የዓረፋ በዓልን በትውልድ መንደራቸው ለማክበር የሄዱ የስልጤ ዞን ተወላጆች የምርጫ ድምፅ ለመስጠት ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ ነው
*******************
የዘንድሮውን የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በትውልድ ቀያቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር በጋራ ለማክበር ወደ ስልጤ ዞን ተጉዘው የነበሩ በርካታ የዞኑ ተወላጆች፣ ድምፅ ለመስጠት ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ላይ ይገኛሉ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ውስጥ በሚገኙ 10ሩ ወረዳዎችና 5 የከተማ አስተዳደሮች በዓሉን ለማክበር የሄዱ የአካባቢው ተወላጆች ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ መሆናቸውን ለኢቢሲ ተናግረዋል።
ለመመለሳቸው ዋነኛው ምክንያት በነገው ዕለት በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በመሳተፍ የዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም እና ድምፅ ለመስጠት መሆኑን ተናግረዋል።
ተጓዦቹ ያለምንም እንግልት በሰዓቱ ደርሰው ድምፃቸውን መስጠት እንዲችሉ የዞኑ አመራርሮች እና የትራንስፖርት ዘርፍ አስተባባሪዎች በትብብር እየሠሩ ነው።
በዚህ ከፍተኛ የሕዝብ ፍሰት ምክንያት ከወራቤ እና ከተለያዩ የስልጤ ዞን ወረዳዎች ወደ አዲስ አበባ በሚወስዱ መንገዶች ላይ ከፍተኛ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እየታየ ይገኛል።
በአሚር ጌቱ
#ebc #ethiopia #democracy
*******************
የዘንድሮውን የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በትውልድ ቀያቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር በጋራ ለማክበር ወደ ስልጤ ዞን ተጉዘው የነበሩ በርካታ የዞኑ ተወላጆች፣ ድምፅ ለመስጠት ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ላይ ይገኛሉ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ውስጥ በሚገኙ 10ሩ ወረዳዎችና 5 የከተማ አስተዳደሮች በዓሉን ለማክበር የሄዱ የአካባቢው ተወላጆች ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ መሆናቸውን ለኢቢሲ ተናግረዋል።
ለመመለሳቸው ዋነኛው ምክንያት በነገው ዕለት በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በመሳተፍ የዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም እና ድምፅ ለመስጠት መሆኑን ተናግረዋል።
ተጓዦቹ ያለምንም እንግልት በሰዓቱ ደርሰው ድምፃቸውን መስጠት እንዲችሉ የዞኑ አመራርሮች እና የትራንስፖርት ዘርፍ አስተባባሪዎች በትብብር እየሠሩ ነው።
በዚህ ከፍተኛ የሕዝብ ፍሰት ምክንያት ከወራቤ እና ከተለያዩ የስልጤ ዞን ወረዳዎች ወደ አዲስ አበባ በሚወስዱ መንገዶች ላይ ከፍተኛ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እየታየ ይገኛል።
በአሚር ጌቱ
#ebc #ethiopia #democracy
4 days ago