Logo
SeledaPost
"ተመልሰን ቦምብ ልናዘንብ እንችላለን" - የትራምፕ ዛቻ

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በስምምነቱ መሰረት ካልተጓዘች አዲስ ጥቃት አመራለሁ ሲሉ ዛቱ፡፡

በቡድን ሰባት ጉባዔ ፈረንሳይ የሚገኙት ትራምፕ ከኢራን ጋር የተደረሰው ስምምነት “ገና እንዳልተገባደደ” ጠቅሰው በመግባቢያ ሰነዱ አተገባበር ደስተኛ ካልሆኑ ቴህራን ላይ ጥቃት መፈጸም እንደሚቀጥሉ አስጠንቅቀዋል፡፡

ኢራን ከእስራኤልና አሜሪካ ጋር ስምምነት ላይ ከደረሰች በኋላ በሰጡት የመጀመሪያ አስተያየት "ጥቃቱ በዚሁ ከቀጠለ ጠንካራ ምላሽ የምንሰጥ ይሆናል" ሲሉ ትራምፕ ተደምጠዋል።

ፕሬዝዳንቱ "ተመልሰን ቦምብ ልናዘንብ እንችላለን" ሲሉም ዝተዋል።

"የመግባቢያ ስምምነቱ አልተጠናቀቀም" ያሉት ትራምፕ "ካልወደድኩት ወታደራዊ እርምጃ እንወስዳለን" ሲሉም የመፍረስ አደጋ እንዳለው ጠቁመዋል።

"ስምምነቱ በብዙ ምክንያት አስፈላጊ ነው" ካሉ በኋላ "99.9% የተስማማንበት ኢራን የኑክሌር መሳሪያ እንደማይኖራት ነው" ብለዋል።

ኢራን ለመልሶ ግንባታ የሚሆን 300 ዶላር ካሳ ይከፈላታል መባሉን "ውሸት ነው፣ ሳንቲም አናወጣም" ሲሉ አስተባብለዋል።   #thetimesofisrael

Seledadotio
Seledadotio
1 day ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.