18 hours ago
"ወንድሜ ፑቲን መጸዳጃ ቤት ሆኜ አጠቃላይ የሩስያን የጂፒኤስ ስርዓት ማቋረጥ እችላለሁ" ኢሎን መስክ
#ethiopia | ስታርሊንክ በስትራቴጂካዊ እንቅስቃሴዎቻችን ላይ ጣልቃ እየገባበት ያለበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ለኢሎን መስክ የ48 ሰዓት የጊዜ ገደብ ከተሰጠውና "ትዕግስታችንን አትፈታተን" የሚል ማስጠንቀቂያ ከቀረበበት በኋላ ቢሊየነሩ አሻፈረኝ ብሏል።
መስክ ለቀረበበት ማስጠንቀቂያ በሰጠው ቀጥተኛና ያልተጠበቀ ምላሽ "ወንድሜ ከመጸዳጃ ቤት ቁጭ ብዬ በስልኬ ብቻ የሀገራችሁን ሙሉ የጂፒኤስ (GPS) ስርዓት ማቋረጥ እችላለሁ" በማለት መልስ ሰጥቷል።
ይህ ድፍረት የተቀላቀለበትና ያልተጠበቀ ምላሽ ባለሃብቱ ላይ ምን መዘዝ ይዞበት እንደሚመጣ ወደፊት የምናየው ቢሆንም አንዳንዶች ''ፑቲን ሚሳዔል እንዳይተኩስበት ፈርተናል'' በማለት ተሳልቀዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ስታርሊንክ በስትራቴጂካዊ እንቅስቃሴዎቻችን ላይ ጣልቃ እየገባበት ያለበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ለኢሎን መስክ የ48 ሰዓት የጊዜ ገደብ ከተሰጠውና "ትዕግስታችንን አትፈታተን" የሚል ማስጠንቀቂያ ከቀረበበት በኋላ ቢሊየነሩ አሻፈረኝ ብሏል።
መስክ ለቀረበበት ማስጠንቀቂያ በሰጠው ቀጥተኛና ያልተጠበቀ ምላሽ "ወንድሜ ከመጸዳጃ ቤት ቁጭ ብዬ በስልኬ ብቻ የሀገራችሁን ሙሉ የጂፒኤስ (GPS) ስርዓት ማቋረጥ እችላለሁ" በማለት መልስ ሰጥቷል።
ይህ ድፍረት የተቀላቀለበትና ያልተጠበቀ ምላሽ ባለሃብቱ ላይ ምን መዘዝ ይዞበት እንደሚመጣ ወደፊት የምናየው ቢሆንም አንዳንዶች ''ፑቲን ሚሳዔል እንዳይተኩስበት ፈርተናል'' በማለት ተሳልቀዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ለኢራን የጦር መሳሪያ እንደማይሸጡ የገቡትን ቃል እንደሚያምኑ ከገለጹ በኋላ፣ ሁለቱም ሀገራት (ቻይና እና ሩሲያ) ኢራንን እንደማይረዱ ሺን እና የሩሲያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን እንደሚያምኗቸው ተናግረዋል።
የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተያየት የተደመጠው የአሜሪካው መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴዝ "ቻይና እና ሩሲያ በተለያየ ደረጃ ኢራን እያደረገች ያለውን እንቅስቃሴ እያገዙ ነው" በማለት ከሰጡት ማብራሪያ ጋር የሚቃረን ሆኖ ተገኝቷል።
ትራምፕ ዓርብ ዕለት በሰጡት አስተያየት "እንግዲህ፣ እነሱ [ኢራንን] እያገዙ ስለመሆኑ የማውቀው ነገር የለም። እኔ የምነግራችሁ ፕሬዝዳንት ሺ በዚህ ጉዳይ እንደማይሳተፉ ነግረውኛል፤ ፕሬዝዳንት ፑቲንም ተመሳሳይ ነገር ነው ያሉት። እኔ ደግሞ አምናቸዋለሁ። ምናልባት የረጅም ጊዜ ግንኙነት ስላላቸው የሚያደርጓቸው አንዳንድ ጥቃቅን ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ፤ ነገር ግን እስካሁን ድረስ ቢያንስ የጎላ እና ትልቅ የሚባል ነገር የለም። እኔን ማሳዘን ይፈልጋሉ ብዬ አላስብም" ብለዋል።
የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተያየት የተደመጠው የአሜሪካው መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴዝ "ቻይና እና ሩሲያ በተለያየ ደረጃ ኢራን እያደረገች ያለውን እንቅስቃሴ እያገዙ ነው" በማለት ከሰጡት ማብራሪያ ጋር የሚቃረን ሆኖ ተገኝቷል።
ትራምፕ ዓርብ ዕለት በሰጡት አስተያየት "እንግዲህ፣ እነሱ [ኢራንን] እያገዙ ስለመሆኑ የማውቀው ነገር የለም። እኔ የምነግራችሁ ፕሬዝዳንት ሺ በዚህ ጉዳይ እንደማይሳተፉ ነግረውኛል፤ ፕሬዝዳንት ፑቲንም ተመሳሳይ ነገር ነው ያሉት። እኔ ደግሞ አምናቸዋለሁ። ምናልባት የረጅም ጊዜ ግንኙነት ስላላቸው የሚያደርጓቸው አንዳንድ ጥቃቅን ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ፤ ነገር ግን እስካሁን ድረስ ቢያንስ የጎላ እና ትልቅ የሚባል ነገር የለም። እኔን ማሳዘን ይፈልጋሉ ብዬ አላስብም" ብለዋል።
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሴርጌይ ላቭሮቭ እና የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በፊሊፒንስ ማኒላ በተካሄደው የአሴያን ቀጠናዊ ፎረም ጎን ለጎን ባደረጉት ስብሰባ፣ በዩክሬን ግጭት እና በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ መደበኛ ሁኔታ በመመለስ ዙሪያ መምከራቸውን የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ሴርጌይ ላቭሮቭ ሩሲያ የዩክሬንን ግጭት በፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ያላትን ዝግጁነት በድጋሚ ያረጋገጡ ሲሆን፤ ሞስኮ በነሐሴ 2025 (እ.ኤ.አ.) በአላስካ በተካሄደው ጉባኤ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በፕሬዝዳንት ቪላዲሚር ፑቲን የቀረቡትን የመፍትሔ ሀሳቦች አሁንም እንደምትቀበልና እንደምትደግፍ ገልጸዋል።
ሁለቱ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች በቀጣይም በሁለቱ አገራት እና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የሚያደርጉትን ግንኙነትና ውይይት አጠናክረው ለመቀጠል መስማማታቸውን መግለጫው አክሎ አመልክቷል።
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ሴርጌይ ላቭሮቭ ሩሲያ የዩክሬንን ግጭት በፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ያላትን ዝግጁነት በድጋሚ ያረጋገጡ ሲሆን፤ ሞስኮ በነሐሴ 2025 (እ.ኤ.አ.) በአላስካ በተካሄደው ጉባኤ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በፕሬዝዳንት ቪላዲሚር ፑቲን የቀረቡትን የመፍትሔ ሀሳቦች አሁንም እንደምትቀበልና እንደምትደግፍ ገልጸዋል።
ሁለቱ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች በቀጣይም በሁለቱ አገራት እና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የሚያደርጉትን ግንኙነትና ውይይት አጠናክረው ለመቀጠል መስማማታቸውን መግለጫው አክሎ አመልክቷል።
18 days ago
የፑቲን "ስውሯ ልጅ" በፓሪስ መሸታ ቤቶች እየሰራች ነው ተባለ
#ethiopia | የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ድብቅ ልጅ እንደሆነች የሚነገርላት ኤሊዛቬታ ክሪቮኖጊክ (ሉኢዛ ሮዞቫ) ከሞስኮ የሥልጣን ማዕከል ርቃ በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ ውስጥ ፍጹም የተለየ ሕይወት እየመራች ይገኛል።
ምንም እንኳን ፕሬዝዳንቱ በይፋ አባትነታቸውን አምነው ተቀብለው ባያውቁም እና ጉዳዩ በይፋ ባይረጋገጥም የተሾለኩ ሰነዶችና የምርመራ ዘገባዎች ግን የጉዞ መረጃዎቿን ዋቢ በማድረግ ደምድመዋል።
የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ለጉዳዩ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ አለመስጠቱም የታሪኩን ምስጢራዊነት ይበልጥ አጉልቶታል።
ይህች አወዛጋቢ ወጣት በፓሪስ የስነ-ጥበብ እና የባህል አስተዳደር ትምህርቷን የተከታተለች ሲሆን በምሽት ቤቶች ውስጥ ከመስራቷም በላይ በተለያዩ ስሞች በዲጄነት የሙዚቃ አጫዋችነት ሙያ ላይ ተሰማርታ ትገኛለች።
አባቷ ተብሎ የሚገመቱት ፑቲን የዓለማችንን ኃያል ሀገር ሩሲያን ከክሬምሊን ሆነው በብረት እጅ ሲመሩ እሷ ግን ማንነቷን ደብቃ በፓሪስ የምሽት ክለቦችና በስነ-ጥበብ ዓለም ውስጥ አዲስ ሕይወት መገንባቷ እጅግ አስደናቂ ንፅፅርን ፈጥሯል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ድብቅ ልጅ እንደሆነች የሚነገርላት ኤሊዛቬታ ክሪቮኖጊክ (ሉኢዛ ሮዞቫ) ከሞስኮ የሥልጣን ማዕከል ርቃ በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ ውስጥ ፍጹም የተለየ ሕይወት እየመራች ይገኛል።
ምንም እንኳን ፕሬዝዳንቱ በይፋ አባትነታቸውን አምነው ተቀብለው ባያውቁም እና ጉዳዩ በይፋ ባይረጋገጥም የተሾለኩ ሰነዶችና የምርመራ ዘገባዎች ግን የጉዞ መረጃዎቿን ዋቢ በማድረግ ደምድመዋል።
የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ለጉዳዩ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ አለመስጠቱም የታሪኩን ምስጢራዊነት ይበልጥ አጉልቶታል።
ይህች አወዛጋቢ ወጣት በፓሪስ የስነ-ጥበብ እና የባህል አስተዳደር ትምህርቷን የተከታተለች ሲሆን በምሽት ቤቶች ውስጥ ከመስራቷም በላይ በተለያዩ ስሞች በዲጄነት የሙዚቃ አጫዋችነት ሙያ ላይ ተሰማርታ ትገኛለች።
አባቷ ተብሎ የሚገመቱት ፑቲን የዓለማችንን ኃያል ሀገር ሩሲያን ከክሬምሊን ሆነው በብረት እጅ ሲመሩ እሷ ግን ማንነቷን ደብቃ በፓሪስ የምሽት ክለቦችና በስነ-ጥበብ ዓለም ውስጥ አዲስ ሕይወት መገንባቷ እጅግ አስደናቂ ንፅፅርን ፈጥሯል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹በሞስኮ 1000 ድሮን ስናበር የፑቲን ካልኩሌሽን ይለወጣል›› ሲሉ ዘለንስኪ ገለፁ፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ ከፋይናንሺያል ታይምስ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ከሩሲያ ጋር የሚደረገውን ጦርነት ውጤት የሚለውጠው በአየር የበላይነት መያዝ መሆኑን አስታወቁ፡፡
ፕሬዝደንቱ በጦርነቱ በባህር ሀይልና በምድር ጦር ድል መቀዳጀታቸውን ጠቅሰው ወሳኙና ቀጣዩ በአየር ሀይል የበላይነት መቀዳጀት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹በዚህ ጦርነት አሸናፊ የሚሆነው ብልህ እንደሆነ አምናለሁ›› ያሉት ዘለንስኪ ጨምረውም ‹‹በጦር ሜዳ ላይ ጠላት እንዳይንቀሳቀስ ካደረከው በምድር ጦር የበላይነት ይዘህ አቁመኸዋል ማለት ነው፡፡ የሩሲያን መርከቦች በባህር ድሮኖቻችን እንዳይንቀሳቀሱ እንዳደረግነው በባህር ሀይልም የበላይነትን ጨብጠናል፡፡ ስለዚህም አሁን የሚቀረን ሰማዩ ነው›› በማለት አስረድተዋል፡፡
አስከትለውም ‹‹በዚህ በሰማይ ላይ በሚደረግ ውድድር ማን ሰፊ ግዛት አለው የሚለው አይሰራም፡፡ በፊቱንም ተፎካካሪ እንደነበርነው ሁሉ አሁን ወደዚያ ገብተናል›› ካሉ በኋላ ዩክሬይን ረጅም ርቀት ላይ የማጥቃት አቅሟ እየተጠናከረ መምጣቱን ገልፀው አንድ ድክመት እንዳለባት ግን አልሸሸጉም፡፡ እንዳስረዱትም እሱም ፀረ ሚሳኤል መከላከያ ነው፡፡ ፓትሪዮት ፓክ 3 የተሰኙት እነዚህ መከላከያዎች እያጠሯቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹አውሮፓ በዚህ ረገድ የምታሳየውን ቸልተኝነት ማቆም አለባት፡፡ ቴክኖሎጂዎችንና የኢንዱስትሪ አቅሟን ከሌሎች አገራት ጋር መጋራት ይኖርባታል፡፡ ምክንያቱም ለሁሉም የሚበቃ ፓትሪዮት ሚሳኤል አይኖርም›› ብለዋል፡፡ ዘለንስኪ እንዳብራሩት ፓትሪዮት ሚሳኤሎችን የምታመርተው አሜሪካ ብቻ ስትሆን ይህ ሚሳኤል በአውሮፓ ውስጥ እንዲመረት ፈቃድ ልትሰጥ ይገባታል፡፡ አውሮፓውያንም ከአሜሪካ ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ጥያቄ ማቅረብና መወትወት እንዳለባቸው አሳስበው ዩክሬይን በራሷ መንገድ ለአሜሪካ ጥያቄውን ማቅረቧን አስታውቀዋል፡፡
አገራቸው በክሬሚያ ግዛት ውስጥ የምታደርገውን ረጅም ርቀት ጥቃት እንደምትቀጥል የገለፁት ዘለንስኪ ኢላማቸውም ወታደራዊ ማእከላት፣ የነዳጅ ዴፖዎች፣ የአየር መቃወሚያዎችና የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች እንደሚሆኑ አስረድተዋል፡፡ ይህንን የሚያደርጉትም ሩሲያ በሀይል ዘርፍና በወደብ መሰረተ ልማቶቿ ላይ ጥቃት ከደረሰባት በኋላ ወታደራዊ ተቋሞቿን በክሬሚያ ስላሰፈረች መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም በዋና ከተማ ሞስኮ ላይ ጥቃት የመቀጠል እቅድ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ እንደፕሬዝደንቱ ገለፃ የክሬሚሊን መሪው ጥቃቱ ሞስኮና ሴንት ፒትስበርግ እስከሚደርስ ድረስ ብዙም አላሳሰባቸውም ነበር፡፡
ጨምረውም ‹‹ፑቲን ክሬሚሊን በጣም ሩቅ ቦታ እንደሆነ አስቦ ነበር፡፡ ነገር ግን ሞስኮ ውስጥ ጥቃት መፈፀሙን ሲሰማ ስሜቱ እየገባው መጥቷል›› ካሉ በኋላ በቀጣይነት የሚያደርጉት ጥቃት የበለጠ ፑቲን የጦርነቱን እውነታ እንዲጋፈጡ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ አስከትለውም ‹‹በሞስኮ ላይ በመቶዎች አይደለም በሺህ የሚቆጠሩ ድሮኖችን ስናበር የፑቲን ካልኩሌሽን ይለወጣል፡፡ እኛ ወደሞስኮ እጅግ በቀረብን ቁጥር ጦርነቱን ለማቆም አዲስ ምእራፍ ይከፈታል፡፡ ፑቲንም የራሱን ደህንነት ለመጠበቅ ሲል ሰላምን ይመርጣል›› በማለት አስረድተዋል፡፡
ፕሬዝደንቱ በጦርነቱ በባህር ሀይልና በምድር ጦር ድል መቀዳጀታቸውን ጠቅሰው ወሳኙና ቀጣዩ በአየር ሀይል የበላይነት መቀዳጀት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹በዚህ ጦርነት አሸናፊ የሚሆነው ብልህ እንደሆነ አምናለሁ›› ያሉት ዘለንስኪ ጨምረውም ‹‹በጦር ሜዳ ላይ ጠላት እንዳይንቀሳቀስ ካደረከው በምድር ጦር የበላይነት ይዘህ አቁመኸዋል ማለት ነው፡፡ የሩሲያን መርከቦች በባህር ድሮኖቻችን እንዳይንቀሳቀሱ እንዳደረግነው በባህር ሀይልም የበላይነትን ጨብጠናል፡፡ ስለዚህም አሁን የሚቀረን ሰማዩ ነው›› በማለት አስረድተዋል፡፡
አስከትለውም ‹‹በዚህ በሰማይ ላይ በሚደረግ ውድድር ማን ሰፊ ግዛት አለው የሚለው አይሰራም፡፡ በፊቱንም ተፎካካሪ እንደነበርነው ሁሉ አሁን ወደዚያ ገብተናል›› ካሉ በኋላ ዩክሬይን ረጅም ርቀት ላይ የማጥቃት አቅሟ እየተጠናከረ መምጣቱን ገልፀው አንድ ድክመት እንዳለባት ግን አልሸሸጉም፡፡ እንዳስረዱትም እሱም ፀረ ሚሳኤል መከላከያ ነው፡፡ ፓትሪዮት ፓክ 3 የተሰኙት እነዚህ መከላከያዎች እያጠሯቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹አውሮፓ በዚህ ረገድ የምታሳየውን ቸልተኝነት ማቆም አለባት፡፡ ቴክኖሎጂዎችንና የኢንዱስትሪ አቅሟን ከሌሎች አገራት ጋር መጋራት ይኖርባታል፡፡ ምክንያቱም ለሁሉም የሚበቃ ፓትሪዮት ሚሳኤል አይኖርም›› ብለዋል፡፡ ዘለንስኪ እንዳብራሩት ፓትሪዮት ሚሳኤሎችን የምታመርተው አሜሪካ ብቻ ስትሆን ይህ ሚሳኤል በአውሮፓ ውስጥ እንዲመረት ፈቃድ ልትሰጥ ይገባታል፡፡ አውሮፓውያንም ከአሜሪካ ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ጥያቄ ማቅረብና መወትወት እንዳለባቸው አሳስበው ዩክሬይን በራሷ መንገድ ለአሜሪካ ጥያቄውን ማቅረቧን አስታውቀዋል፡፡
አገራቸው በክሬሚያ ግዛት ውስጥ የምታደርገውን ረጅም ርቀት ጥቃት እንደምትቀጥል የገለፁት ዘለንስኪ ኢላማቸውም ወታደራዊ ማእከላት፣ የነዳጅ ዴፖዎች፣ የአየር መቃወሚያዎችና የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች እንደሚሆኑ አስረድተዋል፡፡ ይህንን የሚያደርጉትም ሩሲያ በሀይል ዘርፍና በወደብ መሰረተ ልማቶቿ ላይ ጥቃት ከደረሰባት በኋላ ወታደራዊ ተቋሞቿን በክሬሚያ ስላሰፈረች መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም በዋና ከተማ ሞስኮ ላይ ጥቃት የመቀጠል እቅድ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ እንደፕሬዝደንቱ ገለፃ የክሬሚሊን መሪው ጥቃቱ ሞስኮና ሴንት ፒትስበርግ እስከሚደርስ ድረስ ብዙም አላሳሰባቸውም ነበር፡፡
ጨምረውም ‹‹ፑቲን ክሬሚሊን በጣም ሩቅ ቦታ እንደሆነ አስቦ ነበር፡፡ ነገር ግን ሞስኮ ውስጥ ጥቃት መፈፀሙን ሲሰማ ስሜቱ እየገባው መጥቷል›› ካሉ በኋላ በቀጣይነት የሚያደርጉት ጥቃት የበለጠ ፑቲን የጦርነቱን እውነታ እንዲጋፈጡ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ አስከትለውም ‹‹በሞስኮ ላይ በመቶዎች አይደለም በሺህ የሚቆጠሩ ድሮኖችን ስናበር የፑቲን ካልኩሌሽን ይለወጣል፡፡ እኛ ወደሞስኮ እጅግ በቀረብን ቁጥር ጦርነቱን ለማቆም አዲስ ምእራፍ ይከፈታል፡፡ ፑቲንም የራሱን ደህንነት ለመጠበቅ ሲል ሰላምን ይመርጣል›› በማለት አስረድተዋል፡፡
1 month ago
ሀያላኖቹ ሊመክሩ ነው
#ethiopia | የሩሲያ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ ለመነጋገር መስማማታቸውን ክሬምሊን አስታውቃለች።
የሁለቱ መሪዎች ውይይት የሚደረገው መች እንደሆነ ክሪምሊን አልገለፀም።
ሆኖም በአንካራ ከሚካሄደው የኔቶ የመሪዎች ጉባኤ መጠናቀቅ በኋላ ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።
ስማቸው ያልተገለፀ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን እንደገለጹት ፕሬዚዳንት ትራምፕ በዚሁ ከኔቶ ጉባኤ ጎን ለጎን ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ጋር ይወያያሉ ብለዋል።
የዚህ ውይይታቸውን ዋና ዓላማም በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ለማቆም የሚያስችል ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንደገና ለመጀመር ያለመ ነው ብለዋል።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭም መሪዎቹ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለመቀጠል መስማማታቸውን አረጋግጠዋል።
ትራምፕ ከዘሌንስኪ ጋር ከተወያዩ በኋላ ከፑቲን ጋር በስልክ እንደሚወያዩ የክሬምሊን ቃል አቀባይ አረጋግጠዋል ሲል የፃፈው አርቲ ኒውስ ነው።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #kremlinspokesperson #peskove #putintrump #rtnews
#ethiopia | የሩሲያ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ ለመነጋገር መስማማታቸውን ክሬምሊን አስታውቃለች።
የሁለቱ መሪዎች ውይይት የሚደረገው መች እንደሆነ ክሪምሊን አልገለፀም።
ሆኖም በአንካራ ከሚካሄደው የኔቶ የመሪዎች ጉባኤ መጠናቀቅ በኋላ ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።
ስማቸው ያልተገለፀ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን እንደገለጹት ፕሬዚዳንት ትራምፕ በዚሁ ከኔቶ ጉባኤ ጎን ለጎን ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ጋር ይወያያሉ ብለዋል።
የዚህ ውይይታቸውን ዋና ዓላማም በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ለማቆም የሚያስችል ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንደገና ለመጀመር ያለመ ነው ብለዋል።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭም መሪዎቹ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለመቀጠል መስማማታቸውን አረጋግጠዋል።
ትራምፕ ከዘሌንስኪ ጋር ከተወያዩ በኋላ ከፑቲን ጋር በስልክ እንደሚወያዩ የክሬምሊን ቃል አቀባይ አረጋግጠዋል ሲል የፃፈው አርቲ ኒውስ ነው።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #kremlinspokesperson #peskove #putintrump #rtnews
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በቱርክ ከሚካሄደው የኔቶ ጉባኤ ዋዜማ ላይ ሩሲያ በዩክሬን ኪየቭ ክልል ላይ በፈጸመችው የባሊስቲክ ሚሳኤል ጥቃት ቢያንስ ስምንት ሰዎች ሲሞቱ በደርዘን የሚቆጠሩ ደግሞ መቁሰላቸውን ባለስልጣናት ገለጹ።
ይህ ጥቃት ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ በዋና ከተማዋ እና አካባቢዋ ላይ ሲፈጸም ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ሩሲያ ሰፊ ወረራ ከጀመረች ከአራት ዓመታት በላይ ያስቆጠረውን የዚህን ጦርነት አድማስ መስፋፋት በሚያሳይ መልኩ፣ ሁለቱም ወገኖች የረጅም ርቀት ጥቃቶቻቸውን አጠናክረዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የዩክሬኑ አቻቸው ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ነገ በቱርክ ዋና ከተማ አንካራ በሚጀመረው ጉባኤ ጎን ለጎን ስለ ጦርነቱ ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህም በኋላ፣ ዋሽንግተን የቆመውን የሰላም ጥረት ዳግም ለማንቀሳቀስ በምታደርገው ጥረት፣ ትራምፕ ከሩሲያ መሪ ቭላድሚር ፑቲን ጋር ለመነጋገር አቅደዋል።
በኪየቭ የሚገኝ አንድ የኤ.ኤፍ.ፒ ጋዜጠኛ ዛሬ ሰኞ ማለዳ ላይ በተሰጠው የባሊስቲክ ሚሳኤል ማስጠንቀቂያ ወቅት ከ10 በላይ ፍንዳታዎችን ሰምቷል። ከ30 ደቂቃዎች ገደማ በኋላም፣ ሌሎች ተከታታይ ፍንዳታዎች ሲያስተጋቡ ጋዜጠኞቹ በሰማይ ላይ በርካታ ብልጭታዎችን ተመልክተዋል።
ባለስልጣናት እንዳስታወቁት በዋና ከተማዋ ኪየቭ ሰባት ሰዎች ሲገደሉ፣ ከከተማዋ በስተሰሜን ምዕራብ በምትገኘው ቡቻ ወረዳ ደግሞ አንድ ሰው ህይወቱ አልፏል። በተጨማሪም በኪየቭ እና አካባቢዋ ቢያንስ 34 ሰዎች ቆስለዋል።
ይህ ጥቃት ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ በዋና ከተማዋ እና አካባቢዋ ላይ ሲፈጸም ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ሩሲያ ሰፊ ወረራ ከጀመረች ከአራት ዓመታት በላይ ያስቆጠረውን የዚህን ጦርነት አድማስ መስፋፋት በሚያሳይ መልኩ፣ ሁለቱም ወገኖች የረጅም ርቀት ጥቃቶቻቸውን አጠናክረዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የዩክሬኑ አቻቸው ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ነገ በቱርክ ዋና ከተማ አንካራ በሚጀመረው ጉባኤ ጎን ለጎን ስለ ጦርነቱ ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህም በኋላ፣ ዋሽንግተን የቆመውን የሰላም ጥረት ዳግም ለማንቀሳቀስ በምታደርገው ጥረት፣ ትራምፕ ከሩሲያ መሪ ቭላድሚር ፑቲን ጋር ለመነጋገር አቅደዋል።
በኪየቭ የሚገኝ አንድ የኤ.ኤፍ.ፒ ጋዜጠኛ ዛሬ ሰኞ ማለዳ ላይ በተሰጠው የባሊስቲክ ሚሳኤል ማስጠንቀቂያ ወቅት ከ10 በላይ ፍንዳታዎችን ሰምቷል። ከ30 ደቂቃዎች ገደማ በኋላም፣ ሌሎች ተከታታይ ፍንዳታዎች ሲያስተጋቡ ጋዜጠኞቹ በሰማይ ላይ በርካታ ብልጭታዎችን ተመልክተዋል።
ባለስልጣናት እንዳስታወቁት በዋና ከተማዋ ኪየቭ ሰባት ሰዎች ሲገደሉ፣ ከከተማዋ በስተሰሜን ምዕራብ በምትገኘው ቡቻ ወረዳ ደግሞ አንድ ሰው ህይወቱ አልፏል። በተጨማሪም በኪየቭ እና አካባቢዋ ቢያንስ 34 ሰዎች ቆስለዋል።
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹ከፑቲን ጋር በኮንስታንቲኖቭካ መነጋገር እፈልጋለሁ›› ሲሉ ዘለንስኪ ተናገሩ፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ በማህበራዊ ሚዲያቸው ላይ በዶኔስክ ግዛት የሚገኘውን ኮንስታንቲኖቭካ ከተማ በተመለከተ አስተያየት ፅፈዋል፡፡
በዚህ አስተያየታቸው የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ይህችን ከተማ መቆጣጠራቸውን በተመለከተ የተሰራጨውን ዘገባ ‹‹ፍፁም ውሸት ነው›› ብለውታል፡፡ ሲናገሩም ‹‹በአሜሪካ የነፃነት በአል ዋዜማ ላይ ፑቲን በጦር ግንባር ስላለው ሁኔታ የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨት የአለምን ህዝብና የአሜሪካን ፕሬዝደንት ለመዋሸት ወስኗል፡፡›› ብለዋል፡፡
ጨምረውም ‹‹በእርግጥ በጦር ግንባር ያለው እውነታ እሱ እንደተናገረው እደለም፡፡ ይህ የተለመደ የሩሲያ ውሸት ነው፡፡ ነገር ግን ኮንስታንቲኖቭካ ከተማ እነሱ እንደሚሉት በሩሲያ ቁጥጥር ስር ከዋለ ፑቲን በዚያች ከተማ ይጥራኝና ሄጄ ጦርነቱን ማቆም በሚቻልበት መንገድ ላይ አወራዋለሁ፡፡ እውነታው ፑቲን ከሚናገረው የተለየ ቢሆንም በጦር ግንባር ያለውን ሁኔታ አይለውጠውም›› ብለዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአንድ ቀን በፊት የሩሲያ ሚዲያዎች ፕሬዝደንት ፑቲንን እንደምንጭነት በመጥቀስ ኮንስታንቲኖቭካ በቁጥጥር ስር መዋሏን ዘግበው ነበር፡፡
በዚህ አስተያየታቸው የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ይህችን ከተማ መቆጣጠራቸውን በተመለከተ የተሰራጨውን ዘገባ ‹‹ፍፁም ውሸት ነው›› ብለውታል፡፡ ሲናገሩም ‹‹በአሜሪካ የነፃነት በአል ዋዜማ ላይ ፑቲን በጦር ግንባር ስላለው ሁኔታ የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨት የአለምን ህዝብና የአሜሪካን ፕሬዝደንት ለመዋሸት ወስኗል፡፡›› ብለዋል፡፡
ጨምረውም ‹‹በእርግጥ በጦር ግንባር ያለው እውነታ እሱ እንደተናገረው እደለም፡፡ ይህ የተለመደ የሩሲያ ውሸት ነው፡፡ ነገር ግን ኮንስታንቲኖቭካ ከተማ እነሱ እንደሚሉት በሩሲያ ቁጥጥር ስር ከዋለ ፑቲን በዚያች ከተማ ይጥራኝና ሄጄ ጦርነቱን ማቆም በሚቻልበት መንገድ ላይ አወራዋለሁ፡፡ እውነታው ፑቲን ከሚናገረው የተለየ ቢሆንም በጦር ግንባር ያለውን ሁኔታ አይለውጠውም›› ብለዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአንድ ቀን በፊት የሩሲያ ሚዲያዎች ፕሬዝደንት ፑቲንን እንደምንጭነት በመጥቀስ ኮንስታንቲኖቭካ በቁጥጥር ስር መዋሏን ዘግበው ነበር፡፡
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) "በመጪው ምርጫ 33 ፐርሰንት ሩሲያዊያን ፑቲንን እንደማይመርጡ መረጃ አግኝቻለሁ" ሲሉ ዘለንስኪ ገለፁ፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ የዛሬ መልእክታቸውን የጀመሩት ‹‹የዩክሬይንን ስለላ ስራዎች ለምትደግፉ ወዳጆቻችንና ጥብቅ መረጃ ለምትሰጡን ሁሉ አመሰግናለሁ›› በማለት ነው፡፡ ሲቀጥሉም የስለላ ተቋሞቻቸው በሩሲያ ያለውን ውስጣዊ ሁኔታ የሚመለከተ መረጃ እንዳደረሷቸው አስታውቀዋል፡፡
በመረጃው መሰረት ሩሲያዊያን በፕሬዝደንት ፑቲን እርምጃ ደስተኛ እንዳልሆኑ መረዳታቸውን ገልፀውም በመጪው ምርጫ 33 ፐርሰንት ያህሉ ሩሲያዊያን ፕሬዝደንቱን እንደማይመርጡ የሚያሳይ ዶክመንት እንዳለ አስታውቀዋል፡፡ ሾልኮ በወጣው መረጃ የፕሬዝደንቱን እርምጃ የሚደግፉት 55 ፐርሰንት መሆናቸውን ያስታወቁት ዘለንስኪ ‹‹ይህም የሩሲያ ገዢ ፓርቲ ተቀባይነት ከቀን ወደቀን እየወረደ መሆኑን የሚያሳይ ነው›› ብለዋል፡፡ የሩሲያ አጠቃላይ ብሄራዊ ምርጫ የፊታችን ሴፕቴምበር 20 የሚከናወን ሲሆን ዘለንስኪ እንዳሉት በሚቀጥሉት ወራት ደግሞ 33 ፐርሰንቱ ሊጨምር ይችላል፡፡
በመረጃው መሰረት ሩሲያዊያን በፕሬዝደንት ፑቲን እርምጃ ደስተኛ እንዳልሆኑ መረዳታቸውን ገልፀውም በመጪው ምርጫ 33 ፐርሰንት ያህሉ ሩሲያዊያን ፕሬዝደንቱን እንደማይመርጡ የሚያሳይ ዶክመንት እንዳለ አስታውቀዋል፡፡ ሾልኮ በወጣው መረጃ የፕሬዝደንቱን እርምጃ የሚደግፉት 55 ፐርሰንት መሆናቸውን ያስታወቁት ዘለንስኪ ‹‹ይህም የሩሲያ ገዢ ፓርቲ ተቀባይነት ከቀን ወደቀን እየወረደ መሆኑን የሚያሳይ ነው›› ብለዋል፡፡ የሩሲያ አጠቃላይ ብሄራዊ ምርጫ የፊታችን ሴፕቴምበር 20 የሚከናወን ሲሆን ዘለንስኪ እንዳሉት በሚቀጥሉት ወራት ደግሞ 33 ፐርሰንቱ ሊጨምር ይችላል፡፡
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእንግሊዝ የጦር ኃይሎች የእንግሊዝን የባህር ወሽመጥ ለማቋረጥ ስትሞክር የነበረችን የሩሲያ ድብቅ የነዳጅ ጫኝ መርከብ አግደው በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ሮይተርስ ዘገበ።
የእንግሊዝ መከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ "ስሚርቶስ" የተሰኘችው ይህች መርከብ በሮያል ማሪን ኮማንዶዎች እና ከብሔራዊ የወንጀል ኤጀንሲ በተውጣጡ ልዩ የህግ አስከባሪ መኮንኖች አማካኝነት ነው በቁጥጥር ስር የዋለችው።
መርከቧ ምርመራው እስኪጠናቀቅ ድረስ በደቡባዊ የሀገሪቱ የባህር ጠረፍ አካባቢ ተይዛ ክትትል እንደሚደረግባት መግለጫው አክሎ አስታውቋል። ሚኒስቴሩ አያይዞም ይህ በሀገሪቱ የግዛት ውሃ ውስጥ የተወሰደው የህግ ማስከበር እርምጃ አገር በቀል እና ዓለም አቀፍ ህጎችን በተከተለ መልኩ የተፈጸመ መሆኑን አብራርቷል።
የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪየር ስታርመር መርከቧ በቁጥጥር ስር እንድትውል ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሰጡት እሳቸው መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኤክስ (ትዊተር) ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ይህ የተሳካ ዘመቻ በሩሲያ ላይ ሌላ ከባድ ምት ያሳረፈ ሲሆን፣ በዩክሬን ውስጥ ለሚካሄደው የፑቲን ጦርነት ነዳጅ ለሚያቀርቡ አካላት ከዚህ በኋላ መደበቅ እንደማይችሉ ግልጽ ማሳሰቢያ የሚሰጥ ነው" በማለት እርምጃውን ገልጸውታል።
የእንግሊዝ መከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ "ስሚርቶስ" የተሰኘችው ይህች መርከብ በሮያል ማሪን ኮማንዶዎች እና ከብሔራዊ የወንጀል ኤጀንሲ በተውጣጡ ልዩ የህግ አስከባሪ መኮንኖች አማካኝነት ነው በቁጥጥር ስር የዋለችው።
መርከቧ ምርመራው እስኪጠናቀቅ ድረስ በደቡባዊ የሀገሪቱ የባህር ጠረፍ አካባቢ ተይዛ ክትትል እንደሚደረግባት መግለጫው አክሎ አስታውቋል። ሚኒስቴሩ አያይዞም ይህ በሀገሪቱ የግዛት ውሃ ውስጥ የተወሰደው የህግ ማስከበር እርምጃ አገር በቀል እና ዓለም አቀፍ ህጎችን በተከተለ መልኩ የተፈጸመ መሆኑን አብራርቷል።
የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪየር ስታርመር መርከቧ በቁጥጥር ስር እንድትውል ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሰጡት እሳቸው መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኤክስ (ትዊተር) ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ይህ የተሳካ ዘመቻ በሩሲያ ላይ ሌላ ከባድ ምት ያሳረፈ ሲሆን፣ በዩክሬን ውስጥ ለሚካሄደው የፑቲን ጦርነት ነዳጅ ለሚያቀርቡ አካላት ከዚህ በኋላ መደበቅ እንደማይችሉ ግልጽ ማሳሰቢያ የሚሰጥ ነው" በማለት እርምጃውን ገልጸውታል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ብሪክስ 50% የሚሆነውን የዓለም ዕድገት መሸፈኑ ጅማሮ ነው - ባለሙያ
#ethiopia | "የአሜሪካ ዶላር ወይም ዩሮ ወይም እንደ ስዊፍት ያሉ አጋች አሠራሮች ሲተኩ፤ እውነተኛው የደቡባዊ ዓለም ፖለቲካዊ እና የኢኮኖሚ አቅም ሊንፀባረቅ ይችላል" ሲሉ ፖል ጎንቻሮፍ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"ብሪክስ እና አጋር ሀገራቱ፤ በአንጻራዊነት በአሜሪካ ወይም የአውሮፓ ኅብረት መመሪያ ረብ የለሽ ማኅበራዊ ሙከራዎችን መፈጸም ሳይጠበቅባቸው በማኅበራዊ፣ በፖለቲካዊ እና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ተጨባጭ እርምጃዎችን የመውሰድ ዝንባሌ አላቸው" ሲሉ አንጋፋው የፋይናንስ ተንታኝ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ጎንቻሮፍ ይህን ያሉት ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በስፒፍ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት 5 ዓመታት የብሪክስ ሀገራት ዓለም አቀፍ የጂዲፒ ዕድገት ከቡድን 7 18% አንጻር 50% የሚሆነውን እንደሚሸፍን መግለጻቸውን ተከትሎ ነው ያለው ስፑትኒክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | "የአሜሪካ ዶላር ወይም ዩሮ ወይም እንደ ስዊፍት ያሉ አጋች አሠራሮች ሲተኩ፤ እውነተኛው የደቡባዊ ዓለም ፖለቲካዊ እና የኢኮኖሚ አቅም ሊንፀባረቅ ይችላል" ሲሉ ፖል ጎንቻሮፍ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"ብሪክስ እና አጋር ሀገራቱ፤ በአንጻራዊነት በአሜሪካ ወይም የአውሮፓ ኅብረት መመሪያ ረብ የለሽ ማኅበራዊ ሙከራዎችን መፈጸም ሳይጠበቅባቸው በማኅበራዊ፣ በፖለቲካዊ እና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ተጨባጭ እርምጃዎችን የመውሰድ ዝንባሌ አላቸው" ሲሉ አንጋፋው የፋይናንስ ተንታኝ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ጎንቻሮፍ ይህን ያሉት ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በስፒፍ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት 5 ዓመታት የብሪክስ ሀገራት ዓለም አቀፍ የጂዲፒ ዕድገት ከቡድን 7 18% አንጻር 50% የሚሆነውን እንደሚሸፍን መግለጻቸውን ተከትሎ ነው ያለው ስፑትኒክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 months ago
ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር በአካል ለመወያየት ጥሪ አቀረቡ
#ethiopia | ዩክሬንና ሩሲያ በቀጥታ በመገናኘት ጦርነቱን እንዲያቆሙ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (ቪዲዮ) ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ በአካል ለመገናኘት ጥሪ ማቅረባቸው ተሰማ።
የአሜሪካ ትኩረት ሙሉ በሙሉ ወደ ኢራን ጉዳይ በዞረበት በዚህ ወቅት፣ ጦርነቱ እንደገና የአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ እስኪሆን ድረስ ዝም ብሎ መጠበቅ ስህተት መሆኑን እና ሰላም ሊመጣ የሚችለው በሁለቱ አገራት ቀጥተኛ ንግግር ብቻ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ለሚካሄደው ድርድር እንዲረዳ ሙሉ የተኩስ አቁም እንዲታወጅ የጠየቁ ቢሆንም፣ ቭላድሚር ፑቲን ግን ከዚህ ቀደም የተኩስ አቁም ጥያቄውን ውድቅ አድርገውታል።
የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰውና ለፑቲን ገለጻ እንደሚደረግላቸው ያረጋገጠ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ሩሲያ ዘለንስኪ ወደ ሞስኮ መጥተው መወያየት እንደሚችሉ ገልጻ ነበር።
ቭላድሚር ፑቲን ስምምነት ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን ቢናገሩም፣ ዩክሬን ዶኔትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ኬርሰን እና ዛፖሪዢያ ከተባሉ አራት ክልሎች እንድትወጣ እና የኔቶ አባል የመሆን ጥረቷን እንድታቆም የሚሉትን ጠንካራ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል፡፡
ዩክሬን ግን ይህንን ግዛቶቿን አሳልፋ መስጠት የሩሲያን ዳግም ወረራ የሚያበረታታ መሆኑን በመግለጽ የሩሲያን ቅድመ ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጋለች።
በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሁለቱ መሪዎች መገናኘት "በጣም ጥሩ ነገር ነው" ሲሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጋዜጣ + #russian #uk #peace #nowar
#ethiopia | ዩክሬንና ሩሲያ በቀጥታ በመገናኘት ጦርነቱን እንዲያቆሙ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (ቪዲዮ) ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ በአካል ለመገናኘት ጥሪ ማቅረባቸው ተሰማ።
የአሜሪካ ትኩረት ሙሉ በሙሉ ወደ ኢራን ጉዳይ በዞረበት በዚህ ወቅት፣ ጦርነቱ እንደገና የአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ እስኪሆን ድረስ ዝም ብሎ መጠበቅ ስህተት መሆኑን እና ሰላም ሊመጣ የሚችለው በሁለቱ አገራት ቀጥተኛ ንግግር ብቻ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ለሚካሄደው ድርድር እንዲረዳ ሙሉ የተኩስ አቁም እንዲታወጅ የጠየቁ ቢሆንም፣ ቭላድሚር ፑቲን ግን ከዚህ ቀደም የተኩስ አቁም ጥያቄውን ውድቅ አድርገውታል።
የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰውና ለፑቲን ገለጻ እንደሚደረግላቸው ያረጋገጠ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ሩሲያ ዘለንስኪ ወደ ሞስኮ መጥተው መወያየት እንደሚችሉ ገልጻ ነበር።
ቭላድሚር ፑቲን ስምምነት ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን ቢናገሩም፣ ዩክሬን ዶኔትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ኬርሰን እና ዛፖሪዢያ ከተባሉ አራት ክልሎች እንድትወጣ እና የኔቶ አባል የመሆን ጥረቷን እንድታቆም የሚሉትን ጠንካራ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል፡፡
ዩክሬን ግን ይህንን ግዛቶቿን አሳልፋ መስጠት የሩሲያን ዳግም ወረራ የሚያበረታታ መሆኑን በመግለጽ የሩሲያን ቅድመ ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጋለች።
በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሁለቱ መሪዎች መገናኘት "በጣም ጥሩ ነገር ነው" ሲሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጋዜጣ + #russian #uk #peace #nowar
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) "የፕሬዝደንት ዘለንስኪ ደብዳቤ ደርሶናል" ስትል ሩሲያ አስታወቀች፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ የፃፉት ግልፅ ደብዳቤ እንደደረሳት ሩሲያ ይፋ አደረገች፡፡ የሩሲያ ቤተመንግስት የሆነው ክሬሚሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ዛሬ በፒትስበርግ እየተከናወነ ባለው አለም አቀፍ የኢኮኖሚ ፎረም ላይ በሰጡት ቃለምልልስ ‹‹ዘለንስኪ የፃፉትን ደብዳቤ በተመለከተ የሰማነው ትላንት ነበር፡፡
ይህንንም ለፕሬዝደንት ፑቲን እንዲደርሳቸው አድርገናል›› ብለዋል፡፡ በደብዳቤው ላይ ፕሬዝደንት ፑቲን ምን አስተያየት እንደሰጡ ተጠይቀው ሲመልሱ ግን ‹‹በዚህ ጉዳይ ከዚህ በላይ መሄድ አልፈልግም›› በማለት ገልፀዋል፡፡ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ ትላንት በፃፉት ግልፅ ደብዳቤ ጦርነቱን ለማቆም የሚያስችል ውይይት በቀጥታ ከሩሲያው አቻቸው ጋር ማድረግ እንደሚፈልጉ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡
በደብዳቤያቸው ከፑቲን ጋር ገለልተኛ በሆነ አገር ለምሳሌ በስዊዘርላንድ፣ በቱርክ ወይንም በአረብ አገራት ውስጥ ፊት ለፊት በመገናኘት ፍላጎት እንዳላቸው የጠቀሱ ሲሆን ውይይቱም ከተኩስ ማቆም አንስቶ እስከ ምርኮኛ መለዋወጥ ድረስ ቢሆን ደስ እንደሚላቸው አስታውቀው ነበር፡፡
ይህንንም ለፕሬዝደንት ፑቲን እንዲደርሳቸው አድርገናል›› ብለዋል፡፡ በደብዳቤው ላይ ፕሬዝደንት ፑቲን ምን አስተያየት እንደሰጡ ተጠይቀው ሲመልሱ ግን ‹‹በዚህ ጉዳይ ከዚህ በላይ መሄድ አልፈልግም›› በማለት ገልፀዋል፡፡ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ ትላንት በፃፉት ግልፅ ደብዳቤ ጦርነቱን ለማቆም የሚያስችል ውይይት በቀጥታ ከሩሲያው አቻቸው ጋር ማድረግ እንደሚፈልጉ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡
በደብዳቤያቸው ከፑቲን ጋር ገለልተኛ በሆነ አገር ለምሳሌ በስዊዘርላንድ፣ በቱርክ ወይንም በአረብ አገራት ውስጥ ፊት ለፊት በመገናኘት ፍላጎት እንዳላቸው የጠቀሱ ሲሆን ውይይቱም ከተኩስ ማቆም አንስቶ እስከ ምርኮኛ መለዋወጥ ድረስ ቢሆን ደስ እንደሚላቸው አስታውቀው ነበር፡፡
2 months ago
"ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከእኔ ጋር ፊት ለፊት ይወያዩ" - ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ
"ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" - ክሬምሊን
******************
በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ሊያስቆም ይችላል የተባለ አዲስ የዲፕሎማሲ ሐሳብ ከወደ ኪዬቭ ተሰምቷል።
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቀን እንዲቆርጡ ጠይቀዋል።
ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በላኩት ደብዳቤ፤ "ቀን አስቀምጥ እና ፊት ለፊት እንገናኝ" ያሉ ሲሆን፣ በገለልተኛ ሀገር ውስጥ ቀጥታ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
በተጨማሪም በውይይቱ ላይ አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገራት እንዲገኙ እንደሚፈልጉ በደብዳቤያቸው ጠቅሰዋል።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ድሚትሪ ፔስኮቭ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት የላኩት ደብዳቤ እንደደረሳቸው ያረጋገጡ ሲሆን፣ "ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" ብለዋል።
በዚህ ሰዓት የዓለም ትኩረት ያረፈው በአንድ ጥያቄ ላይ ነው፤ ፕሬዚዳንት ፑቲን የዩክሬኑ አቻቸው ያቀረቡላቸውን ጥሪ ይቀበሉ ይሆን? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#ebc #ukraine #russia #zelensky #putin #peacetalks #diplomacy
"ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" - ክሬምሊን
******************
በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ሊያስቆም ይችላል የተባለ አዲስ የዲፕሎማሲ ሐሳብ ከወደ ኪዬቭ ተሰምቷል።
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቀን እንዲቆርጡ ጠይቀዋል።
ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በላኩት ደብዳቤ፤ "ቀን አስቀምጥ እና ፊት ለፊት እንገናኝ" ያሉ ሲሆን፣ በገለልተኛ ሀገር ውስጥ ቀጥታ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
በተጨማሪም በውይይቱ ላይ አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገራት እንዲገኙ እንደሚፈልጉ በደብዳቤያቸው ጠቅሰዋል።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ድሚትሪ ፔስኮቭ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት የላኩት ደብዳቤ እንደደረሳቸው ያረጋገጡ ሲሆን፣ "ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" ብለዋል።
በዚህ ሰዓት የዓለም ትኩረት ያረፈው በአንድ ጥያቄ ላይ ነው፤ ፕሬዚዳንት ፑቲን የዩክሬኑ አቻቸው ያቀረቡላቸውን ጥሪ ይቀበሉ ይሆን? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#ebc #ukraine #russia #zelensky #putin #peacetalks #diplomacy
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ቻይና እና ሩሲያ የኢራንን ከፍተኛ መጠን ያለው የበለጸገ ዩራኒየም ደህንነት ለማረጋገጥ እና ለማከማቸት በድርድር ላይ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተገለጸ።
በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢራን ጉዳዮች ጊዜያዊ ዳይሬክተር የነበሩት ጆይ ሁድ ለአልጀዚራ እንደተናገሩት፣ የኢራን ከፍተኛ መጠን ያለው የበለጸገ ዩራኒየም ከአሜሪካ ጋር ለሚደረግ ማንኛውም የሰላም ስምምነት "የሁሉም ነገር ቁልፍ" ነው። ዳይሬክተሩ አክለውም፣ 441 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የኢራን ዩራኒየም እስከ 60 በመቶ የበለጸገ በመሆኑ ለሲቪል (ሰላማዊ) አገልግሎት የሚውልበት ምንም ዓይነት ዕድል እንደሌለው እና ለወታደራዊ የጦር መሳሪያ ማምረቻ ብቻ ሊያገለግል እንደሚችል አስረድተዋል።
በመሆኑም "በመጨረሻ ሩሲያ እና ቻይናም ቢሆኑ ይህ ዩራኒየም ከኢራን ወጥቶ ደህንነቱ በተጠበቀ ስፍራ እንዲቀመጥ (ወደ እነርሱ እንዲዘዋወር) መስማማታቸው አይቀርም" ብለዋል።
የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ እና የሩሲያው ቭላድሚር ፑቲን በዚህ ሳምንት ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኢራንን ዩራኒየም ስለመረከብ እና ማከማቸት ጉዳይ ተነጋግረው ሊሆን እንደሚችል ጆይ ሁድ ግምታቸውን አስቀምጠዋል። "በቤጂንግ በዚህ ጉዳይ ላይ ጸጥ ያለ (ሚስጥራዊ) ውይይት ተደርጎ ሊሆን ይችላል፤ ምናልባትም ከኢራናውያን ጋርም እየተነጋገሩ ይሆናል። ይህንን ወደፊት የምናየው ይሆናል" በማለት ሁኔታውን አብራርተዋል።
በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢራን ጉዳዮች ጊዜያዊ ዳይሬክተር የነበሩት ጆይ ሁድ ለአልጀዚራ እንደተናገሩት፣ የኢራን ከፍተኛ መጠን ያለው የበለጸገ ዩራኒየም ከአሜሪካ ጋር ለሚደረግ ማንኛውም የሰላም ስምምነት "የሁሉም ነገር ቁልፍ" ነው። ዳይሬክተሩ አክለውም፣ 441 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የኢራን ዩራኒየም እስከ 60 በመቶ የበለጸገ በመሆኑ ለሲቪል (ሰላማዊ) አገልግሎት የሚውልበት ምንም ዓይነት ዕድል እንደሌለው እና ለወታደራዊ የጦር መሳሪያ ማምረቻ ብቻ ሊያገለግል እንደሚችል አስረድተዋል።
በመሆኑም "በመጨረሻ ሩሲያ እና ቻይናም ቢሆኑ ይህ ዩራኒየም ከኢራን ወጥቶ ደህንነቱ በተጠበቀ ስፍራ እንዲቀመጥ (ወደ እነርሱ እንዲዘዋወር) መስማማታቸው አይቀርም" ብለዋል።
የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ እና የሩሲያው ቭላድሚር ፑቲን በዚህ ሳምንት ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኢራንን ዩራኒየም ስለመረከብ እና ማከማቸት ጉዳይ ተነጋግረው ሊሆን እንደሚችል ጆይ ሁድ ግምታቸውን አስቀምጠዋል። "በቤጂንግ በዚህ ጉዳይ ላይ ጸጥ ያለ (ሚስጥራዊ) ውይይት ተደርጎ ሊሆን ይችላል፤ ምናልባትም ከኢራናውያን ጋርም እየተነጋገሩ ይሆናል። ይህንን ወደፊት የምናየው ይሆናል" በማለት ሁኔታውን አብራርተዋል።
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥምረት በኢራን ላይ የተከፈተው ጦርነት የዓለምን የነዳጅ ገበያ እያናጋው ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ የሩሲያ ድፍድፍ ነዳጅ የዚህ ቀውስ ዋነኛ ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱን አልጀዚራ የኢነርጂ ተንታኞችን ጠቅሶ ዘገበ።
የነዳጅ ዋጋ መናር እና የዓለም ሀገራት የገጠማቸውን የኃይል አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ ያደረጉት ሽሚያ ለሩሲያ ከፍተኛ ገቢ እያስገኘላት ይገኛል።
1. የሆርሙዝ የባህር በር መዘጋት እና የትራምፕ ያልተጠበቀ ውሳኔ
የኢራን መንግስት በቀን 20 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ የሚንሸራሸርበትንና የዓለምን 20 በመቶ የነዳጅ ፍላጎት የሚሸፍነውን የሆርሙዝ የባህር በር ሙሉ በሙሉ መዝጋቱ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ከ65 ዶላር ተነስቶ ከ100 ዶላር በላይ እንዲያልፍ አድርጎታል። አንዳንድ ባለሙያዎች ዋጋው እስከ 200 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል እየገመቱ ነው።
ይህንን ተከትሎ የገጠመውን የነዳጅ እጥረት ለማቃለል፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ ከተወያዩ በኋላ፣ በሩሲያ ነዳጅ ላይ ተጥሎ የነበረውን ማዕቀብ ለተወሰኑ ሀገራት በጊዜያዊነት ለማላላት ወስነዋል። ይህ ውሳኔ ሩሲያ የዓለምን የነዳጅ ፍላጎት ክፍተት እንድትሞላ ትልቅ ዕድል ሰጥቷታል።
2. ሩሲያ በሁለት ሳምንት ውስጥ ያገኘችው ግዙፍ ገቢ
ከዚህ ቀደም በምዕራባውያን ማዕቀብ ምክንያት ከአንድ በርሜል 60 ዶላር በታች ይሸጥ የነበረው የሩሲያ "ኡራልስ" (Urals) ነዳጅ፣ አሁን ላይ ፍላጎቱ በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ ወደ 90 ዶላር ተጠግቷል። ይህም የቡድን 7 ሀገራት ጥለውት ከነበረው የዋጋ ጣሪያ እጅግ የላቀ ነው።
የኃይል ምርምር ተቋማት መረጃ እንደሚያሳየው፣ ጦርነቱ ከጀመረበት ካለፈው የካቲት ወር ማጠናቀቂያ ጀምሮ ባሉት የመጀመሪያዎቹ ሁለት ሳምንታት ብቻ ሩሲያ ተጨማሪ 672 ሚሊዮን ዩሮ (777 ሚሊዮን ዶላር) ማግኘት ችላለች።
3. የመርከቦች አቅጣጫ መቀየር እና ዋና ገዢዎች
ህንድ ከአሜሪካ የፋይናንስ ሚኒስቴር የሩሲያን ነዳጅ ለመግዛት ልዩ ፈቃድ በማግኘቷ፣ ቀደም ሲል ወደ ቻይና ያመሩ የነበሩ በርካታ የሩሲያ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች አቅጣጫቸውን በመቀየር ወደ ህንድ ወደቦች እየገቡ ይገኛሉ።
በአሁኑ ወቅት የሩሲያ ነዳጅ ዋነኛ ገዢዎች ህንድ እና ቻይና ሲሆኑ፣ ቱርክም በኢራን የጋዝ ማውጫ ላይ ከተሰነዘረው ጥቃት በኋላ የገጠማትን የሃይል እጥረት ለመቅረፍ የሩሲያን ነዳጅ በከፍተኛ ሁኔታ እየገዛች ትገኛለች። ከእነዚህም በተጨማሪ ሩሲያ "የጥላ መርከቦች" (Shadow fleet) የሚባሉትን ያልተመዘገቡ አሮጌ መርከቦችን በመጠቀም ነዳጇን ወደ ተለያዩ የእስያ ሀገራት በድብቅ እያጓጓዘች ነው።
4. ሌሎች ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ሀገራት
ከኦፔክ ውጭ የሆኑት ኖርዌይ እና ካናዳ የዚህ ነዳጅ ቀውስ ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ሀገራት ናቸው። ኖርዌይ ለአውሮፓ ሀገራት የምታቀርበውን የነዳጅ እና ጋዝ ምርት ለማሳደግ ቃል የገባች ሲሆን፣ ካናዳም ወደ አሜሪካ የምትልከውን መጠን ለመጨመር እየሞከረች ነው። ሆኖም ሁለቱም ሀገራት በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርታቸውን በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ የማምረቻ እና የቧንቧ መሰረተ ልማት እጥረት ይፈታተናቸዋል።
የነዳጅ ዋጋ መናር እና የዓለም ሀገራት የገጠማቸውን የኃይል አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ ያደረጉት ሽሚያ ለሩሲያ ከፍተኛ ገቢ እያስገኘላት ይገኛል።
1. የሆርሙዝ የባህር በር መዘጋት እና የትራምፕ ያልተጠበቀ ውሳኔ
የኢራን መንግስት በቀን 20 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ የሚንሸራሸርበትንና የዓለምን 20 በመቶ የነዳጅ ፍላጎት የሚሸፍነውን የሆርሙዝ የባህር በር ሙሉ በሙሉ መዝጋቱ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ከ65 ዶላር ተነስቶ ከ100 ዶላር በላይ እንዲያልፍ አድርጎታል። አንዳንድ ባለሙያዎች ዋጋው እስከ 200 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል እየገመቱ ነው።
ይህንን ተከትሎ የገጠመውን የነዳጅ እጥረት ለማቃለል፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ ከተወያዩ በኋላ፣ በሩሲያ ነዳጅ ላይ ተጥሎ የነበረውን ማዕቀብ ለተወሰኑ ሀገራት በጊዜያዊነት ለማላላት ወስነዋል። ይህ ውሳኔ ሩሲያ የዓለምን የነዳጅ ፍላጎት ክፍተት እንድትሞላ ትልቅ ዕድል ሰጥቷታል።
2. ሩሲያ በሁለት ሳምንት ውስጥ ያገኘችው ግዙፍ ገቢ
ከዚህ ቀደም በምዕራባውያን ማዕቀብ ምክንያት ከአንድ በርሜል 60 ዶላር በታች ይሸጥ የነበረው የሩሲያ "ኡራልስ" (Urals) ነዳጅ፣ አሁን ላይ ፍላጎቱ በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ ወደ 90 ዶላር ተጠግቷል። ይህም የቡድን 7 ሀገራት ጥለውት ከነበረው የዋጋ ጣሪያ እጅግ የላቀ ነው።
የኃይል ምርምር ተቋማት መረጃ እንደሚያሳየው፣ ጦርነቱ ከጀመረበት ካለፈው የካቲት ወር ማጠናቀቂያ ጀምሮ ባሉት የመጀመሪያዎቹ ሁለት ሳምንታት ብቻ ሩሲያ ተጨማሪ 672 ሚሊዮን ዩሮ (777 ሚሊዮን ዶላር) ማግኘት ችላለች።
3. የመርከቦች አቅጣጫ መቀየር እና ዋና ገዢዎች
ህንድ ከአሜሪካ የፋይናንስ ሚኒስቴር የሩሲያን ነዳጅ ለመግዛት ልዩ ፈቃድ በማግኘቷ፣ ቀደም ሲል ወደ ቻይና ያመሩ የነበሩ በርካታ የሩሲያ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች አቅጣጫቸውን በመቀየር ወደ ህንድ ወደቦች እየገቡ ይገኛሉ።
በአሁኑ ወቅት የሩሲያ ነዳጅ ዋነኛ ገዢዎች ህንድ እና ቻይና ሲሆኑ፣ ቱርክም በኢራን የጋዝ ማውጫ ላይ ከተሰነዘረው ጥቃት በኋላ የገጠማትን የሃይል እጥረት ለመቅረፍ የሩሲያን ነዳጅ በከፍተኛ ሁኔታ እየገዛች ትገኛለች። ከእነዚህም በተጨማሪ ሩሲያ "የጥላ መርከቦች" (Shadow fleet) የሚባሉትን ያልተመዘገቡ አሮጌ መርከቦችን በመጠቀም ነዳጇን ወደ ተለያዩ የእስያ ሀገራት በድብቅ እያጓጓዘች ነው።
4. ሌሎች ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ሀገራት
ከኦፔክ ውጭ የሆኑት ኖርዌይ እና ካናዳ የዚህ ነዳጅ ቀውስ ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ሀገራት ናቸው። ኖርዌይ ለአውሮፓ ሀገራት የምታቀርበውን የነዳጅ እና ጋዝ ምርት ለማሳደግ ቃል የገባች ሲሆን፣ ካናዳም ወደ አሜሪካ የምትልከውን መጠን ለመጨመር እየሞከረች ነው። ሆኖም ሁለቱም ሀገራት በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርታቸውን በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ የማምረቻ እና የቧንቧ መሰረተ ልማት እጥረት ይፈታተናቸዋል።
3 months ago
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቤጂንግ ገቡ
#ethiopia | ፑቲን ቤጂንግ ሲደርሱ በቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ግንቦት 12 ፑቲን እና ሺ ጂንፒንግ በመጀመሪያ በጥቂት ቡድን፣ በመቀጠልም የየአገራቱ ልዑካን ቡድን አባላት በሚሳተፉበት ሰፊ ስብሰባ ላይ ውይይት ያደርጋሉ።
በተጨማሪም የሩሲያ እና የቻይና መሪዎች የሚሳተፉበት የሻይ ሥነ-ሥርዓት አቀባበል ተዘጋጅቷል ያለው ስፑትኒክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #get
#ethiopia | ፑቲን ቤጂንግ ሲደርሱ በቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ግንቦት 12 ፑቲን እና ሺ ጂንፒንግ በመጀመሪያ በጥቂት ቡድን፣ በመቀጠልም የየአገራቱ ልዑካን ቡድን አባላት በሚሳተፉበት ሰፊ ስብሰባ ላይ ውይይት ያደርጋሉ።
በተጨማሪም የሩሲያ እና የቻይና መሪዎች የሚሳተፉበት የሻይ ሥነ-ሥርዓት አቀባበል ተዘጋጅቷል ያለው ስፑትኒክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #get
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ሩሲያ ከ64 ሺህ በላይ ወታደሮች የሚሳተፉበት የኒውክሌይር ጦር መሳሪያ ልምምድ ማድረግ ጀመረች፡፡ የሩሲያ መከላከያ ሀይል በአይነቱ ትልቅ የሚባል የኒውክሌይር ጦር መሳሪያ ልምምድ ዛሬ መጀመሩን አስታውቋል፡፡
ለ3 ቀናት በሚቆየው በዚህ ልምምድ ላይ ከ64,000 በላይ ወታደሮችና ከ7,800 በላይ የጦር መሳሪያዎች፣ ወታደራዊ ቁሳቁሶችና ተሸከርካሪዎች እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡ ከእነዚህ መካከል 200 ሚሳኤል ማስወንጨፊያዎች፣ ከ140 በላይ የጦር ጀቶች፣ 73 ጀልባዎች፣ 13 ባህር ሰርጓጆችና ስምንት ሚሳኤል ተሸካሚ ባህር ሰርጓጅ መርከቦች እንደሚገኙበት የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር አስረድቷል፡፡
እንደመግለጫው በዚህ ልምምድ ላይ የተለያዩ አይነት የባለስቲክና ክሩዝ ሚሳኤሎችን የማስወንጨፍ ሙከራም የሚከናወን ሲሆን አላማውም ‹‹ወረራ የሚከሰት ከሆነ የጦር ሀይሉ በኒውክሌይር ጦር መሳሪያ ብቃት ያለው እንዲሆን ለማዘጋጀት›› መሆኑን ገልጿል፡፡ በዚህ ልምምድ ወቅት በቤላሩስ በተቀመጠው የኒውክሌይር ጦር መሳሪያ ጥምር ስልጠና የሚከናወን ይሆናል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የቤላሩስ መከላከያ ሀይል በበኩሉ ከሩሲያ ጋር በመሆን የኒውክሌይር ጦር መሳሪያ ልምምድ እያከናወነ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ይህ ልምምድ የተጀመረው የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በቻይና ጉብኝት በሚያደርጉበት ወቅት ነው፡፡
ለ3 ቀናት በሚቆየው በዚህ ልምምድ ላይ ከ64,000 በላይ ወታደሮችና ከ7,800 በላይ የጦር መሳሪያዎች፣ ወታደራዊ ቁሳቁሶችና ተሸከርካሪዎች እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡ ከእነዚህ መካከል 200 ሚሳኤል ማስወንጨፊያዎች፣ ከ140 በላይ የጦር ጀቶች፣ 73 ጀልባዎች፣ 13 ባህር ሰርጓጆችና ስምንት ሚሳኤል ተሸካሚ ባህር ሰርጓጅ መርከቦች እንደሚገኙበት የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር አስረድቷል፡፡
እንደመግለጫው በዚህ ልምምድ ላይ የተለያዩ አይነት የባለስቲክና ክሩዝ ሚሳኤሎችን የማስወንጨፍ ሙከራም የሚከናወን ሲሆን አላማውም ‹‹ወረራ የሚከሰት ከሆነ የጦር ሀይሉ በኒውክሌይር ጦር መሳሪያ ብቃት ያለው እንዲሆን ለማዘጋጀት›› መሆኑን ገልጿል፡፡ በዚህ ልምምድ ወቅት በቤላሩስ በተቀመጠው የኒውክሌይር ጦር መሳሪያ ጥምር ስልጠና የሚከናወን ይሆናል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የቤላሩስ መከላከያ ሀይል በበኩሉ ከሩሲያ ጋር በመሆን የኒውክሌይር ጦር መሳሪያ ልምምድ እያከናወነ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ይህ ልምምድ የተጀመረው የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በቻይና ጉብኝት በሚያደርጉበት ወቅት ነው፡፡
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቻይናን ሊጎበኙ ነው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪው ሳምንት በቻይና ይፋዊ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ክሬምሊን አስታውቋል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቀናት በፊት በቻይና ይፋዊ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፥ በቤጂንግ ቆይታቸው ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በሁለትዮሽና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ሺ ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጉብኝት በኋላ በቀናት ልዩነት የሩሲያ አቻቸውን ቭላድሚር ፑቲን ይቀበላሉ፡፡
ፕሬዚዳንት ፑቲን ከመጪው ማክሰኞ ጀምሮ በሚያደርጉት የሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት በንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ዙሪያ ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር እንደሚመክሩ ተገልጿል፡፡
ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የጠበቀ አጋርነትና ስትራቴጂያዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመ መሆኑን የፕሬዚዳንቱን ጽ/ቤት ጠቅሶ የሩሲያ የዜና ወኪል ታስ ዘግቧል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቻይና ቆይታቸው ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከል የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት አንዱ እንደነበር ይታወሳል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪው ሳምንት በቻይና ይፋዊ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ክሬምሊን አስታውቋል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቀናት በፊት በቻይና ይፋዊ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፥ በቤጂንግ ቆይታቸው ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በሁለትዮሽና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ሺ ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጉብኝት በኋላ በቀናት ልዩነት የሩሲያ አቻቸውን ቭላድሚር ፑቲን ይቀበላሉ፡፡
ፕሬዚዳንት ፑቲን ከመጪው ማክሰኞ ጀምሮ በሚያደርጉት የሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት በንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ዙሪያ ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር እንደሚመክሩ ተገልጿል፡፡
ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የጠበቀ አጋርነትና ስትራቴጂያዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመ መሆኑን የፕሬዚዳንቱን ጽ/ቤት ጠቅሶ የሩሲያ የዜና ወኪል ታስ ዘግቧል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቻይና ቆይታቸው ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከል የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት አንዱ እንደነበር ይታወሳል፡፡
3 months ago
በኤራን ዩራንየም ጉዳይ ሩስያ ድጋፍ የማድረግ ሃሳብ ማቅረቧን ኢራን አረጋገጠች
ኢራን ከምዕራቡ ዓለም ጋር በሚያወዛግባት በኒዩክልየር ጉዳይ ላይ ሩስያ የበኩሏን ድጋፍ የማድረግ ሃሳብ እንዳቀረበች ኢራን አረጋገጠች። የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ፤ ዛሬ ኒውዴልሂ ውስጥ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በሩስያ ጉብኝታቸው ወቅት ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ስለ ዩራንየም ጉዳይ መነጋገራቸውን ገልጸው፤ ድጋፍ ለመስጠት ላቀረቡት ሀሳባቸውም አመሰግናቸዋለሁ ብለዋል።
ከብሪክስ አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን አራግቺ በሰጡት በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ፑቲን በቅርቡ ስለዚሁ ጉዳይ የተናገሩትን አረጋግጠዋል። ፑቲን ባለፈው ሳምንት ሀገራቸው በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተጎናጸፈችው ድል በተዘከረበት የመታሰቢያ እለት ሩሲያ በከፍተኛ ደረጃ የበለፀገ ዩራኒየምን ከኢራን ወስዳ ለማከማቸት ዝግጁ መሆኗን አስታውቀው ነበር።
የኢራን የኒዩክልየር መርሀ ግብር ሲያወዛግብ ብዙ ዓመታት አስቆጥሯል። ዩናይትድ ስቴትስ እሥራኤል እና ምዕራባውያን ሀገራት ቴህራን የኒዩክልየር ጦር መሣሪያዎችን ለማምረት ትፈልጋለች ሲሉ ይከሷታል። ኢራን ግን ይህን ታስተባብላለች። ምዕራቡ ዓለም ኢራን አሁን ያላት የዩራንየም ክምችት ከለማ በርካታ የኒዩክልየር ጦር መሣሪያዎች ለመስራት በቂ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት አለው።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን የሚገኘው ዩራንየም ከሀገሪቱ እንዲወጣ ግፊት እያደረጉ ነው። ዩራንየሙ ከምድር በታች ከሚገኙ የኢራን የኒዩክልየር ተቋማት በአንዱ ውስጥ ተከማችቷል ተብሎ ይገመታል።
DW Amharic
ኢራን ከምዕራቡ ዓለም ጋር በሚያወዛግባት በኒዩክልየር ጉዳይ ላይ ሩስያ የበኩሏን ድጋፍ የማድረግ ሃሳብ እንዳቀረበች ኢራን አረጋገጠች። የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ፤ ዛሬ ኒውዴልሂ ውስጥ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በሩስያ ጉብኝታቸው ወቅት ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ስለ ዩራንየም ጉዳይ መነጋገራቸውን ገልጸው፤ ድጋፍ ለመስጠት ላቀረቡት ሀሳባቸውም አመሰግናቸዋለሁ ብለዋል።
ከብሪክስ አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን አራግቺ በሰጡት በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ፑቲን በቅርቡ ስለዚሁ ጉዳይ የተናገሩትን አረጋግጠዋል። ፑቲን ባለፈው ሳምንት ሀገራቸው በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተጎናጸፈችው ድል በተዘከረበት የመታሰቢያ እለት ሩሲያ በከፍተኛ ደረጃ የበለፀገ ዩራኒየምን ከኢራን ወስዳ ለማከማቸት ዝግጁ መሆኗን አስታውቀው ነበር።
የኢራን የኒዩክልየር መርሀ ግብር ሲያወዛግብ ብዙ ዓመታት አስቆጥሯል። ዩናይትድ ስቴትስ እሥራኤል እና ምዕራባውያን ሀገራት ቴህራን የኒዩክልየር ጦር መሣሪያዎችን ለማምረት ትፈልጋለች ሲሉ ይከሷታል። ኢራን ግን ይህን ታስተባብላለች። ምዕራቡ ዓለም ኢራን አሁን ያላት የዩራንየም ክምችት ከለማ በርካታ የኒዩክልየር ጦር መሣሪያዎች ለመስራት በቂ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት አለው።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን የሚገኘው ዩራንየም ከሀገሪቱ እንዲወጣ ግፊት እያደረጉ ነው። ዩራንየሙ ከምድር በታች ከሚገኙ የኢራን የኒዩክልየር ተቋማት በአንዱ ውስጥ ተከማችቷል ተብሎ ይገመታል።
DW Amharic
3 months ago
ሩሲያ ሰይጣን ሁለት ከተሰኘዉ ሚሳኤል የበለጠና በዓለም ላይ እጅግ ኃይለኛ የተባለዉን የሚሳኤል ሙከራ አደረገች
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የኒውክሌርን አቅም ያለው ሳርማት መሳሪያ የአለም "ኃይለኛ" ሚሳኤል ሙከራን ሩሲያ አዲስ አህጉር አቀፍ ባሊስቲክ ሚሳኤል ሙከራ አድርጋለች ሲሉ ተናገሩ።ሞስኮ ማክሰኞ እለት በተሳካ ሁኔታ ሙከራዉ መደረጉን የሩስያ የስትራቴጂክ ሚሳኤል ጦር አዛዥ ሰርጌይ ካራካዬቭን ለፑቲን ሪፖርተ ማቅረባቸዉን የመንግስት ቴሌቪዥን በምስል ባወጣዉ ዘገባ አሰራጭቷል።
ፑቲን የሳርማት ሚሳኤል በዓመቱ መጨረሻ ወደ ፍልሚያ አገልግሎት እንደሚገባ ተናግረዋል። በቴሌቭዥን ዘገባዉ ላይ "ይህ በዓለም ላይ በጣም ኃይለኛው ሚሳኤል ነው" በማለት የጦርነት መጠን ላይ ከምዕራባውያን አቻዎች በአራት እጥፍ እንደሚበልጥ ተመላክቷል፡፡ፑቲን ሳርማት ከ 35,000 ኪ.ሜ የሚበልጥ ርቀት በመጓዝ የከርሰ ምድር በረራ ችሎታ እንዳለው እና "ወደ ሁሉም ነባር እና የወደፊት የፀረ-ሚሳኤል መከላከያ ስርዓቶች ውስጥ ዘልቆ መግባት ይችላል" ብለዋል ።
ይህዉ ቴክኖሎጂ ከዓመታት ውድቀት በኋላ የመጣ ስኬት ነዉ፡፡የሳርማት ልማት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ20111 ሲሆን ሚሳኤሉ አንድ የታወቀ የተሳካ ሙከራ ብቻ ተደርጎለታል፤ በ 2024 ዓመት በሙከራ ወቅት ከፍተኛ ፍንዳታ ደርሶበት እንደነበር ይታወሳል፡፡በምዕራቡ ዓለም "ሰይጣን ሁለት" ተብሎ የተሰየመው ሳርማት ወደ 40 የሚጠጉ በሶቪየት የተሰሩ የቮዬቮዳ ሚሳኤሎችን ለመተካት ታስቦ ነው። ፑቲን እንዳሉት ሳርማት እንደ ቮዬቮዳ ኃይለኛ ቢሆንም ከፍተኛ እና ትክክለኛነት አለው ብለዋል፡፡
በስምዖን ደረጄ
seledadotio
seledadotio
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የኒውክሌርን አቅም ያለው ሳርማት መሳሪያ የአለም "ኃይለኛ" ሚሳኤል ሙከራን ሩሲያ አዲስ አህጉር አቀፍ ባሊስቲክ ሚሳኤል ሙከራ አድርጋለች ሲሉ ተናገሩ።ሞስኮ ማክሰኞ እለት በተሳካ ሁኔታ ሙከራዉ መደረጉን የሩስያ የስትራቴጂክ ሚሳኤል ጦር አዛዥ ሰርጌይ ካራካዬቭን ለፑቲን ሪፖርተ ማቅረባቸዉን የመንግስት ቴሌቪዥን በምስል ባወጣዉ ዘገባ አሰራጭቷል።
ፑቲን የሳርማት ሚሳኤል በዓመቱ መጨረሻ ወደ ፍልሚያ አገልግሎት እንደሚገባ ተናግረዋል። በቴሌቭዥን ዘገባዉ ላይ "ይህ በዓለም ላይ በጣም ኃይለኛው ሚሳኤል ነው" በማለት የጦርነት መጠን ላይ ከምዕራባውያን አቻዎች በአራት እጥፍ እንደሚበልጥ ተመላክቷል፡፡ፑቲን ሳርማት ከ 35,000 ኪ.ሜ የሚበልጥ ርቀት በመጓዝ የከርሰ ምድር በረራ ችሎታ እንዳለው እና "ወደ ሁሉም ነባር እና የወደፊት የፀረ-ሚሳኤል መከላከያ ስርዓቶች ውስጥ ዘልቆ መግባት ይችላል" ብለዋል ።
ይህዉ ቴክኖሎጂ ከዓመታት ውድቀት በኋላ የመጣ ስኬት ነዉ፡፡የሳርማት ልማት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ20111 ሲሆን ሚሳኤሉ አንድ የታወቀ የተሳካ ሙከራ ብቻ ተደርጎለታል፤ በ 2024 ዓመት በሙከራ ወቅት ከፍተኛ ፍንዳታ ደርሶበት እንደነበር ይታወሳል፡፡በምዕራቡ ዓለም "ሰይጣን ሁለት" ተብሎ የተሰየመው ሳርማት ወደ 40 የሚጠጉ በሶቪየት የተሰሩ የቮዬቮዳ ሚሳኤሎችን ለመተካት ታስቦ ነው። ፑቲን እንዳሉት ሳርማት እንደ ቮዬቮዳ ኃይለኛ ቢሆንም ከፍተኛ እና ትክክለኛነት አለው ብለዋል፡፡
በስምዖን ደረጄ
seledadotio
seledadotio
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፣ አዲሱ ስትራቴጂካዊ የኒውክሌር አህጉር አቋራጭ ባለስቲክ ሚሳኤል 'ሳርማት' በዚህ አመት መጨረሻ ላይ ይፋዊ ስምሪት እንደሚያገኝ አስታወቁ። ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያስታወቁት ማክሰኞ ዕለት የተካሄደውን የሚሳኤሉን የሙከራ ትርኢት ተከትሎ በሰጡት መግለጫ ነው።
ሳርማት (በኔቶ መጠሪያ "ሰይጣን ዳግማዊ" የሚባለው፣ ሩሲያ ከሶቪየት ህብረት ውድቀት በኋላ ካመረተቻቸው አህጉር አቋራጭ ሚሳኤሎች መካከል "እጅግ ከባድ" በሚል ምድብ የተመደበው የመጀመሪያው ነው።
በአሜሪካ ወይም በአውሮፓ በሺዎች የሚቆጠሩ ማይሎች ርቀት ላይ የሚገኙ ኢላማዎችን በኒውክሌር አረር ለመምታት የተነደፈው ይህ ሚሳኤል፣ ለዓመታት ባጋጠመው መጓተት እና መዘግየት ምክንያት ስምሪቱ ሲራዘም መቆየቱ ይታወሳል።
ፕሬዝዳንት ፑቲን በቴሌቪዥን መስኮት በሰጡት ቃል፣ የሳርማት የኒውክሌር አረር የማፈንዳት አቅም ከማንኛውም የምዕራባውያን አቻው ከአራት እጥፍ በላይ እንደሚበልጥ፣ እና ከ35,000 ኪ.ሜ (21,750 ማይል) በላይ ርቀት መምታት እንደሚችል አስረድተዋል።
"አሁን ያሉትንም ሆነ ወደፊት የሚመጡትን ፀረ-ሚሳኤል መከላከያ ስርዓቶች ጥሶ የመግባት አቅም አለው" ያሉት ፑቲን፣ የጦር መሳሪያውን "በአለም ላይ እጅግ ሀይለኛው የሚሳኤል ስርዓት" ሲሉ በከፍተኛ ኩራት ገልጸውታል።
የምዕራባውያን የፀጥታ ተንታኞች ግን ፑቲን በ2018 እ.ኤ.አ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሳወቁትን የጦር መሳሪያ ዘመናዊ የማድረግ ፕሮግራም አካል የሆኑትን አዳዲስ የኒውክሌር መሳሪያዎች አቅም አጋንነው እየገለፁ ነው ሲሉ ይሞግታሉ። ባለሙያዎቹ እንደሚሉት፣ ሳርማት ከዚህ ቀደም ውድቀቶች አጋጥመውታል፤ ለአብነትም በመስከረም 2024 የተደረገው ሙከራ በሚሳኤል ማስወንጨፊያው ላይ ጥልቅ ጉድጓድ ጥሎ ማለፉን ያስታውሳሉ።
ይሁን እንጂ የሩሲያ ስትራቴጂካዊ የሚሳኤል ሃይሎች አዛዥ የሆኑት ሰርጌይ ካራካዬቭ፣ የማክሰኞው የሳርማት ሙከራ የተሳካ እንደነበር ለፑቲን ሪፖርት ሲያደርጉ በመንግስት ቴሌቪዥን ታይተዋል። ካራካዬቭ እንዳሉት፣ "ሳርማት የሚሳኤል ስርዓት የተገጠመላቸው ማስወንጨፊያዎች መሰማራታቸው... የስትራቴጂካዊ የኒውክሌር ሃይሎችን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድጋል።"
እ.ኤ.አ በ2022 የዩክሬን ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ ፑቲን የሩሲያን የኒውክሌር መሳሪያ ብዛት እና ሀይል ለአለም በተደጋጋሚ ሲያስታውሱ ቆይተዋል። ይህ አካሄዳቸው ምዕራባውያን በዩክሬን ጦርነት ውስጥ ጣልቃ እንዳይገቡ ለማስፈራራት ያለመ መሆኑ ይነገራል።
የተባበሩት መንግስታት ትጥቅ ማስፈታት ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ፓቬል ፖድቪግ በበኩላቸው፣ የሩሲያ "ትልቁ ሚሳኤል" በዚህ ዓመት መሰማራቱ እውን መሆኑን ቢያምኑም፣ ይህ ግን "የሩሲያን ስትራቴጂካዊ ሃይሎች የመከላከል አቅም ላይ ጉልህ ለውጥ ያመጣል" ብለው እንደማያስቡ ተናግረዋል።
የሩሲያው የዜና ወኪል እንደዘገበው፣ ክሬምሊን ለሚሳኤል ሙከራው አሜሪካን አስቀድሞ አሳውቆ ነበር። ሆኖም፣ ሞስኮ እና ዋሽንግተን የ 'ኒው ስታርት' የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ቁጥጥር ስምምነት ጊዜው ካበቃ በኋላ ከፍተኛ ወታደራዊ ውይይት እንደገና ለመጀመር ቢስማሙም፣ እስካሁን ወደ ተግባር አልገቡም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ አዲስ ስምምነት የጦር መሳሪያዋ እያደገ የመጣችውን ቻይናንም ሊያካትት ይገባል በማለት በተደጋጋሚ ጫና ቢያደርጉም፣ ቤይጂንግ ግን ይህንን ውድቅ አድርጋዋለች። በሌላ በኩል፣ ሩሲያ 'ኒው ስታርት' እንዲራዘም ለምታቀርበው ጥያቄ ትራምፕ ዝምታን የመረጡ ሲሆን፣ ሁለቱም ሀገራት በተደጋጋሚ አንዱ ሌላውን ስምምነቱን አላከበረም ሲሉ ይወነጃጀላሉ።
ሳርማት (በኔቶ መጠሪያ "ሰይጣን ዳግማዊ" የሚባለው፣ ሩሲያ ከሶቪየት ህብረት ውድቀት በኋላ ካመረተቻቸው አህጉር አቋራጭ ሚሳኤሎች መካከል "እጅግ ከባድ" በሚል ምድብ የተመደበው የመጀመሪያው ነው።
በአሜሪካ ወይም በአውሮፓ በሺዎች የሚቆጠሩ ማይሎች ርቀት ላይ የሚገኙ ኢላማዎችን በኒውክሌር አረር ለመምታት የተነደፈው ይህ ሚሳኤል፣ ለዓመታት ባጋጠመው መጓተት እና መዘግየት ምክንያት ስምሪቱ ሲራዘም መቆየቱ ይታወሳል።
ፕሬዝዳንት ፑቲን በቴሌቪዥን መስኮት በሰጡት ቃል፣ የሳርማት የኒውክሌር አረር የማፈንዳት አቅም ከማንኛውም የምዕራባውያን አቻው ከአራት እጥፍ በላይ እንደሚበልጥ፣ እና ከ35,000 ኪ.ሜ (21,750 ማይል) በላይ ርቀት መምታት እንደሚችል አስረድተዋል።
"አሁን ያሉትንም ሆነ ወደፊት የሚመጡትን ፀረ-ሚሳኤል መከላከያ ስርዓቶች ጥሶ የመግባት አቅም አለው" ያሉት ፑቲን፣ የጦር መሳሪያውን "በአለም ላይ እጅግ ሀይለኛው የሚሳኤል ስርዓት" ሲሉ በከፍተኛ ኩራት ገልጸውታል።
የምዕራባውያን የፀጥታ ተንታኞች ግን ፑቲን በ2018 እ.ኤ.አ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሳወቁትን የጦር መሳሪያ ዘመናዊ የማድረግ ፕሮግራም አካል የሆኑትን አዳዲስ የኒውክሌር መሳሪያዎች አቅም አጋንነው እየገለፁ ነው ሲሉ ይሞግታሉ። ባለሙያዎቹ እንደሚሉት፣ ሳርማት ከዚህ ቀደም ውድቀቶች አጋጥመውታል፤ ለአብነትም በመስከረም 2024 የተደረገው ሙከራ በሚሳኤል ማስወንጨፊያው ላይ ጥልቅ ጉድጓድ ጥሎ ማለፉን ያስታውሳሉ።
ይሁን እንጂ የሩሲያ ስትራቴጂካዊ የሚሳኤል ሃይሎች አዛዥ የሆኑት ሰርጌይ ካራካዬቭ፣ የማክሰኞው የሳርማት ሙከራ የተሳካ እንደነበር ለፑቲን ሪፖርት ሲያደርጉ በመንግስት ቴሌቪዥን ታይተዋል። ካራካዬቭ እንዳሉት፣ "ሳርማት የሚሳኤል ስርዓት የተገጠመላቸው ማስወንጨፊያዎች መሰማራታቸው... የስትራቴጂካዊ የኒውክሌር ሃይሎችን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድጋል።"
እ.ኤ.አ በ2022 የዩክሬን ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ ፑቲን የሩሲያን የኒውክሌር መሳሪያ ብዛት እና ሀይል ለአለም በተደጋጋሚ ሲያስታውሱ ቆይተዋል። ይህ አካሄዳቸው ምዕራባውያን በዩክሬን ጦርነት ውስጥ ጣልቃ እንዳይገቡ ለማስፈራራት ያለመ መሆኑ ይነገራል።
የተባበሩት መንግስታት ትጥቅ ማስፈታት ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ፓቬል ፖድቪግ በበኩላቸው፣ የሩሲያ "ትልቁ ሚሳኤል" በዚህ ዓመት መሰማራቱ እውን መሆኑን ቢያምኑም፣ ይህ ግን "የሩሲያን ስትራቴጂካዊ ሃይሎች የመከላከል አቅም ላይ ጉልህ ለውጥ ያመጣል" ብለው እንደማያስቡ ተናግረዋል።
የሩሲያው የዜና ወኪል እንደዘገበው፣ ክሬምሊን ለሚሳኤል ሙከራው አሜሪካን አስቀድሞ አሳውቆ ነበር። ሆኖም፣ ሞስኮ እና ዋሽንግተን የ 'ኒው ስታርት' የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ቁጥጥር ስምምነት ጊዜው ካበቃ በኋላ ከፍተኛ ወታደራዊ ውይይት እንደገና ለመጀመር ቢስማሙም፣ እስካሁን ወደ ተግባር አልገቡም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ አዲስ ስምምነት የጦር መሳሪያዋ እያደገ የመጣችውን ቻይናንም ሊያካትት ይገባል በማለት በተደጋጋሚ ጫና ቢያደርጉም፣ ቤይጂንግ ግን ይህንን ውድቅ አድርጋዋለች። በሌላ በኩል፣ ሩሲያ 'ኒው ስታርት' እንዲራዘም ለምታቀርበው ጥያቄ ትራምፕ ዝምታን የመረጡ ሲሆን፣ ሁለቱም ሀገራት በተደጋጋሚ አንዱ ሌላውን ስምምነቱን አላከበረም ሲሉ ይወነጃጀላሉ።
3 months ago
"የዩክሬን ግጭት ወደ ማብቂያው እየተቃረበ ነው"፦ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን
*************************
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የዩክሬን ግጭት ወደ ማብቂያው ምዕራፍ እየተቃረበ መሆኑን ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት በሩሲያና በመላው ዓለም የተከበረውን የ79ኛው የድል ቀን በዓል ተከትሎ በሞስኮ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው።
ፕሬዚዳንት ፑቲን በሰጡት ማብራሪያ "ጉዳዩ ወደ ዩክሬን ግጭት ማጠቃለያ እያመራ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም በሩሲያና በዩክሬን መካከል የመጨረሻው የሰላም ስምምነት ላይ መድረስ ከተቻለ፣ ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በሦስተኛ ሀገር ለመገናኘትና ለመወያየት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በሞስኮ በተካሄደው የድል ቀን በዓል ላይ ለመሳተፍ ከመጡ የውጭ ሀገራት መሪዎች ጋር ተከታታይ ስብሰባዎችን ያደረጉት ፑቲን፣ ስለ ሩሲያ-ቻይና ግንኙነትና ስለ ዓለም አቀፍ ጉዳዮችም ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።
ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ግጭቱን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ስምምነቶች ላይ መድረስ ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በብሌን ደምበሎ
#russia #ukraine #vladimirputin #globalnews #peacetalks
*************************
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የዩክሬን ግጭት ወደ ማብቂያው ምዕራፍ እየተቃረበ መሆኑን ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት በሩሲያና በመላው ዓለም የተከበረውን የ79ኛው የድል ቀን በዓል ተከትሎ በሞስኮ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው።
ፕሬዚዳንት ፑቲን በሰጡት ማብራሪያ "ጉዳዩ ወደ ዩክሬን ግጭት ማጠቃለያ እያመራ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም በሩሲያና በዩክሬን መካከል የመጨረሻው የሰላም ስምምነት ላይ መድረስ ከተቻለ፣ ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በሦስተኛ ሀገር ለመገናኘትና ለመወያየት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በሞስኮ በተካሄደው የድል ቀን በዓል ላይ ለመሳተፍ ከመጡ የውጭ ሀገራት መሪዎች ጋር ተከታታይ ስብሰባዎችን ያደረጉት ፑቲን፣ ስለ ሩሲያ-ቻይና ግንኙነትና ስለ ዓለም አቀፍ ጉዳዮችም ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።
ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ግጭቱን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ስምምነቶች ላይ መድረስ ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በብሌን ደምበሎ
#russia #ukraine #vladimirputin #globalnews #peacetalks
3 months ago
የዩክሬን ግጭት 'እየተጠናቀቀ ነው' ብለው እንደሚያስቡ ፑቲን ተናገሩ
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አገራቸው ከዩክሬን ጋር እያካሄደች ያለችው ጦርነት እያበቃ ነው ብለው እንደሚያስቡ ተናገሩ።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት ሶቪየት ኅብረት ናዚ ጀርመንን ድል ያደረገችበትን በዓል ካከበረች በኋላ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት ነው።
"ጉዳዩ እየተጠናቀቀ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ በዩክሬን እየተካሄደ ስለሚገኘው "ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ተናግረው ምዕራባውያን ለኪዬቭ መንግሥትን የሚያደርጉትን ድጋፍ ኮንነዋል።
የሩሲያ ዓመታዊ የድል በዓል ዩክሬን በቀዩ አደባባይ በድሮኖች ጥቃት ልታደርስ ትችላለች በሚል ስጋት የተለመደውን የታንክ እና የሚሳኤል ሠልፍ አላካሄዱም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመጨረሻ ደቂቃ ባደራደሩት እና በሞስኮ እና በኪየቭ መካከል በተደረገ የተኩስ አቁም ስምምነት የጥቃት ስጋቱ ቀንሶ ሠልፉ ያለ ምንም አደጋ ተጠናቋል።
ፑቲን አስተያየትቱን የሰጡት የድል ቀን ንግግራቸውን ጦርነቱን ምክንያታዊነት ለማረጋገጥ ከተጠቀሙ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው።
በንግግራቸውም ሩሲያ "ፍትሃዊ" ጦርነት እየተዋጋች እንደሆነ እና ዩክሬንን "በኔቶ የሚታጠቀ እና የሚደገፍ ጠበኛ ኃይል" ብለው ጠርተዋታል።
ምዕራባውያን ዩክሬንን ስለመርዳታቸው በተመለከተ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት የተጠየቁት ፑቲን "እርዳታ ቃል ገብተው እስከ ዛሬ ድረስም ከሩሲያ ጋር ግጭቱን ማቀጣጠል ጀመሩ። ጉዳዩ እያበቃ ነው ብዬ ባስብም ግን ከባድ ጉዳይ ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
የሩሲያ ኃይሎች በ2014 ክሬሚያን እና የምሥራቅ ዩክሬን ክፍሎችን የተቆጣጠሩ ሲሆን እአአ በየካቲት 2022 የዩክሬን ሙሉ ወረራን ጀመሩ።
ፑቲን የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪን የሚያገኙት ዘላቂ የሰላም ስምምነት ከተደረሰ በኋላ ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል።
"በሦስተኛ አገር መገናኘትም ቢቻልም ግን በዚህ ዝግጅት ላይ ለመሳተፍ እና ለመፈረም የረዥም ጊዜ ታሪካዊ እይታን ለመፍጠር የሰላም ስምምነት ላይ የመጨረሻ ስምምነቶች ከተደረሱ በኋላ ብቻ ነው። ይህም የመጨረሻ እርምጃ መሆን አለበት" ሲሉ አክለዋል።
ዜሌንስኪ በግል ሊያገኟቸው ዝግጁ መሆናቸውን ቢሰሙም "እንዲህ አይነት መግለጫዎችን ስንሰማ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም" ብለዋል ፑቲን።
ፑቲን ለአውሮፓ አዲስ የደህንነት ስምምነቶችን ለመደራደር ፈቃደኛ እንደሆኑ እና የሚመርጡት የድርድር አጋር የጀርመን የቀድሞ ቻንስለር ጄርሃርድ ሽሮደር እንደሆኑ ጠቅሰዋል።
የቀድሞው ቻንስለር የፑቲን የረዠም ጊዜ ወዳጅ ሲሆኑ በሩሲያ መንግሥት ባለቤትነት ስር ላሉ የኤነርጂ ኩባንያዎች ላይ በመሥራታቸው ምክንያት አወዛጋቢ ናቸው።
ባለፈው ሳምንት የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ የአውሮፓ ኅብረት ከሩሲያ ጋር ለመደራደር "ተስፋ" እንዳለው እና ዜሌንስኪ እንዲህ ዓይነት እርምጃን እንደሚደግፉ እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
በፋይናንሺያል ታይምስ በተጠቀሰው የኮስታ ንግግር መሠረት የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች "ይህንን ለማድረግ ትክክለኛው ጊዜ ሲመጣ ከሩሲያ ጋር በብቃት ለመወያየት ምን እንደሚያስፈልገን" እየተማከሩ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
በአሜሪካ በተመራው የተኩስ አቁም ስምምነት መሠረት ኪዬቭ እና ሞስኮ አንድ ሺህ እስረኞችን ለመለዋወጥም ተስማምተዋል። ፑቲን ቅዳሜ ዕለት ሩሲያ ስለልውውጡ ምንም ዓይነት መረጃ ከዩክሬን በኩል እስካሁን እንዳልሰማች ተናግረዋል።
በሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በ'ቀዩ አደባባይ' ሠልፍ ላይ ምንም ዓይነት ወታደራዊ መሳሪያ ያልታየ ሲሆን ክሪምሊን በተለምዶ የሩሲያን ወታደራዊ ኃይል ለዓለም አቀፍ መድረክ የምታሳይበት ሰልፍ ነው።
በዝግጅቱ ላይ የተሳተፉት ጋዜጠኞች በጣም ጥቂት የነበሩ ሲሆን ብዙ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ፈቃድ አልተሰጣቸውም።
BBC
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አገራቸው ከዩክሬን ጋር እያካሄደች ያለችው ጦርነት እያበቃ ነው ብለው እንደሚያስቡ ተናገሩ።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት ሶቪየት ኅብረት ናዚ ጀርመንን ድል ያደረገችበትን በዓል ካከበረች በኋላ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት ነው።
"ጉዳዩ እየተጠናቀቀ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ በዩክሬን እየተካሄደ ስለሚገኘው "ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ተናግረው ምዕራባውያን ለኪዬቭ መንግሥትን የሚያደርጉትን ድጋፍ ኮንነዋል።
የሩሲያ ዓመታዊ የድል በዓል ዩክሬን በቀዩ አደባባይ በድሮኖች ጥቃት ልታደርስ ትችላለች በሚል ስጋት የተለመደውን የታንክ እና የሚሳኤል ሠልፍ አላካሄዱም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመጨረሻ ደቂቃ ባደራደሩት እና በሞስኮ እና በኪየቭ መካከል በተደረገ የተኩስ አቁም ስምምነት የጥቃት ስጋቱ ቀንሶ ሠልፉ ያለ ምንም አደጋ ተጠናቋል።
ፑቲን አስተያየትቱን የሰጡት የድል ቀን ንግግራቸውን ጦርነቱን ምክንያታዊነት ለማረጋገጥ ከተጠቀሙ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው።
በንግግራቸውም ሩሲያ "ፍትሃዊ" ጦርነት እየተዋጋች እንደሆነ እና ዩክሬንን "በኔቶ የሚታጠቀ እና የሚደገፍ ጠበኛ ኃይል" ብለው ጠርተዋታል።
ምዕራባውያን ዩክሬንን ስለመርዳታቸው በተመለከተ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት የተጠየቁት ፑቲን "እርዳታ ቃል ገብተው እስከ ዛሬ ድረስም ከሩሲያ ጋር ግጭቱን ማቀጣጠል ጀመሩ። ጉዳዩ እያበቃ ነው ብዬ ባስብም ግን ከባድ ጉዳይ ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
የሩሲያ ኃይሎች በ2014 ክሬሚያን እና የምሥራቅ ዩክሬን ክፍሎችን የተቆጣጠሩ ሲሆን እአአ በየካቲት 2022 የዩክሬን ሙሉ ወረራን ጀመሩ።
ፑቲን የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪን የሚያገኙት ዘላቂ የሰላም ስምምነት ከተደረሰ በኋላ ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል።
"በሦስተኛ አገር መገናኘትም ቢቻልም ግን በዚህ ዝግጅት ላይ ለመሳተፍ እና ለመፈረም የረዥም ጊዜ ታሪካዊ እይታን ለመፍጠር የሰላም ስምምነት ላይ የመጨረሻ ስምምነቶች ከተደረሱ በኋላ ብቻ ነው። ይህም የመጨረሻ እርምጃ መሆን አለበት" ሲሉ አክለዋል።
ዜሌንስኪ በግል ሊያገኟቸው ዝግጁ መሆናቸውን ቢሰሙም "እንዲህ አይነት መግለጫዎችን ስንሰማ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም" ብለዋል ፑቲን።
ፑቲን ለአውሮፓ አዲስ የደህንነት ስምምነቶችን ለመደራደር ፈቃደኛ እንደሆኑ እና የሚመርጡት የድርድር አጋር የጀርመን የቀድሞ ቻንስለር ጄርሃርድ ሽሮደር እንደሆኑ ጠቅሰዋል።
የቀድሞው ቻንስለር የፑቲን የረዠም ጊዜ ወዳጅ ሲሆኑ በሩሲያ መንግሥት ባለቤትነት ስር ላሉ የኤነርጂ ኩባንያዎች ላይ በመሥራታቸው ምክንያት አወዛጋቢ ናቸው።
ባለፈው ሳምንት የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ የአውሮፓ ኅብረት ከሩሲያ ጋር ለመደራደር "ተስፋ" እንዳለው እና ዜሌንስኪ እንዲህ ዓይነት እርምጃን እንደሚደግፉ እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
በፋይናንሺያል ታይምስ በተጠቀሰው የኮስታ ንግግር መሠረት የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች "ይህንን ለማድረግ ትክክለኛው ጊዜ ሲመጣ ከሩሲያ ጋር በብቃት ለመወያየት ምን እንደሚያስፈልገን" እየተማከሩ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
በአሜሪካ በተመራው የተኩስ አቁም ስምምነት መሠረት ኪዬቭ እና ሞስኮ አንድ ሺህ እስረኞችን ለመለዋወጥም ተስማምተዋል። ፑቲን ቅዳሜ ዕለት ሩሲያ ስለልውውጡ ምንም ዓይነት መረጃ ከዩክሬን በኩል እስካሁን እንዳልሰማች ተናግረዋል።
በሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በ'ቀዩ አደባባይ' ሠልፍ ላይ ምንም ዓይነት ወታደራዊ መሳሪያ ያልታየ ሲሆን ክሪምሊን በተለምዶ የሩሲያን ወታደራዊ ኃይል ለዓለም አቀፍ መድረክ የምታሳይበት ሰልፍ ነው።
በዝግጅቱ ላይ የተሳተፉት ጋዜጠኞች በጣም ጥቂት የነበሩ ሲሆን ብዙ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ፈቃድ አልተሰጣቸውም።
BBC
Sponsored by
Surafel
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከዩክሬን ጋር እየተካሄደ ያለው ጦርነት መቋጫው እየተቃረበ መሆኑን እንደሚያስቡ ተናገሩ።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያስታወቁት፣ ሩሲያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ወታደራዊ ትርኢቱ እና ድምቀቱ የተቀነሰውን የዘንድሮውን የድል ቀን (Victory Day) በዓል ካካሄደች በኋላ በክሬምሊን ለተገኙ ጋዜጠኞች በሰጡት አጭር አስተያየት ነው።
"ጉዳዩ ወደ ማብቂያው እየመጣ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ የተናገሩት ፑቲን፣ ጦርነቱ መቼ እና በምን ሁኔታ ሊጠናቀቅ እንደሚችል ግን ምንም ዓይነት ተጨማሪ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያስታወቁት፣ ሩሲያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ወታደራዊ ትርኢቱ እና ድምቀቱ የተቀነሰውን የዘንድሮውን የድል ቀን (Victory Day) በዓል ካካሄደች በኋላ በክሬምሊን ለተገኙ ጋዜጠኞች በሰጡት አጭር አስተያየት ነው።
"ጉዳዩ ወደ ማብቂያው እየመጣ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ የተናገሩት ፑቲን፣ ጦርነቱ መቼ እና በምን ሁኔታ ሊጠናቀቅ እንደሚችል ግን ምንም ዓይነት ተጨማሪ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
3 months ago
ሩሲያ 81ኛውን የድል በዓሏን በታላቅ ወታደራዊ ትርዒት እያከበረች ነው
#ethiopia | መላው የሩሲያ ህዝብና መንግስት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ናዚ ጀርመንን ድል ያደረጉበትን 81ኛ ዓመት በታላቅ ድምቀት እያከበሩ ይገኛሉ። በሞስኮ የቀዩ አደባባይ (Red Square) በተካሄደው ደማቅ ስነ-ስርዓት ላይ፣ የሀገሪቱ ወታደራዊ ጥንካሬ የታየበትና የታሪክ ጀግኖች የታሰቡበት ነበር።
ፕሬዚዳንቱ በክብር እንግድነት ለተገኙ የጦር አርበኞችና ለዓለም መሪዎች ባደረጉት ንግግር፣ የሶቪየት ህብረት ወታደሮች ለሰው ልጅ ነጻነት የከፈሉትን መስዋዕትነት በዝርዝር አንስተዋል። "ዓለምን ከናዚ አስከፊ አገዛዝ የታደጉትና ለአውሮፓውያን ነጻነትን ያመጡት የሶቪየት ልጆች ናቸው" ሲሉ የአያቶቻቸውን ጀግንነት አውስተዋል።
በዓሉን ለየት የሚያደርገው በዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች የታጀበው ሰልፍ ነው። በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች፣ ታንኮችና ዘመናዊ ሚሳኤሎች በአደባባዩ ላይ የተመለከቱ ሲሆን፣ የሩሲያ የአየር ኃይልም በሰማይ ላይ አስደናቂ ትርዒት አሳይቷል።
ፑቲን ባስተላለፉት መልእክት፣ ይህ ድል ለሩሲያውያን የኩራት ምንጭ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ ትውልድ የሰላምና የጥንካሬ ትምህርት መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል።
ይህ 81ኛው የድል በዓል ሩሲያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ተጽዕኖ ዳግም ለማሳየት የተጠቀመችበት አጋጣሚ ሆኖ አልፏል። በበዓሉ ላይ የተለያዩ የሀገራት መሪዎች መገኘታቸውም ለክብረ በዓሉ የላቀ ዲፕሎማሲያዊ ትርጉም ሰጥቶታል።
"ወታደሮቻችን ለመላው አውሮፓውያን ነጻነትና ክብር የህይወት መስዋዕትነት ከፍለዋል" — ቭላድሚር ፑቲን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ሩሲያ #የድልበዓል #victoryday81 #ሞስኮ #ታሪክ #ወታደራዊትርዒት #ናዚድል #ፑቲን
#ethiopia | መላው የሩሲያ ህዝብና መንግስት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ናዚ ጀርመንን ድል ያደረጉበትን 81ኛ ዓመት በታላቅ ድምቀት እያከበሩ ይገኛሉ። በሞስኮ የቀዩ አደባባይ (Red Square) በተካሄደው ደማቅ ስነ-ስርዓት ላይ፣ የሀገሪቱ ወታደራዊ ጥንካሬ የታየበትና የታሪክ ጀግኖች የታሰቡበት ነበር።
ፕሬዚዳንቱ በክብር እንግድነት ለተገኙ የጦር አርበኞችና ለዓለም መሪዎች ባደረጉት ንግግር፣ የሶቪየት ህብረት ወታደሮች ለሰው ልጅ ነጻነት የከፈሉትን መስዋዕትነት በዝርዝር አንስተዋል። "ዓለምን ከናዚ አስከፊ አገዛዝ የታደጉትና ለአውሮፓውያን ነጻነትን ያመጡት የሶቪየት ልጆች ናቸው" ሲሉ የአያቶቻቸውን ጀግንነት አውስተዋል።
በዓሉን ለየት የሚያደርገው በዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች የታጀበው ሰልፍ ነው። በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች፣ ታንኮችና ዘመናዊ ሚሳኤሎች በአደባባዩ ላይ የተመለከቱ ሲሆን፣ የሩሲያ የአየር ኃይልም በሰማይ ላይ አስደናቂ ትርዒት አሳይቷል።
ፑቲን ባስተላለፉት መልእክት፣ ይህ ድል ለሩሲያውያን የኩራት ምንጭ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ ትውልድ የሰላምና የጥንካሬ ትምህርት መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል።
ይህ 81ኛው የድል በዓል ሩሲያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ተጽዕኖ ዳግም ለማሳየት የተጠቀመችበት አጋጣሚ ሆኖ አልፏል። በበዓሉ ላይ የተለያዩ የሀገራት መሪዎች መገኘታቸውም ለክብረ በዓሉ የላቀ ዲፕሎማሲያዊ ትርጉም ሰጥቶታል።
"ወታደሮቻችን ለመላው አውሮፓውያን ነጻነትና ክብር የህይወት መስዋዕትነት ከፍለዋል" — ቭላድሚር ፑቲን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ሩሲያ #የድልበዓል #victoryday81 #ሞስኮ #ታሪክ #ወታደራዊትርዒት #ናዚድል #ፑቲን
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በዛሬው ዕለት በሞስኮ ቀይ አደባባይ የተለመደውን የታንክ እና የሚሳኤል ማጓጓዣዎችን ትዕይንት የቀነሰ የድል ቀን በዓል አክብረዋል። ሩሲያ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ናዚ ጀርመንን ያሸነፈችበትን 81ኛ ዓመት ለማሰብ በተዘጋጀው በዚህ በዓል ላይ ወታደራዊ ትርኢቱ እንዲቀነስ የተደረገው፣ በዩክሬን ባለው "ወቅታዊ የጦርነት ሁኔታ" እና ኪየቭ በምታስወነጭፋቸው የረጅም ርቀት ድሮኖች ስጋት ምክንያት መሆኑ ተነግሯል።
ለ45 ደቂቃዎች ብቻ በዘለቀው በዚህ ዝግጅት ላይ ከሩሲያ ወታደሮች ጋር በዩክሬን አብረዋቸው ሲዋጉ የነበሩ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮችም ተሳትፈዋል። ሩሲያ ሁልጊዜም ግዙፍ ወታደራዊ አቅሟን የምታሳይበት ይህ በዓል፣ ዘንድሮ ታላላቅ የጦር መሳሪያዎችን በአካል ከማሳየት ይልቅ በግዙፍ ስክሪኖች ላይ በምስል ማሳየትን መርጧል። የውጭ ሀገራት መሪዎች እና የአለም አቀፍ ሚዲያዎች ተሳትፎም እጅግ አነስተኛ ሲሆን፣ እንደ ሲኤንኤን ባሉት ሚዲያዎች ተሰጥቶ የነበረው ፈቃድም በድንገት ተነጥቋል። ፕሬዝዳንት ፑቲን በከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ ታጅበው ባደረጉት ንግግር፣ አሁን በዩክሬን እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጋር በማነጻጸር፣ ጦራቸው "በሙሉ የኔቶ ኃይል የሚደገፈውን አጥቂ ኃይል" እየተጋፈጠ መሆኑን ተናግረዋል።
የዘንድሮውን የድል በዓል ለየት የሚያደርገው በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አደራዳሪነት ከሜይ 9 እስከ 11 የሚቆይ የሶስት ቀናት የተኩስ አቁም እና የ1,000 እስረኞች ልውውጥ ስምምነት መደረጉ ነው። ይህንን ተከትሎ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ ለሩሲያ የድል ቀን ሰልፍ መካሄድ በፌዝ መልክ "ፈቃድ" መስጠታቸውን ገልጸው፣ "ከቀይ አደባባይ ይልቅ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱት የዩክሬን እስረኞች ህይወት ይበልጥብናል" ብለዋል። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፣ በበኩላቸው "ሩሲያ በድል ቀኗ ለመኩራት የማንም ፈቃድ አያስፈልጋትም" ሲሉ መልስ ሰጥተዋል። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴርም በዓሉን ለማስተጓጎል የሚሞክር ካለ በኪየቭ ማእከል ላይ መጠነ ሰፊ የሚሳኤል ጥቃት እንደሚፈጽም ዝቶ ነበር።
ከበዓሉ ድምቀት ጀርባ ግን ሩሲያ በዩክሬን የከፈተችው እና "የሶስት ቀናት ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ስትል የጀመረችው ጦርነት አራት ዓመታትን አስቆጥሮ እጅግ አድካሚ እና ደም አፋሳሽ ወደሆነ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተለያዩ ገለልተኛ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከጦርነቱ መጀመርያ እስከ 2025 መገባደጃ ድረስ ወደ 352,000 የሚጠጉ የሩሲያ ወታደሮች ህይወታቸውን አጥተዋል። ምንም እንኳን ሞስኮ አሁንም ዩክሬንን የማሸነፍ አቅሙም ሆነ ጽናቱ እንዳላት ብትገልጽም፣ የሩሲያ ጦር በጦር ሜዳ እያሳየ ያለው ግስጋሴ እጅግ አዝጋሚ (በቀን 70 ሜትር ብቻ) ከመሆኑም በላይ፣ የጦርነቱ ወጪ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን እንደቀጠለ የፖለቲካ እና የጦርነት ጉዳዮች ተንታኞች ያብራራሉ።
ለ45 ደቂቃዎች ብቻ በዘለቀው በዚህ ዝግጅት ላይ ከሩሲያ ወታደሮች ጋር በዩክሬን አብረዋቸው ሲዋጉ የነበሩ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮችም ተሳትፈዋል። ሩሲያ ሁልጊዜም ግዙፍ ወታደራዊ አቅሟን የምታሳይበት ይህ በዓል፣ ዘንድሮ ታላላቅ የጦር መሳሪያዎችን በአካል ከማሳየት ይልቅ በግዙፍ ስክሪኖች ላይ በምስል ማሳየትን መርጧል። የውጭ ሀገራት መሪዎች እና የአለም አቀፍ ሚዲያዎች ተሳትፎም እጅግ አነስተኛ ሲሆን፣ እንደ ሲኤንኤን ባሉት ሚዲያዎች ተሰጥቶ የነበረው ፈቃድም በድንገት ተነጥቋል። ፕሬዝዳንት ፑቲን በከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ ታጅበው ባደረጉት ንግግር፣ አሁን በዩክሬን እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጋር በማነጻጸር፣ ጦራቸው "በሙሉ የኔቶ ኃይል የሚደገፈውን አጥቂ ኃይል" እየተጋፈጠ መሆኑን ተናግረዋል።
የዘንድሮውን የድል በዓል ለየት የሚያደርገው በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አደራዳሪነት ከሜይ 9 እስከ 11 የሚቆይ የሶስት ቀናት የተኩስ አቁም እና የ1,000 እስረኞች ልውውጥ ስምምነት መደረጉ ነው። ይህንን ተከትሎ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ ለሩሲያ የድል ቀን ሰልፍ መካሄድ በፌዝ መልክ "ፈቃድ" መስጠታቸውን ገልጸው፣ "ከቀይ አደባባይ ይልቅ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱት የዩክሬን እስረኞች ህይወት ይበልጥብናል" ብለዋል። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፣ በበኩላቸው "ሩሲያ በድል ቀኗ ለመኩራት የማንም ፈቃድ አያስፈልጋትም" ሲሉ መልስ ሰጥተዋል። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴርም በዓሉን ለማስተጓጎል የሚሞክር ካለ በኪየቭ ማእከል ላይ መጠነ ሰፊ የሚሳኤል ጥቃት እንደሚፈጽም ዝቶ ነበር።
ከበዓሉ ድምቀት ጀርባ ግን ሩሲያ በዩክሬን የከፈተችው እና "የሶስት ቀናት ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ስትል የጀመረችው ጦርነት አራት ዓመታትን አስቆጥሮ እጅግ አድካሚ እና ደም አፋሳሽ ወደሆነ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተለያዩ ገለልተኛ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከጦርነቱ መጀመርያ እስከ 2025 መገባደጃ ድረስ ወደ 352,000 የሚጠጉ የሩሲያ ወታደሮች ህይወታቸውን አጥተዋል። ምንም እንኳን ሞስኮ አሁንም ዩክሬንን የማሸነፍ አቅሙም ሆነ ጽናቱ እንዳላት ብትገልጽም፣ የሩሲያ ጦር በጦር ሜዳ እያሳየ ያለው ግስጋሴ እጅግ አዝጋሚ (በቀን 70 ሜትር ብቻ) ከመሆኑም በላይ፣ የጦርነቱ ወጪ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን እንደቀጠለ የፖለቲካ እና የጦርነት ጉዳዮች ተንታኞች ያብራራሉ።
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር 81ኛውን የናዚ ጀርመን ሽንፈት የድል በዓል ምክንያት በማድረግ ለአርብ እና ቅዳሜ የሚቆይ የአንድ ወገን የተኩስ አቁም አዋጅ አውጇል። ሆኖም ዩክሬን የበዓሉን ስነ-ስርዓት ለማስተጓጎል ከሞከረች በኪቭ ከተማ መሀል ላይ "መጠነ ሰፊ የሚሳኤል ጥቃት" እንደሚፈጽም አስጠንቅቋል። ሚኒስቴሩ በኪቭ የሚገኙ ንፁሃን ዜጎች እና የውጭ ዲፕሎማቲክ ሚሲዮን ሰራተኞች ከተማዋን በፍጥነት ለቀው እንዲወጡ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
ለዚህ የሩሲያ እርምጃ ፈጣን ምላሽ የሰጡት የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ ሀገራቸው ከረቡዕ እኩለ ሌሊት ጀምሮ የተኩስ አቁሙን ተግባራዊ እንደምታደርግ እና ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከሩሲያ ለሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት ተመሳሳይ የአፀፋ ምላሽ እንደምትሰጥ ገልጸዋል። ዘለንስኪ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ያለ ዩክሬን በጎ ፈቃድ በሞስኮ ወታደራዊ ትርኢት ማካሄድ እንደማይችል ማመኑን ጠቅሰው፣ ክሬምሊን ጦርነቱን ለማስቆም እውነተኛ እርምጃዎችን እንዲወስድ አሳስበዋል።
ዛሬ የወጡት እነዚህ መግለጫዎች የተሰሙት፣ ሩሲያ በሞስኮ ቀይ አደባባይ የምታካሂደውን ታሪካዊ ወታደራዊ ትርኢት አሳንሳ ለማክበር በዝግጅት ላይ ባለችበት ወቅት ነው። የሩሲያ ባለስልጣናት ይህን ውሳኔ ያሳለፉት ዩክሬን ጥልቀት ባላቸው የሩሲያ ግዛቶች ውስጥ የምታደርሰውን የድሮን ጥቃት በመስጋት መሆኑ ተገልጿል። በዚህም ምክንያት ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ታንኮች፣ ሚሳኤሎች እና ሌሎች ከባድ የጦር መሳሪያዎች በዘንድሮው የሞስኮ ትርኢት ላይ አይቀርቡም። በሌሎች የሩሲያ ከተሞች የሚካሄዱ አነስተኛ ትርኢቶችም በጸጥታ ስጋት ምክንያት ተሰርዘዋል ወይም ተቀንሰዋል።
በአርሜኒያ በተካሄደው የአውሮፓ መሪዎች ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ፣ የሩሲያ ባለስልጣናት በቀይ አደባባይ ላይ ድሮኖች ሊያንዣብቡ ይችላሉ ብለው መፍራታቸው አሁን ላይ ጠንካራ አለመሆናቸውን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ባለፈው ሳምንት ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት የዘንድሮውን የድል በዓል የተኩስ አቁም ሀሳብ አንስተው እንደነበር የተዘገበ ሲሆን፣ የዘንድሮውን በዓል ለመታደም የስሎቫኪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮበርት ፊኮ በሞስኮ እንደሚገኙ ይጠበቃል።
ለዚህ የሩሲያ እርምጃ ፈጣን ምላሽ የሰጡት የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ ሀገራቸው ከረቡዕ እኩለ ሌሊት ጀምሮ የተኩስ አቁሙን ተግባራዊ እንደምታደርግ እና ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከሩሲያ ለሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት ተመሳሳይ የአፀፋ ምላሽ እንደምትሰጥ ገልጸዋል። ዘለንስኪ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ያለ ዩክሬን በጎ ፈቃድ በሞስኮ ወታደራዊ ትርኢት ማካሄድ እንደማይችል ማመኑን ጠቅሰው፣ ክሬምሊን ጦርነቱን ለማስቆም እውነተኛ እርምጃዎችን እንዲወስድ አሳስበዋል።
ዛሬ የወጡት እነዚህ መግለጫዎች የተሰሙት፣ ሩሲያ በሞስኮ ቀይ አደባባይ የምታካሂደውን ታሪካዊ ወታደራዊ ትርኢት አሳንሳ ለማክበር በዝግጅት ላይ ባለችበት ወቅት ነው። የሩሲያ ባለስልጣናት ይህን ውሳኔ ያሳለፉት ዩክሬን ጥልቀት ባላቸው የሩሲያ ግዛቶች ውስጥ የምታደርሰውን የድሮን ጥቃት በመስጋት መሆኑ ተገልጿል። በዚህም ምክንያት ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ታንኮች፣ ሚሳኤሎች እና ሌሎች ከባድ የጦር መሳሪያዎች በዘንድሮው የሞስኮ ትርኢት ላይ አይቀርቡም። በሌሎች የሩሲያ ከተሞች የሚካሄዱ አነስተኛ ትርኢቶችም በጸጥታ ስጋት ምክንያት ተሰርዘዋል ወይም ተቀንሰዋል።
በአርሜኒያ በተካሄደው የአውሮፓ መሪዎች ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ፣ የሩሲያ ባለስልጣናት በቀይ አደባባይ ላይ ድሮኖች ሊያንዣብቡ ይችላሉ ብለው መፍራታቸው አሁን ላይ ጠንካራ አለመሆናቸውን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ባለፈው ሳምንት ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት የዘንድሮውን የድል በዓል የተኩስ አቁም ሀሳብ አንስተው እንደነበር የተዘገበ ሲሆን፣ የዘንድሮውን በዓል ለመታደም የስሎቫኪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮበርት ፊኮ በሞስኮ እንደሚገኙ ይጠበቃል።
3 months ago
የትራምፕና የፑቲን የ90 ደቂቃ የስልክ ወግ
#ethiopian | የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ለ90 ደቂቃ የቆየ ሰፊ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን የክሬምሊን የውጭ ፖሊሲ አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ አረጋገጡ። በመሪዎቹ ውይይት ወቅት በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት እና የዩክሬን ወቅታዊ ሁኔታ ዋነኛ የመነጋገሪያ አጀንዳዎች ነበሩ።
ቭላድሚር ፑቲን በውይይቱ ወቅት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲራዘም ላደረጉት ጥረት አድናቆታቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ጦርነቱ ያስከተለውን ሰብአዊና ፖለቲካዊ ቀውስ በተመለከተም መክረዋል።
ምንም እንኳን ሩሲያ በዲፕሎማሲው ረገድ ከኢራን ጎን መቆሟን ብታሳውቅም፣ የምዕራባውያን የስለላ ተቋማት ግን ሞስኮ ለቴህራን የስለላና የድሮን ድጋፍ በማድረግ አሜሪካን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች እንዲፈጸሙ ታግዛለች የሚል ጥርጣሬ አላቸው
።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ስለ ውይይቱ በሰጡት ማብራሪያ፣ ከፑቲን ጋር ውጤታማ ቆይታ ማድረጋቸውንና መሪውን ለረጅም ጊዜ እንደሚያውቋቸው ገልጸዋል።
ፑቲን የኢራን የተቀበረ ዩራኒየም ወደ ሞስኮ እንዲዛወር ድጋፍ ለማድረግ ፍላጎት ማሳየታቸውን የጠቀሱት ትራምፕ፣ እርሳቸው ግን የሩሲያው መሪ ትኩረቱን በዩክሬን ያለውን ጦርነት በአፋጣኝ በማቆም ላይ እንዲያደርግ ማሳሰቢያ መስጠታቸውን ተናግረዋል።
በመጨረሻም ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት የሚቋጭበት ጊዜ እጅግ መቅረቡን በመጠቆም ለቀጣናው ሰላም ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#donaldtrump #vladimirputin #russiaukrainewar #middleeastconflict #usrussiarelations #globalpolitics #geopolitics #iranceasefire
#ethiopian | የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ለ90 ደቂቃ የቆየ ሰፊ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን የክሬምሊን የውጭ ፖሊሲ አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ አረጋገጡ። በመሪዎቹ ውይይት ወቅት በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት እና የዩክሬን ወቅታዊ ሁኔታ ዋነኛ የመነጋገሪያ አጀንዳዎች ነበሩ።
ቭላድሚር ፑቲን በውይይቱ ወቅት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲራዘም ላደረጉት ጥረት አድናቆታቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ጦርነቱ ያስከተለውን ሰብአዊና ፖለቲካዊ ቀውስ በተመለከተም መክረዋል።
ምንም እንኳን ሩሲያ በዲፕሎማሲው ረገድ ከኢራን ጎን መቆሟን ብታሳውቅም፣ የምዕራባውያን የስለላ ተቋማት ግን ሞስኮ ለቴህራን የስለላና የድሮን ድጋፍ በማድረግ አሜሪካን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች እንዲፈጸሙ ታግዛለች የሚል ጥርጣሬ አላቸው
።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ስለ ውይይቱ በሰጡት ማብራሪያ፣ ከፑቲን ጋር ውጤታማ ቆይታ ማድረጋቸውንና መሪውን ለረጅም ጊዜ እንደሚያውቋቸው ገልጸዋል።
ፑቲን የኢራን የተቀበረ ዩራኒየም ወደ ሞስኮ እንዲዛወር ድጋፍ ለማድረግ ፍላጎት ማሳየታቸውን የጠቀሱት ትራምፕ፣ እርሳቸው ግን የሩሲያው መሪ ትኩረቱን በዩክሬን ያለውን ጦርነት በአፋጣኝ በማቆም ላይ እንዲያደርግ ማሳሰቢያ መስጠታቸውን ተናግረዋል።
በመጨረሻም ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት የሚቋጭበት ጊዜ እጅግ መቅረቡን በመጠቆም ለቀጣናው ሰላም ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#donaldtrump #vladimirputin #russiaukrainewar #middleeastconflict #usrussiarelations #globalpolitics #geopolitics #iranceasefire
3 months ago
በጥብቅ ቁጥጥር ስር ባለው የሆርሙዝ ወሽመጥ የታየችው ሚስጥራዊዋ መርከብ!
#ethiopia | በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት በከረረበት በዚህ ወቅት፣ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቅርብ አጋር ጋር ግንኙነት እንዳላት የተነገረላት አንዲት ቅንጡ መርከብ ስልታዊ ጠቀሜታ ያለውን የሆርሙዝ ወሽመጥን አቋርጣ ማለፏ የዓለምን መገናኛ ብዙኃን ትኩረት ስቧል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ማዕቀብ የተጣለባቸው የሩሲያ ባለሀብቶች ንብረት እንደሆነች የሚጠረጠረው ይህች መርከብ፣ በዓለም አቀፍ የባህር ላይ እንቅስቃሴ ተቆጣጣሪዎች አይን ውስጥ የገባችው ባልተለመደ የጉዞ መስመር ላይ በመገኘቷ እና ማዕቀቦችን በግልጽ በመቃወም ጉዞዋን በመቀጠሏ ነው።
የዓለማችን ግዙፍ የነዳጅ ማጓጓዣ መስመር በሆነው እና ከፍተኛ ወታደራዊ ጥበቃ በሚደረግበት የሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ መታየቷ፣ በቀጠናው ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ሽኩቻ ዳግም ሊያቀጣጥል እንደሚችል ስጋት ፈጥሯል።
ይህች መርከብ ከክሬምሊን ጋር ጥብቅ ቁርኝት ካላቸው ቢሊየነሮች ጋር በቀጥታ የተገናኘች መሆኗ መረጋገጡ ደግሞ የጉዳዩን ክብደት ከፍ አድርጎታል።
በተለይም የአሜሪካ የገንዘብ ሚኒስቴር ማዕቀብ የጣለባቸው ንብረቶች እና ግለሰቦች፣ እንደ ሆርሙዝ ወሽመጥ ያሉ በአሜሪካ የጦር መርከቦች ጭምር ክትትል የሚደረግባቸውን ቀጠናዎች እንዴት በነፃነት ማለፍ እንደሚችሉ አዳዲስ ጥያቄዎችን እያስነሳ ይገኛል።
ይህ እንቅስቃሴ በምዕራባውያን ዘንድ እንደ ትልቅ ድፍረት የተቆጠረ ሲሆን፣ መርከቧ ማዕቀቡን ተላልፋ ይህን ስልታዊ የባህር መስመር ስታቋርጥ ከጀርባዋ ትልቅ የፖለቲካ መልዕክት እንዳለ ያሳብቃል።
የመርከቧ ጉዞ በወቅታዊው የሩሲያ እና የምዕራባውያን ፍጥጫ መካከል መከሰቱ ጉዳዩን ይበልጥ ያወሳስበዋል።
መርከቧ ቀጥሎ የምታርፍበት ወደብ የት ሊሆን እንደሚችል እና በመንገዷ ላይ ሊያጋጥሟት የሚችሉ የህግ እንቅፋቶች ምን እንደሆኑ አሁንም በቅርብ ክትትል እየተደረገባቸው ያሉ ነጥቦች ናቸው።
እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ ይህ በባህር ላይ የተከወነው ትርኢት ለባለቤቶቿ የቅንጦት ማሳያ ብቻ ሳይሆን፣ ለዓለም አቀፍ ህጎችና ማዕቀቦች የተሰጠ ግልጽ ምላሽ ይመስላል። በቀጠናው ያለውን ወታደራዊ ንቃትም ከፍ እንዲል ያደረገው ይህ ክስተት፣ መርከቧ የያዘችው ምስጢርና ቀጣይ መድረሻዋ ለዓለም አቀፉ ፖለቲካ አዲስ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ethiopia | በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት በከረረበት በዚህ ወቅት፣ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቅርብ አጋር ጋር ግንኙነት እንዳላት የተነገረላት አንዲት ቅንጡ መርከብ ስልታዊ ጠቀሜታ ያለውን የሆርሙዝ ወሽመጥን አቋርጣ ማለፏ የዓለምን መገናኛ ብዙኃን ትኩረት ስቧል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ማዕቀብ የተጣለባቸው የሩሲያ ባለሀብቶች ንብረት እንደሆነች የሚጠረጠረው ይህች መርከብ፣ በዓለም አቀፍ የባህር ላይ እንቅስቃሴ ተቆጣጣሪዎች አይን ውስጥ የገባችው ባልተለመደ የጉዞ መስመር ላይ በመገኘቷ እና ማዕቀቦችን በግልጽ በመቃወም ጉዞዋን በመቀጠሏ ነው።
የዓለማችን ግዙፍ የነዳጅ ማጓጓዣ መስመር በሆነው እና ከፍተኛ ወታደራዊ ጥበቃ በሚደረግበት የሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ መታየቷ፣ በቀጠናው ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ሽኩቻ ዳግም ሊያቀጣጥል እንደሚችል ስጋት ፈጥሯል።
ይህች መርከብ ከክሬምሊን ጋር ጥብቅ ቁርኝት ካላቸው ቢሊየነሮች ጋር በቀጥታ የተገናኘች መሆኗ መረጋገጡ ደግሞ የጉዳዩን ክብደት ከፍ አድርጎታል።
በተለይም የአሜሪካ የገንዘብ ሚኒስቴር ማዕቀብ የጣለባቸው ንብረቶች እና ግለሰቦች፣ እንደ ሆርሙዝ ወሽመጥ ያሉ በአሜሪካ የጦር መርከቦች ጭምር ክትትል የሚደረግባቸውን ቀጠናዎች እንዴት በነፃነት ማለፍ እንደሚችሉ አዳዲስ ጥያቄዎችን እያስነሳ ይገኛል።
ይህ እንቅስቃሴ በምዕራባውያን ዘንድ እንደ ትልቅ ድፍረት የተቆጠረ ሲሆን፣ መርከቧ ማዕቀቡን ተላልፋ ይህን ስልታዊ የባህር መስመር ስታቋርጥ ከጀርባዋ ትልቅ የፖለቲካ መልዕክት እንዳለ ያሳብቃል።
የመርከቧ ጉዞ በወቅታዊው የሩሲያ እና የምዕራባውያን ፍጥጫ መካከል መከሰቱ ጉዳዩን ይበልጥ ያወሳስበዋል።
መርከቧ ቀጥሎ የምታርፍበት ወደብ የት ሊሆን እንደሚችል እና በመንገዷ ላይ ሊያጋጥሟት የሚችሉ የህግ እንቅፋቶች ምን እንደሆኑ አሁንም በቅርብ ክትትል እየተደረገባቸው ያሉ ነጥቦች ናቸው።
እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ ይህ በባህር ላይ የተከወነው ትርኢት ለባለቤቶቿ የቅንጦት ማሳያ ብቻ ሳይሆን፣ ለዓለም አቀፍ ህጎችና ማዕቀቦች የተሰጠ ግልጽ ምላሽ ይመስላል። በቀጠናው ያለውን ወታደራዊ ንቃትም ከፍ እንዲል ያደረገው ይህ ክስተት፣ መርከቧ የያዘችው ምስጢርና ቀጣይ መድረሻዋ ለዓለም አቀፉ ፖለቲካ አዲስ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
Comments