5 hours ago
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት የትራምፕን የጦርነት ስልጣን ለመገደብ ድምፅ ሰጡ
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ተጨማሪ የወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስዱ የሚያግድ የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በየካቲት ወር የጀመረውን ጦርነት በአደባባይ በመቃወም አራት ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር ከተቀላቀሉ በኋላ፤ የውሳኔ ሃሳቡ በ2መቶ15 ለ 2መቶ8 ድምፅ ሊጸድቅ ችሏል።
ይህ የተወካዮች ምክር ቤት በትራምፕ የጦርነት ስልጣን ላይ ገደብ ለመጣል የሞከረው ለአራተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ተቺዎች ፕሬዝዳንቱ የኮንግረሱን ፈቃድ ሳያገኙ እርምጃ እየወሰዱ ነው በማለት ይወቅሳሉ።
የምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳብ አሁንም በሪፐብሊካኖች በሚመራው የአሜሪካ ሴኔት መፅደቅ ይኖርበታል፤ይሁን እንጂ ሴኔቱ ቢቀበለው እንኳ እርምጃው በኢራን ላይ የሚሰነዘረውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ለመግታት መቻሉ አጠራጣሪ ነው፡፡
ውሳኔው ከዚህ ቀደም ሰባት ጊዜ ሳይሳካ ቀርቶ ባለፈው ግንቦት ወር ሴኔቱ መሰል የውሳኔ ሃሳብን ያራመደ ቢሆንም እስካሁን ሙሉ ድምፅ ለመስጠት ወደ መድረክ አላመጣውም።
እሮብ ዕለት የተካሄደው ድምፅ በትራምፕ እና ሪፐብሊካን ፓርቲ ውስጥ ያለውን ልዩነት የሚያሳይ የቅርብ ጊዜ ምልክት ነው ፡፡
ይህ የሆነው ደግሞ በኮንግረስ ውስጥ ባሉ ወግ አጥባቂዎች ተቃውሞ ምክንያት አስተዳደሩ ለፖለቲካ አጋሮቹ ሊመድበው የነበረውን የ1.8 ቢሊየን ዶላር "ፀረ-የጦር መሣሪያ ታጣቂነት" ፈንድ ዕቅዱን ለመሰረዝ በተገደደ በጥቂት ቀናት ውስጥ ነው።
በተወካዮች ምክር ቤት የሚገኙ ቶማስ ማሲ፣ ብሪያን ፊትዝፓትሪክ፣ ቶም ባሬት እና ዋረን ዴቪድሰን የተባሉ ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር በመተባበር ረቡዕ ዕለት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በተጨማሪም ከዚህ ቀደም መሰል እርምጃዎችን ተቃውመው የነበሩት የሜይን ግዛት ዲሞክራት ጃሬድ ጎልደን በዚህ ጊዜ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
ከሚቺጋን የመጡት ሪፐብሊካን ቶም ባሬትበበኩላቸው "ጦርነት የሚያውጀው ኮንግረስ ብቻ ነው፤ ይህ ደግሞ በእርግጥ ልንጠብቀው የሚገባ ጉዳይ ነው" ብለዋል።
በዚህ ድምፅ አሰጣጥ ምክንያት ከትራምፕ ሊሰነዘርባቸው ስለሚችለው የአጸፋ እርምጃ ተጠይቀው ሲመልሱ፡ "ትክክል ነው ብዬ ላመንኩበት ነገር በህሊናዬ ነው ድምፅ የሰጠሁት እናም የሚመጣውን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነኝ" ብለዋል።
በተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ መሪ የሆኑት ዲሞክራቱ ግሬገሪ ሚክስ፣ የተሰጠውን ድምፅ "በፕሬዝዳንት ትራምፕ ህገ-ወጥ እና ከፍተኛ ኪሳራ እያስከተለ ባለው የኢራን ጦርነት ላይ የተሰነዘረ ጠንካራ የሁለቱ ፓርቲዎች ተግሳጽ እና ጦርነቱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማቆም የተነገደ የመጀመሪያው እርምጃ ነው" ሲሉ ገልጸውታል።
ሚክስ አክለውም ትራምፕ በሀገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ እንዲንር ከማድረጋቸው እና ለኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ የመፈለጉን ሂደት ይበልጥ አስቸጋሪ ከማድረጋቸው ባለፈ የጦርነቱን የተቀመጡ ግቦች ማሳካት አልቻሉም ብለዋል።
የውሳኔ ሃሳቡን በጋራ ያዘጋጁት ሚክስ "የዚህ ውሳኔ መጽደቅ ትልቅ የማዕዘን ድንጋይ ነው ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሪፐብሊካኖች በመካከለኛው ምስራቅ ሌላ ማብቂያ የሌለው ጦርነት የማይፈልጉትን የመራጮቻቸውን ድምፅ እየሰሙ ነው" ብለዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በየካቲት 28 በኢራን ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው የሚታወቁ ሲሆን ኢራንም በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው ለሚገኙ የአሜሪካ አጋር ሀገራት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ምላሽ የሰጠች ሲሆን ለአለም አቀፍ የመርከብ ትራንስፖርት ወሳኝ የውሃ መስመር የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ በውጤታማነት ዘግታለች።
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ተጨማሪ የወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስዱ የሚያግድ የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በየካቲት ወር የጀመረውን ጦርነት በአደባባይ በመቃወም አራት ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር ከተቀላቀሉ በኋላ፤ የውሳኔ ሃሳቡ በ2መቶ15 ለ 2መቶ8 ድምፅ ሊጸድቅ ችሏል።
ይህ የተወካዮች ምክር ቤት በትራምፕ የጦርነት ስልጣን ላይ ገደብ ለመጣል የሞከረው ለአራተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ተቺዎች ፕሬዝዳንቱ የኮንግረሱን ፈቃድ ሳያገኙ እርምጃ እየወሰዱ ነው በማለት ይወቅሳሉ።
የምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳብ አሁንም በሪፐብሊካኖች በሚመራው የአሜሪካ ሴኔት መፅደቅ ይኖርበታል፤ይሁን እንጂ ሴኔቱ ቢቀበለው እንኳ እርምጃው በኢራን ላይ የሚሰነዘረውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ለመግታት መቻሉ አጠራጣሪ ነው፡፡
ውሳኔው ከዚህ ቀደም ሰባት ጊዜ ሳይሳካ ቀርቶ ባለፈው ግንቦት ወር ሴኔቱ መሰል የውሳኔ ሃሳብን ያራመደ ቢሆንም እስካሁን ሙሉ ድምፅ ለመስጠት ወደ መድረክ አላመጣውም።
እሮብ ዕለት የተካሄደው ድምፅ በትራምፕ እና ሪፐብሊካን ፓርቲ ውስጥ ያለውን ልዩነት የሚያሳይ የቅርብ ጊዜ ምልክት ነው ፡፡
ይህ የሆነው ደግሞ በኮንግረስ ውስጥ ባሉ ወግ አጥባቂዎች ተቃውሞ ምክንያት አስተዳደሩ ለፖለቲካ አጋሮቹ ሊመድበው የነበረውን የ1.8 ቢሊየን ዶላር "ፀረ-የጦር መሣሪያ ታጣቂነት" ፈንድ ዕቅዱን ለመሰረዝ በተገደደ በጥቂት ቀናት ውስጥ ነው።
በተወካዮች ምክር ቤት የሚገኙ ቶማስ ማሲ፣ ብሪያን ፊትዝፓትሪክ፣ ቶም ባሬት እና ዋረን ዴቪድሰን የተባሉ ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር በመተባበር ረቡዕ ዕለት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በተጨማሪም ከዚህ ቀደም መሰል እርምጃዎችን ተቃውመው የነበሩት የሜይን ግዛት ዲሞክራት ጃሬድ ጎልደን በዚህ ጊዜ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
ከሚቺጋን የመጡት ሪፐብሊካን ቶም ባሬትበበኩላቸው "ጦርነት የሚያውጀው ኮንግረስ ብቻ ነው፤ ይህ ደግሞ በእርግጥ ልንጠብቀው የሚገባ ጉዳይ ነው" ብለዋል።
በዚህ ድምፅ አሰጣጥ ምክንያት ከትራምፕ ሊሰነዘርባቸው ስለሚችለው የአጸፋ እርምጃ ተጠይቀው ሲመልሱ፡ "ትክክል ነው ብዬ ላመንኩበት ነገር በህሊናዬ ነው ድምፅ የሰጠሁት እናም የሚመጣውን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነኝ" ብለዋል።
በተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ መሪ የሆኑት ዲሞክራቱ ግሬገሪ ሚክስ፣ የተሰጠውን ድምፅ "በፕሬዝዳንት ትራምፕ ህገ-ወጥ እና ከፍተኛ ኪሳራ እያስከተለ ባለው የኢራን ጦርነት ላይ የተሰነዘረ ጠንካራ የሁለቱ ፓርቲዎች ተግሳጽ እና ጦርነቱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማቆም የተነገደ የመጀመሪያው እርምጃ ነው" ሲሉ ገልጸውታል።
ሚክስ አክለውም ትራምፕ በሀገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ እንዲንር ከማድረጋቸው እና ለኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ የመፈለጉን ሂደት ይበልጥ አስቸጋሪ ከማድረጋቸው ባለፈ የጦርነቱን የተቀመጡ ግቦች ማሳካት አልቻሉም ብለዋል።
የውሳኔ ሃሳቡን በጋራ ያዘጋጁት ሚክስ "የዚህ ውሳኔ መጽደቅ ትልቅ የማዕዘን ድንጋይ ነው ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሪፐብሊካኖች በመካከለኛው ምስራቅ ሌላ ማብቂያ የሌለው ጦርነት የማይፈልጉትን የመራጮቻቸውን ድምፅ እየሰሙ ነው" ብለዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በየካቲት 28 በኢራን ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው የሚታወቁ ሲሆን ኢራንም በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው ለሚገኙ የአሜሪካ አጋር ሀገራት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ምላሽ የሰጠች ሲሆን ለአለም አቀፍ የመርከብ ትራንስፖርት ወሳኝ የውሃ መስመር የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ በውጤታማነት ዘግታለች።
13 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በ2022ቱ የኳታር ዓለም ዋንጫ ማሳረጊያ ላይ ፈረንሳይ በፍጻሜው ብትሸነፍም ኪሊያን ምባፔ ሃት-ትሪክ ሰርቶ የወርቅ ጫማውን ሲቀበል ፊቱ ላይ ምንም ዓይነት ፈገግታ አልነበረም። ግቦች ለቡድን ድል ሙሉ ዋስትና ባይሆኑም፣ አንድ አደገኛ አጥቂ ግን ለቡድኑ ሁሌም ትልቅ ተስፋ እና ዕድል ፈጣሪ ነው። የ2026ቱ ታላቁ እና ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማዕበል እየተቃረበ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የወርቅ ጫማ አሸናፊዎችን ታሪካዊ ዳራ እና ቀጣዮቹን አጓጊ ተገማቾች በጥልቀት እንቃኛለን።
ለእንግሊዛዊው ኮከብ ሃሪ ኬን ጥሩ ያልሆነ ዜና አለ ታሪክ እንደሚነግረን በ30 ዓመት እና ከዚያ በላይ ዕድሜ ላይ ሆኖ የወርቅ ጫማ ማሸነፍ እጅግ ከባድ ነው። ይህ ክስተት በታሪክ የተመዘገበው አንድ ጊዜ ብቻ ሲሆን፣ በ1998ቱ የፈረንሳይ ዓለም ዋንጫ ክሮኤሺያዊው ዳቮር ሱከር በ30 ዓመቱ 6 ግቦችን በማስቆጠር ነበር ይህን ተአምር ያሳካው። ሱከር ለዚህ ሕግ ብቸኛው ልዩ ማሳያ ሲሆን፣ በአማካይ የወርቅ ጫማ አሸናፊዎች ዕድሜ 24.7 ዓመት ነው። በ2022 ምባፔ በ24 ዓመቱ 35 ዓመት የነበረውን ሊዮኔል ሜሲን በአንድ ግብ ብቻ በልጦ ማሸነፉ የዕድሜ አማካዩን በትንሹ ዝቅ አድርጎታል። በታሪክ በለጋ ዕድሜው ይህን ክብር ያገኘው ሀንጋሪያዊው ፍሎሪያን አልበርት ሲሆን፣ በ1962ቱ የቺሊ ውድድር ላይ በ20 ዓመት ከስምንት ወር ዕድሜው አሸንፏል። ይህንን ታሪካዊ ሪከርድ ለመስበር የስፔኑ የ18 ዓመት ታዳጊ ላሚን ያማል በአሁኑ ወቅት በጉጉት ዓይኑን ጥሏል።
በሌላ በኩል ደግሞ ብቻውን የሚያጨበጭብ እጅ የለምና አንድ ስኬታማ አጥቂ ጥሩ የኳስ አቅርቦት እና ቡድኑ በውድድሩ ሩቅ መጓዝ መቻል ያስፈልገዋል። አምስት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያነሳችው ብራዚል፣ ከ1938ቱ ሊዮኒዳስ እስከ 2002ቱ ሮናልዶ ድረስ ስድስት አደገኛ የወርቅ ጫማ አሸናፊዎችን ማፍራቷ አያስገርምም። በምድብ ጨዋታዎች ብዙ ግብ ማስቆጠር ጥሩ ጅምር ቢሆንም፣ ቡድንዎ ወደ ጥሎ ማለፍ ካላደገ ግን ትልቅ ኪሳራ ነው። ለምሳሌ በ2018ቱ የሩሲያ ውድድር ክርስቲያኖ ሮናልዶ በምድብ ጨዋታዎች 4 ግቦችን ቢያገባም ፖርቱጋል በ16ቱ ዙር በመውደቋ ዕድሉን አጥቷል፤ በአንጻሩ 6 ግቦችን አግብቶ ከእንግሊዝ ጋር ግማሽ ፍጻሜ የደረሰው ሃሪ ኬን አሸናፊ ሆኗል። የዚህ ሕግ ብቸኛው ልዩነት የ1994ቱ ኦሌግ ሳሌንኮ ሲሆን፣ ሩሲያ ከምድቧ ባትሻገርም በካሜሩን ላይ በምድብ ጨዋታ 5 ግቦችን (በድምሩ 6 ግቦች) በማስቆጠር ሀገሩ ከመመለሱ በፊት የወርቅ ጫማውን አረጋግጦ ነበር።
በክለብ ደረጃ የሚታይ ስኬትም ለዓለም ዋንጫው ትልቅ መነሻ ነው። ጀርመናዊው ቶማስ ሙለር በ2010 ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያቀና ለሀገሩ አንድም ግብ አግብቶ ባያውቅም፣ በባየር ሙኒክ ስኬታማ የውድድር ዓመት አሳልፎ መምጣቱ በዓለም ዋንጫው የወርቅ ጫማ እንዲያሸንፍ ረድቶታል። ታሪክ እንደሚጠቅሰው ክለባቸው ከምርጥ አራት ውጪ ሆኖ የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አግቢ በመሆን ያጠናቀቁ ተጫዋቾች በታሪክ ሁለት ብቻ ናቸው። ግብ ሲገጣጠም ደግሞ ፊፋ አሸናፊውን ለመለየት አሲስትን የሚቆጥር ሲሆን፣ በ2010 ሙለር፣ ቪያ፣ ስናይደር እና ፎርላን እኩል 5 ግቦች በነበራቸው ወቅት ሙለር በ3 አሲስት አሸንፏል። አሲስትም እኩል ከሆነ ደግሞ አነስተኛ ደቂቃ የተጫወተው ተጫዋች የወርቅ ጫማውን በበላይነት ይወስዳል።
የ2026ቱ የወርቅ ጫማ ፉክክርም እጅግ የበረታ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ማንም ተጫዋች የወርቅ ጫማን ከሁለት ጊዜ በላይ አላሸነፈም፤ ዘንድሮ ግን ምባፔ እና ሃሪ ኬን ይህንን ታሪክ ለመጻፍ ትልቅ ዕድል አላቸው። ምባፔ በማጣሪያው 4 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን ጠንካራዋ ፈረንሳይ ሩቅ ስለምትጓዝ ተመራጭ ነው። የ32 ዓመቱ ሃሪ ኬን ዕድሜው ቢገፋም፣ በዘንድሮው የክለብ ቆይታው 54 ግቦችን አስቆጥሮ በታላቅ ብቃት ላይ ይገኛል። በሌላ በኩል የ38 ዓመቱ ሜሲ ካቢኔ ውስጥ 8 የባሎን ዶር ክብሮች ቢኖሩም የወርቅ ጫማ ባለመኖሩ ይህ ውድድር የመጨረሻ ዕድሉ ነው። አርጀንቲና ከእርሱ በተጨማሪ በኮፓ አሜሪካ 2024 የወርቅ ጫማ ያሸነፈውን ላውታሮ ማርቲኔዝን እና በአትሌቲኮ ማድሪድ ድንቅ ጊዜ ያሳለፈውን ጁሊያን አልቫሬዝን ይዛ ትቀርባለች። የስፔኑ ታዳጊ ላሚን ያማል፣ የ41 ዓመቱ ፖርቱጋላዊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ለማንችስተር ሲቲ 26 የሊግ ግቦችን ያገባው ኤርሊንግ ሀላንድ፣ በሪያል ማድሪድ ድንቅ ጊዜ ያሳለፈው ቪኒሽየስ ጁኒየር እና ፈረንሳዊው ኡስማን ዴምቤሌም ዋናዎቹ ተፎካካሪዎች ናቸው።
ከነዚህ ዋና ዋና ተገማቾች በተጨማሪ ያልተጠበቁ ድብቅ አደጋዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ። የዩሮ 2024 የፍጻሜ አሸናፊ ግብ ያስቆጠረው የስፔኑ ሚኬል ኦያርዛባል በማጣሪያው ድንቅ ብቃት ያሳየ ሲሆን፣ ስዊድናውያኑ አሌክሳንደር ኢሳክ እና ቪክቶር ዮከረስ፣ እንዲሁም ብራዚላውያኑ ራፊንሃ እና ኢጎር ቲያጎ አስገራሚ ተፎካካሪዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ለባየር ሙኒክ 22 ግቦችን እና 30 አሲስቶችን ያደረገው ፈረንሳዊው ማይክል ኦሊሴ እና በማንኛውም ሰዓት ጨዋታን መለወጥ የሚችለው የናፖሊው አጥቂ ቤልጅየማዊው ሮሜሉ ሉካኩ የውድድሩ አስገራሚ ድብቅ ዕጩዎች ተብለው ተጠቅሰዋል።
ለእንግሊዛዊው ኮከብ ሃሪ ኬን ጥሩ ያልሆነ ዜና አለ ታሪክ እንደሚነግረን በ30 ዓመት እና ከዚያ በላይ ዕድሜ ላይ ሆኖ የወርቅ ጫማ ማሸነፍ እጅግ ከባድ ነው። ይህ ክስተት በታሪክ የተመዘገበው አንድ ጊዜ ብቻ ሲሆን፣ በ1998ቱ የፈረንሳይ ዓለም ዋንጫ ክሮኤሺያዊው ዳቮር ሱከር በ30 ዓመቱ 6 ግቦችን በማስቆጠር ነበር ይህን ተአምር ያሳካው። ሱከር ለዚህ ሕግ ብቸኛው ልዩ ማሳያ ሲሆን፣ በአማካይ የወርቅ ጫማ አሸናፊዎች ዕድሜ 24.7 ዓመት ነው። በ2022 ምባፔ በ24 ዓመቱ 35 ዓመት የነበረውን ሊዮኔል ሜሲን በአንድ ግብ ብቻ በልጦ ማሸነፉ የዕድሜ አማካዩን በትንሹ ዝቅ አድርጎታል። በታሪክ በለጋ ዕድሜው ይህን ክብር ያገኘው ሀንጋሪያዊው ፍሎሪያን አልበርት ሲሆን፣ በ1962ቱ የቺሊ ውድድር ላይ በ20 ዓመት ከስምንት ወር ዕድሜው አሸንፏል። ይህንን ታሪካዊ ሪከርድ ለመስበር የስፔኑ የ18 ዓመት ታዳጊ ላሚን ያማል በአሁኑ ወቅት በጉጉት ዓይኑን ጥሏል።
በሌላ በኩል ደግሞ ብቻውን የሚያጨበጭብ እጅ የለምና አንድ ስኬታማ አጥቂ ጥሩ የኳስ አቅርቦት እና ቡድኑ በውድድሩ ሩቅ መጓዝ መቻል ያስፈልገዋል። አምስት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያነሳችው ብራዚል፣ ከ1938ቱ ሊዮኒዳስ እስከ 2002ቱ ሮናልዶ ድረስ ስድስት አደገኛ የወርቅ ጫማ አሸናፊዎችን ማፍራቷ አያስገርምም። በምድብ ጨዋታዎች ብዙ ግብ ማስቆጠር ጥሩ ጅምር ቢሆንም፣ ቡድንዎ ወደ ጥሎ ማለፍ ካላደገ ግን ትልቅ ኪሳራ ነው። ለምሳሌ በ2018ቱ የሩሲያ ውድድር ክርስቲያኖ ሮናልዶ በምድብ ጨዋታዎች 4 ግቦችን ቢያገባም ፖርቱጋል በ16ቱ ዙር በመውደቋ ዕድሉን አጥቷል፤ በአንጻሩ 6 ግቦችን አግብቶ ከእንግሊዝ ጋር ግማሽ ፍጻሜ የደረሰው ሃሪ ኬን አሸናፊ ሆኗል። የዚህ ሕግ ብቸኛው ልዩነት የ1994ቱ ኦሌግ ሳሌንኮ ሲሆን፣ ሩሲያ ከምድቧ ባትሻገርም በካሜሩን ላይ በምድብ ጨዋታ 5 ግቦችን (በድምሩ 6 ግቦች) በማስቆጠር ሀገሩ ከመመለሱ በፊት የወርቅ ጫማውን አረጋግጦ ነበር።
በክለብ ደረጃ የሚታይ ስኬትም ለዓለም ዋንጫው ትልቅ መነሻ ነው። ጀርመናዊው ቶማስ ሙለር በ2010 ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያቀና ለሀገሩ አንድም ግብ አግብቶ ባያውቅም፣ በባየር ሙኒክ ስኬታማ የውድድር ዓመት አሳልፎ መምጣቱ በዓለም ዋንጫው የወርቅ ጫማ እንዲያሸንፍ ረድቶታል። ታሪክ እንደሚጠቅሰው ክለባቸው ከምርጥ አራት ውጪ ሆኖ የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አግቢ በመሆን ያጠናቀቁ ተጫዋቾች በታሪክ ሁለት ብቻ ናቸው። ግብ ሲገጣጠም ደግሞ ፊፋ አሸናፊውን ለመለየት አሲስትን የሚቆጥር ሲሆን፣ በ2010 ሙለር፣ ቪያ፣ ስናይደር እና ፎርላን እኩል 5 ግቦች በነበራቸው ወቅት ሙለር በ3 አሲስት አሸንፏል። አሲስትም እኩል ከሆነ ደግሞ አነስተኛ ደቂቃ የተጫወተው ተጫዋች የወርቅ ጫማውን በበላይነት ይወስዳል።
የ2026ቱ የወርቅ ጫማ ፉክክርም እጅግ የበረታ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ማንም ተጫዋች የወርቅ ጫማን ከሁለት ጊዜ በላይ አላሸነፈም፤ ዘንድሮ ግን ምባፔ እና ሃሪ ኬን ይህንን ታሪክ ለመጻፍ ትልቅ ዕድል አላቸው። ምባፔ በማጣሪያው 4 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን ጠንካራዋ ፈረንሳይ ሩቅ ስለምትጓዝ ተመራጭ ነው። የ32 ዓመቱ ሃሪ ኬን ዕድሜው ቢገፋም፣ በዘንድሮው የክለብ ቆይታው 54 ግቦችን አስቆጥሮ በታላቅ ብቃት ላይ ይገኛል። በሌላ በኩል የ38 ዓመቱ ሜሲ ካቢኔ ውስጥ 8 የባሎን ዶር ክብሮች ቢኖሩም የወርቅ ጫማ ባለመኖሩ ይህ ውድድር የመጨረሻ ዕድሉ ነው። አርጀንቲና ከእርሱ በተጨማሪ በኮፓ አሜሪካ 2024 የወርቅ ጫማ ያሸነፈውን ላውታሮ ማርቲኔዝን እና በአትሌቲኮ ማድሪድ ድንቅ ጊዜ ያሳለፈውን ጁሊያን አልቫሬዝን ይዛ ትቀርባለች። የስፔኑ ታዳጊ ላሚን ያማል፣ የ41 ዓመቱ ፖርቱጋላዊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ለማንችስተር ሲቲ 26 የሊግ ግቦችን ያገባው ኤርሊንግ ሀላንድ፣ በሪያል ማድሪድ ድንቅ ጊዜ ያሳለፈው ቪኒሽየስ ጁኒየር እና ፈረንሳዊው ኡስማን ዴምቤሌም ዋናዎቹ ተፎካካሪዎች ናቸው።
ከነዚህ ዋና ዋና ተገማቾች በተጨማሪ ያልተጠበቁ ድብቅ አደጋዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ። የዩሮ 2024 የፍጻሜ አሸናፊ ግብ ያስቆጠረው የስፔኑ ሚኬል ኦያርዛባል በማጣሪያው ድንቅ ብቃት ያሳየ ሲሆን፣ ስዊድናውያኑ አሌክሳንደር ኢሳክ እና ቪክቶር ዮከረስ፣ እንዲሁም ብራዚላውያኑ ራፊንሃ እና ኢጎር ቲያጎ አስገራሚ ተፎካካሪዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ለባየር ሙኒክ 22 ግቦችን እና 30 አሲስቶችን ያደረገው ፈረንሳዊው ማይክል ኦሊሴ እና በማንኛውም ሰዓት ጨዋታን መለወጥ የሚችለው የናፖሊው አጥቂ ቤልጅየማዊው ሮሜሉ ሉካኩ የውድድሩ አስገራሚ ድብቅ ዕጩዎች ተብለው ተጠቅሰዋል።
19 hours ago
♦️በሠንዳፋ አንድ አትሌት በጥይት ተመቶ ህይወቱ ማለፉ ብዙዎችን አስደንግጧል
👉አትሌቲክሱ ላይ የተፈጠረው ምንድነው?
👉ከአትሌት በተተኮሠ ጥይት የአንድ አትሌት ህይወት መጥፋቱ ተሠምቷል
👉ገዳዩ አትሌት ሟቹን አትሌት በጥይት ተኩሶ ገድሎ ሊያመልጥ ሲል በቦታው የነበሩ አርሶ አደሮች ተቷኩሰው ወደ ከተማ ሳይገባ ተይዟል
👉ገዳዩ አትሌት ከነመሳሪያው እጅ ከፍንጅ ተይዞ በቁጥጥር ስር ውሏል
👉 ለግድያ ያበቃቸው ምክንያት እየተጣራ ነው።
👉የገዳይም የሟችም ማንነት እንገልፃለን
👉በቀጣይ የሚመለከታቸውን አነጋግረን ሙሉውንና ትክክለኛውን መረጃ ይዘን እንቀርባለን
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
👉አትሌቲክሱ ላይ የተፈጠረው ምንድነው?
👉ከአትሌት በተተኮሠ ጥይት የአንድ አትሌት ህይወት መጥፋቱ ተሠምቷል
👉ገዳዩ አትሌት ሟቹን አትሌት በጥይት ተኩሶ ገድሎ ሊያመልጥ ሲል በቦታው የነበሩ አርሶ አደሮች ተቷኩሰው ወደ ከተማ ሳይገባ ተይዟል
👉ገዳዩ አትሌት ከነመሳሪያው እጅ ከፍንጅ ተይዞ በቁጥጥር ስር ውሏል
👉 ለግድያ ያበቃቸው ምክንያት እየተጣራ ነው።
👉የገዳይም የሟችም ማንነት እንገልፃለን
👉በቀጣይ የሚመለከታቸውን አነጋግረን ሙሉውንና ትክክለኛውን መረጃ ይዘን እንቀርባለን
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
21 hours ago
የም/ቤቱ 23ኛ መደበኛ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል
#ethiopia | ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ያካሄዳል።
ምክር ቤቱ በነገው ስብሰባው በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር መካከል የተደረጉ የብድር ስምምነቶችን ለማፅደቅ የወጡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ በአንጎላ ሪፐብሊክ፣ በባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ እንዲሁም በኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥታት መካከል የተፈረሙትን የሁለትዮሽ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆች አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያፀድቃል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በተያያዘም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም የኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያፀድቃል።
በመጨረሻም ምክር ቤቱ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ፣ የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ፣ የምግብ ሥርዓትና ሥርዓተ ምግብ፣ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ እንዲሁም የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች ይመራል ያለው መናኸሪያ ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ያካሄዳል።
ምክር ቤቱ በነገው ስብሰባው በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር መካከል የተደረጉ የብድር ስምምነቶችን ለማፅደቅ የወጡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ በአንጎላ ሪፐብሊክ፣ በባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ እንዲሁም በኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥታት መካከል የተፈረሙትን የሁለትዮሽ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆች አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያፀድቃል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በተያያዘም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም የኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያፀድቃል።
በመጨረሻም ምክር ቤቱ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ፣ የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ፣ የምግብ ሥርዓትና ሥርዓተ ምግብ፣ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ እንዲሁም የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች ይመራል ያለው መናኸሪያ ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
21 hours ago
ይህንን ያውቃሉ❓❓
የሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ በወረዳ ጽሕፈት ቤቶቹ የሚሰጣቸውን የኩነት (የልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ሞትና ጉዲፈቻ) ማስረጃዎችን የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት ተገልጋዮች ይዘው መቅረብ የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎችንና ደጋፊ ሰነዶችን እንደሚከተለው ያሳውቃል።
ለእያንዳንዱ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ልዩ ቅድመ ሁኔታዎች
1. የልደት ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ፦ በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የልደት ማስረጃ
አገልግሎቱ የሚሰጠው ከሁለቱ አንዱ ወላጅ በአካል ሲገኝ ነው (የወላጆች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ያስፈልጋል)።
ምዝገባው በሞግዚትነት ከሆነ የፍርድ ቤት የሞግዚትነት ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ፦ ባለጉዳዩ በአካል መቅረብ አለበት። በአካል መቅረብ ካልቻለ፣ ጉዳዩን የሚገልጽ ልዩ ውክልና ከወካይና ተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ጋር ማቅረብ ይኖርበታል።
2. የጋብቻ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የጋብቻ ማስረጃ መያዝ።
ለግልባጭ ወይም ለእርማት አገልግሎት፦ የተጋቢዎች ሁለት ሁለት (2) ጉርድ ፎቶግራፍ።
በውክልና የሚጠየቅ ከሆነ (ለእርማት፣ ዕድሳትና ግልባጭ)፦ ባልና ሚስት ጉዳዩን በግልጽ የሚያሳይ ውክልና፣ የወካዮች እና የተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ወይም የታደሰ የመኖሪያ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው።
3. የፍቺ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የፍቺ ማስረጃ
የህግ አስገዳጅነቱ የተረጋገጠ የፍርድ ቤት የፍቺ ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
4. የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
በወረዳ የተመዘገበ የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት እና የፍርድ ቤት ውሳኔ ሰነድ
ጉዲፈቻ አድራጊዎች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በመያዝ በአካል መቅረብ አለባቸው።
ጉዳዩ በውክልና ከሆነ፣ይህንኑ የሚያስረዳ ልዩ ውክልና መቅረብ አለበት።
5. የሞት ማስረጃ ለማረጋገጥ
በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የሞት ማስረጃ የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት
ከሟች ጋር አብሮ ይኖር የነበረ ሰው፣ እርሱ ከሌለ የሟች የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመዶች፣ እነዚህም ከሌሉ የቅርብ ጎረቤት ወይም ስለሟቹ መሞት የሚያውቅ ማንኛውም ሰው የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በማቅረብ ማስመዝገብና ማረጋገጥ ይችላል።
ሟች የውጭ ሀገር ዜጋ ከሆነ ከሆስፒታል የተሰጠ የማሳወቂያ ወረቀት መቅረብ አለበት።
ማሳሰቢያ፡- ለሁሉም ከላይ ለተዘረዘሩት የኩነት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስፈልግ ደጋፊ ሰነድ
• የታደሰ ብሔራዊ መታወቂያ / የታደሰ ፓስፖርት / የትውልደ ኢትዮጵያ የውጭ ዜግነት መታወቂያ (የቢጫ ካርድ)።
• ከዝቅተኛው አስተዳደር ጽ/ቤት መደበኛ ነዋሪነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ / የስደተኛነት ማስረጃ / የመኖሪያ ፈቃድ።
• ከሚሰራበት መስሪያ ቤት ባልደረባነቱንና ዜግነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ ከመስሪያ ቤቱ መታወቂያ ጋር / የመከላከያ ሰራዊት ከሆነ የመከላከያ ሰራዊት መታወቂያ መያዝ
• የጠፋ ሰርተፍኬት ግልባጭ ለመውሰድ፦ ከፖሊስ የተሰጠ የጠፋ ሰነድ ማረጋገጫ ማቅረብ ግዴታ ነው።
• ከወረዳ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከወረዳው ስለመውጣታቸው የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ያስፈልጋቸዋል።
• ከክፍለ ከተማ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከሰነዱ በስተጀርባ የማረጋገጫ ማህተም ማረፍ ይኖርበታል።
• ከውጭ ሀገር የሚመጣ ውክልና፦ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በፌደራል ሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ መረጋገጥ አለበት።
Seledadotio
Seledadotio
የሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ በወረዳ ጽሕፈት ቤቶቹ የሚሰጣቸውን የኩነት (የልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ሞትና ጉዲፈቻ) ማስረጃዎችን የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት ተገልጋዮች ይዘው መቅረብ የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎችንና ደጋፊ ሰነዶችን እንደሚከተለው ያሳውቃል።
ለእያንዳንዱ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ልዩ ቅድመ ሁኔታዎች
1. የልደት ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ፦ በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የልደት ማስረጃ
አገልግሎቱ የሚሰጠው ከሁለቱ አንዱ ወላጅ በአካል ሲገኝ ነው (የወላጆች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ያስፈልጋል)።
ምዝገባው በሞግዚትነት ከሆነ የፍርድ ቤት የሞግዚትነት ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ፦ ባለጉዳዩ በአካል መቅረብ አለበት። በአካል መቅረብ ካልቻለ፣ ጉዳዩን የሚገልጽ ልዩ ውክልና ከወካይና ተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ጋር ማቅረብ ይኖርበታል።
2. የጋብቻ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የጋብቻ ማስረጃ መያዝ።
ለግልባጭ ወይም ለእርማት አገልግሎት፦ የተጋቢዎች ሁለት ሁለት (2) ጉርድ ፎቶግራፍ።
በውክልና የሚጠየቅ ከሆነ (ለእርማት፣ ዕድሳትና ግልባጭ)፦ ባልና ሚስት ጉዳዩን በግልጽ የሚያሳይ ውክልና፣ የወካዮች እና የተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ወይም የታደሰ የመኖሪያ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው።
3. የፍቺ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የፍቺ ማስረጃ
የህግ አስገዳጅነቱ የተረጋገጠ የፍርድ ቤት የፍቺ ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
4. የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
በወረዳ የተመዘገበ የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት እና የፍርድ ቤት ውሳኔ ሰነድ
ጉዲፈቻ አድራጊዎች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በመያዝ በአካል መቅረብ አለባቸው።
ጉዳዩ በውክልና ከሆነ፣ይህንኑ የሚያስረዳ ልዩ ውክልና መቅረብ አለበት።
5. የሞት ማስረጃ ለማረጋገጥ
በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የሞት ማስረጃ የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት
ከሟች ጋር አብሮ ይኖር የነበረ ሰው፣ እርሱ ከሌለ የሟች የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመዶች፣ እነዚህም ከሌሉ የቅርብ ጎረቤት ወይም ስለሟቹ መሞት የሚያውቅ ማንኛውም ሰው የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በማቅረብ ማስመዝገብና ማረጋገጥ ይችላል።
ሟች የውጭ ሀገር ዜጋ ከሆነ ከሆስፒታል የተሰጠ የማሳወቂያ ወረቀት መቅረብ አለበት።
ማሳሰቢያ፡- ለሁሉም ከላይ ለተዘረዘሩት የኩነት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስፈልግ ደጋፊ ሰነድ
• የታደሰ ብሔራዊ መታወቂያ / የታደሰ ፓስፖርት / የትውልደ ኢትዮጵያ የውጭ ዜግነት መታወቂያ (የቢጫ ካርድ)።
• ከዝቅተኛው አስተዳደር ጽ/ቤት መደበኛ ነዋሪነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ / የስደተኛነት ማስረጃ / የመኖሪያ ፈቃድ።
• ከሚሰራበት መስሪያ ቤት ባልደረባነቱንና ዜግነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ ከመስሪያ ቤቱ መታወቂያ ጋር / የመከላከያ ሰራዊት ከሆነ የመከላከያ ሰራዊት መታወቂያ መያዝ
• የጠፋ ሰርተፍኬት ግልባጭ ለመውሰድ፦ ከፖሊስ የተሰጠ የጠፋ ሰነድ ማረጋገጫ ማቅረብ ግዴታ ነው።
• ከወረዳ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከወረዳው ስለመውጣታቸው የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ያስፈልጋቸዋል።
• ከክፍለ ከተማ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከሰነዱ በስተጀርባ የማረጋገጫ ማህተም ማረፍ ይኖርበታል።
• ከውጭ ሀገር የሚመጣ ውክልና፦ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በፌደራል ሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ መረጋገጥ አለበት።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 day ago
♦️የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የሚያዘጋጀው ዓመታዊው የግማሽ ማራትን ውድድር እሁድ ይካሄዳል
♦️የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ በዴንማርክ ኮፐንሃገን አለም አቀፍ ውድድር ላይ ይሳተፋሉ
እ.ኤ.አ አቆጣጠር ሴፔቴምበር 20 ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው የአለም አትሌቲክስ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌቶች በወንድም በሴቶችም የሚመረጡበት የአዲስ አበባ ግማሽ ማራቶን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል።
ጅማሬውንና ፍፃሜውን መስቀል አደባባይ የሚያደርገውና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ የሚያከናውነው 19ኛው የ21 ኪ.ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር በርካታ አትሌቶች በወንድም በሴትም የሚሳተፉበት ሲሆን በውድድሩ የተሻሉ ሆነው የሚያጠናቅቁ አትሌትች በሁለቱም ፃታ ሀገራቸውን ወክለው ሴፕቴምበር 20 በዴንማርክ ኮፐንሃገን የግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ የሚያሳትፋቸውን ትኬት ይቆርጣሉ።
የአለም የግማሽ ማራቶን(የጎዳና ውድድርን)በሁለቱም ፆታ ሪከርዱን የያዙት ኢትዮጵያዊያን አቴሌቶች ሲሆኑ በወንዶች አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ 57:30፣በሴቶች ደግሞ ለተሠንበት ግደይ 1:02:52 በሆነ ሠዓት በመግባትና በማሸነፍ የሪከርዱ ባለቤቶች ሆነዋል።
የአለም ግማሽ ማራቶን በዴንማርክ ኮፐንሃገን ሲካሄድ ከግማሽ ማራቶኑ በተጨማሪ የ5ኪ.ሜ እና የ1 ማይልስ ወይም የ1,609ኪ.ሜ ውድድርም እንደሚካሄድ ከተያዘው ፕሮግራም ለመረዳት ተችሏል።
ለሴፕቴምበር 20 የዴንማርክ ኮፐንሃገን የአለም አቀፍ ግማሽ ማራቶን የሚያሳልፈውን ትኬት የሚያስገኘው የአዲስ አበባው ግማሽ ማራቶን ውድድርን አስመልክቶ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የፊታችን ዓርብ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሠጥ ቀይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
♦️የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ በዴንማርክ ኮፐንሃገን አለም አቀፍ ውድድር ላይ ይሳተፋሉ
እ.ኤ.አ አቆጣጠር ሴፔቴምበር 20 ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው የአለም አትሌቲክስ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌቶች በወንድም በሴቶችም የሚመረጡበት የአዲስ አበባ ግማሽ ማራቶን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል።
ጅማሬውንና ፍፃሜውን መስቀል አደባባይ የሚያደርገውና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ የሚያከናውነው 19ኛው የ21 ኪ.ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር በርካታ አትሌቶች በወንድም በሴትም የሚሳተፉበት ሲሆን በውድድሩ የተሻሉ ሆነው የሚያጠናቅቁ አትሌትች በሁለቱም ፃታ ሀገራቸውን ወክለው ሴፕቴምበር 20 በዴንማርክ ኮፐንሃገን የግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ የሚያሳትፋቸውን ትኬት ይቆርጣሉ።
የአለም የግማሽ ማራቶን(የጎዳና ውድድርን)በሁለቱም ፆታ ሪከርዱን የያዙት ኢትዮጵያዊያን አቴሌቶች ሲሆኑ በወንዶች አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ 57:30፣በሴቶች ደግሞ ለተሠንበት ግደይ 1:02:52 በሆነ ሠዓት በመግባትና በማሸነፍ የሪከርዱ ባለቤቶች ሆነዋል።
የአለም ግማሽ ማራቶን በዴንማርክ ኮፐንሃገን ሲካሄድ ከግማሽ ማራቶኑ በተጨማሪ የ5ኪ.ሜ እና የ1 ማይልስ ወይም የ1,609ኪ.ሜ ውድድርም እንደሚካሄድ ከተያዘው ፕሮግራም ለመረዳት ተችሏል።
ለሴፕቴምበር 20 የዴንማርክ ኮፐንሃገን የአለም አቀፍ ግማሽ ማራቶን የሚያሳልፈውን ትኬት የሚያስገኘው የአዲስ አበባው ግማሽ ማራቶን ውድድርን አስመልክቶ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የፊታችን ዓርብ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሠጥ ቀይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
1 day ago
ዛሬ የአርሰናል እግር ኳስ ክለብን እና በኢትዮጵያ የሚገኙ እልል ያሉ ላደጋፊዎቹ ያለንን አድናቆት እና አክብሮት የምንገልጸበትን ይህን ድንቅ ዝግጅት በመደገፋችን እጅግ ኩራት ይሰማናል። አርሰናል በአለም ላይ ካሉ እውቅ የእግር ኳስ ክለቦች አንዱ ሲሆን፣ በአገራችንም ለክለቡ ጥልቅ ፍቅር ያላቸው ታማኝ ደጋፊዎች አሉት።
ከኢትዮጵያ ብራንዶች በግንባር ቀደም ከሚጠሩት መሃል እንደመሆናችን፣ ሐበሻ በእግር ኳስ፣ በመዝናኛ እና የስፖርት አድናቂዎችን በአንድነት የሚያሰባስበው የዚህ ዝግጅት አካል በመሆኗናችን ክብር ይሰማናል።
በሐበሻ የላቀ ጥራትን፣ ከኢትዮጵያ ባህል፣ ቅርስ እና እሴቶች ጋር ያለንን ጠንካራ ትስስር ይበልጥ እያጠበቅን፣ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ምርቶች እና የማይረሱ ልምዶችን ለደንበኞቻችን እንዲሁም ለስፖርት ቤተሰቡ በሙሉ በማቅረባችን እንኮራለን።
የጋራ ፍላጎቶችን እና መገለጫዎችን በማክበር እና ማሕበረሰቡን የሚያቀራርቡ ሁኔታዎችን በመፍጠር ረገድ ታላላቅ ብራንዶች ከምርት ያለፈ ፋይዳ እንዳላቸው እናምናለን። እንደዚህ ባሉ አጋርነቶች አማካኝነትም ተጠቃሚዎቻችንን የሚያነሳሱ፣ የሚያሳትፉ እና የሚያዝናኑ መድረኮችን መደገፋችንን እንቀጥላለን።
ለዝግጅቱ አዘጋጆች፣ ለአርሰናል ደጋፊዎች እና ዛሬ ከእኛ ጋር ለተገኙት በሙሉ እናመሰግናለን።
ሐበሻ – በኢትዮጵያዊነታችን የምንኮራ፣ ለጥራት የቆምን፣ በፈጠራ የምንመራ፣ እና ልዩ ድባብ በመፍጠር ሰዎችን በአንድነት ለማዝናናት በቁርጠኛነት የተነሳን።
ከኢትዮጵያ ብራንዶች በግንባር ቀደም ከሚጠሩት መሃል እንደመሆናችን፣ ሐበሻ በእግር ኳስ፣ በመዝናኛ እና የስፖርት አድናቂዎችን በአንድነት የሚያሰባስበው የዚህ ዝግጅት አካል በመሆኗናችን ክብር ይሰማናል።
በሐበሻ የላቀ ጥራትን፣ ከኢትዮጵያ ባህል፣ ቅርስ እና እሴቶች ጋር ያለንን ጠንካራ ትስስር ይበልጥ እያጠበቅን፣ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ምርቶች እና የማይረሱ ልምዶችን ለደንበኞቻችን እንዲሁም ለስፖርት ቤተሰቡ በሙሉ በማቅረባችን እንኮራለን።
የጋራ ፍላጎቶችን እና መገለጫዎችን በማክበር እና ማሕበረሰቡን የሚያቀራርቡ ሁኔታዎችን በመፍጠር ረገድ ታላላቅ ብራንዶች ከምርት ያለፈ ፋይዳ እንዳላቸው እናምናለን። እንደዚህ ባሉ አጋርነቶች አማካኝነትም ተጠቃሚዎቻችንን የሚያነሳሱ፣ የሚያሳትፉ እና የሚያዝናኑ መድረኮችን መደገፋችንን እንቀጥላለን።
ለዝግጅቱ አዘጋጆች፣ ለአርሰናል ደጋፊዎች እና ዛሬ ከእኛ ጋር ለተገኙት በሙሉ እናመሰግናለን።
ሐበሻ – በኢትዮጵያዊነታችን የምንኮራ፣ ለጥራት የቆምን፣ በፈጠራ የምንመራ፣ እና ልዩ ድባብ በመፍጠር ሰዎችን በአንድነት ለማዝናናት በቁርጠኛነት የተነሳን።
1 day ago
የምርጫ ቦርድ ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም አካል ራሱን አሸናፊ አድርጎ ከመግለጽ ይቆጠብ":-ኢሰመጉ‼️
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ባወጣው የምርጫ መታዘብ ቅድመ መግለጫ ላይ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጥብቅ ማሳሰቢያ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም ግለሰብ፣ የፖለቲካ ድርጅት ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ጊዜያዊ ውጤት በማጋራት ማኅበረሰቡን ከማደናገር እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
የምልከታ ስፋት፦ኢሰመጉ ባሰማራቸው 433 ታዛቢዎች አማካኝነት ከ800 በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን ተከታትሏል።
⚠️ የተስተዋሉ ዋና ዋና ተግዳሮቶች፦
* የአዲሱ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥልት መጀመሩ የሚበረታታ ቢሆንም፣ የአስፈጻሚዎች ሥልጠና ማነስ ለመራጮች መጨናነቅና ለሰዓት መራዘም ምክንያት ሆኗል።
* በበርካታ አካባቢዎች የትራንስፖርት መቋረጥ፣ በአዲስ አበባ የሰልፍ አስተባባሪዎች ማነስ እና በመራጮች ላይ የደረሰ የእንግልት ሰዓት።
* በሐዋሳና አካባቢው በሚገኙ ውስን ጣቢያዎች የምርጫ አስፈጻሚዎች በሚስጥራዊ ድምፅ መስጫ ቦታ በመግባት የሥነ-ልቦና ጫና ማድረጋቸው እና ያልተመረጡ ወረቀቶችን ወደ ሳጥን ማስገባት የመሳሰሉ የነፃነት መብትን የገደቡ ክስተቶች መታየታቸው።
✅ በበጎ ጎን የተነሱ ነጥቦች፦
* የመራጮች ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ በቂ የቁሳቁስ አቅርቦት እና በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች የጎላ የጸጥታ መደፍረስ ሳይኖር ሂደቱ መጠናቀቁ።
"ኢሰመጉ ምርጫ ቦርድ በአንጻራዊነት ስኬታማና ሰላማዊ ምርጫ ማከናወኑን በመግለጽ ዕውቅና የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይ ግን የተስተዋሉ ችግሮችን በዝርዝር ለይቶ እንዲያርም ጥሪ አቅርቧል።"
Seledadotio
Seledadotio
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ባወጣው የምርጫ መታዘብ ቅድመ መግለጫ ላይ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጥብቅ ማሳሰቢያ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም ግለሰብ፣ የፖለቲካ ድርጅት ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ጊዜያዊ ውጤት በማጋራት ማኅበረሰቡን ከማደናገር እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
የምልከታ ስፋት፦ኢሰመጉ ባሰማራቸው 433 ታዛቢዎች አማካኝነት ከ800 በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን ተከታትሏል።
⚠️ የተስተዋሉ ዋና ዋና ተግዳሮቶች፦
* የአዲሱ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥልት መጀመሩ የሚበረታታ ቢሆንም፣ የአስፈጻሚዎች ሥልጠና ማነስ ለመራጮች መጨናነቅና ለሰዓት መራዘም ምክንያት ሆኗል።
* በበርካታ አካባቢዎች የትራንስፖርት መቋረጥ፣ በአዲስ አበባ የሰልፍ አስተባባሪዎች ማነስ እና በመራጮች ላይ የደረሰ የእንግልት ሰዓት።
* በሐዋሳና አካባቢው በሚገኙ ውስን ጣቢያዎች የምርጫ አስፈጻሚዎች በሚስጥራዊ ድምፅ መስጫ ቦታ በመግባት የሥነ-ልቦና ጫና ማድረጋቸው እና ያልተመረጡ ወረቀቶችን ወደ ሳጥን ማስገባት የመሳሰሉ የነፃነት መብትን የገደቡ ክስተቶች መታየታቸው።
✅ በበጎ ጎን የተነሱ ነጥቦች፦
* የመራጮች ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ በቂ የቁሳቁስ አቅርቦት እና በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች የጎላ የጸጥታ መደፍረስ ሳይኖር ሂደቱ መጠናቀቁ።
"ኢሰመጉ ምርጫ ቦርድ በአንጻራዊነት ስኬታማና ሰላማዊ ምርጫ ማከናወኑን በመግለጽ ዕውቅና የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይ ግን የተስተዋሉ ችግሮችን በዝርዝር ለይቶ እንዲያርም ጥሪ አቅርቧል።"
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ማንቸስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን አማካይ ኤደርሰንን ከአታላንታ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሱ ተረጋገጠ። ለሳምንታት የዘለቀው ድርድር በተሳካ ሁኔታ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ዩናይትድ ለ26 ዓመቱ ተጫዋች 40.5 ሚሊዮን ዩሮ ቋሚ ክፍያ እና 4.5 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ማበረታቻዎችን በማካተት በድምሩ የ45 ሚሊዮን ዩሮ ጥቅል ለአታላንታ ለመክፈል ተስማምቷል። ይህ ዝውውር በመጪው የውድድር ዘመን የክለቡ አሰልጣኝ ለሆኑት ማይክል ካሪክ የክረምቱ የመጀመሪያው ፈራሚ ያደርገዋል።
ኤደርሰን በኦልድ ትራፎርድ እስከ ሰኔ 2030 ድረስ የሚያቆየውን የአራት ዓመት ኮንትራት ለመፈረም በግል ጥቅማጥቅሞች ላይ የተስማማ ሲሆን፣ ውሉን ለተጨማሪ 12 ወራት የማራዘም አማራጭም በስምምነቱ ውስጥ ተካቷል። ተጫዋቹ የህክምና ምርመራውን ካጠናቀቀ በኋላ በሀምሌ ወር መጀመሪያ ላይ ዝውውሩ በይፋ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።
ኤደርሰን በ2027 ነፃ ወኪል የመሆን ዕድል ስለነበረው፣ ሌሎች ታላላቅ ክለቦች ቢፈልጉትም ቅድሚያ ለዩናይትድ በመስጠቱ ክለቡ ከዚህ ቀደም በገበያው ይገመት ከነበረው ዋጋ በጣም ባነሰ መልኩ ሊያገኘው ችሏል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በ2026-27 የውድድር ዘመን በቻምፒየንስ ሊግ የሚሳተፍ በመሆኑ፣ እንዲሁም ካሴሚሮ ክለቡን መልቀቁን ተከትሎ ክፍት የሆነውን የአማካይ ክፍል ለማጠናከር ይህ ዝውውር ወሳኝ ጅምር ሆኖለታል። በቀጣይም በዚሁ የሜዳ ክፍል ላይ ተጨማሪ ተጫዋቾችን ያመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የስፖርት ተንታኞች ማርክ ኬሪ እና ላውሪ ዊትዌል እንዳስነበቡት፣ኤደርሰን በሜዳ ላይ ልክ እንደ "ፓክ-ማን" የጨዋታ አደጋዎችን በማጽዳት፣ ኳሶችን በማቋረጥ እና መልሶ በመቀማት ከፍተኛ ብቃት ያለው ተጫዋች ነው። ኳስን በመቆጣጠር እና አጫጭር ኳሶችን በማቀበል ከሀገሩ ልጅ ካሴሚሮ የተሻለ ብቃት እንዳለው የሚነገርለት ሲሆን፣ ኳስን ወደ ፊት ይዘው ለሚሮጡ አጥቂዎችም ጥሩ አቀባይ ነው። በሁለቱም የግብ ክልሎች መካከል እየተመላለሰ የሚጫወተው ይህ ብራዚላዊ አሰልጣኞች እጅግ የሚወዱት ዓይነት ተጫዋች ነው። ሁልጊዜ የዜና ርዕስ ባይሆንም፣ በሜዳ ላይ ለሚኖረው የቡድን ስብስብ ወሳኝ ሞተር በመሆን የቡድን አጋሮቹ በሙሉ አቅማቸው እንዲጫወቱ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ኤደርሰን በኦልድ ትራፎርድ እስከ ሰኔ 2030 ድረስ የሚያቆየውን የአራት ዓመት ኮንትራት ለመፈረም በግል ጥቅማጥቅሞች ላይ የተስማማ ሲሆን፣ ውሉን ለተጨማሪ 12 ወራት የማራዘም አማራጭም በስምምነቱ ውስጥ ተካቷል። ተጫዋቹ የህክምና ምርመራውን ካጠናቀቀ በኋላ በሀምሌ ወር መጀመሪያ ላይ ዝውውሩ በይፋ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።
ኤደርሰን በ2027 ነፃ ወኪል የመሆን ዕድል ስለነበረው፣ ሌሎች ታላላቅ ክለቦች ቢፈልጉትም ቅድሚያ ለዩናይትድ በመስጠቱ ክለቡ ከዚህ ቀደም በገበያው ይገመት ከነበረው ዋጋ በጣም ባነሰ መልኩ ሊያገኘው ችሏል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በ2026-27 የውድድር ዘመን በቻምፒየንስ ሊግ የሚሳተፍ በመሆኑ፣ እንዲሁም ካሴሚሮ ክለቡን መልቀቁን ተከትሎ ክፍት የሆነውን የአማካይ ክፍል ለማጠናከር ይህ ዝውውር ወሳኝ ጅምር ሆኖለታል። በቀጣይም በዚሁ የሜዳ ክፍል ላይ ተጨማሪ ተጫዋቾችን ያመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የስፖርት ተንታኞች ማርክ ኬሪ እና ላውሪ ዊትዌል እንዳስነበቡት፣ኤደርሰን በሜዳ ላይ ልክ እንደ "ፓክ-ማን" የጨዋታ አደጋዎችን በማጽዳት፣ ኳሶችን በማቋረጥ እና መልሶ በመቀማት ከፍተኛ ብቃት ያለው ተጫዋች ነው። ኳስን በመቆጣጠር እና አጫጭር ኳሶችን በማቀበል ከሀገሩ ልጅ ካሴሚሮ የተሻለ ብቃት እንዳለው የሚነገርለት ሲሆን፣ ኳስን ወደ ፊት ይዘው ለሚሮጡ አጥቂዎችም ጥሩ አቀባይ ነው። በሁለቱም የግብ ክልሎች መካከል እየተመላለሰ የሚጫወተው ይህ ብራዚላዊ አሰልጣኞች እጅግ የሚወዱት ዓይነት ተጫዋች ነው። ሁልጊዜ የዜና ርዕስ ባይሆንም፣ በሜዳ ላይ ለሚኖረው የቡድን ስብስብ ወሳኝ ሞተር በመሆን የቡድን አጋሮቹ በሙሉ አቅማቸው እንዲጫወቱ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ፈረንሳያዊው ተከላካይ ኢብራሂማ ኮናቴ ወደ ስፔኑ ታላቅ ክለብ ሪያል ማድሪድ የሚያደርገው ዝውውር መገባደጃው ላይ መድረሱን ምንጮች አረጋገጡ። ባለፉት 48 ሰዓታት ውስጥ በተደረጉት የድርድር ሒደቶች ከፍተኛ መሻሻል የታየ ሲሆን፣ በቅርቡ 27ኛ ዓመት የልደት በዓሉን ያከበረው ኮናቴ በአራት ዓመት ኮንትራት እና በፊርማ ክፍያ ጉዳዮች ላይ ከስምምነት ለመድረስ ጥቂት ዝርዝር ጉዳዮች ብቻ ቀርተውታል።
የማድሪድ ኃላፊዎች በፓሪስ የተወለደውን ይህንን ተከላካይ ለማስፈረም ከወራት በፊት ጀምሮ ፍላጎት ያሳዩ ቢሆንም፣ የተጫዋቹ ቀዳሚ ምርጫ ግን በሊቨርፑል መቆየት ነበር። ይሁን እንጂ ከክለቡ ጋር አዲስ ኮንትራት ለመፈራረም ባለመቻሉ፣ እ.ኤ.አ. በ2021 ከሌይፕዚግ ተነስቶ ያቀናበትን አንፊልድን በነጻ ዝውውር ለመልቀቅ ተገዷል።
ኮናቴ ሊቨርፑልን እንደሚለቅ በተረጋገጠበት ወቅት ሪያል ማድሪድ ፈጣን ጥያቄ በማቅረብ ቀዳሚው ቢሆንም፣ ባየር ሙኒክን፣ ባርሴሎናን እና የሳውዲ ክለቦችን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ክለቦች የተከላካዩን ፊርማ ለማግኘት ጥረት አድርገው እንደነበር ምንጮች ጠቁመዋል።
ይህ ዝውውር ዕውን የሚሆን ከሆነ፣ ኮናቴ በሳንቲያጎ በርናባው ከሚገኙት የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አጋሮቹ ኪሊያን ምባፔ፣ ኦሬልየን ቹአሜኒ፣ ኤድዋርዶ ካማቪንጋ እና ፈርላንድ ሜንዲ ጋር ዳግም ይገናኛል። ተጫዋቹ በዓለማችን ትልቁን ክለብ ለመቀላቀል መቃረቡ እጅግ እንዳስደሰተው የተገለጸ ሲሆን፣ በቀጣዩ ሳምንት ከፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ጋር ወደ ዓለም ዋንጫው ከማምራቱ በፊት የዝውውር ሒደቱ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ማየት ይፈልጋል።
የማድሪድ ኃላፊዎች በፓሪስ የተወለደውን ይህንን ተከላካይ ለማስፈረም ከወራት በፊት ጀምሮ ፍላጎት ያሳዩ ቢሆንም፣ የተጫዋቹ ቀዳሚ ምርጫ ግን በሊቨርፑል መቆየት ነበር። ይሁን እንጂ ከክለቡ ጋር አዲስ ኮንትራት ለመፈራረም ባለመቻሉ፣ እ.ኤ.አ. በ2021 ከሌይፕዚግ ተነስቶ ያቀናበትን አንፊልድን በነጻ ዝውውር ለመልቀቅ ተገዷል።
ኮናቴ ሊቨርፑልን እንደሚለቅ በተረጋገጠበት ወቅት ሪያል ማድሪድ ፈጣን ጥያቄ በማቅረብ ቀዳሚው ቢሆንም፣ ባየር ሙኒክን፣ ባርሴሎናን እና የሳውዲ ክለቦችን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ክለቦች የተከላካዩን ፊርማ ለማግኘት ጥረት አድርገው እንደነበር ምንጮች ጠቁመዋል።
ይህ ዝውውር ዕውን የሚሆን ከሆነ፣ ኮናቴ በሳንቲያጎ በርናባው ከሚገኙት የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አጋሮቹ ኪሊያን ምባፔ፣ ኦሬልየን ቹአሜኒ፣ ኤድዋርዶ ካማቪንጋ እና ፈርላንድ ሜንዲ ጋር ዳግም ይገናኛል። ተጫዋቹ በዓለማችን ትልቁን ክለብ ለመቀላቀል መቃረቡ እጅግ እንዳስደሰተው የተገለጸ ሲሆን፣ በቀጣዩ ሳምንት ከፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ጋር ወደ ዓለም ዋንጫው ከማምራቱ በፊት የዝውውር ሒደቱ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ማየት ይፈልጋል።
2 days ago
በአዲስ አበባ ስታዲየም :
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።
በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።
በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።
ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።
የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።
በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።
በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።
ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።
የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 days ago
የኢትዮጵያ መርከብ የሆርሙዝ ሰርጥን በሰላም መሻገሯ ተሰማ
በመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ምክንያት ከፍተኛ ስጋት በነበረበት የሆርሙዝ ሰርጥ አካባቢ፣ የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ንብረት የሆነችው “አሶሳ” መርከብ ከሆርሙዝ ሰርጥ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው ኮርፋካን ወደብ በመድረስ ወሳኝ የሕክምና እና የንግድ ጭነቶችን በተሳካ ሁኔታ ጭና ወደ ሀገሯ ተመልሳለች።
ይህ ስኬት የኢትዮጵያን ባሕረኞች ቁርጠኝነት እና የኢትዮጵያን የባሕር ሎጅስቲክስ ብቃት በተግባር ያሳየ ነው ተብሎለታለ።
Seledadotio
Seledadotio
በመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ምክንያት ከፍተኛ ስጋት በነበረበት የሆርሙዝ ሰርጥ አካባቢ፣ የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ንብረት የሆነችው “አሶሳ” መርከብ ከሆርሙዝ ሰርጥ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው ኮርፋካን ወደብ በመድረስ ወሳኝ የሕክምና እና የንግድ ጭነቶችን በተሳካ ሁኔታ ጭና ወደ ሀገሯ ተመልሳለች።
ይህ ስኬት የኢትዮጵያን ባሕረኞች ቁርጠኝነት እና የኢትዮጵያን የባሕር ሎጅስቲክስ ብቃት በተግባር ያሳየ ነው ተብሎለታለ።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች
ኢትዮጵያ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀውን የተበታተነ የንግድ አስተዳደር ሥርዓት ለመቀየርና ለላኪዎች፣ አስመጪዎችና ባለሀብቶች ግልጽና ሊተነበይ የሚችል አሠራር ለመፍጠር የሚያስችላትን የመጀመሪያውን ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች።
በተጠናቀቀው ሳምንት በሚኒስትሮች ምክርቤት የጸደቀው ይህ ፖሊሲ፣ ለበርካታ አስርት ዓመታት የሀገሪቱን የንግድ ዘርፍ ተወዳዳሪነት ሲያዳክሙና ለብልሹ አሠራር በር ሲከፍቱ የቆዩትን እርስ በርሳቸው የሚጋጩ መመሪያዎችንና አሠራሮችን ሙሉ በሙሉ የሚተካ ነው።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ እንደገለጹት፣ አዲሱ ማዕቀፍ በተደጋጋሚ ለሚቀያየሩ መመሪያዎች እውቅና የማይሰጥ በመሆኑ በንግድ ቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ መረጋጋት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል።
ፖሊሲው የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከለመደው ያልተቀነባበሩ የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት ጥገኝነት በማውጣት፣ ወደ ማኑፋክቸሪንግ፣ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶች፣ አገልግሎቶችና ቱሪዝም ዘርፎች ላይ እንዲያተኩር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የንግድ ልማት አገልግሎትና ፖሊሲ ጥበቃ ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ ካሳሁን ማሞ፣ ምክር ቤቱ እንዲህ ዓይነት ሁሉን አቀፍ ፖሊሲ እንዲወጣ ለረጅም ጊዜ ሲወተውት እንደነበር አስታውሰዋል። ፖሊሲው የግል ባለሀብቱ በልበ ሙሉነት እንዲያቅድና ኢንቨስት እንዲያደርግ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
Via capital
ኢትዮጵያ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀውን የተበታተነ የንግድ አስተዳደር ሥርዓት ለመቀየርና ለላኪዎች፣ አስመጪዎችና ባለሀብቶች ግልጽና ሊተነበይ የሚችል አሠራር ለመፍጠር የሚያስችላትን የመጀመሪያውን ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች።
በተጠናቀቀው ሳምንት በሚኒስትሮች ምክርቤት የጸደቀው ይህ ፖሊሲ፣ ለበርካታ አስርት ዓመታት የሀገሪቱን የንግድ ዘርፍ ተወዳዳሪነት ሲያዳክሙና ለብልሹ አሠራር በር ሲከፍቱ የቆዩትን እርስ በርሳቸው የሚጋጩ መመሪያዎችንና አሠራሮችን ሙሉ በሙሉ የሚተካ ነው።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ እንደገለጹት፣ አዲሱ ማዕቀፍ በተደጋጋሚ ለሚቀያየሩ መመሪያዎች እውቅና የማይሰጥ በመሆኑ በንግድ ቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ መረጋጋት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል።
ፖሊሲው የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከለመደው ያልተቀነባበሩ የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት ጥገኝነት በማውጣት፣ ወደ ማኑፋክቸሪንግ፣ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶች፣ አገልግሎቶችና ቱሪዝም ዘርፎች ላይ እንዲያተኩር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የንግድ ልማት አገልግሎትና ፖሊሲ ጥበቃ ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ ካሳሁን ማሞ፣ ምክር ቤቱ እንዲህ ዓይነት ሁሉን አቀፍ ፖሊሲ እንዲወጣ ለረጅም ጊዜ ሲወተውት እንደነበር አስታውሰዋል። ፖሊሲው የግል ባለሀብቱ በልበ ሙሉነት እንዲያቅድና ኢንቨስት እንዲያደርግ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
Via capital
Sponsored by
Surafel
2 days ago
የአርሰናል የፕሪሚየር ሊግ ድል በአዲስ አበባ "WE CHAMPIONS 2026" ታሪካዊ ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው
#fastmereja | አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ ያነሳውን የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ለማክበር ግንቦት 29/2018 በአዲስ አበባ ስታዲየም ታሪካዊ የእግር ኳስና የመዝናኛ ፌስቲቫል ይካሄዳል። በቫርደስ ኢንተርቴይመንት የተዘጋጀውና በአዋሽ ባንክ (አዋሽብር ፕሮ) ዋና ስፖንሰርነት የሚከናወነው ይህ ዝግጅት፣ ከ30 ሺህ በላይ ታዳሚዎችን እና ዓለም አቀፍ እንግዶችን በአንድ ላይ ያሰባስባል።
ዝግጅቱ የክለቡን ድል ከመዘከር ባለፈ፣ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ አቅሟን ለዓለም የምታሳይበት መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል። በስፍራውም ታዋቂ ድምፃውያን እና የስፖርት ቤተሰቦች ይታደማሉ።
በክስተቱ ላይ የቀድሞው የአርሰናል እና የኮትዲቯር ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቡዌ በልዩ እንግድነት ይገኛል። ከእርሱ በተጨማሪ በዓለም ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያዎች አንዱ የሆነው AFTV ልዑካን ቡድን ወደ ኢትዮጵያ ይመጣል። በቡድኑ ውስጥ፡
ሊ ዳጅስ (Lee Judges) – አቅራቢ (ዩናይትድ ኪንግደም)
ሴሲል ጂ ቶማስ (Cecil Jee Thomas) – አቅራቢ (ዩናይትድ ኪንግደም)
ጀረሚ (Jeremy) – ዲጂታል ይዘት ፈጣሪ (ደቡብ አፍሪካ) ይገኙበታል።
በዚህ ዝግጀት ላይ ከ 10 በላይ የሆኑ እውቅ እና ወጣት ኢትዮጵያዊ ድምፃዊያን የሙዚቃ ስራቸው እንደሚያቀረቡ ተገልጾ ከነዚህም መካከል ታደለ ሮባ ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ) ፣ ሳሚ ዳን ፣ አስጌ ዴንዳሾ ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ሮቤል ሚዲቅሳ ፣ ዮ ማሪዮስ ፣ ሚክ ዋን ፣ አማኑኤል የማነ ፣ አዲስ ሙላት እንዲሁም እውቁ የዳስሆል/የአፍሮቢትስ ሙዚቃ ተጫዋቹ ፍራንኪዬ ዲ እና ሌሎችም ድምፃዊያን የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ::
የዝግጅቱ ብቸኛ የትኬት መሸጫ መድረክ "አዋሽብር ፕሮ" ነው። ደጋፊዎች ትኬታቸውን በሚከተሉት መንገዶች ማግኘት ይችላሉ፦
በአዋሽብር ፕሮ አፕሊኬሽን
በአዋሽ ባንክ ቅርንጫፎች (ከ1,000 በላይ ቅርንጫፎች)
በአዋሽ ብር ፕሮ ኤጀንቶች
በአዲስ አበባ ስታዲየም በተዘጋጁ ጊዜያዊ መሸጫ ጣቢያዎች (ከግንቦት 25 እስከ ግንቦት 29)
ከግዢው ጋር በተያያዘ፣ ትኬታቸውን በቅድሚያ ለሚገዙ ደጋፊዎች የ"WE CHAMPIONS 2026" ይፋዊ ማሊያ የማግኘት ዕድል ተመቻችቷል።
#fastmereja | አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ ያነሳውን የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ለማክበር ግንቦት 29/2018 በአዲስ አበባ ስታዲየም ታሪካዊ የእግር ኳስና የመዝናኛ ፌስቲቫል ይካሄዳል። በቫርደስ ኢንተርቴይመንት የተዘጋጀውና በአዋሽ ባንክ (አዋሽብር ፕሮ) ዋና ስፖንሰርነት የሚከናወነው ይህ ዝግጅት፣ ከ30 ሺህ በላይ ታዳሚዎችን እና ዓለም አቀፍ እንግዶችን በአንድ ላይ ያሰባስባል።
ዝግጅቱ የክለቡን ድል ከመዘከር ባለፈ፣ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ አቅሟን ለዓለም የምታሳይበት መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል። በስፍራውም ታዋቂ ድምፃውያን እና የስፖርት ቤተሰቦች ይታደማሉ።
በክስተቱ ላይ የቀድሞው የአርሰናል እና የኮትዲቯር ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቡዌ በልዩ እንግድነት ይገኛል። ከእርሱ በተጨማሪ በዓለም ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያዎች አንዱ የሆነው AFTV ልዑካን ቡድን ወደ ኢትዮጵያ ይመጣል። በቡድኑ ውስጥ፡
ሊ ዳጅስ (Lee Judges) – አቅራቢ (ዩናይትድ ኪንግደም)
ሴሲል ጂ ቶማስ (Cecil Jee Thomas) – አቅራቢ (ዩናይትድ ኪንግደም)
ጀረሚ (Jeremy) – ዲጂታል ይዘት ፈጣሪ (ደቡብ አፍሪካ) ይገኙበታል።
በዚህ ዝግጀት ላይ ከ 10 በላይ የሆኑ እውቅ እና ወጣት ኢትዮጵያዊ ድምፃዊያን የሙዚቃ ስራቸው እንደሚያቀረቡ ተገልጾ ከነዚህም መካከል ታደለ ሮባ ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ) ፣ ሳሚ ዳን ፣ አስጌ ዴንዳሾ ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ሮቤል ሚዲቅሳ ፣ ዮ ማሪዮስ ፣ ሚክ ዋን ፣ አማኑኤል የማነ ፣ አዲስ ሙላት እንዲሁም እውቁ የዳስሆል/የአፍሮቢትስ ሙዚቃ ተጫዋቹ ፍራንኪዬ ዲ እና ሌሎችም ድምፃዊያን የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ::
የዝግጅቱ ብቸኛ የትኬት መሸጫ መድረክ "አዋሽብር ፕሮ" ነው። ደጋፊዎች ትኬታቸውን በሚከተሉት መንገዶች ማግኘት ይችላሉ፦
በአዋሽብር ፕሮ አፕሊኬሽን
በአዋሽ ባንክ ቅርንጫፎች (ከ1,000 በላይ ቅርንጫፎች)
በአዋሽ ብር ፕሮ ኤጀንቶች
በአዲስ አበባ ስታዲየም በተዘጋጁ ጊዜያዊ መሸጫ ጣቢያዎች (ከግንቦት 25 እስከ ግንቦት 29)
ከግዢው ጋር በተያያዘ፣ ትኬታቸውን በቅድሚያ ለሚገዙ ደጋፊዎች የ"WE CHAMPIONS 2026" ይፋዊ ማሊያ የማግኘት ዕድል ተመቻችቷል።
2 days ago
ቴክቦል (Teqball)፦ ተወዳጅነትን እያገኘ የመጣው አዲሱ የኳስ ስፖርት
*****************
ቴክቦል የእግር ኳስ ክህሎትን ከጠረጴዛ ቴኒስ ሕግጋት ጋር አጣምሮ የያዘ፣ ኳሱ በእጅ ሳይነካ በታጠፈ ጠረጴዛ ላይ የሚጫወቱት አስደሳች ስፖርት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም ተወዳጅነትን እያገኘ የመጣ የስፖርት አይነት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት በይፋ ያስመረቁት ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለው የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ይህንን የስፖርት ዓይነት ያካተተ ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ይህ ስፖርት ለመጀመሪያ ጊዜ እ.አ.አ በ2012 በሃንጋሪ የተዋወቀ የስፖርት አይነት ሲሆን፣ ጋቦር ቦርሳኒ፣ ቪክቶር ሁሳር እና ጂዮርጂ ጋትያን በተባሉ ሦስት ግለሰቦች አማካኝነት እንደተጀመረ ይገለፃል።
የቴክቦል ዋነኛው መለያ ባህሪ "ቴክቦርድ" (Teqboard) ተብሎ የሚጠራውና መሃሉ ከፍ ብሎ ጫፎቹ ወደ ታች የታጠፈ ልዩ ጠረጴዛ መሆኑ ነው። ይህ የጠረጴዛው ቅርጽ ኳሱ በየትኛውም አቅጣጫ እንዲነጥርና ጨዋታው ፍጥነትና ከፍተኛ ክህሎት እንዲኖረው ያደርጋል።
የስፖርቱ ሕጎች በጣም ቀላልና ለማንም ሰው ለመረዳት ምቹ ሲሆኑ፣ በሁለት ተቃራኒ ተጫዋቾች (አንድ ለአንድ) ወይም በቡድን (ሁለት ለሁለት) ሊጫወቱት የሚችሉት ስፖርት ነው።
ልክ እንደ እግር ኳስ ሁሉ፣ ኳሱን በእጅ መንካት በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን፤ ተጫዋቾች ኳሱን በጭንቅላታቸው፣ በደረታቸው፣ በትከሻቸው ወይም በእግራቸው መምታት ይችላሉ።
አንድ ተጫዋች ወይም ቡድን ኳሱ ወደ ተቃራኒው ወገን ከመሻገሩ በፊት ቢበዛ ሦስት ጊዜ ብቻ የመንካት መብት አለው።
በአንድ የሰውነት ክፍል (በእግር ብቻ፣ በደረት ብቻ አልያም በጭንቅላት ብቻ) በተከታታይ ሁለትጊዜ ኳሱን መንካት አይፈቀድም። ይህም ተጫዋቾች የተለያዩ የሰውነት ክፍሎቻቸውን እንዲጠቀሙና የተለየ ብቃት እንዲያሳዩ ያስገድዳቸዋል።
በአሁኑ ወቅት ቴክቦል በዓለም አቀፍ ደረጃ በፌዴሬሽን የሚመራ ሲሆን፣ ወደ ኦሎምፒክ ስፖርቶች እንዲካተትም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። እንደ ሮናልዲንሆ ያሉ ታዋቂ የዓለም እግር ኳስ ተጫዋቾች የስፖርቱ አምባሳደር በመሆን እያስተዋወቁት ይገኛሉ።
ስፖርቱ ምንም ዓይነት የአካል ንክኪ ስለሌለውና በትንሽ ቦታ ላይ ሊከናወን ስለሚችል ጉዳትን የሚቀንስ ከመሆኑም በላይ ለተጫዋቾች ትኩረትን፣ ቅልጥፍናን እና የኳስ ቁጥጥርን ለማሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ አለው።
በተጨማሪም የልብ ጤናን የሚያሻሽል፣ አእምሮን የሚያነቃቃ እንዲሁም የአይን፣ የእግር እና የአእምሮ ቅንጅትን በማሳደግ ፈጣን ውሳኔ የመስጠት ብቃትን የሚያዳብር ስፖርት ነው፤ ዕድሜና ጾታ ሳይለይ ሁሉም ሰው ሊጫወተው ስለሚችል፣ የአእምሮ ውጥረትን ለመቀነስና ማኅበራዊ ግንኙነትን ለማጠናከር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
በዘረንቶስ ሰለሞን
Ethiopian Broadcasting Corporation #teqboard #teqball
*****************
ቴክቦል የእግር ኳስ ክህሎትን ከጠረጴዛ ቴኒስ ሕግጋት ጋር አጣምሮ የያዘ፣ ኳሱ በእጅ ሳይነካ በታጠፈ ጠረጴዛ ላይ የሚጫወቱት አስደሳች ስፖርት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም ተወዳጅነትን እያገኘ የመጣ የስፖርት አይነት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት በይፋ ያስመረቁት ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለው የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ይህንን የስፖርት ዓይነት ያካተተ ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ይህ ስፖርት ለመጀመሪያ ጊዜ እ.አ.አ በ2012 በሃንጋሪ የተዋወቀ የስፖርት አይነት ሲሆን፣ ጋቦር ቦርሳኒ፣ ቪክቶር ሁሳር እና ጂዮርጂ ጋትያን በተባሉ ሦስት ግለሰቦች አማካኝነት እንደተጀመረ ይገለፃል።
የቴክቦል ዋነኛው መለያ ባህሪ "ቴክቦርድ" (Teqboard) ተብሎ የሚጠራውና መሃሉ ከፍ ብሎ ጫፎቹ ወደ ታች የታጠፈ ልዩ ጠረጴዛ መሆኑ ነው። ይህ የጠረጴዛው ቅርጽ ኳሱ በየትኛውም አቅጣጫ እንዲነጥርና ጨዋታው ፍጥነትና ከፍተኛ ክህሎት እንዲኖረው ያደርጋል።
የስፖርቱ ሕጎች በጣም ቀላልና ለማንም ሰው ለመረዳት ምቹ ሲሆኑ፣ በሁለት ተቃራኒ ተጫዋቾች (አንድ ለአንድ) ወይም በቡድን (ሁለት ለሁለት) ሊጫወቱት የሚችሉት ስፖርት ነው።
ልክ እንደ እግር ኳስ ሁሉ፣ ኳሱን በእጅ መንካት በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን፤ ተጫዋቾች ኳሱን በጭንቅላታቸው፣ በደረታቸው፣ በትከሻቸው ወይም በእግራቸው መምታት ይችላሉ።
አንድ ተጫዋች ወይም ቡድን ኳሱ ወደ ተቃራኒው ወገን ከመሻገሩ በፊት ቢበዛ ሦስት ጊዜ ብቻ የመንካት መብት አለው።
በአንድ የሰውነት ክፍል (በእግር ብቻ፣ በደረት ብቻ አልያም በጭንቅላት ብቻ) በተከታታይ ሁለትጊዜ ኳሱን መንካት አይፈቀድም። ይህም ተጫዋቾች የተለያዩ የሰውነት ክፍሎቻቸውን እንዲጠቀሙና የተለየ ብቃት እንዲያሳዩ ያስገድዳቸዋል።
በአሁኑ ወቅት ቴክቦል በዓለም አቀፍ ደረጃ በፌዴሬሽን የሚመራ ሲሆን፣ ወደ ኦሎምፒክ ስፖርቶች እንዲካተትም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። እንደ ሮናልዲንሆ ያሉ ታዋቂ የዓለም እግር ኳስ ተጫዋቾች የስፖርቱ አምባሳደር በመሆን እያስተዋወቁት ይገኛሉ።
ስፖርቱ ምንም ዓይነት የአካል ንክኪ ስለሌለውና በትንሽ ቦታ ላይ ሊከናወን ስለሚችል ጉዳትን የሚቀንስ ከመሆኑም በላይ ለተጫዋቾች ትኩረትን፣ ቅልጥፍናን እና የኳስ ቁጥጥርን ለማሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ አለው።
በተጨማሪም የልብ ጤናን የሚያሻሽል፣ አእምሮን የሚያነቃቃ እንዲሁም የአይን፣ የእግር እና የአእምሮ ቅንጅትን በማሳደግ ፈጣን ውሳኔ የመስጠት ብቃትን የሚያዳብር ስፖርት ነው፤ ዕድሜና ጾታ ሳይለይ ሁሉም ሰው ሊጫወተው ስለሚችል፣ የአእምሮ ውጥረትን ለመቀነስና ማኅበራዊ ግንኙነትን ለማጠናከር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
በዘረንቶስ ሰለሞን
Ethiopian Broadcasting Corporation #teqboard #teqball
2 days ago
የእንጦጦ-ቀጨኔ መድኃኔዓለም የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቋል።
22.25 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው ይህ ፕሮጀክት፣ የተጎዱ አካባቢዎችን ወደ ማራኪ እና የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉ ለምለም አረንጓዴ ሥፍራዎች የቀየረ ነው።
የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ምሰሶዎች፦
ሥነ-ምህዳርን መልሶ ማቋቋም እና የከተማ ግብርና፦
ፕሮጀክቱ በባሕር ዛፍ ምክንያት የተጎዳ 36 ሄክታር መሬትን ጨምሮ፣ በአጠቃላይ 438 ሄክታር የተጎዳ መሬትን አክሞ ዳግም አቋቁሟል። በተጨማሪም የከተማ ግብርና እና ብዝሃ-ሕይወትን ለማጠናከር አዲስ የ9.5 ሄክታር የፍራፍሬ ፓርክ እና 210 ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን አካቷል።
የውሃ ማጣሪያ እና መሠረተ-ልማት፦
በእንጦጦ-ቀጨኔ ኮሪደር ላይ 39 የወንዝ መገደቢያዎችን እና ሦስት የወንዝ ውሃ ማጣሪያ ሥርዓቶችን በመገንባት የአካባቢ ጥበቃና ዘላቂነት እንዲጠናከር ተደርጓል።
የአረንጓዴ ትራንስፖርት አማራጮች እና ቱሪዝም ፦
አረንጓዴ የትራንስፖርት አማራጮችንና መዝናኛን በማስፋፋት፣ ፕሮጀክቱ 19.4 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገዶችን፣ 7.7 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መስመሮችን እና 4 ኪሎ ሜትር የተራራ መውጫ (የእግር ጉዞ) መንገዶችን ያካተተ ሲሆን፣ ይህም ጤናማ፣ ምቹ እና ንቁ ማኅበረሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
#pmoethiopia #ethiopiadelivers
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ከሶማሌላንድ ጋር ያለውን ግንኙነት እና ትብብር ማሻሻል በሚችልባቸው መስኮች ዙሪያ የተዘጋጀ ዝርዝር ሪፖርት ለኮንግረስ ቀረበ። የ2026 የብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የበጀት አዋጅን መሠረት አድርጎ የወጣው ይህ ሪፖርት፣ አሜሪካ የሶማሊያን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት (ሶማሌላንድን ጨምሮ) እንደምትቀበል በድጋሚ ያረጋገጠ ሲሆን፣ በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ ከሶማሌላንድ ባለስልጣናት ጋር አዎንታዊ እና ገንቢ ግንኙነቷን እንደምትቀጥል አስታውቋል። ሪፖርቱ ግንኙነቱ ሊሻሻልባቸው የሚችሉ ሦስት ዋና ዋና መስኮችን በዝርዝር አስቀምጧል፡-
በአፍሪካ ቀንድ ያለው የጸጥታ ሁኔታ አሁንም ውስብስብ መሆኑን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ የጽንፈኛ ኃይሎች ስጋት እና የቀጠናው አለመግባባቶች አሳሳቢ እንደሆኑ ገልጿል። ይሁን እንጂ ሶማሌላንድ ከየመን እና ከባቢ ኤል-ማንደብ ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ ያላት ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ፣ ከቀይ ባህር እስከ ህንድ ውቅያኖስ ያለውን የንግድ እና ወታደራዊ የባህር ላይ ጉዞ ነፃነት ለማረጋገጥ ወሳኝ አጋር ያደርጋታል። በተጨማሪም የሁቲ ታጣቂዎች እና የአልቃይዳ ትልቁ ክንፍ ከሆነው አል-ሸባብ ጋር ያላቸውን ትስስር ለመቆጣጠር እና የሽብርተኞችን እንቅስቃሴ ለመግታት የሶማሌላንድ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ አመቺ መሆኑ ተገልጿል። ለዚህም ሲባል የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ (AFRICOM) ከሶማሌላንድ ባለስልጣናት ጋር መደበኛ ግንኙነት እያደረገ መሆኑ ታውቋል።
በሞቃዲሾ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በጸጥታ፣ በሰብአዊ እርዳታ እና በኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ ለመምከር ወደ ሶማሌላንድ መደበኛ ጉብኝቶችን እንደሚያደርግ ሪፖርቱ ጠቅሷል። ሆኖም የአሜሪካ መንግሥት ሠራተኞች ወደ ስፍራው የሚያደርጉት ጉዞ ልክ እንደሌላው የሶማሊያ ክፍል ጥብቅ የጸጥታ መስፈርቶችን የሚጠይቅ ነው። በመሆኑም የንግድ ያልሆኑ አውሮፕላኖችን እና ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ የጸጥታ ጥበቃዎችን መጠቀም ግድ ይላል። ይህንን ሒደት ለማቀላጠፍ ኤምባሲው ከአፍሪካ ዕዝ ወታደራዊ ሀብቶች ጋር በቅርበት በማስተባበር እየሰራ ይገኛል።
የሶማሌላንድ ባለስልጣናት አሜሪካ በማዕድን፣ በመሰረተ ልማት፣ በንግድ እና በኢኮኖሚ ዕድገት ዘርፎች ኢንቨስት እንድታደርግ ሰፊ ማበረታቻ እያደረጉ መሆኑን ሪፖርቱ አስፍሯል። የሶማሌላንድ ወደቦች በቀጠናው ላሉ ሌሎች መጨናነቅ ለሚታይባቸው ወደቦች እንደ አማራጭ ሊያገለግሉ እንደሚችሉ የተገለጸ ሲሆን፣ እየተገነባ ያለው የበርበራ አውሮፕላን ማረፊያ እና ወደብ ለሶማሌላንድም ሆነ የባህር በር ለሌላት ኢትዮጵያ የንግድ እና የትራንስፖርት ማዕከል እየሆነ መምጣቱ፣ ለአሜሪካ የኢንቨስትመንት እና የንግድ ዕድሎችን ሊፈጥር እንደሚችል ተገምቷል።
ነገር ግን የቀጠናው የጸጥታ ስጋት፣ በሶማሌላንድ ፖለቲካዊ ቁመና ላይ ያለው አለመግባባት እና ባለስልጣናቱ ከሶማሊያ ብሔራዊ መንግሥት ጋር ለመተባበር ፈቃደኛ አለመሆናቸው፣ በአሜሪካ የኢንቨስትመንት፣ የባንክ እና የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ከባድ ተግዳሮት እንደፈጠረ ሪፖርቱ አብራርቷል።
በአፍሪካ ቀንድ ያለው የጸጥታ ሁኔታ አሁንም ውስብስብ መሆኑን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ የጽንፈኛ ኃይሎች ስጋት እና የቀጠናው አለመግባባቶች አሳሳቢ እንደሆኑ ገልጿል። ይሁን እንጂ ሶማሌላንድ ከየመን እና ከባቢ ኤል-ማንደብ ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ ያላት ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ፣ ከቀይ ባህር እስከ ህንድ ውቅያኖስ ያለውን የንግድ እና ወታደራዊ የባህር ላይ ጉዞ ነፃነት ለማረጋገጥ ወሳኝ አጋር ያደርጋታል። በተጨማሪም የሁቲ ታጣቂዎች እና የአልቃይዳ ትልቁ ክንፍ ከሆነው አል-ሸባብ ጋር ያላቸውን ትስስር ለመቆጣጠር እና የሽብርተኞችን እንቅስቃሴ ለመግታት የሶማሌላንድ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ አመቺ መሆኑ ተገልጿል። ለዚህም ሲባል የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ (AFRICOM) ከሶማሌላንድ ባለስልጣናት ጋር መደበኛ ግንኙነት እያደረገ መሆኑ ታውቋል።
በሞቃዲሾ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በጸጥታ፣ በሰብአዊ እርዳታ እና በኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ ለመምከር ወደ ሶማሌላንድ መደበኛ ጉብኝቶችን እንደሚያደርግ ሪፖርቱ ጠቅሷል። ሆኖም የአሜሪካ መንግሥት ሠራተኞች ወደ ስፍራው የሚያደርጉት ጉዞ ልክ እንደሌላው የሶማሊያ ክፍል ጥብቅ የጸጥታ መስፈርቶችን የሚጠይቅ ነው። በመሆኑም የንግድ ያልሆኑ አውሮፕላኖችን እና ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ የጸጥታ ጥበቃዎችን መጠቀም ግድ ይላል። ይህንን ሒደት ለማቀላጠፍ ኤምባሲው ከአፍሪካ ዕዝ ወታደራዊ ሀብቶች ጋር በቅርበት በማስተባበር እየሰራ ይገኛል።
የሶማሌላንድ ባለስልጣናት አሜሪካ በማዕድን፣ በመሰረተ ልማት፣ በንግድ እና በኢኮኖሚ ዕድገት ዘርፎች ኢንቨስት እንድታደርግ ሰፊ ማበረታቻ እያደረጉ መሆኑን ሪፖርቱ አስፍሯል። የሶማሌላንድ ወደቦች በቀጠናው ላሉ ሌሎች መጨናነቅ ለሚታይባቸው ወደቦች እንደ አማራጭ ሊያገለግሉ እንደሚችሉ የተገለጸ ሲሆን፣ እየተገነባ ያለው የበርበራ አውሮፕላን ማረፊያ እና ወደብ ለሶማሌላንድም ሆነ የባህር በር ለሌላት ኢትዮጵያ የንግድ እና የትራንስፖርት ማዕከል እየሆነ መምጣቱ፣ ለአሜሪካ የኢንቨስትመንት እና የንግድ ዕድሎችን ሊፈጥር እንደሚችል ተገምቷል።
ነገር ግን የቀጠናው የጸጥታ ስጋት፣ በሶማሌላንድ ፖለቲካዊ ቁመና ላይ ያለው አለመግባባት እና ባለስልጣናቱ ከሶማሊያ ብሔራዊ መንግሥት ጋር ለመተባበር ፈቃደኛ አለመሆናቸው፣ በአሜሪካ የኢንቨስትመንት፣ የባንክ እና የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ከባድ ተግዳሮት እንደፈጠረ ሪፖርቱ አብራርቷል።
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የነበረው የዲፕሎማሲ ድርድር ቢቋረጥም ምንም እንደማይገዳቸው እና የነዳጅ ዋጋ ንረትም ፈጽሞ እንደማያሳስባቸው በአደባባይ መግለጻቸውን ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ ገበያ በከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ ወድቋል። ከዋሽንግተን ዲሲ የወጡ ወቅታዊ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፣ ይህ አስተያየት ከተሰማበት ከጥቂት ደቂቃዎች ጀምሮ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከባድ ስጋት ተፈጥሯል።
ይህ አሳሳቢ ዜና መሰራጨት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የወደፊቱ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ በከፍተኛ ፍጥነት በማሻቀብ አንድ በርሜል ከመቶ ዶላር በላይ የዋጋ ጣሪያን ጥሶ አልፏል። የዛሬው የገበያ ውሎ ሲጀመር ከዚህ ዋጋ በእጅጉ ያነሰ የነበረ ቢሆንም፣ የፖለቲካው ውጥረት እና የትራምፕ ግዴለሽነት የተሞላበት ንግግር የገበያውን መረጋጋት በአጭር ጊዜ ውስጥ አናግቶታል።
ይባስ ብሎም በገበያው ውስጥ ያለውን አሳሳቢ የነዳጅ ክምችት እጥረት በቅርበት የሚከታተሉ አንድ የኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ፣ የአቅርቦት እጥረቱን ተከትሎ የአንድ በርሜል ነዳጅ ዋጋ እስከ መቶ ሃምሳ ወይም መቶ ስልሳ ዶላር ሊደርስ እንደሚችል አስደንጋጭ ትንበያቸውን አስቀምጠዋል። ይህ ዓይነቱ አስፈሪ የዋጋ ንረት እውን ከሆነ፣ የትራንስፖርት እና የማምረቻ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ የከፋ እና በቀላሉ ሊቀለበስ የማይችል የኢኮኖሚ ቀውስ እንደሚያስከትል የዘርፉ ባለሙያዎች አጥብቀው እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።
ይህ አሳሳቢ ዜና መሰራጨት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የወደፊቱ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ በከፍተኛ ፍጥነት በማሻቀብ አንድ በርሜል ከመቶ ዶላር በላይ የዋጋ ጣሪያን ጥሶ አልፏል። የዛሬው የገበያ ውሎ ሲጀመር ከዚህ ዋጋ በእጅጉ ያነሰ የነበረ ቢሆንም፣ የፖለቲካው ውጥረት እና የትራምፕ ግዴለሽነት የተሞላበት ንግግር የገበያውን መረጋጋት በአጭር ጊዜ ውስጥ አናግቶታል።
ይባስ ብሎም በገበያው ውስጥ ያለውን አሳሳቢ የነዳጅ ክምችት እጥረት በቅርበት የሚከታተሉ አንድ የኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ፣ የአቅርቦት እጥረቱን ተከትሎ የአንድ በርሜል ነዳጅ ዋጋ እስከ መቶ ሃምሳ ወይም መቶ ስልሳ ዶላር ሊደርስ እንደሚችል አስደንጋጭ ትንበያቸውን አስቀምጠዋል። ይህ ዓይነቱ አስፈሪ የዋጋ ንረት እውን ከሆነ፣ የትራንስፖርት እና የማምረቻ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ የከፋ እና በቀላሉ ሊቀለበስ የማይችል የኢኮኖሚ ቀውስ እንደሚያስከትል የዘርፉ ባለሙያዎች አጥብቀው እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።
3 days ago
በኬንያ የአሜሪካ የኢቦላ ማቆያ ማዕከል ሊገነባ ነው መባሉ ህዝባዊ ተቃውሞ አስነሳ
#fastmereja በኬንያ ላይኪፒያ ግዛት ናኙኪ ከተማ የአሜሪካ መንግስት ሊገነባው ባቀደው የኢቦላ መከላከያ ማኳያ ማዕከል ላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ዛሬ ሰኞ ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ አደረጉ።
ነዋሪዎቹ የኢቦላ ቫይረስ ተጋላጭ የሆኑ አሜሪካውያንን ለማቆየት በኬንያ አየር ኃይል የጦር ሰፈር ውስጥ ሊገነባ የታቀደውን ባለ 50 አልጋ ማዕከል የተቃወሙት፣ አስቀድሞ ምንም ዓይነት የሕዝብ ውይይትና ምክክር ሳይደረግበት በምስጢር የተወሰነ ነው በሚል ነው።
ነዋሪዎችና ፖሊስ ወደ ግጭት ውስጥ የገቡ ሲሆን የጸጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ሰልፈኞችን ለመበተን መገደዳቸው ታውቋል። በተፈጠረው ግርግር ሳቢያ የናኙኪ ከተማ የንግድና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ የተስተጓጎለ ሲሆን፣ ማዕከሉ ሊገነባ ነው የሚለው ዜና የአካባቢውን የቱሪዝም ዘርፍ ክፉኛ መምታቱ ተገልጿል። በርካታ ዓለም አቀፍ ቱሪስቶች ወደ አካባቢው የሚያደርጉትን የሆቴልና የሆምስቴይ የቦታ ማስያዣ ጥያቄዎችን በጅምላ እየሰረዙ መሆኑን የዘርፉ ባለቤቶች በምሬት ተናግረዋል።
የአካባቢው የንግድ ምክር ቤትና የፖለቲካ መሪዎች መንግስትን በግልጽ እየተቹ ሲሆን፣ የአገሪቱ የጤና ሥርዓት መሰረታዊ ክትባቶችን እንኳን ማቅረብ ባልቻለበት ሁኔታ ዓለም አቀፍ አደጋ የሆነውን የኢቦላ ማቆያ ማዕከል መቀበል አደገኛ መሆኑን ገልጸዋል።
#fastmereja በኬንያ ላይኪፒያ ግዛት ናኙኪ ከተማ የአሜሪካ መንግስት ሊገነባው ባቀደው የኢቦላ መከላከያ ማኳያ ማዕከል ላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ዛሬ ሰኞ ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ አደረጉ።
ነዋሪዎቹ የኢቦላ ቫይረስ ተጋላጭ የሆኑ አሜሪካውያንን ለማቆየት በኬንያ አየር ኃይል የጦር ሰፈር ውስጥ ሊገነባ የታቀደውን ባለ 50 አልጋ ማዕከል የተቃወሙት፣ አስቀድሞ ምንም ዓይነት የሕዝብ ውይይትና ምክክር ሳይደረግበት በምስጢር የተወሰነ ነው በሚል ነው።
ነዋሪዎችና ፖሊስ ወደ ግጭት ውስጥ የገቡ ሲሆን የጸጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ሰልፈኞችን ለመበተን መገደዳቸው ታውቋል። በተፈጠረው ግርግር ሳቢያ የናኙኪ ከተማ የንግድና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ የተስተጓጎለ ሲሆን፣ ማዕከሉ ሊገነባ ነው የሚለው ዜና የአካባቢውን የቱሪዝም ዘርፍ ክፉኛ መምታቱ ተገልጿል። በርካታ ዓለም አቀፍ ቱሪስቶች ወደ አካባቢው የሚያደርጉትን የሆቴልና የሆምስቴይ የቦታ ማስያዣ ጥያቄዎችን በጅምላ እየሰረዙ መሆኑን የዘርፉ ባለቤቶች በምሬት ተናግረዋል።
የአካባቢው የንግድ ምክር ቤትና የፖለቲካ መሪዎች መንግስትን በግልጽ እየተቹ ሲሆን፣ የአገሪቱ የጤና ሥርዓት መሰረታዊ ክትባቶችን እንኳን ማቅረብ ባልቻለበት ሁኔታ ዓለም አቀፍ አደጋ የሆነውን የኢቦላ ማቆያ ማዕከል መቀበል አደገኛ መሆኑን ገልጸዋል።
Sponsored by
Surafel
3 days ago
ሀገሬ ቲቪ አልታገደም!
* የአለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በነፃ ያስተላልፋል
#ethiopia | የሀገሬ ቴሌቪዥን የዓለም ዋንጫን በቀጥታ የማስተላለፍ መብት ማግኘቱን ተከትሎ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ኢቢሲ ጋር በተያያዘ እገዳ ሊጣልበት ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ሙሉ በሙሉ ከእውነት የራቀ መሆኑን የጣቢያው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ንዋይ ይመር ገለጹ።
ዋና ስራ አስፈፃሚው ከታዲያስ አዲስ የሬዲዮ ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት የጣቢያው የስርጭት መብት ሙሉ በሙሉ ህጋዊ በሆነ መንገድ የተገኘ መሆኑን አስረድተዋል።
የስምምነቱን ህጋዊነት በተመለከተም ስርጭቱ የተገኘው የፊፋ ወኪል ከሆነው የፈረንሳዩ ኒው ወርልድ ቲቪ ኩባንያ ጋር በስዊዘርላንድ ህግ መሰረት አለምአቀፋዊ ውል በመፈረም በመሆኑ በሀገር ውስጥ የሚወሩ ወሬዎች ስምምነቱን ሊያስተጓጉሉ እንደማይችሉ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን አቋም በተመለከተም ከባለስልጣኑ ኃላፊዎች ጋር መነጋገራቸውንና ምንም አይነት እገዳን የሚጠቁም ደብዳቤም ሆነ ስሜት አለመኖሩን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ከቶጎ ሎሜ የመጡ የፊፋ የቴክኒክ ባለሙያዎች ለጣቢያው ሰራተኞች የስርጭትና የቴክኒክ ስልጠናዎችን ሰጥተው ማጠናቀቃቸውንና ጣቢያው ስርጭቱን ለመጀመር በሙሉ ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በመጨረሻም ስፖርት አፍቃሪው ማህበረሰብና ስፖንሰር አድራጊ ድርጅቶች በማህበራዊ ሚዲያ በሚለቀቁ ላልተረጋገጡ ወሬዎች ሳይደናገጡ የሀገሬ ቲቪ በኢትዮሳት ሳተላይት አማካኝነት ጨዋታዎቹን በነፃ ወደ እያንዳንዱ ቤት እንደሚያደርስ ዋና ስራ አስፈፃሚው ማረጋገጫ ሰጥተዋል።
#worldcup #hagaretv #sports #football #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
* የአለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በነፃ ያስተላልፋል
#ethiopia | የሀገሬ ቴሌቪዥን የዓለም ዋንጫን በቀጥታ የማስተላለፍ መብት ማግኘቱን ተከትሎ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ኢቢሲ ጋር በተያያዘ እገዳ ሊጣልበት ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ሙሉ በሙሉ ከእውነት የራቀ መሆኑን የጣቢያው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ንዋይ ይመር ገለጹ።
ዋና ስራ አስፈፃሚው ከታዲያስ አዲስ የሬዲዮ ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት የጣቢያው የስርጭት መብት ሙሉ በሙሉ ህጋዊ በሆነ መንገድ የተገኘ መሆኑን አስረድተዋል።
የስምምነቱን ህጋዊነት በተመለከተም ስርጭቱ የተገኘው የፊፋ ወኪል ከሆነው የፈረንሳዩ ኒው ወርልድ ቲቪ ኩባንያ ጋር በስዊዘርላንድ ህግ መሰረት አለምአቀፋዊ ውል በመፈረም በመሆኑ በሀገር ውስጥ የሚወሩ ወሬዎች ስምምነቱን ሊያስተጓጉሉ እንደማይችሉ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን አቋም በተመለከተም ከባለስልጣኑ ኃላፊዎች ጋር መነጋገራቸውንና ምንም አይነት እገዳን የሚጠቁም ደብዳቤም ሆነ ስሜት አለመኖሩን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ከቶጎ ሎሜ የመጡ የፊፋ የቴክኒክ ባለሙያዎች ለጣቢያው ሰራተኞች የስርጭትና የቴክኒክ ስልጠናዎችን ሰጥተው ማጠናቀቃቸውንና ጣቢያው ስርጭቱን ለመጀመር በሙሉ ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በመጨረሻም ስፖርት አፍቃሪው ማህበረሰብና ስፖንሰር አድራጊ ድርጅቶች በማህበራዊ ሚዲያ በሚለቀቁ ላልተረጋገጡ ወሬዎች ሳይደናገጡ የሀገሬ ቲቪ በኢትዮሳት ሳተላይት አማካኝነት ጨዋታዎቹን በነፃ ወደ እያንዳንዱ ቤት እንደሚያደርስ ዋና ስራ አስፈፃሚው ማረጋገጫ ሰጥተዋል።
#worldcup #hagaretv #sports #football #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 days ago
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን : 5ቱ አዲሶቹ ተጫዋቾች
#ethiopia | በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲካተቱ የተመረጡት አዲሶቹ ተጫዋቾች ሙሴ ከቤላ፣ ጀሚል ያዕቆብ፣ ሳሙኤል ዮሐንስ፣ ፍፁም ፍትሕአለው እና ሮኆቦት ሶላሎ ናቸው።
ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ዋሊያዎቹ አዲስ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ዝርዝር ይፋ ሆኗል።
በዚህም መሰረት ሙሴ ከቤላ፣ ጀሚል ያዕቆብ፣ ሳሙኤል ዮሐንስ፣ ፍፁም ፍትሕአለው እና ሮኆቦት ሶላሎ ለመጀመሪያ ጊዜ የአገሪቱን ዋና ብሔራዊ ቡድን እንዲቀላቀሉ እድል አግኝተዋል።
ተጫዋቾቹ ባሳዩት ብቃት መሰረት በምርጫው ውስጥ ሊካተቱ የቻሉ ሲሆን፣ ይህ አዲስ ጥሪ ለስብስብ ጥንካሬ እና ለተተኪ ስፖርተኞች መፈራረቅ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
#የኢትዮጵያእግርኳስ #ዋሊያዎቹ #ብሔራዊቡድን #ስፖርት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲካተቱ የተመረጡት አዲሶቹ ተጫዋቾች ሙሴ ከቤላ፣ ጀሚል ያዕቆብ፣ ሳሙኤል ዮሐንስ፣ ፍፁም ፍትሕአለው እና ሮኆቦት ሶላሎ ናቸው።
ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ዋሊያዎቹ አዲስ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ዝርዝር ይፋ ሆኗል።
በዚህም መሰረት ሙሴ ከቤላ፣ ጀሚል ያዕቆብ፣ ሳሙኤል ዮሐንስ፣ ፍፁም ፍትሕአለው እና ሮኆቦት ሶላሎ ለመጀመሪያ ጊዜ የአገሪቱን ዋና ብሔራዊ ቡድን እንዲቀላቀሉ እድል አግኝተዋል።
ተጫዋቾቹ ባሳዩት ብቃት መሰረት በምርጫው ውስጥ ሊካተቱ የቻሉ ሲሆን፣ ይህ አዲስ ጥሪ ለስብስብ ጥንካሬ እና ለተተኪ ስፖርተኞች መፈራረቅ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
#የኢትዮጵያእግርኳስ #ዋሊያዎቹ #ብሔራዊቡድን #ስፖርት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 days ago
የስፖርት ይዘት ፈጣሪዎች ወድድር ተወዳዳሪ እጩዎችን መጠቆም ተጀመረ።
በ Actually Creative እና E-Receipt የሚዘጋጀው የመጀመሪያው የቲክቶክ የስፖርት ይዘት ፈጣሪዎች ውድድር በቅርብ ቀን ሊካሄድ መሆኑ ተገለፀ።
Sport creators cup የስፖርት ይዘት ፈጣሪዎች በማዝናናት፣ በማስተማርና በማነቃቃት ላሳለፉበት ዓመት እውቅናና ማበረታቻ እንዲሆን ይህ ውድድር የተዘጋጀ ሲሆን ፣ ከ1.5 ሚለየን ብር በላይ ሽልማትም ለተወዳዳሪዎች እንደተዘጋጀ ለማወቅ ተችሏል።
በሁሉም የስፖርት ዘርፍ የሚገኙ ይዘት ፈጣሪዎች የሚሳተፉበት ሲሆን የሚወዳደሩበት (Category) ምድብ በቅርቡ ይፋ ይደረጋል
እርሶም በውድድሩ ሊሳተፍ እንዲሁም ሊሸለም ይገባዋል የምትሉን ይዘት ፈጣሪ (ቲክቶከር) ከስር በተቀመጠው ሊንክ በኩል ጥቆማ እንድታረጉ ጥሪ ቀርቧል።
Sport creators cup
Actually creative
E-Receipt
http://etsportok.com
በ Actually Creative እና E-Receipt የሚዘጋጀው የመጀመሪያው የቲክቶክ የስፖርት ይዘት ፈጣሪዎች ውድድር በቅርብ ቀን ሊካሄድ መሆኑ ተገለፀ።
Sport creators cup የስፖርት ይዘት ፈጣሪዎች በማዝናናት፣ በማስተማርና በማነቃቃት ላሳለፉበት ዓመት እውቅናና ማበረታቻ እንዲሆን ይህ ውድድር የተዘጋጀ ሲሆን ፣ ከ1.5 ሚለየን ብር በላይ ሽልማትም ለተወዳዳሪዎች እንደተዘጋጀ ለማወቅ ተችሏል።
በሁሉም የስፖርት ዘርፍ የሚገኙ ይዘት ፈጣሪዎች የሚሳተፉበት ሲሆን የሚወዳደሩበት (Category) ምድብ በቅርቡ ይፋ ይደረጋል
እርሶም በውድድሩ ሊሳተፍ እንዲሁም ሊሸለም ይገባዋል የምትሉን ይዘት ፈጣሪ (ቲክቶከር) ከስር በተቀመጠው ሊንክ በኩል ጥቆማ እንድታረጉ ጥሪ ቀርቧል።
Sport creators cup
Actually creative
E-Receipt
http://etsportok.com
4 days ago
ታዋቂዋ ማራቶን አትሌት ፋጡማ ሮባ እና ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ከዓመታት በኋላ በደስታ ተገናኙ
#ethiopia | የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ካስጠሩ ስመ ጥር የስፖርት ባልባለቶች መካከል አንዷ የሆነችው አትሌት ፋጡማ ሮባ እና ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ከረጅም ዓመታት በኋላ በድጋሚ ተገናኝተዋል።
አትሌት ፋጡማ ሮባ በታሪካዊው የአትላንታ ኦሎምፒክ በሴቶች ማራቶን ውድድር ለኢትዮጵያ ከአርባ ዓመታት በኋላ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘች ታላቅ ባለውለታ ናት።
በወቅቱ ይህንን ታላቅ ድል ተቀዳጅታ ወደ ሀገሯ ስትመለስ በነበረው ከፍተኛ የደስታ ድባብ ውስጥ ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ለኢትዮጵያ ሬድዮ ፕሮግራም የሚሆን አጭር ቃለ መጠይቅ አድርጎላት እንደነበር ይታወሳል።
ያኔ በወጣትነት ዘመናቸው በስራ አጋጣሚ ተገናኝተው የተነሱትን የማይረሳ ትዝታ የያዘ ፎቶግራፍ በማስታወስ፣ ከአያሌ ዓመታት በኋላ አሁን ላይ በድጋሚ በመገናኘታቸው ለተባረከው ዕድሜና ለአምላክ ምስጋና በማቅረብ ለታዋቂዋ አትሌት መልካም ጤንነትና ረጅም ዕድሜ ተመኝቷል።
ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ በኦንታሪዮ፣ ቶሮንቶ ካናዳ 🇨🇦 ነዋሪ ነው።
#sport #marathon #atlanta1996 #olympics #athletics #history #legend #ethiopianathletes #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ካስጠሩ ስመ ጥር የስፖርት ባልባለቶች መካከል አንዷ የሆነችው አትሌት ፋጡማ ሮባ እና ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ከረጅም ዓመታት በኋላ በድጋሚ ተገናኝተዋል።
አትሌት ፋጡማ ሮባ በታሪካዊው የአትላንታ ኦሎምፒክ በሴቶች ማራቶን ውድድር ለኢትዮጵያ ከአርባ ዓመታት በኋላ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘች ታላቅ ባለውለታ ናት።
በወቅቱ ይህንን ታላቅ ድል ተቀዳጅታ ወደ ሀገሯ ስትመለስ በነበረው ከፍተኛ የደስታ ድባብ ውስጥ ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ለኢትዮጵያ ሬድዮ ፕሮግራም የሚሆን አጭር ቃለ መጠይቅ አድርጎላት እንደነበር ይታወሳል።
ያኔ በወጣትነት ዘመናቸው በስራ አጋጣሚ ተገናኝተው የተነሱትን የማይረሳ ትዝታ የያዘ ፎቶግራፍ በማስታወስ፣ ከአያሌ ዓመታት በኋላ አሁን ላይ በድጋሚ በመገናኘታቸው ለተባረከው ዕድሜና ለአምላክ ምስጋና በማቅረብ ለታዋቂዋ አትሌት መልካም ጤንነትና ረጅም ዕድሜ ተመኝቷል።
ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ በኦንታሪዮ፣ ቶሮንቶ ካናዳ 🇨🇦 ነዋሪ ነው።
#sport #marathon #atlanta1996 #olympics #athletics #history #legend #ethiopianathletes #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 days ago
የአርሰናል የሻምፒዮንስ ሊግ የዋንጫ ህልም በፍጹም ቅጣት ምት መክሸፍ እና አጨቃጫቂው የምሽቱ ጨዋታ
#ethiopia | በለንደን የሚገኙት አለባቸው ደሳለኝ አበሻ እንደዘገቡት የፒኤስጂ እና የአርሰናል የሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ፍልሚያ በዳኝነት ውሳኔዎች ታጅቦ እጅግ አነጋጋሪ በሆነ መልኩ ተጠናቋል።
በውድድር ዘመኑ በሻምፒዮንስ ሊጉ ምንም ሳይሸነፍ ለፍጻሜ የደረሰው አርሰናል መደበኛውና ተጨማሪው ሰዓት 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ከተጠናቀቀ በኋላ በተሰጠው የፍጹም ቅጣት ምት 4 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፎ ዋንጫውን አጥቷል። ይህ ምሽት ለአርሰናል ደጋፊዎች እጅግ ልብ ሰባሪ ነበር።
ስለ ጨዋታው የስፖርት ተንታኞችና ጋዜጠኞች የሰጧቸውን ዋና ዋና አስተያየቶች ከመመልከታችን በፊት የጨዋታውን አጠቃላይ ገጽታ በወፍ በረር እንቃኝ።
የአርሰናል የመከላከል ጥበብ እና የኮከቦች መዛል
ጨዋታው ከተጀመረበት ደቂቃ አንስቶ እስከ ፍጹም ቅጣት ምት ድረስ የአርሰናል የመከላከል ብቃት ፍጹም ሊደነቅ የሚገባው ነበር። ፒኤስጂ በዚህ የውድድር ዘመን እንደፈለገ ጎል እያዘነበ የመጣ ፈጣንና ጠንካራ የፊት መስመር ጥቃት ያለው ክለብ መሆኑ ይታወቃል።
አርሰናል ግን እስከ መጨረሻው ደቂቃ ድረስ በከፍተኛ ዲሲፕሊን ተቆልፎ የፒኤስጂን አስፈሪ የማጥቃት ኃይል አምክኖ የዋለበት መንገድ ቡድኑ ምን ያህል ጠንካራ መዋቅር እንዳለው ያሳየበት ምሽት ነበር። ነገር ግን የኳስ ጨካኝነት እዚህ ላይ ነው 120 ደቂቃ ሙሉ በጥንካሬ ተከላክለህ በመጨረሻው የዕድል ፈተና በፍጹም ቅጣት ምት ዋንጫውን ማጣት በእውነትም ያማል።
በርካታ ተንታኞች በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የአሰላለፍ ውሳኔ ላይ ትኩረት አድርገዋል። በተለይም ቶማስ ፓርቴይን ወይም የተለመዱ ተከላካዮችን ከመጠቀም ይልቅ ክሪስቲያን ሞስኬራን በቀኝ ተከላካይነት መሰለፉ ስህተት እንደነበር አንስተው ተችተዋል። ፒኤስጂ በሁለተኛው አጋማሽ በክቪቻ ኳራፅኬሊያ በኩል ጫና ሲፈጥር ሞስኬራ ፍጹም ቅጣት ምት የተሰጠበትን ጥፋት በመስራቱ የጨዋታውን አቅጣጫ ቀይሮታል ብለዋል።
አርሰናል ጨዋታውን በካይ ሀቨርትዝ ቀደመ ግብ ድንቅ አጀማመር ቢያደርግም በሁለተኛው አጋማሽ እና በትርፍ ሰዓት ላይ ቡድኑ በከፍተኛ ሁኔታ መዛሉ ታይቷል። ፒኤስጂ 72 በመቶ የኳስ ቁጥጥር የበላይነት የነበረው ሲሆን አርሰናል ሙሉ ጨዋታውን በመከላከል ማሳለፉ ለፍጹም ቅጣት ምት ሲደርሱ ተጫዋቾቹ ላይ የትኩረት ማጣት እንዲከሰትና የአርሰናል አስደናቂ ጥንካሬ እንዲዝል አድርጎታል።
የዳኝነት ውሳኔዎች እና የቪዲዮ ረዳት ዳኛ (VAR) ውዝግብ
የዳኝነት ውሳኔው በማህበራዊ ሚዲያ በተለይም በኤክስ እና በፌስቡክ ላይ በደጋፊዎችና በስፖርት ተንታኞች መካከል እጅግ ሞቅ ያለና የአርሰናልን ደጋፊዎች ያስቆጣ አጀንዳ ሆኗል። ዳኛው አድላዊ ነበሩ በሚል ማህበራዊ ሚዲያውን እያነጋገሩ ያሉት 3 ዋና ዋና አጨቃጫቂ ውሳኔዎች የሚከተሉት ናቸው።
በኖኒ ማዱዌኬ ላይ የተፈጸመው ጥፋት እና የቪዲዮ ረዳት ዳኛ ዝምታ ጉዳይ በትክክል ፍጹም ቅጣት ምት መሆን ነበረበት ተብሏል። የፒኤስጂው ተከላካይ ኑኖ ሜንዴስ በሳጥን ውስጥ ማዱዌኬን በግልጽ ሲገፋውና ሲያንገላታው ቢታይም የቪዲዮ ረዳት ዳኛው ዋናውን ዳኛ ሄዶ በስክሪን እንኳ እንዲያይ አለመጋበዙ ግልጽ አድሎ ነው በሚል የአርሰናል ደጋፊዎች ቁጣቸውን እየገለፁ ይገኛሉ። ገለልተኛ ተንታኞችም የግፊው ኃይል ለፍጹም ቅጣት ምት በቂ ባይሆን እንኳ ጉዳዩ ቢያንስ በቪዲዮ ረዳት ዳኛ መታየት እንደነበረበት ይስማማሉ።
የእርምጃዎች ድርብ መስፈርት በሁለተኛው አጋማሽ ክሪስቲያን ሞስኬራ በክቪቻ ኳራፅኬሊያ ላይ በሰራው ጥፋት ፒኤስጂ በቀላሉ የፍጹም ቅጣት ምት አግኝቷል። ብዙዎች ኳራፅኬሊያ በቀላሉ ነው የወደቀው ዳኛው ግን ለፒኤስጂ የነበራቸው አዝማሚያ ለስላሳ ስለነበር ወዲያውኑ ፍጹም ቅጣት ምት ሰጡ በማለት ይተቻሉ። በተመሳሳይ ጥፋት በአርሰናል በኩል የቀረቡት ጥያቄዎች ውድቅ መደረጋቸው የዳኛውን ሚዛናዊነት ጥያቄ ውስጥ ጥሎታል።
የሰዓት ማጥፋት እርምጃዎች መዘግየትን በተመለከተ የፒኤስጂ ተጫዋቾች ሆን ብለው ሰዓት ሲያጠፉ እና ጨዋታውን ሲያደናቅፉ ዳኛው ጥብቅ እርምጃ አለመውሰዳቸው ሌላው ቅሬታ ነው። በተቃራኒው በአርሰናል ተጫዋቾች ላይ የተሰጡት የቅጣት ውሳኔዎች ፍጹም ጥብቅ እና ቡድኑን የተጫኑ ነበሩ ተብሏል።
የአርሰናል የቀድሞ ኮከብ አለን ስሚዝ ጨምሮ በርካታ ተንታኞች እንደሚስማሙት ዳኛው በጨዋታው ላይ የተጠቀሙት ድርብ መስፈርት አርሰናል ዋንጫውን እንዲያጣ ትልቅ ተፅዕኖ አሳድሯል።
የስፖርት ተንታኞች እንደሚሉት የፍጹም ቅጣት ምት ሁሌም የዕድል ጉዳይ ነው።
በጨዋታው ላይ ኤበሬቺ ኤዜ ሳይጠቀምበት የቀረውን ኳስ ዴቪድ ራያ የኑኖ ሜንዴስን መቅጫ ምት በማዳን ተስፋ ቢመልስም በመጨረሻው ወሳኝ ምት ተከላካዩ ጋብሬል ማጋልሃሽ ኳሱን ወደ ላይ መስቀሉ ጨካኝ የሆነ የውጤት መደምደሚያ ነበር። ሆኖም ጋብሬል በጨዋታው ላይ የነበረው ድንቅ የመከላከል ብቃት ሳይዘነጋ ይህ ስህተት እሱን ብቻ ተጠያቂ ሊያደርገው እንደማይገባ ተንታኞች ይሟገታሉ።
የሳካ እና ኦዴጋርድ መቀየር ስህተት ነበር?
ሚኬል አርቴታ ቡካዮ ሳካንና ማርቲን ኦዴጋርድን በማስወጣቱ ለሽንፈቱ ምክንያት ሆኗል ለሚለው ጥያቄ ተንታኞች ሁለት ዋና ዋና እይታዎችን እያነሱ ነው።
በአንድ በኩል ሳካ እና ኦዴጋርድ የቡድኑ መሪዎች ብቻ ሳይሆኑ በፍጹም ቅጣት ምት ወቅት እጅግ አስተማማኝ የተረጋጉና ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች ናቸው። እነሱ በሌሉበት ሜዳ ላይ የቀሩት ወጣት ወይም የተከላካይ መስመር ተጫዋቾች እንደ ጋብሬል ማጋልሃሽ የፍጹም ቅጣት ምት የመምታት ከባድ ጫና እንዲወድቅባቸው አድርጓል። በተጨማሪም ሁለቱ ኮከቦች ሲወጡ አርሰናል ኳስን መስርቶ ማጥቃትና ፒኤስጂን ወደ ኋላ ማስጨነቅ ሙሉ በሙሉ አቆመ።
ይህም ፒኤስጂዎች ያለ ምንም ስጋት ሙሉ ኃይላቸውን ወደ አርሰናል ሳጥን እንዲልኩና በአርሰናል ተከላካዮች ላይ ከፍተኛ የአእምሮና የሰውነት ድካም እንዲፈጠር አድርጓል ይላሉ።
በሌላ በኩል ጨዋታው ወደ ትርፍ ሰዓት ሲያመራ ሳካ እና ኦዴጋርድ በፒኤስጂ ተጫዋቾች ከፍተኛ ክትትልና ጫና ስለነበረባቸው በከፍተኛ ሁኔታ ዝለው ነበር።
አርቴታ እነሱን የቀየረው የጡንቻ ጉዳት እንዳይገጥማቸውና ትኩስ ጉልበት ያላቸውን ተጫዋቾች ለምሳሌ ማዱዌኬን በማስገባት የፒኤስጂን መስመር ለመስበር በማሰብ ሊሆን ይችላል የሚሉም አሉ።
ሆኖም አርቴታ ጨዋታውን በ120 ደቂቃ ውስጥ ለመጨረስ ወይም በመከላከል ለመጨረስ አስቦ ሊሆን ይችላል ነገር ግን ጨዋታው ወደ ፍጹም ቅጣት ምት ማምራቱ የማይቀር መሆኑን እያወቀ ሁለቱን ምርጥ የቅጣት ምት መቺዎቹን እና የቡድኑን የልብ ትርታዎች ቀይሮ ማስወጣቱ በታክቲክ ደረጃ ትልቅ ስህተት እንደነበር ይነገራል።
ይህ የሻምፒዮንስ ሊግ ሽንፈት ለአርሰናል እና ለደጋፊዎቹ እጅግ መራራ ምሽት ቢሆንም ክለቡ በዚህ የውድድር ዘመን የኢንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን በማንሳቱ ትልቅ ስኬት ማስመዝገቡ አይዘነጋም።
ቡድኑ ካሳየው አስደናቂ ጥንካሬ እና መዋቅር አንፃር በቀጣይ ዓመታት ይበልጥ ጠንክሮ እና ተምሮበት እንደሚመለስ የስፖርት ተንታኞች ትልቅ ተስፋ ጥለውበታል።
አለባቸው ደሳለኝ ለንደን 🇬🇧
#arsenal #psg #championsleague #football #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በለንደን የሚገኙት አለባቸው ደሳለኝ አበሻ እንደዘገቡት የፒኤስጂ እና የአርሰናል የሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ፍልሚያ በዳኝነት ውሳኔዎች ታጅቦ እጅግ አነጋጋሪ በሆነ መልኩ ተጠናቋል።
በውድድር ዘመኑ በሻምፒዮንስ ሊጉ ምንም ሳይሸነፍ ለፍጻሜ የደረሰው አርሰናል መደበኛውና ተጨማሪው ሰዓት 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ከተጠናቀቀ በኋላ በተሰጠው የፍጹም ቅጣት ምት 4 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፎ ዋንጫውን አጥቷል። ይህ ምሽት ለአርሰናል ደጋፊዎች እጅግ ልብ ሰባሪ ነበር።
ስለ ጨዋታው የስፖርት ተንታኞችና ጋዜጠኞች የሰጧቸውን ዋና ዋና አስተያየቶች ከመመልከታችን በፊት የጨዋታውን አጠቃላይ ገጽታ በወፍ በረር እንቃኝ።
የአርሰናል የመከላከል ጥበብ እና የኮከቦች መዛል
ጨዋታው ከተጀመረበት ደቂቃ አንስቶ እስከ ፍጹም ቅጣት ምት ድረስ የአርሰናል የመከላከል ብቃት ፍጹም ሊደነቅ የሚገባው ነበር። ፒኤስጂ በዚህ የውድድር ዘመን እንደፈለገ ጎል እያዘነበ የመጣ ፈጣንና ጠንካራ የፊት መስመር ጥቃት ያለው ክለብ መሆኑ ይታወቃል።
አርሰናል ግን እስከ መጨረሻው ደቂቃ ድረስ በከፍተኛ ዲሲፕሊን ተቆልፎ የፒኤስጂን አስፈሪ የማጥቃት ኃይል አምክኖ የዋለበት መንገድ ቡድኑ ምን ያህል ጠንካራ መዋቅር እንዳለው ያሳየበት ምሽት ነበር። ነገር ግን የኳስ ጨካኝነት እዚህ ላይ ነው 120 ደቂቃ ሙሉ በጥንካሬ ተከላክለህ በመጨረሻው የዕድል ፈተና በፍጹም ቅጣት ምት ዋንጫውን ማጣት በእውነትም ያማል።
በርካታ ተንታኞች በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የአሰላለፍ ውሳኔ ላይ ትኩረት አድርገዋል። በተለይም ቶማስ ፓርቴይን ወይም የተለመዱ ተከላካዮችን ከመጠቀም ይልቅ ክሪስቲያን ሞስኬራን በቀኝ ተከላካይነት መሰለፉ ስህተት እንደነበር አንስተው ተችተዋል። ፒኤስጂ በሁለተኛው አጋማሽ በክቪቻ ኳራፅኬሊያ በኩል ጫና ሲፈጥር ሞስኬራ ፍጹም ቅጣት ምት የተሰጠበትን ጥፋት በመስራቱ የጨዋታውን አቅጣጫ ቀይሮታል ብለዋል።
አርሰናል ጨዋታውን በካይ ሀቨርትዝ ቀደመ ግብ ድንቅ አጀማመር ቢያደርግም በሁለተኛው አጋማሽ እና በትርፍ ሰዓት ላይ ቡድኑ በከፍተኛ ሁኔታ መዛሉ ታይቷል። ፒኤስጂ 72 በመቶ የኳስ ቁጥጥር የበላይነት የነበረው ሲሆን አርሰናል ሙሉ ጨዋታውን በመከላከል ማሳለፉ ለፍጹም ቅጣት ምት ሲደርሱ ተጫዋቾቹ ላይ የትኩረት ማጣት እንዲከሰትና የአርሰናል አስደናቂ ጥንካሬ እንዲዝል አድርጎታል።
የዳኝነት ውሳኔዎች እና የቪዲዮ ረዳት ዳኛ (VAR) ውዝግብ
የዳኝነት ውሳኔው በማህበራዊ ሚዲያ በተለይም በኤክስ እና በፌስቡክ ላይ በደጋፊዎችና በስፖርት ተንታኞች መካከል እጅግ ሞቅ ያለና የአርሰናልን ደጋፊዎች ያስቆጣ አጀንዳ ሆኗል። ዳኛው አድላዊ ነበሩ በሚል ማህበራዊ ሚዲያውን እያነጋገሩ ያሉት 3 ዋና ዋና አጨቃጫቂ ውሳኔዎች የሚከተሉት ናቸው።
በኖኒ ማዱዌኬ ላይ የተፈጸመው ጥፋት እና የቪዲዮ ረዳት ዳኛ ዝምታ ጉዳይ በትክክል ፍጹም ቅጣት ምት መሆን ነበረበት ተብሏል። የፒኤስጂው ተከላካይ ኑኖ ሜንዴስ በሳጥን ውስጥ ማዱዌኬን በግልጽ ሲገፋውና ሲያንገላታው ቢታይም የቪዲዮ ረዳት ዳኛው ዋናውን ዳኛ ሄዶ በስክሪን እንኳ እንዲያይ አለመጋበዙ ግልጽ አድሎ ነው በሚል የአርሰናል ደጋፊዎች ቁጣቸውን እየገለፁ ይገኛሉ። ገለልተኛ ተንታኞችም የግፊው ኃይል ለፍጹም ቅጣት ምት በቂ ባይሆን እንኳ ጉዳዩ ቢያንስ በቪዲዮ ረዳት ዳኛ መታየት እንደነበረበት ይስማማሉ።
የእርምጃዎች ድርብ መስፈርት በሁለተኛው አጋማሽ ክሪስቲያን ሞስኬራ በክቪቻ ኳራፅኬሊያ ላይ በሰራው ጥፋት ፒኤስጂ በቀላሉ የፍጹም ቅጣት ምት አግኝቷል። ብዙዎች ኳራፅኬሊያ በቀላሉ ነው የወደቀው ዳኛው ግን ለፒኤስጂ የነበራቸው አዝማሚያ ለስላሳ ስለነበር ወዲያውኑ ፍጹም ቅጣት ምት ሰጡ በማለት ይተቻሉ። በተመሳሳይ ጥፋት በአርሰናል በኩል የቀረቡት ጥያቄዎች ውድቅ መደረጋቸው የዳኛውን ሚዛናዊነት ጥያቄ ውስጥ ጥሎታል።
የሰዓት ማጥፋት እርምጃዎች መዘግየትን በተመለከተ የፒኤስጂ ተጫዋቾች ሆን ብለው ሰዓት ሲያጠፉ እና ጨዋታውን ሲያደናቅፉ ዳኛው ጥብቅ እርምጃ አለመውሰዳቸው ሌላው ቅሬታ ነው። በተቃራኒው በአርሰናል ተጫዋቾች ላይ የተሰጡት የቅጣት ውሳኔዎች ፍጹም ጥብቅ እና ቡድኑን የተጫኑ ነበሩ ተብሏል።
የአርሰናል የቀድሞ ኮከብ አለን ስሚዝ ጨምሮ በርካታ ተንታኞች እንደሚስማሙት ዳኛው በጨዋታው ላይ የተጠቀሙት ድርብ መስፈርት አርሰናል ዋንጫውን እንዲያጣ ትልቅ ተፅዕኖ አሳድሯል።
የስፖርት ተንታኞች እንደሚሉት የፍጹም ቅጣት ምት ሁሌም የዕድል ጉዳይ ነው።
በጨዋታው ላይ ኤበሬቺ ኤዜ ሳይጠቀምበት የቀረውን ኳስ ዴቪድ ራያ የኑኖ ሜንዴስን መቅጫ ምት በማዳን ተስፋ ቢመልስም በመጨረሻው ወሳኝ ምት ተከላካዩ ጋብሬል ማጋልሃሽ ኳሱን ወደ ላይ መስቀሉ ጨካኝ የሆነ የውጤት መደምደሚያ ነበር። ሆኖም ጋብሬል በጨዋታው ላይ የነበረው ድንቅ የመከላከል ብቃት ሳይዘነጋ ይህ ስህተት እሱን ብቻ ተጠያቂ ሊያደርገው እንደማይገባ ተንታኞች ይሟገታሉ።
የሳካ እና ኦዴጋርድ መቀየር ስህተት ነበር?
ሚኬል አርቴታ ቡካዮ ሳካንና ማርቲን ኦዴጋርድን በማስወጣቱ ለሽንፈቱ ምክንያት ሆኗል ለሚለው ጥያቄ ተንታኞች ሁለት ዋና ዋና እይታዎችን እያነሱ ነው።
በአንድ በኩል ሳካ እና ኦዴጋርድ የቡድኑ መሪዎች ብቻ ሳይሆኑ በፍጹም ቅጣት ምት ወቅት እጅግ አስተማማኝ የተረጋጉና ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች ናቸው። እነሱ በሌሉበት ሜዳ ላይ የቀሩት ወጣት ወይም የተከላካይ መስመር ተጫዋቾች እንደ ጋብሬል ማጋልሃሽ የፍጹም ቅጣት ምት የመምታት ከባድ ጫና እንዲወድቅባቸው አድርጓል። በተጨማሪም ሁለቱ ኮከቦች ሲወጡ አርሰናል ኳስን መስርቶ ማጥቃትና ፒኤስጂን ወደ ኋላ ማስጨነቅ ሙሉ በሙሉ አቆመ።
ይህም ፒኤስጂዎች ያለ ምንም ስጋት ሙሉ ኃይላቸውን ወደ አርሰናል ሳጥን እንዲልኩና በአርሰናል ተከላካዮች ላይ ከፍተኛ የአእምሮና የሰውነት ድካም እንዲፈጠር አድርጓል ይላሉ።
በሌላ በኩል ጨዋታው ወደ ትርፍ ሰዓት ሲያመራ ሳካ እና ኦዴጋርድ በፒኤስጂ ተጫዋቾች ከፍተኛ ክትትልና ጫና ስለነበረባቸው በከፍተኛ ሁኔታ ዝለው ነበር።
አርቴታ እነሱን የቀየረው የጡንቻ ጉዳት እንዳይገጥማቸውና ትኩስ ጉልበት ያላቸውን ተጫዋቾች ለምሳሌ ማዱዌኬን በማስገባት የፒኤስጂን መስመር ለመስበር በማሰብ ሊሆን ይችላል የሚሉም አሉ።
ሆኖም አርቴታ ጨዋታውን በ120 ደቂቃ ውስጥ ለመጨረስ ወይም በመከላከል ለመጨረስ አስቦ ሊሆን ይችላል ነገር ግን ጨዋታው ወደ ፍጹም ቅጣት ምት ማምራቱ የማይቀር መሆኑን እያወቀ ሁለቱን ምርጥ የቅጣት ምት መቺዎቹን እና የቡድኑን የልብ ትርታዎች ቀይሮ ማስወጣቱ በታክቲክ ደረጃ ትልቅ ስህተት እንደነበር ይነገራል።
ይህ የሻምፒዮንስ ሊግ ሽንፈት ለአርሰናል እና ለደጋፊዎቹ እጅግ መራራ ምሽት ቢሆንም ክለቡ በዚህ የውድድር ዘመን የኢንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን በማንሳቱ ትልቅ ስኬት ማስመዝገቡ አይዘነጋም።
ቡድኑ ካሳየው አስደናቂ ጥንካሬ እና መዋቅር አንፃር በቀጣይ ዓመታት ይበልጥ ጠንክሮ እና ተምሮበት እንደሚመለስ የስፖርት ተንታኞች ትልቅ ተስፋ ጥለውበታል።
አለባቸው ደሳለኝ ለንደን 🇬🇧
#arsenal #psg #championsleague #football #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
4 days ago
ራይድ ትራንስፖርት ተሸለመ
RIDE በAfrica's Best Brands Award ላይ Most Admired Ethiopian Brand በመሆን ለከፍተኛ ሽልማት በቅቷል::
በአዲስ አበባ United Nations Economic Commission for Africa (ECA) በተደረገው የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ ድርጅታችን ይህንን ታላቅ ክብርና ሽልማት በማግኘቱ የተሰማን ደስታ እየገለፅን ÷ በመላው የራይድ ቤተሰብ ስም ለማመስገን እንወዳለን::
ድርጅታችን በ2006 ዓ.ም RIDE የተሰኘውን የንግድ ስም እና ምልክት በኢትዮዽያ አዕምሮ ንብረት ጥበቃ በማስመዝገብ በኢትዮዽያ የመጀመርያውን የኤሌክትሮኒክ ታክሲ አገልግሎት ዘርፍ ፈር - ቀዳጅ ሲሆን በአሁን ወቅት በስፋት አገልግሎቱን እያቀረበ ይገኛል:: በተጨማሪም በFood Delivery እና ተዛማች አገልግሎቶች ላይ በመሪነት እያገለገለ ይገኛል::
ይህንን ትልቅ ብራንድ ስንገነባ በነበረው ሂደት ከጎናችን ለነበራችሁ አሽከርካሪዎች ÷ ደንበኞቻችን እና መላው የራይድ ቤተሰቦች በቀጣይም ከኢትዮዽያ አልፎ በአፍሪካ በምናደርገው ጉዞ አብረውን በዘላቂነት እንደሚወዳጁን እንተማመናለን::
ከRIDE ጋር ወደፊት💛!
RIDE በAfrica's Best Brands Award ላይ Most Admired Ethiopian Brand በመሆን ለከፍተኛ ሽልማት በቅቷል::
በአዲስ አበባ United Nations Economic Commission for Africa (ECA) በተደረገው የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ ድርጅታችን ይህንን ታላቅ ክብርና ሽልማት በማግኘቱ የተሰማን ደስታ እየገለፅን ÷ በመላው የራይድ ቤተሰብ ስም ለማመስገን እንወዳለን::
ድርጅታችን በ2006 ዓ.ም RIDE የተሰኘውን የንግድ ስም እና ምልክት በኢትዮዽያ አዕምሮ ንብረት ጥበቃ በማስመዝገብ በኢትዮዽያ የመጀመርያውን የኤሌክትሮኒክ ታክሲ አገልግሎት ዘርፍ ፈር - ቀዳጅ ሲሆን በአሁን ወቅት በስፋት አገልግሎቱን እያቀረበ ይገኛል:: በተጨማሪም በFood Delivery እና ተዛማች አገልግሎቶች ላይ በመሪነት እያገለገለ ይገኛል::
ይህንን ትልቅ ብራንድ ስንገነባ በነበረው ሂደት ከጎናችን ለነበራችሁ አሽከርካሪዎች ÷ ደንበኞቻችን እና መላው የራይድ ቤተሰቦች በቀጣይም ከኢትዮዽያ አልፎ በአፍሪካ በምናደርገው ጉዞ አብረውን በዘላቂነት እንደሚወዳጁን እንተማመናለን::
ከRIDE ጋር ወደፊት💛!
4 days ago
የዓረፋ በዓልን በትውልድ መንደራቸው ለማክበር የሄዱ የስልጤ ዞን ተወላጆች የምርጫ ድምፅ ለመስጠት ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ ነው
*******************
የዘንድሮውን የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በትውልድ ቀያቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር በጋራ ለማክበር ወደ ስልጤ ዞን ተጉዘው የነበሩ በርካታ የዞኑ ተወላጆች፣ ድምፅ ለመስጠት ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ላይ ይገኛሉ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ውስጥ በሚገኙ 10ሩ ወረዳዎችና 5 የከተማ አስተዳደሮች በዓሉን ለማክበር የሄዱ የአካባቢው ተወላጆች ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ መሆናቸውን ለኢቢሲ ተናግረዋል።
ለመመለሳቸው ዋነኛው ምክንያት በነገው ዕለት በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በመሳተፍ የዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም እና ድምፅ ለመስጠት መሆኑን ተናግረዋል።
ተጓዦቹ ያለምንም እንግልት በሰዓቱ ደርሰው ድምፃቸውን መስጠት እንዲችሉ የዞኑ አመራርሮች እና የትራንስፖርት ዘርፍ አስተባባሪዎች በትብብር እየሠሩ ነው።
በዚህ ከፍተኛ የሕዝብ ፍሰት ምክንያት ከወራቤ እና ከተለያዩ የስልጤ ዞን ወረዳዎች ወደ አዲስ አበባ በሚወስዱ መንገዶች ላይ ከፍተኛ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እየታየ ይገኛል።
በአሚር ጌቱ
#ebc #ethiopia #democracy
*******************
የዘንድሮውን የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በትውልድ ቀያቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር በጋራ ለማክበር ወደ ስልጤ ዞን ተጉዘው የነበሩ በርካታ የዞኑ ተወላጆች፣ ድምፅ ለመስጠት ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ላይ ይገኛሉ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ውስጥ በሚገኙ 10ሩ ወረዳዎችና 5 የከተማ አስተዳደሮች በዓሉን ለማክበር የሄዱ የአካባቢው ተወላጆች ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ መሆናቸውን ለኢቢሲ ተናግረዋል።
ለመመለሳቸው ዋነኛው ምክንያት በነገው ዕለት በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በመሳተፍ የዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም እና ድምፅ ለመስጠት መሆኑን ተናግረዋል።
ተጓዦቹ ያለምንም እንግልት በሰዓቱ ደርሰው ድምፃቸውን መስጠት እንዲችሉ የዞኑ አመራርሮች እና የትራንስፖርት ዘርፍ አስተባባሪዎች በትብብር እየሠሩ ነው።
በዚህ ከፍተኛ የሕዝብ ፍሰት ምክንያት ከወራቤ እና ከተለያዩ የስልጤ ዞን ወረዳዎች ወደ አዲስ አበባ በሚወስዱ መንገዶች ላይ ከፍተኛ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እየታየ ይገኛል።
በአሚር ጌቱ
#ebc #ethiopia #democracy
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ዛሬ ምሽት በተካሄደው የምዕራቡ ዞን የፍጻሜ ማጣሪያ ሰባተኛ እና ወሳኝ ጨዋታ.. ሳን አንቶኒዮ ስፐርስ ኦክላሆማ ሲቲ ታንደርን 111 ለ 103 በሆነ ውጤት በማሸነፍ አጓጊውን ተከታታይ ፍልሚያ በድል አጠናቋል። ይህ የሁለቱ ወጣት እና ሀያል የቅርጫት ኳስ ቡድኖች ግጥሚያ፣ የብሔራዊ የቅርጫት ኳስ ማህበሩን የወደፊት እጣ ፈንታ ማን ይቆጣጠራል ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ድንቅ መድረክ ነበር። አሸናፊው ስፐርስ በመጪው ረቡዕ ከኒው ዮርክ ኒክስ ጋር ታላቁን የፍጻሜ ጨዋታ ይጀምራል።
በአንጻሩ ለቀጣዮቹ አመታት የሊጉ የበላይ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ታንደር፣ ከዚህ ሽንፈት አገግሞ እንዴት ሊሻሻል እንደሚችል በቁጭት የሚያስብበት ጊዜ ላይ ደርሷል።
ይህ እጅግ ተጠባቂ ጨዋታ በዋናነት "ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ከ ቪክቶር ዌምባንያማ" ወይም የሊጉ ኮከብ ተጫዋች ከአመቱ ምርጥ ተከላካይ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ ተብሎ ተሰይሞ ነበር። ነገር ግን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ በቅጣት ወንበር ላይ በተቀመጠበት ወሳኝ ሰዓት፣ የስፐርስ ተቀያሪ ግዙፍ ተጫዋች የሆነው ሉክ ኮርኔት ያደረገው ድንቅ የኳስ መግታት (ብሎክ) የጨዋታውን ሚዛን ሙሉ በሙሉ ወደ ሳን አንቶኒዮ አዘንብሎታል
ምንም እንኳን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ ለመውጣት ቢገደድም፣ 22 ነጥቦችን እና 7 የተመለሱ ኳሶችን በማስቆጠር ስፐርስን በግንባር ቀደምትነት መርቷል። በሌላ በኩል ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር 35 ነጥቦችን እና 9 ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል የነበረበትን ከፍተኛ ጫና ለመወጣት አስደናቂ ጥረት አድርጓል።
የታንደር ሌሎች ቁልፍ ኳስ አቀጣጣዮች የሆኑት ጃለን ዊሊያምስ እና አጃይ ሚቼል በጉዳት ምክንያት ከሜዳ መራቃቸው፣ በሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ላይ እጅግ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮበታል። ቡድኑን ወደ ፍጻሜው ለማድረስ የማይቻለውን ሁሉ ቢሞክርም፣ በዙሪያው ከነበሩት ሌሎች ተጫዋቾች በቂ ድጋፍ ማግኘት አልቻለም።
የታንደር ተቀያሪ ተጫዋቾች በተለይም ጄይሊን ዊሊያምስ 11 ነጥብ፣ 10 የተመለሱ ኳሶች እና 4 ኳሶችን በማቀበል ጥሩ ቢንቀሳቀስም፤ ቼት ሆልምግሬን ግን እጅግ ደካማ አቋም አሳይቷል። ሆልምግሬን ከሞከራቸው ሁለት ኳሶች አንዱን ብቻ በማስቆጠር 4 ነጥብ ይዞ የወጣ ሲሆን፣ ከመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በኋላ ወደ ቀለበት ምንም አይነት ሙከራ አላደረገም። ዌምባንያማ በቅዳሜውም ሆነ በአጠቃላይ ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ሆልምግሬንን ሙሉ በሙሉ ከጨዋታ ውጪ አድርጎታል።
አሁን ሳን አንቶኒዮ ስፐርስ በሊጉ ታሪክ ምርጥ የሚባለውን የ14 ተከታታይ ጨዋታዎች የማሸነፍ ጉዞ እያደረገ ከሚገኘው ኒው ዮርክ ኒክስ ጋር በፍጻሜው ይፋለማል። ዕድሜያቸው 25 እና ከዚያ በታች የሆኑ አምስት ወጣት ተጫዋቾችን የሚያሰልፈው ስፐርስ፣ ሀያሉን ታንደርን ሊያሸንፍ ይችላል ብሎ መጠበቅ ለብዙዎች አዳጋች ነበር። አሁን ግን ተጠራጣሪዎች ሁሉ ተሳስተው የወጣቶቹ ስብስብ ታሪክ ጽፏል!
በአንጻሩ ለቀጣዮቹ አመታት የሊጉ የበላይ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ታንደር፣ ከዚህ ሽንፈት አገግሞ እንዴት ሊሻሻል እንደሚችል በቁጭት የሚያስብበት ጊዜ ላይ ደርሷል።
ይህ እጅግ ተጠባቂ ጨዋታ በዋናነት "ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ከ ቪክቶር ዌምባንያማ" ወይም የሊጉ ኮከብ ተጫዋች ከአመቱ ምርጥ ተከላካይ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ ተብሎ ተሰይሞ ነበር። ነገር ግን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ በቅጣት ወንበር ላይ በተቀመጠበት ወሳኝ ሰዓት፣ የስፐርስ ተቀያሪ ግዙፍ ተጫዋች የሆነው ሉክ ኮርኔት ያደረገው ድንቅ የኳስ መግታት (ብሎክ) የጨዋታውን ሚዛን ሙሉ በሙሉ ወደ ሳን አንቶኒዮ አዘንብሎታል
ምንም እንኳን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ ለመውጣት ቢገደድም፣ 22 ነጥቦችን እና 7 የተመለሱ ኳሶችን በማስቆጠር ስፐርስን በግንባር ቀደምትነት መርቷል። በሌላ በኩል ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር 35 ነጥቦችን እና 9 ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል የነበረበትን ከፍተኛ ጫና ለመወጣት አስደናቂ ጥረት አድርጓል።
የታንደር ሌሎች ቁልፍ ኳስ አቀጣጣዮች የሆኑት ጃለን ዊሊያምስ እና አጃይ ሚቼል በጉዳት ምክንያት ከሜዳ መራቃቸው፣ በሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ላይ እጅግ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮበታል። ቡድኑን ወደ ፍጻሜው ለማድረስ የማይቻለውን ሁሉ ቢሞክርም፣ በዙሪያው ከነበሩት ሌሎች ተጫዋቾች በቂ ድጋፍ ማግኘት አልቻለም።
የታንደር ተቀያሪ ተጫዋቾች በተለይም ጄይሊን ዊሊያምስ 11 ነጥብ፣ 10 የተመለሱ ኳሶች እና 4 ኳሶችን በማቀበል ጥሩ ቢንቀሳቀስም፤ ቼት ሆልምግሬን ግን እጅግ ደካማ አቋም አሳይቷል። ሆልምግሬን ከሞከራቸው ሁለት ኳሶች አንዱን ብቻ በማስቆጠር 4 ነጥብ ይዞ የወጣ ሲሆን፣ ከመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በኋላ ወደ ቀለበት ምንም አይነት ሙከራ አላደረገም። ዌምባንያማ በቅዳሜውም ሆነ በአጠቃላይ ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ሆልምግሬንን ሙሉ በሙሉ ከጨዋታ ውጪ አድርጎታል።
አሁን ሳን አንቶኒዮ ስፐርስ በሊጉ ታሪክ ምርጥ የሚባለውን የ14 ተከታታይ ጨዋታዎች የማሸነፍ ጉዞ እያደረገ ከሚገኘው ኒው ዮርክ ኒክስ ጋር በፍጻሜው ይፋለማል። ዕድሜያቸው 25 እና ከዚያ በታች የሆኑ አምስት ወጣት ተጫዋቾችን የሚያሰልፈው ስፐርስ፣ ሀያሉን ታንደርን ሊያሸንፍ ይችላል ብሎ መጠበቅ ለብዙዎች አዳጋች ነበር። አሁን ግን ተጠራጣሪዎች ሁሉ ተሳስተው የወጣቶቹ ስብስብ ታሪክ ጽፏል!
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በህንድ ኮልካታ ከተማ የሚገኘው ግዙፉ የሊዮኔል ሜሲ ሀውልት የተተከለው በዲሴምበር ወር ተጨዋቹ በአገሪቱ ውስጥ ያደረገውን ጉብኝት በማስመልከት ነበር፡፡ ይህ 21 ሜትር የሚረዝመውና ወርቃማ ቀለም የተቀባው ሀውልት በዌስት ቤንጋል ግዛት ኮልካታ ከተማ እምብርት ላይ ቆሞ ቆይቷል፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ይህ ሀውልት በንፋስ እየወዛወዘ ይገኛል፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ሰራተኞች ሀውልቱ እንዳይወድቅ የተለያዩ ገመዶችን በመጠቀም እንዲጠናከር አድርገውታል፡፡
ይሁን እንጂ የከተማው ባለስልጣናት ዛሬ በሰጡት መግለጫ ሀውልቱ ከዚህ በኋላ ለደህንነት አስጊ በመሆኑ እንደሚነሳ አስታውቀዋል፡፡ የዌስት ቤንጋል ግዛት የፓርላማ አባል የሆኑት ሻራዳዋት ሙከርጂ ለኤኤፍፒ ሲናገሩ ‹‹ሀውልቱ በንፋስ እየተወዛወዘ መሆኑን ሰምተናል፡፡ የግዛቱ መሀንዲሶችም ለደህንነት አስጊ መሆኑን ገልፀውልናል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሀውልቱን ማንሳት ከማቆም የበለጠ ቀላል ነው፡፡ ስለዚህም በተቻለ ፍጥነት የምናነሳው ይሆናል›› ያሉ ሲሆን ሀውልቱ ሌላ ቦታ ስለመተከል አለመተከሉ ያሉት ነገር የለም፡፡
ህንድ 1.4 ቢሊዮን ህዝብ ያላት አገር ብትሆንም በአገሪቱ ውስጥ ተወዳጅ የሆነው ስፖርት ክሪኬትስ ነው፡፡ በእግር ኳስ ከአለም በ142ተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የፊፋ መረጃ ያሳያል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አርጀንቲናዊው የ38 አመቱ የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ከሳምንታት በኋላ በሚጀመረው የአለም ዋንጫ ላይ እንደሚሳተፍ እስካሁን በይፋ ማረጋገጫ አልሰጠም፡፡ በውድድሩ የሚሳተፍ ከሆነ ግን በአለም ዋንጫ ላይ 6 ጊዜ በመሳተፍ ሪከርድን የሚጋራ ይሆናል፡፡
ይሁን እንጂ የከተማው ባለስልጣናት ዛሬ በሰጡት መግለጫ ሀውልቱ ከዚህ በኋላ ለደህንነት አስጊ በመሆኑ እንደሚነሳ አስታውቀዋል፡፡ የዌስት ቤንጋል ግዛት የፓርላማ አባል የሆኑት ሻራዳዋት ሙከርጂ ለኤኤፍፒ ሲናገሩ ‹‹ሀውልቱ በንፋስ እየተወዛወዘ መሆኑን ሰምተናል፡፡ የግዛቱ መሀንዲሶችም ለደህንነት አስጊ መሆኑን ገልፀውልናል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሀውልቱን ማንሳት ከማቆም የበለጠ ቀላል ነው፡፡ ስለዚህም በተቻለ ፍጥነት የምናነሳው ይሆናል›› ያሉ ሲሆን ሀውልቱ ሌላ ቦታ ስለመተከል አለመተከሉ ያሉት ነገር የለም፡፡
ህንድ 1.4 ቢሊዮን ህዝብ ያላት አገር ብትሆንም በአገሪቱ ውስጥ ተወዳጅ የሆነው ስፖርት ክሪኬትስ ነው፡፡ በእግር ኳስ ከአለም በ142ተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የፊፋ መረጃ ያሳያል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አርጀንቲናዊው የ38 አመቱ የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ከሳምንታት በኋላ በሚጀመረው የአለም ዋንጫ ላይ እንደሚሳተፍ እስካሁን በይፋ ማረጋገጫ አልሰጠም፡፡ በውድድሩ የሚሳተፍ ከሆነ ግን በአለም ዋንጫ ላይ 6 ጊዜ በመሳተፍ ሪከርድን የሚጋራ ይሆናል፡፡
8 days ago
አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መዲናችን አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በባለፉት 10 ቀናት ብቻ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ብለዋል።
ለአብነትም ፦
1. በኢንዱስትሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ይህ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው።
2. የማህበራዊ ልማት (የመኖሪያ ቤቶች)፤ ሶስቱ የበጎነት መንደሮችን በአዲስ ከተማ፣ በኮልፌ ቀራንዮ እና የካ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ የመኖርያ ቤቶች ለሀገር ባለውለታዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች እና ለአካል ጉዳተኞች የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
3. የመዝናኛ እና የህዝብ ፓርኮች ፤በአዲስ ከተማ (አስኮ አዲስ ሰፈር) በ30 ሺህ ካሬ ሜትር እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻ እና የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ተመርቀዋል። እነዚህ ማዕከላት ህፃናትን፣ ወጣቶችን እና አረጋውያንን ያካተቱ፣ ማህበረሰቡ በጋራ የሚጠቀምባቸው ናቸው።
4. የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ አካል የሆነው 7ኛው የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
5. ዘመናዊ የገበያና የትራንስፖርት ማዕከል፤ አይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአድዋ የገበያ ማዕከል እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተርሚናል ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የዚህ ማዕከል ሱቆች እና ካፍቴሪያዎች ለፒያሳ ልማት ተነሺዎች በዕጣ ተላልፈዋል።
6. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ፣ 16 ሱቆችን እና 18 ሼዶችን የያዘ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
7. የስፖርት እና የወጣቶች ማዕከል፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየም፣ 5 ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ 95 የህፃናት መጫወቻዎች፣ 6 የህፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከላት፣ ካፍቴሪያዎች እና አምፊ ቲያትሮችን ጨምሮ ለወጣቶች ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
8. በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ሁለት ት/ቤቶች እና ሶስት የህፃናት ማቆያ ማእከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረገዋል ።
9. የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎች ለነበሩ 400 ነዋሪዎቻችን መነሻ ካፒታልና የመስሪያ ቁሳቁስ በማሟሟላት ከተረጂነት ወደ የስራ እድል ተጠቃሚነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
10. 7ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በላፍቶ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።
11. ዘመናዊ የጤና አገልግሎት ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እና እጅግ ዘመናዊ የሆነው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለምርቃት በቅቷል።
አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ተብሎ እንደተከናወነ ያነሳሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ ነገር ግን እውነታው ቀድሞ ያልተሰራ ለምርጫም ሊደርስ አይችልም፤ ተሰርቶም ለምርጫ ከዋለ ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ ይሁን እንጂ ችግር የለውም ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መዲናችን አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በባለፉት 10 ቀናት ብቻ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ብለዋል።
ለአብነትም ፦
1. በኢንዱስትሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ይህ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው።
2. የማህበራዊ ልማት (የመኖሪያ ቤቶች)፤ ሶስቱ የበጎነት መንደሮችን በአዲስ ከተማ፣ በኮልፌ ቀራንዮ እና የካ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ የመኖርያ ቤቶች ለሀገር ባለውለታዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች እና ለአካል ጉዳተኞች የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
3. የመዝናኛ እና የህዝብ ፓርኮች ፤በአዲስ ከተማ (አስኮ አዲስ ሰፈር) በ30 ሺህ ካሬ ሜትር እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻ እና የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ተመርቀዋል። እነዚህ ማዕከላት ህፃናትን፣ ወጣቶችን እና አረጋውያንን ያካተቱ፣ ማህበረሰቡ በጋራ የሚጠቀምባቸው ናቸው።
4. የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ አካል የሆነው 7ኛው የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
5. ዘመናዊ የገበያና የትራንስፖርት ማዕከል፤ አይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአድዋ የገበያ ማዕከል እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተርሚናል ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የዚህ ማዕከል ሱቆች እና ካፍቴሪያዎች ለፒያሳ ልማት ተነሺዎች በዕጣ ተላልፈዋል።
6. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ፣ 16 ሱቆችን እና 18 ሼዶችን የያዘ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
7. የስፖርት እና የወጣቶች ማዕከል፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየም፣ 5 ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ 95 የህፃናት መጫወቻዎች፣ 6 የህፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከላት፣ ካፍቴሪያዎች እና አምፊ ቲያትሮችን ጨምሮ ለወጣቶች ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
8. በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ሁለት ት/ቤቶች እና ሶስት የህፃናት ማቆያ ማእከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረገዋል ።
9. የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎች ለነበሩ 400 ነዋሪዎቻችን መነሻ ካፒታልና የመስሪያ ቁሳቁስ በማሟሟላት ከተረጂነት ወደ የስራ እድል ተጠቃሚነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
10. 7ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በላፍቶ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።
11. ዘመናዊ የጤና አገልግሎት ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እና እጅግ ዘመናዊ የሆነው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለምርቃት በቅቷል።
አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ተብሎ እንደተከናወነ ያነሳሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ ነገር ግን እውነታው ቀድሞ ያልተሰራ ለምርጫም ሊደርስ አይችልም፤ ተሰርቶም ለምርጫ ከዋለ ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ ይሁን እንጂ ችግር የለውም ብለዋል፡፡
8 days ago
ቀኝ አዝማች በኩረ ምዕመናን ትዛዙ ኮሬ የኢትዮጵያን ባህል፣ ቱሪዝምና በጎ አድራጎት በማስፋፋት የሚታወቁ ታዋቂ ኢንተርፕረነር፣ የባህል አምባሳደር እና ሀገር በቀል ሽማግሌ ናቸው። በተለይም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን እና ግዙፍ የባህል ምግብ ቤቶች አንዱ የሆነውን ዮድ አቢሲኒያ (Yod Abyssinia) ባህላዊ ምግብ ቤት በመመስረታቸው በሰፊው ይታወቃሉ።
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ