2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውጤት ቀውስ ውስጥ የሚገኘው አንጋፋው ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ፣ በ1990ዎቹ ክለቡን በማሰልጠን ስኬታማ ጊዜያትን ያሳለፉትን ትውልደ ሰርቢያዊ አሰልጣኝ ስሎቦዳን ሚቾን ዳግም ወደ ኢትዮጵያ አስመጥቷል።
ፈረሰኞቹ በፕሪሚየር ሊጉ ከውጤት ርቀው መቆየታቸው፣ በተለይም ባለፈው ሳምንት በነበረው ተጠባቂው የሸገር ደርቢ በባላንጣቸው ኢትዮጵያ ቡና የ3 ለ 1 ያልተጠበቀ ሽንፈት ማስተናገዳቸው የክለቡን አመራሮች አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስዱ አስገድዷቸዋል። ይህንን የደርቢ ሽንፈት ተከትሎም፣ የቀድሞ አሰልጣኙን በፍጥነት ወደ አዲስ አበባ የማምጣቱ ሂደት እንደተፈጸመ ታውቋል።
አሰልጣኝ ሚቾ ዛሬ አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፣ ከክለቡ ተጫዋቾች እና አሁን ካለው የአሰልጣኝ ስታፍ ጋር ትውውቅ አድርገዋል። ነገ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚያደርገውን ጨዋታም በመከታተል የቡድኑን ወቅታዊ አቋም በቅርበት ይገመግማሉ ተብሎ ይጠበቃል። አሰልጣኙ ዛሬ በነበረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአርባምንጭ ከተማ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታ ላይ፣ በስታዲየም ተገኝተው ከቅዱስ ጊዮርጊስ ዋና አሰልጣኝ እና ምክትል አሰልጣኝ መሀል ተቀምጠው ጨዋታውን ሲከታተሉ ታይተዋል።
በቀጣይ ቀሪ የሊጉ ጨዋታዎች ላይ የቅዱስ ጊዮርጊስ ልምምድ፣ የአጨዋወት ፍልስፍና እና የተጫዋቾች አሰላለፍ ምርጫ ሙሉ በሙሉ በአሰልጣኝ ሚቾ የሚመራ ይሆናል። ይሁን እንጂ አሰልጣኙ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እስካሁን ህጋዊ ምዝገባ ያላደረጉ በመሆናቸው፣ በጨዋታ ቀናት ከፊት ለፊት (በሜዳው ዳር) ወጥተው መመሪያ ከመስጠት ይልቅ፣ ከጀርባ ሆነው የክለቡን ስራዎች በበላይነት እንደሚመሩ ከወጣው መረጃ ለመረዳት ተችሏል።
ይህ የፈረሰኞቹ ያልተጠበቀ እርምጃ ክለቡን ወደ ቀድሞ የድል መንገዱ ይመልሰው ይሆን? የፕሪሚየር ሊጉ ቀሪ ጨዋታዎች የሚመልሱት ይሆናል።
ፈረሰኞቹ በፕሪሚየር ሊጉ ከውጤት ርቀው መቆየታቸው፣ በተለይም ባለፈው ሳምንት በነበረው ተጠባቂው የሸገር ደርቢ በባላንጣቸው ኢትዮጵያ ቡና የ3 ለ 1 ያልተጠበቀ ሽንፈት ማስተናገዳቸው የክለቡን አመራሮች አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስዱ አስገድዷቸዋል። ይህንን የደርቢ ሽንፈት ተከትሎም፣ የቀድሞ አሰልጣኙን በፍጥነት ወደ አዲስ አበባ የማምጣቱ ሂደት እንደተፈጸመ ታውቋል።
አሰልጣኝ ሚቾ ዛሬ አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፣ ከክለቡ ተጫዋቾች እና አሁን ካለው የአሰልጣኝ ስታፍ ጋር ትውውቅ አድርገዋል። ነገ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚያደርገውን ጨዋታም በመከታተል የቡድኑን ወቅታዊ አቋም በቅርበት ይገመግማሉ ተብሎ ይጠበቃል። አሰልጣኙ ዛሬ በነበረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአርባምንጭ ከተማ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታ ላይ፣ በስታዲየም ተገኝተው ከቅዱስ ጊዮርጊስ ዋና አሰልጣኝ እና ምክትል አሰልጣኝ መሀል ተቀምጠው ጨዋታውን ሲከታተሉ ታይተዋል።
በቀጣይ ቀሪ የሊጉ ጨዋታዎች ላይ የቅዱስ ጊዮርጊስ ልምምድ፣ የአጨዋወት ፍልስፍና እና የተጫዋቾች አሰላለፍ ምርጫ ሙሉ በሙሉ በአሰልጣኝ ሚቾ የሚመራ ይሆናል። ይሁን እንጂ አሰልጣኙ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እስካሁን ህጋዊ ምዝገባ ያላደረጉ በመሆናቸው፣ በጨዋታ ቀናት ከፊት ለፊት (በሜዳው ዳር) ወጥተው መመሪያ ከመስጠት ይልቅ፣ ከጀርባ ሆነው የክለቡን ስራዎች በበላይነት እንደሚመሩ ከወጣው መረጃ ለመረዳት ተችሏል።
ይህ የፈረሰኞቹ ያልተጠበቀ እርምጃ ክለቡን ወደ ቀድሞ የድል መንገዱ ይመልሰው ይሆን? የፕሪሚየር ሊጉ ቀሪ ጨዋታዎች የሚመልሱት ይሆናል።
2 months ago
የሸገር ንግሥና ለቡናማዎቹ
#ethiopia | ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ረታ
መላው የአዲስ አበባ ስፖርት ቤተሰብ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የሸገር ደርቢ በኢትዮጵያ ቡና አሸናፊነት ተጠናቋል።
ቡናማዎቹ በወጣት ተጫዋቾቻቸው ፈጣን እንቅስቃሴና በታክቲክ ብልጫ ፈረሰኞቹን በማስገረም የ3 ነጥብና የክብር ባለቤት ሆነዋል።
ለኢትዮጵያ ቡና ግቦቹን ያስቆጠሩ፦
ኦካይ ጁል (በእረፍት ሰዓት ቡድኑን ወደ ጨዋታው የመለሰች ወሳኝ ግብ)
ቢኒያም ጌታቸው
ዘላለም አባተ
ለቅዱስ ጊዮርጊስ፦ ፍፁም ጥላሁን ቀዳሚዋን ግብ ቢያስቆጥርም፣ የፈረሰኞቹን መሪነት ማስጠበቅ አልተቻለም።
የአዲስ አበባ ስታዲየም በቡናማና በአረንጓዴ/ቢጫ ቀለማት ደምቆ የዋለ ሲሆን፣ በተለይ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በታላቅ የደስታ ስሜት ሸገርን አውርተዋታል።
ይህ ድል ለቡናማዎቹ ከ3 ነጥብ በላይ የክብርና የኩራት ምንጭ ሆኖላቸዋል።
ዛሬ ለኢትዮጵያ ስፖርት ልዩ ቀን ነው። ለንደን ላይ ዮሚፍና ትዕግስት አሰፋ ታሪክ ሲሰሩ፣ አዲስ አበባ ደግሞ በሸገር ደርቢ ሙቀት ስትቃጠል ውላለች። ኢትዮጵያ ቡና ያሳየው ቁርጠኝነትና የወጣቶቹ ብቃት የሚደንቅ ነው። ፈረሰኞቹ መሪነታቸውን ማስጠበቅ አለመቻላቸው ለደጋፊዎቻቸው ባይዋጥም፣ ለኳስ አፍቃሪው ግን ጨዋታው እጅግ አስደሳች ነበር።
ሸገር ዛሬ ቡናማ ሆና አድራለች። እንኳን ደስ አላችሁ ቡናማዎቹ!
#getu #shegerderby #ethiopiabunna #stgeorge #ethiopianpremierleague #footballethiopia #addisababa #derbyday #matchday #ኢትዮጵያቡና #ቅዱስጊዮርጊስ #የሸገርደርቢ #ድል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ረታ
መላው የአዲስ አበባ ስፖርት ቤተሰብ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የሸገር ደርቢ በኢትዮጵያ ቡና አሸናፊነት ተጠናቋል።
ቡናማዎቹ በወጣት ተጫዋቾቻቸው ፈጣን እንቅስቃሴና በታክቲክ ብልጫ ፈረሰኞቹን በማስገረም የ3 ነጥብና የክብር ባለቤት ሆነዋል።
ለኢትዮጵያ ቡና ግቦቹን ያስቆጠሩ፦
ኦካይ ጁል (በእረፍት ሰዓት ቡድኑን ወደ ጨዋታው የመለሰች ወሳኝ ግብ)
ቢኒያም ጌታቸው
ዘላለም አባተ
ለቅዱስ ጊዮርጊስ፦ ፍፁም ጥላሁን ቀዳሚዋን ግብ ቢያስቆጥርም፣ የፈረሰኞቹን መሪነት ማስጠበቅ አልተቻለም።
የአዲስ አበባ ስታዲየም በቡናማና በአረንጓዴ/ቢጫ ቀለማት ደምቆ የዋለ ሲሆን፣ በተለይ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በታላቅ የደስታ ስሜት ሸገርን አውርተዋታል።
ይህ ድል ለቡናማዎቹ ከ3 ነጥብ በላይ የክብርና የኩራት ምንጭ ሆኖላቸዋል።
ዛሬ ለኢትዮጵያ ስፖርት ልዩ ቀን ነው። ለንደን ላይ ዮሚፍና ትዕግስት አሰፋ ታሪክ ሲሰሩ፣ አዲስ አበባ ደግሞ በሸገር ደርቢ ሙቀት ስትቃጠል ውላለች። ኢትዮጵያ ቡና ያሳየው ቁርጠኝነትና የወጣቶቹ ብቃት የሚደንቅ ነው። ፈረሰኞቹ መሪነታቸውን ማስጠበቅ አለመቻላቸው ለደጋፊዎቻቸው ባይዋጥም፣ ለኳስ አፍቃሪው ግን ጨዋታው እጅግ አስደሳች ነበር።
ሸገር ዛሬ ቡናማ ሆና አድራለች። እንኳን ደስ አላችሁ ቡናማዎቹ!
#getu #shegerderby #ethiopiabunna #stgeorge #ethiopianpremierleague #footballethiopia #addisababa #derbyday #matchday #ኢትዮጵያቡና #ቅዱስጊዮርጊስ #የሸገርደርቢ #ድል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
ቅዱስ ጊዮርጊስ ለሼህ መሐመድ ሁሴን አል-አሙዲ ያላቸውን ጥልቅ ክብር ገለጹ
#fastmereja I የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ለክለቡ ህልውና እና ስኬት ተወዳዳሪ የሌለው ውለታ ለዋሉለት ለታዋቂው ባለሀብት ለሼህ መሐመድ ሁሴን አል-አሙዲ ልዩ የምስጋና መልዕክት አስተላለፉ።
ደጋፊዎቹ በመልዕክታቸው እንደገለጹት፤ ሼህ መሐመድ ያለምንም የግል ጥቅም ፍላጎት፣ ያላቸውን ሀብት ለክለቡ ውጤታማነት በማዋል ደጋፊው በርካታ የደስታ ጊዜያትን እንዲያሳልፍ አድርገዋል። በተለይም ክለቡ አሁን ላይ ባለበት አስቸጋሪ ወቅት "አለሁላችሁ" በማለት በድጋሚ ያሳዩት ቁርጠኝነት የሚደነቅ መሆኑ ተጠቅሷል።
"ውለታዎን ታሪክ አይዘነጋውም፤ እኛም ጊዮርጊሳውያን በሚገባ እናስታውሰዋለን" በሚል የቀረበው ይኸው መግለጫ፣ ባለሀብቱ ለኢትዮጵያ ስፖርት ዕድገት በተለይም ለፈረሰኞቹ ክለብ ያደረጉት አስተዋጽኦ በታሪክ ማህደር ደምቆ የሚቀመጥ መሆኑን ያመላክታል። ሼህ መሐመድ አል-አሙዲ ለዓመታት የክለቡ የጀርባ አጥንት በመሆን ከፍተኛ የገንዘብና የማቴሪያል ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወቃል።
#fastmereja I የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ለክለቡ ህልውና እና ስኬት ተወዳዳሪ የሌለው ውለታ ለዋሉለት ለታዋቂው ባለሀብት ለሼህ መሐመድ ሁሴን አል-አሙዲ ልዩ የምስጋና መልዕክት አስተላለፉ።
ደጋፊዎቹ በመልዕክታቸው እንደገለጹት፤ ሼህ መሐመድ ያለምንም የግል ጥቅም ፍላጎት፣ ያላቸውን ሀብት ለክለቡ ውጤታማነት በማዋል ደጋፊው በርካታ የደስታ ጊዜያትን እንዲያሳልፍ አድርገዋል። በተለይም ክለቡ አሁን ላይ ባለበት አስቸጋሪ ወቅት "አለሁላችሁ" በማለት በድጋሚ ያሳዩት ቁርጠኝነት የሚደነቅ መሆኑ ተጠቅሷል።
"ውለታዎን ታሪክ አይዘነጋውም፤ እኛም ጊዮርጊሳውያን በሚገባ እናስታውሰዋለን" በሚል የቀረበው ይኸው መግለጫ፣ ባለሀብቱ ለኢትዮጵያ ስፖርት ዕድገት በተለይም ለፈረሰኞቹ ክለብ ያደረጉት አስተዋጽኦ በታሪክ ማህደር ደምቆ የሚቀመጥ መሆኑን ያመላክታል። ሼህ መሐመድ አል-አሙዲ ለዓመታት የክለቡ የጀርባ አጥንት በመሆን ከፍተኛ የገንዘብና የማቴሪያል ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወቃል።
3 months ago
ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ለሼህ መሀመድ አሊ አልአሙዲ ያላቸውን አክብሮት ገለጹ
#ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስ ግዙፉ ክለብ ቅዱስ ጊዮርጊስ (ፈረሰኞቹ) ላለፉት 30 ዓመታት ላደረጉላቸው ወደር የለሽ ድጋፍ ለታዋቂው ባለሀብት ሼህ መሀመድ አሊ አልአሙዲ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ክለቡ ባወጣው መግለጫ፣ ሼህ አላሙዲ ያለምንም የግል ጥቅም ፍላጎት ሀብታቸውን ለክለቡ ስኬት በማዋላቸው ደጋፊው በርካታ የደስታ ጊዜያትን እንዲያሳልፍ ምክንያት መሆናቸውን አስታውሷል። "እስካሁን በተገቢው መልኩ ምስጋና አላቀረብንልዎትም" ያለው ክለቡ፣ አሁን ግን ታሪካዊ ውለታቸውን በይፋ እውቅና ሰጥቷል።
ባለሀብቱ ላለፉት 30 ዓመታት ያላሰለሰ ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተገልጿል።
ከየትኛውም ክለብ በተለየ መልኩ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ስኬት የነበራቸው አስተዋጽኦ ተወድሷል።
ክለቡ በአሁኑ ወቅት ባለበት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ሼህ አላሙዲ "አለሁ" ማለታቸው ለክለቡ ትልቅ ብርታት መሆኑ ተጠቁሟል።
"ውለታዎን ታሪክ አይዘነጋውም፤ እኛም ጊዮርጊሳውያን በሚገባ እናስታውሰዋለን" በሚል ጥልቅ መልዕክት የታጀበው ይህ ምስጋና፣ በፈረሰኞቹ ቤት የባለሀብቱ ስፍራ ምን ያህል የላቀ መሆኑን ዳግም አረጋግጧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #stgeorgesa #saintgeorgefc #sheikhalamoudi #ethiopianfootball #kidusgiorgis #ፈረሰኞቹ #ቅዱስጊዮርጊስ
#ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስ ግዙፉ ክለብ ቅዱስ ጊዮርጊስ (ፈረሰኞቹ) ላለፉት 30 ዓመታት ላደረጉላቸው ወደር የለሽ ድጋፍ ለታዋቂው ባለሀብት ሼህ መሀመድ አሊ አልአሙዲ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ክለቡ ባወጣው መግለጫ፣ ሼህ አላሙዲ ያለምንም የግል ጥቅም ፍላጎት ሀብታቸውን ለክለቡ ስኬት በማዋላቸው ደጋፊው በርካታ የደስታ ጊዜያትን እንዲያሳልፍ ምክንያት መሆናቸውን አስታውሷል። "እስካሁን በተገቢው መልኩ ምስጋና አላቀረብንልዎትም" ያለው ክለቡ፣ አሁን ግን ታሪካዊ ውለታቸውን በይፋ እውቅና ሰጥቷል።
ባለሀብቱ ላለፉት 30 ዓመታት ያላሰለሰ ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተገልጿል።
ከየትኛውም ክለብ በተለየ መልኩ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ስኬት የነበራቸው አስተዋጽኦ ተወድሷል።
ክለቡ በአሁኑ ወቅት ባለበት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ሼህ አላሙዲ "አለሁ" ማለታቸው ለክለቡ ትልቅ ብርታት መሆኑ ተጠቁሟል።
"ውለታዎን ታሪክ አይዘነጋውም፤ እኛም ጊዮርጊሳውያን በሚገባ እናስታውሰዋለን" በሚል ጥልቅ መልዕክት የታጀበው ይህ ምስጋና፣ በፈረሰኞቹ ቤት የባለሀብቱ ስፍራ ምን ያህል የላቀ መሆኑን ዳግም አረጋግጧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #stgeorgesa #saintgeorgefc #sheikhalamoudi #ethiopianfootball #kidusgiorgis #ፈረሰኞቹ #ቅዱስጊዮርጊስ
3 months ago
የአንድነት ጥሪ
🌎 በመላው ዓለም ለምትገኙ የፈረሰኞቹ ደጋፊዎች በሙሉ
#ethiopia | የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብን ታሪካዊ ክብር ለመታደግ የቀረበ አንድነት ጥሪ ከቀድሞ የክለቡ ተጫዋቾችና የክለቡ አሁናዊ ሁኔታ እጅግ ያሳሰባቸው ከክለቡ ደጋፊዎች የቀረበ ጥሪ ለክለቡ የቦርድ አባላት፣ ለስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና በመላው ዓለም ለምትገኙ የፈረሰኞቹ ደጋፊዎች በሙሉ፦
ለዘጠኝ አስርተ ዓመታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርታዊ ክለብ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነት መለያ፣ የጽናት ተምሳሌትና የድል አድራጊነት ማማ ሆኖ ቆይቷል። ዛሬ ግን ይህ ታላቅ ተቋም ታሪካዊ በሆነ አስቸጋሪ ወቅት ላይ ይገኛል።
በደጋፊዎች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት፣ የሚለዋወጡት አሳዛኝ ቃላት እና በክለቡ አመራሮች መካከል የተፈጠረው ቀውስ የክለቡን የቦርድ አስተዳደር በሕግ እንዲታገድ አድርጎታል። ይህ ሁኔታ የክለቡን ህልውና አደጋ ላይ ከመጣሉም በላይ ለውድቀት አፋፍ እያደረሰው ይገኛል።
እኛ የቀድሞ የክለቡ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች፣ ክለባችን ሲፈርስ ዝም ብሎ ማየት የታሪክ ተጠያቂነት እንደሆነ እናምናለን። በመሆኑም፣ ክለባችንን ከመፍረስ ለመታደግና ሁሉንም ወገኖች አሸናፊ የሚያደርግ መፍትሄ ለማምጣት ይህንን የአንድነት ጥሪ በይፋ አቅርበናል።
የመፍትሄ ሀሳቦች
የክለባችንን ክብር ለመመለስ የሚከተሉት ሁለት ነጥቦች በአስቸኳይ እንዲተገበሩ ጥሪያችንን እናቀርባለን፦
፩. የቃላት ጦርነት ይቁም (ክብርን መልሶ ማግኘት)
በተለያዩ ወገኖች መካከል የሚደረጉ እርስ በርስ የሚያቃቅሩ፣ ለክለቡ ክብር የማይመጥኑና የጠላትነት መንፈስን የሚያንጸባርቁ የግንኙነት መንገዶች በአስቸኳይ ይቆሙ።
ቁርጠኝነት፦ ሁሉም ደጋፊዎችና አመራሮች በማህበራዊ ሚዲያም ሆነ በአካል የሚያደርጉትን የቃላት ምልልስ በመግታት፣ ለሰላማዊ ውይይት ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ እንጠይቃለን።
ግቡ፦ የሰለጠነና ለክለቡ እድገት የሚበጅ የውይይት ድባብ መፍጠር ነው።
፪. በጠቅላላ ጉባኤ አማካኝነት አጥኚና መፍትሄ አፍላቂ ኮሚቴ ይቋቋም
በክለቡ መተዳደሪያ ደንብና ሕግጋት መሠረት፣ የአመራር ክፍተቱን ለመሙላትና የሕግ ጥያቄዎችን ለመመለስ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ በአስቸኳይ ይጠራ።
ተግባር፦ ጠቅላላ ጉባኤው ጉዳዩን በጥልቀት መርምሮ ለሁሉም ወገኖች ተቀባይነት ያለውና ክለቡን ወደ ቀድሞ ጥንካሬው የሚመልስ "አጥኚና መፍትሄ አፍላቂ ኮሚቴ" እንዲያቋቁም እንጠይቃለን።
ውጤቱ፦ የግለሰቦች ፍላጎት ሳይሆን የክለቡ ህልውና የበላይነት የሚረጋገጥበት የአሸናፊነት መንገድ መጥረግ ነው።
ማጠቃለያ
ቅዱስ ጊዮርጊስ የግለሰቦች ሳይሆን የሚሊዮኖች ኩራትና የሀገር ሀብት ነው። ዛሬ የምናደርገው ውሳኔ ለቀጣዩ ትውልድ የምናስተላልፈውን ክለብ ዕጣ ፈንታ ይወስናል።
ልዩነቶቻችንን በውይይት ፈተን፣ ታሪካዊውን ክለባችንን ከውድቀት እንታደግ!
ፈረሰኛው ዳግም ይጋልባል!
የቀድሞ ተጫዋቾችና የደጋፊዎች ጥምረት
ST George Former Players and Supporters Association in USA 🇺🇸
አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ!
🌎 በመላው ዓለም ለምትገኙ የፈረሰኞቹ ደጋፊዎች በሙሉ
#ethiopia | የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብን ታሪካዊ ክብር ለመታደግ የቀረበ አንድነት ጥሪ ከቀድሞ የክለቡ ተጫዋቾችና የክለቡ አሁናዊ ሁኔታ እጅግ ያሳሰባቸው ከክለቡ ደጋፊዎች የቀረበ ጥሪ ለክለቡ የቦርድ አባላት፣ ለስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና በመላው ዓለም ለምትገኙ የፈረሰኞቹ ደጋፊዎች በሙሉ፦
ለዘጠኝ አስርተ ዓመታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርታዊ ክለብ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነት መለያ፣ የጽናት ተምሳሌትና የድል አድራጊነት ማማ ሆኖ ቆይቷል። ዛሬ ግን ይህ ታላቅ ተቋም ታሪካዊ በሆነ አስቸጋሪ ወቅት ላይ ይገኛል።
በደጋፊዎች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት፣ የሚለዋወጡት አሳዛኝ ቃላት እና በክለቡ አመራሮች መካከል የተፈጠረው ቀውስ የክለቡን የቦርድ አስተዳደር በሕግ እንዲታገድ አድርጎታል። ይህ ሁኔታ የክለቡን ህልውና አደጋ ላይ ከመጣሉም በላይ ለውድቀት አፋፍ እያደረሰው ይገኛል።
እኛ የቀድሞ የክለቡ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች፣ ክለባችን ሲፈርስ ዝም ብሎ ማየት የታሪክ ተጠያቂነት እንደሆነ እናምናለን። በመሆኑም፣ ክለባችንን ከመፍረስ ለመታደግና ሁሉንም ወገኖች አሸናፊ የሚያደርግ መፍትሄ ለማምጣት ይህንን የአንድነት ጥሪ በይፋ አቅርበናል።
የመፍትሄ ሀሳቦች
የክለባችንን ክብር ለመመለስ የሚከተሉት ሁለት ነጥቦች በአስቸኳይ እንዲተገበሩ ጥሪያችንን እናቀርባለን፦
፩. የቃላት ጦርነት ይቁም (ክብርን መልሶ ማግኘት)
በተለያዩ ወገኖች መካከል የሚደረጉ እርስ በርስ የሚያቃቅሩ፣ ለክለቡ ክብር የማይመጥኑና የጠላትነት መንፈስን የሚያንጸባርቁ የግንኙነት መንገዶች በአስቸኳይ ይቆሙ።
ቁርጠኝነት፦ ሁሉም ደጋፊዎችና አመራሮች በማህበራዊ ሚዲያም ሆነ በአካል የሚያደርጉትን የቃላት ምልልስ በመግታት፣ ለሰላማዊ ውይይት ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ እንጠይቃለን።
ግቡ፦ የሰለጠነና ለክለቡ እድገት የሚበጅ የውይይት ድባብ መፍጠር ነው።
፪. በጠቅላላ ጉባኤ አማካኝነት አጥኚና መፍትሄ አፍላቂ ኮሚቴ ይቋቋም
በክለቡ መተዳደሪያ ደንብና ሕግጋት መሠረት፣ የአመራር ክፍተቱን ለመሙላትና የሕግ ጥያቄዎችን ለመመለስ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ በአስቸኳይ ይጠራ።
ተግባር፦ ጠቅላላ ጉባኤው ጉዳዩን በጥልቀት መርምሮ ለሁሉም ወገኖች ተቀባይነት ያለውና ክለቡን ወደ ቀድሞ ጥንካሬው የሚመልስ "አጥኚና መፍትሄ አፍላቂ ኮሚቴ" እንዲያቋቁም እንጠይቃለን።
ውጤቱ፦ የግለሰቦች ፍላጎት ሳይሆን የክለቡ ህልውና የበላይነት የሚረጋገጥበት የአሸናፊነት መንገድ መጥረግ ነው።
ማጠቃለያ
ቅዱስ ጊዮርጊስ የግለሰቦች ሳይሆን የሚሊዮኖች ኩራትና የሀገር ሀብት ነው። ዛሬ የምናደርገው ውሳኔ ለቀጣዩ ትውልድ የምናስተላልፈውን ክለብ ዕጣ ፈንታ ይወስናል።
ልዩነቶቻችንን በውይይት ፈተን፣ ታሪካዊውን ክለባችንን ከውድቀት እንታደግ!
ፈረሰኛው ዳግም ይጋልባል!
የቀድሞ ተጫዋቾችና የደጋፊዎች ጥምረት
ST George Former Players and Supporters Association in USA 🇺🇸
አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ!
4 months ago
ምንተስኖት አዳነ በይፋ ከሜዳ መራቁን አሳወቀ
#ethiopia | ከፈረሰኞቹ ቤት ተገኝቶ በኢትዮጵያ እግርኳስ ላይ ትልቅ አሻራውን ያሳረፈው ምንተስኖት፣ ከ17 ዓመታት ድንቅ ጉዞ በኋላ "ጫማዬን ሰቅያለሁ" ሲል አዲሱን የሕይወት ምዕራፍ ተቀብሏል።
የምንተስኖት አዳነ የስኬት ጉዞ በአጭሩ፦
* የፈረሰኞቹ ምልክት፦ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት ለ13 ዓመታት በቆየባቸው ጊዜያት 6 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን በማንሳት የታሪክ አካል ሆኗል።
* የመጨረሻው ድምቀት፦ ባለፈው የውድድር ዓመት ከኢትዮጵያ መድን ጋር ድንቅ ጊዜን አሳልፎ ሻምፒዮን መሆን ችሏል።
* የብሔራዊ ቡድን አገልጋይ፦ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) በተከላካይ መስመር ላይ የነበረው አስተዋጽኦ የሚዘነጋ አይደለም።
"አዲስ ምዕራፍ"
ምንተስኖት ስንብቱን ሲያበስር እንዲህ ብሏል፦
"በኢትዮጵያ እግርኳስ ውስጥ ለነበረኝ ቆይታ አመስጋኝ ነኝ። አሁን አዲስ ምዕራፍ የምጀምርበት ነው፤ ደስ የሚልና ስኬታማ ጊዜ ነበረኝ።"
ለአንድ ተጫዋች ከሜዳ መራቅ ከባድ ቢሆንም፣ ምንተስኖት ግን በስኬት ማማ ላይ ሆኖ መሰናበቱን መርጧል። ለኢትዮጵያ እግርኳስ ላበረከተው አስተዋጽኦ ትልቅ ምስጋና ይገባዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #mintesnotadane #photocredittikvah #ethiopianfootball #kidusgiorgis #ethiopiamedhin #legend #retirement #የኢትዮጵያፕሪሚየርሊግ
#ethiopia | ከፈረሰኞቹ ቤት ተገኝቶ በኢትዮጵያ እግርኳስ ላይ ትልቅ አሻራውን ያሳረፈው ምንተስኖት፣ ከ17 ዓመታት ድንቅ ጉዞ በኋላ "ጫማዬን ሰቅያለሁ" ሲል አዲሱን የሕይወት ምዕራፍ ተቀብሏል።
የምንተስኖት አዳነ የስኬት ጉዞ በአጭሩ፦
* የፈረሰኞቹ ምልክት፦ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት ለ13 ዓመታት በቆየባቸው ጊዜያት 6 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን በማንሳት የታሪክ አካል ሆኗል።
* የመጨረሻው ድምቀት፦ ባለፈው የውድድር ዓመት ከኢትዮጵያ መድን ጋር ድንቅ ጊዜን አሳልፎ ሻምፒዮን መሆን ችሏል።
* የብሔራዊ ቡድን አገልጋይ፦ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) በተከላካይ መስመር ላይ የነበረው አስተዋጽኦ የሚዘነጋ አይደለም።
"አዲስ ምዕራፍ"
ምንተስኖት ስንብቱን ሲያበስር እንዲህ ብሏል፦
"በኢትዮጵያ እግርኳስ ውስጥ ለነበረኝ ቆይታ አመስጋኝ ነኝ። አሁን አዲስ ምዕራፍ የምጀምርበት ነው፤ ደስ የሚልና ስኬታማ ጊዜ ነበረኝ።"
ለአንድ ተጫዋች ከሜዳ መራቅ ከባድ ቢሆንም፣ ምንተስኖት ግን በስኬት ማማ ላይ ሆኖ መሰናበቱን መርጧል። ለኢትዮጵያ እግርኳስ ላበረከተው አስተዋጽኦ ትልቅ ምስጋና ይገባዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #mintesnotadane #photocredittikvah #ethiopianfootball #kidusgiorgis #ethiopiamedhin #legend #retirement #የኢትዮጵያፕሪሚየርሊግ
4 months ago
የዛሬ ጨዋታዎች
🇪🇹 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የጥሎ ማለፍ ፍልሚያዎች
የአገር ውስጥ እግር ኳስ ዛሬ በታላላቅ ክለቦች ግጥሚያ ይሞቃል። በተለይ በ "አፄዎቹ" እና በ "ፈረሰኞቹ" መካከል የሚደረገው ጨዋታ የሁሉንም ትኩረት ስቧል።
* 07:00 | ወልዋሎ አዲግራት ዩ. ከ አርባምንጭ ከተማ
* 09:00 | መቐለ 70 እንደርታ ከ ኢትዮጵያ ቡና
* 10:00 | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ (ተጠባቂው የሳምንቱ ጨዋታ)
* 12:00 | ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ነጌሌ አርሲ
🏴 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ
በእንግሊዝ ሊግ ዛሬ የምሽቱ ማሳረጊያ የሚሆነው በቶተንሀም እና በማንችስተር ሲቲ መካከል የሚደረገው ፍልሚያ ነው። ፔፕ ጋርዲዮላ ወደ ሰሜን ለንደን የሚያቀኑት ወሳኝ ነጥብ ፍለጋ ነው።
* 11:00 | አስቶን ቪላ ከ ብሬንትፎርድ
* 11:00 | ማንችስተር ዪናይትድ ከ ፉልሀም
* 01:30 | ቶተንሀም ከ ማንችስተር ሲቲ
🇪🇸 ላ ሊጋ እና 🇮🇹 ሴሪ አ
በስፔን ሪያል ማድሪድ የደረጃ ሰንጠረዡን ለመምራት ራዮን ያስተናግዳል፤ በጣሊያን ደግሞ ጁቬንቱስ እና ኢንተር ሚላን የድል ጉዟቸውን ለመቀጠል ወደ ሜዳ ይገባሉ።
* 10:00 | ሪያል ማድሪድ ከ ራዮ ቫይካኖ
* 11:00 | ኮሞ ከ አታላንታ
* 02:00 | ክሪሞኔንሴ ከ ኢንተር ሚላን
* 04:45 | ፓርማ ከ ጁቬንቱስ
መልካም የኳስ ምሽት ይሁንላችሁ!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopianpremierleague #premierleague #laliga #seriea #matchday #footballethiopia #realmadrid #mancity #saintgeorgesa
🇪🇹 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የጥሎ ማለፍ ፍልሚያዎች
የአገር ውስጥ እግር ኳስ ዛሬ በታላላቅ ክለቦች ግጥሚያ ይሞቃል። በተለይ በ "አፄዎቹ" እና በ "ፈረሰኞቹ" መካከል የሚደረገው ጨዋታ የሁሉንም ትኩረት ስቧል።
* 07:00 | ወልዋሎ አዲግራት ዩ. ከ አርባምንጭ ከተማ
* 09:00 | መቐለ 70 እንደርታ ከ ኢትዮጵያ ቡና
* 10:00 | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ (ተጠባቂው የሳምንቱ ጨዋታ)
* 12:00 | ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ነጌሌ አርሲ
🏴 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ
በእንግሊዝ ሊግ ዛሬ የምሽቱ ማሳረጊያ የሚሆነው በቶተንሀም እና በማንችስተር ሲቲ መካከል የሚደረገው ፍልሚያ ነው። ፔፕ ጋርዲዮላ ወደ ሰሜን ለንደን የሚያቀኑት ወሳኝ ነጥብ ፍለጋ ነው።
* 11:00 | አስቶን ቪላ ከ ብሬንትፎርድ
* 11:00 | ማንችስተር ዪናይትድ ከ ፉልሀም
* 01:30 | ቶተንሀም ከ ማንችስተር ሲቲ
🇪🇸 ላ ሊጋ እና 🇮🇹 ሴሪ አ
በስፔን ሪያል ማድሪድ የደረጃ ሰንጠረዡን ለመምራት ራዮን ያስተናግዳል፤ በጣሊያን ደግሞ ጁቬንቱስ እና ኢንተር ሚላን የድል ጉዟቸውን ለመቀጠል ወደ ሜዳ ይገባሉ።
* 10:00 | ሪያል ማድሪድ ከ ራዮ ቫይካኖ
* 11:00 | ኮሞ ከ አታላንታ
* 02:00 | ክሪሞኔንሴ ከ ኢንተር ሚላን
* 04:45 | ፓርማ ከ ጁቬንቱስ
መልካም የኳስ ምሽት ይሁንላችሁ!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopianpremierleague #premierleague #laliga #seriea #matchday #footballethiopia #realmadrid #mancity #saintgeorgesa
5 months ago
ፈረሰኛውና ፈረሶቹ በጥቅሻ የሚግባቡበት ምድር‼️
🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎
#ethiopia | ምድሩ ለፈረሶች ተመርጦ የተፈጠረ ይመስላል፤ ሕዝቡም ፈረስን ከሰማይ በአደራ የተቀበለ ደገኛ ሕዝብ ። የአገው ታሪክ በፈረስ ኮቴ በለምለም ምድር የተጻፈ በትውልድ የሚነበብ ሕያው ብራና ነው። 🐎🐎🐎
የአገው ታሪክ እንደ አምፖል ከጣራ በታች ሳይሆን እንደፀሐይ ከሰማይ በታች የሚያበራ ብርሃናማ የተጋድሎ ታሪክ ነው። አክሱም ሲነሳ ፈረሰኛው አገውና ፈረሶቹ በዚያ ይነሳሉ ።
ላሊበላም ሲዘከር ከነ ዛጉዌ ሥርወ መንግስታቸው ንጉስም ቅዱስም፤ ካህንም አናጺም፤ መሪም ዘካሪም ኾነው
ፈረስ ጋላቢዎቹ አገዎች፣ ከተጋላቢዎቹ ፈረሶቻቸው ጋር በወርቅ ቀለም ተጽፈው በዚያ አሉ።
የፓን አፍሪካኒዝም የልደት ምስክር ወረቀት አድዋ ሲነሳም ፈረሰኞቹ አገዎችና ፈረሶች፤ በአይበገሬነት ታሪካቸው በደማቁ ድላቸው በዚያ አሉ። በአድዋ ተራራ ከተቀበሩ እልፍ አርበኞች አጽም ጋር የፈረሶች አጽምም በዚያ አለ። ፈረሰኛውና ፈረሶቹ በየታሪኩ ምዕራፍ ለሀገር ግንባታ ጡብ ደርድረዋል፤ የስማቸውንም ሐውልት አቁመዋል ። 🐎🐎🐎
የፈረስን ውለታ አገው ያውቀዋል፤ እንኳን ለባለውለታው ፈረስ፤ ነፍስ ላለው ፍጥረት ሁሉ የሚራራው የአገው ሕዝብ፤ ፈረስን እንደ ልጁ መርጦ ይመግበዋል። በሥርዓትና በማዕረግ ያሳድገዋል፣ በትጋትና በሥልጣኔ ይገራዋል፣ በግርማና በሞገስ በተዋቡ አልባሳትና ጌጦች ይሸልመዋል። ፈረሱን በልኩ እንዲሠራ በሚገባውም እንዲያርፍ ያደርገዋል። 🐎🐎🐎
ፈረሱም ለአባቱ ለአገው ሕዝብ እንደሚታዘዘው ለሌላው የሚገራና የሚታዘዝ አይመስልም ። በእርሻው በኩል በግራም በቀኝም ተጠምዶ ትከሻው እስኪላጥ አርሶ፣ ወቅቶ፣ አዝመራ ተሸክሞ ወደ ጎተራ አስገብቶ አገልግሏል ። 🐎🐎🐎
አገው ልጁን ቢድር ሙሽሮቹን እንደሊሞዚን ተሸክሞ ጫጉላ አውጥቷል ። ቢታመም እንደ አምፑላንስ ኾኖ ሐኪም ደጅ አድርሷል ። ሞት መከራ ቢመጣ ከአልቃሽና አስለቃሽ ጋር ደክሞ፣ አልቅሶ በክብር ይሸኛል ። ዘመድ ቢናፍቁ ፈጣን ትራንስፖርት ኾኖ ወንዝ አሻግሮ ዘመድ በማገናኘት ናፍቆትን አስወጥቷል ። 🐎🐎🐎
አይሞሎ አይሞሎ ሞሎ ዎ!
ሲዋጋ ውሎ ሲዋጋ አመሸ፣
ጋሻውን በዘንግ እያንኮላሸ፡፡
ቦራ ብሎ ጠራው ጀግና ፈረሱን፣
እንኳን አግዜር ሰጠው የተመኘውን፡፡
የጀግናው ባለሟል እኔነኝ ፈረስ፣
ከተፋፋመው ጦር አብሬ ምደርስ፡፡
ጀግናው ፈረሰኛ መጣ ገሰገሰ፤
የጠላቱን ምሽግ እየደረመሰ። የተባለለት ...🐎🐎🐎
ጠላት ቢመጣ ጦር ሜዳ አድርሶ፣ ጠላትን እየረገጠ፣ በጌታው ፋንታ በጦሩም፣ በጎራዴውም፣ በጥይቱም እየቆሰለና እየሞተ ተዋግቷል ። ክብረ በዓላቱን ትርዒት እንደሰለጠነ ወታደር በሥርዓት ተሰልፈው ሰላምታ እየሰጡ ያደምቁታል። 🐎🐎🐎
ለዚህም በአገው ምድር ፈረስ፤ አርበኝነት፣ ነጻነት፣ ድል አድራጊነት፣ የሀገር ፍቅር እና አንድነት የሚንጸባረቅበት የድል ምልክት ኾኖ ይዘከራል ። ፈረሰኛው በንፁህ ባርኔጣ፣ በሎፊሳ፣ በነጭ ኮት እና ሱሪ (ግርቭ ታምባ) በገምባሌ እና አለንጋውን ከሰነደቁ ፤ ጋሻውን ከዘንጉ ጋር ይዞ ከመድመቁ በላይ፤ ፈረሱ በኮርቻ፣ በልቫቭ፣ በልጓም፣ በአምፓጉሲ እና በወደሊ ቀይ አበባ ይደምቃል፡፡ 🐎🐎🐎
የፈረሱ ሰላምታ አሰጣጥ፣ የድንግል ዓሳ ትርዒት፣ የስግሪያ፣ የጉግስ ፣ እና ሽርጥ ትርዒት ሲካሄድ ማየት ልብን ቀጥ የሚያደርግ ደስታ ይሰጣል። ፈረሰኛውና ፈረሱ በጥቅሻ የሚግባቡበት፣ የፈረስ ማዕበል በቀይ ጌጥ ተውቦ የሚፈስበት ትርዒት በአገው ምድር ሰማይ ሥር ይታያል። 🐎🐎🐎
ለሕጻናት ፈረሰኞች የሚታዘዝ ፈረስ በዚያ አለ፤ ለዐይነ ሥውሩ የሚታዘዝ መንገድ መሪ ብቻ ሳይሆን ከዐይናማዎቹ ጋር ተወዳድሮ አሸናፊ ፈረስ በዚያ አለ። ሴት ፈረሰኞች የሳይንስን የዙረት ስሌት ሽረው እየተሽከረከሩ የሚጋልቡት ፈረስ፣ በምልክት ተረድቶ የሚሽከረከር ፈረስ በአገው ምድር ይታያል ። 🐎🐎🐎
በአገው ምድር ሰባቱ ወንድማማቾች «አንክሺ፣ ባንጂ፣ ዚጋሚ፣ አዚኒ፣ ኳኩሪ፣ ቻሪና ሚቲክሊ» እንደአንድ ልብ መካሪ እንድ ቃል ተናጋሪ ናቸው። ፈረስ 🐎 ልዩ ምልክታቸው ስልጣኔ መለያቸው ነው።
ፀሐዩ አይሰማም እንጅ ከተሰማህ ለፀሐዩ አዊት ድጋግ (የአገው ጥላ) አለ። ለሆድህ አትጨነቅ አብዚ፣ ጉዝጉዝ፣ በመልክ በመልኩ ከጠላው ከጠጁና ከብርዙ ጋር በበቃኝ ይቀርባል ። በአገው ምድር የምታየውን ዐይተህ ታደንቀዋለህ፣ እያሰብኸው ትደመማለህ እንጅ ለመጻፍ እንዴት ይቻላል ?
በዚያ ምድር የተገኘህ፣ ፈረሰኛውና ፈረሶቹ በጥቅሻ ሲግባቡ ያየህ፣ ከፈረሱ ጋር ተጫወት።
አይሞሎ አይሞሎ ሞሎ ዎ! 🐎🐎
የፈንዞ ጌታ፣ የጥሪኝ ጌታ የሻሾ ጌታ፤ 🐎🐎
ጀምር ጨዋታ በል ጋሻ ምታ ግጠም እስክስታ ።
👉62 ሺህ ፈረሰኞችና ፈረሶች ያሉት፣ 🐎🐎🐎
👉86 ዓመታትን በሦስት ዐለቃ እየተመራ ዛሬ ላይ የደረሰ፣
👉ባህልን፣ ታሪክን፣ ባለውለታን የሚዘክር፣
👉 የድል አድራጊነት ምልክትና አንድነትን የሚያጠናክር፣
‼️ የአገው ፈረሰኞች 🐎 ማኅበር ‼️👌
እንኳን አደረሳችሁ ‼️
እንኮዋን 86ንቲ አጋው ፌሬስቴኑ ባልስ ታምፅኾስ‼️
🐎🐎🐎 የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን 🐎🐎🐎
🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎🐎
#ethiopia | ምድሩ ለፈረሶች ተመርጦ የተፈጠረ ይመስላል፤ ሕዝቡም ፈረስን ከሰማይ በአደራ የተቀበለ ደገኛ ሕዝብ ። የአገው ታሪክ በፈረስ ኮቴ በለምለም ምድር የተጻፈ በትውልድ የሚነበብ ሕያው ብራና ነው። 🐎🐎🐎
የአገው ታሪክ እንደ አምፖል ከጣራ በታች ሳይሆን እንደፀሐይ ከሰማይ በታች የሚያበራ ብርሃናማ የተጋድሎ ታሪክ ነው። አክሱም ሲነሳ ፈረሰኛው አገውና ፈረሶቹ በዚያ ይነሳሉ ።
ላሊበላም ሲዘከር ከነ ዛጉዌ ሥርወ መንግስታቸው ንጉስም ቅዱስም፤ ካህንም አናጺም፤ መሪም ዘካሪም ኾነው
ፈረስ ጋላቢዎቹ አገዎች፣ ከተጋላቢዎቹ ፈረሶቻቸው ጋር በወርቅ ቀለም ተጽፈው በዚያ አሉ።
የፓን አፍሪካኒዝም የልደት ምስክር ወረቀት አድዋ ሲነሳም ፈረሰኞቹ አገዎችና ፈረሶች፤ በአይበገሬነት ታሪካቸው በደማቁ ድላቸው በዚያ አሉ። በአድዋ ተራራ ከተቀበሩ እልፍ አርበኞች አጽም ጋር የፈረሶች አጽምም በዚያ አለ። ፈረሰኛውና ፈረሶቹ በየታሪኩ ምዕራፍ ለሀገር ግንባታ ጡብ ደርድረዋል፤ የስማቸውንም ሐውልት አቁመዋል ። 🐎🐎🐎
የፈረስን ውለታ አገው ያውቀዋል፤ እንኳን ለባለውለታው ፈረስ፤ ነፍስ ላለው ፍጥረት ሁሉ የሚራራው የአገው ሕዝብ፤ ፈረስን እንደ ልጁ መርጦ ይመግበዋል። በሥርዓትና በማዕረግ ያሳድገዋል፣ በትጋትና በሥልጣኔ ይገራዋል፣ በግርማና በሞገስ በተዋቡ አልባሳትና ጌጦች ይሸልመዋል። ፈረሱን በልኩ እንዲሠራ በሚገባውም እንዲያርፍ ያደርገዋል። 🐎🐎🐎
ፈረሱም ለአባቱ ለአገው ሕዝብ እንደሚታዘዘው ለሌላው የሚገራና የሚታዘዝ አይመስልም ። በእርሻው በኩል በግራም በቀኝም ተጠምዶ ትከሻው እስኪላጥ አርሶ፣ ወቅቶ፣ አዝመራ ተሸክሞ ወደ ጎተራ አስገብቶ አገልግሏል ። 🐎🐎🐎
አገው ልጁን ቢድር ሙሽሮቹን እንደሊሞዚን ተሸክሞ ጫጉላ አውጥቷል ። ቢታመም እንደ አምፑላንስ ኾኖ ሐኪም ደጅ አድርሷል ። ሞት መከራ ቢመጣ ከአልቃሽና አስለቃሽ ጋር ደክሞ፣ አልቅሶ በክብር ይሸኛል ። ዘመድ ቢናፍቁ ፈጣን ትራንስፖርት ኾኖ ወንዝ አሻግሮ ዘመድ በማገናኘት ናፍቆትን አስወጥቷል ። 🐎🐎🐎
አይሞሎ አይሞሎ ሞሎ ዎ!
ሲዋጋ ውሎ ሲዋጋ አመሸ፣
ጋሻውን በዘንግ እያንኮላሸ፡፡
ቦራ ብሎ ጠራው ጀግና ፈረሱን፣
እንኳን አግዜር ሰጠው የተመኘውን፡፡
የጀግናው ባለሟል እኔነኝ ፈረስ፣
ከተፋፋመው ጦር አብሬ ምደርስ፡፡
ጀግናው ፈረሰኛ መጣ ገሰገሰ፤
የጠላቱን ምሽግ እየደረመሰ። የተባለለት ...🐎🐎🐎
ጠላት ቢመጣ ጦር ሜዳ አድርሶ፣ ጠላትን እየረገጠ፣ በጌታው ፋንታ በጦሩም፣ በጎራዴውም፣ በጥይቱም እየቆሰለና እየሞተ ተዋግቷል ። ክብረ በዓላቱን ትርዒት እንደሰለጠነ ወታደር በሥርዓት ተሰልፈው ሰላምታ እየሰጡ ያደምቁታል። 🐎🐎🐎
ለዚህም በአገው ምድር ፈረስ፤ አርበኝነት፣ ነጻነት፣ ድል አድራጊነት፣ የሀገር ፍቅር እና አንድነት የሚንጸባረቅበት የድል ምልክት ኾኖ ይዘከራል ። ፈረሰኛው በንፁህ ባርኔጣ፣ በሎፊሳ፣ በነጭ ኮት እና ሱሪ (ግርቭ ታምባ) በገምባሌ እና አለንጋውን ከሰነደቁ ፤ ጋሻውን ከዘንጉ ጋር ይዞ ከመድመቁ በላይ፤ ፈረሱ በኮርቻ፣ በልቫቭ፣ በልጓም፣ በአምፓጉሲ እና በወደሊ ቀይ አበባ ይደምቃል፡፡ 🐎🐎🐎
የፈረሱ ሰላምታ አሰጣጥ፣ የድንግል ዓሳ ትርዒት፣ የስግሪያ፣ የጉግስ ፣ እና ሽርጥ ትርዒት ሲካሄድ ማየት ልብን ቀጥ የሚያደርግ ደስታ ይሰጣል። ፈረሰኛውና ፈረሱ በጥቅሻ የሚግባቡበት፣ የፈረስ ማዕበል በቀይ ጌጥ ተውቦ የሚፈስበት ትርዒት በአገው ምድር ሰማይ ሥር ይታያል። 🐎🐎🐎
ለሕጻናት ፈረሰኞች የሚታዘዝ ፈረስ በዚያ አለ፤ ለዐይነ ሥውሩ የሚታዘዝ መንገድ መሪ ብቻ ሳይሆን ከዐይናማዎቹ ጋር ተወዳድሮ አሸናፊ ፈረስ በዚያ አለ። ሴት ፈረሰኞች የሳይንስን የዙረት ስሌት ሽረው እየተሽከረከሩ የሚጋልቡት ፈረስ፣ በምልክት ተረድቶ የሚሽከረከር ፈረስ በአገው ምድር ይታያል ። 🐎🐎🐎
በአገው ምድር ሰባቱ ወንድማማቾች «አንክሺ፣ ባንጂ፣ ዚጋሚ፣ አዚኒ፣ ኳኩሪ፣ ቻሪና ሚቲክሊ» እንደአንድ ልብ መካሪ እንድ ቃል ተናጋሪ ናቸው። ፈረስ 🐎 ልዩ ምልክታቸው ስልጣኔ መለያቸው ነው።
ፀሐዩ አይሰማም እንጅ ከተሰማህ ለፀሐዩ አዊት ድጋግ (የአገው ጥላ) አለ። ለሆድህ አትጨነቅ አብዚ፣ ጉዝጉዝ፣ በመልክ በመልኩ ከጠላው ከጠጁና ከብርዙ ጋር በበቃኝ ይቀርባል ። በአገው ምድር የምታየውን ዐይተህ ታደንቀዋለህ፣ እያሰብኸው ትደመማለህ እንጅ ለመጻፍ እንዴት ይቻላል ?
በዚያ ምድር የተገኘህ፣ ፈረሰኛውና ፈረሶቹ በጥቅሻ ሲግባቡ ያየህ፣ ከፈረሱ ጋር ተጫወት።
አይሞሎ አይሞሎ ሞሎ ዎ! 🐎🐎
የፈንዞ ጌታ፣ የጥሪኝ ጌታ የሻሾ ጌታ፤ 🐎🐎
ጀምር ጨዋታ በል ጋሻ ምታ ግጠም እስክስታ ።
👉62 ሺህ ፈረሰኞችና ፈረሶች ያሉት፣ 🐎🐎🐎
👉86 ዓመታትን በሦስት ዐለቃ እየተመራ ዛሬ ላይ የደረሰ፣
👉ባህልን፣ ታሪክን፣ ባለውለታን የሚዘክር፣
👉 የድል አድራጊነት ምልክትና አንድነትን የሚያጠናክር፣
‼️ የአገው ፈረሰኞች 🐎 ማኅበር ‼️👌
እንኳን አደረሳችሁ ‼️
እንኮዋን 86ንቲ አጋው ፌሬስቴኑ ባልስ ታምፅኾስ‼️
🐎🐎🐎 የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን 🐎🐎🐎
Sponsored by
Surafel
5 months ago
🔥 እንዳያመልጥዎ! | የኮከቦች ጨዋታ በአዲስ አበባ ስታዲየም
#ethiopia | ነገ፣ እሁድ የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች (በውጭ እና በሀገር ውስጥ ያሉ) የሚገናኙበት ልዩ ጨዋታ ይደረጋል።
ተሳታፊዎች እነማን ናቸው?
በውጪ የሚኖሩ የቀድሞ ኮከቦች 🆚 በሀገር ውስጥ ያሉ ኮከቦች
(እነ አሸናፊ ግርማ፣ ዮርዳኖስ ዓባይ እና ሽመልስ በቀለን ጨምሮ)
📅 ቀን፡ ነገ እሁድ
⏰ ሰዓት፡ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 ቦታ፡ አዲስ አበባ ስታዲየም
ቤተሰብ ይሁኑ፣ ይዝናኑ!
🛡️ የማይደፈረው የመሀል ደጀን - አሸናፊ ግርማ ⚽️
በኢትዮጵያ እግር ኳስ በተለይም በቅዱስ ጊዮርጊስ እና በብሔራዊ ቡድን ታሪክ ውስጥ በጠንካራ ተከላካይነቱ እና በዲሲፕሊኑ የሚታወቀው አሸናፊ ግርማ!
በቀኝ ተከላካይነት ቦታ ላይ በሚያሳየው አስደናቂ ብቃት፣ ወደ ፊት ሄዶ ኳስ በማሻገር እና የቡድንን ሞራል በመጠበቅ ረገድ አሸናፊ ተወዳዳሪ አልነበረውም። "ፈረሰኞቹ" በስኬት በቆዩባቸው ዓመታት የአሸናፊ ግርማ ሚና እጅግ ከፍተኛ ነበር።
ለክለቡም ሆነ ለሀገሩ በታማኝነት ያገለገለ እውነተኛ የስፖርት ሰው! 🙌
⚽️ የጎል ማሽኑ - ዮርዳኖስ ዓባይ! 🥅
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ካፈራቸው፣ መረብን ማራድ የዘወትር ተግባራቸው ከሆነ ምርጥ አጥቂዎች አንዱ!
ዮርዳኖስ ዓባይ በመብራት ኃይል (ኤሌክትሪክ) እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ባሳለፈው ጊዜ በግዙፍ ሰውነቱ፣ በአየር ላይ ኳስ አጠቃቀሙ እና በድንቅ የጨረስ አቅሙ ይታወሳል።
በተለይም ወደ የመን በማምራት በ አል ሳቅር ክለብ የሰራው ታሪክ እና የሰበራቸው የጎል ክብረወሰኖች ስሙን በውጭ ሀገር ጭምር ገናና አድርገውታል።
ከዓመታት በኋላ ይህንን "የጎል አዳኝ" ነገ እሁድ በአዲስ አበባ ስታዲየም በሚደረገው የናፍቆት ጨዋታ ላይ ልንመለከተው ነው።
⚽️ የሜዳው ታንክ - ፍቅሩ ተፈራ! 🇪🇹
በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ተክለ ሰውነቱ፣ ጉልበቱ እና አጨራረሱ ለየት ያለ ድንቅ አጥቂ!
ፍቅሩ ተፈራ (ሌሜሳ) ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች በውጭ ሀገር ፕሮፌሽናል ሊጎች ተፈላጊ እንዲሆኑ በር የከፈተ ፈር ቀዳጅ ነው። ከቅዱስ ጊዮርጊስ ተነስቶ በደቡብ አፍሪካው ታላቅ ክለብ ኦርላንዶ ፓይሬትስ እና ሱፐር ስፖርት ዩናይትድ ያሳየው ብቃት አይረሳም።
በተለይም በሕንድ ሱፐር ሊግ (ISL) ታሪክ የመጀመሪያውን ጎል ለአትሌቲኮ ደ ኮልካታ በማስቆጠር ስሙን በታሪክ መዝገብ ላይ አሰፍሯል። የተከላካዮችን ጥንካሬ የሚፈትነው ጉልበቱ እና አልፎ አልፎ የሚያስቆጥራቸው "አክሮባቲክ" ጎሎች የፍቅሩ መለያዎች ናቸው።
ለኢትዮጵያ እግር ኳስ በዓለም አቀፍ መድረክ ተጠሪ ለነበረው ለዚህ ጀግና ክብር ይገባዋል! 🙌
#fikrutefera #ethiopianlegend #orlandopirates #isl #historymaker #waliyas #shimelisbekele #ethiopianfootball #waliyas #legend #playmaker #sport #football #ethiopia #legendsgame #addisababa #ashenafigirma #saintgeorgefc #ethiopianfootball #legend #defender #waliyas #yordanosabay #goalmachine #ethiopianfootball #legend #waliyas #yemenleague
#ethiopia | ነገ፣ እሁድ የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች (በውጭ እና በሀገር ውስጥ ያሉ) የሚገናኙበት ልዩ ጨዋታ ይደረጋል።
ተሳታፊዎች እነማን ናቸው?
በውጪ የሚኖሩ የቀድሞ ኮከቦች 🆚 በሀገር ውስጥ ያሉ ኮከቦች
(እነ አሸናፊ ግርማ፣ ዮርዳኖስ ዓባይ እና ሽመልስ በቀለን ጨምሮ)
📅 ቀን፡ ነገ እሁድ
⏰ ሰዓት፡ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 ቦታ፡ አዲስ አበባ ስታዲየም
ቤተሰብ ይሁኑ፣ ይዝናኑ!
🛡️ የማይደፈረው የመሀል ደጀን - አሸናፊ ግርማ ⚽️
በኢትዮጵያ እግር ኳስ በተለይም በቅዱስ ጊዮርጊስ እና በብሔራዊ ቡድን ታሪክ ውስጥ በጠንካራ ተከላካይነቱ እና በዲሲፕሊኑ የሚታወቀው አሸናፊ ግርማ!
በቀኝ ተከላካይነት ቦታ ላይ በሚያሳየው አስደናቂ ብቃት፣ ወደ ፊት ሄዶ ኳስ በማሻገር እና የቡድንን ሞራል በመጠበቅ ረገድ አሸናፊ ተወዳዳሪ አልነበረውም። "ፈረሰኞቹ" በስኬት በቆዩባቸው ዓመታት የአሸናፊ ግርማ ሚና እጅግ ከፍተኛ ነበር።
ለክለቡም ሆነ ለሀገሩ በታማኝነት ያገለገለ እውነተኛ የስፖርት ሰው! 🙌
⚽️ የጎል ማሽኑ - ዮርዳኖስ ዓባይ! 🥅
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ካፈራቸው፣ መረብን ማራድ የዘወትር ተግባራቸው ከሆነ ምርጥ አጥቂዎች አንዱ!
ዮርዳኖስ ዓባይ በመብራት ኃይል (ኤሌክትሪክ) እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ባሳለፈው ጊዜ በግዙፍ ሰውነቱ፣ በአየር ላይ ኳስ አጠቃቀሙ እና በድንቅ የጨረስ አቅሙ ይታወሳል።
በተለይም ወደ የመን በማምራት በ አል ሳቅር ክለብ የሰራው ታሪክ እና የሰበራቸው የጎል ክብረወሰኖች ስሙን በውጭ ሀገር ጭምር ገናና አድርገውታል።
ከዓመታት በኋላ ይህንን "የጎል አዳኝ" ነገ እሁድ በአዲስ አበባ ስታዲየም በሚደረገው የናፍቆት ጨዋታ ላይ ልንመለከተው ነው።
⚽️ የሜዳው ታንክ - ፍቅሩ ተፈራ! 🇪🇹
በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ተክለ ሰውነቱ፣ ጉልበቱ እና አጨራረሱ ለየት ያለ ድንቅ አጥቂ!
ፍቅሩ ተፈራ (ሌሜሳ) ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች በውጭ ሀገር ፕሮፌሽናል ሊጎች ተፈላጊ እንዲሆኑ በር የከፈተ ፈር ቀዳጅ ነው። ከቅዱስ ጊዮርጊስ ተነስቶ በደቡብ አፍሪካው ታላቅ ክለብ ኦርላንዶ ፓይሬትስ እና ሱፐር ስፖርት ዩናይትድ ያሳየው ብቃት አይረሳም።
በተለይም በሕንድ ሱፐር ሊግ (ISL) ታሪክ የመጀመሪያውን ጎል ለአትሌቲኮ ደ ኮልካታ በማስቆጠር ስሙን በታሪክ መዝገብ ላይ አሰፍሯል። የተከላካዮችን ጥንካሬ የሚፈትነው ጉልበቱ እና አልፎ አልፎ የሚያስቆጥራቸው "አክሮባቲክ" ጎሎች የፍቅሩ መለያዎች ናቸው።
ለኢትዮጵያ እግር ኳስ በዓለም አቀፍ መድረክ ተጠሪ ለነበረው ለዚህ ጀግና ክብር ይገባዋል! 🙌
#fikrutefera #ethiopianlegend #orlandopirates #isl #historymaker #waliyas #shimelisbekele #ethiopianfootball #waliyas #legend #playmaker #sport #football #ethiopia #legendsgame #addisababa #ashenafigirma #saintgeorgefc #ethiopianfootball #legend #defender #waliyas #yordanosabay #goalmachine #ethiopianfootball #legend #waliyas #yemenleague
6 months ago
ላይት ኢንቨስትመንት ከፈረሰኞቹ ጋር አዲስ አጋርነት መሰረተ
#ethiopia | በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ፈርቀዳጅ የሆነው የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ (ፈረሰኞቹ) ከላይት ኢንቨስትመንትስ ኃ.የተ.የግ.ማህበር የኃይል ሰጪ መጠጥ ድርጅት ጋር ቢሾፍቱ በሚገኘው የክለቡ አካዳሚ ስምምነታቸውን በፊርማ አረጋግጠዋል።
ይህ ስምምነት ለአንድ አመት የሚቆይ ሲሆን በዋናነት ክለቡ ለሚያደርጋቸው ውድድሮች እና ልምምዶች የሚያስፈልገውን የኃይል ሰጪ መጠጥ አቅርቦት ላይ ያተኮረ እና፣ ለተጫዋቾቹ ብቃት መሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ታምኖበታል።
ድርጅቱ ለክለቡ ተጫዋቾች እና የቴክኒክ ቡድን አባላት በቂ የኃይል ሰጪ መጠጥ በቋሚነት ያቀርባል የተባለ ሲሆን በምላሹም የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ላይት ኢንቨስትመንት ኃ.የተ.የግ.ማህበርን ይፋዊ የኋይል ሰጪ አቅራቢ አድርግ ተቀብሏል።
መጠጡ ተጫዋቾች በጨዋታ ወቅት የሚያጡትን ኃይል በፍጥነት እንዲተኩ እና የትኩረት አቅማቸው እንዲጨምር ለማገዝ ታስቦ የቀረበ ነው።
የክለቡ አመራሮች በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት፣ እንዲህ ያሉ ትብብሮች ለኢትዮጵያ እግር ኳስ እድገት እና ለክለቦች አቅም መጎልበት ወሳኝ ናቸው ያሉ ሲሆን "ተጫዋቾቻችን በሜዳ ላይ የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ዘመናዊ የአቅርቦት ስርዓት መዘርጋት አለብን፤ ይህ ስምምነትም የዚሁ አካል ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
የኃይል ሰጪ መጠጥ አምራች ድርጅቱ በበኩሉ፣ በኢትዮጵያ ትልቅ ስም ካለው እና በርካታ ደጋፊ ካለው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ጋር መስራት ምርቱን ለተጠቃሚዎች ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርለት ገልጿል።
ይህ አዲስ ጥምረት በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን ግንኙነት ከማጠናከሩ ባለፈ፣ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ውስጥ ያሉ ሌሎች ክለቦችም መሰል ትብብሮች እንዲያደርጉ የሚያበረታታ እርምጃ ሆኖ ተመዝግቧል።
የላይት ኢንቨስትመንት ኃ.የተ.የግ.ማህበር የሚያመርተው የኋይል ሰጪ ኤሌክትሮ ላይት በውስጡ የቫይታሚን ሲ፣ ቫይታሚን ቢ እንዲሁም ግሉኮስን የያዘ ተበጥብጦ የሚጠጣ ሃይል ሰጪ ነው።
#ethiopia | በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ፈርቀዳጅ የሆነው የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ (ፈረሰኞቹ) ከላይት ኢንቨስትመንትስ ኃ.የተ.የግ.ማህበር የኃይል ሰጪ መጠጥ ድርጅት ጋር ቢሾፍቱ በሚገኘው የክለቡ አካዳሚ ስምምነታቸውን በፊርማ አረጋግጠዋል።
ይህ ስምምነት ለአንድ አመት የሚቆይ ሲሆን በዋናነት ክለቡ ለሚያደርጋቸው ውድድሮች እና ልምምዶች የሚያስፈልገውን የኃይል ሰጪ መጠጥ አቅርቦት ላይ ያተኮረ እና፣ ለተጫዋቾቹ ብቃት መሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ታምኖበታል።
ድርጅቱ ለክለቡ ተጫዋቾች እና የቴክኒክ ቡድን አባላት በቂ የኃይል ሰጪ መጠጥ በቋሚነት ያቀርባል የተባለ ሲሆን በምላሹም የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ላይት ኢንቨስትመንት ኃ.የተ.የግ.ማህበርን ይፋዊ የኋይል ሰጪ አቅራቢ አድርግ ተቀብሏል።
መጠጡ ተጫዋቾች በጨዋታ ወቅት የሚያጡትን ኃይል በፍጥነት እንዲተኩ እና የትኩረት አቅማቸው እንዲጨምር ለማገዝ ታስቦ የቀረበ ነው።
የክለቡ አመራሮች በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት፣ እንዲህ ያሉ ትብብሮች ለኢትዮጵያ እግር ኳስ እድገት እና ለክለቦች አቅም መጎልበት ወሳኝ ናቸው ያሉ ሲሆን "ተጫዋቾቻችን በሜዳ ላይ የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ዘመናዊ የአቅርቦት ስርዓት መዘርጋት አለብን፤ ይህ ስምምነትም የዚሁ አካል ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
የኃይል ሰጪ መጠጥ አምራች ድርጅቱ በበኩሉ፣ በኢትዮጵያ ትልቅ ስም ካለው እና በርካታ ደጋፊ ካለው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ጋር መስራት ምርቱን ለተጠቃሚዎች ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርለት ገልጿል።
ይህ አዲስ ጥምረት በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን ግንኙነት ከማጠናከሩ ባለፈ፣ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ውስጥ ያሉ ሌሎች ክለቦችም መሰል ትብብሮች እንዲያደርጉ የሚያበረታታ እርምጃ ሆኖ ተመዝግቧል።
የላይት ኢንቨስትመንት ኃ.የተ.የግ.ማህበር የሚያመርተው የኋይል ሰጪ ኤሌክትሮ ላይት በውስጡ የቫይታሚን ሲ፣ ቫይታሚን ቢ እንዲሁም ግሉኮስን የያዘ ተበጥብጦ የሚጠጣ ሃይል ሰጪ ነው።
7 months ago
ፈረሰኞቹ ወሳኝ ድል አሳክተዋል !
#ethiopia | በ ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባሕርዳር ከተማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 3ለ1 አሸንፈዋል።
የፈረሰኞቹን የማሸነፊያ ግቦች አቤል ያለው 2x እና አዲሱ አቱላ ሲያስቆጥሩ በረከት ጥጋቡ ለጣና ሞገዶቹ ከመረብ አሳርፏል።
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመጀመሪያ አራት የሊግ መርሐግብሮች ሶስቱን በአሸናፊነት መወጣት ችለዋል።
ባሕርዳር ከተማ ያለፉትን አራት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም በሶስቱ አቻ ሲለያይ በአንዱ ተሸንፏል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
6️⃣ ቅዱስ ጊዮርጊስ :- 9 ነጥብ
8️⃣ ባሕርዳር ከተማ :- 6 ነጥብ
ቀጣይ መርሐግብር ?
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ሀድያ ሆሳዕና
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከ ባሕርዳር ከተማ #ts #sport #gtmc
#ethiopia | በ ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባሕርዳር ከተማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 3ለ1 አሸንፈዋል።
የፈረሰኞቹን የማሸነፊያ ግቦች አቤል ያለው 2x እና አዲሱ አቱላ ሲያስቆጥሩ በረከት ጥጋቡ ለጣና ሞገዶቹ ከመረብ አሳርፏል።
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመጀመሪያ አራት የሊግ መርሐግብሮች ሶስቱን በአሸናፊነት መወጣት ችለዋል።
ባሕርዳር ከተማ ያለፉትን አራት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም በሶስቱ አቻ ሲለያይ በአንዱ ተሸንፏል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
6️⃣ ቅዱስ ጊዮርጊስ :- 9 ነጥብ
8️⃣ ባሕርዳር ከተማ :- 6 ነጥብ
ቀጣይ መርሐግብር ?
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ሀድያ ሆሳዕና
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከ ባሕርዳር ከተማ #ts #sport #gtmc
7 months ago
ሸገር ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ
#ethiopia | በ4ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሸገር ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በማሸነፍ የውድድር ዓመቱን የመጀመርያ ድል አግኝቷል።
በአዲስ አበባ ስቴዲየም በተደረገው ጨዋታ ያሬድ መኮንን የሸገር ከተማን የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።
የፕሪሚየር ሊጉ እንግዳ ሸገር ከተማ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አሳክቷል።
አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀራቸው ፈረሰኞቹ በውድድር ዓመቱ ለመጀመርያ ጊዜ የተሸነፉበትም ሆኗል።
በአንተነህ ሲሳይ
#ethiopia | በ4ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሸገር ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በማሸነፍ የውድድር ዓመቱን የመጀመርያ ድል አግኝቷል።
በአዲስ አበባ ስቴዲየም በተደረገው ጨዋታ ያሬድ መኮንን የሸገር ከተማን የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።
የፕሪሚየር ሊጉ እንግዳ ሸገር ከተማ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አሳክቷል።
አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀራቸው ፈረሰኞቹ በውድድር ዓመቱ ለመጀመርያ ጊዜ የተሸነፉበትም ሆኗል።
በአንተነህ ሲሳይ
Sponsored by
Surafel
Comments