1 month ago
“የሕይወት መንገድ” ለንባብ በቃ
#ethiopia | የመጀመሪያው የጉራጊኛ ረጅም ልቦለድ ደራሲ 16ኛው መጽሐፋቸውን ለንባብ አብቅተዋል።
የመጀመሪያው የጉራጊኛ ረጅም ልቦለድ “የጫሙት ሽካ”ን በመጻፍ በኢትዮጵያ የሥነ-ጽሑፍ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት አንጋፋው ደራሲ አጋዝ ገብረኢየሱስ ኃይለማርያም “የሕይወት መንገድ” የተሰኘውን 16ኛው መጽሐፋቸው ዛሬ ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ አስመርቀዋል።
ደራሲው በጉራጊኛ፣ በአማርኛና በእንግሊዝኛ 16 መጽሐፍትን የጻፉ ሲሆን፣ ለጉራጌ ቋንቋና ባህል ጥበቃ፣ አንድነትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
ከዚህም ባሻገር የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅት (ጉህራልድ) መሥራች በመሆን “በማኅበረሰብ ልማት” ዘርፍ ጉልህ ይታወሳሉ።
አጋዝ ገብረየሱስ በድርሰት ሥራ ላበረከቱት ልዩ አስተዋፅኦ ዕውቅና ከኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ተበርክቶላቸዋል።
እርሳቸውም መጻሕፍታቸውን ሲያሳትሙ ለትልቅ ማህበረሰባዊ ዓላማ እንደነበር በማስታወስ በ97 አመታቸው እንዲህ አይነት እውቅናና ክብር በማግኘታቸው የተሰማቸውን ልዩ ደስታ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ፕሬዝዳንት ደራሲ አበረ አዳሙ አጋዝ ገብረየሱስ የፅናት ተምሳሌት መሆናቸውን ያስረዱ ሲሆን “የደራሲያን ማህበርም እውቅና በመስጠቱ ኩራት ይሰማዋል” ብለዋል።
የጉራጌ ዞን አስተዳደር ፅህፈት ቤት ሀላፊና በመድረኩ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ደሳለኝ ገብሬ በመርሀ ግብሩ ባደረጉት ንግግር አጋዝ ገብረየሱስ ለአዲሱ ትውልድ አርአያ የሚሆኑ በተለይም በድርሰቱ መስክ ትልቅ አሻራ ያኖሩ በመሆናቸው እናከብራቸዋለን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ደራሲ ገብረየሱስ በሁለቱ የጉራጌ ዞኖች ለሚገኙ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚውል 1000 መጽሃፍትን በልገሳ ያበረከቱ ሲሆን የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልዴ መጻህፍቱን ለማሰራጨት ሀላፊነት ወስደዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ካሚል ኑረዲን በመድረኩ የመጽሐፍ ዳሰሳ ያቀረቡ ሲሆን የደራሲው የበኩር ልጅ ኢትዮጵያ ገብረየሱስ የ“እንኳን ደስ አልዎ” መልዕክትና የቤተሰባዊ ምስክርነት ንግግር አድርገዋል።
መፅሐፉ በደራሲ ብርሀነ ዓለሙ የተሰናዳ ሲሆን የምረቃ ስነ-ስርዓቱን ተወዳጅ ሚድያና ኮሙኒኬሽን ከሶዶ ለማ ሚዲያ ጋር በመሆን አዘጋጅተውታል።
በሔኖክ ወ/ገብርኤል
#የሕይወትመንገድ #ደራሲአጋዝገብረየሱስሀይለማርያም #ጌጡተመስገን #ሚዲያናኮሚኒኬሽን #getutemsgen #mediacommunication
#ethiopia | የመጀመሪያው የጉራጊኛ ረጅም ልቦለድ ደራሲ 16ኛው መጽሐፋቸውን ለንባብ አብቅተዋል።
የመጀመሪያው የጉራጊኛ ረጅም ልቦለድ “የጫሙት ሽካ”ን በመጻፍ በኢትዮጵያ የሥነ-ጽሑፍ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት አንጋፋው ደራሲ አጋዝ ገብረኢየሱስ ኃይለማርያም “የሕይወት መንገድ” የተሰኘውን 16ኛው መጽሐፋቸው ዛሬ ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ አስመርቀዋል።
ደራሲው በጉራጊኛ፣ በአማርኛና በእንግሊዝኛ 16 መጽሐፍትን የጻፉ ሲሆን፣ ለጉራጌ ቋንቋና ባህል ጥበቃ፣ አንድነትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
ከዚህም ባሻገር የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅት (ጉህራልድ) መሥራች በመሆን “በማኅበረሰብ ልማት” ዘርፍ ጉልህ ይታወሳሉ።
አጋዝ ገብረየሱስ በድርሰት ሥራ ላበረከቱት ልዩ አስተዋፅኦ ዕውቅና ከኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ተበርክቶላቸዋል።
እርሳቸውም መጻሕፍታቸውን ሲያሳትሙ ለትልቅ ማህበረሰባዊ ዓላማ እንደነበር በማስታወስ በ97 አመታቸው እንዲህ አይነት እውቅናና ክብር በማግኘታቸው የተሰማቸውን ልዩ ደስታ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ፕሬዝዳንት ደራሲ አበረ አዳሙ አጋዝ ገብረየሱስ የፅናት ተምሳሌት መሆናቸውን ያስረዱ ሲሆን “የደራሲያን ማህበርም እውቅና በመስጠቱ ኩራት ይሰማዋል” ብለዋል።
የጉራጌ ዞን አስተዳደር ፅህፈት ቤት ሀላፊና በመድረኩ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ደሳለኝ ገብሬ በመርሀ ግብሩ ባደረጉት ንግግር አጋዝ ገብረየሱስ ለአዲሱ ትውልድ አርአያ የሚሆኑ በተለይም በድርሰቱ መስክ ትልቅ አሻራ ያኖሩ በመሆናቸው እናከብራቸዋለን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ደራሲ ገብረየሱስ በሁለቱ የጉራጌ ዞኖች ለሚገኙ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚውል 1000 መጽሃፍትን በልገሳ ያበረከቱ ሲሆን የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልዴ መጻህፍቱን ለማሰራጨት ሀላፊነት ወስደዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ካሚል ኑረዲን በመድረኩ የመጽሐፍ ዳሰሳ ያቀረቡ ሲሆን የደራሲው የበኩር ልጅ ኢትዮጵያ ገብረየሱስ የ“እንኳን ደስ አልዎ” መልዕክትና የቤተሰባዊ ምስክርነት ንግግር አድርገዋል።
መፅሐፉ በደራሲ ብርሀነ ዓለሙ የተሰናዳ ሲሆን የምረቃ ስነ-ስርዓቱን ተወዳጅ ሚድያና ኮሙኒኬሽን ከሶዶ ለማ ሚዲያ ጋር በመሆን አዘጋጅተውታል።
በሔኖክ ወ/ገብርኤል
#የሕይወትመንገድ #ደራሲአጋዝገብረየሱስሀይለማርያም #ጌጡተመስገን #ሚዲያናኮሚኒኬሽን #getutemsgen #mediacommunication
2 months ago
ከስምምነት የደረሱባቸው ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው?
#ethiopia | አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም ከስምምነት የደረሱባቸው የመግባቢያ ነጥቦች ይፋ ሆኑ።
አሜሪካ እና ኢራን ከሦስት ወራት በላይ የዘለቀውን ጦርነት ለማስቆም የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታወቁ።
በመካከለኛው ምሥራቅ ብሎም በመላው ዓለም ከባድ ቀውስን አስከትሎ የቆየውን ጦርነት ለማስቆም ለወራት ሲደረግ የነበረው ድርድረ አርብ ዕለት ስዊትዘርላንድ ውስጥ በሚካሄድ የፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ይቋጫል ተብሏል።
አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱ እንዲቆም በደረሱት የመግባቢያ ስምምነት ላይ ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች ጦርነቱ እንደሚቆም እና የሆርሙዝ ወሽመጥ እንደሚከፈት ተዘግቧል።
የኢራን ብሔራዊ መገናኛ ብዙኃን በቴህራን እና ዋሺንግተን መካከል ጦርነቱን ለማስቆም ስምምነት በተደረሰበት የመግባቢያ ሰነድ ውስጥ የተካተቱ ነጥቦችን ይፋ አድረገዋል።
የመገናኛ ብዙኃኑ ባቀረቧቸው ዝርዝሮች ውስጥ የተካተቱት ነጥቦች በሁለቱም ወገን ማረጋገጫ አልተሰጠባቸውም።
ሜህር የዜና ወኪል ከዘረዘራቸው ነጥቦች መካከል፦
* በሁሉም ግንባሮች ሊባኖስን ጨምሮ በቋሚነት ተኩስ ይቆማል
* አሜሪካ በኢራን ውስጣዊ ጉዳይ ጣልቃ አትገባም
* በ30 ቀናት ውስጥ የአሜሪካ የባሕር ዕገዳ ይነሳል
* የአሜሪካ ጦር ከኢራን ለቅቆ ይወጣል
* የሆርሙዝ ወሽመጥ “በኢራናውያን ቁጥጥር” በ30 ቀናት ውስጥ ዳግም ይከፈታል
* አሜሪካ እና አጋሮቿ 300 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የመልሶ ግንባታ ዕቅድ ያቀርባሉ
* በኢራን የነዳጅ ዘይት እና ኢነርጂ ምርቶች ላይ የተጣለውን ማዕቀብ ማንሳት
* ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ላለማምረት ዳግም ታረጋግጣለች
አሜሪካ በቀጣናው ያላትን ጦር አትጨምርም እና አዲስ ማዕቀብም አትጥልም።
* ሜህር አክሎም የስምምነቱ መጨረሻ የኢራን እንዳይንቀሳቀሱ የታገዱ ግማሽ ሃብቷ እስኪለቀቅ፣ የኢራን ነዳጅ ዘይት ላይ የተጣለው ማዕቀብ እና የባሕር ላይ ዕገዳው እስኪነሳ ድረስ የመጨረሻው ድርድር አይጀመርም ሲል ዘግቧል።
እንዲሁም የመጨረሻው ስምምነት በተባበሩት መንግሥታት በፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ እንደሚጸድቅ ዘግቧል።
#አሜሪካ #ኢራን #ጦርነት #ስምምነት #bbc #ጌጡተመስገን #ሚዲያኮሚኒኬሽን #getutemsgen #mediacommunication
#ethiopia | አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም ከስምምነት የደረሱባቸው የመግባቢያ ነጥቦች ይፋ ሆኑ።
አሜሪካ እና ኢራን ከሦስት ወራት በላይ የዘለቀውን ጦርነት ለማስቆም የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታወቁ።
በመካከለኛው ምሥራቅ ብሎም በመላው ዓለም ከባድ ቀውስን አስከትሎ የቆየውን ጦርነት ለማስቆም ለወራት ሲደረግ የነበረው ድርድረ አርብ ዕለት ስዊትዘርላንድ ውስጥ በሚካሄድ የፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ይቋጫል ተብሏል።
አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱ እንዲቆም በደረሱት የመግባቢያ ስምምነት ላይ ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች ጦርነቱ እንደሚቆም እና የሆርሙዝ ወሽመጥ እንደሚከፈት ተዘግቧል።
የኢራን ብሔራዊ መገናኛ ብዙኃን በቴህራን እና ዋሺንግተን መካከል ጦርነቱን ለማስቆም ስምምነት በተደረሰበት የመግባቢያ ሰነድ ውስጥ የተካተቱ ነጥቦችን ይፋ አድረገዋል።
የመገናኛ ብዙኃኑ ባቀረቧቸው ዝርዝሮች ውስጥ የተካተቱት ነጥቦች በሁለቱም ወገን ማረጋገጫ አልተሰጠባቸውም።
ሜህር የዜና ወኪል ከዘረዘራቸው ነጥቦች መካከል፦
* በሁሉም ግንባሮች ሊባኖስን ጨምሮ በቋሚነት ተኩስ ይቆማል
* አሜሪካ በኢራን ውስጣዊ ጉዳይ ጣልቃ አትገባም
* በ30 ቀናት ውስጥ የአሜሪካ የባሕር ዕገዳ ይነሳል
* የአሜሪካ ጦር ከኢራን ለቅቆ ይወጣል
* የሆርሙዝ ወሽመጥ “በኢራናውያን ቁጥጥር” በ30 ቀናት ውስጥ ዳግም ይከፈታል
* አሜሪካ እና አጋሮቿ 300 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የመልሶ ግንባታ ዕቅድ ያቀርባሉ
* በኢራን የነዳጅ ዘይት እና ኢነርጂ ምርቶች ላይ የተጣለውን ማዕቀብ ማንሳት
* ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ላለማምረት ዳግም ታረጋግጣለች
አሜሪካ በቀጣናው ያላትን ጦር አትጨምርም እና አዲስ ማዕቀብም አትጥልም።
* ሜህር አክሎም የስምምነቱ መጨረሻ የኢራን እንዳይንቀሳቀሱ የታገዱ ግማሽ ሃብቷ እስኪለቀቅ፣ የኢራን ነዳጅ ዘይት ላይ የተጣለው ማዕቀብ እና የባሕር ላይ ዕገዳው እስኪነሳ ድረስ የመጨረሻው ድርድር አይጀመርም ሲል ዘግቧል።
እንዲሁም የመጨረሻው ስምምነት በተባበሩት መንግሥታት በፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ እንደሚጸድቅ ዘግቧል።
#አሜሪካ #ኢራን #ጦርነት #ስምምነት #bbc #ጌጡተመስገን #ሚዲያኮሚኒኬሽን #getutemsgen #mediacommunication
Comments