2 days ago
እባካችሁ በኦቲዝም ስም አትነግዱ!
"ከወላጆች አይን እንባ በዝታለች፣ እግዚአብሄርም ያያል !"
( መላኩ ብርሃኑ)
ኢትዮጵያ ውስጥ ኦቲዝም "እጅግ በጣም ውድ" ችግር ነው፡፡ ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ የወላጅን ሸክም ለማቅለል የተዘረጋ ምንም አይነት ስርዓት ስለሌለ ኦቲዝም ወደአንድ ቤት ሲመጣ የዚያ ቤት ህይወት ከመሰረቱ ይናጋል።
ልጆቹ የሙሉ ጊዜ ጥበቃ ስለሚያስፈልጋቸው ወላጅ እየሰራ ከሆነ ስራውን፣ እየተማረ ከሆነም ትምህርቱን ለመተው ይገደዳል። ይህ ደግሞ ለኦኮኖሚ ጫና፣ ለስነልቡና ቀውስ፣ ለማህበራዊ ግንኙነት መዳከምና አልፎ ተርፎም ለከባድ የጤና ቀውስ ይዳርጋል።
እስኪ አስቡት !
ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ልጅ ኦቲዝም እንዳለበት ለመመርመር (Diagnose) ለማድረግ የላብሯቶሪ ወጪውን ሳይጨምር ለህክምና ባለሙያው ብቻ የሚከፈል እስከ 20 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ይደርሳል።
እስከ 25 ሺህ ብር የሚደርስ የሃገር ውስጥ ምርመራን እንተወውና እንደ yeast overgrowth, heavy metal test, OAT test, FRAT test ውጪ ልኮ ለማሰራት ከ100 -200 ሺህ ብር በላይ ይጠየቃል።
ኦቲዝም ያላቸው ልጆች ብዙውን ጊዜ ከአንጀታቸው ጋር የተያያዘ የጤና ችግር አለባቸው ተብሎ ስለሚታመን 'ግሉቲን እና ኬዚን' የሚባሉ ንጥረነገሮች ካሏቸው ምግቦች ነጻ መሆን አለባቸው። እኛ ሃገር ደግሞ “ግሉቲን ፍሪ፣ ኬዚን ፍሪ” የሚባሉት የምግብ አይነቶች በአቅርቦት ደረጃ ውስንና በጣም ውድ ናቸው።ከሰንዴ ዘርና ከወተት መራቅ አለባቸው።
ለነሱ የሚሆን ወተት ለመስራት የሚጠቅም አንድ ኪሎ 'አልመንድ' የሚባል ፍሬ በትንሹ እስከ 5 ሺህ ብር ያስወጣል። ምግባቸው ውድ በሆነው የንጹህ የወይራ ዘይት ካልሆነ በቀር በሌላ መሰራት አይችልም። ስኳርና ሰውሰራሽ ማጣፈጫ ስለማይጠቀሙ በምትኩ ቴምር ለመግዛት በኪሎ ከ1500-3500 ብር ድረስ ይጠይቃል።
በዚህ ሳቢያ ልጆቹ የሚወስዱት ምግብ አይነት ስለሚያንስ እንዳይጎዱ ሲባል 'ሰፕሊመንት' ያስፈልጋቸዋል። ለምሳሌ ለነሱ የሚሆን የአሳ ዘይት ዋጋው ከ 12 ሺህ እስከ 35ሺህ ብር ይሸጣል። ለጥቂት ቀን ብቻ የሚሆን ቫይታሚን ዲ ደግሞ እስከ 5 ሺህ ብር ይሸጣል። አቅም ላለው ወላጅ እንኳን ሌሎች ሌሎች ተጨምረው የሰፕሊመንት ዋጋ ብቻ በወር ከ50 ሺህ ብር በላይ ያስወጣዋል።
በአጠቃላይ ለአንድ ኦቲዝም ላለበት ልጅ የሚወጣው የአንድ ወር የምግብ ወጪ አንድ ቤት ውስጥ ለሙሉ ቤተሰብ ከሚወጣው የቀለብ ወጪ ይበልጣል።
ኦቲዝም በሽታ ስላልሆነ መድሃኒት የለውም፡፡ ለኦቲዝም የሚደረገው ድጋፍ በአብዛኛው የንግግር፣ የባህሪና የአካልና ሰውነት ቅንጅት ቴራፒ ነው፡፡ እዚህ ጋር ደግሞ ነጋዴዎቹ ተሰብስበዋል።
የሚችሉትም የማይችሉትም የሆነች ዛኒጋባ ተከራይተው እንሰጣለን ለሚሉት ተራፒ የሚያስከፍሉት ዋጋ በጣም ውድ ነው። ለአንድ ልጅ በወር 30 ሰዓት ቴራፒ ለመስጠት የሚከፈለው ገንዘብ የአንድ ልጅን የ6 ወር የግል ትምህርት ቤት ክፍያ ይበልጣል።
በቁጥር ጥቂት የሆኑት 'የልዩ ፍላጎት አካቶ' ያላቸው ትምህርት ቤቶች ክፍያ ዋጋ ደግሞ አይወራ። ታዋቂ ነን የሚሉት አንዳንዶቹ ትምህርት ቤቶች በወር እስከ 100 ሺህ ብር ያስከፍላሉ። በጨበጣ ያለምንም እውቀት ኦቲዝምን ቢዝነስ ያደረጉ አንዳንድ ነጋዴ ግለሰቦች የከፈቱት ትምህርት ቤት ደሞ አለ። አዳሪ ብለው እስከ 300ሺህ ብር በወር ያስከፍላሉ።
ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤቶች እንኳን የማያስከፍሉትን አይነት ገንዘብ የሚያስከፍሉ አካቶ ት/ቤቶችና በኦቲዝም ስም የተቋቋሙ ተቋማት በጣም ብዙ ናቸው፡፡
በዚህ ላይ ልጁ ትምህርት ቤት ሲሄድም ሆነ ሲመለስ ሰርቪስ የሚጠቀም ከሆነ ወላጆች ለመጓጓዣው ከመደበኞቹ ህጻናት በእጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ፡፡
ይህን ይህን ሳይ በሃገሬ ተስፋ እቆርጣለሁ። ስርዓት ያልተዘረጋለት፣ ደንብና ህግ ያልወጣለት፣ በሙስና ሰንሰለት የተጨማለቀ ፣ ከኤንጂኦ እስከ ግለሰቦች ድረስ በኦቲዝም ስም የጦፈ ንግድ ሲካሄድ ሃይ ባይ የታጣበት ሃገር ላይ ነን ያለነው።
እንደኔ ጠለቅ ብሎ ለሚያየው እዚህ ዘርፍ ላይ ያለው መጨመላለቅና ብዝበዛ በጣም ይሰቀጥጣል፡፡
መቼም በጥቂቱ ካነሳሁት እውነት አንጻር በዚህ ዘመን የኑሮ ውድነት አንድ ወላጅ ቤት ኦቲዝም ሲደረብበት በስነልቡናም፣ በገንዘብም ምን ያህል ከባድ የህይወት መርግ እንደሚፈጥር ካሰባችሁት ይበቃል፡፡
እናንት 'ሞራል አልባ' ነጋዴዎች! እንዲህ ባለ 'ውድ' ችግር ላይ አይናችሁን አጥባችሁ ገንዘብ ለማጋበስና መሄጃ አጥቶ የተቸገረውን ወላጅ ለመበዝበዝ እንዴት ህሊናችሁ እሺ አላችሁ ግን? (በርግጥ ህሊና የላችሁም!)
በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡ይህ'ኮ ኢሰብአዊነት ነው። ወንጀል ነው። የሞራል ዝቅጠት ነው። ዛሬ ከኔ ባልተሻለ ጥቂት ንባብ ብቻ ተነስታችሁ ቤት ተከራይታችሁና ማዕከል ከፍታችሁ ‘ባለሙያ ነን’ እያላችሁ 'ቢዝነስ' የምትሰሩ ፣ ቲክቶኩንና ሶሻል ሚዲያውን ያጣበባችሁ ሰዎች ... ምናችሁን ነው የሚያማችሁ? ነገ'ኮ ይህ በህጋዊነት ሽፋን ያለቁጥጥር በተለቀቀ ሜዳ ላይ ስትፋንኑ የበደላችሁት ወላጅ እንባ ቤታችሁ ድረስ ይመጣል።
ኦቲዝም ላይ እንሰራለን ብላችሁ የምትደሰኩሩ ሃኪሞችምም፣ ሳይኮሎጂስቶችም፣ ቴራፒስቶችም፣ አካቶ ትምህርት ቤቶችም፣ማዕከላትም ቆም ብላችሁ ብታስቡ ይበጃችኋል!
ይህ ምርጫ ያጣ… ተመልካች ያጣ፣ ልጄ ቢሻሻልልኝ ብሎ እዚህም እዚያም መፍትሄ ፍለጋ የሚኳትን ወላጅ በኦቲዝም ምክንያት ጥሪቱን አሟጦ ሌሎች ልጆቹን የሚያሳድግበትና ቤቱን የሚመራበት ገንዘብ እስኪያጣ ድረስ ሲቸገር እናንተ አላግባብ በዘረፋችሁት ገንዘብ ሰላም፣ ጤናና የሰላም እንጀራ አይኖራችሁም ።
አያሳዝናችሁም ግን ? በናንተ የዋጋ ውድነትና ሳቢያ አቅም አጥቶ ዕድሜውን ሙሉ ‘ለልጄ ይህንን ሳላደርግለት’ ብሎ በጸጸት እንባ የሚታጠብ ወላጅ ግን አያሳዝናችሁም?
በዚህ ወላጅ ላይ ህይወት ላይ እየተጫወታችሁ እስከመቼ ራሳችሁን ታበለጽጋላችሁ ?
አንድ ቀን ግን ይመጣል! አላግባብ ለምትሰበስቡት ትርፍ አንድ ቀን እግዚአብሄር ይፈርድባችኋል ! የወላጅ እንባ በቤታችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይመጣል። ያኔ እናንተም ቁጭ ብላችሁ ታለቅሳላችሁ !
(ማሳሰቢያ ፤ ይህ ጽሁፍ በሃቅ የሚሰሩ፣ ልጆቹንና ወላጆችን ለመርዳት የሚለፉትን ባለሙያዎች አይመለከትም)
ሜርድ!!
"ከወላጆች አይን እንባ በዝታለች፣ እግዚአብሄርም ያያል !"
( መላኩ ብርሃኑ)
ኢትዮጵያ ውስጥ ኦቲዝም "እጅግ በጣም ውድ" ችግር ነው፡፡ ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ የወላጅን ሸክም ለማቅለል የተዘረጋ ምንም አይነት ስርዓት ስለሌለ ኦቲዝም ወደአንድ ቤት ሲመጣ የዚያ ቤት ህይወት ከመሰረቱ ይናጋል።
ልጆቹ የሙሉ ጊዜ ጥበቃ ስለሚያስፈልጋቸው ወላጅ እየሰራ ከሆነ ስራውን፣ እየተማረ ከሆነም ትምህርቱን ለመተው ይገደዳል። ይህ ደግሞ ለኦኮኖሚ ጫና፣ ለስነልቡና ቀውስ፣ ለማህበራዊ ግንኙነት መዳከምና አልፎ ተርፎም ለከባድ የጤና ቀውስ ይዳርጋል።
እስኪ አስቡት !
ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ልጅ ኦቲዝም እንዳለበት ለመመርመር (Diagnose) ለማድረግ የላብሯቶሪ ወጪውን ሳይጨምር ለህክምና ባለሙያው ብቻ የሚከፈል እስከ 20 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ይደርሳል።
እስከ 25 ሺህ ብር የሚደርስ የሃገር ውስጥ ምርመራን እንተወውና እንደ yeast overgrowth, heavy metal test, OAT test, FRAT test ውጪ ልኮ ለማሰራት ከ100 -200 ሺህ ብር በላይ ይጠየቃል።
ኦቲዝም ያላቸው ልጆች ብዙውን ጊዜ ከአንጀታቸው ጋር የተያያዘ የጤና ችግር አለባቸው ተብሎ ስለሚታመን 'ግሉቲን እና ኬዚን' የሚባሉ ንጥረነገሮች ካሏቸው ምግቦች ነጻ መሆን አለባቸው። እኛ ሃገር ደግሞ “ግሉቲን ፍሪ፣ ኬዚን ፍሪ” የሚባሉት የምግብ አይነቶች በአቅርቦት ደረጃ ውስንና በጣም ውድ ናቸው።ከሰንዴ ዘርና ከወተት መራቅ አለባቸው።
ለነሱ የሚሆን ወተት ለመስራት የሚጠቅም አንድ ኪሎ 'አልመንድ' የሚባል ፍሬ በትንሹ እስከ 5 ሺህ ብር ያስወጣል። ምግባቸው ውድ በሆነው የንጹህ የወይራ ዘይት ካልሆነ በቀር በሌላ መሰራት አይችልም። ስኳርና ሰውሰራሽ ማጣፈጫ ስለማይጠቀሙ በምትኩ ቴምር ለመግዛት በኪሎ ከ1500-3500 ብር ድረስ ይጠይቃል።
በዚህ ሳቢያ ልጆቹ የሚወስዱት ምግብ አይነት ስለሚያንስ እንዳይጎዱ ሲባል 'ሰፕሊመንት' ያስፈልጋቸዋል። ለምሳሌ ለነሱ የሚሆን የአሳ ዘይት ዋጋው ከ 12 ሺህ እስከ 35ሺህ ብር ይሸጣል። ለጥቂት ቀን ብቻ የሚሆን ቫይታሚን ዲ ደግሞ እስከ 5 ሺህ ብር ይሸጣል። አቅም ላለው ወላጅ እንኳን ሌሎች ሌሎች ተጨምረው የሰፕሊመንት ዋጋ ብቻ በወር ከ50 ሺህ ብር በላይ ያስወጣዋል።
በአጠቃላይ ለአንድ ኦቲዝም ላለበት ልጅ የሚወጣው የአንድ ወር የምግብ ወጪ አንድ ቤት ውስጥ ለሙሉ ቤተሰብ ከሚወጣው የቀለብ ወጪ ይበልጣል።
ኦቲዝም በሽታ ስላልሆነ መድሃኒት የለውም፡፡ ለኦቲዝም የሚደረገው ድጋፍ በአብዛኛው የንግግር፣ የባህሪና የአካልና ሰውነት ቅንጅት ቴራፒ ነው፡፡ እዚህ ጋር ደግሞ ነጋዴዎቹ ተሰብስበዋል።
የሚችሉትም የማይችሉትም የሆነች ዛኒጋባ ተከራይተው እንሰጣለን ለሚሉት ተራፒ የሚያስከፍሉት ዋጋ በጣም ውድ ነው። ለአንድ ልጅ በወር 30 ሰዓት ቴራፒ ለመስጠት የሚከፈለው ገንዘብ የአንድ ልጅን የ6 ወር የግል ትምህርት ቤት ክፍያ ይበልጣል።
በቁጥር ጥቂት የሆኑት 'የልዩ ፍላጎት አካቶ' ያላቸው ትምህርት ቤቶች ክፍያ ዋጋ ደግሞ አይወራ። ታዋቂ ነን የሚሉት አንዳንዶቹ ትምህርት ቤቶች በወር እስከ 100 ሺህ ብር ያስከፍላሉ። በጨበጣ ያለምንም እውቀት ኦቲዝምን ቢዝነስ ያደረጉ አንዳንድ ነጋዴ ግለሰቦች የከፈቱት ትምህርት ቤት ደሞ አለ። አዳሪ ብለው እስከ 300ሺህ ብር በወር ያስከፍላሉ።
ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤቶች እንኳን የማያስከፍሉትን አይነት ገንዘብ የሚያስከፍሉ አካቶ ት/ቤቶችና በኦቲዝም ስም የተቋቋሙ ተቋማት በጣም ብዙ ናቸው፡፡
በዚህ ላይ ልጁ ትምህርት ቤት ሲሄድም ሆነ ሲመለስ ሰርቪስ የሚጠቀም ከሆነ ወላጆች ለመጓጓዣው ከመደበኞቹ ህጻናት በእጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ፡፡
ይህን ይህን ሳይ በሃገሬ ተስፋ እቆርጣለሁ። ስርዓት ያልተዘረጋለት፣ ደንብና ህግ ያልወጣለት፣ በሙስና ሰንሰለት የተጨማለቀ ፣ ከኤንጂኦ እስከ ግለሰቦች ድረስ በኦቲዝም ስም የጦፈ ንግድ ሲካሄድ ሃይ ባይ የታጣበት ሃገር ላይ ነን ያለነው።
እንደኔ ጠለቅ ብሎ ለሚያየው እዚህ ዘርፍ ላይ ያለው መጨመላለቅና ብዝበዛ በጣም ይሰቀጥጣል፡፡
መቼም በጥቂቱ ካነሳሁት እውነት አንጻር በዚህ ዘመን የኑሮ ውድነት አንድ ወላጅ ቤት ኦቲዝም ሲደረብበት በስነልቡናም፣ በገንዘብም ምን ያህል ከባድ የህይወት መርግ እንደሚፈጥር ካሰባችሁት ይበቃል፡፡
እናንት 'ሞራል አልባ' ነጋዴዎች! እንዲህ ባለ 'ውድ' ችግር ላይ አይናችሁን አጥባችሁ ገንዘብ ለማጋበስና መሄጃ አጥቶ የተቸገረውን ወላጅ ለመበዝበዝ እንዴት ህሊናችሁ እሺ አላችሁ ግን? (በርግጥ ህሊና የላችሁም!)
በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡ይህ'ኮ ኢሰብአዊነት ነው። ወንጀል ነው። የሞራል ዝቅጠት ነው። ዛሬ ከኔ ባልተሻለ ጥቂት ንባብ ብቻ ተነስታችሁ ቤት ተከራይታችሁና ማዕከል ከፍታችሁ ‘ባለሙያ ነን’ እያላችሁ 'ቢዝነስ' የምትሰሩ ፣ ቲክቶኩንና ሶሻል ሚዲያውን ያጣበባችሁ ሰዎች ... ምናችሁን ነው የሚያማችሁ? ነገ'ኮ ይህ በህጋዊነት ሽፋን ያለቁጥጥር በተለቀቀ ሜዳ ላይ ስትፋንኑ የበደላችሁት ወላጅ እንባ ቤታችሁ ድረስ ይመጣል።
ኦቲዝም ላይ እንሰራለን ብላችሁ የምትደሰኩሩ ሃኪሞችምም፣ ሳይኮሎጂስቶችም፣ ቴራፒስቶችም፣ አካቶ ትምህርት ቤቶችም፣ማዕከላትም ቆም ብላችሁ ብታስቡ ይበጃችኋል!
ይህ ምርጫ ያጣ… ተመልካች ያጣ፣ ልጄ ቢሻሻልልኝ ብሎ እዚህም እዚያም መፍትሄ ፍለጋ የሚኳትን ወላጅ በኦቲዝም ምክንያት ጥሪቱን አሟጦ ሌሎች ልጆቹን የሚያሳድግበትና ቤቱን የሚመራበት ገንዘብ እስኪያጣ ድረስ ሲቸገር እናንተ አላግባብ በዘረፋችሁት ገንዘብ ሰላም፣ ጤናና የሰላም እንጀራ አይኖራችሁም ።
አያሳዝናችሁም ግን ? በናንተ የዋጋ ውድነትና ሳቢያ አቅም አጥቶ ዕድሜውን ሙሉ ‘ለልጄ ይህንን ሳላደርግለት’ ብሎ በጸጸት እንባ የሚታጠብ ወላጅ ግን አያሳዝናችሁም?
በዚህ ወላጅ ላይ ህይወት ላይ እየተጫወታችሁ እስከመቼ ራሳችሁን ታበለጽጋላችሁ ?
አንድ ቀን ግን ይመጣል! አላግባብ ለምትሰበስቡት ትርፍ አንድ ቀን እግዚአብሄር ይፈርድባችኋል ! የወላጅ እንባ በቤታችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይመጣል። ያኔ እናንተም ቁጭ ብላችሁ ታለቅሳላችሁ !
(ማሳሰቢያ ፤ ይህ ጽሁፍ በሃቅ የሚሰሩ፣ ልጆቹንና ወላጆችን ለመርዳት የሚለፉትን ባለሙያዎች አይመለከትም)
ሜርድ!!
3 days ago
የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ
#fastmereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች" ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
"የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን" ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው 'አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ' አወድሶታል።
"የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን" ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441' የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
"የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም" ያሉት አቶ አምሳሉ፣ "ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው" በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት 'የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር' ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ "ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው" ብለዋል።
በግዛቲቱ 'መጋቢት 2፣ 2026 'ለ130ኛው የዓድዋ በዓል' መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
'መጋቢት 2' የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ 'የአድዋ ቀን' ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው' ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
#fastmereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች" ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
"የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን" ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው 'አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ' አወድሶታል።
"የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን" ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441' የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
"የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም" ያሉት አቶ አምሳሉ፣ "ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው" በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት 'የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር' ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ "ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው" ብለዋል።
በግዛቲቱ 'መጋቢት 2፣ 2026 'ለ130ኛው የዓድዋ በዓል' መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
'መጋቢት 2' የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ 'የአድዋ ቀን' ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው' ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በምርምር እና በስትራቴጂያዊ ትንተና የተደገፈ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ለንባብ ሊቀርብ መሆኑ ተገለጸ።
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው ሲሆኑ፣ ደራሲው በአማራና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳዮች ትንታኔዎችን በማቅረብ የሚታወቁ ነባር ፖለቲከኛ ናቸው፡፡
ዶክተር ቹቹ በአዲሱ ሥራቸው በተከዜ ተፋሰስ እና በወልቃይት-ጠገዴ፣ ጠለምት ቀጠና ዙሪያ የሚታዩ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊ፣ ማኅበራዊ እና የደኅንነት ጉዳዮችን በምሁራዊ መንገድ የሚተነትን መሆኑ ተጠቁሟል።
ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተከዜ ተፋሰስ የውኃ ምንጭ ወይም የተፈጥሮ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ከቀጠናዊ የኃይል ሚዛን፣ ከሕዝቦች ማንነት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ስትራቴጂያዊ ቀጠና ነው። መጽሐፉም ይህንን አቀራረብ በመነሻ በማድረግ የአካባቢውን ፖለቲካዊ እውነታ በጂኦ-ፖለቲካ፣ በኃይል፣ በማንነት እና በብሔራዊ ደኅንነት ማዕቀፎች አንጻር ይመረምራል።
መጽሐፉ በተለይ በ2013 ዓ.ም. በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ጦርነት እንደ መነሻ በመውሰድ፣ የተከዜ ተፋሰስ በሀገሪቱ የደኅንነት አወቃቀር ውስጥ ያለውን ስልታዊ ሚና በዝርዝር ያስረዳል። ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተፋሰሱን ይዞታ መቆጣጠር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት፣ በውኃ ሀብት አስተዳደር እና በቀጠናዊ ግንኙነቶች ላይ ወሳኝ ተፅዕኖ ያሳድራል።
በአጠቃላይ 20 ምዕራፎችን ያካተተው መጽሐፉ በአራት ዋና ክፍሎች ተዋቅሯል።
የመጀመሪያው ክፍል በጂኦ-ፖለቲካ ላይ ያተኩራል፤ የተከዜ ተፋሰስ ከኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ፖለቲካ እና ከቀጠናዊ የኃይል አሰላለፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ይተነትናል።
ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ኃይልን እንደ ፖለቲካዊ መሣሪያ በመመልከት፣ አካባቢውን መቆጣጠር ለባለቤቱ የሚሰጠውን ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ተምሳሌታዊ ጥቅሞች ያብራራል። እንደ መጽሐፉ ገለጻ፣ ተከዜ ተራ የመሬት ክፍል ሳይሆን የተለያዩ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች የሚገናኙበት የኃይል መድረክ ነው።
ሦስተኛው ክፍል በማንነት ፖለቲካ ላይ ያተኩራል። በዚህ ክፍል የብሔር ፌዴራሊዝም፣ የሥነ-ሕዝብ ለውጦች፣ የነባር እና የመጤ ትርክቶች እንዲሁም የማንነት ጥያቄዎች በታሪካዊ እና በንድፈ-ሐሳባዊ መሠረቶች ይመረመራሉ።
ደራሲው በወልቃይት፣ በጠገዴ እና በጠለምት አካባቢዎች የተፈጠሩ የማንነት ግጭቶችን እና የሕዝብ አወቃቀር ለውጦችን በሕጋዊ እና በታሪካዊ ማስረጃዎች ተደግፈው መቅረባቸውን ያስረዳሉ።
አራተኛው እና የመጨረሻው ክፍል የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳዮችን ያዳስሳል። ይህ ክፍል የውኃ ደኅንነት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፣ የውጭ ስጋቶች፣ የፌዴራላዊ አንድነት ተግዳሮቶች እና የሰላም ግንባታ አማራጮችን በስፋት ይተነትናል።
በመጨረሻም ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች የሚጠቅሙ የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን ያቀርባል።ከይዘቱ ባሻገር መጽሐፉ የተለያዩ የአገር ውስጥ፣ የቀጠና እና የዓለም አቀፍ ተዋናዮችን ሚና በጥልቀት የሚያብራራ መሆኑ ተገልጿል። የፌዴራል መንግሥት፣ የክልል ፖለቲካ ኃይሎች፣ ጎረቤት አገራት እና በቀጠናው ፍላጎት ያላቸው ዓለም አቀፍ ኃይሎች በተከዜ ፖለቲካ ላይ የሚኖራቸው ተፅዕኖ በተለየ ትኩረት ቀርቧል።
ደራሲው መጽሐፉ ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለታሪክ ተመራማሪዎች፣ ለደኅንነት ባለሙያዎች፣ ለዲፕሎማቶች እና ለከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ጠቃሚ የማጣቀሻ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።
የመጽሐፉ ዋና ዓላማም በተከዜ ተፋሰስ ዙሪያ ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን በምሁራዊ እይታ በማቅረብ፣ ለዘላቂ ሰላም፣ ለአገራዊ አንድነት እና ለጋራ ልማት የሚረዱ የፖሊሲ አማራጮችን ማበርከት መሆኑ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ በከፍተኛ የቋንቋ ደረጃ እና በምሁራዊ ጥልቀት የተጻፈ ነው የተባለለት ሲሆን፤ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ትንተናዎች ከታሪካዊ እውነታዎች ጋር ይበልጥ የተሰናሰሉ፣ መሆኑ ሥራው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው እንዳረጋገጡት፣ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘው መጽሐፋቸው የፊታችን ዕረቡ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በገበያ ላይ ይውላል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው ሲሆኑ፣ ደራሲው በአማራና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳዮች ትንታኔዎችን በማቅረብ የሚታወቁ ነባር ፖለቲከኛ ናቸው፡፡
ዶክተር ቹቹ በአዲሱ ሥራቸው በተከዜ ተፋሰስ እና በወልቃይት-ጠገዴ፣ ጠለምት ቀጠና ዙሪያ የሚታዩ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊ፣ ማኅበራዊ እና የደኅንነት ጉዳዮችን በምሁራዊ መንገድ የሚተነትን መሆኑ ተጠቁሟል።
ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተከዜ ተፋሰስ የውኃ ምንጭ ወይም የተፈጥሮ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ከቀጠናዊ የኃይል ሚዛን፣ ከሕዝቦች ማንነት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ስትራቴጂያዊ ቀጠና ነው። መጽሐፉም ይህንን አቀራረብ በመነሻ በማድረግ የአካባቢውን ፖለቲካዊ እውነታ በጂኦ-ፖለቲካ፣ በኃይል፣ በማንነት እና በብሔራዊ ደኅንነት ማዕቀፎች አንጻር ይመረምራል።
መጽሐፉ በተለይ በ2013 ዓ.ም. በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ጦርነት እንደ መነሻ በመውሰድ፣ የተከዜ ተፋሰስ በሀገሪቱ የደኅንነት አወቃቀር ውስጥ ያለውን ስልታዊ ሚና በዝርዝር ያስረዳል። ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተፋሰሱን ይዞታ መቆጣጠር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት፣ በውኃ ሀብት አስተዳደር እና በቀጠናዊ ግንኙነቶች ላይ ወሳኝ ተፅዕኖ ያሳድራል።
በአጠቃላይ 20 ምዕራፎችን ያካተተው መጽሐፉ በአራት ዋና ክፍሎች ተዋቅሯል።
የመጀመሪያው ክፍል በጂኦ-ፖለቲካ ላይ ያተኩራል፤ የተከዜ ተፋሰስ ከኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ፖለቲካ እና ከቀጠናዊ የኃይል አሰላለፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ይተነትናል።
ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ኃይልን እንደ ፖለቲካዊ መሣሪያ በመመልከት፣ አካባቢውን መቆጣጠር ለባለቤቱ የሚሰጠውን ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ተምሳሌታዊ ጥቅሞች ያብራራል። እንደ መጽሐፉ ገለጻ፣ ተከዜ ተራ የመሬት ክፍል ሳይሆን የተለያዩ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች የሚገናኙበት የኃይል መድረክ ነው።
ሦስተኛው ክፍል በማንነት ፖለቲካ ላይ ያተኩራል። በዚህ ክፍል የብሔር ፌዴራሊዝም፣ የሥነ-ሕዝብ ለውጦች፣ የነባር እና የመጤ ትርክቶች እንዲሁም የማንነት ጥያቄዎች በታሪካዊ እና በንድፈ-ሐሳባዊ መሠረቶች ይመረመራሉ።
ደራሲው በወልቃይት፣ በጠገዴ እና በጠለምት አካባቢዎች የተፈጠሩ የማንነት ግጭቶችን እና የሕዝብ አወቃቀር ለውጦችን በሕጋዊ እና በታሪካዊ ማስረጃዎች ተደግፈው መቅረባቸውን ያስረዳሉ።
አራተኛው እና የመጨረሻው ክፍል የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳዮችን ያዳስሳል። ይህ ክፍል የውኃ ደኅንነት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፣ የውጭ ስጋቶች፣ የፌዴራላዊ አንድነት ተግዳሮቶች እና የሰላም ግንባታ አማራጮችን በስፋት ይተነትናል።
በመጨረሻም ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች የሚጠቅሙ የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን ያቀርባል።ከይዘቱ ባሻገር መጽሐፉ የተለያዩ የአገር ውስጥ፣ የቀጠና እና የዓለም አቀፍ ተዋናዮችን ሚና በጥልቀት የሚያብራራ መሆኑ ተገልጿል። የፌዴራል መንግሥት፣ የክልል ፖለቲካ ኃይሎች፣ ጎረቤት አገራት እና በቀጠናው ፍላጎት ያላቸው ዓለም አቀፍ ኃይሎች በተከዜ ፖለቲካ ላይ የሚኖራቸው ተፅዕኖ በተለየ ትኩረት ቀርቧል።
ደራሲው መጽሐፉ ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለታሪክ ተመራማሪዎች፣ ለደኅንነት ባለሙያዎች፣ ለዲፕሎማቶች እና ለከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ጠቃሚ የማጣቀሻ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።
የመጽሐፉ ዋና ዓላማም በተከዜ ተፋሰስ ዙሪያ ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን በምሁራዊ እይታ በማቅረብ፣ ለዘላቂ ሰላም፣ ለአገራዊ አንድነት እና ለጋራ ልማት የሚረዱ የፖሊሲ አማራጮችን ማበርከት መሆኑ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ በከፍተኛ የቋንቋ ደረጃ እና በምሁራዊ ጥልቀት የተጻፈ ነው የተባለለት ሲሆን፤ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ትንተናዎች ከታሪካዊ እውነታዎች ጋር ይበልጥ የተሰናሰሉ፣ መሆኑ ሥራው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው እንዳረጋገጡት፣ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘው መጽሐፋቸው የፊታችን ዕረቡ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በገበያ ላይ ይውላል፡፡
6 days ago
በኢትዮጵያውያን ዲያስፖራ ላይ ያተኮረ መጽሐፍ ተመረቀ።
በአይናለም አዱኛ (ዶ/ር) የተጻፈውና በኢትዮጵያውያን ዲያስፖራ ላይ ትኩረቱን ያደረገው "Walking Between Worlds: Letter to the Next Generation of the Ethiopian Diaspora" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል።
በትናንትናው ዕለት በአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ሲመረቅም የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ፣የአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶር ሳሙኤል ክፍሌን ጨምሮ ምሑራን ዲያስፖራዎችና በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ስለኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ በምሁራንና በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
በአሜሪካ ሀገር ካሊፎርንያ ግዛት ኑሯቸውን ያደረጉት ዓይናለም አዱኛ(ዶ/ር) ከ38 ዓመታት በላይ ኖረዋል።
መጽሐፉ በውጭ የውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ልጆቻቸው ስለሀገራቸው እንዲያውቁ እና የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ የሚያደርግ ነው ብለዋል።
በውጭ ሀገር የነበራቸውን የረጅም ጊዜ ልምድና ገጠመኝ በመነሳት እንደጻፉትና ለሌሎች ዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን አስተማሪ ታሪኮችን የያዘ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ በዚህ ወቅት እንዳሉትም በርካታ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ሀገራት እንደሚኖሩ ገልጸው በሀገራቸው ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት እየተሳተፉ ይገኛል።
ዶር ዓይናለም አዱኛ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ምሳሌ የሚሆን ተግባር መስራታቸውን በመግለጽ ይህ በጎ ተግባር መቀጠል አለብ ብለዋል።
መጽሐፉ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ለንባብ የበቃ ሲሆን 480 ገጽ ያለው ነው።
በአይናለም አዱኛ (ዶ/ር) የተጻፈውና በኢትዮጵያውያን ዲያስፖራ ላይ ትኩረቱን ያደረገው "Walking Between Worlds: Letter to the Next Generation of the Ethiopian Diaspora" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል።
በትናንትናው ዕለት በአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ሲመረቅም የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ፣የአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶር ሳሙኤል ክፍሌን ጨምሮ ምሑራን ዲያስፖራዎችና በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ስለኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ በምሁራንና በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
በአሜሪካ ሀገር ካሊፎርንያ ግዛት ኑሯቸውን ያደረጉት ዓይናለም አዱኛ(ዶ/ር) ከ38 ዓመታት በላይ ኖረዋል።
መጽሐፉ በውጭ የውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ልጆቻቸው ስለሀገራቸው እንዲያውቁ እና የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ የሚያደርግ ነው ብለዋል።
በውጭ ሀገር የነበራቸውን የረጅም ጊዜ ልምድና ገጠመኝ በመነሳት እንደጻፉትና ለሌሎች ዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን አስተማሪ ታሪኮችን የያዘ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ በዚህ ወቅት እንዳሉትም በርካታ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ሀገራት እንደሚኖሩ ገልጸው በሀገራቸው ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት እየተሳተፉ ይገኛል።
ዶር ዓይናለም አዱኛ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ምሳሌ የሚሆን ተግባር መስራታቸውን በመግለጽ ይህ በጎ ተግባር መቀጠል አለብ ብለዋል።
መጽሐፉ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ለንባብ የበቃ ሲሆን 480 ገጽ ያለው ነው።
6 days ago
በኢትዮጵያውያን ዲያስፖራ የሕይወት ተሞክሮ ላይ የሚያተኩር አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቃ
#ethiopia | በአይናለም አዱኛ (ዶክተር) የተሰናዳውና በውጭ አገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሕይወትና ተግዳሮቶች ላይ የሚያጠነጥነው "Walking Between Worlds: Letter to the Next Generation of the Ethiopian Diaspora" የተሰኘው መጽሐፍ በይፋ ተመርቋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትናንት በተከናወነው የገበያ ማቅረቢያ ሥነ ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ፣ ታዋቂ ምሁራን፣ ዳያስፖራዎችና በርካታ የክብር እንግዶች ታድመዋል።
በዕለቱም በምሁራንና በተሳታፊዎች አማካኝነት ስለ ዲያስፖራው ማኅበረሰብ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
ለአምስት አሥርት ዓመታት ገደማ (ከ38 ዓመታት በላይ) በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት የኖሩት ደራሲዋ ዶክተር ዓይናለም አዱኛ፣ መጽሐፉ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ትውልደ ኢትዮጵያውያን ልጆቻቸው ስለ አገራቸው በቂ ዕውቀት እንዲኖራቸውና የሚጠበቅባቸውን አገራዊ ኃላፊነት እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
በስደት ዓለም ያሳለፉትን የረጅም ጊዜ የሕይወት ተሞክሮና ገጠመኝ መሠረት በማድረግ ያዘጋጁት ይህ መጽሐፍ ለሌሎች ወገኖች ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ መሆኑንም አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ በበኩላቸው በዓለም ዙሪያ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በንቃት እየተሳተፉ እንደሚገኙ ጠቁመው፣ ዶክተር ዓይናለም ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን በጎ ተግባር ማከናወናቸውንና እንዲህ ዓይነቱ አበረታች ሥራ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።
በእንግሊዘኛ ቋንቋ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ ባለ 480 ገጽ ሆኖ ለንባብ መብቃቱ ታውቋል።
#diaspora #ethiopiandiaspora #booklaunch #aau #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአይናለም አዱኛ (ዶክተር) የተሰናዳውና በውጭ አገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሕይወትና ተግዳሮቶች ላይ የሚያጠነጥነው "Walking Between Worlds: Letter to the Next Generation of the Ethiopian Diaspora" የተሰኘው መጽሐፍ በይፋ ተመርቋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትናንት በተከናወነው የገበያ ማቅረቢያ ሥነ ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ፣ ታዋቂ ምሁራን፣ ዳያስፖራዎችና በርካታ የክብር እንግዶች ታድመዋል።
በዕለቱም በምሁራንና በተሳታፊዎች አማካኝነት ስለ ዲያስፖራው ማኅበረሰብ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
ለአምስት አሥርት ዓመታት ገደማ (ከ38 ዓመታት በላይ) በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት የኖሩት ደራሲዋ ዶክተር ዓይናለም አዱኛ፣ መጽሐፉ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ትውልደ ኢትዮጵያውያን ልጆቻቸው ስለ አገራቸው በቂ ዕውቀት እንዲኖራቸውና የሚጠበቅባቸውን አገራዊ ኃላፊነት እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
በስደት ዓለም ያሳለፉትን የረጅም ጊዜ የሕይወት ተሞክሮና ገጠመኝ መሠረት በማድረግ ያዘጋጁት ይህ መጽሐፍ ለሌሎች ወገኖች ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ መሆኑንም አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ በበኩላቸው በዓለም ዙሪያ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በንቃት እየተሳተፉ እንደሚገኙ ጠቁመው፣ ዶክተር ዓይናለም ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን በጎ ተግባር ማከናወናቸውንና እንዲህ ዓይነቱ አበረታች ሥራ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።
በእንግሊዘኛ ቋንቋ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ ባለ 480 ገጽ ሆኖ ለንባብ መብቃቱ ታውቋል።
#diaspora #ethiopiandiaspora #booklaunch #aau #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
7 days ago
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያዘጋጀው 18ኛው የመጻሕፍት ኤግዚቢሽን በይፋ መካሄድ ጀመረ
#ethiopia | ታላቅ የዕውቀት እና የባህል መድረክ የሆነው ባለታሪኩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በድምቀት መካሄዱን ቀጥሏል።
በዝግጅቱ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ባደረጉት ንግግር ተቋሙ ላለፉት አሥር ዓመታት ለንባብ ባህል ማደግና ለመጻሕፍት ስርጭት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ሲሠራ መቆየቱን ጠቁመው፣ የዚህን ዓውደ ርዕይ ቀጣይነት በላቀ ሁኔታ ማስጠበቅና ይበልጥ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲው ፕረስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶክተር ደርብ አዶ በበኩላቸው ዝግጅቱ በየጊዜው በይዘቱም ሆነ በተሳታፊዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን በዝርዝር አብራርተዋል።
በዚህ ታላቅ የዕውቀት መድረክ ላይ ከ45 በላይ የሚሆኑ መጽሐፍት አከፋፋዮች፣ ዋና ዋና አሳታሚዎችና ታዋቂ የመጽሐፍት መደብሮች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው መጻሕፍት ከ20 እስከ 50 በመቶ በሚደርስ ትልቅ ቅናሽ ለጎብኚዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
ከሽያጭና ከግዢ ስምምነቶች ባሻገርም የአዳዲስ መጻሕፍት ምረቃ ሥነ ሥርዓቶች፣ አንጋፋ ደራሲያንና ምሁራን ለወጣቱ ትውልድ ጠቃሚ ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉባቸው የውይይት መድረኮች እንዲሁም የሕፃናትን የንባብ ልማድ የሚያበረታቱ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች በዓውደ ርዕዩ ቀናት ውስጥ የሚጠበቁ ማራኪ መርሃግብሮች መሆናቸው ታውቋል።
#aaubookfair2018 #ethiopianliterature #readtolead #addisababauniversity #bookfair #ethiopia #ንባብለህይወት #የመጽሐፍትዓውደር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ታላቅ የዕውቀት እና የባህል መድረክ የሆነው ባለታሪኩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በድምቀት መካሄዱን ቀጥሏል።
በዝግጅቱ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ባደረጉት ንግግር ተቋሙ ላለፉት አሥር ዓመታት ለንባብ ባህል ማደግና ለመጻሕፍት ስርጭት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ሲሠራ መቆየቱን ጠቁመው፣ የዚህን ዓውደ ርዕይ ቀጣይነት በላቀ ሁኔታ ማስጠበቅና ይበልጥ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲው ፕረስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶክተር ደርብ አዶ በበኩላቸው ዝግጅቱ በየጊዜው በይዘቱም ሆነ በተሳታፊዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን በዝርዝር አብራርተዋል።
በዚህ ታላቅ የዕውቀት መድረክ ላይ ከ45 በላይ የሚሆኑ መጽሐፍት አከፋፋዮች፣ ዋና ዋና አሳታሚዎችና ታዋቂ የመጽሐፍት መደብሮች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው መጻሕፍት ከ20 እስከ 50 በመቶ በሚደርስ ትልቅ ቅናሽ ለጎብኚዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
ከሽያጭና ከግዢ ስምምነቶች ባሻገርም የአዳዲስ መጻሕፍት ምረቃ ሥነ ሥርዓቶች፣ አንጋፋ ደራሲያንና ምሁራን ለወጣቱ ትውልድ ጠቃሚ ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉባቸው የውይይት መድረኮች እንዲሁም የሕፃናትን የንባብ ልማድ የሚያበረታቱ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች በዓውደ ርዕዩ ቀናት ውስጥ የሚጠበቁ ማራኪ መርሃግብሮች መሆናቸው ታውቋል።
#aaubookfair2018 #ethiopianliterature #readtolead #addisababauniversity #bookfair #ethiopia #ንባብለህይወት #የመጽሐፍትዓውደር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
7 days ago
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ተጀመረ
*******************
ትልቅ የዕውቀት እና የባህል መድረክ የሆነው 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በድምቀት ይካሄዳል።
ዩኒቨርስቲው 10 ዓመታትን በተሻገሩት ጊዜያት ለንባብና ለመፃህፍት ትልቅ ትኩረት በመስጠት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ዩኒቨርስቲው የአውደርዕዩን ቀጣይነት ማስጠበቅና ለውጡ የፈጠረውን እድል ተጠቅሞ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
በአውደ ርዕዩ ከ45 በላይ መጽሐፍት አከፋፋዮች፣ አሳታሚዎችና የመጽሐፍት መደብሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው መጽሐፍት ለጎብኚዎች እንደቀረቡም ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕረስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶ/ር ደርብ አዶ አውደ ርዕዩ ከዘመኑ ጋር እያደገ በስፋትም በተሳታፊዎች ቁጥርም መሻሻሉን ተናግረዋል።
ያነጋገርናቸው መፃህፍት ሻጮችም በአውደርዕዩ ከ20 እስከ 50 በመቶ ቅናሽ በሚሆን ዋጋ መፅሀፍቶችን እየሸጡ እንደሆነ ገልፀውልናል።
የአዳዲስ መጽሐፍት ምረቃ ሥነ ሥርዓቶች፣ ታዋቂና አንጋፋ ደራሲያን ተሞክሯቸውን ለወጣቱ ትውልድ የሚያካፍሉባቸው የውይይት መድረኮች እንዲሁም የሕፃናት የንባብ ማበረታቻ ልዩ ዝግጅቶችም ዓውደርዕዩ በሚቀጥልባቸው ቀናት የሚጠበቁ መርሃግብሮች ናቸው።
በዳዊት ጣሰው
Ethiopian Broadcasting Corporation #አዲስአበባዩኒቨርስቲ #መጽሐፍት #ኢትዮጵያ
*******************
ትልቅ የዕውቀት እና የባህል መድረክ የሆነው 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በድምቀት ይካሄዳል።
ዩኒቨርስቲው 10 ዓመታትን በተሻገሩት ጊዜያት ለንባብና ለመፃህፍት ትልቅ ትኩረት በመስጠት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ዩኒቨርስቲው የአውደርዕዩን ቀጣይነት ማስጠበቅና ለውጡ የፈጠረውን እድል ተጠቅሞ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
በአውደ ርዕዩ ከ45 በላይ መጽሐፍት አከፋፋዮች፣ አሳታሚዎችና የመጽሐፍት መደብሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው መጽሐፍት ለጎብኚዎች እንደቀረቡም ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕረስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶ/ር ደርብ አዶ አውደ ርዕዩ ከዘመኑ ጋር እያደገ በስፋትም በተሳታፊዎች ቁጥርም መሻሻሉን ተናግረዋል።
ያነጋገርናቸው መፃህፍት ሻጮችም በአውደርዕዩ ከ20 እስከ 50 በመቶ ቅናሽ በሚሆን ዋጋ መፅሀፍቶችን እየሸጡ እንደሆነ ገልፀውልናል።
የአዳዲስ መጽሐፍት ምረቃ ሥነ ሥርዓቶች፣ ታዋቂና አንጋፋ ደራሲያን ተሞክሯቸውን ለወጣቱ ትውልድ የሚያካፍሉባቸው የውይይት መድረኮች እንዲሁም የሕፃናት የንባብ ማበረታቻ ልዩ ዝግጅቶችም ዓውደርዕዩ በሚቀጥልባቸው ቀናት የሚጠበቁ መርሃግብሮች ናቸው።
በዳዊት ጣሰው
Ethiopian Broadcasting Corporation #አዲስአበባዩኒቨርስቲ #መጽሐፍት #ኢትዮጵያ
13 days ago
በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል የተካሄደው የቁጣ ስልክ ጥሪ
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
22 days ago
"ምስጉን ሰው" የተሰኘው መጽሐፍ በድምቀት ተመረቀ
#ethiopia | የአቶ ታምራት ተመስገንን የሕይወት እና የሥራ ታሪክ የሚተርከው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በዲ ሊዮፖል ሆቴል በተካሄደ ስነ-ስርዓት በይፋ ተመረቀ።
ሰም እና ወርቅ ሚዲያ እና ኢንተርቴይመንት ባዘጋጀው በዚህ የመጽሐፍ የምረቃ መርሃ-ግብር ላይ የክብር እንግዶች፣ አንጋፋ የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች፣ የባለታሪኩ ወዳጆች እና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ እንግዶች ታድመዋል።
መጽሐፉ በጉራጌ ዞን በእንደጋኝ ወረዳ ተወልደው በሊስትሮነትና በሌሎች እጅግ አነስተኛ የጉልበት ሥራዎች ሕይወታቸውን የጀመሩትን የአቶ ታምራት ተመስገንን የትግል ጉዞ በሰፊው ይዳስሳል።
ባለታሪኩ ይህንን ፈታኝ የሕይወት ውጣ ውረድ በፅናት አልፈው ሀገሪቱ ካሏት ታላላቅ የግንባታ ኮንትራክተሮች አንዱ ለመሆን የቻሉ ሲሆን፣ ለበርካታ ዜጎችም የሥራ ዕድል በመፍጠር በሙያቸው እንዲበቁ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው በምረቃው ላይ ተገልጿል።
አቶ ታምራት ከጠንካራ የሥራ ባህላቸው ባሻገር በማኅበረሰባዊ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸውም በሰፊው እንደሚታወቁ በመጽሐፉ ተብራርቷል።
በችግር የተዘጉ ቤቶችን በመክፈት፣ አቅመ ደካሞችን በመደገፍ እንዲሁም ህሙማንን በማሳከም ኃላፊነታቸውን የተወጡ ምስጉን ሰው ናቸው። በተጨማሪም መንገዶችን፣ ቤተ እምነቶችን፣ የሕክምና ተቋማትን እና ትምህርት ቤቶችን በገንዘባቸውና በሙያቸው በመደገፍና በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቁ አድርገዋል።
ይህ የባለታሪኩን አርዓያነት ያለው ሕይወት አጉልቶ የሚያሳየው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው መጽሐፍ፣ በሃያሲና የሥነ-ጽሑፍ መምህር ባዩልኝ አያሌው እንዲሁም በደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ ተጽፎ ለንባብ የበቃ ነው።
የሕይወት ታሪክ መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች እና በአርባ ሁለት ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በሶስት መቶ ሰማንያ ሁለት ገጾች ተቀነባብሮ ቀርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | የአቶ ታምራት ተመስገንን የሕይወት እና የሥራ ታሪክ የሚተርከው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በዲ ሊዮፖል ሆቴል በተካሄደ ስነ-ስርዓት በይፋ ተመረቀ።
ሰም እና ወርቅ ሚዲያ እና ኢንተርቴይመንት ባዘጋጀው በዚህ የመጽሐፍ የምረቃ መርሃ-ግብር ላይ የክብር እንግዶች፣ አንጋፋ የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች፣ የባለታሪኩ ወዳጆች እና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ እንግዶች ታድመዋል።
መጽሐፉ በጉራጌ ዞን በእንደጋኝ ወረዳ ተወልደው በሊስትሮነትና በሌሎች እጅግ አነስተኛ የጉልበት ሥራዎች ሕይወታቸውን የጀመሩትን የአቶ ታምራት ተመስገንን የትግል ጉዞ በሰፊው ይዳስሳል።
ባለታሪኩ ይህንን ፈታኝ የሕይወት ውጣ ውረድ በፅናት አልፈው ሀገሪቱ ካሏት ታላላቅ የግንባታ ኮንትራክተሮች አንዱ ለመሆን የቻሉ ሲሆን፣ ለበርካታ ዜጎችም የሥራ ዕድል በመፍጠር በሙያቸው እንዲበቁ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው በምረቃው ላይ ተገልጿል።
አቶ ታምራት ከጠንካራ የሥራ ባህላቸው ባሻገር በማኅበረሰባዊ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸውም በሰፊው እንደሚታወቁ በመጽሐፉ ተብራርቷል።
በችግር የተዘጉ ቤቶችን በመክፈት፣ አቅመ ደካሞችን በመደገፍ እንዲሁም ህሙማንን በማሳከም ኃላፊነታቸውን የተወጡ ምስጉን ሰው ናቸው። በተጨማሪም መንገዶችን፣ ቤተ እምነቶችን፣ የሕክምና ተቋማትን እና ትምህርት ቤቶችን በገንዘባቸውና በሙያቸው በመደገፍና በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቁ አድርገዋል።
ይህ የባለታሪኩን አርዓያነት ያለው ሕይወት አጉልቶ የሚያሳየው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው መጽሐፍ፣ በሃያሲና የሥነ-ጽሑፍ መምህር ባዩልኝ አያሌው እንዲሁም በደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ ተጽፎ ለንባብ የበቃ ነው።
የሕይወት ታሪክ መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች እና በአርባ ሁለት ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በሶስት መቶ ሰማንያ ሁለት ገጾች ተቀነባብሮ ቀርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
Sponsored by
Surafel
28 days ago
የስመኝ ግዛውን መፅሐፍ ይግዙ!!!!!
*48 ሰዓት ሳይሞላ 1000 የመፅሀፍ ኮፒ በቅድመ ሽያጭ ተሸጠ
#ethiopia | ቅዳሜ ግንቦት 8 2018 ምሽት ላይ የተጀመረው "የእናቴ ሮሚዬ" የቅድመ ግዢ ቻሌንጅ ተጠናክሯል። 1000 መፅሀፎች በመሸጣቸው ደራሲዋ ስመኝ ግዛው የከበረ ምስጋናዋን አቅርባለች።
ከደራሲዋ ጎን ቆሞ ቻሌንጁን ያስጀመራት ተወዳጅ ሚድያም የማስተዋወቁን እና መፅሀፉን ግዟት በሚል የጀመረውን ቅስቀሳ አጠናክሮ ይቀጥላል ።
ተወዳጅ ሚድያ ስመኝን ለሚያውቁ ሁሉ መረጃውን በቴሌግራም ፣ በሜሴንጀር እና በሌሎችም መንገዶች እያደረሰ ሲሆን መፅሀፍ የገዙ ሰዎችን ከእነ ስማቸው እና አጭር ታሪካቸው ማውጣታችን ይከተላል። ድር ቢያብር አንበሳ ያስር እንዲሉ ነገ እርስዎም መፅሀፍ ቢያሳትሙ አጠገብዎ ሰው ያስፈልጋልና ነገ ሳይሉ ዛሬ በቻሌንጁ ይሳተፉ።
የቅድመ-መጽሐፍ ግዢ (Pre-Order) እና የአጋርነት ጥሪ!
ላለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት በጋዜጠኝነት እና በድንቅ የፈጠራ ሥራዎቿ የምናውቃት ደራሲ ስመኝ ግዛው፣ «የእናቴ ሮሚዮ» የተሰኘውን አዲስ የአጫጭር ልቦለዶች መድብል ለንባብ ልታበቃ ጥቂት ቀናት ቀርተዋታል።
በመሆኑም፣ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን፣ የደራሲዋ ሥራዎች አድናቂዎች፣ ተቋማትና ወዳጆች መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ ፓኬጆች በመግዛት አጋርነታችሁን እንድታሳዩ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
የቅድመ-ግዢ ፓኬጆች እና የዋጋ ዝርዝር፦
• 5 መጽሐፍ፦ 2,500 ብር
• 10 መጽሐፍት፦ 5,000 ብር
• 20 መጽሐፍት፦ 10,000 ብር
• 30 መጽሐፍት፦ 15,000 ብር
• 40 መጽሐፍት፦ 20,000 ብር
• 50 መጽሐፍት፦ 25,000 ብር
💳 የክፍያ እና የምዝገባ መመሪያ፦
1. ክፍያውን በሚከተለው የባንክ አካውንት ያስገቡ፦
o የባንክ አካውንት ቁጥር ፦ ኢት. ንግድ ባንክ 1000345019158
o ቴሌ ብር፦ ____0966925299
o የአካውንት ስም፦ ስመኝ ግዛው
2. ክፍያውን ከፈጸሙ በኋላ፣ የማረጋገጫ ደረሰኙን (Screenshot) በቴሌግራም አድራሻችን ይላኩ፦
የቴሌግራም ሊንክ/ዩዘርኔም፦ https://t.me/SimegnGizaw
• አስፈላጊ ማሳሰቢያ፦ መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ በመግዛት ለምታሳዩት ድጋፍና ውድ አጋርነት ልዩ እውቅና ለመስጠት ስለምንፈልግ፤ ከክፍያ ደረሰኙ ጋር ስለራስዎ የሚገልጽ አጭር መግለጫ (Bio) እና ፎቶግራፍዎን አያይዘው እንዲልኩልን በአክብሮት እንመክራለን።
ስለ ቅን አጋርነታችሁ አስቀድመን እናመሰግናለን!
*48 ሰዓት ሳይሞላ 1000 የመፅሀፍ ኮፒ በቅድመ ሽያጭ ተሸጠ
#ethiopia | ቅዳሜ ግንቦት 8 2018 ምሽት ላይ የተጀመረው "የእናቴ ሮሚዬ" የቅድመ ግዢ ቻሌንጅ ተጠናክሯል። 1000 መፅሀፎች በመሸጣቸው ደራሲዋ ስመኝ ግዛው የከበረ ምስጋናዋን አቅርባለች።
ከደራሲዋ ጎን ቆሞ ቻሌንጁን ያስጀመራት ተወዳጅ ሚድያም የማስተዋወቁን እና መፅሀፉን ግዟት በሚል የጀመረውን ቅስቀሳ አጠናክሮ ይቀጥላል ።
ተወዳጅ ሚድያ ስመኝን ለሚያውቁ ሁሉ መረጃውን በቴሌግራም ፣ በሜሴንጀር እና በሌሎችም መንገዶች እያደረሰ ሲሆን መፅሀፍ የገዙ ሰዎችን ከእነ ስማቸው እና አጭር ታሪካቸው ማውጣታችን ይከተላል። ድር ቢያብር አንበሳ ያስር እንዲሉ ነገ እርስዎም መፅሀፍ ቢያሳትሙ አጠገብዎ ሰው ያስፈልጋልና ነገ ሳይሉ ዛሬ በቻሌንጁ ይሳተፉ።
የቅድመ-መጽሐፍ ግዢ (Pre-Order) እና የአጋርነት ጥሪ!
ላለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት በጋዜጠኝነት እና በድንቅ የፈጠራ ሥራዎቿ የምናውቃት ደራሲ ስመኝ ግዛው፣ «የእናቴ ሮሚዮ» የተሰኘውን አዲስ የአጫጭር ልቦለዶች መድብል ለንባብ ልታበቃ ጥቂት ቀናት ቀርተዋታል።
በመሆኑም፣ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን፣ የደራሲዋ ሥራዎች አድናቂዎች፣ ተቋማትና ወዳጆች መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ ፓኬጆች በመግዛት አጋርነታችሁን እንድታሳዩ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
የቅድመ-ግዢ ፓኬጆች እና የዋጋ ዝርዝር፦
• 5 መጽሐፍ፦ 2,500 ብር
• 10 መጽሐፍት፦ 5,000 ብር
• 20 መጽሐፍት፦ 10,000 ብር
• 30 መጽሐፍት፦ 15,000 ብር
• 40 መጽሐፍት፦ 20,000 ብር
• 50 መጽሐፍት፦ 25,000 ብር
💳 የክፍያ እና የምዝገባ መመሪያ፦
1. ክፍያውን በሚከተለው የባንክ አካውንት ያስገቡ፦
o የባንክ አካውንት ቁጥር ፦ ኢት. ንግድ ባንክ 1000345019158
o ቴሌ ብር፦ ____0966925299
o የአካውንት ስም፦ ስመኝ ግዛው
2. ክፍያውን ከፈጸሙ በኋላ፣ የማረጋገጫ ደረሰኙን (Screenshot) በቴሌግራም አድራሻችን ይላኩ፦
የቴሌግራም ሊንክ/ዩዘርኔም፦ https://t.me/SimegnGizaw
• አስፈላጊ ማሳሰቢያ፦ መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ በመግዛት ለምታሳዩት ድጋፍና ውድ አጋርነት ልዩ እውቅና ለመስጠት ስለምንፈልግ፤ ከክፍያ ደረሰኙ ጋር ስለራስዎ የሚገልጽ አጭር መግለጫ (Bio) እና ፎቶግራፍዎን አያይዘው እንዲልኩልን በአክብሮት እንመክራለን።
ስለ ቅን አጋርነታችሁ አስቀድመን እናመሰግናለን!
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ ነዳጅ ማደያዎች የሳይበር ጥቃት እንደደረሰባቸው ተዘገበ፡፡ ሲኤንኤን እንዳቀረበው ዘገባ በበርካታ የአሜሪካ ግዛቶች ውስጥ የሚገኙ የነዳጅ መቆጣጠሪያ ስርአቶች ላይ የሳይበር ጥቃት ተፈፅሟል፡፡ ጥቃቱ ያነጣጠረው በአውቶማቲክ የነዳጅ ማጠራቀሚያ መለኪያ ስርአቶች ላይ እንደሆነ የጠቀሰው ዘገባው በዚህም እነዚህ ሲስተሞች በኦንላይን ካለፓስወርድ እንዲሰሩ መደረጋቸውን አስረድቷል፡፡
ጥቃት ፈፃሚዎቹ በአንዳንድ ነዳጅ ማደያዎች ላይ በስክሪን ላይ የሚታየውን የንባብ መጠን እስከመቀየር መድረሳቸውንም ገልጿል፡፡ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ምንጮቹን የጠቀሰው ዘገባው በዚህ ጥቃት በማከማቻ ውስጥ በሚገኝ ነዳጅ መጠን ላይ ምንም ችግር አለመከሰቱን አስታውቆ ነገር ግን ከፍተኛ የደህንነት ስጋትን የሚፈጥር መሆኑን አስረድቷል፡፡
እንዲህ አይነት ጥቃቶች የነዳጅ ፍሰትን ለመደበቅ የሚያስችሉ በመሆናቸው በሰውና በንብረት ላይ አደጋ ሊያደርሱ እንደሚችሉም አሳስቧል፡፡ በጉዳዩ ላይ ምርመራ እያደረጉ ያሉ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ለዜና አውታሩ ሲናገሩ ከዚህ ጥቃት በስተጀርባ ኢራን ልትኖርበት እንደምትችል አስታውቋል፡፡
ጥቃት ፈፃሚዎቹ በአንዳንድ ነዳጅ ማደያዎች ላይ በስክሪን ላይ የሚታየውን የንባብ መጠን እስከመቀየር መድረሳቸውንም ገልጿል፡፡ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ምንጮቹን የጠቀሰው ዘገባው በዚህ ጥቃት በማከማቻ ውስጥ በሚገኝ ነዳጅ መጠን ላይ ምንም ችግር አለመከሰቱን አስታውቆ ነገር ግን ከፍተኛ የደህንነት ስጋትን የሚፈጥር መሆኑን አስረድቷል፡፡
እንዲህ አይነት ጥቃቶች የነዳጅ ፍሰትን ለመደበቅ የሚያስችሉ በመሆናቸው በሰውና በንብረት ላይ አደጋ ሊያደርሱ እንደሚችሉም አሳስቧል፡፡ በጉዳዩ ላይ ምርመራ እያደረጉ ያሉ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ለዜና አውታሩ ሲናገሩ ከዚህ ጥቃት በስተጀርባ ኢራን ልትኖርበት እንደምትችል አስታውቋል፡፡
1 month ago
የጋዜጠኛና ደራሲ ስመኝ ግዛው አዲስ መጽሐፍ በቅርቡ ለንባብ ይበቃል
#ethiopia | ለዛ ባላቸው ጽሁፎቿ የምትታወቀው ጋዜጠኛ፣ ገጣሚና ደራሲ ስመኝ ግዛው የእናቴ "ሮሚዮ" እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች የተሰኘ አዲስ መጽሐፏን ለገበያ ልታቀርብ መሆኑን ገልጻለች።
የእናቴ "ሮሚዮ" መጽሐፍ ተራ የሚመስሉ ነገር ግን ጥልቅ ትርጉም ያላቸውን የሕይወት ክስተቶች በረቂቅ አጻጻፍ የሚያስቃኙ 20 አጫጭር ታሪኮችን በውስጡ አካትቷል።
ታሪኮቹ በእውነተኛ የፍቅርና የትዳር ሕይወት ውጣ ውረዶች ላይ የሚያተኩሩ ሲሆን ስሜትን በሚነኩ ግጥሞችም የታጀቡ መሆናቸውን ደራሲዋ አስታውቃለች።
በ 220 ገጾች ተቀንብቦ የቀረበው ይህ ሥራ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ረዳት ፕሮፌሰር መኩሪያ መካሻ ግምገማ የተደረገበት ሲሆን መጽሐፉ በሳል ይዘትና ልዩ አቀራረብ እንዳለው ምሁሩ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
የመጽሐፍ ምርቃቱ ከጥቂት ቀናት በኋላ እንደሚከናወንም ታውቋል።
#የእናቴሮሚዮ #ስመኝግዛው #አዲስመጽሐፍ #ስነጽሁፍ #ኢትዮጵያ #አጫጭርታሪኮች #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ለዛ ባላቸው ጽሁፎቿ የምትታወቀው ጋዜጠኛ፣ ገጣሚና ደራሲ ስመኝ ግዛው የእናቴ "ሮሚዮ" እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች የተሰኘ አዲስ መጽሐፏን ለገበያ ልታቀርብ መሆኑን ገልጻለች።
የእናቴ "ሮሚዮ" መጽሐፍ ተራ የሚመስሉ ነገር ግን ጥልቅ ትርጉም ያላቸውን የሕይወት ክስተቶች በረቂቅ አጻጻፍ የሚያስቃኙ 20 አጫጭር ታሪኮችን በውስጡ አካትቷል።
ታሪኮቹ በእውነተኛ የፍቅርና የትዳር ሕይወት ውጣ ውረዶች ላይ የሚያተኩሩ ሲሆን ስሜትን በሚነኩ ግጥሞችም የታጀቡ መሆናቸውን ደራሲዋ አስታውቃለች።
በ 220 ገጾች ተቀንብቦ የቀረበው ይህ ሥራ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ረዳት ፕሮፌሰር መኩሪያ መካሻ ግምገማ የተደረገበት ሲሆን መጽሐፉ በሳል ይዘትና ልዩ አቀራረብ እንዳለው ምሁሩ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
የመጽሐፍ ምርቃቱ ከጥቂት ቀናት በኋላ እንደሚከናወንም ታውቋል።
#የእናቴሮሚዮ #ስመኝግዛው #አዲስመጽሐፍ #ስነጽሁፍ #ኢትዮጵያ #አጫጭርታሪኮች #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
የአሜሪካ የነዳጅ ማደያዎች በኢራን ሃከሮች የሳይበር ጥቃት ተሰነዘረባቸው
በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች በሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች የነዳጅ መጠን መቆጣጠሪያ ስርዓቶች ላይ ለተሰነዘሩት ተከታታይ የሳይበር ጥቃቶች ከኢራን ጋር ግንኙነት ያላቸው ሃከሮች ሳይሆኑ አይቀሩም ሲል CNN የሀገሪቱን ባለስልጣናት ጠቅሶ ዘግቧል።
ሃከሮቹ ጥቃቱን የፈጸሙት ያለ ምንም የይለፍ ቃል በቀጥታ ከኢንተርኔት ጋር የተገናኙ አውቶማቲክ የነዳጅ ታንከር መቆጣጠሪያዎችን በመጠቀም ነው። በዚህም ጥቃት በማደያዎቹ ስክሪን ላይ የሚታየውን የነዳጅ መጠን ንባብ ማዛባት የቻሉ ሲሆን፣ በትክክለኛው ታንከሮቹ ውስጥ ባለው የነዳጅ መጠን ላይም የተወሰነ ጉዳት አድርሰዋል።
seledadotio
seledadotio
በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች በሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች የነዳጅ መጠን መቆጣጠሪያ ስርዓቶች ላይ ለተሰነዘሩት ተከታታይ የሳይበር ጥቃቶች ከኢራን ጋር ግንኙነት ያላቸው ሃከሮች ሳይሆኑ አይቀሩም ሲል CNN የሀገሪቱን ባለስልጣናት ጠቅሶ ዘግቧል።
ሃከሮቹ ጥቃቱን የፈጸሙት ያለ ምንም የይለፍ ቃል በቀጥታ ከኢንተርኔት ጋር የተገናኙ አውቶማቲክ የነዳጅ ታንከር መቆጣጠሪያዎችን በመጠቀም ነው። በዚህም ጥቃት በማደያዎቹ ስክሪን ላይ የሚታየውን የነዳጅ መጠን ንባብ ማዛባት የቻሉ ሲሆን፣ በትክክለኛው ታንከሮቹ ውስጥ ባለው የነዳጅ መጠን ላይም የተወሰነ ጉዳት አድርሰዋል።
seledadotio
seledadotio
1 month ago
1 ሺህ 139 የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች በስነምግባር ጥሰት ተቀጡ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የሥነ ምግባር ጉድለትና ብልሹ አሠራር በፈጸሙ 1 ሺህ 139 ሠራተኞቹ ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን መውሰዱን አስታወቀ።
እርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል 16 ሠራተኞች ከሥራ የተሰናበቱ ሲሆን 721 የሚሆኑት ደግሞ የደሞዝ ቅጣት ተጥሎባቸዋል። ቀሪዎቹ 402 ሠራተኞች የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል።
ከተወሰዱት እርምጃዎች ውስጥ 103ቱ ከደንበኞች በደረሱ ጥቆማዎች መሠረት የተከናወኑ ሲሆኑ ቀሪዎቹ 1 ሺህ 36 ጉዳዮች በተቋሙ የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት የተደረሰባቸው ናቸው።
ተቋሙ የሙስና መጠቆሚያ መተግበሪያንና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ከደንበኞች የደረሱትን 427 ጥቆማዎች መመርመሩን ገልጿል።
በዚህም መሠረት በደንበኞች ጥቆማ ምክንያት 7 ሠራተኞች ከሥራ የተሰናበቱ ሲሆን 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 14 የጽሑፍ ማስጠንቀቂያና 2 ከኃላፊነት የማንሳት እርምጃዎች ተፈጽመዋል።
አገልግሎቱ የብልሹ አሠራር ጥቆማዎች ከሚቀርቡባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል የአዲስ ቆጣሪ ጥያቄ፣ የኃይል መቆራረጥ፣ የጥገና መዘግየት፣ የቆጣሪ ንባብና የቢል አሰባሰብ እንዲሁም የንብረት አያያዝ እንደሚገኙበት ጠቅሷል።
ደንበኞች በድረ ገጽ (www.eeuethics.et) አማካኝነት ጥቆማዎችን እንዲሰጡ ያበረታታው ተቋሙ፣ ለጠቋሚዎች አስፈላጊውን ጥበቃና እውቅና እንደሚሰጥም አረጋግጧል።
ይህም አሠራር ተቋሙ ብልሹ አሠራሮችን ለመታገል ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት #ሙስና #አስተዳደራዊእርምጃ #መልካምአስተዳደር #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የሥነ ምግባር ጉድለትና ብልሹ አሠራር በፈጸሙ 1 ሺህ 139 ሠራተኞቹ ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን መውሰዱን አስታወቀ።
እርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል 16 ሠራተኞች ከሥራ የተሰናበቱ ሲሆን 721 የሚሆኑት ደግሞ የደሞዝ ቅጣት ተጥሎባቸዋል። ቀሪዎቹ 402 ሠራተኞች የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል።
ከተወሰዱት እርምጃዎች ውስጥ 103ቱ ከደንበኞች በደረሱ ጥቆማዎች መሠረት የተከናወኑ ሲሆኑ ቀሪዎቹ 1 ሺህ 36 ጉዳዮች በተቋሙ የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት የተደረሰባቸው ናቸው።
ተቋሙ የሙስና መጠቆሚያ መተግበሪያንና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ከደንበኞች የደረሱትን 427 ጥቆማዎች መመርመሩን ገልጿል።
በዚህም መሠረት በደንበኞች ጥቆማ ምክንያት 7 ሠራተኞች ከሥራ የተሰናበቱ ሲሆን 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 14 የጽሑፍ ማስጠንቀቂያና 2 ከኃላፊነት የማንሳት እርምጃዎች ተፈጽመዋል።
አገልግሎቱ የብልሹ አሠራር ጥቆማዎች ከሚቀርቡባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል የአዲስ ቆጣሪ ጥያቄ፣ የኃይል መቆራረጥ፣ የጥገና መዘግየት፣ የቆጣሪ ንባብና የቢል አሰባሰብ እንዲሁም የንብረት አያያዝ እንደሚገኙበት ጠቅሷል።
ደንበኞች በድረ ገጽ (www.eeuethics.et) አማካኝነት ጥቆማዎችን እንዲሰጡ ያበረታታው ተቋሙ፣ ለጠቋሚዎች አስፈላጊውን ጥበቃና እውቅና እንደሚሰጥም አረጋግጧል።
ይህም አሠራር ተቋሙ ብልሹ አሠራሮችን ለመታገል ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት #ሙስና #አስተዳደራዊእርምጃ #መልካምአስተዳደር #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
አቶ ዘገየ አስፋው አረፉ
#ethiopia | ከሁለት ቀን በፊት በኦቦ ሌንጮ ለታ የመፅሐፍ ምረቃ መርሀ ግብር ላይ በስካይ ላይት አብረውን ታድመው የነበሩት የ84 አመቱ አቶ ዘገየ አስፋው ትናንት ሌሊት ማረፋቸው ተነገረ።
ዘገየ አስፋው (Zegeye Asfaw) በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ሚና የነበራቸው አንጋፋ ምሁር፣ የህግ ባለሙያ እና የቀድሞ ሚኒስትር ነበሩ። በተለይም በደርግ ዘመን የነበረውን ታሪካዊ "መሬት ላራሹ" አዋጅ በማርቀቅና በማስፈጸም ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ሰው እንደነበሩ ይነገርላቸዋል።
ዋና ዋና የሥራ መስኮች
የመሬት ስርአት ለውጥ፡ አቶ ዘገየ በ1967 ዓ.ም የወጣውን የመሬት ይዞታ አዋጅ በማርቀቅ ረገድ ትልቅ ድርሻ የነበራቸው ሲሆን፣ የመሬትና የሕዝብ ማስፈር ሚኒስትር በመሆንም አገልግለዋል።
የመንግሥት የኃላፊነት ደረጃዎች፡ በኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት ወቅት (1983-1984 ዓ.ም) የግብርና ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።
የሲቪል ማህበረሰብ ተሳትፎ፡ ሁንዴ (Hundee) የተባለውን መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት በመመሥረት በግብርናና በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ በርካታ ሥራዎችን አከናውነዋል።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፡ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር በመሆን በማገልገል ላይ ነበሩ።
የሕይወት ታሪክና የትምህርት ዝግጅት
በ1934 ዓ.ም በምዕራብ ሸዋ የተወለዱት አቶ ዘገየ፣ ትምህርታቸውን በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) በሕግ ትምህርት ተከታትለዋል። በተማሪዎች እንቅስቃሴ ወቅትም ንቁ ተሳትፎ ነበራቸው። በፖለቲካዊ አቋማቸው ምክንያት በተለያዩ ሥርዓቶች የእስር እንግልት ደርሶባቸዋል፤ ለምሳሌ በደርግ ዘመን ለ10 ዓመታት ታስረዋል።
የሥነ-ጽሑፍ ሥራ
የአቶ ዘገየን የሕይወት ጉዞና የኢትዮጵያን የመሬት ፖለቲካ ታሪክ የሚተርክ Land to the Tiller የተሰኘ መጽሐፍ በኤን ኦስትሁይዘን (Ann Oosthuizen) ተጽፎ ለንባብ በቅቷል።
በ1987 ዓ.ም (እ.ኤ.አ. 1995) የመሠረቱት ሁንዴ (HUNDEE) የተባለውን መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት በሚከተሉት ላይ ያተኩራል፦
የሴቶች መብት፡ ሴቶች የመሬት ባለቤትነት መብት እንዲኖራቸውና በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ ይሠራል።
የአካባቢ ጥበቃ፡ በገጠር አካባቢዎች የደን መልሶ ልማትና የውሃ ጥበቃ ሥራዎችን ያከናውናል።
የአርሶ አደሮች ማህበራት፡ ገበሬዎች ምርታቸውን በፍትሐዊ ዋጋ እንዲሸጡ የገበያ ትስስር ይፈጥራል።
መሬት ላራሹ" እንደ መጽሐፍ
እ.ኤ.አ. በ2020 የታተመው Land to the Tiller: An Interview with Zegeye Asfaw የተሰኘው መጽሐፍ በአን ኦስትሁይዘን (Ann Oosthuizen) የተዘጋጀ ሲሆን፣ የአቶ ዘገየን የሕይወት ታሪክና የኢትዮጵያን የመሬት ፖለቲካ ትግል በዝርዝር ይተርካል። መጽሐፉ የሚከተሉትን ነጥቦች ያካትታል፦
የታሪክ ምስክርነት፡ አቶ ዘገየ በሦስት የተለያዩ መንግሥታት (በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣ በደርግ እና በሽግግር መንግሥቱ) ውስጥ ስለነበራቸው ቆይታ እና በመሬት ማሻሻያ ዙሪያ ስለነበረው ትግል በዝርዝር ይገልጻሉ።
የግል መስዋዕትነት፡ ፖሊሲውን ለማስፈጸም ሲሉ የከፈሉትን ዋጋ፣ በተለይም በደርግ እስር ቤት ያሳለፏቸውን 10 ዓመታት ይተርካል።
የሰሜንና የደቡብ ልዩነት፡ በኢትዮጵያ ሰሜናዊ ክፍል የነበረውን የ"ርስት" ሥርዓት እና በደቡብ የነበረውን የ"ጭሰኝነት" ሥርዓት ታሪካዊ ዳራ ይተነትናል።
"መሬት ላራሹ" እንደ ፖሊሲ (1967 ዓ.ም)
አቶ ዘገየ የካቲት 25 ቀን 1967 ዓ.ም የወጣውን የገጠር መሬት ይዞታ አዋጅ (Proclamation 31/1975) በማርቀቅ ግንባር ቀደም ነበሩ። ይህ አዋጅ፦ [1]
የዘመናት የፊውዳል ጭቆናን በማክተም መሬት ለመንግሥትና ለሕዝብ እንዲሆን አድርጓል።
ጭሰኝነትን እና ማንኛውንም ዓይነት የመሬት ኪራይ ወይም የጉልበት ብዝበዛ አግዷል።
ገበሬው በራሱ መሬት ላይ ባለቤት (ይዞታ ያለው) እንዲሆን በማድረግ የኢትዮጵያን የክፍለ ሀብት ስርጭት ለውጧል።#ተወዳጅ ሚድያ (ዕዝራ እጅጉ)
#ethiopia | ከሁለት ቀን በፊት በኦቦ ሌንጮ ለታ የመፅሐፍ ምረቃ መርሀ ግብር ላይ በስካይ ላይት አብረውን ታድመው የነበሩት የ84 አመቱ አቶ ዘገየ አስፋው ትናንት ሌሊት ማረፋቸው ተነገረ።
ዘገየ አስፋው (Zegeye Asfaw) በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ሚና የነበራቸው አንጋፋ ምሁር፣ የህግ ባለሙያ እና የቀድሞ ሚኒስትር ነበሩ። በተለይም በደርግ ዘመን የነበረውን ታሪካዊ "መሬት ላራሹ" አዋጅ በማርቀቅና በማስፈጸም ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ሰው እንደነበሩ ይነገርላቸዋል።
ዋና ዋና የሥራ መስኮች
የመሬት ስርአት ለውጥ፡ አቶ ዘገየ በ1967 ዓ.ም የወጣውን የመሬት ይዞታ አዋጅ በማርቀቅ ረገድ ትልቅ ድርሻ የነበራቸው ሲሆን፣ የመሬትና የሕዝብ ማስፈር ሚኒስትር በመሆንም አገልግለዋል።
የመንግሥት የኃላፊነት ደረጃዎች፡ በኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት ወቅት (1983-1984 ዓ.ም) የግብርና ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።
የሲቪል ማህበረሰብ ተሳትፎ፡ ሁንዴ (Hundee) የተባለውን መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት በመመሥረት በግብርናና በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ በርካታ ሥራዎችን አከናውነዋል።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፡ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር በመሆን በማገልገል ላይ ነበሩ።
የሕይወት ታሪክና የትምህርት ዝግጅት
በ1934 ዓ.ም በምዕራብ ሸዋ የተወለዱት አቶ ዘገየ፣ ትምህርታቸውን በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) በሕግ ትምህርት ተከታትለዋል። በተማሪዎች እንቅስቃሴ ወቅትም ንቁ ተሳትፎ ነበራቸው። በፖለቲካዊ አቋማቸው ምክንያት በተለያዩ ሥርዓቶች የእስር እንግልት ደርሶባቸዋል፤ ለምሳሌ በደርግ ዘመን ለ10 ዓመታት ታስረዋል።
የሥነ-ጽሑፍ ሥራ
የአቶ ዘገየን የሕይወት ጉዞና የኢትዮጵያን የመሬት ፖለቲካ ታሪክ የሚተርክ Land to the Tiller የተሰኘ መጽሐፍ በኤን ኦስትሁይዘን (Ann Oosthuizen) ተጽፎ ለንባብ በቅቷል።
በ1987 ዓ.ም (እ.ኤ.አ. 1995) የመሠረቱት ሁንዴ (HUNDEE) የተባለውን መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት በሚከተሉት ላይ ያተኩራል፦
የሴቶች መብት፡ ሴቶች የመሬት ባለቤትነት መብት እንዲኖራቸውና በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ ይሠራል።
የአካባቢ ጥበቃ፡ በገጠር አካባቢዎች የደን መልሶ ልማትና የውሃ ጥበቃ ሥራዎችን ያከናውናል።
የአርሶ አደሮች ማህበራት፡ ገበሬዎች ምርታቸውን በፍትሐዊ ዋጋ እንዲሸጡ የገበያ ትስስር ይፈጥራል።
መሬት ላራሹ" እንደ መጽሐፍ
እ.ኤ.አ. በ2020 የታተመው Land to the Tiller: An Interview with Zegeye Asfaw የተሰኘው መጽሐፍ በአን ኦስትሁይዘን (Ann Oosthuizen) የተዘጋጀ ሲሆን፣ የአቶ ዘገየን የሕይወት ታሪክና የኢትዮጵያን የመሬት ፖለቲካ ትግል በዝርዝር ይተርካል። መጽሐፉ የሚከተሉትን ነጥቦች ያካትታል፦
የታሪክ ምስክርነት፡ አቶ ዘገየ በሦስት የተለያዩ መንግሥታት (በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣ በደርግ እና በሽግግር መንግሥቱ) ውስጥ ስለነበራቸው ቆይታ እና በመሬት ማሻሻያ ዙሪያ ስለነበረው ትግል በዝርዝር ይገልጻሉ።
የግል መስዋዕትነት፡ ፖሊሲውን ለማስፈጸም ሲሉ የከፈሉትን ዋጋ፣ በተለይም በደርግ እስር ቤት ያሳለፏቸውን 10 ዓመታት ይተርካል።
የሰሜንና የደቡብ ልዩነት፡ በኢትዮጵያ ሰሜናዊ ክፍል የነበረውን የ"ርስት" ሥርዓት እና በደቡብ የነበረውን የ"ጭሰኝነት" ሥርዓት ታሪካዊ ዳራ ይተነትናል።
"መሬት ላራሹ" እንደ ፖሊሲ (1967 ዓ.ም)
አቶ ዘገየ የካቲት 25 ቀን 1967 ዓ.ም የወጣውን የገጠር መሬት ይዞታ አዋጅ (Proclamation 31/1975) በማርቀቅ ግንባር ቀደም ነበሩ። ይህ አዋጅ፦ [1]
የዘመናት የፊውዳል ጭቆናን በማክተም መሬት ለመንግሥትና ለሕዝብ እንዲሆን አድርጓል።
ጭሰኝነትን እና ማንኛውንም ዓይነት የመሬት ኪራይ ወይም የጉልበት ብዝበዛ አግዷል።
ገበሬው በራሱ መሬት ላይ ባለቤት (ይዞታ ያለው) እንዲሆን በማድረግ የኢትዮጵያን የክፍለ ሀብት ስርጭት ለውጧል።#ተወዳጅ ሚድያ (ዕዝራ እጅጉ)
1 month ago
የአንጋፋው ፖለቲከኛ ሌንጮ ለታን የግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞ የሚዳስስ መጽሐፍ ሊመረቅ ነው።
#fastmereja I አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታ ላለፉት 50 ዓመታት በኦሮሞ ብሔራዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ የነበራቸውን ሚና እና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ የሚያዘክር ልዩ የክብር መርሃ ግብር ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገለጸ።
በዕለቱ የፖለቲከኛው የሕይወት ታሪክ ላይ የሚያተኩርና በደራሲ ዙፋን ኡርጋ የተሰናዳ "የሌንጮ ለታ የሕይወት ታሪክ" መጽሐፍ በኦሮምኛና በአማርኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ ለንባብ እንደሚበቃ የመርሃ ግብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ይህ መርሃ ግብር በዋናነት ሦስት ዓላማዎችን ያሰነቀ ሲሆን፥ የመጀመሪያው የአቶ ሌንጮ ለታን የትግል ሕይወት ማክበርና ለኦሮሞ የፖለቲካ ትግል ዕድገት የነበራቸውን ፋና ወጊነት ዕውቅና መስጠት ነው።
ሁለተኛው ዓላማ የሌንጮ ለታን ፍልስፍናዊና ፖለቲካዊ ሐሳቦች፣ በተለይም በብሔርተኝነት፣ በሀገራዊ ግንባታ እና በአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ጥልቅ ትንታኔ የሚዳስስ ምሁራዊ መድረክ መፍጠር እንደሆነ ተገልጿል። በሦስተኛ ደረጃ መርሃ ግብሩ የፖለቲካ ትግሉን ሰብዓዊ ገጽታ ለማሳየት ያለመ ሲሆን፣ ይህም የአቶ ሌንጮን ቤተሰባዊ ሕይወትና ከትግሉ ጋር የነበረውን መስተጋብር የሚቃኝ ይሆናል።
በዝግጅቱ ላይ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ የፓናል ውይይት፣ የቤተሰብ አባላት ምስክርነት እና የመጽሐፍ ዳሰሳ የሚቀርብ ሲሆን፥ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አንጋፋ ታጋዮች፣ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች እንደሚታደሙ ይጠበቃል።
#fastmereja I አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታ ላለፉት 50 ዓመታት በኦሮሞ ብሔራዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ የነበራቸውን ሚና እና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ የሚያዘክር ልዩ የክብር መርሃ ግብር ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገለጸ።
በዕለቱ የፖለቲከኛው የሕይወት ታሪክ ላይ የሚያተኩርና በደራሲ ዙፋን ኡርጋ የተሰናዳ "የሌንጮ ለታ የሕይወት ታሪክ" መጽሐፍ በኦሮምኛና በአማርኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ ለንባብ እንደሚበቃ የመርሃ ግብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ይህ መርሃ ግብር በዋናነት ሦስት ዓላማዎችን ያሰነቀ ሲሆን፥ የመጀመሪያው የአቶ ሌንጮ ለታን የትግል ሕይወት ማክበርና ለኦሮሞ የፖለቲካ ትግል ዕድገት የነበራቸውን ፋና ወጊነት ዕውቅና መስጠት ነው።
ሁለተኛው ዓላማ የሌንጮ ለታን ፍልስፍናዊና ፖለቲካዊ ሐሳቦች፣ በተለይም በብሔርተኝነት፣ በሀገራዊ ግንባታ እና በአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ጥልቅ ትንታኔ የሚዳስስ ምሁራዊ መድረክ መፍጠር እንደሆነ ተገልጿል። በሦስተኛ ደረጃ መርሃ ግብሩ የፖለቲካ ትግሉን ሰብዓዊ ገጽታ ለማሳየት ያለመ ሲሆን፣ ይህም የአቶ ሌንጮን ቤተሰባዊ ሕይወትና ከትግሉ ጋር የነበረውን መስተጋብር የሚቃኝ ይሆናል።
በዝግጅቱ ላይ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ የፓናል ውይይት፣ የቤተሰብ አባላት ምስክርነት እና የመጽሐፍ ዳሰሳ የሚቀርብ ሲሆን፥ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አንጋፋ ታጋዮች፣ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች እንደሚታደሙ ይጠበቃል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የኤሌክትሪክ ወርሃዊ ክፍያ ላይ የተደረገ የታሪፍ ጭማሪ አለመኖሩ ተነገረ
ካለፉት 3 ወራት ወዲህ በኤሌክትሪክ ወርሃዊ ክፍያ ላይ ከፍተኛ ጭማሪ መደረጉን ነዋሪዎች ቅሬታቸዉን ለጣቢያችን ብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።
በጉዳዩ ዙሪያ ብስራት ሬዲዮ ያነጋገራቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የማርኬቲንግ ፣ሽያጭ እና የደንበኞች አገልግሎት ስራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ደንድር ወርሃዊ ክፍያ አጠቃቀምን መሠረት አድርጎ በተቀመጠዉ መደብ ዉስጥ ያለዉ ታሪፍ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል ።
ባለፈዉ ወር 100 ኪሎ ዋት የተጠቀመ ደንበኛ በዚህም ወር 100 ኪሎ ዋት ቢጠቀም በየሩቭ ዓመቱ ከሚጨምረዉ ታሪፍ ዉጪ ሌላ ተጨማሪ ጭማሪ እንደማይኖር አቶ ኢሳያስ ጨምረዉ ገልፀዋል ።
ከንባብ ጋር በተያያዘ ብዙ ስራ እየተከናወነ ቢሆንም የተወሰኑ ክፍተቶች መኖራቸዉን የገለፀዉ አገልግሎቱ እነዚህን ክፍተቶች ለማስተካከል ደንበኞች ቤታቸዉ ሆነዉ ንባብ መላክ የሚችሉበትን የቴሌግራም ቦት ስርዓት በሁሉም ሪጅንኞች ተግባራዊ መደረጉን አስታውቋል ።
በ5 ዓመት ጊዜ ዉስጥ 4.65 ሚሊዮን ቆጣሪዎችን ወደ ስማርት ለመቀየር መታቀዱን የገለፁት አቶ ኢሳያስ እስከ እዛ ባለዉ ጊዜ ዉስጥ የድህረ ክፍያ ቆጣሪ ተጠቃሚ ደንበኞች እንዲከፍሉ የሚጠበቀዉ አጠቃቀማቸዉን መሠረት ያደረገ ክፍያ ብቻ ነዉ ብለዋል ።
ጭማሪ ተደርጎብናል የሚሉ ደንበኞች ካሉ በንባብ ስህተትም ይሁን ሳይከፈል የተጠራቀመ ኖሮ ከሆነ ማየት እንደሚቻል ተገልጿል ።
seledadotio
seledadotio
ካለፉት 3 ወራት ወዲህ በኤሌክትሪክ ወርሃዊ ክፍያ ላይ ከፍተኛ ጭማሪ መደረጉን ነዋሪዎች ቅሬታቸዉን ለጣቢያችን ብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።
በጉዳዩ ዙሪያ ብስራት ሬዲዮ ያነጋገራቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የማርኬቲንግ ፣ሽያጭ እና የደንበኞች አገልግሎት ስራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ደንድር ወርሃዊ ክፍያ አጠቃቀምን መሠረት አድርጎ በተቀመጠዉ መደብ ዉስጥ ያለዉ ታሪፍ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል ።
ባለፈዉ ወር 100 ኪሎ ዋት የተጠቀመ ደንበኛ በዚህም ወር 100 ኪሎ ዋት ቢጠቀም በየሩቭ ዓመቱ ከሚጨምረዉ ታሪፍ ዉጪ ሌላ ተጨማሪ ጭማሪ እንደማይኖር አቶ ኢሳያስ ጨምረዉ ገልፀዋል ።
ከንባብ ጋር በተያያዘ ብዙ ስራ እየተከናወነ ቢሆንም የተወሰኑ ክፍተቶች መኖራቸዉን የገለፀዉ አገልግሎቱ እነዚህን ክፍተቶች ለማስተካከል ደንበኞች ቤታቸዉ ሆነዉ ንባብ መላክ የሚችሉበትን የቴሌግራም ቦት ስርዓት በሁሉም ሪጅንኞች ተግባራዊ መደረጉን አስታውቋል ።
በ5 ዓመት ጊዜ ዉስጥ 4.65 ሚሊዮን ቆጣሪዎችን ወደ ስማርት ለመቀየር መታቀዱን የገለፁት አቶ ኢሳያስ እስከ እዛ ባለዉ ጊዜ ዉስጥ የድህረ ክፍያ ቆጣሪ ተጠቃሚ ደንበኞች እንዲከፍሉ የሚጠበቀዉ አጠቃቀማቸዉን መሠረት ያደረገ ክፍያ ብቻ ነዉ ብለዋል ።
ጭማሪ ተደርጎብናል የሚሉ ደንበኞች ካሉ በንባብ ስህተትም ይሁን ሳይከፈል የተጠራቀመ ኖሮ ከሆነ ማየት እንደሚቻል ተገልጿል ።
seledadotio
seledadotio
1 month ago
የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል
#ethiopia | ኢትዮጵያ በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ የ1 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ የምታገኝበትን ስምምነት ሁለቱ አገራት መፈራረማቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለፓርላማ ተናግሯል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ይህን የተናገረው ከሰሞኑ የዘጠኝ ወር የስራ ክንውን ሪፖርቱን በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የስራ ክንውን ሪፖርት በንባብ ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል ብለዋል።
ከዚህ ውስጥ 33.5 ቢሊዮን ዶላር የውጪ ብድር እዳ እንደሆነ እና ቀሪው 18.3 ቢሊዮን ዶላሩ ደግሞ የሀገር ውስጥ እዳ መሆኑን አቶ አህመድ አብራርተዋል።
ከ33.5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ እዳ ውስጥ ደግሞ 22.1 ቢሊዮን ዶላሩ የፌደራል መንግስት እዳ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ቀሪው 11.5 ቢሊዮን ዶላር ደግሞ የመንግስት የልማት ድርጅቶች እዳ እንደሆነም አክለዋል።
ከሀገር ውስጥ ብድሩ ማለትም ከ18.3ቢሊዮን ዲላር ውስጥ ደግሞ 17.5 የፌደራል መንግስት እዳ እንደሆነ እና 0.8 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ነው ብለዋል አቶ አህመድ ።
የመንግስት የልማት ድርጅቶች እዳ ዝቅ ያለበትን ምክንያት አቶ አህመድ ሲያስረዱ በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት አብዛኛው ከንግድ ባንክ ተበድረው የነበረው ብድር ወደ ገንዘብ ሚኒስቴር በመዞሩ በበጀት መከፍል በመጀመሩ እንደሆነ አሳውቀዋል።
አጠቃላይ የኢትዮጵያ እዳ ሁኔታ በእሳቸው አገላለጽ "በጣም በጣም "ጤናማ እንደሆነ ለቋሚ ኮሚቴው ያስረዱት ሚኒስትሩ የውጪ እዳ የመክፈል አቅማችንም "ከጊዜ ወደ ጊዜ "እየጨመረ ነው ብለዋል።
የሀገር ውስጥ ብድር ደግሞ ጭማሪ አሳይቷል ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናግረዋል፡፡
ይህ ደግሞ ለማስተካከል በዘላቂ (sustainable) የፋይናንስ መርህን በመከተል የሚሰራ ስራ ይኖራል ነው ያሉት ሚኒስትር አህመድ።
በእዳ ክፍያን ክንውን ሪፖርታቸው ደገሞ በበጀት ዓመቱ ለሀገር ውስጥ እና የውጪ እዳ ክፍያ 463.4 ቢሊዮን ብር ተመድቦ የነበረ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት የአግልግሎት ክፍያን ጨምሮ 226.5 ቢሊዮን ብር ተከፍሏል።
እንዲሁም የውጭ ሃብት አሰባሰብን በተመለከተ በዓመቱ ከተለያዪ ተቋማት 4 ቢሊዮን ዶላር ለመሰብሰብ ማታቀዱን እንዲሁም በዘጠኝ ወሩ ደግሞ 3.1 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ታቅዶ ከዛ ውስጥ 2 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከእቅዱ በ1.1 ዶላር ያነሰ ተግኝቷል ተብሏል።
ይህም የእቅዱን 65.1 በመቶ ሲሆን ከተገኘው ገንዘብ ውስጥ 914.2 ሚሊዮን ዶላሩ ከአለም ባንክ መገኘቱን አቶ አህመድ ተናግረዋል።
የውጪ ሃብት ግኝቱ በቀጣይ ሁለት ወራት ከፍ ይላል ተብሎ እንደሚጠበቅ ያስረዱት ሚኒስትሩ ባለፈው አሜሪካ ተደርጎ በነበረው የአልም ባንክ እና የገንዘብ ድርጅት ስብሰባ ላይ ለበጀት ድጋፍ ለአደጋ ምላሽና ለነዳጅ ማሻሻያ ማስኬጃ የሚያስችሉ ምላሾች መገኘታቸውን የገንዘብ ሚኒስትሩ ሪፖርት ያክላል።
የአሜሪካ የተራድዖ ድርጅት እርዳታ መቋረጥ የጤና፣ ትምህርት፣ ግብርና የእቅም ግንባታ ስራዎች ላይ ጫና መፍጠሩን ያስታወሱት ሚኒስትሩ በቅርቡ ድርድር በማድረግ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ በዓመቱ በመንግስት በኩል ፈሰስ እንዲደረግ ከአሜሪካ መንግስት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል ብለዋል።
ይህም ስምምነት በቅርቡ በካቢኔ እንደሚጸድቅ አቶ አህመድ ጠቁመዋል ያለው ሸገር ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ethiopia | ኢትዮጵያ በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ የ1 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ የምታገኝበትን ስምምነት ሁለቱ አገራት መፈራረማቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለፓርላማ ተናግሯል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ይህን የተናገረው ከሰሞኑ የዘጠኝ ወር የስራ ክንውን ሪፖርቱን በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የስራ ክንውን ሪፖርት በንባብ ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል ብለዋል።
ከዚህ ውስጥ 33.5 ቢሊዮን ዶላር የውጪ ብድር እዳ እንደሆነ እና ቀሪው 18.3 ቢሊዮን ዶላሩ ደግሞ የሀገር ውስጥ እዳ መሆኑን አቶ አህመድ አብራርተዋል።
ከ33.5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ እዳ ውስጥ ደግሞ 22.1 ቢሊዮን ዶላሩ የፌደራል መንግስት እዳ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ቀሪው 11.5 ቢሊዮን ዶላር ደግሞ የመንግስት የልማት ድርጅቶች እዳ እንደሆነም አክለዋል።
ከሀገር ውስጥ ብድሩ ማለትም ከ18.3ቢሊዮን ዲላር ውስጥ ደግሞ 17.5 የፌደራል መንግስት እዳ እንደሆነ እና 0.8 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ነው ብለዋል አቶ አህመድ ።
የመንግስት የልማት ድርጅቶች እዳ ዝቅ ያለበትን ምክንያት አቶ አህመድ ሲያስረዱ በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት አብዛኛው ከንግድ ባንክ ተበድረው የነበረው ብድር ወደ ገንዘብ ሚኒስቴር በመዞሩ በበጀት መከፍል በመጀመሩ እንደሆነ አሳውቀዋል።
አጠቃላይ የኢትዮጵያ እዳ ሁኔታ በእሳቸው አገላለጽ "በጣም በጣም "ጤናማ እንደሆነ ለቋሚ ኮሚቴው ያስረዱት ሚኒስትሩ የውጪ እዳ የመክፈል አቅማችንም "ከጊዜ ወደ ጊዜ "እየጨመረ ነው ብለዋል።
የሀገር ውስጥ ብድር ደግሞ ጭማሪ አሳይቷል ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናግረዋል፡፡
ይህ ደግሞ ለማስተካከል በዘላቂ (sustainable) የፋይናንስ መርህን በመከተል የሚሰራ ስራ ይኖራል ነው ያሉት ሚኒስትር አህመድ።
በእዳ ክፍያን ክንውን ሪፖርታቸው ደገሞ በበጀት ዓመቱ ለሀገር ውስጥ እና የውጪ እዳ ክፍያ 463.4 ቢሊዮን ብር ተመድቦ የነበረ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት የአግልግሎት ክፍያን ጨምሮ 226.5 ቢሊዮን ብር ተከፍሏል።
እንዲሁም የውጭ ሃብት አሰባሰብን በተመለከተ በዓመቱ ከተለያዪ ተቋማት 4 ቢሊዮን ዶላር ለመሰብሰብ ማታቀዱን እንዲሁም በዘጠኝ ወሩ ደግሞ 3.1 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ታቅዶ ከዛ ውስጥ 2 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከእቅዱ በ1.1 ዶላር ያነሰ ተግኝቷል ተብሏል።
ይህም የእቅዱን 65.1 በመቶ ሲሆን ከተገኘው ገንዘብ ውስጥ 914.2 ሚሊዮን ዶላሩ ከአለም ባንክ መገኘቱን አቶ አህመድ ተናግረዋል።
የውጪ ሃብት ግኝቱ በቀጣይ ሁለት ወራት ከፍ ይላል ተብሎ እንደሚጠበቅ ያስረዱት ሚኒስትሩ ባለፈው አሜሪካ ተደርጎ በነበረው የአልም ባንክ እና የገንዘብ ድርጅት ስብሰባ ላይ ለበጀት ድጋፍ ለአደጋ ምላሽና ለነዳጅ ማሻሻያ ማስኬጃ የሚያስችሉ ምላሾች መገኘታቸውን የገንዘብ ሚኒስትሩ ሪፖርት ያክላል።
የአሜሪካ የተራድዖ ድርጅት እርዳታ መቋረጥ የጤና፣ ትምህርት፣ ግብርና የእቅም ግንባታ ስራዎች ላይ ጫና መፍጠሩን ያስታወሱት ሚኒስትሩ በቅርቡ ድርድር በማድረግ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ በዓመቱ በመንግስት በኩል ፈሰስ እንዲደረግ ከአሜሪካ መንግስት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል ብለዋል።
ይህም ስምምነት በቅርቡ በካቢኔ እንደሚጸድቅ አቶ አህመድ ጠቁመዋል ያለው ሸገር ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹በማንኛውም አገር ላይ ፀብ ማንሳት አንፈልግም፣ ነገር ግን ማንም ይሁን በእኛ ላይ ጥቃት የፈፀመ ምላሹን ያገኛል›› ሲሉ የሱዳን ባለስልጣናት ተናገሩ፡፡ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትርና የጦር ሀይሉ ቃል አቀባይ ትላንት ምሽት ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡ ሲሆን በዚህ መግለጫ ላይ የተነሱትን ሀሳቦች ሬዲዮ ዳባንጋ በአጭሩ አቅርቧቸዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሞሂ አልዲን ሰላም በመግለጫቸው በካርቱም አየር ማረፊያ ላይ ትላንት ለተፈፀመው ጥቃት ኢትዮጵያና ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ተሳታፊ መሆናቸውን መግለፃቸውን የጠቀሰው ዘገባው ‹‹በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኤመሬትስ ላይ ለከፈትነው ክስ ይህንን ማስረጃ አድርገን እናቀርባለን›› ማለታቸውን አስረድቷል፡፡
ጨምረውም ‹‹የትላንቱ ድርጊት እኛ እንደእህት ከምናያት ኢትዮጵያ ወረራ እንደተካሄደብን ማረጋገጫ ነው›› ያሉት ሚኒስትሩ ይህን ጥቃት የተፈፀመው ‹‹ጠላቶች›› ያሏቸው አካላት ሰዎች ወደካርቱም በፈቃደኝነት እየተመለሱ መሆኑን በማየት የፈፀሙት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በማስከተልም ‹‹ኢትዮጵያና ኤመሬትስ የተሳሳተ መንገድን መርጠዋል፡፡ በዚህ ደግሞ ይቆጫቸዋል›› ያሉት ሚኒስትሩ በተለይ የኢትዮጵያ መንግስት የሁለቱን አገራት ግንኙነት እንዳበላሸ አድርገው መግለፃቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡
ጨምሮም ለዚህ ድርጊት ተመጣጣኝ መልስ የመስጠት ህጋዊ መብት እንዳላቸው ያስረዱት ሚኒስትሩ ‹‹በማንኛውም አገር ላይ ፀብ ማንሳት አንፈልግም፣ ነገር ግን ማንም ይሁን በእኛ ላይ ጥቃት የፈፀመ ምላሹን ያገኛል›› ማለታቸውን ጠቅሷል፡፡ የሱዳን ጦር ሀይል ቃል አቀባይ የሆኑት ብርጋዴር ጄኔራል አሲም አውድ አብደልዋሀብ በበኩላቸው በንባብ ባሰሙት መግለጫ ከተለያዩ መረጃዎችና ሪፖርቶች በመነሳት ድርጊቱ የተጀመረው በማርች ወር መጀመሪያ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ጨምረውም 3 ድሮኖች ከባህር ዳር ተነስተው በኋይት ናይል፣ ብሉ ናይል፣ ሰሜንና ደቡብ ኮርዶፋን ግዛቶች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን አውስተዋል፡፡
ከዚያም ማርች 17 ቀን ከእነዚህ ድሮኖች አንደኛው ተመቶ መውደቁንና በዚህ ድሮን ላይ በተደረገው ምርመራ አምራቹን ለመረዳት መቻላቸውን አስታውቀዋል፡፡ ይህ የመለያ ቁጥሩ ‹‹ኤስ 88›› የሆነው ድሮን ባለቤትነቱ የዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ መሆኑን ለማወቅ መቻላቸውን ጠቅሰው ድሮኑ በኢትዮጵያ ክልል ውስጥ በባህር ዳር አየር ማረፊያ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን መረዳታቸውን ገልፀዋል፡፡
ካገኙት መረጃ በመነሳት ይህ ድሮን በተደጋጋሚ የሱዳንን አየር ክልል ጥሶ በኩምሩክ አካባቢና በሰሜናዊ ኮርዶፋን ጥቃት እንደፈፀመ አስረድተዋል፡፡ ቃል አቀባዩ ሲቀጥሉም ከሜይ 1 እስከ ሜይ 4 ባሉት ቀናት ደግሞ እንደገና ከባህር ዳር ተነስቶ የሱዳንን አየር ክልል በመጣስ በጀበል አውሊያ የተሰኘው አካባቢ እስከሚደርስ ድረስ ክትትል ሲያደርጉበት እንደነበር አስታውቀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ይህ ማስረጃ የሚያሳየው ኤመሬትስና ኢትዮጵያ የአየር ክልላችንን እንደጣሱ ነው፡፡ እንዲህ አይነት ድርጊትን በዝምታ አናልፈውም›› ሲሉም ተናግረዋል፡፡ የሱዳን ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ካሊድ አልአሲር ደግሞ የካርቱም አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሰላማዊ መሰረተ ልማት መሆኑን ገልፀው ከደህንነት ጋር የተገናኙ ቴክኒካል ጉዳዮች ካለቁ በኋላ አየር ማረፊያው መልሶ ስራ እንደሚጀምር አስረድተዋል፡፡ በአየር ማረፊያው ላይ ጉዳት ያልደረሰ ቢሆንም በብሎክ 5 በኩል ባለው መውጫ አንድ ቤት ተመቶ ሁለት ወንድማማቾች መቁሰላቸውንም አስታውቀዋል፡፡
ጨምረውም ‹‹የትላንቱ ድርጊት እኛ እንደእህት ከምናያት ኢትዮጵያ ወረራ እንደተካሄደብን ማረጋገጫ ነው›› ያሉት ሚኒስትሩ ይህን ጥቃት የተፈፀመው ‹‹ጠላቶች›› ያሏቸው አካላት ሰዎች ወደካርቱም በፈቃደኝነት እየተመለሱ መሆኑን በማየት የፈፀሙት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በማስከተልም ‹‹ኢትዮጵያና ኤመሬትስ የተሳሳተ መንገድን መርጠዋል፡፡ በዚህ ደግሞ ይቆጫቸዋል›› ያሉት ሚኒስትሩ በተለይ የኢትዮጵያ መንግስት የሁለቱን አገራት ግንኙነት እንዳበላሸ አድርገው መግለፃቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡
ጨምሮም ለዚህ ድርጊት ተመጣጣኝ መልስ የመስጠት ህጋዊ መብት እንዳላቸው ያስረዱት ሚኒስትሩ ‹‹በማንኛውም አገር ላይ ፀብ ማንሳት አንፈልግም፣ ነገር ግን ማንም ይሁን በእኛ ላይ ጥቃት የፈፀመ ምላሹን ያገኛል›› ማለታቸውን ጠቅሷል፡፡ የሱዳን ጦር ሀይል ቃል አቀባይ የሆኑት ብርጋዴር ጄኔራል አሲም አውድ አብደልዋሀብ በበኩላቸው በንባብ ባሰሙት መግለጫ ከተለያዩ መረጃዎችና ሪፖርቶች በመነሳት ድርጊቱ የተጀመረው በማርች ወር መጀመሪያ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ጨምረውም 3 ድሮኖች ከባህር ዳር ተነስተው በኋይት ናይል፣ ብሉ ናይል፣ ሰሜንና ደቡብ ኮርዶፋን ግዛቶች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን አውስተዋል፡፡
ከዚያም ማርች 17 ቀን ከእነዚህ ድሮኖች አንደኛው ተመቶ መውደቁንና በዚህ ድሮን ላይ በተደረገው ምርመራ አምራቹን ለመረዳት መቻላቸውን አስታውቀዋል፡፡ ይህ የመለያ ቁጥሩ ‹‹ኤስ 88›› የሆነው ድሮን ባለቤትነቱ የዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ መሆኑን ለማወቅ መቻላቸውን ጠቅሰው ድሮኑ በኢትዮጵያ ክልል ውስጥ በባህር ዳር አየር ማረፊያ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን መረዳታቸውን ገልፀዋል፡፡
ካገኙት መረጃ በመነሳት ይህ ድሮን በተደጋጋሚ የሱዳንን አየር ክልል ጥሶ በኩምሩክ አካባቢና በሰሜናዊ ኮርዶፋን ጥቃት እንደፈፀመ አስረድተዋል፡፡ ቃል አቀባዩ ሲቀጥሉም ከሜይ 1 እስከ ሜይ 4 ባሉት ቀናት ደግሞ እንደገና ከባህር ዳር ተነስቶ የሱዳንን አየር ክልል በመጣስ በጀበል አውሊያ የተሰኘው አካባቢ እስከሚደርስ ድረስ ክትትል ሲያደርጉበት እንደነበር አስታውቀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ይህ ማስረጃ የሚያሳየው ኤመሬትስና ኢትዮጵያ የአየር ክልላችንን እንደጣሱ ነው፡፡ እንዲህ አይነት ድርጊትን በዝምታ አናልፈውም›› ሲሉም ተናግረዋል፡፡ የሱዳን ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ካሊድ አልአሲር ደግሞ የካርቱም አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሰላማዊ መሰረተ ልማት መሆኑን ገልፀው ከደህንነት ጋር የተገናኙ ቴክኒካል ጉዳዮች ካለቁ በኋላ አየር ማረፊያው መልሶ ስራ እንደሚጀምር አስረድተዋል፡፡ በአየር ማረፊያው ላይ ጉዳት ያልደረሰ ቢሆንም በብሎክ 5 በኩል ባለው መውጫ አንድ ቤት ተመቶ ሁለት ወንድማማቾች መቁሰላቸውንም አስታውቀዋል፡፡
1 month ago
ኢትዮጵያዊቷ ጀሚላ ተሰማ በታዋቂው የፔንክራፍት (PenCraft) የዓለም አቀፍ መጽሐፍት ሽልማት አሸናፊ ሆነች
#fastmereja I በትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ጀሚላ ተሰማ የተዘጋጀው “የሚዛናዊ ሕይወት ጆርናል” (The Balanced Life Journal) በአሜሪካ ላስ ቬጋስ በተካሄደው 9ኛው የጸሐፊያን ንባብ (Authors Reading) የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ የክብር ባለቤት ሆኗል። መጽሐፉ በምርጥ የሥነ-ልቦና እና የግል ዕድገት (Best Book for Nonfiction Self-help) ዘርፍ የ“PenCraft Award” አሸናፊ ሆነ።
የቴክኖሎጂ ባለሙያ እና የ“አመኒም ሶሊዩሽንስ” አይቲ ትምህርት ቤት መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆነችው ጀሚላ ተሰማ፣ ይህን ሽልማት ያገኘችው በሰዎች የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ ጥልቅ ለውጥ የሚያመጣ ሥራ በማቅረቧ ነው። ጆርናሉ ግለሰቦች ሕይወታቸውን በስድስት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ እንዲገነቡ የሚያስችል ሳይንሳዊ መመሪያዎችን አካቷል።
እነዚህም፦
ጤና እና መንፈሳዊ ሕይወት
የግል እና የሙያ ዕድገት
የፋይናንስ አስተዳደር እና ማኅበራዊ ግንኙነት
ጆርናሉ ከንድፈ-ሐሳብ ባለፈ በጸሐፊዋ እውነተኛ የሕይወት ተሞክሮ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ለየት ያደርገዋል። በዘመናዊው ዓለም የተዛባውን የሕይወት ዘይቤ ለማስተካከል እና የታቀደ ሕይወትን ለመምራት ለሚፈልጉ ሁሉ እንደ መፍትሔ ቀርቧል።
ይህ ዓለም አቀፍ ዕውቅና የጆርናሉን ተደራሽነት ይበልጥ እንደሚያሰፋው የገለጹት ባለሙያዋ፣ በቀጣይ ሰፋ ያሉ የማኅበረሰብ ስልጠናዎችን እና የተሳትፎ መድረኮችን ለማዘጋጀት ማቀዳቸውን አስታውቀዋል። ጀሚላ ተሰማ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ካላት ከፍተኛ ተጽዕኖ በተጨማሪ አሁን በሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ማስጠራት ችላለች።
#fastmereja I በትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ጀሚላ ተሰማ የተዘጋጀው “የሚዛናዊ ሕይወት ጆርናል” (The Balanced Life Journal) በአሜሪካ ላስ ቬጋስ በተካሄደው 9ኛው የጸሐፊያን ንባብ (Authors Reading) የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ የክብር ባለቤት ሆኗል። መጽሐፉ በምርጥ የሥነ-ልቦና እና የግል ዕድገት (Best Book for Nonfiction Self-help) ዘርፍ የ“PenCraft Award” አሸናፊ ሆነ።
የቴክኖሎጂ ባለሙያ እና የ“አመኒም ሶሊዩሽንስ” አይቲ ትምህርት ቤት መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆነችው ጀሚላ ተሰማ፣ ይህን ሽልማት ያገኘችው በሰዎች የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ ጥልቅ ለውጥ የሚያመጣ ሥራ በማቅረቧ ነው። ጆርናሉ ግለሰቦች ሕይወታቸውን በስድስት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ እንዲገነቡ የሚያስችል ሳይንሳዊ መመሪያዎችን አካቷል።
እነዚህም፦
ጤና እና መንፈሳዊ ሕይወት
የግል እና የሙያ ዕድገት
የፋይናንስ አስተዳደር እና ማኅበራዊ ግንኙነት
ጆርናሉ ከንድፈ-ሐሳብ ባለፈ በጸሐፊዋ እውነተኛ የሕይወት ተሞክሮ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ለየት ያደርገዋል። በዘመናዊው ዓለም የተዛባውን የሕይወት ዘይቤ ለማስተካከል እና የታቀደ ሕይወትን ለመምራት ለሚፈልጉ ሁሉ እንደ መፍትሔ ቀርቧል።
ይህ ዓለም አቀፍ ዕውቅና የጆርናሉን ተደራሽነት ይበልጥ እንደሚያሰፋው የገለጹት ባለሙያዋ፣ በቀጣይ ሰፋ ያሉ የማኅበረሰብ ስልጠናዎችን እና የተሳትፎ መድረኮችን ለማዘጋጀት ማቀዳቸውን አስታውቀዋል። ጀሚላ ተሰማ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ካላት ከፍተኛ ተጽዕኖ በተጨማሪ አሁን በሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ማስጠራት ችላለች።
2 months ago
Abebe Tilahun culture & Sport:
ለፈረንጅ ሚስቶች የቆመች ሐውልት‼️
የመጽሐፉ ርዕስ፦ የፈረንጅ ሚስት
ደራሲት፦ እስከዳር ግርማይ
የገጽ ብዛት ፦ 119
የመጽሐፉ ዋጋ ፦ 150 ብር
እትም፦ 3ኛ /2017 ዓ.ም
ዘውግ፦ ግለ ማስታወሻ (Memoir)+
አርታኢያን፦ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል እና አርቲስት አዜብ ወርቁ
👉መንደርደሪያ
ካርል ሮጀርስ (Carl Rogers) የተባለው ታዋቂው አሜሪካዊ የሥነ-ልቦና ባለሙያ "On Becoming a Person" በተሰኘ መጽሐፉ ላይ በሰዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት በማጥናት እንዲህ ይላል። “What is most personal is most universal.” ፦ “እጅግ ሲበዛ ግላዊ የሆነው ነገር፣ እጅግ ሲበዛ ዓለማቀፋዊ ነው።”
ግለ-ማስታወሻ (Memoir)፤ ከሕይወት ውስጥ አንድን ወሳኝ ክስተት፣ ስሜት ወይም ጭብጥ (Theme) መርጦ ይተነትናል። ትኩረቱ "ከገጠመኝ ነገር ምን ተማርኩ? ምን ተሰማኝ?" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር ግለ-ማስታወሻ ከታሪክ ይልቅ ትርጓሜና ስሜት ላይ ያተኩራል።
አንድ ሰው ለብቻው የሚሰማው፣ ለሌላ ሰው ለመናገር የሚፈራው ወይም "እኔ ብቻ ነኝ እንዲህ የሚሰማኝ" ብሎ የሚያስበው የግል ስሜት (ለምሳሌ፦ የፍርሃት፣ የብቸኝነት ስሜት፣ ወይም የናፍቆት፣ የመበሳጨትና የመብከንከን ስሜት) በሚገርም ሁኔታ ሌሎች ሰዎችም በውስጣቸው የሚሰማቸው ነው።
ስለሆነም ጸሐፊዋ እስከዳር ስለ ራሷና በዙሪያዋ ስላሉ ተመሳሳይ ሰዎች እጅግ ጥብቅና ግላዊ የሆኑ ጉዳዮችን በሐቀኝነት ስትናገር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በታሪኳ ውስጥ የራሳቸውን ስሜት አግኝተውታል። የሥነ-ልቦና ጠበብት አንድ ሰው ወደ ራሱ ማንነት (Inner self) በጥልቀት በወረደ ቁጥር፣ ከግል ማንነቱ ባለፈ የሰው ልጅን የጋራ ማንነት (Collective Human Experience) ያገኛል ብለው ያምናሉና በፈረንጅ ሚስት የሆነውም ይሄው ነው።
ሌላኛው ጄምስ ጆይስ (James Joyce)የተባለ ምሁር "በተለየው (in the particular) ውስጥ ሁልጊዜም ዓለማቀፋዊውን (the universal) ነገር እናገኛለን።" በማለት በሥነ-ጽሑፍ ሥራዎቹ የግል ተሞክሮን ማዕከል ማድረጉን ገልጿል። እንዲሁም ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን (Ralph Waldo Emerson) "በገዛ ልብህ ውስጥ የምታምነው እውነት ለሁሉም ሰዎች እውነት ነው።" በሚል ሀሳብ ተመሳሳይ ፍልስፍናን አራምዷል።
በአጠቃላይ አባባሉ "የሰው ልጅ ስሜትና ተፈጥሮ በየትኛውም ቦታ አንድ ነው" የሚለውን መሠረታዊ እውነት የሚያሳይ ነው። የፈረንጅ ሚስት የሚለው ግለ-ማስታወሻ በራስ ሕይወት መስኮትነት ዓለምን የማሳያ ጥበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ጸሐፊዋ በራሷ ሕይወት ውስጥ ያለውን ትርጉም ስትፈልግ፣ አንባቢው ደግሞ በጸሐፊው ታሪክ ውስጥ የራሱንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ያያል፣ ይታዘባል።
የፈረንጅ ሚስት
👉ግላዊና ዓለማቀፋዊ ሀሳብ፤ ጸሐፊዋ ስለ ራሷ ብቻ ስታወራ ለአንባቢው አሰልቺ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በግል ሕይወቷ በፈረንጅ ሚስትነቷ፣ በኢትዮጵያዊነቷ፣ የደረሰባትን ሐዘን፣ ፍቅር፣ ክህደት ወይም መገለል በሐቀኝነት ስለገለጠችው፣ አንባቢያን በራሳቸው ሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት አጋጥሟቸው ስለሚያውቅ ከጸሐፊዋ ጋር፣ እንደግል በሀሳብ፣ እንደማኅበረሰብ በአባልነት ይቆራኛሉ።
ሰው ወደ ራሱ ውስጠት በጥልቀት በቆፈረ ቁጥር፣ የሁሉንም ሰው የጋራ ምንጭ ያገኛል። የራስን እውነተኛ ስሜት፣ ስቃይ እና ደስታ መፈለግ እና እዚያ ጥልቀት ላይ ሲደርሱ የምናገኘው ራስን ብቻ ሳይሆን መላውን የሰው ልጅ የሚያገናኘውን የጋራ ክር ነው። ለዚህ ነው ግላዊ ማስታወሻዎች (Memoirs) በሚገባ ተቆፍረው ሲጻፉ ዓለምን ሁሉ የመንካት አቅም የሚኖራቸው።
በሥነ-ጽሑፍ እና በፈጠራ ድርሰት ዓለም ውስጥ በስፋት የምትታወቀው አሜሪካዊት ጸሐፊ ማያ አንጄሉ (Maya Angelou) “In the particular is contained the universal.” ፦ በተለየው/በግል ታሪክ ውስጥ፣ ዓለማቀፋዊው እውነት ይገኛል። ብላለች ።
ይህች የፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ከኢትዮጵያዊ ወንድ ውጭ ላገባችሁ ቀወል ስም የፈረንጅ ሚስት ለምትባሉ ሁሉ ሴቶች የቆመች ቅልብጭ ያለች ሐውልት ናት።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ውስጥ ፤
ሐቀኝነት (Honesty)አለ፦ ግለ-ማስታወሻ ጸሐፊዋ ራሷን ብቻ ያሞግሰችበት ሳይሆን፣ ድክመትና ስህተቶችንም ጭምር የገለጥችበት መጽሐፍ ነው። ሐቀኝነት ከሌለ አንባቢው በታሪኩ አይመሰጥም።
የራስ መተማመኗን ፈረንጅ የማግባት ውጤት ሲያደርጉት፤ ሐበሻ ብታገባ ኖሮ በዚህ የራስ መተማመኗ ድሮ እንደሚፈታት ሲያሙላት በስላቅ ሐቋን ትጠይቃለች።
"እውነት የሀገሬ ሴቶች ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና በራሳችሁ
የምትተማመኑ ከሆናችሁ ትዳራችሁ አይጸናም?
ደመወዛችሁ ከባለቤታችሁ ደመወዝ ሲበልጥ፣ ሥልጣናችሁ ከትዳራችሁ በላይ ሲገዝፍ ትፋታላችሁ?
ወይስ ትዳራችሁን መርጣችሁ፣ የመጣላችሁን ዕድል አሳልፋችሁ ለወንድ እና ላላገቡ ሴቶች ትሰጣላችሁ?
የሀገሬ ወንዶችስ? በሥራ፣ በደመወዝ ወይም በሥልጣን የምትበልጣችሁን ሴት ማግባት ትፈራላችሁ እንዴ?"
መልስ አትፈልግም።
ይልቁንስ ደራሲዋ ጥያቄዎቹን የምታቀርበው ምላሽ ፈልጋ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡን በመስታወት ፊት አቁማ ራሱን እንዲታዘብ ለማድረግ ነው።
ጭብጥ (Theme)አለ፦ ታሪኳ የሚሽከረከርበት አንድ ማዕከላዊ እውነት አለው ። ማዕከላዊ እውነቷ በማኅበረሰባችን ዘንድ ለፈረንጅ ሚስት ያለውን ስሁት አመለካከት ማረም፣ እውነቷንና ጽናቷን በመግለጽ ማንነቷን ማሳየት ነው። ለእያንዳንዱ ገጠመኟ በተግባር የተፈጸመ ምሳሌ ያልደበዘዘ ትውስታ ተቀምጧል ።
በማኅበረሰባችን ዘንድ የፈረንጅ ሚስትን ከሚያራክስበት ዝቅጠታዊ ልማድ የባሰ የሀብታም ቅምጥን የሚያሞግስበትና የሚያከብርበት የስብእና ንጥፈት እንዴት እንዳብከነከናት በሚቆጠቁጥ መልኩ የማዕከላዊ ጭብጡ ማጠንጠኛ ሆኗል ።
ደሞ ለምን ፈረንጅ አገባሽ ? እያሉ የጅል ጥያቄ ለሚጠይቁ አድርቅ ጋዜጠኞች ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ በጥያቄያቸው እንዲያፍሩ የምታደርግበት ጥበብ የፈረንጁ ባሏ ምክርና የጭብጧ ማጠናከሪያ ነበር።
"ባለቤቴ ሁል ጊዜ የማይደረስ ጥያቄ ለሚጠይቅሽ ሰው፤ የጠየቀሽን ጥያቄ መልሰሽ ራሱን ጠይቂው። መልሱ ካላጠገበሽ ምን ማለትህ ነው? ብለሽ ይበልጥ እንዲያብራራልሽ እንደገና ጠይቂው። ስህተቱን
እስኪረዳው ተፋተኚው። እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ከአምስት
ጥያቄዎች በላይ መመለስ አይችሉም፤ የሚለኝን ሳስበው ተግባራዊ እያደረግኩ።" ትለናለች። (ገጽ34)
ጥበባዊ አቀራረብ አለ፦ ምንም እንኳን እውነተኛ ታሪክ ቢሆንም፣ እንደ ልብ-ወለድ (Fiction) የታሪክ አወቃቀር፣ ገጸ-ባህሪያት አሳሳል እና የቃላት ምርጫ (Imagery) ተጠቀማለች። እንደ ገጸ ባሕርይ ራሷን እና በዙሪያዋ ያሉ ተመሳሳይ ሕይወት የሚጋሩ ወዳጆቿን፣ ቤተሰቦቿን እና በመንገዷ የገጠሟትን አካታለች። የታሪክ አወቃቀሩ ከአንዱ የሕይወት ገጠመኝ ወደ ሌላኛው የሕይወት ገጠመኝ እየተሻገረች፣ በትውስታ እያጀበች በምሳሌ አዋቅራ የልቧን እውነት የሕይወቷን ትርክት ቀንጭባ አቅርባዋለች።
የቃላት አመራረጧ ትኩሳቷን በመግለጥ እንደ እሳት የሚጋረፉ ፣ ስታዝን የሚለዝቡ፣ ስትቆጣ የሚንጣጡ ቃላት ናቸው።
ለምሳሌ የሀብታም ቅምጥን የገለጠችበትን ቃላት ተመልከቱ፦ "የሀብታም ቅምጥ የከተማው ሁሉ ወንድ የሚመኛት፣ ያሳደጓት የሰፈር ጎረምሶች ዓይናቸው እያየ ለባለጸጋ አሳልፈው በመስጠታቸው የሚቆጩባት፣ ዘመድ አዝማዶቿ የእሷ ስኬት የልጆቻቸው ባለመሆኑ የሚቀኑባት፣ የሰፈሩ ሰዎች ለአቅመ ሔዋን ላልደረሱ ልጆቻቸው "አርአያነቷን" እንዲከተሉ ጀብዳቸውን የሚነግሩላት፤ በየቦታው ትንሽዬ "ፈጣሪ" ሆና ብዙ "ደቀ መዛሙርት" ያፈራች ሴት ናት።" (ገጽ 27)
ውስጣዊ ሙግት (Internal Dialogue/ አለ፦ በሆነባት በተደረገባት ነገር ብቻ ሳይሆን፤ የወጣችበት ማኅበረሰብ ግንዛቤ ባለበት ቆሞ መቅረት ጭምር ሲያብሰከስካት ፤ እንደግል መብቷን፣ እንደማኅበረሰብ ውበቷን ስትገፈፍ የምትናገራቸው ቃላት የውስጧን መብከንከን ይገልጻሉ።
"የማዝነው፤ ማኅበረሰባችን በየመንገዱ መሰደቧን እንዳላየ እንዳልሰማ ሆኖ ስለሚያልፋት ብቻ አይደለም ። ከሐበሻ ወንድ ወጭ ሲሆን በፍቅር የማትወድቅ፣ ከሀገሯ ቋንቋ በቀር የፍቅር ቃላት የማትሰማ፣ ጠረን ለምዳ የማትሸነፍ ናት፤ ብለው በመወሰናቸውና የስሜት ሕዋሳቷ ለሌላ ሀገር ዜጋም ቢሆን እንደሚሠሩ ባለማወቃቸውም እንጂ!" (ገጽ16)
"ውጭ ሀገር ስንኖር አለመከበራችን በምንም መልኩ ልክ አይደለም፤ በሰው ሀገር ስንከፋ የሚሰማን ስሜት ፣ ከራሳችን ሀገር ከሚደርስብን የጥቃት ስሜት ጋር ካነጻጸርነው ግን፣ የሕመሙ ክብደት በሰው ሀገር
ሲሆን ይቀንሳል።
ሀገር ያስከፋን ጊዜ ግን ወዴት አቤት ይባላል? የራስ ሕዝብስ ለማን ይከሰሳል?" እያለች ምሯን ትናገራለች።
እናቴ አሳዛኝና አንጀት ቆራጭ ነገሮች ሲገጥሟት፦ "ከቀላድም ባይረዝም ከመጫኛም ባይበልጥ፤
አንጀት ያልቅ የለም ወይ ሲቆረጥ ሲቆረጥ።" ትላለች ።
የማኅበረሰባዊ መገፋት አንጀት ይቆርጣል ፤ አይመልሰኝ አሰኝቶ ድንጋይ ያስወረውራል። በጊዜ ሊታረም ከዘመኑ ጋርም ሊዘምን የሚገባ እንጅ የምናጌጥበት ነውር መሆን የለበትም ።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ
ደራሲዋ እስከዳር ግርማይና መሰል የፈረንጅ ሚስቶች ያለፈና ያለን ቁስል በቃላት አስጊጣ በመግለጧ ግላዊ እፎይታ ፣ ሕሊናዊ ፈውስ አግኝተውበታል፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።
በመሰል ፈተና ውስጥ ያሉ ሰዎች የግለ ማስታወሻዎቹን ሂደትና መፍትሔ አይተው ተስፋ የሚሰጥ ትምህርት ያገኛሉ። በማኅበረሰባዊ ሂሷም ብዙዎች ራሳቸውን እንዲታዘቡ ራሳቸውን እንዲመረምሩና እንዲታረሙ ኮርኩራለች።
እስከዳር በራሷ የተወሰነ ዘመንና ማኅበረሰብ ውስጥ ለፈረንጅ ሚስት የነበረን አመለካከት ለትውልድ በማስተላለፍ የታሪክ ምስክር በመሆን፤ ለፈረንጅ ሚስቶች ሐውልት አቁማለች።
ማጠቃለያ
ደራሲ እስከዳር ግርማይ በመጽሐፏ ውስጥ 'የፈረንጅ ሚስት' የሚለውን ስም ከስድብነት ወደ ማንነት (Identity)፣ ከማንነትም ወደ ተጋድሎ (Resistance) ቀይራዋለች። ይህ መጽሐፍ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነትን እና የዘመናዊነትን (Modernity) ግጭት፣ እንዲሁም የሴትነትን ነፃነት የሚፈትን፣ ማኅበረሰባዊ ሕጸፅን ነቅሶ የሚያሳይ መስታወት ነው።
👉እስከዬ አሁንም ያላወጣሽው ብዙ ግላዊ "የመሬማውያን ጉዳይ" አለና በጥልቀት ቆፍረሽ ታወጭው ዘንድ አደራ እላለሁ 🙏
👉የፈረንጅ ሚስት በዶክመንተሪ ቢዘጋጅ ደግሞ ከንባብ የራቀውና የስድብ መጋዘን ከሆነው የማኅበረሰብ ክፍል ውስጥ በእጁ ላይ ገብተሽ ትነግሪዋለሽ። የፈረንጅ ሚስት ማለት በምን የሕይወት ሸለቆ ውስጥ አልፋ ምርጫዋን የምታስከብር እንደሆነች ታሳያቸዋለሽ።
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
ለፈረንጅ ሚስቶች የቆመች ሐውልት‼️
የመጽሐፉ ርዕስ፦ የፈረንጅ ሚስት
ደራሲት፦ እስከዳር ግርማይ
የገጽ ብዛት ፦ 119
የመጽሐፉ ዋጋ ፦ 150 ብር
እትም፦ 3ኛ /2017 ዓ.ም
ዘውግ፦ ግለ ማስታወሻ (Memoir)+
አርታኢያን፦ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል እና አርቲስት አዜብ ወርቁ
👉መንደርደሪያ
ካርል ሮጀርስ (Carl Rogers) የተባለው ታዋቂው አሜሪካዊ የሥነ-ልቦና ባለሙያ "On Becoming a Person" በተሰኘ መጽሐፉ ላይ በሰዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት በማጥናት እንዲህ ይላል። “What is most personal is most universal.” ፦ “እጅግ ሲበዛ ግላዊ የሆነው ነገር፣ እጅግ ሲበዛ ዓለማቀፋዊ ነው።”
ግለ-ማስታወሻ (Memoir)፤ ከሕይወት ውስጥ አንድን ወሳኝ ክስተት፣ ስሜት ወይም ጭብጥ (Theme) መርጦ ይተነትናል። ትኩረቱ "ከገጠመኝ ነገር ምን ተማርኩ? ምን ተሰማኝ?" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር ግለ-ማስታወሻ ከታሪክ ይልቅ ትርጓሜና ስሜት ላይ ያተኩራል።
አንድ ሰው ለብቻው የሚሰማው፣ ለሌላ ሰው ለመናገር የሚፈራው ወይም "እኔ ብቻ ነኝ እንዲህ የሚሰማኝ" ብሎ የሚያስበው የግል ስሜት (ለምሳሌ፦ የፍርሃት፣ የብቸኝነት ስሜት፣ ወይም የናፍቆት፣ የመበሳጨትና የመብከንከን ስሜት) በሚገርም ሁኔታ ሌሎች ሰዎችም በውስጣቸው የሚሰማቸው ነው።
ስለሆነም ጸሐፊዋ እስከዳር ስለ ራሷና በዙሪያዋ ስላሉ ተመሳሳይ ሰዎች እጅግ ጥብቅና ግላዊ የሆኑ ጉዳዮችን በሐቀኝነት ስትናገር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በታሪኳ ውስጥ የራሳቸውን ስሜት አግኝተውታል። የሥነ-ልቦና ጠበብት አንድ ሰው ወደ ራሱ ማንነት (Inner self) በጥልቀት በወረደ ቁጥር፣ ከግል ማንነቱ ባለፈ የሰው ልጅን የጋራ ማንነት (Collective Human Experience) ያገኛል ብለው ያምናሉና በፈረንጅ ሚስት የሆነውም ይሄው ነው።
ሌላኛው ጄምስ ጆይስ (James Joyce)የተባለ ምሁር "በተለየው (in the particular) ውስጥ ሁልጊዜም ዓለማቀፋዊውን (the universal) ነገር እናገኛለን።" በማለት በሥነ-ጽሑፍ ሥራዎቹ የግል ተሞክሮን ማዕከል ማድረጉን ገልጿል። እንዲሁም ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን (Ralph Waldo Emerson) "በገዛ ልብህ ውስጥ የምታምነው እውነት ለሁሉም ሰዎች እውነት ነው።" በሚል ሀሳብ ተመሳሳይ ፍልስፍናን አራምዷል።
በአጠቃላይ አባባሉ "የሰው ልጅ ስሜትና ተፈጥሮ በየትኛውም ቦታ አንድ ነው" የሚለውን መሠረታዊ እውነት የሚያሳይ ነው። የፈረንጅ ሚስት የሚለው ግለ-ማስታወሻ በራስ ሕይወት መስኮትነት ዓለምን የማሳያ ጥበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ጸሐፊዋ በራሷ ሕይወት ውስጥ ያለውን ትርጉም ስትፈልግ፣ አንባቢው ደግሞ በጸሐፊው ታሪክ ውስጥ የራሱንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ያያል፣ ይታዘባል።
የፈረንጅ ሚስት
👉ግላዊና ዓለማቀፋዊ ሀሳብ፤ ጸሐፊዋ ስለ ራሷ ብቻ ስታወራ ለአንባቢው አሰልቺ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በግል ሕይወቷ በፈረንጅ ሚስትነቷ፣ በኢትዮጵያዊነቷ፣ የደረሰባትን ሐዘን፣ ፍቅር፣ ክህደት ወይም መገለል በሐቀኝነት ስለገለጠችው፣ አንባቢያን በራሳቸው ሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት አጋጥሟቸው ስለሚያውቅ ከጸሐፊዋ ጋር፣ እንደግል በሀሳብ፣ እንደማኅበረሰብ በአባልነት ይቆራኛሉ።
ሰው ወደ ራሱ ውስጠት በጥልቀት በቆፈረ ቁጥር፣ የሁሉንም ሰው የጋራ ምንጭ ያገኛል። የራስን እውነተኛ ስሜት፣ ስቃይ እና ደስታ መፈለግ እና እዚያ ጥልቀት ላይ ሲደርሱ የምናገኘው ራስን ብቻ ሳይሆን መላውን የሰው ልጅ የሚያገናኘውን የጋራ ክር ነው። ለዚህ ነው ግላዊ ማስታወሻዎች (Memoirs) በሚገባ ተቆፍረው ሲጻፉ ዓለምን ሁሉ የመንካት አቅም የሚኖራቸው።
በሥነ-ጽሑፍ እና በፈጠራ ድርሰት ዓለም ውስጥ በስፋት የምትታወቀው አሜሪካዊት ጸሐፊ ማያ አንጄሉ (Maya Angelou) “In the particular is contained the universal.” ፦ በተለየው/በግል ታሪክ ውስጥ፣ ዓለማቀፋዊው እውነት ይገኛል። ብላለች ።
ይህች የፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ከኢትዮጵያዊ ወንድ ውጭ ላገባችሁ ቀወል ስም የፈረንጅ ሚስት ለምትባሉ ሁሉ ሴቶች የቆመች ቅልብጭ ያለች ሐውልት ናት።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ውስጥ ፤
ሐቀኝነት (Honesty)አለ፦ ግለ-ማስታወሻ ጸሐፊዋ ራሷን ብቻ ያሞግሰችበት ሳይሆን፣ ድክመትና ስህተቶችንም ጭምር የገለጥችበት መጽሐፍ ነው። ሐቀኝነት ከሌለ አንባቢው በታሪኩ አይመሰጥም።
የራስ መተማመኗን ፈረንጅ የማግባት ውጤት ሲያደርጉት፤ ሐበሻ ብታገባ ኖሮ በዚህ የራስ መተማመኗ ድሮ እንደሚፈታት ሲያሙላት በስላቅ ሐቋን ትጠይቃለች።
"እውነት የሀገሬ ሴቶች ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና በራሳችሁ
የምትተማመኑ ከሆናችሁ ትዳራችሁ አይጸናም?
ደመወዛችሁ ከባለቤታችሁ ደመወዝ ሲበልጥ፣ ሥልጣናችሁ ከትዳራችሁ በላይ ሲገዝፍ ትፋታላችሁ?
ወይስ ትዳራችሁን መርጣችሁ፣ የመጣላችሁን ዕድል አሳልፋችሁ ለወንድ እና ላላገቡ ሴቶች ትሰጣላችሁ?
የሀገሬ ወንዶችስ? በሥራ፣ በደመወዝ ወይም በሥልጣን የምትበልጣችሁን ሴት ማግባት ትፈራላችሁ እንዴ?"
መልስ አትፈልግም።
ይልቁንስ ደራሲዋ ጥያቄዎቹን የምታቀርበው ምላሽ ፈልጋ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡን በመስታወት ፊት አቁማ ራሱን እንዲታዘብ ለማድረግ ነው።
ጭብጥ (Theme)አለ፦ ታሪኳ የሚሽከረከርበት አንድ ማዕከላዊ እውነት አለው ። ማዕከላዊ እውነቷ በማኅበረሰባችን ዘንድ ለፈረንጅ ሚስት ያለውን ስሁት አመለካከት ማረም፣ እውነቷንና ጽናቷን በመግለጽ ማንነቷን ማሳየት ነው። ለእያንዳንዱ ገጠመኟ በተግባር የተፈጸመ ምሳሌ ያልደበዘዘ ትውስታ ተቀምጧል ።
በማኅበረሰባችን ዘንድ የፈረንጅ ሚስትን ከሚያራክስበት ዝቅጠታዊ ልማድ የባሰ የሀብታም ቅምጥን የሚያሞግስበትና የሚያከብርበት የስብእና ንጥፈት እንዴት እንዳብከነከናት በሚቆጠቁጥ መልኩ የማዕከላዊ ጭብጡ ማጠንጠኛ ሆኗል ።
ደሞ ለምን ፈረንጅ አገባሽ ? እያሉ የጅል ጥያቄ ለሚጠይቁ አድርቅ ጋዜጠኞች ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ በጥያቄያቸው እንዲያፍሩ የምታደርግበት ጥበብ የፈረንጁ ባሏ ምክርና የጭብጧ ማጠናከሪያ ነበር።
"ባለቤቴ ሁል ጊዜ የማይደረስ ጥያቄ ለሚጠይቅሽ ሰው፤ የጠየቀሽን ጥያቄ መልሰሽ ራሱን ጠይቂው። መልሱ ካላጠገበሽ ምን ማለትህ ነው? ብለሽ ይበልጥ እንዲያብራራልሽ እንደገና ጠይቂው። ስህተቱን
እስኪረዳው ተፋተኚው። እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ከአምስት
ጥያቄዎች በላይ መመለስ አይችሉም፤ የሚለኝን ሳስበው ተግባራዊ እያደረግኩ።" ትለናለች። (ገጽ34)
ጥበባዊ አቀራረብ አለ፦ ምንም እንኳን እውነተኛ ታሪክ ቢሆንም፣ እንደ ልብ-ወለድ (Fiction) የታሪክ አወቃቀር፣ ገጸ-ባህሪያት አሳሳል እና የቃላት ምርጫ (Imagery) ተጠቀማለች። እንደ ገጸ ባሕርይ ራሷን እና በዙሪያዋ ያሉ ተመሳሳይ ሕይወት የሚጋሩ ወዳጆቿን፣ ቤተሰቦቿን እና በመንገዷ የገጠሟትን አካታለች። የታሪክ አወቃቀሩ ከአንዱ የሕይወት ገጠመኝ ወደ ሌላኛው የሕይወት ገጠመኝ እየተሻገረች፣ በትውስታ እያጀበች በምሳሌ አዋቅራ የልቧን እውነት የሕይወቷን ትርክት ቀንጭባ አቅርባዋለች።
የቃላት አመራረጧ ትኩሳቷን በመግለጥ እንደ እሳት የሚጋረፉ ፣ ስታዝን የሚለዝቡ፣ ስትቆጣ የሚንጣጡ ቃላት ናቸው።
ለምሳሌ የሀብታም ቅምጥን የገለጠችበትን ቃላት ተመልከቱ፦ "የሀብታም ቅምጥ የከተማው ሁሉ ወንድ የሚመኛት፣ ያሳደጓት የሰፈር ጎረምሶች ዓይናቸው እያየ ለባለጸጋ አሳልፈው በመስጠታቸው የሚቆጩባት፣ ዘመድ አዝማዶቿ የእሷ ስኬት የልጆቻቸው ባለመሆኑ የሚቀኑባት፣ የሰፈሩ ሰዎች ለአቅመ ሔዋን ላልደረሱ ልጆቻቸው "አርአያነቷን" እንዲከተሉ ጀብዳቸውን የሚነግሩላት፤ በየቦታው ትንሽዬ "ፈጣሪ" ሆና ብዙ "ደቀ መዛሙርት" ያፈራች ሴት ናት።" (ገጽ 27)
ውስጣዊ ሙግት (Internal Dialogue/ አለ፦ በሆነባት በተደረገባት ነገር ብቻ ሳይሆን፤ የወጣችበት ማኅበረሰብ ግንዛቤ ባለበት ቆሞ መቅረት ጭምር ሲያብሰከስካት ፤ እንደግል መብቷን፣ እንደማኅበረሰብ ውበቷን ስትገፈፍ የምትናገራቸው ቃላት የውስጧን መብከንከን ይገልጻሉ።
"የማዝነው፤ ማኅበረሰባችን በየመንገዱ መሰደቧን እንዳላየ እንዳልሰማ ሆኖ ስለሚያልፋት ብቻ አይደለም ። ከሐበሻ ወንድ ወጭ ሲሆን በፍቅር የማትወድቅ፣ ከሀገሯ ቋንቋ በቀር የፍቅር ቃላት የማትሰማ፣ ጠረን ለምዳ የማትሸነፍ ናት፤ ብለው በመወሰናቸውና የስሜት ሕዋሳቷ ለሌላ ሀገር ዜጋም ቢሆን እንደሚሠሩ ባለማወቃቸውም እንጂ!" (ገጽ16)
"ውጭ ሀገር ስንኖር አለመከበራችን በምንም መልኩ ልክ አይደለም፤ በሰው ሀገር ስንከፋ የሚሰማን ስሜት ፣ ከራሳችን ሀገር ከሚደርስብን የጥቃት ስሜት ጋር ካነጻጸርነው ግን፣ የሕመሙ ክብደት በሰው ሀገር
ሲሆን ይቀንሳል።
ሀገር ያስከፋን ጊዜ ግን ወዴት አቤት ይባላል? የራስ ሕዝብስ ለማን ይከሰሳል?" እያለች ምሯን ትናገራለች።
እናቴ አሳዛኝና አንጀት ቆራጭ ነገሮች ሲገጥሟት፦ "ከቀላድም ባይረዝም ከመጫኛም ባይበልጥ፤
አንጀት ያልቅ የለም ወይ ሲቆረጥ ሲቆረጥ።" ትላለች ።
የማኅበረሰባዊ መገፋት አንጀት ይቆርጣል ፤ አይመልሰኝ አሰኝቶ ድንጋይ ያስወረውራል። በጊዜ ሊታረም ከዘመኑ ጋርም ሊዘምን የሚገባ እንጅ የምናጌጥበት ነውር መሆን የለበትም ።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ
ደራሲዋ እስከዳር ግርማይና መሰል የፈረንጅ ሚስቶች ያለፈና ያለን ቁስል በቃላት አስጊጣ በመግለጧ ግላዊ እፎይታ ፣ ሕሊናዊ ፈውስ አግኝተውበታል፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።
በመሰል ፈተና ውስጥ ያሉ ሰዎች የግለ ማስታወሻዎቹን ሂደትና መፍትሔ አይተው ተስፋ የሚሰጥ ትምህርት ያገኛሉ። በማኅበረሰባዊ ሂሷም ብዙዎች ራሳቸውን እንዲታዘቡ ራሳቸውን እንዲመረምሩና እንዲታረሙ ኮርኩራለች።
እስከዳር በራሷ የተወሰነ ዘመንና ማኅበረሰብ ውስጥ ለፈረንጅ ሚስት የነበረን አመለካከት ለትውልድ በማስተላለፍ የታሪክ ምስክር በመሆን፤ ለፈረንጅ ሚስቶች ሐውልት አቁማለች።
ማጠቃለያ
ደራሲ እስከዳር ግርማይ በመጽሐፏ ውስጥ 'የፈረንጅ ሚስት' የሚለውን ስም ከስድብነት ወደ ማንነት (Identity)፣ ከማንነትም ወደ ተጋድሎ (Resistance) ቀይራዋለች። ይህ መጽሐፍ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነትን እና የዘመናዊነትን (Modernity) ግጭት፣ እንዲሁም የሴትነትን ነፃነት የሚፈትን፣ ማኅበረሰባዊ ሕጸፅን ነቅሶ የሚያሳይ መስታወት ነው።
👉እስከዬ አሁንም ያላወጣሽው ብዙ ግላዊ "የመሬማውያን ጉዳይ" አለና በጥልቀት ቆፍረሽ ታወጭው ዘንድ አደራ እላለሁ 🙏
👉የፈረንጅ ሚስት በዶክመንተሪ ቢዘጋጅ ደግሞ ከንባብ የራቀውና የስድብ መጋዘን ከሆነው የማኅበረሰብ ክፍል ውስጥ በእጁ ላይ ገብተሽ ትነግሪዋለሽ። የፈረንጅ ሚስት ማለት በምን የሕይወት ሸለቆ ውስጥ አልፋ ምርጫዋን የምታስከብር እንደሆነች ታሳያቸዋለሽ።
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ከመቃብር በላይ የሚውል መልካም ስም
በአሰላ የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ መታሰቢያ ሙዚየም ተመረቀ!
#ethiopia | ባለፉት ጥቂት ሰዓታት በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ አንድ ታሪካዊ ክስተት ተከናውኗል።
በሀገርና በቤተክርስቲያን ዘንድ እጅግ የሚከበሩትና "መጋቤ በረከት" የሚል ማዕረግ የተሰጣቸው የታላቁ አባት የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ የመታሰቢያ ህንፃ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።
የልጆች ስጦታ፦
እኚህ ታላቅ አባት ካረፉ አንድ ዓመት ሲሞላቸው ልጆቻቸው ከአባታቸው የተረከቡትን በጎነት ለታሪክ እንዲተርፍ ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን ባለ ሁለት ወለል ሙዚየም ገንብተው ለምረቃ አብቅተዋል።
"ጊዳድ" መጽሐፍ፦
የአባታቸውን የህይወት ጉዞ፣ የንግድ ስኬትና የቤተሰብ አመራር ጥበብ የሚዳስሰው "ጊዳድ" የተሰኘው መጽሐፍ በጸሐፊ ሌሊሳ ኢድሪስ ተዘጋጅቶ በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ ለንባብ በቅቷል።
ታሪካዊ ምስክርነት፦
ሙዚየሙ የአባቱን መልካም ስራዎች የሚገልጹ ፎቶግራፎች፣ ቁሳቁሶችና መረጃዎችን የያዘ ሲሆን፤ አዳራሽና ቢሮዎችንም ያካተተ ዘመናዊ ህንፃ ነው።
መጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ (1949 - 2017 ዓ.ም)
በአርሲ ዞን ተወልደው በንግዱ ዓለም ስኬታማ የነበሩ ሲሆን፤ አምስት ልጆችን በስነ-ምግባር አሳድገው ለሀገር ያበቁ ታላቅ አባት ናቸው።
በቤተክርስቲያን ግንባታ፣ በማህበራዊ ልማትና በሽምግልና ስራቸው "የቱሩፋት አበጋዝ" ተብለው ይወደሳሉ።
እውነትን በመናገርና ችግረኞችን በመርዳት የሚታወቁት እኚህ አባት፣ በ68 ዓመታቸው ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ማረፋቸው ይታወሳል።
ሀብት ለራስ ብቻ ሳይሆን እንዲህ ለታሪክና ለወገን ሲተርፍ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል። የመጋቤ በረከት ግርማ ልጆች ለአባታቸው ያደረጉት ይህ ተግባር፣ ማንኛውም ሰው በህይወት ዘመኑ የሚዘራው በጎነት እንዲህ በክብር እንደሚታጨድ ማሳያ ነው። አሰላ ዛሬ የአንድ ብርቱ አባት ታሪክ ህያው ሆኖ ሲታደስ ውላለች!
መልካም ስራ ከመቃብር በላይ ይውላል!
#getu #megabebereketgirma #asella #legacy #gidatbook #ethiopianhistory #ethiopianorthodox #arsi #inspiration #መጋቤበረከትግርማ #አሰላ #ታሪክ #ጊዳድ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
በአሰላ የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ መታሰቢያ ሙዚየም ተመረቀ!
#ethiopia | ባለፉት ጥቂት ሰዓታት በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ አንድ ታሪካዊ ክስተት ተከናውኗል።
በሀገርና በቤተክርስቲያን ዘንድ እጅግ የሚከበሩትና "መጋቤ በረከት" የሚል ማዕረግ የተሰጣቸው የታላቁ አባት የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ የመታሰቢያ ህንፃ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።
የልጆች ስጦታ፦
እኚህ ታላቅ አባት ካረፉ አንድ ዓመት ሲሞላቸው ልጆቻቸው ከአባታቸው የተረከቡትን በጎነት ለታሪክ እንዲተርፍ ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን ባለ ሁለት ወለል ሙዚየም ገንብተው ለምረቃ አብቅተዋል።
"ጊዳድ" መጽሐፍ፦
የአባታቸውን የህይወት ጉዞ፣ የንግድ ስኬትና የቤተሰብ አመራር ጥበብ የሚዳስሰው "ጊዳድ" የተሰኘው መጽሐፍ በጸሐፊ ሌሊሳ ኢድሪስ ተዘጋጅቶ በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ ለንባብ በቅቷል።
ታሪካዊ ምስክርነት፦
ሙዚየሙ የአባቱን መልካም ስራዎች የሚገልጹ ፎቶግራፎች፣ ቁሳቁሶችና መረጃዎችን የያዘ ሲሆን፤ አዳራሽና ቢሮዎችንም ያካተተ ዘመናዊ ህንፃ ነው።
መጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ (1949 - 2017 ዓ.ም)
በአርሲ ዞን ተወልደው በንግዱ ዓለም ስኬታማ የነበሩ ሲሆን፤ አምስት ልጆችን በስነ-ምግባር አሳድገው ለሀገር ያበቁ ታላቅ አባት ናቸው።
በቤተክርስቲያን ግንባታ፣ በማህበራዊ ልማትና በሽምግልና ስራቸው "የቱሩፋት አበጋዝ" ተብለው ይወደሳሉ።
እውነትን በመናገርና ችግረኞችን በመርዳት የሚታወቁት እኚህ አባት፣ በ68 ዓመታቸው ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ማረፋቸው ይታወሳል።
ሀብት ለራስ ብቻ ሳይሆን እንዲህ ለታሪክና ለወገን ሲተርፍ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል። የመጋቤ በረከት ግርማ ልጆች ለአባታቸው ያደረጉት ይህ ተግባር፣ ማንኛውም ሰው በህይወት ዘመኑ የሚዘራው በጎነት እንዲህ በክብር እንደሚታጨድ ማሳያ ነው። አሰላ ዛሬ የአንድ ብርቱ አባት ታሪክ ህያው ሆኖ ሲታደስ ውላለች!
መልካም ስራ ከመቃብር በላይ ይውላል!
#getu #megabebereketgirma #asella #legacy #gidatbook #ethiopianhistory #ethiopianorthodox #arsi #inspiration #መጋቤበረከትግርማ #አሰላ #ታሪክ #ጊዳድ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ
#ethiopia | የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #tikvah #education #exam #12grade #graduated
#ethiopia | የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #tikvah #education #exam #12grade #graduated
2 months ago
የፈተና የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆነ‼️
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ይሰጣል።
seledadotio
seledadotio
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ይሰጣል።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
tikvahethiopia
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
tikvahethiopia
2 months ago
የኦሮሞን የታሪክና የጥበብ ክፍተቶችን ለመሙላት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ!
#fastmereja :የኦሮሞ ምርምር ማህበር(ORA) ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 2ኛው ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በዛሬዉ ዕለት በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል መካሄድ ጀመረ።
"የኦሮሞ የወደፊት ታሪክ፣ እውቀት፣ ባህል እና አስተዳደርን መቀረጽ'' በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ኮንፈረንስ ላይ የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የታሪክ ፕሮፌሰሮችና ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት የተጋበዙ ምሁራን ተገኝተዋል፡፡
የማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር በቀለ ጉተማ እንደገለጹት፤ ማህበሩ የተመሰረተው በኦሮሞ ታሪክ፣ ባህልና ቋንቋ ዙሪያ ያሉ የእውቀት ክፍተቶችን በመረጃ ላይ በተመሰረተ ምርምር ለመሙላት መሆኑን አስረድተዋል።
ፕሮፌሰሩ አክለውም፣ ብዙ ጊዜ የኦሮሞ ታሪክ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ብቻ ተደርጎ የሚወራው የተሳሳተ አመለካከት በምርምር ሊታረም እንደሚገባና ህዝቡ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የሚገባውን ስፍራ እንዲያገኝ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አያይዘዉ ገልፀዋል።
ማህበሩ ከተመሰረተባቸው ያለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ተገልፆ እስካሁን 7 የምርምር መጻሕፍት ለንባብ የበቁ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል በሦስት ቋንቋዎች የተዘጋጀውና የፊንፊኔን ታሪክ የሚተነትነው “ፊንፊኔ፡ ትላንትና ዛሬ" (Finfinne: Past and Present) የተሰኘው መጽሐፍ አንዱ መሆኑን ገልፀዋል።
ማህበሩ በቀጣይ ሁለት ዓመታት ውስጥ በገዳ ሥርዓት፣ በኢኮኖሚና ቢዝነስ እንዲሁም በኢሬቻ ላይ የሚያተኩሩ 6 አዳዲስ መጻሕፍትን ለማተም ዝግጅቱን ማጠናቀቁም ተጠቁሟል።
በዚህ ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ኮንፈረንስ ላይ በታሪክ፣ በፖለቲካ፣ በሀገር በቀል ፍልስፍናዎች፣ በአንትሮፖሎጂ፣ በባህልና በቋንቋ ዙሪያ ያተኮሩ 24 የምርምርና ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። ከእነዚህም መካከል ግማሽ ያህሉ ተመርጠው በመጽሐፍ መልክ እንደሚታተሙ ነዉ የተገለፀዉ።
በኮንፈረንሱ ላይ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ከኖርዌይ፣ ከጃፓን፣ ከደቡብ አፍሪካ እና ከአሜሪካ የመጡ ምሁራን በአካልና በበይነ-መረብ እየተሳተፉ የሚገኙ ሲሆን የማህበሩ ስራዎች ለኢትዮጵያ ሀገረ-መንግስት ግንባታና በህዝቦች መካከል መከባበር እንዲሰፍን ትልቅ ሚና እንዳላቸውም ተገልጿል።
#fastmereja :የኦሮሞ ምርምር ማህበር(ORA) ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 2ኛው ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በዛሬዉ ዕለት በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል መካሄድ ጀመረ።
"የኦሮሞ የወደፊት ታሪክ፣ እውቀት፣ ባህል እና አስተዳደርን መቀረጽ'' በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ኮንፈረንስ ላይ የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የታሪክ ፕሮፌሰሮችና ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት የተጋበዙ ምሁራን ተገኝተዋል፡፡
የማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር በቀለ ጉተማ እንደገለጹት፤ ማህበሩ የተመሰረተው በኦሮሞ ታሪክ፣ ባህልና ቋንቋ ዙሪያ ያሉ የእውቀት ክፍተቶችን በመረጃ ላይ በተመሰረተ ምርምር ለመሙላት መሆኑን አስረድተዋል።
ፕሮፌሰሩ አክለውም፣ ብዙ ጊዜ የኦሮሞ ታሪክ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ብቻ ተደርጎ የሚወራው የተሳሳተ አመለካከት በምርምር ሊታረም እንደሚገባና ህዝቡ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የሚገባውን ስፍራ እንዲያገኝ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አያይዘዉ ገልፀዋል።
ማህበሩ ከተመሰረተባቸው ያለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ተገልፆ እስካሁን 7 የምርምር መጻሕፍት ለንባብ የበቁ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል በሦስት ቋንቋዎች የተዘጋጀውና የፊንፊኔን ታሪክ የሚተነትነው “ፊንፊኔ፡ ትላንትና ዛሬ" (Finfinne: Past and Present) የተሰኘው መጽሐፍ አንዱ መሆኑን ገልፀዋል።
ማህበሩ በቀጣይ ሁለት ዓመታት ውስጥ በገዳ ሥርዓት፣ በኢኮኖሚና ቢዝነስ እንዲሁም በኢሬቻ ላይ የሚያተኩሩ 6 አዳዲስ መጻሕፍትን ለማተም ዝግጅቱን ማጠናቀቁም ተጠቁሟል።
በዚህ ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ኮንፈረንስ ላይ በታሪክ፣ በፖለቲካ፣ በሀገር በቀል ፍልስፍናዎች፣ በአንትሮፖሎጂ፣ በባህልና በቋንቋ ዙሪያ ያተኮሩ 24 የምርምርና ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። ከእነዚህም መካከል ግማሽ ያህሉ ተመርጠው በመጽሐፍ መልክ እንደሚታተሙ ነዉ የተገለፀዉ።
በኮንፈረንሱ ላይ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ከኖርዌይ፣ ከጃፓን፣ ከደቡብ አፍሪካ እና ከአሜሪካ የመጡ ምሁራን በአካልና በበይነ-መረብ እየተሳተፉ የሚገኙ ሲሆን የማህበሩ ስራዎች ለኢትዮጵያ ሀገረ-መንግስት ግንባታና በህዝቦች መካከል መከባበር እንዲሰፍን ትልቅ ሚና እንዳላቸውም ተገልጿል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የደራሲው 30ኛ መጽሐፍ
ቀሚሳም
#ethiopia | የደራሲ ዘላለም የሳጥንወርቅ - "ቀሚሳም" ርዕስ የያዘ 30ኛ መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል።
ደራሲው በአሥር አመታት ውስጥ 30 መጽሐፍት የጻፈ ሲሆን በቀጣይ በአዳዲስ ስራዎች እንደሚመጣ ተናግሯል::
ከልጅነት የመሆን መሻት ውስጥ በዳዴ ያልተቀደሙ ባለቀለም ምናቦች... ቁጡ መላክ ሰይፍ ላይ ወደቁ..."እንዳትቆም.. እንዳትተኛ" እንሆ . . በመንፈቀ ለሊት የተወለዱ ቃል እና ህይወት! . . እፎይ!!
በአስር አመታት ውስጥ በደራሲው የተጻፉ
እፀ ሳቤቅ
እፀ ጦስ
አፀ ሲና
ብኤልዜቡል
ብስለት
ስቶስጥራ
ሽርፍራፊ ልቦች
ፍካት እና ንጋት
ሰውነት
የህይወት ዋጋ
ፊት እና ኀላ
አዳፋ ነፍሶች
እንደ ፍቅር
እውነት
አሁን
የነፍስ ዜማ
ጌጣም አልቦዎች
ልጃገረድ ልብ
የህይወት ህግ
ዝም
ጥቁር ነኝ
ትርታ
ብር አምባር
ታላቅነት
የኔ ማር
ቦሌ ኤድናሞል ጋ
ልባም ሴት
ኑሮ በዘዴ
ማንነት
ቀ ሚ ሳ ሞ
መጽሐፉ ለገሀር በሚገኘው ጃፋር መጽሐፍት መደብር ይገኛል::
ቀሚሳም
#ethiopia | የደራሲ ዘላለም የሳጥንወርቅ - "ቀሚሳም" ርዕስ የያዘ 30ኛ መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል።
ደራሲው በአሥር አመታት ውስጥ 30 መጽሐፍት የጻፈ ሲሆን በቀጣይ በአዳዲስ ስራዎች እንደሚመጣ ተናግሯል::
ከልጅነት የመሆን መሻት ውስጥ በዳዴ ያልተቀደሙ ባለቀለም ምናቦች... ቁጡ መላክ ሰይፍ ላይ ወደቁ..."እንዳትቆም.. እንዳትተኛ" እንሆ . . በመንፈቀ ለሊት የተወለዱ ቃል እና ህይወት! . . እፎይ!!
በአስር አመታት ውስጥ በደራሲው የተጻፉ
እፀ ሳቤቅ
እፀ ጦስ
አፀ ሲና
ብኤልዜቡል
ብስለት
ስቶስጥራ
ሽርፍራፊ ልቦች
ፍካት እና ንጋት
ሰውነት
የህይወት ዋጋ
ፊት እና ኀላ
አዳፋ ነፍሶች
እንደ ፍቅር
እውነት
አሁን
የነፍስ ዜማ
ጌጣም አልቦዎች
ልጃገረድ ልብ
የህይወት ህግ
ዝም
ጥቁር ነኝ
ትርታ
ብር አምባር
ታላቅነት
የኔ ማር
ቦሌ ኤድናሞል ጋ
ልባም ሴት
ኑሮ በዘዴ
ማንነት
ቀ ሚ ሳ ሞ
መጽሐፉ ለገሀር በሚገኘው ጃፋር መጽሐፍት መደብር ይገኛል::
2 months ago
ኦሮሞ ምርምር ማኅከልና የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከል በጥምረት የተዘጋጀውሁለተኛ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ Ethiopian SkylightHotel እየተካሄደ ነው።
የኦሮሞ ምርምር ማኅከል እአአ በ2022 በተለያዩ ዘርፎች ላይበኦሮሞ ዙሪያ ምርምር ለማካሄድ ተመሰረተ፡፡በዚሁ መሰረትባለፉት አራት ዓመታት የኦሮሞ ባህል፣ ታሪክ፣ፍልስፍና፣ምጣኔሃብት፣ቋንቀቋ እና በመሳሰሉት ዘርፎች ላይ ምርምር በማድረግበመጵሐፍ መልክ ማሳተም ችሏል።
ይህ ማኅበር የተመሰረተው ከሌሎች ተመሳሳይ ዘርፍ ላይበተሰማሩት ተቋማት ለምሳሌ ያህል እንደ Oromo StudiesAssociation (OSA) እና በለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትውስጥ (የግልና የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች) በተቋቋሙት ጋርለመወዳደር ሳይሆን በሉት ክፍተቶችን በመሙላትና በትብብርአብሮ ለመስራት ነው። ስለዚህ አብረን በመሆን የሰፊውን ኦሮሞህዝብ ተሪክና ዘርፈ-ብዙ ምርምሮች አድርገን ወደፊትእንራመዳለን።
እንደሚታወቀው የኦሮሞ ህዝብ በሚንኖርበት የመሬት በቆዳስፋትና ብዛት ግዙፍ ህዝብ ነው። ከመሬት ቆዳ ስፋትና ብዛትባሻገር፣ ኦሮሞ የብዝሃ-በህል፣ ፍልስፍና፣ታሪክ፣ፖለቲካ፣እሴት፣የአከባቢ ጥበቃ፣ህክምናና የመሳሰሉትባለቤት ነው። ይሁን እንጂ እነዚህን ዘርፈ-ብዙ ታርኮችን በቂምርምሮችን በማድረግ ለማውጣትና ለትውልድ ለማስተላለፍበተለያዩ ምክንያቶች እድል ሳያገኝ ቀርቷል። አሁን ግን አነዚህንሀገር በቀል እውቀቶችን ወደ ጎን የማግፋት ጊዜ ለይመለስአብቅቷል። በዓለም-አቀፍ ደረጃም ብሆን በተለያዩ አሳማኝምክንያቶች ሀገራትና ህዝቦች ወደ ቀደምት ማንነታቸው ለመመለስ እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸው ይታወቃል። ስለዚህይህንን የዓለም ለውጥ ውስጥ የኦሮሞን ታሪክና ዘርፈ-ብዙ ሀገርበቀል እውቀቶችን ከተደበቁበት ለማውጣና ትውልድንለማስተማር የኦሮሞ ምርምር ማኅከል መመስረት በጣም ወሳኝናአስፈላጊ ነው።
ይህንኑ ዓላማ በመያዝ የተመሠረተው ማኅከላችንየመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ በማድረግናየተለያዩ መጵሐፍትን በእንግሊዘኛ፣ በአፋን ኦሮሞና አማርኛቋንቋ አሳትሞ በራሱ መጵሐፍት መሸጫ አቋቋሞ ለአንባብያንአድርሷል። አሁን ደግሞ ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከል ጋር በመተባበርበጥምረት ሁለተኛ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ "ስር-መሠረታችንን ማክበር፣ ነገያችንን መቅረፅ: የኦሮሞታሪክ፣እውቀት፣በህልና አስተዳደር፣ ድሮ፣ዘንድሮና ወደፊት"በሚል መሪ ርዕስ አዘጋጅቷል። የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከልየበህል፣ወግ፣ትውፊት፣ስነ-ፅሑፍና ስነ-ጥበብ ላይ ምርምርበማድረግና በትያትር መልክ ለማህበረሰብ በመድረስ ላይ ይገኛል።
በEthiopian Skylight Hotel በመካሄድ ላይ በሚገኘው ሁለተኛዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ላይ 25 የተመረጡ ኦሮሞ ላይየሚያጠነጥኑ የምርምር ፅሑፎች ይቀርባሉ። እነዚህ የጥናትፅሑፎች አዳዲስና ጠቃሚ መረጃዎችንና እውቀትእንደሚያመነጩ ተስፋ እናደርጋለን።
ኦሮሞ ምርምር ማኅከልና የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከል በጥምረት የተዘጋጀውሁለተኛ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ Ethiopian SkylightHotel እየተካሄደ ነው።
የኦሮሞ ምርምር ማኅከል እአአ በ2022 በተለያዩ ዘርፎች ላይበኦሮሞ ዙሪያ ምርምር ለማካሄድ ተመሰረተ፡፡በዚሁ መሰረትባለፉት አራት ዓመታት የኦሮሞ ባህል፣ ታሪክ፣ፍልስፍና፣ምጣኔሃብት፣ቋንቀቋ እና በመሳሰሉት ዘርፎች ላይ ምርምር በማድረግበመጵሐፍ መልክ ማሳተም ችሏል።
ይህ ማኅበር የተመሰረተው ከሌሎች ተመሳሳይ ዘርፍ ላይበተሰማሩት ተቋማት ለምሳሌ ያህል እንደ Oromo StudiesAssociation (OSA) እና በለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትውስጥ (የግልና የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች) በተቋቋሙት ጋርለመወዳደር ሳይሆን በሉት ክፍተቶችን በመሙላትና በትብብርአብሮ ለመስራት ነው። ስለዚህ አብረን በመሆን የሰፊውን ኦሮሞህዝብ ተሪክና ዘርፈ-ብዙ ምርምሮች አድርገን ወደፊትእንራመዳለን።
እንደሚታወቀው የኦሮሞ ህዝብ በሚንኖርበት የመሬት በቆዳስፋትና ብዛት ግዙፍ ህዝብ ነው። ከመሬት ቆዳ ስፋትና ብዛትባሻገር፣ ኦሮሞ የብዝሃ-በህል፣ ፍልስፍና፣ታሪክ፣ፖለቲካ፣እሴት፣የአከባቢ ጥበቃ፣ህክምናና የመሳሰሉትባለቤት ነው። ይሁን እንጂ እነዚህን ዘርፈ-ብዙ ታርኮችን በቂምርምሮችን በማድረግ ለማውጣትና ለትውልድ ለማስተላለፍበተለያዩ ምክንያቶች እድል ሳያገኝ ቀርቷል። አሁን ግን አነዚህንሀገር በቀል እውቀቶችን ወደ ጎን የማግፋት ጊዜ ለይመለስአብቅቷል። በዓለም-አቀፍ ደረጃም ብሆን በተለያዩ አሳማኝምክንያቶች ሀገራትና ህዝቦች ወደ ቀደምት ማንነታቸው ለመመለስ እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸው ይታወቃል። ስለዚህይህንን የዓለም ለውጥ ውስጥ የኦሮሞን ታሪክና ዘርፈ-ብዙ ሀገርበቀል እውቀቶችን ከተደበቁበት ለማውጣና ትውልድንለማስተማር የኦሮሞ ምርምር ማኅከል መመስረት በጣም ወሳኝናአስፈላጊ ነው።
ይህንኑ ዓላማ በመያዝ የተመሠረተው ማኅከላችንየመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ በማድረግናየተለያዩ መጵሐፍትን በእንግሊዘኛ፣ በአፋን ኦሮሞና አማርኛቋንቋ አሳትሞ በራሱ መጵሐፍት መሸጫ አቋቋሞ ለአንባብያንአድርሷል። አሁን ደግሞ ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከል ጋር በመተባበርበጥምረት ሁለተኛ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ "ስር-መሠረታችንን ማክበር፣ ነገያችንን መቅረፅ: የኦሮሞታሪክ፣እውቀት፣በህልና አስተዳደር፣ ድሮ፣ዘንድሮና ወደፊት"በሚል መሪ ርዕስ አዘጋጅቷል። የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከልየበህል፣ወግ፣ትውፊት፣ስነ-ፅሑፍና ስነ-ጥበብ ላይ ምርምርበማድረግና በትያትር መልክ ለማህበረሰብ በመድረስ ላይ ይገኛል።
በEthiopian Skylight Hotel በመካሄድ ላይ በሚገኘው ሁለተኛዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ላይ 25 የተመረጡ ኦሮሞ ላይየሚያጠነጥኑ የምርምር ፅሑፎች ይቀርባሉ። እነዚህ የጥናትፅሑፎች አዳዲስና ጠቃሚ መረጃዎችንና እውቀትእንደሚያመነጩ ተስፋ እናደርጋለን።
ኮንፈረንሱ ላይ የቀድሞ የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) እና ብርሃኑ መገርሳ ሌንጂሶ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታን ጨምሮ ከመላው ኢትዮጵያ የተወጣጡ ምሁራን፣የታሪክ ጸሐፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኦሮሞ ምርምር ማኅከል እአአ በ2022 በተለያዩ ዘርፎች ላይበኦሮሞ ዙሪያ ምርምር ለማካሄድ ተመሰረተ፡፡በዚሁ መሰረትባለፉት አራት ዓመታት የኦሮሞ ባህል፣ ታሪክ፣ፍልስፍና፣ምጣኔሃብት፣ቋንቀቋ እና በመሳሰሉት ዘርፎች ላይ ምርምር በማድረግበመጵሐፍ መልክ ማሳተም ችሏል።
ይህ ማኅበር የተመሰረተው ከሌሎች ተመሳሳይ ዘርፍ ላይበተሰማሩት ተቋማት ለምሳሌ ያህል እንደ Oromo StudiesAssociation (OSA) እና በለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትውስጥ (የግልና የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች) በተቋቋሙት ጋርለመወዳደር ሳይሆን በሉት ክፍተቶችን በመሙላትና በትብብርአብሮ ለመስራት ነው። ስለዚህ አብረን በመሆን የሰፊውን ኦሮሞህዝብ ተሪክና ዘርፈ-ብዙ ምርምሮች አድርገን ወደፊትእንራመዳለን።
እንደሚታወቀው የኦሮሞ ህዝብ በሚንኖርበት የመሬት በቆዳስፋትና ብዛት ግዙፍ ህዝብ ነው። ከመሬት ቆዳ ስፋትና ብዛትባሻገር፣ ኦሮሞ የብዝሃ-በህል፣ ፍልስፍና፣ታሪክ፣ፖለቲካ፣እሴት፣የአከባቢ ጥበቃ፣ህክምናና የመሳሰሉትባለቤት ነው። ይሁን እንጂ እነዚህን ዘርፈ-ብዙ ታርኮችን በቂምርምሮችን በማድረግ ለማውጣትና ለትውልድ ለማስተላለፍበተለያዩ ምክንያቶች እድል ሳያገኝ ቀርቷል። አሁን ግን አነዚህንሀገር በቀል እውቀቶችን ወደ ጎን የማግፋት ጊዜ ለይመለስአብቅቷል። በዓለም-አቀፍ ደረጃም ብሆን በተለያዩ አሳማኝምክንያቶች ሀገራትና ህዝቦች ወደ ቀደምት ማንነታቸው ለመመለስ እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸው ይታወቃል። ስለዚህይህንን የዓለም ለውጥ ውስጥ የኦሮሞን ታሪክና ዘርፈ-ብዙ ሀገርበቀል እውቀቶችን ከተደበቁበት ለማውጣና ትውልድንለማስተማር የኦሮሞ ምርምር ማኅከል መመስረት በጣም ወሳኝናአስፈላጊ ነው።
ይህንኑ ዓላማ በመያዝ የተመሠረተው ማኅከላችንየመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ በማድረግናየተለያዩ መጵሐፍትን በእንግሊዘኛ፣ በአፋን ኦሮሞና አማርኛቋንቋ አሳትሞ በራሱ መጵሐፍት መሸጫ አቋቋሞ ለአንባብያንአድርሷል። አሁን ደግሞ ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከል ጋር በመተባበርበጥምረት ሁለተኛ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ "ስር-መሠረታችንን ማክበር፣ ነገያችንን መቅረፅ: የኦሮሞታሪክ፣እውቀት፣በህልና አስተዳደር፣ ድሮ፣ዘንድሮና ወደፊት"በሚል መሪ ርዕስ አዘጋጅቷል። የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከልየበህል፣ወግ፣ትውፊት፣ስነ-ፅሑፍና ስነ-ጥበብ ላይ ምርምርበማድረግና በትያትር መልክ ለማህበረሰብ በመድረስ ላይ ይገኛል።
በEthiopian Skylight Hotel በመካሄድ ላይ በሚገኘው ሁለተኛዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ላይ 25 የተመረጡ ኦሮሞ ላይየሚያጠነጥኑ የምርምር ፅሑፎች ይቀርባሉ። እነዚህ የጥናትፅሑፎች አዳዲስና ጠቃሚ መረጃዎችንና እውቀትእንደሚያመነጩ ተስፋ እናደርጋለን።
ኦሮሞ ምርምር ማኅከልና የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከል በጥምረት የተዘጋጀውሁለተኛ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ Ethiopian SkylightHotel እየተካሄደ ነው።
የኦሮሞ ምርምር ማኅከል እአአ በ2022 በተለያዩ ዘርፎች ላይበኦሮሞ ዙሪያ ምርምር ለማካሄድ ተመሰረተ፡፡በዚሁ መሰረትባለፉት አራት ዓመታት የኦሮሞ ባህል፣ ታሪክ፣ፍልስፍና፣ምጣኔሃብት፣ቋንቀቋ እና በመሳሰሉት ዘርፎች ላይ ምርምር በማድረግበመጵሐፍ መልክ ማሳተም ችሏል።
ይህ ማኅበር የተመሰረተው ከሌሎች ተመሳሳይ ዘርፍ ላይበተሰማሩት ተቋማት ለምሳሌ ያህል እንደ Oromo StudiesAssociation (OSA) እና በለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትውስጥ (የግልና የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች) በተቋቋሙት ጋርለመወዳደር ሳይሆን በሉት ክፍተቶችን በመሙላትና በትብብርአብሮ ለመስራት ነው። ስለዚህ አብረን በመሆን የሰፊውን ኦሮሞህዝብ ተሪክና ዘርፈ-ብዙ ምርምሮች አድርገን ወደፊትእንራመዳለን።
እንደሚታወቀው የኦሮሞ ህዝብ በሚንኖርበት የመሬት በቆዳስፋትና ብዛት ግዙፍ ህዝብ ነው። ከመሬት ቆዳ ስፋትና ብዛትባሻገር፣ ኦሮሞ የብዝሃ-በህል፣ ፍልስፍና፣ታሪክ፣ፖለቲካ፣እሴት፣የአከባቢ ጥበቃ፣ህክምናና የመሳሰሉትባለቤት ነው። ይሁን እንጂ እነዚህን ዘርፈ-ብዙ ታርኮችን በቂምርምሮችን በማድረግ ለማውጣትና ለትውልድ ለማስተላለፍበተለያዩ ምክንያቶች እድል ሳያገኝ ቀርቷል። አሁን ግን አነዚህንሀገር በቀል እውቀቶችን ወደ ጎን የማግፋት ጊዜ ለይመለስአብቅቷል። በዓለም-አቀፍ ደረጃም ብሆን በተለያዩ አሳማኝምክንያቶች ሀገራትና ህዝቦች ወደ ቀደምት ማንነታቸው ለመመለስ እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸው ይታወቃል። ስለዚህይህንን የዓለም ለውጥ ውስጥ የኦሮሞን ታሪክና ዘርፈ-ብዙ ሀገርበቀል እውቀቶችን ከተደበቁበት ለማውጣና ትውልድንለማስተማር የኦሮሞ ምርምር ማኅከል መመስረት በጣም ወሳኝናአስፈላጊ ነው።
ይህንኑ ዓላማ በመያዝ የተመሠረተው ማኅከላችንየመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ በማድረግናየተለያዩ መጵሐፍትን በእንግሊዘኛ፣ በአፋን ኦሮሞና አማርኛቋንቋ አሳትሞ በራሱ መጵሐፍት መሸጫ አቋቋሞ ለአንባብያንአድርሷል። አሁን ደግሞ ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከል ጋር በመተባበርበጥምረት ሁለተኛ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ "ስር-መሠረታችንን ማክበር፣ ነገያችንን መቅረፅ: የኦሮሞታሪክ፣እውቀት፣በህልና አስተዳደር፣ ድሮ፣ዘንድሮና ወደፊት"በሚል መሪ ርዕስ አዘጋጅቷል። የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሎሬት ፀጋዬገ/መድህን የበህል ጥናትና ምርምር ማዕከልየበህል፣ወግ፣ትውፊት፣ስነ-ፅሑፍና ስነ-ጥበብ ላይ ምርምርበማድረግና በትያትር መልክ ለማህበረሰብ በመድረስ ላይ ይገኛል።
በEthiopian Skylight Hotel በመካሄድ ላይ በሚገኘው ሁለተኛዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ላይ 25 የተመረጡ ኦሮሞ ላይየሚያጠነጥኑ የምርምር ፅሑፎች ይቀርባሉ። እነዚህ የጥናትፅሑፎች አዳዲስና ጠቃሚ መረጃዎችንና እውቀትእንደሚያመነጩ ተስፋ እናደርጋለን።
ኮንፈረንሱ ላይ የቀድሞ የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) እና ብርሃኑ መገርሳ ሌንጂሶ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታን ጨምሮ ከመላው ኢትዮጵያ የተወጣጡ ምሁራን፣የታሪክ ጸሐፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
2 months ago
56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መሸጫ ተመሰገነ
#ethiopia | ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ " ትውልድን በስነ ጽሑፍ ማስተሳሰር " በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የመጻሕፍ አውደ ርእይ እና የውይይት መድረክ ላይ 56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መደብር ተመሰገነ።
በዚህ የለባዊ አካዳሚ የተማሪዎች ካውንስልና የቤተ መጻሕፍ ሰራተኞች በጋር በመሆን በአዘጋጁት መድረክ ላይ ነው የዕውቀት በር መጻሕፍ መደብርን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው አቶ ደመላሽ ከበደ የአባቱን ርእይ በማስቀጠል ለአደረገው አበርክቶ ከለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ የምስጋና ሰርተፍኬት የተሰጠው።
በምስጋና መድረኩ ላይ እንደ ደምመላሽ ከበደ የቤተሰብን ርእይ የሚያስቀጥሉና ንባብ ባህል እንዲሆን የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ያስፈልጉናል ተብሏል።
አካዳሚው የአዘጋጀውን የአውደ ርእይና የውይይት መድረክ በንግግር የከፈቱት የለባዊ መስራች እና ዳሬክተር ፓኖስ ሐዛንድሪያስ (ፕር) በንግግራቸው ለባዊ አንባቢ ተማሪዎችን ለማፍራት ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ ይህ ደራሲያንን ፣ አሳታሚያንን እና ባለመደብሮችን እየጋበዘ የሚያዘጋጀው የውይይት መድርክ ነው ብለዋል።
በዕለቱ የተጋበዙት ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ኃያልነህ ሙላት፣ የፀሐይ አሳታሚ መስራችና ስራ አሰኪያጅ አቶ ኤሊያስ ወንድሙ እና ባለብዙ ተሰጠዋ ወት ሊያ ባፈና ሰለስነ ጽሑፍ ያላቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን ስለየዕውቀት በርም ታሪክ ለተማሪዎቹ አጋርተዋል።
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ ኢትዮጵያዊነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ የትምህርት ስርዓት ቀርጾ ልዩ ፍላጎትን ጨምሮ ከመዋለ ህጻናት እሰከ አስራ ሁለተኛ ክፍል እያስተማር እንዲሚገኝ ይታወቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ " ትውልድን በስነ ጽሑፍ ማስተሳሰር " በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የመጻሕፍ አውደ ርእይ እና የውይይት መድረክ ላይ 56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መደብር ተመሰገነ።
በዚህ የለባዊ አካዳሚ የተማሪዎች ካውንስልና የቤተ መጻሕፍ ሰራተኞች በጋር በመሆን በአዘጋጁት መድረክ ላይ ነው የዕውቀት በር መጻሕፍ መደብርን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው አቶ ደመላሽ ከበደ የአባቱን ርእይ በማስቀጠል ለአደረገው አበርክቶ ከለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ የምስጋና ሰርተፍኬት የተሰጠው።
በምስጋና መድረኩ ላይ እንደ ደምመላሽ ከበደ የቤተሰብን ርእይ የሚያስቀጥሉና ንባብ ባህል እንዲሆን የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ያስፈልጉናል ተብሏል።
አካዳሚው የአዘጋጀውን የአውደ ርእይና የውይይት መድረክ በንግግር የከፈቱት የለባዊ መስራች እና ዳሬክተር ፓኖስ ሐዛንድሪያስ (ፕር) በንግግራቸው ለባዊ አንባቢ ተማሪዎችን ለማፍራት ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ ይህ ደራሲያንን ፣ አሳታሚያንን እና ባለመደብሮችን እየጋበዘ የሚያዘጋጀው የውይይት መድርክ ነው ብለዋል።
በዕለቱ የተጋበዙት ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ኃያልነህ ሙላት፣ የፀሐይ አሳታሚ መስራችና ስራ አሰኪያጅ አቶ ኤሊያስ ወንድሙ እና ባለብዙ ተሰጠዋ ወት ሊያ ባፈና ሰለስነ ጽሑፍ ያላቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን ስለየዕውቀት በርም ታሪክ ለተማሪዎቹ አጋርተዋል።
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ ኢትዮጵያዊነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ የትምህርት ስርዓት ቀርጾ ልዩ ፍላጎትን ጨምሮ ከመዋለ ህጻናት እሰከ አስራ ሁለተኛ ክፍል እያስተማር እንዲሚገኝ ይታወቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
2 months ago
56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መሸጫ ተመሰገነ
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ " ትውልድን በስነ ጽሑፍ ማስተሳሰር " በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የመጻሕፍ አውደ ርእይ እና የውይይት መድረክ ላይ 56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መደብር ተመሰገነ።
በዚህ የለባዊ አካዳሚ የተማሪዎች ካውንስልና የቤተ መጻሕፍ ሰራተኞች በጋር በመሆን በአዘጋጁት መድረክ ላይ ነው የዕውቀት በር መጻሕፍ መደብርን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው አቶ ደመላሽ ከበደ የአባቱን ርእይ በማስቀጠል ለአደረገው አበርክቶ ከለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ የምስጋና ሰርተፍኬት የተሰጠው።
በምስጋና መድረኩ ላይ እንደ ደምመላሽ ከበደ የቤተሰብን ርእይ የሚያስቀጥሉና ንባብ ባህል እንዲሆን የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ያስፈልጉናል ተብሏል።
አካዳሚው የአዘጋጀውን የአውደ ርእይና የውይይት መድረክ በንግግር የከፈቱት የለባዊ መስራች እና ዳሬክተር ፓኖስ ሐዛንድሪያስ (ፕር) በንግግራቸው ለባዊ አንባቢ ተማሪዎችን ለማፍራት ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ ይህ ደራሲያንን ፣ አሳታሚያንን እና ባለመደብሮችን እየጋበዘ የሚያዘጋጀው የውይይት መድርክ ነው ብለዋል።
በዕለቱ የተጋበዙት ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ኃያልነህ ሙላት፣ የፀሐይ አሳታሚ መስራችና ስራ አሰኪያጅ አቶ ኤሊያስ ወንድሙ እና ባለብዙ ተሰጠዋ ወት ሊያ ባፈና ሰለስነ ጽሑፍ ያላቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን ስለየዕውቀት በርም ታሪክ ለተማሪዎቹ አጋርተዋል።
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ ኢትዮጵያዊነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ የትምህርት ስርዓት ቀርጾ ልዩ ፍላጎትን ጨምሮ ከመዋለ ህጻናት እሰከ አስራ ሁለተኛ ክፍል እያስተማር እንዲሚገኝ ይታወቃል።
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ " ትውልድን በስነ ጽሑፍ ማስተሳሰር " በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የመጻሕፍ አውደ ርእይ እና የውይይት መድረክ ላይ 56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መደብር ተመሰገነ።
በዚህ የለባዊ አካዳሚ የተማሪዎች ካውንስልና የቤተ መጻሕፍ ሰራተኞች በጋር በመሆን በአዘጋጁት መድረክ ላይ ነው የዕውቀት በር መጻሕፍ መደብርን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው አቶ ደመላሽ ከበደ የአባቱን ርእይ በማስቀጠል ለአደረገው አበርክቶ ከለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ የምስጋና ሰርተፍኬት የተሰጠው።
በምስጋና መድረኩ ላይ እንደ ደምመላሽ ከበደ የቤተሰብን ርእይ የሚያስቀጥሉና ንባብ ባህል እንዲሆን የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ያስፈልጉናል ተብሏል።
አካዳሚው የአዘጋጀውን የአውደ ርእይና የውይይት መድረክ በንግግር የከፈቱት የለባዊ መስራች እና ዳሬክተር ፓኖስ ሐዛንድሪያስ (ፕር) በንግግራቸው ለባዊ አንባቢ ተማሪዎችን ለማፍራት ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ ይህ ደራሲያንን ፣ አሳታሚያንን እና ባለመደብሮችን እየጋበዘ የሚያዘጋጀው የውይይት መድርክ ነው ብለዋል።
በዕለቱ የተጋበዙት ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ኃያልነህ ሙላት፣ የፀሐይ አሳታሚ መስራችና ስራ አሰኪያጅ አቶ ኤሊያስ ወንድሙ እና ባለብዙ ተሰጠዋ ወት ሊያ ባፈና ሰለስነ ጽሑፍ ያላቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን ስለየዕውቀት በርም ታሪክ ለተማሪዎቹ አጋርተዋል።
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ ኢትዮጵያዊነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ የትምህርት ስርዓት ቀርጾ ልዩ ፍላጎትን ጨምሮ ከመዋለ ህጻናት እሰከ አስራ ሁለተኛ ክፍል እያስተማር እንዲሚገኝ ይታወቃል።
Sponsored by
Surafel
Comments