3 days ago
እስካሁን ያላባራው የአሜሪካ እና የኢራን ውዝግብ
******************
በአሜሪካ፣ እስራኤል እና ኢራን መካከል ስላለው የተኩስ አቁም ድርድር እርስ በርሱ የሚጋጭ መረጃ እየወጣ ነው።
ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ቅርበት ያላቸው የኢራን የዜና ወኪሎች ፋርስ እና ተስኒም፣ ኢራን ከተኩስ አቁም አደራዳሪዎች ጋር የምታደርገውን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ ማቋረጧን ዘግበዋል።
ኢራን በሊባኖስ (በእስራኤል እና በሂዝቦላህ መካከል) ያለው ግጭት ካልቆመ በስተቀር ድርድሩ እንደማይቀጥል ገልጻለች።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን “ሀሰት” ሲሉ ይህን ዘገባ አስተባብለዋል። "ንግግሩ ትናንትም ዛሬም ያለማቋረጥ እንደቀጠለ ነው፤ ኢራን ስምምነት ላይ የምትደርስበት ጊዜው አሁን ነው" ብለዋል።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ስለ ግንኙነቱ መቋረጥ የተባለውን ባያረጋግጡም፣ ስለ ኑክሌር ድርድሩ ሂደት ግን ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
ኢራን በሆርሙዝ የንግድ መስመር ላይ ያላትን ስትራቴጂያዊ የበላይነት በመጠቀም፣ አሜሪካ እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እንድታስቆም እየጠየቀች ትገኛለች።
#middleeast #iran #usa #trump
******************
በአሜሪካ፣ እስራኤል እና ኢራን መካከል ስላለው የተኩስ አቁም ድርድር እርስ በርሱ የሚጋጭ መረጃ እየወጣ ነው።
ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ቅርበት ያላቸው የኢራን የዜና ወኪሎች ፋርስ እና ተስኒም፣ ኢራን ከተኩስ አቁም አደራዳሪዎች ጋር የምታደርገውን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ ማቋረጧን ዘግበዋል።
ኢራን በሊባኖስ (በእስራኤል እና በሂዝቦላህ መካከል) ያለው ግጭት ካልቆመ በስተቀር ድርድሩ እንደማይቀጥል ገልጻለች።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን “ሀሰት” ሲሉ ይህን ዘገባ አስተባብለዋል። "ንግግሩ ትናንትም ዛሬም ያለማቋረጥ እንደቀጠለ ነው፤ ኢራን ስምምነት ላይ የምትደርስበት ጊዜው አሁን ነው" ብለዋል።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ስለ ግንኙነቱ መቋረጥ የተባለውን ባያረጋግጡም፣ ስለ ኑክሌር ድርድሩ ሂደት ግን ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
ኢራን በሆርሙዝ የንግድ መስመር ላይ ያላትን ስትራቴጂያዊ የበላይነት በመጠቀም፣ አሜሪካ እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እንድታስቆም እየጠየቀች ትገኛለች።
#middleeast #iran #usa #trump
11 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ከኢራን ጋር እየተደረገ ያለውን የድርድር ሂደት ተከትሎ፣ የኢራን የበለጸገ የዩራኒየም ክምችት ለአሜሪካ ተላልፎ መሰጠት አሊያም በዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ቁጥጥር ስር በሌላ ቦታ መወገድ እንዳለበት አጥብቀው አሳሰቡ።
ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ "የበለጸገው ዩራኒየም ወዲያውኑ ወደ አሜሪካ ተልኮ እዚያው እንዲወገድ ይደረጋል፤ ወይም ደግሞ በተሻለ ሁኔታ ከእስላማዊቷ የኢራን ሪፐብሊክ ጋር በመቀናጀት ባለበት ቦታ አሊያም በሌላ ተቀባይነት ባለው ስፍራ የአቶሚክ ኢነርጂ ኮሚሽን ወይም ሌላ አቻ ተቋም በታዛቢነት በተገኘበት እንዲወገድ ይደረጋል" በማለት ጽፈዋል።
ትራምፕ መወገድ አለበት ያሉት በኢራን እጅ የሚገኘውን 440 ኪሎ ግራም በከፍተኛ ሁኔታ የበለጸገ ዩራኒየም ብቻ ይሁን ወይም አጠቃላይ የዩራኒየም ክምችቱን ስለመሆኑ በግልጽ ያብራሩት ነገር የለም። ሆኖም የአሜሪካ ባለስልጣናት አጠቃላይ የዩራኒየም ክምችቱ ሊወገድ እንደሚገባ ሲገልጹ መቆየታቸው ተዘግቧል።
በሌላ በኩል የኢራን ባለስልጣናት፣ አሁን በመካሄድ ላይ ባለው ድርድር መሰረት ሊደረስበት የታሰበው የ60 ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነት ተግባራዊ መሆን እስኪጀምር ድረስ፣ በኑክሌር ጉዳዩ ላይ ለመወያየት ፈቃደኛ አለመሆናቸውን አበክረው ገልጸዋል።
ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ "የበለጸገው ዩራኒየም ወዲያውኑ ወደ አሜሪካ ተልኮ እዚያው እንዲወገድ ይደረጋል፤ ወይም ደግሞ በተሻለ ሁኔታ ከእስላማዊቷ የኢራን ሪፐብሊክ ጋር በመቀናጀት ባለበት ቦታ አሊያም በሌላ ተቀባይነት ባለው ስፍራ የአቶሚክ ኢነርጂ ኮሚሽን ወይም ሌላ አቻ ተቋም በታዛቢነት በተገኘበት እንዲወገድ ይደረጋል" በማለት ጽፈዋል።
ትራምፕ መወገድ አለበት ያሉት በኢራን እጅ የሚገኘውን 440 ኪሎ ግራም በከፍተኛ ሁኔታ የበለጸገ ዩራኒየም ብቻ ይሁን ወይም አጠቃላይ የዩራኒየም ክምችቱን ስለመሆኑ በግልጽ ያብራሩት ነገር የለም። ሆኖም የአሜሪካ ባለስልጣናት አጠቃላይ የዩራኒየም ክምችቱ ሊወገድ እንደሚገባ ሲገልጹ መቆየታቸው ተዘግቧል።
በሌላ በኩል የኢራን ባለስልጣናት፣ አሁን በመካሄድ ላይ ባለው ድርድር መሰረት ሊደረስበት የታሰበው የ60 ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነት ተግባራዊ መሆን እስኪጀምር ድረስ፣ በኑክሌር ጉዳዩ ላይ ለመወያየት ፈቃደኛ አለመሆናቸውን አበክረው ገልጸዋል።
11 days ago
"ስራዎች አሁንም ቀጥለዋል፣ የሆርሙዝ ሰርጥን ለመክፈት ተጨባጭ ነገር አሳይተዋል፤ በኑክሌር ጉዳይም ጉልህ ድርድር ይደረጋል" - ማርክ ሩቢዮ
የአሜሪካ እና ኢራን ውይይት በቅርብ ቀን ውስጥ እንደሚጀመር ተጠቁሟል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ማርክ ሩቢዮ "ስምምነቱ በአንድም በሌላም መንገድ ይደረጋል" ብለዋል።
በህንድ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ሩቢዮ "ጦርነቱን የሚቋጨው ስምምነቱ ዛሬም ሊፈፀም ይችላል" ሲሉ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
"ስራዎች አሁንም ቀጥለዋል፣ የሆርሙዝ ሰርጥን ለመክፈት ተጨባጭ ነገር አሳይተዋል፤ በኑክሌር ጉዳይም ጉልህ ድርድር ይደረጋል" በማለት ተናግረዋል።
ሩቢዮ "ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አይቸኩሉም፣ መጥፎ ስምምነት አይፈርሙም" ባይ ናቸው።
ዩናይትድ ስቴትስ ለዲፕሎማሲ "ቅድሚያ እድል እንደምትሰጥ" አብራርተዋል። #trtworld
Seledadotio
Seledadotio
የአሜሪካ እና ኢራን ውይይት በቅርብ ቀን ውስጥ እንደሚጀመር ተጠቁሟል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ማርክ ሩቢዮ "ስምምነቱ በአንድም በሌላም መንገድ ይደረጋል" ብለዋል።
በህንድ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ሩቢዮ "ጦርነቱን የሚቋጨው ስምምነቱ ዛሬም ሊፈፀም ይችላል" ሲሉ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
"ስራዎች አሁንም ቀጥለዋል፣ የሆርሙዝ ሰርጥን ለመክፈት ተጨባጭ ነገር አሳይተዋል፤ በኑክሌር ጉዳይም ጉልህ ድርድር ይደረጋል" በማለት ተናግረዋል።
ሩቢዮ "ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አይቸኩሉም፣ መጥፎ ስምምነት አይፈርሙም" ባይ ናቸው።
ዩናይትድ ስቴትስ ለዲፕሎማሲ "ቅድሚያ እድል እንደምትሰጥ" አብራርተዋል። #trtworld
Seledadotio
Seledadotio
12 days ago
"ኢራን ለስምምነት በጣም ተቃርባለች" - ትራምፕ
"ስምምነቱ በአሜሪካ እንደሚነገረው የተቃረነ መግለጫ አይደለም" - እስማኤል ባቃይ
አሜሪካ እና ኢራን የሰላም ስምምነት ለማድረግ ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገለጸ።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ "ኢራን ለስምምነት በጣም ተቃርባለች" ብለዋል። "ስምምነቱ ኢራን የኑክሌር መሳሪያ በፍጹም እንዳትጠቀም ይከለክላል" ነው ያሉት።
ትራምፕ "የምንፈልገውን ካገኘን ብቻ የስምምነቱን ፊርማ አስቀምጣለሁ" ሲሉ ገልጸዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባቃይ በበኩላቸው "ስምምነቱ የተጠናቀቀው ባለፈው ሳምንት ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
ባቃይ "ስምምነቱ በአሜሪካ እንደሚነገረው የተቃረነ መግለጫ አይደለም" ብለዋል።
"እቅዳችን 14 ነጥቦችን ያካተተ ነው" ያሉት ባቃይ "የመጨረሻው ስምምነት ከ30-60 ባሉት ቀናት ውስጥ ይደረጋል" ብለዋል።
ቃል አቀባዩ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኑክሌር ጉዳይ አንዱ የስምምነት አካል መሆኑን በተመለከተ ስለሰጡት አስተያየት "ስለስምምነቱ ይዘት አላውቅም፤ ስለዚያ ምንም አልልም" ብለዋል።
ይሁን እንጂ የኑክሌር እና የሚሳዔል ምርት እንዲሁም የሆርሙዝ ሰርጥ የሁለቱ ሀገራት የስምምነት አካል መሆኑ ተገልጿል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት በኢራን ላይ ሊፈፅሙት የነበረውን ወረራ በሳውዲ አረቢያ፣ ኳታር እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ጥያቄ መሰረት መተዋቸውን ገልፀዋል። #bbc #aljazeera
Seledadotio
Seledadotio
"ስምምነቱ በአሜሪካ እንደሚነገረው የተቃረነ መግለጫ አይደለም" - እስማኤል ባቃይ
አሜሪካ እና ኢራን የሰላም ስምምነት ለማድረግ ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገለጸ።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ "ኢራን ለስምምነት በጣም ተቃርባለች" ብለዋል። "ስምምነቱ ኢራን የኑክሌር መሳሪያ በፍጹም እንዳትጠቀም ይከለክላል" ነው ያሉት።
ትራምፕ "የምንፈልገውን ካገኘን ብቻ የስምምነቱን ፊርማ አስቀምጣለሁ" ሲሉ ገልጸዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባቃይ በበኩላቸው "ስምምነቱ የተጠናቀቀው ባለፈው ሳምንት ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
ባቃይ "ስምምነቱ በአሜሪካ እንደሚነገረው የተቃረነ መግለጫ አይደለም" ብለዋል።
"እቅዳችን 14 ነጥቦችን ያካተተ ነው" ያሉት ባቃይ "የመጨረሻው ስምምነት ከ30-60 ባሉት ቀናት ውስጥ ይደረጋል" ብለዋል።
ቃል አቀባዩ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኑክሌር ጉዳይ አንዱ የስምምነት አካል መሆኑን በተመለከተ ስለሰጡት አስተያየት "ስለስምምነቱ ይዘት አላውቅም፤ ስለዚያ ምንም አልልም" ብለዋል።
ይሁን እንጂ የኑክሌር እና የሚሳዔል ምርት እንዲሁም የሆርሙዝ ሰርጥ የሁለቱ ሀገራት የስምምነት አካል መሆኑ ተገልጿል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት በኢራን ላይ ሊፈፅሙት የነበረውን ወረራ በሳውዲ አረቢያ፣ ኳታር እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ጥያቄ መሰረት መተዋቸውን ገልፀዋል። #bbc #aljazeera
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
17 days ago
“ጥቃቱን ለጊዜው ትቼዋለሁ”ትራምፕ
። ። ። ። ። : : : : : : : : : :
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ሊፈፅሙት የነበረውን ጥቃት ማራዘማቸውን አሳውቀዋል።
የባህረ ሰላጤው አገራት ሳውዲ አረቢያ፣ኳታርና አረብ ኤሚሬቶች እንዲሁም ሌሎች አገራት ኢራን ላይ ጥቃት እንዳይሰነዝር ጠይቀውኛል ብለዋል ትራምፕ።
ለማክሰኞ ቀን ተቆርጦለት የነበረው ጥቃት ለዲፕሎማሲ ጊዜ መግዣ በሚል ለአሁኑ ቆሟል።
በዕርግጥ ጥቃቱ ለሁለት እና ሶስት ቀናት ያህል እንደተራዘመ መነገሩ ያን ያህል ዘላቂ ሰላም ላያመጣ ይችላል።
ፔንታጎን ቢያንስ ለአሁኑ እርምጃ እንዳይወስድ በትራምፕ ታዟል።
ትራምፕ ኢራን ጋር ያለው ውይይት በጎ ባለመሆኑ ነገ ወደ ጥቃቱ እንመለሳለን በሚልም ዝተዋል።
የትኛውም ስምምነት ቴህራን ኑክሌር ቦምብ እንዳትታጠቅ ማድረግ አለበት የሪፐብሊካኑ ዕምነት ነው።
ፕሬዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ሚዲያቸው ላይ ተቀባይነት የሌለው ሀሳብ ኢራን የምተቀርብ ከሆነ የጦር ሚኒስቴሩ(ፔንታጎን) ወደ ጥቃት ለመመለስ በተጠንቀ ቅ ላይ እንዲቆይም አዘዋል።
ትራምፕ ማክሰኞ የያዙትን ጥቃት አራዘሙ እንጂ ኢራን ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ለማድረስ አሁንም ተዘጋጅተዋል ተብሏል።
ኢራን የመደራደሪያ ነጥቧን በፓኪስታን በኩል ለአሜሪካ መላኳም የሚዘነጋ አይደለም።
ዘገባው የአር ቲ ነው።
seledadotio
seledadotio
። ። ። ። ። : : : : : : : : : :
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ሊፈፅሙት የነበረውን ጥቃት ማራዘማቸውን አሳውቀዋል።
የባህረ ሰላጤው አገራት ሳውዲ አረቢያ፣ኳታርና አረብ ኤሚሬቶች እንዲሁም ሌሎች አገራት ኢራን ላይ ጥቃት እንዳይሰነዝር ጠይቀውኛል ብለዋል ትራምፕ።
ለማክሰኞ ቀን ተቆርጦለት የነበረው ጥቃት ለዲፕሎማሲ ጊዜ መግዣ በሚል ለአሁኑ ቆሟል።
በዕርግጥ ጥቃቱ ለሁለት እና ሶስት ቀናት ያህል እንደተራዘመ መነገሩ ያን ያህል ዘላቂ ሰላም ላያመጣ ይችላል።
ፔንታጎን ቢያንስ ለአሁኑ እርምጃ እንዳይወስድ በትራምፕ ታዟል።
ትራምፕ ኢራን ጋር ያለው ውይይት በጎ ባለመሆኑ ነገ ወደ ጥቃቱ እንመለሳለን በሚልም ዝተዋል።
የትኛውም ስምምነት ቴህራን ኑክሌር ቦምብ እንዳትታጠቅ ማድረግ አለበት የሪፐብሊካኑ ዕምነት ነው።
ፕሬዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ሚዲያቸው ላይ ተቀባይነት የሌለው ሀሳብ ኢራን የምተቀርብ ከሆነ የጦር ሚኒስቴሩ(ፔንታጎን) ወደ ጥቃት ለመመለስ በተጠንቀ ቅ ላይ እንዲቆይም አዘዋል።
ትራምፕ ማክሰኞ የያዙትን ጥቃት አራዘሙ እንጂ ኢራን ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ለማድረስ አሁንም ተዘጋጅተዋል ተብሏል።
ኢራን የመደራደሪያ ነጥቧን በፓኪስታን በኩል ለአሜሪካ መላኳም የሚዘነጋ አይደለም።
ዘገባው የአር ቲ ነው።
seledadotio
seledadotio
17 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው "የባህረ ሰላጤው ዓለም አቀፍ ፎረም" ዋና ዳይሬክተር ዳኒያ ታፌር ለአልጀዚራ በሰጡት ማብራሪያ፤ የባህረ ሰላጤው ሀገራት "በቀጠናው ውስጥ ውጥረቱ ይበልጥ እንዲባባስ ፍጹም እንደማይፈልጉ" አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ታፌር እንዳብራሩት "የእነዚህ ሀገራት ዋነኛ ፍላጎት በአሁኑ ወቅት የተደቀነባቸውን ቀውስ በዘላቂነት የሚፈታ መፍትሔ ማግኘት ነው" ያሉ ሲሆን፣ የቴህራን የኑክሌር መርሃ ግብር ለዋሽንግተን ዋነኛ ስጋት ቢሆንም ለባህረ ሰላጤው ሀገራት ግን "ቀዳሚ አጀንዳቸው እንዳልሆነ" ጠቁመዋል።
እነዚህ የባህረ ሰላጤው ሀገራት ከኑክሌሩ ጉዳይ ይልቅ አሁን ላይ እጅግ አሳሳቢ በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ በአስቸኳይ እንዲከፈት እና በኢራን መደበኛ ሚሳኤሎች የተደቀነባቸውን የደህንነት ስጋት ማስወገድ ላይ በእጅጉ እንደሚያተኩሩ ታፌር ገልጸዋል።
አክለውም "እኔ እንደማስበው ውጥረቱን ማርገብ እና የሁሉም ወገኖችን ቅሬታና ስጋት ሊፈታ የሚችል ስምምነት ላይ መድረስ ለባህረ ሰላጤው ሀገራት ሁሉንም ነገር የሚያሳካ እጅግ ተመራጭ መፍትሔ ነው" ብለዋል።
ታፌር እንዳብራሩት "የእነዚህ ሀገራት ዋነኛ ፍላጎት በአሁኑ ወቅት የተደቀነባቸውን ቀውስ በዘላቂነት የሚፈታ መፍትሔ ማግኘት ነው" ያሉ ሲሆን፣ የቴህራን የኑክሌር መርሃ ግብር ለዋሽንግተን ዋነኛ ስጋት ቢሆንም ለባህረ ሰላጤው ሀገራት ግን "ቀዳሚ አጀንዳቸው እንዳልሆነ" ጠቁመዋል።
እነዚህ የባህረ ሰላጤው ሀገራት ከኑክሌሩ ጉዳይ ይልቅ አሁን ላይ እጅግ አሳሳቢ በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ በአስቸኳይ እንዲከፈት እና በኢራን መደበኛ ሚሳኤሎች የተደቀነባቸውን የደህንነት ስጋት ማስወገድ ላይ በእጅጉ እንደሚያተኩሩ ታፌር ገልጸዋል።
አክለውም "እኔ እንደማስበው ውጥረቱን ማርገብ እና የሁሉም ወገኖችን ቅሬታና ስጋት ሊፈታ የሚችል ስምምነት ላይ መድረስ ለባህረ ሰላጤው ሀገራት ሁሉንም ነገር የሚያሳካ እጅግ ተመራጭ መፍትሔ ነው" ብለዋል።
18 days ago
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን "ጊዜው እያለቀ ነው" ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳየ
በመካከለኛው ምስራቅ ባለው የጂኦፖለቲካ ውጥረት ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ ለዋጋው መጨመር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም የሚደረገው ድርድር በመቀዝቀዙ ለኢራን "ጊዜው እያለቀ ነው" ሲሉ ማስጠንቀቃቸው በምክንያትነት ተጠቅሷል።
የዓለምን 20 በመቶ የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ትራንስፖርት የሚያስተናግደው የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት፣ በአቡ ዳቢ የሚገኘው የባራካ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ አቅራቢያ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃ እሳት መነሳ ምክንያት በነዳጅ አቅርቦት ላይ ስጋት መፍጠሩን ቢቢሲ ዘግቧል።
በዛሬው ዕለት ብሬንት የተሰኘው ድፍድፍ ነዳጅ በ1.7 በመቶ በመጨመር አንድ በርሜል በ111.13 ዶላር ደርሷል።
seledadotio
seledadotio
በመካከለኛው ምስራቅ ባለው የጂኦፖለቲካ ውጥረት ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ ለዋጋው መጨመር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም የሚደረገው ድርድር በመቀዝቀዙ ለኢራን "ጊዜው እያለቀ ነው" ሲሉ ማስጠንቀቃቸው በምክንያትነት ተጠቅሷል።
የዓለምን 20 በመቶ የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ትራንስፖርት የሚያስተናግደው የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት፣ በአቡ ዳቢ የሚገኘው የባራካ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ አቅራቢያ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃ እሳት መነሳ ምክንያት በነዳጅ አቅርቦት ላይ ስጋት መፍጠሩን ቢቢሲ ዘግቧል።
በዛሬው ዕለት ብሬንት የተሰኘው ድፍድፍ ነዳጅ በ1.7 በመቶ በመጨመር አንድ በርሜል በ111.13 ዶላር ደርሷል።
seledadotio
seledadotio
19 days ago
በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኑክሌር ማዕከል ላይ የተሰነዘረው የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት በአካባቢው ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቀነ
#ethiopia | የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የፕሬዝዳንት አማካሪ አንዋር ጋርጋሽ በባራካ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የተሰነዘረውን የሽብር ጥቃት አውግዘዋል።
ድርጊቱ ዓለም አቀፍ ህጎችን የጣሰና ቀጠናውን ለአደገኛ ውጥረት አጋላጭ መሆኑንም ገልጸዋል።
ጥቃቱ በቀጥታም ይሁን በሉካconfiguration በኩል የተፈጸመ ቢሆንም በኤምሬትስና በአካባቢው በሚኖሩ ንፁሃን ዜጎች ህይወት ላይ የተጋረጠ የንቀት ወንጀል መሆኑን አማካሪው አስታውቀዋል።
ጋርጋሽ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የሀገራቸውን ጽኑ አቋም ሲያብራሩ የኤምሬትስን እጅ ማንም ሊጠመዝዝ እንደማይችል አስገንዝበዋል።
በተያያዘ ዜና ኳታር በባራካ የኑክሌር ጣቢያ ላይ የተፈጸመውን የድሮን ጥቃት አጥብቃ የኮነነች ሲሆን ድርጊቱ ዓለም አቀፍ ህግን በግልጽ የጣሰና ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋት ከባድ ስጋት መሆኑን ገልጻለች።
የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ መሰረተ ልማቶችንና ቁልፍ የሲቪል ተቋማትን ኢላማ በማድረግ ሁሉንም ቀይ መስመሮች ያለፈ ነው ሲል ወቅሷል።
በተጨማሪም ኳታር ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ጎን በሙሉ ልብ እንደምትቆም የገለጸች ሲሆን ሀገሪቱ ሉዓላዊነቷን፣ ደህንነቷንና የተቋማቶቿን ሰላም ለመጠበቅ ለምትወስደው ማንኛውም እርምጃ ሙሉ ድጋፍ እንደምታደርግ ሚኒስቴሩ በይፋ አስታውቋል።
#uae #qatar #middleeast #securitynews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የፕሬዝዳንት አማካሪ አንዋር ጋርጋሽ በባራካ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የተሰነዘረውን የሽብር ጥቃት አውግዘዋል።
ድርጊቱ ዓለም አቀፍ ህጎችን የጣሰና ቀጠናውን ለአደገኛ ውጥረት አጋላጭ መሆኑንም ገልጸዋል።
ጥቃቱ በቀጥታም ይሁን በሉካconfiguration በኩል የተፈጸመ ቢሆንም በኤምሬትስና በአካባቢው በሚኖሩ ንፁሃን ዜጎች ህይወት ላይ የተጋረጠ የንቀት ወንጀል መሆኑን አማካሪው አስታውቀዋል።
ጋርጋሽ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የሀገራቸውን ጽኑ አቋም ሲያብራሩ የኤምሬትስን እጅ ማንም ሊጠመዝዝ እንደማይችል አስገንዝበዋል።
በተያያዘ ዜና ኳታር በባራካ የኑክሌር ጣቢያ ላይ የተፈጸመውን የድሮን ጥቃት አጥብቃ የኮነነች ሲሆን ድርጊቱ ዓለም አቀፍ ህግን በግልጽ የጣሰና ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋት ከባድ ስጋት መሆኑን ገልጻለች።
የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ መሰረተ ልማቶችንና ቁልፍ የሲቪል ተቋማትን ኢላማ በማድረግ ሁሉንም ቀይ መስመሮች ያለፈ ነው ሲል ወቅሷል።
በተጨማሪም ኳታር ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ጎን በሙሉ ልብ እንደምትቆም የገለጸች ሲሆን ሀገሪቱ ሉዓላዊነቷን፣ ደህንነቷንና የተቋማቶቿን ሰላም ለመጠበቅ ለምትወስደው ማንኛውም እርምጃ ሙሉ ድጋፍ እንደምታደርግ ሚኒስቴሩ በይፋ አስታውቋል።
#uae #qatar #middleeast #securitynews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
19 days ago
የሰላም ድርድር መቋረጥ፣ የሆርሙዝ ሰርጥ አዳዲስ ክልከላዎች እና የባራካህ የኑክሌር ጣቢያ ጥቃት
**************
በመካከለኛው ምሥራቅ የሰላም ድርድር ጥረቶች፣ በሆርሙዝ ሰርጥ የባሕር ላይ መተላለፊያ ቁጥጥር እና በተመዘገቡ የጸጥታ ስጋቶች ዙሪያ አዳዲስ ክስተቶች ተመዝግበዋል።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የነበረው ቀጥተኛ ድርድር መቋረጡን ተከትሎ ዲፕሎማሲያዊ ውጥረቱ ያሻቀበ ሲሆን፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴን ለመቆጣጠርም አዳዲስ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የፓኪስታን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሞህሲን ናቅቪ አስቀድሞ ያልተገለጸ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ቴህራን መግባታቸውን የፓኪስታኑ ‘ዶን’ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ይህ አስቸኳይ ጉብኝት የተደረገው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የቅርብ ጊዜ የሰላም አማራጭ ውድቅ ማድረጋቸውን ተከትሎ፣ የሰላም ድርድሩ ሙሉ በሙሉ እንዳይደናቀፍ ለማድረግ የተጀመረው የሽምግልና ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።
የኢራኑ ‘ተስኒም’ የዜና ወኪል በበኩሉ፣ ሚኒስትሩ ከኢራን አቻቸው ኤስካንዳር ሞሜኒ እና ከፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ ጋር ተገናኝተው በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል ያለውን የሰላም ድርድር ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ጠቁሟል።
ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ እንዳስነበበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራንን የሰላም ሃሳብ ውድቅ ቢያደርጉም፤ ኢራን የኑክሌር መርሐ ግብሯን ለ20 ዓመታት እንድታግድ የሚጠይቅ አማራጭ አቅርበዋል።
ይሁን እንጂ የኢራን ባለሥልጣናት በአሜሪካ ወገን ምንም ዓይነት ተጨባጭ የዲፕሎማሲ አካሄድ ለውጥ አልታየም ሲሉ መተቸታቸውን መህር የዜና ወኪል ዘግቧል።
የሆርሙዝ ሰርጥን በተመለከተ ኢራን የባሕር ላይ መተላለፊያውን ለመቆጣጠር አዲስ “ሙያዊ የአሠራር ሥርዓት” ያለችውን የቁጥጥር ሥርዓት ይፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደኅንነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዝን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ አዲሱ አሠራር ከኢራን ጋር ለሚተባበሩ የንግድ መርከቦች ብቻ ቅድሚያ የሚሰጥ ሲሆን፣ የአሜሪካ ደጋፊ ለሆኑ መርከቦች ግን ዝግ ይሆናል።
በተጨማሪም ኢራን በዲጂታል እና በቢትኮይን ክፍያ የሚሠራ “ሆርሙዝ ሴፍ” የተባለ አዲስ የባሕር ላይ መድን ይፋ ማድረጓን ፋርስ የዜና ወኪል አረጋግጧል።
በሆርሙዝ ሰርጥ ያለው የባሕር ላይ ትራፊክ አሁንም እንደቀዘቀዘ መሆኑን እና አንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት መርከቦቻቸው በሰላም እንዲያልፉ ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ድርድር መጀመራቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል።
በሌላ በኩል የቀጣናውን ሰላም ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርግ ክስተት ተመዝግቧል። በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በሚገኘው የባራካህ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የድሮን ጥቃት ደርሷል።
‘አሶሺዬትድ ፕሬስ' እንደዘገበው ጥቃቱ ከኃይል ማመንጫው የውስጠኛው አጥር ውጭ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ጄነሬተር ላይ እሳት ቢያስነሳም፣ የኢምሬቶች ባለሥልጣናት እሳቱን በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን እና ምንም ዓይነት የጨረር ስጋትም ሆነ የሰው ጉዳት አለመድረሱን አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ (IAEA) ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ ጥቃቱን “ተቀባይነት የሌለው” ሲሉ አውግዘውታል።
በመካከለኛው ምሥራቅ በአንድ በኩል ዲፕሎማሲያዊ የሰላም ጥረቶች ቢቀጥሉም፣ በሌላ በኩል እየተከሰቱ ያሉ የጸጥታ ስጋቶች ቀውሱ ወደ ከፋ ጦርነት እንዳያመራ ከፍተኛ ስጋት መፍጠራቸውን ዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ ተንታኞች በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።
በለሚ ታደሰ
#middleeastcrisis #peacetalks #straitofhormuz #diplomacy #globalenergy
**************
በመካከለኛው ምሥራቅ የሰላም ድርድር ጥረቶች፣ በሆርሙዝ ሰርጥ የባሕር ላይ መተላለፊያ ቁጥጥር እና በተመዘገቡ የጸጥታ ስጋቶች ዙሪያ አዳዲስ ክስተቶች ተመዝግበዋል።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የነበረው ቀጥተኛ ድርድር መቋረጡን ተከትሎ ዲፕሎማሲያዊ ውጥረቱ ያሻቀበ ሲሆን፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴን ለመቆጣጠርም አዳዲስ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የፓኪስታን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሞህሲን ናቅቪ አስቀድሞ ያልተገለጸ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ቴህራን መግባታቸውን የፓኪስታኑ ‘ዶን’ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ይህ አስቸኳይ ጉብኝት የተደረገው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የቅርብ ጊዜ የሰላም አማራጭ ውድቅ ማድረጋቸውን ተከትሎ፣ የሰላም ድርድሩ ሙሉ በሙሉ እንዳይደናቀፍ ለማድረግ የተጀመረው የሽምግልና ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።
የኢራኑ ‘ተስኒም’ የዜና ወኪል በበኩሉ፣ ሚኒስትሩ ከኢራን አቻቸው ኤስካንዳር ሞሜኒ እና ከፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ ጋር ተገናኝተው በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል ያለውን የሰላም ድርድር ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ጠቁሟል።
ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ እንዳስነበበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራንን የሰላም ሃሳብ ውድቅ ቢያደርጉም፤ ኢራን የኑክሌር መርሐ ግብሯን ለ20 ዓመታት እንድታግድ የሚጠይቅ አማራጭ አቅርበዋል።
ይሁን እንጂ የኢራን ባለሥልጣናት በአሜሪካ ወገን ምንም ዓይነት ተጨባጭ የዲፕሎማሲ አካሄድ ለውጥ አልታየም ሲሉ መተቸታቸውን መህር የዜና ወኪል ዘግቧል።
የሆርሙዝ ሰርጥን በተመለከተ ኢራን የባሕር ላይ መተላለፊያውን ለመቆጣጠር አዲስ “ሙያዊ የአሠራር ሥርዓት” ያለችውን የቁጥጥር ሥርዓት ይፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደኅንነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዝን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ አዲሱ አሠራር ከኢራን ጋር ለሚተባበሩ የንግድ መርከቦች ብቻ ቅድሚያ የሚሰጥ ሲሆን፣ የአሜሪካ ደጋፊ ለሆኑ መርከቦች ግን ዝግ ይሆናል።
በተጨማሪም ኢራን በዲጂታል እና በቢትኮይን ክፍያ የሚሠራ “ሆርሙዝ ሴፍ” የተባለ አዲስ የባሕር ላይ መድን ይፋ ማድረጓን ፋርስ የዜና ወኪል አረጋግጧል።
በሆርሙዝ ሰርጥ ያለው የባሕር ላይ ትራፊክ አሁንም እንደቀዘቀዘ መሆኑን እና አንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት መርከቦቻቸው በሰላም እንዲያልፉ ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ድርድር መጀመራቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል።
በሌላ በኩል የቀጣናውን ሰላም ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርግ ክስተት ተመዝግቧል። በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በሚገኘው የባራካህ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የድሮን ጥቃት ደርሷል።
‘አሶሺዬትድ ፕሬስ' እንደዘገበው ጥቃቱ ከኃይል ማመንጫው የውስጠኛው አጥር ውጭ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ጄነሬተር ላይ እሳት ቢያስነሳም፣ የኢምሬቶች ባለሥልጣናት እሳቱን በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን እና ምንም ዓይነት የጨረር ስጋትም ሆነ የሰው ጉዳት አለመድረሱን አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ (IAEA) ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ ጥቃቱን “ተቀባይነት የሌለው” ሲሉ አውግዘውታል።
በመካከለኛው ምሥራቅ በአንድ በኩል ዲፕሎማሲያዊ የሰላም ጥረቶች ቢቀጥሉም፣ በሌላ በኩል እየተከሰቱ ያሉ የጸጥታ ስጋቶች ቀውሱ ወደ ከፋ ጦርነት እንዳያመራ ከፍተኛ ስጋት መፍጠራቸውን ዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ ተንታኞች በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።
በለሚ ታደሰ
#middleeastcrisis #peacetalks #straitofhormuz #diplomacy #globalenergy
22 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በመካከለኛው ምስራቅ ካለው ጦርነት ጥላ ስር በዴልሂ በተካሄደው የብሪክስ ታዳጊ ኢኮኖሚ ሀገራት ስብሰባ ላይ፣ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሜሪካ እና እስራኤል እየፈጸሙት ያለውን "የዓለም አቀፍ ህግ ጥሰት" አባል ሀገራቱ እንዲያወግዙ ሐሙስ ዕለት ጥሪ አቀረቡ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አባስ አራግቺ፣ የአሜሪካ አጋር የሆነችውን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን (ዩኤኢ) በኢራን ላይ በሚካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ "ቀጥተኛ ተሳትፎ አላት" ሲሉ በግልፅ ከሰዋል። የካቲት 28 ከተጀመረው የአሜሪካ እና እስራኤል ጦርነት ወዲህ፣ የኢራን እና የዩኤኢ ባለስልጣናት በአንድ ስብሰባ ላይ ተገናኝተው ይህ አይነት ክስ ሲሰነዘር የመጀመሪያው ነው። ዩኤኢን ወክለው በስብሰባው ላይ የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ካሊፋ ሻሂን አል ማራር ናቸው።
አራግቺ ኢራን "የህገ-ወጥ መስፋፋት እና የጦርነት ቀስቃሾች ሰለባ" መሆኗን ገልጸው፤ የብሪክስ ፕላስ ስብስብ (ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ግብጽ፣ ኢትዮጵያ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ኢራን እና ዩኤኢ) "የምዕራባውያንን የበላይነት እና አሜሪካ ያለአንዳች ተጠያቂነት የምታደርገውን የዘፈቀደ ድርጊት" እንዲቋቋሙ ጠይቀዋል። በመሆኑም አባል ሀገራቱ እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሜሪካ እና እስራኤልን እንዲያወግዙ አሳስበዋል።
አሜሪካ እና እስራኤል ላደረሱባት ጥቃት አጸፋውን ለመመለስ ኢራን ዩኤኢን ጨምሮ በባህረ ሰላጤው ሀገራት ላይ ጥቃት መሰንዘሯ ይታወሳል። ይህ በመካከላቸው ያለው ልዩነት፣ ውሳኔዎችን በጋራ ስምምነት በሚያሳልፈው የብሪክስ ስብስብ ውስጥ የጋራ መግለጫ ለማውጣት አስቸጋሪ ሊያደርገው እንደሚችል ተገምቷል። ዩኤኢ እና ሌሎች የብሪክስ ሀገራት ለአራግቺ ንግግር የሰጡት ምላሽ ወዲያውኑ አልታወቀም።
የ2026ቱ የብሪክስ ሊቀመንበር የሆነችው እና ከዩኤኢ ጋር ያላት አጋርነት እያደገ የመጣው ህንድ፣ ጦርነቱን ተከትሎ ኢራን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን መዝጋቷ ከፍተኛ ተጽዕኖ ካሳደረባቸው ሀገራት ዋነኛዋ ናት።
ይህ የውሃ መስመር ከዓለም የነዳጅ ማጓጓዣ ውስጥ ወደ አንድ አምስተኛውን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ መዘጋቱ በቅርብ ታሪክ ውስጥ ከታዩት ትላልቅ የአቅርቦት መስተጓጎሎች አንዱን አስከትሏል። የዓለማችን ሶስተኛዋ ትልቋ የነዳጅ አስመጪ የሆነችው ህንድ በባህረ ሰላጤው መዘጋት የተነሳ ከፍተኛ የአቅርቦት እጥረት ያጋጠማት ሲሆን፣ በመርከቦች ላይ በሚደርሰው ጥቃት የባህር ላይ ሰራተኞቿን አጥታለች።
ምንም እንኳን የተኩስ አቁም ስምምነት ቢኖርም፣ አልፎ አልፎ የሚታዩ ጥቃቶች አሁንም እንደቀጠሉ ናቸው። እሮብ እለት የቁም እንስሳትን ጭና ከሶማሊያ ወደ ዩኤኢ ስትጓዝ የነበረች በህንድ የተመዘገበች መርከብ በኦማን ባህር ውስጥ በእሳት አደጋ መስጠሟ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁሉም 14 የቡድን አባላት በኦማን የባህር ዳርቻ ጠባቂዎች ተረፈዋል። ህንድ የጥቃቱን ምንነት ባትገልጽም፣ የብሪታንያ የባህር ላይ አደጋ አስተዳደር ቡድን 'ቫንጋርድ' ግን አደጋው በድሮን ወይም በሚሳኤል ጥቃት ምክንያት የተፈጠረ ፍንዳታ ሊሆን እንደሚችል ገልጿል።
የህንዱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሱብራህማንያም ጃይሻንካር፣ "እየቀጠለ ያለው ውጥረት፣ በባህር ላይ ትራፊክ ላይ የተጋረጠው አደጋ እና የኃይል አቅርቦት መሰረተ ልማቶች መስተጓጎል የሁኔታውን አሳሳቢነት (ተሰባሪነት) ያሳያል" ብለዋል። አክለውም የሆርሙዝ እና የቀይ ባህርን ጨምሮ በዓለም አቀፍ የውሃ መስመሮች ላይ ደህንነቱ የተጠበቀ የባህር ላይ ጉዞ ለዓለም ኢኮኖሚ ደህንነት ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል።
ጃይሻንካር ማንኛውንም ወገን በስም ባይጠቅሱም፣ "ከዓለም አቀፍ ህግ እና ከተባበሩት መንግስታት ቻርተር ጋር የማይጣጣሙ የአንድዮሽ የማስገደድ (የጫና) እርምጃዎች እና ማዕቀቦች መጨመራቸውን" ተችተዋል። እነዚህ እርምጃዎች በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን አብዝተው እንደሚጎዱ በማንሳት፣ "እነዚህ ተገቢ ያልሆኑ እርምጃዎች ውይይትን እና ዲፕሎማሲን ሊተኩ አይችሉም" ብለዋል።
በሌላ ዜና ከብሪክስ ስብሰባ ጋር በተገጣጠመው የቤጂንግ ጉብኝታቸው፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በኢራን ጦርነት ዙሪያ መወያየታቸው ተገልጿል። የዋይት ሃውስ ባለስልጣን እንዳረጋገጡት፣ ሁለቱ መሪዎች የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ክፍት መሆን እንዳለበት እና ቴህራን መቼም ቢሆን የኑክሌር የጦር መሳሪያ ሊኖራት እንደማይገባ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አባስ አራግቺ፣ የአሜሪካ አጋር የሆነችውን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን (ዩኤኢ) በኢራን ላይ በሚካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ "ቀጥተኛ ተሳትፎ አላት" ሲሉ በግልፅ ከሰዋል። የካቲት 28 ከተጀመረው የአሜሪካ እና እስራኤል ጦርነት ወዲህ፣ የኢራን እና የዩኤኢ ባለስልጣናት በአንድ ስብሰባ ላይ ተገናኝተው ይህ አይነት ክስ ሲሰነዘር የመጀመሪያው ነው። ዩኤኢን ወክለው በስብሰባው ላይ የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ካሊፋ ሻሂን አል ማራር ናቸው።
አራግቺ ኢራን "የህገ-ወጥ መስፋፋት እና የጦርነት ቀስቃሾች ሰለባ" መሆኗን ገልጸው፤ የብሪክስ ፕላስ ስብስብ (ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ግብጽ፣ ኢትዮጵያ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ኢራን እና ዩኤኢ) "የምዕራባውያንን የበላይነት እና አሜሪካ ያለአንዳች ተጠያቂነት የምታደርገውን የዘፈቀደ ድርጊት" እንዲቋቋሙ ጠይቀዋል። በመሆኑም አባል ሀገራቱ እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሜሪካ እና እስራኤልን እንዲያወግዙ አሳስበዋል።
አሜሪካ እና እስራኤል ላደረሱባት ጥቃት አጸፋውን ለመመለስ ኢራን ዩኤኢን ጨምሮ በባህረ ሰላጤው ሀገራት ላይ ጥቃት መሰንዘሯ ይታወሳል። ይህ በመካከላቸው ያለው ልዩነት፣ ውሳኔዎችን በጋራ ስምምነት በሚያሳልፈው የብሪክስ ስብስብ ውስጥ የጋራ መግለጫ ለማውጣት አስቸጋሪ ሊያደርገው እንደሚችል ተገምቷል። ዩኤኢ እና ሌሎች የብሪክስ ሀገራት ለአራግቺ ንግግር የሰጡት ምላሽ ወዲያውኑ አልታወቀም።
የ2026ቱ የብሪክስ ሊቀመንበር የሆነችው እና ከዩኤኢ ጋር ያላት አጋርነት እያደገ የመጣው ህንድ፣ ጦርነቱን ተከትሎ ኢራን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን መዝጋቷ ከፍተኛ ተጽዕኖ ካሳደረባቸው ሀገራት ዋነኛዋ ናት።
ይህ የውሃ መስመር ከዓለም የነዳጅ ማጓጓዣ ውስጥ ወደ አንድ አምስተኛውን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ መዘጋቱ በቅርብ ታሪክ ውስጥ ከታዩት ትላልቅ የአቅርቦት መስተጓጎሎች አንዱን አስከትሏል። የዓለማችን ሶስተኛዋ ትልቋ የነዳጅ አስመጪ የሆነችው ህንድ በባህረ ሰላጤው መዘጋት የተነሳ ከፍተኛ የአቅርቦት እጥረት ያጋጠማት ሲሆን፣ በመርከቦች ላይ በሚደርሰው ጥቃት የባህር ላይ ሰራተኞቿን አጥታለች።
ምንም እንኳን የተኩስ አቁም ስምምነት ቢኖርም፣ አልፎ አልፎ የሚታዩ ጥቃቶች አሁንም እንደቀጠሉ ናቸው። እሮብ እለት የቁም እንስሳትን ጭና ከሶማሊያ ወደ ዩኤኢ ስትጓዝ የነበረች በህንድ የተመዘገበች መርከብ በኦማን ባህር ውስጥ በእሳት አደጋ መስጠሟ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁሉም 14 የቡድን አባላት በኦማን የባህር ዳርቻ ጠባቂዎች ተረፈዋል። ህንድ የጥቃቱን ምንነት ባትገልጽም፣ የብሪታንያ የባህር ላይ አደጋ አስተዳደር ቡድን 'ቫንጋርድ' ግን አደጋው በድሮን ወይም በሚሳኤል ጥቃት ምክንያት የተፈጠረ ፍንዳታ ሊሆን እንደሚችል ገልጿል።
የህንዱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሱብራህማንያም ጃይሻንካር፣ "እየቀጠለ ያለው ውጥረት፣ በባህር ላይ ትራፊክ ላይ የተጋረጠው አደጋ እና የኃይል አቅርቦት መሰረተ ልማቶች መስተጓጎል የሁኔታውን አሳሳቢነት (ተሰባሪነት) ያሳያል" ብለዋል። አክለውም የሆርሙዝ እና የቀይ ባህርን ጨምሮ በዓለም አቀፍ የውሃ መስመሮች ላይ ደህንነቱ የተጠበቀ የባህር ላይ ጉዞ ለዓለም ኢኮኖሚ ደህንነት ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል።
ጃይሻንካር ማንኛውንም ወገን በስም ባይጠቅሱም፣ "ከዓለም አቀፍ ህግ እና ከተባበሩት መንግስታት ቻርተር ጋር የማይጣጣሙ የአንድዮሽ የማስገደድ (የጫና) እርምጃዎች እና ማዕቀቦች መጨመራቸውን" ተችተዋል። እነዚህ እርምጃዎች በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን አብዝተው እንደሚጎዱ በማንሳት፣ "እነዚህ ተገቢ ያልሆኑ እርምጃዎች ውይይትን እና ዲፕሎማሲን ሊተኩ አይችሉም" ብለዋል።
በሌላ ዜና ከብሪክስ ስብሰባ ጋር በተገጣጠመው የቤጂንግ ጉብኝታቸው፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በኢራን ጦርነት ዙሪያ መወያየታቸው ተገልጿል። የዋይት ሃውስ ባለስልጣን እንዳረጋገጡት፣ ሁለቱ መሪዎች የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ክፍት መሆን እንዳለበት እና ቴህራን መቼም ቢሆን የኑክሌር የጦር መሳሪያ ሊኖራት እንደማይገባ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
22 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ሀሙስ ዕለት በቤጂንግ ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ባደረጉት ስብሰባ በታይዋን ጉዳይ ላይ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል። ጉዳዩ በአግባቡ ካልተያዘ በሁለቱ ሀገራት መካከል አለመግባባቶች እና ግጭቶች ሊፈጠሩ እንደሚችሉ ሺ ማስጠንቀቃቸውን የቻይና መንግስት ሚዲያ ዘግቧል።
በጉባኤያቸው ወቅት ሁለቱ መሪዎች ካለፈው ዓመት የንግድ ጦርነት በኋላ የንግድ ግንኙነታቸውን ለማረጋጋት አልመዋል። በተጨማሪም አሜሪካ ከኢራን ጋር ስላላት ጦርነት እርግጠኛ ባልሆነው ሁኔታ ላይ እየመከሩ ይገኛሉ። ነገር ግን ቻይና፣ ታይዋን በአሜሪካ እና ቻይና ግንኙነት ውስጥ ቀዳሚ ትኩረት የምትሰጠው ጉዳይ መሆኗን ግልጽ አድርጋለች።
በዝግ የተካሄደው ይህ ስብሰባ 2 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ያህል የፈጀ ሲሆን፣ ዋይት ሃውስ ስብሰባውን "ጥሩ" ሲል ገልጾታል። በኋላ በተካሄደው ሀገር አቀፍ የራት ግብዣ ላይ፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ሺ ጂንፒንግን እና ባለቤታቸውን በመጪው ሴፕቴምበር 24 በዋይት ሃውስ አጸፋዊ ጉብኝት እንዲያደርጉ መጋበዛቸውን ተናግረዋል።
በርካታ የአሜሪካ የንግድ ተቋማት መሪዎች በሁለትዮሽ ስብሰባው ላይ በከፊል መሳተፋቸውን ዋይት ሃውስ የገለጸ ሲሆን፣ ትራምፕ እያንዳንዳቸውን እንዳስተዋወቋቸው የቻይና ሚዲያዎች ጠቁመዋል። እንደ ቴስላው ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢሎን ማስክ፣ የኤንቪዲያው ጄንሰን ሁዋንግ እና ከኃላፊነት ሊለቁ የሆኑት የአፕሉ ቲም ኩክ የመሳሰሉ ታዋቂ ግለሰቦች በስብሰባው ላይ ተገኝተዋል። ቻይና ለነዚህ ኩባንያዎች ቁልፍ ገበያ ናት። ዋይት ሃውስ ባወጣው መግለጫ፣ ሁለቱ ወገኖች የአሜሪካ የንግድ ተቋማት ወደ ቻይና ገበያ ያላቸውን ተደራሽነት ማስፋት እና የቻይናን ኢንቨስትመንት መጨመርን ጨምሮ በሀገራቱ መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ለማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መወያየታቸውን አስታውቋል።
ትራምፕ እና ሺ ስለ ታይዋን ተወያይተው እንደሆነ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሁለቱም ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ነገር ግን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማኦ ኒንግ በኤክስ ላይ ባሰፈሩት መግለጫ፣ ሺ ለትራምፕ የታይዋን ጥያቄ በቻይና እና አሜሪካ ግንኙነት ውስጥ በጣም አስፈላጊው ጉዳይ መሆኑን ማስገንዘባቸውን ጽፈዋል። በአግባቡ ከተያዘ የሁለትዮሽ ግንኙነቱ አጠቃላይ መረጋጋት እንደሚኖረው፤ አለበለዚያ ግን ሁለቱ ሀገራት ግጭት ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉ አሳስበዋል። በተጨማሪም ሺ የታይዋን ነፃነት እና የባህር ላይ ሰላም እንደ እሳት እና ውሃ የማይጣጣሙ ናቸው ማለታቸው ተዘግቧል።
ዋይት ሃውስ ስለ ስብሰባው ባወጣው መግለጫ ላይ ታይዋንን አላነሳም። ቻይና ታይዋንን እንደራሷ ግዛት የምትቆጥራት ሲሆን፣ አስፈላጊ ከሆነም በኃይል ለመቆጣጠር እንደማታመነታ ስትገልጽ ቆይታለች። አሜሪካ በበኩሏ ለታይዋን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ የምታደርግ ቢሆንም፣ ከቻይና ጋር ጦርነት ቢነሳ ታይዋንን ትከላከል እንደሆነ በግልጽ ከመናገር ትቆጠባለች።
በራት ግብዣው ላይ ሁለቱም መሪዎች እርስ በርሳቸው ተሞካሽተዋል። ትራምፕ እጅግ በጣም አዎንታዊ እና ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን ሲናገሩ፣ ሺ ደግሞ የቻይና ብሔር እና አሜሪካን እንደገና ታላቅ ማድረግ አብረው ሊሄዱ ይችላሉ ብለዋል። ሁለቱም መሪዎች የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አስፈላጊነት አጽንኦት የሰጡ ሲሆን ታሪካዊ ግንኙነታቸውንም አስታውሰዋል።
ሁለቱም ወገኖች በንግድ ጉዳይ ላይ አዎንታዊ መንፈስ አሳይተዋል። የቻይናው ዜና ወኪል ሺንዋ እንደዘገበው፣ ሺ ለትራምፕ የቻይና እና አሜሪካ የኢኮኖሚ ትስስር የጋራ ተጠቃሚነት ያለው መሆኑን ብለዋቸዋል። ሺ አክለውም የንግድ ጦርነት አሸናፊ እንደሌለው እውነታዎች ደጋግመው አሳይተዋል፤ አለመግባባቶች ሲኖሩ እኩልነት ላይ የተመሰረተ ምክክር ብቸኛው ትክክለኛ ምርጫ ነው ማለታቸው ተዘግቧል።
በኢራን ጉዳይ ላይ፣ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ለነፃ የኃይል ፍሰት ክፍት ሆኖ እንዲቀጥል ሁለቱ መሪዎች መስማማታቸውን ዋይት ሃውስ ገልጿል። ፕሬዚዳንት ሺ ቻይና በባህረ ሰላጤው አካባቢ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ማድረግን እንደምትቃወም እና ወደፊት ከባህረ ሰላጤው ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ ተጨማሪ የአሜሪካ ነዳጅ ለመግዛት ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል። ሁለቱም ሀገራት ኢራን መቼም ቢሆን የኑክሌር ጦር መሳሪያ ሊኖራት እንደማይገባ ተስማምተዋል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከኢራን ጋር ስላለው ጦርነት ከንግድ ጉዳይ እኩል ይነሳል ብለው እንዳልጠበቁ ተናግረዋል። የአሜሪካ የግምጃ ቤት ፀሐፊ ስኮት ቤሴንት፣ ቻይና ከአሜሪካ የበለጠ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ እንዲከፈት ፍላጎት እንዳላት ገልጸው፣ ቻይና ከሚያስፈልጋት የኃይል አቅርቦት ውስጥ አንድ ሦስተኛውን የምታገኘው ከባህረ ሰላጤው በመሆኑ መከፈቱ ለእሷም ትልቅ ጥቅም አለው ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በበኩላቸው ቻይና በኢራን ላይ ያላትን ተጽዕኖ እንድትጠቀም አሜሪካ እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
ሀሙስ ጠዋት ቤጂንግ በሚገኘው የህዝብ አዳራሽ ውጭ ትራምፕ እና ሺ እጅ ለእጅ በመጨባበጥ ቀናቸውን ጀምረዋል። አቀባበሉ ወታደራዊ ትርኢቶችን እና የሁለቱን ሀገራት ባንዲራ የሚያውለበልቡ ህጻናትን ያካተተ ነበር። የተረጋጋ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለዓለም ጠቃሚ ነው ያሉት ሺ፣ አጋሮች እንጂ ተቀናቃኞች መሆን የለብንም ብለዋል። ትራምፕ በበኩላቸው ከሺ ጋር ያላቸውን የግል ወዳጅነት በማድነቅ ታላቅ መሪ በማለት አሞካሽተዋቸዋል።
ስብሰባውን የተካፈሉት የአሜሪካ ኩባንያ ዋና ስራ አስፈፃሚዎች (CEOs) ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ መጠናቀቁን ገልጸዋል። የግምጃ ቤት ፀሐፊ ስኮት ቤሴንት ሀሙስ ዕለት እንዳሉት፣ ሁለቱ ሀገራት በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የቁጥጥር ማዕቀፎች ዙሪያ ውይይት ይጀምራሉ። ሁለቱ የኤአይ ልዕለ ኃያላን ሀገራት መነጋገር ሊጀምሩ ነው ሲሉ ቤሴንት አክለው ገልጸዋል።
በጉባኤያቸው ወቅት ሁለቱ መሪዎች ካለፈው ዓመት የንግድ ጦርነት በኋላ የንግድ ግንኙነታቸውን ለማረጋጋት አልመዋል። በተጨማሪም አሜሪካ ከኢራን ጋር ስላላት ጦርነት እርግጠኛ ባልሆነው ሁኔታ ላይ እየመከሩ ይገኛሉ። ነገር ግን ቻይና፣ ታይዋን በአሜሪካ እና ቻይና ግንኙነት ውስጥ ቀዳሚ ትኩረት የምትሰጠው ጉዳይ መሆኗን ግልጽ አድርጋለች።
በዝግ የተካሄደው ይህ ስብሰባ 2 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ያህል የፈጀ ሲሆን፣ ዋይት ሃውስ ስብሰባውን "ጥሩ" ሲል ገልጾታል። በኋላ በተካሄደው ሀገር አቀፍ የራት ግብዣ ላይ፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ሺ ጂንፒንግን እና ባለቤታቸውን በመጪው ሴፕቴምበር 24 በዋይት ሃውስ አጸፋዊ ጉብኝት እንዲያደርጉ መጋበዛቸውን ተናግረዋል።
በርካታ የአሜሪካ የንግድ ተቋማት መሪዎች በሁለትዮሽ ስብሰባው ላይ በከፊል መሳተፋቸውን ዋይት ሃውስ የገለጸ ሲሆን፣ ትራምፕ እያንዳንዳቸውን እንዳስተዋወቋቸው የቻይና ሚዲያዎች ጠቁመዋል። እንደ ቴስላው ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢሎን ማስክ፣ የኤንቪዲያው ጄንሰን ሁዋንግ እና ከኃላፊነት ሊለቁ የሆኑት የአፕሉ ቲም ኩክ የመሳሰሉ ታዋቂ ግለሰቦች በስብሰባው ላይ ተገኝተዋል። ቻይና ለነዚህ ኩባንያዎች ቁልፍ ገበያ ናት። ዋይት ሃውስ ባወጣው መግለጫ፣ ሁለቱ ወገኖች የአሜሪካ የንግድ ተቋማት ወደ ቻይና ገበያ ያላቸውን ተደራሽነት ማስፋት እና የቻይናን ኢንቨስትመንት መጨመርን ጨምሮ በሀገራቱ መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ለማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መወያየታቸውን አስታውቋል።
ትራምፕ እና ሺ ስለ ታይዋን ተወያይተው እንደሆነ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሁለቱም ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ነገር ግን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማኦ ኒንግ በኤክስ ላይ ባሰፈሩት መግለጫ፣ ሺ ለትራምፕ የታይዋን ጥያቄ በቻይና እና አሜሪካ ግንኙነት ውስጥ በጣም አስፈላጊው ጉዳይ መሆኑን ማስገንዘባቸውን ጽፈዋል። በአግባቡ ከተያዘ የሁለትዮሽ ግንኙነቱ አጠቃላይ መረጋጋት እንደሚኖረው፤ አለበለዚያ ግን ሁለቱ ሀገራት ግጭት ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉ አሳስበዋል። በተጨማሪም ሺ የታይዋን ነፃነት እና የባህር ላይ ሰላም እንደ እሳት እና ውሃ የማይጣጣሙ ናቸው ማለታቸው ተዘግቧል።
ዋይት ሃውስ ስለ ስብሰባው ባወጣው መግለጫ ላይ ታይዋንን አላነሳም። ቻይና ታይዋንን እንደራሷ ግዛት የምትቆጥራት ሲሆን፣ አስፈላጊ ከሆነም በኃይል ለመቆጣጠር እንደማታመነታ ስትገልጽ ቆይታለች። አሜሪካ በበኩሏ ለታይዋን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ የምታደርግ ቢሆንም፣ ከቻይና ጋር ጦርነት ቢነሳ ታይዋንን ትከላከል እንደሆነ በግልጽ ከመናገር ትቆጠባለች።
በራት ግብዣው ላይ ሁለቱም መሪዎች እርስ በርሳቸው ተሞካሽተዋል። ትራምፕ እጅግ በጣም አዎንታዊ እና ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን ሲናገሩ፣ ሺ ደግሞ የቻይና ብሔር እና አሜሪካን እንደገና ታላቅ ማድረግ አብረው ሊሄዱ ይችላሉ ብለዋል። ሁለቱም መሪዎች የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አስፈላጊነት አጽንኦት የሰጡ ሲሆን ታሪካዊ ግንኙነታቸውንም አስታውሰዋል።
ሁለቱም ወገኖች በንግድ ጉዳይ ላይ አዎንታዊ መንፈስ አሳይተዋል። የቻይናው ዜና ወኪል ሺንዋ እንደዘገበው፣ ሺ ለትራምፕ የቻይና እና አሜሪካ የኢኮኖሚ ትስስር የጋራ ተጠቃሚነት ያለው መሆኑን ብለዋቸዋል። ሺ አክለውም የንግድ ጦርነት አሸናፊ እንደሌለው እውነታዎች ደጋግመው አሳይተዋል፤ አለመግባባቶች ሲኖሩ እኩልነት ላይ የተመሰረተ ምክክር ብቸኛው ትክክለኛ ምርጫ ነው ማለታቸው ተዘግቧል።
በኢራን ጉዳይ ላይ፣ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ለነፃ የኃይል ፍሰት ክፍት ሆኖ እንዲቀጥል ሁለቱ መሪዎች መስማማታቸውን ዋይት ሃውስ ገልጿል። ፕሬዚዳንት ሺ ቻይና በባህረ ሰላጤው አካባቢ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ማድረግን እንደምትቃወም እና ወደፊት ከባህረ ሰላጤው ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ ተጨማሪ የአሜሪካ ነዳጅ ለመግዛት ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል። ሁለቱም ሀገራት ኢራን መቼም ቢሆን የኑክሌር ጦር መሳሪያ ሊኖራት እንደማይገባ ተስማምተዋል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከኢራን ጋር ስላለው ጦርነት ከንግድ ጉዳይ እኩል ይነሳል ብለው እንዳልጠበቁ ተናግረዋል። የአሜሪካ የግምጃ ቤት ፀሐፊ ስኮት ቤሴንት፣ ቻይና ከአሜሪካ የበለጠ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ እንዲከፈት ፍላጎት እንዳላት ገልጸው፣ ቻይና ከሚያስፈልጋት የኃይል አቅርቦት ውስጥ አንድ ሦስተኛውን የምታገኘው ከባህረ ሰላጤው በመሆኑ መከፈቱ ለእሷም ትልቅ ጥቅም አለው ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በበኩላቸው ቻይና በኢራን ላይ ያላትን ተጽዕኖ እንድትጠቀም አሜሪካ እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
ሀሙስ ጠዋት ቤጂንግ በሚገኘው የህዝብ አዳራሽ ውጭ ትራምፕ እና ሺ እጅ ለእጅ በመጨባበጥ ቀናቸውን ጀምረዋል። አቀባበሉ ወታደራዊ ትርኢቶችን እና የሁለቱን ሀገራት ባንዲራ የሚያውለበልቡ ህጻናትን ያካተተ ነበር። የተረጋጋ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለዓለም ጠቃሚ ነው ያሉት ሺ፣ አጋሮች እንጂ ተቀናቃኞች መሆን የለብንም ብለዋል። ትራምፕ በበኩላቸው ከሺ ጋር ያላቸውን የግል ወዳጅነት በማድነቅ ታላቅ መሪ በማለት አሞካሽተዋቸዋል።
ስብሰባውን የተካፈሉት የአሜሪካ ኩባንያ ዋና ስራ አስፈፃሚዎች (CEOs) ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ መጠናቀቁን ገልጸዋል። የግምጃ ቤት ፀሐፊ ስኮት ቤሴንት ሀሙስ ዕለት እንዳሉት፣ ሁለቱ ሀገራት በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የቁጥጥር ማዕቀፎች ዙሪያ ውይይት ይጀምራሉ። ሁለቱ የኤአይ ልዕለ ኃያላን ሀገራት መነጋገር ሊጀምሩ ነው ሲሉ ቤሴንት አክለው ገልጸዋል።
Sponsored by
Surafel
30 days ago
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ጦርነት ሊያበቃ ነው? አዲሱ ስምምነት ምን ይዟል?
********************
ኢራን ከአሜሪካ የቀረበላትን አዲስ የውሳኔ ሃሳብ እየመረመረች መሆኑን ያስታወቀች ሲሆን፣ ሁለቱ ወገኖች በባህረ ሰላጤው ያለውን ጦርነት በይፋ ለማቆም በሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ላይ ለመስማማት መቃረባቸው ተሰምቷል።
የፓኪስታን እና ሌሎች ከሽምግልና ሂደቱ ጋር ግንኙነት ያላቸው ምንጮች እንደገለጹት፣ ስምምነቱ ጦርነቱን የሚገታ ባለ 14 ነጥብ የውሳኔ ሃሳብ የያዘ ነው።
ይህ የአንድ ገጽ ሰነድ እንደ የኑክሌር መርሃ ግብር ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን ለጊዜው ወደ ጎን በመተው፣ ይልቁንም በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ በኩል ያለውን የመርከብ ጉዞ መክፈት፣ በኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ማንሳት እና በቀጣይ ውይይቶች በኑክሌር መርሃ ግብሩ ላይ ገደቦችን ስለማድረግ በሚሉ ነጥቦች ላይ ትኩረት ያደርጋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ ሀገራቸው አቋሟን በሽምግልናው ግንባር ቀደም ሚና ባላት ፓኪስታን በኩል የምታሳውቅ መሆኑን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ባሰፈሩት ጽሑፍ "ኢራን በተስማማንበት ጉዳይ ላይ ከተስማማች" ጦርነቱ ሊያበቃ እንደሚችል የገለጹ ቢሆንም፣ ስምምነት ለመፈረም ፊት ለፊት ለመገናኘት ግን ገና መሆኑን ለኒውዮርክ ፖስት ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የአሜሪካ ወታደራዊ አጋር የሆነችው እስራኤል ስለ ስምምነቱ መቃረብ መረጃው እንደሌላት ገልጻ፣ ለተጨማሪ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ዝግጅት እያደረገች መሆኑን አስታውቃለች።
በመሀመድ ፊጣሞ
#ebc #iran #usa #peacedeal #donaldtrump #gulfwar #worldpolitics
********************
ኢራን ከአሜሪካ የቀረበላትን አዲስ የውሳኔ ሃሳብ እየመረመረች መሆኑን ያስታወቀች ሲሆን፣ ሁለቱ ወገኖች በባህረ ሰላጤው ያለውን ጦርነት በይፋ ለማቆም በሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ላይ ለመስማማት መቃረባቸው ተሰምቷል።
የፓኪስታን እና ሌሎች ከሽምግልና ሂደቱ ጋር ግንኙነት ያላቸው ምንጮች እንደገለጹት፣ ስምምነቱ ጦርነቱን የሚገታ ባለ 14 ነጥብ የውሳኔ ሃሳብ የያዘ ነው።
ይህ የአንድ ገጽ ሰነድ እንደ የኑክሌር መርሃ ግብር ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን ለጊዜው ወደ ጎን በመተው፣ ይልቁንም በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ በኩል ያለውን የመርከብ ጉዞ መክፈት፣ በኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ማንሳት እና በቀጣይ ውይይቶች በኑክሌር መርሃ ግብሩ ላይ ገደቦችን ስለማድረግ በሚሉ ነጥቦች ላይ ትኩረት ያደርጋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ ሀገራቸው አቋሟን በሽምግልናው ግንባር ቀደም ሚና ባላት ፓኪስታን በኩል የምታሳውቅ መሆኑን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ባሰፈሩት ጽሑፍ "ኢራን በተስማማንበት ጉዳይ ላይ ከተስማማች" ጦርነቱ ሊያበቃ እንደሚችል የገለጹ ቢሆንም፣ ስምምነት ለመፈረም ፊት ለፊት ለመገናኘት ግን ገና መሆኑን ለኒውዮርክ ፖስት ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የአሜሪካ ወታደራዊ አጋር የሆነችው እስራኤል ስለ ስምምነቱ መቃረብ መረጃው እንደሌላት ገልጻ፣ ለተጨማሪ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ዝግጅት እያደረገች መሆኑን አስታውቃለች።
በመሀመድ ፊጣሞ
#ebc #iran #usa #peacedeal #donaldtrump #gulfwar #worldpolitics
1 month ago
ኮዬ ፈጬ የሚገኘው "ሸገር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት"
#fastmereja I የሀገሪቱን ምርጥ አእምሮዎች (Top Scorers) በመሰብሰብ የሚያስተምረው በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ሸገር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (SIT) በሚዲያ ባለሙያዎች እና በማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ተጎበኘ።
ተቋሙ በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ 242 ተማሪዎችን ተቀብሎ በስድስት ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ዘርፎች ትምህርት እየሰጠ ይገኛል።
ከባህላዊው ሴሚስተር በተለየ በዓመት ሦስት "ኳርተሮች" የሚጠቀምበትን ሥርዓት የዘረጋው ኢንስቲትዩቱ፣ የአሜሪካውን በርክሌይ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል የተከተለ ዓለም አቀፍ ካሪኩለም ተግባራዊ አድርጓል። ትምህርቱ የሚሰጠው በሀይብሪድ (በአካልና በቨርቹዋል) ሲሆን፣ በናሳ፣ ጎግል እና ማይክሮሶፍት የሚሰሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ዜጋ ፕሮፌሰሮች ዋናውን ሌክቸር ይመራሉ።
ተቋሙ ትኩረት ያደረገባቸው ስድስት ቁልፍ ዘርፎች፦
📌 አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)
📌 ስፔስ ሳይንስና ኢንጂነሪንግ
📌 ኑክሌር ኢንጂነሪንግ
📌 ባዮ ቴክኖሎጂ
📌 ኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ
📌 ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ናቸው።
የኢንስቲትዩቱ በአራት ዓመት ውስጥ አጠቃላይ የተማሪዎችን ብዛት ከ2,000 እንዳይበልጥ ገድቦ ጥራት ያለው ትምህርት ለመስጠት አቅዷል።
#fastmereja I የሀገሪቱን ምርጥ አእምሮዎች (Top Scorers) በመሰብሰብ የሚያስተምረው በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ሸገር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (SIT) በሚዲያ ባለሙያዎች እና በማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ተጎበኘ።
ተቋሙ በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ 242 ተማሪዎችን ተቀብሎ በስድስት ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ዘርፎች ትምህርት እየሰጠ ይገኛል።
ከባህላዊው ሴሚስተር በተለየ በዓመት ሦስት "ኳርተሮች" የሚጠቀምበትን ሥርዓት የዘረጋው ኢንስቲትዩቱ፣ የአሜሪካውን በርክሌይ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል የተከተለ ዓለም አቀፍ ካሪኩለም ተግባራዊ አድርጓል። ትምህርቱ የሚሰጠው በሀይብሪድ (በአካልና በቨርቹዋል) ሲሆን፣ በናሳ፣ ጎግል እና ማይክሮሶፍት የሚሰሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ዜጋ ፕሮፌሰሮች ዋናውን ሌክቸር ይመራሉ።
ተቋሙ ትኩረት ያደረገባቸው ስድስት ቁልፍ ዘርፎች፦
📌 አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)
📌 ስፔስ ሳይንስና ኢንጂነሪንግ
📌 ኑክሌር ኢንጂነሪንግ
📌 ባዮ ቴክኖሎጂ
📌 ኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ
📌 ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ናቸው።
የኢንስቲትዩቱ በአራት ዓመት ውስጥ አጠቃላይ የተማሪዎችን ብዛት ከ2,000 እንዳይበልጥ ገድቦ ጥራት ያለው ትምህርት ለመስጠት አቅዷል።
1 month ago
አሜሪካ ጦሯን ከአውሮፓ ልታስወጣ እንደምትችል ተገለጸ።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጀርመን የሚገኙትን የአሜሪካ ወታደሮች ቁጥር ለመቀነስ ማሰባቸውን አስታውቀዋል።
ይህ ውሳኔ የመጣው በኢራን ጦርነት ጀርመን ለአሜሪካ "በቂ ድጋፍ" ባለማድረጓ ነው ተብሏል።
በአንፃሩ የጀርመን መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ መርዝ በቅርቡ በአንድ መድረክ ላይ ኢራናውያን "ከጠበቅነው በላይ ናቸው" ሲሉ ማሞካሸታቸው ትራምፕን አስቆጥቷቸዋል።
መርዝ ኢራን የኑክሌር ፕሮግራም ቢኖራት ችግር እንደሌለውም ተናግረዋል። #defence24
seledadotio
seledadotio
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጀርመን የሚገኙትን የአሜሪካ ወታደሮች ቁጥር ለመቀነስ ማሰባቸውን አስታውቀዋል።
ይህ ውሳኔ የመጣው በኢራን ጦርነት ጀርመን ለአሜሪካ "በቂ ድጋፍ" ባለማድረጓ ነው ተብሏል።
በአንፃሩ የጀርመን መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ መርዝ በቅርቡ በአንድ መድረክ ላይ ኢራናውያን "ከጠበቅነው በላይ ናቸው" ሲሉ ማሞካሸታቸው ትራምፕን አስቆጥቷቸዋል።
መርዝ ኢራን የኑክሌር ፕሮግራም ቢኖራት ችግር እንደሌለውም ተናግረዋል። #defence24
seledadotio
seledadotio
1 month ago
የሩሲያ የኑክሌር ሚሳኤል ተሸካሚ አውሮፕላኖች ለሰዓታት የቆየ የቅኝት በረራ አደረጉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሩሲያ ስትራቴጂካዊ የኒውክሌር ሚሳኤል ተሸካሚ አውሮፕላኖች በባሬንትስ እና ኖርዌይ ባህሮች ላይ ለሰባት ሰዓታት የቆየ የቅኝት በረራ አድርገዋል።
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፤ ሁለት የሩሲያ ቲዩ-95ኤምኤስ ስትራቴጂካዊ የኒውክሌር ሚሳኤል ተሸካሚ አውሮፕላኖች ገለልተኛ በሆነው የውሃ አካል ላይ ያደረጉት ለሰዓታት የቆየ በረራ ስኬታማ መሆኑን አስታውቋል።
የሩሲያ ኤሮስፔስ ኃይል የረጅም ርቀት አቪዬሽን አካል የሆኑት እነዚህ አውሮፕላኖች በረራውን ያካሄዱት በተያዘላቸው መርሐ ግብር መሰረት እንደሆነ ተገልጿል።
በበረራው ወቅት የአውሮፕላኑ አብራሪዎች በአየር ላይ ነዳጅ የመሙላት ልምምድ ያደረጉ ሲሆን፤ በኤስዩ-30ኤስኤም የጦር አውሮፕላኖችም እጀባ እንደተደረገላቸው ተጠቁሟል።
የሩሲያ ስትራቴጂካዊ የኒውክሌር ሚሳኤል ተሸካሚ አውሮፕላኖች በጉዟቸው ወቅት በተለያዩ መስመሮች ላይ የውጭ ሀገራት ተዋጊ ጄቶች ክትትል ሲያደርጉባቸው እንደነበርም ሚኒስቴሩ በመግለጫው አመልክቷል።
የሀገሪቱ አየር ኃይል የሚያደርጋቸው ማናቸውም በረራዎች ዓለም አቀፍ የአየር ክልል አጠቃቀም ደንቦችን በጥብቅ የተከተሉ ናቸው ሲልም አረጋግጧል።
የሩሲያ የረጅም ርቀት አቪዬሽን ቡድኖች በአርክቲክ፣ በሰሜን አትላንቲክ፣ በፓስፊክ ውቅያኖስ፣ በባልቲክ እና ጥቁር ባሕር ገለልተኛ ውሃዎች ላይ በየጊዜው ተመሳሳይ በረራዎችን እንደሚያደርጉ የአናዶሉ ዘገባ ያመላክታል።
በሶስና አለማየሁ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሩሲያ ስትራቴጂካዊ የኒውክሌር ሚሳኤል ተሸካሚ አውሮፕላኖች በባሬንትስ እና ኖርዌይ ባህሮች ላይ ለሰባት ሰዓታት የቆየ የቅኝት በረራ አድርገዋል።
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፤ ሁለት የሩሲያ ቲዩ-95ኤምኤስ ስትራቴጂካዊ የኒውክሌር ሚሳኤል ተሸካሚ አውሮፕላኖች ገለልተኛ በሆነው የውሃ አካል ላይ ያደረጉት ለሰዓታት የቆየ በረራ ስኬታማ መሆኑን አስታውቋል።
የሩሲያ ኤሮስፔስ ኃይል የረጅም ርቀት አቪዬሽን አካል የሆኑት እነዚህ አውሮፕላኖች በረራውን ያካሄዱት በተያዘላቸው መርሐ ግብር መሰረት እንደሆነ ተገልጿል።
በበረራው ወቅት የአውሮፕላኑ አብራሪዎች በአየር ላይ ነዳጅ የመሙላት ልምምድ ያደረጉ ሲሆን፤ በኤስዩ-30ኤስኤም የጦር አውሮፕላኖችም እጀባ እንደተደረገላቸው ተጠቁሟል።
የሩሲያ ስትራቴጂካዊ የኒውክሌር ሚሳኤል ተሸካሚ አውሮፕላኖች በጉዟቸው ወቅት በተለያዩ መስመሮች ላይ የውጭ ሀገራት ተዋጊ ጄቶች ክትትል ሲያደርጉባቸው እንደነበርም ሚኒስቴሩ በመግለጫው አመልክቷል።
የሀገሪቱ አየር ኃይል የሚያደርጋቸው ማናቸውም በረራዎች ዓለም አቀፍ የአየር ክልል አጠቃቀም ደንቦችን በጥብቅ የተከተሉ ናቸው ሲልም አረጋግጧል።
የሩሲያ የረጅም ርቀት አቪዬሽን ቡድኖች በአርክቲክ፣ በሰሜን አትላንቲክ፣ በፓስፊክ ውቅያኖስ፣ በባልቲክ እና ጥቁር ባሕር ገለልተኛ ውሃዎች ላይ በየጊዜው ተመሳሳይ በረራዎችን እንደሚያደርጉ የአናዶሉ ዘገባ ያመላክታል።
በሶስና አለማየሁ
1 month ago
የካንሰር ሕክምናን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረው ''ክብር ደስታ'' የካንሰር ማዕከል ተመረቀ!
#fastmereja : በኢትዮጵያ የካንሰር ሕክምና ተደራሽነትን ለማስፋትና ታካሚዎች ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚሄዱበትን እንግልት ለማስቀረት ያለመው ''ክብር ደስታ የካንሰር ማዕከል" በአዲስ አበባ ከተማ በይፋ ተመረቀ፡፡
ማዕከሉ ''ክብር" እና "ደስታ" የሚሉትን እሴቶች በመያዝ፣ ታካሚዎችን በሰብአዊ ክብርና በደስታ ማገልገልን ዓላማ ያደረገ ሲሆን፤ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ከርኅራኄ ጋር በማጣመር አዲስ የሕክምና ምዕራፍ እንደሚከፍት ይጠበቃል።
የማዕከሉ አንዱ ትልቅ ስኬት በኢትዮጵያ ውስጥ ብቸኛው የተሟላ የጡት ካንሰር ምርመራና ሕክምና መስጠት የሚችል ተቋም መሆኑ ነው፡፡ ለዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ እንደ 3D ማሞግራፊ (3D Mammography)፣ ስቴሪዮታክቲክባዮፕሲ (Stereotactic Biopsy) እና የጡት ኤም.አር.አይ (Breast MRI) ያሉ እጅግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን አሟልቷል፡፡
ማዕከሉ መጀመሪያ ትኩረቱን በጡት ካንሰር ላይ ቢያደርግም፣ በአሁኑ ወቅት ሌሎች የካንሰር ዓይነቶችንም ማከም መጀመሩ ተገልፆ በዘርፉ የሰለጠኑ የኦንኮሎጂ ስፔሻሊስቶች፣ ጠቅላላ ሐኪሞች እና የኦንኮሎጂ ነርሶች በቡድን በመሆን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የተቀናጀ ሕክምና ለታካሚዎች ይሰጣሉ ተብሏል።
ክብር ደስታ የካንሰር ማዕከል በረዳት ሜዲካል ፕላዛ (Redat Medical Plaza) ውስጥ ስትራቴጂካዊ በሆነ መልኩ መገኘቱ ታካሚዎች ከአንድ ጣራ ሥር ሁሉንም አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችላቸዉ ሲሆን ይህም የተቀናጀ የካንሰር ቀዶ ጥገና፣ የኑክሌርሜዲስን፣ የላቦራቶሪ እና የድንገተኛ አደጋ ሕክምናን ያጠቃልላል።
በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ ካንሰር በጊዜ ከተደረሰበት መዳን የሚችል ሲሆን ማዕከሉ ታካሚዎች ከበሽታው አገግመው የተሻለ ሕይወት እንዲመሩ የሚያስችል (CANCERVIVE/CANTHRIVE) የስነ-ልቦና እና የህክምና ድጋፍ ለመስጠት መዘጋጀቱንም አስታውቋል።
በምረቃው ወቅት የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘዉዴን ጨምሮ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና የዘርፉ ተዋናዮች የተገኙ ሲሆን፤ ይህ ማዕከል መከፈቱ በኢትዮጵያ የጤናው ዘርፍ ያለውን ክፍተት ከመሙላቱም በላይ፣ ዜጎች በሀገራቸው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሕክምና እንዲያገኙ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።
#fastmereja : በኢትዮጵያ የካንሰር ሕክምና ተደራሽነትን ለማስፋትና ታካሚዎች ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚሄዱበትን እንግልት ለማስቀረት ያለመው ''ክብር ደስታ የካንሰር ማዕከል" በአዲስ አበባ ከተማ በይፋ ተመረቀ፡፡
ማዕከሉ ''ክብር" እና "ደስታ" የሚሉትን እሴቶች በመያዝ፣ ታካሚዎችን በሰብአዊ ክብርና በደስታ ማገልገልን ዓላማ ያደረገ ሲሆን፤ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ከርኅራኄ ጋር በማጣመር አዲስ የሕክምና ምዕራፍ እንደሚከፍት ይጠበቃል።
የማዕከሉ አንዱ ትልቅ ስኬት በኢትዮጵያ ውስጥ ብቸኛው የተሟላ የጡት ካንሰር ምርመራና ሕክምና መስጠት የሚችል ተቋም መሆኑ ነው፡፡ ለዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ እንደ 3D ማሞግራፊ (3D Mammography)፣ ስቴሪዮታክቲክባዮፕሲ (Stereotactic Biopsy) እና የጡት ኤም.አር.አይ (Breast MRI) ያሉ እጅግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን አሟልቷል፡፡
ማዕከሉ መጀመሪያ ትኩረቱን በጡት ካንሰር ላይ ቢያደርግም፣ በአሁኑ ወቅት ሌሎች የካንሰር ዓይነቶችንም ማከም መጀመሩ ተገልፆ በዘርፉ የሰለጠኑ የኦንኮሎጂ ስፔሻሊስቶች፣ ጠቅላላ ሐኪሞች እና የኦንኮሎጂ ነርሶች በቡድን በመሆን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የተቀናጀ ሕክምና ለታካሚዎች ይሰጣሉ ተብሏል።
ክብር ደስታ የካንሰር ማዕከል በረዳት ሜዲካል ፕላዛ (Redat Medical Plaza) ውስጥ ስትራቴጂካዊ በሆነ መልኩ መገኘቱ ታካሚዎች ከአንድ ጣራ ሥር ሁሉንም አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችላቸዉ ሲሆን ይህም የተቀናጀ የካንሰር ቀዶ ጥገና፣ የኑክሌርሜዲስን፣ የላቦራቶሪ እና የድንገተኛ አደጋ ሕክምናን ያጠቃልላል።
በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ ካንሰር በጊዜ ከተደረሰበት መዳን የሚችል ሲሆን ማዕከሉ ታካሚዎች ከበሽታው አገግመው የተሻለ ሕይወት እንዲመሩ የሚያስችል (CANCERVIVE/CANTHRIVE) የስነ-ልቦና እና የህክምና ድጋፍ ለመስጠት መዘጋጀቱንም አስታውቋል።
በምረቃው ወቅት የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘዉዴን ጨምሮ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና የዘርፉ ተዋናዮች የተገኙ ሲሆን፤ ይህ ማዕከል መከፈቱ በኢትዮጵያ የጤናው ዘርፍ ያለውን ክፍተት ከመሙላቱም በላይ፣ ዜጎች በሀገራቸው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሕክምና እንዲያገኙ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።
1 month ago
"ፓኪስታን ገለልተኛ አይደለችም" በቴህራንና በዋሽንግተን ድርድር ላይ አዲስ ውዝግብ
#ethiopia | የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በኦማንና በፓኪስታን እያደረጉት ያለው የዲፕሎማሲ "ጥረት" በሀገር ቤት ተቃውሞ ገጠመው። የኢራን ብሔራዊ ደህንነትና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚሽን ቃል አቀባይ ኢብራሂም ሬዛኢ፤ ፓኪስታን በአሜሪካና በኢራን መካከል ለሚደረገው ድርድር "ትክክለኛ አስታራቂ አይደለችም" ሲሉ በግልጽ ተናግረዋል።
እንደ ሬዛኢ ገለጻ፣ ፓኪስታን ለሽምግልና የሚያስፈልገው ተዓማኒነትና ገለልተኝነት ይጎድላታል።
የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ከሰሞኑ በኢስላማባድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ጋር ተወያይተዋል። ይሁን እንጂ ኢብራሂም ሬዛኢ በኤክስ (X) ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጠንከር ያለ መልዕክት የሚከተሉትን ነጥቦች አንስተዋል፦
ፓኪስታን ምንም እንኳ ጥሩ ጎረቤት ብትሆንም፣ ለዋሽንግተን ስለምታደላ ለድርድር ምቹ አይደለችም።
ፓኪስታን አሜሪካን በግልጽ ከመተቸት ትቆጠባለች፤ ይህም ከአስታራቂነት ባህሪ ጋር ይጋጫል።
አሜሪካ በሊባኖስ ጉዳይና በታገዱ የኢራን ንብረቶች ላይ የገባችውን ቃል እንድትፈጽም ፓኪስታን አስፈላጊውን ተፅዕኖ አልፈጠረችም።
የኢራን ሚዲያዎች እንደሚጠቁሙት፣ የሰላም ድርድሩ ከኑክሌር ፋይል በዘለለ ስሱና ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮችን አካቷል፦
፦ አዲስ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት።
፦ ኢራን ላለፉት ዓመታት ለደረሰባት ኪሳራ ካሳ መጠየቅ።
፦ ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃዎች እንዳይወሰዱ ዋስትና ማግኘት።
፦ በአሜሪካ የተጣሉ የባህር ላይ ገደቦችን ማንሳት።
በአንድ በኩል ሚኒስትር አራግቺ በኢስላማባድና በሙስካት የዲፕሎማሲ ደጃፎችን ሲያንኳኩ፣ በሌላ በኩል በቴህራን ያሉ ህግ አውጪዎች የአደራዳሪውን ማንነት ጥያቄ ውስጥ መክተታቸው ድርድሩን ምን ያህል ውስብስብ እንደሚያደርገው አመላካች ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ኢራን #ፓኪስታን #አሜሪካ #ዲፕሎማሲ #የሰላምድርድር #መካከለኛው ምስራቅ #ዜና #iran #pakistan #usa
#ethiopia | የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በኦማንና በፓኪስታን እያደረጉት ያለው የዲፕሎማሲ "ጥረት" በሀገር ቤት ተቃውሞ ገጠመው። የኢራን ብሔራዊ ደህንነትና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚሽን ቃል አቀባይ ኢብራሂም ሬዛኢ፤ ፓኪስታን በአሜሪካና በኢራን መካከል ለሚደረገው ድርድር "ትክክለኛ አስታራቂ አይደለችም" ሲሉ በግልጽ ተናግረዋል።
እንደ ሬዛኢ ገለጻ፣ ፓኪስታን ለሽምግልና የሚያስፈልገው ተዓማኒነትና ገለልተኝነት ይጎድላታል።
የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ከሰሞኑ በኢስላማባድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ጋር ተወያይተዋል። ይሁን እንጂ ኢብራሂም ሬዛኢ በኤክስ (X) ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጠንከር ያለ መልዕክት የሚከተሉትን ነጥቦች አንስተዋል፦
ፓኪስታን ምንም እንኳ ጥሩ ጎረቤት ብትሆንም፣ ለዋሽንግተን ስለምታደላ ለድርድር ምቹ አይደለችም።
ፓኪስታን አሜሪካን በግልጽ ከመተቸት ትቆጠባለች፤ ይህም ከአስታራቂነት ባህሪ ጋር ይጋጫል።
አሜሪካ በሊባኖስ ጉዳይና በታገዱ የኢራን ንብረቶች ላይ የገባችውን ቃል እንድትፈጽም ፓኪስታን አስፈላጊውን ተፅዕኖ አልፈጠረችም።
የኢራን ሚዲያዎች እንደሚጠቁሙት፣ የሰላም ድርድሩ ከኑክሌር ፋይል በዘለለ ስሱና ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮችን አካቷል፦
፦ አዲስ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት።
፦ ኢራን ላለፉት ዓመታት ለደረሰባት ኪሳራ ካሳ መጠየቅ።
፦ ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃዎች እንዳይወሰዱ ዋስትና ማግኘት።
፦ በአሜሪካ የተጣሉ የባህር ላይ ገደቦችን ማንሳት።
በአንድ በኩል ሚኒስትር አራግቺ በኢስላማባድና በሙስካት የዲፕሎማሲ ደጃፎችን ሲያንኳኩ፣ በሌላ በኩል በቴህራን ያሉ ህግ አውጪዎች የአደራዳሪውን ማንነት ጥያቄ ውስጥ መክተታቸው ድርድሩን ምን ያህል ውስብስብ እንደሚያደርገው አመላካች ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ኢራን #ፓኪስታን #አሜሪካ #ዲፕሎማሲ #የሰላምድርድር #መካከለኛው ምስራቅ #ዜና #iran #pakistan #usa
1 month ago
ሁለቱ ሀገራት ተደራዳሪዎች ልከዋል?
#ethiopia | ኢራን እና አሜሪካ የልዑካን ቡድናቸውን ወደ ፓኪስታን መላካቸው ተዘግቧል።
ከአሜሪካ በኩል የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ የሚመራ፣ ከኢራን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ የሚመራ የተደራዳሪ ቡድን ወደ ኢስላማባድ አቅንቷል ተብሏል።
ባሳለፍነው ሰኞ እለት ሊጀመር የታቀደው ሁለተኛው ዙር ድርድር የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ለመሳተፍ ወደ ፓኪስታን ቢያቀኑም፣ የኢራን ተደራዳሪዎች ባለመገኘታቸው ድርድሩ ሳይካሄድ ቀርቷል።
የኢራኑ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ግን የኢራን በወቅቱ ተደራዳሪዎች "ወደ ፓኪስታን ማቅናታቸውን" ገልጸው ነበር። ይህ ንግግራቸው ግን መጨረሻው እውነት ሆኖ አልተገኘም።
አሁን ደግሞ የአልጄዚራ ዘገባ እንዳለው ከሆነ፣ ኢራን እና አሜሪካ የልዑካን ቡድናቸውን ወደ ፓኪስታን ልከዋል።
ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም በነበራቸው ውይይት የኑክሌር ምርት ጉዳይ ዋነኛ ማጠንጠኛ ቢሆንም አሁን ደግሞ የሆርሙዝ ሰርጥ የመስተዳደር ኃላፊነት ሌላ አጀንዳ ሆኗል ተብሏል።
በአንፃሩ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለ15 የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ለተጨማሪ ቀናት መራዘሙን ማስታወቃቸው አይዘነጋም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #aljazeera #thiqaheth
#ethiopia | ኢራን እና አሜሪካ የልዑካን ቡድናቸውን ወደ ፓኪስታን መላካቸው ተዘግቧል።
ከአሜሪካ በኩል የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ የሚመራ፣ ከኢራን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ የሚመራ የተደራዳሪ ቡድን ወደ ኢስላማባድ አቅንቷል ተብሏል።
ባሳለፍነው ሰኞ እለት ሊጀመር የታቀደው ሁለተኛው ዙር ድርድር የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ለመሳተፍ ወደ ፓኪስታን ቢያቀኑም፣ የኢራን ተደራዳሪዎች ባለመገኘታቸው ድርድሩ ሳይካሄድ ቀርቷል።
የኢራኑ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ግን የኢራን በወቅቱ ተደራዳሪዎች "ወደ ፓኪስታን ማቅናታቸውን" ገልጸው ነበር። ይህ ንግግራቸው ግን መጨረሻው እውነት ሆኖ አልተገኘም።
አሁን ደግሞ የአልጄዚራ ዘገባ እንዳለው ከሆነ፣ ኢራን እና አሜሪካ የልዑካን ቡድናቸውን ወደ ፓኪስታን ልከዋል።
ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም በነበራቸው ውይይት የኑክሌር ምርት ጉዳይ ዋነኛ ማጠንጠኛ ቢሆንም አሁን ደግሞ የሆርሙዝ ሰርጥ የመስተዳደር ኃላፊነት ሌላ አጀንዳ ሆኗል ተብሏል።
በአንፃሩ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለ15 የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ለተጨማሪ ቀናት መራዘሙን ማስታወቃቸው አይዘነጋም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #aljazeera #thiqaheth
1 month ago
የኢራን ዩራኒየም እና የሰላም ድርድሩ አዲስ ማነቆ!
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ "ኢራን የዩራኒየም ክምችቷን አሳልፋ ለመስጠት ተስማምታለች" በማለት ቢናገሩም ኢራን ግን "ፈጽሞ የማይታሰብ ነው" በማለት ውሳኔዋን አስታውቃለች።
ዩራኒየም ከመሬት የሚወጣ ማዕድን ቢሆንም ግን እንደወጣ በቀጥታ ጥቅም ላይ አይውልም። ጠቃሚው ክፍል እንዲበዛ የማድረግ ሂደት "ማበልጸግ" ይባላል። ዝቅተኛ ደረጃው ዩራኒየም በትንሹ ከበለፀገ ለቤት ውስጥ መብራትና ለፋብሪካዎች ኃይል ይሰጣል። ከፍተኛ ደረጃው ዩራኒየም በጣም ከበለፀገ ግን ወደ "ኑክሌር ቦምብ" ይቀየራል።
ኢራን ከፍተኛ መጠን ያለው ዩራኒየም አከማችታለች። አሜሪካ ደግሞ "ይህ ክምችት ወደ ቦምብ ሊቀየር ይችላል" የሚል ስጋት አላት ለዚህም ነው ትራምፕ "ኢራን ክምችቱን አሳልፋ ትስጥ" የሚል ግፊት የሚያደርጉት። ኢራን ግን "ለሃይል ማመንጫ ስለምፈልገው ክምችቱን አሳልፌ አልሰጥም" እያለች ነው።
ሁለቱ ሀገራት ለሰላም ድርድር እየተዘጋጁ ቢሆንም ይህ የዩራኒየም ክምችት ጉዳይ ግን ድርድሩን ከባድ ሊያደርገው እንደሚችል ተገምቷል። ኢራን "አልሰጥም" ማለቷ በአሜሪካ በኩል ተጨማሪ ማዕቀቦች ሊመጡ እንደሚችሉ ፍንጭ እየሰጠ ነው።
seledadotio
seledadotio
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ "ኢራን የዩራኒየም ክምችቷን አሳልፋ ለመስጠት ተስማምታለች" በማለት ቢናገሩም ኢራን ግን "ፈጽሞ የማይታሰብ ነው" በማለት ውሳኔዋን አስታውቃለች።
ዩራኒየም ከመሬት የሚወጣ ማዕድን ቢሆንም ግን እንደወጣ በቀጥታ ጥቅም ላይ አይውልም። ጠቃሚው ክፍል እንዲበዛ የማድረግ ሂደት "ማበልጸግ" ይባላል። ዝቅተኛ ደረጃው ዩራኒየም በትንሹ ከበለፀገ ለቤት ውስጥ መብራትና ለፋብሪካዎች ኃይል ይሰጣል። ከፍተኛ ደረጃው ዩራኒየም በጣም ከበለፀገ ግን ወደ "ኑክሌር ቦምብ" ይቀየራል።
ኢራን ከፍተኛ መጠን ያለው ዩራኒየም አከማችታለች። አሜሪካ ደግሞ "ይህ ክምችት ወደ ቦምብ ሊቀየር ይችላል" የሚል ስጋት አላት ለዚህም ነው ትራምፕ "ኢራን ክምችቱን አሳልፋ ትስጥ" የሚል ግፊት የሚያደርጉት። ኢራን ግን "ለሃይል ማመንጫ ስለምፈልገው ክምችቱን አሳልፌ አልሰጥም" እያለች ነው።
ሁለቱ ሀገራት ለሰላም ድርድር እየተዘጋጁ ቢሆንም ይህ የዩራኒየም ክምችት ጉዳይ ግን ድርድሩን ከባድ ሊያደርገው እንደሚችል ተገምቷል። ኢራን "አልሰጥም" ማለቷ በአሜሪካ በኩል ተጨማሪ ማዕቀቦች ሊመጡ እንደሚችሉ ፍንጭ እየሰጠ ነው።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ኢራን አሜሪካ 10 የመደራደሪያ ነጥቦቻችንን ተቀብላለች በሚል መረጃ ማሰራጨቷን ተከትሎ "የኢራን 10 የመደራደሪያ ነጥቦች ቀልድ ናቸው ሲሉ ትራምፕ ያጣጣሉ ሲሆን ምክትል ፕሬዝዳቱም ጆን ቫንስ በ AI የተፃፈ አስቂኝ ቀልድ ነው፣ወዲያውኑ ወደ ቆሻሻ ቦታ ጥለነዋል" ሲሉ አጣጥለውታል።
ሙሉ ስምምነት እንከሚፈፀም ድረስ የአሜሪካ ጦር አሁንም በኢራን ይቆያል ሲሉ ትራምፕ ገልፀዋል።
ሁሉም መርከቦች አውሮፕላኖች እና ወታደራዊ አባላት ባሉበት ይቆያሉ በማንኛውም ምክንያት ስምምነቱ የሚቋረጥ ከሆነ ማንም አይቶት በማያውቅ ሁኔታ ተኩስ ይጀመራል ያውም ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ በማለት ተናግሯል።
ኢራን ኑክሌር ቦንብ አይኖራትም፣የሆርሙዝ ሰርጥም ይከፈታል ብለዋል።
seledadotio
seledadotio
ሙሉ ስምምነት እንከሚፈፀም ድረስ የአሜሪካ ጦር አሁንም በኢራን ይቆያል ሲሉ ትራምፕ ገልፀዋል።
ሁሉም መርከቦች አውሮፕላኖች እና ወታደራዊ አባላት ባሉበት ይቆያሉ በማንኛውም ምክንያት ስምምነቱ የሚቋረጥ ከሆነ ማንም አይቶት በማያውቅ ሁኔታ ተኩስ ይጀመራል ያውም ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ በማለት ተናግሯል።
ኢራን ኑክሌር ቦንብ አይኖራትም፣የሆርሙዝ ሰርጥም ይከፈታል ብለዋል።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
''ሊባኖስ ገና ቅጣቷን አልጨረሰችም'' ኔታንያሁ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት አዲስ መልክ እየያዘ ባለበት በዚህ ወቅት፣ እስራኤል ሌሊቱን ይፋ የተደረገውን ባለ ሁለት ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት እንደምትደግፍ አስታውቃለች። ይሁን እንጂ ይህ ስምምነት "ሊባኖስን እንደማያካትት" ግልጽ በማድረግ ጉዳዩን ወደ ሌላ አቅጣጫ መልሳዋለች።
የጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ በኢራን እና በምዕራባውያን መካከል የተደረሰውን ስምምነት መቀበሏን አረጋግጧል።
እንደ እስራኤል መግለጫ ከሆነ፣ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት የሚቆየው ይሄው ስምምነት የሚከተሉትን ዋና ዋና ጉዳዮች ይዟል፦
እስራኤል በኢራን ላይ የምታደርሰውን ወታደራዊ እርምጃ ታቆማለች።
ኢራን ወሳኝ የሆነውን የሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ለትራንስፖርት ክፍት ታደርጋለች።
ኢራን በአሜሪካ፣ በእስራኤል እና በቀጠናው አገራት ላይ የምታደርሰውን ማንኛውንም ጥቃት ለሁለት ሳምንታት ሙሉ በሙሉ ታቆማለች።
አሜሪካ ኢራን "የኑክሌር፣ የሚሳኤል እና የሽብር ስጋት እንዳትሆን" የምታደርገውን ጥረት እስራኤል እንደምትደግፍ ገልጻለች።
የዚህ ስምምነት ትልቁ አነጋጋሪ ነጥብ በሊባኖስ በኩል ያለው ግንኙነት ነው። የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ስምምነቱ ሊባኖስንም እንደሚያካትት ቀደም ብለው ቢናገሩም፣ የእስራኤል ወገን ግን ይህንን በፍጹም ውድቅ አድርጎታል።
"ይህ ስምምነት ሊባኖስን አያካትትም" ሲል የኔታንያሁ ቢሮ በግልጽ አስታውቋል።
ይህም ማለት እስራኤል ከኢራን ጋር "ጊዜያዊ ሰላም" ብታወርድም፣ በሰሜን በኩል ከሂዝቦላህ ጋር የምታደርገው ፍልሚያ እንደማይቆም ፍንጭ ሰጥታለች። ቀጠናው ለሁለት ሳምንታት "እፎይ" ቢልም፣ የሊባኖስ ሰማይ ግን አሁንም በስጋት እንደተሸፈነ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #israel #iran #ceasefire #lebanon #middleeastnews #breakingnews
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት አዲስ መልክ እየያዘ ባለበት በዚህ ወቅት፣ እስራኤል ሌሊቱን ይፋ የተደረገውን ባለ ሁለት ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት እንደምትደግፍ አስታውቃለች። ይሁን እንጂ ይህ ስምምነት "ሊባኖስን እንደማያካትት" ግልጽ በማድረግ ጉዳዩን ወደ ሌላ አቅጣጫ መልሳዋለች።
የጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ በኢራን እና በምዕራባውያን መካከል የተደረሰውን ስምምነት መቀበሏን አረጋግጧል።
እንደ እስራኤል መግለጫ ከሆነ፣ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት የሚቆየው ይሄው ስምምነት የሚከተሉትን ዋና ዋና ጉዳዮች ይዟል፦
እስራኤል በኢራን ላይ የምታደርሰውን ወታደራዊ እርምጃ ታቆማለች።
ኢራን ወሳኝ የሆነውን የሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ለትራንስፖርት ክፍት ታደርጋለች።
ኢራን በአሜሪካ፣ በእስራኤል እና በቀጠናው አገራት ላይ የምታደርሰውን ማንኛውንም ጥቃት ለሁለት ሳምንታት ሙሉ በሙሉ ታቆማለች።
አሜሪካ ኢራን "የኑክሌር፣ የሚሳኤል እና የሽብር ስጋት እንዳትሆን" የምታደርገውን ጥረት እስራኤል እንደምትደግፍ ገልጻለች።
የዚህ ስምምነት ትልቁ አነጋጋሪ ነጥብ በሊባኖስ በኩል ያለው ግንኙነት ነው። የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ስምምነቱ ሊባኖስንም እንደሚያካትት ቀደም ብለው ቢናገሩም፣ የእስራኤል ወገን ግን ይህንን በፍጹም ውድቅ አድርጎታል።
"ይህ ስምምነት ሊባኖስን አያካትትም" ሲል የኔታንያሁ ቢሮ በግልጽ አስታውቋል።
ይህም ማለት እስራኤል ከኢራን ጋር "ጊዜያዊ ሰላም" ብታወርድም፣ በሰሜን በኩል ከሂዝቦላህ ጋር የምታደርገው ፍልሚያ እንደማይቆም ፍንጭ ሰጥታለች። ቀጠናው ለሁለት ሳምንታት "እፎይ" ቢልም፣ የሊባኖስ ሰማይ ግን አሁንም በስጋት እንደተሸፈነ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #israel #iran #ceasefire #lebanon #middleeastnews #breakingnews
2 months ago
ትራምፕ ኑክሌር ሊጠቀሙ ይችላሉ‼️
ትራምፕ የኒውክሌር ጦር መሳሪያን በኢራን ላይ ሊያሰማራ ይችላል የሚል ስጋት መኖሩን ዘጋርዲያን ዘግቧል።
በአሜሪካ መንግስታዊ ስርዓት ፕሬዚዳንቱ የኒውክሌር ቦንብን የማዘዝ ብቸኛ ስልጣን አላቸው። በዚህ የኑክሌር ትዕዛዝ ሰንሰለት ውስጥ የፕሬዝዳንቱን የኑክሌር ትዕዛዝ ማንም ሰው ጣልቃ ገብቶ ማስቆም አይችልም።
Image:-AI generated
seledadotio
seledadotio
ትራምፕ የኒውክሌር ጦር መሳሪያን በኢራን ላይ ሊያሰማራ ይችላል የሚል ስጋት መኖሩን ዘጋርዲያን ዘግቧል።
በአሜሪካ መንግስታዊ ስርዓት ፕሬዚዳንቱ የኒውክሌር ቦንብን የማዘዝ ብቸኛ ስልጣን አላቸው። በዚህ የኑክሌር ትዕዛዝ ሰንሰለት ውስጥ የፕሬዝዳንቱን የኑክሌር ትዕዛዝ ማንም ሰው ጣልቃ ገብቶ ማስቆም አይችልም።
Image:-AI generated
seledadotio
seledadotio
2 months ago
ጦርነቱ አድማሱን እያሰፋ ነው‼️
እስራኤል ከደቂቃዎች በፊት የኢራንን የውሃ ማመንጫ ተቋምን እና የኑክሌር ማመንጫ ሀይልን መታለች።
ኢራን በውሃ እጥረት የምትሰቃይ ሀገር መሆኗ ይታወቃል።
ከዚህ በተጨማሪ የኢራን የብረታ ብረት ፋብሪካ በአሜሪካ እና እስራኤል በዛሬው ዕለት ወድሟል።
ኢራን ይህንን ተከትሎ የአሜሪካ የጦር ቤዝ ያለባቸው የሁሉንም ሀገራትን የብረታ ብረት ፋብሪካ ላይ ጥቃት እንደምትፈፅም ዝታለች።
የአሜሪካ እና እስራኤል ጋር ግንኙነት ያላቸው የቀጠናው ፋብሪካዎች ሰራተኞቻቸውን በአስቸኳይ እንዲያስወጡ ኢራን ትዕዛዝ አስተላልፋለች።
seledadotio
seledadotio
እስራኤል ከደቂቃዎች በፊት የኢራንን የውሃ ማመንጫ ተቋምን እና የኑክሌር ማመንጫ ሀይልን መታለች።
ኢራን በውሃ እጥረት የምትሰቃይ ሀገር መሆኗ ይታወቃል።
ከዚህ በተጨማሪ የኢራን የብረታ ብረት ፋብሪካ በአሜሪካ እና እስራኤል በዛሬው ዕለት ወድሟል።
ኢራን ይህንን ተከትሎ የአሜሪካ የጦር ቤዝ ያለባቸው የሁሉንም ሀገራትን የብረታ ብረት ፋብሪካ ላይ ጥቃት እንደምትፈፅም ዝታለች።
የአሜሪካ እና እስራኤል ጋር ግንኙነት ያላቸው የቀጠናው ፋብሪካዎች ሰራተኞቻቸውን በአስቸኳይ እንዲያስወጡ ኢራን ትዕዛዝ አስተላልፋለች።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
በኢራን የዩራኒየም ማበልጸጊያ ጣቢያ ላይ የአየር ጥቃት ተሰነዘረ
በመካከለኛው ኢራን ያዝድ ከተማ አቅራቢያ የሚገኘውና "ቢጫው ኬክ" ተብሎ የሚጠራውን የዩራኒየም ዱቄት የሚያመርተው ፋብሪካ የአየር ጥቃት እንደተሰነዘረበት የኢራን መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
የአገሪቱ የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ጥቃቱ በፈቃድ በ"አሜሪካ-በእስራኤል " የተፈጸመ መሆኑን ገልጿል።
የፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው ከሆነ፣ ጥቃቱ በፈርዱ አካባቢ በሚገኘው የዩራኒየም ማቀነባበሪያ ላይ ያረፈ ቢሆንም፣ እስካሁን በደረሰው የመጀመሪያ ደረጃ ግምገማ ምንም ዓይነት የጨረር ስርጭት አለመከሰቱ ገልፇል።
በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ የሚደርስ የጤና ስጋት እንደሌለ ተገልጿል።
"ቢጫው ኬክ" ለኑክሌር ጦር መሣሪያ ዝግጅት ወይም ለሃይል ማመንጫነት የሚያገለግለው ዩራኒየም እንዲበለጽግ የሚደረግበት የመጀመሪያው ወሳኝ ግብዓት ነው።
በመካከለኛው ኢራን ያዝድ ከተማ አቅራቢያ የሚገኘውና "ቢጫው ኬክ" ተብሎ የሚጠራውን የዩራኒየም ዱቄት የሚያመርተው ፋብሪካ የአየር ጥቃት እንደተሰነዘረበት የኢራን መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
የአገሪቱ የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ጥቃቱ በፈቃድ በ"አሜሪካ-በእስራኤል " የተፈጸመ መሆኑን ገልጿል።
የፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው ከሆነ፣ ጥቃቱ በፈርዱ አካባቢ በሚገኘው የዩራኒየም ማቀነባበሪያ ላይ ያረፈ ቢሆንም፣ እስካሁን በደረሰው የመጀመሪያ ደረጃ ግምገማ ምንም ዓይነት የጨረር ስርጭት አለመከሰቱ ገልፇል።
በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ የሚደርስ የጤና ስጋት እንደሌለ ተገልጿል።
"ቢጫው ኬክ" ለኑክሌር ጦር መሣሪያ ዝግጅት ወይም ለሃይል ማመንጫነት የሚያገለግለው ዩራኒየም እንዲበለጽግ የሚደረግበት የመጀመሪያው ወሳኝ ግብዓት ነው።
2 months ago
አሜሪካ ለኢራን ባለ 15 ነጥብ የተኩስ አቁም የስምምነት ሃሳብ በፓኪስታን በኩል ማቅረቧ ተዘገበ።
አሜሪካ የተኩስ አቁም ሃሳቡን በፓኪስታን አምባሳደሮች በኩል ለኢራን ማቅረቧን የኢስላማባድ ባለስልጣናት ዛሬ አረጋግጠዋል። አሜሪካ የሰላም የስምምነት ሃሳብ ማቅረቧ የተሰማው ተጨማሪ የአየር ወለድ ወታደሮቿን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሃገራት እያሰማራች ባለችበት ወቅት ነው።
በፓኪስታን በኩል ለኢራን ቀረበ የተባለው የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ "የሰላም ዕቅድ" 15 ነጥቦች ያካተተ ሲሆን አብዛኞቹ ሐሳቦች ኢራንን የሚያስገድዱ ናቸው ተብሏል።
ከእነዚህ መካከል በኢራን የሚሳይል ፕሮግራም ላይ ገደብ መጣል እና በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል መርከቦች በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ መፍቀድ ፣ የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ፣ የኢራንን የኑክሌር መርሃ ግብር መቀነስ ፣ በሲቪል የኑክሌር መስክ ላይ መተባበር እና በኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ማንሳት እንደሚገኙበት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የፓኪስታን ባለስጣናት ተናግረዋል።
አሜሪካ የተኩስ አቁም ሃሳብ አቀረበች ይባል እንጂ ተጨማሪ ወታደሮችን ወደ ቀጣናው ከመላክ ግን አላቀባትም። አሜሪካ በትንሹ 1,000 የሚሆኑ የ82ኛው የአየር ወለድ ክፍለ ጦር አባላት ወደ ቀጠናው እንደሚላኩ ተገልጿል። ይህም ቀደም ብለው ከተሰማሩት 5,000 የባህር ኃይል ወታደሮች በተጨማሪ ነው።
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ "ትክክለኛ ሰዎች" ካሏቸው ጋር የኢራን ጦርነትን ለማብቃት እየተነጋገረች እንደምትገኝ በዋይት ሐውስ ለጋዜጠኞች ተናግረው ነበር። ፕሬዝደንቱ ኢራን ሥምምነት ላይ የመድረስ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።
አንድ የኢራን ወታደራዊ ቃል አቀባይ ግን ዩናይትድ ስቴትስ ከራሷ ጋር እየተደራደረች እንደሆነ በመግለጽ የተባለውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት አጣጥለዋል።
ኢራን በእስራኤል እና በሌሎች የባህረ ሰላጤው ሃገራት ላይ የምትፈጽማቸውን ጥቃቶች አጠናክራ መቀጠሏን አሶሽየትድ ፕረስ ዘግቧል። በዚህም በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በደረሰ ጥቃት ከፍተኛ እሳት መነሳቱና ከፍተኛ ጭስ ሲወጣ መታየቱ ተነግሯል።
የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት በሰሜን ምዕራብ ኢራን በሚገኘው ቃዝቪን ከተማ ላይ ሰፊ የአየር ድብደባ መጀመሩን አስታውቋል።
የኢራን ጤና ሚኒስቴር በአሜሪካ እና እስራኤል ጥምር ጥቃት የሟቾች ቁጥር ከ1,500 በላይ መድረሱን ገልጿል።
እስራኤል በተናጥል ባደረሰችው ጥቃት ሊባኖስ ውስጥ ከ1,000 በላይ ሰዎች ተገድለዋል።
ኢራን በበኩሏ ባደረሰችው የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃት እስራኤል ውስጥ 16 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል። በተጨማሪም 13 የአሜሪካ ወታደራዊ አባላት ሕይወታቸውን አጥተዋል።
በጦርነቱ ለጊዜው በቁጥር ያልተገለጸ በሺዎች በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
በጦርነቱ ምክንያት የጨመረው የነዳጅ ዋጋ አሁንም መቀነስ አላሳየም ። በአሁኑ ወቅት አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ በ100 ዶላር አካባቢ እየተሸጠ ይገኛል። ይህም ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት ከነበረው ዋጋ የ40 በመቶ ጭማሪ አለው።
DW Amharic
አሜሪካ የተኩስ አቁም ሃሳቡን በፓኪስታን አምባሳደሮች በኩል ለኢራን ማቅረቧን የኢስላማባድ ባለስልጣናት ዛሬ አረጋግጠዋል። አሜሪካ የሰላም የስምምነት ሃሳብ ማቅረቧ የተሰማው ተጨማሪ የአየር ወለድ ወታደሮቿን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሃገራት እያሰማራች ባለችበት ወቅት ነው።
በፓኪስታን በኩል ለኢራን ቀረበ የተባለው የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ "የሰላም ዕቅድ" 15 ነጥቦች ያካተተ ሲሆን አብዛኞቹ ሐሳቦች ኢራንን የሚያስገድዱ ናቸው ተብሏል።
ከእነዚህ መካከል በኢራን የሚሳይል ፕሮግራም ላይ ገደብ መጣል እና በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል መርከቦች በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ መፍቀድ ፣ የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ፣ የኢራንን የኑክሌር መርሃ ግብር መቀነስ ፣ በሲቪል የኑክሌር መስክ ላይ መተባበር እና በኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ማንሳት እንደሚገኙበት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የፓኪስታን ባለስጣናት ተናግረዋል።
አሜሪካ የተኩስ አቁም ሃሳብ አቀረበች ይባል እንጂ ተጨማሪ ወታደሮችን ወደ ቀጣናው ከመላክ ግን አላቀባትም። አሜሪካ በትንሹ 1,000 የሚሆኑ የ82ኛው የአየር ወለድ ክፍለ ጦር አባላት ወደ ቀጠናው እንደሚላኩ ተገልጿል። ይህም ቀደም ብለው ከተሰማሩት 5,000 የባህር ኃይል ወታደሮች በተጨማሪ ነው።
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ "ትክክለኛ ሰዎች" ካሏቸው ጋር የኢራን ጦርነትን ለማብቃት እየተነጋገረች እንደምትገኝ በዋይት ሐውስ ለጋዜጠኞች ተናግረው ነበር። ፕሬዝደንቱ ኢራን ሥምምነት ላይ የመድረስ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።
አንድ የኢራን ወታደራዊ ቃል አቀባይ ግን ዩናይትድ ስቴትስ ከራሷ ጋር እየተደራደረች እንደሆነ በመግለጽ የተባለውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት አጣጥለዋል።
ኢራን በእስራኤል እና በሌሎች የባህረ ሰላጤው ሃገራት ላይ የምትፈጽማቸውን ጥቃቶች አጠናክራ መቀጠሏን አሶሽየትድ ፕረስ ዘግቧል። በዚህም በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በደረሰ ጥቃት ከፍተኛ እሳት መነሳቱና ከፍተኛ ጭስ ሲወጣ መታየቱ ተነግሯል።
የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት በሰሜን ምዕራብ ኢራን በሚገኘው ቃዝቪን ከተማ ላይ ሰፊ የአየር ድብደባ መጀመሩን አስታውቋል።
የኢራን ጤና ሚኒስቴር በአሜሪካ እና እስራኤል ጥምር ጥቃት የሟቾች ቁጥር ከ1,500 በላይ መድረሱን ገልጿል።
እስራኤል በተናጥል ባደረሰችው ጥቃት ሊባኖስ ውስጥ ከ1,000 በላይ ሰዎች ተገድለዋል።
ኢራን በበኩሏ ባደረሰችው የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃት እስራኤል ውስጥ 16 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል። በተጨማሪም 13 የአሜሪካ ወታደራዊ አባላት ሕይወታቸውን አጥተዋል።
በጦርነቱ ለጊዜው በቁጥር ያልተገለጸ በሺዎች በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
በጦርነቱ ምክንያት የጨመረው የነዳጅ ዋጋ አሁንም መቀነስ አላሳየም ። በአሁኑ ወቅት አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ በ100 ዶላር አካባቢ እየተሸጠ ይገኛል። ይህም ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት ከነበረው ዋጋ የ40 በመቶ ጭማሪ አለው።
DW Amharic
2 months ago
በኩዌት የኑክሌር ስጋት ማስጠንቀቂያ ተሰጠ
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ቀውስ ተከትሎ፣ የኩዌት መንግስት ሊኖር ስለሚችል የኑክሌር ጨረር ስርጭት ለዜጎቹ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል።
ባለስልጣናቱ ህዝቡ ምንም አይነት ድንጋጤ ውስጥ ሳይገባ በቤቱ እንዲቆይ አሳስበዋል። በቤት ውስጥ በሚቆዩበት ወቅትም ማንኛውንም የውጭ አየር ወደ ውስጥ እንዳይገባ መስኮቶችንና በሮችን በጥንቃቄ እንዲዘጉ መመሪያ ተሰጥቷል።
ይህ እርምጃ የተወሰደው በጎረቤት ሀገር ኢራን የሚገኘው የቡሸር የኑክሌር ጣቢያ ጥቃት እንደደረሰበት የሚገልጹ ዘገባዎች ከወጡ በኋላ ለጥንቃቄ ሲባል እንደሆነ ታውቋል።
የኩዌት የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲሱን የብሔራዊ የአደጋ ጊዜ ማስጠንቀቂያ ስርዓት በመጠቀም መረጃው ለሁሉም ነዋሪዎች እንዲደርስ እያደረገ ይገኛል።
ምንጭ፦ የኩዌት ብሔራዊ የዜና አገልግሎት (KUNA)
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ቀውስ ተከትሎ፣ የኩዌት መንግስት ሊኖር ስለሚችል የኑክሌር ጨረር ስርጭት ለዜጎቹ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል።
ባለስልጣናቱ ህዝቡ ምንም አይነት ድንጋጤ ውስጥ ሳይገባ በቤቱ እንዲቆይ አሳስበዋል። በቤት ውስጥ በሚቆዩበት ወቅትም ማንኛውንም የውጭ አየር ወደ ውስጥ እንዳይገባ መስኮቶችንና በሮችን በጥንቃቄ እንዲዘጉ መመሪያ ተሰጥቷል።
ይህ እርምጃ የተወሰደው በጎረቤት ሀገር ኢራን የሚገኘው የቡሸር የኑክሌር ጣቢያ ጥቃት እንደደረሰበት የሚገልጹ ዘገባዎች ከወጡ በኋላ ለጥንቃቄ ሲባል እንደሆነ ታውቋል።
የኩዌት የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲሱን የብሔራዊ የአደጋ ጊዜ ማስጠንቀቂያ ስርዓት በመጠቀም መረጃው ለሁሉም ነዋሪዎች እንዲደርስ እያደረገ ይገኛል።
ምንጭ፦ የኩዌት ብሔራዊ የዜና አገልግሎት (KUNA)
2 months ago
ትራምፕ ከኢራን ጋር ድርድር መጀመራቸውንና "ውድ ስጦታ" ማግኘታቸውን ገለጹ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደራቸው ከኢራን ጋር ቀጥተኛ ድርድር መጀመሩን በኦቫል ኦፊስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንቱ ኢራን ጦርነቱን ለማቆም እና ስምምነት ላይ ለመድረስ ከፍተኛ ፍላጎት እያሳየች መሆኑን ገልጸው፣ ትላንትናም ከነዳጅ እና ጋዝ ጋር የተያያዘ "ታላቅ ስጦታ" ለአሜሪካ ልካለች ብለዋል።
ትራምፕ ቀደም ሲል በኢራን የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር አቅደው እንደነበር ቢናገሩም፣ ቴህራን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ የድርድር ጥያቄ ማቅረቧን ጠቁመዋል።
በድርድሩ ላይ ጃሬድ ኩሽነር፣ ስቲቭ ዊትኮፍ፣ ማርኮ ሩቢዮ እና ጄዲ ቫንስ እየተሳተፉ መሆኑንም ገልጸዋል።
ዋናው የድርድር ነጥብ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት ማድረግ ሲሆን፣ የሲቢኤስ ኒውስ መረጃ ደግሞ ኢራን በአማላጅ በኩል ከአሜሪካ መልእክት እንደደረሳት አረጋግጧል።
ምንም እንኳን የተወሰኑ የቅርብ አማካሪዎቻቸው (እንደ ፒት ሄግሴት ያሉ) በሁኔታው ቅር ቢሰኙም፣ ጉዳዩ በቅርቡ እልባት እንደሚያገኝ ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል፣ ሳዑዲ አረቢያ አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርገውን ጫና እንድትቀጥል ግፊት እያደረገች መሆኑ ተመልክቷል።
ምንጮች ፦ CBS News, AP
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደራቸው ከኢራን ጋር ቀጥተኛ ድርድር መጀመሩን በኦቫል ኦፊስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንቱ ኢራን ጦርነቱን ለማቆም እና ስምምነት ላይ ለመድረስ ከፍተኛ ፍላጎት እያሳየች መሆኑን ገልጸው፣ ትላንትናም ከነዳጅ እና ጋዝ ጋር የተያያዘ "ታላቅ ስጦታ" ለአሜሪካ ልካለች ብለዋል።
ትራምፕ ቀደም ሲል በኢራን የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር አቅደው እንደነበር ቢናገሩም፣ ቴህራን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ የድርድር ጥያቄ ማቅረቧን ጠቁመዋል።
በድርድሩ ላይ ጃሬድ ኩሽነር፣ ስቲቭ ዊትኮፍ፣ ማርኮ ሩቢዮ እና ጄዲ ቫንስ እየተሳተፉ መሆኑንም ገልጸዋል።
ዋናው የድርድር ነጥብ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት ማድረግ ሲሆን፣ የሲቢኤስ ኒውስ መረጃ ደግሞ ኢራን በአማላጅ በኩል ከአሜሪካ መልእክት እንደደረሳት አረጋግጧል።
ምንም እንኳን የተወሰኑ የቅርብ አማካሪዎቻቸው (እንደ ፒት ሄግሴት ያሉ) በሁኔታው ቅር ቢሰኙም፣ ጉዳዩ በቅርቡ እልባት እንደሚያገኝ ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል፣ ሳዑዲ አረቢያ አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርገውን ጫና እንድትቀጥል ግፊት እያደረገች መሆኑ ተመልክቷል።
ምንጮች ፦ CBS News, AP
2 months ago
ትራምፕ፡ "የደወሉት ኢራኖች ናቸው፤ እኔ አይደለሁም"
ዶናልድ ትራምፕ ከአሜሪካ ጋር እየተደረገ ስላለው ድርድር "የደወሉት ኢራኖች እንጂ እኔ አይደለሁም" ሲሉ ተናግረዋል።
ቴህራን ንግግር እያደረግን አይደለም በማለት ብታስተባብልም፣ ትራምፕ ግን ከኢራን "ከፍተኛ አመራሮች" ጋር እስከ እሁድ ምሽት ድርድር ሲካሄድ እንደነበር ገልጸዋል።
በዚህ ንግግር ውስጥ የ15 ነጥብ ስምምነት ላይ ለመድረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑንና ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ላለመያዝ መስማማቷን ጠቁመዋል።
ይሁን እንጂ ትራምፕ "ስምምነት ላይ ለመድረስ ዋስትና መስጠት አልችልም" ሲሉ ጥንቃቄ የታከለበት አስተያየት ሰጥተዋል።
በሌላ በኩል የኢራን ባለሥልጣናት የትራምፕ ንግግር "የገበያ ዋጋን ለመቆጣጠር የታለመ የሐሰት ዜና ነው" ሲሉ ነቅፈውታል።
ምንጭ: ፎክስ ኒውስ
ዶናልድ ትራምፕ ከአሜሪካ ጋር እየተደረገ ስላለው ድርድር "የደወሉት ኢራኖች እንጂ እኔ አይደለሁም" ሲሉ ተናግረዋል።
ቴህራን ንግግር እያደረግን አይደለም በማለት ብታስተባብልም፣ ትራምፕ ግን ከኢራን "ከፍተኛ አመራሮች" ጋር እስከ እሁድ ምሽት ድርድር ሲካሄድ እንደነበር ገልጸዋል።
በዚህ ንግግር ውስጥ የ15 ነጥብ ስምምነት ላይ ለመድረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑንና ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ላለመያዝ መስማማቷን ጠቁመዋል።
ይሁን እንጂ ትራምፕ "ስምምነት ላይ ለመድረስ ዋስትና መስጠት አልችልም" ሲሉ ጥንቃቄ የታከለበት አስተያየት ሰጥተዋል።
በሌላ በኩል የኢራን ባለሥልጣናት የትራምፕ ንግግር "የገበያ ዋጋን ለመቆጣጠር የታለመ የሐሰት ዜና ነው" ሲሉ ነቅፈውታል።
ምንጭ: ፎክስ ኒውስ
Sponsored by
Surafel
3 months ago
🔴 አሜሪካ የኢራንን ምሽጎች ሰባሪ ግዙፍ ቦምቦችን በብሪታንያ ማከማቸት ጀመረች
የመጨረሻው ምዕራፍ?
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ወታደራዊ ውጥረት ተከትሎ፣ ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን የሚገኙ ጥልቅ የከርሰ-ምድር ምሽጎችን እና የኑክሌር ተቋማትን የማውደም አቅም ያላቸውን "ባንከር በስተር" (Bunker Buster) ቦምቦችን በብሪታንያ የአየር ኃይል ጣቢያዎች ላይ እያከማቸች መሆኑ ተሰማ።
የዘመቻው እና የዝግጅቱ ዝርዝር ነጥቦች፦
* ስልታዊ ዝርጋታ፦ ታዋቂዎቹ B-1 እና B-52 የቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች በብሪታንያው አር.ኤ.ኤፍ ፌርፎርድ (RAF Fairford) የጦር ሰፈር በብዛት እየታዩ ሲሆን፣ እነዚህ አውሮፕላኖች እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የ "ጂ.ቢ.ዩ" (GBU) ዝርያ ያላቸውን ቦምቦች ታጥቀዋል።
* ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ (Operation Epic Fury)፦ ይህ ወታደራዊ ዝግጅት በኢራን ተራራማ ስፍራዎች እና ከመሬት በታች የተገነቡ የሚሳኤል ማከማቻዎችን ኢላማ ያደረገው ግዙፍ ዘመቻ አካል እንደሆነ ተገልጿል።
* የቀጣናው ውጥረት፦ የአሜሪካ ጥቃት የኢራኑን መንፈሳዊ መሪ አሊ ካሜኒን መግደሉን ተከትሎ፣ ኢራን በአካባቢው በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ የሚሳኤል አጸፋዊ እርምጃ እንደምትወስድ ዝታለች።
* የአጋሮች ሚና፦ የብሪታንያ መንግሥት ለአሜሪካ የአየር ኃይል ጣቢያዎቹን ለ "መከላከያ ዓላማ" እንዲውሉ የፈቀደ ቢሆንም፣ አሜሪካ ግን ከእነዚህ ጣቢያዎች በመነሳት ረጅም ርቀት በመብረር ጥቃቷን ለማጠናከር እየተዘጋጀች መሆኑ ታውቋል።
ይህ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግጭቱ ወደ ሰፊ ቀጠናዊ ጦርነት ሊያመራ ይችላል በሚል በከፍተኛ ስጋት እንዲጠባበቅ አድርጎታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #usa #iran #militaryaction #operationepicfury #raffairford #middleeasttension #b52 #breakingnews #globalconflict
የመጨረሻው ምዕራፍ?
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ወታደራዊ ውጥረት ተከትሎ፣ ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን የሚገኙ ጥልቅ የከርሰ-ምድር ምሽጎችን እና የኑክሌር ተቋማትን የማውደም አቅም ያላቸውን "ባንከር በስተር" (Bunker Buster) ቦምቦችን በብሪታንያ የአየር ኃይል ጣቢያዎች ላይ እያከማቸች መሆኑ ተሰማ።
የዘመቻው እና የዝግጅቱ ዝርዝር ነጥቦች፦
* ስልታዊ ዝርጋታ፦ ታዋቂዎቹ B-1 እና B-52 የቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች በብሪታንያው አር.ኤ.ኤፍ ፌርፎርድ (RAF Fairford) የጦር ሰፈር በብዛት እየታዩ ሲሆን፣ እነዚህ አውሮፕላኖች እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የ "ጂ.ቢ.ዩ" (GBU) ዝርያ ያላቸውን ቦምቦች ታጥቀዋል።
* ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ (Operation Epic Fury)፦ ይህ ወታደራዊ ዝግጅት በኢራን ተራራማ ስፍራዎች እና ከመሬት በታች የተገነቡ የሚሳኤል ማከማቻዎችን ኢላማ ያደረገው ግዙፍ ዘመቻ አካል እንደሆነ ተገልጿል።
* የቀጣናው ውጥረት፦ የአሜሪካ ጥቃት የኢራኑን መንፈሳዊ መሪ አሊ ካሜኒን መግደሉን ተከትሎ፣ ኢራን በአካባቢው በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ የሚሳኤል አጸፋዊ እርምጃ እንደምትወስድ ዝታለች።
* የአጋሮች ሚና፦ የብሪታንያ መንግሥት ለአሜሪካ የአየር ኃይል ጣቢያዎቹን ለ "መከላከያ ዓላማ" እንዲውሉ የፈቀደ ቢሆንም፣ አሜሪካ ግን ከእነዚህ ጣቢያዎች በመነሳት ረጅም ርቀት በመብረር ጥቃቷን ለማጠናከር እየተዘጋጀች መሆኑ ታውቋል።
ይህ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግጭቱ ወደ ሰፊ ቀጠናዊ ጦርነት ሊያመራ ይችላል በሚል በከፍተኛ ስጋት እንዲጠባበቅ አድርጎታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #usa #iran #militaryaction #operationepicfury #raffairford #middleeasttension #b52 #breakingnews #globalconflict