4 hours ago
"ወንድሜ ፑቲን መጸዳጃ ቤት ሆኜ አጠቃላይ የሩስያን የጂፒኤስ ስርዓት ማቋረጥ እችላለሁ" ኢሎን መስክ
#ethiopia | ስታርሊንክ በስትራቴጂካዊ እንቅስቃሴዎቻችን ላይ ጣልቃ እየገባበት ያለበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ለኢሎን መስክ የ48 ሰዓት የጊዜ ገደብ ከተሰጠውና "ትዕግስታችንን አትፈታተን" የሚል ማስጠንቀቂያ ከቀረበበት በኋላ ቢሊየነሩ አሻፈረኝ ብሏል።
መስክ ለቀረበበት ማስጠንቀቂያ በሰጠው ቀጥተኛና ያልተጠበቀ ምላሽ "ወንድሜ ከመጸዳጃ ቤት ቁጭ ብዬ በስልኬ ብቻ የሀገራችሁን ሙሉ የጂፒኤስ (GPS) ስርዓት ማቋረጥ እችላለሁ" በማለት መልስ ሰጥቷል።
ይህ ድፍረት የተቀላቀለበትና ያልተጠበቀ ምላሽ ባለሃብቱ ላይ ምን መዘዝ ይዞበት እንደሚመጣ ወደፊት የምናየው ቢሆንም አንዳንዶች ''ፑቲን ሚሳዔል እንዳይተኩስበት ፈርተናል'' በማለት ተሳልቀዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ስታርሊንክ በስትራቴጂካዊ እንቅስቃሴዎቻችን ላይ ጣልቃ እየገባበት ያለበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ለኢሎን መስክ የ48 ሰዓት የጊዜ ገደብ ከተሰጠውና "ትዕግስታችንን አትፈታተን" የሚል ማስጠንቀቂያ ከቀረበበት በኋላ ቢሊየነሩ አሻፈረኝ ብሏል።
መስክ ለቀረበበት ማስጠንቀቂያ በሰጠው ቀጥተኛና ያልተጠበቀ ምላሽ "ወንድሜ ከመጸዳጃ ቤት ቁጭ ብዬ በስልኬ ብቻ የሀገራችሁን ሙሉ የጂፒኤስ (GPS) ስርዓት ማቋረጥ እችላለሁ" በማለት መልስ ሰጥቷል።
ይህ ድፍረት የተቀላቀለበትና ያልተጠበቀ ምላሽ ባለሃብቱ ላይ ምን መዘዝ ይዞበት እንደሚመጣ ወደፊት የምናየው ቢሆንም አንዳንዶች ''ፑቲን ሚሳዔል እንዳይተኩስበት ፈርተናል'' በማለት ተሳልቀዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
5 hours ago
ቤተሰብ ለመጠየቅ የሄደችውን ባለትዳር አስገድዶ መድፈር የፈፀመው አጓቷ እና ሌላኛው ተከሳሽ በእስራት ተቀጡ
በካምባ ዙሪያ ወረዳ ኦቶሎ ቀበሌ ከርሼ በተባለ አካባቢ ነው የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው።
ፖሊስ እንዳታወቀው ተበዳይ 22 ዓመቷ ሲሆ ባለትዳር ናት ቤተሰቦቿን ለመጠየቅ በመንገድ ላይ እየተጓዘች ባለችበት ወቅት ተከሳሾቹ እንዳገኟት ተገልጿል።
በዚህም ከተከሳሾቹ መካከል አንደኛው የተበዳይዋ አጎት ሲሆን ይህንን የቤተሰብ ቅርበት በመጠቀም ተበዳይዋ ሌሊቱን በሌላኛው ተከሳሽ ቤት አድራ በማግስቱ እንድትጓዝ በማሳመን ይዟት ይሄዳል።
ሆኖም በጫካ ውስጥ ከደረሱ በኋላ ተከሳሾቹ ተበዳይዋን በዱላ በመምታት ራሷን መከላከል እንዳትችል ካደረጉ በኋላ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈፀማቸውን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በደረሰው ወንጀል ተበዳይዋ ያቀረበችውን አቤቱታ ተከትሎ ፖሊስ ምርመራ በማካሄድ የተበዳይዋን ቃል ጨምሮ በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች የተደገፈ መሆኑን በመግለጽ የምርመራ መዝገቡ ለዐቃቤ ህግ ይልካል።
ዐቃቤ ህግም ክስ መስርቶ ጉዳዩን ለካምባ ዙሪያ ወረዳ ፍርድ ቤት ያቀርባል።ፍርድ ቤቱም በጉዳዩ ላይ የቀረቡትን ማስረጃዎችና የተከራካሪ ወገኖችን አቋም ከመረመረ በኋላ፣ የዋና ወንጀል አድራጊው ከተበዳይዋ ጋር የቅርብ የስጋ ዝምድና ያለው በመሆኑ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት 1ኛ ተከሳሽ አየለ ባርጋደ በ14 ዓመት ፅኑ እስራት፣ 2ኛ ተከሳሽ ጹንዖ ገርሻ ደግሞ በ13 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ መወሰኑን ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በካምባ ዙሪያ ወረዳ ኦቶሎ ቀበሌ ከርሼ በተባለ አካባቢ ነው የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው።
ፖሊስ እንዳታወቀው ተበዳይ 22 ዓመቷ ሲሆ ባለትዳር ናት ቤተሰቦቿን ለመጠየቅ በመንገድ ላይ እየተጓዘች ባለችበት ወቅት ተከሳሾቹ እንዳገኟት ተገልጿል።
በዚህም ከተከሳሾቹ መካከል አንደኛው የተበዳይዋ አጎት ሲሆን ይህንን የቤተሰብ ቅርበት በመጠቀም ተበዳይዋ ሌሊቱን በሌላኛው ተከሳሽ ቤት አድራ በማግስቱ እንድትጓዝ በማሳመን ይዟት ይሄዳል።
ሆኖም በጫካ ውስጥ ከደረሱ በኋላ ተከሳሾቹ ተበዳይዋን በዱላ በመምታት ራሷን መከላከል እንዳትችል ካደረጉ በኋላ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈፀማቸውን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በደረሰው ወንጀል ተበዳይዋ ያቀረበችውን አቤቱታ ተከትሎ ፖሊስ ምርመራ በማካሄድ የተበዳይዋን ቃል ጨምሮ በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች የተደገፈ መሆኑን በመግለጽ የምርመራ መዝገቡ ለዐቃቤ ህግ ይልካል።
ዐቃቤ ህግም ክስ መስርቶ ጉዳዩን ለካምባ ዙሪያ ወረዳ ፍርድ ቤት ያቀርባል።ፍርድ ቤቱም በጉዳዩ ላይ የቀረቡትን ማስረጃዎችና የተከራካሪ ወገኖችን አቋም ከመረመረ በኋላ፣ የዋና ወንጀል አድራጊው ከተበዳይዋ ጋር የቅርብ የስጋ ዝምድና ያለው በመሆኑ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት 1ኛ ተከሳሽ አየለ ባርጋደ በ14 ዓመት ፅኑ እስራት፣ 2ኛ ተከሳሽ ጹንዖ ገርሻ ደግሞ በ13 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ መወሰኑን ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
5 hours ago
አቃቢ ህግ አቅርቦት የነበረው አቤቱታ ውድቅ ተደረገ
በ'ፊንቴክ ኢንቨስትመንት' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች የዋስትና መብታቸው ተነስቶ ጉዳያቸውን በእስር ላይ ሆነው እንዲከታተሉ አቃቢ ህግ አቅርቦት የነበረው አቤቱታ ውድቅ እንዲደረግ እና በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ብይን ተሰጠ።
አቃቢ ህግ በከፍተኛ የኢንቨስትመንት ማጭበርበር ወንጀል ተከሰው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙ ተከሳሾች እና ጠበቃቸው፣ የተከሰሱበት የክስ መዝገቡ በክርክር ሂደት ላይ የሚገኝ እና በችሎት ውሳኔ ያልተሰጠበት ሆኖ እያለ በሚዲያ ላይ በመቅረብ ከክሱ አውድ ውጪ የሆነ ማብራሪያ በመስጠታቸው የፍትሕ ሂደቱን ተጽዕኖ ውስጥ ለመክተት እና ምስክሮችን ላይ ተጽዕኖ ለማድረግ ሞክረዋል በሚል የዋስትና መብታቸው ተነስቶ ከማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ የሚል አቤቱታ አቅርቦ ነበር።
በተጨማሪም ዘገባው የተጫነበት ሚዲያ ይቅርታ እንዲጠይቅ እና ቪዲዮውን እንዲያወርድ ፣ በወንጀል ህግ አንቀጽ 457 ስር በቀጥታ እንዲቀጡ እንዲወሰን የሚሉ አቤቱታዎችንም አቃቢ ህግ አካቷል።
Seledadotio
Seledadotio
በ'ፊንቴክ ኢንቨስትመንት' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች የዋስትና መብታቸው ተነስቶ ጉዳያቸውን በእስር ላይ ሆነው እንዲከታተሉ አቃቢ ህግ አቅርቦት የነበረው አቤቱታ ውድቅ እንዲደረግ እና በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ብይን ተሰጠ።
አቃቢ ህግ በከፍተኛ የኢንቨስትመንት ማጭበርበር ወንጀል ተከሰው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙ ተከሳሾች እና ጠበቃቸው፣ የተከሰሱበት የክስ መዝገቡ በክርክር ሂደት ላይ የሚገኝ እና በችሎት ውሳኔ ያልተሰጠበት ሆኖ እያለ በሚዲያ ላይ በመቅረብ ከክሱ አውድ ውጪ የሆነ ማብራሪያ በመስጠታቸው የፍትሕ ሂደቱን ተጽዕኖ ውስጥ ለመክተት እና ምስክሮችን ላይ ተጽዕኖ ለማድረግ ሞክረዋል በሚል የዋስትና መብታቸው ተነስቶ ከማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ የሚል አቤቱታ አቅርቦ ነበር።
በተጨማሪም ዘገባው የተጫነበት ሚዲያ ይቅርታ እንዲጠይቅ እና ቪዲዮውን እንዲያወርድ ፣ በወንጀል ህግ አንቀጽ 457 ስር በቀጥታ እንዲቀጡ እንዲወሰን የሚሉ አቤቱታዎችንም አቃቢ ህግ አካቷል።
Seledadotio
Seledadotio
5 hours ago
ሞተር ብስክሌት በመጠቀም የቅሚያ ወንጀል የፈፀመው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡
ዳግም ሙላት የተባለው ተጠርጣሪ ሞተር ብስክሌት በመጠቀም የቅሚያ ወንጀሉን የፈፀመው ሀምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ጎሮ ትምህርት ቤት አካባቢ ከቀኑ 5፡00 ሠዓት ነው፡፡
የግል ተበዳይ አብዱልከሪም አማን መንገድ ላይ ቆመው ታክሲ በሚጠብቁበት ወቅት ተጠርጣሪው የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3-7850 አ/አ ሞተር ባይስክል እያሽከረከረ ከኋላቸው በመምጣት 100ሺህ ብር የሚያወጣ ሳምሰንግ ስልክ ቀምቶ ከአካባቢው ለመሰወር ሲሞክር በህብረተሰቡና በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የሰፈራ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡
አብዛኛው የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች የትራፊክ ህግን በማክበርና ወንጀልን ለመከላከል የበኩላቸውን ድጋፍ እያደረጉ ቢገኙም መሰል ግለሰቦች መኖራቸውን በመረዳት ህብረተሰቡ ንብረቱ ላይ በቂ ጥንቃቄና ትኩረት ሊያደርግ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅለይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል ፡፡
ዳግም ሙላት የተባለው ተጠርጣሪ ሞተር ብስክሌት በመጠቀም የቅሚያ ወንጀሉን የፈፀመው ሀምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ጎሮ ትምህርት ቤት አካባቢ ከቀኑ 5፡00 ሠዓት ነው፡፡
የግል ተበዳይ አብዱልከሪም አማን መንገድ ላይ ቆመው ታክሲ በሚጠብቁበት ወቅት ተጠርጣሪው የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3-7850 አ/አ ሞተር ባይስክል እያሽከረከረ ከኋላቸው በመምጣት 100ሺህ ብር የሚያወጣ ሳምሰንግ ስልክ ቀምቶ ከአካባቢው ለመሰወር ሲሞክር በህብረተሰቡና በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የሰፈራ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡
አብዛኛው የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች የትራፊክ ህግን በማክበርና ወንጀልን ለመከላከል የበኩላቸውን ድጋፍ እያደረጉ ቢገኙም መሰል ግለሰቦች መኖራቸውን በመረዳት ህብረተሰቡ ንብረቱ ላይ በቂ ጥንቃቄና ትኩረት ሊያደርግ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅለይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል ፡፡
6 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ በመገንባት ላይ ባለው "በዳ ቡና" (የቡና ከፍታ) የተሰኘ የፓርክ ፕሮጀክት ምክንያት፣ አስተዳደሩ ህያዋንን ከመኖሪያቸው ከማፈናቀል አልፎ ታሪካዊ እና ሀይማኖታዊ ክብር ያላቸውን የመቃብር ስፍራዎች ለማፍረስ እንቅስቃሴ መጀመሩን ተከትሎ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ እና ውጥረት መንገሱ ተጋለጠ።
የአካባቢው ምንጮች ባወጡት መረጃ መሰረት፣ የጅማ ከተማ አስተዳደር ታሪካዊውን የአባ ጅፋር ቤተ-መንግስት የሚያጠቃልል ሰፊ የፓርክ ግንባታ እያከናወነ ይገኛል። ይህንን የፓርክ ግንባታ ተከትሎ በቤተ-መንግስቱ ዙሪያ ይኖሩ የነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ቀድመው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ ፕሮጀክቱ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች እና ራሳቸው አባ ጅፋር ያረፉበትን ታላቁን የመቃብር ስፍራ (ቀብሪ ጀመዓ) እንዲሁም ታሪካዊውን "የ40ዎቹ መስጊድ" አጠቃልሏል በሚል ስፍራውን በማፍረስ አስከሬን ለማውጣት ዝግጅት መጠናቀቁ ተገልጿል።
ከቀናት በፊት የከተማው አስተዳደር መቃብሮቹን ለማፍረስ ከባድ ማሽኖችን ይዞ ወደ ስፍራው ያመራ ቢሆንም፣ የአካባቢው ማህበረሰብ በከፍተኛ ተቃውሞ ወጥቶ ከማሽኖቹ ፊት በመቆም ድርጊቱን ለጊዜው ሊያስቆመው መቻሉ ታውቋል።
ሆኖም የጅማ ከተማ ካቢኔ አመራሮች፣ ይህ ታሪካዊ የመቃብር ስፍራ እንዲፈርስ እና አስከሬን እንዲወጣ የተሰጠው ትዕዛዝ በቀጥታ ከኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የመጣ በመሆኑ፣ ትዕዛዙን ወደ ኋላ መመለስም ሆነ ማፍረሱን ማቆም እንደማይችሉ መናገራቸውን ነዋሪዎች አጋልጠዋል። የአስተዳደሩ ዕቅድ የመቃብር ስፍራውን በማፍረስ የሟቾችን አጥንት ሰብስቦ፣ እስላማዊ ህግጋትን በሚጻረር መልኩ በአንድ የጋራ ጉድጓድ ውስጥ በጅምላ ለመቅበር መሆኑ ማህበረሰቡን ክፉኛ አስቆጥቷል።
ይህ የመንግስት እርምጃ የእስልምና ሀይማኖት ህግን፣ የአካባቢውን ታላቅ ባህል፣ ሞራላዊ እሴት (ሰፉ) እና የጅማን ህዝብ ክብር በእጅጉ የሚነካ እና የሚያዋርድ ታሪካዊ ስህተት መሆኑን የሚገልጹት ነዋሪዎቹ፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ)፣ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች (ኡለማዎች) አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጡበት፣ እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ለህዝቡ ድምጽ በመሆን ይህን ህገ-ወጥ እና አሳዛኝ ድርጊት እንዲያስቆሙላቸው አጥብቀው ተማጽነዋል።
የአካባቢው ምንጮች ባወጡት መረጃ መሰረት፣ የጅማ ከተማ አስተዳደር ታሪካዊውን የአባ ጅፋር ቤተ-መንግስት የሚያጠቃልል ሰፊ የፓርክ ግንባታ እያከናወነ ይገኛል። ይህንን የፓርክ ግንባታ ተከትሎ በቤተ-መንግስቱ ዙሪያ ይኖሩ የነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ቀድመው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ ፕሮጀክቱ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች እና ራሳቸው አባ ጅፋር ያረፉበትን ታላቁን የመቃብር ስፍራ (ቀብሪ ጀመዓ) እንዲሁም ታሪካዊውን "የ40ዎቹ መስጊድ" አጠቃልሏል በሚል ስፍራውን በማፍረስ አስከሬን ለማውጣት ዝግጅት መጠናቀቁ ተገልጿል።
ከቀናት በፊት የከተማው አስተዳደር መቃብሮቹን ለማፍረስ ከባድ ማሽኖችን ይዞ ወደ ስፍራው ያመራ ቢሆንም፣ የአካባቢው ማህበረሰብ በከፍተኛ ተቃውሞ ወጥቶ ከማሽኖቹ ፊት በመቆም ድርጊቱን ለጊዜው ሊያስቆመው መቻሉ ታውቋል።
ሆኖም የጅማ ከተማ ካቢኔ አመራሮች፣ ይህ ታሪካዊ የመቃብር ስፍራ እንዲፈርስ እና አስከሬን እንዲወጣ የተሰጠው ትዕዛዝ በቀጥታ ከኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የመጣ በመሆኑ፣ ትዕዛዙን ወደ ኋላ መመለስም ሆነ ማፍረሱን ማቆም እንደማይችሉ መናገራቸውን ነዋሪዎች አጋልጠዋል። የአስተዳደሩ ዕቅድ የመቃብር ስፍራውን በማፍረስ የሟቾችን አጥንት ሰብስቦ፣ እስላማዊ ህግጋትን በሚጻረር መልኩ በአንድ የጋራ ጉድጓድ ውስጥ በጅምላ ለመቅበር መሆኑ ማህበረሰቡን ክፉኛ አስቆጥቷል።
ይህ የመንግስት እርምጃ የእስልምና ሀይማኖት ህግን፣ የአካባቢውን ታላቅ ባህል፣ ሞራላዊ እሴት (ሰፉ) እና የጅማን ህዝብ ክብር በእጅጉ የሚነካ እና የሚያዋርድ ታሪካዊ ስህተት መሆኑን የሚገልጹት ነዋሪዎቹ፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ)፣ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች (ኡለማዎች) አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጡበት፣ እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ለህዝቡ ድምጽ በመሆን ይህን ህገ-ወጥ እና አሳዛኝ ድርጊት እንዲያስቆሙላቸው አጥብቀው ተማጽነዋል።
6 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ውጥረት በነገሰበት በአሁኑ ወቅት፣ የቀይ ባህር ቀጠና ሀገራት የራሳቸውን የጋራ ደህንነት እና ሰፋ ያለ የትብብር ማዕቀፍ መዘርጋት ከምንጊዜውም በላይ አጣዳፊ መሆኑን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ይህንን ያስታወቁት ኤርትራ ከጥቂት ዓመታት በፊት በቀይ ባህር እና አደን ባህረ ሰላጤ ዳርቻ ሀገራት ምክር ቤት አቅርባው የነበረውን ባለ 12 ነጥብ የደህንነት እና የትብብር ሰነድ ዳግም በትዊተር (ኤክስ) ገጻቸው ይፋ ባደረጉበት ወቅት ነው።
ከዚህ የጸጥታ ማዕቀፍ ጀርባ ያለው ዋነኛ የፖለቲካ እና የኦፕሬሽን ስሌት፣ የቀጠናው ሀገራት በጉዳያቸው ላይ ሙሉ ባለቤትነት እና ወሳኝነት እንዲኖራቸው ማድረግ መሆኑን ሰነዱ ያብራራል። በተለይም ቀጠናውን ከዓለም አቀፍ ኃያላን ሀገራት የፉክክር እና የፖላራይዜሽን አውድማነት ማዳን፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥ አቅምን በመገንባት በዋና ባለድርሻ አካላት መካከል ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ የኤርትራ ቁልፍ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ፍላጎት መሆኑ ተጠቁሟል። ይህ ማዕቀፍ አሁን ካለው ተለዋዋጭ የቀጠናው የጂኦ-ፖለቲካዊ እውነታ አንጻር፣ በየጊዜው በሚደረጉ ጥልቅ ውይይቶች ሊዳብር የሚችል መሰረታዊ ግብዓት መሆኑንም ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጉት ሰነድ በዋናነት በቀይ ባህር እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያሉትን እውነታዎች ከሁሉም አቅጣጫዎች አድልዎ በሌለው መንገድ መገምገም እና ግቦችን በግልጽ ማስቀመጥ ላይ ያተኩራል። ከዚህም ባሻገር በቀይ ባህር ሰላም እና ደህንነት ላይ የተጋረጡ ስጋቶችን በዝርዝር በመለየት እና በመፈረጅ፣ እነዚህን ስጋቶች ለመቆጣጠር እና ለማስወገድ የሚያስችሉ ተግባራዊ ስትራቴጂዎችን ከገንቢ የትብብር ፖሊሲዎች ጋር በማስተሳሰር መንደፍ እንደሚያስፈልግ ሰነዱ ያብራራል። እነዚህን ስትራቴጂዎች ወደ መሬት ለማውረድም ዝርዝር እቅዶችን፣ የአፈጻጸም ዘዴዎችን፣ መዋቅሮችን እና አስፈላጊ ግብዓቶችን ማሰባሰብ ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል።
የዚህ ስትራቴጂካዊ ሰነድ እጅግ አሳሳቢ እና ትልቁን ፖለቲካዊ አንድምታ የያዘው ክፍል፣ የባህር ዳርቻ ሀገራት የሉዓላዊነት እና ራስን በራስ የመከላከል መብትን የሚመለከተው ነው። ማንኛውም የሚዋቀር የቀጠናው የደህንነት ማዕቀፍ በሉዓላዊነት መከበር እና በዓለም አቀፍ ህግ ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት ሰነዱ ያስገድዳል። በተለይም ሁሉም የባህር ዳርቻ ሀገራት የራሳቸውን የባህር ኃይል እና የመከላከያ አቅም በራሳቸው መገንባት እንዳለባቸው እና ይህንንም የጸጥታ ኃላፊነት ለሌሎች የውጭ ኃይሎች በውክልና መስጠት እንደሌለባቸው ኤርትራ በጥብቅ አሳስባለች።
በተናጠል አቅም ሊፈቱ የማይችሉ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ ሀገራቱ በጋራ ጥረት እና ቅንጅት መፍታት እንደሚገባቸው ሰነዱ ያስቀምጣል። ሆኖም ከቀጠናው የጋራ አቅም በላይ ለሆኑ ልዩ ተልዕኮዎች የውጭ ኃይሎችን ማሳተፍ የሚቻለው፣ ሁሉም የሚመለከታቸው የቀጠናው ሀገራት በመግባባት ላይ በተመሰረተ ማዕቀፍ ሲስማሙ ብቻ መሆኑን ሰነዱ ይደነግጋል። በመጨረሻም እነዚህን ውስብስብ ጉዳዮች በሙያዊ መንገድ የሚከታተሉ እና የሚፈቱ ብቁ ኮሚቴዎች መቋቋም እንዳለባቸው በማስገንዘብ ሰነዱ ይቋጫል።
ከዚህ የጸጥታ ማዕቀፍ ጀርባ ያለው ዋነኛ የፖለቲካ እና የኦፕሬሽን ስሌት፣ የቀጠናው ሀገራት በጉዳያቸው ላይ ሙሉ ባለቤትነት እና ወሳኝነት እንዲኖራቸው ማድረግ መሆኑን ሰነዱ ያብራራል። በተለይም ቀጠናውን ከዓለም አቀፍ ኃያላን ሀገራት የፉክክር እና የፖላራይዜሽን አውድማነት ማዳን፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥ አቅምን በመገንባት በዋና ባለድርሻ አካላት መካከል ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ የኤርትራ ቁልፍ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ፍላጎት መሆኑ ተጠቁሟል። ይህ ማዕቀፍ አሁን ካለው ተለዋዋጭ የቀጠናው የጂኦ-ፖለቲካዊ እውነታ አንጻር፣ በየጊዜው በሚደረጉ ጥልቅ ውይይቶች ሊዳብር የሚችል መሰረታዊ ግብዓት መሆኑንም ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጉት ሰነድ በዋናነት በቀይ ባህር እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያሉትን እውነታዎች ከሁሉም አቅጣጫዎች አድልዎ በሌለው መንገድ መገምገም እና ግቦችን በግልጽ ማስቀመጥ ላይ ያተኩራል። ከዚህም ባሻገር በቀይ ባህር ሰላም እና ደህንነት ላይ የተጋረጡ ስጋቶችን በዝርዝር በመለየት እና በመፈረጅ፣ እነዚህን ስጋቶች ለመቆጣጠር እና ለማስወገድ የሚያስችሉ ተግባራዊ ስትራቴጂዎችን ከገንቢ የትብብር ፖሊሲዎች ጋር በማስተሳሰር መንደፍ እንደሚያስፈልግ ሰነዱ ያብራራል። እነዚህን ስትራቴጂዎች ወደ መሬት ለማውረድም ዝርዝር እቅዶችን፣ የአፈጻጸም ዘዴዎችን፣ መዋቅሮችን እና አስፈላጊ ግብዓቶችን ማሰባሰብ ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል።
የዚህ ስትራቴጂካዊ ሰነድ እጅግ አሳሳቢ እና ትልቁን ፖለቲካዊ አንድምታ የያዘው ክፍል፣ የባህር ዳርቻ ሀገራት የሉዓላዊነት እና ራስን በራስ የመከላከል መብትን የሚመለከተው ነው። ማንኛውም የሚዋቀር የቀጠናው የደህንነት ማዕቀፍ በሉዓላዊነት መከበር እና በዓለም አቀፍ ህግ ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት ሰነዱ ያስገድዳል። በተለይም ሁሉም የባህር ዳርቻ ሀገራት የራሳቸውን የባህር ኃይል እና የመከላከያ አቅም በራሳቸው መገንባት እንዳለባቸው እና ይህንንም የጸጥታ ኃላፊነት ለሌሎች የውጭ ኃይሎች በውክልና መስጠት እንደሌለባቸው ኤርትራ በጥብቅ አሳስባለች።
በተናጠል አቅም ሊፈቱ የማይችሉ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ ሀገራቱ በጋራ ጥረት እና ቅንጅት መፍታት እንደሚገባቸው ሰነዱ ያስቀምጣል። ሆኖም ከቀጠናው የጋራ አቅም በላይ ለሆኑ ልዩ ተልዕኮዎች የውጭ ኃይሎችን ማሳተፍ የሚቻለው፣ ሁሉም የሚመለከታቸው የቀጠናው ሀገራት በመግባባት ላይ በተመሰረተ ማዕቀፍ ሲስማሙ ብቻ መሆኑን ሰነዱ ይደነግጋል። በመጨረሻም እነዚህን ውስብስብ ጉዳዮች በሙያዊ መንገድ የሚከታተሉ እና የሚፈቱ ብቁ ኮሚቴዎች መቋቋም እንዳለባቸው በማስገንዘብ ሰነዱ ይቋጫል።
6 hours ago
በሁለቱ የኢሕአፓ ፖለቲከኞች እና በተቃዋሚዎች ጠበቃው አበራ ንጉሥ ላይ 12 የምርመራ ቀናት ተፈቀደ
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት "በሽብር ወንጀል" የተጠረጠሩት ፖለቲከኞቹ አበበ አካሉ እና ይሳቅ ወልዳይ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ ላይ የ12 የምርመራ ቀናት መፍቀዱን ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።
ዛሬ አርብ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም. ረፋድ ላይ የተሰየመው ችሎት የመርማሪ ፖሊስን ጥያቄ የተቀበለው፣ ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ለተነሳው ጥርጣሬ በማስረጃነት የቀረቡት ቃለ መጠይቆች ላይ "የሽብር መነሻ ሐሳብ በማግኘታቸው" እንደሆነ ጠበቃው ገልጸዋል።
ሁለቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ፖለቲከኞች እና ለተቃዋሚዎች ጥብቅና በመቆም የሚታወቁት አበራ በቁጥጥር ስር የዋሉት ሰኞ ሐምሌ 27 ነበር። በፌደራል ፖሊስ አባላት በተያዙ ሁለተኛው ቀን ረቡዕ ዕለት በከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።
መርማሪ ፖሊስ ሦስቱ ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ "በመንግሥት የፀጥታ ተቋማት እና በመንግሥትት ከፍተኛ አመራሮች ላይ የሽብር ጥቃት" ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ለፍርድ ቤት ገልጿል።
ድርጊቱን ሊፈጽሙ የነበሩት "ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ድብቅ ግንኙነት በማድረግ" እንደሆነ የገለጸው ፖሊስ፤ "ጽምዶ [ተ]ብሎ ከሚጠራው ኃይል ጋር በቀናጀት" ምልመላ እና ስለላ ሲያከናውኑ እንደነበር በመጥቀስም ወንጅሏል።
በዚህ ጉዳይ ላይ "ሥራውን አጠናቅቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የሕግ አካል ለመላክ" እንዲችልም 14 የምርመራ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ፣ በሦስቱ ግለሰቦች ላይ የቀረበውን ውንጀላ ለማስረዳት በቀረቡት በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ የተደረጉ ቃለ መጠይቆች 'የሽብር ይዘት አላቸው ወይስ የላቸውም' የሚለውን ለመወሰን ለዛሬ አርብ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ፍርድ ቤቱ በዛሬው ችሎት በመርማሪ ፖሊስ ቀረቡትን "የሐሰት ፕሮፓጋንዳ" ቪድዮ ሊንኮች መመልከቱን እንደገለጸ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ዳኞች በቀረቡላቸው የቪዲዮ ሊንኮች ላይ "የሽብር ይዘት" የሚያገኙ ከሆነ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ሊፈቀድ እንደሚችል፤ ካልሆነ ደግሞ በዋስትና ሊወጡ ይችሉ እንደነበር ጠበቃው አስረድተዋል።
እንደ ጠበቃው ገለጻ፣ ቪዲዮዎቹን የተመለከቱን ዳኞች ለፖሊስ ጥርጣሪ "መነሻ የሚሆኑ ይዘቶችን አግኝተናል" ብለዋል።
ዳኞች "በሰማነው ድምፅ ላይ ድርጊቱ የሽብር ሊመስል የሚችል የመነሻ ሀሳብ አግኝተናል። በተወሰነ መልኩ የመነሻ ሀሳብ ስላገኘን ለፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል" እንዳሉ ጠበቃው አስረድተዋል።
በዚህም መሠረት መርማሪ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት ውስጥ ተጠርጣሪዎቹ "ፍርድ ቤት ከቀረቡበት ቀን ጀምሮ የሚታሰብ የ12 ቀን የምርመራ ጊዜ" መፍቀዳቸውን ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ በቀጣዩ በሚኖረው ቀጠሮ ላይ "ፖሊስ ምርመራውን ጨርሶ" እንዲቀርብ ትዕዛዝ መሰጠቱንም ጠበቃ ሰለሞን ተናግረዋል።
BBC Amharic
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት "በሽብር ወንጀል" የተጠረጠሩት ፖለቲከኞቹ አበበ አካሉ እና ይሳቅ ወልዳይ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ ላይ የ12 የምርመራ ቀናት መፍቀዱን ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።
ዛሬ አርብ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም. ረፋድ ላይ የተሰየመው ችሎት የመርማሪ ፖሊስን ጥያቄ የተቀበለው፣ ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ለተነሳው ጥርጣሬ በማስረጃነት የቀረቡት ቃለ መጠይቆች ላይ "የሽብር መነሻ ሐሳብ በማግኘታቸው" እንደሆነ ጠበቃው ገልጸዋል።
ሁለቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ፖለቲከኞች እና ለተቃዋሚዎች ጥብቅና በመቆም የሚታወቁት አበራ በቁጥጥር ስር የዋሉት ሰኞ ሐምሌ 27 ነበር። በፌደራል ፖሊስ አባላት በተያዙ ሁለተኛው ቀን ረቡዕ ዕለት በከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።
መርማሪ ፖሊስ ሦስቱ ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ "በመንግሥት የፀጥታ ተቋማት እና በመንግሥትት ከፍተኛ አመራሮች ላይ የሽብር ጥቃት" ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ለፍርድ ቤት ገልጿል።
ድርጊቱን ሊፈጽሙ የነበሩት "ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ድብቅ ግንኙነት በማድረግ" እንደሆነ የገለጸው ፖሊስ፤ "ጽምዶ [ተ]ብሎ ከሚጠራው ኃይል ጋር በቀናጀት" ምልመላ እና ስለላ ሲያከናውኑ እንደነበር በመጥቀስም ወንጅሏል።
በዚህ ጉዳይ ላይ "ሥራውን አጠናቅቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የሕግ አካል ለመላክ" እንዲችልም 14 የምርመራ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ፣ በሦስቱ ግለሰቦች ላይ የቀረበውን ውንጀላ ለማስረዳት በቀረቡት በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ የተደረጉ ቃለ መጠይቆች 'የሽብር ይዘት አላቸው ወይስ የላቸውም' የሚለውን ለመወሰን ለዛሬ አርብ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ፍርድ ቤቱ በዛሬው ችሎት በመርማሪ ፖሊስ ቀረቡትን "የሐሰት ፕሮፓጋንዳ" ቪድዮ ሊንኮች መመልከቱን እንደገለጸ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ዳኞች በቀረቡላቸው የቪዲዮ ሊንኮች ላይ "የሽብር ይዘት" የሚያገኙ ከሆነ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ሊፈቀድ እንደሚችል፤ ካልሆነ ደግሞ በዋስትና ሊወጡ ይችሉ እንደነበር ጠበቃው አስረድተዋል።
እንደ ጠበቃው ገለጻ፣ ቪዲዮዎቹን የተመለከቱን ዳኞች ለፖሊስ ጥርጣሪ "መነሻ የሚሆኑ ይዘቶችን አግኝተናል" ብለዋል።
ዳኞች "በሰማነው ድምፅ ላይ ድርጊቱ የሽብር ሊመስል የሚችል የመነሻ ሀሳብ አግኝተናል። በተወሰነ መልኩ የመነሻ ሀሳብ ስላገኘን ለፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል" እንዳሉ ጠበቃው አስረድተዋል።
በዚህም መሠረት መርማሪ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት ውስጥ ተጠርጣሪዎቹ "ፍርድ ቤት ከቀረቡበት ቀን ጀምሮ የሚታሰብ የ12 ቀን የምርመራ ጊዜ" መፍቀዳቸውን ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ በቀጣዩ በሚኖረው ቀጠሮ ላይ "ፖሊስ ምርመራውን ጨርሶ" እንዲቀርብ ትዕዛዝ መሰጠቱንም ጠበቃ ሰለሞን ተናግረዋል።
BBC Amharic
7 hours ago
የጡት ማጥባት እና የወሊድ ፈቃድ ጉዳይ የስርዓተ ፆታ እኩልነትን እንደሚያስፈልገው ተገለጸ
#ethiopia | የህፃናት ጡት ማጥባት የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ከስርዓተ ፆታ እኩልነት እና ከሴቶች የኢኮኖሚ ተሳትፎ ጋር напрямую የሚያያዝ መሆኑ ተጠቆመ።
ጡት ማጥባት ሴቶች ከሚያከናውኗቸው በርካታ ክፍያ የሌላቸው የቤት ውስጥ ሀላፊነቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ በተለይም ተቀጥረው የሚሰሩ እናቶች የስራ ቦታቸው ምቹ ካልሆነ ስራቸውን የመተው ወይም የልጆቻቸውን ጤና የመሰዋት አስቸጋሪ ምርጫ ውስጥ ይወድቃሉ።
የጤናው ዘርፍ ባለሙያዎች ህፃናት ሙሉ ጤንነት እንዲኖራቸው የመጀመሪያዎቹን ስድስት ወራት አጥብቆ ማጥባት አስፈላጊ መሆኑን ቢያስረዱም፣ በኢትዮጵያ የወጣው የአሰሪና ሰራተኛ እንዲሁም የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ የሚፈቅደው የወሊድ ፈቃድ አራት ወራትን ብቻ ነው። ይህም እናቶች ከወለዱ ከስድስት ወር በፊት ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ በማድረግ ሙሉ በሙሉ ጡት የማጥባት ሂደቱን ፈታኝ ያደርገዋል።
በአለም አቀፉ የስራ ድርጅት የቀረበ ጥናት እንደሚያሳየው እ.ኤ.አ እስከ 2023 ድረስ በአለም ዙሪያ 748 ሚሊዮን ሴቶች በወሊድ እና ስራ መካከል በመሃል በመሃል ምርጫ በማጣታቸው ምክንያት ከስራ ገበታቸው ለመፈናቀል ተገደዋል።
በመሆኑም በኢትዮጵያ የሚገኙ እናቶች ሳይጨነቁ በሙያቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የተቋማት ድጋፍ የሚፈልግ ሲሆን፣ ለዚህም መፍትሄ የሚሆኑ ዋና ዋና ነጥቦች ተቀምጠዋል
የህፃናት ማቆያ ቦታዎችን ማዘጋጀት
ለጡት ማጥባት እና ማለቢያ የሚሆኑ የተለዩ ክፍሎችን ማመቻቸት
እናቶች ከወለዱ በኋላ ወደ ስራ የሚመለሱበትን ጊዜ ማራዘም (ለምሳሌ የፋይናንስ እና የአለም አቀፍ ተቋማት እንደሚያደርጉት የወሊድ ፈቃድን ወደ ስድስት ወር ማሳደግ)
በአጠቃላይ የጡት ማጥባት ጉዳይ የሴቶች የግል ሀላፊነት ብቻ ሳይሆን የቤተሰብ፣ የማህበረሰብ እና የጠቅላላ ተቋማት የተቀናጀ ድጋፍ የሚጠይቅ አንኳር ጉዳይ ነው።
#breastfeeding #maternalhealth #genderquality #ethiopianwomen #workingmothers #parentalleave #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የህፃናት ጡት ማጥባት የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ከስርዓተ ፆታ እኩልነት እና ከሴቶች የኢኮኖሚ ተሳትፎ ጋር напрямую የሚያያዝ መሆኑ ተጠቆመ።
ጡት ማጥባት ሴቶች ከሚያከናውኗቸው በርካታ ክፍያ የሌላቸው የቤት ውስጥ ሀላፊነቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ በተለይም ተቀጥረው የሚሰሩ እናቶች የስራ ቦታቸው ምቹ ካልሆነ ስራቸውን የመተው ወይም የልጆቻቸውን ጤና የመሰዋት አስቸጋሪ ምርጫ ውስጥ ይወድቃሉ።
የጤናው ዘርፍ ባለሙያዎች ህፃናት ሙሉ ጤንነት እንዲኖራቸው የመጀመሪያዎቹን ስድስት ወራት አጥብቆ ማጥባት አስፈላጊ መሆኑን ቢያስረዱም፣ በኢትዮጵያ የወጣው የአሰሪና ሰራተኛ እንዲሁም የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ የሚፈቅደው የወሊድ ፈቃድ አራት ወራትን ብቻ ነው። ይህም እናቶች ከወለዱ ከስድስት ወር በፊት ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ በማድረግ ሙሉ በሙሉ ጡት የማጥባት ሂደቱን ፈታኝ ያደርገዋል።
በአለም አቀፉ የስራ ድርጅት የቀረበ ጥናት እንደሚያሳየው እ.ኤ.አ እስከ 2023 ድረስ በአለም ዙሪያ 748 ሚሊዮን ሴቶች በወሊድ እና ስራ መካከል በመሃል በመሃል ምርጫ በማጣታቸው ምክንያት ከስራ ገበታቸው ለመፈናቀል ተገደዋል።
በመሆኑም በኢትዮጵያ የሚገኙ እናቶች ሳይጨነቁ በሙያቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የተቋማት ድጋፍ የሚፈልግ ሲሆን፣ ለዚህም መፍትሄ የሚሆኑ ዋና ዋና ነጥቦች ተቀምጠዋል
የህፃናት ማቆያ ቦታዎችን ማዘጋጀት
ለጡት ማጥባት እና ማለቢያ የሚሆኑ የተለዩ ክፍሎችን ማመቻቸት
እናቶች ከወለዱ በኋላ ወደ ስራ የሚመለሱበትን ጊዜ ማራዘም (ለምሳሌ የፋይናንስ እና የአለም አቀፍ ተቋማት እንደሚያደርጉት የወሊድ ፈቃድን ወደ ስድስት ወር ማሳደግ)
በአጠቃላይ የጡት ማጥባት ጉዳይ የሴቶች የግል ሀላፊነት ብቻ ሳይሆን የቤተሰብ፣ የማህበረሰብ እና የጠቅላላ ተቋማት የተቀናጀ ድጋፍ የሚጠይቅ አንኳር ጉዳይ ነው።
#breastfeeding #maternalhealth #genderquality #ethiopianwomen #workingmothers #parentalleave #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
8 hours ago
የትራፊክ ጉዳት ካደረሱ አሽከርካሪዎች ውጪ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ማገድ ለጊዘው እንዲቆም ተደረገ
የደንብ 557/2016 ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ አስኪጸድቅ የትራፊክ ጉዳት ካደረሱ አሽከርካሪዎች ውጪ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ማገድ ለጊዘው እንዲቆም ተደርጓል::
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማጅመንት ባለሰልጣን የደንብ ተላላፊዎችን የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ መቀበልም ሆነ ሰሌዳ መፍታት ሳያስፈልግ የዲጂታል የትራፊክ ቁጥጥር እና ቅጣት ማስፈጸሚያ ሲስተም ስርዓት በመዘርጋት የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክን ለመቆጣጣር የወጣውን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 557/2016 የቅጣት አወሳሰንን እየተገበረ ይገኛል፡፡
በመሆኑም ከደንቡ ተግባር ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ በደንብ መተላላፍ የነጥብ ጣሪያ ደርሰው የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫቸው ታግዶ የተሀድሶ ስልጠና እንዲወስድና እና ነጥባቸው ሳይሞላም አስቀድሞ ስልጠና ወስደው ነጥብ የሚቀንስላቸው ደንብ ተላላፊዎች በደንቡ አንቀፅ 96 ንኡስ አንቀጽ 1 እና 2 ላይ በሁለቱም የእውቅና ክህሎት ስልጠና ወስደው የወሰዱበትን ማረጋጋጫ ሲያቀርቡ እግዱ እንደሚነሳ ይደነግጋል፡፤
ይሁን እንጂ ከአፈጻጸም አንጻር ይኸው አገራዊ ደንብ በሌሎች ክልሎች ተግባራዊ ባለመደረጉ እና በአዲስ አበባ ከተማ በሚያሽከረክሩ ደንብ ተላላፊዎች ላይ ብቻ መተግበሩ በደንብ ተላላፊዎች ዘንድ የፍትሀዊነት ጥያቄ ሲያስነሳ ቆይቷል፡፡
ባለሰልጣን መ/ቤቱም ይህንኑ የፍትሀዊነት ጥያቄ ለመንገድ ደህንነት ፈንድ አገልግሎት ባሳወቀው መሰረት አና ተቋሙም ችግሩን በመረዳት በቀን 23/11/2018 በቁጥር 1904/18 በተጻፈ ደብዳቤ ምላሽ ሰጥቶበታል፡፡
በምላሹም ከደንብ ትግበራ ጋር በተያያዘ ተደጋጋሚ ደንብ ተላላፊዎች የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃዳቸው ታግዶ የተሀድሶ ስልጠና የሚያገኙበትን ሂደት የተሳካ ለማድረግ መመሪያ ሲዘጋጅ መቆየቱን አመላክቷል፡፡
እንዲሁም መመሪያውም ያለበትን ሂደቶች አልፎ በአሁኑ ወቅት ለፍትህ ሚኒስቴር መላኩንና በሌሎች ክልሎችም ወጥ የሆነ አሰራር ለመዘርጋት ሲባል ለጊዜው የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፍቃዱን የማገዱ ተግባር አንዲዘገይ በማለት አሳውቋል ፡፡
በመሆኑም የደንብ መተላለፉ የገንዘብ ቅጣቶቹ እንደተጠበቁ ሆነው ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያው ጸድቆ እስኪላክ ድረስ የትራፊክ ጉዳት ካደረሱ አሽከርካሪዎች ውጪ ለጊዜው በነጥብ እና በቆይታ /ሳይከፍል 6 ወር የቆየ/ ከዚህ በፊት የታገዱትም ሆነ በቀጣይ የሚታገድ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ መቆሙን ገልጿል፡፡ ከእግዱ መቆም በስተቀር ደንብ ተላላፊዎች ያሉባቸውን የቅጣት ክፍያ መክፈል እንደሚጠበቅባቸውም ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን
የደንብ 557/2016 ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ አስኪጸድቅ የትራፊክ ጉዳት ካደረሱ አሽከርካሪዎች ውጪ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ማገድ ለጊዘው እንዲቆም ተደርጓል::
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማጅመንት ባለሰልጣን የደንብ ተላላፊዎችን የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ መቀበልም ሆነ ሰሌዳ መፍታት ሳያስፈልግ የዲጂታል የትራፊክ ቁጥጥር እና ቅጣት ማስፈጸሚያ ሲስተም ስርዓት በመዘርጋት የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክን ለመቆጣጣር የወጣውን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 557/2016 የቅጣት አወሳሰንን እየተገበረ ይገኛል፡፡
በመሆኑም ከደንቡ ተግባር ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ በደንብ መተላላፍ የነጥብ ጣሪያ ደርሰው የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫቸው ታግዶ የተሀድሶ ስልጠና እንዲወስድና እና ነጥባቸው ሳይሞላም አስቀድሞ ስልጠና ወስደው ነጥብ የሚቀንስላቸው ደንብ ተላላፊዎች በደንቡ አንቀፅ 96 ንኡስ አንቀጽ 1 እና 2 ላይ በሁለቱም የእውቅና ክህሎት ስልጠና ወስደው የወሰዱበትን ማረጋጋጫ ሲያቀርቡ እግዱ እንደሚነሳ ይደነግጋል፡፤
ይሁን እንጂ ከአፈጻጸም አንጻር ይኸው አገራዊ ደንብ በሌሎች ክልሎች ተግባራዊ ባለመደረጉ እና በአዲስ አበባ ከተማ በሚያሽከረክሩ ደንብ ተላላፊዎች ላይ ብቻ መተግበሩ በደንብ ተላላፊዎች ዘንድ የፍትሀዊነት ጥያቄ ሲያስነሳ ቆይቷል፡፡
ባለሰልጣን መ/ቤቱም ይህንኑ የፍትሀዊነት ጥያቄ ለመንገድ ደህንነት ፈንድ አገልግሎት ባሳወቀው መሰረት አና ተቋሙም ችግሩን በመረዳት በቀን 23/11/2018 በቁጥር 1904/18 በተጻፈ ደብዳቤ ምላሽ ሰጥቶበታል፡፡
በምላሹም ከደንብ ትግበራ ጋር በተያያዘ ተደጋጋሚ ደንብ ተላላፊዎች የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃዳቸው ታግዶ የተሀድሶ ስልጠና የሚያገኙበትን ሂደት የተሳካ ለማድረግ መመሪያ ሲዘጋጅ መቆየቱን አመላክቷል፡፡
እንዲሁም መመሪያውም ያለበትን ሂደቶች አልፎ በአሁኑ ወቅት ለፍትህ ሚኒስቴር መላኩንና በሌሎች ክልሎችም ወጥ የሆነ አሰራር ለመዘርጋት ሲባል ለጊዜው የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፍቃዱን የማገዱ ተግባር አንዲዘገይ በማለት አሳውቋል ፡፡
በመሆኑም የደንብ መተላለፉ የገንዘብ ቅጣቶቹ እንደተጠበቁ ሆነው ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያው ጸድቆ እስኪላክ ድረስ የትራፊክ ጉዳት ካደረሱ አሽከርካሪዎች ውጪ ለጊዜው በነጥብ እና በቆይታ /ሳይከፍል 6 ወር የቆየ/ ከዚህ በፊት የታገዱትም ሆነ በቀጣይ የሚታገድ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ መቆሙን ገልጿል፡፡ ከእግዱ መቆም በስተቀር ደንብ ተላላፊዎች ያሉባቸውን የቅጣት ክፍያ መክፈል እንደሚጠበቅባቸውም ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን
Sponsored by
Surafel
8 hours ago
ነገ ነሐሴ 2 ቀን በተለያዩ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ይቋረጣል
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ባቀደው መሠረት፣ ነገ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦቱ ለጊዜው ይቋረጣል።
⏰ከጠዋቱ 2፡00-9፡30
👉ጀርመን አደባባይ፣ ጎፋ ካምፕ፣ መካነ ኢየሱስ፣ ጎፋ ዳታ ሴንተር፣ ጎፋ ስቶር፣ ኳስ ሜዳ፣ አይሱዙ ጋራዥ፣ ሶፉመር ብሎኬት ማምረቻ፣ ባቱ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢው፣
👉መካኒሳ አረቄ ፋብሪካ፣ አሚጎ ካፌ፣ ቫቲካን ኤምባሲ፣መካኒሳ አቦ ቤ/ክ፣ የመከላከያ ሚ/ር፣ ጥቁር አባይ የቤትና የቢሮ ዕቃዎች ማምረቻ፣ ሰላም አስከባሪ እና አካባቢው፣
👉ካራ ቆሬ፣ መድኃኔዓለም፣ኢትዮሆፕ ት/ቤት፣ ካራቆሬ ውሃ፣ ካራቆሬ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢው፣
👉አየር ጤና፣ መድሐኒዓለም መውጫ፣ ሬዲዮ ፋና፣ ቻይና ካምፕ፣ ዘነብ ወርቅ እና አካባቢው፣
⏰ከጠዋቱ 3፡00-10፡30
👉አራብሳ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ጨርቆስ አራብራ፣ አራብሳ አዲሱ ኮንዶሚንየም በከፊል፣ ገላን በከፊል፣ አራብሳ ኮንዶሚየም እና አካባቢው፣
👉 ኢትዮ ቻይና፣ የአስተማሪዎች መኖሪያ ቤት፣ ለሚኩራ ወረዳ 5፣ አራብሳ ፓሊስ ጣቢያ፣ አቦ ቤተክርስቲያን እና አካባቢው፣ የውሃ ማጣሪያ ታንከር፣ ቴሌ ታወር እና አካባቢው፣
⏰ ከጠዋቱ 3፡00-10፡00
👉ሰበታ ከተማ፣ አለምገና ሚካኤል፣ ኢትዮ ሴራሚክ፣ ሜታ፣ ገዳም ሰፈር፣ ዳለቲ ኢንዱስትሪ፣ ዳለቲ ቄራ፣ ገዳምባ፣ አለምገና ኢንዱስትሪ እና አካባቢው፣
👉 ሱሉልታ ከተማ፣ ጭሮ ደደር ወረዳ፣ መልካ ቦሎ ወረዳ፣ ሜታ ወረዳ፣ ጎሮ ጉቱ ወረዳ እና አካባቢዎች፣
⏰ ከጠዋቱ 3፡00-11፡00
👉ቂሊንጦ ኮንዶሚየም፣ አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዮኒቨርስቲ፣ ቂሊንጦ ላይ ሰፈር፣ ቂሊንጦ ሚካኤል፣ ሌስ ፍራንስ ት/ቤት፣ ቤጂንግ ሆስፒታል፣ አሳማ ጊቢ እና አካባቢው፣
👉 ኮዬ አደባባይ፣ ዋሊያ ቢራ፣ አለም ባንክ፣ ኢንዲያና ት/ቤት፣ ታፍ ማደያ፣ አቃቂ ብሩህ ተስፋ ት/ቤት፣ ኮፊ ሲቲ እና አካባቢው፣
⏰ ከጠዋቱ 2፡00-11፡30
👉ገላን ልደታ ቤ/ክ አካባቢ፣ገላን ኮንዶሚኒየም፣ ገላን ብሎኬት ማምረቻ፣ገላን ከርሰ ምድር እና አከባቢው
👉አዳማ፣ አዳሚቱሉ፣ መቂ ከተማ፣ በህርዳር ቀበሌ 16፣ ህዳሴ ሰፈር እና አከባቢው የሃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ባቀደው መሠረት፣ ነገ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦቱ ለጊዜው ይቋረጣል።
⏰ከጠዋቱ 2፡00-9፡30
👉ጀርመን አደባባይ፣ ጎፋ ካምፕ፣ መካነ ኢየሱስ፣ ጎፋ ዳታ ሴንተር፣ ጎፋ ስቶር፣ ኳስ ሜዳ፣ አይሱዙ ጋራዥ፣ ሶፉመር ብሎኬት ማምረቻ፣ ባቱ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢው፣
👉መካኒሳ አረቄ ፋብሪካ፣ አሚጎ ካፌ፣ ቫቲካን ኤምባሲ፣መካኒሳ አቦ ቤ/ክ፣ የመከላከያ ሚ/ር፣ ጥቁር አባይ የቤትና የቢሮ ዕቃዎች ማምረቻ፣ ሰላም አስከባሪ እና አካባቢው፣
👉ካራ ቆሬ፣ መድኃኔዓለም፣ኢትዮሆፕ ት/ቤት፣ ካራቆሬ ውሃ፣ ካራቆሬ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢው፣
👉አየር ጤና፣ መድሐኒዓለም መውጫ፣ ሬዲዮ ፋና፣ ቻይና ካምፕ፣ ዘነብ ወርቅ እና አካባቢው፣
⏰ከጠዋቱ 3፡00-10፡30
👉አራብሳ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ጨርቆስ አራብራ፣ አራብሳ አዲሱ ኮንዶሚንየም በከፊል፣ ገላን በከፊል፣ አራብሳ ኮንዶሚየም እና አካባቢው፣
👉 ኢትዮ ቻይና፣ የአስተማሪዎች መኖሪያ ቤት፣ ለሚኩራ ወረዳ 5፣ አራብሳ ፓሊስ ጣቢያ፣ አቦ ቤተክርስቲያን እና አካባቢው፣ የውሃ ማጣሪያ ታንከር፣ ቴሌ ታወር እና አካባቢው፣
⏰ ከጠዋቱ 3፡00-10፡00
👉ሰበታ ከተማ፣ አለምገና ሚካኤል፣ ኢትዮ ሴራሚክ፣ ሜታ፣ ገዳም ሰፈር፣ ዳለቲ ኢንዱስትሪ፣ ዳለቲ ቄራ፣ ገዳምባ፣ አለምገና ኢንዱስትሪ እና አካባቢው፣
👉 ሱሉልታ ከተማ፣ ጭሮ ደደር ወረዳ፣ መልካ ቦሎ ወረዳ፣ ሜታ ወረዳ፣ ጎሮ ጉቱ ወረዳ እና አካባቢዎች፣
⏰ ከጠዋቱ 3፡00-11፡00
👉ቂሊንጦ ኮንዶሚየም፣ አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዮኒቨርስቲ፣ ቂሊንጦ ላይ ሰፈር፣ ቂሊንጦ ሚካኤል፣ ሌስ ፍራንስ ት/ቤት፣ ቤጂንግ ሆስፒታል፣ አሳማ ጊቢ እና አካባቢው፣
👉 ኮዬ አደባባይ፣ ዋሊያ ቢራ፣ አለም ባንክ፣ ኢንዲያና ት/ቤት፣ ታፍ ማደያ፣ አቃቂ ብሩህ ተስፋ ት/ቤት፣ ኮፊ ሲቲ እና አካባቢው፣
⏰ ከጠዋቱ 2፡00-11፡30
👉ገላን ልደታ ቤ/ክ አካባቢ፣ገላን ኮንዶሚኒየም፣ ገላን ብሎኬት ማምረቻ፣ገላን ከርሰ ምድር እና አከባቢው
👉አዳማ፣ አዳሚቱሉ፣ መቂ ከተማ፣ በህርዳር ቀበሌ 16፣ ህዳሴ ሰፈር እና አከባቢው የሃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
8 hours ago
የየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሚያሰራውን ቤተሰሊሆም አጠቃላይ ሆስፒታል ህንፃ ግንባታን አስመልክቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡
ከሁሉ አሰቀድመን እግዚአብሔር አምላካችን ለ2018 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሁላችንንም በሰላም በጤና ስላደረሰን እናመሰግነዋለን፡፡የተከበራችሁ አበው መነኮሳት፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ካህናት እና ዲያቆናት፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣ ምዕመናን እና ወጣቶች በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተከታዮች እንዲሁም ይህን መልእክት ለመላው ዓለም ለማስተላለፍ የተገኛችሁ የሚድያ አካላት በሙሉ በእግዚአብሔር ስም የከበረ ሰላምታችንን ጥንታዊ እና ታሪካዊ ከሆነው ከየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እናቀርባለን፡፡
“በኂሩተ ጻድቃን ትረትዕ ሀገር”
“በጻድቃን ልማት ከተማ ደስ ይላታል”
ምሳ 11፥10
እግዚአብሔር በንጉሱ ሰሎሞን ላይ አድሮ የተናገረውን መነሻ በማድረግ ልማት ለቤተከርስቲያን ፣ልማት ለሀገር፣ልማት ለማኅበረ ስብእ አስፈላጊ መሆኑን በማሰብ በአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለሚገነባው ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል የህንፃ ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ ግብር የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡ የእግዚአበሔር ሰላም ከሁላችንም ጋር ይሁን፡፡ አሜን።
1. ታሪካዊ ዳራ እና የልማት መነሻ
ከአክሱም ዘመነ መንግሥት (በአባ ሰላማ ዘመን) የጀመረውና ከ1600 ዓመታት በላይ የዘለቀው የየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፤ የኢትዮጵያን ጥንታዊነትና የአዲስ አበባን ከተማ አመሰራረት የሚተርክ ህያው ቅርስ ነው።ይህ ታሪካዊ ደብር በአብርሃ ወአጽብሃ፣ በዳግማዊ አጼ ምኒልክና በንግሥት ጣይቱ፣ እንዲሁም በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት በርካታ የታሪክና የፈተና ምዕራፎችን አልፎ ዛሬ ላይ ደርሷል።
ደብሩ ከሃይማኖታዊ አገልግሎቱ ባሻገር፣ የአዲስ አበባ የመጀመሪያው የቀብር ቦታ በመሆን የሊቃውንቱና የካህናቱ እንዲሁም የታላቁ ሐኪም ወርቅነህ እሸቴን፣ የኢትዮጵያ ታላላቅ ጄነራሎችና ፊት አውራሪዎችን ዓጽም በክበር ማረፊያ ሆኗል፡፡ የጸሎትና ማህበራዊ አገልግሎት እንዲሁም ለአካባቢው አብያተ ክርስቲያናት መመስረት ባደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይታወቃል። ዛሬ ይህ ታሪካዊ ደብር ጥንታዊ ታሪኩንና መንፈሳዊ ታላቅነቱን በዘመናዊ ማህበራዊ ልማት ለመድገም፣አካላዊ ፈውስን በሳይንሳዊ ሕክምና የመንፈሳዊ ፈውስን በፀሎትና በጠበል የሚያዋህድ ታላቅ የልማት ፕሮጀክት ይፋአድርጓል።
2. የሆስፒታሉ ይዘት፣ ራዕይና ሰብዓዊ ተልዕኮ
ቤተክርስቲያኑ ባለ 15 ወለል ማለትም (2 Basement+G+ 12ወለል) የሆነውን «ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል» ህንፃ ግንባታ የጀመረ ሲሆን፣ የመጀመሪያውን ምዕራፍ የመሰረት ቁፋሮና የአፈር ናዳ መከላከያ (ሾሪንግ) ሥራ በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
ይህ በ1000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈውና ባለ 250 የህሙማን ሕክምና መስጫ አልጋ አቅም የሚኖረው ዘመናዊ ሆስፒታል፤ የተመላላሽ ክሊኒኮችን፣ የፅኑ ሕክምና (ICU)፣ የቀዶ ጥገና ክፍሎችን እንዲሁም ለእናቶችና ሕጻናት ጤና፣ ለልብ ሕክምናና ለተላላፊ በሽታዎች መከላከያ የሚሆኑ ልዩ ልዩ ማዕከላትን ያካትታል። ተቋሙ የጤና አጠባበቅን እንደ ንግድ ሳይሆን እንደ ሰብዓዊና መንፈሳዊ አገልግሎት በመመልከት፣ለሁሉም የማህበረሰቡ አባላት በሙሉ ጥራት ያለው፣ ተደራሽና አቅምን ያገናዘበ የሕክምና አገልግሎት ያቀርባል።
3. የግንባታ ወጪ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ጥሪ
በህንፃ ባለሙያዎች ጥናት መሠረት ለህንፃ ግንባታው አጠቃላይ ወጪ ብር 405,040,000 (አራት መቶ አምስትሚሊዮን አርባ ሺህ ብር) እንደሚሆን ተገምቷል።ይህ ወጪ በየጊዜው በሚታየው የዋጋ ንረት ምክንያት ሊጨምር እንደሚችል ይታሰባል፡፡
ይህንን ከፍተኛ ወጪ ለመሸፈንና ቀጣዩን ወሳኝ የግንባታምዕራፍ ለመጀመር ቤተ ክርስቲያኑ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ምዕመናንን፣ የንግዱን ማህበረሰብና የልማት አጋሮችን ያሳተፈ የሀብት ማሰባሰቢያ ስልት ቀይሷል።
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ እና የልማት ኮሚቴው ምዕመናን በሰጦታቸው ከእግዚአብሔር የሚያገኙትን በረከት በማሰብ፦ «ይህ ታላቅ የማህበራዊና የጤና ልማት ፕሮጀክት ፍጻሜ እንዲያገኝ የዓላማው ደጋፊዎች ሁሉ የእርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉና አሻራቸውን እንዲያኖሩ በሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል ስም እንማጸናለን» ሲል ጥሪውን ያስተላልፋል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ዝርዝር፦
• ቀን፦ ነሐሴ 8፣ 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም
• ሰዓት፦ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ
የገቢ ማሰባሰቢያ የባንክ አማራጮች፦
• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብቁጥር፦
1000000764087 እንዲሁም
አጭር ቁጥር 1277
• አባይ ባንክ ሂሳብ ቁጥር፦ 1227
• አዋሽ ባንክ ሂሳብ ቁጥር
013521784586601
• ስዊፍት ኮድ AWINETAA
• ወገን ፈንድ 👉 ሊንክ ኮመንት ላይ አለ
ለተጨማሪ መረጃ፦
• ስልክ ቁጥር፦
0945881188 እና 0945771188
• Email፦ Seyoumwgebrielgmail .com
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።
ከሁሉ አሰቀድመን እግዚአብሔር አምላካችን ለ2018 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሁላችንንም በሰላም በጤና ስላደረሰን እናመሰግነዋለን፡፡የተከበራችሁ አበው መነኮሳት፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ካህናት እና ዲያቆናት፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣ ምዕመናን እና ወጣቶች በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተከታዮች እንዲሁም ይህን መልእክት ለመላው ዓለም ለማስተላለፍ የተገኛችሁ የሚድያ አካላት በሙሉ በእግዚአብሔር ስም የከበረ ሰላምታችንን ጥንታዊ እና ታሪካዊ ከሆነው ከየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እናቀርባለን፡፡
“በኂሩተ ጻድቃን ትረትዕ ሀገር”
“በጻድቃን ልማት ከተማ ደስ ይላታል”
ምሳ 11፥10
እግዚአብሔር በንጉሱ ሰሎሞን ላይ አድሮ የተናገረውን መነሻ በማድረግ ልማት ለቤተከርስቲያን ፣ልማት ለሀገር፣ልማት ለማኅበረ ስብእ አስፈላጊ መሆኑን በማሰብ በአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለሚገነባው ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል የህንፃ ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ ግብር የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡ የእግዚአበሔር ሰላም ከሁላችንም ጋር ይሁን፡፡ አሜን።
1. ታሪካዊ ዳራ እና የልማት መነሻ
ከአክሱም ዘመነ መንግሥት (በአባ ሰላማ ዘመን) የጀመረውና ከ1600 ዓመታት በላይ የዘለቀው የየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፤ የኢትዮጵያን ጥንታዊነትና የአዲስ አበባን ከተማ አመሰራረት የሚተርክ ህያው ቅርስ ነው።ይህ ታሪካዊ ደብር በአብርሃ ወአጽብሃ፣ በዳግማዊ አጼ ምኒልክና በንግሥት ጣይቱ፣ እንዲሁም በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት በርካታ የታሪክና የፈተና ምዕራፎችን አልፎ ዛሬ ላይ ደርሷል።
ደብሩ ከሃይማኖታዊ አገልግሎቱ ባሻገር፣ የአዲስ አበባ የመጀመሪያው የቀብር ቦታ በመሆን የሊቃውንቱና የካህናቱ እንዲሁም የታላቁ ሐኪም ወርቅነህ እሸቴን፣ የኢትዮጵያ ታላላቅ ጄነራሎችና ፊት አውራሪዎችን ዓጽም በክበር ማረፊያ ሆኗል፡፡ የጸሎትና ማህበራዊ አገልግሎት እንዲሁም ለአካባቢው አብያተ ክርስቲያናት መመስረት ባደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይታወቃል። ዛሬ ይህ ታሪካዊ ደብር ጥንታዊ ታሪኩንና መንፈሳዊ ታላቅነቱን በዘመናዊ ማህበራዊ ልማት ለመድገም፣አካላዊ ፈውስን በሳይንሳዊ ሕክምና የመንፈሳዊ ፈውስን በፀሎትና በጠበል የሚያዋህድ ታላቅ የልማት ፕሮጀክት ይፋአድርጓል።
2. የሆስፒታሉ ይዘት፣ ራዕይና ሰብዓዊ ተልዕኮ
ቤተክርስቲያኑ ባለ 15 ወለል ማለትም (2 Basement+G+ 12ወለል) የሆነውን «ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል» ህንፃ ግንባታ የጀመረ ሲሆን፣ የመጀመሪያውን ምዕራፍ የመሰረት ቁፋሮና የአፈር ናዳ መከላከያ (ሾሪንግ) ሥራ በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
ይህ በ1000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈውና ባለ 250 የህሙማን ሕክምና መስጫ አልጋ አቅም የሚኖረው ዘመናዊ ሆስፒታል፤ የተመላላሽ ክሊኒኮችን፣ የፅኑ ሕክምና (ICU)፣ የቀዶ ጥገና ክፍሎችን እንዲሁም ለእናቶችና ሕጻናት ጤና፣ ለልብ ሕክምናና ለተላላፊ በሽታዎች መከላከያ የሚሆኑ ልዩ ልዩ ማዕከላትን ያካትታል። ተቋሙ የጤና አጠባበቅን እንደ ንግድ ሳይሆን እንደ ሰብዓዊና መንፈሳዊ አገልግሎት በመመልከት፣ለሁሉም የማህበረሰቡ አባላት በሙሉ ጥራት ያለው፣ ተደራሽና አቅምን ያገናዘበ የሕክምና አገልግሎት ያቀርባል።
3. የግንባታ ወጪ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ጥሪ
በህንፃ ባለሙያዎች ጥናት መሠረት ለህንፃ ግንባታው አጠቃላይ ወጪ ብር 405,040,000 (አራት መቶ አምስትሚሊዮን አርባ ሺህ ብር) እንደሚሆን ተገምቷል።ይህ ወጪ በየጊዜው በሚታየው የዋጋ ንረት ምክንያት ሊጨምር እንደሚችል ይታሰባል፡፡
ይህንን ከፍተኛ ወጪ ለመሸፈንና ቀጣዩን ወሳኝ የግንባታምዕራፍ ለመጀመር ቤተ ክርስቲያኑ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ምዕመናንን፣ የንግዱን ማህበረሰብና የልማት አጋሮችን ያሳተፈ የሀብት ማሰባሰቢያ ስልት ቀይሷል።
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ እና የልማት ኮሚቴው ምዕመናን በሰጦታቸው ከእግዚአብሔር የሚያገኙትን በረከት በማሰብ፦ «ይህ ታላቅ የማህበራዊና የጤና ልማት ፕሮጀክት ፍጻሜ እንዲያገኝ የዓላማው ደጋፊዎች ሁሉ የእርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉና አሻራቸውን እንዲያኖሩ በሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል ስም እንማጸናለን» ሲል ጥሪውን ያስተላልፋል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ዝርዝር፦
• ቀን፦ ነሐሴ 8፣ 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም
• ሰዓት፦ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ
የገቢ ማሰባሰቢያ የባንክ አማራጮች፦
• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብቁጥር፦
1000000764087 እንዲሁም
አጭር ቁጥር 1277
• አባይ ባንክ ሂሳብ ቁጥር፦ 1227
• አዋሽ ባንክ ሂሳብ ቁጥር
013521784586601
• ስዊፍት ኮድ AWINETAA
• ወገን ፈንድ 👉 ሊንክ ኮመንት ላይ አለ
ለተጨማሪ መረጃ፦
• ስልክ ቁጥር፦
0945881188 እና 0945771188
• Email፦ Seyoumwgebrielgmail .com
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።
9 hours ago
ተወዳጇ አርቲስት ቬሮኒካ አዳነህ በነፃ ለSUSU HUMAN HAIR አምባሳደር ሆነች!!!
በህይወቴ ብዙ ፈተናዎችን እና ተስፋ የሚያስቆርጡ ውጣ ውረዶችን አሳልፌያለሁ። ነገር ግን ከልጅነቴ ጀምሮ ያሰብኩትን ነገር ከማሳካት የሚያስቆመኝ ምንም አይነት ችግር ሆነ ፈተና አልነበረም።
በስደት ሀገር እንደማንኛውም ስደተኛ ሰው ቤት ተቀጥሬ እሰራ ነበር። ከዛ በመውጣት የራሴን ስራ ለመስራት ሞከርኩ። በትንሽዬ የሴቶች የውበት ሳሎን በመጀመር፣ በሊባኖስ ዋና ከተማ ታዋቂ የሂውማን ሄር (Human Hair) አስመጪ እስከመሆን ደረስኩ። ህይወቴ እየተለወጠ፣ እያደግኩ እና እየተሳካልኝ ሲመጣ በማህበራዊ ሚዲያ (በቲክቶክ) ብቅ አልኩ በሀቢባ ቤት LIVE በመግባት እውቅናንም ማግኘት ጀመርኩ ሀቢባ ታዋቂ ለመሆኔ ምክንያት ሆነችኝ። ያኔም ነው ቬሮኒካ አዳነ ያወቀችኝ እንደምወዳት እና አድናቂዋ እንደሆንኩኝ በሷ ሙዚቃ በምሰራቸው ቪድዎች አየች ኮሜንት ለመጀርያ ጊዜ ስትፅፍልኝ የነበረውን ስሜት አልረሳውም። በቬሮኒካም ምክንያት በደንብ ታዋቂ መሆን ጀመርኩ፤
በዚያም ብዙ ወዳጆችን በማፍራት ስሜ በሀገሬ በኢትዮጵያም መታወቅ ጀመረ፤ ተደራሽነቴ እየሰፋ ሄዶ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ሀገራት ያሉ ደንበኞችን ማፈራት ቻልኩ። የመጀመሪያ ልጄንም በዚህ ስራ ላይ እያለሁ ወለድኩ፤ ይህም ይበልጥ ጠንካራ አደረገኝ።
ነገር ግን፣ ምንም በማላውቀው ምክንያት
ሁለት ወር እስራት ገጠመኝ ከዛ በኋላ ከእስር ቤት ወጥቼ ወደ ሀገሬ ገባው በህይወቴ ትልቁን ፈተና የተፈተንኩት ያኔ ነበር ለአስር ዓመታት የለፋሁበትን ህይወት፣ ስራዬን እና ከልጄ ጋር የነበረኝን አንድነት እንደ ቀልድ አጣሁት።
እውነት ለመናገር ያኔ ተስፋዬ ተሟጦ አልቆ ነበር። ነገር ግን ፈጣሪ ሁሌም አለ፤ አይተወኝም። ጠንካራ ሴት ነኝና በህይወቴ እንደ ሀቢባ እና ቬሮኒካ አዳነ ያሉ ጠንካራ ሴቶችን ላከልኝ። ልወድቅ ስል ደገፉኝ፤ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ያሉ ውድ የኢትዮጵያ ህዝቦችና የሚወዱኝ ሰዎች ትልቅ ድጋፍ ሆኑኝ።
ከዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ በኋላ፣ የምወዳት እና የማደንቃት አርቲስት ቬሮኒካ አዳነ በህይወቴ የማልረሳውን ትልቅ ውለታ ውላልኛለች፤ *«የሁለት ዓመት በነፃ ያለ ምንም ክፍያ የ’ሱሱ ሂውማን ሄር’ (Susu Human Hair) አምባሳደር ነኝ»* ብላ ሰርፕራይዝ አደረገችኝ። ይህ የህይወቴ ትልቁ ሰርፕራይዝ ነበር! ልጄም ወደ ሀገሩ ተመለሰ። በሀቢባ፣ በወዳጆቿ እና በአድናቂዎቼ አማካኝነትም የገንዘብ ድጋፍ ተደረገልኝ።
አሁን የህይወቴ ትልቁ ምዕራፍ ላይ እገኛለሁ። የሂውማን ሄር መሸጫዬን እና የውበት ሳሎኔን እዚሁ ሀገሬ ላይ ልከፍት ነው። ቬሮኒካ አዳነ የ2 ዓመት አምባሳደሬ ሆና በነፃ ትሰራለች፤ ከቻይና ሂውማን ሄር ኩባንያ ጋርም አብሬ እየሰራሁ እገኛለሁ።
አሁን ማንም ሊያስቆመኝ አይችልም! ፈጣሪ ሳይደግስ አይጣላም ከፍ እንድል ምክንያት ሆነውኛል
ከፈተናዎች ማዶ የተገነባ ስኬት:- የሱመያ ዋሪስ የህይወት ጉዞ
እኔ SUSU HUMAN HAIR ነኝ።
በህይወቴ ብዙ ፈተናዎችን እና ተስፋ የሚያስቆርጡ ውጣ ውረዶችን አሳልፌያለሁ። ነገር ግን ከልጅነቴ ጀምሮ ያሰብኩትን ነገር ከማሳካት የሚያስቆመኝ ምንም አይነት ችግር ሆነ ፈተና አልነበረም።
በስደት ሀገር እንደማንኛውም ስደተኛ ሰው ቤት ተቀጥሬ እሰራ ነበር። ከዛ በመውጣት የራሴን ስራ ለመስራት ሞከርኩ። በትንሽዬ የሴቶች የውበት ሳሎን በመጀመር፣ በሊባኖስ ዋና ከተማ ታዋቂ የሂውማን ሄር (Human Hair) አስመጪ እስከመሆን ደረስኩ። ህይወቴ እየተለወጠ፣ እያደግኩ እና እየተሳካልኝ ሲመጣ በማህበራዊ ሚዲያ (በቲክቶክ) ብቅ አልኩ በሀቢባ ቤት LIVE በመግባት እውቅናንም ማግኘት ጀመርኩ ሀቢባ ታዋቂ ለመሆኔ ምክንያት ሆነችኝ። ያኔም ነው ቬሮኒካ አዳነ ያወቀችኝ እንደምወዳት እና አድናቂዋ እንደሆንኩኝ በሷ ሙዚቃ በምሰራቸው ቪድዎች አየች ኮሜንት ለመጀርያ ጊዜ ስትፅፍልኝ የነበረውን ስሜት አልረሳውም። በቬሮኒካም ምክንያት በደንብ ታዋቂ መሆን ጀመርኩ፤
በዚያም ብዙ ወዳጆችን በማፍራት ስሜ በሀገሬ በኢትዮጵያም መታወቅ ጀመረ፤ ተደራሽነቴ እየሰፋ ሄዶ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ሀገራት ያሉ ደንበኞችን ማፈራት ቻልኩ። የመጀመሪያ ልጄንም በዚህ ስራ ላይ እያለሁ ወለድኩ፤ ይህም ይበልጥ ጠንካራ አደረገኝ።
ነገር ግን፣ ምንም በማላውቀው ምክንያት
ሁለት ወር እስራት ገጠመኝ ከዛ በኋላ ከእስር ቤት ወጥቼ ወደ ሀገሬ ገባው በህይወቴ ትልቁን ፈተና የተፈተንኩት ያኔ ነበር ለአስር ዓመታት የለፋሁበትን ህይወት፣ ስራዬን እና ከልጄ ጋር የነበረኝን አንድነት እንደ ቀልድ አጣሁት።
እውነት ለመናገር ያኔ ተስፋዬ ተሟጦ አልቆ ነበር። ነገር ግን ፈጣሪ ሁሌም አለ፤ አይተወኝም። ጠንካራ ሴት ነኝና በህይወቴ እንደ ሀቢባ እና ቬሮኒካ አዳነ ያሉ ጠንካራ ሴቶችን ላከልኝ። ልወድቅ ስል ደገፉኝ፤ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ያሉ ውድ የኢትዮጵያ ህዝቦችና የሚወዱኝ ሰዎች ትልቅ ድጋፍ ሆኑኝ።
ከዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ በኋላ፣ የምወዳት እና የማደንቃት አርቲስት ቬሮኒካ አዳነ በህይወቴ የማልረሳውን ትልቅ ውለታ ውላልኛለች፤ *«የሁለት ዓመት በነፃ ያለ ምንም ክፍያ የ’ሱሱ ሂውማን ሄር’ (Susu Human Hair) አምባሳደር ነኝ»* ብላ ሰርፕራይዝ አደረገችኝ። ይህ የህይወቴ ትልቁ ሰርፕራይዝ ነበር! ልጄም ወደ ሀገሩ ተመለሰ። በሀቢባ፣ በወዳጆቿ እና በአድናቂዎቼ አማካኝነትም የገንዘብ ድጋፍ ተደረገልኝ።
አሁን የህይወቴ ትልቁ ምዕራፍ ላይ እገኛለሁ። የሂውማን ሄር መሸጫዬን እና የውበት ሳሎኔን እዚሁ ሀገሬ ላይ ልከፍት ነው። ቬሮኒካ አዳነ የ2 ዓመት አምባሳደሬ ሆና በነፃ ትሰራለች፤ ከቻይና ሂውማን ሄር ኩባንያ ጋርም አብሬ እየሰራሁ እገኛለሁ።
አሁን ማንም ሊያስቆመኝ አይችልም! ፈጣሪ ሳይደግስ አይጣላም ከፍ እንድል ምክንያት ሆነውኛል
ከፈተናዎች ማዶ የተገነባ ስኬት:- የሱመያ ዋሪስ የህይወት ጉዞ
እኔ SUSU HUMAN HAIR ነኝ።
10 hours ago
በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ወሰነ።
የተላለፈው መግለጫ ከዩቲዩብ እንዲወርድ እና ይቅርታ እንዲጠየቅ ፍርድ ቤቱ አዟል።
ዐቃቤ ሕግ አርቲስቶቹ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ መግለጫ በመስጠታቸው የዋስትና መብታቸው ተነስቶ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ያቀረበውን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጎታል።
ዛሬ ነሀሴ 01 2018 ዓ/ም ጠዋት በነበረው ችሎት ተጠርጣሪ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ለዐቃቤ ሕግ አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ ለምን መግለጫ እንደሰጡም ለችሎቱ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።
አርቲስቶቹ በማብራሪያቸው ድርጊቱን የፈጸሙት በማኅበራዊ ሚዲያ ከሚደርስባቸው ስም ማጥፋትና መልካም ስም ከማጉደፍ ራሳቸውን ለመከላከል አስበው እንደሆነ አስረድተዋል።
ጉዳዩን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለከሰዓት 9:00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው ፍርድ ቤቱ፤ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠትና ማብራሪያ ማቅረብ ጥፋት መሆኑን አመልክቷል።
በማኅበራዊ ሚዲያ ለሚጠፋ ስም መልስ ለመስጠት እንኳን ቢሆን ድርጊቱን ፈጽሟል የሚሉትን አካል በሕግ መጠየቅ ሲገባ መግለጫ መስጠቱ ተገቢ እንዳልሆነ ጠቁሟል።
ሆኖም «በጥቃቅን ጥፋቶች የዋስትና መብትን ማገድ ተገቢ ሆኖ አላገኘነውም» ሲል ዐቃቤ ሕግ የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።
በተጨማሪም አርቲስቶቹና ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣ ወይም በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ አልተቀበለውም።
በዚህም መሠረት መግለጫ የሰጡት አርቲስቶች ሌላ ጊዜ ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጽሙ በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ውሳኔ ተሰጥቷል።
በሌላ በኩል «እግረኛው» በተሰኘው የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ እንዲተላለፍ ያደረገው አቶ ተክለሃይማኖት አዳነ ቪዲዮውን ከዩቲዩብ (YouTube) ላይ እንዲያወርድና ይቅርታ እንዲጠይቅ ፍርድ ቤቱ አዟል።
የመደበኛው የሕግ ሂደት ቀጠሮ ለጥቅምት 02 ቀን 2019 ዓ.ም የተቀጠረ መሆኑ ታውቋል።
ገዛ ጌታሁን
የተላለፈው መግለጫ ከዩቲዩብ እንዲወርድ እና ይቅርታ እንዲጠየቅ ፍርድ ቤቱ አዟል።
ዐቃቤ ሕግ አርቲስቶቹ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ መግለጫ በመስጠታቸው የዋስትና መብታቸው ተነስቶ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ያቀረበውን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጎታል።
ዛሬ ነሀሴ 01 2018 ዓ/ም ጠዋት በነበረው ችሎት ተጠርጣሪ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ለዐቃቤ ሕግ አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ ለምን መግለጫ እንደሰጡም ለችሎቱ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።
አርቲስቶቹ በማብራሪያቸው ድርጊቱን የፈጸሙት በማኅበራዊ ሚዲያ ከሚደርስባቸው ስም ማጥፋትና መልካም ስም ከማጉደፍ ራሳቸውን ለመከላከል አስበው እንደሆነ አስረድተዋል።
ጉዳዩን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለከሰዓት 9:00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው ፍርድ ቤቱ፤ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠትና ማብራሪያ ማቅረብ ጥፋት መሆኑን አመልክቷል።
በማኅበራዊ ሚዲያ ለሚጠፋ ስም መልስ ለመስጠት እንኳን ቢሆን ድርጊቱን ፈጽሟል የሚሉትን አካል በሕግ መጠየቅ ሲገባ መግለጫ መስጠቱ ተገቢ እንዳልሆነ ጠቁሟል።
ሆኖም «በጥቃቅን ጥፋቶች የዋስትና መብትን ማገድ ተገቢ ሆኖ አላገኘነውም» ሲል ዐቃቤ ሕግ የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።
በተጨማሪም አርቲስቶቹና ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣ ወይም በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ አልተቀበለውም።
በዚህም መሠረት መግለጫ የሰጡት አርቲስቶች ሌላ ጊዜ ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጽሙ በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ውሳኔ ተሰጥቷል።
በሌላ በኩል «እግረኛው» በተሰኘው የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ እንዲተላለፍ ያደረገው አቶ ተክለሃይማኖት አዳነ ቪዲዮውን ከዩቲዩብ (YouTube) ላይ እንዲያወርድና ይቅርታ እንዲጠይቅ ፍርድ ቤቱ አዟል።
የመደበኛው የሕግ ሂደት ቀጠሮ ለጥቅምት 02 ቀን 2019 ዓ.ም የተቀጠረ መሆኑ ታውቋል።
ገዛ ጌታሁን
11 hours ago
በአርባምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት የመብራት ምሰሶ ላይ ጉዳት ያደረሰው አሽከርካሪ 1 ሚሊዮን ብር ተቀጣ
በአርባምንጭ ከተማ በኮሪደር ልማት ሥራ የተተከለ ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራት ምሰሶ (ፖል) በመግጨት ውድመት ያደረሰ አሽከርካሪ በቁጥጥር ሥር ውሎ 1 ሚሊዮን ብር እንዲቀጣና የወደመውን ሀብት በራሱ ወጪ ወደ ነበረበት እንዲመልስ ተወሰነ።
በከተማዋ ሲቀላ ክፍለ ከተማ አሽከርካሪው ተሽከርካሪ ለማንቀሳቀስ ባልተፈቀደ ቦታ ላይ በማሽከርከር በከፍተኛ ወጪ የተተከለውን ስማርት የመብራት ምሰሶ በመግጨት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ የአርባምንጭ ከተማ ደንብ አስከባሪ ጽሕፈት ቤት ከከተማው ትራፊክ ፖሊስ ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል ጥፋተኛውን አሽከርካሪ በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል።
የከተማው ደንብ አስከባሪ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰራዊት ገዛኸኝ እንዳስታወቁት፣ በቸልተኝነት በሚፈጸሙ ጥፋቶች የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት እንዳይባክን እና አስተማሪ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ሲባል የተሰበረውንና የወደመውን ስማርት የመብራት ምሰሶ በራሱ ወጪ ወደ ነበረበት እንዲመልስ።
ጥፋተኛውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ከነዋሪዎች የተገኘው የጥቆማ ትብብር ከፍተኛ ሚና እንደነበረው የገለጹት አቶ ሰራዊት፣ ለኅብረተሰቡ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ኃላፊው አክለውም ለከተማዋ እድገትና ለነዋሪዎች ምቾት በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የኮሪደር ልማት ሥራዎችንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በሚያበላሹ ወይም ሕግ በሚተላለፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስበዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በአርባምንጭ ከተማ በኮሪደር ልማት ሥራ የተተከለ ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራት ምሰሶ (ፖል) በመግጨት ውድመት ያደረሰ አሽከርካሪ በቁጥጥር ሥር ውሎ 1 ሚሊዮን ብር እንዲቀጣና የወደመውን ሀብት በራሱ ወጪ ወደ ነበረበት እንዲመልስ ተወሰነ።
በከተማዋ ሲቀላ ክፍለ ከተማ አሽከርካሪው ተሽከርካሪ ለማንቀሳቀስ ባልተፈቀደ ቦታ ላይ በማሽከርከር በከፍተኛ ወጪ የተተከለውን ስማርት የመብራት ምሰሶ በመግጨት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ የአርባምንጭ ከተማ ደንብ አስከባሪ ጽሕፈት ቤት ከከተማው ትራፊክ ፖሊስ ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል ጥፋተኛውን አሽከርካሪ በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል።
የከተማው ደንብ አስከባሪ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰራዊት ገዛኸኝ እንዳስታወቁት፣ በቸልተኝነት በሚፈጸሙ ጥፋቶች የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት እንዳይባክን እና አስተማሪ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ሲባል የተሰበረውንና የወደመውን ስማርት የመብራት ምሰሶ በራሱ ወጪ ወደ ነበረበት እንዲመልስ።
ጥፋተኛውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ከነዋሪዎች የተገኘው የጥቆማ ትብብር ከፍተኛ ሚና እንደነበረው የገለጹት አቶ ሰራዊት፣ ለኅብረተሰቡ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ኃላፊው አክለውም ለከተማዋ እድገትና ለነዋሪዎች ምቾት በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የኮሪደር ልማት ሥራዎችንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በሚያበላሹ ወይም ሕግ በሚተላለፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስበዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
12 hours ago
በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች ላይ ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው አቤቱታ ላይ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ከሰዓት ቀጠሮ ተሰጠ።
በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ መጠነ ሰፊ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው ታዋቂ አርቲስቶች፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 2 ቀን 2019 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።
ነገር ግን ተከሳሾቹ "እግረኛው" በተሰኘ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ ቀርበው መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ፣ ዐቃቤ ሕግ ባለ 5 ገጽ የክስ አቤቱታ አቅርቦ ስለነበር ጉዳዩ ከሰዓት በኋላ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተደርጎ ፣ ለዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 4፡00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ጠዋት በነበረው ችሎት ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነን ጨምሮ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ዐቃቤ ሕግ ላቀረበው አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም በሕግ በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ለምን መግለጫ እንደሰጡ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።
ተከሳሾቹ በሰጡት ምላሽ፦ "እኛ የኪነ ጥበብ ሰዎች ነን፤ ነገር ግን በመልካም ስማችን ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ስለተከፈተብንና ስማችን በመጥፋቱ ሥራችን ስለተበላሸ ነው ምላሽ ለመስጠት የተገደድነው" ብለዋል።
"ለምሳሌ በዚህ ምክንያት አምስት የሥራ ውሎች ተቋርጠውብኛል፤ እኔና ጓደኛዬ የምንሰራው የቴሌቪዥን ፕሮግራምም እንዲቋረጥ ተደርጓል" ሲል አርቲስት ይገረም ደጀኔ ለችሎቱ አብራርቷል።
በነበረው መግለጫ የፍርድ ቤቱን የሕግ ሂደት እንዳያስተጓጉሉ ጥንቃቄ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል።
አርቲስቶቹን በማኅበራዊ ሚዲያ አናግሮ መግለጫቸውን ያስተላለፈው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በበኩሉ፦ "እኔ ይህን ፕሮግራም ሳቀርብ የመጀመሪያዬ አይደለም፤ አርቲስቶቹ በሕግ ከመያዛቸው አስቀድሞ አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬን በፊንቴክ ዙሪያ ተገልጋዮች ስለሚያነሱት ቅሬታ ጠይቄ ሰርቻለሁ፤ ከዚያ በኋላም አርቲስቶቹን ጥፋተኛ አድርገው በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የሚዘግቡትን መረጃዎች መነሻ በማድረግ የጠየቅኋቸው ሰዎች አሉ። አሁን እነሱን ያናገርኩት ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የፍትሕ ሂደቱን እንደማይጎዳ የሕግ ባለሙያ አማክሬ ነው" ሲል ለችሎቱ አስረድቷል።
ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የተሰጠው መግለጫ ከፍርድ ቤት ውጭ ውሳኔ መስጠት እንደሆነና በሕግ ሂደት ላይ ባለ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠት በሕግ ወንጀል መሆኑ መደነገጉን አብራርቷል።
ቀጥሎም "ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ የአርቲስቶችን ጠበቃ ስለ መዝገቡ ጠይቆ ጠበቃው 'በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ አልሰጥም' ሲሉ 'ፈሪ ነህ ማለት ነው?' በማለት ተናግሯል፤ ይህም የተሳሳተ አካሄድ ነው።
ማንም ቢሆን መግለጫ መስጠት በሕግ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አያውቅም ተብሎ አይገመትም፤ “የመጣው ይምጣ” በሚል ስሜት የተሰጠ መግለጫ እንደሆነ ስለምናምን፣ ፍርድ ቤቱ በአቤቱታው ላይ የተጠቀሱትን መርምሮ ተገቢውን ውሳኔ እንዲሰጥልን" ሲል ጠይቋል።
ዐቃቤ ሕግ ከትላንት በፊቱ ችሎት በጽሑፍ ባቀረበው አቤቱታ፦
• የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ፣
• የወንጀል ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ፣ ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖትን ጨምሮ ድርጊቱን ለምን እንደፈጸሙ ተጠይቀው በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣
• ፍርድ ቤቱ ቀጥታ የማይቀጣቸው ከሆነ፣ ዐቃቤ ሕግ በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው እንዲያደርግ፣
• በተላለፈው ቪዲዮ ላይ ይቅርታ ተጠይቆ ከማኅበራዊ ሚዲያ እንዲወርድ ትዕዛዝ እንዲሰጥበት፣ የሚሉ ነጥቦች ይገኙበታል።
ግራ ቀኙን ያደመጠው ችሎቱ የቀረቡትን አቤቱታዎች መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ከሰዓት 9፡00 ሰዓት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ገዛ ጌታሁን
በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ መጠነ ሰፊ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው ታዋቂ አርቲስቶች፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 2 ቀን 2019 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።
ነገር ግን ተከሳሾቹ "እግረኛው" በተሰኘ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ ቀርበው መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ፣ ዐቃቤ ሕግ ባለ 5 ገጽ የክስ አቤቱታ አቅርቦ ስለነበር ጉዳዩ ከሰዓት በኋላ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተደርጎ ፣ ለዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 4፡00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ጠዋት በነበረው ችሎት ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነን ጨምሮ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ዐቃቤ ሕግ ላቀረበው አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም በሕግ በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ለምን መግለጫ እንደሰጡ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።
ተከሳሾቹ በሰጡት ምላሽ፦ "እኛ የኪነ ጥበብ ሰዎች ነን፤ ነገር ግን በመልካም ስማችን ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ስለተከፈተብንና ስማችን በመጥፋቱ ሥራችን ስለተበላሸ ነው ምላሽ ለመስጠት የተገደድነው" ብለዋል።
"ለምሳሌ በዚህ ምክንያት አምስት የሥራ ውሎች ተቋርጠውብኛል፤ እኔና ጓደኛዬ የምንሰራው የቴሌቪዥን ፕሮግራምም እንዲቋረጥ ተደርጓል" ሲል አርቲስት ይገረም ደጀኔ ለችሎቱ አብራርቷል።
በነበረው መግለጫ የፍርድ ቤቱን የሕግ ሂደት እንዳያስተጓጉሉ ጥንቃቄ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል።
አርቲስቶቹን በማኅበራዊ ሚዲያ አናግሮ መግለጫቸውን ያስተላለፈው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በበኩሉ፦ "እኔ ይህን ፕሮግራም ሳቀርብ የመጀመሪያዬ አይደለም፤ አርቲስቶቹ በሕግ ከመያዛቸው አስቀድሞ አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬን በፊንቴክ ዙሪያ ተገልጋዮች ስለሚያነሱት ቅሬታ ጠይቄ ሰርቻለሁ፤ ከዚያ በኋላም አርቲስቶቹን ጥፋተኛ አድርገው በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የሚዘግቡትን መረጃዎች መነሻ በማድረግ የጠየቅኋቸው ሰዎች አሉ። አሁን እነሱን ያናገርኩት ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የፍትሕ ሂደቱን እንደማይጎዳ የሕግ ባለሙያ አማክሬ ነው" ሲል ለችሎቱ አስረድቷል።
ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የተሰጠው መግለጫ ከፍርድ ቤት ውጭ ውሳኔ መስጠት እንደሆነና በሕግ ሂደት ላይ ባለ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠት በሕግ ወንጀል መሆኑ መደነገጉን አብራርቷል።
ቀጥሎም "ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ የአርቲስቶችን ጠበቃ ስለ መዝገቡ ጠይቆ ጠበቃው 'በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ አልሰጥም' ሲሉ 'ፈሪ ነህ ማለት ነው?' በማለት ተናግሯል፤ ይህም የተሳሳተ አካሄድ ነው።
ማንም ቢሆን መግለጫ መስጠት በሕግ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አያውቅም ተብሎ አይገመትም፤ “የመጣው ይምጣ” በሚል ስሜት የተሰጠ መግለጫ እንደሆነ ስለምናምን፣ ፍርድ ቤቱ በአቤቱታው ላይ የተጠቀሱትን መርምሮ ተገቢውን ውሳኔ እንዲሰጥልን" ሲል ጠይቋል።
ዐቃቤ ሕግ ከትላንት በፊቱ ችሎት በጽሑፍ ባቀረበው አቤቱታ፦
• የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ፣
• የወንጀል ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ፣ ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖትን ጨምሮ ድርጊቱን ለምን እንደፈጸሙ ተጠይቀው በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣
• ፍርድ ቤቱ ቀጥታ የማይቀጣቸው ከሆነ፣ ዐቃቤ ሕግ በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው እንዲያደርግ፣
• በተላለፈው ቪዲዮ ላይ ይቅርታ ተጠይቆ ከማኅበራዊ ሚዲያ እንዲወርድ ትዕዛዝ እንዲሰጥበት፣ የሚሉ ነጥቦች ይገኙበታል።
ግራ ቀኙን ያደመጠው ችሎቱ የቀረቡትን አቤቱታዎች መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ከሰዓት 9፡00 ሰዓት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ገዛ ጌታሁን
12 hours ago
አርቲስት ቬሮኒካ አዳነህ ለ«ሱሱ ሂውማን ሄር» የሁለት ዓመት የበጎ ፈቃድ አምባሳደር ሆነች!
#fastmereja :-በስደት ሀገር ከነበረ ከባድ የህይወት ውጣ ውረድ እና የእስራት ፈተና በመውጣት በጠንካራ ማንነቷ የራሷን ስኬት መገንባት የቻለችው ስራ ፈጣሪ ሱመያ ዋሪስ፣ በሀገሯ አዲስ የንግድ ምዕራፍ መጀመሯን በዛሬዉ እለት አስታወቀች።
በስደት ሀገር በሰው ቤት ተቀጣሪነት በመጀመር፣ በኋላም በሊባኖስ ዋና ከተማ በትንሽ የሴቶች ውበት ሳሎን ተነስታ ታዋቂ የሂውማን ሄር (Human Hair) አስመጪ መሆን የቻለችው ሱመያ፤ የማህበራዊ ሚዲያ (ቲክቶክ) አጠቃቀሟ እና ከአርቲስት ቬሮኒካ አዳነህ የተደረገላት ድጋፍ ለስኬቷ ትልቅ መንገድ መክፈቱን ገልጻለች።
በጉዞዋ ላይ ባጋጠማት ድንገተኛ የእስራት ፈተና ላለፉት 10 ዓመታት የደከመችበትን ሀብትና ንብረት ብታጣይም፣ ወደ ሀገሯ ኢትዮጵያ ከተመለሰች በኋላ በፈጣሪ እርዳታ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ባሉ ኢትዮጵያውያን፣ በወዳጇ ሀቢባ እንዲሁም በአርቲስት ቬሮኒካ አዳነህ ያልተቋረጠ ደጋፊነት መልሳ መቆም እንደቻለች ገልፃለች።
ድምጻዊ እና አርቲስት ቬሮኒካ አዳነህ ለሱመያ ዋሪስ ባደረገችላት ትልቅ ሰርፕራይዝ፣ ለ«ሱሱ ሂውማን ሄር» (Susu Human Hair) ለሁለት ዓመታት ያህል ያለ ምንም ክፍያ በነፃ የብራንድ አምባሳደር ሆና ለመስራት ተስማምታለች።
በተጨማሪም ሱመያ ዋሪስ በሀገሯ ኢትዮጵያ ግዙፍ የሂውማን ሄር መሸጫ እና ዘመናዊ የውበት ሳሎን ለመክፈት ዝግጅቷን ያጠናቀቀች ሲሆን፣ ጥራት ያላቸውን የፀጉር ምርቶች በቀጥታ ከቻይና ግዙፍ የሂውማን ሄርኩባንያዎች ጋር በመስራት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ደንበኞች ለማቅረብ ስምምነት ላይ መድረሷ ተገልጿል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ በድጋሚ ለመክፈት ዝግጅቷን ማጠናቀቋን እንዲሁም ከቻይና ሂውማን ሄር ኩባንያ ጋር አብራ መስራት መጀመሯን አክላ አስታውቃለች።
ወደፊትም ተደራሽነቷን በማስፋት በተለያዩ ሀገራት የተለያዩ ቅርንጫፎችን የመክፈት እቅድ እንዳላትም ነዉ የገለፀችዉ።
#fastmereja :-በስደት ሀገር ከነበረ ከባድ የህይወት ውጣ ውረድ እና የእስራት ፈተና በመውጣት በጠንካራ ማንነቷ የራሷን ስኬት መገንባት የቻለችው ስራ ፈጣሪ ሱመያ ዋሪስ፣ በሀገሯ አዲስ የንግድ ምዕራፍ መጀመሯን በዛሬዉ እለት አስታወቀች።
በስደት ሀገር በሰው ቤት ተቀጣሪነት በመጀመር፣ በኋላም በሊባኖስ ዋና ከተማ በትንሽ የሴቶች ውበት ሳሎን ተነስታ ታዋቂ የሂውማን ሄር (Human Hair) አስመጪ መሆን የቻለችው ሱመያ፤ የማህበራዊ ሚዲያ (ቲክቶክ) አጠቃቀሟ እና ከአርቲስት ቬሮኒካ አዳነህ የተደረገላት ድጋፍ ለስኬቷ ትልቅ መንገድ መክፈቱን ገልጻለች።
በጉዞዋ ላይ ባጋጠማት ድንገተኛ የእስራት ፈተና ላለፉት 10 ዓመታት የደከመችበትን ሀብትና ንብረት ብታጣይም፣ ወደ ሀገሯ ኢትዮጵያ ከተመለሰች በኋላ በፈጣሪ እርዳታ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ባሉ ኢትዮጵያውያን፣ በወዳጇ ሀቢባ እንዲሁም በአርቲስት ቬሮኒካ አዳነህ ያልተቋረጠ ደጋፊነት መልሳ መቆም እንደቻለች ገልፃለች።
ድምጻዊ እና አርቲስት ቬሮኒካ አዳነህ ለሱመያ ዋሪስ ባደረገችላት ትልቅ ሰርፕራይዝ፣ ለ«ሱሱ ሂውማን ሄር» (Susu Human Hair) ለሁለት ዓመታት ያህል ያለ ምንም ክፍያ በነፃ የብራንድ አምባሳደር ሆና ለመስራት ተስማምታለች።
በተጨማሪም ሱመያ ዋሪስ በሀገሯ ኢትዮጵያ ግዙፍ የሂውማን ሄር መሸጫ እና ዘመናዊ የውበት ሳሎን ለመክፈት ዝግጅቷን ያጠናቀቀች ሲሆን፣ ጥራት ያላቸውን የፀጉር ምርቶች በቀጥታ ከቻይና ግዙፍ የሂውማን ሄርኩባንያዎች ጋር በመስራት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ደንበኞች ለማቅረብ ስምምነት ላይ መድረሷ ተገልጿል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ በድጋሚ ለመክፈት ዝግጅቷን ማጠናቀቋን እንዲሁም ከቻይና ሂውማን ሄር ኩባንያ ጋር አብራ መስራት መጀመሯን አክላ አስታውቃለች።
ወደፊትም ተደራሽነቷን በማስፋት በተለያዩ ሀገራት የተለያዩ ቅርንጫፎችን የመክፈት እቅድ እንዳላትም ነዉ የገለፀችዉ።
13 hours ago
የየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሚያሰራውን ቤተሰሊሆም አጠቃላይ ሆስፒታል ህንፃ ግንባታን አስመልክቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡
ከሁሉ አሰቀድመን እግዚአብሔር አምላካችን ለ2018 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሁላችንንም በሰላም በጤና ስላደረሰን እናመሰግነዋለን፡፡የተከበራችሁ አበው መነኮሳት፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ካህናት እና ዲያቆናት፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣ ምዕመናን እና ወጣቶች በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተከታዮች እንዲሁም ይህን መልእክት ለመላው ዓለም ለማስተላለፍ የተገኛችሁ የሚድያ አካላት በሙሉ በእግዚአብሔር ስም የከበረ ሰላምታችንን ጥንታዊ እና ታሪካዊ ከሆነው ከየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እናቀርባለን፡፡
“በኂሩተ ጻድቃን ትረትዕ ሀገር”
“በጻድቃን ልማት ከተማ ደስ ይላታል”
ምሳ 11፥10
እግዚአብሔር በንጉሱ ሰሎሞን ላይ አድሮ የተናገረውን መነሻ በማድረግ ልማት ለቤተከርስቲያን ፣ልማት ለሀገር፣ልማት ለማኅበረ ስብእ አስፈላጊ መሆኑን በማሰብ በአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለሚገነባው ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል የህንፃ ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ ግብር የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡ የእግዚአበሔር ሰላም ከሁላችንም ጋር ይሁን፡፡ አሜን።
1. ታሪካዊ ዳራ እና የልማት መነሻ
ከአክሱም ዘመነ መንግሥት (በአባ ሰላማ ዘመን) የጀመረውና ከ1600 ዓመታት በላይ የዘለቀው የየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፤ የኢትዮጵያን ጥንታዊነትና የአዲስ አበባን ከተማ አመሰራረት የሚተርክ ህያው ቅርስ ነው።ይህ ታሪካዊ ደብር በአብርሃ ወአጽብሃ፣ በዳግማዊ አጼ ምኒልክና በንግሥት ጣይቱ፣ እንዲሁም በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት በርካታ የታሪክና የፈተና ምዕራፎችን አልፎ ዛሬ ላይ ደርሷል።
ደብሩ ከሃይማኖታዊ አገልግሎቱ ባሻገር፣ የአዲስ አበባ የመጀመሪያው የቀብር ቦታ በመሆን የሊቃውንቱና የካህናቱ እንዲሁም የታላቁ ሐኪም ወርቅነህ እሸቴን፣ የኢትዮጵያ ታላላቅ ጄነራሎችና ፊት አውራሪዎችን ዓጽም በክበር ማረፊያ ሆኗል፡፡ የጸሎትና ማህበራዊ አገልግሎት እንዲሁም ለአካባቢው አብያተ ክርስቲያናት መመስረት ባደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይታወቃል። ዛሬ ይህ ታሪካዊ ደብር ጥንታዊ ታሪኩንና መንፈሳዊ ታላቅነቱን በዘመናዊ ማህበራዊ ልማት ለመድገም፣አካላዊ ፈውስን በሳይንሳዊ ሕክምና የመንፈሳዊ ፈውስን በፀሎትና በጠበል የሚያዋህድ ታላቅ የልማት ፕሮጀክት ይፋአድርጓል።
2. የሆስፒታሉ ይዘት፣ ራዕይና ሰብዓዊ ተልዕኮ
ቤተክርስቲያኑ ባለ 15 ወለል ማለትም (2 Basement+G+ 12ወለል) የሆነውን «ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል» ህንፃ ግንባታ የጀመረ ሲሆን፣ የመጀመሪያውን ምዕራፍ የመሰረት ቁፋሮና የአፈር ናዳ መከላከያ (ሾሪንግ) ሥራ በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
ይህ በ1000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈውና ባለ 250 የህሙማን ሕክምና መስጫ አልጋ አቅም የሚኖረው ዘመናዊ ሆስፒታል፤ የተመላላሽ ክሊኒኮችን፣ የፅኑ ሕክምና (ICU)፣ የቀዶ ጥገና ክፍሎችን እንዲሁም ለእናቶችና ሕጻናት ጤና፣ ለልብ ሕክምናና ለተላላፊ በሽታዎች መከላከያ የሚሆኑ ልዩ ልዩ ማዕከላትን ያካትታል። ተቋሙ የጤና አጠባበቅን እንደ ንግድ ሳይሆን እንደ ሰብዓዊና መንፈሳዊ አገልግሎት በመመልከት፣ለሁሉም የማህበረሰቡ አባላት በሙሉ ጥራት ያለው፣ ተደራሽና አቅምን ያገናዘበ የሕክምና አገልግሎት ያቀርባል።
3. የግንባታ ወጪ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ጥሪ
በህንፃ ባለሙያዎች ጥናት መሠረት ለህንፃ ግንባታው አጠቃላይ ወጪ ብር 405,040,000 (አራት መቶ አምስትሚሊዮን አርባ ሺህ ብር) እንደሚሆን ተገምቷል።ይህ ወጪ በየጊዜው በሚታየው የዋጋ ንረት ምክንያት ሊጨምር እንደሚችል ይታሰባል፡፡
ይህንን ከፍተኛ ወጪ ለመሸፈንና ቀጣዩን ወሳኝ የግንባታምዕራፍ ለመጀመር ቤተ ክርስቲያኑ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ምዕመናንን፣ የንግዱን ማህበረሰብና የልማት አጋሮችን ያሳተፈ የሀብት ማሰባሰቢያ ስልት ቀይሷል።
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ እና የልማት ኮሚቴው ምዕመናን በሰጦታቸው ከእግዚአብሔር የሚያገኙትን በረከት በማሰብ፦ «ይህ ታላቅ የማህበራዊና የጤና ልማት ፕሮጀክት ፍጻሜ እንዲያገኝ የዓላማው ደጋፊዎች ሁሉ የእርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉና አሻራቸውን እንዲያኖሩ በሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል ስም እንማጸናለን» ሲል ጥሪውን ያስተላልፋል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ዝርዝር፦
• ቀን፦ ነሐሴ 8፣ 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም
• ሰዓት፦ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ
የገቢ ማሰባሰቢያ የባንክ አማራጮች፦
• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብቁጥር፦
1000000764087 እንዲሁም
አጭር ቁጥር 1277
• አባይ ባንክ ሂሳብ ቁጥር፦ 1227
• አዋሽ ባንክ ሂሳብ ቁጥር
013521784586601
• ስዊፍት ኮድ AWINETAA
• ወገን ፈንድ 👉 https://www.wegenfund.com/...
ለተጨማሪ መረጃ፦
• ስልክ ቁጥር፦
0945881188 እና 0945771188
• Email፦ Seyoumwgebrielgmail .com
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።
ከሁሉ አሰቀድመን እግዚአብሔር አምላካችን ለ2018 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሁላችንንም በሰላም በጤና ስላደረሰን እናመሰግነዋለን፡፡የተከበራችሁ አበው መነኮሳት፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ካህናት እና ዲያቆናት፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣ ምዕመናን እና ወጣቶች በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተከታዮች እንዲሁም ይህን መልእክት ለመላው ዓለም ለማስተላለፍ የተገኛችሁ የሚድያ አካላት በሙሉ በእግዚአብሔር ስም የከበረ ሰላምታችንን ጥንታዊ እና ታሪካዊ ከሆነው ከየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እናቀርባለን፡፡
“በኂሩተ ጻድቃን ትረትዕ ሀገር”
“በጻድቃን ልማት ከተማ ደስ ይላታል”
ምሳ 11፥10
እግዚአብሔር በንጉሱ ሰሎሞን ላይ አድሮ የተናገረውን መነሻ በማድረግ ልማት ለቤተከርስቲያን ፣ልማት ለሀገር፣ልማት ለማኅበረ ስብእ አስፈላጊ መሆኑን በማሰብ በአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለሚገነባው ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል የህንፃ ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ ግብር የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡ የእግዚአበሔር ሰላም ከሁላችንም ጋር ይሁን፡፡ አሜን።
1. ታሪካዊ ዳራ እና የልማት መነሻ
ከአክሱም ዘመነ መንግሥት (በአባ ሰላማ ዘመን) የጀመረውና ከ1600 ዓመታት በላይ የዘለቀው የየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፤ የኢትዮጵያን ጥንታዊነትና የአዲስ አበባን ከተማ አመሰራረት የሚተርክ ህያው ቅርስ ነው።ይህ ታሪካዊ ደብር በአብርሃ ወአጽብሃ፣ በዳግማዊ አጼ ምኒልክና በንግሥት ጣይቱ፣ እንዲሁም በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት በርካታ የታሪክና የፈተና ምዕራፎችን አልፎ ዛሬ ላይ ደርሷል።
ደብሩ ከሃይማኖታዊ አገልግሎቱ ባሻገር፣ የአዲስ አበባ የመጀመሪያው የቀብር ቦታ በመሆን የሊቃውንቱና የካህናቱ እንዲሁም የታላቁ ሐኪም ወርቅነህ እሸቴን፣ የኢትዮጵያ ታላላቅ ጄነራሎችና ፊት አውራሪዎችን ዓጽም በክበር ማረፊያ ሆኗል፡፡ የጸሎትና ማህበራዊ አገልግሎት እንዲሁም ለአካባቢው አብያተ ክርስቲያናት መመስረት ባደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይታወቃል። ዛሬ ይህ ታሪካዊ ደብር ጥንታዊ ታሪኩንና መንፈሳዊ ታላቅነቱን በዘመናዊ ማህበራዊ ልማት ለመድገም፣አካላዊ ፈውስን በሳይንሳዊ ሕክምና የመንፈሳዊ ፈውስን በፀሎትና በጠበል የሚያዋህድ ታላቅ የልማት ፕሮጀክት ይፋአድርጓል።
2. የሆስፒታሉ ይዘት፣ ራዕይና ሰብዓዊ ተልዕኮ
ቤተክርስቲያኑ ባለ 15 ወለል ማለትም (2 Basement+G+ 12ወለል) የሆነውን «ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል» ህንፃ ግንባታ የጀመረ ሲሆን፣ የመጀመሪያውን ምዕራፍ የመሰረት ቁፋሮና የአፈር ናዳ መከላከያ (ሾሪንግ) ሥራ በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
ይህ በ1000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈውና ባለ 250 የህሙማን ሕክምና መስጫ አልጋ አቅም የሚኖረው ዘመናዊ ሆስፒታል፤ የተመላላሽ ክሊኒኮችን፣ የፅኑ ሕክምና (ICU)፣ የቀዶ ጥገና ክፍሎችን እንዲሁም ለእናቶችና ሕጻናት ጤና፣ ለልብ ሕክምናና ለተላላፊ በሽታዎች መከላከያ የሚሆኑ ልዩ ልዩ ማዕከላትን ያካትታል። ተቋሙ የጤና አጠባበቅን እንደ ንግድ ሳይሆን እንደ ሰብዓዊና መንፈሳዊ አገልግሎት በመመልከት፣ለሁሉም የማህበረሰቡ አባላት በሙሉ ጥራት ያለው፣ ተደራሽና አቅምን ያገናዘበ የሕክምና አገልግሎት ያቀርባል።
3. የግንባታ ወጪ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ጥሪ
በህንፃ ባለሙያዎች ጥናት መሠረት ለህንፃ ግንባታው አጠቃላይ ወጪ ብር 405,040,000 (አራት መቶ አምስትሚሊዮን አርባ ሺህ ብር) እንደሚሆን ተገምቷል።ይህ ወጪ በየጊዜው በሚታየው የዋጋ ንረት ምክንያት ሊጨምር እንደሚችል ይታሰባል፡፡
ይህንን ከፍተኛ ወጪ ለመሸፈንና ቀጣዩን ወሳኝ የግንባታምዕራፍ ለመጀመር ቤተ ክርስቲያኑ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ምዕመናንን፣ የንግዱን ማህበረሰብና የልማት አጋሮችን ያሳተፈ የሀብት ማሰባሰቢያ ስልት ቀይሷል።
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ እና የልማት ኮሚቴው ምዕመናን በሰጦታቸው ከእግዚአብሔር የሚያገኙትን በረከት በማሰብ፦ «ይህ ታላቅ የማህበራዊና የጤና ልማት ፕሮጀክት ፍጻሜ እንዲያገኝ የዓላማው ደጋፊዎች ሁሉ የእርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉና አሻራቸውን እንዲያኖሩ በሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል ስም እንማጸናለን» ሲል ጥሪውን ያስተላልፋል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ዝርዝር፦
• ቀን፦ ነሐሴ 8፣ 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም
• ሰዓት፦ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ
የገቢ ማሰባሰቢያ የባንክ አማራጮች፦
• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብቁጥር፦
1000000764087 እንዲሁም
አጭር ቁጥር 1277
• አባይ ባንክ ሂሳብ ቁጥር፦ 1227
• አዋሽ ባንክ ሂሳብ ቁጥር
013521784586601
• ስዊፍት ኮድ AWINETAA
• ወገን ፈንድ 👉 https://www.wegenfund.com/...
ለተጨማሪ መረጃ፦
• ስልክ ቁጥር፦
0945881188 እና 0945771188
• Email፦ Seyoumwgebrielgmail .com
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።
13 hours ago
ሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ኩባንያዎቹ ምን እየሰሩ ነው?
👉የብረት ፋብሪካው በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ከአካባቢ ብከላ ነጻ የሆነ የምርት ሂደት መጀመሩ ተነግሯል፡፡
በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ኃ/የተ/ግ/ማ እንደ አገር በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የተቀመጠውን የኢንደስትሪ ቅጥር ግቢ ሁለት በመቶ ከባቢ በአረንገዴ የመሸፈን ሃላፊነት ተወጥተው ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት አቅራቢያ የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ልማት ላይ በጉልህ መሳተፍ እንደቀጠሉ ተገለጠ፡፡
ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት የቢሾፍቱ ከተማ ቅጥር ግቢ እና አካባቢው በሚገኙ የተራቆቱ ስፍራዎቸን በአረንጓዴ የመሸፈን ስራ አጠናክረው የቀጠለ መሆኑ ታውቋል፡፡
በዚህም ዘንድሮው የክረምት ወቅት ከመንግስት ተረክበው መልሶ እንዲያገግም እየተንከባከቡት በሚገኘው ዲባዬ ተራራ በተከታታይ ለ 5ኛ አመት የተከላ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡
ሀሙስ ሐምሌ 30 ቀን በተከናወነው እና የሁለቱ ኩባንያ ሰራተኞች በተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቢሾፍቱ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ኃላፊ ጣይቱ ያሚ የሁለቱ ድርጅቶች የአረንጓዴ ልማት ተግባር በአካባቢው ለሚገኙ በርካታ ኢንደስትሪዎች አርአያ እና ቀዳሚ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከኢንደስትሪ ግቢ 2 በመቶ በአረንጓዴ መሸፈን አለበት የሚለውን ህግ በተገቢው ሁለቱም ድርጅቶች መወጣታቸውን አስታውሰው፡፡
በተጨማሪነት በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ከኢንደስትሪ ስፍራዎቻቸው ባለፈ በአዋሳኝ የመንገድ አካባቢዎች እንዲሁም የተራቆቱ ቦታዎችን ወደ ጫካ የመለወጥ ስራን እንዲወጡ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጣቸውን ቦታዎች በዛፍ የመሸፈን ስራ ለአመታት በከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰሩ እንደቆዩ ነው የተናገሩት፡፡
ከተማ አሰስተዳደሩ በአረንጓዴ ልማት ሆነ ሌሎች ማህበራዊ ሃላፊነት ስራዎች ጥሪ ባደረገ ጊዜ ቀድመው የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወሱት የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ጣይቱ ይህን መልካም ተግባር ሌሎች በተሞክሮ እንዲወስዱት ነው ያሳሰቡት፡፡
በተከላው ወቅት የግዙፉ ብረት አምራች ስቲሊ አር ኤም አይ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ሰለሞን ደስታ እንደገለፁት ድርጅታቸው ስቲሊ በመርህ ደረጃ የተያዘውን የማህበራዊ ሃላፊነት የመወጣት ተግባር በህብረተሰብ ድጋፍ ላይ ብቻ ያተኮረ አለመሆኑን አስታውሰው፡፡
በአካባቢ ጠበቃ የሚሰራው ስራ የኩባንያው አይነተኛ መርህ መሆኑን እንደ ተጨማሪ የማህበራዊ ሃላፊነት ስራ ተግባር ለአብነት አንስተዋል፡፡
በዚህም ስቲሊ አር ኤም አይ ማምረት ከጀመረበት ያለፉት ሁለት አስርት አመታት ወደ ስራ ካስገባቸው እንደ ዘመናዊ ትምህርት ቤት እንዲሁም የውሃ አቅርቦት አይነት ጉልህ ማህበራዊ ሃላፊነት ባልተናነሰ በአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡
በግቢያችን በመንግስት ከተቀመጠው የሁለት በመቶ አረንጓዴ ሽፋን አልፈናል ያሉት ኢ/ር ሰለሞን ለምግብነት የሚያገለግሉ ዛፎችን የመትከል ግቡም ውጤታማ እየሆነልን ነው ሲሉ ነው ያከሉት።
ዋና ስራ አስኪያጁ በተጨማሪነት በአካበቢው በሚገኙ ተራራማ ቦታዎች ችግኝ በመትከል እና በቋሚነት ባለሞያ ቀጥሮ በመንከባከብ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘት መቻሉንም እንደ ከፍተኛ ተጠቃሽ ውጤት አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም ኩባያው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በማድረግ ዘመናዊ የምርት ሂደትን ያስተዋወቀ መሆኑን ጠቅሰው። ይህም የአካባቢ ጥበቃ አካል ነው ሲሉ በአገር ደረጃ በዘመናዊነት ቀዳሚ የሆነው የብረት ፋብሪካ የስራ ሂደት ጠቅሰዋል፡፡
በተመሳሳይ ከፍተኛ ተኪ የብረት ምርት እና የግንባታ ግብአቶችን በማምረት ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት መቆየት የቻለው የአስመን ስራ አስኪያጅ አቶ ኑሩ እሸቱ የአረንጓዴ አሻራ ስራ የኩባንያቸው ባህል መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጠል መሆኑን ነው የገለፁት፡፡
እንደ አስመን ስራ አስኪያጅ ገለፃ የኩባንያውን ሰራተኛና የአካበባቢውን ነዋሪ በማሳተፍ ሲከናወን የቆየው የአካባቢ ጥበቃ ስራ በተለይ አሁን በፋብሪካዎቹ እና የችግኝ ተከላ በሚከናወንበት አቅራቢያ በሚገኘው በአቡሴራ እየተገነባ የሚገኘው የቢሾፍቱ አየር መንገድ ምቹ እና አረንጓዴ ከባቢ በመፍጠር የራሱ ሚና አለው ሲሉ ነው የገለጹት፡፡
የሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የቦርድ ተወካይ አቶ ግርማ አዲስ በበኩላቸው ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን አረጋውያን የማገዝ፣ ተንከባካቢ የሌላቸው ህጻናትን ከጎናቸው በመሆን አሌንታነት በማረጋገጥ፣ የምገባ ማዕከላትን በማቋቋም፣ በተለያየ ምክንያት እና እንደ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ አይነት አጣዳፊ ሁኔታ ሲያጋጥም ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ በማድረግ የወገን ደራሽ የመሆን ሚናቸውን ከምስረታቸው ጀምሮ እንደተገበሩ ገልፀዋል፡፡
ይህንኑ ተግባር ወደ ፊትም በተቀናጀ መልኩ እንደ ግሩፕ ለማከናወን ፋውንዴሽን መቋቋሙን ነው አክለው የገለጹት፡፡
👉የብረት ፋብሪካው በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ከአካባቢ ብከላ ነጻ የሆነ የምርት ሂደት መጀመሩ ተነግሯል፡፡
በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ኃ/የተ/ግ/ማ እንደ አገር በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የተቀመጠውን የኢንደስትሪ ቅጥር ግቢ ሁለት በመቶ ከባቢ በአረንገዴ የመሸፈን ሃላፊነት ተወጥተው ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት አቅራቢያ የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ልማት ላይ በጉልህ መሳተፍ እንደቀጠሉ ተገለጠ፡፡
ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት የቢሾፍቱ ከተማ ቅጥር ግቢ እና አካባቢው በሚገኙ የተራቆቱ ስፍራዎቸን በአረንጓዴ የመሸፈን ስራ አጠናክረው የቀጠለ መሆኑ ታውቋል፡፡
በዚህም ዘንድሮው የክረምት ወቅት ከመንግስት ተረክበው መልሶ እንዲያገግም እየተንከባከቡት በሚገኘው ዲባዬ ተራራ በተከታታይ ለ 5ኛ አመት የተከላ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡
ሀሙስ ሐምሌ 30 ቀን በተከናወነው እና የሁለቱ ኩባንያ ሰራተኞች በተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቢሾፍቱ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ኃላፊ ጣይቱ ያሚ የሁለቱ ድርጅቶች የአረንጓዴ ልማት ተግባር በአካባቢው ለሚገኙ በርካታ ኢንደስትሪዎች አርአያ እና ቀዳሚ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከኢንደስትሪ ግቢ 2 በመቶ በአረንጓዴ መሸፈን አለበት የሚለውን ህግ በተገቢው ሁለቱም ድርጅቶች መወጣታቸውን አስታውሰው፡፡
በተጨማሪነት በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ከኢንደስትሪ ስፍራዎቻቸው ባለፈ በአዋሳኝ የመንገድ አካባቢዎች እንዲሁም የተራቆቱ ቦታዎችን ወደ ጫካ የመለወጥ ስራን እንዲወጡ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጣቸውን ቦታዎች በዛፍ የመሸፈን ስራ ለአመታት በከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰሩ እንደቆዩ ነው የተናገሩት፡፡
ከተማ አሰስተዳደሩ በአረንጓዴ ልማት ሆነ ሌሎች ማህበራዊ ሃላፊነት ስራዎች ጥሪ ባደረገ ጊዜ ቀድመው የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወሱት የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ጣይቱ ይህን መልካም ተግባር ሌሎች በተሞክሮ እንዲወስዱት ነው ያሳሰቡት፡፡
በተከላው ወቅት የግዙፉ ብረት አምራች ስቲሊ አር ኤም አይ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ሰለሞን ደስታ እንደገለፁት ድርጅታቸው ስቲሊ በመርህ ደረጃ የተያዘውን የማህበራዊ ሃላፊነት የመወጣት ተግባር በህብረተሰብ ድጋፍ ላይ ብቻ ያተኮረ አለመሆኑን አስታውሰው፡፡
በአካባቢ ጠበቃ የሚሰራው ስራ የኩባንያው አይነተኛ መርህ መሆኑን እንደ ተጨማሪ የማህበራዊ ሃላፊነት ስራ ተግባር ለአብነት አንስተዋል፡፡
በዚህም ስቲሊ አር ኤም አይ ማምረት ከጀመረበት ያለፉት ሁለት አስርት አመታት ወደ ስራ ካስገባቸው እንደ ዘመናዊ ትምህርት ቤት እንዲሁም የውሃ አቅርቦት አይነት ጉልህ ማህበራዊ ሃላፊነት ባልተናነሰ በአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡
በግቢያችን በመንግስት ከተቀመጠው የሁለት በመቶ አረንጓዴ ሽፋን አልፈናል ያሉት ኢ/ር ሰለሞን ለምግብነት የሚያገለግሉ ዛፎችን የመትከል ግቡም ውጤታማ እየሆነልን ነው ሲሉ ነው ያከሉት።
ዋና ስራ አስኪያጁ በተጨማሪነት በአካበቢው በሚገኙ ተራራማ ቦታዎች ችግኝ በመትከል እና በቋሚነት ባለሞያ ቀጥሮ በመንከባከብ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘት መቻሉንም እንደ ከፍተኛ ተጠቃሽ ውጤት አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም ኩባያው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በማድረግ ዘመናዊ የምርት ሂደትን ያስተዋወቀ መሆኑን ጠቅሰው። ይህም የአካባቢ ጥበቃ አካል ነው ሲሉ በአገር ደረጃ በዘመናዊነት ቀዳሚ የሆነው የብረት ፋብሪካ የስራ ሂደት ጠቅሰዋል፡፡
በተመሳሳይ ከፍተኛ ተኪ የብረት ምርት እና የግንባታ ግብአቶችን በማምረት ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት መቆየት የቻለው የአስመን ስራ አስኪያጅ አቶ ኑሩ እሸቱ የአረንጓዴ አሻራ ስራ የኩባንያቸው ባህል መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጠል መሆኑን ነው የገለፁት፡፡
እንደ አስመን ስራ አስኪያጅ ገለፃ የኩባንያውን ሰራተኛና የአካበባቢውን ነዋሪ በማሳተፍ ሲከናወን የቆየው የአካባቢ ጥበቃ ስራ በተለይ አሁን በፋብሪካዎቹ እና የችግኝ ተከላ በሚከናወንበት አቅራቢያ በሚገኘው በአቡሴራ እየተገነባ የሚገኘው የቢሾፍቱ አየር መንገድ ምቹ እና አረንጓዴ ከባቢ በመፍጠር የራሱ ሚና አለው ሲሉ ነው የገለጹት፡፡
የሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የቦርድ ተወካይ አቶ ግርማ አዲስ በበኩላቸው ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን አረጋውያን የማገዝ፣ ተንከባካቢ የሌላቸው ህጻናትን ከጎናቸው በመሆን አሌንታነት በማረጋገጥ፣ የምገባ ማዕከላትን በማቋቋም፣ በተለያየ ምክንያት እና እንደ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ አይነት አጣዳፊ ሁኔታ ሲያጋጥም ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ በማድረግ የወገን ደራሽ የመሆን ሚናቸውን ከምስረታቸው ጀምሮ እንደተገበሩ ገልፀዋል፡፡
ይህንኑ ተግባር ወደ ፊትም በተቀናጀ መልኩ እንደ ግሩፕ ለማከናወን ፋውንዴሽን መቋቋሙን ነው አክለው የገለጹት፡፡
Sponsored by
Surafel
14 hours ago
''ቅዱስ ጊዮርጊስን መምራት ሃገር እንደመምራት ነው!'' - አቶ አብነት ገ/መስቀል
#ethiopia | ሼህ ሞሐመድ ሁሴን አል አሙዲ በኢትዮጵያ ባላቸው ግዙፍ የነዳጅ ኩባንያ ''ኖክ'' 15% ድርሻ እንዲሁም የ40% ድርሻ ባለቤት የሆኑበት ''ቦሌ ታወር'' በሽርክና እንዲሁም እንደወዳጅ ከሼኹ ጋር 32 ዓመታት አብረው የቆዩት አቶ አብነት ገ/መስቀል ከሥራ ከተሰናበቱ በኋላ የነበራቸውን አነጋጋሪ ገጠመኞች ''በነገራችን ላይ'' በተሰኘው የጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ ዝግጅት ላይ ቀርበው ተናግረዋል።
እንደ አቶ አብነት ገለጻ ቢሊየነሩ አል አሙዲ እጅግ ለጋስ የነበሩ ሲሆን ለህክምና፣ ለትምህርት፣ ለአየር መንገድ ትኬት እንዲሁም ለቤትና ለመኪና ስጦታዎች በወር እስከ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ያወጡ እንደነበር ተናግረዋል።
ሆኖም ይህ ገደብ የለሽ ልግስና በብዙዎች ዘንድ ለግል ጥቅም ሲባል ሲበዘበዝ እንደነበርና ሰዎችን ከእሳቸው ጋር በማገናኘት ብቻ የኮሚሽን መረብ የዘረጉ አካላት እንደነበሩም ከጋዜጠኛው የተጠየቁት አቶ አብነት ''እኔ ይሄን አድርጌ አላውቅም ብለዋል'' ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ከሼህ አል አሙዲ ጋር ያላቸው የቅርብ ግንኙነት ቢቋረጥም አቶ አብነት የኢንቨስተሩን በጎ አድራጊነት፣ መልካም ስብዕና እና በርካታ የሥራ ዕድሎችን የመፍጠር አዎንታዊ ሚና መስክረዋል።
በሌላ በኩል አል አሙዲ በሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ እና የኤክስፖርት ዘርፎች ላይ ባፈሰሱት መዋለ ነዋይ በኢትዮጵያ ቁጥር አንድ ባለሃብት አስብሏቸዋል።
በሼህ ሞሐመድ እና በአቶ አብነት መካከል ምን ተፈጠረ?
ቅ. ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ምን ገጠመው?
ማን ገደለው? ማን አዳነው?
በነገራችን ላይ!!
እሁድ ምሽት 3:00 ላይ በ arts tv
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ሼህ ሞሐመድ ሁሴን አል አሙዲ በኢትዮጵያ ባላቸው ግዙፍ የነዳጅ ኩባንያ ''ኖክ'' 15% ድርሻ እንዲሁም የ40% ድርሻ ባለቤት የሆኑበት ''ቦሌ ታወር'' በሽርክና እንዲሁም እንደወዳጅ ከሼኹ ጋር 32 ዓመታት አብረው የቆዩት አቶ አብነት ገ/መስቀል ከሥራ ከተሰናበቱ በኋላ የነበራቸውን አነጋጋሪ ገጠመኞች ''በነገራችን ላይ'' በተሰኘው የጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ ዝግጅት ላይ ቀርበው ተናግረዋል።
እንደ አቶ አብነት ገለጻ ቢሊየነሩ አል አሙዲ እጅግ ለጋስ የነበሩ ሲሆን ለህክምና፣ ለትምህርት፣ ለአየር መንገድ ትኬት እንዲሁም ለቤትና ለመኪና ስጦታዎች በወር እስከ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ያወጡ እንደነበር ተናግረዋል።
ሆኖም ይህ ገደብ የለሽ ልግስና በብዙዎች ዘንድ ለግል ጥቅም ሲባል ሲበዘበዝ እንደነበርና ሰዎችን ከእሳቸው ጋር በማገናኘት ብቻ የኮሚሽን መረብ የዘረጉ አካላት እንደነበሩም ከጋዜጠኛው የተጠየቁት አቶ አብነት ''እኔ ይሄን አድርጌ አላውቅም ብለዋል'' ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ከሼህ አል አሙዲ ጋር ያላቸው የቅርብ ግንኙነት ቢቋረጥም አቶ አብነት የኢንቨስተሩን በጎ አድራጊነት፣ መልካም ስብዕና እና በርካታ የሥራ ዕድሎችን የመፍጠር አዎንታዊ ሚና መስክረዋል።
በሌላ በኩል አል አሙዲ በሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ እና የኤክስፖርት ዘርፎች ላይ ባፈሰሱት መዋለ ነዋይ በኢትዮጵያ ቁጥር አንድ ባለሃብት አስብሏቸዋል።
በሼህ ሞሐመድ እና በአቶ አብነት መካከል ምን ተፈጠረ?
ቅ. ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ምን ገጠመው?
ማን ገደለው? ማን አዳነው?
በነገራችን ላይ!!
እሁድ ምሽት 3:00 ላይ በ arts tv
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
14 hours ago
ቋሚ ሲኖዶስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጉዳይ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ማስረጃ እንዲቀርብ ጥሪ አቀረበ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ምርመራ ለማካሄድ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሕዝብ መረጃና ማስረጃ እንዲያቀርብ ጥሪ አቀረበ።
ኮሚቴው እንደገለጸው፣ በሀገረ ስብከቱና በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃ የተከሰቱ ሕገ-ወጥ ቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር፣ ሕገ-ወጥ የፋይናንስ አሠራሮችና የገንዘብ ዝውውሮች፣ ሕገ-ወጥ የቦታና የቤት ኪራይ ውሎች፣ ተደራራቢ ሥራዎችና መሰል ጉዳዮችን በዝርዝር በማጣራት ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ሪፖርት ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀርባል።
በዚህ ሂደት የማጣራት ሥራው በማስረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ተቋም ተኮርና ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጣ እንዲሆን መረጃዎችን መሰብሰብ፣ መተንተን እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት ዋና የሥራ አቅጣጫው መሆኑን ገልጿል።
ኮሚቴው በተለይም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተጠቀሱት እና ተመሳሳይ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምክንያት ተጎጂ የሆኑ እና በቂ ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች፣ በሥራ ሰዓት የማስረጃቸውን ኮፒ በመያዝ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በተከፈተው የመረጃ መሰብሰቢያ ቢሮ በመቅረብ፣ በጽሑፍ፣ በድምፅ ወይም በምስል መረጃ እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
በተጨማሪም መረጃ የሚያቀርቡ ሰዎች በዚህ ምክንያት ማንኛውም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው በቋሚ ሲኖዶስ ዋስትና መሰጠቱን አስታውቆ፣ ማንኛውም አካል ያለውን መረጃና ማስረጃ በነጻነት እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርቧል።
መግለጫው በአጣሪ ኮሚቴው በሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ምርመራ ለማካሄድ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሕዝብ መረጃና ማስረጃ እንዲያቀርብ ጥሪ አቀረበ።
ኮሚቴው እንደገለጸው፣ በሀገረ ስብከቱና በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃ የተከሰቱ ሕገ-ወጥ ቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር፣ ሕገ-ወጥ የፋይናንስ አሠራሮችና የገንዘብ ዝውውሮች፣ ሕገ-ወጥ የቦታና የቤት ኪራይ ውሎች፣ ተደራራቢ ሥራዎችና መሰል ጉዳዮችን በዝርዝር በማጣራት ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ሪፖርት ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀርባል።
በዚህ ሂደት የማጣራት ሥራው በማስረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ተቋም ተኮርና ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጣ እንዲሆን መረጃዎችን መሰብሰብ፣ መተንተን እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት ዋና የሥራ አቅጣጫው መሆኑን ገልጿል።
ኮሚቴው በተለይም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተጠቀሱት እና ተመሳሳይ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምክንያት ተጎጂ የሆኑ እና በቂ ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች፣ በሥራ ሰዓት የማስረጃቸውን ኮፒ በመያዝ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በተከፈተው የመረጃ መሰብሰቢያ ቢሮ በመቅረብ፣ በጽሑፍ፣ በድምፅ ወይም በምስል መረጃ እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
በተጨማሪም መረጃ የሚያቀርቡ ሰዎች በዚህ ምክንያት ማንኛውም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው በቋሚ ሲኖዶስ ዋስትና መሰጠቱን አስታውቆ፣ ማንኛውም አካል ያለውን መረጃና ማስረጃ በነጻነት እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርቧል።
መግለጫው በአጣሪ ኮሚቴው በሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
15 hours ago
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ፤አደረሰን🙏
የፍልሰታ ጾም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፍልሰቷንና ክብሯን በማሰብ የሚጾም የጸሎት፣ የንስሐ፣ የምልጃና የምሕረት ጾም ነው። ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋዋ ከሞትና መቃብር መለየትና ማረግን ያመለክታል። በእነዚህ የተቀደሱ ቀናት ምእመናን በጾም፣ በስግደት፣ በጸሎትና በምጽዋት በመትጋት የእግዚአብሔርን ምሕረት ይለምናሉ፤ “እምነት ያለው ሥራ ይኑረው” እንዲል ቃሉ፣ ጾም ከምጽዋት ጋር ሲታጀብ በፊቱ የተወደደ መሥዋዕት ይሆናል።
“ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም” በከባድ ንፋስና ዝናብ ምክንያት ቤተ መቅደሱ ፈርሶ ይገኛል፣ መነኮሳቱም በድርቅና በርሃብ ከባድ ፈተና ውስጥ ናቸው።
መሬቱ ደርቋል፣ ከጸሎት መልስ የሚቀመስ እህል ጠፍቷል፣ መነኮሳቱ በረሃብና በችግር እየተፈተኑ የዕለት ሕይወታቸውን ለመግፋት በእጅጉ ተቸግረዋል።
የምግብ እጥረት ችግር በየቀኑ እየበረታባቸው ነው። ይህ የእነርሱ ብቻ ፈተና ሳይሆን የሁላችንም ፈተና ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፥26) ላይ፡- «አንድም ብልት ቢሰቃይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ይሰቃያሉ፤ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል» ይላል፡፡በዚህ ምዕራፍ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እያንዳንዱ ምእመን የአንዱ መከራ የሁሉም መከራ፣ የአንዱም ክብር የሁሉም ደስታ መሆኑን ያስተምራል።
ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ ጾም ከምጽዋትና ከርኅራኄ እንደማይለይ ታስተምረናለች፡፡እግዚአብሔርም፦ "የምወደው ጾም ይህ አይደለምን?… ለተራበ እንጀራህን መቁረስ፣ ድሆችንም ወደ ቤትህ ማስገባት ነው።" ይላል (ኢሳይያስ 58፥6–7) ። በዚህ ቅዱስ ወቅት የጾማችን ፍሬ በምጽዋትና በፍቅር ሥራ ሊገለጥ ይገባል።
"በጎ ማድረግንና መለገስን አትርሱ፤ እንዲህ ያለውን መሥዋዕት እግዚአብሔር ይወዳልና።"(ዕብራውያን 13፥16) እንዲል ቃሉ፤በዚህ የፍልሰታ ጾም የጸሎታችንን ፍሬ በምጽዋት እናሳይ፤ ለቤተ መቅደሱ መልሶ መገንባት፣ ለመነኮሳቱ ምግብና መሠረታዊ ፍላጎቶች ማሟላት በአቅማችን እንረባረብ።
ዛሬ የምንሰጠው ትንሽ ድጋፍ የተራበን ያጸናል፣ የፈረሰውን ያቆማል፣ በልባቸው ተስፋን ያበራል። እንግዲህ በዚህ የተቀደሰ የፍልሰታ ጾም ወቅት በጸሎት፣ በምጽዋትና በፍቅር ሥራ አንድ እንሁን፤ ገዳማዊያኑን ስንደግፍ እኛም የበረከቱ ተሳታፊ እንሆናለንና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፡- ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡- 1000766349227
አቢሲንያ ባንክ ፡- 262281132
ለበለጠ መረጃ:- 0944672222 ወይም 0916106921
የፍልሰታ ጾም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፍልሰቷንና ክብሯን በማሰብ የሚጾም የጸሎት፣ የንስሐ፣ የምልጃና የምሕረት ጾም ነው። ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋዋ ከሞትና መቃብር መለየትና ማረግን ያመለክታል። በእነዚህ የተቀደሱ ቀናት ምእመናን በጾም፣ በስግደት፣ በጸሎትና በምጽዋት በመትጋት የእግዚአብሔርን ምሕረት ይለምናሉ፤ “እምነት ያለው ሥራ ይኑረው” እንዲል ቃሉ፣ ጾም ከምጽዋት ጋር ሲታጀብ በፊቱ የተወደደ መሥዋዕት ይሆናል።
“ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም” በከባድ ንፋስና ዝናብ ምክንያት ቤተ መቅደሱ ፈርሶ ይገኛል፣ መነኮሳቱም በድርቅና በርሃብ ከባድ ፈተና ውስጥ ናቸው።
መሬቱ ደርቋል፣ ከጸሎት መልስ የሚቀመስ እህል ጠፍቷል፣ መነኮሳቱ በረሃብና በችግር እየተፈተኑ የዕለት ሕይወታቸውን ለመግፋት በእጅጉ ተቸግረዋል።
የምግብ እጥረት ችግር በየቀኑ እየበረታባቸው ነው። ይህ የእነርሱ ብቻ ፈተና ሳይሆን የሁላችንም ፈተና ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፥26) ላይ፡- «አንድም ብልት ቢሰቃይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ይሰቃያሉ፤ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል» ይላል፡፡በዚህ ምዕራፍ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እያንዳንዱ ምእመን የአንዱ መከራ የሁሉም መከራ፣ የአንዱም ክብር የሁሉም ደስታ መሆኑን ያስተምራል።
ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ ጾም ከምጽዋትና ከርኅራኄ እንደማይለይ ታስተምረናለች፡፡እግዚአብሔርም፦ "የምወደው ጾም ይህ አይደለምን?… ለተራበ እንጀራህን መቁረስ፣ ድሆችንም ወደ ቤትህ ማስገባት ነው።" ይላል (ኢሳይያስ 58፥6–7) ። በዚህ ቅዱስ ወቅት የጾማችን ፍሬ በምጽዋትና በፍቅር ሥራ ሊገለጥ ይገባል።
"በጎ ማድረግንና መለገስን አትርሱ፤ እንዲህ ያለውን መሥዋዕት እግዚአብሔር ይወዳልና።"(ዕብራውያን 13፥16) እንዲል ቃሉ፤በዚህ የፍልሰታ ጾም የጸሎታችንን ፍሬ በምጽዋት እናሳይ፤ ለቤተ መቅደሱ መልሶ መገንባት፣ ለመነኮሳቱ ምግብና መሠረታዊ ፍላጎቶች ማሟላት በአቅማችን እንረባረብ።
ዛሬ የምንሰጠው ትንሽ ድጋፍ የተራበን ያጸናል፣ የፈረሰውን ያቆማል፣ በልባቸው ተስፋን ያበራል። እንግዲህ በዚህ የተቀደሰ የፍልሰታ ጾም ወቅት በጸሎት፣ በምጽዋትና በፍቅር ሥራ አንድ እንሁን፤ ገዳማዊያኑን ስንደግፍ እኛም የበረከቱ ተሳታፊ እንሆናለንና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፡- ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡- 1000766349227
አቢሲንያ ባንክ ፡- 262281132
ለበለጠ መረጃ:- 0944672222 ወይም 0916106921
17 hours ago
❤እንኳን ለፆመ ፍልሰታ ለእመቤታቸን በሰላም አደረሳቹ እያልን❤ ፡:
የእረፍት ቀን ሰንበትን እለተ እሁድን የት ሊያሳልፋ አሰቡ እውነተኛ ሰላም በሚገኝበት በእግዚአብሔር ቤት ኑ እለተ ሰንበትን ወደ ተለያዩ ገዳማት በረከትን በመቀበል በማግኘት እንቀደስ እንላለን፡፡
ማህበራችን ጎዶልያስ የጉዞ ማህበር እና መዝሙር ቤት የፍልሠታ ፆምን አስመልክቶ በልዩ አገልግሎት አብረን እንጓዝ ይላል ፡፡
ትኬቱን በአሉበት ቦታ ሆነው በባንክ መቁርጥ ይችላሉ
ለበለጠ መረጃ 📞 09 47 15 15 15
በማህበሩ ስልክ ቁጥር ደውለው ቦታውን ይያዙ መልካም ሁሉ ከእናንተው ጋር ይሁን ለቤተክርስቲያናችን ሰላሙን አንድነቱን ያድልልን
መነሻ ቦታዎች
👉 ኮዬ ኮንደሚንየም መስቀለኛ
👉 ቱሉ ዲምቱ አደባባይ
👉 ጎሮ አደባባይ
👉 መገናኛ አደባባይ
👉 ጣፎ አደባባይ
ደውለው ይመዝገቡ 09 47 15 15 15
19 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በህጻናት ክትባት እና በኦቲዝም ዙሪያ አዲስ አስፈጻሚ ትዕዛዝ በቀጣዩ ሳምንት ሊያወጣ እንደሚችል ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጮች አጋለጡ። አስርተ ዓመታትን ያስቆጠሩ ሳይንሳዊ ምርምሮች በክትባት እና በኦቲዝም መካከል ምንም ዓይነት ግንኙነት እንደሌለ በተደጋጋሚ ቢያረጋግጡም፣ ፕሬዝዳንቱ በዚህ ጉዳይ ላይ ተጨማሪ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ፍላጎት ማሳየታቸው ተገልጿል።
የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ ኩሽ ዴሳይ እንዳሉት፣ "አሜሪካ በዓለም ምርጡን የህጻናት የክትባት መርሐ-ግብር ሊኖራት ይገባል" የሚለው የፕሬዝዳንቱ አቋም ግልጽ ነው። አስተዳደሩም ጥያቄ እና ስጋት ላላቸው በርካታ ወላጆች በሳይንስ ላይ የተመሰረተ ምላሽ ለመስጠት ቁርጠኛ መሆኑን ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል። ከዚህ ቀደም ትራምፕ በግንቦት ወር ባወጡት ትዕዛዝ የክትባት መጠኖችን በመቀነስ ከሌሎች ሀገራት ጋር ለማስተካከል የሞከሩ ሲሆን፣ የጤና እና የሰብዓዊ አገልግሎት ጸሐፊው ሮበርት ኤፍ. ኬኔዲ ጁኒየር መደበኛ የክትባት መርሐ-ግብሮችን ለመቀየር ያደረጉት ሙከራ በፍርድ ቤት መታገዱ ይታወሳል።
ባለፈው ሳምንት በካምፕ ዴቪድ በተካሄደ የካቢኔ ስብሰባ ላይ ፕሬዝዳንት ትራምፕ፣ ቀደም ሲል የጸረ-ክትባት ቡድንን ሲመሩ ለነበሩት ሮበርት ኤፍ. ኬኔዲ ጁኒየር ስለ ኦቲዝም መንስኤ ምርምር ሂደት በአደባባይ የጠየቋቸው ሲሆን፣ ኬኔዲም "መልስ ይዘን እንመጣለን" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ይህ አዲስ ትዕዛዝ፣ ከመጪው የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት አወዛጋቢ ጉዳዮችን ላለማንሳት የጤና ባለስልጣናት ይዘውት የነበረውን ስትራቴጂ የሚቀለብስ እና ርዕሱን ዳግም ወደ አደባባይ የሚያመጣው እንደሚሆን ተገምቷል።
የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ ኩሽ ዴሳይ እንዳሉት፣ "አሜሪካ በዓለም ምርጡን የህጻናት የክትባት መርሐ-ግብር ሊኖራት ይገባል" የሚለው የፕሬዝዳንቱ አቋም ግልጽ ነው። አስተዳደሩም ጥያቄ እና ስጋት ላላቸው በርካታ ወላጆች በሳይንስ ላይ የተመሰረተ ምላሽ ለመስጠት ቁርጠኛ መሆኑን ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል። ከዚህ ቀደም ትራምፕ በግንቦት ወር ባወጡት ትዕዛዝ የክትባት መጠኖችን በመቀነስ ከሌሎች ሀገራት ጋር ለማስተካከል የሞከሩ ሲሆን፣ የጤና እና የሰብዓዊ አገልግሎት ጸሐፊው ሮበርት ኤፍ. ኬኔዲ ጁኒየር መደበኛ የክትባት መርሐ-ግብሮችን ለመቀየር ያደረጉት ሙከራ በፍርድ ቤት መታገዱ ይታወሳል።
ባለፈው ሳምንት በካምፕ ዴቪድ በተካሄደ የካቢኔ ስብሰባ ላይ ፕሬዝዳንት ትራምፕ፣ ቀደም ሲል የጸረ-ክትባት ቡድንን ሲመሩ ለነበሩት ሮበርት ኤፍ. ኬኔዲ ጁኒየር ስለ ኦቲዝም መንስኤ ምርምር ሂደት በአደባባይ የጠየቋቸው ሲሆን፣ ኬኔዲም "መልስ ይዘን እንመጣለን" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ይህ አዲስ ትዕዛዝ፣ ከመጪው የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት አወዛጋቢ ጉዳዮችን ላለማንሳት የጤና ባለስልጣናት ይዘውት የነበረውን ስትራቴጂ የሚቀለብስ እና ርዕሱን ዳግም ወደ አደባባይ የሚያመጣው እንደሚሆን ተገምቷል።
19 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በደቡብ ሱዳን መዲና ጁባ በሚገኝ አንድ ጠባብ የወርቅ ገበያ ውስጥ፣ በኮንትሮባንድ ከሱዳን የሚገባው ወርቅ ህጋዊ ሽፋን ተሰጥቶት ወደ ዱባይ እንዴት እንደሚላክ ለግል ደህንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ (F.A. በሚል ምህጻረ ቃል የተገለጹ) አንድ ነጋዴ አጋልጠዋል።
ነጋዴው ለሱዳን ትሪቢዩን እንደገለጹት፣ በየብስ ድንበር በኩል የሚደረገው የሱዳን ወርቅ ዝውውር አሁንም አልቆመም። ከዳርፉር እና ከደቡብ ኮርዶፋን ማዕድን ማውጫዎች የሚነሱ የጭነት መኪናዎች እና ሞተር ብስክሌቶች ቁጥጥር በማይደረግባቸው የድንበር መስመሮች በኩል ወርቁን ያለማቋረጥ ያጓጉዛሉ።
ወርቁ ወደ ጁባ የሚገባው ባልተጣራ እና ጥሬ በሆነ መልኩ መሆኑን ያስረዱት ነጋዴው፤ ደላሎች እና የሀገር ውስጥ ነጋዴዎች ማዕድኑን በሱዳን ማዕከላዊ ባንክ ከሚሰጠው መደበኛ የምንዛሬ ተመን እጅግ በተሻለ ዋጋ በአሜሪካ ዶላር በጥሬ ገንዘብ እንደሚገዙት አብራርተዋል።
ይህንን ወርቅ ህጋዊ ለማድረግ፣ ነጋዴዎቹ ማዕድኑን ዳግም በማቅለጥ እና በመቀላቀል አዲስ ቅርጽ ይሰጡታል። በመቀጠልም ወርቁ በደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያ ወይም ምዕራብ ባህር ኤል ጋዛል ግዛቶች እንደተመረተ የሚያስመስል የሀሰት ሰነድ ይዘጋጅለታል። ይህ የሀሰት ሰነድ ወርቁ ያለምንም ህጋዊ እንቅፋት በጁባ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል በአየር ጭነት ወደ አረብ ኤምሬትስ (ዱባይ) እና ዓለም አቀፍ ማጣሪያዎች እንዲላክ ያስችለዋል።
ይህ የምስክርነት ቃል በሱዳን የወርቅ አቅርቦት ሰንሰለት ላይ የታየውን መዋቅራዊ ለውጥ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይህንን የተወሳሰበ ሂደት "የእሴት ሰንሰለት ዳግም ምህንድስና እና የመነሻ ሀገር ማጭበርበር" ሲሉ ይጠሩታል። በዚህም ህገ-ወጥ አውታረ መረቦች ጎረቤት ሀገራትን (በተለይም ደቡብ ሱዳንን) እንደ መሸጋገሪያ በመጠቀም ዓለም አቀፍ ማዕቀቦችን በማለፍ የማዕድኑን ህጋዊ ማንነት ይቀይራሉ።
በ2017 የጀበል አሜር የወርቅ ማዕድን ማውጫን በኃይል የተቆጣጠሩት የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይል (RSF) አዛዥ ሞሃመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ)፣ ከማዕድኑ የሚገኘውን ትርፍ ከRSF ጋር ግንኙነት ላላቸው 50 ገደማ ኩባንያዎች እንዲገባ ማድረጋቸው ይታወሳል። በ2019 ሄሜቲ የሱዳንን ኢኮኖሚ ለማረጋጋት በሚል ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ድጋፍ አቅርበው ነበር።
መረጃውን ያጋለጡት ነጋዴ አክለውም፣ ባለፈው መጋቢት ወር ብቻ ከጁባ ወደ አረብ ኤምሬትስ በተደረጉ ሁለት በረራዎች 115 ኪሎ ግራም የሚመዝን የሱዳን የኮንትሮባንድ ወርቅ መጓጓዙን ተናግረዋል። ይሁን እንጂ ሱዳን ትሪቢዩን ይህንን የተወሰነ መረጃ በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ እንዳልቻለ በዘገባው አስፍሯል።
ነጋዴው ለሱዳን ትሪቢዩን እንደገለጹት፣ በየብስ ድንበር በኩል የሚደረገው የሱዳን ወርቅ ዝውውር አሁንም አልቆመም። ከዳርፉር እና ከደቡብ ኮርዶፋን ማዕድን ማውጫዎች የሚነሱ የጭነት መኪናዎች እና ሞተር ብስክሌቶች ቁጥጥር በማይደረግባቸው የድንበር መስመሮች በኩል ወርቁን ያለማቋረጥ ያጓጉዛሉ።
ወርቁ ወደ ጁባ የሚገባው ባልተጣራ እና ጥሬ በሆነ መልኩ መሆኑን ያስረዱት ነጋዴው፤ ደላሎች እና የሀገር ውስጥ ነጋዴዎች ማዕድኑን በሱዳን ማዕከላዊ ባንክ ከሚሰጠው መደበኛ የምንዛሬ ተመን እጅግ በተሻለ ዋጋ በአሜሪካ ዶላር በጥሬ ገንዘብ እንደሚገዙት አብራርተዋል።
ይህንን ወርቅ ህጋዊ ለማድረግ፣ ነጋዴዎቹ ማዕድኑን ዳግም በማቅለጥ እና በመቀላቀል አዲስ ቅርጽ ይሰጡታል። በመቀጠልም ወርቁ በደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያ ወይም ምዕራብ ባህር ኤል ጋዛል ግዛቶች እንደተመረተ የሚያስመስል የሀሰት ሰነድ ይዘጋጅለታል። ይህ የሀሰት ሰነድ ወርቁ ያለምንም ህጋዊ እንቅፋት በጁባ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል በአየር ጭነት ወደ አረብ ኤምሬትስ (ዱባይ) እና ዓለም አቀፍ ማጣሪያዎች እንዲላክ ያስችለዋል።
ይህ የምስክርነት ቃል በሱዳን የወርቅ አቅርቦት ሰንሰለት ላይ የታየውን መዋቅራዊ ለውጥ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይህንን የተወሳሰበ ሂደት "የእሴት ሰንሰለት ዳግም ምህንድስና እና የመነሻ ሀገር ማጭበርበር" ሲሉ ይጠሩታል። በዚህም ህገ-ወጥ አውታረ መረቦች ጎረቤት ሀገራትን (በተለይም ደቡብ ሱዳንን) እንደ መሸጋገሪያ በመጠቀም ዓለም አቀፍ ማዕቀቦችን በማለፍ የማዕድኑን ህጋዊ ማንነት ይቀይራሉ።
በ2017 የጀበል አሜር የወርቅ ማዕድን ማውጫን በኃይል የተቆጣጠሩት የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይል (RSF) አዛዥ ሞሃመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ)፣ ከማዕድኑ የሚገኘውን ትርፍ ከRSF ጋር ግንኙነት ላላቸው 50 ገደማ ኩባንያዎች እንዲገባ ማድረጋቸው ይታወሳል። በ2019 ሄሜቲ የሱዳንን ኢኮኖሚ ለማረጋጋት በሚል ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ድጋፍ አቅርበው ነበር።
መረጃውን ያጋለጡት ነጋዴ አክለውም፣ ባለፈው መጋቢት ወር ብቻ ከጁባ ወደ አረብ ኤምሬትስ በተደረጉ ሁለት በረራዎች 115 ኪሎ ግራም የሚመዝን የሱዳን የኮንትሮባንድ ወርቅ መጓጓዙን ተናግረዋል። ይሁን እንጂ ሱዳን ትሪቢዩን ይህንን የተወሰነ መረጃ በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ እንዳልቻለ በዘገባው አስፍሯል።
Sponsored by
Surafel
21 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዛሬ 15 ዓመት ገደማ በፈረንጆቹ ግንቦት 2011፣ በአሜሪካ ዋሽንግተን ግዛት የምትገኝ አንዲት ትንሽ ከተማ በአሰቃቂ ድርጊት ተናወጠች። ከትውልድ አገሯ ኢትዮጵያ የተሻለ ሕይወትና ፍቅር ፍለጋ የመጣችው የ13 ዓመቷ ታዳጊ ሃና አለሙ (Hana Williams)፣ ማንም ሰብዓዊ ፍጡር ሊሸከመው የማይችለውን ስቃይና ፍጹም ጭካኔ በአሳዳጊ ወላጆቿ እጅ ካስተናገደች በኋላ፣ በአንድ ቀዝቃዛ ምሽት በጭቃ ላይ ወድቃ ሕይወቷ አለፈ።
ሃና ከዚህ ዓለም ብትለይም፣ የእሷን አሳዛኝ ታሪክ የሚሰማ ማንኛውም ሰው ልብ ዛሬም ድረስ በሐዘንና በቁጭት ይደማል። ዛሬም ድረስ ብዙዎችን ምሽት ላይ እንቅልፍ የሚነሳው ይህ ታሪክ፣ በቅርቡ በአዲስ አሁናዊ ዜና ወደ አደባባይ መጥቷል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የወጣው የመጨረሻውና አሁናዊው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ያቺን ንጽሕት ሕፃን በረሃብና በብርድ አሰቃይተው የገደሏት ጨካኞቹ አሳዳጊ ወላጆቿ — ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ—ከተፈረደባቸው የረጅም ዓመታት እስራት ለማምለጥ የሙጥኝ ያሉበት የመጨረሻው የይግባኝ ተስፋቸው ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል።
ፍርድ ቤቱ በቅርቡ በሰጠው ውሳኔ፣ ወንጀለኞቹ "በፍርድ ሂደቱ ላይ ስህተት ተፈጽሟል፣ በድጋሚ ይታይልን" በማለት ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ አድርጎታል። የዋሽንግተን ግዛት ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ባወጣው ባለ ብዙ ገጽ ዝርዝር ውሳኔ፣ የተሰጣቸው የ37 እና የ28 ዓመታት የእስራት ፍርድ ፍጹም ፍትሐዊ መሆኑንና በአንዲት አቅመ-ቢስ ሕፃን ላይ የፈጸሙት ግፍ ይቅር የማይባል መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል። ይህም ማለት ሁለቱም ጨካኝ ወላጆች ዕድሜያቸውን በሙሉ በጠበቀ ጥበቃ ሥር ባሉ የሴቶችና የወንዶች ማረሚያ ቤቶች ውስጥ አሳልፈው ይጨርሳሉ።
ምንም እንኳ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ወንጀለኞቹ ከእስር ቤት አምልጠው በነፃነት አየር እንዳይተነፍሱ ቢያደርግም፣ በጉዲፈቻ ስም ተሰርቆ የጠፋውን የሃናን የልጅነት ጊዜና የተቀጠፈውን ውድ ሕይወቷን መመለስ አይችልም። ዛሬም ድረስ በአሜሪካና በኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ውስጥ ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ያለፈው የሃና ታሪክ፣ የሕፃናትን መብት ለማስከበርና መሰል ግፎችን ለመከላከል የሚደረገውን ትግል በሐዘን ማስታወሻነት እየመራ ይገኛል።
ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ምድራዊ ፍቅር የተነፈገችው ሃና አለሙ፣ ዛሬ ካለችበት ዓለም ሆና ወንጀለኞቿ ከእስር ቤት የብረት ዘንጎች በስተጀርባ ሆነው ዋጋቸውን ሲከፍሉ እያየች ይሆን? ብዙዎች አሁንም የሚመኙት አንድ ነገር ብቻ ነው — ይህች ንጽሕት ነፍስ በምድር ላይ ያጣችውን ሰላምና እቅፍ በሰማይ አግኝታ ለዘላለም እንድታርፍ። ክሪሚናል ማተር የተሰኘው የሰብ አዊ መብት ተሟጋች ዛሬ ባወጣው ጽሑፍ "የ13 ዓመቷ የሃና ግሬስ-ሮዝ ዊሊያምስ ታሪክ እውነቱን ለመናገር ሌሊት እንቅልፍ የሚነሳኝ እና ዕረፍት የሚያሳጣኝ ታሪክ ነው። የተሻለ ሕይወት ታገኛለች በሚል ተስፋ ከኢትዮጵያ በጉዲፈቻ ወደ አሜሪካዋ ዋሽንግተን ግዛት ብትወሰድም፣ የገጠማት ግን ሊታሰብ የማይችል ዘግናኝ ጭካኔ ነበር። አሳዳጊ ወላጆቿ የሆኑት ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ባደረሱባት በደል እና እንግልት፣ እ.ኤ.አ. በ2011 በከፍተኛ ቅዝቃዜ (Hypothermia) ምክንያት ለሞት እንድትዳረግ በማድረጋቸው ጥፋተኛ ተብለው ተፈርዶባቸዋል።
ሊጠብቋት እና ሊንከባከቧት ኃላፊነት በወሰዱ ሰዎች፣ እንዲህ ባለች ምስኪን ልጅ ላይ እንዴት ይህን ያህል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ሊፈጸም እንደቻለ ለማሰብ እና ለመቀበል ይከብደኛል። በዚህች ምድር ላይ የተነፈገችውን ሰላም በመጨረሻው ዓለም እንዳገኘችው ተስፋ አደርጋለሁ።" ብሏል።
ሃና ከዚህ ዓለም ብትለይም፣ የእሷን አሳዛኝ ታሪክ የሚሰማ ማንኛውም ሰው ልብ ዛሬም ድረስ በሐዘንና በቁጭት ይደማል። ዛሬም ድረስ ብዙዎችን ምሽት ላይ እንቅልፍ የሚነሳው ይህ ታሪክ፣ በቅርቡ በአዲስ አሁናዊ ዜና ወደ አደባባይ መጥቷል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የወጣው የመጨረሻውና አሁናዊው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ያቺን ንጽሕት ሕፃን በረሃብና በብርድ አሰቃይተው የገደሏት ጨካኞቹ አሳዳጊ ወላጆቿ — ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ—ከተፈረደባቸው የረጅም ዓመታት እስራት ለማምለጥ የሙጥኝ ያሉበት የመጨረሻው የይግባኝ ተስፋቸው ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል።
ፍርድ ቤቱ በቅርቡ በሰጠው ውሳኔ፣ ወንጀለኞቹ "በፍርድ ሂደቱ ላይ ስህተት ተፈጽሟል፣ በድጋሚ ይታይልን" በማለት ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ አድርጎታል። የዋሽንግተን ግዛት ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ባወጣው ባለ ብዙ ገጽ ዝርዝር ውሳኔ፣ የተሰጣቸው የ37 እና የ28 ዓመታት የእስራት ፍርድ ፍጹም ፍትሐዊ መሆኑንና በአንዲት አቅመ-ቢስ ሕፃን ላይ የፈጸሙት ግፍ ይቅር የማይባል መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል። ይህም ማለት ሁለቱም ጨካኝ ወላጆች ዕድሜያቸውን በሙሉ በጠበቀ ጥበቃ ሥር ባሉ የሴቶችና የወንዶች ማረሚያ ቤቶች ውስጥ አሳልፈው ይጨርሳሉ።
ምንም እንኳ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ወንጀለኞቹ ከእስር ቤት አምልጠው በነፃነት አየር እንዳይተነፍሱ ቢያደርግም፣ በጉዲፈቻ ስም ተሰርቆ የጠፋውን የሃናን የልጅነት ጊዜና የተቀጠፈውን ውድ ሕይወቷን መመለስ አይችልም። ዛሬም ድረስ በአሜሪካና በኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ውስጥ ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ያለፈው የሃና ታሪክ፣ የሕፃናትን መብት ለማስከበርና መሰል ግፎችን ለመከላከል የሚደረገውን ትግል በሐዘን ማስታወሻነት እየመራ ይገኛል።
ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ምድራዊ ፍቅር የተነፈገችው ሃና አለሙ፣ ዛሬ ካለችበት ዓለም ሆና ወንጀለኞቿ ከእስር ቤት የብረት ዘንጎች በስተጀርባ ሆነው ዋጋቸውን ሲከፍሉ እያየች ይሆን? ብዙዎች አሁንም የሚመኙት አንድ ነገር ብቻ ነው — ይህች ንጽሕት ነፍስ በምድር ላይ ያጣችውን ሰላምና እቅፍ በሰማይ አግኝታ ለዘላለም እንድታርፍ። ክሪሚናል ማተር የተሰኘው የሰብ አዊ መብት ተሟጋች ዛሬ ባወጣው ጽሑፍ "የ13 ዓመቷ የሃና ግሬስ-ሮዝ ዊሊያምስ ታሪክ እውነቱን ለመናገር ሌሊት እንቅልፍ የሚነሳኝ እና ዕረፍት የሚያሳጣኝ ታሪክ ነው። የተሻለ ሕይወት ታገኛለች በሚል ተስፋ ከኢትዮጵያ በጉዲፈቻ ወደ አሜሪካዋ ዋሽንግተን ግዛት ብትወሰድም፣ የገጠማት ግን ሊታሰብ የማይችል ዘግናኝ ጭካኔ ነበር። አሳዳጊ ወላጆቿ የሆኑት ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ባደረሱባት በደል እና እንግልት፣ እ.ኤ.አ. በ2011 በከፍተኛ ቅዝቃዜ (Hypothermia) ምክንያት ለሞት እንድትዳረግ በማድረጋቸው ጥፋተኛ ተብለው ተፈርዶባቸዋል።
ሊጠብቋት እና ሊንከባከቧት ኃላፊነት በወሰዱ ሰዎች፣ እንዲህ ባለች ምስኪን ልጅ ላይ እንዴት ይህን ያህል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ሊፈጸም እንደቻለ ለማሰብ እና ለመቀበል ይከብደኛል። በዚህች ምድር ላይ የተነፈገችውን ሰላም በመጨረሻው ዓለም እንዳገኘችው ተስፋ አደርጋለሁ።" ብሏል።
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የሀገሪቱን የትውልድ ዜግነት መብት ለመገደብ ያለመ አዲስ ነገር ግን ጠበብ ያለ ማዕቀፍ ያላቸውን ሁለት አስፈጻሚ ትዕዛዞች ሐሙስ ዕለት ፈርመዋል። ይህ አዲስ እርምጃ፣ ፕሬዝዳንቱ ቀደም ሲል ያወጡት ተመሳሳይ ትዕዛዝ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ውድቅ መደረጉን ተከትሎ፣ የአሜሪካን ህገ-መንግስት ድንጋጌ ዳግም ለመሞገት የተደረገ ሙከራ ነው።
በትራምፕ የሪፐብሊካን አስተዳደር የጸረ-ስደተኞች ፖሊሲ ውስጥ የትውልድ ዜግነትን መገደብ ቀዳሚው አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል። በተለይም ነፍሰጡር የውጭ ዜጎች ልጆቻቸውን በአሜሪካ ምድር በመውለድ ዜግነት ለማግኘት የሚያደርጉትን ጉዞ ወይም ዋይት ሀውስ "የወሊድ ቱሪዝም" በማለት የሚጠራውን አሰራር ዋነኛ ኢላማው አድርጓል።
ባለፈው ሰኔ 30 ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የትራምፕን የመጀመሪያ ትዕዛዝ "ከህገ-መንግስቱ ጋር የሚጻረር ነው" በማለት ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ፣ ፕሬዝዳንቱ ኮንግረሱ ህግ እንዲያወጣ ጥሪ አቅርበው ነበር። ሆኖም ሐሙስ ዕለት ፖሊሲን የሚያወጡ ነገር ግን የህግ አስገዳጅነት የሌላቸውን አስፈጻሚ ትዕዛዞችን መፈረምን መርጠዋል። የትራምፕ አስተዳደር እንደሚለው፣ እነዚህ አዳዲስ መመሪያዎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካስቀመጣቸው ገደቦች ውጪ የሆኑ ናቸው። ይህም የወሊድ ቱሪዝምን ጨምሮ የትውልድ ዜግነት መብት የማይገባቸውን ሰዎች ምድብ ለማስፋት ያስችለዋል ብሏል። በትራምፕ ትዕዛዝ መሰረት፣ እነዚህ ምድቦች "ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካወጀው የትውልድ ዜግነት ደንብ ስር አይወድቁም።"
በዋይት ሀውስ የፕሬዝዳንቱ ረዳት የሆኑት ስቴፈን ሚለር በትዕዛዙ የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ፣ "ይህ ትዕዛዝ ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ የወሊድ ቱሪዝም ልምምድ ሙሉ በሙሉ ታግዷል። ይህ ማለት ማንም ሰው ለዚህ አታላይ ዓላማ ቪዛ ማግኘት አይፈቀድለትም" ሲሉ ተናግረዋል።
አዳዲሶቹ ትዕዛዞች ከወሊድ ቱሪዝም ባሻገር፣ በአሜሪካ ለሚገኙ የውጭ መንግስታት ሰራተኞች እና እንደ 'ጠላት' (Alien Enemies) ለተፈረጁ የውጭ ዜጎች የሚወለዱ ልጆችን የዜግነት መብት ይገድባሉ። ከዚህም በተጨማሪ ኮንግረሱ አዲስ ህግ ካጸደቀ፣ በአሜሪካ ግዛቶች (Territories) ውስጥ የሚወለዱ ሰዎች አውቶማቲክ ዜግነት እንዳያገኙ ሊያደርግ እንደሚችል ተጠቁሟል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የተሰጠውን የ6 ለ 3 የድምጽ ውሳኔ አጥብቀው ተችተዋል። "በትውልድ ዜግነት ላይ ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ አጋጥሞናል... በጣም ተቀራራቢ ድምጽ ቢሆንም፣ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ ነው" ብለዋል። አክለውም፣ "ሰዎች ዜግነትን ማግኛ መንገድ አድርገው ንግድ እየገነቡበት ነው። አሰራሩ እንደዚህ መሆን አልነበረበትም፤ ይህ አሳፋሪ ነው። ዜግነትን በገንዘብ እየገዙ ነው፣ እኛ ደግሞ ይህ እንዲሆን አንፈቅድም" ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
የአሜሪካ ህገ-መንግስት 14ኛው ማሻሻያ ከውጭ ዲፕሎማቶች ወይም ወራሪ የጠላት ኃይል አባላት ልጆች ውጪ፣ በአሜሪካ ምድር ለሚወለዱ ህጻናት በሙሉ የዜግነት መብትን እንደሚያረጋግጥ በህግ ሲተረጎም ቆይቷል። ትራምፕ ግን ይህ ህግ የወጣው ከእርስ በርስ ጦርነቱ በኋላ ለባሮች ልጆች ዜግነት ለመስጠት መሆኑን በመጥቀስ፣ የአሁኑ አሰራር የህጉን መንፈስ የሳተ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዋና ዳኛ ጆን ሮበርትስ በውሳኔያቸው ላይ፣ የ14ኛው ማሻሻያ አርቃቂዎች ይህንን ቃል ኪዳን በሀገሪቱ ውስጥ ለተወለደ እያንዳንዱ ነጻ ሰው እንዳሰፉት አስታውሰው፣ "ዜግነት በዚያን ጊዜም ሆነ አሁን መብቶችን የማግኘት እና በፖለቲካዊ ማህበረሰባችን ውስጥ በነጻነት የመሳተፍ መብት ነው። ይህንን ቃል ኪዳን ዛሬም እንጠብቃለን" በማለት የህገ-መንግስቱን ሰፊ ትርጉም አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በ2020 የትራምፕ የመጀመሪያ የስልጣን ዘመን አዲስ የተወለደ ልጅ የአሜሪካ ዜግነት እንዲያገኝ በሚል ዓላማ የቱሪስት እና የንግድ ቪዛዎችን መጠቀምን የሚከለክል የፌዴራል ደንብ ወጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ የወሊድ ቱሪዝምን ሙሉ በሙሉ የሚከለክል ግልጽ ህግ በአሜሪካ የለም። ይህን መሰል ማጭበርበር ላይ የሚሳተፉ ሰዎች በህግ ሊጠየቁ ቢችሉም፣ የትራምፕ አዳዲስ አስፈጻሚ ትዕዛዞች በፍርድ ቤቶች በኩል ጠንካራ የህግ ተግዳሮት እንደሚገጥማቸው በሰፊው ይጠበቃል።
በትራምፕ የሪፐብሊካን አስተዳደር የጸረ-ስደተኞች ፖሊሲ ውስጥ የትውልድ ዜግነትን መገደብ ቀዳሚው አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል። በተለይም ነፍሰጡር የውጭ ዜጎች ልጆቻቸውን በአሜሪካ ምድር በመውለድ ዜግነት ለማግኘት የሚያደርጉትን ጉዞ ወይም ዋይት ሀውስ "የወሊድ ቱሪዝም" በማለት የሚጠራውን አሰራር ዋነኛ ኢላማው አድርጓል።
ባለፈው ሰኔ 30 ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የትራምፕን የመጀመሪያ ትዕዛዝ "ከህገ-መንግስቱ ጋር የሚጻረር ነው" በማለት ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ፣ ፕሬዝዳንቱ ኮንግረሱ ህግ እንዲያወጣ ጥሪ አቅርበው ነበር። ሆኖም ሐሙስ ዕለት ፖሊሲን የሚያወጡ ነገር ግን የህግ አስገዳጅነት የሌላቸውን አስፈጻሚ ትዕዛዞችን መፈረምን መርጠዋል። የትራምፕ አስተዳደር እንደሚለው፣ እነዚህ አዳዲስ መመሪያዎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካስቀመጣቸው ገደቦች ውጪ የሆኑ ናቸው። ይህም የወሊድ ቱሪዝምን ጨምሮ የትውልድ ዜግነት መብት የማይገባቸውን ሰዎች ምድብ ለማስፋት ያስችለዋል ብሏል። በትራምፕ ትዕዛዝ መሰረት፣ እነዚህ ምድቦች "ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካወጀው የትውልድ ዜግነት ደንብ ስር አይወድቁም።"
በዋይት ሀውስ የፕሬዝዳንቱ ረዳት የሆኑት ስቴፈን ሚለር በትዕዛዙ የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ፣ "ይህ ትዕዛዝ ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ የወሊድ ቱሪዝም ልምምድ ሙሉ በሙሉ ታግዷል። ይህ ማለት ማንም ሰው ለዚህ አታላይ ዓላማ ቪዛ ማግኘት አይፈቀድለትም" ሲሉ ተናግረዋል።
አዳዲሶቹ ትዕዛዞች ከወሊድ ቱሪዝም ባሻገር፣ በአሜሪካ ለሚገኙ የውጭ መንግስታት ሰራተኞች እና እንደ 'ጠላት' (Alien Enemies) ለተፈረጁ የውጭ ዜጎች የሚወለዱ ልጆችን የዜግነት መብት ይገድባሉ። ከዚህም በተጨማሪ ኮንግረሱ አዲስ ህግ ካጸደቀ፣ በአሜሪካ ግዛቶች (Territories) ውስጥ የሚወለዱ ሰዎች አውቶማቲክ ዜግነት እንዳያገኙ ሊያደርግ እንደሚችል ተጠቁሟል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የተሰጠውን የ6 ለ 3 የድምጽ ውሳኔ አጥብቀው ተችተዋል። "በትውልድ ዜግነት ላይ ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ አጋጥሞናል... በጣም ተቀራራቢ ድምጽ ቢሆንም፣ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ ነው" ብለዋል። አክለውም፣ "ሰዎች ዜግነትን ማግኛ መንገድ አድርገው ንግድ እየገነቡበት ነው። አሰራሩ እንደዚህ መሆን አልነበረበትም፤ ይህ አሳፋሪ ነው። ዜግነትን በገንዘብ እየገዙ ነው፣ እኛ ደግሞ ይህ እንዲሆን አንፈቅድም" ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
የአሜሪካ ህገ-መንግስት 14ኛው ማሻሻያ ከውጭ ዲፕሎማቶች ወይም ወራሪ የጠላት ኃይል አባላት ልጆች ውጪ፣ በአሜሪካ ምድር ለሚወለዱ ህጻናት በሙሉ የዜግነት መብትን እንደሚያረጋግጥ በህግ ሲተረጎም ቆይቷል። ትራምፕ ግን ይህ ህግ የወጣው ከእርስ በርስ ጦርነቱ በኋላ ለባሮች ልጆች ዜግነት ለመስጠት መሆኑን በመጥቀስ፣ የአሁኑ አሰራር የህጉን መንፈስ የሳተ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዋና ዳኛ ጆን ሮበርትስ በውሳኔያቸው ላይ፣ የ14ኛው ማሻሻያ አርቃቂዎች ይህንን ቃል ኪዳን በሀገሪቱ ውስጥ ለተወለደ እያንዳንዱ ነጻ ሰው እንዳሰፉት አስታውሰው፣ "ዜግነት በዚያን ጊዜም ሆነ አሁን መብቶችን የማግኘት እና በፖለቲካዊ ማህበረሰባችን ውስጥ በነጻነት የመሳተፍ መብት ነው። ይህንን ቃል ኪዳን ዛሬም እንጠብቃለን" በማለት የህገ-መንግስቱን ሰፊ ትርጉም አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በ2020 የትራምፕ የመጀመሪያ የስልጣን ዘመን አዲስ የተወለደ ልጅ የአሜሪካ ዜግነት እንዲያገኝ በሚል ዓላማ የቱሪስት እና የንግድ ቪዛዎችን መጠቀምን የሚከለክል የፌዴራል ደንብ ወጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ የወሊድ ቱሪዝምን ሙሉ በሙሉ የሚከለክል ግልጽ ህግ በአሜሪካ የለም። ይህን መሰል ማጭበርበር ላይ የሚሳተፉ ሰዎች በህግ ሊጠየቁ ቢችሉም፣ የትራምፕ አዳዲስ አስፈጻሚ ትዕዛዞች በፍርድ ቤቶች በኩል ጠንካራ የህግ ተግዳሮት እንደሚገጥማቸው በሰፊው ይጠበቃል።
1 day ago
ቋሚ ሲኖዶስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጉዳይ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ማስረጃ እንዲቀርብ ጥሪ አቀረበ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ምርመራ ለማካሄድ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሕዝብ መረጃና ማስረጃ እንዲያቀርብ ጥሪ አቀረበ።
ኮሚቴው እንደገለጸው፣ በሀገረ ስብከቱና በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃ የተከሰቱ ሕገ-ወጥ ቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር፣ ሕገ-ወጥ የፋይናንስ አሠራሮችና የገንዘብ ዝውውሮች፣ ሕገ-ወጥ የቦታና የቤት ኪራይ ውሎች፣ ተደራራቢ ሥራዎችና መሰል ጉዳዮችን በዝርዝር በማጣራት ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ሪፖርት ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀርባል።
በዚህ ሂደት የማጣራት ሥራው በማስረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ተቋም ተኮርና ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጣ እንዲሆን መረጃዎችን መሰብሰብ፣ መተንተን እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት ዋና የሥራ አቅጣጫው መሆኑን ገልጿል።
ኮሚቴው በተለይም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተጠቀሱት እና ተመሳሳይ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምክንያት ተጎጂ የሆኑ እና በቂ ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች፣ በሥራ ሰዓት የማስረጃቸውን ኮፒ በመያዝ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በተከፈተው የመረጃ መሰብሰቢያ ቢሮ በመቅረብ፣ በጽሑፍ፣ በድምፅ ወይም በምስል መረጃ እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
በተጨማሪም መረጃ የሚያቀርቡ ሰዎች በዚህ ምክንያት ማንኛውም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው በቋሚ ሲኖዶስ ዋስትና መሰጠቱን አስታውቆ፣ ማንኛውም አካል ያለውን መረጃና ማስረጃ በነጻነት እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርቧል።
መግለጫው በአጣሪ ኮሚቴው በሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ምርመራ ለማካሄድ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሕዝብ መረጃና ማስረጃ እንዲያቀርብ ጥሪ አቀረበ።
ኮሚቴው እንደገለጸው፣ በሀገረ ስብከቱና በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃ የተከሰቱ ሕገ-ወጥ ቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር፣ ሕገ-ወጥ የፋይናንስ አሠራሮችና የገንዘብ ዝውውሮች፣ ሕገ-ወጥ የቦታና የቤት ኪራይ ውሎች፣ ተደራራቢ ሥራዎችና መሰል ጉዳዮችን በዝርዝር በማጣራት ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ሪፖርት ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀርባል።
በዚህ ሂደት የማጣራት ሥራው በማስረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ተቋም ተኮርና ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጣ እንዲሆን መረጃዎችን መሰብሰብ፣ መተንተን እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት ዋና የሥራ አቅጣጫው መሆኑን ገልጿል።
ኮሚቴው በተለይም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተጠቀሱት እና ተመሳሳይ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምክንያት ተጎጂ የሆኑ እና በቂ ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች፣ በሥራ ሰዓት የማስረጃቸውን ኮፒ በመያዝ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በተከፈተው የመረጃ መሰብሰቢያ ቢሮ በመቅረብ፣ በጽሑፍ፣ በድምፅ ወይም በምስል መረጃ እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
በተጨማሪም መረጃ የሚያቀርቡ ሰዎች በዚህ ምክንያት ማንኛውም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው በቋሚ ሲኖዶስ ዋስትና መሰጠቱን አስታውቆ፣ ማንኛውም አካል ያለውን መረጃና ማስረጃ በነጻነት እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርቧል።
መግለጫው በአጣሪ ኮሚቴው በሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዩኤን ዋች ‹‹የኤርትራ በሰብአዊ ምክር ቤት መመረጥ አስከፊ ቀልድ ነው›› አለ፡፡ መቀመጫውን በጄኔቭ ያደረገውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን አሰራር የሚከታተለው ‹ዩኤን ዋች›› ዛሬ ባወጣው መግለጫ ኤርትራ በተመድ ሰብአዊ መብት ምክር ቤት ውስጥ የማህበራዊ መድረክ ሊቀመንበር ሆና መመረጧን አጥብቆ እንደሚቃወም ገለፀ፡፡ ውሳኔውንም ‹‹በአለም ላይ ካሉ ጨቋኝ መንግስታት አንዱን የሰብአዊ መብትን ለማሳደግ በሚጥር አካል ውስጥ ሀላፊነት መስጠር አስከፊ ቀልድ ነው›› ብሎታል፡፡ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ሂሌል ኑየር ሲናገሩ ‹‹ኤርትራ በወታደራዊ ሀይል የምትተዳደር የአንድ ፓርቲ አምባገነን አገር ስትሆን በፍሪደም ሀውስ ከ100 ነጥብ ውስጥ 3 ያገኘች ናት፡፡ ይህ ማለት የሰብአዊ መብት ሪከርዷ እጅግ የከፋ ነው›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹የኤርትራ መንግስት እ.ኤ.አ ከ1993 አገሪቱ ነፃ ከወጣችበት ጊዜ አንስቶ ምንም አይነት ብሄራዊ ምርጫ አላካሄደም፡፡
እንደባርነት የሚቆጠር የግዳጅ ወታደራዊ አገልግሎትን ያስፈፅማል፡፡ የሚተቹትንና ጋዜጠኞችን ለአስርት አመታት ያለምንም ክስ ያስራል፡፡ የፖለቲካ እስረኞችንና የሀይማኖት አባቶችን ያሰቃያል፡፡ ይህ የአፍሪካ ሰሜን ኮሪያ ተብሎ የሚጠራው መንግስት ከሰብአዊ መብቶች ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፡፡ የኤርትራን መንግስት እዚህ ወንበር ላይ ማስቀመጥ እጅግ መጥፎ ቀልድ ነው›› በማለት አስረድተዋል፡፡ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት የራሱን ደንቦች ማክበር እያቃተው ለመሆኑ ይህ ትልቅ ማሳያ መሆኑን ጠቀሱት ዳይሬክተሩ አስከትለውም ‹‹በሰብአዊ መብት ምክር ቤቱ ውስጥ የተወከሉትን ሁለንተናዊ መብቶች እንደሚከላከሉ የሚናገሩ መንግስታት በተለይም እንደፈረንሳይ፣ እንግሊዝ፣ ኔዘርላንድስ፣ ጣሊያን፣ ስፔን፣ ብራዚልና ስዊዘርላንድ የመሳሰሉ የምክር ቤቱ አባላት ይህንን የኤርትራን ሹመት አውግዘው መግለጫ እንዲያወጡ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
ይህ አፀያፊ ሹመት እንዲቀለበስ በማድረግም የኤርትራ መንግስት በሰብአዊ መብት ረገድ ምንም እውቅና እንዳይሰጠው ማድረግ ያስፈልጋል›› ብለዋል፡፡ በማጠቃለያቸውም ‹‹ይህ ሹመት አምባገነንነትን የሚሸልምና የሰብአዊ መብት ምክር ቤቱ የተነሳለትን አላማ የሚክድ ነው፡፡ አለም ይህንን እየተመለከተ ነው፡፡ ዝም የሚሉ ዲሞክራሲዎች ለዚህ አሳፋሪ ውሳኔ ሀላፊነቱን ይወስዳሉ›› በማለት መግለፃቸውን ከመግለጫው ላይ ተመልክተናል፡፡
እንደባርነት የሚቆጠር የግዳጅ ወታደራዊ አገልግሎትን ያስፈፅማል፡፡ የሚተቹትንና ጋዜጠኞችን ለአስርት አመታት ያለምንም ክስ ያስራል፡፡ የፖለቲካ እስረኞችንና የሀይማኖት አባቶችን ያሰቃያል፡፡ ይህ የአፍሪካ ሰሜን ኮሪያ ተብሎ የሚጠራው መንግስት ከሰብአዊ መብቶች ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፡፡ የኤርትራን መንግስት እዚህ ወንበር ላይ ማስቀመጥ እጅግ መጥፎ ቀልድ ነው›› በማለት አስረድተዋል፡፡ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት የራሱን ደንቦች ማክበር እያቃተው ለመሆኑ ይህ ትልቅ ማሳያ መሆኑን ጠቀሱት ዳይሬክተሩ አስከትለውም ‹‹በሰብአዊ መብት ምክር ቤቱ ውስጥ የተወከሉትን ሁለንተናዊ መብቶች እንደሚከላከሉ የሚናገሩ መንግስታት በተለይም እንደፈረንሳይ፣ እንግሊዝ፣ ኔዘርላንድስ፣ ጣሊያን፣ ስፔን፣ ብራዚልና ስዊዘርላንድ የመሳሰሉ የምክር ቤቱ አባላት ይህንን የኤርትራን ሹመት አውግዘው መግለጫ እንዲያወጡ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
ይህ አፀያፊ ሹመት እንዲቀለበስ በማድረግም የኤርትራ መንግስት በሰብአዊ መብት ረገድ ምንም እውቅና እንዳይሰጠው ማድረግ ያስፈልጋል›› ብለዋል፡፡ በማጠቃለያቸውም ‹‹ይህ ሹመት አምባገነንነትን የሚሸልምና የሰብአዊ መብት ምክር ቤቱ የተነሳለትን አላማ የሚክድ ነው፡፡ አለም ይህንን እየተመለከተ ነው፡፡ ዝም የሚሉ ዲሞክራሲዎች ለዚህ አሳፋሪ ውሳኔ ሀላፊነቱን ይወስዳሉ›› በማለት መግለፃቸውን ከመግለጫው ላይ ተመልክተናል፡፡
1 day ago
አልማ ለ2019 በጀት ዓመት ከ4.3 ቢሊዮን ብር በላይ የልማት ሀብት ለማሰባሰብ አቀደ
#ethiopia | የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በመገምገም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን ያስተዋወቀ ሲሆን፣ የዕቅዱን ስኬት ለማረጋገጥ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍን በሙሉ ማጠናቀቅ እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መላኩ ፈንታ አሳስበዋል።
በዋና መሥሪያ ቤቱ ለሁለት ቀናት በተካሄደው የምክክር መድረክ፣ ከ11 ዞኖች የተውጣጡ የማኔጅመንት አባላትና የወረዳ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈው በቀጣዩ ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተወያይተዋል።
ስትራቴጂክና ኢኖቬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበረ መኩሪያ እንደገለጹት፣ በ2019 በጀት ዓመት ከአባላት 4.3 ቢሊዮን ብር፣ ከዳያስፖራ ከ34 ሚሊዮን ዶላር በላይ እና ከአጋር ተቋማት 55 ሚሊዮን ዶላር የልማት ሀብት ለማሰባሰብ ታቅዷል።
በተያዘው ዕቅድ 2,051 የመማሪያ ክፍሎች፣ 38 የጤና ተቋማት፣ 8 የቴክኒክ ኮሌጅ ወርክሾፖች እና 2 ሸዶች እንዲገነቡ ታቅዷል። ይህን ግዙፍ ዕቅድ ለማሳካት የህዝብ ተሳትፎን ማሳደግ፣ ከአጋር አካላትና ከዳያስፖራው ጋር የተጠናከረ ትብብር መፍጠር ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል።
አቶ መላኩ ፈንታ በማጠቃለያ ንግግራቸው፣ በ2019 በጀት ዓመት የዲጂታል ሽግግርን ማፋጠን፣ የአፈጻጸም ጥራትን ማሻሻል፣ የተቋሙን ብራንድ ማጠናከርና ዘላቂ የፋይናንስ አቅም መፍጠር ዋና ትኩረቶች እንደሚሆኑ ገልጸዋል።
በመድረኩ መጨረሻ በ2018 በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የዞንና የወረዳ አልማ ጽሕፈት ቤቶች፣ እንዲሁም ለተመራጭ ሠራተኞች የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በመገምገም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን ያስተዋወቀ ሲሆን፣ የዕቅዱን ስኬት ለማረጋገጥ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍን በሙሉ ማጠናቀቅ እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መላኩ ፈንታ አሳስበዋል።
በዋና መሥሪያ ቤቱ ለሁለት ቀናት በተካሄደው የምክክር መድረክ፣ ከ11 ዞኖች የተውጣጡ የማኔጅመንት አባላትና የወረዳ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈው በቀጣዩ ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተወያይተዋል።
ስትራቴጂክና ኢኖቬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበረ መኩሪያ እንደገለጹት፣ በ2019 በጀት ዓመት ከአባላት 4.3 ቢሊዮን ብር፣ ከዳያስፖራ ከ34 ሚሊዮን ዶላር በላይ እና ከአጋር ተቋማት 55 ሚሊዮን ዶላር የልማት ሀብት ለማሰባሰብ ታቅዷል።
በተያዘው ዕቅድ 2,051 የመማሪያ ክፍሎች፣ 38 የጤና ተቋማት፣ 8 የቴክኒክ ኮሌጅ ወርክሾፖች እና 2 ሸዶች እንዲገነቡ ታቅዷል። ይህን ግዙፍ ዕቅድ ለማሳካት የህዝብ ተሳትፎን ማሳደግ፣ ከአጋር አካላትና ከዳያስፖራው ጋር የተጠናከረ ትብብር መፍጠር ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል።
አቶ መላኩ ፈንታ በማጠቃለያ ንግግራቸው፣ በ2019 በጀት ዓመት የዲጂታል ሽግግርን ማፋጠን፣ የአፈጻጸም ጥራትን ማሻሻል፣ የተቋሙን ብራንድ ማጠናከርና ዘላቂ የፋይናንስ አቅም መፍጠር ዋና ትኩረቶች እንደሚሆኑ ገልጸዋል።
በመድረኩ መጨረሻ በ2018 በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የዞንና የወረዳ አልማ ጽሕፈት ቤቶች፣ እንዲሁም ለተመራጭ ሠራተኞች የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
1 day ago
ሰሜን ኮሪያ ወደ ጃፓን ባሕር ባሊስቲክ ሚሳይል አስወነጨፈ
#ethiopia | ሰሜን ኮሪያ ዛሬ ከምሥራቅ ጠረፏ ከዎንሳን (Wonsan) አካባቢ ወደ ጃፓን ባሕር (በደቡብ ኮሪያ “ምሥራቅ ባሕር” ተብሎ የሚጠራው) አጭር ርቀት የሚጓዝ ተጠርጣሪ ባሊስቲክ ሚሳይል ማስወንጨፏን የደቡብ ኮሪያ ጦር እና የጃፓን ባሕር ዳርቻ ጥበቃ አስታውቀዋል።
በጃፓን ባለሥልጣናት መረጃ መሠረት ሚሳይሉ በጃፓን ግዛት ወይም በኢኮኖሚያዊ የባሕር ቀጠናዋ (EEZ) ውስጥ አላረፈም፤ እስካሁንም የደረሰ ጉዳት ወይም ሰው ጉዳት አልተዘገበም።
የደቡብ ኮሪያ፣ የአሜሪካ እና የጃፓን ወታደራዊ ኃይሎች የሚሳይሉን አይነትና የበረራ መረጃ በጋራ እየመረመሩ ነው።
ይህ የሚሳይል ሙከራ በአሜሪካና በደቡብ ኮሪያ የጋራ ወታደራዊ ልምምዶች ሊጀመሩ ጥቂት ቀናት ሲቀሩ የተፈጸመ ሲሆን፣ ፒዮንግያንግ እነዚህን ልምምዶች ለወረራ ዝግጅት አድርጋ እንደምትመለከታቸው ትገልጻለች።
ከቀናት በፊትም ሰሜን ኮሪያ በጃፓን የመከላከያ አቅም መስፋፋት ምክንያት “ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃዎች” ልትወስድ እንደምትችል አስጠንቅቃ ነበር።
የደቡብ ኮሪያ እና የጃፓን መንግሥታት የሚሳይሉን ሙከራ በማውገዝ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ምክር ቤት ውሳኔዎችን የሚጥስ ነው ብለዋል፤ በቀጣይ ተጨማሪ የሚሳይል ሙከራዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም በከፍተኛ ንቃት እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | ሰሜን ኮሪያ ዛሬ ከምሥራቅ ጠረፏ ከዎንሳን (Wonsan) አካባቢ ወደ ጃፓን ባሕር (በደቡብ ኮሪያ “ምሥራቅ ባሕር” ተብሎ የሚጠራው) አጭር ርቀት የሚጓዝ ተጠርጣሪ ባሊስቲክ ሚሳይል ማስወንጨፏን የደቡብ ኮሪያ ጦር እና የጃፓን ባሕር ዳርቻ ጥበቃ አስታውቀዋል።
በጃፓን ባለሥልጣናት መረጃ መሠረት ሚሳይሉ በጃፓን ግዛት ወይም በኢኮኖሚያዊ የባሕር ቀጠናዋ (EEZ) ውስጥ አላረፈም፤ እስካሁንም የደረሰ ጉዳት ወይም ሰው ጉዳት አልተዘገበም።
የደቡብ ኮሪያ፣ የአሜሪካ እና የጃፓን ወታደራዊ ኃይሎች የሚሳይሉን አይነትና የበረራ መረጃ በጋራ እየመረመሩ ነው።
ይህ የሚሳይል ሙከራ በአሜሪካና በደቡብ ኮሪያ የጋራ ወታደራዊ ልምምዶች ሊጀመሩ ጥቂት ቀናት ሲቀሩ የተፈጸመ ሲሆን፣ ፒዮንግያንግ እነዚህን ልምምዶች ለወረራ ዝግጅት አድርጋ እንደምትመለከታቸው ትገልጻለች።
ከቀናት በፊትም ሰሜን ኮሪያ በጃፓን የመከላከያ አቅም መስፋፋት ምክንያት “ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃዎች” ልትወስድ እንደምትችል አስጠንቅቃ ነበር።
የደቡብ ኮሪያ እና የጃፓን መንግሥታት የሚሳይሉን ሙከራ በማውገዝ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ምክር ቤት ውሳኔዎችን የሚጥስ ነው ብለዋል፤ በቀጣይ ተጨማሪ የሚሳይል ሙከራዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም በከፍተኛ ንቃት እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
Comments