1 day ago
የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን ዓለም አቀፍ የቱሪዝም መዳረሻነት ለማስቀጠል…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን ብዝኃ ሕይወት በመጠበቅ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም መዳረሻነቱን ለማስቀጠል እየተሰራ ነው፡፡
በፓርኩ ባለፉት 10 ዓመታት የአፍሪካ ዋይልድ ላይፍ ፋውንዴሽን ያከናወናቸው የጥበቃና ልማት ስራዎችን በተመለከተ በጎንደር ከተማ ውይይት ተካሂዷል።
የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን ለመጠበቅ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት የፓርኩን ሕልውና ለማስጠበቅ ከመንግስትና ከማህበረሰቡ ጋር በቅንጅት በተሰራው ስራ ፓርኩን ከአደጋ ስጋት ማላቀቅ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
እንደ ሀገር ብሔራዊ ፓርኮችን በመጠበቅ የቱሪዝም ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፥ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን ጠብቆ በማቆየት ጠቀሜታውን ማሳደግ ይገባል ብለዋል።
የፓርኩን ብዝኃ ህይወት በመጠበቅ ዓለም ዓቀፍ የቱሪዝም መዳረሻነቱን ለማስቀጠል እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡
የአፍሪካ ዋይልድ ላይፍ ፋውንዴሽን ፓርኩ እንዲጠበቅና እንዲለማ በማድረግና በዙሪያው ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን በማሟላት በፓርኩ ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መቀነስ መቻሉ ተጠቁሟል፡፡
በሙሉጌታ ደሴ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን ብዝኃ ሕይወት በመጠበቅ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም መዳረሻነቱን ለማስቀጠል እየተሰራ ነው፡፡
በፓርኩ ባለፉት 10 ዓመታት የአፍሪካ ዋይልድ ላይፍ ፋውንዴሽን ያከናወናቸው የጥበቃና ልማት ስራዎችን በተመለከተ በጎንደር ከተማ ውይይት ተካሂዷል።
የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን ለመጠበቅ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት የፓርኩን ሕልውና ለማስጠበቅ ከመንግስትና ከማህበረሰቡ ጋር በቅንጅት በተሰራው ስራ ፓርኩን ከአደጋ ስጋት ማላቀቅ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
እንደ ሀገር ብሔራዊ ፓርኮችን በመጠበቅ የቱሪዝም ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፥ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን ጠብቆ በማቆየት ጠቀሜታውን ማሳደግ ይገባል ብለዋል።
የፓርኩን ብዝኃ ህይወት በመጠበቅ ዓለም ዓቀፍ የቱሪዝም መዳረሻነቱን ለማስቀጠል እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡
የአፍሪካ ዋይልድ ላይፍ ፋውንዴሽን ፓርኩ እንዲጠበቅና እንዲለማ በማድረግና በዙሪያው ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን በማሟላት በፓርኩ ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መቀነስ መቻሉ ተጠቁሟል፡፡
በሙሉጌታ ደሴ
5 days ago
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት የ24 ምርጫ ክልል ውጤቶችን ይፋ አድርጓል።
#fastmereja I ዛሬ ይፋ በተደረጉት ውጤቶች ብልጽግና ፓርቲ በኦሮሚያ ክልል እና በጋምቤላ ክልል፥ ለህዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው ሁሉም እጩዎች ወንበሩን አግኝተዋል።
በአማራ ክልል በጎንደር ዙሪያ 4 ምርጫ ክልል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ እጩ የሆኑት አቶ ጣሂር ሙሐመድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፓርቲያቸውን ወክለው ወንበር ሲያገኙ፤ በቀሪዎቹ ለህዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤት ብልጽግና ፓርቲ ያቀረባቸው እጩዎች ወንበሩን አግኝተዋል።
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ወክለው ለክልል ምክር ቤት የተወዳደሩት ሀሲል አርባብ ሀሚስ አንድ መቀመጫ ሲያገኙ፥ ብልጽግና ፓርቲ በምርጫ ክልሉ ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው 8 እጩዎች መቀመጫ አግኝተዋል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ዛሬ ውጤታቸው ይፋ የተደረጉ የምርጫ ክልሎች አንድ ፓርቲ ብቻ የተወዳደረባቸው እና በድምጽ ቆጠራው አሸናፊ በሆኑትና ከታች ባሉት መካከል ያለው የድምጽ ልዩነት "በሺዎች" ልዩነት ያላቸው መሆኑን አስረድተዋል።
በሌላ በኩል ሰብሳቢዋ ምርጫ ከተካሄደባቸው 1,138 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 816 የሚሆኑት የማዳመር ሥራቸውን አጠናቀው ወደ ማዕከል ውጤታቸውን መላካቸውን አስታውቀዋል።
ቦርዱ ይፋ የተደረጉ ውጤቶችን በዌብሳይቱ ላይ እንደሚለጥፍ ገልጿል።
ማስታወሻ ፦ ከላይ የቀረቡት ውጤቶች ቦርዱ በዛሬው ዕለት ይፋ ያደረጋቸውን ብቻ የሚመለከት ነው።
ዘገባው የቲክቫህ ኢትዮጵያ
#fastmereja I ዛሬ ይፋ በተደረጉት ውጤቶች ብልጽግና ፓርቲ በኦሮሚያ ክልል እና በጋምቤላ ክልል፥ ለህዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው ሁሉም እጩዎች ወንበሩን አግኝተዋል።
በአማራ ክልል በጎንደር ዙሪያ 4 ምርጫ ክልል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ እጩ የሆኑት አቶ ጣሂር ሙሐመድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፓርቲያቸውን ወክለው ወንበር ሲያገኙ፤ በቀሪዎቹ ለህዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤት ብልጽግና ፓርቲ ያቀረባቸው እጩዎች ወንበሩን አግኝተዋል።
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ወክለው ለክልል ምክር ቤት የተወዳደሩት ሀሲል አርባብ ሀሚስ አንድ መቀመጫ ሲያገኙ፥ ብልጽግና ፓርቲ በምርጫ ክልሉ ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው 8 እጩዎች መቀመጫ አግኝተዋል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ዛሬ ውጤታቸው ይፋ የተደረጉ የምርጫ ክልሎች አንድ ፓርቲ ብቻ የተወዳደረባቸው እና በድምጽ ቆጠራው አሸናፊ በሆኑትና ከታች ባሉት መካከል ያለው የድምጽ ልዩነት "በሺዎች" ልዩነት ያላቸው መሆኑን አስረድተዋል።
በሌላ በኩል ሰብሳቢዋ ምርጫ ከተካሄደባቸው 1,138 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 816 የሚሆኑት የማዳመር ሥራቸውን አጠናቀው ወደ ማዕከል ውጤታቸውን መላካቸውን አስታውቀዋል።
ቦርዱ ይፋ የተደረጉ ውጤቶችን በዌብሳይቱ ላይ እንደሚለጥፍ ገልጿል።
ማስታወሻ ፦ ከላይ የቀረቡት ውጤቶች ቦርዱ በዛሬው ዕለት ይፋ ያደረጋቸውን ብቻ የሚመለከት ነው።
ዘገባው የቲክቫህ ኢትዮጵያ
5 days ago
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት የ24 ምርጫ ክልል ውጤቶችን ይፋ አድርጓል
#ethiopia | ዛሬ ይፋ በተደረጉት ውጤቶች ብልጽግና ፓርቲ በኦሮሚያ ክልል እና በጋምቤላ ክልል፥ ለህዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው ሁሉም እጩዎች ወንበሩን አግኝተዋል።
በአማራ ክልል በጎንደር ዙሪያ 4 ምርጫ ክልል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ እጩ የሆኑት አቶ ጣሂር ሙሐመድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፓርቲያቸውን ወክለው ወንበር ሲያገኙ፤ በቀሪዎቹ ለህዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤት ብልጽግና ፓርቲ ያቀረባቸው እጩዎች ወንበሩን አግኝተዋል።
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ወክለው ለክልል ምክር ቤት የተወዳደሩት ሀሲል አርባብ ሀሚስ አንድ መቀመጫ ሲያገኙ፥ ብልጽግና ፓርቲ በምርጫ ክልሉ ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው 8 እጩዎች መቀመጫ አግኝተዋል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ዛሬ ውጤታቸው ይፋ የተደረጉ የምርጫ ክልሎች አንድ ፓርቲ ብቻ የተወዳደረባቸው እና በድምጽ ቆጠራው አሸናፊ በሆኑትና ከታች ባሉት መካከል ያለው የድምጽ ልዩነት "በሺዎች" ልዩነት ያላቸው መሆኑን አስረድተዋል።
በሌላ በኩል ሰብሳቢዋ ምርጫ ከተካሄደባቸው 1,138 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 816 የሚሆኑት የማዳመር ሥራቸውን አጠናቀው ወደ ማዕከል ውጤታቸውን መላካቸውን አስታውቀዋል ያለው ቲክቫህ ነው።
ቦርዱ ይፋ የተደረጉ ውጤቶችን በዌብሳይቱ ላይ እንደሚለጥፍ ገልጿል።
#ማስታወሻ ፦ ከላይ የቀረቡት ውጤቶች ቦርዱ በዛሬው ዕለት ይፋ ያደረጋቸውን ብቻ የሚመለከት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ዛሬ ይፋ በተደረጉት ውጤቶች ብልጽግና ፓርቲ በኦሮሚያ ክልል እና በጋምቤላ ክልል፥ ለህዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው ሁሉም እጩዎች ወንበሩን አግኝተዋል።
በአማራ ክልል በጎንደር ዙሪያ 4 ምርጫ ክልል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ እጩ የሆኑት አቶ ጣሂር ሙሐመድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፓርቲያቸውን ወክለው ወንበር ሲያገኙ፤ በቀሪዎቹ ለህዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤት ብልጽግና ፓርቲ ያቀረባቸው እጩዎች ወንበሩን አግኝተዋል።
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ወክለው ለክልል ምክር ቤት የተወዳደሩት ሀሲል አርባብ ሀሚስ አንድ መቀመጫ ሲያገኙ፥ ብልጽግና ፓርቲ በምርጫ ክልሉ ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው 8 እጩዎች መቀመጫ አግኝተዋል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ዛሬ ውጤታቸው ይፋ የተደረጉ የምርጫ ክልሎች አንድ ፓርቲ ብቻ የተወዳደረባቸው እና በድምጽ ቆጠራው አሸናፊ በሆኑትና ከታች ባሉት መካከል ያለው የድምጽ ልዩነት "በሺዎች" ልዩነት ያላቸው መሆኑን አስረድተዋል።
በሌላ በኩል ሰብሳቢዋ ምርጫ ከተካሄደባቸው 1,138 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 816 የሚሆኑት የማዳመር ሥራቸውን አጠናቀው ወደ ማዕከል ውጤታቸውን መላካቸውን አስታውቀዋል ያለው ቲክቫህ ነው።
ቦርዱ ይፋ የተደረጉ ውጤቶችን በዌብሳይቱ ላይ እንደሚለጥፍ ገልጿል።
#ማስታወሻ ፦ ከላይ የቀረቡት ውጤቶች ቦርዱ በዛሬው ዕለት ይፋ ያደረጋቸውን ብቻ የሚመለከት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
9 days ago
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና በአርሲ ዞን በተፈጸሙ ጥቃቶች የሰው ህይወት ጠፋ
በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ምርጫውን ለማደናቀፍና በህዝቡ ላይ ሽብር ለመፍጠር የታለሙ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ።
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች የስፖርት ውድድር (Champions League) በመመልከት ላይ እያሉ በተሰነዘረ ጥቃት አንድ ተማሪ ሲሞት 26 የሚሆኑት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ "ሸኔ" ተብሎ በሚጠራው ቡድን በተሰነዘረ ጥቃት አምስት የሚሊሻ አባላት፣ ሶስት የፖሊስ አባላት እና አራት ሲቪሎች መገደላቸውን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በጥቃቱ አንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፣ የመንግስት ጤና ጣቢያ እና የቀበሌ ጽህፈት ቤት መቃጠላቸው እንዲሁም 65 የግለሰብ ቤቶች መውደማቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም በሸርካ እና በእንቆሌ ዋቤ ወረዳዎች ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውና ታግተው የነበሩ ግለሰቦች ህይወት ማለፉ በመግለጫው ተጠቅሷል።
Seledadotio
Seledadotio
በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ምርጫውን ለማደናቀፍና በህዝቡ ላይ ሽብር ለመፍጠር የታለሙ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ።
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች የስፖርት ውድድር (Champions League) በመመልከት ላይ እያሉ በተሰነዘረ ጥቃት አንድ ተማሪ ሲሞት 26 የሚሆኑት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ "ሸኔ" ተብሎ በሚጠራው ቡድን በተሰነዘረ ጥቃት አምስት የሚሊሻ አባላት፣ ሶስት የፖሊስ አባላት እና አራት ሲቪሎች መገደላቸውን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በጥቃቱ አንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፣ የመንግስት ጤና ጣቢያ እና የቀበሌ ጽህፈት ቤት መቃጠላቸው እንዲሁም 65 የግለሰብ ቤቶች መውደማቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም በሸርካ እና በእንቆሌ ዋቤ ወረዳዎች ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውና ታግተው የነበሩ ግለሰቦች ህይወት ማለፉ በመግለጫው ተጠቅሷል።
Seledadotio
Seledadotio
13 days ago
በጎንደር የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤት መለጠፍ ተጀምሯል በጎንደር ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራ ተጠናቅቆ ጊዜያዊ ውጤት መለጠፍ ተጀምሯል፡፡ በትናንትናው ዕለት በተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በጎንደር ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጽ መስጠቱ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት በከተማዋ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደት የተጠናቀቀ ሲሆን፥ ጊዜያዊ ውጤቶችም…
13 days ago
በጎንደር የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤት መለጠፍ ተጀምሯል
በጎንደር ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራ ተጠናቅቆ ጊዜያዊ ውጤት መለጠፍ ተጀምሯል፡፡
በትናንትናው ዕለት በተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በጎንደር ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጽ መስጠቱ ይታወቃል፡፡
በዚህም መሰረት በከተማዋ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደት የተጠናቀቀ ሲሆን፥ ጊዜያዊ ውጤቶችም በምርጫ ጣቢያዎቹ እየተለጠፉ ይገኛሉ፡፡
በግዛቸው ግርማዬ
Seledadotio
Seledadotio
በጎንደር ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራ ተጠናቅቆ ጊዜያዊ ውጤት መለጠፍ ተጀምሯል፡፡
በትናንትናው ዕለት በተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በጎንደር ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጽ መስጠቱ ይታወቃል፡፡
በዚህም መሰረት በከተማዋ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደት የተጠናቀቀ ሲሆን፥ ጊዜያዊ ውጤቶችም በምርጫ ጣቢያዎቹ እየተለጠፉ ይገኛሉ፡፡
በግዛቸው ግርማዬ
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
13 days ago
ከዛሬው ምርጫ ጋር ተያይዘው አጃኢብ የሚያስብሉ መረጃዎች፡-
- በሰርጋቸው ዕለት ድምጽ የሰጡ ሙሽሮች
- “በምርጫ ሀገርን ለትውልድ እያስተላለፍኩ ነው” የ90 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ እማሆይ አዳነች
- “ለልጆቻችን የነገ ተስፋና እጣ ፋንታ ስንል መርጠናል” ያምራል ቅኔው የሚመስል መረጃ
- የምመርጠው ጠባቂ እንዲኖረኝ ነው - በደብረ ብርሃን ከተማ ድምፃቸውን የሰጡት የ95 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ
- እድሜ ያልበገራቸው የጎሬ ከተማ ነዋሪ የ85 ዓመት መራጭ
- በጎንደር መንታ ሕጻናት ልጆችን ታቅፈው ድምጽ የሰጡ እናቶች
- አርቲስቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጻቸውን ሰጥተዋል
- በአፋር ክልል የሁለት እጅ አካል ጉዳት ያለበት ዜጋ ድምጽ ሲሰጥ
- የቀረበውን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ድምፅ የሰጡት የቀድሞ ታጣቂዎች
Seledadotio
Seledadotio
- በሰርጋቸው ዕለት ድምጽ የሰጡ ሙሽሮች
- “በምርጫ ሀገርን ለትውልድ እያስተላለፍኩ ነው” የ90 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ እማሆይ አዳነች
- “ለልጆቻችን የነገ ተስፋና እጣ ፋንታ ስንል መርጠናል” ያምራል ቅኔው የሚመስል መረጃ
- የምመርጠው ጠባቂ እንዲኖረኝ ነው - በደብረ ብርሃን ከተማ ድምፃቸውን የሰጡት የ95 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ
- እድሜ ያልበገራቸው የጎሬ ከተማ ነዋሪ የ85 ዓመት መራጭ
- በጎንደር መንታ ሕጻናት ልጆችን ታቅፈው ድምጽ የሰጡ እናቶች
- አርቲስቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጻቸውን ሰጥተዋል
- በአፋር ክልል የሁለት እጅ አካል ጉዳት ያለበት ዜጋ ድምጽ ሲሰጥ
- የቀረበውን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ድምፅ የሰጡት የቀድሞ ታጣቂዎች
Seledadotio
Seledadotio
18 days ago
ጤና ሚኒስቴር ከጣሊያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ሐኪሞች ላከናወኑት የሕፃናት ነጻ የልብ ቀዶ ሕክምና ምስጋናና ዕውቅና ሰጠ
የጤና ሚኒስቴር በኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ አማካይነት ከጣልያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎች፣ ከኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት 80 የልብ ሕሙማን ሕፃናት በሁለት ጊዜ ምልልስ
በ15 ቀናት ጊዜያት ውስጥ የነጻ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት
በመስጠታቸው የምስጋናና የእውቅና ሠርተፊኬት ሰጠ።
ትላንት ግንቦት 18/2018 ዓ.ም በአራዳ ፓርክ በተከናወነው መርሐግብር ባለሙያዎቹ አገልግሎቱን የሰጡት በሁለት ዙር ተልእኮ መኾኑ የተጠቀሰ ሲሆን 48 ሕፃናት በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል፣ 9 ሕፃናት በጂግጂጋ እንዲሁም 23 ሕፃናት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (በጎንደር ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ) የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መኾናቸው ተነግሯል።
በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ለተሰጠው አገልግሎት በጤና ሚኒስቴር፣ በራሳቸው ስምና ከሁሉም በላይ በዚህ ሕክምና ተጠቃሚ በሆነው ማህበረሰብ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ይህ መልካም ተግባር ቀጣይነት እንዲኖረው የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል። በቀጣይም ለሚከናወኑ መሰል ተግባራት ጤና ሚኒስቴርም አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ለዚህ ዓላማ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለኸርት ቱ ኸርት ችልድረን ኤይድ በገንዘብ እና በቴክኒክ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ይህ የበጎ ፈቃድ አገልግከሎት በ45 ቀናት ለ175 ሕፃናት የልብ ቀዶ ሕክምና ለመስጠት በጤና ሚኒስቴር፣ በኸርት ቱ ኸርት ችልድረንስ ኤይድ እና በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት መካከል የተደረገ ስምምነት አካል ነው።
አቶ ብርሃን ተድላ የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር የተከናወነውን የበጎ ተግባር ትልቅ ዋጋ መስጠቱ ሌሎችም ተመሳሳይ ተልእኮዎች በአርአያነት የሚታይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ኽርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በገባው ቃል መሰረት ስራዎቹ በአጭር ጊዜያት እንደሚያጠናቅቅም አቶ ብርሃን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ለስራው የስምምነቱ አካል የኾኑ የመንግስት፣ የግል ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት ያበረከቱት አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ መኾኑን በማስታወስ የስራው አጠቃላይ ሪፖርት እኤአ ጁን 10 ከተጠናቀቀ በኋላ ሌላ የምስጋና መርሐግብር እንደሚኖር ዶ/ር አስቻለው ወርቁ የጤና ሚኒስቴር አማካሪ አረጋግጠዋል።
የጤና ሚኒስቴር በኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ አማካይነት ከጣልያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎች፣ ከኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት 80 የልብ ሕሙማን ሕፃናት በሁለት ጊዜ ምልልስ
በ15 ቀናት ጊዜያት ውስጥ የነጻ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት
በመስጠታቸው የምስጋናና የእውቅና ሠርተፊኬት ሰጠ።
ትላንት ግንቦት 18/2018 ዓ.ም በአራዳ ፓርክ በተከናወነው መርሐግብር ባለሙያዎቹ አገልግሎቱን የሰጡት በሁለት ዙር ተልእኮ መኾኑ የተጠቀሰ ሲሆን 48 ሕፃናት በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል፣ 9 ሕፃናት በጂግጂጋ እንዲሁም 23 ሕፃናት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (በጎንደር ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ) የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መኾናቸው ተነግሯል።
በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ለተሰጠው አገልግሎት በጤና ሚኒስቴር፣ በራሳቸው ስምና ከሁሉም በላይ በዚህ ሕክምና ተጠቃሚ በሆነው ማህበረሰብ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ይህ መልካም ተግባር ቀጣይነት እንዲኖረው የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል። በቀጣይም ለሚከናወኑ መሰል ተግባራት ጤና ሚኒስቴርም አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ለዚህ ዓላማ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለኸርት ቱ ኸርት ችልድረን ኤይድ በገንዘብ እና በቴክኒክ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ይህ የበጎ ፈቃድ አገልግከሎት በ45 ቀናት ለ175 ሕፃናት የልብ ቀዶ ሕክምና ለመስጠት በጤና ሚኒስቴር፣ በኸርት ቱ ኸርት ችልድረንስ ኤይድ እና በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት መካከል የተደረገ ስምምነት አካል ነው።
አቶ ብርሃን ተድላ የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር የተከናወነውን የበጎ ተግባር ትልቅ ዋጋ መስጠቱ ሌሎችም ተመሳሳይ ተልእኮዎች በአርአያነት የሚታይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ኽርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በገባው ቃል መሰረት ስራዎቹ በአጭር ጊዜያት እንደሚያጠናቅቅም አቶ ብርሃን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ለስራው የስምምነቱ አካል የኾኑ የመንግስት፣ የግል ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት ያበረከቱት አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ መኾኑን በማስታወስ የስራው አጠቃላይ ሪፖርት እኤአ ጁን 10 ከተጠናቀቀ በኋላ ሌላ የምስጋና መርሐግብር እንደሚኖር ዶ/ር አስቻለው ወርቁ የጤና ሚኒስቴር አማካሪ አረጋግጠዋል።
18 days ago
ጤና ሚኒስቴር ከጣሊያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ሐኪሞች ላከናወኑት የሕፃናት ነጻ የልብ ቀዶ ሕክምና ምስጋናና ዕውቅና ሰጠ
#ethiopia | የጤና ሚኒስቴር በኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ አማካይነት ከጣልያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎች፣ ከኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት 80 የልብ ሕሙማን ሕፃናት በሁለት ጊዜ ምልልስ በ15 ቀናት ጊዜያት ውስጥ የነጻ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት በመስጠታቸው የምስጋናና የእውቅና ሠርተፊኬት ሰጠ።
ትላንት ግንቦት 18/2018 ዓ.ም በአራዳ ፓርክ በተከናወነው መርሐግብር ባለሙያዎቹ አገልግሎቱን የሰጡት በሁለት ዙር ተልእኮ መኾኑ የተጠቀሰ ሲሆን 48 ሕፃናት በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል፣ 9 ሕፃናት በጂግጂጋ እንዲሁም 23 ሕፃናት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (በጎንደር ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ) የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መኾናቸው ተነግሯል።
በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ለተሰጠው አገልግሎት በጤና ሚኒስቴር፣ በራሳቸው ስምና ከሁሉም በላይ በዚህ ሕክምና ተጠቃሚ በሆነው ማህበረሰብ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ይህ መልካም ተግባር ቀጣይነት እንዲኖረው የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል። በቀጣይም ለሚከናወኑ መሰል ተግባራት ጤና ሚኒስቴርም አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ለዚህ ዓላማ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለኸርት ቱ ኸርት ችልድረን ኤይድ በገንዘብ እና በቴክኒክ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ይህ የበጎ ፈቃድ አገልግከሎት በ45 ቀናት ለ175 ሕፃናት የልብ ቀዶ ሕክምና ለመስጠት በጤና ሚኒስቴር፣ በኸርት ቱ ኸርት ችልድረንስ ኤይድ እና በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት መካከል የተደረገ ስምምነት አካል ነው።
አቶ ብርሃን ተድላ የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር የተከናወነውን የበጎ ተግባር ትልቅ ዋጋ መስጠቱ ሌሎችም ተመሳሳይ ተልእኮዎች በአርአያነት የሚታይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ኽርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በገባው ቃል መሰረት ስራዎቹ በአጭር ጊዜያት እንደሚያጠናቅቅም አቶ ብርሃን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ለስራው የስምምነቱ አካል የኾኑ የመንግስት፣ የግል ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት ያበረከቱት አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ መኾኑን በማስታወስ የስራው አጠቃላይ ሪፖርት እኤአ ጁን 10 ከተጠናቀቀ በኋላ ሌላ የምስጋና መርሐግብር እንደሚኖር ዶ/ር አስቻለው ወርቁ የጤና ሚኒስቴር አማካሪ አረጋግጠዋል።
#ethiopia | የጤና ሚኒስቴር በኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ አማካይነት ከጣልያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎች፣ ከኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት 80 የልብ ሕሙማን ሕፃናት በሁለት ጊዜ ምልልስ በ15 ቀናት ጊዜያት ውስጥ የነጻ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት በመስጠታቸው የምስጋናና የእውቅና ሠርተፊኬት ሰጠ።
ትላንት ግንቦት 18/2018 ዓ.ም በአራዳ ፓርክ በተከናወነው መርሐግብር ባለሙያዎቹ አገልግሎቱን የሰጡት በሁለት ዙር ተልእኮ መኾኑ የተጠቀሰ ሲሆን 48 ሕፃናት በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል፣ 9 ሕፃናት በጂግጂጋ እንዲሁም 23 ሕፃናት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (በጎንደር ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ) የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መኾናቸው ተነግሯል።
በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ለተሰጠው አገልግሎት በጤና ሚኒስቴር፣ በራሳቸው ስምና ከሁሉም በላይ በዚህ ሕክምና ተጠቃሚ በሆነው ማህበረሰብ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ይህ መልካም ተግባር ቀጣይነት እንዲኖረው የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል። በቀጣይም ለሚከናወኑ መሰል ተግባራት ጤና ሚኒስቴርም አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ለዚህ ዓላማ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለኸርት ቱ ኸርት ችልድረን ኤይድ በገንዘብ እና በቴክኒክ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ይህ የበጎ ፈቃድ አገልግከሎት በ45 ቀናት ለ175 ሕፃናት የልብ ቀዶ ሕክምና ለመስጠት በጤና ሚኒስቴር፣ በኸርት ቱ ኸርት ችልድረንስ ኤይድ እና በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት መካከል የተደረገ ስምምነት አካል ነው።
አቶ ብርሃን ተድላ የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር የተከናወነውን የበጎ ተግባር ትልቅ ዋጋ መስጠቱ ሌሎችም ተመሳሳይ ተልእኮዎች በአርአያነት የሚታይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ኽርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በገባው ቃል መሰረት ስራዎቹ በአጭር ጊዜያት እንደሚያጠናቅቅም አቶ ብርሃን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ለስራው የስምምነቱ አካል የኾኑ የመንግስት፣ የግል ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት ያበረከቱት አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ መኾኑን በማስታወስ የስራው አጠቃላይ ሪፖርት እኤአ ጁን 10 ከተጠናቀቀ በኋላ ሌላ የምስጋና መርሐግብር እንደሚኖር ዶ/ር አስቻለው ወርቁ የጤና ሚኒስቴር አማካሪ አረጋግጠዋል።
21 days ago
በጎንደር ከተማ በ115 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባ የማገገሚያ ማዕከል ተመረቀ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ በ115 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባ በተለያዩ ምክንያቶች ጥቃት የሚደርስባቸው ሴቶች የሥነ ልቦና እንክብካቤ አገልግሎት የሚያገኙበት የማገገሚያ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እና ሌሎች የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው ማዕከሉ የተመረቀው።
የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ብርቱካን ሲሳይ እንዳሉት÷ ማገገሚያ ማዕከሉ በአንድ ጊዜ ከ25 እስከ 50 ሰዎችን ተቀብሎ የማስተናገድ አቅም አለው።
ከጎንደር ከተማ በተጨማሪ ሌሎች የጎንደር አካባቢ ዞኖች በማዕከሉ ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ጠቁመዋል።
የማገገሚያ ማዕከሉ በአማራ ክልል ሴቶች ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ እና በክልሉ በጦርነት የተጎዱ አካባቢዎች መልሶ ማቋቋም ፈንድ ጽህፈት ቤት ትብብር የተገነባ መሆኑ ተገልጿል።
በምናለ አየነው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ በ115 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባ በተለያዩ ምክንያቶች ጥቃት የሚደርስባቸው ሴቶች የሥነ ልቦና እንክብካቤ አገልግሎት የሚያገኙበት የማገገሚያ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እና ሌሎች የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው ማዕከሉ የተመረቀው።
የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ብርቱካን ሲሳይ እንዳሉት÷ ማገገሚያ ማዕከሉ በአንድ ጊዜ ከ25 እስከ 50 ሰዎችን ተቀብሎ የማስተናገድ አቅም አለው።
ከጎንደር ከተማ በተጨማሪ ሌሎች የጎንደር አካባቢ ዞኖች በማዕከሉ ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ጠቁመዋል።
የማገገሚያ ማዕከሉ በአማራ ክልል ሴቶች ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ እና በክልሉ በጦርነት የተጎዱ አካባቢዎች መልሶ ማቋቋም ፈንድ ጽህፈት ቤት ትብብር የተገነባ መሆኑ ተገልጿል።
በምናለ አየነው
24 days ago
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ ተጀመረ
#ethiopia | በከባድ የልብ ሕመም ለሚሰቃዩ ሕፃናት ተስፋና ፈውስን ይዞ የመጣውና ለሦስት ቀናት የሚቆየው የነፃ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዛሬ በይፋ መካሄድ ጀምሯል።
ለዚህ ታላቅ ሰብአዊ ተልዕኮ ወደ ስፍራው ለገሰገሰው ዓለም አቀፍ የሕክምና ቡድን ዛሬ ጠዋት ደማቅ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት የተደረገለት ሲሆን፣ ቡድኑም የሕይወት አድን ሥራውን ወዲያውኑ አግልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ይህ አገር አቀፍ ጠቀሜታ ያለው ተነሳሽነት ሊሳካ የቻለው በHeart to Heart Children’s Aid፣ በኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል፣ በፓድሬ ፒዮ ኢጣሊያ፣ በኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር እና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ መካከል በተደረገ ጠንካራ ትብብር ሲሆን፣ ይህም በኢትዮጵያ ለሚገኙ የልብ ህመም ተጋላጭ ለሆኑ ሕፃናት ልዩ የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የታሰበ መሆኑ ተገልጿል።
በዛሬው ዕለት ሥራቸውን በይፋ የጀመሩት ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ዓለም አቀፍ የልብ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስቶችና የሕክምና ባለሙያዎች፣ የላቀ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምናና ልዩ የልብ ሕክምና አገልግሎቶችን ለሕጻናቱ ሙሉ በሙሉ መሆኑን ጎንደር ዩኒቨርስቲ ገልጿል።
በዚህ ወሳኝ የሕክምና ዘመቻ ወደ 20 የሚጠጉ ሕፃናት ቀጥተኛ የጤና ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ዘመቻ በአሁኑ ወቅት ሕጻናቱን ያለ ምንም ክፍያ ከማከም ባለፈ፣ ወደፊት አገሪቱ በዘርፉ ራሷን እንድትችል በዓለም አቀፍ ባለሙያዎችና በአገር ውስጥ የጤና ባለሙያዎች መካከል የእውቀትና የባለሙያ ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ይሰጣል ተብላል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን ዛሬ ለህክምና ቡድኑ ባደረጉት የአቀባበል መርሐ ግብር ላይ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የተቀበሉ ሲሆን፣ ለሁሉም አጋር ድርጅቶች ስላሳዩት ሰብአዊነትና ፈጣን ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ይህ ተነሳሽነት የዓለም አቀፍ አጋርነት፣ የርኅራኄ እና የሕክምና አንድነት ትልቅ ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ ወደፊት በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የሕፃናት ልብ ሕክምና አገልግሎትን በዘላቂነት ለመገንባትና ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ብለዋል።
በተጨማሪም ዘመቻው የሕፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ ለቤተሰቦቻቸው ተስፋን የሚመልስና የሕፃናትን ጤናና የወደፊት ሕይወት ለመጠበቅ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | በከባድ የልብ ሕመም ለሚሰቃዩ ሕፃናት ተስፋና ፈውስን ይዞ የመጣውና ለሦስት ቀናት የሚቆየው የነፃ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዛሬ በይፋ መካሄድ ጀምሯል።
ለዚህ ታላቅ ሰብአዊ ተልዕኮ ወደ ስፍራው ለገሰገሰው ዓለም አቀፍ የሕክምና ቡድን ዛሬ ጠዋት ደማቅ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት የተደረገለት ሲሆን፣ ቡድኑም የሕይወት አድን ሥራውን ወዲያውኑ አግልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ይህ አገር አቀፍ ጠቀሜታ ያለው ተነሳሽነት ሊሳካ የቻለው በHeart to Heart Children’s Aid፣ በኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል፣ በፓድሬ ፒዮ ኢጣሊያ፣ በኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር እና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ መካከል በተደረገ ጠንካራ ትብብር ሲሆን፣ ይህም በኢትዮጵያ ለሚገኙ የልብ ህመም ተጋላጭ ለሆኑ ሕፃናት ልዩ የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የታሰበ መሆኑ ተገልጿል።
በዛሬው ዕለት ሥራቸውን በይፋ የጀመሩት ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ዓለም አቀፍ የልብ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስቶችና የሕክምና ባለሙያዎች፣ የላቀ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምናና ልዩ የልብ ሕክምና አገልግሎቶችን ለሕጻናቱ ሙሉ በሙሉ መሆኑን ጎንደር ዩኒቨርስቲ ገልጿል።
በዚህ ወሳኝ የሕክምና ዘመቻ ወደ 20 የሚጠጉ ሕፃናት ቀጥተኛ የጤና ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ዘመቻ በአሁኑ ወቅት ሕጻናቱን ያለ ምንም ክፍያ ከማከም ባለፈ፣ ወደፊት አገሪቱ በዘርፉ ራሷን እንድትችል በዓለም አቀፍ ባለሙያዎችና በአገር ውስጥ የጤና ባለሙያዎች መካከል የእውቀትና የባለሙያ ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ይሰጣል ተብላል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን ዛሬ ለህክምና ቡድኑ ባደረጉት የአቀባበል መርሐ ግብር ላይ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የተቀበሉ ሲሆን፣ ለሁሉም አጋር ድርጅቶች ስላሳዩት ሰብአዊነትና ፈጣን ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ይህ ተነሳሽነት የዓለም አቀፍ አጋርነት፣ የርኅራኄ እና የሕክምና አንድነት ትልቅ ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ ወደፊት በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የሕፃናት ልብ ሕክምና አገልግሎትን በዘላቂነት ለመገንባትና ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ብለዋል።
በተጨማሪም ዘመቻው የሕፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ ለቤተሰቦቻቸው ተስፋን የሚመልስና የሕፃናትን ጤናና የወደፊት ሕይወት ለመጠበቅ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
Sponsored by
Surafel
24 days ago
በጎንደር ነፃ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ ተጀመረ
#fastmereja በከባድ የልብ ሕመም ለሚሰቃዩ ሕፃናት ተስፋና ፈውስን ይዞ የመጣውና ለሦስት ቀናት የሚቆየው የነፃ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዛሬ በይፋ መካሄድ ጀምሯል። ለዚህ ታላቅ ሰብአዊ ተልዕኮ ወደ ስፍራው ለገሰገሰው ዓለም አቀፍ የሕክምና ቡድን ዛሬ ጠዋት ደማቅ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት የተደረገለት ሲሆን፣ ቡድኑም ወዲያውኑ ሥራውን በይፋ አስጀምሯል። ይህ ሕይወት አታራፊ ተነሳሽነት ሊሳካ የቻለው በHeart to Heart Children’s Aid፣ በኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል፣ በፓድሬ ፒዮ ኢጣሊያ፣ በኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር እና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ መካከል በተደረገ ጠንካራ ትብብር ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ተጋላጭ ሕፃናት ልዩ የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተፈጠረውን የጋራ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው።
በዛሬው ዕለት ሥራቸውን በይፋ የጀመሩት ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ዓለም አቀፍ የልብ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስቶችና የሕክምና ባለሙያዎች፣ የላቀ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምናና ልዩ የልብ ሕክምና አገልግሎቶችን ለሕጻናቱ ሙሉ በሙሉ በነፃ መስጠት ጀምረዋል። በዚህ ወሳኝ የሕክምና ጣልቃ ገብነት ወደ 20 የሚጠጉ ሕፃናት ቀጥተኛ ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ዘመቻ በአሁኑ ወቅት ሕጻናቱን በነፃ ከማከም ባለፈ፣ ወደፊት አገሪቱ በዘርፉ ራሷን እንድትችል በዓለም አቀፍ ባለሙያዎችና በአገር ውስጥ የጤና ባለሙያዎች መካከል የእውቀትና የባለሙያ ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ዛሬውኑ ትልቅ ዕድልና መሠረት እየጣለ ይገኛል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን ዛሬ በነበረው የአቀባበል መርሐ-ግብር ላይ ዓለም አቀፉን የሕክምና ቡድን ከፍተኛ አክብሮት ባለው ስሜት እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የተቀበሉ ሲሆን፥ ለሁሉም አጋር ድርጅቶች ስላሳዩት ሰብአዊነትና ፈጣን ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ይህ ተነሳሽነት የዓለም አቀፍ አጋርነት፣ የርኅራኄ እና የሕክምና አንድነት ትልቅ ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ ወደፊት በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የሕፃናት ልብ ሕክምና አገልግሎትን በዘላቂነት ለመገንባትና ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ብለዋል። በተጨማሪም ዘመቻው የሕፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ ለቤተሰቦቻቸው ተስፋን የሚመልስና የሕፃናትን ጤናና የወደፊት ሕይወት ለመጠበቅ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል::
#fastmereja በከባድ የልብ ሕመም ለሚሰቃዩ ሕፃናት ተስፋና ፈውስን ይዞ የመጣውና ለሦስት ቀናት የሚቆየው የነፃ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምና ዘመቻ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዛሬ በይፋ መካሄድ ጀምሯል። ለዚህ ታላቅ ሰብአዊ ተልዕኮ ወደ ስፍራው ለገሰገሰው ዓለም አቀፍ የሕክምና ቡድን ዛሬ ጠዋት ደማቅ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት የተደረገለት ሲሆን፣ ቡድኑም ወዲያውኑ ሥራውን በይፋ አስጀምሯል። ይህ ሕይወት አታራፊ ተነሳሽነት ሊሳካ የቻለው በHeart to Heart Children’s Aid፣ በኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል፣ በፓድሬ ፒዮ ኢጣሊያ፣ በኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር እና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ መካከል በተደረገ ጠንካራ ትብብር ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ተጋላጭ ሕፃናት ልዩ የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተፈጠረውን የጋራ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው።
በዛሬው ዕለት ሥራቸውን በይፋ የጀመሩት ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ዓለም አቀፍ የልብ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስቶችና የሕክምና ባለሙያዎች፣ የላቀ የሕፃናት ልብ ቀዶ ሕክምናና ልዩ የልብ ሕክምና አገልግሎቶችን ለሕጻናቱ ሙሉ በሙሉ በነፃ መስጠት ጀምረዋል። በዚህ ወሳኝ የሕክምና ጣልቃ ገብነት ወደ 20 የሚጠጉ ሕፃናት ቀጥተኛ ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ዘመቻ በአሁኑ ወቅት ሕጻናቱን በነፃ ከማከም ባለፈ፣ ወደፊት አገሪቱ በዘርፉ ራሷን እንድትችል በዓለም አቀፍ ባለሙያዎችና በአገር ውስጥ የጤና ባለሙያዎች መካከል የእውቀትና የባለሙያ ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ዛሬውኑ ትልቅ ዕድልና መሠረት እየጣለ ይገኛል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን ዛሬ በነበረው የአቀባበል መርሐ-ግብር ላይ ዓለም አቀፉን የሕክምና ቡድን ከፍተኛ አክብሮት ባለው ስሜት እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የተቀበሉ ሲሆን፥ ለሁሉም አጋር ድርጅቶች ስላሳዩት ሰብአዊነትና ፈጣን ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ይህ ተነሳሽነት የዓለም አቀፍ አጋርነት፣ የርኅራኄ እና የሕክምና አንድነት ትልቅ ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ ወደፊት በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የሕፃናት ልብ ሕክምና አገልግሎትን በዘላቂነት ለመገንባትና ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ብለዋል። በተጨማሪም ዘመቻው የሕፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ ለቤተሰቦቻቸው ተስፋን የሚመልስና የሕፃናትን ጤናና የወደፊት ሕይወት ለመጠበቅ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል::
25 days ago
በአማራ ክልል በጎንደር፣ በጎጃም እና በወሎ የብልፅግና ፓርቲ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ እና የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው
****************
7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ በምዕራብ ጎንደር ዞን ምድረገነት ከተማ፣ ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ፤ በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ ከተማ እንዲሁም የባቲ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች የተሳተፉበት የምርጫ ቅስቀሳ እና የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ አባላት እና ደጋፊዎች "በጸና እና በተደራጀ የሴቶች ድምጽ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር እናሻግራለን!" በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ ተገኝተዉ ለፓርቲው ያላቸዉ ፅኑ ድጋፍ እየገለፁ ይገኛሉ።
በተመሳሳይ በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ ከተማ የብልፅግና የምርጫ ቅስቀሳ ነዋሪዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች በተገኙበት በድምቀት እየተካሄደ ነዉ።
"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሀሳብ የባቲ ከተማ ሴቶች የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ እና የድጋፍ ሰልፍ በባቲ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢቢሲ #ብልፅግና #ምርጫ #ድጋፍ #ኢትዮጵያ
****************
7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ በምዕራብ ጎንደር ዞን ምድረገነት ከተማ፣ ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ፤ በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ ከተማ እንዲሁም የባቲ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች የተሳተፉበት የምርጫ ቅስቀሳ እና የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ አባላት እና ደጋፊዎች "በጸና እና በተደራጀ የሴቶች ድምጽ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር እናሻግራለን!" በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ ተገኝተዉ ለፓርቲው ያላቸዉ ፅኑ ድጋፍ እየገለፁ ይገኛሉ።
በተመሳሳይ በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ ከተማ የብልፅግና የምርጫ ቅስቀሳ ነዋሪዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች በተገኙበት በድምቀት እየተካሄደ ነዉ።
"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሀሳብ የባቲ ከተማ ሴቶች የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ እና የድጋፍ ሰልፍ በባቲ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢቢሲ #ብልፅግና #ምርጫ #ድጋፍ #ኢትዮጵያ
27 days ago
በሕዝብ ልብና አእምሮ ውስጥ የኖሩት ሊቅ፡- ዶ/ር ዘኪ አብዱራህማን!
በጎንደር ሕዝብና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ልብ ውስጥ የማይረሳ አሻራ ያኖሩ፤ እርሳቸውም ጎንደርን በልባቸው ያተሙ፤ ታዋቂውና ተወዳጁ የጉበት፣ የቆሽትና የሀሞት ቀዶ ሕክምና ሰብ-ስፔሻሊስት ናቸው ዶክተር ዘኪ አብዱራህማን። አገራቸውንና ወገናቸውን ከልብ የሚያፈቅሩ፥ በትምህርታቸው የተመሰከረላቸው እና በተማሪዎቻቸው በእጅጉ የሚወደዱ ምሁር ናቸው። የሀገር ሀብት!
ከተማሪነት እስከ መምህርነትና ስመ-ጥር ሐኪምነት ወደቀሰሙበትና በቅንነት ወዳገለገሉበት ቀደመ ቤታቸው እንኳን በደህና መጡ። መምጣትዎ ለዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ ታላቅ ደስታና ኩራት ነው። በጎንደር ሕዝብ እቅፍ ሆነው የወጣትነት ጊዜያቸውን ያሳለፉ ሁሉ ሁልጊዜም ከጎንደር አይለዩም!
እንደ ዶ/ር ዘኪ ዓይነት ለአገርና ለወገን የሚተርፉ እና ለተተኪ ትውልድ አርአያ የሚሆኑ ሊቃውንትን ማፍራት በመቻሉ ጎንደር ዩኒቨርስቲ ኩራትና ክብር ይሰማዋል!!!
የጎንደር ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አፀደ ወይን
በጎንደር ሕዝብና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ልብ ውስጥ የማይረሳ አሻራ ያኖሩ፤ እርሳቸውም ጎንደርን በልባቸው ያተሙ፤ ታዋቂውና ተወዳጁ የጉበት፣ የቆሽትና የሀሞት ቀዶ ሕክምና ሰብ-ስፔሻሊስት ናቸው ዶክተር ዘኪ አብዱራህማን። አገራቸውንና ወገናቸውን ከልብ የሚያፈቅሩ፥ በትምህርታቸው የተመሰከረላቸው እና በተማሪዎቻቸው በእጅጉ የሚወደዱ ምሁር ናቸው። የሀገር ሀብት!
ከተማሪነት እስከ መምህርነትና ስመ-ጥር ሐኪምነት ወደቀሰሙበትና በቅንነት ወዳገለገሉበት ቀደመ ቤታቸው እንኳን በደህና መጡ። መምጣትዎ ለዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ ታላቅ ደስታና ኩራት ነው። በጎንደር ሕዝብ እቅፍ ሆነው የወጣትነት ጊዜያቸውን ያሳለፉ ሁሉ ሁልጊዜም ከጎንደር አይለዩም!
እንደ ዶ/ር ዘኪ ዓይነት ለአገርና ለወገን የሚተርፉ እና ለተተኪ ትውልድ አርአያ የሚሆኑ ሊቃውንትን ማፍራት በመቻሉ ጎንደር ዩኒቨርስቲ ኩራትና ክብር ይሰማዋል!!!
የጎንደር ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አፀደ ወይን
1 month ago
የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲና የፕሮግራም ክርክር በጎንደር ዩኒቨርሲቲ
#fastmereja I በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ጥናት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት፣ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ ያተኮረ የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲና የፕሮግራም ክርክር ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ተካሄደ። በመድረኩ ላይ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች በልማት ፖሊሲዎች፣ በሀገራዊ ጥቅምና ፍላጎቶች ዙሪያ የየራሳቸውን አማራጭ ሃሳቦች አቅርበዋል።
በዩኒቨርሲቲው የፕሬዚዳንት ህንፃ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስራት አፀደወይን የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ወቅት መድረኩ ሙሉ በሙሉ አካዳሚያዊ፣ ገለልተኛና ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንደሚመራ አረጋግጠዋል። ዜጎች ሉዓላዊ ፍቃዳቸውን ተጠቅመው መፃኢ እድላቸውን የሚወስኑበት ወቅት መሆኑን የገለጹት ዶ/ር አስራት፣ ታዳሚው የቀረቡትን ሃሳቦች በሂሳዊ መንገድ እንዲመረምር አሳስበዋል።
የስትራቴጂና ወቅታዊ ጉዳዮች ጥናት ክፍል አስተባባሪ አቶ ሀቢብ ሰይድ በበኩላቸው፣ ዳይሬክቶሬቱ ሀገራዊ ጉዳዮችን በገለልተኝነት የመመርመርና ስትራቴጂካዊ አማራጮችን የማመንጨት ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። ክርክሩ ከመጀመሩ በፊት "የውይይት ባህል ለሀገር ግንባታ" እና "የውክልና ዲሞክራሲና የምርጫ ስርዓት" በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምሁራዊ የመነሻ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በአቶ ጀምበሩ አረጋ አወያይነት በተመራው የፓርቲዎች ክርክር፣ ተወካዮቹ ከታዳሚዎች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ መርሃ ግብሩም መምህራን፣ ተማሪዎች፣ የሲቪክ ማህበራትና የሚዲያ አካላት በተገኙበት በሰላም ተጠናቋል።
#fastmereja I በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ጥናት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት፣ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ ያተኮረ የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲና የፕሮግራም ክርክር ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ተካሄደ። በመድረኩ ላይ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች በልማት ፖሊሲዎች፣ በሀገራዊ ጥቅምና ፍላጎቶች ዙሪያ የየራሳቸውን አማራጭ ሃሳቦች አቅርበዋል።
በዩኒቨርሲቲው የፕሬዚዳንት ህንፃ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስራት አፀደወይን የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ወቅት መድረኩ ሙሉ በሙሉ አካዳሚያዊ፣ ገለልተኛና ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንደሚመራ አረጋግጠዋል። ዜጎች ሉዓላዊ ፍቃዳቸውን ተጠቅመው መፃኢ እድላቸውን የሚወስኑበት ወቅት መሆኑን የገለጹት ዶ/ር አስራት፣ ታዳሚው የቀረቡትን ሃሳቦች በሂሳዊ መንገድ እንዲመረምር አሳስበዋል።
የስትራቴጂና ወቅታዊ ጉዳዮች ጥናት ክፍል አስተባባሪ አቶ ሀቢብ ሰይድ በበኩላቸው፣ ዳይሬክቶሬቱ ሀገራዊ ጉዳዮችን በገለልተኝነት የመመርመርና ስትራቴጂካዊ አማራጮችን የማመንጨት ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። ክርክሩ ከመጀመሩ በፊት "የውይይት ባህል ለሀገር ግንባታ" እና "የውክልና ዲሞክራሲና የምርጫ ስርዓት" በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምሁራዊ የመነሻ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በአቶ ጀምበሩ አረጋ አወያይነት በተመራው የፓርቲዎች ክርክር፣ ተወካዮቹ ከታዳሚዎች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ መርሃ ግብሩም መምህራን፣ ተማሪዎች፣ የሲቪክ ማህበራትና የሚዲያ አካላት በተገኙበት በሰላም ተጠናቋል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ዲኬ ሆልዲንግስ የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ የውጭ ምንዛሬን እያዳነ መሆኑን ገለጸ
#fastmereja I በአራተኛው ዙር "የኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ የተሳተፈው ዲኬ ሆልዲንግስ (DK Holdings)፣ ትራክተሮችንና የግብርና መሣሪያዎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የውጭ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ መተካት መቻሉን አስታወቀ። ኩባንያው በአሁኑ ወቅት ምርቶቹን እስከ 70 በመቶ የሚደርስ የሀገር ውስጥ ግብዓት በመጠቀም እያመረተ ይገኛል።
የኩባንያው ተወካይ አቶ ታረቀኝ ይልማ ለፋስት መረጃ እንደገለጹት፣ ድርጅቱ በግብርናው ዘርፍ ያለውን የቴክኖሎጂ ክፍተት ለመሙላት ሚዛን አማን ላይ ግዙፍ የትራክተር ማምረቻ ፋብሪካ እየገነባ ነው። ከትራክተር ባሻገር እንደ ማረሻ፣ መከትከቻ፣ የበቆሎ መፈልፈያ እና መውቂያ ያሉ የግብርና መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎችና ማሽነሪዎች እያመረተ ለገበሬው እያቀረበ ይገኛል።
ኩባንያው የኤሌክትሪክ ፍጆታን የሚቆጥቡና የክልሎችን ባህላዊ እሴት የሚያንፀባርቁ "ስማርት ፖሎችን" (ዘመናዊ የጎዳና መብራት ምሶሶዎች) በማምረት በጎንደር፣ በሚዛንና በቢሾፍቱ ከተሞች ተግባራዊ አድርጓል።
ቀደም ሲል 100 ፐርሰንት ከውጭ ይገቡ የነበሩ ትራንስፎርመሮችን የሀገሪቱን የጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ በሀገር ውስጥ እያመረተ ነው። ለከተማ ውበትና ለጽዳት አገልግሎት የሚውሉ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ጋንዳዎችን በስፋት እያቀረበ ይገኛል።
ዲኬ ሆልዲንግስ እነዚህን ምርቶች በሀገር ውስጥ ማምረቱ በከፍተኛ ዶላር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም የኢንዱስትሪ ማሽኖችን የመገጣጠም እና የመተከል ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
#fastmereja I በአራተኛው ዙር "የኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ የተሳተፈው ዲኬ ሆልዲንግስ (DK Holdings)፣ ትራክተሮችንና የግብርና መሣሪያዎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የውጭ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ መተካት መቻሉን አስታወቀ። ኩባንያው በአሁኑ ወቅት ምርቶቹን እስከ 70 በመቶ የሚደርስ የሀገር ውስጥ ግብዓት በመጠቀም እያመረተ ይገኛል።
የኩባንያው ተወካይ አቶ ታረቀኝ ይልማ ለፋስት መረጃ እንደገለጹት፣ ድርጅቱ በግብርናው ዘርፍ ያለውን የቴክኖሎጂ ክፍተት ለመሙላት ሚዛን አማን ላይ ግዙፍ የትራክተር ማምረቻ ፋብሪካ እየገነባ ነው። ከትራክተር ባሻገር እንደ ማረሻ፣ መከትከቻ፣ የበቆሎ መፈልፈያ እና መውቂያ ያሉ የግብርና መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎችና ማሽነሪዎች እያመረተ ለገበሬው እያቀረበ ይገኛል።
ኩባንያው የኤሌክትሪክ ፍጆታን የሚቆጥቡና የክልሎችን ባህላዊ እሴት የሚያንፀባርቁ "ስማርት ፖሎችን" (ዘመናዊ የጎዳና መብራት ምሶሶዎች) በማምረት በጎንደር፣ በሚዛንና በቢሾፍቱ ከተሞች ተግባራዊ አድርጓል።
ቀደም ሲል 100 ፐርሰንት ከውጭ ይገቡ የነበሩ ትራንስፎርመሮችን የሀገሪቱን የጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ በሀገር ውስጥ እያመረተ ነው። ለከተማ ውበትና ለጽዳት አገልግሎት የሚውሉ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ጋንዳዎችን በስፋት እያቀረበ ይገኛል።
ዲኬ ሆልዲንግስ እነዚህን ምርቶች በሀገር ውስጥ ማምረቱ በከፍተኛ ዶላር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም የኢንዱስትሪ ማሽኖችን የመገጣጠም እና የመተከል ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
1 month ago
የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት በባህር ዳር ከተማ ተመረቀ
#ethiopia | በውቧ ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።
በደቡባዊ የጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በጎርጎራ በኩል የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ብርሃን ወደ ሌላኛው የሀይቁ ዳርቻ ያሸጋገረ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በገበታ ለሀገር እቅድ አማካኝነት ሁለት የጣና ሀይቅ ዳርቻዎችን በቱሪዝም ለማስተሳሰር የነደፉትን ታላቅ ራዕይ ዳር ያደረሰ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታሪካዊቷን የጎርጎራ ከተማ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ በዐፄ ፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር የሚገኙ የቤተ መንግስት ቅርሶችን በከፍተኛ ጥራት በማደስ ለዘላቂ ቱሪዝም ዝግጁ እንዲሆኑ አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ለጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃ እና ለግብርና ልማት የሚውለው የመገጭ ግድብ ግንባታ ለውሃ ቱሪዝም አዲስ እድል ይዞ እየመጣ ይገኛል።
ይህንን መንግስታዊ ራዕይ በግል ኢንቨስትመንት በማገዝ የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መስራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በሁለት አመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ገንብተው አጠናቀዋል።
ግለሰቡ በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ እና በጎንደር ቅርሶች ጥገና ላይ የነበራቸውን ውጤታማ ተሳትፎ አሁን ደግሞ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ውስጥ በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ በኩል በስፋት ለመቀጠል ተዘጋጅተዋል።
አቶ ካሳሁን ለእነዚህ ስራዎች ስኬት የፌዴራል እና የክልል መንግስታት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ወደፊትም የፈለገ ግዮን እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርቶች በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር በመሆን ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን አለም አቀፍ በሚል መሪ ቃል ጥራት ያለው አገልግሎት ለጎብኚዎች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
#bahirdar #tanalake #tourismethiopia #beaikainvestment #rodahospitality #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በውቧ ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።
በደቡባዊ የጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በጎርጎራ በኩል የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ብርሃን ወደ ሌላኛው የሀይቁ ዳርቻ ያሸጋገረ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በገበታ ለሀገር እቅድ አማካኝነት ሁለት የጣና ሀይቅ ዳርቻዎችን በቱሪዝም ለማስተሳሰር የነደፉትን ታላቅ ራዕይ ዳር ያደረሰ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታሪካዊቷን የጎርጎራ ከተማ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ በዐፄ ፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር የሚገኙ የቤተ መንግስት ቅርሶችን በከፍተኛ ጥራት በማደስ ለዘላቂ ቱሪዝም ዝግጁ እንዲሆኑ አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ለጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃ እና ለግብርና ልማት የሚውለው የመገጭ ግድብ ግንባታ ለውሃ ቱሪዝም አዲስ እድል ይዞ እየመጣ ይገኛል።
ይህንን መንግስታዊ ራዕይ በግል ኢንቨስትመንት በማገዝ የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መስራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በሁለት አመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ገንብተው አጠናቀዋል።
ግለሰቡ በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ እና በጎንደር ቅርሶች ጥገና ላይ የነበራቸውን ውጤታማ ተሳትፎ አሁን ደግሞ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ውስጥ በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ በኩል በስፋት ለመቀጠል ተዘጋጅተዋል።
አቶ ካሳሁን ለእነዚህ ስራዎች ስኬት የፌዴራል እና የክልል መንግስታት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ወደፊትም የፈለገ ግዮን እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርቶች በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር በመሆን ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን አለም አቀፍ በሚል መሪ ቃል ጥራት ያለው አገልግሎት ለጎብኚዎች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
#bahirdar #tanalake #tourismethiopia #beaikainvestment #rodahospitality #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
ገበታ ለሀገር ! ገበታ ለጣና!
ባህርዳር የግዙፉን የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት የምረቃ ስነስርአት እያስተናገደች ነው!
______________________________
ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በውቧ ባህር ዳር ከተማ የግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መመረቅ ተበስሯል።
በደቡባዊ የጣና ሐይቅ ዳርቻ፤ በባህር ዳር ከተማ የተገነባው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ለጣና የቀረበ የጎርጎራን ብርሃን በሌላኛው ዳርቻ ያስቀጠለ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ይህ ውጥን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ የጎርጎራን ታላቅ ስራ ሙሉ ለማድረግ በሌላኛው የጣና አቅጣጫ፥ በውቧ ባህር ዳር የሚተሳሰሩ ሁለት የአንድ ሐይቅ ዳርቻ ገናና ህልሞችን ለማሳካት በገበታ ለሃገር ያለሙት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ ቀደምቷን የዐፄ ሱስኒዮስ መናገሻ ጎርጎራን ከዘመናት ጨለማ በኋላ ታላቅ ብርሃን እንድትጎናፀፍ ያደረጉበትን እጅግ ድንቅ አሻራ ተከትሎ ዳግም በዐፄ ሱስኒዮስ ልጅ በፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር አዲስ ነገር አሳዩ።
በመከራ ውስጥ የኖረውን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ እንደ አዲስ ነፍስ የዘራበትን የቅርስ ጥገና እና ልማት ዕውን አደረጉ። ይህ የቅርስ ጥገናና ልማት የዓለም ቅርሱን ታሪክ ወደ ላቀ ስኬት ያሻገረ የዘላቂ ቱሪዝም ትልቅ አቅም ነው።
የቀጠናውን መፃኢ ዕድል ነገውን ያስናፍቃል ያስባለው ሌላው ፕሮጀክት በጎንደር ከተማ የሚገኘው የመገጭ የመጠጥ፣ የመስኖ እና ሁለንተናዊ ልማት አቅም የሆነው ግድብ ነው። ግድቡ የውሃ እጥረት ላለባት ጎንደር ከቱሪዝም ልማት አኳያ ለውሃ ቱሪዝምና መዝናኛ ኢንቨስትመንት አዲስ ዕድል ይዞ እየመጣ ነው።
የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት በገበታ ለሀገር እንደለማው ሁሉ ይህ ራዕይ እንዲዘልቅና እንዲስፋፋ ገበታ ለሀገር በግል ኢንቨስትመንትም እንዲቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት የመሪነት ሚና ሀሳባቸውን በመግዛት የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መሥራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በገበታ ለሀገር ማዕቀፍ ውስጥ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጭ አድርገው በሁለት አመት ከስድስት ወር ግዜ ውስጥ እውን አድርገዋል።
ከዚህ ሪዞርት እና ከሌሎች ገናና ውጥኖች ዕውን መሆን ጀርባ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት በመወጣት ረገድ ከሀገር ልማት ጎን የቆመው የቤአኢካ ንግድና ኢንቨስትመንት ሚና የላቀ ነው።
በተለይም የድርጅቱ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሀገር ወዳዱ አቶ ካሳሁን ምስጋናው በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ በኮንትራክተርነት በታሰበው ጊዜ፣ በታለመው ጥራት እና በሚያኮራ ኃላፊነትን የመወጣት ስኬት አጠናቀዋል።
በተመሳሳይ እንደ ሀገርም ባልተለመደ ሁኔታ በሀገር ልጅ ብቃት እና ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር ምስጋና የቀረበለትን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ የቅርስ ጥገናና ልማት ስራ ሌላው ስለ ሀገር የተወጡት ኃላፊነት ነው።
በዚሁ 'በጎንደር እስከ ምፅአት' በሚል ሲፌዝበት የኖረውን የመገጭ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጠ ከባድ የቁጭት አደራ እና ኃላፊነት ተረክበው የግንባታ ሂደቱን በሚያስደንቅ ፍጥነት አሳክተው በመጠናቀቂያው ምዕራፍ ሊገኝ ችሏል።
አሁን ደግሞ በሀገር በቀሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትልቅ ቦታ የተሰጠው የቱሪዝም ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ውጥንን ለፍሬ ያበቁት አቶ ካሳሁን ምስጋናው በሌሎች ኢንቨስትመንቶቻቸው ካሳኩት ልምድ በመነሳት መንግስት ትልቅ ትኩረት የሰጠውን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ በግሉ ዘርፍ ለማልማት፣ ከመገንባት ልምድና አቅማቸው በተጨማሪ ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕን አቋቁመዋል።
አቶ ካሳሁን እነኚህ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሆነው ሀገር እና ህዝብ የጣሉባቸውን ኃላፊነቶች እንዲወጡ በማስቻል ረገድ የፌዴራል ፣ የክልል አንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ትልቁን ሚና እንደተጫዎቱ አፅንዎት ሰጥተው ገልጸዋል።
በተለይም የክልሉ መንግስት የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይን የቱሪዝም አብዮት ራዕይ ተቀብሎ ድርጅታቸው እና እሳቸው የተጣለባቸውን አደራ በአግባቡ እንዲወጡ ላደረገው ከፍተኛ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በቀጣይ የማስፋፊያ ስራዎቹ ተጨማሪ አያሌ እቅዶችን የያዘው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ከጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት ጋር በመቀናጀት በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር ይተዳደራል።
ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን እና ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በመያዝ ስራ የጀመረ፤ በቀጣይ ለማስተዳደር በሚረከባቸውም እራሱ በሚገነባቸውም የሆስፒታሊቲ ተቋማት የላቀ፣ ዘመናዊና ተወዳዳሪ አገልግሎትን ለመስጠት 'ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን ዓለም አቀፍ!' በሚል ፍልስፍና ኢንቨስትመንቱን የተቀላቀለ ሀገር በቀል ተቋም ነው።
በገበታ ለሃገር ማእቀፍ ውስጥ በግል ኢንቨትመንት የታነጸው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምርቃት ተበስሯል።
ባህርዳር የግዙፉን የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት የምረቃ ስነስርአት እያስተናገደች ነው!
______________________________
ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በውቧ ባህር ዳር ከተማ የግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መመረቅ ተበስሯል።
በደቡባዊ የጣና ሐይቅ ዳርቻ፤ በባህር ዳር ከተማ የተገነባው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ለጣና የቀረበ የጎርጎራን ብርሃን በሌላኛው ዳርቻ ያስቀጠለ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ይህ ውጥን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ የጎርጎራን ታላቅ ስራ ሙሉ ለማድረግ በሌላኛው የጣና አቅጣጫ፥ በውቧ ባህር ዳር የሚተሳሰሩ ሁለት የአንድ ሐይቅ ዳርቻ ገናና ህልሞችን ለማሳካት በገበታ ለሃገር ያለሙት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ ቀደምቷን የዐፄ ሱስኒዮስ መናገሻ ጎርጎራን ከዘመናት ጨለማ በኋላ ታላቅ ብርሃን እንድትጎናፀፍ ያደረጉበትን እጅግ ድንቅ አሻራ ተከትሎ ዳግም በዐፄ ሱስኒዮስ ልጅ በፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር አዲስ ነገር አሳዩ።
በመከራ ውስጥ የኖረውን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ እንደ አዲስ ነፍስ የዘራበትን የቅርስ ጥገና እና ልማት ዕውን አደረጉ። ይህ የቅርስ ጥገናና ልማት የዓለም ቅርሱን ታሪክ ወደ ላቀ ስኬት ያሻገረ የዘላቂ ቱሪዝም ትልቅ አቅም ነው።
የቀጠናውን መፃኢ ዕድል ነገውን ያስናፍቃል ያስባለው ሌላው ፕሮጀክት በጎንደር ከተማ የሚገኘው የመገጭ የመጠጥ፣ የመስኖ እና ሁለንተናዊ ልማት አቅም የሆነው ግድብ ነው። ግድቡ የውሃ እጥረት ላለባት ጎንደር ከቱሪዝም ልማት አኳያ ለውሃ ቱሪዝምና መዝናኛ ኢንቨስትመንት አዲስ ዕድል ይዞ እየመጣ ነው።
የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት በገበታ ለሀገር እንደለማው ሁሉ ይህ ራዕይ እንዲዘልቅና እንዲስፋፋ ገበታ ለሀገር በግል ኢንቨስትመንትም እንዲቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት የመሪነት ሚና ሀሳባቸውን በመግዛት የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መሥራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በገበታ ለሀገር ማዕቀፍ ውስጥ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጭ አድርገው በሁለት አመት ከስድስት ወር ግዜ ውስጥ እውን አድርገዋል።
ከዚህ ሪዞርት እና ከሌሎች ገናና ውጥኖች ዕውን መሆን ጀርባ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት በመወጣት ረገድ ከሀገር ልማት ጎን የቆመው የቤአኢካ ንግድና ኢንቨስትመንት ሚና የላቀ ነው።
በተለይም የድርጅቱ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሀገር ወዳዱ አቶ ካሳሁን ምስጋናው በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ በኮንትራክተርነት በታሰበው ጊዜ፣ በታለመው ጥራት እና በሚያኮራ ኃላፊነትን የመወጣት ስኬት አጠናቀዋል።
በተመሳሳይ እንደ ሀገርም ባልተለመደ ሁኔታ በሀገር ልጅ ብቃት እና ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር ምስጋና የቀረበለትን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ የቅርስ ጥገናና ልማት ስራ ሌላው ስለ ሀገር የተወጡት ኃላፊነት ነው።
በዚሁ 'በጎንደር እስከ ምፅአት' በሚል ሲፌዝበት የኖረውን የመገጭ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጠ ከባድ የቁጭት አደራ እና ኃላፊነት ተረክበው የግንባታ ሂደቱን በሚያስደንቅ ፍጥነት አሳክተው በመጠናቀቂያው ምዕራፍ ሊገኝ ችሏል።
አሁን ደግሞ በሀገር በቀሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትልቅ ቦታ የተሰጠው የቱሪዝም ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ውጥንን ለፍሬ ያበቁት አቶ ካሳሁን ምስጋናው በሌሎች ኢንቨስትመንቶቻቸው ካሳኩት ልምድ በመነሳት መንግስት ትልቅ ትኩረት የሰጠውን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ በግሉ ዘርፍ ለማልማት፣ ከመገንባት ልምድና አቅማቸው በተጨማሪ ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕን አቋቁመዋል።
አቶ ካሳሁን እነኚህ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሆነው ሀገር እና ህዝብ የጣሉባቸውን ኃላፊነቶች እንዲወጡ በማስቻል ረገድ የፌዴራል ፣ የክልል አንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ትልቁን ሚና እንደተጫዎቱ አፅንዎት ሰጥተው ገልጸዋል።
በተለይም የክልሉ መንግስት የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይን የቱሪዝም አብዮት ራዕይ ተቀብሎ ድርጅታቸው እና እሳቸው የተጣለባቸውን አደራ በአግባቡ እንዲወጡ ላደረገው ከፍተኛ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በቀጣይ የማስፋፊያ ስራዎቹ ተጨማሪ አያሌ እቅዶችን የያዘው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ከጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት ጋር በመቀናጀት በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር ይተዳደራል።
ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን እና ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በመያዝ ስራ የጀመረ፤ በቀጣይ ለማስተዳደር በሚረከባቸውም እራሱ በሚገነባቸውም የሆስፒታሊቲ ተቋማት የላቀ፣ ዘመናዊና ተወዳዳሪ አገልግሎትን ለመስጠት 'ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን ዓለም አቀፍ!' በሚል ፍልስፍና ኢንቨስትመንቱን የተቀላቀለ ሀገር በቀል ተቋም ነው።
በገበታ ለሃገር ማእቀፍ ውስጥ በግል ኢንቨትመንት የታነጸው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምርቃት ተበስሯል።
2 months ago
በ1.9 ቢሊዮን ብር የተገነባው ኃይሌ ሆቴል ደብረ ብርሃን ተመረቀ
#fastmereja | በታዋቂው አትሌትና ኢንተርፕረነር ኃይሌ ገብረስላሴ ባለቤትነት የሚመራው የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ግሩፕ፣ በ1.9 ቢሊዮን ብር ወጪ ያስገነባውን ዘመናዊ ሆቴል ዛሬ ሚያዝያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ከተማ በድምቀት አስመረቀ። ሆቴሉ የድርጅቱ 11ኛ መዳረሻ ሆኖ ተመዝግቧል።
ይህ ግዙፍ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት በኢንዱስትሪ ከተማዋ ደብረ ብርሃን ያለውን ከፍተኛ የእንግዳ ማረፊያ ፍላጎት ለመሙላትና የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ተገልጿል። ሆቴሉ በህንፃ ጥራቱና በውስጡ በያዛቸው ዘመናዊ መገልገያዎች በከተማዋ ቀዳሚ ተጠቃሽ ሆኗል።
በ1.9 ቢሊዮን ብር የተገነባው ይህ ሆቴል፣ ለታላላቅ እንግዶችና ለቱሪስቶች ምቹ የሆኑ 123 መኝታ ክፍሎችን ይዟል። ከዚህም በተጨማሪ አራት የተለያዩ ሬስቶራንቶች፣ የመጠጥ አገልግሎት የሚሰጡ ባሮች፣ ጂምና የሳውና አገልግሎቶችን ያካተተ ነው። ትላልቅ ስብሰባዎችንና ማህበራዊ ኩነቶችን ለማስተናገድ የሚያስችሉ ስድስት ዘመናዊ አዳራሾችም ተገንብተውለታል።
የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ግሩፕ ባወጣው መረጃ መሰረት፣ ሆቴሉ በአሁኑ ወቅት ለ200 በላይ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፤ በቀጣይ በሙሉ አቅሙ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የሠራተኞቹ ቁጥር ወደ 300 ከፍ እንደሚል ታውቋል።
ሻለቃ ኃይሌ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገረውበቀጣይ በጎንደር፣ በሐረር እና በድሬዳዋ ከተሞች የሚገነቡ ሆቴሎችን በማጠናቀቅ ለምረቃ እንደሚያበቃ ተጠቁሟል። ይህም ድርጅቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የኢንቨስትመንት አሻራ ይበልጥ እንደሚያሰፋው ታምኖበታል። ከኢትዮጵያ ውጪ ኃይሌ ሆቴል በሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ለማስፋት እንቅስቃሴ እንደተጀመረ ተነግሯል።
#fastmereja | በታዋቂው አትሌትና ኢንተርፕረነር ኃይሌ ገብረስላሴ ባለቤትነት የሚመራው የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ግሩፕ፣ በ1.9 ቢሊዮን ብር ወጪ ያስገነባውን ዘመናዊ ሆቴል ዛሬ ሚያዝያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ከተማ በድምቀት አስመረቀ። ሆቴሉ የድርጅቱ 11ኛ መዳረሻ ሆኖ ተመዝግቧል።
ይህ ግዙፍ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት በኢንዱስትሪ ከተማዋ ደብረ ብርሃን ያለውን ከፍተኛ የእንግዳ ማረፊያ ፍላጎት ለመሙላትና የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ተገልጿል። ሆቴሉ በህንፃ ጥራቱና በውስጡ በያዛቸው ዘመናዊ መገልገያዎች በከተማዋ ቀዳሚ ተጠቃሽ ሆኗል።
በ1.9 ቢሊዮን ብር የተገነባው ይህ ሆቴል፣ ለታላላቅ እንግዶችና ለቱሪስቶች ምቹ የሆኑ 123 መኝታ ክፍሎችን ይዟል። ከዚህም በተጨማሪ አራት የተለያዩ ሬስቶራንቶች፣ የመጠጥ አገልግሎት የሚሰጡ ባሮች፣ ጂምና የሳውና አገልግሎቶችን ያካተተ ነው። ትላልቅ ስብሰባዎችንና ማህበራዊ ኩነቶችን ለማስተናገድ የሚያስችሉ ስድስት ዘመናዊ አዳራሾችም ተገንብተውለታል።
የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ግሩፕ ባወጣው መረጃ መሰረት፣ ሆቴሉ በአሁኑ ወቅት ለ200 በላይ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፤ በቀጣይ በሙሉ አቅሙ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የሠራተኞቹ ቁጥር ወደ 300 ከፍ እንደሚል ታውቋል።
ሻለቃ ኃይሌ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገረውበቀጣይ በጎንደር፣ በሐረር እና በድሬዳዋ ከተሞች የሚገነቡ ሆቴሎችን በማጠናቀቅ ለምረቃ እንደሚያበቃ ተጠቁሟል። ይህም ድርጅቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የኢንቨስትመንት አሻራ ይበልጥ እንደሚያሰፋው ታምኖበታል። ከኢትዮጵያ ውጪ ኃይሌ ሆቴል በሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ለማስፋት እንቅስቃሴ እንደተጀመረ ተነግሯል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
በጎንደር ፍቅረኛውን በግፍ ገድሎ የዘረፈው ግለሰብ በ25 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ
#ethiopia | በማዕከላዊ ጎንደር ዞን፣ ማራኪ ክፍለ ከተማ ውስጥ የፍቅር ጓደኛውን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሎ ገንዘብ የዘረፈው ብሩክ (ሰለሞን) ደጀን የተባለ ግለሰብ የ25 ዓመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት።
ግለሰቡ ወንጀሉን የፈጸመው "ባህር ዳር የታመመ ቤተሰብ እንጠይቅ" በሚል ሰበብ ሟች ጥጋብ (እናንየ) ሙላትን ይዟት ከወጣ በኋላ ነው።
ለሁለት ቀናት ያህል በተለያዩ ሆቴሎች ካቆያት በኋላ፣ ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ሌሊት 11 ሰዓት ላይ "ቤተክርስቲያን ተሳልመን እንመለስ" በማለት አታሎ አቡነ ሃራ ቤተክርስቲያን አቅራቢያ ወደሚገኝ ጫካ በመውሰድ በፌሮ ብረት ጭንቅላቷን ደጋግሞ በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል።
ግድያውን ከፈጸመ በኋላም የሟችን ሞባይል ስልክ እና በባንክ የነበራትን 465,214 ብር ወደ ተለያዩ ሰዎች አካውንት አስተላልፎ ወስዷል። በተጨማሪም የሟችን ስልክ በመጠቀም ለወንድሟ "ፀበል ቦታ ነኝ፣ ብር ስለቸገረኝ ላኩልኝ" የሚል የሐሰት አጭር መልእክት በመላክ ተጨማሪ 86,000 ብር አጭበርብሮ ተቀብሏል።
የሟች ቤተሰቦች ባደረባቸው ጥርጣሬ ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ መሰረት በተደረገ ምርመራ ተከሳሹ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በዐቃቤ ሕግ የቀረበበትን የሰው እና የሰነድ ማስረጃ መርምሮ ጥፋተኛነቱን በማረጋገጡ፣ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባዋለው ችሎት በ25 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ የመጨረሻ ውሳኔ አስተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጎንደር #ፍትህ #ወንጀል_እና_ቅጣት #ኢትዮጵያ #ዜና #gondar #crimenews #ethiopia
#ethiopia | በማዕከላዊ ጎንደር ዞን፣ ማራኪ ክፍለ ከተማ ውስጥ የፍቅር ጓደኛውን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሎ ገንዘብ የዘረፈው ብሩክ (ሰለሞን) ደጀን የተባለ ግለሰብ የ25 ዓመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት።
ግለሰቡ ወንጀሉን የፈጸመው "ባህር ዳር የታመመ ቤተሰብ እንጠይቅ" በሚል ሰበብ ሟች ጥጋብ (እናንየ) ሙላትን ይዟት ከወጣ በኋላ ነው።
ለሁለት ቀናት ያህል በተለያዩ ሆቴሎች ካቆያት በኋላ፣ ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ሌሊት 11 ሰዓት ላይ "ቤተክርስቲያን ተሳልመን እንመለስ" በማለት አታሎ አቡነ ሃራ ቤተክርስቲያን አቅራቢያ ወደሚገኝ ጫካ በመውሰድ በፌሮ ብረት ጭንቅላቷን ደጋግሞ በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል።
ግድያውን ከፈጸመ በኋላም የሟችን ሞባይል ስልክ እና በባንክ የነበራትን 465,214 ብር ወደ ተለያዩ ሰዎች አካውንት አስተላልፎ ወስዷል። በተጨማሪም የሟችን ስልክ በመጠቀም ለወንድሟ "ፀበል ቦታ ነኝ፣ ብር ስለቸገረኝ ላኩልኝ" የሚል የሐሰት አጭር መልእክት በመላክ ተጨማሪ 86,000 ብር አጭበርብሮ ተቀብሏል።
የሟች ቤተሰቦች ባደረባቸው ጥርጣሬ ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ መሰረት በተደረገ ምርመራ ተከሳሹ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በዐቃቤ ሕግ የቀረበበትን የሰው እና የሰነድ ማስረጃ መርምሮ ጥፋተኛነቱን በማረጋገጡ፣ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባዋለው ችሎት በ25 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ የመጨረሻ ውሳኔ አስተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጎንደር #ፍትህ #ወንጀል_እና_ቅጣት #ኢትዮጵያ #ዜና #gondar #crimenews #ethiopia
2 months ago
ዳሌ እና መገጣጠሚያ አከባቢ ለሚከሰት ስብራት ወጌሻ የህክምና አማራጭ ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት ተነገረ
በተለያዩ አደጋዎች የሚከሰት የዳሌ አንጓ መገጣጠሚያ ስብራትና እዛዉ መሠረቱ ላይ የሚከሰቱ ስብራቶች በአፋጣኝ ህክምና ካላገኙ ዉጤታቸዉ የከፋ መሆኑ ተነግሯል ።
የመኪና ፣የሞተርና የመዉደቅ አደጋዎች ከተከሰቱ በኃላ ብሽሽት አከባቢ ከፍተኛ የሆነ ህመም ኖር ለማጠፍና ለመዘርጋት መቸገር ፣ለመንቀሳቀስ መቸገር ፣በእግር መሬት መርገጥና መራመድ አለመቻል እና የእግር ማጠር ስብራት ተከስቶ ሊሆን ስለሚችል ፈጥኖ ወደ ጤና ተቋም መሄድ አስፈላጊ ነዉ ተብሏል ።
በጎንደር ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል የአጥንት እና መገጣጠሚያ ስፔሻሊስት እንዲሁም የያኔት ጎንደር ስፔሻላይዝድ የህክምና ማዕከል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ጌታነህ ወርቅነህ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ የዳሌ አንጓ ስብራት ያጋጠማቸው ሰዎች በ48 ሰዓታት ዉስጥ ህክምና ካልተደረገላቸዉ የደም መርጋት ፣ኢንፌክሽን ፣የዉስጥ ቁስለት ሊያጋጥማቸዉ ይችላል ብለዋል ።
አብዛኛዉን ጊዜ በተለይም ደግሞ ወጣቶች ወጌሻ ህክምና ላይ ቆይተዉ ዘግይተዉ ወደ ህክምና ተቋማት የሚመጡ በመሆኑ ስብራቱን ወደ ነበረበት ለመመለስ አስቸጋሪ መሆኑ ተጠቁሟል ።ዕድሜያቸዉ ከ60 ዓመት በታች ሆነዉ ከፍተኛ አደጋ የደረሰባቸዉ ወጣቶች በ48 ሰዓታት ዉስጥ ወይንም ከበዛ ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ዉስጥ ወደ ህክምና ተቋም ከመጡ ወደነበረበት ለመመለስ የሚደረግ ህክምና መኖሩን የገለፁት ዶክተር ጌታነህ ከዘገዩ ግን የግማሽ ዳሌ ንቅለ ተከላ እና የሙሉ ዳሌ ንቅለ ተከላ ህክምና ይደረጋል ብለዋል ።
በቶሎ ህክምና ካገኙ ግን ሌሎች ተጓዳኝ የአጥንት መሳሳት ችግር ካለ ለዚሁ የሚያግዝ አጥንት የሚያጠነክር መድኃኒት ለመስጠት እንደሚቻል ጨምረዉ ገልፀዋል ።
seledadotio
በተለያዩ አደጋዎች የሚከሰት የዳሌ አንጓ መገጣጠሚያ ስብራትና እዛዉ መሠረቱ ላይ የሚከሰቱ ስብራቶች በአፋጣኝ ህክምና ካላገኙ ዉጤታቸዉ የከፋ መሆኑ ተነግሯል ።
የመኪና ፣የሞተርና የመዉደቅ አደጋዎች ከተከሰቱ በኃላ ብሽሽት አከባቢ ከፍተኛ የሆነ ህመም ኖር ለማጠፍና ለመዘርጋት መቸገር ፣ለመንቀሳቀስ መቸገር ፣በእግር መሬት መርገጥና መራመድ አለመቻል እና የእግር ማጠር ስብራት ተከስቶ ሊሆን ስለሚችል ፈጥኖ ወደ ጤና ተቋም መሄድ አስፈላጊ ነዉ ተብሏል ።
በጎንደር ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል የአጥንት እና መገጣጠሚያ ስፔሻሊስት እንዲሁም የያኔት ጎንደር ስፔሻላይዝድ የህክምና ማዕከል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ጌታነህ ወርቅነህ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ የዳሌ አንጓ ስብራት ያጋጠማቸው ሰዎች በ48 ሰዓታት ዉስጥ ህክምና ካልተደረገላቸዉ የደም መርጋት ፣ኢንፌክሽን ፣የዉስጥ ቁስለት ሊያጋጥማቸዉ ይችላል ብለዋል ።
አብዛኛዉን ጊዜ በተለይም ደግሞ ወጣቶች ወጌሻ ህክምና ላይ ቆይተዉ ዘግይተዉ ወደ ህክምና ተቋማት የሚመጡ በመሆኑ ስብራቱን ወደ ነበረበት ለመመለስ አስቸጋሪ መሆኑ ተጠቁሟል ።ዕድሜያቸዉ ከ60 ዓመት በታች ሆነዉ ከፍተኛ አደጋ የደረሰባቸዉ ወጣቶች በ48 ሰዓታት ዉስጥ ወይንም ከበዛ ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ዉስጥ ወደ ህክምና ተቋም ከመጡ ወደነበረበት ለመመለስ የሚደረግ ህክምና መኖሩን የገለፁት ዶክተር ጌታነህ ከዘገዩ ግን የግማሽ ዳሌ ንቅለ ተከላ እና የሙሉ ዳሌ ንቅለ ተከላ ህክምና ይደረጋል ብለዋል ።
በቶሎ ህክምና ካገኙ ግን ሌሎች ተጓዳኝ የአጥንት መሳሳት ችግር ካለ ለዚሁ የሚያግዝ አጥንት የሚያጠነክር መድኃኒት ለመስጠት እንደሚቻል ጨምረዉ ገልፀዋል ።
seledadotio
3 months ago
የፕሮፌሰር ማለደ ማሩ የሕይወት ታሪክ ተፅፎ ተመረቀ
(ከዕዝራ እጅጉ ሙላት)
#ethiopia | ለግማሽ ክፍለ ዘመን ወይም ለ 52 ዓመታት በሕክምናው ዘርፍ ያገለገሉት የፕሮፌሰር ማለደ ማሩ የሕይወት ታሪክ ተፅፎ ቅዳሜ መጋቢት 19 2018 ዓ.ም ተመርቋል።
ቀበና በሚገኘው የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ማህበር አዳራሽ በተካሄደው የምረቃ መርሀ ግብር፣ የፕሮፌሰሩ አብሮ አደጎች እና ተማሪዎች የተገኙ ሲሆን የመፅሐፉም ደራሲ ዶክተር ሰሎሞን በርሄ ናቸው።
ፕሮፌሰር ማለደ ማሩ፣ ለልብ ህክምና ከፍተኛ ትኩረት የሰጡ ባለሙያ ሲሆኑ የጎንደር ዩኒቨርሲቲም አምና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአስተዳደር ህንፃውን በስማቸው ሰይሞ ትልቅ ዕውቅና መስጠቱም ይታወቃል።
በመፅሐፍ ምረቃ መርሀ- ግብሩ ላይ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ዶክተር አፀደ ወይን አስራት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት፣ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን ሰዎች በሕይወት እያሉ የሙያ ታሪካቸው በዚህ መልኩ ተሰንዶ በመፅሐፍ መልክ መቅረቡ ለአዲሱ አገር ተረካቢ ትውልድ ትልቅ ነገር ነው ብለዋል።
"የቼቼላው አባታችን " በሚል ርዕስ ታሪካቸው በመታተሙ ደስ የተሰኙት ታላቁ የአገር ባለውለታ ፕሮፌሰር ማለደ ማሩ፣ በመሸብኝ ሰዓት ስላስታወሳችሁኝ አመሠግናለሁ ብለዋል።
ይህን የእርሳቸውን መፅሐፍ ለማሳተም ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራው የተከናወነ ሲሆን ባለታሪኩ ፕሮፌሰር ማለደም ለኮሚቴው ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
"የቼቼላው አባታችን "የተሰኘው በፕሮፌሰር ማለደ ማሩ ላይ ትኩረቱን ያደረገ መፅሐፍ 200 ገፆች ያሉት ሲሆን በ1000 ቅጂዎች ለህትመት የበቃ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
መፅሐፉ ከነገ መጋቢት 21 2018 አንስቶ በጃፋር የመፅሃፍ መደብር የሚገኝ ሲሆን ዋጋውም ብር 500 መሆኑን ደራሲው ለተወዳጅ ሚድያ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። በተጨማሪም መፅሐፉ በባህርዳር እና በጎንደር የመፅሐፍ መሸጫ መደብሮች እንደሚገኝ ተነግሯል።
(ከዕዝራ እጅጉ ሙላት)
#ethiopia | ለግማሽ ክፍለ ዘመን ወይም ለ 52 ዓመታት በሕክምናው ዘርፍ ያገለገሉት የፕሮፌሰር ማለደ ማሩ የሕይወት ታሪክ ተፅፎ ቅዳሜ መጋቢት 19 2018 ዓ.ም ተመርቋል።
ቀበና በሚገኘው የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ማህበር አዳራሽ በተካሄደው የምረቃ መርሀ ግብር፣ የፕሮፌሰሩ አብሮ አደጎች እና ተማሪዎች የተገኙ ሲሆን የመፅሐፉም ደራሲ ዶክተር ሰሎሞን በርሄ ናቸው።
ፕሮፌሰር ማለደ ማሩ፣ ለልብ ህክምና ከፍተኛ ትኩረት የሰጡ ባለሙያ ሲሆኑ የጎንደር ዩኒቨርሲቲም አምና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአስተዳደር ህንፃውን በስማቸው ሰይሞ ትልቅ ዕውቅና መስጠቱም ይታወቃል።
በመፅሐፍ ምረቃ መርሀ- ግብሩ ላይ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ዶክተር አፀደ ወይን አስራት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት፣ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን ሰዎች በሕይወት እያሉ የሙያ ታሪካቸው በዚህ መልኩ ተሰንዶ በመፅሐፍ መልክ መቅረቡ ለአዲሱ አገር ተረካቢ ትውልድ ትልቅ ነገር ነው ብለዋል።
"የቼቼላው አባታችን " በሚል ርዕስ ታሪካቸው በመታተሙ ደስ የተሰኙት ታላቁ የአገር ባለውለታ ፕሮፌሰር ማለደ ማሩ፣ በመሸብኝ ሰዓት ስላስታወሳችሁኝ አመሠግናለሁ ብለዋል።
ይህን የእርሳቸውን መፅሐፍ ለማሳተም ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራው የተከናወነ ሲሆን ባለታሪኩ ፕሮፌሰር ማለደም ለኮሚቴው ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
"የቼቼላው አባታችን "የተሰኘው በፕሮፌሰር ማለደ ማሩ ላይ ትኩረቱን ያደረገ መፅሐፍ 200 ገፆች ያሉት ሲሆን በ1000 ቅጂዎች ለህትመት የበቃ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
መፅሐፉ ከነገ መጋቢት 21 2018 አንስቶ በጃፋር የመፅሃፍ መደብር የሚገኝ ሲሆን ዋጋውም ብር 500 መሆኑን ደራሲው ለተወዳጅ ሚድያ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። በተጨማሪም መፅሐፉ በባህርዳር እና በጎንደር የመፅሐፍ መሸጫ መደብሮች እንደሚገኝ ተነግሯል።
3 months ago
የሕይወት አድን ጥሪ
እህታችን መሠረት ፈንታቢልን (አስካለ ማርያምን) በጋራ እንታደጋት
ከ2010 ዓ.ም. ጀምሮ በኩላሊት ሕመም ስትሰቃይ የቆየችው እህታችን መሠረት ፈንታቢል፣ አሁን ላይ ሕይወቷን ለማዳን የእያንዳንዳችን የጋራ ርብርብ ያስፈልጋታል።
መሠረት በባህር ዳር፣ በጎንደርና በአዲስ አበባ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ለዓመታት ስትታከም ቆይታለች።
በ2015 ዓ.ም. አረጋዊ አባቷ ኩላሊታቸውን ቢሰጧትም፣ ከሁለት ቀን በኋላ ሳይሳካ ቀርቶ ኩላሊቱ ሥራ አቁሟል።
ከኩላሊቱ በተጨማሪ በ2017 ዓ.ም. የልብ ቧንቧ ጥበት አጋጥሟት የልብ ሕክምና አድርጋለች።
በአሁኑ ወቅት በየሳምንቱ ሦስት ጊዜ የዲያሊሲስ (Dialysis) ሕክምና እያደረገች ሲሆን፣ ይህ ሕክምና አጥንቷንና ሌላው ሰውነቷን እየጎዳው ይገኛል።
ልጆቿና ቤተሰቧ ካሉበት ጭንቀት እንዲገላገሉና መሠረት የተሻለ ሕክምና አግኝታ ወደ ጤናዋ እንድትመለስ የገንዘብ ድጋፍ ያስፈልጋታል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
1000706400544
አቢሲኒያ ባንክ (BoA)
230444447
https://gofund.me/0b08e84b...
ነገ በእኛም ላይ ምን እንደሚገጥመን አናውቅምና፣ ዛሬ ለወገን ደራሽ በመሆን እህታችንን እናሳክማት።
አቅማችሁ የፈቀደውን በመለገስና ይህንን መረጃ ለሌሎች በማጋራት (Share) እንተባበር።
#getu #ethiopia #healthalert #kidneyfailure #supportmeseret #addisababa #charityethiopia #communitysupport #savealife #እህታችንንእንታደጋት #የኩላሊትሕክምና #የሕይወትአድንጥሪ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
እህታችን መሠረት ፈንታቢልን (አስካለ ማርያምን) በጋራ እንታደጋት
ከ2010 ዓ.ም. ጀምሮ በኩላሊት ሕመም ስትሰቃይ የቆየችው እህታችን መሠረት ፈንታቢል፣ አሁን ላይ ሕይወቷን ለማዳን የእያንዳንዳችን የጋራ ርብርብ ያስፈልጋታል።
መሠረት በባህር ዳር፣ በጎንደርና በአዲስ አበባ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ለዓመታት ስትታከም ቆይታለች።
በ2015 ዓ.ም. አረጋዊ አባቷ ኩላሊታቸውን ቢሰጧትም፣ ከሁለት ቀን በኋላ ሳይሳካ ቀርቶ ኩላሊቱ ሥራ አቁሟል።
ከኩላሊቱ በተጨማሪ በ2017 ዓ.ም. የልብ ቧንቧ ጥበት አጋጥሟት የልብ ሕክምና አድርጋለች።
በአሁኑ ወቅት በየሳምንቱ ሦስት ጊዜ የዲያሊሲስ (Dialysis) ሕክምና እያደረገች ሲሆን፣ ይህ ሕክምና አጥንቷንና ሌላው ሰውነቷን እየጎዳው ይገኛል።
ልጆቿና ቤተሰቧ ካሉበት ጭንቀት እንዲገላገሉና መሠረት የተሻለ ሕክምና አግኝታ ወደ ጤናዋ እንድትመለስ የገንዘብ ድጋፍ ያስፈልጋታል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
1000706400544
አቢሲኒያ ባንክ (BoA)
230444447
https://gofund.me/0b08e84b...
ነገ በእኛም ላይ ምን እንደሚገጥመን አናውቅምና፣ ዛሬ ለወገን ደራሽ በመሆን እህታችንን እናሳክማት።
አቅማችሁ የፈቀደውን በመለገስና ይህንን መረጃ ለሌሎች በማጋራት (Share) እንተባበር።
#getu #ethiopia #healthalert #kidneyfailure #supportmeseret #addisababa #charityethiopia #communitysupport #savealife #እህታችንንእንታደጋት #የኩላሊትሕክምና #የሕይወትአድንጥሪ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ከአዲስ ዘመን እስከ ኢትዮጵያን ኔክስት ቶፕ ሞዴል
የሞዴል ሰለሞን አዲስ የጽናት ጉዞ
#ethiopia | የብዙ ከያንያን እና የጥበብ ሰዎች መፍለቂያ ከሆነችው አዲስ ዘመን ከተማ የተነሳው ወጣት ሰለሞን አዲስ፣ ዛሬ በኢትዮጵያ ሞዴሊንግ ዘርፍ ስሙ በጉልህ እየተነሳ ይገኛል።
ሰለሞን ትምህርትን ከህልም፣ ሥራን ደግሞ ከጽናት ጋር አጣምሮ የያዘ የዘመኑ ወጣት ተምሳሌት ነው።
ሰለሞን በአካዳሚክ ዘርፍ እራሱን በሚገባ ያበቃ ባለሙያ ነው። በቅየሳ (Surveying) እና በአውቶ መካኒክ በደረጃ 4 የሰለጠነ ሲሆን፣ በማኔጅመንት የመጀመሪያ ዲግሪውን ይዟል።
በሥራው ዓለምም በአማራ ልማት ማኅበር (አልማ) በግንባታ ክትትል ባለሙያነት ከማገልገሉም በላይ፣ ለ8 ዓመታት የራሱን የህንፃ ሥራ አማካሪ ቢሮ በመክፈት በርካታ ፕላኖችን ቀርጿል።
ሞዴሊንግ የሰለሞን የልጅነት ሕልም ቢሆንም፣ ጉዞው ግን አልጋ በአልጋ አልነበረም። በጎንደር የጀመረው ስልጠና በቂ ስላልነበረ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በሆቴል ሪሴብሽን ሥራ እየተዳደረ በዞላ ሞዴሊንግ ትምህርት ቤት ስልጠናውን ቀጥሏል።
ሕይወት ከባድ በነበረችባቸው ጊዜያት ተስፋ ባለመቁረጥ ለዓመት ተምሮ የ"ኮንፊደንስ" ተሸላሚ በመሆን ተመርቋል።
ዛሬ ሰለሞን በሥራው አድጎ "Night Manager" ለመሆን መብቃቱ ብቻ ሳይሆን፣ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረውን "Ethiopian Next Top Model" ውድድርን ተቀላቅሎ በአዲስ አበባና በመላው ሀገሪቱ ታዋቂነትን እያተረፈ ይገኛል።
"በሕይወት ውስጥ ተስፋ አለመቁረጥን ተምሬያለሁ" የሚለው ሰለሞን፣ በአባይ ቲቪ በሚተላለፈው በዚህ ውድድር ላይ እያሳየው ላለው ብቃት የደጋፊዎቹን ምስጋናና ማበረታቻ በክብር ይቀበላል። ለዚህ ስኬት ላበቁት የአባይ ቲቪ እና የውድድሩ አዘጋጅ መልካም ሚካኤልም ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል።
ሰለሞን አዲስ ለወጣቶች የሚነግረን አንድ ትልቅ እውነት አለ፦ "ያሰብከውን ለማሳካት ከጣርክ፣ አንድ ቀን ማሳካትህ አይቀሬ ነው!"
#getu #solomonaddis #ethiopiannexttopmodel #modeling #inspiration #successstory #ethiopia #addiszemen #abaytv #ሞዴል #ሰለሞንአዲስ #ኢትዮጵያ #ተስፋአለመቁረጥ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የሞዴል ሰለሞን አዲስ የጽናት ጉዞ
#ethiopia | የብዙ ከያንያን እና የጥበብ ሰዎች መፍለቂያ ከሆነችው አዲስ ዘመን ከተማ የተነሳው ወጣት ሰለሞን አዲስ፣ ዛሬ በኢትዮጵያ ሞዴሊንግ ዘርፍ ስሙ በጉልህ እየተነሳ ይገኛል።
ሰለሞን ትምህርትን ከህልም፣ ሥራን ደግሞ ከጽናት ጋር አጣምሮ የያዘ የዘመኑ ወጣት ተምሳሌት ነው።
ሰለሞን በአካዳሚክ ዘርፍ እራሱን በሚገባ ያበቃ ባለሙያ ነው። በቅየሳ (Surveying) እና በአውቶ መካኒክ በደረጃ 4 የሰለጠነ ሲሆን፣ በማኔጅመንት የመጀመሪያ ዲግሪውን ይዟል።
በሥራው ዓለምም በአማራ ልማት ማኅበር (አልማ) በግንባታ ክትትል ባለሙያነት ከማገልገሉም በላይ፣ ለ8 ዓመታት የራሱን የህንፃ ሥራ አማካሪ ቢሮ በመክፈት በርካታ ፕላኖችን ቀርጿል።
ሞዴሊንግ የሰለሞን የልጅነት ሕልም ቢሆንም፣ ጉዞው ግን አልጋ በአልጋ አልነበረም። በጎንደር የጀመረው ስልጠና በቂ ስላልነበረ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በሆቴል ሪሴብሽን ሥራ እየተዳደረ በዞላ ሞዴሊንግ ትምህርት ቤት ስልጠናውን ቀጥሏል።
ሕይወት ከባድ በነበረችባቸው ጊዜያት ተስፋ ባለመቁረጥ ለዓመት ተምሮ የ"ኮንፊደንስ" ተሸላሚ በመሆን ተመርቋል።
ዛሬ ሰለሞን በሥራው አድጎ "Night Manager" ለመሆን መብቃቱ ብቻ ሳይሆን፣ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረውን "Ethiopian Next Top Model" ውድድርን ተቀላቅሎ በአዲስ አበባና በመላው ሀገሪቱ ታዋቂነትን እያተረፈ ይገኛል።
"በሕይወት ውስጥ ተስፋ አለመቁረጥን ተምሬያለሁ" የሚለው ሰለሞን፣ በአባይ ቲቪ በሚተላለፈው በዚህ ውድድር ላይ እያሳየው ላለው ብቃት የደጋፊዎቹን ምስጋናና ማበረታቻ በክብር ይቀበላል። ለዚህ ስኬት ላበቁት የአባይ ቲቪ እና የውድድሩ አዘጋጅ መልካም ሚካኤልም ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል።
ሰለሞን አዲስ ለወጣቶች የሚነግረን አንድ ትልቅ እውነት አለ፦ "ያሰብከውን ለማሳካት ከጣርክ፣ አንድ ቀን ማሳካትህ አይቀሬ ነው!"
#getu #solomonaddis #ethiopiannexttopmodel #modeling #inspiration #successstory #ethiopia #addiszemen #abaytv #ሞዴል #ሰለሞንአዲስ #ኢትዮጵያ #ተስፋአለመቁረጥ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
"እንዛታ"
— አዲስ ትውፊታዊ ቴአትር ነገ በባህር ዳር በድምቀት ይመረቃል!
#ethiopia | በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ዝክረ ታሪክ ጽሕፈት ቤት የተዘጋጀውና የአዝማሪዎችን እውነተኛ ሕይወት የሚዳስሰው "እንዛታ" የተሰኘ ድንቅ ትውፊታዊ ቴአትር ነገ ይመረቃል።
ቴአትሩ በጎንደር የሚገኙ አዝማሪዎች መንደር "ቡርቧክስ" ድረስ በመሄድ፣ የአዝማሪዎችን አጠቃላይ የሕይወት ዘይቤ በጥናት ላይ ተመስርቶ የቀረበ ነው።
የአዝማሪዎችን እውነተኛ የኑሮ ገጽታ፣ ሳቅ፣ ደስታና ሐዘን በመሰንቆ ክርና በአውታር መካከል የተደበቁ የሕይወት መንገዶችን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
# እንዛታ !!
ገብረማርያም ይርጋ #gebremaryam Yirga
የአብክመ ባህል ኪነጥበብ እና ዝክረ ታሪክ ጽ/ቤት
#እንዛታ #ባህርዳር #ትውፊታዊቴአትር #አዝማሪ #ኢትዮጵያ #ኪነጥበብ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
— አዲስ ትውፊታዊ ቴአትር ነገ በባህር ዳር በድምቀት ይመረቃል!
#ethiopia | በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ዝክረ ታሪክ ጽሕፈት ቤት የተዘጋጀውና የአዝማሪዎችን እውነተኛ ሕይወት የሚዳስሰው "እንዛታ" የተሰኘ ድንቅ ትውፊታዊ ቴአትር ነገ ይመረቃል።
ቴአትሩ በጎንደር የሚገኙ አዝማሪዎች መንደር "ቡርቧክስ" ድረስ በመሄድ፣ የአዝማሪዎችን አጠቃላይ የሕይወት ዘይቤ በጥናት ላይ ተመስርቶ የቀረበ ነው።
የአዝማሪዎችን እውነተኛ የኑሮ ገጽታ፣ ሳቅ፣ ደስታና ሐዘን በመሰንቆ ክርና በአውታር መካከል የተደበቁ የሕይወት መንገዶችን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
# እንዛታ !!
ገብረማርያም ይርጋ #gebremaryam Yirga
የአብክመ ባህል ኪነጥበብ እና ዝክረ ታሪክ ጽ/ቤት
#እንዛታ #ባህርዳር #ትውፊታዊቴአትር #አዝማሪ #ኢትዮጵያ #ኪነጥበብ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
ተጠርጣሪው ተያዘ
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በጎንደር ከተማ የሰው ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ አጥፍቶ ከአካባቢው የተሰወረውን ተጠርጣሪ በዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp) አማካኝነት በቀረበ ጥቆማ በድሬዳዋ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ የሰው ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ አጥፍቶ ከአካባቢው የተሰወረውን ተጠርጣሪ በዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp) አማካኝነት በቀረበ ጥቆማ በድሬዳዋ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታውቋል፡፡
ተጠርጣሪ ሙሉቀን ተስፋዬ ደምሌ የጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 ነዋሪ ሲሆን የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ዳግም ባዘዘው ነጋ ከተባለው ወጣት ጋር ምሽት አብረው ሲዝናኑ ቆይተው በመካከላቸው በተፈጠረው አለመግባባት ተጠርጣሪው ዳግም ባዘዘውን በአሰቃቂ ሁኔታ ከገደለ በኋላ ከአካባቢው በመሰወር በድሬዳዋ ከተማ ተደብቆ ይኖር ነበር፡፡
የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp) አማካኝነት ከአማራ ክልል በደረሰ ጥቆማ መሰረት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳዳር ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ባካሄደው ተከታታይነት ያለው ብርቱ ክትትል ተጠርጣሪውን መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ በቁጥጥር ሥር አውሎ ለአማራ ክልል ጎንደር ከተማ ፖሊስ አሳልፎ መስጠቱን ገልጿል፡፡
አሁን ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp)፣ በሰው አልባ ፖሊስ ጣቢያ (Smart Police Station) እና በሌሎች ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ወንጀልን በብቃት እየተከላከለ መሆኑን በመግለፅ ህብረተሰቡ የወንጀል ተግባራትን፣ ስጋትና አጠራጣሪ ሁኔታዎችን በዜጎች መተግበሪያ (EFPApp)፡ በስማርት ፖሊስ ስቴሽን (SPS) እንዲሁም በነፃ የስልክ መስመር 991 መረጃን ለፖሊስ በማድረስ ፈጣን ምላሽ ማግኘት እንደሚችል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል::
Ethiopian Federal Police
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በጎንደር ከተማ የሰው ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ አጥፍቶ ከአካባቢው የተሰወረውን ተጠርጣሪ በዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp) አማካኝነት በቀረበ ጥቆማ በድሬዳዋ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ የሰው ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ አጥፍቶ ከአካባቢው የተሰወረውን ተጠርጣሪ በዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp) አማካኝነት በቀረበ ጥቆማ በድሬዳዋ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታውቋል፡፡
ተጠርጣሪ ሙሉቀን ተስፋዬ ደምሌ የጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 ነዋሪ ሲሆን የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ዳግም ባዘዘው ነጋ ከተባለው ወጣት ጋር ምሽት አብረው ሲዝናኑ ቆይተው በመካከላቸው በተፈጠረው አለመግባባት ተጠርጣሪው ዳግም ባዘዘውን በአሰቃቂ ሁኔታ ከገደለ በኋላ ከአካባቢው በመሰወር በድሬዳዋ ከተማ ተደብቆ ይኖር ነበር፡፡
የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp) አማካኝነት ከአማራ ክልል በደረሰ ጥቆማ መሰረት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳዳር ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ባካሄደው ተከታታይነት ያለው ብርቱ ክትትል ተጠርጣሪውን መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ በቁጥጥር ሥር አውሎ ለአማራ ክልል ጎንደር ከተማ ፖሊስ አሳልፎ መስጠቱን ገልጿል፡፡
አሁን ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp)፣ በሰው አልባ ፖሊስ ጣቢያ (Smart Police Station) እና በሌሎች ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ወንጀልን በብቃት እየተከላከለ መሆኑን በመግለፅ ህብረተሰቡ የወንጀል ተግባራትን፣ ስጋትና አጠራጣሪ ሁኔታዎችን በዜጎች መተግበሪያ (EFPApp)፡ በስማርት ፖሊስ ስቴሽን (SPS) እንዲሁም በነፃ የስልክ መስመር 991 መረጃን ለፖሊስ በማድረስ ፈጣን ምላሽ ማግኘት እንደሚችል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል::
Ethiopian Federal Police
3 months ago
አንጋፋው የጎንደር ኢማም ኡስታዝ ሙሐመድ ዘይኑ ተገደሉ
በጎንደር ከተማ የታወቁት የመስጂድ ኢማም ኡስታዝ ሙሐመድ ዘይኑ ትላንት ምሽት በታጣቂዎች እጅ መገደላቸው ተሰማ።
እንደ ሀሩን ሚዲያ ዘገባ ከሆነ ግድያው የተፈጸመው ኡስታዙ የተራዊህ ሰላት ሰግደው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በወላጅ አባታቸውና በወንድማቸው ፊት ነው።
ታጣቂዎቹ በወቅቱ በነበሩ 11 ሰዎች ላይም ከባድ ድብደባና ዘረፋ መፈፀማቸውን በዘገባው ተመላክቷል።
ድርጊቱ የተፈጸመው በከተማዋ መሀል "ቅዳሜ ገበያ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፣ ከጃሚዓል ከቢር መስጂድ ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ነውም ተብሏል
ዛሬ ቀብራቸው የተፈፀመው ኡስታዝ ሙሐመድ ዘይኑ ለረጅም ዓመታት የከተማዋን ዑለማ ምክር ቤት ያገለገሉ ሲሆን፣ በቁርዓን አቀራረባቸውና በታታሪ የሃይማኖት አገልጋይነታቸው የሚታወቁ አንጋፋ ምሁር ነበሩ።
ድርጊቱ በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ሃዘንን ፈጥሯል።
seledadotio
seledadotio
በጎንደር ከተማ የታወቁት የመስጂድ ኢማም ኡስታዝ ሙሐመድ ዘይኑ ትላንት ምሽት በታጣቂዎች እጅ መገደላቸው ተሰማ።
እንደ ሀሩን ሚዲያ ዘገባ ከሆነ ግድያው የተፈጸመው ኡስታዙ የተራዊህ ሰላት ሰግደው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በወላጅ አባታቸውና በወንድማቸው ፊት ነው።
ታጣቂዎቹ በወቅቱ በነበሩ 11 ሰዎች ላይም ከባድ ድብደባና ዘረፋ መፈፀማቸውን በዘገባው ተመላክቷል።
ድርጊቱ የተፈጸመው በከተማዋ መሀል "ቅዳሜ ገበያ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፣ ከጃሚዓል ከቢር መስጂድ ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ነውም ተብሏል
ዛሬ ቀብራቸው የተፈፀመው ኡስታዝ ሙሐመድ ዘይኑ ለረጅም ዓመታት የከተማዋን ዑለማ ምክር ቤት ያገለገሉ ሲሆን፣ በቁርዓን አቀራረባቸውና በታታሪ የሃይማኖት አገልጋይነታቸው የሚታወቁ አንጋፋ ምሁር ነበሩ።
ድርጊቱ በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ሃዘንን ፈጥሯል።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
አንጋፋው የጎንደር ኢማም ኡስታዝ ሙሐመድ ዘይኑ ተገደሉ
በጎንደር ከተማ የታወቁት የመስጂድ ኢማም ኡስታዝ ሙሐመድ ዘይኑ ትላንት ምሽት በታጣቂዎች እጅ መገደላቸው ተሰማ።
እንደ ሀሩን ሚዲያ ዘገባ ከሆነ ግድያው የተፈጸመው ኡስታዙ የተራዊህ ሰላት ሰግደው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በወላጅ አባታቸውና በወንድማቸው ፊት ነው።
ታጣቂዎቹ በወቅቱ በነበሩ 11 ሰዎች ላይም ከባድ ድብደባና ዘረፋ መፈፀማቸውን በዘገባው ተመላክቷል።
ድርጊቱ የተፈጸመው በከተማዋ መሀል "ቅዳሜ ገበያ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፣ ከጃሚዓል ከቢር መስጂድ ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ነውም ተብሏል
ዛሬ ቀብራቸው የተፈፀመው ኡስታዝ ሙሐመድ ዘይኑ ለረጅም ዓመታት የከተማዋን ዑለማ ምክር ቤት ያገለገሉ ሲሆን፣ በቁርዓን አቀራረባቸውና በታታሪ የሃይማኖት አገልጋይነታቸው የሚታወቁ አንጋፋ ምሁር ነበሩ።
ድርጊቱ በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ሃዘንን ፈጥሯል።
በጎንደር ከተማ የታወቁት የመስጂድ ኢማም ኡስታዝ ሙሐመድ ዘይኑ ትላንት ምሽት በታጣቂዎች እጅ መገደላቸው ተሰማ።
እንደ ሀሩን ሚዲያ ዘገባ ከሆነ ግድያው የተፈጸመው ኡስታዙ የተራዊህ ሰላት ሰግደው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በወላጅ አባታቸውና በወንድማቸው ፊት ነው።
ታጣቂዎቹ በወቅቱ በነበሩ 11 ሰዎች ላይም ከባድ ድብደባና ዘረፋ መፈፀማቸውን በዘገባው ተመላክቷል።
ድርጊቱ የተፈጸመው በከተማዋ መሀል "ቅዳሜ ገበያ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፣ ከጃሚዓል ከቢር መስጂድ ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ነውም ተብሏል
ዛሬ ቀብራቸው የተፈፀመው ኡስታዝ ሙሐመድ ዘይኑ ለረጅም ዓመታት የከተማዋን ዑለማ ምክር ቤት ያገለገሉ ሲሆን፣ በቁርዓን አቀራረባቸውና በታታሪ የሃይማኖት አገልጋይነታቸው የሚታወቁ አንጋፋ ምሁር ነበሩ።
ድርጊቱ በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ሃዘንን ፈጥሯል።
Sponsored by
Surafel
4 months ago
"የተከዜ አዳኝ መንገድ" የወልቃይት ጠገዴ የማንነት ትግልና የታሪክ ሰነድ
ከከፋኝ እስከ ነፃነት የወልቃይት ሕዝብ የሕልውና ጉዞ የሚተርከው አዲሱ መጽሐፍ ለንባብ በቃ
* "ታሪኩን የማያውቅ ለመገዛት የተዘጋጀ ነው" አቶ አሸተ ደምለው
በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አቶ አሸተ ደምለው የተፃፈውና የሕዝቡን የዘመናት የማንነትና የሕልውና ትግል የሚተርከው "የተከዜ አዳኝ መንገድ" መጽሐፍ በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ በድምቀት ተመረቀ።
በ175 ገጾች የተቀነበበው ይህ መጽሐፍ ታዋቂው የፍልስፍና መምህር ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ የጎንደር ከተማ ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው ምሁራን በተገኙበት ለንባብ በቅቷል።
የመጽሐፉ ደራሲ አቶ አሸተ ደምለው በምረቃው ላይ እንደገለጹት መጽሐፉ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ "ማንነቴ አማራ ነው" በሚል "ከፋኝ" በተሰኘ አደረጃጀት ሲያደርግ የነበረውን መራራ ትግል በዝርዝር ያሳያል። ሕወሓት በሕዝቡ ላይ የፈጸመውን ዘግናኝ ግፎች የሚያጋልጥ መሆኑንም ጠቅሰዋል
ደራሲው አክለውም የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ፍላጎት ከትግራይ ወገኖቹ ጋር በሰላምና በአንድነት መኖር ቢሆንም ሰላም በአንድ ወገን ጥረት ብቻ የማይረጋገጥ በመሆኑ ሁሌም ለሕልውና ዝግጁ መሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።
የመጽሐፉን አስፈላጊነት አስመልክቶ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ በሰጡት አስተያየት "ታሪካቸውን የማያውቁ ለመገዛት የተዘጋጁ ናቸው" በማለት መጽሐፉ የሕወሓትን የጥፋት መንገድ ከማጋለጥ ባለፈ ከችግሮች መውጫ መንገዱን የሚያመላክት መሆኑን ገልጸዋል።
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሶስዮሎጂ መምህር የሆኑት ሃቢብ ሰዒድ በበኩላቸው መጽሐፉ የታሪክና የማታገያ ሰነድ በመሆኑ ለቀጣዩ ትውልድ እውነትን የሚያሳይ ትልቅ አሻራ መሆኑን አስረድተዋል።
የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ሕዝቡ የነበረበትን የግፍ ቀንበር ሰብሮ ዛሬ በገዛ ልጆቹ እየተመራ ለዚህ መብቃቱ የትግሉ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።
ደራሲ አቶ አሸተ ደምለው ከዚህ ቀደም "የተከዜ አዳኝ ትውልድ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃታቸው የሚታወስ ሲሆን አዲሱ መጽሐፋቸው የዚያ ቀጣይ ክፍል ተደርጎ ተወስዷል።
ከከፋኝ እስከ ነፃነት የወልቃይት ሕዝብ የሕልውና ጉዞ የሚተርከው አዲሱ መጽሐፍ ለንባብ በቃ
* "ታሪኩን የማያውቅ ለመገዛት የተዘጋጀ ነው" አቶ አሸተ ደምለው
በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አቶ አሸተ ደምለው የተፃፈውና የሕዝቡን የዘመናት የማንነትና የሕልውና ትግል የሚተርከው "የተከዜ አዳኝ መንገድ" መጽሐፍ በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ በድምቀት ተመረቀ።
በ175 ገጾች የተቀነበበው ይህ መጽሐፍ ታዋቂው የፍልስፍና መምህር ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ የጎንደር ከተማ ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው ምሁራን በተገኙበት ለንባብ በቅቷል።
የመጽሐፉ ደራሲ አቶ አሸተ ደምለው በምረቃው ላይ እንደገለጹት መጽሐፉ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ "ማንነቴ አማራ ነው" በሚል "ከፋኝ" በተሰኘ አደረጃጀት ሲያደርግ የነበረውን መራራ ትግል በዝርዝር ያሳያል። ሕወሓት በሕዝቡ ላይ የፈጸመውን ዘግናኝ ግፎች የሚያጋልጥ መሆኑንም ጠቅሰዋል
ደራሲው አክለውም የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ፍላጎት ከትግራይ ወገኖቹ ጋር በሰላምና በአንድነት መኖር ቢሆንም ሰላም በአንድ ወገን ጥረት ብቻ የማይረጋገጥ በመሆኑ ሁሌም ለሕልውና ዝግጁ መሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።
የመጽሐፉን አስፈላጊነት አስመልክቶ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ በሰጡት አስተያየት "ታሪካቸውን የማያውቁ ለመገዛት የተዘጋጁ ናቸው" በማለት መጽሐፉ የሕወሓትን የጥፋት መንገድ ከማጋለጥ ባለፈ ከችግሮች መውጫ መንገዱን የሚያመላክት መሆኑን ገልጸዋል።
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሶስዮሎጂ መምህር የሆኑት ሃቢብ ሰዒድ በበኩላቸው መጽሐፉ የታሪክና የማታገያ ሰነድ በመሆኑ ለቀጣዩ ትውልድ እውነትን የሚያሳይ ትልቅ አሻራ መሆኑን አስረድተዋል።
የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ሕዝቡ የነበረበትን የግፍ ቀንበር ሰብሮ ዛሬ በገዛ ልጆቹ እየተመራ ለዚህ መብቃቱ የትግሉ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።
ደራሲ አቶ አሸተ ደምለው ከዚህ ቀደም "የተከዜ አዳኝ ትውልድ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃታቸው የሚታወስ ሲሆን አዲሱ መጽሐፋቸው የዚያ ቀጣይ ክፍል ተደርጎ ተወስዷል።
Comments