሚያስፈልግ አሳስባለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #እስራኤል #ኢራን #ጄዲ_ቫንስ #ዶናልድ_ትራምፕ #የመካከለኛው_ምሥራቅ_ጦርነት #የኒውክሌር_ስምምነት
6 days ago
ቤጂንግ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች ሙሉ በሙሉ እንዲወድሙ ጥሪ አቀረበች
#ethiopia | በከፍተኛ የጂኦፖለቲካዊ መግለጫ፣ ቻይና ለዓለም አቀፍ ሰላም መረጋገጥ እና ለሦስተኛው የዓለም ጦርነት መከላከል ብቸኛው መንገድ አጠቃላይ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ መሆኑን በይፋ አስታወቀች። የቻይና ባለሥልጣናት እንደ አሜሪካ ያሉ ታላላቅ ኃያላን ሀገራት እና የእስራኤልን ተሳትፎ የሚያካትተው የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ተዋናዮች የኒውክሌር ዛቻዎችን በአስቸኳይ ማቆም እና ሙሉ በሙሉ ወደ ዲ-ኤስካሌሽን (ውጥረትን ወደ መቀነስ) ማምራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ቤጂንግ ይህንን ዓለም አቀፋዊ ለውጥ በይፋ ብታስተዋውቅም፣ ተቺዎች ቻይና እራሷ የራሷን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ክምችት በከፍተኛ ፍጥነት እያሳደገች መሆኑን በስፋት እየነቀፉ ይገኛሉ። እ.ኤ.አ. በ2026 የዓለም አቀፍ የኒውክሌር ወጪ ከፍተኛ ታሪካዊ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ ተፈጻሚ ሊሆን የሚችል እውነተኛ ግብ ነው ወይስ ፈጽሞ የማይሳካ ምናባዊ ምኞት? የሚለው ክርክር ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ በሁለት መከፈሉን ቀጥሏል።
እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ በኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች ሙሉ በሙሉ መጥፋት የዓለም ሰላም ይረጋገጣል ብለው ያምናሉ ወይስ አሁን ያለው የጦር መሣሪያ እሽቅድምድም የማይቀር ነው?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በከፍተኛ የጂኦፖለቲካዊ መግለጫ፣ ቻይና ለዓለም አቀፍ ሰላም መረጋገጥ እና ለሦስተኛው የዓለም ጦርነት መከላከል ብቸኛው መንገድ አጠቃላይ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ መሆኑን በይፋ አስታወቀች። የቻይና ባለሥልጣናት እንደ አሜሪካ ያሉ ታላላቅ ኃያላን ሀገራት እና የእስራኤልን ተሳትፎ የሚያካትተው የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ተዋናዮች የኒውክሌር ዛቻዎችን በአስቸኳይ ማቆም እና ሙሉ በሙሉ ወደ ዲ-ኤስካሌሽን (ውጥረትን ወደ መቀነስ) ማምራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ቤጂንግ ይህንን ዓለም አቀፋዊ ለውጥ በይፋ ብታስተዋውቅም፣ ተቺዎች ቻይና እራሷ የራሷን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ክምችት በከፍተኛ ፍጥነት እያሳደገች መሆኑን በስፋት እየነቀፉ ይገኛሉ። እ.ኤ.አ. በ2026 የዓለም አቀፍ የኒውክሌር ወጪ ከፍተኛ ታሪካዊ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ ተፈጻሚ ሊሆን የሚችል እውነተኛ ግብ ነው ወይስ ፈጽሞ የማይሳካ ምናባዊ ምኞት? የሚለው ክርክር ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ በሁለት መከፈሉን ቀጥሏል።
እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ በኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች ሙሉ በሙሉ መጥፋት የዓለም ሰላም ይረጋገጣል ብለው ያምናሉ ወይስ አሁን ያለው የጦር መሣሪያ እሽቅድምድም የማይቀር ነው?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
7 days ago
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ እወስዳለው ያሉትን ጥቃት እንደተዉት አስታወቁ
**************
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ውይይት መሻሻል እንዳሳየ እና ከስምምነት ሊደረስ እንደሚችል በመግለፅ በኢራን ላይ ሊሰነዝሩት ያሰቡትን ጥቃት ማቋረጣቸውን አስታውቀዋል።
ትራምፕ ትናንት ሐሙስ ኻርግ ደሴት ላይ ኢራንን “ክፉኛ እንመታለን” ብለው ቢዝቱም፤ ሊያደርሱት የነበረውን ጥቃት ለመሰረዝ መወሰናቸውን ነው የተናገሩት።
ከኢራን ጋር የሚፈረመው የመግባቢያ ሰነድ “የመጨረሻ ደረጃ” ላይ መድረሱን ጠቅሰው በዚህ ሳምንት ስምምነቱ ሊገባደድ እንደሚችል አስረድተዋል። ስምምነቱ የሚፈረመው አውሮፓ ውስጥ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
ስምምነቱ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት የሚያግድ እንዲሁም በአፋጣኝ የሆርሙዝ ወሽመጥ እንዲከፈት የሚያስገድድ እንደሚሆን ትራምፕ አስረግጠው ተናግረዋል።
ትራምፕ ይህንን ቢሉም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስምምነት ላይ ለመድረስ አለመቃረባቸውን አስታውቀዋል።
አሜሪካ በድርድሩ “ከልክ ያለፈ ጥያቄ” እያቀረበች እንደሆነም ጠቅሰዋል።
ኳታር ሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት እያደረገች እንደሆነ ተጠቁሟል።
ትራምፕ ኢራን ላይ ጥቃት እንደማይፈጸም መግለጻቸውን ተከትሎ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ቅናሽ ማሳየቱን የዘገበው ቢቢሲ ነው ።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢራን #አሜሪካ #ትራምፕ #ሆርሙዝ
**************
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ውይይት መሻሻል እንዳሳየ እና ከስምምነት ሊደረስ እንደሚችል በመግለፅ በኢራን ላይ ሊሰነዝሩት ያሰቡትን ጥቃት ማቋረጣቸውን አስታውቀዋል።
ትራምፕ ትናንት ሐሙስ ኻርግ ደሴት ላይ ኢራንን “ክፉኛ እንመታለን” ብለው ቢዝቱም፤ ሊያደርሱት የነበረውን ጥቃት ለመሰረዝ መወሰናቸውን ነው የተናገሩት።
ከኢራን ጋር የሚፈረመው የመግባቢያ ሰነድ “የመጨረሻ ደረጃ” ላይ መድረሱን ጠቅሰው በዚህ ሳምንት ስምምነቱ ሊገባደድ እንደሚችል አስረድተዋል። ስምምነቱ የሚፈረመው አውሮፓ ውስጥ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
ስምምነቱ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት የሚያግድ እንዲሁም በአፋጣኝ የሆርሙዝ ወሽመጥ እንዲከፈት የሚያስገድድ እንደሚሆን ትራምፕ አስረግጠው ተናግረዋል።
ትራምፕ ይህንን ቢሉም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስምምነት ላይ ለመድረስ አለመቃረባቸውን አስታውቀዋል።
አሜሪካ በድርድሩ “ከልክ ያለፈ ጥያቄ” እያቀረበች እንደሆነም ጠቅሰዋል።
ኳታር ሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት እያደረገች እንደሆነ ተጠቁሟል።
ትራምፕ ኢራን ላይ ጥቃት እንደማይፈጸም መግለጻቸውን ተከትሎ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ቅናሽ ማሳየቱን የዘገበው ቢቢሲ ነው ።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢራን #አሜሪካ #ትራምፕ #ሆርሙዝ
Sponsored by
Surafel
7 days ago
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን ላይ የሚደርሰው ጥቃት ‘እንደቆመ’ አስታወቁ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ላይ የሚሰነዘረው ጥቃት ‘እንደተገታ’ አስታወቁ።
ከኢራን ጋር የሚደረገው ውይይት መሻሻል እንዳሳየ እና ከስምምነት ሊደረስ እንደሚችልም ገልጸዋል።
ትራምፕ ትናንት ሐሙስ ኢራንን “ክፉኛ እንመታለን” ብለው ቢዝቱም፤ ሊያደርሱት የነበረውን ጥቃት ለመሰረዝ መወሰናቸውን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንቱ ኻርግ ደሴት ላይ ጥቃት እንደሚፈጸም አስጠንቅቀው ነበር።
ከኢራን ጋር የሚፈረመው የመግባቢያ ሰነድ “የመጨረሻ ደረጃ” ላይ መድረሱን ጠቅሰው በዚህ ሳምንት ስምምነቱ ሊገባደድ እንደሚችል አስረድተዋል። ስምምነቱ የሚፈረመው አውሮፓ ውስጥ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
ስምምነቱ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት የሚያግድ እንዲሁም በአፋጣኝ የሆርሙዝ ወሽመጥ እንዲከፈት የሚያስገድድ እንደሚሆን ትራምፕ አስረግጠው ተናግረዋል።
ትራምፕ ይህንን ቢሉም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስምምነት ላይ ለመድረስ አለመቃረባቸውን አስታውቀዋል።
አሜሪካ በድርድሩ “ከልክ ያለፈ ጥያቄ” እያቀረበች እንደሆነም ጠቅሰዋል።
ኳታር ሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት እያደረገች እንደሆነ ተጠቁሟል።
ትራምፕ ኢራን ላይ ጥቃት እንደማይፈጸም መግለጻቸውን ተከትሎ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ቀንሷል።
BBC
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ላይ የሚሰነዘረው ጥቃት ‘እንደተገታ’ አስታወቁ።
ከኢራን ጋር የሚደረገው ውይይት መሻሻል እንዳሳየ እና ከስምምነት ሊደረስ እንደሚችልም ገልጸዋል።
ትራምፕ ትናንት ሐሙስ ኢራንን “ክፉኛ እንመታለን” ብለው ቢዝቱም፤ ሊያደርሱት የነበረውን ጥቃት ለመሰረዝ መወሰናቸውን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንቱ ኻርግ ደሴት ላይ ጥቃት እንደሚፈጸም አስጠንቅቀው ነበር።
ከኢራን ጋር የሚፈረመው የመግባቢያ ሰነድ “የመጨረሻ ደረጃ” ላይ መድረሱን ጠቅሰው በዚህ ሳምንት ስምምነቱ ሊገባደድ እንደሚችል አስረድተዋል። ስምምነቱ የሚፈረመው አውሮፓ ውስጥ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
ስምምነቱ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት የሚያግድ እንዲሁም በአፋጣኝ የሆርሙዝ ወሽመጥ እንዲከፈት የሚያስገድድ እንደሚሆን ትራምፕ አስረግጠው ተናግረዋል።
ትራምፕ ይህንን ቢሉም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስምምነት ላይ ለመድረስ አለመቃረባቸውን አስታውቀዋል።
አሜሪካ በድርድሩ “ከልክ ያለፈ ጥያቄ” እያቀረበች እንደሆነም ጠቅሰዋል።
ኳታር ሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት እያደረገች እንደሆነ ተጠቁሟል።
ትራምፕ ኢራን ላይ ጥቃት እንደማይፈጸም መግለጻቸውን ተከትሎ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ቀንሷል።
BBC
14 days ago
''ሰውየውን ማግኘት እፈልጋለሁ''
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
14 days ago
''ሰውየውን ማግኘት እፈልጋለሁ''
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
15 days ago
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት የትራምፕን የጦርነት ስልጣን ለመገደብ ድምፅ ሰጡ
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ተጨማሪ የወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስዱ የሚያግድ የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በየካቲት ወር የጀመረውን ጦርነት በአደባባይ በመቃወም አራት ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር ከተቀላቀሉ በኋላ፤ የውሳኔ ሃሳቡ በ2መቶ15 ለ 2መቶ8 ድምፅ ሊጸድቅ ችሏል።
ይህ የተወካዮች ምክር ቤት በትራምፕ የጦርነት ስልጣን ላይ ገደብ ለመጣል የሞከረው ለአራተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ተቺዎች ፕሬዝዳንቱ የኮንግረሱን ፈቃድ ሳያገኙ እርምጃ እየወሰዱ ነው በማለት ይወቅሳሉ።
የምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳብ አሁንም በሪፐብሊካኖች በሚመራው የአሜሪካ ሴኔት መፅደቅ ይኖርበታል፤ይሁን እንጂ ሴኔቱ ቢቀበለው እንኳ እርምጃው በኢራን ላይ የሚሰነዘረውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ለመግታት መቻሉ አጠራጣሪ ነው፡፡
ውሳኔው ከዚህ ቀደም ሰባት ጊዜ ሳይሳካ ቀርቶ ባለፈው ግንቦት ወር ሴኔቱ መሰል የውሳኔ ሃሳብን ያራመደ ቢሆንም እስካሁን ሙሉ ድምፅ ለመስጠት ወደ መድረክ አላመጣውም።
እሮብ ዕለት የተካሄደው ድምፅ በትራምፕ እና ሪፐብሊካን ፓርቲ ውስጥ ያለውን ልዩነት የሚያሳይ የቅርብ ጊዜ ምልክት ነው ፡፡
ይህ የሆነው ደግሞ በኮንግረስ ውስጥ ባሉ ወግ አጥባቂዎች ተቃውሞ ምክንያት አስተዳደሩ ለፖለቲካ አጋሮቹ ሊመድበው የነበረውን የ1.8 ቢሊየን ዶላር "ፀረ-የጦር መሣሪያ ታጣቂነት" ፈንድ ዕቅዱን ለመሰረዝ በተገደደ በጥቂት ቀናት ውስጥ ነው።
በተወካዮች ምክር ቤት የሚገኙ ቶማስ ማሲ፣ ብሪያን ፊትዝፓትሪክ፣ ቶም ባሬት እና ዋረን ዴቪድሰን የተባሉ ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር በመተባበር ረቡዕ ዕለት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በተጨማሪም ከዚህ ቀደም መሰል እርምጃዎችን ተቃውመው የነበሩት የሜይን ግዛት ዲሞክራት ጃሬድ ጎልደን በዚህ ጊዜ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
ከሚቺጋን የመጡት ሪፐብሊካን ቶም ባሬትበበኩላቸው "ጦርነት የሚያውጀው ኮንግረስ ብቻ ነው፤ ይህ ደግሞ በእርግጥ ልንጠብቀው የሚገባ ጉዳይ ነው" ብለዋል።
በዚህ ድምፅ አሰጣጥ ምክንያት ከትራምፕ ሊሰነዘርባቸው ስለሚችለው የአጸፋ እርምጃ ተጠይቀው ሲመልሱ፡ "ትክክል ነው ብዬ ላመንኩበት ነገር በህሊናዬ ነው ድምፅ የሰጠሁት እናም የሚመጣውን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነኝ" ብለዋል።
በተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ መሪ የሆኑት ዲሞክራቱ ግሬገሪ ሚክስ፣ የተሰጠውን ድምፅ "በፕሬዝዳንት ትራምፕ ህገ-ወጥ እና ከፍተኛ ኪሳራ እያስከተለ ባለው የኢራን ጦርነት ላይ የተሰነዘረ ጠንካራ የሁለቱ ፓርቲዎች ተግሳጽ እና ጦርነቱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማቆም የተነገደ የመጀመሪያው እርምጃ ነው" ሲሉ ገልጸውታል።
ሚክስ አክለውም ትራምፕ በሀገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ እንዲንር ከማድረጋቸው እና ለኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ የመፈለጉን ሂደት ይበልጥ አስቸጋሪ ከማድረጋቸው ባለፈ የጦርነቱን የተቀመጡ ግቦች ማሳካት አልቻሉም ብለዋል።
የውሳኔ ሃሳቡን በጋራ ያዘጋጁት ሚክስ "የዚህ ውሳኔ መጽደቅ ትልቅ የማዕዘን ድንጋይ ነው ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሪፐብሊካኖች በመካከለኛው ምስራቅ ሌላ ማብቂያ የሌለው ጦርነት የማይፈልጉትን የመራጮቻቸውን ድምፅ እየሰሙ ነው" ብለዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በየካቲት 28 በኢራን ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው የሚታወቁ ሲሆን ኢራንም በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው ለሚገኙ የአሜሪካ አጋር ሀገራት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ምላሽ የሰጠች ሲሆን ለአለም አቀፍ የመርከብ ትራንስፖርት ወሳኝ የውሃ መስመር የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ በውጤታማነት ዘግታለች።
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ተጨማሪ የወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስዱ የሚያግድ የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በየካቲት ወር የጀመረውን ጦርነት በአደባባይ በመቃወም አራት ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር ከተቀላቀሉ በኋላ፤ የውሳኔ ሃሳቡ በ2መቶ15 ለ 2መቶ8 ድምፅ ሊጸድቅ ችሏል።
ይህ የተወካዮች ምክር ቤት በትራምፕ የጦርነት ስልጣን ላይ ገደብ ለመጣል የሞከረው ለአራተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ተቺዎች ፕሬዝዳንቱ የኮንግረሱን ፈቃድ ሳያገኙ እርምጃ እየወሰዱ ነው በማለት ይወቅሳሉ።
የምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳብ አሁንም በሪፐብሊካኖች በሚመራው የአሜሪካ ሴኔት መፅደቅ ይኖርበታል፤ይሁን እንጂ ሴኔቱ ቢቀበለው እንኳ እርምጃው በኢራን ላይ የሚሰነዘረውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ለመግታት መቻሉ አጠራጣሪ ነው፡፡
ውሳኔው ከዚህ ቀደም ሰባት ጊዜ ሳይሳካ ቀርቶ ባለፈው ግንቦት ወር ሴኔቱ መሰል የውሳኔ ሃሳብን ያራመደ ቢሆንም እስካሁን ሙሉ ድምፅ ለመስጠት ወደ መድረክ አላመጣውም።
እሮብ ዕለት የተካሄደው ድምፅ በትራምፕ እና ሪፐብሊካን ፓርቲ ውስጥ ያለውን ልዩነት የሚያሳይ የቅርብ ጊዜ ምልክት ነው ፡፡
ይህ የሆነው ደግሞ በኮንግረስ ውስጥ ባሉ ወግ አጥባቂዎች ተቃውሞ ምክንያት አስተዳደሩ ለፖለቲካ አጋሮቹ ሊመድበው የነበረውን የ1.8 ቢሊየን ዶላር "ፀረ-የጦር መሣሪያ ታጣቂነት" ፈንድ ዕቅዱን ለመሰረዝ በተገደደ በጥቂት ቀናት ውስጥ ነው።
በተወካዮች ምክር ቤት የሚገኙ ቶማስ ማሲ፣ ብሪያን ፊትዝፓትሪክ፣ ቶም ባሬት እና ዋረን ዴቪድሰን የተባሉ ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር በመተባበር ረቡዕ ዕለት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በተጨማሪም ከዚህ ቀደም መሰል እርምጃዎችን ተቃውመው የነበሩት የሜይን ግዛት ዲሞክራት ጃሬድ ጎልደን በዚህ ጊዜ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
ከሚቺጋን የመጡት ሪፐብሊካን ቶም ባሬትበበኩላቸው "ጦርነት የሚያውጀው ኮንግረስ ብቻ ነው፤ ይህ ደግሞ በእርግጥ ልንጠብቀው የሚገባ ጉዳይ ነው" ብለዋል።
በዚህ ድምፅ አሰጣጥ ምክንያት ከትራምፕ ሊሰነዘርባቸው ስለሚችለው የአጸፋ እርምጃ ተጠይቀው ሲመልሱ፡ "ትክክል ነው ብዬ ላመንኩበት ነገር በህሊናዬ ነው ድምፅ የሰጠሁት እናም የሚመጣውን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነኝ" ብለዋል።
በተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ መሪ የሆኑት ዲሞክራቱ ግሬገሪ ሚክስ፣ የተሰጠውን ድምፅ "በፕሬዝዳንት ትራምፕ ህገ-ወጥ እና ከፍተኛ ኪሳራ እያስከተለ ባለው የኢራን ጦርነት ላይ የተሰነዘረ ጠንካራ የሁለቱ ፓርቲዎች ተግሳጽ እና ጦርነቱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማቆም የተነገደ የመጀመሪያው እርምጃ ነው" ሲሉ ገልጸውታል።
ሚክስ አክለውም ትራምፕ በሀገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ እንዲንር ከማድረጋቸው እና ለኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ የመፈለጉን ሂደት ይበልጥ አስቸጋሪ ከማድረጋቸው ባለፈ የጦርነቱን የተቀመጡ ግቦች ማሳካት አልቻሉም ብለዋል።
የውሳኔ ሃሳቡን በጋራ ያዘጋጁት ሚክስ "የዚህ ውሳኔ መጽደቅ ትልቅ የማዕዘን ድንጋይ ነው ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሪፐብሊካኖች በመካከለኛው ምስራቅ ሌላ ማብቂያ የሌለው ጦርነት የማይፈልጉትን የመራጮቻቸውን ድምፅ እየሰሙ ነው" ብለዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በየካቲት 28 በኢራን ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው የሚታወቁ ሲሆን ኢራንም በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው ለሚገኙ የአሜሪካ አጋር ሀገራት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ምላሽ የሰጠች ሲሆን ለአለም አቀፍ የመርከብ ትራንስፖርት ወሳኝ የውሃ መስመር የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ በውጤታማነት ዘግታለች።
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ወራትን ያስቆጠረውን ጦርነት ለማቆም ተጀምሮ የነበረው የተኩስ አቁም ስምምነት ድርድር ባለፈው የሳምንት መጨረሻ ያለ ምንም መሻሻል መጓተቱን ተከትሎ፣ አሜሪካ እና ኢራን አዳዲስ ጥቃቶችን መለዋወጣቸው ተነግሯል። የአሜሪካ ጦር በኢራን ላይ የራስ መከላከል ጥቃቶችን መፈጸሙን እና ወደ መርከቦች እንዲሁም የባህረ ሰላጤው ሀገራት የተተኮሱ የባሊስቲክ ሚሳኤሎችንና ድሮኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል። የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) በሆርሙዝ ስትሬት በምትገኘው ቄሽም ደሴት ላይ የፈጸመው ጥቃት፣ ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ለሞከረችው ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ መሆኑን ገልጿል። በዚህም የኢራን ወታደራዊ የምድር መቆጣጠሪያ ጣቢያ ዒላማ የተደረገ ሲሆን፣ በሕጋዊ መንገድ ቀጠናውን እያቋረጡ በነበሩ የሲቪል መርከበኞች ላይ የተተኮሱ ሦስት ድሮኖችን አሜሪካ አክሽፋለች። በተጨማሪም ወደ ኩዌት የተተኮሱ ሁለት የኢራን ሚሳኤሎች መንገድ ላይ ሲከሽፉ፣ ወደ ባህሬን የተተኮሱ ሦስት ሚሳኤሎች ደግሞ በአሜሪካ እና በባህሬን የአየር መከላከያ ኃይሎች መክሸፋቸው ተገልጿል።
በበኩሏ ኢራን ለአሜሪካ ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን በመጠቀም በአንድ የቀጠናው ሀገር ውስጥ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች እና ሄሊኮፕተሮች ላይ ጥቃት ማድረሷን አስታውቃለች። የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) የሆርሙዝ ስትሬትን ደህንነት ማወክ በአሜሪካ ጦር ላይ ከባድ ዋጋ ያስከፍላል ሲልም አስጠንቅቋል።
ከዚህ ቀደም የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ሚያዝያ 13 የጀመረውን የሆርሙዝ ስትሬት የባህር ላይ እገዳ አካል በማድረግ፣ ወደ ኢራኗ ኻርግ ደሴት በማምራት ላይ በነበረችው እና በቦትስዋና ባንዲራ በምትጓዘው 'ኤም/ቲ ሌክሲ' በተሰኘች ባዶ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት ማድረሱን ገልጿል። የመርከቧ ሰራተኞች በ24 ሰዓታት ውስጥ የተሰጣቸውን ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ባለመቀበላቸው፣ የአሜሪካ አውሮፕላን በመርከቧ የሞተር ክፍል ላይ የሄልፋየር ሚሳኤል የተኮሰ ሲሆን፣ አሜሪካ ይህ ጥቃት ሲፈጸም የሚያሳይ የቪዲዮ ምስል ይፋ አድርጋለች። የባህር ላይ እገዳው ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን 6 የንግድ መርከቦች ከጥቅም ውጪ ሲሆኑ፣ 122 መርከቦች ደግሞ አቅጣጫቸውን እንዲቀይሩ ተደርጓል።
ይህ ውጥረት የተባባሰው፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ሳምንት ተቺዎቻቸው ዘና እንዲሉ መክረው፣ ኢራን ስምምነት ላይ መድረስ እንደምትፈልግ እና ይህም ለአሜሪካ ጥሩ እንደሚሆን በተናገሩበት ወቅት ነው። የሲቢኤስ ኒውስ እንደዘገበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ሊኖር ስለሚችለው የሰላም ስምምነት ማዕቀፍ ማስተካከያ እንዲደረግ ጠይቀዋል። ማስተካከያው የሆርሙዝ ስትሬትን ጉዳይ፣ ከፍተኛ ማዕድን ያለው ዩራኒየምን ከኢራን ማውጣትን እና የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም በተመለከተ አዲስ ድርድር መክፈትን ያካተተ ነው። ሆኖም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኢል ባጋኢ ሰኞ ዕለት በሰጡት ምላሽ፣ ይህ ጉዳይ በድርድሩ ጠረጴዛ ላይ እንዳልነበረ ገልጸው፣ ዋሽንግተን ሁልጊዜ አቋሟን እንደምትቀይር እና አዳዲስ ወይም የሚጋጩ ፍላጎቶችን እንደምታቀርብ ከሰዋል።
ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሜሪካ ኮንግረስ ፊት ቀርበው ቃላቸውን የሰጡት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ አሜሪካ ስትሬቱን ክፍት ለማድረግ ስትል ለኢራን ማዕቀብ የማንሳት ጥያቄን አላቀረበችም ብለዋል። ማንኛውም ማዕቀብ የማንሳት ጉዳይ ማዕቀቦቹ በመጀመሪያ ከተጣሉበት ምክንያት፣ ማለትም ከኒውክሌር ፕሮግራማቸው ጋር የተያያዘ ቅድመ ሁኔታን መሰረት ያደረገ ነው በማለት አስረድተዋል። ኮሚቴው ውስጥ ካሉ ሴናተሮች ጋር በነበራቸው ውጥረት የበዛበት የቃላት ልውውጥ ወቅትም፣ ሚኒስትሩ ጦርነቱ አብቅቷል ማለታቸው ተዘግቧል።
በበኩሏ ኢራን ለአሜሪካ ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን በመጠቀም በአንድ የቀጠናው ሀገር ውስጥ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች እና ሄሊኮፕተሮች ላይ ጥቃት ማድረሷን አስታውቃለች። የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) የሆርሙዝ ስትሬትን ደህንነት ማወክ በአሜሪካ ጦር ላይ ከባድ ዋጋ ያስከፍላል ሲልም አስጠንቅቋል።
ከዚህ ቀደም የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ሚያዝያ 13 የጀመረውን የሆርሙዝ ስትሬት የባህር ላይ እገዳ አካል በማድረግ፣ ወደ ኢራኗ ኻርግ ደሴት በማምራት ላይ በነበረችው እና በቦትስዋና ባንዲራ በምትጓዘው 'ኤም/ቲ ሌክሲ' በተሰኘች ባዶ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት ማድረሱን ገልጿል። የመርከቧ ሰራተኞች በ24 ሰዓታት ውስጥ የተሰጣቸውን ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ባለመቀበላቸው፣ የአሜሪካ አውሮፕላን በመርከቧ የሞተር ክፍል ላይ የሄልፋየር ሚሳኤል የተኮሰ ሲሆን፣ አሜሪካ ይህ ጥቃት ሲፈጸም የሚያሳይ የቪዲዮ ምስል ይፋ አድርጋለች። የባህር ላይ እገዳው ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን 6 የንግድ መርከቦች ከጥቅም ውጪ ሲሆኑ፣ 122 መርከቦች ደግሞ አቅጣጫቸውን እንዲቀይሩ ተደርጓል።
ይህ ውጥረት የተባባሰው፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ሳምንት ተቺዎቻቸው ዘና እንዲሉ መክረው፣ ኢራን ስምምነት ላይ መድረስ እንደምትፈልግ እና ይህም ለአሜሪካ ጥሩ እንደሚሆን በተናገሩበት ወቅት ነው። የሲቢኤስ ኒውስ እንደዘገበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ሊኖር ስለሚችለው የሰላም ስምምነት ማዕቀፍ ማስተካከያ እንዲደረግ ጠይቀዋል። ማስተካከያው የሆርሙዝ ስትሬትን ጉዳይ፣ ከፍተኛ ማዕድን ያለው ዩራኒየምን ከኢራን ማውጣትን እና የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም በተመለከተ አዲስ ድርድር መክፈትን ያካተተ ነው። ሆኖም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኢል ባጋኢ ሰኞ ዕለት በሰጡት ምላሽ፣ ይህ ጉዳይ በድርድሩ ጠረጴዛ ላይ እንዳልነበረ ገልጸው፣ ዋሽንግተን ሁልጊዜ አቋሟን እንደምትቀይር እና አዳዲስ ወይም የሚጋጩ ፍላጎቶችን እንደምታቀርብ ከሰዋል።
ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሜሪካ ኮንግረስ ፊት ቀርበው ቃላቸውን የሰጡት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ አሜሪካ ስትሬቱን ክፍት ለማድረግ ስትል ለኢራን ማዕቀብ የማንሳት ጥያቄን አላቀረበችም ብለዋል። ማንኛውም ማዕቀብ የማንሳት ጉዳይ ማዕቀቦቹ በመጀመሪያ ከተጣሉበት ምክንያት፣ ማለትም ከኒውክሌር ፕሮግራማቸው ጋር የተያያዘ ቅድመ ሁኔታን መሰረት ያደረገ ነው በማለት አስረድተዋል። ኮሚቴው ውስጥ ካሉ ሴናተሮች ጋር በነበራቸው ውጥረት የበዛበት የቃላት ልውውጥ ወቅትም፣ ሚኒስትሩ ጦርነቱ አብቅቷል ማለታቸው ተዘግቧል።
19 days ago
ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደራደሩባቸው ነጥቦች የበለጠ እንዲጠናከሩ መጠየቃቸው ተዘገበ
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚደረገው ድርድር የቀረቡ በርካታ ነጥቦች ላይ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
ኒው ዮርክ ታይምስ እንደዘገበው፤ ትራምፕ የድርድር ነጥቦቹ የበለጠ እንዲጠናከሩ ይፈልጋሉ። እንደ አዲስ ክለሳ የተደረገበት የድርድር ማዕቀፍም ለኢራን ተልኳል።
አክሲዮስ ባወጣው ዘገባ፤ ከኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ዩራንየም የማበልጸግ ሒደት ጋር የሚያያዙ የድርድሩ ነጥቦች እንዲጠናከሩ ትራምፕ ጠይቀዋል።
ትራምፕ የስምምነቱን ረቂቅ ከተመለከቱ በኋላ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን ኒው ዮርክ ታይምስ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
ትራምፕ እንዲደረግ የጠየቁት ለውጥ ድርድሩን በምን መንገድ ሊቀይረው እንደሚችል ግልጽ አይደለም።
የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ክምችት ትራምፕ ጠንካራ ለውጥ እንዲደረግባቸው ከጠየቋቸው ነጥቦች መካከል እንደሚገኝበት አክሲዮስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት እነዚህ ለውጦች ድርድሩን በቀናት ሊያራዝሙ ይችላሉ።
ትራምፕ ባለፈው አርብ በዋይት ሀውስ አስቸኳይ ስብሰባ ቢያደርጉም የመጨረሻ ውሳኔያቸው ይፋ አልሆነም።
የስምምነቱ ረቂቅ የትራምፕን ይሁንታ እየጠበቀ እንደነበር ኤኤፍፒ ዘግቧል። የኢራን ባለሥልጣናትም ረቂቁን ማጽደቃቸውን አላሳወቁም።
BBC
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚደረገው ድርድር የቀረቡ በርካታ ነጥቦች ላይ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
ኒው ዮርክ ታይምስ እንደዘገበው፤ ትራምፕ የድርድር ነጥቦቹ የበለጠ እንዲጠናከሩ ይፈልጋሉ። እንደ አዲስ ክለሳ የተደረገበት የድርድር ማዕቀፍም ለኢራን ተልኳል።
አክሲዮስ ባወጣው ዘገባ፤ ከኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ዩራንየም የማበልጸግ ሒደት ጋር የሚያያዙ የድርድሩ ነጥቦች እንዲጠናከሩ ትራምፕ ጠይቀዋል።
ትራምፕ የስምምነቱን ረቂቅ ከተመለከቱ በኋላ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን ኒው ዮርክ ታይምስ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
ትራምፕ እንዲደረግ የጠየቁት ለውጥ ድርድሩን በምን መንገድ ሊቀይረው እንደሚችል ግልጽ አይደለም።
የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ክምችት ትራምፕ ጠንካራ ለውጥ እንዲደረግባቸው ከጠየቋቸው ነጥቦች መካከል እንደሚገኝበት አክሲዮስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት እነዚህ ለውጦች ድርድሩን በቀናት ሊያራዝሙ ይችላሉ።
ትራምፕ ባለፈው አርብ በዋይት ሀውስ አስቸኳይ ስብሰባ ቢያደርጉም የመጨረሻ ውሳኔያቸው ይፋ አልሆነም።
የስምምነቱ ረቂቅ የትራምፕን ይሁንታ እየጠበቀ እንደነበር ኤኤፍፒ ዘግቧል። የኢራን ባለሥልጣናትም ረቂቁን ማጽደቃቸውን አላሳወቁም።
BBC
23 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (ዩኤኢ) በሚገኘው የባራካህ የኒውክሌር ማብላያ ጣቢያ ላይ የተፈጸመውን የድሮን ጥቃት አጥብቆ አውግዟል።
ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ፣ ጥቃቱ የዓለም አቀፍ ህግን የጣሰ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን፤ ይሁን እንጂ ለጥቃቱ ማንንም አካል በግልጽ ተጠያቂ ከማድረግ ተቆጥቧል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀችው፣ ከኢራቅ ግዛት የተነሱ ስድስት የድሮን ጥቃቶች የተሰነዘሩባት ሲሆን፣ ከእነዚህም አንዱ በኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያው ላይ የእሳት አደጋ አስከትሏል።
ኢራቅ በኢራን የሚደገፉ ጠንካራ ታጣቂ ቡድኖች የሚንቀሳቀሱባት ሀገር መሆኗ ይታወቃል። እነዚህ ታጣቂ ቡድኖች አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ባካሄዱት ጦርነት ወቅት፣ "በኢራቅ እና በቀጠናው በሚገኙ የጠላት የጦር ሰፈሮች" ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ኃላፊነት ሲወስዱ ቆይተዋል ሲል ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ፣ ጥቃቱ የዓለም አቀፍ ህግን የጣሰ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን፤ ይሁን እንጂ ለጥቃቱ ማንንም አካል በግልጽ ተጠያቂ ከማድረግ ተቆጥቧል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀችው፣ ከኢራቅ ግዛት የተነሱ ስድስት የድሮን ጥቃቶች የተሰነዘሩባት ሲሆን፣ ከእነዚህም አንዱ በኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያው ላይ የእሳት አደጋ አስከትሏል።
ኢራቅ በኢራን የሚደገፉ ጠንካራ ታጣቂ ቡድኖች የሚንቀሳቀሱባት ሀገር መሆኗ ይታወቃል። እነዚህ ታጣቂ ቡድኖች አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ባካሄዱት ጦርነት ወቅት፣ "በኢራቅ እና በቀጠናው በሚገኙ የጠላት የጦር ሰፈሮች" ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ኃላፊነት ሲወስዱ ቆይተዋል ሲል ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
Sponsored by
Surafel
26 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ሊያደርጉት ነው በተባለው አዲስ ስምምነት ዙሪያ፣ የሪፐብሊካን ፓርቲ ታላላቅ ፖለቲከኞች የተለያየ እና የሚጋጭ አቋም እያንጸባረቁ ይገኛሉ። እስካሁን በይፋ የተደረሰ ስምምነትም ሆነ የወጣ ዝርዝር መረጃ ባይኖርም፣ ሊኖር ይችላል የተባለው ስምምነት በፓርቲው ውስጥ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።
ታዋቂው ሴኔተር ቴድ ክሩዝ በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ስጋት እንዳደረባቸው ገልጸዋል። ሴኔተሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸው ትክክለኛ እርምጃ ቢሆንም፣ ስምምነቱ ኢራን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንድታገኝ፣ ዩራኒየም እንድታበለጽግ፣ የኒውክሌር መሳሪያ እንድትሰራ እና የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን እንድትቆጣጠር የሚፈቅድ ከሆነ ግን "አስከፊ ስህተት" ይሆናል በማለት አጥብቀው አስጠንቅቀዋል።
በተመሳሳይ ሴኔተር ቶም ቲሊስ ሂደቱ ትርጉም እንደማይሰጣቸው ተናግረዋል። የመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴዝ ከሳምንታት በፊት የኢራን መከላከያ ሙሉ በሙሉ መውደሙን እና የኒውክሌር ማዕድኑን በእጅ ማስገባት የጊዜ ጉዳይ ብቻ መሆኑን ተናግረው እንደነበር ያስታወሱት ሴኔተሩ፣ አሁን ላይ የኒውክሌር ማቴሪያሉ በኢራን ውስጥ ሊቀር እንደሚችል የሚጠቁሙ ሀሳቦች ለምን እንደሚነሱ በጥያቄ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ስምምነቱን በአዎንታዊ መልኩ የሚመለከቱ የፓርቲው አባላት አልጠፉም። ኮንግረስማን ቶማስ ማሲ ለኤንቢሲ (NBC) በሰጡት አስተያየት፣ እንደ ሊንድሴይ ግርሃም እና ቴድ ክሩዝ ያሉ ሴኔተሮች ስምምነቱን አጥብቀው የሚቃወሙት ከሆነ፣ ስምምነቱ "በጣም ጥሩ" ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።
ኮንግረስማን ማሲ ባለፈው ዓመት የአሜሪካ ጦር ያለ ኮንግረሱ ፈቃድ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስድ የሚከለክል የውሳኔ ሀሳብ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል።
እንዲሁም የሴኔቱ አብላጫ ድምጽ አስተባባሪ የሆኑት ጆን ባራሶ፣ የስምምነቱ ዝርዝር ሁኔታ ገና ባይታወቅም፣ የትራምፕ የሀይል እርምጃ እና የአሜሪካ ጥንካሬ ኢራንን ተገዳ ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንድትመጣ አድርጓታል በማለት ለሂደቱ ያላቸውን አዎንታዊ አቋም አንጸባርቀዋል።
ታዋቂው ሴኔተር ቴድ ክሩዝ በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ስጋት እንዳደረባቸው ገልጸዋል። ሴኔተሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸው ትክክለኛ እርምጃ ቢሆንም፣ ስምምነቱ ኢራን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንድታገኝ፣ ዩራኒየም እንድታበለጽግ፣ የኒውክሌር መሳሪያ እንድትሰራ እና የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን እንድትቆጣጠር የሚፈቅድ ከሆነ ግን "አስከፊ ስህተት" ይሆናል በማለት አጥብቀው አስጠንቅቀዋል።
በተመሳሳይ ሴኔተር ቶም ቲሊስ ሂደቱ ትርጉም እንደማይሰጣቸው ተናግረዋል። የመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴዝ ከሳምንታት በፊት የኢራን መከላከያ ሙሉ በሙሉ መውደሙን እና የኒውክሌር ማዕድኑን በእጅ ማስገባት የጊዜ ጉዳይ ብቻ መሆኑን ተናግረው እንደነበር ያስታወሱት ሴኔተሩ፣ አሁን ላይ የኒውክሌር ማቴሪያሉ በኢራን ውስጥ ሊቀር እንደሚችል የሚጠቁሙ ሀሳቦች ለምን እንደሚነሱ በጥያቄ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ስምምነቱን በአዎንታዊ መልኩ የሚመለከቱ የፓርቲው አባላት አልጠፉም። ኮንግረስማን ቶማስ ማሲ ለኤንቢሲ (NBC) በሰጡት አስተያየት፣ እንደ ሊንድሴይ ግርሃም እና ቴድ ክሩዝ ያሉ ሴኔተሮች ስምምነቱን አጥብቀው የሚቃወሙት ከሆነ፣ ስምምነቱ "በጣም ጥሩ" ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።
ኮንግረስማን ማሲ ባለፈው ዓመት የአሜሪካ ጦር ያለ ኮንግረሱ ፈቃድ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስድ የሚከለክል የውሳኔ ሀሳብ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል።
እንዲሁም የሴኔቱ አብላጫ ድምጽ አስተባባሪ የሆኑት ጆን ባራሶ፣ የስምምነቱ ዝርዝር ሁኔታ ገና ባይታወቅም፣ የትራምፕ የሀይል እርምጃ እና የአሜሪካ ጥንካሬ ኢራንን ተገዳ ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንድትመጣ አድርጓታል በማለት ለሂደቱ ያላቸውን አዎንታዊ አቋም አንጸባርቀዋል።
26 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በኢራን ጉዳይ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ጥልቅ እና ወሳኝ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ እንዳሰፈሩት፣ የሁለቱ መሪዎች ውይይት የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን መልሶ ለመክፈት በተደረሰው የመግባቢያ ሰነድ እና በኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ዙሪያ ወደፊት በሚደረገው የመጨረሻው የድርድር ሂደት ላይ ያተኮረ ነበር።
ኔታንያሁ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለእስራኤል ደህንነት ላሳዩት የማይናወጥ ቁርጠኝነት ጥልቅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተለይም "ኦፕሬሽን ሮሪንግ ላይየን" እና "ኤፒክ ፊዩሪ" በተባሉት ወታደራዊ ዘመቻዎች የአሜሪካ እና የእስራኤል ጦር የኢራንን ስጋት ለመመከት ትከሻ ለትከሻ ተሰልፈው መዋጋታቸውን በኩራት አስታውሰዋል።
በውይይታቸው ወቅት ሁለቱ መሪዎች ከኢራን ጋር የሚደረግ ማንኛውም የመጨረሻ ስምምነት የኒውክሌር አደጋን ሙሉ በሙሉ ማስወገድ እንዳለበት በጽኑ ተስማምተዋል። ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የኢራንን የኒውክሌር ማበልጸጊያ ጣቢያዎችን ሙሉ በሙሉ ማፍረስ እና የበለጸገውን የኒውክሌር ማዕድን ከኢራን ግዛት ጠራርጎ ማስወጣት የግድ እንደሚል አስምረውበታል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በበኩላቸው፣ እስራኤል ሊባኖስን ጨምሮ በየትኛውም ግንባር ከሚቃጣባት ጥቃት እና ስጋት ራስዋን የመከላከል ሙሉ መብት እንዳላት ዳግም አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ መግለጫቸውን ሲያጠቃልሉ፣ በእነርሱ እና በሀገሮቻቸው መካከል ያለው አጋርነት በጦር ሜዳ የተረጋገጠ እና ከምንጊዜውም በላይ የጠነከረ መሆኑን ገልጸው፣ የሁለቱም መሪዎች ፖሊሲ አሁንም እንዳልተቀየረ እና ኢራን የኒውክሌር መሳሪያ ፈጽሞ እንደማይኖራት በማሳሰብ የጋራ አቋማቸውን አስተጋብተዋል።
ኔታንያሁ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለእስራኤል ደህንነት ላሳዩት የማይናወጥ ቁርጠኝነት ጥልቅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተለይም "ኦፕሬሽን ሮሪንግ ላይየን" እና "ኤፒክ ፊዩሪ" በተባሉት ወታደራዊ ዘመቻዎች የአሜሪካ እና የእስራኤል ጦር የኢራንን ስጋት ለመመከት ትከሻ ለትከሻ ተሰልፈው መዋጋታቸውን በኩራት አስታውሰዋል።
በውይይታቸው ወቅት ሁለቱ መሪዎች ከኢራን ጋር የሚደረግ ማንኛውም የመጨረሻ ስምምነት የኒውክሌር አደጋን ሙሉ በሙሉ ማስወገድ እንዳለበት በጽኑ ተስማምተዋል። ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የኢራንን የኒውክሌር ማበልጸጊያ ጣቢያዎችን ሙሉ በሙሉ ማፍረስ እና የበለጸገውን የኒውክሌር ማዕድን ከኢራን ግዛት ጠራርጎ ማስወጣት የግድ እንደሚል አስምረውበታል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በበኩላቸው፣ እስራኤል ሊባኖስን ጨምሮ በየትኛውም ግንባር ከሚቃጣባት ጥቃት እና ስጋት ራስዋን የመከላከል ሙሉ መብት እንዳላት ዳግም አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ መግለጫቸውን ሲያጠቃልሉ፣ በእነርሱ እና በሀገሮቻቸው መካከል ያለው አጋርነት በጦር ሜዳ የተረጋገጠ እና ከምንጊዜውም በላይ የጠነከረ መሆኑን ገልጸው፣ የሁለቱም መሪዎች ፖሊሲ አሁንም እንዳልተቀየረ እና ኢራን የኒውክሌር መሳሪያ ፈጽሞ እንደማይኖራት በማሳሰብ የጋራ አቋማቸውን አስተጋብተዋል።
26 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ስማቸው ያልተጠቀሰ አንድ የእስራኤል ባለስልጣን በአሜሪካ እና በኢራን መካከል እየተደረገ ባለው ስምምነት ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ስጋት ገልጸዋል። ባለስልጣኑ ለቻናል 12 የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል፣ አሁን እየተረቀቀ ያለው ስምምነት "መጥፎ" መሆኑን ተናግረዋል።
የስምምነቱ ማዕቀፍ ቴህራን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን ከኒውክሌር መሳሪያ ባልተናነሰ መልኩ እንደ ጦር መሳሪያ አድርጋ መጠቀም እንደምትችል የሚያሳይ እና የሚያስተምር መሆኑን ባለስልጣኑ አስረድተዋል።
እነዚህ ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣን አክለውም፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስምምነቱ በኢኮኖሚ ላይ የተመሰረተ እንደሚሆን ያምናሉ ብለዋል።
ይህም ማለት በኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ላይ ምንም አይነት የድርድር ለውጥ እና ማቋረጫ ላይ ሳይደረስ ይህን ወሳኝ የዓለም የውሃ ላይ መስመር (የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን) ክፍት ለማድረግ እንደሚያስችል ፕሬዝዳንቱ ማሰባቸውን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ባለስልጣኑ ለዜና አውታሩ እንደገለጹት፣ ይህ የመጀመርያው የስምምነት ምዕራፍ ከተጠናቀቀ በኋላ ቀጣዩ ደረጃ ምን ሊሆን እንደሚችል እስካሁን ምንም የታወቀና ግልጽ የሆነ ነገር የለም።
የስምምነቱ ማዕቀፍ ቴህራን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን ከኒውክሌር መሳሪያ ባልተናነሰ መልኩ እንደ ጦር መሳሪያ አድርጋ መጠቀም እንደምትችል የሚያሳይ እና የሚያስተምር መሆኑን ባለስልጣኑ አስረድተዋል።
እነዚህ ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣን አክለውም፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስምምነቱ በኢኮኖሚ ላይ የተመሰረተ እንደሚሆን ያምናሉ ብለዋል።
ይህም ማለት በኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ላይ ምንም አይነት የድርድር ለውጥ እና ማቋረጫ ላይ ሳይደረስ ይህን ወሳኝ የዓለም የውሃ ላይ መስመር (የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን) ክፍት ለማድረግ እንደሚያስችል ፕሬዝዳንቱ ማሰባቸውን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ባለስልጣኑ ለዜና አውታሩ እንደገለጹት፣ ይህ የመጀመርያው የስምምነት ምዕራፍ ከተጠናቀቀ በኋላ ቀጣዩ ደረጃ ምን ሊሆን እንደሚችል እስካሁን ምንም የታወቀና ግልጽ የሆነ ነገር የለም።
27 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር እየተደረገ ያለው ስምምነት "በአብዛኛው ድርድር የተደረገበት እና የተጠናቀቀ" መሆኑን ገልጸው፣ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ያደረጉት የስልክ ውይይትም የተሳካ እንደነበር አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንቱ ኔታንያሁን በማያካትተው እና ከሌሎች የመካከለኛው ምስራቅ መሪዎች ጋር ባደረጉት ሌላ የስልክ ውይይትም ስኬታማ ንግግር ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። ይህ አዲስ ስምምነት፣ ጦርነቱ ከጀመረበት ካለፉት ሶስት ወራት አንስቶ በቴህራን ተዘግቶ የቆየውን እና ለዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት እጅግ ወሳኝ የሆነውን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ክፍት ማድረግን እንደሚያካትት ተነግሯል።
ይሁን እንጂ ትራምፕ በጦርነቱ ወቅት ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳታገኝ እንደሚከለክሉ እና ያላትን 60 በመቶ የበለጸገ የዩራኒየም ክምችት እንድታስረክብ ሲያሳስቡ ቢቆዩም፣ አሁን በተደረገው ስምምነት ማብራሪያ ላይ ስለ ኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ያነሱት ነገር የለም።
ትራምፕ በ'ትሩዝ ሶሻል' ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ በዋይት ሀውስ ኦቫል ኦፊስ ሆነው ከቀጠናው ሀገራት መሪዎች ጋር የሰላም መግባቢያ ሰነድን በተመለከተ "በጣም ጥሩ የስልክ ውይይት" ማድረጋቸውን ገልጸዋል። አክለውም "በአሜሪካ፣ በኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ ኢራን እና በሌሎችም ሀገራት መካከል የሚደረገው ይህ ስምምነት በአብዛኛው ድርድር የተደረገበት ሲሆን፣ የመጨረሻ ማጽደቂያዎችን ብቻ የሚጠብቅ ነው" ብለዋል።
በእስራኤል በኩል ግን የስምምነቱን ውሎች በተመለከተ ከፍተኛ ስጋት መኖሩ ተዘግቧል። ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁም ይህንኑ ጉዳይ ለመወያየት የጥምረት መንግስቱን መሪዎች እና የጸጥታ ሀላፊዎችን ዛሬ ማምሻውን ሰብስበዋል።
ምንም እንኳን በእስራኤል በኩል ስጋቶች ቢኖሩም፣ ትራምፕ ከእስራኤሉ አቻቸው ጋር የነበራቸው ቆይታ አዎንታዊ መሆኑን ጽፈዋል። "ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢቢ ኔታንያሁ ጋር ለብቻው ያደረግኩት የስልክ ውይይት በጣም በጥሩ ሁኔታ ተጠናቋል" ያሉት ትራምፕ፣ "የስምምነቱ የመጨረሻ ዝርዝር ጉዳዮች አሁን ላይ እየተመከረባቸው ሲሆን በቅርቡም ይፋ ይደረጋሉ። ከሌሎች የስምምነቱ አካላት በተጨማሪ፣ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤም ክፍት ይሆናል" በማለት አረጋግጠዋል።
ፕሬዝዳንቱ ኔታንያሁን በማያካትተው እና ከሌሎች የመካከለኛው ምስራቅ መሪዎች ጋር ባደረጉት ሌላ የስልክ ውይይትም ስኬታማ ንግግር ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። ይህ አዲስ ስምምነት፣ ጦርነቱ ከጀመረበት ካለፉት ሶስት ወራት አንስቶ በቴህራን ተዘግቶ የቆየውን እና ለዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት እጅግ ወሳኝ የሆነውን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ክፍት ማድረግን እንደሚያካትት ተነግሯል።
ይሁን እንጂ ትራምፕ በጦርነቱ ወቅት ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳታገኝ እንደሚከለክሉ እና ያላትን 60 በመቶ የበለጸገ የዩራኒየም ክምችት እንድታስረክብ ሲያሳስቡ ቢቆዩም፣ አሁን በተደረገው ስምምነት ማብራሪያ ላይ ስለ ኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ያነሱት ነገር የለም።
ትራምፕ በ'ትሩዝ ሶሻል' ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ በዋይት ሀውስ ኦቫል ኦፊስ ሆነው ከቀጠናው ሀገራት መሪዎች ጋር የሰላም መግባቢያ ሰነድን በተመለከተ "በጣም ጥሩ የስልክ ውይይት" ማድረጋቸውን ገልጸዋል። አክለውም "በአሜሪካ፣ በኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ ኢራን እና በሌሎችም ሀገራት መካከል የሚደረገው ይህ ስምምነት በአብዛኛው ድርድር የተደረገበት ሲሆን፣ የመጨረሻ ማጽደቂያዎችን ብቻ የሚጠብቅ ነው" ብለዋል።
በእስራኤል በኩል ግን የስምምነቱን ውሎች በተመለከተ ከፍተኛ ስጋት መኖሩ ተዘግቧል። ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁም ይህንኑ ጉዳይ ለመወያየት የጥምረት መንግስቱን መሪዎች እና የጸጥታ ሀላፊዎችን ዛሬ ማምሻውን ሰብስበዋል።
ምንም እንኳን በእስራኤል በኩል ስጋቶች ቢኖሩም፣ ትራምፕ ከእስራኤሉ አቻቸው ጋር የነበራቸው ቆይታ አዎንታዊ መሆኑን ጽፈዋል። "ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢቢ ኔታንያሁ ጋር ለብቻው ያደረግኩት የስልክ ውይይት በጣም በጥሩ ሁኔታ ተጠናቋል" ያሉት ትራምፕ፣ "የስምምነቱ የመጨረሻ ዝርዝር ጉዳዮች አሁን ላይ እየተመከረባቸው ሲሆን በቅርቡም ይፋ ይደረጋሉ። ከሌሎች የስምምነቱ አካላት በተጨማሪ፣ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤም ክፍት ይሆናል" በማለት አረጋግጠዋል።
27 days ago
#ethiopia | ቻይና እና የኢትዮጵያን ኒውክሌር | ልጄን አፋልጉኝ | እርምጃ እንወስዳለን | ሀገራችሁ ገብታችሁ ተከራከሩ | የክትባቱ ነገር
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
28 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና | ዋሽንግተን) የትራምፕ አስተዳደር በኢራን ላይ አዲስ ዙር ወታደራዊ ጥቃት ለመክፈት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጮች አርብ ዕለት አስታወቁ። ይሁን እንጂ የዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አሁንም የቀጠሉ ሲሆን፣ እስከ አርብ ከሰዓት በኋላ ድረስ በጥቃቱ መከፈት ላይ የተሰጠ የመጨረሻ ውሳኔ የለም።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልእክት፣ "ከመንግስት ስራ ጋር በተያያዙ አጣዳፊ ሁኔታዎች" ምክንያት በዚህ የሳምንት መጨረሻ በሚካሄደው የልጃቸው ዶናልድ ትራምፕ ጁኒየር የሰርግ ስነስርዓት ላይ መገኘት እንደማይችሉ ገልጸዋል። በመጀመሪያ የመታሰቢያ ቀን (Memorial Day) የሳምንት መጨረሻ በዓልን በኒው ጀርሲ በሚገኘው የጎልፍ ማረፊያቸው ለማሳለፍ አቅደው የነበረ ቢሆንም፣ ክስተቶችን ተከትሎ ወደ ዋይት ሀውስ እንደሚመለሱ ታውቋል።
ሊኖር ይችላል ተብሎ በሚጠበቀው አዲስ ጥቃት ምክንያት፣ አንዳንድ የአሜሪካ ጦር እና የስለላ ማህበረሰብ አባላት የመታሰቢያ ቀን የዕረፍት ዕቅዳቸውን መሰረዛቸውን በርካታ ምንጮች ጠቁመዋል። የመከላከያ እና የስለላ ባለስልጣናት በባህር ማዶ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ውስጥ ያሉ ወታደሮች ዝርዝር ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ሲሆን፤ ይህ እርምጃ ኢራን ልትወስድ ከምትችለው የአጸፋ ጥቃት ስጋት አንጻር በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን የአሜሪካ ጦር ቁጥር ለመቀነስ ያለመ ነው።
አሜሪካ እና ኢራን ከሚያዝያ ወር መጀመሪያ አንስቶ በነበረው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ምክንያት እርስ በእርስ ከመጠቃቃት ተቆጥበው የቆዩ ሲሆን፣ ይህ ጊዜም ዘላቂ ስምምነት ላይ ለመድረስ ለሚደረገው ቀጥተኛ ያልሆነ ድርድር ዕድል የሰጠ ነበር። የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ አና ኬሊ ለሲቢኤስ ኒውስ እንደተናገሩት፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "ኢራን መቼም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት መሆን አትችልም፤ እንዲሁም ያበለጸገችውን ዩራኒየም ማስቀመጥ አትችልም" በማለት ቀይ መስመራቸውን በሚገባ ግልጽ አድርገዋል። አክለውም፣ ፕሬዝዳንቱ ሁልጊዜም ሁሉንም አማራጮች እንደሚያስቀምጡ እና ኢራን ስምምነት ላይ መድረስ ካልቻለች የሚጠብቃትን መዘዝ አስጠንቅቀዋል ብለዋል።
በሌላ በኩል የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ረቡዕ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ ከአሜሪካም ሆነ ከእስራኤል በሀገሪቱ ላይ ተጨማሪ ጥቃት ከተሰነዘረ፣ ግጭቱ ከመካከለኛው ምስራቅም አልፎ ሊሰፋ እንደሚችል እና ማንም ሊገምተው በማይችለው ቦታ ላይ አውዳሚ ምት እንደሚሰጥ አጸፋዊ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል።
ቴህራን ወደ ሶስት ወር ገደማ የተጠጋውን እና የዓለምን የነዳጅ ገበያ በማናወጥ ዋጋ ያንረውን ጦርነት ለማስቆም የቀረበላትን የቅርብ ጊዜ የአሜሪካ የውሳኔ ሃሳብ እየገመገመች ትገኛለች። ረቡዕ ዕለት ለኢራን የተላከው ይህ ሰነድ፣ "የመጨረሻው ግብዣ" መሆኑን እና ይህ ውድቅ ከተደረገ ወታደራዊ ጥቃቱ እንደገና እንደሚቀጥል የሚያስጠነቅቅ መልዕክት አብሮት እንደነበር ምንጮች አመልክተዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ አርብ ዕለት፣ "ኢራን ስምምነት ለማድረግ እጅግ ጓጉታለች፣ ምን እንደሚፈጠር አብረን እናያለን" ሲሉ የኢራንን ምላሽ ለመጠበቅ ጥቂት ቀናት እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
ከማቅናታቸው በፊት ለጋዜጠኞች እንደገለጹት፣ አሜሪካ የኢራንን ምላሽ እንደ ዋነኛ አገናኝ ሆኖ እያገለገለ ባለው የፓኪስታን አምባሳደር (ፊልድ ማርሻል) በኩል ትጠብቃለች። ሩቢዮ ትራምፕ ከጥቃት ይልቅ ለዲፕሎማሲ ቅድሚያ እንደሚሰጡ እና በድርድሩ መሻሻሎች ቢኖሩም ገና ብዙ መስራት እንደሚቀር ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ፣ ኢራን በራሷ ፈቃድ የሆርሙዝ ባህር ሰላጤን ክፍት የማታደርግ ከሆነ፣ በወታደራዊ ኃይል አስገድዶ ለመክፈት ከኔቶ አጋሮች ጋር በስዊድን ውይይት መደረጉን እና ይህም እንደ "ፕላን ቢ" (Plan B) መያዙን አመላክተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በዋሽንግተን የሚገኙ የሪፐብሊካን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስልጣናቸውን የሚገድብ የውሳኔ ሃሳብ ለማሳለፍ ጀምረውት የነበረውን ጥረት አቋርጠዋል። አባላቱ ይህንን ያደረጉት ውሳኔውን ለማሳለፍ የሚያስችል በቂ የድምጽ ድጋፍ ማግኘት እንደማይችሉ በማረጋገጣቸው ነው።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልእክት፣ "ከመንግስት ስራ ጋር በተያያዙ አጣዳፊ ሁኔታዎች" ምክንያት በዚህ የሳምንት መጨረሻ በሚካሄደው የልጃቸው ዶናልድ ትራምፕ ጁኒየር የሰርግ ስነስርዓት ላይ መገኘት እንደማይችሉ ገልጸዋል። በመጀመሪያ የመታሰቢያ ቀን (Memorial Day) የሳምንት መጨረሻ በዓልን በኒው ጀርሲ በሚገኘው የጎልፍ ማረፊያቸው ለማሳለፍ አቅደው የነበረ ቢሆንም፣ ክስተቶችን ተከትሎ ወደ ዋይት ሀውስ እንደሚመለሱ ታውቋል።
ሊኖር ይችላል ተብሎ በሚጠበቀው አዲስ ጥቃት ምክንያት፣ አንዳንድ የአሜሪካ ጦር እና የስለላ ማህበረሰብ አባላት የመታሰቢያ ቀን የዕረፍት ዕቅዳቸውን መሰረዛቸውን በርካታ ምንጮች ጠቁመዋል። የመከላከያ እና የስለላ ባለስልጣናት በባህር ማዶ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ውስጥ ያሉ ወታደሮች ዝርዝር ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ሲሆን፤ ይህ እርምጃ ኢራን ልትወስድ ከምትችለው የአጸፋ ጥቃት ስጋት አንጻር በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን የአሜሪካ ጦር ቁጥር ለመቀነስ ያለመ ነው።
አሜሪካ እና ኢራን ከሚያዝያ ወር መጀመሪያ አንስቶ በነበረው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ምክንያት እርስ በእርስ ከመጠቃቃት ተቆጥበው የቆዩ ሲሆን፣ ይህ ጊዜም ዘላቂ ስምምነት ላይ ለመድረስ ለሚደረገው ቀጥተኛ ያልሆነ ድርድር ዕድል የሰጠ ነበር። የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ አና ኬሊ ለሲቢኤስ ኒውስ እንደተናገሩት፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "ኢራን መቼም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት መሆን አትችልም፤ እንዲሁም ያበለጸገችውን ዩራኒየም ማስቀመጥ አትችልም" በማለት ቀይ መስመራቸውን በሚገባ ግልጽ አድርገዋል። አክለውም፣ ፕሬዝዳንቱ ሁልጊዜም ሁሉንም አማራጮች እንደሚያስቀምጡ እና ኢራን ስምምነት ላይ መድረስ ካልቻለች የሚጠብቃትን መዘዝ አስጠንቅቀዋል ብለዋል።
በሌላ በኩል የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ረቡዕ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ ከአሜሪካም ሆነ ከእስራኤል በሀገሪቱ ላይ ተጨማሪ ጥቃት ከተሰነዘረ፣ ግጭቱ ከመካከለኛው ምስራቅም አልፎ ሊሰፋ እንደሚችል እና ማንም ሊገምተው በማይችለው ቦታ ላይ አውዳሚ ምት እንደሚሰጥ አጸፋዊ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል።
ቴህራን ወደ ሶስት ወር ገደማ የተጠጋውን እና የዓለምን የነዳጅ ገበያ በማናወጥ ዋጋ ያንረውን ጦርነት ለማስቆም የቀረበላትን የቅርብ ጊዜ የአሜሪካ የውሳኔ ሃሳብ እየገመገመች ትገኛለች። ረቡዕ ዕለት ለኢራን የተላከው ይህ ሰነድ፣ "የመጨረሻው ግብዣ" መሆኑን እና ይህ ውድቅ ከተደረገ ወታደራዊ ጥቃቱ እንደገና እንደሚቀጥል የሚያስጠነቅቅ መልዕክት አብሮት እንደነበር ምንጮች አመልክተዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ አርብ ዕለት፣ "ኢራን ስምምነት ለማድረግ እጅግ ጓጉታለች፣ ምን እንደሚፈጠር አብረን እናያለን" ሲሉ የኢራንን ምላሽ ለመጠበቅ ጥቂት ቀናት እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
ከማቅናታቸው በፊት ለጋዜጠኞች እንደገለጹት፣ አሜሪካ የኢራንን ምላሽ እንደ ዋነኛ አገናኝ ሆኖ እያገለገለ ባለው የፓኪስታን አምባሳደር (ፊልድ ማርሻል) በኩል ትጠብቃለች። ሩቢዮ ትራምፕ ከጥቃት ይልቅ ለዲፕሎማሲ ቅድሚያ እንደሚሰጡ እና በድርድሩ መሻሻሎች ቢኖሩም ገና ብዙ መስራት እንደሚቀር ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ፣ ኢራን በራሷ ፈቃድ የሆርሙዝ ባህር ሰላጤን ክፍት የማታደርግ ከሆነ፣ በወታደራዊ ኃይል አስገድዶ ለመክፈት ከኔቶ አጋሮች ጋር በስዊድን ውይይት መደረጉን እና ይህም እንደ "ፕላን ቢ" (Plan B) መያዙን አመላክተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በዋሽንግተን የሚገኙ የሪፐብሊካን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስልጣናቸውን የሚገድብ የውሳኔ ሃሳብ ለማሳለፍ ጀምረውት የነበረውን ጥረት አቋርጠዋል። አባላቱ ይህንን ያደረጉት ውሳኔውን ለማሳለፍ የሚያስችል በቂ የድምጽ ድጋፍ ማግኘት እንደማይችሉ በማረጋገጣቸው ነው።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥምረት በኢራን ላይ የተከፈተውን ጦርነት ተከትሎ፣ የእስራኤል የደህንነት አካላት የኢራንን መንግስት ለመገልበጥ አቅደውት የነበረው እጅግ አስገራሚ ሚስጥራዊ ዕቅድ ይፋ መሆኑን ኒው ዮርክ ታይምስ ዘገበ። እንደ ዘገባው ከሆነ፣ ዕቅዱ በጦርነቱ መጀመሪያ ላይ የኢራኑን የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒን እና ሌሎች ከፍተኛ የሀገሪቱን ባለስልጣናት በመግደል፣ በምትካቸው የቀድሞውን አወዛጋቢ ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድን አዲስ የኢራን መሪ አድርጎ መሾም የሚል ነበር።
የሆሎኮስት (የአይሁዶች እልቂት) እውነታን በመካድ እና "እስራኤል ከካርታ ላይ መጥፋት አለባት" በሚሉ ቀስቃሽ ንግግሮቹ የሚታወቀው እንዲሁም የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም በፅኑ ሲደግፍ የነበረው አህመዲነጃድ ለዚህ ቦታ መመረጡ፣ ለኢራን የፖለቲካ ተንታኞች እጅግ ያልተጠበቀ እና አስገራሚ ምርጫ ሆኖባቸዋል። ኒው ዮርክ ታይምስ እንደገለጸው፣ አህመዲነጃድ ከዚህ ቀደም ከኢራኑ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ጠንከር ያለ የፖለቲካ ቅራኔ ውስጥ ገብቶ በቁም እስረኝነት ላይ ይገኝ የነበረ ቢሆንም፣ እስራኤል ግን እሱን እንደ አማራጭ መሪ ለመጠቀም ሚስጥራዊ ምክክር አድርጋበት ነበር።
ነገር ግን ዕቅዱ ሳይሳካ የቀረው አህመዲነጃድ ከቁም እስራት ለማምለጥ ሲሞክር በእስራኤል የአየር ድብደባ ሳቢያ ቴህራን ውስጥ በመቁሰሉ እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በአደባባይ ባለመታየቱ እንደሆነ ተገልጿል። እስራኤል ካዘጋጀቻቸው ዘርፈ ብዙ የጦርነት ምዕራፎች መካከል የመጀመሪያው በአሜሪካ እና በእስራኤል የአየር ጥቃት የኢራን መሪዎችን መምታት እና የኩርድ ታጣቂዎችን በኢራን ላይ ማሰለፍ የነበረ ቢሆንም፣ የኩርዶች ወረራ ግን ሳይሳካ ቀርቷል። ሆኖም እስራኤል በደረሰው የፖለቲካ ጫና እና በዋና ዋና መሰረተ ልማቶች ላይ በደረሰው ውድመት ሳቢያ የኢራን ገዥ መደብ ሙሉ በሙሉ ይፈራርሳል፤ ከዚያም ያዘጋጀነው "አማራጭ መንግስት" ስልጣኑን ይረከባል የሚል እምነት ነበራት።
የሆሎኮስት (የአይሁዶች እልቂት) እውነታን በመካድ እና "እስራኤል ከካርታ ላይ መጥፋት አለባት" በሚሉ ቀስቃሽ ንግግሮቹ የሚታወቀው እንዲሁም የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም በፅኑ ሲደግፍ የነበረው አህመዲነጃድ ለዚህ ቦታ መመረጡ፣ ለኢራን የፖለቲካ ተንታኞች እጅግ ያልተጠበቀ እና አስገራሚ ምርጫ ሆኖባቸዋል። ኒው ዮርክ ታይምስ እንደገለጸው፣ አህመዲነጃድ ከዚህ ቀደም ከኢራኑ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ጠንከር ያለ የፖለቲካ ቅራኔ ውስጥ ገብቶ በቁም እስረኝነት ላይ ይገኝ የነበረ ቢሆንም፣ እስራኤል ግን እሱን እንደ አማራጭ መሪ ለመጠቀም ሚስጥራዊ ምክክር አድርጋበት ነበር።
ነገር ግን ዕቅዱ ሳይሳካ የቀረው አህመዲነጃድ ከቁም እስራት ለማምለጥ ሲሞክር በእስራኤል የአየር ድብደባ ሳቢያ ቴህራን ውስጥ በመቁሰሉ እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በአደባባይ ባለመታየቱ እንደሆነ ተገልጿል። እስራኤል ካዘጋጀቻቸው ዘርፈ ብዙ የጦርነት ምዕራፎች መካከል የመጀመሪያው በአሜሪካ እና በእስራኤል የአየር ጥቃት የኢራን መሪዎችን መምታት እና የኩርድ ታጣቂዎችን በኢራን ላይ ማሰለፍ የነበረ ቢሆንም፣ የኩርዶች ወረራ ግን ሳይሳካ ቀርቷል። ሆኖም እስራኤል በደረሰው የፖለቲካ ጫና እና በዋና ዋና መሰረተ ልማቶች ላይ በደረሰው ውድመት ሳቢያ የኢራን ገዥ መደብ ሙሉ በሙሉ ይፈራርሳል፤ ከዚያም ያዘጋጀነው "አማራጭ መንግስት" ስልጣኑን ይረከባል የሚል እምነት ነበራት።
1 month ago
ኢራን በጦርነቱ ለደረሰባት ውድመት ካሳ እንዲሁም የአሜሪካ ወታደሮች እንዲወጡ የሚጠይቅ ሃሳብ አቀረበች
ኢራን በሁሉም ግንባሮች የተከፈቱ ጦርነቶች እንዲቆሙ እና ለደረሰባት ጉዳት ካሳ እንዲከፈላት የሚጠይቅ የስምምነት ሃሳብ አቀረበች።
አዲሱ የሰላም ዕቅድ በሊባኖስ ውስጥ የሚካሄደውን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች የሚደረጉ ጦርነቶች እንዲቆሙ፣ በኢራን አቅራቢያ የሰፈሩ የአሜሪካ ወታደሮች እንዲወጡ እና በጦርነቱ ለደረሰባት ውድመት ካሳን እንዲከፈላት የሚጠይቅ መሆኑን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ቴህራን የሰላም ዕቅዱን በሚመለከት በሰጠችው የመጀመሪያ አስተያየት ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ካዘም ጋሪባባዲ ማዕቀቦች እንዲነሱ፣ እንዳይንቀሳቀሱ የታገዱ ንብረቶቿ እንዲለቀቁ አንዲሁም የአሜሪካ ባሕር ኃይል የጣለውን እገዳ እንዲያነሳ መጠየቃቸውን ኢርና የዜና ወኪል ዘግቧል።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ የቴህራን አዲሱ ዕቅድ ከዚህ በፊት ካቀረበችው እና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ቆሻሻ” ሲሉ ውደቅ ካደረጉት ብዙም የተለየ አይደለም።
ትራምፕ ሰኞ ዕለት አቅደውት የነበረውን ጥቃት ያቆሙት ቴህራን ለዋሺንግተን አዲስ ሰላም ዕቅድ መላኳን ተከትሎ መሆኑን ተናግረው፤ የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም ለመገደብ እና ከስምምነት ላይ ለመድረስ “በጣም ጥሩ ዕድል አለ” ብለዋል።
ትራምፕ በማኅበራዊ ሚዲያ ልጥፋቸው ላይ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ “አሜሪካ እንዲሁም የመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ሊቀበሉት የሚችሉት ስምምነት ላይ ሊደረስ ይችላል” በማለት ጥቃቱ እንዲዘገይ መጠየቃቸውን ተናግረዋል።
ዶናልድ ትራምፕ ሰኞ ዕለት ቴህራን የኒውክሌር የጦር መሣሪያ እንዳታገኝ የሚያደርግ ስምምነት ላይ መድረስ ከተቻለ ደስተኛ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
BBC
ኢራን በሁሉም ግንባሮች የተከፈቱ ጦርነቶች እንዲቆሙ እና ለደረሰባት ጉዳት ካሳ እንዲከፈላት የሚጠይቅ የስምምነት ሃሳብ አቀረበች።
አዲሱ የሰላም ዕቅድ በሊባኖስ ውስጥ የሚካሄደውን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች የሚደረጉ ጦርነቶች እንዲቆሙ፣ በኢራን አቅራቢያ የሰፈሩ የአሜሪካ ወታደሮች እንዲወጡ እና በጦርነቱ ለደረሰባት ውድመት ካሳን እንዲከፈላት የሚጠይቅ መሆኑን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ቴህራን የሰላም ዕቅዱን በሚመለከት በሰጠችው የመጀመሪያ አስተያየት ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ካዘም ጋሪባባዲ ማዕቀቦች እንዲነሱ፣ እንዳይንቀሳቀሱ የታገዱ ንብረቶቿ እንዲለቀቁ አንዲሁም የአሜሪካ ባሕር ኃይል የጣለውን እገዳ እንዲያነሳ መጠየቃቸውን ኢርና የዜና ወኪል ዘግቧል።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ የቴህራን አዲሱ ዕቅድ ከዚህ በፊት ካቀረበችው እና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ቆሻሻ” ሲሉ ውደቅ ካደረጉት ብዙም የተለየ አይደለም።
ትራምፕ ሰኞ ዕለት አቅደውት የነበረውን ጥቃት ያቆሙት ቴህራን ለዋሺንግተን አዲስ ሰላም ዕቅድ መላኳን ተከትሎ መሆኑን ተናግረው፤ የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም ለመገደብ እና ከስምምነት ላይ ለመድረስ “በጣም ጥሩ ዕድል አለ” ብለዋል።
ትራምፕ በማኅበራዊ ሚዲያ ልጥፋቸው ላይ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ “አሜሪካ እንዲሁም የመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ሊቀበሉት የሚችሉት ስምምነት ላይ ሊደረስ ይችላል” በማለት ጥቃቱ እንዲዘገይ መጠየቃቸውን ተናግረዋል።
ዶናልድ ትራምፕ ሰኞ ዕለት ቴህራን የኒውክሌር የጦር መሣሪያ እንዳታገኝ የሚያደርግ ስምምነት ላይ መድረስ ከተቻለ ደስተኛ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
BBC
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማቆም የሚደረገው የሰላም ድርድር መጓተቱን ተከትሎ ለቴህራን "ጊዜ እያለቀባችሁ ነው" የሚል ከባድ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ 'ትሩዝ ሶሻል' በተሰኘው የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ፣ "በፍጥነት ቢንቀሳቀሱ ይሻላቸዋል፤ አለበለዚያ ከነሱ የሚተርፍ ምንም ነገር አይኖርም። አሁን ወሳኙ ነገር ጊዜ ነው!" ሲሉ ጽፈዋል። ይህ የትራምፕ ማስጠንቀቂያ የተሰማው፣ እሁድ ዕለት ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጋር በስልክ ሊነጋገሩ በተቀጠሩበት ወቅት ነው።
በሌላ በኩል የኢራን ሚዲያዎች፣ አሜሪካ ጦርነቱን ለማቆም ቴህራን ላቀረበችው የቅርብ ጊዜ የድርድር ሀሳብ ምንም ዓይነት ተጨባጭ ማግባቢያ አላቀረበችም ሲሉ ዘግበዋል። ከፊል-መንግስታዊ የሆነው 'ሜህር' የዜና ወኪል፣ ከዋሽንግተን በኩል የማግባባት ፍላጎት አለመታየቱ የሰላም ድርድሩን ወደ ማይወጣበት "እንቅፋት" እንደሚመራው ማስታወቁን ቀደም ሲል በዘ-ሐበሻ ዜና ማስነበባችን አይዘነጋም። ከዚህ ቀደም ትራምፕ የኢራንን የድርድር ሀሳብ "ቆሻሻ" እና "ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው" ሲሉ ያጣጣሉት ሲሆን፣ በሚያዝያ ወር መጀመሪያ ላይ የተኩስ አቁሙ ከመታወጁ ጥቂት ቀደም ብሎም ኢራን ጦርነቱን ለማቆም ካልተስማማች "አንድ ሙሉ ስልጣኔ" ሊጠፋ እንደሚችል ዝተው ነበር። ይሁን እንጂ የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋኢ፣ የሀገራቸው የድርድር ጥያቄዎች "ኃላፊነት የተሞላባቸው" እና "ለጋስ" መሆናቸውን አስረድተዋል።
'ታስኒም' የተሰኘው የኢራን የዜና ወኪል እንዳስነበበው፣ የቴህራን ጥያቄዎች በሁሉም ግንባሮች (በሊባኖስ የሂዝቦላህ ይዞታዎች ላይ እስራኤል የምታደርገውን ጥቃት ጨምሮ) ጦርነቱ በአፋጣኝ እንዲቆም፣ አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችው የባህር ላይ እገዳ እንዲነሳ እና በቀጣይ በኢራን ላይ ጥቃት ላለመፈጸሙ ዋስትና እንዲሰጥ የሚሉትን ያካትታል። በተጨማሪም የጦርነት ካሳ ክፍያ እንዲፈጸም እና የሆርሙዝ ስትሬት ሉዓላዊነት በኢራን ስር መሆኑ ላይ አጽንኦት ተሰጥቶበታል። በአንጻሩ አሜሪካ ለኢራን ጥያቄዎች ምላሽ አምስት ቅድመ-ሁኔታዎችን ማስቀመጧን 'ፋርስ' የዜና ወኪል ዘግቧል። ከእነዚህም መካከል ኢራን አንድ የኒውክሌር ጣቢያ ብቻ እንዲኖራት እና የበለጸገ የዩራኒየም ክምችቷን ወደ አሜሪካ እንድታስተላልፍ የሚሉት ይገኙበታል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ አርብ ዕለት በሰጡት አስተያየት፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ትልቅ የልዩነት ነጥብ የሆነውን የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ እንድታጠፋ ከማስገደድ ይልቅ፣ ለ20 ዓመታት እንድታግደው የሚለውን ሀሳብ ሊቀበሉት እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
አሜሪካ እና እስራኤል የካቲት 21 በኢራን ላይ ግዙፍ የአየር ጥቃት መክፈታቸው ይታወሳል። የሰላም ድርድሩን ለማመቻቸት የታሰበው የተኩስ አቁም አልፎ አልፎ ከሚደረጉ የተኩስ ልውውጦች በስተቀር በአብዛኛው እየተከበረ ይገኛል። ይሁን እንጂ ኢራን 20 በመቶ የሚሆነው የዓለም የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ምርት የሚያልፍበትን ወሳኙን የሆርሙዝ ስትሬት መቆጣጠሯን ቀጥላለች። ኢራን ለአሜሪካ እና እስራኤል ጥቃቶች አጸፋ ነው ያለችው ይህ የስትሬት መዘጋት፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ ንረትን አስከትሏል። በበኩሏ አሜሪካ ቴህራን በድርድሩ ቅድመ-ሁኔታዎች እንድትስማማ ጫና ለመፍጠር በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ አጠናክራ ቀጥላለች። በአሁኑ ሰዓት ፓኪስታን በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የአስታራቂነት ሚና እየተጫወተች ቢሆንም፣ የሁለቱ ወገኖች የድርድር አቋም ግን አሁንም እጅግ የተራራቀ መሆኑ እየታየ ነው።
በሌላ በኩል የኢራን ሚዲያዎች፣ አሜሪካ ጦርነቱን ለማቆም ቴህራን ላቀረበችው የቅርብ ጊዜ የድርድር ሀሳብ ምንም ዓይነት ተጨባጭ ማግባቢያ አላቀረበችም ሲሉ ዘግበዋል። ከፊል-መንግስታዊ የሆነው 'ሜህር' የዜና ወኪል፣ ከዋሽንግተን በኩል የማግባባት ፍላጎት አለመታየቱ የሰላም ድርድሩን ወደ ማይወጣበት "እንቅፋት" እንደሚመራው ማስታወቁን ቀደም ሲል በዘ-ሐበሻ ዜና ማስነበባችን አይዘነጋም። ከዚህ ቀደም ትራምፕ የኢራንን የድርድር ሀሳብ "ቆሻሻ" እና "ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው" ሲሉ ያጣጣሉት ሲሆን፣ በሚያዝያ ወር መጀመሪያ ላይ የተኩስ አቁሙ ከመታወጁ ጥቂት ቀደም ብሎም ኢራን ጦርነቱን ለማቆም ካልተስማማች "አንድ ሙሉ ስልጣኔ" ሊጠፋ እንደሚችል ዝተው ነበር። ይሁን እንጂ የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋኢ፣ የሀገራቸው የድርድር ጥያቄዎች "ኃላፊነት የተሞላባቸው" እና "ለጋስ" መሆናቸውን አስረድተዋል።
'ታስኒም' የተሰኘው የኢራን የዜና ወኪል እንዳስነበበው፣ የቴህራን ጥያቄዎች በሁሉም ግንባሮች (በሊባኖስ የሂዝቦላህ ይዞታዎች ላይ እስራኤል የምታደርገውን ጥቃት ጨምሮ) ጦርነቱ በአፋጣኝ እንዲቆም፣ አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችው የባህር ላይ እገዳ እንዲነሳ እና በቀጣይ በኢራን ላይ ጥቃት ላለመፈጸሙ ዋስትና እንዲሰጥ የሚሉትን ያካትታል። በተጨማሪም የጦርነት ካሳ ክፍያ እንዲፈጸም እና የሆርሙዝ ስትሬት ሉዓላዊነት በኢራን ስር መሆኑ ላይ አጽንኦት ተሰጥቶበታል። በአንጻሩ አሜሪካ ለኢራን ጥያቄዎች ምላሽ አምስት ቅድመ-ሁኔታዎችን ማስቀመጧን 'ፋርስ' የዜና ወኪል ዘግቧል። ከእነዚህም መካከል ኢራን አንድ የኒውክሌር ጣቢያ ብቻ እንዲኖራት እና የበለጸገ የዩራኒየም ክምችቷን ወደ አሜሪካ እንድታስተላልፍ የሚሉት ይገኙበታል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ አርብ ዕለት በሰጡት አስተያየት፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ትልቅ የልዩነት ነጥብ የሆነውን የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ እንድታጠፋ ከማስገደድ ይልቅ፣ ለ20 ዓመታት እንድታግደው የሚለውን ሀሳብ ሊቀበሉት እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
አሜሪካ እና እስራኤል የካቲት 21 በኢራን ላይ ግዙፍ የአየር ጥቃት መክፈታቸው ይታወሳል። የሰላም ድርድሩን ለማመቻቸት የታሰበው የተኩስ አቁም አልፎ አልፎ ከሚደረጉ የተኩስ ልውውጦች በስተቀር በአብዛኛው እየተከበረ ይገኛል። ይሁን እንጂ ኢራን 20 በመቶ የሚሆነው የዓለም የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ምርት የሚያልፍበትን ወሳኙን የሆርሙዝ ስትሬት መቆጣጠሯን ቀጥላለች። ኢራን ለአሜሪካ እና እስራኤል ጥቃቶች አጸፋ ነው ያለችው ይህ የስትሬት መዘጋት፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ ንረትን አስከትሏል። በበኩሏ አሜሪካ ቴህራን በድርድሩ ቅድመ-ሁኔታዎች እንድትስማማ ጫና ለመፍጠር በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ አጠናክራ ቀጥላለች። በአሁኑ ሰዓት ፓኪስታን በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የአስታራቂነት ሚና እየተጫወተች ቢሆንም፣ የሁለቱ ወገኖች የድርድር አቋም ግን አሁንም እጅግ የተራራቀ መሆኑ እየታየ ነው።
1 month ago
የኢራን እና አሜሪካ ድርድር እንዲቀጥል የቅድመ ሁኔታዎች ልውውጥ መደረጉ ተገለጸ
ኢራን ላቀረበችው የሰላም ዕቅድ አሜሪካ ባለ አምስት ነጥብ ምላሽ መስጠቷን የቴህራን መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
ለወታደራዊ እና ደኅንነት ተቋማት ቅርብ የሆነው ፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው፤ አሜሪካ ካስቀመጠችው ቅድመ ሁኔታ መካከል ቴህራን አንድ የኒውክሌር ተቋም ብቻ እንዲኖራት የሚጠይቀው ይገኝበታል።
የኢራን ጦርነት የሚቆመው ቅድመ ሁኔታዎች ተከብረው ድርድር ሲካሄድ መሆኑም ተመልክቷል።
ኢራን ለጦርነቱ ካሳ እንዲሰጣት ብትጠይቅም አሜሪካ ጥያቄውን አልተቀበለችም።
ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች ጦርነትን ማቆም የኢራን ቅድመ ሁኔታ ነው።
በተጨማሪም ማዕቀቦች እንዲነሱ ቴህራን ያቀረበችውን ጥያቄ ዋሽንግተን አልተቀበለችም።
ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ ሉዓላዊነቷ እንዲከበር መጠየቋም ተገልጿል።
የፓኪስታንየአገር ውስጥ ሚኒስትር ሞህሲን ናቂቭ በኢራን እና አሜሪካ መካከል የተቋረጠውን የሰላም ንግግር ለማስቀጠል ቴህራን ገብተዋል።
BBC
ኢራን ላቀረበችው የሰላም ዕቅድ አሜሪካ ባለ አምስት ነጥብ ምላሽ መስጠቷን የቴህራን መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
ለወታደራዊ እና ደኅንነት ተቋማት ቅርብ የሆነው ፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው፤ አሜሪካ ካስቀመጠችው ቅድመ ሁኔታ መካከል ቴህራን አንድ የኒውክሌር ተቋም ብቻ እንዲኖራት የሚጠይቀው ይገኝበታል።
የኢራን ጦርነት የሚቆመው ቅድመ ሁኔታዎች ተከብረው ድርድር ሲካሄድ መሆኑም ተመልክቷል።
ኢራን ለጦርነቱ ካሳ እንዲሰጣት ብትጠይቅም አሜሪካ ጥያቄውን አልተቀበለችም።
ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች ጦርነትን ማቆም የኢራን ቅድመ ሁኔታ ነው።
በተጨማሪም ማዕቀቦች እንዲነሱ ቴህራን ያቀረበችውን ጥያቄ ዋሽንግተን አልተቀበለችም።
ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ ሉዓላዊነቷ እንዲከበር መጠየቋም ተገልጿል።
የፓኪስታንየአገር ውስጥ ሚኒስትር ሞህሲን ናቂቭ በኢራን እና አሜሪካ መካከል የተቋረጠውን የሰላም ንግግር ለማስቀጠል ቴህራን ገብተዋል።
BBC
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ የሆኑት የባህር ኃይል አድሚራል ብራድ ኩፐር፣ አሜሪካ በየካቲት ወር መገባደጃ ላይ የጀመረችው "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊዩሪ" የተሰኘው ወታደራዊ ዘመቻ የኢራንን ወታደራዊ አቅም እና በቀጠናው ያላትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት ሙሉ በሙሉ ማዳከሙን አስታወቁ። አዛዡ ይህንን የተናገሩት በዋሽንግተን ዲሲ ለሴኔቱ የጦር ኃይሎች ኮሚቴ ስለ 2027 የበጀት ዓመት ጥያቄ እና በቀጠናው ስላለው ወታደራዊ አሰላለፍ ምስክርነት በሰጡበት ወቅት ነው።
አዛዡ በምስክርነታቸው እንዳብራሩት፣ የአሜሪካ ኃይሎች ከ40 ቀናት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወታደራዊ ግባቸውን በማሳካት የኢራንን የመከላከል አቅም ክፉኛ መትተዋል። በተለይም ባለፈው ዓመት ሚያዝያ እና ጥቅምት ወራት በእስራኤል ላይ ታይቶ የማያውቅ የጅምላ ሚሳኤል ጥቃት የፈጸመችው ኢራን፣ አሁን ላይ ይህን መሰል ጥቃት የመፈጸም አቅሟ በአሜሪካ ኃይሎች ተወግዷል። አድሚራል ኩፐር አክለውም፣ የኢራን የድሮን፣ የሚሳኤል እና የባህር ኃይል መከላከያ ኢንዱስትሪ በ90 በመቶ መውደሙን እና ቀሪ አቅሟ 10 በመቶ ብቻ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኢራን የባህር ኃይል ይህንን ከባድ ውድመት ተቋቁሞ አቅሙን መልሶ ለመገንባት ከ5 እስከ 10 ዓመታት ሊወስድበት እንደሚችልም ወታደራዊ ግምገማቸውን አቅርበዋል።
ይህ ወታደራዊ እርምጃ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን መቼም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዳይኖራት ያስቀመጡትን ብሔራዊ ግብ ለማሳካት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ከዚህም ባሻገር ኢራን በቀጠናው ለሚገኙ አሸባሪ ቡድኖች ስታደርግ የነበረው ቀጥተኛ ያልሆነ ድጋፍ ክፉኛ ተመቷል። ለዓመታት በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እና የጦር መሣሪያ ሲቀርብላቸው የነበሩት እንደ ሐማስ፣ ሕዝቦላህ እና ሁቲ ያሉ የተኪ ተዋጊ (Proxy) ቡድኖች፣ በዘመቻው ምክንያት ከኢራን የሚያገኙት ማንኛውም ዓይነት ትጥቅም ሆነ ሃብት መቋረጡን አዛዡ አብራርተዋል። ይህ ድል በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን፣ ለወራት የተደረገ ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ እና የዓመታት ልምድ ውጤት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
"ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊዩሪ" የአሜሪካን ወታደራዊ የበላይነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ ካሉ አጋር አገራት ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገሩ ተገልጿል። አድሚራል ኩፐር እንደገለጹት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ባህሬን፣ ኩዌት፣ ኳታር እና ሳዑዲ አረቢያ ከአሜሪካ ጋር ጎን ለጎን በመቆም ራሳቸውንም ሆነ አሜሪካውያንን በመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። በተጨማሪም ይህ ግዙፍ ወታደራዊ ስኬት ያለ ዮርዳኖስ እና እስራኤል የጠበቀ አጋርነት ሊሳካ እንደማይችል በመግለጽ፣ ዘመቻው በቀጠናው ያለውን የጸጥታ ትብብር ምን ያህል እንዳጠናከረው መስክረዋል።
አዛዡ በምስክርነታቸው እንዳብራሩት፣ የአሜሪካ ኃይሎች ከ40 ቀናት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወታደራዊ ግባቸውን በማሳካት የኢራንን የመከላከል አቅም ክፉኛ መትተዋል። በተለይም ባለፈው ዓመት ሚያዝያ እና ጥቅምት ወራት በእስራኤል ላይ ታይቶ የማያውቅ የጅምላ ሚሳኤል ጥቃት የፈጸመችው ኢራን፣ አሁን ላይ ይህን መሰል ጥቃት የመፈጸም አቅሟ በአሜሪካ ኃይሎች ተወግዷል። አድሚራል ኩፐር አክለውም፣ የኢራን የድሮን፣ የሚሳኤል እና የባህር ኃይል መከላከያ ኢንዱስትሪ በ90 በመቶ መውደሙን እና ቀሪ አቅሟ 10 በመቶ ብቻ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኢራን የባህር ኃይል ይህንን ከባድ ውድመት ተቋቁሞ አቅሙን መልሶ ለመገንባት ከ5 እስከ 10 ዓመታት ሊወስድበት እንደሚችልም ወታደራዊ ግምገማቸውን አቅርበዋል።
ይህ ወታደራዊ እርምጃ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን መቼም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዳይኖራት ያስቀመጡትን ብሔራዊ ግብ ለማሳካት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ከዚህም ባሻገር ኢራን በቀጠናው ለሚገኙ አሸባሪ ቡድኖች ስታደርግ የነበረው ቀጥተኛ ያልሆነ ድጋፍ ክፉኛ ተመቷል። ለዓመታት በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እና የጦር መሣሪያ ሲቀርብላቸው የነበሩት እንደ ሐማስ፣ ሕዝቦላህ እና ሁቲ ያሉ የተኪ ተዋጊ (Proxy) ቡድኖች፣ በዘመቻው ምክንያት ከኢራን የሚያገኙት ማንኛውም ዓይነት ትጥቅም ሆነ ሃብት መቋረጡን አዛዡ አብራርተዋል። ይህ ድል በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን፣ ለወራት የተደረገ ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ እና የዓመታት ልምድ ውጤት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
"ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊዩሪ" የአሜሪካን ወታደራዊ የበላይነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ ካሉ አጋር አገራት ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገሩ ተገልጿል። አድሚራል ኩፐር እንደገለጹት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ባህሬን፣ ኩዌት፣ ኳታር እና ሳዑዲ አረቢያ ከአሜሪካ ጋር ጎን ለጎን በመቆም ራሳቸውንም ሆነ አሜሪካውያንን በመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። በተጨማሪም ይህ ግዙፍ ወታደራዊ ስኬት ያለ ዮርዳኖስ እና እስራኤል የጠበቀ አጋርነት ሊሳካ እንደማይችል በመግለጽ፣ ዘመቻው በቀጠናው ያለውን የጸጥታ ትብብር ምን ያህል እንዳጠናከረው መስክረዋል።
1 month ago
ትራምፕ ከቻይናው መሪ ጋር ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዳይኖራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተናገሩ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ዢ ጂንፒንግ ጋር ቴህራን የኒውክሌር መሣሪያ ሊኖራት እንደማይገባ መስማማታቸውን ተናገሩ።
ፕሬዚዳንቱ የሁለት ቀናት ጎብኝታቸውን አጠናቅቀው ከመመለሳቸው በፊት በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ ከፕሬዚዳንት ዢ ጋር “ሌሎች ሊፈቱት የማይችሉትን በርካታ ችግሮችን ፈትተናል” ብለዋል።
ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው አቻቸው ጋር በኢራን ጦርነት፣ በታይዋን፣ በንግድ እና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
ዢ ከፕሬዚዳንት ትራምፕ ጋር ስላደረጓቸው ውይይቶች በዝርዝር የተናገሩት ነገር የለም።
ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን የዘጋችው የአሜሪካ እና እስራኤል በጥምረት በመሆን ጦርነት ከከፈቱባት በኋላ ነው።
የሆርሙዝ ወሽመጥ መዘጋት የዓለም የኢነርጂ አቅርቦት ላይ መስተጓጎልን በመፍጠር የዋጋ ንረት አስከትሏል።
የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር ለከዚህ ቀደም ባወጣው መግለጫ “ይህ መፈጠር ያልነበረበት ግጭት፣ የሚቀጥልበት ምክንያት የለም” ብሏል።
ትራምፕ በፎክስ ኒውስ “ሃኒቲ” ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ወቅት ቴህራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት መሟጠጡን ሲገልጹ “ከዚህ በላይ ትዕግሥት ሊኖረኝ አይችልም። ከስምምነት መድረስ አለባቸው” ብለዋል።
BBC
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ዢ ጂንፒንግ ጋር ቴህራን የኒውክሌር መሣሪያ ሊኖራት እንደማይገባ መስማማታቸውን ተናገሩ።
ፕሬዚዳንቱ የሁለት ቀናት ጎብኝታቸውን አጠናቅቀው ከመመለሳቸው በፊት በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ ከፕሬዚዳንት ዢ ጋር “ሌሎች ሊፈቱት የማይችሉትን በርካታ ችግሮችን ፈትተናል” ብለዋል።
ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው አቻቸው ጋር በኢራን ጦርነት፣ በታይዋን፣ በንግድ እና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
ዢ ከፕሬዚዳንት ትራምፕ ጋር ስላደረጓቸው ውይይቶች በዝርዝር የተናገሩት ነገር የለም።
ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን የዘጋችው የአሜሪካ እና እስራኤል በጥምረት በመሆን ጦርነት ከከፈቱባት በኋላ ነው።
የሆርሙዝ ወሽመጥ መዘጋት የዓለም የኢነርጂ አቅርቦት ላይ መስተጓጎልን በመፍጠር የዋጋ ንረት አስከትሏል።
የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር ለከዚህ ቀደም ባወጣው መግለጫ “ይህ መፈጠር ያልነበረበት ግጭት፣ የሚቀጥልበት ምክንያት የለም” ብሏል።
ትራምፕ በፎክስ ኒውስ “ሃኒቲ” ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ወቅት ቴህራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት መሟጠጡን ሲገልጹ “ከዚህ በላይ ትዕግሥት ሊኖረኝ አይችልም። ከስምምነት መድረስ አለባቸው” ብለዋል።
BBC
1 month ago
ሩሲያ በሩዋንዳ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ለመገንባት ስምምነት ላይ ደረሰች - ሮሳቶም
ኩባንያው በአሁኑ ወቅት 26 ግዙፍ እና 2 አነስተኛ የኃይል ማመንጫዎችን እየገነባ ሲሆን በሥራ ላይ ካሉት በተጨማሪ የተንሳፋፊ ኃይል ማመንጫ ትዕዛዞችን እየተቀበለ መሆኑን የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሌክሲ ሊካቼቭ ገልጸዋል።
ሮሳቶም ከካዛክስታን፣ ቬትናም እና ምያንማር ጋር የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ለመገንባት ስምምነት ላይ እንደደረሰ እና ከኢንዶኔዥያ ጋር የተደረገው ድርድር በቅርቡ መጠናቀቁንም ተናግረዋል።
seledadotio
seledadotio
ኩባንያው በአሁኑ ወቅት 26 ግዙፍ እና 2 አነስተኛ የኃይል ማመንጫዎችን እየገነባ ሲሆን በሥራ ላይ ካሉት በተጨማሪ የተንሳፋፊ ኃይል ማመንጫ ትዕዛዞችን እየተቀበለ መሆኑን የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሌክሲ ሊካቼቭ ገልጸዋል።
ሮሳቶም ከካዛክስታን፣ ቬትናም እና ምያንማር ጋር የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ለመገንባት ስምምነት ላይ እንደደረሰ እና ከኢንዶኔዥያ ጋር የተደረገው ድርድር በቅርቡ መጠናቀቁንም ተናግረዋል።
seledadotio
seledadotio
Comments