2 hours ago
በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፍራንስ 24 ምርጫውን አስመልክቶ በሰራው ዘገባ ላይ የአዲስ አበባን ልማት “አስከፊ” ብሎ በመፈረጅ ያሰራጨው ዘገባ የያዛቸው መረጃዎች “ከእውነት የራቁ ናቸው” አለ
#ethiopia | በፈረንሳይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ፍራንስ 24 ባለፈው ሰኞ የተካሄደውን 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በተመለከተ በሰራው ዘገባ “ምርጫውን የይስሙላ” እንዲሁም የአዲስ አበባን ልማት “አስከፊ” ሲል መግለጹ፣ ኢትዮጵያ ያለችበንት ሁኔታ እና እውነታ ያላገናዘበ ነው ሲል የተቃውሞ መግለጫ አውጥቷል።
ኤምባሲው ፍራንስ 24 የቴሌቪዥን ጣቢያ ከሳቢን ፕላኔል ከተባሉ “እንግዳ” ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ፤ የቀረቡትን ሀሳቦች፣ አሳሳችና ወገንተኝነት የተሞላባቸው ትችቶች ናቸው በማለት በጽኑ እንደሚቃወም አስታውቋል፡፡ ኤምባሲው ባወጣው መግለጫ የጣቢያው ዘገባ የሀገሪቱን ነባራዊ እውነታም ሆነ የመንግሥትን ሰፊ ጥረቶች የማያንጸባርቅ አሳሳች ትርክት ነው ሲል ፈርጆታል።
አክሎም ባለፉት ዓመታት ተመዝግበዋል ያላቸው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ስኬቶችን ወደ ጎን በመተው አስተዳደሩን በ“እርስ በርስ ጦርነት” ብቻ ከፋፍሎ ለመግለጽ የተደረገው ሙከራ ማጋነንና ከተጨባጭ እውነታ የራቀ መሆኑን ጠቅሷል። ኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ቀጣናዊ ሁኔታዎች ውስጥም ሆና በዋና ዋና ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የተመሰከረለትን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግባለች ሲል ምላሽ ሰጥቷል።
በተጨማሪም የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና የመሠረተ ልማት ማዘመን ሥራዎችን “አስከፊ” ሲል የገለጸበትን አግባብ፣ ኤምባሲው ውድቅ እንደሚያደርገው በመግለጽ ይህ የልማት ፕሮጀክት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ሕይወት እየቀየረ ያለና በዋና ከተማዋም ሆነ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች በከፍተኛ ደረጃ አድናቆት የተቸረው ስኬት ነው በማለት አወድሷል።
ኤምባሲው አክሎም በምርጫው ላይ ስለአሳታፊነትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን አስመልክቶ የሰራውና የተቸበት መንገድ በስህተት የተሞሉ ናቸው ሲል በጽኑ ነቅፏል። የፈረንሳዩ የዜና አውታር በሰራው ዘገባ “በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ግማሽ ያህሉ የምርጫ ክልሎች አልመረጡም” ማለቱን በተመለከተ ደግሞ ይህ መረጃ ሙሉ በሙሉ ሐሰት መሆኑን ኤምባሲው በአሐዛዊ መረጃዎች አስደግፎ ተከላክሏል።
ለአብነትም “በአማራ ክልል ከ138 የምርጫ ክልል በስምንቱ ብቻ አለመካሄዱን በመጥቀስ፣ ይህም ከክልሉ አጠቃላይ ቁጥር 6 በመቶ ብቻ መሆኑን” አመልክቷል።
እንዲሁም በቴክኖሎጂ እና አጠቃላይ ሂደቱ ዲሞክራሲን የተከተለ መሆኑን በመግለጽ መገናኛ ብዙኃኑ የሰራቸው እና ያሰራጫቸው መረጃዎች እውነታን ያላገናዘቡ ናቸው ሲል አጣጥሏል፡፡
ምርጫው በተለይም በዴሞክራሲ ምህዳር መስፋትና መገናኛ ብዙኃን ተሳትፎ ዙሪያ የይስሙላ እንደነበር በዘገባው መጠቀሱን ያወሳው መግለጫው፤ የተመራጮችን፣ የሲቪል ማህበራት፣ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ ታዛቢዎችን፣ የሚዲያ ብዛት እና የሚዘግቡ ጋዜጠኞችን ቁጥር እንዲሁም በአጠቃላይ ምርጫው ላይ ያሉ ቁጥሮችን በመጥቀስ ውድቅ አድርጎታል።
ኤምባሲው አክሎም ሚዲያው የውጭ ወገኖችን ማለትም የአፍሪካ ሕብረት እና የኢጋድን ታዛቢዎችን ሚና ለማሳነስ “ትላልቅ ግድፈቶችን ሪፖርት አያደርጉም” ማለቱ የተቋማቱን ስራ ማሳነስ ነው ብሎታል ። የሁለቱንም ተቋማት ልዑካን የሚመሩትን ኃላፊዎች ማንነት በመግለጽ አንጋፋ ተቋማትና መሪዎችን ማጣጣል የአስተሳሰብ አድሏዊነት ማሳያ ነው በማለት ኮንኖታል።
በመጨረሻም የዚህ ምርጫ ውጤት የሀገሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወሰነው በራሱ በኢትዮጵያ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንጂ ከውጭ በሚሰጡ መግለጫዎችና አስተያየቶች አይደለም ሲል አስታውቋል።
#አዲስ_ማለዳ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen
#ethiopia | በፈረንሳይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ፍራንስ 24 ባለፈው ሰኞ የተካሄደውን 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በተመለከተ በሰራው ዘገባ “ምርጫውን የይስሙላ” እንዲሁም የአዲስ አበባን ልማት “አስከፊ” ሲል መግለጹ፣ ኢትዮጵያ ያለችበንት ሁኔታ እና እውነታ ያላገናዘበ ነው ሲል የተቃውሞ መግለጫ አውጥቷል።
ኤምባሲው ፍራንስ 24 የቴሌቪዥን ጣቢያ ከሳቢን ፕላኔል ከተባሉ “እንግዳ” ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ፤ የቀረቡትን ሀሳቦች፣ አሳሳችና ወገንተኝነት የተሞላባቸው ትችቶች ናቸው በማለት በጽኑ እንደሚቃወም አስታውቋል፡፡ ኤምባሲው ባወጣው መግለጫ የጣቢያው ዘገባ የሀገሪቱን ነባራዊ እውነታም ሆነ የመንግሥትን ሰፊ ጥረቶች የማያንጸባርቅ አሳሳች ትርክት ነው ሲል ፈርጆታል።
አክሎም ባለፉት ዓመታት ተመዝግበዋል ያላቸው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ስኬቶችን ወደ ጎን በመተው አስተዳደሩን በ“እርስ በርስ ጦርነት” ብቻ ከፋፍሎ ለመግለጽ የተደረገው ሙከራ ማጋነንና ከተጨባጭ እውነታ የራቀ መሆኑን ጠቅሷል። ኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ቀጣናዊ ሁኔታዎች ውስጥም ሆና በዋና ዋና ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የተመሰከረለትን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግባለች ሲል ምላሽ ሰጥቷል።
በተጨማሪም የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና የመሠረተ ልማት ማዘመን ሥራዎችን “አስከፊ” ሲል የገለጸበትን አግባብ፣ ኤምባሲው ውድቅ እንደሚያደርገው በመግለጽ ይህ የልማት ፕሮጀክት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ሕይወት እየቀየረ ያለና በዋና ከተማዋም ሆነ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች በከፍተኛ ደረጃ አድናቆት የተቸረው ስኬት ነው በማለት አወድሷል።
ኤምባሲው አክሎም በምርጫው ላይ ስለአሳታፊነትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን አስመልክቶ የሰራውና የተቸበት መንገድ በስህተት የተሞሉ ናቸው ሲል በጽኑ ነቅፏል። የፈረንሳዩ የዜና አውታር በሰራው ዘገባ “በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ግማሽ ያህሉ የምርጫ ክልሎች አልመረጡም” ማለቱን በተመለከተ ደግሞ ይህ መረጃ ሙሉ በሙሉ ሐሰት መሆኑን ኤምባሲው በአሐዛዊ መረጃዎች አስደግፎ ተከላክሏል።
ለአብነትም “በአማራ ክልል ከ138 የምርጫ ክልል በስምንቱ ብቻ አለመካሄዱን በመጥቀስ፣ ይህም ከክልሉ አጠቃላይ ቁጥር 6 በመቶ ብቻ መሆኑን” አመልክቷል።
እንዲሁም በቴክኖሎጂ እና አጠቃላይ ሂደቱ ዲሞክራሲን የተከተለ መሆኑን በመግለጽ መገናኛ ብዙኃኑ የሰራቸው እና ያሰራጫቸው መረጃዎች እውነታን ያላገናዘቡ ናቸው ሲል አጣጥሏል፡፡
ምርጫው በተለይም በዴሞክራሲ ምህዳር መስፋትና መገናኛ ብዙኃን ተሳትፎ ዙሪያ የይስሙላ እንደነበር በዘገባው መጠቀሱን ያወሳው መግለጫው፤ የተመራጮችን፣ የሲቪል ማህበራት፣ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ ታዛቢዎችን፣ የሚዲያ ብዛት እና የሚዘግቡ ጋዜጠኞችን ቁጥር እንዲሁም በአጠቃላይ ምርጫው ላይ ያሉ ቁጥሮችን በመጥቀስ ውድቅ አድርጎታል።
ኤምባሲው አክሎም ሚዲያው የውጭ ወገኖችን ማለትም የአፍሪካ ሕብረት እና የኢጋድን ታዛቢዎችን ሚና ለማሳነስ “ትላልቅ ግድፈቶችን ሪፖርት አያደርጉም” ማለቱ የተቋማቱን ስራ ማሳነስ ነው ብሎታል ። የሁለቱንም ተቋማት ልዑካን የሚመሩትን ኃላፊዎች ማንነት በመግለጽ አንጋፋ ተቋማትና መሪዎችን ማጣጣል የአስተሳሰብ አድሏዊነት ማሳያ ነው በማለት ኮንኖታል።
በመጨረሻም የዚህ ምርጫ ውጤት የሀገሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወሰነው በራሱ በኢትዮጵያ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንጂ ከውጭ በሚሰጡ መግለጫዎችና አስተያየቶች አይደለም ሲል አስታውቋል።
#አዲስ_ማለዳ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen
4 hours ago
የኢቦላ ስጋት እና የሀገራት ጥንቃቄ
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን (UAE) ጨምሮ በርካታ ሀገራት የኢቦላ ቫይረስ ወደ ሀገራቸው እንዳይገባ ጠንካራ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምረዋል።
በዚህም መሰረት ሦስት ሀገራት ዜጎች ከዛሬ ጀምሮ ለጊዜው ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል።
እነዚህ ሀገራትም፦
* ዲ.አር. ኮንጎ (DRC)
* ደቡብ ሱዳን እና
* ኡጋንዳ ናቸው።
Via GN
በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የአፍሪካ መገናኛ ማዕከል እንደመሆናችን መጠን፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የሚመለከታቸው የጤና ተቋማት ይህንን ወቅታዊ ሁኔታ በአስቸኳይ አይተው፣ የህዝባችንን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አፋጣኝ ውሳኔና የጥንቃቄ እርምጃ ቢወስዱበት መልካም ነው እንላለን።
ጤና ለሀገራችን! 🇪🇹
Seledadotio
Seledadotio
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን (UAE) ጨምሮ በርካታ ሀገራት የኢቦላ ቫይረስ ወደ ሀገራቸው እንዳይገባ ጠንካራ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምረዋል።
በዚህም መሰረት ሦስት ሀገራት ዜጎች ከዛሬ ጀምሮ ለጊዜው ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል።
እነዚህ ሀገራትም፦
* ዲ.አር. ኮንጎ (DRC)
* ደቡብ ሱዳን እና
* ኡጋንዳ ናቸው።
Via GN
በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የአፍሪካ መገናኛ ማዕከል እንደመሆናችን መጠን፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የሚመለከታቸው የጤና ተቋማት ይህንን ወቅታዊ ሁኔታ በአስቸኳይ አይተው፣ የህዝባችንን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አፋጣኝ ውሳኔና የጥንቃቄ እርምጃ ቢወስዱበት መልካም ነው እንላለን።
ጤና ለሀገራችን! 🇪🇹
Seledadotio
Seledadotio
20 hours ago
አዲስ ዓለም አቀፍ የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር አዲስ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ በጋራ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
ይህ አዲስ የቪዛ ካርድ ደንበኞች ወደተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚጓዙበት ወቅት የገንዘብ ክፍያዎችን በቀላሉ ለመፈጸም የሚያስችላቸው ሲሆን፣ ካርዱን በሚጠቀሙበት ጊዜም የሸባ ማይልስ ማበረታቻ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
አገልግሎቱን ለማግኘት ግን የሁለቱም ተቋማት ማለትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኛ መሆን ያስፈልጋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ እንደገለጹት፣ የአሁኑ ዘመን የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በስፋት የሚፈልግ በመሆኑ ይህ ይፋ የተደረገው ዓለም አቀፍ ካርድ የባንኩን ደንበኞች የውጭ ሀገር የንግድና የገንዘብ ዝውውር በእጅጉ የሚያቀላጥፍ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ በበኩላቸው፣ አየር መንገዱ የደንበኞቹን የአገልግሎት እርካታ ለማሳደግና አሠራሩን ዘመናዊ ለማድረግ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ አዲሱ የክፍያ ካርድ የሁለቱንም አንጋፋ ተቋማት ደንበኞች በእጅጉ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ማብራራታቸውን አሚኮ በዘገባው አስፍሯል።
#የኢትዮጵያንግድባንክ #የኢትዮጵያአየርመንገድ #ቪዛካርድ #የዲጂታልክፍያ #የባንክአገልግሎት #የአየርጉዞ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር አዲስ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ በጋራ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
ይህ አዲስ የቪዛ ካርድ ደንበኞች ወደተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚጓዙበት ወቅት የገንዘብ ክፍያዎችን በቀላሉ ለመፈጸም የሚያስችላቸው ሲሆን፣ ካርዱን በሚጠቀሙበት ጊዜም የሸባ ማይልስ ማበረታቻ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
አገልግሎቱን ለማግኘት ግን የሁለቱም ተቋማት ማለትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኛ መሆን ያስፈልጋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ እንደገለጹት፣ የአሁኑ ዘመን የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በስፋት የሚፈልግ በመሆኑ ይህ ይፋ የተደረገው ዓለም አቀፍ ካርድ የባንኩን ደንበኞች የውጭ ሀገር የንግድና የገንዘብ ዝውውር በእጅጉ የሚያቀላጥፍ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ በበኩላቸው፣ አየር መንገዱ የደንበኞቹን የአገልግሎት እርካታ ለማሳደግና አሠራሩን ዘመናዊ ለማድረግ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ አዲሱ የክፍያ ካርድ የሁለቱንም አንጋፋ ተቋማት ደንበኞች በእጅጉ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ማብራራታቸውን አሚኮ በዘገባው አስፍሯል።
#የኢትዮጵያንግድባንክ #የኢትዮጵያአየርመንገድ #ቪዛካርድ #የዲጂታልክፍያ #የባንክአገልግሎት #የአየርጉዞ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
20 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹የሱማሌ ህዝብ ጥምረት›› ምርጫውን እንደሚቃወም አስታወቀ፡፡ ራሱን ‹‹የሱማሌ ህዝብ ጥምረት›› ብሎ የሚጠራውና በኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር(ኦብነግ)፣ በኮንግረስ ፎር ሱማሊያ ኮዝ(ሲኤስሲ)ና በሱማሊያ ክልል ዲሞክራሲያዊ ጥምረት(ኤስአርዲኤ) አማካኝነት መመስረቱን የሚናገረው ጥምረት ዛሬ ባወጣው መግለጫ በምርጫው ላይ ጠንካራ ተቃውሞ አቅርቧል፡፡
በኦብነግ ማህበራዊ ሚዲያ አማካኝነት ይፋ ባደረገው በዚህ መግለጫው ‹‹ግንቦት 24 ቀን በኢትዮጵያ ውስጥ የተካሄደው ብሄራዊ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሀዊና ሁሉን አቀፍ ወይንም ተአማኒ አይደለም›› ብሏል፡፡ ጨምሮም የምርጫው ሂደት የዲሞክራሲን ዝቅተኛ መስፈርቶች እንኳ እንዳላሟላ ገልፆ ‹‹በምርጫው ሂደት ፖለቲካዊ ጭቆና፣ በተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ ላይ ገደብ፣ ማስፈራራት፣ እኩል ያልሆነ ፖለቲካዊ ውድድርና የመንግስትን ሀብት አለአግባብ መጠቀም ሰፍኖበት ነበር›› በማለት አስረድቷል፡፡
አስከትሎም ከአንዳንድ አለም አቀፍ ተቋማት ብሄራዊ ምርጫ ቦርድን የሚያወድሱ መግለጫዎች መውጣታቸው እንዳሳሰበው የገለፀው መግለጫው፣ ‹‹እንዲህ አይነት ግምገማዎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህዝቦች የገጠማቸውን እውነታ አያንፀባርቅም›› ብሏል፡፡
በኦብነግ ማህበራዊ ሚዲያ አማካኝነት ይፋ ባደረገው በዚህ መግለጫው ‹‹ግንቦት 24 ቀን በኢትዮጵያ ውስጥ የተካሄደው ብሄራዊ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሀዊና ሁሉን አቀፍ ወይንም ተአማኒ አይደለም›› ብሏል፡፡ ጨምሮም የምርጫው ሂደት የዲሞክራሲን ዝቅተኛ መስፈርቶች እንኳ እንዳላሟላ ገልፆ ‹‹በምርጫው ሂደት ፖለቲካዊ ጭቆና፣ በተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ ላይ ገደብ፣ ማስፈራራት፣ እኩል ያልሆነ ፖለቲካዊ ውድድርና የመንግስትን ሀብት አለአግባብ መጠቀም ሰፍኖበት ነበር›› በማለት አስረድቷል፡፡
አስከትሎም ከአንዳንድ አለም አቀፍ ተቋማት ብሄራዊ ምርጫ ቦርድን የሚያወድሱ መግለጫዎች መውጣታቸው እንዳሳሰበው የገለፀው መግለጫው፣ ‹‹እንዲህ አይነት ግምገማዎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህዝቦች የገጠማቸውን እውነታ አያንፀባርቅም›› ብሏል፡፡
Sponsored by
Surafel
21 hours ago
አየር መንገዱ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲስ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ ይፋ አደረጉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር አዲስ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ ይፋ አድርገዋል።
የክፍያ ካርዱ ደንበኞች በየትኛውም የዓለም ክፍል ሆነው በቀላሉ ግብይት እንዲፈጽሙ የሚያስችል ነው።
በተለይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሼባ ማይልስ አባላት የሆኑ መንገደኞች በሚደርሱበት ማንኛውም የዓለም መዳረሻ ፈጣን፣ ቀላልና አስተማማኝ ክፍያዎችን እንዲፈጽሙ ያስችላል።
ካርዱ አስተማማኝ የደኅንነት ጥበቃ ሥርዓት ያለውና የሦስቱንም ተቋማት ዓርማና ምልክት በአንድ ላይ የያዘ መሆኑም ተገልጿል፡፡
አዲሱ ዓለም አቀፍ የግብይት ካርድ ለደንበኞች ልዩ ልዩ ሽልማቶችን እና ጥቅማ ጥቅሞችን የሚያስገኝ ሲሆን፥ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞች ክፍት መሆኑም ነው የተገለጸው።
የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በየጉዟቸው የሚያደርጉት ግብይት ተጠራቅሞ ወደ ጉዞ ዕድል የሚቀየር ሲሆን፥ ካርዱን በሽያጭ ማሽን ወይም በኢ-ኮሜርስ አማካኝነት ለኦንላይን ግብይት በሚጠቀሙበት ወቅት ለተጨማሪ ሽልማት የመታጨት እድላቸውን የሚያሰፋ ነው፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር አዲስ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ ይፋ አድርገዋል።
የክፍያ ካርዱ ደንበኞች በየትኛውም የዓለም ክፍል ሆነው በቀላሉ ግብይት እንዲፈጽሙ የሚያስችል ነው።
በተለይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሼባ ማይልስ አባላት የሆኑ መንገደኞች በሚደርሱበት ማንኛውም የዓለም መዳረሻ ፈጣን፣ ቀላልና አስተማማኝ ክፍያዎችን እንዲፈጽሙ ያስችላል።
ካርዱ አስተማማኝ የደኅንነት ጥበቃ ሥርዓት ያለውና የሦስቱንም ተቋማት ዓርማና ምልክት በአንድ ላይ የያዘ መሆኑም ተገልጿል፡፡
አዲሱ ዓለም አቀፍ የግብይት ካርድ ለደንበኞች ልዩ ልዩ ሽልማቶችን እና ጥቅማ ጥቅሞችን የሚያስገኝ ሲሆን፥ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞች ክፍት መሆኑም ነው የተገለጸው።
የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በየጉዟቸው የሚያደርጉት ግብይት ተጠራቅሞ ወደ ጉዞ ዕድል የሚቀየር ሲሆን፥ ካርዱን በሽያጭ ማሽን ወይም በኢ-ኮሜርስ አማካኝነት ለኦንላይን ግብይት በሚጠቀሙበት ወቅት ለተጨማሪ ሽልማት የመታጨት እድላቸውን የሚያሰፋ ነው፡፡
22 hours ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር አዲስ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ ይፋ አደረጉ
*************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዓለም አቀፉ ቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር፣ ደንበኞች በየትኛውም የዓለም ክፍል ሆነው በቀላሉ ግብይት እንዲፈጽሙ የሚያስችል አዲስ የተቀናጀ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ በይፋ አስጀምረዋል።
ይህ አዲስ የክፍያ ካርድ በተለይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ“ሸባ ማይልስ” አባላት የሆኑ መንገደኞች በሚደርሱበት ማንኛውም የዓለም መዳረሻ ፈጣን፣ ቀላል እና አስተማማኝ ክፍያዎችን እንዲፈጽሙ ዕድል ይሰጣቸዋል።
ካርዱ የዕለት ተዕለት ግብይቶችን ከማቅለሉ ባሻገር፣ ለአጠቃቀም እጅግ ቀላልና አስተማማኝ የደኅንነት ጥበቃ ሥርዓት ያለው መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም የሦስቱንም ተቋማት ዓርማና ምልክት በአንድ ላይ የያዘ ነው።
አዲሱ ዓለም አቀፍ የግብይት ካርድ ለደንበኞች ልዩ ልዩ ሽልማቶችንና ጥቅማጥቅሞችን የሚያስገኝ ሲሆን፣ ለአዲስም ሆነ ለነባር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞች ክፍት መሆኑ ተረጋግጧል።
የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በየጉዟቸው የሚያደርጉት ግብይት ተጠራቅሞ ወደ ጉዞ ዕድል (ማይልስ) የሚቀየርላቸው ሲሆን፣ ካርዱን በሽያጭ ማሽን (POS) ወይም በኢ-ኮሜርስ (e-commerce) አማካኝነት ለኦንላይን ግብይት በሚጠቀሙበት ወቅትም ለተጨማሪ ሽልማቶች ያላቸውን ዕጩነት በከፍተኛ ደረጃ ያሰፋላቸዋል።
ይህ አገልግሎት የሮያሊቲ (ታማኝ) ደንበኞችን ክብርና ጥቅማጥቅም ከመጠበቁ በላይ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደንበኞቹን ዘመናዊ ፍላጎት ለማሟላት ለሚያደርገው ጉዞ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተጠቅሷል።
በሌላ በኩልbox እነዚህ ሁለቱ አንጋፋ ሀገራዊ ተቋማት ከዓለም አቀፉ ቪዛ ካርድ ጋር በጋራ ለመሥራት መፈራረማቸው ተቀባይነታቸውንና የገበያ ድርሻቸውን ይበልጥ የሚያሳድግላቸው ሲሆን፣ ለቪዛ ካርድም ቢሆን በማደግ ላይ ወዳሉ ሀገራት ገበያ ለመግባትና ተደራሽነቱን ለማስፋት ምቹ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርለት ተገልጿል።
በሳራ ሳህለሥላሴ
#commercialbankofethiopia #ethiopianairlines #visacard #cobrandedcard #shebamiles #digitalpayment #ethiopianbroadcastingcorporation
*************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዓለም አቀፉ ቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር፣ ደንበኞች በየትኛውም የዓለም ክፍል ሆነው በቀላሉ ግብይት እንዲፈጽሙ የሚያስችል አዲስ የተቀናጀ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ በይፋ አስጀምረዋል።
ይህ አዲስ የክፍያ ካርድ በተለይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ“ሸባ ማይልስ” አባላት የሆኑ መንገደኞች በሚደርሱበት ማንኛውም የዓለም መዳረሻ ፈጣን፣ ቀላል እና አስተማማኝ ክፍያዎችን እንዲፈጽሙ ዕድል ይሰጣቸዋል።
ካርዱ የዕለት ተዕለት ግብይቶችን ከማቅለሉ ባሻገር፣ ለአጠቃቀም እጅግ ቀላልና አስተማማኝ የደኅንነት ጥበቃ ሥርዓት ያለው መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም የሦስቱንም ተቋማት ዓርማና ምልክት በአንድ ላይ የያዘ ነው።
አዲሱ ዓለም አቀፍ የግብይት ካርድ ለደንበኞች ልዩ ልዩ ሽልማቶችንና ጥቅማጥቅሞችን የሚያስገኝ ሲሆን፣ ለአዲስም ሆነ ለነባር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞች ክፍት መሆኑ ተረጋግጧል።
የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በየጉዟቸው የሚያደርጉት ግብይት ተጠራቅሞ ወደ ጉዞ ዕድል (ማይልስ) የሚቀየርላቸው ሲሆን፣ ካርዱን በሽያጭ ማሽን (POS) ወይም በኢ-ኮሜርስ (e-commerce) አማካኝነት ለኦንላይን ግብይት በሚጠቀሙበት ወቅትም ለተጨማሪ ሽልማቶች ያላቸውን ዕጩነት በከፍተኛ ደረጃ ያሰፋላቸዋል።
ይህ አገልግሎት የሮያሊቲ (ታማኝ) ደንበኞችን ክብርና ጥቅማጥቅም ከመጠበቁ በላይ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደንበኞቹን ዘመናዊ ፍላጎት ለማሟላት ለሚያደርገው ጉዞ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተጠቅሷል።
በሌላ በኩልbox እነዚህ ሁለቱ አንጋፋ ሀገራዊ ተቋማት ከዓለም አቀፉ ቪዛ ካርድ ጋር በጋራ ለመሥራት መፈራረማቸው ተቀባይነታቸውንና የገበያ ድርሻቸውን ይበልጥ የሚያሳድግላቸው ሲሆን፣ ለቪዛ ካርድም ቢሆን በማደግ ላይ ወዳሉ ሀገራት ገበያ ለመግባትና ተደራሽነቱን ለማስፋት ምቹ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርለት ተገልጿል።
በሳራ ሳህለሥላሴ
#commercialbankofethiopia #ethiopianairlines #visacard #cobrandedcard #shebamiles #digitalpayment #ethiopianbroadcastingcorporation
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን አጠቃላይ ምርጫ የታዘቡት የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ልዑካን ቡድኖች የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶቻቸውን በአዲስ አበባ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ አድርገዋል። ሁለቱም ተቋማት በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር እንዲሁም እምነትን ለማጎልበት አካቶ አጠቃላይ እና ቀጣይነት ያለው የፖለቲካ ውይይት መደረግ እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል።
በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው መግለጫ፣ በፖለቲካ ኃይሎች መካከል ልዩነቶችን ለመፍታት እና ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን ለማጠናከር ውይይት ወሳኝ መሆኑን ገልጿል። ይህ ውይይት በሀገሪቱ ሕገ-መንግሥታዊ ማዕቀፍ ውስጥ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና የዜጎችን ተሳትፎ ለማሳደግ መርዳት እንዳለበት ቡድኑ ጠቁሟል። በተጨማሪም የፖለቲካ ብዙሃነትን ማሳደግ እና ዜጎች መብቶቻቸውን በነፃነት የሚለማመዱበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ በትግራይ እና ምርጫ ባልተካሄደባቸው ሌሎች አካባቢዎች ላይ ቡድኑ ለምን ምክረ-ሐሳብ አላካተተም ተብሎ ለቀረበለት ጥያቄ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጸጥታ ሁኔታው ሲሻሻል ምርጫውን ለማካሄድ ዝግጁ መሆኑን እንዳረጋገጠላቸው ኬንያታ ምላሽ ሰጥተዋል። ታዛቢ ቡድኑ ይህንን ያልተጠናቀቀ የምርጫ ሂደት በቀጣይ እንደሚከታተልም ገልጿል።
በሌላ በኩል በምርጫው ወቅት የአንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ፈቃድ መታገድን እና የሚዲያ ነፃነትን በተመለከተ ለቀረበው ጥያቄ ታዛቢ ቡድኑ ቀጥተኛ ምላሽ ከመስጠት የተቆጠበ ሲሆን፣ ዝርዝር ምልከታው በመጨረሻው ሪፖርት ላይ እንደሚወጣ አስታውቋል። ገዥው የብልጽግና ፓርቲ በምርጫ ሊሸነፍ የሚችልበት እውነተኛ ዕድል ስለመኖሩ እና ስለ ምርጫው ተወዳዳሪነት ለቀረበው ጥያቄ ኬንያታ ሲመልሱ፣ ምርጫው ተወዳዳሪ እንደነበር በመግለጽ ተሟግተዋል። በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ውስጥ መሳተፍ የውጤቱን አለመታወቅ እና የሽንፈትን ዕድል መቀበልን አብሮ የሚያካትት መሆኑን አብራርተዋል። የአፍሪካ ኅብረት ለዚህ ምርጫ ከተለያዩ 37 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 73 የአጭር ጊዜ ታዛቢዎችን አሰማርቶ የነበረ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ ወራት የተሟላ የመጨረሻ ሪፖርት እንደሚያወጣ አስታውቋል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ዋንዲራ ስፔሲዮሳ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ ታዛቢ ቡድን በበኩሉ፣ ምርጫው በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስተዋወቃቸው ተቋማዊ እና ቴክኖሎጂያዊ ማሻሻያዎች ምክንያት ውድድሩን የበርካታ አዳዲስ ነገሮች ማሳያ ምርጫ ሲል ጠርቶታል። የኢጋድ ልዑክ 26 ታዛቢዎችን በሰባት ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች አሰማርቶ የነበረ መሆኑም ታውቋል።
በዘንድሮው የኢትዮጵያ 7ኛ አጠቃላይ ምርጫ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ውድድሩ ከ547 የምርጫ ክልሎች ውስጥ በ501ዱ እና በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉ 52 ሺህ ገደማ የምርጫ ጣቢያዎች ተካሂዷል።
ይሁን እንጂ በምርጫው ዕለት በጸጥታ ስጋት ምክንያት 143 የምርጫ ጣቢያዎች ሳይከፈቱ ቀርተዋል። በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች፣ በተለይም እንደ ቢሎኖፓ፣ መቆሳቺ፣ ቀርሳ እና ኩታበር ባሉ አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጥ ከተጀመረ በኋላ በጸጥታ እክሎች ምክንያት መቋረጡን ቦርዱ አስታውቋል። በትግራይ ክልል እንዲሁም በአማራና በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች በጸጥታና በሎጅስቲክስ ምክንያት ድምጽ አልተሰጠም። ይህ ከመደረጉ በፊት ተቃዋሚዎችና ታዛቢዎች በእነዚህ አካባቢዎች ያለው ግጭት የመራጮችን ተሳትፎ ሊጎዳ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸው ነበር። ምንም እንኳን እነዚህ መስተጓጎሎች ቢያጋጥሙም፣ በአብዛኛዎቹ የሀገሪቱ አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጡ በሰላማዊ መንገድ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ የዚህ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት በመጪው ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው መግለጫ፣ በፖለቲካ ኃይሎች መካከል ልዩነቶችን ለመፍታት እና ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን ለማጠናከር ውይይት ወሳኝ መሆኑን ገልጿል። ይህ ውይይት በሀገሪቱ ሕገ-መንግሥታዊ ማዕቀፍ ውስጥ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና የዜጎችን ተሳትፎ ለማሳደግ መርዳት እንዳለበት ቡድኑ ጠቁሟል። በተጨማሪም የፖለቲካ ብዙሃነትን ማሳደግ እና ዜጎች መብቶቻቸውን በነፃነት የሚለማመዱበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ በትግራይ እና ምርጫ ባልተካሄደባቸው ሌሎች አካባቢዎች ላይ ቡድኑ ለምን ምክረ-ሐሳብ አላካተተም ተብሎ ለቀረበለት ጥያቄ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጸጥታ ሁኔታው ሲሻሻል ምርጫውን ለማካሄድ ዝግጁ መሆኑን እንዳረጋገጠላቸው ኬንያታ ምላሽ ሰጥተዋል። ታዛቢ ቡድኑ ይህንን ያልተጠናቀቀ የምርጫ ሂደት በቀጣይ እንደሚከታተልም ገልጿል።
በሌላ በኩል በምርጫው ወቅት የአንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ፈቃድ መታገድን እና የሚዲያ ነፃነትን በተመለከተ ለቀረበው ጥያቄ ታዛቢ ቡድኑ ቀጥተኛ ምላሽ ከመስጠት የተቆጠበ ሲሆን፣ ዝርዝር ምልከታው በመጨረሻው ሪፖርት ላይ እንደሚወጣ አስታውቋል። ገዥው የብልጽግና ፓርቲ በምርጫ ሊሸነፍ የሚችልበት እውነተኛ ዕድል ስለመኖሩ እና ስለ ምርጫው ተወዳዳሪነት ለቀረበው ጥያቄ ኬንያታ ሲመልሱ፣ ምርጫው ተወዳዳሪ እንደነበር በመግለጽ ተሟግተዋል። በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ውስጥ መሳተፍ የውጤቱን አለመታወቅ እና የሽንፈትን ዕድል መቀበልን አብሮ የሚያካትት መሆኑን አብራርተዋል። የአፍሪካ ኅብረት ለዚህ ምርጫ ከተለያዩ 37 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 73 የአጭር ጊዜ ታዛቢዎችን አሰማርቶ የነበረ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ ወራት የተሟላ የመጨረሻ ሪፖርት እንደሚያወጣ አስታውቋል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ዋንዲራ ስፔሲዮሳ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ ታዛቢ ቡድን በበኩሉ፣ ምርጫው በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስተዋወቃቸው ተቋማዊ እና ቴክኖሎጂያዊ ማሻሻያዎች ምክንያት ውድድሩን የበርካታ አዳዲስ ነገሮች ማሳያ ምርጫ ሲል ጠርቶታል። የኢጋድ ልዑክ 26 ታዛቢዎችን በሰባት ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች አሰማርቶ የነበረ መሆኑም ታውቋል።
በዘንድሮው የኢትዮጵያ 7ኛ አጠቃላይ ምርጫ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ውድድሩ ከ547 የምርጫ ክልሎች ውስጥ በ501ዱ እና በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉ 52 ሺህ ገደማ የምርጫ ጣቢያዎች ተካሂዷል።
ይሁን እንጂ በምርጫው ዕለት በጸጥታ ስጋት ምክንያት 143 የምርጫ ጣቢያዎች ሳይከፈቱ ቀርተዋል። በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች፣ በተለይም እንደ ቢሎኖፓ፣ መቆሳቺ፣ ቀርሳ እና ኩታበር ባሉ አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጥ ከተጀመረ በኋላ በጸጥታ እክሎች ምክንያት መቋረጡን ቦርዱ አስታውቋል። በትግራይ ክልል እንዲሁም በአማራና በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች በጸጥታና በሎጅስቲክስ ምክንያት ድምጽ አልተሰጠም። ይህ ከመደረጉ በፊት ተቃዋሚዎችና ታዛቢዎች በእነዚህ አካባቢዎች ያለው ግጭት የመራጮችን ተሳትፎ ሊጎዳ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸው ነበር። ምንም እንኳን እነዚህ መስተጓጎሎች ቢያጋጥሙም፣ በአብዛኛዎቹ የሀገሪቱ አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጡ በሰላማዊ መንገድ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ የዚህ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት በመጪው ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
1 day ago
አዲስ አበባ ፡ የኤምኤምኤ እና የቦክስ ስፖርት ውድድር ሊካሄድ ነው
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት የንክኪ ስፖርት ሁነቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነው የኢትዮ ፋይት ናይት የውድድር መድረክ ይፋ ሆኗል::
ዝግጅቱ የአዲስ አበባ ኪክ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ነሀሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (Aug 29/2026) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል::
በዚህ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ላይ በድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገራችንን ወክለው ደግሞ ቢኒያም ሽብሬ፣ ክብሮም ንጉሴ እና አገረሰላም አርባን ጨምሮ በርካታ ስፖርተኞች ወደ መድረኩ ይወርዳሉ::
በጠቅላላው ከ6 እስከ 8 የሚደርሱ ብርቱ ፍልሚያዎች የሚስተናገዱ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የተመረጡት በውድድር ታሪካቸው፣ በዓለም አቀፍ ልምዳቸው፣ በአካል ብቃት ጥንካሬያቸው እና ማራኪ ትዕይንት ማሳየት በሚችሉበት ብቃታቸው ላይ ተመስርቶ ነው::
አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ህግ መሰረት አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ፣ የክብደት ልኬትና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደቶችን ያጠናቀቁ ሲሆን ዝርዝር የክብደት መጠናቸውና ዜግነታቸው በቅርቡ ይፋ ይደረጋል::
ይህንን ታሪካዊ ፍልሚያ ለመታደም ከ8,000 እስከ 10,000 የሚደርሱ የስፖርት አፍቃሪዎች በአዳራሹ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አዘጋጆቹ የአፍሪካንና የሀገራችንን ስፖርታዊ አቅም ለዓለም የሚያስተዋውቅ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ፍጹም ሙያዊ ብቃት የተላበሰ ዝግጅት ለማቅረብ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል::
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ የንክኪ ስፖርቶችን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ አትሌቶች ሙያዊ መድረክ መፍጠር፣ ወጣቶችን ማነሳሳት፣ ስፖርታዊ ቱሪዝምን በአዲስ አበባና በኢትዮጵያ ማስፋፋት እንዲሁም ሀገራችንን የዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዕከል ማድረግ ነው::
ዝግጅቱ የሚስተናገድበት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር (AICC) ዘመናዊ የዲጂታል ምስልና የድምፅ መገልገያ መሳሪያዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለታዳሚው ምቹ መዝናኛን ለመፍጠር ተመራጭ አድርጎታል::
ገራሚ ኢቨንትስ የዝግጅቱን አጠቃላይ የፕሮዳክሽን ስራ በማስተናገድ ከባለቤቶቹ ጋር በጋራ የሚሰራ ሲሆን ለአትሌቶች ስልጠና፣ ለደህንነት፣ ለቦታ ዝግጅትና ለሎጂስቲክስ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሷል::
ይህንን ውድድር በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማዘጋጀት የታቀደ በመሆኑ፣ የዝግጅቱን ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በስፖንሰርሺፕ፣ በሚዲያ ሽፋን፣ በዲጂታል ግብይትና በቪአይፒ ተሳትፎ ላይ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል::
የመግቢያ ትኬት ዋጋንና የስርጭት ሽፋንን በተመለከተ ከሚዲያ አጋሮች ጋር ውይይት እየተደረገ ሲሆን የቴሌቪዥንና የዲጂታል ቀጥታ ስርጭት መረጃዎች በቅርቡ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል::
#mma #boxing #ethiofightnight #sportstourism #aicc #ethiopianathletes #geramievents #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት የንክኪ ስፖርት ሁነቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነው የኢትዮ ፋይት ናይት የውድድር መድረክ ይፋ ሆኗል::
ዝግጅቱ የአዲስ አበባ ኪክ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ነሀሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (Aug 29/2026) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል::
በዚህ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ላይ በድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገራችንን ወክለው ደግሞ ቢኒያም ሽብሬ፣ ክብሮም ንጉሴ እና አገረሰላም አርባን ጨምሮ በርካታ ስፖርተኞች ወደ መድረኩ ይወርዳሉ::
በጠቅላላው ከ6 እስከ 8 የሚደርሱ ብርቱ ፍልሚያዎች የሚስተናገዱ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የተመረጡት በውድድር ታሪካቸው፣ በዓለም አቀፍ ልምዳቸው፣ በአካል ብቃት ጥንካሬያቸው እና ማራኪ ትዕይንት ማሳየት በሚችሉበት ብቃታቸው ላይ ተመስርቶ ነው::
አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ህግ መሰረት አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ፣ የክብደት ልኬትና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደቶችን ያጠናቀቁ ሲሆን ዝርዝር የክብደት መጠናቸውና ዜግነታቸው በቅርቡ ይፋ ይደረጋል::
ይህንን ታሪካዊ ፍልሚያ ለመታደም ከ8,000 እስከ 10,000 የሚደርሱ የስፖርት አፍቃሪዎች በአዳራሹ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አዘጋጆቹ የአፍሪካንና የሀገራችንን ስፖርታዊ አቅም ለዓለም የሚያስተዋውቅ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ፍጹም ሙያዊ ብቃት የተላበሰ ዝግጅት ለማቅረብ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል::
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ የንክኪ ስፖርቶችን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ አትሌቶች ሙያዊ መድረክ መፍጠር፣ ወጣቶችን ማነሳሳት፣ ስፖርታዊ ቱሪዝምን በአዲስ አበባና በኢትዮጵያ ማስፋፋት እንዲሁም ሀገራችንን የዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዕከል ማድረግ ነው::
ዝግጅቱ የሚስተናገድበት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር (AICC) ዘመናዊ የዲጂታል ምስልና የድምፅ መገልገያ መሳሪያዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለታዳሚው ምቹ መዝናኛን ለመፍጠር ተመራጭ አድርጎታል::
ገራሚ ኢቨንትስ የዝግጅቱን አጠቃላይ የፕሮዳክሽን ስራ በማስተናገድ ከባለቤቶቹ ጋር በጋራ የሚሰራ ሲሆን ለአትሌቶች ስልጠና፣ ለደህንነት፣ ለቦታ ዝግጅትና ለሎጂስቲክስ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሷል::
ይህንን ውድድር በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማዘጋጀት የታቀደ በመሆኑ፣ የዝግጅቱን ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በስፖንሰርሺፕ፣ በሚዲያ ሽፋን፣ በዲጂታል ግብይትና በቪአይፒ ተሳትፎ ላይ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል::
የመግቢያ ትኬት ዋጋንና የስርጭት ሽፋንን በተመለከተ ከሚዲያ አጋሮች ጋር ውይይት እየተደረገ ሲሆን የቴሌቪዥንና የዲጂታል ቀጥታ ስርጭት መረጃዎች በቅርቡ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል::
#mma #boxing #ethiofightnight #sportstourism #aicc #ethiopianathletes #geramievents #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 day ago
የአለልኝ አዘነ ገዳዮች ተብለው የ16 እና 15 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ግለሰቦች፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲለቀቁ ተወሰነ።"
የአለልኝ አዘነ ጉዳይ፡ የይግባኝ ሰሚው ችሎት ውሳኔ ቤተሰቡን ለከፍተኛ ሀዘን እና ድንጋጤ ዳርጓል
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ማህበረሰብን በከፍተኛ ሁኔታ ያሳዘነው እና የብዙ ኢትዮጵያውያንን ልብ ሰርስሮ የገባው የሟች አለልኝ አዘነ የፍትሕ ሂደት፣ አሁን ላይ አሳዛኝ እና አነጋጋሪ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ባለፈው ጊዜ በግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በቅደም ተከተል 16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወ/ሮ አደይ ጌታቸው እና ሉንጎ ሉቃስ፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲሰናበቱ መወሰኑን የሟች ቤተሰቦች አረጋግጠዋል።
ይህ ውሳኔ ቤተሰቡን ከዚህ ቀደም ከነበሩበት ሀዘን ባሻገር፣ ለከፍተኛ የስነ-ልቦና ቀውስ እና ብስጭት ዳርጓቸዋል። የቤተሰብ አባላት እንደገለጹት፣ ወንጀሉ ተፈጽሞ፣ ጥፋተኞች ተለይተውና በፍርድ ቤት ውሳኔ ተላልፎባቸው የነበረ ቢሆንም፣ በይግባኝ ሰበብ እንዲህ በነፃ መለቀቃቸው ተቀባይነት የሌለው እና የፍትሕ ሥርዓቱን የሚያጠይቅ ሆኖ አግኝተውታል።
በችሎቱ ውሎ ወቅት የነበረው ውጥረት፣ የቤተሰቡ ለቅሶ እና ሰቆቃ፣ እንዲሁም በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የነበራቸው የመጨረሻ ተስፋ መሟጠጡ መላውን የፍትህ ናፋቂ ማህበረሰብ በእጅጉ አሳዝኗል።
ቤተሰቡ እንደገለጸው፣ ድርጊቱ የተፈጸመበት ቦታ እርባምንጭ ሆኖ ሳለ፣ የፍርድ ሂደቱ ወደ ወላይታ ሶዶ ተዛውሮ የወሰደው ቅርፅና ውጤት ለቤተሰቡ ድርብ ስቃይ ሆኗል።
ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ የፍትሕ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክርክር ሊያስነሳ እንደሚችል እየተነገረ ነው። በተለይም የወንጀል ድርጊት ተረጋግጦ በነበረበት መዝገብ ላይ እንዲህ ያለ የይግባኝ ውሳኔ መሰጠቱ፣ በፍትሕ ተቋማት ላይ ያለው የመተማመን ቀውስ እንዲባባስ ማድረጉ አልቀረም።
የሕግ ባለሙያዎች እንደሚናገሩት፣ ጉዳዩ በሰብአዊ መብት እና በሕግ የበላይነት መርህ መሠረት በሰፊው ሊጤን የሚገባው ሆኗል።
የሟች ቤተሰብ አባላት በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ይገኛሉ፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናቸው እንዲቆም እና የፍትሕ ጥያቄውን እንዲያቀናጅ ጥሪ አቅርበዋል።
Via ጉርሻ
የአለልኝ አዘነ ጉዳይ፡ የይግባኝ ሰሚው ችሎት ውሳኔ ቤተሰቡን ለከፍተኛ ሀዘን እና ድንጋጤ ዳርጓል
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ማህበረሰብን በከፍተኛ ሁኔታ ያሳዘነው እና የብዙ ኢትዮጵያውያንን ልብ ሰርስሮ የገባው የሟች አለልኝ አዘነ የፍትሕ ሂደት፣ አሁን ላይ አሳዛኝ እና አነጋጋሪ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ባለፈው ጊዜ በግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በቅደም ተከተል 16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወ/ሮ አደይ ጌታቸው እና ሉንጎ ሉቃስ፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲሰናበቱ መወሰኑን የሟች ቤተሰቦች አረጋግጠዋል።
ይህ ውሳኔ ቤተሰቡን ከዚህ ቀደም ከነበሩበት ሀዘን ባሻገር፣ ለከፍተኛ የስነ-ልቦና ቀውስ እና ብስጭት ዳርጓቸዋል። የቤተሰብ አባላት እንደገለጹት፣ ወንጀሉ ተፈጽሞ፣ ጥፋተኞች ተለይተውና በፍርድ ቤት ውሳኔ ተላልፎባቸው የነበረ ቢሆንም፣ በይግባኝ ሰበብ እንዲህ በነፃ መለቀቃቸው ተቀባይነት የሌለው እና የፍትሕ ሥርዓቱን የሚያጠይቅ ሆኖ አግኝተውታል።
በችሎቱ ውሎ ወቅት የነበረው ውጥረት፣ የቤተሰቡ ለቅሶ እና ሰቆቃ፣ እንዲሁም በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የነበራቸው የመጨረሻ ተስፋ መሟጠጡ መላውን የፍትህ ናፋቂ ማህበረሰብ በእጅጉ አሳዝኗል።
ቤተሰቡ እንደገለጸው፣ ድርጊቱ የተፈጸመበት ቦታ እርባምንጭ ሆኖ ሳለ፣ የፍርድ ሂደቱ ወደ ወላይታ ሶዶ ተዛውሮ የወሰደው ቅርፅና ውጤት ለቤተሰቡ ድርብ ስቃይ ሆኗል።
ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ የፍትሕ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክርክር ሊያስነሳ እንደሚችል እየተነገረ ነው። በተለይም የወንጀል ድርጊት ተረጋግጦ በነበረበት መዝገብ ላይ እንዲህ ያለ የይግባኝ ውሳኔ መሰጠቱ፣ በፍትሕ ተቋማት ላይ ያለው የመተማመን ቀውስ እንዲባባስ ማድረጉ አልቀረም።
የሕግ ባለሙያዎች እንደሚናገሩት፣ ጉዳዩ በሰብአዊ መብት እና በሕግ የበላይነት መርህ መሠረት በሰፊው ሊጤን የሚገባው ሆኗል።
የሟች ቤተሰብ አባላት በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ይገኛሉ፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናቸው እንዲቆም እና የፍትሕ ጥያቄውን እንዲያቀናጅ ጥሪ አቅርበዋል።
Via ጉርሻ
Sponsored by
Surafel
1 day ago
የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ በንጹሃን ላይ የተፈጸመውን ግድያና ቃጠሎ አወገዘ
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ ዞን አሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ፣ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ እና የአብያተ ክርስቲያናት ቃጠሎ በጽኑ ማውገዙን አስታወቀ።
ጉባኤው በጥቃቱ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጾ፣ ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።
ቀደም ሲል ተመሳሳይ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ጥበቃ እንዲደረግ መጠየቁን ያስታወሰው ጉባኤው፣ አሁንም ችግሩ ባለመቀረፉ ተጨማሪ ጉዳት መድረሱ ሃዘኑን እጥፍ ድርብ እንዳደረገው ገልጿል።
በመሆኑም መንግሥት የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ ተቀዳሚ ኃላፊነቱን እንዲወጣ፣ ለተፈናቀሉና ስጋት ላለባቸው ዜጎች አስተማማኝ ጥበቃ እንዲያደርግ እንዲሁም ወንጀለኞችን በአፋጣኝ ለፍርድ እንዲያቀርብ በጥብቅ አሳስቧል።
አባል ተቋማት ድርጊቱን በአንድነት እንዲያወግዙና የአካባቢው ማህበረሰብም በጋራ እንዲተጋገዝ ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ ዞን አሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ፣ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ እና የአብያተ ክርስቲያናት ቃጠሎ በጽኑ ማውገዙን አስታወቀ።
ጉባኤው በጥቃቱ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጾ፣ ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።
ቀደም ሲል ተመሳሳይ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ጥበቃ እንዲደረግ መጠየቁን ያስታወሰው ጉባኤው፣ አሁንም ችግሩ ባለመቀረፉ ተጨማሪ ጉዳት መድረሱ ሃዘኑን እጥፍ ድርብ እንዳደረገው ገልጿል።
በመሆኑም መንግሥት የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ ተቀዳሚ ኃላፊነቱን እንዲወጣ፣ ለተፈናቀሉና ስጋት ላለባቸው ዜጎች አስተማማኝ ጥበቃ እንዲያደርግ እንዲሁም ወንጀለኞችን በአፋጣኝ ለፍርድ እንዲያቀርብ በጥብቅ አሳስቧል።
አባል ተቋማት ድርጊቱን በአንድነት እንዲያወግዙና የአካባቢው ማህበረሰብም በጋራ እንዲተጋገዝ ጥሪ አቅርቧል።
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዛሬ ጌታቸው ረዳ በቲአርቲ ቴሌቭዥን የተናገራቸውን ማቅረባችን ይታወሳል። ለጌታቸው ረዳ በዛው ቲሌቭዥን የሰጠውን ምላሽ ተከትሎ ከቀረቡት መካከል የአማራ ማህበር በሰሜን አሜሪካ አባሉ ሮቤል ዓለሙ አንዱ ነው። እርሱ የሰጠው አስተያየት እንደሚከተለው ቀርቧል።
"ሰኞ ዕለት [የምርጫው ቀን] የታየው ነገር የዲሞክራሲ አስመሳይነት ነበር፤ ምክንያቱም በኢትዮጵያ ያለው የአሁኑ እውነታ ከዚያ የራቀ ነው። ይህን ለመረዳት የዐቢይ አሕመድን አስተዳደር የሰብዓዊ መብት አያያዝ ታሪክ መመልከት ብቻ በቂ ነው፣ ይህም በዓለም ላይ ካሉ በጣም አስከፊዎች መካከል ይመደባል። እንደ ምሳሌ ብንወስድ... ባለፉት አምስት ዓመታት የታጠቁ ግጭቶች ሲካሄዱበት በነበረው፣ እና ባለፉት ሦስት ዓመታት ደግሞ በዐቢይ 'የኦሮሞ ብልጽግና ፓርቲ' አስተዳደር ሥር ባሉ የመንግሥት ኃይሎች በኩል የአማራ ክልል የዕለት ተዕለት የጭካኔ ድርጊቶች እያስተናገደ ይገኛል። ባለፈው ወር የለምኪን ኢንስቲትዩት የዐቢይ ጦርነት በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ነው በማለት የዘር ማጥፋት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል፤ እናም ድርጅታችን በመንግሥት ኃይሎች የጤና ጣቢያዎችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ ቤቶችን፣ የአምልኮ ቦታዎችን እና ሌሎች የሲቪል ተቋማትን ዒላማ ያደረጉ፣ እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሞት የዳረጉ ከ370 በላይ የአየር ድብደባዎችን መዝግቧል። የቅርብ ጊዜ የቢቢሲ ሪፖርት ከአነስተኛ የጤና ማዕከላት በተወሰደ ናሙና፣ በአማራ ክልል በሺዎች የሚቆጠሩ የአስገድዶ መድፈር ጉዳዮችን ያሳየ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ በመንግሥት ኃይሎች የተፈጸሙ መሆናቸው ተመላክቷል። ባለፈው ሳምንትም፣ የጤና እና የግጭት ጥበቃ ጥምረት በጤና አጠባበቅ ላይ እየጨመረ ያለውን ጥቃት የሚያሳይ ሪፖርት አውጥቷል።
"ዩኒሴፍ ከ9 ሚሊዮን በላይ ልጆች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ሪፖርት አድርጓል፣ ከነዚህ ውስጥ ግማሹ ከአማራ ክልል ናቸው። እናም በአጎራባች ኦሮሚያ ክልል፣ በብሔረሰብ አማራዎች እና በኦርቶዶክስ ክርስቲያን ማኅበረሰቦች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ቀጥሏል። ምርጫው ዕለትም በምስራቅ አርሲ አካባቢ የነቃ ጭፍጨፋ ሲካሄድ፣ የአካባቢው ታጣቂዎች ተሳታፊ ሆነዋል። በወለጋ አካባቢ ደግሞ በፌዴራል እና በኦሮሚያ ክልል ኃይሎች በኩል ቀጣይነት ያለው ጥቃት እና የከበባ ሁኔታ ይታያል። ስለዚህ በጣም አሳሳቢ የሆነ የሰብዓዊ መብት ቀውስ አለ፣ የፖለቲካ ብዝሃነት የለም፣ የሐሳብ ነጻነት የለም፣ የተዘጋ የሲቪክ ምህዳር አለ፣ ነጻ ፕሬስ የለም፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በአማራ ማንነታቸው፣ በፖለቲካዊ እምነታቸው ታስረዋል፣ ወይም በአንዳንድ ሁኔታዎች ያለምንም ምክንያት ታስረዋል። ከእነዚህም መካከል የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፣ የፓርላማ አባላት፣ ነጻ ጋዜጠኞች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ መሪዎች ይገኛሉ፤ እነዚህ ሰዎች በጣም ከባድ በደል ይደርስባቸዋል።"
"ሰኞ ዕለት [የምርጫው ቀን] የታየው ነገር የዲሞክራሲ አስመሳይነት ነበር፤ ምክንያቱም በኢትዮጵያ ያለው የአሁኑ እውነታ ከዚያ የራቀ ነው። ይህን ለመረዳት የዐቢይ አሕመድን አስተዳደር የሰብዓዊ መብት አያያዝ ታሪክ መመልከት ብቻ በቂ ነው፣ ይህም በዓለም ላይ ካሉ በጣም አስከፊዎች መካከል ይመደባል። እንደ ምሳሌ ብንወስድ... ባለፉት አምስት ዓመታት የታጠቁ ግጭቶች ሲካሄዱበት በነበረው፣ እና ባለፉት ሦስት ዓመታት ደግሞ በዐቢይ 'የኦሮሞ ብልጽግና ፓርቲ' አስተዳደር ሥር ባሉ የመንግሥት ኃይሎች በኩል የአማራ ክልል የዕለት ተዕለት የጭካኔ ድርጊቶች እያስተናገደ ይገኛል። ባለፈው ወር የለምኪን ኢንስቲትዩት የዐቢይ ጦርነት በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ነው በማለት የዘር ማጥፋት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል፤ እናም ድርጅታችን በመንግሥት ኃይሎች የጤና ጣቢያዎችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ ቤቶችን፣ የአምልኮ ቦታዎችን እና ሌሎች የሲቪል ተቋማትን ዒላማ ያደረጉ፣ እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሞት የዳረጉ ከ370 በላይ የአየር ድብደባዎችን መዝግቧል። የቅርብ ጊዜ የቢቢሲ ሪፖርት ከአነስተኛ የጤና ማዕከላት በተወሰደ ናሙና፣ በአማራ ክልል በሺዎች የሚቆጠሩ የአስገድዶ መድፈር ጉዳዮችን ያሳየ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ በመንግሥት ኃይሎች የተፈጸሙ መሆናቸው ተመላክቷል። ባለፈው ሳምንትም፣ የጤና እና የግጭት ጥበቃ ጥምረት በጤና አጠባበቅ ላይ እየጨመረ ያለውን ጥቃት የሚያሳይ ሪፖርት አውጥቷል።
"ዩኒሴፍ ከ9 ሚሊዮን በላይ ልጆች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ሪፖርት አድርጓል፣ ከነዚህ ውስጥ ግማሹ ከአማራ ክልል ናቸው። እናም በአጎራባች ኦሮሚያ ክልል፣ በብሔረሰብ አማራዎች እና በኦርቶዶክስ ክርስቲያን ማኅበረሰቦች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ቀጥሏል። ምርጫው ዕለትም በምስራቅ አርሲ አካባቢ የነቃ ጭፍጨፋ ሲካሄድ፣ የአካባቢው ታጣቂዎች ተሳታፊ ሆነዋል። በወለጋ አካባቢ ደግሞ በፌዴራል እና በኦሮሚያ ክልል ኃይሎች በኩል ቀጣይነት ያለው ጥቃት እና የከበባ ሁኔታ ይታያል። ስለዚህ በጣም አሳሳቢ የሆነ የሰብዓዊ መብት ቀውስ አለ፣ የፖለቲካ ብዝሃነት የለም፣ የሐሳብ ነጻነት የለም፣ የተዘጋ የሲቪክ ምህዳር አለ፣ ነጻ ፕሬስ የለም፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በአማራ ማንነታቸው፣ በፖለቲካዊ እምነታቸው ታስረዋል፣ ወይም በአንዳንድ ሁኔታዎች ያለምንም ምክንያት ታስረዋል። ከእነዚህም መካከል የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፣ የፓርላማ አባላት፣ ነጻ ጋዜጠኞች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ መሪዎች ይገኛሉ፤ እነዚህ ሰዎች በጣም ከባድ በደል ይደርስባቸዋል።"
2 days ago
"እውነቱን ለመናገር፣ ከሥልጣን በመነሳቴ የተለየ ቅሬታ ወይም ቁጣ የለኝም። በፖለቲካችን ውስጥ የተወሰነ ጤናማ አካሄድ ለማስገባት የምችለውን ያህል ጥሬያለሁ፤ ምናልባትም ሙሉ በሙሉ ባይሆንም በከፊል አልተሳካልኝም (ክሽፏል)። ስለዚህ እኔ እንደማስበው፣ ከሥልጣን የምነሳበት ጊዜው ደርሶ ነበር። ምክንያቱም የሥልጣን ዘመኑ የሁለት ዓመት ሲሆን፣ ያ የሁለት ዓመት ጊዜ ደግሞ አብቅቶ ነበር። ይህንን የምልበት ምክንያት... ከእኔ ሥልጣን የተረከበው ሰው እኔን ለመተካት ያላደረገው ጥረት አልነበረም። ስለዚህ መናደድ ካለብኝ፣ ከማንም በላይ በእሱ ላይ መናደድ ነበረብኝ፤ ነገር ግን ጉዳዩ የኔ መናደድ አይደለም።
"ዋናው ነጥብ ተቋማት እስካሉ ድረስ ነገሮች አስቀድመው የሚታወቁበትና የተረጋጉ የሚሆኑበት ሥርዓት እንዲኖር የተወሰኑ ሕጎችን ማክበር ይጠይቀናል። አሁን ያለው የህወሓት አመራር ያደረገው ነገር ግን መፈንቅለ-ሥልጣን በማካሄድ ራሱን እንደ ሕጋዊ አካል አድርጎ መሾም ነው፤ ነገር ግን ሕጋዊ አይደለም። በመሆኑም ይህ አካል ለነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ የሚያስፈልገውን አስተማማኝ ጸጥታ ማረጋገጥ አይችልም።"
ጌታቸው ረዳ ዛሬ ለቲአርቲ ከሰጡት ቃለምልልስ
"ዋናው ነጥብ ተቋማት እስካሉ ድረስ ነገሮች አስቀድመው የሚታወቁበትና የተረጋጉ የሚሆኑበት ሥርዓት እንዲኖር የተወሰኑ ሕጎችን ማክበር ይጠይቀናል። አሁን ያለው የህወሓት አመራር ያደረገው ነገር ግን መፈንቅለ-ሥልጣን በማካሄድ ራሱን እንደ ሕጋዊ አካል አድርጎ መሾም ነው፤ ነገር ግን ሕጋዊ አይደለም። በመሆኑም ይህ አካል ለነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ የሚያስፈልገውን አስተማማኝ ጸጥታ ማረጋገጥ አይችልም።"
ጌታቸው ረዳ ዛሬ ለቲአርቲ ከሰጡት ቃለምልልስ
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ታዋቂዋ ኢትዮጵያዊት አርቲስት መሰረት መብራቴ፣ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ላይ እየደረሰ ያለውን ተደጋጋሚ ጥቃት፣ መፈናቀል እና ግድያ በተመለከተ መንግሥትን እና የፍትሕ አካላትን ክፉኛ የሚወቅስ ጠንካራ መልእክት አስተላለፈች። አርቲስቷ በማኅበራዊ ትስስር ገጿ ባጋራችው እና በማህበራዊ ትሥሥር ላይ በግልጽ በሚታየው ጽሁፍ፣ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ያልቻለውን ሥርዓት እና የሕግ ማስከበር ክፍተቱን በጽኑ ተችታለች።
በመልእክቷም "የኦርቶዶክሳውያን ሞትና መከራ እስከመቼ?!" በማለት መሠረታዊ የፍትሕ ጥያቄ ያነሳች ሲሆን፣ ምስራቅ አርሲን "የደም ምድር" ስትል ገልጻዋለች። ድርጊቱ ማቆሚያ የሌለው እልቂት እና ሰሚ የሌለው ጩኸት መሆኑን የጠቀሰችው አርቲስቷ የንጹሃን ደም ፍትሕ እየጠየቀ መሆኑን በአጽንኦት አስገንዝባለች። በተለይም በመልእክቷ ላይ "ከምድራዊ ዳኛ ፍትህ ባናገኝ፣ የሰማዩ አምላክ ይፈርዳችኋል!!!" በማለት ያሰፈረችው ሐሳብ የሕግ የበላይነት መጓደልን እና ምድራዊ የፍትሕ ተቋማት የዜጎችን ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ያሳዩትን ደካማ አፈጻጸም በቀጥታ የሚሞግት ወሳኝ መልእክት ነው።
በቅርብ ዓመታት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም በምስራቅ አርሲ እና አካባቢው ማንነትን እና ሃይማኖትን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች መበራከታቸውን የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት ተቋማት እና እንደ ኢዜማ፣ እናት ፓርቲ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል። በእነዚህ ክስተቶች የተነሳ በርካታ ዜጎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ አያሌዎች ደግሞ ከቀያቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገዋል።
በዚህ አውድ ውስጥ የሀገሪቱ ታዋቂ ግለሰቦች እና የኪነ-ጥበብ ሰዎች ከዝምታ ወጥተው ድምፃቸውን ማሰማት መጀመራቸው ትልቅ ትርጉም አለው። እንደ መሰረት መብራቴ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች እንዲህ ያሉ የአደባባይ ጩኸቶችን ማሰማታቸው፣ ችግሩ ብሔራዊ ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረጉም ባለፈ የፍትሕ ተቋማት እና የጸጥታ ኃይሎች በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት በአፋጣኝ አምነው ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ከፍተኛ ማኅበራዊ ጫና ይፈጥራል።
አርቲስት መሰረት መብራቴ "ወገኖቼ ነፍሳችሁን በቅዱሳን እቅፍ ይቀበለው" በማለት በግፉ ሕይወታቸውን ላጡ ንጹሃን ዜጎች ያላትን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ መልእክቷን አጠቃላለች።
በመልእክቷም "የኦርቶዶክሳውያን ሞትና መከራ እስከመቼ?!" በማለት መሠረታዊ የፍትሕ ጥያቄ ያነሳች ሲሆን፣ ምስራቅ አርሲን "የደም ምድር" ስትል ገልጻዋለች። ድርጊቱ ማቆሚያ የሌለው እልቂት እና ሰሚ የሌለው ጩኸት መሆኑን የጠቀሰችው አርቲስቷ የንጹሃን ደም ፍትሕ እየጠየቀ መሆኑን በአጽንኦት አስገንዝባለች። በተለይም በመልእክቷ ላይ "ከምድራዊ ዳኛ ፍትህ ባናገኝ፣ የሰማዩ አምላክ ይፈርዳችኋል!!!" በማለት ያሰፈረችው ሐሳብ የሕግ የበላይነት መጓደልን እና ምድራዊ የፍትሕ ተቋማት የዜጎችን ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ያሳዩትን ደካማ አፈጻጸም በቀጥታ የሚሞግት ወሳኝ መልእክት ነው።
በቅርብ ዓመታት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም በምስራቅ አርሲ እና አካባቢው ማንነትን እና ሃይማኖትን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች መበራከታቸውን የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት ተቋማት እና እንደ ኢዜማ፣ እናት ፓርቲ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል። በእነዚህ ክስተቶች የተነሳ በርካታ ዜጎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ አያሌዎች ደግሞ ከቀያቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገዋል።
በዚህ አውድ ውስጥ የሀገሪቱ ታዋቂ ግለሰቦች እና የኪነ-ጥበብ ሰዎች ከዝምታ ወጥተው ድምፃቸውን ማሰማት መጀመራቸው ትልቅ ትርጉም አለው። እንደ መሰረት መብራቴ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች እንዲህ ያሉ የአደባባይ ጩኸቶችን ማሰማታቸው፣ ችግሩ ብሔራዊ ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረጉም ባለፈ የፍትሕ ተቋማት እና የጸጥታ ኃይሎች በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት በአፋጣኝ አምነው ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ከፍተኛ ማኅበራዊ ጫና ይፈጥራል።
አርቲስት መሰረት መብራቴ "ወገኖቼ ነፍሳችሁን በቅዱሳን እቅፍ ይቀበለው" በማለት በግፉ ሕይወታቸውን ላጡ ንጹሃን ዜጎች ያላትን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ መልእክቷን አጠቃላለች።
2 days ago
ቀዝቀዝ ሞቅ የሚለው የሩስያ ዩክሬን ጦርነት ዛሬ ሌላ እልቂት አስመዝግቧል
#ethiopia | በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት፣ ሩሲያ በቅርብ ጊዜ ውስጥ በዩክሬን ላይ የሰነዘረችው እጅግ ከፍተኛ የተባለው የአየር ጥቃት የ18 ሰዎችን ህይወት ማለፉ ተረጋግጧል።
ከተጎጂዎቹ መካከል የስምንት ዓመት ህጻን እና አንዲት ሴት ከፍርስራሽ ውስጥ አስከሬናቸው የተገኘ ሲሆን፣ በጥቃቱ ሳቢያ በድኒፕሮ 12 እንዲሁም በዋና ከተማዋ ኪየቭ 6 ሰዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ እንደተናገሩት፣ የሩሲያ ኢላማዎች በመላው ዩክሬን የሚገኙ የሲቪል መሰረተ ልማቶችና የኃይል ማመንጫ ተቋማት የነበሩ ሲሆን፣ ከሟቾቹ በተጨማሪ ከ100 በላይ ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በሌላ በኩል ሩሲያ ጥቃቱን የፈጸመችው ቀደም ሲል 21 ተማሪዎች ለተገደሉበት ጥቃት ምላሽ ለመስጠት መሆኑን አስታውቃለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የሩሲያ_ዩክሬን_ጦርነት #የአየር_ጥቃት #ዩክሬን #ሩሲያ #ሰብአዊ_ቀውስ
#ethiopia | በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት፣ ሩሲያ በቅርብ ጊዜ ውስጥ በዩክሬን ላይ የሰነዘረችው እጅግ ከፍተኛ የተባለው የአየር ጥቃት የ18 ሰዎችን ህይወት ማለፉ ተረጋግጧል።
ከተጎጂዎቹ መካከል የስምንት ዓመት ህጻን እና አንዲት ሴት ከፍርስራሽ ውስጥ አስከሬናቸው የተገኘ ሲሆን፣ በጥቃቱ ሳቢያ በድኒፕሮ 12 እንዲሁም በዋና ከተማዋ ኪየቭ 6 ሰዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ እንደተናገሩት፣ የሩሲያ ኢላማዎች በመላው ዩክሬን የሚገኙ የሲቪል መሰረተ ልማቶችና የኃይል ማመንጫ ተቋማት የነበሩ ሲሆን፣ ከሟቾቹ በተጨማሪ ከ100 በላይ ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በሌላ በኩል ሩሲያ ጥቃቱን የፈጸመችው ቀደም ሲል 21 ተማሪዎች ለተገደሉበት ጥቃት ምላሽ ለመስጠት መሆኑን አስታውቃለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የሩሲያ_ዩክሬን_ጦርነት #የአየር_ጥቃት #ዩክሬን #ሩሲያ #ሰብአዊ_ቀውስ
Sponsored by
Surafel
2 days ago
የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡
ምርጫውን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የኅብረቱ አባል ሀገራትና በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡
ሀገራቱ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እጩዎችና የሲቪል ተቋማት ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡
የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በምርጫው ላይ ለነበራቸው የታዛቢነት ሚና እውቅና እንደሚሰጡም ሀገራቱ አረጋግጠዋል፡፡
#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያመርጣለች #በምርጫብቻ #ፋናዲጂታል #election #fanadigital #ethiopia #ethiopiavoted #democracy #fanatelevision
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡
ምርጫውን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የኅብረቱ አባል ሀገራትና በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡
ሀገራቱ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እጩዎችና የሲቪል ተቋማት ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡
የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በምርጫው ላይ ለነበራቸው የታዛቢነት ሚና እውቅና እንደሚሰጡም ሀገራቱ አረጋግጠዋል፡፡
#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያመርጣለች #በምርጫብቻ #ፋናዲጂታል #election #fanadigital #ethiopia #ethiopiavoted #democracy #fanatelevision
2 days ago
በካርዳችን ያጸናናትን ሀገር በአንድነታችን እንገንባት
*****************
( የዕለቱ መልዕክት)
የአንድ ሀገር ህልውና እና ጥንካሬ መሰረቱ የህዝቡ አንድነት፤ ትብብርና ቁርጠኝነት ነው። ሰኞ ዕለት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያሳየው ታሪካዊ ተሳትፎ የዚሁ እውነት ህያው ማረጋገጫ ነው።
የራሳቸውን ፍላጎት በራሳቸው ለመወሰን፣ የወደፊት የ5 ዓመት እጣ ፈንታቸውን በራሳቸዉ እጅ ለመጻፍ ከ54 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን ሰጥተዋል።
ይህ ቁጥር ዝም ብሎ ስታቲስቲክስ ሳይሆን የህዝባችንን ፍጹም መነሳሳትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ያለውን ጽኑ አቋም ፍንትው አድርጎ ያሳየ ታላቅ ኩራት ነው።
ከወዲያ ማዶ ሆኖ ማውራት ለነጋሪው ቀላል ነው፤ እንደሚባለው ሀገርን ማቅናትና ዲሞክራሲን መገንባት በወሬ ሳይሆን በተግባርና በጽናት የሚገኝ መሆኑን መራጩ ህዝብ በግልጽ አስመስክሯል።
ማለዳው ገና ሳይቀድ፣ ንጋቱ ሳይተካ ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያው የተሰለፈው ህዝብ ያሳየው ትዕግስት የሚደነቅ ነው። የጠዋቱ ቅዝቃዜና ብርድ፣ የቀትሩ አስገዳጅ ጸሀይም ሆነ ከባዱ ዝናብ ሳይበግረው፤ ረጃጅም ሰልፎችንና የአካል ድካምን ተቋቁሞ ከሌሊት እስከ ሌሊት የቆመው ለራሱ ጥቅም ብቻ አልነበረም።
ይልቁንም፣ "የቆረጠ አይመለስም" እንደሚባለው የነገዋን ኢትዮጵያ ለማጽናት፣ ጠንካራና የማይናወጥ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ባለው ጽኑ ህልም እንጂ።
ይህ ጽናት ህዝቡ የሀገር ጉዳይ ከምንም ነገር እንደሚቀድም ብሄራዊ ጥቅም እና ሉዓላዊነት የሚከበሩት ደግሞ በዜጎች ንቁ ተሳትፎ መሆኑን ያሳየበት የታሪክ አሻራ ነው።
ህዝቡ ፍላጎቱን በምርጫ ካርዱ መግለጹ የዲሞክራሲ ባህላችን ከቃል ባለፈ ወደ ተግባር እየተሸጋገረ ለመምጣቱ ትልቅ ማሳያ ነው። "ስልጣን የህዝብ ነው" የሚለው መርህ መሬት የረገጠው፣ ዜጎች ያለ ምንም ስጋትና በከፍተኛ ተነሳሽነት መብታቸውን ሲጠቀሙ ነው።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው ታሪካዊ ክስተት ኢትዮጵያ መምረጧን ብቻ ሳይሆን በልጆቿ ጽናት መጽናቷንና ወደፊት መራመዷን ጭምር ያበሰረ ነው።
አሁን የምርጫው ውጤት እስኪገለጽ ድረስ ባለው ወቅት፣ ሁላችንም ልባችንን ሰብስበን፣ የተጀመረውን የሰላምና የዲሞክራሲ ጉዞ ማገዝ ይኖርብናል። ምክንያቱም "በአንድ እጅ አያጨበጭቡም" እና ሀገርን የመስራት፣ ተቋማትን የማጠንከርና ሰላምን የማስፈን ኃላፊነት የሁላችንም የጋራ የቤት ስራ ነው።
የህዝብ ስልጣን ባለቤትነት የሚረጋገጠው በዚህ መልኩ በካርድ በሚሰጥ ድምጽ እና በሚታይ ቁርጠኝነት ነው። ትናንት የፈሰሰው ድካምና መስዋዕትነት፣ ዛሬ ለምናየው የነጻነት አየር መሰረት ሆኗል። ህዝባችን ያሳየው ታላቅ የሀገር ፍቅር የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ ለመገንባት መተኪያ የሌለው የሞራል ስንቅ ነው።
አሁን ኑ፣ እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በምርጫ ካርዳችን ያጸናናትን ሀገር በስራችንና በአንድነታችን እንገንባት።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጽናትና ፍቅር ለዘላለም ትኑር!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*****************
( የዕለቱ መልዕክት)
የአንድ ሀገር ህልውና እና ጥንካሬ መሰረቱ የህዝቡ አንድነት፤ ትብብርና ቁርጠኝነት ነው። ሰኞ ዕለት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያሳየው ታሪካዊ ተሳትፎ የዚሁ እውነት ህያው ማረጋገጫ ነው።
የራሳቸውን ፍላጎት በራሳቸው ለመወሰን፣ የወደፊት የ5 ዓመት እጣ ፈንታቸውን በራሳቸዉ እጅ ለመጻፍ ከ54 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን ሰጥተዋል።
ይህ ቁጥር ዝም ብሎ ስታቲስቲክስ ሳይሆን የህዝባችንን ፍጹም መነሳሳትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ያለውን ጽኑ አቋም ፍንትው አድርጎ ያሳየ ታላቅ ኩራት ነው።
ከወዲያ ማዶ ሆኖ ማውራት ለነጋሪው ቀላል ነው፤ እንደሚባለው ሀገርን ማቅናትና ዲሞክራሲን መገንባት በወሬ ሳይሆን በተግባርና በጽናት የሚገኝ መሆኑን መራጩ ህዝብ በግልጽ አስመስክሯል።
ማለዳው ገና ሳይቀድ፣ ንጋቱ ሳይተካ ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያው የተሰለፈው ህዝብ ያሳየው ትዕግስት የሚደነቅ ነው። የጠዋቱ ቅዝቃዜና ብርድ፣ የቀትሩ አስገዳጅ ጸሀይም ሆነ ከባዱ ዝናብ ሳይበግረው፤ ረጃጅም ሰልፎችንና የአካል ድካምን ተቋቁሞ ከሌሊት እስከ ሌሊት የቆመው ለራሱ ጥቅም ብቻ አልነበረም።
ይልቁንም፣ "የቆረጠ አይመለስም" እንደሚባለው የነገዋን ኢትዮጵያ ለማጽናት፣ ጠንካራና የማይናወጥ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ባለው ጽኑ ህልም እንጂ።
ይህ ጽናት ህዝቡ የሀገር ጉዳይ ከምንም ነገር እንደሚቀድም ብሄራዊ ጥቅም እና ሉዓላዊነት የሚከበሩት ደግሞ በዜጎች ንቁ ተሳትፎ መሆኑን ያሳየበት የታሪክ አሻራ ነው።
ህዝቡ ፍላጎቱን በምርጫ ካርዱ መግለጹ የዲሞክራሲ ባህላችን ከቃል ባለፈ ወደ ተግባር እየተሸጋገረ ለመምጣቱ ትልቅ ማሳያ ነው። "ስልጣን የህዝብ ነው" የሚለው መርህ መሬት የረገጠው፣ ዜጎች ያለ ምንም ስጋትና በከፍተኛ ተነሳሽነት መብታቸውን ሲጠቀሙ ነው።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው ታሪካዊ ክስተት ኢትዮጵያ መምረጧን ብቻ ሳይሆን በልጆቿ ጽናት መጽናቷንና ወደፊት መራመዷን ጭምር ያበሰረ ነው።
አሁን የምርጫው ውጤት እስኪገለጽ ድረስ ባለው ወቅት፣ ሁላችንም ልባችንን ሰብስበን፣ የተጀመረውን የሰላምና የዲሞክራሲ ጉዞ ማገዝ ይኖርብናል። ምክንያቱም "በአንድ እጅ አያጨበጭቡም" እና ሀገርን የመስራት፣ ተቋማትን የማጠንከርና ሰላምን የማስፈን ኃላፊነት የሁላችንም የጋራ የቤት ስራ ነው።
የህዝብ ስልጣን ባለቤትነት የሚረጋገጠው በዚህ መልኩ በካርድ በሚሰጥ ድምጽ እና በሚታይ ቁርጠኝነት ነው። ትናንት የፈሰሰው ድካምና መስዋዕትነት፣ ዛሬ ለምናየው የነጻነት አየር መሰረት ሆኗል። ህዝባችን ያሳየው ታላቅ የሀገር ፍቅር የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ ለመገንባት መተኪያ የሌለው የሞራል ስንቅ ነው።
አሁን ኑ፣ እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በምርጫ ካርዳችን ያጸናናትን ሀገር በስራችንና በአንድነታችን እንገንባት።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጽናትና ፍቅር ለዘላለም ትኑር!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
3 days ago
የሕዝብ ጽናት፦ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የስኬት ምስጢር
*****************
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ተቋማት ግንባታና ተዓማኒነትን ለማረጋገጥ የተከናወነው ተግባር ተጨባጭ ፍሬ እያፈራ መሆኑን የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተግባር አሳይቷል።
በምርጫው ዕለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፁ እንዳይባክን እና ሉዓላዊ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ጽናት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት ሀገሩን ለማጽናት የከፈለው ታላቅ የዜግነት መስዋዕትነት ሆኖ ተመዝግቧል።
በምርጫው ዕለት ሕዝባችን ቁር ሳይበግረው ጎሕ ከመቅደዱ፣ የምርጫ ጣቢያዎችም ከመከፈታቸው በፊት በየምድብ ስፍራው በመድረስና ረጃጅም ሰልፎችን በመታገስ ጽናቱን አሳይቷል።
እናቶች፣ አባቶች፣ ወጣቶችና አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች የመራጭነት ካርዳቸውን በመያዝ በየምርጫ ጣቢያዎቻቸው በማለዳ ደርሰዋል።
ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀምና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት ያደረጉት ኃላፊነት የተሞላበት እንቅስቃሴና ያሳዩት ጽናት እጅግ የሚያስደንቅ ነበር።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስምሪት የተሰጣቸው አስመራጮች፣ ታዛቢዎችና የጸጥታ አካላትም አስቀድመው በየምድብ ጣቢያዋቻቸው በመገኘት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ተወጥተዋል።
የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ምሽት 12 ሰዓት ላይ መጠናቀቅ የነበረበት ቢሆንም፣ በነበረው ከፍተኛ የመራጮች ቁጥርና የሂደት መጓተት ችግር ምክንያት በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ሂደቱ እስከ እኩለ ሌሊትና ከዚያም በላይ እንዲራዘም ተደርጓል።
ይህን ተከትሎም ምርጫው በስኬት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህም ሀገራችን ማንኛውንም ታላቅ ሁነት በብቃት ማካሄድ እንደምትችል ዳግም ያረጋገጠችበት ሆኗል።
ይህም ሕዝባችን ምርጫ ተራ ሁነት ሳይሆን፣ የሀገርን እጣ ፈንታ መወሰኛ ታላቅ ዕድል መሆኑን በተግባር ያሳየበት ነው።
በአጠቃላይ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ያሳየው የፖለቲካ ብስለትና ጽናት፣ የሰላም እና የሀገር ወዳድነቱ መገለጫ ነው።
አዎ፣ ምርጫው ሕዝባችን ለነገዋ ኢትዮጵያ ጠንካራ የዴሞክራሲ መሠረት ለመጣል ያለውን የላቀ ፍላጎት በግልጽ ያሳየበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
በመሐመድ ፊጣሞ
#ኢትዮጵያ_መርጣለች #ኢትዮጵያ_አሸንፋለች
*****************
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ተቋማት ግንባታና ተዓማኒነትን ለማረጋገጥ የተከናወነው ተግባር ተጨባጭ ፍሬ እያፈራ መሆኑን የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተግባር አሳይቷል።
በምርጫው ዕለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፁ እንዳይባክን እና ሉዓላዊ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ጽናት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት ሀገሩን ለማጽናት የከፈለው ታላቅ የዜግነት መስዋዕትነት ሆኖ ተመዝግቧል።
በምርጫው ዕለት ሕዝባችን ቁር ሳይበግረው ጎሕ ከመቅደዱ፣ የምርጫ ጣቢያዎችም ከመከፈታቸው በፊት በየምድብ ስፍራው በመድረስና ረጃጅም ሰልፎችን በመታገስ ጽናቱን አሳይቷል።
እናቶች፣ አባቶች፣ ወጣቶችና አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች የመራጭነት ካርዳቸውን በመያዝ በየምርጫ ጣቢያዎቻቸው በማለዳ ደርሰዋል።
ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀምና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት ያደረጉት ኃላፊነት የተሞላበት እንቅስቃሴና ያሳዩት ጽናት እጅግ የሚያስደንቅ ነበር።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስምሪት የተሰጣቸው አስመራጮች፣ ታዛቢዎችና የጸጥታ አካላትም አስቀድመው በየምድብ ጣቢያዋቻቸው በመገኘት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ተወጥተዋል።
የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ምሽት 12 ሰዓት ላይ መጠናቀቅ የነበረበት ቢሆንም፣ በነበረው ከፍተኛ የመራጮች ቁጥርና የሂደት መጓተት ችግር ምክንያት በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ሂደቱ እስከ እኩለ ሌሊትና ከዚያም በላይ እንዲራዘም ተደርጓል።
ይህን ተከትሎም ምርጫው በስኬት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህም ሀገራችን ማንኛውንም ታላቅ ሁነት በብቃት ማካሄድ እንደምትችል ዳግም ያረጋገጠችበት ሆኗል።
ይህም ሕዝባችን ምርጫ ተራ ሁነት ሳይሆን፣ የሀገርን እጣ ፈንታ መወሰኛ ታላቅ ዕድል መሆኑን በተግባር ያሳየበት ነው።
በአጠቃላይ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ያሳየው የፖለቲካ ብስለትና ጽናት፣ የሰላም እና የሀገር ወዳድነቱ መገለጫ ነው።
አዎ፣ ምርጫው ሕዝባችን ለነገዋ ኢትዮጵያ ጠንካራ የዴሞክራሲ መሠረት ለመጣል ያለውን የላቀ ፍላጎት በግልጽ ያሳየበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
በመሐመድ ፊጣሞ
#ኢትዮጵያ_መርጣለች #ኢትዮጵያ_አሸንፋለች
3 days ago
"ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ... አገር ሆና እንድትቀጥል ለማየት ነው ምኞታችንና ጸሎታችን!!"
#ethiopia | የዘንድሮውን የ7ኛ ዙር አገራዊ ምርጫ ለመታዘብ የሚያስችለኝን ዕድል አግኝቼ ነበር። እናም በግልና የተለያዩ ተቋማትን ወክለን የመጣን የአገር ውስጥ ታዛቢ ቡድን አባላት ምርጫውን ለመታዘብ ከመጡ የአፍሪካ ኅብረት እና የኢጋድ የታዛቢ ቡድን አባላት ጋር በስካይ ላይት ሆቴል የትውውቅና ሰፋ ያለ የጋራ ውይይት አድርገን ነበር።
በዚህ ውይይት ላይም የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪና የቀድሞ የኡጋንዳ የቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ዶ/ር ዋንዲራ ካዚብዌ በምክር መልኩ ለወጣቶች ያነሱት ሐሳብ ቀልቤን ገዛው። እናም ከእኚህ ጉምቱ ፖለቲከኛ አፍሪካዊ እናት ከሐሳባቸው ጥቂት ሰበዞችን ለመምዘዝ ወደድኹ።
በአገራቸው ኡጋንዳ ፖለቲካ ውስጥ የሴቶችን/የእናቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ትርጉም ባለው መንገድ በመቀየር ጉልህ አሻራ ያኖሩት የህክምና ሳይንስን ከሥነ-መንግሥት ትምህርት ጋር ያጣጣሙ እኚህ አፍሪካዊ ምሁር እናት በውይይታችን መካከል እንዲህ አሉን።
"When women lead, even water climbs uphill."
"ሴቶች ሲመሩ ውኃ ሳይቀር እንኳን ሽቅብ ይፈሳል፤" የሚል አፍሪካዊ አባባል አለ።
መቼም ለዚህ አባባል እናንት ኢትዮጵያውያን ሕያው ምስክሮች ናችሁ። ከኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ፣ የዐድዋውን ጦርነት በሴትነት ብልሃት ከመሩት እቴጌ ጣይቱ ድረስ የአገራችሁ የፖለቲካ ታሪክ በሴቶች ጉልህ ተሳትፎና አሻራ የደመቀ ነው።
በእውነት በእነዚህ ጀግኖች እናቶቻችሁ ታሪክ ልትኮሩ፤ ልትደነቁ ይገባችኋል።
ዶ/ር ካዚብዌ ቁጭት በቀላቀለ ስሜት ያነሱትን ሌላኛው የሐሳባቸውን ሰበዝ ለዚህች አጭር ማስታወሻ መደምደሚያ ይሆነኝ ዘንድ መረጥኩት።
እኛ አፍሪካውያን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንደ ሸቀጥ ዕቃ ሙሉ በሙሉ ከምዕራቡ ዓለም ለማስገባት የምናደርገውን ልፋት ቆም ብለን መፈተሽ ይገባናል። ከሌሎች የምንቀበለውን ያህል እኛ አፍሪካውያን ለተቀረው ዓለም ልንሰጠው የምንችላቸው በርካታ ነገሮች አሉን።
አፍሪካ ለሺህ ዓመታት የቆየ የራሷ የሆነ ግዙፍ ታሪክ፤ ገናና ሥልጣኔ፤ በዘመናት ተፈትኖ ያለፈ የዳበረ ባህላዊ የፖለቲካ ሥርዓት ያላት አህጉር ናት። እናንት ኢትዮጵያውያን ደግሞ በዚህ የአኅጉራችን የአፍሪካ የሺህ ዘመናት ታሪክና ባህል ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳላችሁ።
ከአክሱም ገናና ሥልጣኔ የቅኝ ገዢዎችንና የተስፋፊዎችን ቅስም እስካንኮታኮተው የዐድዋ ድል ድረስ አኩሪ ታሪክ ያላችሁ ታላቅ ሕዝብ ናችሁ።
አብዛኛው የታሪካችሁ ምዕራፍ ሲገለጽም- የአንድነትን፤ የኅብረትን ኃይል ቀድሞ የተረዳችሁ ጠቢባን ሕዝቦች መሆናችሁን ነው የሚመስክረው። እናም ዛሬ ልዩነታችሁን በማጥበብ አንድነታችሁን አጠናከሩ፤ ኅብረታችሁን አጎልብቱ። አንድነት ኃይል ነው!!
ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ፤ በጦርነት ሳይሆን በሰላም ያሸበረቀ፤ በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር የተዋበ አፍሪካዊ ተምሳሌትነቷንና እናትነቷን ያስመሰከረች አገር ሆና እንድትቀጥል ነው ምኞታችን፤ ተስፋችንና ጸሎታችን።
እግዚአብሔር አፍሪካን ይባርክ፤ አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!!
ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ አበው፤ ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን በመጡ ማግሥት- ኢትዮጵያውያን እናቶች ይጸልዩልኛል፤ የእናቶቼ ጸሎታቸውና ምርቃታቸው ያግዘኛል፤ ጉልበት ይሆነኛል። የሚል ቃልን አብዝተን ከአንደበታቸው አንሰማ ነበር። ዛሬስ...?!
ታላቁ መጽሐፍ፤ "የእናት ምርቃት ቤትን ያጸናል፤" እንዲል በእናቶቻችን ምርቃትና ጸሎት የሁላችን ቤት የሆነች ኢትዮጵያ፤ አፍሪካ የአንድነት መሠረቷ ጸንቶና ሰላሟ ተጠብቆ በአንድነት ጸንታ ትኖር ዘንድ በመመኘት ልሰናበት።
ሰላም!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)፤
#ethiopia | የዘንድሮውን የ7ኛ ዙር አገራዊ ምርጫ ለመታዘብ የሚያስችለኝን ዕድል አግኝቼ ነበር። እናም በግልና የተለያዩ ተቋማትን ወክለን የመጣን የአገር ውስጥ ታዛቢ ቡድን አባላት ምርጫውን ለመታዘብ ከመጡ የአፍሪካ ኅብረት እና የኢጋድ የታዛቢ ቡድን አባላት ጋር በስካይ ላይት ሆቴል የትውውቅና ሰፋ ያለ የጋራ ውይይት አድርገን ነበር።
በዚህ ውይይት ላይም የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪና የቀድሞ የኡጋንዳ የቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ዶ/ር ዋንዲራ ካዚብዌ በምክር መልኩ ለወጣቶች ያነሱት ሐሳብ ቀልቤን ገዛው። እናም ከእኚህ ጉምቱ ፖለቲከኛ አፍሪካዊ እናት ከሐሳባቸው ጥቂት ሰበዞችን ለመምዘዝ ወደድኹ።
በአገራቸው ኡጋንዳ ፖለቲካ ውስጥ የሴቶችን/የእናቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ትርጉም ባለው መንገድ በመቀየር ጉልህ አሻራ ያኖሩት የህክምና ሳይንስን ከሥነ-መንግሥት ትምህርት ጋር ያጣጣሙ እኚህ አፍሪካዊ ምሁር እናት በውይይታችን መካከል እንዲህ አሉን።
"When women lead, even water climbs uphill."
"ሴቶች ሲመሩ ውኃ ሳይቀር እንኳን ሽቅብ ይፈሳል፤" የሚል አፍሪካዊ አባባል አለ።
መቼም ለዚህ አባባል እናንት ኢትዮጵያውያን ሕያው ምስክሮች ናችሁ። ከኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ፣ የዐድዋውን ጦርነት በሴትነት ብልሃት ከመሩት እቴጌ ጣይቱ ድረስ የአገራችሁ የፖለቲካ ታሪክ በሴቶች ጉልህ ተሳትፎና አሻራ የደመቀ ነው።
በእውነት በእነዚህ ጀግኖች እናቶቻችሁ ታሪክ ልትኮሩ፤ ልትደነቁ ይገባችኋል።
ዶ/ር ካዚብዌ ቁጭት በቀላቀለ ስሜት ያነሱትን ሌላኛው የሐሳባቸውን ሰበዝ ለዚህች አጭር ማስታወሻ መደምደሚያ ይሆነኝ ዘንድ መረጥኩት።
እኛ አፍሪካውያን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንደ ሸቀጥ ዕቃ ሙሉ በሙሉ ከምዕራቡ ዓለም ለማስገባት የምናደርገውን ልፋት ቆም ብለን መፈተሽ ይገባናል። ከሌሎች የምንቀበለውን ያህል እኛ አፍሪካውያን ለተቀረው ዓለም ልንሰጠው የምንችላቸው በርካታ ነገሮች አሉን።
አፍሪካ ለሺህ ዓመታት የቆየ የራሷ የሆነ ግዙፍ ታሪክ፤ ገናና ሥልጣኔ፤ በዘመናት ተፈትኖ ያለፈ የዳበረ ባህላዊ የፖለቲካ ሥርዓት ያላት አህጉር ናት። እናንት ኢትዮጵያውያን ደግሞ በዚህ የአኅጉራችን የአፍሪካ የሺህ ዘመናት ታሪክና ባህል ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳላችሁ።
ከአክሱም ገናና ሥልጣኔ የቅኝ ገዢዎችንና የተስፋፊዎችን ቅስም እስካንኮታኮተው የዐድዋ ድል ድረስ አኩሪ ታሪክ ያላችሁ ታላቅ ሕዝብ ናችሁ።
አብዛኛው የታሪካችሁ ምዕራፍ ሲገለጽም- የአንድነትን፤ የኅብረትን ኃይል ቀድሞ የተረዳችሁ ጠቢባን ሕዝቦች መሆናችሁን ነው የሚመስክረው። እናም ዛሬ ልዩነታችሁን በማጥበብ አንድነታችሁን አጠናከሩ፤ ኅብረታችሁን አጎልብቱ። አንድነት ኃይል ነው!!
ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ፤ በጦርነት ሳይሆን በሰላም ያሸበረቀ፤ በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር የተዋበ አፍሪካዊ ተምሳሌትነቷንና እናትነቷን ያስመሰከረች አገር ሆና እንድትቀጥል ነው ምኞታችን፤ ተስፋችንና ጸሎታችን።
እግዚአብሔር አፍሪካን ይባርክ፤ አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!!
ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ አበው፤ ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን በመጡ ማግሥት- ኢትዮጵያውያን እናቶች ይጸልዩልኛል፤ የእናቶቼ ጸሎታቸውና ምርቃታቸው ያግዘኛል፤ ጉልበት ይሆነኛል። የሚል ቃልን አብዝተን ከአንደበታቸው አንሰማ ነበር። ዛሬስ...?!
ታላቁ መጽሐፍ፤ "የእናት ምርቃት ቤትን ያጸናል፤" እንዲል በእናቶቻችን ምርቃትና ጸሎት የሁላችን ቤት የሆነች ኢትዮጵያ፤ አፍሪካ የአንድነት መሠረቷ ጸንቶና ሰላሟ ተጠብቆ በአንድነት ጸንታ ትኖር ዘንድ በመመኘት ልሰናበት።
ሰላም!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)፤
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) "እኛ እንደ ፓርቲ ትልቅ ትዕግስት አድርገን ነበር። መንግስትን እነዚህን እነዚህን ነገሮች አስተካክሉ ብለን በተደጋጋሚ ጠየቅን፣ መንግስት ግን እምቢ አለ። አሁን ላይ ቢሮዎቻችን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ተዘግተዋል። አባሎቻችን ታስረዋል። አሁን ባለው የፖለቲካ ሁኔታ ሰላማዊ ትግል ለማድረግ በጣም አስቸጋሪ ነው። በአንድ በኩል ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንገነባለን ይባላል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ከፍተኛ የሆነ አፈና እና እስር አለ። ይህ ምርጫ ዴሞክራሲን ለማስፈን ሳይሆን፣ የፓርላማ ወንበር ለማግኘት ተብሎ የሚደረግ ቲያትር ወይም ድራማ ነው። ለምሳሌ የፓርላማውን ወንበር ብንወስድ፣ ከ547ቱ ወንበሮች ውስጥ ከ350 በላይ የሚሆኑት ገዥው ፓርቲ ያለምንም ተወዳዳሪ ብቻውን የሚወዳደርባቸው ናቸው። ታዲያ ይህ ምን ዓይነት ምርጫ ነው? እኛ አዲስ አበባ ላይ ሆነን፣ ከዚህ 100 ኪሎሜትር ርቃ ወደምትገኘው አምቦ ከተማ ሄደን እንኳን አባሎቻችንን ማግኘት ወይም ስብሰባ ማድረግ አንችልም። ስብሰባ ብናደርግ አባሎቻችን ይያዛሉ፣ ይታሰራሉ፣ እንግልት ይደርስባቸዋል። ታዲያ በዚህ ሁኔታ እንዴት ነው ምርጫ ውስጥ የምንገባው? የምርጫ ቦርድን እና ሌሎች ተቋማትን ገለልተኝነት በተመለከተ፣ ተቋማቱ ሙሉ በሙሉ ገለልተኛ አይደሉም። መቶ በመቶ በሚባል ደረጃ በገዥው ፓርቲ ቁጥጥር ስር ያሉ ናቸው።"
ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ለቢቢሲ ስለ ምርጫው የሰጡት አስተያየት
ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ለቢቢሲ ስለ ምርጫው የሰጡት አስተያየት
3 days ago
ተፈጸመ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 days ago
ጸሎት በጤናችን ላይ የሚያመጣው አስገራሚ ለውጥ
በሜሪላንድ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ትምህርት ቤት ተመራማሪዎች አማካኝነት የተካሄደ አዲስ ሳይንሳዊ ጥናት እንደሚያሳየው፣ በቀን ለአምስት ደቂቃ ብቻ የሚደረግ የጸሎት ሥነ-ሥርዓት በሰዎች ላይ የሚከሰትን ከፍተኛ የሕመም ስሜትና ጭንቀትን በከፍተኛ ሁኔታ የመቀነስ አቅም አለው።
ይህ "ፕሮክሲማል ኢንተርሴሰሪ ፕሬየር (PIP)" ወይም በአካል ተገኝቶ ለሌላ ሰው ደኅንነት የሚደረግ የፊት ለፊት ጸሎት በመባል የሚታወቀው ልምምድ፣ በሙከራው ወቅት ከተሳተፉት መካከል ከሙዚቃ ማዳመጥ ይልቅ የላቀና ዘላቂ እፎይታን መስጠት መቻሉ ተረጋግጧል።
በጥናቱ ላይ የተሳተፉት ዶክተር ካትሪን ጃኮብሰን እንደገለጹት፣ ይህ የጸሎት አገልግሎት በሕክምና ተቋማት ውስጥ እንዲካተት 97% የሚሆኑት ታካሚዎች ሙሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በሜሪላንድ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ትምህርት ቤት ተመራማሪዎች አማካኝነት የተካሄደ አዲስ ሳይንሳዊ ጥናት እንደሚያሳየው፣ በቀን ለአምስት ደቂቃ ብቻ የሚደረግ የጸሎት ሥነ-ሥርዓት በሰዎች ላይ የሚከሰትን ከፍተኛ የሕመም ስሜትና ጭንቀትን በከፍተኛ ሁኔታ የመቀነስ አቅም አለው።
ይህ "ፕሮክሲማል ኢንተርሴሰሪ ፕሬየር (PIP)" ወይም በአካል ተገኝቶ ለሌላ ሰው ደኅንነት የሚደረግ የፊት ለፊት ጸሎት በመባል የሚታወቀው ልምምድ፣ በሙከራው ወቅት ከተሳተፉት መካከል ከሙዚቃ ማዳመጥ ይልቅ የላቀና ዘላቂ እፎይታን መስጠት መቻሉ ተረጋግጧል።
በጥናቱ ላይ የተሳተፉት ዶክተር ካትሪን ጃኮብሰን እንደገለጹት፣ ይህ የጸሎት አገልግሎት በሕክምና ተቋማት ውስጥ እንዲካተት 97% የሚሆኑት ታካሚዎች ሙሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
3 days ago
🚨 "እባካችሁ ድምፅ ሁኑን!" — ከምስራቅ አርሲ ጫካዎች የተሰማ የድረሱልን ጥሪ!
መላው አገር በምርጫው ትኩረት በተጠመደበት በዚህ ወቅት፣ በምስራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ጥቃት እየተፈጸመ ይገኛል።
📌 እስካሁን የደረሰው ጉዳት፦
የሕይወት መጥፋት፦ከ37 በላይ ንጹሐን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።
የንብረት ውድመት፦234 መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል።
የሃይማኖት ተቋማት፦ታሪካዊው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል እና የኩፍቴና መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል።
⚠️ ወቅታዊ ሁኔታ፦
ጥቃቱ አሁንም በተለያዩ ቀበሌዎች (ዘዲቡ፣ እሬቻ ሚካኤል፣ ሱንቴ ማርያም...) የቀጠለ ሲሆን፣ አቅመ-ቢስ እናቶችና ሕፃናት ሕይወታቸውን ለማዳን ንብረታቸውን ጥለው በጫካዎች ውስጥ ተደብቀው ይገኛሉ።
🙏 ነፍስ ይማር!
መላው አገር በምርጫው ትኩረት በተጠመደበት በዚህ ወቅት፣ በምስራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ጥቃት እየተፈጸመ ይገኛል።
📌 እስካሁን የደረሰው ጉዳት፦
የሕይወት መጥፋት፦ከ37 በላይ ንጹሐን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።
የንብረት ውድመት፦234 መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል።
የሃይማኖት ተቋማት፦ታሪካዊው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል እና የኩፍቴና መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል።
⚠️ ወቅታዊ ሁኔታ፦
ጥቃቱ አሁንም በተለያዩ ቀበሌዎች (ዘዲቡ፣ እሬቻ ሚካኤል፣ ሱንቴ ማርያም...) የቀጠለ ሲሆን፣ አቅመ-ቢስ እናቶችና ሕፃናት ሕይወታቸውን ለማዳን ንብረታቸውን ጥለው በጫካዎች ውስጥ ተደብቀው ይገኛሉ።
🙏 ነፍስ ይማር!
3 days ago
ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡
ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡
ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
3 days ago
ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች! - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
***********************
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችውን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት። ለሀገራቸው የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች። ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል። ዛሬ የተደገመውም ይኸው ነው።
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች። ለዚህ ደግሞ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር።
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል። እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈው ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው።
ምርጫው እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተው ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም። ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል። ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃው ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫውን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች።
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ግንቦት 25 2018፣ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ
#ebc #ethiopia #gcs
***********************
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችውን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት። ለሀገራቸው የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች። ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል። ዛሬ የተደገመውም ይኸው ነው።
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች። ለዚህ ደግሞ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር።
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል። እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈው ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው።
ምርጫው እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተው ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም። ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል። ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃው ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫውን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች።
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ግንቦት 25 2018፣ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ
#ebc #ethiopia #gcs
3 days ago
የኢራኑ ፕሬዚዳንት የስራ
መልቀቂያ ማቅረባቸው ተሰማ
የኢራኑ ፕሬዚዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ለሀገሪቱ የበላይ መሪ ጽህፈት ቤት ይፋዊ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ምንጭ ለኢራን ኢንተርናሽናል ገልጧል። እሁድ ዕለት በተላከው በዚህ ደብዳቤ ላይ ፕሬዝዳንቱና መንግስታቸው በሀገሪቱ ዋና ዋና እና ወሳኝ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ውስጥ ሙሉ በሙሉ መገለላቸውን ፔዜሽኪያን አጽንኦት ሰጥተውበታል። በዚህም ምክንያት በተፈጠረው ክፍተት የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር ውስጥ ያሉ ጽንፈኛ አንጃዎች የሀገሪቱን ጉዳዮች እንዲቆጣጠሩ ዕድል እንደሰጣቸው ምንጩ ጠቁሟል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ በእንዲህ ያለ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ መንግስትን መምራትም ሆነ ህጋዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደማይችሉ በመግለጽ፣ በአስቸኳይ ከስልጣናቸው ለመልቀቅ መጠየቃቸውን አስታውቀዋል።
የበላይ መሪው ሞጅታባ ኻሜኒ የፕሬዝዳንቱን መልቀቂያ ይቀበሉት አይቀበሉት እስካሁን ግልጽ ባይሆንም፣ የደብዳቤው ይዘት ግን በከፍተኛ የስልጣን እርከን ላይ ታይቶ የማይታወቅና ጥልቅ የሆነ የስልጣን ክፍፍል መኖሩን በግልጽ ያሳያል። ይህ ክስተት የመጣው በመንግስትና በኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ-ደህንነት ተቋማት መካከል ለወራት የዘለቀው ውጥረት ከተቀሰቀሰ በኋላ ነው።
ኢራን ኢንተርናሽናል ቀደም ሲል እንደዘገበው፣ የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር የፕሬዝዳንቱን በርካታ ስልጣኖች ደረጃ በደረጃ በመገደብ ቁልፍ የመንግስት አካላትን በቁጥጥሩ ስር አውሏል። የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ፣ ይህ ሁኔታ የፔዜሽኪያን አስተዳደር በፖለቲካዊና አስፈፃሚ የውሳኔ ማጣት አዙሪት ውስጥ እንዲገባ ያደረገው ሲሆን፣ ይህም ዲፕሎማሲያዊ ድርድሮች ወደፊት እንዳይራመዱና በካቢኔ መዋቅር ላይ የሚፈለጉ ለውጦች እንዳይተገበሩ እንቅፋት ሆኗል።
Seledadotio
መልቀቂያ ማቅረባቸው ተሰማ
የኢራኑ ፕሬዚዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ለሀገሪቱ የበላይ መሪ ጽህፈት ቤት ይፋዊ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ምንጭ ለኢራን ኢንተርናሽናል ገልጧል። እሁድ ዕለት በተላከው በዚህ ደብዳቤ ላይ ፕሬዝዳንቱና መንግስታቸው በሀገሪቱ ዋና ዋና እና ወሳኝ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ውስጥ ሙሉ በሙሉ መገለላቸውን ፔዜሽኪያን አጽንኦት ሰጥተውበታል። በዚህም ምክንያት በተፈጠረው ክፍተት የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር ውስጥ ያሉ ጽንፈኛ አንጃዎች የሀገሪቱን ጉዳዮች እንዲቆጣጠሩ ዕድል እንደሰጣቸው ምንጩ ጠቁሟል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ በእንዲህ ያለ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ መንግስትን መምራትም ሆነ ህጋዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደማይችሉ በመግለጽ፣ በአስቸኳይ ከስልጣናቸው ለመልቀቅ መጠየቃቸውን አስታውቀዋል።
የበላይ መሪው ሞጅታባ ኻሜኒ የፕሬዝዳንቱን መልቀቂያ ይቀበሉት አይቀበሉት እስካሁን ግልጽ ባይሆንም፣ የደብዳቤው ይዘት ግን በከፍተኛ የስልጣን እርከን ላይ ታይቶ የማይታወቅና ጥልቅ የሆነ የስልጣን ክፍፍል መኖሩን በግልጽ ያሳያል። ይህ ክስተት የመጣው በመንግስትና በኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ-ደህንነት ተቋማት መካከል ለወራት የዘለቀው ውጥረት ከተቀሰቀሰ በኋላ ነው።
ኢራን ኢንተርናሽናል ቀደም ሲል እንደዘገበው፣ የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር የፕሬዝዳንቱን በርካታ ስልጣኖች ደረጃ በደረጃ በመገደብ ቁልፍ የመንግስት አካላትን በቁጥጥሩ ስር አውሏል። የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ፣ ይህ ሁኔታ የፔዜሽኪያን አስተዳደር በፖለቲካዊና አስፈፃሚ የውሳኔ ማጣት አዙሪት ውስጥ እንዲገባ ያደረገው ሲሆን፣ ይህም ዲፕሎማሲያዊ ድርድሮች ወደፊት እንዳይራመዱና በካቢኔ መዋቅር ላይ የሚፈለጉ ለውጦች እንዳይተገበሩ እንቅፋት ሆኗል።
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
4 days ago
ሳውዲ አረቢያ በእስራኤል የተፈጸመውን የሊባኖስ ወታደራዊ ወረራ ኮነነች
#ethiopia | እስራኤል በሊባኖስ ላይ የከፈተችውን ወታደራዊ ጥቃት ሳውዲ አረቢያ አጥብቃ ያወገዘች ሲሆን የእስራኤል ጦር የሊባኖስን ድንበር ጥሶ መግባቱንና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት መጣሱን በፍጹም እንደማትቀበለው የሳውዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተጀመረውን ወረራ ለማስቆም እንዲሁም የእስራኤል ወታደራዊ ኃይል በሊባኖስ መሬት ላይ የሚያደርገውን መስፋፋት እንዲያበቃ የድርሻውን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪም የሊባኖስን ሉዓላዊ ፖለቲካዊ መብትና የህዝቧን ሰላም ማስከበር ከዓለም አቀፍ ስምምነቶች አንጻር ወሳኝ መሆኑን ሳውዲ አረቢያ በአጽንኦት ገልጻለች።
የሊባኖስ መንግስት በመላው የአገሪቱ ክልሎች ላይ ሙሉ ስልጣኑን እና ቁጥጥሩን መዘርጋት እንዲችል የጣኢፍ ስምምነት መከበር እንዳለበትም ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል።
በመጨረሻም ማንኛውም ዓይነት የጦር መሳሪያ በመንግስትና በህጋዊ የጸጥታ ተቋማት ቁጥጥር ስር ብቻ እንዲሆን የሊባኖስ ባለስልጣናት ያስተላለፉትን ውሳኔ ወደ ተግባር መለወጥ እንደሚገባ የሳውዲ መንግስት አመልክቷል።
ይህ ተግባር በሊባኖስ ምድር ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
#saudiarabia #israel #lebanon #middleeast #news #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | እስራኤል በሊባኖስ ላይ የከፈተችውን ወታደራዊ ጥቃት ሳውዲ አረቢያ አጥብቃ ያወገዘች ሲሆን የእስራኤል ጦር የሊባኖስን ድንበር ጥሶ መግባቱንና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት መጣሱን በፍጹም እንደማትቀበለው የሳውዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተጀመረውን ወረራ ለማስቆም እንዲሁም የእስራኤል ወታደራዊ ኃይል በሊባኖስ መሬት ላይ የሚያደርገውን መስፋፋት እንዲያበቃ የድርሻውን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪም የሊባኖስን ሉዓላዊ ፖለቲካዊ መብትና የህዝቧን ሰላም ማስከበር ከዓለም አቀፍ ስምምነቶች አንጻር ወሳኝ መሆኑን ሳውዲ አረቢያ በአጽንኦት ገልጻለች።
የሊባኖስ መንግስት በመላው የአገሪቱ ክልሎች ላይ ሙሉ ስልጣኑን እና ቁጥጥሩን መዘርጋት እንዲችል የጣኢፍ ስምምነት መከበር እንዳለበትም ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል።
በመጨረሻም ማንኛውም ዓይነት የጦር መሳሪያ በመንግስትና በህጋዊ የጸጥታ ተቋማት ቁጥጥር ስር ብቻ እንዲሆን የሊባኖስ ባለስልጣናት ያስተላለፉትን ውሳኔ ወደ ተግባር መለወጥ እንደሚገባ የሳውዲ መንግስት አመልክቷል።
ይህ ተግባር በሊባኖስ ምድር ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
#saudiarabia #israel #lebanon #middleeast #news #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 days ago
ትምህርት ቤቶች አይዘጉም‼️
"ትምህርት ቤቶች እስከ ረቡዕ ዝግ ይሆናሉ" በሚል በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ እንደሆነ ተገለጸ።
"ከነገ ጀምሮ ሁሉም መደበኛ ስራዎች ይቀጥላሉ" ምርጫ ቦርድ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዛሬ ግንቦት 24/2018 ከማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ እንደሚገኝ ይታወቃል።
በዚህም መሠረት በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ እና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ እንዲጠቀሙ የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት ከሚሰጡ ተቋማት በስተቀር በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ብቻ ዝግ እንዲያደርጉ ምርጫ ቦርድ ማስታወቁ ይታወቃል::
በዚህም መሰረት ከነገ ማክሰኞ ዕለት ጀምሮ መደበኛ የመንግስትና የግል ተቋማት ስራ እንደሚቀጥል ቦርዱ አመልክቷል።
በአንዳድ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች "ትምህርት ቤቶች እስከ ረቡዕ ዝግ ይሆናሉ" ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ እንደሆነ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
Seledadotio
Seledadotio
"ትምህርት ቤቶች እስከ ረቡዕ ዝግ ይሆናሉ" በሚል በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ እንደሆነ ተገለጸ።
"ከነገ ጀምሮ ሁሉም መደበኛ ስራዎች ይቀጥላሉ" ምርጫ ቦርድ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዛሬ ግንቦት 24/2018 ከማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ እንደሚገኝ ይታወቃል።
በዚህም መሠረት በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ እና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ እንዲጠቀሙ የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት ከሚሰጡ ተቋማት በስተቀር በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ብቻ ዝግ እንዲያደርጉ ምርጫ ቦርድ ማስታወቁ ይታወቃል::
በዚህም መሰረት ከነገ ማክሰኞ ዕለት ጀምሮ መደበኛ የመንግስትና የግል ተቋማት ስራ እንደሚቀጥል ቦርዱ አመልክቷል።
በአንዳድ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች "ትምህርት ቤቶች እስከ ረቡዕ ዝግ ይሆናሉ" ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ እንደሆነ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
ኪዱ አረፈ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
5 days ago
የእንግሊዝ የጉዞ ማሳሰቢያ‼️
ብሪታንያ ወደ ኢትዮጵያ ለሚጓዙ ዜጎቿ የጉዞ ማሳሰቢያ ሰጠች‼️
የብሪታንያ መንግስት ዛሬ ባወጣው የጉዞ ማሳሰቢያ ነገ የሚካሄደውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ ዜጎቿ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል።
ማስጠንቀቂያው አብዛኛውን የኢትዮጵያ ክፍል ለጉዞ አደገኛ አድርጎ በመጥቀስ ዜጎቹ ወደ ትግራይ፣ አማራ፣በአፋር እና ጋምቤላ ክልሎች ሙሉ በሙሉ እና ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት በምትዋሰንባቸው የድንበር አካባቢዎች ከአሥር እስከ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ማንኛውም ዜጋ እንዳይንቀሳቀስ አሳስቧል።
በኦሮሚያ ክልል ከዋና ዋና መንገዶች እና ከተሞች በስተቀር ከኬንያ ጋር በሚያዋስነው ድንበር በ10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕራብ ሸዋ ፣በሰሜን ሸዋ ዞን ምዕራብ ዋናውን የአዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ የሚወስደውን መንገድ ጨምሮ ምዕራብ ወለጋ እና ምስራቅ ወለጋ ዞን፣ ቄለምም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ እንዳይጓዙ አሳስቧል።
ከአዲስ አበባ እስከ አዳማ ካለው የፍጥነት መንገድ በስተቀር የምስራቅ ሸዋ ዞንም ማስጠንቀቂያ ከወጣባቸው ቦታዎች መካከል አንዱ ነው።
በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን፤ በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ደግሞ ከሱዳን ጋር ባለው ድንበር በ20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሜተከል ዞን የማኦኮሞ ልዩ ዞን አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ሁሉንም ጉዞዎች እንዳይደረግ ይመክራል።
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 በሚካሄደው ምርጫ ምክንያት የህዝብ እንደ ባንኮች ያሉ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ስለሚዘጉ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
በምርጫ ጣቢያዎች ዙሪያ ከፍተኛ ጥበቃ ይደረግላቸዋል፣ እንዲሁም የተሽከርካሪና የመታወቂያ ፍተሻዎች ይኖራሉ ብሏል።
አላስፈላጊ ጉዞዎችን ከማድረግ እንዲቆጠቡ ፣ከአካባቢው ባለስልጣናት የተሰጡ መመሪያዎችን እንዲከተሉ እና እና መታወቂያ እንዲይዙ ዜጎቹን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
ብሪታንያ ወደ ኢትዮጵያ ለሚጓዙ ዜጎቿ የጉዞ ማሳሰቢያ ሰጠች‼️
የብሪታንያ መንግስት ዛሬ ባወጣው የጉዞ ማሳሰቢያ ነገ የሚካሄደውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ ዜጎቿ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል።
ማስጠንቀቂያው አብዛኛውን የኢትዮጵያ ክፍል ለጉዞ አደገኛ አድርጎ በመጥቀስ ዜጎቹ ወደ ትግራይ፣ አማራ፣በአፋር እና ጋምቤላ ክልሎች ሙሉ በሙሉ እና ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት በምትዋሰንባቸው የድንበር አካባቢዎች ከአሥር እስከ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ማንኛውም ዜጋ እንዳይንቀሳቀስ አሳስቧል።
በኦሮሚያ ክልል ከዋና ዋና መንገዶች እና ከተሞች በስተቀር ከኬንያ ጋር በሚያዋስነው ድንበር በ10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕራብ ሸዋ ፣በሰሜን ሸዋ ዞን ምዕራብ ዋናውን የአዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ የሚወስደውን መንገድ ጨምሮ ምዕራብ ወለጋ እና ምስራቅ ወለጋ ዞን፣ ቄለምም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ እንዳይጓዙ አሳስቧል።
ከአዲስ አበባ እስከ አዳማ ካለው የፍጥነት መንገድ በስተቀር የምስራቅ ሸዋ ዞንም ማስጠንቀቂያ ከወጣባቸው ቦታዎች መካከል አንዱ ነው።
በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን፤ በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ደግሞ ከሱዳን ጋር ባለው ድንበር በ20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሜተከል ዞን የማኦኮሞ ልዩ ዞን አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ሁሉንም ጉዞዎች እንዳይደረግ ይመክራል።
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 በሚካሄደው ምርጫ ምክንያት የህዝብ እንደ ባንኮች ያሉ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ስለሚዘጉ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
በምርጫ ጣቢያዎች ዙሪያ ከፍተኛ ጥበቃ ይደረግላቸዋል፣ እንዲሁም የተሽከርካሪና የመታወቂያ ፍተሻዎች ይኖራሉ ብሏል።
አላስፈላጊ ጉዞዎችን ከማድረግ እንዲቆጠቡ ፣ከአካባቢው ባለስልጣናት የተሰጡ መመሪያዎችን እንዲከተሉ እና እና መታወቂያ እንዲይዙ ዜጎቹን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
5 days ago
ዴሞክራሲን ለማፅናት የአፍሪካ ሀገራት አንዱ ከሌላው ሊማር ይገባል – ኡሁሩ ኬንያታ
#ethiopia | በአፍሪካ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርና የምርጫ ስርዓትን ለማጠናከር የአፍሪካ ሀገራት አንዳቸው ከሌላቸው ልምድ መቅሰም አለባቸው አሉ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ፡፡
ነገ የሚካሄደውን ምርጫ ለመታዘብ አዲስ አበባ የሚገኙት ኡሁሩ ኬንያታ እንዳሉት፤ በአፍሪካ ህብረት ስር የተካሄዱ ምርጫን የመታዘብ ተግባራት የምርጫ ሂደቶችን ከመከታተል ያለፈ አስተዋጽኦ አላቸው።
ምርጫ የመታዘብ ተግባራቱ በአባል ሀገራቱ መካከል የልምድ ልውውጥና መልካም ተሞክሮዎችን በመቅሰም ዴሞክራሲያዊ ልማትን ለማስፈን ጭምር የተነደፉ ናቸው ብለዋል፡፡
የአፍሪካ ህብረት የዴሞክራሲ ስርዓትን የበለጠ ለማጎልበት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የአቻ ለአቻ ትምህርትን ለማበረታታት የሚደረገው ጥረት አካል በመሆኑ በአህጉሪቱ በሚደረጉ ምርጫዎች በታዛቢነት እንደሚሳተፍ ጠቁመዋል።
የምርጫ ታዛቢነት ተልዕኮዎች እና ሌሎች የአፍሪካ ህብረት አሰራሮች ሀገራት ልምድ እንዲለዋወጡ፣ ስኬታማ አካሄዶችን እንዲለዩ እና የዴሞክራሲ ተቋማትን ሊያጠናክሩ የሚችሉ ትምህርቶችን እንዲለማመዱ እድል ይፈጥራል ነው ያሉት።
የአፍሪካ ሀገራት በሌሎች አህጉራት/አካባቢዎች የተዘጋጁ የአስተዳደር ስልቶችን ለመተግበር በአህጉሪቱ ነባራዊ ሁኔታ እና ልምድ የተደገፈ ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአፍሪካ ሀገራት መካከል የሚደረግ የተሞክሮ ልውውጥ ሀገር በቀል ዴሞክራሲዊ ልምምዶችን ያመጣል ብለዋል፡፡
አፍሪካዊያን መር የሆነ ዴሞክራሲን የማጠናከር አካሄድ “ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄዎች” ለሚለው መርህ ማዕከል ሆኖ እንደሚቀጥል አፅንዖት ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc
#ethiopia | በአፍሪካ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርና የምርጫ ስርዓትን ለማጠናከር የአፍሪካ ሀገራት አንዳቸው ከሌላቸው ልምድ መቅሰም አለባቸው አሉ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ፡፡
ነገ የሚካሄደውን ምርጫ ለመታዘብ አዲስ አበባ የሚገኙት ኡሁሩ ኬንያታ እንዳሉት፤ በአፍሪካ ህብረት ስር የተካሄዱ ምርጫን የመታዘብ ተግባራት የምርጫ ሂደቶችን ከመከታተል ያለፈ አስተዋጽኦ አላቸው።
ምርጫ የመታዘብ ተግባራቱ በአባል ሀገራቱ መካከል የልምድ ልውውጥና መልካም ተሞክሮዎችን በመቅሰም ዴሞክራሲያዊ ልማትን ለማስፈን ጭምር የተነደፉ ናቸው ብለዋል፡፡
የአፍሪካ ህብረት የዴሞክራሲ ስርዓትን የበለጠ ለማጎልበት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የአቻ ለአቻ ትምህርትን ለማበረታታት የሚደረገው ጥረት አካል በመሆኑ በአህጉሪቱ በሚደረጉ ምርጫዎች በታዛቢነት እንደሚሳተፍ ጠቁመዋል።
የምርጫ ታዛቢነት ተልዕኮዎች እና ሌሎች የአፍሪካ ህብረት አሰራሮች ሀገራት ልምድ እንዲለዋወጡ፣ ስኬታማ አካሄዶችን እንዲለዩ እና የዴሞክራሲ ተቋማትን ሊያጠናክሩ የሚችሉ ትምህርቶችን እንዲለማመዱ እድል ይፈጥራል ነው ያሉት።
የአፍሪካ ሀገራት በሌሎች አህጉራት/አካባቢዎች የተዘጋጁ የአስተዳደር ስልቶችን ለመተግበር በአህጉሪቱ ነባራዊ ሁኔታ እና ልምድ የተደገፈ ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአፍሪካ ሀገራት መካከል የሚደረግ የተሞክሮ ልውውጥ ሀገር በቀል ዴሞክራሲዊ ልምምዶችን ያመጣል ብለዋል፡፡
አፍሪካዊያን መር የሆነ ዴሞክራሲን የማጠናከር አካሄድ “ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄዎች” ለሚለው መርህ ማዕከል ሆኖ እንደሚቀጥል አፅንዖት ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc
Sponsored by
Surafel
Comments