2 days ago
በተቋማዊ ሪፎርሙ ሕዝባዊነቱን ያጠናከረው ሠራዊት
**************
የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገር ሉዓላዊነት፣ የሕዝብ ደኅንነት እና የጽናት ታላቅ ምሰሶ ነው።
ባለፉት ስምንት ዓመታት በሠራዊቱ ውስጥ የተተገበሩት ጥልቀት ያላቸው የሪፎርም እና የተቋማዊ መዋቅር ማሻሻያዎች ሠራዊቱን ወደ አዲስ የልህቀት ደረጃ ያሸጋገሩ ናቸው።
ይህ የሪፎርም ሂደት የሠራዊቱን ሕዝባዊነት የበለጠ ያጠናከረ፣ ሙያዊ ገለልተኝነቱን ያረጋገጠ እና መዋቅራዊ አደረጃጀቱን በዘመናዊ ወታደራዊ ሳይንስ መርሆዎች ላይ ያቆመ ነበር።
ተቋሙን ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት በማፅዳት እና አደረጃጀቱን በማዘመን የአየር ኃይል፣ የባሕር ኃይል እንዲሁም የሳይበር ደኅንነት ክፍሎች ዘመኑ የሚጠይቀውን አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የዝግጁነት ደረጃ እንዲላበሱ አስችሏቸዋል።
በተቋማዊ ሪፎርሙ ከተመዘገቡት ዋና ዋና ውጤቶች መካከል በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በሰው ኃይል ግንባታ ላይ የታየው የላቀ ዕድገት ይጠቀሳል።
ሠራዊታችን ዘመናዊ የክትትል ቴክኖሎጂዎችን፣ የሰው አልባ አየር (ድሮን) ሥርዓቶችን እና የተራቀቁ የመረጃ መረቦችን በመታጠቅ ተቋማዊ ቁመናውን አዳብሯል።
በየደረጃው ባሉ ወታደራዊ አካዳሚዎች የተሰጡት የላቁ የስልጠና መርሐ-ግብሮች የሠራዊቱን ሥነ-ልቦናዊና ቴክኒካዊ አቅም በማሳደግ፣ አደጋዎችን በሳይንሳዊ ስልት፣ አነስተኛ የሰው እና የቁሳቁስ ጉዳት በሚያስከትል መልኩ የመከላከልና የማክሸፍ ብቃቱን አጎልብተውለታል።
በሀገራችን ያጋጠሙ ውስብስብ የውስጥ ደኀንነት ፈተናዎችን በማረጋጋት ሂደት ሠራዊቱ ያሳየው አስተዋይነት እና ሕዝባዊ ወገንተኝነት ጎልቶ የወጣበት ነው።
የሕዝብን ሰላም እና ደኅንነት ለማስጠበቅ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች የትዕግሥት እና የሰላም መንገዶችን በማስቀደም፣ የሲቪሎችን ሕይወት ከጉዳት በመጠበቅ እና የሀገር ሀብት የሆኑ መሠረተ-ልማቶችን በጥንቃቄ በመጠበቅ ረገድ ውጤታማ ሥራ ሠርቷል።
ይህም ሠራዊቱ የኃይል አጠቃቀምን የመጨረሻ አማራጭ በማድረግ የሰላም እና የሕግ ሥርዓት ዋስትና መሆኑን ያስመሰከረበት ነው።
ከሀገር ውስጥ ተልዕኮ ባሻገር፣ ሠራዊታችን በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ለሚከናወኑ የሰላም ማስከበር ሥራዎች የጸና አለኝታ ሆኖ ዘልቋል።
በአፍሪካ ኅብረት እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተልዕኮዎች የሚያሳየው የላቀ ሙያዊ ሥነ-ምግባር፣ ለሕዝብ ያለው ቅርበት እና የተላበሰው ሕዝባዊነት የሀገራችንን በጎ ገፅታ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ አድርጎታል።
ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የተገነቡት ዘመናዊ አቅሞች እና ተቋማዊ ነፃነት፣ ሠራዊታችን ወደፊትም የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝብን አደራ በላቀ ብቃት ለመወጣት የሚያስችለውን አስተማማኝ መሠረት ጥለዋል።
በሀብተሚካኤል ክፍሉ
#ethiopiandefenseforce #endf #ethiopianarmy #heroesofethiopia #militarypower #ethiopiandiplomacy
**************
የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገር ሉዓላዊነት፣ የሕዝብ ደኅንነት እና የጽናት ታላቅ ምሰሶ ነው።
ባለፉት ስምንት ዓመታት በሠራዊቱ ውስጥ የተተገበሩት ጥልቀት ያላቸው የሪፎርም እና የተቋማዊ መዋቅር ማሻሻያዎች ሠራዊቱን ወደ አዲስ የልህቀት ደረጃ ያሸጋገሩ ናቸው።
ይህ የሪፎርም ሂደት የሠራዊቱን ሕዝባዊነት የበለጠ ያጠናከረ፣ ሙያዊ ገለልተኝነቱን ያረጋገጠ እና መዋቅራዊ አደረጃጀቱን በዘመናዊ ወታደራዊ ሳይንስ መርሆዎች ላይ ያቆመ ነበር።
ተቋሙን ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት በማፅዳት እና አደረጃጀቱን በማዘመን የአየር ኃይል፣ የባሕር ኃይል እንዲሁም የሳይበር ደኅንነት ክፍሎች ዘመኑ የሚጠይቀውን አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የዝግጁነት ደረጃ እንዲላበሱ አስችሏቸዋል።
በተቋማዊ ሪፎርሙ ከተመዘገቡት ዋና ዋና ውጤቶች መካከል በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በሰው ኃይል ግንባታ ላይ የታየው የላቀ ዕድገት ይጠቀሳል።
ሠራዊታችን ዘመናዊ የክትትል ቴክኖሎጂዎችን፣ የሰው አልባ አየር (ድሮን) ሥርዓቶችን እና የተራቀቁ የመረጃ መረቦችን በመታጠቅ ተቋማዊ ቁመናውን አዳብሯል።
በየደረጃው ባሉ ወታደራዊ አካዳሚዎች የተሰጡት የላቁ የስልጠና መርሐ-ግብሮች የሠራዊቱን ሥነ-ልቦናዊና ቴክኒካዊ አቅም በማሳደግ፣ አደጋዎችን በሳይንሳዊ ስልት፣ አነስተኛ የሰው እና የቁሳቁስ ጉዳት በሚያስከትል መልኩ የመከላከልና የማክሸፍ ብቃቱን አጎልብተውለታል።
በሀገራችን ያጋጠሙ ውስብስብ የውስጥ ደኀንነት ፈተናዎችን በማረጋጋት ሂደት ሠራዊቱ ያሳየው አስተዋይነት እና ሕዝባዊ ወገንተኝነት ጎልቶ የወጣበት ነው።
የሕዝብን ሰላም እና ደኅንነት ለማስጠበቅ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች የትዕግሥት እና የሰላም መንገዶችን በማስቀደም፣ የሲቪሎችን ሕይወት ከጉዳት በመጠበቅ እና የሀገር ሀብት የሆኑ መሠረተ-ልማቶችን በጥንቃቄ በመጠበቅ ረገድ ውጤታማ ሥራ ሠርቷል።
ይህም ሠራዊቱ የኃይል አጠቃቀምን የመጨረሻ አማራጭ በማድረግ የሰላም እና የሕግ ሥርዓት ዋስትና መሆኑን ያስመሰከረበት ነው።
ከሀገር ውስጥ ተልዕኮ ባሻገር፣ ሠራዊታችን በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ለሚከናወኑ የሰላም ማስከበር ሥራዎች የጸና አለኝታ ሆኖ ዘልቋል።
በአፍሪካ ኅብረት እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተልዕኮዎች የሚያሳየው የላቀ ሙያዊ ሥነ-ምግባር፣ ለሕዝብ ያለው ቅርበት እና የተላበሰው ሕዝባዊነት የሀገራችንን በጎ ገፅታ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ አድርጎታል።
ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የተገነቡት ዘመናዊ አቅሞች እና ተቋማዊ ነፃነት፣ ሠራዊታችን ወደፊትም የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝብን አደራ በላቀ ብቃት ለመወጣት የሚያስችለውን አስተማማኝ መሠረት ጥለዋል።
በሀብተሚካኤል ክፍሉ
#ethiopiandefenseforce #endf #ethiopianarmy #heroesofethiopia #militarypower #ethiopiandiplomacy
2 days ago
የኢትዮጵያ አስደናቂ የብዝሃ ኢኮኖሚና እምቅ የቱሪዝም አቅም በሲኤንኤን (CNN) ዕይታ
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) አዲሱ የሱፐርማን ፊልም በጉጉት ሲጠበቅ የነበረ ሲሆን፣ የጄምስ ገን የዲሲ ኮሚክስ ዩኒቨርስ የመጀመሪያው ትልቅ የሲኒማ ፊልም በመሆኑ የተለየ ትኩረት ስቦለታል። በዚህ ፊልም ላይ ከተለመዱት የሱፐርማን ገጸ-ባህሪያት በተጨማሪ ሚስተር ቴሪፊክ የተባለው ገጸ-ባህሪ ተካቷል። ይህ ገጸ-ባህሪ ከፍተኛ የቴክኖሎጂ አቅም ያለው፣ ምጡቅ መሃንዲስ እና ሳይንቲስት፣ እንዲሁም በሰው ለሰው ውጊያ የተካነ ነው። ሚስተር ቴሪፊክን ወክሎ የሚጫወተው ኤዲ ጋቴጊ፣ ለረጅም ጊዜ በፊልም እና ቴሌቪዥን ኢንዱስትሪ ውስጥ የቆየ ቢሆንም፣ የፊቱ ገጽታ እንጂ ስሙ በብዙዎች ዘንድ በደንብ አይታወቅም።
የትውልደ ኬንያዊው አሜሪካዊ ተዋናይ የፊልም ህይወት በ2006 በ'ክራንክ' ፊልም ላይ በታክሲ ሹፌርነት የጀመረ ሲሆን፣ በመቀጠልም በ'ሀውስ'፣ 'ሲኤስአይ፡ ማያሚ' እና የመሳሰሉት የቴሌቪዥን ተከታታይ ፊልሞች ላይ ተሳትፏል። 'ሱፐርማን' ለጋቴጊ የመጀመሪያው የሱፐርሂሮ ፊልም አይደለም። ከዚህ ቀደም በ2011 በወጣው 'ኤክስ-ሜን፡ ፈርስት ክላስ' ፊልም ላይ 'ዳርዊን' የተባለውን ማናቸውንም አደጋዎች ተቋቁሞ በህይወት መቆየት የሚችል የ'ማርቨል' ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከታዋቂ ተዋንያን ጋር ተጫውቷል።
ጋቴጊ ከ'ኤክስ-ሜን' በፊት በታዋቂው የ'ትዋይላይት' ፊልም ላይ ሎረንት የተባለውን ቫምፓየር ሆኖ በመተወን ይታወቃል። ምንም እንኳን ገጸ-ባህሪው በፊልሙ ላይ ቢገደልም፣ ቫምፓየር ሆኖ የመተወን የረጅም ጊዜ ህልም እንደነበረው ተዋናዩ ይናገራል። ከዚህ በተጨማሪ በታዋቂው የ'ብላክሊስት' ተከታታይ ፊልም ላይ፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የጦር ወንጀል የፈጸመውን እና የሲአይኤ ሰላይ የነበረውን ማቲያስ ሰለሞን የተባለ አደገኛ ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከ20 በላይ ክፍሎች ላይ ተሳትፏል።
ተዋናዩ በ2016 በታየው 'ስታርትአፕ' ላይም ሮናልድ ዴሲ በተባለ ዋና ገጸ-ባህሪነት የተጫወተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በአፕል ቲቪ+ (Apple TV+) 'ፎር ኦል ማንካይንድ'በተሰኘው የሳይንስ ልብወለድ ተከታታይ ፊልም ላይ ዴቭ አዬሳ የተባለውን ታዋቂ መሃንዲስ፣ የኩባንያ መስራች እና ነጋዴ ወክሎ በመተወን ላይ ይገኛል። አሁን ደግሞ በ'ሱፐርማን' ፊልም ላይ በሚጫወተው የሚስተር ቴሪፊክ ሚና በድጋሚ የብዙዎችን ትኩረት ወደ ራሱ እየሳበ ይገኛል።
የትውልደ ኬንያዊው አሜሪካዊ ተዋናይ የፊልም ህይወት በ2006 በ'ክራንክ' ፊልም ላይ በታክሲ ሹፌርነት የጀመረ ሲሆን፣ በመቀጠልም በ'ሀውስ'፣ 'ሲኤስአይ፡ ማያሚ' እና የመሳሰሉት የቴሌቪዥን ተከታታይ ፊልሞች ላይ ተሳትፏል። 'ሱፐርማን' ለጋቴጊ የመጀመሪያው የሱፐርሂሮ ፊልም አይደለም። ከዚህ ቀደም በ2011 በወጣው 'ኤክስ-ሜን፡ ፈርስት ክላስ' ፊልም ላይ 'ዳርዊን' የተባለውን ማናቸውንም አደጋዎች ተቋቁሞ በህይወት መቆየት የሚችል የ'ማርቨል' ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከታዋቂ ተዋንያን ጋር ተጫውቷል።
ጋቴጊ ከ'ኤክስ-ሜን' በፊት በታዋቂው የ'ትዋይላይት' ፊልም ላይ ሎረንት የተባለውን ቫምፓየር ሆኖ በመተወን ይታወቃል። ምንም እንኳን ገጸ-ባህሪው በፊልሙ ላይ ቢገደልም፣ ቫምፓየር ሆኖ የመተወን የረጅም ጊዜ ህልም እንደነበረው ተዋናዩ ይናገራል። ከዚህ በተጨማሪ በታዋቂው የ'ብላክሊስት' ተከታታይ ፊልም ላይ፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የጦር ወንጀል የፈጸመውን እና የሲአይኤ ሰላይ የነበረውን ማቲያስ ሰለሞን የተባለ አደገኛ ገጸ-ባህሪን ወክሎ ከ20 በላይ ክፍሎች ላይ ተሳትፏል።
ተዋናዩ በ2016 በታየው 'ስታርትአፕ' ላይም ሮናልድ ዴሲ በተባለ ዋና ገጸ-ባህሪነት የተጫወተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በአፕል ቲቪ+ (Apple TV+) 'ፎር ኦል ማንካይንድ'በተሰኘው የሳይንስ ልብወለድ ተከታታይ ፊልም ላይ ዴቭ አዬሳ የተባለውን ታዋቂ መሃንዲስ፣ የኩባንያ መስራች እና ነጋዴ ወክሎ በመተወን ላይ ይገኛል። አሁን ደግሞ በ'ሱፐርማን' ፊልም ላይ በሚጫወተው የሚስተር ቴሪፊክ ሚና በድጋሚ የብዙዎችን ትኩረት ወደ ራሱ እየሳበ ይገኛል።
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የጀርመን የጂኦ-ሳይንስ ምርምር ማዕከል ባወጣው መረጃ መሰረት፣ በግብጽ የ5.4 ማግኒቲዩድ መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ ከመሬት ወለል በታች 10 ኪሎ ሜትር (6 ማይል) ጥልቀት ላይ የተከሰተ መሆኑን ማዕከሉ አረጋግጧል።
የመሬት መንቀጥቀጡ በግብጽ ብቻ ሳይወሰን፣ አቋርጦ በማለፍ በደቡባዊ እና መካከለኛው እስራኤል ክፍሎችም ድረስ በስፋት ተሰምቷል።
የግብጽ ቀይ ጨረቃ ማህበር አደጋው በተሰማባቸው ግዛቶች ውስጥ የአስቸኳይ ጊዜ ምላሽ እቅዱን ወደ ተግባር ማስገባቱን አስታውቋል። ይሁን እንጂ ማህበሩ እስካሁን ባለው መረጃ የደረሰ የሰው ህይወት መጥፋትም ሆነ የንብረት ውድመት ሪፖርት እንዳልደረሰው ገልጿል።
ባለሥልጣናቱ አጠቃላይ ሁኔታውን ማጣራታቸውን እስኪጨርሱ ድረስ፣ ነዋሪዎች የመሰነጣጠቅ ወይም የጉዳት ምልክት ከሚያሳዩ ሕንፃዎች ርቀው እንዲቆዩ እና ይፋዊ መረጃዎችን ብቻ እንዲከታተሉ ቀይ ጨረቃ ማህበር አጥብቆ አሳስቧል።
የመሬት መንቀጥቀጡ በግብጽ ብቻ ሳይወሰን፣ አቋርጦ በማለፍ በደቡባዊ እና መካከለኛው እስራኤል ክፍሎችም ድረስ በስፋት ተሰምቷል።
የግብጽ ቀይ ጨረቃ ማህበር አደጋው በተሰማባቸው ግዛቶች ውስጥ የአስቸኳይ ጊዜ ምላሽ እቅዱን ወደ ተግባር ማስገባቱን አስታውቋል። ይሁን እንጂ ማህበሩ እስካሁን ባለው መረጃ የደረሰ የሰው ህይወት መጥፋትም ሆነ የንብረት ውድመት ሪፖርት እንዳልደረሰው ገልጿል።
ባለሥልጣናቱ አጠቃላይ ሁኔታውን ማጣራታቸውን እስኪጨርሱ ድረስ፣ ነዋሪዎች የመሰነጣጠቅ ወይም የጉዳት ምልክት ከሚያሳዩ ሕንፃዎች ርቀው እንዲቆዩ እና ይፋዊ መረጃዎችን ብቻ እንዲከታተሉ ቀይ ጨረቃ ማህበር አጥብቆ አሳስቧል።
Sponsored by
Surafel
4 days ago
በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ለትምህርት ጥራት እና ውጤታማነት መጠናከር ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል - የትምህርት ሚኒስቴር
**************************
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ ላይ ውይይት ማድረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች የቀረበው 7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII 2026/27 to 2030/31) ረቂቅ ዕቅድ፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ውጤታማነትን ማጠናከር ዋና ትኩረት እንደሚሆን አመላክቷል።
በረቂቅ ዕቅዱ መሠረት፣ የትምህርት ጥራትን እና ተገቢነትን ለማረጋገጥ ቀደም ሲል የተጀመሩ ሥራዎችን በአዳዲስ አሠራሮች ማጠናከር፣ የትምህርትን ውጤት በተጨባጭ መለካት እና በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ ቅድሚያ የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።
ፕሮግራሙ አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት በውጤታማነት መተግበር፣ ምዘናን በብቃት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ማድረግ፣ የተማሪዎችን የመማር ውጤት ማሻሻል እንዲሁም በቋንቋ፣ በሒሳብ እና በሳይንስ ትምህርቶች ያላቸውን ብቃት ማሳደግን እንደ ዋና ተግባራት አካቷል።
በተጨማሪም የዲጂታል ትምህርትን ማስፋፋት፣ የብሔራዊ ፈተናዎችን ማዘመን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና (TVET) እና በከፍተኛ ትምህርት መካከል ያለውን ቅንጅት ማጠናከር፣ የመምህራንን ሙያዊ ብቃት እና ማበረታቻ ማሻሻል፣ እንዲሁም የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጆችን እና ዩኒቨርሲቲዎችን ማጠናከር በዕቅዱ ውስጥ ተካትተዋል።
ረቂቅ ዕቅዱ የትምህርት ጥራት፣ ተገቢነትን ተደራሽነትን እና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት የተጎዱ የትምህርት ማኅበረሰቦችን መልሶ ማቋቋም፣ ትምህርትን ሳይቋረጥ እንዲዘልቅ የሚያስችል ሥርዓት መገንባት፣ እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች እና የሴት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ እና ውጤታማነት ማረጋገጥ ላይም ልዩ ትኩረት መስጠቱን ያመለክታል።
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ በምክክር መድረኩ ላይ ቀርቦ፣ በክልል እና በከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም በዘርፉ ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት የተደረገበት መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
#ethiopia #ebc #education #ministryofeducation #educationquality
**************************
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ ላይ ውይይት ማድረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች የቀረበው 7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII 2026/27 to 2030/31) ረቂቅ ዕቅድ፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ውጤታማነትን ማጠናከር ዋና ትኩረት እንደሚሆን አመላክቷል።
በረቂቅ ዕቅዱ መሠረት፣ የትምህርት ጥራትን እና ተገቢነትን ለማረጋገጥ ቀደም ሲል የተጀመሩ ሥራዎችን በአዳዲስ አሠራሮች ማጠናከር፣ የትምህርትን ውጤት በተጨባጭ መለካት እና በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ ቅድሚያ የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።
ፕሮግራሙ አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት በውጤታማነት መተግበር፣ ምዘናን በብቃት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ማድረግ፣ የተማሪዎችን የመማር ውጤት ማሻሻል እንዲሁም በቋንቋ፣ በሒሳብ እና በሳይንስ ትምህርቶች ያላቸውን ብቃት ማሳደግን እንደ ዋና ተግባራት አካቷል።
በተጨማሪም የዲጂታል ትምህርትን ማስፋፋት፣ የብሔራዊ ፈተናዎችን ማዘመን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና (TVET) እና በከፍተኛ ትምህርት መካከል ያለውን ቅንጅት ማጠናከር፣ የመምህራንን ሙያዊ ብቃት እና ማበረታቻ ማሻሻል፣ እንዲሁም የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጆችን እና ዩኒቨርሲቲዎችን ማጠናከር በዕቅዱ ውስጥ ተካትተዋል።
ረቂቅ ዕቅዱ የትምህርት ጥራት፣ ተገቢነትን ተደራሽነትን እና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት የተጎዱ የትምህርት ማኅበረሰቦችን መልሶ ማቋቋም፣ ትምህርትን ሳይቋረጥ እንዲዘልቅ የሚያስችል ሥርዓት መገንባት፣ እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች እና የሴት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ እና ውጤታማነት ማረጋገጥ ላይም ልዩ ትኩረት መስጠቱን ያመለክታል።
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ በምክክር መድረኩ ላይ ቀርቦ፣ በክልል እና በከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም በዘርፉ ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት የተደረገበት መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
#ethiopia #ebc #education #ministryofeducation #educationquality
5 days ago
ከወርቅ በእጅጉ ውድ የሆነ አዲስ ማዕድን በሩሲያ ተገኘ? ሳይንቲስቶች ምን አገኙ?
#ethiopia | ሞስኮ – በሩሲያ ሰሜን ምዕራብ በሚገኘው የኮላ (Kola) ባሕረ-ገብ መሬት የኪቢኒ (Khibiny) ተራራ አካባቢ የሚገኘው የኪሮቭስኪ ማዕድን ማውጫ ውስጥ የሩሲያ ተመራማሪዎች ከቀድሞው የአሽክሮፍታይን (Ashcroftine) ቤተሰብ ጋር የተያያዘ አዲስ የማዕድን ዓይነት መለየታቸው በሳይንስ ዓለም ትልቅ ትኩረት ስቧል።
ይህ አዲሱ ማዕድን በጊዜያዊነት “Kola Ashcroftine” በሚል ስያሜ እየተጠራ ሲሆን ከታዋቂው Ashcroftine-(Y) የተለየ ክሪስታል መዋቅር እንዳለው የሳይንሳዊ ጥናቶች ያመለክታሉ።
የሩሲያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ማዕድኑ የኢትሪየም (Yttrium)፣ ሲሊከን፣ ፖታሲየም፣ ሶዲየም፣ ካልሲየም፣ ማንጋኒዝ እና ፍሎሪንን ጨምሮ በርካታ ንጥረ ነገሮችን የያዘ እጅግ ውስብስብ የሲሊኬት ማዕድን ነው።
በነጠላ ክሪስታል ኤክስሬይ ትንተና የተደረገበት ጥናትም ይህ ዓይነት ክሪስታል በውስጡ የናኖ ቱቦችን (nanotubules) የያዘ ልዩ መዋቅር እንዳለው አረጋግጧል።
በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው "በ1 ሚሊሜትር 145 ዶላር ይሸጣል" ወይም "ከወርቅ በእጅጉ ይበልጣል" የሚለው መረጃ ግን በአሁኑ ጊዜ በታተሙ ሳይንሳዊ ጥናቶች ወይም በዓለም የማዕድን ገበያ መረጃዎች የተረጋገጠ አይደለም።
ባለሙያዎች ይህ ግኝት የሳይንስ እና የማዕድን ጥናት እሴት እንዳለው ቢገልጹም፣ የንግድ ዋጋው ገና በግልጽ መልኩ አልተወሰነም።
የኪቢኒ ተራራ እና የኮላ ባሕረ-ገብ መሬት በዓለም ላይ በብዙ ብርቅዬ ማዕድናት የሚታወቅ ክልል ነው። በዚህ አካባቢ ከመቶዎች በላይ አዳዲስ ማዕድናት ተገኝተዋል፤ ከእነዚህም ብዙዎቹ በሌላ የዓለም ክፍል አይገኙም።
ክልሉ በተለይ በሬር አርዝ (Rare Earth Elements) ማዕድናት ምክንያት ለሳይንስና ለከፍተኛ ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ እንዲህ ዓይነት አዲስ ማዕድናት መገኘታቸው የምድር አፈጣጠርን ለመረዳት፣ አዳዲስ ቁሶችን ለማዘጋጀት እና በወደፊት በኤሌክትሮኒክስ፣ በኃይል ቴክኖሎጂና በሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ አዳዲስ አጠቃቀሞችን ለማስገኘት የሚያስችሉ ናቸው።
ሆኖም ይህ ማዕድን በንግድ ደረጃ መመረት ወይም በስፋት መጠቀም ይቻል እንደሆነ ለመወሰን ተጨማሪ የምርምር ሥራዎች እንደሚያስፈልጉ ተገልጿል።
#ethiopia | ሞስኮ – በሩሲያ ሰሜን ምዕራብ በሚገኘው የኮላ (Kola) ባሕረ-ገብ መሬት የኪቢኒ (Khibiny) ተራራ አካባቢ የሚገኘው የኪሮቭስኪ ማዕድን ማውጫ ውስጥ የሩሲያ ተመራማሪዎች ከቀድሞው የአሽክሮፍታይን (Ashcroftine) ቤተሰብ ጋር የተያያዘ አዲስ የማዕድን ዓይነት መለየታቸው በሳይንስ ዓለም ትልቅ ትኩረት ስቧል።
ይህ አዲሱ ማዕድን በጊዜያዊነት “Kola Ashcroftine” በሚል ስያሜ እየተጠራ ሲሆን ከታዋቂው Ashcroftine-(Y) የተለየ ክሪስታል መዋቅር እንዳለው የሳይንሳዊ ጥናቶች ያመለክታሉ።
የሩሲያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ማዕድኑ የኢትሪየም (Yttrium)፣ ሲሊከን፣ ፖታሲየም፣ ሶዲየም፣ ካልሲየም፣ ማንጋኒዝ እና ፍሎሪንን ጨምሮ በርካታ ንጥረ ነገሮችን የያዘ እጅግ ውስብስብ የሲሊኬት ማዕድን ነው።
በነጠላ ክሪስታል ኤክስሬይ ትንተና የተደረገበት ጥናትም ይህ ዓይነት ክሪስታል በውስጡ የናኖ ቱቦችን (nanotubules) የያዘ ልዩ መዋቅር እንዳለው አረጋግጧል።
በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው "በ1 ሚሊሜትር 145 ዶላር ይሸጣል" ወይም "ከወርቅ በእጅጉ ይበልጣል" የሚለው መረጃ ግን በአሁኑ ጊዜ በታተሙ ሳይንሳዊ ጥናቶች ወይም በዓለም የማዕድን ገበያ መረጃዎች የተረጋገጠ አይደለም።
ባለሙያዎች ይህ ግኝት የሳይንስ እና የማዕድን ጥናት እሴት እንዳለው ቢገልጹም፣ የንግድ ዋጋው ገና በግልጽ መልኩ አልተወሰነም።
የኪቢኒ ተራራ እና የኮላ ባሕረ-ገብ መሬት በዓለም ላይ በብዙ ብርቅዬ ማዕድናት የሚታወቅ ክልል ነው። በዚህ አካባቢ ከመቶዎች በላይ አዳዲስ ማዕድናት ተገኝተዋል፤ ከእነዚህም ብዙዎቹ በሌላ የዓለም ክፍል አይገኙም።
ክልሉ በተለይ በሬር አርዝ (Rare Earth Elements) ማዕድናት ምክንያት ለሳይንስና ለከፍተኛ ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ እንዲህ ዓይነት አዲስ ማዕድናት መገኘታቸው የምድር አፈጣጠርን ለመረዳት፣ አዳዲስ ቁሶችን ለማዘጋጀት እና በወደፊት በኤሌክትሮኒክስ፣ በኃይል ቴክኖሎጂና በሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ አዳዲስ አጠቃቀሞችን ለማስገኘት የሚያስችሉ ናቸው።
ሆኖም ይህ ማዕድን በንግድ ደረጃ መመረት ወይም በስፋት መጠቀም ይቻል እንደሆነ ለመወሰን ተጨማሪ የምርምር ሥራዎች እንደሚያስፈልጉ ተገልጿል።
6 days ago
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የCGIAR የመጀመሪያው የቦርድ ሊቀመንበር ሆነው ተሾሙ
#ethiopia | የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ቦሼ በዓለም አቀፍ የግብርና ምርምር ትብብር ተቋም CGIAR አዲስ የተዋቀረው የቦርድ የመጀመሪያ ሊቀመንበር ሆነው መሾማቸውን ተቋሙ በይፋ አስታውቋል። ሹመታቸው ከነሐሴ 1 ቀን 2026 ጀምሮ በይፋ ተግባራዊ ይሆናል።
እንደ CGIAR መግለጫ፣ አዲሱ ቦርድ የተቋሙን የዓለም አቀፍ የግብርና ምርምር ሥራዎች በማስተባበር በምግብ ዋስትና፣ በግብርና ምርታማነት፣ በአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅም እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ዙሪያ የሚከናወኑ ስትራቴጂያዊ ውሳኔዎችን ይመራል።
ሹመቱ የተካሄደው ለወራት የዘለቀ የምልመላና የእጩ ምርጫ ሂደት ተጠናቆ ሲሆን፣ ኃይለማርያም ደሳለኝ በግብርና ፖሊሲ፣ በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ትብብር፣ እንዲሁም በሳይንስን መሠረት ባደረገ የልማት አመራር ያላቸው ልምድ ለሹመታቸው ዋና ምክንያት መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።
የCGIAR ጊዜያዊ የቦርድ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ሮኤል መርክስ በሰጡት መግለጫ፣ ኃይለማርያም በሳይንስ ላይ የተመሰረተ የግብርና ልማትን ለማራመድ ያላቸው ልምድና አመራር ለተቋሙ ትልቅ እሴት እንደሚያመጣ ገልጸዋል።
ኃይለማርያም ደሳለኝ ከ2019 ጀምሮ የAGRA (Alliance for a Green Revolution in Africa) ቦርድ ሊቀመንበር በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን፣ በተጨማሪም የTradeMark Africa ቦርድን ጨምሮ በበርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት የአመራር ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ቦሼ በዓለም አቀፍ የግብርና ምርምር ትብብር ተቋም CGIAR አዲስ የተዋቀረው የቦርድ የመጀመሪያ ሊቀመንበር ሆነው መሾማቸውን ተቋሙ በይፋ አስታውቋል። ሹመታቸው ከነሐሴ 1 ቀን 2026 ጀምሮ በይፋ ተግባራዊ ይሆናል።
እንደ CGIAR መግለጫ፣ አዲሱ ቦርድ የተቋሙን የዓለም አቀፍ የግብርና ምርምር ሥራዎች በማስተባበር በምግብ ዋስትና፣ በግብርና ምርታማነት፣ በአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅም እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ዙሪያ የሚከናወኑ ስትራቴጂያዊ ውሳኔዎችን ይመራል።
ሹመቱ የተካሄደው ለወራት የዘለቀ የምልመላና የእጩ ምርጫ ሂደት ተጠናቆ ሲሆን፣ ኃይለማርያም ደሳለኝ በግብርና ፖሊሲ፣ በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ትብብር፣ እንዲሁም በሳይንስን መሠረት ባደረገ የልማት አመራር ያላቸው ልምድ ለሹመታቸው ዋና ምክንያት መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።
የCGIAR ጊዜያዊ የቦርድ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ሮኤል መርክስ በሰጡት መግለጫ፣ ኃይለማርያም በሳይንስ ላይ የተመሰረተ የግብርና ልማትን ለማራመድ ያላቸው ልምድና አመራር ለተቋሙ ትልቅ እሴት እንደሚያመጣ ገልጸዋል።
ኃይለማርያም ደሳለኝ ከ2019 ጀምሮ የAGRA (Alliance for a Green Revolution in Africa) ቦርድ ሊቀመንበር በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን፣ በተጨማሪም የTradeMark Africa ቦርድን ጨምሮ በበርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት የአመራር ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
9 days ago
ከውኃ ኃይል ባሻገር፤ የኢትዮጵያ አዲሱ የኒዩክሌር ኃይል ጉዞ እና የብልጽግና ተስፋ
****************
ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት የኃይል አቅርቦትና ፍላጎቷን ለማመጣጠን ከውኃ እስከ ንፋስ፣ ከጂኦተርማል እስከ ፀሐይ ኃይል ማመንጫዎችን በመገንባት በአፍሪካ አህጉር ተምሳሌታዊ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች።
ከጊቤ I እስከ ኮይሻ ያሉ ግዙፍ የውኃ ኃይል ማመንጫዎች እንዲሁም ከአባ ሳሙኤል እስከ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዘረጉት መሠረተ ልማቶች ማኅበረሰቡንና የአምራች ኢንዱስትሪዎችን በማንቀሳቀስ ለሀገራችን ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም ሆነዋል።
ሆኖም ዘላቂ የኃይል ፍላጎትን በተወሰኑ አማራጮች ብቻ ማሟላት አዋጭ አለመሆኑን የተረዳው መንግሥት፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ የኒዩክሌር ኃይል አስፈላጊነትን በመገንዘብ ስትራቴጂካዊ የኃይል አቅርቦት ፍኖተ ካርታ በማዘጋጀት ወደ ተግባር ገብቷል።
የኒዩክሌር ቴክኖሎጂ እንደ ፀሐይና ንፋስ ከአየር ንብረት ጋር የማይቀያየርና በቀን 24 ሰዓት በሳምንት 7 ቀን ያለማቋረጥ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው በመሆኑ ለትላልቅ ኢንዱስትሪዎች፣ ለአምራች ሴክተሮችና ለቴክኖሎጂ ማዕከላት የማይንቀሳቀስ መሠረት ይጥላል።
ይህ ቴክኖሎጂ ኤሌክትሪክ በሚያመነጭበት ወቅት ምንም ዓይነት የካርቦን ልቀት የሌለው በመሆኑ ለአየር ንብረት ለውጥ ትግልና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው።
በተጨማሪም ከቅሪተ አካል ነዳጆች የዋጋ መዋዥቅና ጥገኝነት ነፃ የሚያደርግ ሲሆን፣ ከኃይል ማመንጨት ባለፈ በሕክምና፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና ውኃ ማጣራት እንዲሁም ለብዙ ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ አለው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ፈረንሳይ 70 በመቶ የኤሌክትሪክ ፍላጎቷን በኒዩክሌር በመሸፈን አነስተኛ የካርቦን ልቀት ማረጋገጥ ስትችል፤ አሜሪካ፣ ቻይና፣ ደቡብ ኮሪያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶችም በዘርፉ ትልቅ ስኬት አስመዝግበዋል።
ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ በመቅሰም ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል የኒዩክሌር ኃይል ፍኖተ ካርታ ቀርጻለች።
ሀገራችን በዘርፉ የተሻለ ልምድና ተሞክሮ ካለው የሩሲያው ሮሳቶም (Rosatom) ስቴት ኮርፖሬሽን ጋር ስትራቴጂካዊ ስምምነት ያደረገች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም ጠንካራ የደህንነት መሠረተ ልማትና የፋይናንስ ዝግጅት በማጠናከር ቴክኖሎጂውን ለኢንዱስትሪ፣ ለሕክምናና ለሳይንስ ዕድገት ለማዋል የጀመረችውን ጉዞ አጠናክራ ቀጥላለች።
በመሐመድ ፊጣሞ
#ethiopia #nuclearenergy #greeneconomy #sustainabledevelopment #energytransition
****************
ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት የኃይል አቅርቦትና ፍላጎቷን ለማመጣጠን ከውኃ እስከ ንፋስ፣ ከጂኦተርማል እስከ ፀሐይ ኃይል ማመንጫዎችን በመገንባት በአፍሪካ አህጉር ተምሳሌታዊ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች።
ከጊቤ I እስከ ኮይሻ ያሉ ግዙፍ የውኃ ኃይል ማመንጫዎች እንዲሁም ከአባ ሳሙኤል እስከ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዘረጉት መሠረተ ልማቶች ማኅበረሰቡንና የአምራች ኢንዱስትሪዎችን በማንቀሳቀስ ለሀገራችን ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም ሆነዋል።
ሆኖም ዘላቂ የኃይል ፍላጎትን በተወሰኑ አማራጮች ብቻ ማሟላት አዋጭ አለመሆኑን የተረዳው መንግሥት፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ የኒዩክሌር ኃይል አስፈላጊነትን በመገንዘብ ስትራቴጂካዊ የኃይል አቅርቦት ፍኖተ ካርታ በማዘጋጀት ወደ ተግባር ገብቷል።
የኒዩክሌር ቴክኖሎጂ እንደ ፀሐይና ንፋስ ከአየር ንብረት ጋር የማይቀያየርና በቀን 24 ሰዓት በሳምንት 7 ቀን ያለማቋረጥ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው በመሆኑ ለትላልቅ ኢንዱስትሪዎች፣ ለአምራች ሴክተሮችና ለቴክኖሎጂ ማዕከላት የማይንቀሳቀስ መሠረት ይጥላል።
ይህ ቴክኖሎጂ ኤሌክትሪክ በሚያመነጭበት ወቅት ምንም ዓይነት የካርቦን ልቀት የሌለው በመሆኑ ለአየር ንብረት ለውጥ ትግልና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው።
በተጨማሪም ከቅሪተ አካል ነዳጆች የዋጋ መዋዥቅና ጥገኝነት ነፃ የሚያደርግ ሲሆን፣ ከኃይል ማመንጨት ባለፈ በሕክምና፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና ውኃ ማጣራት እንዲሁም ለብዙ ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ አለው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ፈረንሳይ 70 በመቶ የኤሌክትሪክ ፍላጎቷን በኒዩክሌር በመሸፈን አነስተኛ የካርቦን ልቀት ማረጋገጥ ስትችል፤ አሜሪካ፣ ቻይና፣ ደቡብ ኮሪያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶችም በዘርፉ ትልቅ ስኬት አስመዝግበዋል።
ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ በመቅሰም ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል የኒዩክሌር ኃይል ፍኖተ ካርታ ቀርጻለች።
ሀገራችን በዘርፉ የተሻለ ልምድና ተሞክሮ ካለው የሩሲያው ሮሳቶም (Rosatom) ስቴት ኮርፖሬሽን ጋር ስትራቴጂካዊ ስምምነት ያደረገች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም ጠንካራ የደህንነት መሠረተ ልማትና የፋይናንስ ዝግጅት በማጠናከር ቴክኖሎጂውን ለኢንዱስትሪ፣ ለሕክምናና ለሳይንስ ዕድገት ለማዋል የጀመረችውን ጉዞ አጠናክራ ቀጥላለች።
በመሐመድ ፊጣሞ
#ethiopia #nuclearenergy #greeneconomy #sustainabledevelopment #energytransition
11 days ago
የመከላከያ የላቀ የላብራቶሪ ማዕከል እና 7ቱ ልዩ የምርምር ላቦራቶሪዎች
********************************
የሀገራችንን የመከላከያ አቅም በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ እና በምርምር ይበልጥ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የተቋቋመው የመከላከያ የላቀ የላብራቶሪ ማዕከል በ7 ዋና ዋና ዘመናዊ የምርምር ዘርፎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ ይገኛል።
ማዕከሉ ሀገራዊ የዲጂታል እና የመረጃ ደኅንነትን የሚጠበቅበት የሳይበር ደኅንነት፣ ዘመናዊ የኤአይ ቴክኖሎጂን የሚያበለጽገው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ የኃይል አቅርቦትን የሚያሳድገው የኤሌክትሪክ ኃይል፣ እንዲሁም የራስ-ሰር ሥርዓቶችን የሚያመርተው የአውቶሜሽን ላቦራቶሪዎችን አካቶ ይዟል።
በተጨማሪም የመገናኛና የራዳር ሥርዓቶችን የሚያለማው የኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ፣ የቴክኖሎጂ አካላት ፈጣን ቅርፅ ማውጫ የሆነው የ3D ዲዛይንና ፕሮቶታይፕ፣ እና የሕክምና ተግባራዊ ልምምድ ማዕከል የሆነው የነርሲንግ ሲሙሌሽን ላቦራቶሪዎች በማዕከሉ ውስጥ ተካተው በከፍተኛ ቁርጠኝነት አገልግሎትና ምርምር በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
ይህ የላቀ የቴክኖሎጂ ማዕከል ለሀገራችን የመከላከያ ሰራዊት ዘመናዊነት እና ለሀገራዊ ቴክኖሎጂ ዕድገት ታላቅ ምዕራፍ ነው።
#ethiopiandefense #defensetechnology #researchanddevelopment #ethiopia
********************************
የሀገራችንን የመከላከያ አቅም በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ እና በምርምር ይበልጥ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የተቋቋመው የመከላከያ የላቀ የላብራቶሪ ማዕከል በ7 ዋና ዋና ዘመናዊ የምርምር ዘርፎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ ይገኛል።
ማዕከሉ ሀገራዊ የዲጂታል እና የመረጃ ደኅንነትን የሚጠበቅበት የሳይበር ደኅንነት፣ ዘመናዊ የኤአይ ቴክኖሎጂን የሚያበለጽገው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ የኃይል አቅርቦትን የሚያሳድገው የኤሌክትሪክ ኃይል፣ እንዲሁም የራስ-ሰር ሥርዓቶችን የሚያመርተው የአውቶሜሽን ላቦራቶሪዎችን አካቶ ይዟል።
በተጨማሪም የመገናኛና የራዳር ሥርዓቶችን የሚያለማው የኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ፣ የቴክኖሎጂ አካላት ፈጣን ቅርፅ ማውጫ የሆነው የ3D ዲዛይንና ፕሮቶታይፕ፣ እና የሕክምና ተግባራዊ ልምምድ ማዕከል የሆነው የነርሲንግ ሲሙሌሽን ላቦራቶሪዎች በማዕከሉ ውስጥ ተካተው በከፍተኛ ቁርጠኝነት አገልግሎትና ምርምር በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
ይህ የላቀ የቴክኖሎጂ ማዕከል ለሀገራችን የመከላከያ ሰራዊት ዘመናዊነት እና ለሀገራዊ ቴክኖሎጂ ዕድገት ታላቅ ምዕራፍ ነው።
#ethiopiandefense #defensetechnology #researchanddevelopment #ethiopia
Sponsored by
Surafel
12 days ago
ዛሬ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የAI ስታርታፕ ሰልጣኞች በሳይንስ ሙዚየም በደማቅ ሁኔታ አስመርቀናል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
12 days ago
የኢትዮጵያ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ እመርታ
****************
ኢትዮጵያ ግብርና መር ኢኮኖሚዋን ወደ ማኑፋክቸሪንግ እና ኢንዱስትሪ ለማሸጋገር በምታደርገው ጥረት፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ማሳደጓ ጠንካራ መዋቅራዊ መደላድል እየፈጠረ ይገኛል።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ማዕቀፍ የተተገበሩት ፖሊሲዎች የፓርኮቹን አስተዳደር ወደ ግል ዘርፉ በማሸጋገር የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መዋቅር ሙሉ በሙሉ እየቀየሩት ነው።
ይህ ታሪካዊ ሽግግር በተለይም አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ ረገድ አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል።
በማሳያነትም በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ብቻ ከ750 ሚሊዮን ዶላር በላይ የመነሻ ካፒታል ያስመዘገቡ 166 አዳዲስ ባለሀብቶች ወደ ዘርፉ ተቀላቅለዋል።
ይበልጥ ተስፋ የሚሰጠው ደግሞ ከእነዚህ ውስጥ 84 በመቶ የሚሆኑት የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች መሆናቸው ነው። ይህ አዲሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም የፈጠረውን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት እና አቅም በግልጽ የሚያሳይ ነው።
ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖቹ በሥራ ዕድል ፈጠራ በኩል የዜጎችን በተለይም የወጣት ሴቶችን ሕይወት በተጨባጭ እየቀየሩ ነው። በመላው ሀገራችን በሚገኙ ፓርኮች ውስጥ ከ100 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀጥተኛና ቋሚ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።
በኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ትክክለኛ የኢንዱስትሪ ግብዓት ትስስር በመፍጠር የአርሶ አደሩን ምርት ከፋብሪካዎች ጋር በቀጥታ ማስተሳሰር ተችሏል። እስካሁን ባለው ሂደት ከ100 ሺህ በላይ አምራቾች እና አርሶ አደሮች ከትላልቅ ገዢዎች ጋር በቀጥታ ተገናኝተዋል።
በዚህም በአርሶ አደሮች እና በፋብሪካዎች መካከል ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የንግድ ግብይት መፈጸሙ፣ የኢንዱስትሪው ትስስር ምን ያህል ወደ ታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል እንደወረደ ያመላክታል።
የውጭ ምንዛሬን በማመንጨት እና የገቢ ምርቶችን በመተካት በኩል የተመዘገቡት ስኬቶች የኢትዮጵያን የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ።
በ2018 በጀት ዓመት ፓርኮቹ ከወጪ ንግድ 266.9 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት በታሪካቸው ከፍተኛ የተባለ ውጤት አስመዝግበዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ከ26.7 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን የገቢ ምርቶች በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ታድገዋል።
ይህ በፓርኮች የታየው ስኬት በሀገር አቀፍ ደረጃ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስተባባሪነት እየተተገበረ ካለው "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ጋር ተጣምሮ ታላቅ ሀገራዊ ውጤት አምጥቷል።
ንቅናቄው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 13 በመቶ ያሳደገው ሲሆን፣ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ የገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት አስችሏል።
ለእነዚህ ተጨባጭ ለውጦች እና ስኬቶች በዋናነት በምክንያትነት የሚጠቀሰው በቅርቡ የፀደቀው የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጅ እና መንግሥት ያቀረባቸው ሰፊ ማበረታቻዎች ናቸው።
አዲሱ የሕግ ማዕቀፍ ፓርኮቹን በጨርቃጨርቅ ምርት ላይ ብቻ ከነበረ ጥገኝነት አውጥቶ ግብርናን፣ ሳይንስን እና የሎጂስቲክስ አገልግሎትን እንዲያካትቱ አድርጓል።
ከዚህም በተጨማሪ የጉምሩክ ቀረጥ ነፃ መብቶች፣ የዜሮ ምጣኔ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ለኤክስፖርት አምራቾች የተሰጡ የአምስት ዓመት የግብር እፎይታዎች፣ እንዲሁም የውጭ ሀገር ባንኮች በዞኖቹ ውስጥ በነፃነት እንዲሠሩ መፈቀዱ ዘርፉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ አድርጎታል።
የጥራት፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የሠራተኞች ደህንነት (ISO) ደረጃዎችን ያካተተ የተቀናጀ የአመራር ሥርዓት መዘርጋቱም የኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዕድገት ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ጽኑ መሠረት ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #industrialparks #specialeconomiczones #investinethiopia #ethiopiatamirt
****************
ኢትዮጵያ ግብርና መር ኢኮኖሚዋን ወደ ማኑፋክቸሪንግ እና ኢንዱስትሪ ለማሸጋገር በምታደርገው ጥረት፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ማሳደጓ ጠንካራ መዋቅራዊ መደላድል እየፈጠረ ይገኛል።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ማዕቀፍ የተተገበሩት ፖሊሲዎች የፓርኮቹን አስተዳደር ወደ ግል ዘርፉ በማሸጋገር የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መዋቅር ሙሉ በሙሉ እየቀየሩት ነው።
ይህ ታሪካዊ ሽግግር በተለይም አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ ረገድ አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል።
በማሳያነትም በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ብቻ ከ750 ሚሊዮን ዶላር በላይ የመነሻ ካፒታል ያስመዘገቡ 166 አዳዲስ ባለሀብቶች ወደ ዘርፉ ተቀላቅለዋል።
ይበልጥ ተስፋ የሚሰጠው ደግሞ ከእነዚህ ውስጥ 84 በመቶ የሚሆኑት የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች መሆናቸው ነው። ይህ አዲሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም የፈጠረውን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት እና አቅም በግልጽ የሚያሳይ ነው።
ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖቹ በሥራ ዕድል ፈጠራ በኩል የዜጎችን በተለይም የወጣት ሴቶችን ሕይወት በተጨባጭ እየቀየሩ ነው። በመላው ሀገራችን በሚገኙ ፓርኮች ውስጥ ከ100 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀጥተኛና ቋሚ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።
በኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ትክክለኛ የኢንዱስትሪ ግብዓት ትስስር በመፍጠር የአርሶ አደሩን ምርት ከፋብሪካዎች ጋር በቀጥታ ማስተሳሰር ተችሏል። እስካሁን ባለው ሂደት ከ100 ሺህ በላይ አምራቾች እና አርሶ አደሮች ከትላልቅ ገዢዎች ጋር በቀጥታ ተገናኝተዋል።
በዚህም በአርሶ አደሮች እና በፋብሪካዎች መካከል ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የንግድ ግብይት መፈጸሙ፣ የኢንዱስትሪው ትስስር ምን ያህል ወደ ታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል እንደወረደ ያመላክታል።
የውጭ ምንዛሬን በማመንጨት እና የገቢ ምርቶችን በመተካት በኩል የተመዘገቡት ስኬቶች የኢትዮጵያን የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ።
በ2018 በጀት ዓመት ፓርኮቹ ከወጪ ንግድ 266.9 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት በታሪካቸው ከፍተኛ የተባለ ውጤት አስመዝግበዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ከ26.7 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን የገቢ ምርቶች በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ታድገዋል።
ይህ በፓርኮች የታየው ስኬት በሀገር አቀፍ ደረጃ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስተባባሪነት እየተተገበረ ካለው "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ጋር ተጣምሮ ታላቅ ሀገራዊ ውጤት አምጥቷል።
ንቅናቄው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 13 በመቶ ያሳደገው ሲሆን፣ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ የገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት አስችሏል።
ለእነዚህ ተጨባጭ ለውጦች እና ስኬቶች በዋናነት በምክንያትነት የሚጠቀሰው በቅርቡ የፀደቀው የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጅ እና መንግሥት ያቀረባቸው ሰፊ ማበረታቻዎች ናቸው።
አዲሱ የሕግ ማዕቀፍ ፓርኮቹን በጨርቃጨርቅ ምርት ላይ ብቻ ከነበረ ጥገኝነት አውጥቶ ግብርናን፣ ሳይንስን እና የሎጂስቲክስ አገልግሎትን እንዲያካትቱ አድርጓል።
ከዚህም በተጨማሪ የጉምሩክ ቀረጥ ነፃ መብቶች፣ የዜሮ ምጣኔ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ለኤክስፖርት አምራቾች የተሰጡ የአምስት ዓመት የግብር እፎይታዎች፣ እንዲሁም የውጭ ሀገር ባንኮች በዞኖቹ ውስጥ በነፃነት እንዲሠሩ መፈቀዱ ዘርፉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ አድርጎታል።
የጥራት፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የሠራተኞች ደህንነት (ISO) ደረጃዎችን ያካተተ የተቀናጀ የአመራር ሥርዓት መዘርጋቱም የኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዕድገት ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ጽኑ መሠረት ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #industrialparks #specialeconomiczones #investinethiopia #ethiopiatamirt
12 days ago
በህይወት እያሉ ተመሰገኑ
(በዕዝራ እጅጉ)
.የመዲናዋ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና እንዲያገኙ ወሰነ
#ethiopia | አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ ዛሬ ጋቢ በተደረበላቸው ዕለት ደስታቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር።
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት እነዚህ ጉምቱ ባለሙያዎች ከ 35 አመት በላይ በትጋት ያገለገሉ ሲሆን በሙያ አጋሮቻቸው ተከበው አድናቆት ሲቸራቸው ውለዋል።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም ከ 4 ሰዓት ጀምሮ በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በተደረገው መርሀ ግብር የሚድያ ባለሙያዎች እና ወዳጆቻቸው ተገኝተው እኛም አመስጋኞቻችሁ ነን በማለት ለመርሀ ግብሩ ድምቀት ሰጥተዋል።
ባለሙያዎቹን ለማመስገን ራሱን የቻለ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን ይህም ኮሚቴ ባለሙያዎቹ በዘለቄታዊነት የሚታገዙበት መንገድ ያመቻቸ ነው።
ለዝግጅቱ መሳካት በተከፈተው የwhat is up ገፅ ኮሚቴው ውስጥ ተግባራቸውን የተወጡት ጥላሁን ካሣ ፣ሀብታሙ ድረስ ፣ሰለሞን ሀይለኢየሱስ፣ዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)፣ አለም ታደሰ፣ሠናይት ሀይሌ፣እሸቱ ገለቱ፣ ጌጡ ተመስገን እና ግደይ ገብረ ሲሆኑ እነርሱም በዕለቱ እንደተናገሩት ሥራው በአጭር ጊዜ ታስቦ ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ለአንጋፋ ባለሙያዎቹ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና የሚያገኙበት መንገድ ያመቻቸ ሲሆን ይህ የመረዳዳት ባህል ወደፊትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተነግሯል።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
"ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን "የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች እንደነበሩ በዕለቱ ምስክርነት የሰጡ ባልደረቦቻቸው የተናገሩ ሲሆን የምስጋና ቀን መዘጋጀቱ አዲስ የሚመጣውንም ባለሙያ የሚያበረታታ ነው ሲሉ ሀሣብ ሰንዝረዋል።
በዕለቱ የሚድያ ሥራን ከ1950ዎቹ ጀምሮ ያስቃኘ አጭር የትዝታ ዘጋቢ ፊልም የቀረበ ሲሆን ተመስጋኞቹ ከዚህ ቀደም አየር ላይ ያዋሏቸው ሥራዎችም በዕለቱ ለታደሙት እንግዶች ቀርበዋል።
በባልደረቦቻቸው የምስጋና ዝግጅት የተደረገላቸው አዲስአለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ እንደዛሬ ደስ ብሎንም አያውቅ ፣ ይህን መርሀ ግብር በተሳካ መንገድ ዕውን እንዲሆን የጣራችሁ ሁሉ ፈጣሪ መንገዳችሁን ያቃና ሲሉ መርቀዋል።
የአዘጋጅ ኮሚቴው አባል እሸቱ ገለቱ እንዳለው በኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚሠሩ ባልደረቦች የመጠያየቅ ባህልን ከጀመሩ ሁለት አመት እንደሆናቸው ጠቅሰው ይህ የምስጋና መርሀ ግብር የዚያ መጠያየቅ አካል እንደሆነ ጠቁሟል።
ባለሙያዎች ጡረታ ሲወጡ የሚደገፉበት፣ በተለይም በኢኮኖሚ እገዛ የሚያገኙበት ስልት መነደፍ እንዳለበትም ጋዜጠኛ እሸቱ ጥቆማ ሰጥቷል። በተጨማሪም የጤና ሁኔታቸውን፣ የሚከታተሉበት መንገድ መፈጠር እንዳለበትም ተናግሯል።
ከጡረታ በኃላ ምክር በመስጠት ባለሙያዎቹ ልምዳቸውን ማጋራት አለባቸውም ብሏል።ይህንኑ ትልቅ ርዕይ ለማሳካት መንግሥትና የሚመለከታቸው የሚድያ ማህበራት ሊተባበሩ ይገባልም ሲል ሀሣብ አንስቷል።
የእለቱን የምስጋና መሰናዶ እንዲሳካ አቶ ሠርፀፍሬ ስብሓት አዳራሽ በመስጠት ፣ ጋዜጠኛ ማህደረ ታሪኩ ፕሮጀክተር በመለገስ እንዲሁም አልፋ ውሃ፣ ለታዳሚዎች የመስተንግዶ ውሃ በማቅረብ መርሀ ግብሩ የተሳካ እንዲሆን አድርገዋል።
(በዕዝራ እጅጉ)
.የመዲናዋ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና እንዲያገኙ ወሰነ
#ethiopia | አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ ዛሬ ጋቢ በተደረበላቸው ዕለት ደስታቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር።
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት እነዚህ ጉምቱ ባለሙያዎች ከ 35 አመት በላይ በትጋት ያገለገሉ ሲሆን በሙያ አጋሮቻቸው ተከበው አድናቆት ሲቸራቸው ውለዋል።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም ከ 4 ሰዓት ጀምሮ በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በተደረገው መርሀ ግብር የሚድያ ባለሙያዎች እና ወዳጆቻቸው ተገኝተው እኛም አመስጋኞቻችሁ ነን በማለት ለመርሀ ግብሩ ድምቀት ሰጥተዋል።
ባለሙያዎቹን ለማመስገን ራሱን የቻለ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን ይህም ኮሚቴ ባለሙያዎቹ በዘለቄታዊነት የሚታገዙበት መንገድ ያመቻቸ ነው።
ለዝግጅቱ መሳካት በተከፈተው የwhat is up ገፅ ኮሚቴው ውስጥ ተግባራቸውን የተወጡት ጥላሁን ካሣ ፣ሀብታሙ ድረስ ፣ሰለሞን ሀይለኢየሱስ፣ዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)፣ አለም ታደሰ፣ሠናይት ሀይሌ፣እሸቱ ገለቱ፣ ጌጡ ተመስገን እና ግደይ ገብረ ሲሆኑ እነርሱም በዕለቱ እንደተናገሩት ሥራው በአጭር ጊዜ ታስቦ ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ለአንጋፋ ባለሙያዎቹ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና የሚያገኙበት መንገድ ያመቻቸ ሲሆን ይህ የመረዳዳት ባህል ወደፊትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተነግሯል።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
"ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን "የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች እንደነበሩ በዕለቱ ምስክርነት የሰጡ ባልደረቦቻቸው የተናገሩ ሲሆን የምስጋና ቀን መዘጋጀቱ አዲስ የሚመጣውንም ባለሙያ የሚያበረታታ ነው ሲሉ ሀሣብ ሰንዝረዋል።
በዕለቱ የሚድያ ሥራን ከ1950ዎቹ ጀምሮ ያስቃኘ አጭር የትዝታ ዘጋቢ ፊልም የቀረበ ሲሆን ተመስጋኞቹ ከዚህ ቀደም አየር ላይ ያዋሏቸው ሥራዎችም በዕለቱ ለታደሙት እንግዶች ቀርበዋል።
በባልደረቦቻቸው የምስጋና ዝግጅት የተደረገላቸው አዲስአለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ እንደዛሬ ደስ ብሎንም አያውቅ ፣ ይህን መርሀ ግብር በተሳካ መንገድ ዕውን እንዲሆን የጣራችሁ ሁሉ ፈጣሪ መንገዳችሁን ያቃና ሲሉ መርቀዋል።
የአዘጋጅ ኮሚቴው አባል እሸቱ ገለቱ እንዳለው በኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚሠሩ ባልደረቦች የመጠያየቅ ባህልን ከጀመሩ ሁለት አመት እንደሆናቸው ጠቅሰው ይህ የምስጋና መርሀ ግብር የዚያ መጠያየቅ አካል እንደሆነ ጠቁሟል።
ባለሙያዎች ጡረታ ሲወጡ የሚደገፉበት፣ በተለይም በኢኮኖሚ እገዛ የሚያገኙበት ስልት መነደፍ እንዳለበትም ጋዜጠኛ እሸቱ ጥቆማ ሰጥቷል። በተጨማሪም የጤና ሁኔታቸውን፣ የሚከታተሉበት መንገድ መፈጠር እንዳለበትም ተናግሯል።
ከጡረታ በኃላ ምክር በመስጠት ባለሙያዎቹ ልምዳቸውን ማጋራት አለባቸውም ብሏል።ይህንኑ ትልቅ ርዕይ ለማሳካት መንግሥትና የሚመለከታቸው የሚድያ ማህበራት ሊተባበሩ ይገባልም ሲል ሀሣብ አንስቷል።
የእለቱን የምስጋና መሰናዶ እንዲሳካ አቶ ሠርፀፍሬ ስብሓት አዳራሽ በመስጠት ፣ ጋዜጠኛ ማህደረ ታሪኩ ፕሮጀክተር በመለገስ እንዲሁም አልፋ ውሃ፣ ለታዳሚዎች የመስተንግዶ ውሃ በማቅረብ መርሀ ግብሩ የተሳካ እንዲሆን አድርገዋል።
13 days ago
ክንዱ የማይታጠፈው የጀግኖች አምባ!
****************
እስቲ ለአፍታ ቆም ብለን እናስብ፤ የዛሬዋ ኢትዮጵያ የጸጥታና የሉዓላዊነት ምሽግ ምን ያህል ጠንካራ ነው? የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዛሬ የተረከበውን ሀገራዊ አደራ ታሪክን በሚቀይር የልህቀት ከፍታ ላይ አድርሶታል።
እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ በልዩ የሀገር ፍቅር ስሜት እና በጽኑ ኩራት የሚያስደምመው ይህ ተቋም፣ በጥልቅ ሪፎርም ዳግም የተወለደ የሉዓላዊነታችን ሕያው ምሽግ ነው። ሠራዊታችን ዛሬ በተግባር ያረጋገጠው አቅም የውጊያ ክህሎትን ማሳደግ ብቻ አይደለም።
ከዚያም በዘለለ፤ ጦርነትን ቀድሞ የማስቀረት፣ የጥፋት ሥጋትን ገና በእንጭጩ የማምከን እና በማያዳግም የቅድመ መከላከል (Deterrence) ሳይንሳዊ ስትራቴጂ ጠላትን የማንበርከክ እጅግ የላቀ አቅም ነው።
ጠላት ክፉ አስቦት ወደ ኋላ በድንጋጤ እንዲያፈገፍግ የሚያደርገው ይህ ዘመኑን የሚዋጅ ወታደራዊ ጥበብ፣ ኢትዮጵያን የማትደፈር የብረት አጥር አድርጓታል።
በምድር ላይ ከሚታየው አንበሳ መሰል የውጊያ ጀግንነት፣ በአየር ላይ ካለው ንስራዊ የበላይነት፣ እንዲሁም ከሁለት አሥርት ዓመታት በኋላ ዳግም ተቋቁሞ የቀይ ባሕርን ቀጣና በንቃት ከሚቃኘው የባሕር ኃይላችን ልዕልና ጀርባ ያለው ትልቁ ምሥጢር፤ በቴክኖሎጂ የታጀበው ታሪካዊ የተቋም ሪፎርም ነው።
በተለይም ዘመናዊ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን (UAVs)፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን እና ዘመን አመጣሽ የጦር ቴክኖሎጂዎችን በላቀ የሳይበር አቅም በማዋሃድ የገነባው የኤሮስፔስ ልዕልና፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ቀጣናዊ አስፈሪ ኃይል አድርጓታል።
የዘመኑ ሳይንስ በከፍተኛ ደረጃ ያስታጠቃቸው፣ በሥነ ልቦና የገዘፉት የሠራዊቱ አባላት፣ ኢትዮጵያን በላቀ የውጊያ ጥበብ የሚጠብቁ የብረት ካስማዎች ናቸው።
ይህ ታሪካዊና እጅግ ስኬታማ ሪፎርም "ሀገር አስቀድም፣ ራስ አስቀጣይና ብቃት ያለው ተቋም ፍጠር" በሚል የጠለቀ ፖለቲካዊና ተቋማዊ ፍልስፍና የተመራ ነው። መከላከያችን ዛሬ የጦርነት ጋሻችን ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የልማት አቅም፣ የሰላም ኢንጂን እና የሽግግሩ ዘመን ታማኝ ዋልታ ነው።
ሠራዊቱ የፈጠረው ቴክኖሎጂያዊ እና ሳይንሳዊ ብቃት ለሀገር የልማት ጉዞ፣ ለመሠረተ ልማት ደኅንነት እና ለኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነታችን ጥበቃ ትልቅ ትሩፋት እያበረከተ ይገኛል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የነገዋን፣ በለጽጋና ተከብራ የምትኖረውን ጠንካራ ኢትዮጵያ እውን የሚያደርግ የኩራታችን ምንጭ ነው።
ኢትዮጵያ የቱንም ያህል ውጫዊና ውስጣዊ ፈተና ቢገጥማት፣ ይህ በቴክኖሎጂ የረቀቀ፣ በሳይንስ የላቀ፣ ጦርነትን አስቀድሞ በማምከን ዘላቂ ሰላምን የሚያጸና አሸናፊ ኃይል እስካላት ድረስ፣ የማትበገር የነጻነት አምባ ሆና ለዘላለም ትቀጥላለች! ክብራችን፣ ጋሻችን፣ እና የዘመኑ የቴክኖሎጂ ምሽጋችን ለሆነው ጀግናው ሠራዊታችን ማለቂያ የሌለው ክብር ይገባል!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #endf #sovereignty #militarycapability
****************
እስቲ ለአፍታ ቆም ብለን እናስብ፤ የዛሬዋ ኢትዮጵያ የጸጥታና የሉዓላዊነት ምሽግ ምን ያህል ጠንካራ ነው? የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዛሬ የተረከበውን ሀገራዊ አደራ ታሪክን በሚቀይር የልህቀት ከፍታ ላይ አድርሶታል።
እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ በልዩ የሀገር ፍቅር ስሜት እና በጽኑ ኩራት የሚያስደምመው ይህ ተቋም፣ በጥልቅ ሪፎርም ዳግም የተወለደ የሉዓላዊነታችን ሕያው ምሽግ ነው። ሠራዊታችን ዛሬ በተግባር ያረጋገጠው አቅም የውጊያ ክህሎትን ማሳደግ ብቻ አይደለም።
ከዚያም በዘለለ፤ ጦርነትን ቀድሞ የማስቀረት፣ የጥፋት ሥጋትን ገና በእንጭጩ የማምከን እና በማያዳግም የቅድመ መከላከል (Deterrence) ሳይንሳዊ ስትራቴጂ ጠላትን የማንበርከክ እጅግ የላቀ አቅም ነው።
ጠላት ክፉ አስቦት ወደ ኋላ በድንጋጤ እንዲያፈገፍግ የሚያደርገው ይህ ዘመኑን የሚዋጅ ወታደራዊ ጥበብ፣ ኢትዮጵያን የማትደፈር የብረት አጥር አድርጓታል።
በምድር ላይ ከሚታየው አንበሳ መሰል የውጊያ ጀግንነት፣ በአየር ላይ ካለው ንስራዊ የበላይነት፣ እንዲሁም ከሁለት አሥርት ዓመታት በኋላ ዳግም ተቋቁሞ የቀይ ባሕርን ቀጣና በንቃት ከሚቃኘው የባሕር ኃይላችን ልዕልና ጀርባ ያለው ትልቁ ምሥጢር፤ በቴክኖሎጂ የታጀበው ታሪካዊ የተቋም ሪፎርም ነው።
በተለይም ዘመናዊ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን (UAVs)፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን እና ዘመን አመጣሽ የጦር ቴክኖሎጂዎችን በላቀ የሳይበር አቅም በማዋሃድ የገነባው የኤሮስፔስ ልዕልና፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ቀጣናዊ አስፈሪ ኃይል አድርጓታል።
የዘመኑ ሳይንስ በከፍተኛ ደረጃ ያስታጠቃቸው፣ በሥነ ልቦና የገዘፉት የሠራዊቱ አባላት፣ ኢትዮጵያን በላቀ የውጊያ ጥበብ የሚጠብቁ የብረት ካስማዎች ናቸው።
ይህ ታሪካዊና እጅግ ስኬታማ ሪፎርም "ሀገር አስቀድም፣ ራስ አስቀጣይና ብቃት ያለው ተቋም ፍጠር" በሚል የጠለቀ ፖለቲካዊና ተቋማዊ ፍልስፍና የተመራ ነው። መከላከያችን ዛሬ የጦርነት ጋሻችን ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የልማት አቅም፣ የሰላም ኢንጂን እና የሽግግሩ ዘመን ታማኝ ዋልታ ነው።
ሠራዊቱ የፈጠረው ቴክኖሎጂያዊ እና ሳይንሳዊ ብቃት ለሀገር የልማት ጉዞ፣ ለመሠረተ ልማት ደኅንነት እና ለኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነታችን ጥበቃ ትልቅ ትሩፋት እያበረከተ ይገኛል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የነገዋን፣ በለጽጋና ተከብራ የምትኖረውን ጠንካራ ኢትዮጵያ እውን የሚያደርግ የኩራታችን ምንጭ ነው።
ኢትዮጵያ የቱንም ያህል ውጫዊና ውስጣዊ ፈተና ቢገጥማት፣ ይህ በቴክኖሎጂ የረቀቀ፣ በሳይንስ የላቀ፣ ጦርነትን አስቀድሞ በማምከን ዘላቂ ሰላምን የሚያጸና አሸናፊ ኃይል እስካላት ድረስ፣ የማትበገር የነጻነት አምባ ሆና ለዘላለም ትቀጥላለች! ክብራችን፣ ጋሻችን፣ እና የዘመኑ የቴክኖሎጂ ምሽጋችን ለሆነው ጀግናው ሠራዊታችን ማለቂያ የሌለው ክብር ይገባል!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #endf #sovereignty #militarycapability
14 days ago
በህይወት ያለን እንመሰጋገን
አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስአለምና በልሁ ሊመሰነጉ ነው
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ የምስጋና መርሀ ግብር ሊደረግላቸው ነው።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በሚደረገው የምስጋና መርሀ ግብር የባለሙያዎቹ አድናቂዎች እና ወዳጆች ይታደማሉ።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ባለሙያዎችን የማገዝ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች ሲሆኑ ነገር ግን በኑሮ መደገፍ እና መመስገን ያለባቸው በመሆኑ ለዚህ መርሀ ግብር ኮሚቴ ተዋቅሮ እየተሠራ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስአለምና በልሁ ሊመሰነጉ ነው
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ የምስጋና መርሀ ግብር ሊደረግላቸው ነው።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በሚደረገው የምስጋና መርሀ ግብር የባለሙያዎቹ አድናቂዎች እና ወዳጆች ይታደማሉ።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ባለሙያዎችን የማገዝ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች ሲሆኑ ነገር ግን በኑሮ መደገፍ እና መመስገን ያለባቸው በመሆኑ ለዚህ መርሀ ግብር ኮሚቴ ተዋቅሮ እየተሠራ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) በሆሊውድ ዝነኛ የብሎክባስተር ፊልሞች "Godzilla vs. Kong" እና "Godzilla x Kong: The New Empire" ላይ “ጂያ” የተሰኘውን ቁልፍ ገጸ-ባህሪ በመወከል የምትታወቀው የ18 ዓመቷ መስማት የተሳናት ወጣት ተዋናይት ኬይሊ ሆትል ማክሰኞ ጠዋት በደረሰባት ድንገተኛ የመኪና አደጋ ሕይወቷ ማለፉን ፎክስ ኒውስ ዲጂታል አረጋግጧል።
የተዋናይቷ አባት ጆሹዋ ሆትል በሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ስለደረሰው አደጋ በሰጠውና በፌስቡክ በኩል ባስተላለፈው የ23 ደቂቃ የአሜሪካ የምልክት ቋንቋ (ASL) ቀጥታ ስርጭት መግለጫ፣ ልጁ ወደ ሆስፒታል በመጓዝ ላይ እያለች ልቧ መቆሙን በለቅሶ አስታውቋል። ከተከታታይ መስማት የተሳናቸው ትውልዶች በተገኘችውና የቨርጂኒያ ተወላጅ በሆነችው ኬይሊ ሆትል ሞት ሳቢያ መላው የሆሊውድ የኪነ-ጥበብ ማኅበረሰብ በከባድ ሐዘን ውስጥ ወድቋል።
ይህንን ልብ ሰባሪ ክስተት እና የተዋናይቷን አጭር የሕይወት ጉዞ በጥልቀት ስንመለከተው ኬይሊ በሆሊውድ ውስጥ በገንዘብና በጥቅም ብቻ በሚመራው የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ መስማት ለተሳናቸው አካላት እውነተኛና ተጨባጭ የውክልና መድረክ የፈጠረች ስልታዊ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆኗን ያሳያል። በ2021 ዓ.ም. “ጎድዚላ ቨርሰስ ኮንግ” በተሰኘው ታላቅ ፊልም ላይ ከግዙፉ “ኮንግ” ጋር ልዩ የልብ ትስስር ያላትን የጂያን ገጸ-ባህሪ ወክላ ስትወጣ፣ በሆሊውድ ታሪክ ውስጥ መስማት የተሳናቸው ተዋናዮች በትልልቅ የሳይንስ ልብወለድ ፊልሞች ላይ የመሪነት ሚና መጫወት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየች ድንቅ ተሰጥኦ ነበረች።
በ2024 ዓ.ም. በወጣው ሁለተኛው ፊልም ላይም የምልክት ቋንቋን በፊልሙ ውስጥ በስፋት በማስተዋወቅ የራሷን ደማቅ አሻራ አኑራለች።
በተጨማሪም፣ ኬይሊ ሆትል ወደ ትልቁ የፊልም ዓለም ከመግባቷ በፊትም ቢሆን በተለያዩ የንግድ ማስታወቂያዎችና የጥበቃ ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ መስማት ለተሳናቸው ማኅበረሰቦች እኩል ዕድል እንዲሰጥ ስትሟገት የቆየች የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ጭምር ነበረች። ምንም እንኳን ገና በለጋ ዕድሜዋ መክሰሟ እና በሲኒማው ዓለም የጀመረችው ደማቅ ጉዞ በአሰቃቂ የመኪና አደጋ በአጭር የተቀጨ ቢሆንም፣ በሆሊውድ ውስጥ ያሉ መስማት የተሳናቸው ወጣት ተዋናዮች የወደፊት ዕድል እንዲቀየርና ማግለል እንዲቆም ያደረገችው ተጋድሎ ግን ዘላቂ ውርስ ሆኖ የሚቀጥል መሆኑን የፊልም ኢንዱስትሪ ተንታኞች በጥብቅ ያመለክታሉ።
የተዋናይቷ አባት ጆሹዋ ሆትል በሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ስለደረሰው አደጋ በሰጠውና በፌስቡክ በኩል ባስተላለፈው የ23 ደቂቃ የአሜሪካ የምልክት ቋንቋ (ASL) ቀጥታ ስርጭት መግለጫ፣ ልጁ ወደ ሆስፒታል በመጓዝ ላይ እያለች ልቧ መቆሙን በለቅሶ አስታውቋል። ከተከታታይ መስማት የተሳናቸው ትውልዶች በተገኘችውና የቨርጂኒያ ተወላጅ በሆነችው ኬይሊ ሆትል ሞት ሳቢያ መላው የሆሊውድ የኪነ-ጥበብ ማኅበረሰብ በከባድ ሐዘን ውስጥ ወድቋል።
ይህንን ልብ ሰባሪ ክስተት እና የተዋናይቷን አጭር የሕይወት ጉዞ በጥልቀት ስንመለከተው ኬይሊ በሆሊውድ ውስጥ በገንዘብና በጥቅም ብቻ በሚመራው የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ መስማት ለተሳናቸው አካላት እውነተኛና ተጨባጭ የውክልና መድረክ የፈጠረች ስልታዊ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆኗን ያሳያል። በ2021 ዓ.ም. “ጎድዚላ ቨርሰስ ኮንግ” በተሰኘው ታላቅ ፊልም ላይ ከግዙፉ “ኮንግ” ጋር ልዩ የልብ ትስስር ያላትን የጂያን ገጸ-ባህሪ ወክላ ስትወጣ፣ በሆሊውድ ታሪክ ውስጥ መስማት የተሳናቸው ተዋናዮች በትልልቅ የሳይንስ ልብወለድ ፊልሞች ላይ የመሪነት ሚና መጫወት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየች ድንቅ ተሰጥኦ ነበረች።
በ2024 ዓ.ም. በወጣው ሁለተኛው ፊልም ላይም የምልክት ቋንቋን በፊልሙ ውስጥ በስፋት በማስተዋወቅ የራሷን ደማቅ አሻራ አኑራለች።
በተጨማሪም፣ ኬይሊ ሆትል ወደ ትልቁ የፊልም ዓለም ከመግባቷ በፊትም ቢሆን በተለያዩ የንግድ ማስታወቂያዎችና የጥበቃ ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ መስማት ለተሳናቸው ማኅበረሰቦች እኩል ዕድል እንዲሰጥ ስትሟገት የቆየች የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ጭምር ነበረች። ምንም እንኳን ገና በለጋ ዕድሜዋ መክሰሟ እና በሲኒማው ዓለም የጀመረችው ደማቅ ጉዞ በአሰቃቂ የመኪና አደጋ በአጭር የተቀጨ ቢሆንም፣ በሆሊውድ ውስጥ ያሉ መስማት የተሳናቸው ወጣት ተዋናዮች የወደፊት ዕድል እንዲቀየርና ማግለል እንዲቆም ያደረገችው ተጋድሎ ግን ዘላቂ ውርስ ሆኖ የሚቀጥል መሆኑን የፊልም ኢንዱስትሪ ተንታኞች በጥብቅ ያመለክታሉ።
17 days ago
ዓለምን ዳግም ወደ ስጋት የከተተው የቴህራን እና ዋሽንግተን ወታደራዊ ግጭት
**********************
ባለፈው ወር በፓኪስታን አጋዥነት የተደረሰው የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ መፍረሱን ተከትሎ፣ በሁለቱ ኃይላት መካከል ለቀናት የቀጠለው ጥቃት የቀጣናውን የጸጥታና የዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ መስመር ከባድ ሥጋት ላይ ጥሎታል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፍ ሕግጋትን ወደ መጣስ እና የኒውክሌር ተቋማትን ወደ ማጥቃት የተሸጋገረው ይህ አደገኛ ምዕራፍ፣ መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ሊከተው የሚችል አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የግጭቱ መነሻ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ይፋ ባደረገው መግለጫ መሠረት፣ በዮርዳኖስ በሚገኝ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ በተሰነዘረ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውንና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች መውደማቸውን ተከትሎ የተከሰተ ነው።
ዋሽንግተን ለዚህ አጸፋዊ ምላሽ ይሆን ዘንድ በደቡባዊና ደቡብ ምዕራብ ኢራን በሚገኘው የዳርክሆቨይን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ ቦታ ላይ ሳይቀር ያነጣጠረ የሚሳኤል ጥቃት ፈጽማለች።
ፔንታገን ጥቃቱን በቀጥታ ከማረጋገጥም ሆነ ከመካድ የተቆጠበ ቢሆንም፣ "አሜሪካ ወታደሮቿን ከጥቃት ለመከላከልና የኢራንን የማጥቃት አቅም ለማዳከም ማንኛውንም እርምጃ ትወስዳለች" ሲል ድርጊቱን በተዘዋዋሪ ተከላክሏል፤ ጥቃቶቹም በዋናነት የኢራንን ወታደራዊ የሎጅስቲክስ መሠረተ-ልማቶች ላይ ያነጣጠሩ መሆቸውን ትሟገታለች።
ይሁን እንጂ የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ጥቃቱን "የሀገሪቱን የሳይንስ ዕድገትና ነጻነት ለማደናቀፍ የታለመ አረመኔያዊ የሽብር ድርጊት" ሲል በጽኑ ኮንኖታል።
ቴህራን ተቋሙ ሙሉ በሙሉ ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የደኅንነት ጥበቃ ሥርዓት ተገዢና ሰላማዊ መሆኑን በመጥቀስ፣ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሕግን በግልጽ መጣሷን አስታውቃለች።
በአሜሪካ የአየር ጥቃቶች ሳቢያ እስካሁን በኢራን ቢያንስ 50 ሰዎች መገደላቸውንና ከ500 በላይ መቁሰላቸውን የገለጸው የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር፣ በርካታ ድልድዮችና ሲቪል መሠረተ-ልማቶች መውደማቸውን አረጋግጧል።
ለአሜሪካ ጥቃት የኢራን ወታደራዊ ምላሽ ፈጣንና መጠነ-ሰፊ የነበረ ሲሆን፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኃይል "ናስር-2" የተሰኘውንና 20ኛ ምዕራፍ ላይ የደረሰውን የሚሳኤልና የድሮን ጥቃት የሰነዘረ ሲሆን፣ የኢራን መደበኛ ጦር በበኩሉ "ሳዕቃ" የተሰኘውን 15ኛ ምዕራፍ የጥቃት ዘመቻ አካሂዷል።
በጥቃቶቹ በኩዌት የሚገኘው አሊ አል-ሳሌም የአየር ኃይል ሰፈር፣ ካምፕ አሪፍጃን፣ ካምፕ አዳይሪ እና ሚና አብዱላህ የተሰኘው የሎጂስቲክስ ማዕከል በከባድ ሁኔታ ተመተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ፣ በባህሬን የሚገኘው የአሜሪካ አምስተኛ ፍሊት ዋና መሥሪያ ቤት እና በዮርዳኖስ በሚገኘው አል-አዝራቅ የአየር ኃይል ሰፈር ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። ምንም እንኳ የአሜሪካ እና የባሕረ-ሰላጤው አገራት መከላከያ ተቋማት አብዛኞቹን የኢራን ሚሳኤሎችና ድሮኖች ማክሸፋቸውን በይፋ ቢገልጹም፣ የወጡ የሳተላይት ምስሎች ግን የተለየ እውነታ እያሳዩ ነው።
የዋሽንግተን ፖስት የምርመራ ሪፖርት እንደሚያመለክተው፣ በክልሉ በሚገኙ 15 የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ውስጥ የራዳር ሥርዓቶች፣ የፓትሪዮት መከላከያ መሣሪያዎች እና የመጋዘን ተቋማትን ጨምሮ 228 መዋቅሮች በከፊልም ሆነ በሙሉ መውደማቸውን አረጋግጧል።
ይህ ወታደራዊ መካረር በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ መናወጥን አስከትሏል። የኢራንን ይፋዊ አቤቱታ ተከትሎ፣ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ባወጡት መግለጫ፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች ቁጥር 444 እና 533 መሠረት፣ በሰላማዊ የኒውክሌር ተቋማት ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት ዓለም አቀፍ ሕግን የሚጥስ መሆኑን አስታውሰዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ በበኩላቸው፣ የኒውክሌር ተቋማትን ኢላማ ማድረግ የቀጣናውን ውጥረት ወደማይመለስ አደገኛ አደጋ ሊቀይረው እንደሚችል አስጠንቅቀው፣ የጸጥታው ምክር ቤት በአስቸኳይ እንዲመክርና ሁለቱም ወገኖች ራስን የመግታት እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል።
"የኒውክሌር መሠረተ-ልማቶችን ማጥቃት ቀጣናውን ብቻ ሳይሆን መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ውስጥ የሚከት አደገኛ ድርጊት ነው" የሚለው የሰላም ጥሪ መግለጫ የሁኔታውን አሳሳቢነት በግልጽ ያሳያል።
በፖለቲካው ረገድ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የቃላት መለዋወጥ ይበልጥ ጠንክሯል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን በኩዌትና ባህሬን ላሉት የጦር ሰፈሮቿ ተጨማሪ የአየር መከላከያ ዘዴዎችን በፍጥነት ለማስፈር እያቀደች መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ኢራን የኒውክሌር ታጣቂ እንድትሆን ፈጽሞ እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን መንፈሣዊ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ እና የፓርላማው አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባቄር ቃሊባፍ፣ ዋሽንግተን ስምምነቱን በተጠቀሰው መሠረት ደጋግማ መጣሷ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ፊርማ ፍጹም ዋጋ ቢስ መሆኑን ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የሀገሪቱን ደኅንነት ለማረጋገጥ መላው የኢራን ሕዝብ ቅዱስ ያሉት "አንድነት" እንዲኖረው ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዋሽንግተን በኢራን ወደቦች ላይ የባሕር እገዳ ለመጣል መሞከሯን ተከትሎ፣ ቴህራን በበኩሏ የዓለም የነዳጅ ንግድ ወሳኝ የደም ሥር የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥ ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆኑን አውጃለች።
ይህንን የባሕረ-ሰላጤው መዘጋት ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋ (Brent Crude) በአንድ ጀምበር ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ተንታኞች ውጥረቱ በዚህ የሚቀጥል ከሆነ በተለይ በእስያ እና በአውሮፓ አገራት ላይ ከባድ የነዳጅ እጥረትና የዋጋ ግሽበት ሊከሰት እንደሚችልና የንግድ መርከቦች ረጅም ርቀት ወደሚጠይቀው የአፍሪካ አቅጣጫ መስመራቸውን ለመቀየር እየተገደዱ መሆኑን እየገለጹ ይገኛሉ።
ፍጥጫው ወታደራዊ ጡንቻን ከማሳየት አልፎ የዓለምን መደበኛ የኢኮኖሚና የጸጥታ መዋቅር የቀየረ ታሪካዊ ቀውስ ሆኗል።
በሰለሞን ገዳ
**********************
ባለፈው ወር በፓኪስታን አጋዥነት የተደረሰው የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ መፍረሱን ተከትሎ፣ በሁለቱ ኃይላት መካከል ለቀናት የቀጠለው ጥቃት የቀጣናውን የጸጥታና የዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ መስመር ከባድ ሥጋት ላይ ጥሎታል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፍ ሕግጋትን ወደ መጣስ እና የኒውክሌር ተቋማትን ወደ ማጥቃት የተሸጋገረው ይህ አደገኛ ምዕራፍ፣ መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ሊከተው የሚችል አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የግጭቱ መነሻ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ይፋ ባደረገው መግለጫ መሠረት፣ በዮርዳኖስ በሚገኝ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ በተሰነዘረ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውንና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች መውደማቸውን ተከትሎ የተከሰተ ነው።
ዋሽንግተን ለዚህ አጸፋዊ ምላሽ ይሆን ዘንድ በደቡባዊና ደቡብ ምዕራብ ኢራን በሚገኘው የዳርክሆቨይን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ ቦታ ላይ ሳይቀር ያነጣጠረ የሚሳኤል ጥቃት ፈጽማለች።
ፔንታገን ጥቃቱን በቀጥታ ከማረጋገጥም ሆነ ከመካድ የተቆጠበ ቢሆንም፣ "አሜሪካ ወታደሮቿን ከጥቃት ለመከላከልና የኢራንን የማጥቃት አቅም ለማዳከም ማንኛውንም እርምጃ ትወስዳለች" ሲል ድርጊቱን በተዘዋዋሪ ተከላክሏል፤ ጥቃቶቹም በዋናነት የኢራንን ወታደራዊ የሎጅስቲክስ መሠረተ-ልማቶች ላይ ያነጣጠሩ መሆቸውን ትሟገታለች።
ይሁን እንጂ የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ጥቃቱን "የሀገሪቱን የሳይንስ ዕድገትና ነጻነት ለማደናቀፍ የታለመ አረመኔያዊ የሽብር ድርጊት" ሲል በጽኑ ኮንኖታል።
ቴህራን ተቋሙ ሙሉ በሙሉ ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የደኅንነት ጥበቃ ሥርዓት ተገዢና ሰላማዊ መሆኑን በመጥቀስ፣ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሕግን በግልጽ መጣሷን አስታውቃለች።
በአሜሪካ የአየር ጥቃቶች ሳቢያ እስካሁን በኢራን ቢያንስ 50 ሰዎች መገደላቸውንና ከ500 በላይ መቁሰላቸውን የገለጸው የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር፣ በርካታ ድልድዮችና ሲቪል መሠረተ-ልማቶች መውደማቸውን አረጋግጧል።
ለአሜሪካ ጥቃት የኢራን ወታደራዊ ምላሽ ፈጣንና መጠነ-ሰፊ የነበረ ሲሆን፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኃይል "ናስር-2" የተሰኘውንና 20ኛ ምዕራፍ ላይ የደረሰውን የሚሳኤልና የድሮን ጥቃት የሰነዘረ ሲሆን፣ የኢራን መደበኛ ጦር በበኩሉ "ሳዕቃ" የተሰኘውን 15ኛ ምዕራፍ የጥቃት ዘመቻ አካሂዷል።
በጥቃቶቹ በኩዌት የሚገኘው አሊ አል-ሳሌም የአየር ኃይል ሰፈር፣ ካምፕ አሪፍጃን፣ ካምፕ አዳይሪ እና ሚና አብዱላህ የተሰኘው የሎጂስቲክስ ማዕከል በከባድ ሁኔታ ተመተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ፣ በባህሬን የሚገኘው የአሜሪካ አምስተኛ ፍሊት ዋና መሥሪያ ቤት እና በዮርዳኖስ በሚገኘው አል-አዝራቅ የአየር ኃይል ሰፈር ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። ምንም እንኳ የአሜሪካ እና የባሕረ-ሰላጤው አገራት መከላከያ ተቋማት አብዛኞቹን የኢራን ሚሳኤሎችና ድሮኖች ማክሸፋቸውን በይፋ ቢገልጹም፣ የወጡ የሳተላይት ምስሎች ግን የተለየ እውነታ እያሳዩ ነው።
የዋሽንግተን ፖስት የምርመራ ሪፖርት እንደሚያመለክተው፣ በክልሉ በሚገኙ 15 የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ውስጥ የራዳር ሥርዓቶች፣ የፓትሪዮት መከላከያ መሣሪያዎች እና የመጋዘን ተቋማትን ጨምሮ 228 መዋቅሮች በከፊልም ሆነ በሙሉ መውደማቸውን አረጋግጧል።
ይህ ወታደራዊ መካረር በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ መናወጥን አስከትሏል። የኢራንን ይፋዊ አቤቱታ ተከትሎ፣ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ባወጡት መግለጫ፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች ቁጥር 444 እና 533 መሠረት፣ በሰላማዊ የኒውክሌር ተቋማት ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት ዓለም አቀፍ ሕግን የሚጥስ መሆኑን አስታውሰዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ በበኩላቸው፣ የኒውክሌር ተቋማትን ኢላማ ማድረግ የቀጣናውን ውጥረት ወደማይመለስ አደገኛ አደጋ ሊቀይረው እንደሚችል አስጠንቅቀው፣ የጸጥታው ምክር ቤት በአስቸኳይ እንዲመክርና ሁለቱም ወገኖች ራስን የመግታት እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል።
"የኒውክሌር መሠረተ-ልማቶችን ማጥቃት ቀጣናውን ብቻ ሳይሆን መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ውስጥ የሚከት አደገኛ ድርጊት ነው" የሚለው የሰላም ጥሪ መግለጫ የሁኔታውን አሳሳቢነት በግልጽ ያሳያል።
በፖለቲካው ረገድ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የቃላት መለዋወጥ ይበልጥ ጠንክሯል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን በኩዌትና ባህሬን ላሉት የጦር ሰፈሮቿ ተጨማሪ የአየር መከላከያ ዘዴዎችን በፍጥነት ለማስፈር እያቀደች መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ኢራን የኒውክሌር ታጣቂ እንድትሆን ፈጽሞ እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን መንፈሣዊ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ እና የፓርላማው አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባቄር ቃሊባፍ፣ ዋሽንግተን ስምምነቱን በተጠቀሰው መሠረት ደጋግማ መጣሷ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ፊርማ ፍጹም ዋጋ ቢስ መሆኑን ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የሀገሪቱን ደኅንነት ለማረጋገጥ መላው የኢራን ሕዝብ ቅዱስ ያሉት "አንድነት" እንዲኖረው ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዋሽንግተን በኢራን ወደቦች ላይ የባሕር እገዳ ለመጣል መሞከሯን ተከትሎ፣ ቴህራን በበኩሏ የዓለም የነዳጅ ንግድ ወሳኝ የደም ሥር የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥ ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆኑን አውጃለች።
ይህንን የባሕረ-ሰላጤው መዘጋት ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋ (Brent Crude) በአንድ ጀምበር ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ተንታኞች ውጥረቱ በዚህ የሚቀጥል ከሆነ በተለይ በእስያ እና በአውሮፓ አገራት ላይ ከባድ የነዳጅ እጥረትና የዋጋ ግሽበት ሊከሰት እንደሚችልና የንግድ መርከቦች ረጅም ርቀት ወደሚጠይቀው የአፍሪካ አቅጣጫ መስመራቸውን ለመቀየር እየተገደዱ መሆኑን እየገለጹ ይገኛሉ።
ፍጥጫው ወታደራዊ ጡንቻን ከማሳየት አልፎ የዓለምን መደበኛ የኢኮኖሚና የጸጥታ መዋቅር የቀየረ ታሪካዊ ቀውስ ሆኗል።
በሰለሞን ገዳ
17 days ago
የ4 ሺህ ድምፆች ውክልና፡- ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል ሲያድስ
*********************
የጥይት ቋንቋን በሰለጠነ የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት የጦር ሜዳ ጀግንነትን ደግሞ በሐሳብ ልዕልና ለመተካት የሚያስችለው አዲስ የታሪክ ምዕራፍ በኢትዮጵያ ተከፍቷል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን 4 ሺህ ተመካካሪዎች ያካተተውን ሰፊ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን ተከትሎ፣ ይህ ታሪካዊ ክስተት ሀገራችን ከጦርነት አዙሪት ወጥታ ወደ ዘላቂ ሰላምና የሀገር ግንባታ የምትሸጋገርበት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተመላክቷል።
በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በማኅበረሰቡ ዘንድ እንደ ገዳ እና የሽምግልና ሥርዓቶች ያሉ የዳበረ የውይይትና የችግር አፈታት ባህል ቢኖርም፣ የፖለቲካው ማኅበረሰብ ግን ከዚህ እሴት ባለመቅዳቱ "አሸናፊ ወደ ቤተመንግሥት፣ ተሸናፊ ወደ ግዞት" የሚል አጥፊ የፖለቲካ ባህል ስር ሰዶ ቆይቷል።
ይሁንና አሁን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ይህንን የተዛባ የፖለቲካ ትርክት በማረም ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ሂደት ነው።
በጉዳዩ ዙሪያ ሙያዊ ትንታኔያቸውን የሰጡት የማኅበራዊ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪው ረዳት ፕሮፌሰር ጌትነት ተሾመ ኢትዮጵያ ጠንካራ የመንግሥት ምስረታ ታሪክ ያላት ሀገር ብትሆንም፣ በውስጣዊ ክፍፍሎች እና የውጭ ኃይሎች የጂኦ-ፖለቲካ ፍላጎት ምክንያት በሚፈለገው ልክ ማደግ አለመቻሏን ይገልጻሉ።
ይሁንና በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በከተማ ልማት እና በዲፕሎማሲ እያስመዘገበች ያለችውን አበረታች ዕድገት ለማስቀጠል፣ ሀገራዊ ምክክሩ ወቅታዊ እና ወሳኝ መድኃኒት መሆኑን አስምረውበታል።
በየትኛውም የዓለም ክፍል ጦርነት ትርፍ አምጥቶ እንደማያውቅና ይልቁንም አምራች ኃይልን እና ሀገራዊ ኢኮኖሚን እንደሚያወድም ያነሱት ምሁሩ፣ የፖለቲካ ልሂቃን፣ የሚዲያ አካላት እና የሃይማኖት አባቶች አጀንዳዎቻቸውን ኦዲት በማድረግ ለትውልድ የሚሻገር ሀገር ለመገንባት በጋራ ሊቆሙ ይገባል ብለዋል፡፡
በየትኛውም ስሌት የምክክር መድረኩን መጀመር በራሱ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ሰላም እና ልማት ለሚሹ ኃይሎች ታላቅ ድል ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ኢትዮጵያ በርካታ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁማ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራዊ ስኬቶችን ማስመዝገብ የቻለች ሲሆን፣ አሁን ደግሞ ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ መሆን ያለበት ዘላቂ የሀገር ግንባታ ነው።
ሀገረ-መንግሥት የመመስረቱ ሂደት ቀደም ብሎ ቢጠናቀቅም በእኩልነትና በመተባበር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ አንድነትን ለመፍጠር መመካከር የግድ ይላል።
ባለፈው ታሪክ ውስጥ የተፈጠሩ ቁርሾዎችንና ህመሞችን በዛሬው ዘመን የሰብአዊ መብት መነጽር ከመመዘን ይልቅ፣ ያለፈውን እንደ መማሪያ በመውሰድ ለጋራ የወደፊት ራዕይ በጋራ መሥራት ያስፈልጋል፡፡
በዚህ ዘመን እውነተኛ ጀግንነት የሚለካው በጦር ሜዳ ሳይሆን፣ በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ የሰለጠነ ድርድር መሆኑንም ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡
ባለፉት አራት ዓመታት ሰፊ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየው ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ ከ1 ሺህ 200 በላይ ወረዳዎችን በማዳረስና የኅብረተሰቡን አንገብጋቢ አጀንዳዎች በማሰባሰብ የሁሉንም ድምፅ ያካተተ ዴሞክራሲያዊ ሂደት እያስኬደ ይገኛል።
መላው ማኅበረሰብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እየተሳተፈበት የሚገኘው ይህ መድረክ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ሁለት ዓመት ከመዋጋት፣ 20 ዓመት መወያየት ይሻላል" በማለት ያስቀመጡትን መርህ በተግባር የሚተረጉም ነው።
በመሆኑም፣ ይህ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በአንድ አዳራሽ የተሰባሰቡበት ታሪካዊ የምክክር መድረክ፣ ዜጎች ልዩነቶቻቸውን በሰለጠነ መንገድ በማንሸራሸር ለነገዋ ኢትዮጵያ ጠንካራ መሰረት የሚጥሉበት ወርቃማ እድል ነው፡፡
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogue #nationbuilding #ebcdotstream
*********************
የጥይት ቋንቋን በሰለጠነ የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት የጦር ሜዳ ጀግንነትን ደግሞ በሐሳብ ልዕልና ለመተካት የሚያስችለው አዲስ የታሪክ ምዕራፍ በኢትዮጵያ ተከፍቷል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን 4 ሺህ ተመካካሪዎች ያካተተውን ሰፊ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን ተከትሎ፣ ይህ ታሪካዊ ክስተት ሀገራችን ከጦርነት አዙሪት ወጥታ ወደ ዘላቂ ሰላምና የሀገር ግንባታ የምትሸጋገርበት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተመላክቷል።
በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በማኅበረሰቡ ዘንድ እንደ ገዳ እና የሽምግልና ሥርዓቶች ያሉ የዳበረ የውይይትና የችግር አፈታት ባህል ቢኖርም፣ የፖለቲካው ማኅበረሰብ ግን ከዚህ እሴት ባለመቅዳቱ "አሸናፊ ወደ ቤተመንግሥት፣ ተሸናፊ ወደ ግዞት" የሚል አጥፊ የፖለቲካ ባህል ስር ሰዶ ቆይቷል።
ይሁንና አሁን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ይህንን የተዛባ የፖለቲካ ትርክት በማረም ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ሂደት ነው።
በጉዳዩ ዙሪያ ሙያዊ ትንታኔያቸውን የሰጡት የማኅበራዊ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪው ረዳት ፕሮፌሰር ጌትነት ተሾመ ኢትዮጵያ ጠንካራ የመንግሥት ምስረታ ታሪክ ያላት ሀገር ብትሆንም፣ በውስጣዊ ክፍፍሎች እና የውጭ ኃይሎች የጂኦ-ፖለቲካ ፍላጎት ምክንያት በሚፈለገው ልክ ማደግ አለመቻሏን ይገልጻሉ።
ይሁንና በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በከተማ ልማት እና በዲፕሎማሲ እያስመዘገበች ያለችውን አበረታች ዕድገት ለማስቀጠል፣ ሀገራዊ ምክክሩ ወቅታዊ እና ወሳኝ መድኃኒት መሆኑን አስምረውበታል።
በየትኛውም የዓለም ክፍል ጦርነት ትርፍ አምጥቶ እንደማያውቅና ይልቁንም አምራች ኃይልን እና ሀገራዊ ኢኮኖሚን እንደሚያወድም ያነሱት ምሁሩ፣ የፖለቲካ ልሂቃን፣ የሚዲያ አካላት እና የሃይማኖት አባቶች አጀንዳዎቻቸውን ኦዲት በማድረግ ለትውልድ የሚሻገር ሀገር ለመገንባት በጋራ ሊቆሙ ይገባል ብለዋል፡፡
በየትኛውም ስሌት የምክክር መድረኩን መጀመር በራሱ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ሰላም እና ልማት ለሚሹ ኃይሎች ታላቅ ድል ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ኢትዮጵያ በርካታ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁማ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራዊ ስኬቶችን ማስመዝገብ የቻለች ሲሆን፣ አሁን ደግሞ ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ መሆን ያለበት ዘላቂ የሀገር ግንባታ ነው።
ሀገረ-መንግሥት የመመስረቱ ሂደት ቀደም ብሎ ቢጠናቀቅም በእኩልነትና በመተባበር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ አንድነትን ለመፍጠር መመካከር የግድ ይላል።
ባለፈው ታሪክ ውስጥ የተፈጠሩ ቁርሾዎችንና ህመሞችን በዛሬው ዘመን የሰብአዊ መብት መነጽር ከመመዘን ይልቅ፣ ያለፈውን እንደ መማሪያ በመውሰድ ለጋራ የወደፊት ራዕይ በጋራ መሥራት ያስፈልጋል፡፡
በዚህ ዘመን እውነተኛ ጀግንነት የሚለካው በጦር ሜዳ ሳይሆን፣ በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ የሰለጠነ ድርድር መሆኑንም ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡
ባለፉት አራት ዓመታት ሰፊ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየው ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ ከ1 ሺህ 200 በላይ ወረዳዎችን በማዳረስና የኅብረተሰቡን አንገብጋቢ አጀንዳዎች በማሰባሰብ የሁሉንም ድምፅ ያካተተ ዴሞክራሲያዊ ሂደት እያስኬደ ይገኛል።
መላው ማኅበረሰብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እየተሳተፈበት የሚገኘው ይህ መድረክ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ሁለት ዓመት ከመዋጋት፣ 20 ዓመት መወያየት ይሻላል" በማለት ያስቀመጡትን መርህ በተግባር የሚተረጉም ነው።
በመሆኑም፣ ይህ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በአንድ አዳራሽ የተሰባሰቡበት ታሪካዊ የምክክር መድረክ፣ ዜጎች ልዩነቶቻቸውን በሰለጠነ መንገድ በማንሸራሸር ለነገዋ ኢትዮጵያ ጠንካራ መሰረት የሚጥሉበት ወርቃማ እድል ነው፡፡
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogue #nationbuilding #ebcdotstream
Sponsored by
Surafel
17 days ago
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አዲስ ዕይታና ዕድሎች
**********************
ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በባህልና በተፈጥሮ ሀብት የታደለች፣ የበርካታ የዓለም ቅርሶች ባለቤት የሆነች ሀገር ናት። ይሁን እንጂ ይህን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ጥቅም ከመቀየር አንጻር ዘርፉ ለብዙ ዓመታት በርካታ ተግዳሮቶች ሲገጥሙት ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት ግን፣ የመደመር መንግሥት በሰጠው ልዩ ትኩረት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አሮጌውን አካሄድ በመቀየር፣ በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና ሜጋ ፕሮጀክቶች የታገዘ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ቱሪዝም በአብዛኛው የታሪክና የሃይማኖት ቅርሶችን ብቻ ማዕከል ያደረገ ነበር። አሁን ላይ ይህ አካሄድ ተቀይሮ የቱሪስት መዳረሻዎች ብዝኃነትን እንዲያካትቱ ተደርጓል።
በአዲስ አበባ በ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክት የተገነቡት እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የወዳጅነት አደባባይ ያሉ ፕሮጀክቶች ዋና ከተማዋን የቱሪስት ማረፊያና መስኅብ አድርገዋታል።
አንዲሁም በገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተገነቡት የቱሪዝም መስኅቦች የሀገራችን የተፈጥሮ ውበት እና ሥነ-ምህዳር ለዓለም አቀፍ ጎብኝዎች በአዲስ መልክ እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል የቱሪዝም ዕድገት ያለ አስተማማኝ መሠረተ-ልማት ሊታሰብ የማይችል ሲሆን፣ በዚህ ረገድ የተሠሩ ሥራዎችም ለዘርፉ መነቃቃት ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመጨመር እና የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማቶችን በሀገር ውስጥ በማስፋፋት ተጓዦችን ከዓለም ዙሪያ በቀላሉ የማገናኘት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
በተጨማሪም የኢ-ቪዛ አሰጣጥ መዘርጋት እና የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች መዘመን የጎብኝዎችን እንግልት በመቀነስ የጉዞ ሂደቱን ቀላልና ፈጣን በማድረግ ሀገራችን ከዘርፉ ተጠቃሚ እንድትሆን እያስቻላት ነው።
የቱሪዝም ዕድገት ስትራቴጂ ትኩረት የነዋሪውን ማኅበረሰብ ሕይወት መለወጥ ላይ ነው። በአዳዲስ መዳረሻዎች አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦች በዕደ-ጥበብ፣ በቅርስ ጥበቃ፣ በሎጅና በእንግዳ ተቀባይነት ዘርፍ ቀጥተኛ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው። ይህም ቅርሶችና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቁ አድርጓቸዋል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ካለበት "የማይነካ እምቅ አቅም" ተሻግሮ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ምሰሶነት እየተቀየረ ይገኛል። አዳዲስ መዳረሻዎችን ማልማት፣ ጥራትን ማሻሻል እና ዲጂታል ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ፣ ቱሪዝም ለሀገራችን የውጭ ምንዛሪ ግኝትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ቀዳሚው አንቀሳቃሽ ኃይል መሆኑ አይቀሬ ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopianbroadcastingcorporation #tourismethiopia #landoforigins #visitethiopia
**********************
ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በባህልና በተፈጥሮ ሀብት የታደለች፣ የበርካታ የዓለም ቅርሶች ባለቤት የሆነች ሀገር ናት። ይሁን እንጂ ይህን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ጥቅም ከመቀየር አንጻር ዘርፉ ለብዙ ዓመታት በርካታ ተግዳሮቶች ሲገጥሙት ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት ግን፣ የመደመር መንግሥት በሰጠው ልዩ ትኩረት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አሮጌውን አካሄድ በመቀየር፣ በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና ሜጋ ፕሮጀክቶች የታገዘ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ቱሪዝም በአብዛኛው የታሪክና የሃይማኖት ቅርሶችን ብቻ ማዕከል ያደረገ ነበር። አሁን ላይ ይህ አካሄድ ተቀይሮ የቱሪስት መዳረሻዎች ብዝኃነትን እንዲያካትቱ ተደርጓል።
በአዲስ አበባ በ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክት የተገነቡት እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የወዳጅነት አደባባይ ያሉ ፕሮጀክቶች ዋና ከተማዋን የቱሪስት ማረፊያና መስኅብ አድርገዋታል።
አንዲሁም በገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተገነቡት የቱሪዝም መስኅቦች የሀገራችን የተፈጥሮ ውበት እና ሥነ-ምህዳር ለዓለም አቀፍ ጎብኝዎች በአዲስ መልክ እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል የቱሪዝም ዕድገት ያለ አስተማማኝ መሠረተ-ልማት ሊታሰብ የማይችል ሲሆን፣ በዚህ ረገድ የተሠሩ ሥራዎችም ለዘርፉ መነቃቃት ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመጨመር እና የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማቶችን በሀገር ውስጥ በማስፋፋት ተጓዦችን ከዓለም ዙሪያ በቀላሉ የማገናኘት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
በተጨማሪም የኢ-ቪዛ አሰጣጥ መዘርጋት እና የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች መዘመን የጎብኝዎችን እንግልት በመቀነስ የጉዞ ሂደቱን ቀላልና ፈጣን በማድረግ ሀገራችን ከዘርፉ ተጠቃሚ እንድትሆን እያስቻላት ነው።
የቱሪዝም ዕድገት ስትራቴጂ ትኩረት የነዋሪውን ማኅበረሰብ ሕይወት መለወጥ ላይ ነው። በአዳዲስ መዳረሻዎች አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦች በዕደ-ጥበብ፣ በቅርስ ጥበቃ፣ በሎጅና በእንግዳ ተቀባይነት ዘርፍ ቀጥተኛ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው። ይህም ቅርሶችና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቁ አድርጓቸዋል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ካለበት "የማይነካ እምቅ አቅም" ተሻግሮ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ምሰሶነት እየተቀየረ ይገኛል። አዳዲስ መዳረሻዎችን ማልማት፣ ጥራትን ማሻሻል እና ዲጂታል ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ፣ ቱሪዝም ለሀገራችን የውጭ ምንዛሪ ግኝትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ቀዳሚው አንቀሳቃሽ ኃይል መሆኑ አይቀሬ ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopianbroadcastingcorporation #tourismethiopia #landoforigins #visitethiopia
19 days ago
ኢትዮጵያ የአፍሪካን አዲስ የቱሪዝም ካርታ በጥበብ እየሳለች ነው
******************
"ኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ ናት" የሚለው የቆየ አስተሳሰብ ከጊዜ ጋር በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ ይገኛል። ዛሬ ኢትዮጵያ የሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርሶቿን ከዘመናዊ የቱሪዝም ልማቶች ጋር በስምምነት እያጣመረች፣ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች አዲስና ተመራጭ የጉዞ መስመር እየሆነች ነው።
ኢትዮጵያ ታሪክን፣ ተፈጥሮን፣ ባህልን እና ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን በአንድ ወጥ የጉዞ ተሞክሮ ውስጥ አጣምራ የምታቀርብበት አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል።
ዛሬ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ታሪኳን ብቻ አትተርክም፤ ይልቁንም አዲስ የቱሪዝም ታሪክ በተግባር እየጻፈች ትገኛለች። ለምሳሌ ያህል፣ በቅርቡ ተገንብተው ለፍሬ የበቁት የ"ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ታላላቅ ፕሮጀክቶች፣ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ መናፈሻዎች፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና አረንጓዴ ስፍራዎች ኢትዮጵያን ከባህላዊ መዳረሻነት ወደ ዘመናዊ የጉዞ ልምድ እየቀየሯት ይገኛሉ።
በጎርጎራ የጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ የተገነቡት ዘመናዊ የመስተንግዶ ማዕከላት፣ በወንጪ የተራራ ሐይቅን የሚያቅፉት አስደናቂ የእይታ መድረኮች፣ እንዲሁም በሀላላ ኬላ የተፈጥሮንና የታሪክን ውበት የሚያሳዩት መዝናኛዎች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገጽታ በአዲስ መልክ የሳሉት ትልልቅ ስኬቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም የአንድነት ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ፣ የእንጦጦ ተፈጥሮ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የአዲስ አበባ አዳዲስ አረንጓዴ መናፈሻዎች የከተማ ቱሪዝምን ወደ ላቀ የደረጃ ማማ አሸጋግረውታል።
ነገር ግን ሀገራችን የዘመናዊ ቱሪዝም ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ስታስፋፋ የትናንት ታሪኳንና ማንነቷን ከቶም አልዘነጋችም። እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት፣ የአክሱም ሐውልቶች፣ የፋሲል ግቢ፣ የሰሜንና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርኮች፣ እሳተ-ገሞራማው የዳናኪል ምድር እና የአንትሮፖሎጂ መገኛ የሆነው የኦሞ ሸለቆ ያሉ ዓለም አቀፍ ቅርሶች ከአዳዲሶቹ መዳረሻዎች ጋር ተደምረው ለጎብኚዎች ልዩና ድንቅ የጉዞ ተሞክሮ እየፈጠሩ ይገኛሉ።
ዓለም ዛሬ መዝናናትንና መጎብኘትን ብቻ ሳይሆን፣ የማይረሳ ሕያው ተሞክሮን አጥብቆ በሚሻበት በዚህ ዘመን፤ ኢትዮጵያ ያንን ፍላጎት በተፈጥሮ፣ በታሪክ፣ በሕዝቦቿ ሞቅ ያለ ፈገግታና በዘመናዊ ልማቶቿ በአንድ ላይ አሟልታ ታቀርባለች። ዛሬ ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የምትጋብዝበት ምክንያት ትናንቷ ብቻ አይደለም፤ ብሩህ የሆነው ነገዋም ጭምር ነው። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ታሪኳን በአግባቡ ጠብቃ፣ የወደፊቱን የአፍሪካ የቱሪዝም ካርታ በበላይነት እየሳለች ያለች ታላቅ ሀገር መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በልዩ እሸቱ
#ebc #ethiopia #tourism #landoforigins #visitethiopia
******************
"ኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ ናት" የሚለው የቆየ አስተሳሰብ ከጊዜ ጋር በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ ይገኛል። ዛሬ ኢትዮጵያ የሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርሶቿን ከዘመናዊ የቱሪዝም ልማቶች ጋር በስምምነት እያጣመረች፣ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች አዲስና ተመራጭ የጉዞ መስመር እየሆነች ነው።
ኢትዮጵያ ታሪክን፣ ተፈጥሮን፣ ባህልን እና ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን በአንድ ወጥ የጉዞ ተሞክሮ ውስጥ አጣምራ የምታቀርብበት አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል።
ዛሬ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ታሪኳን ብቻ አትተርክም፤ ይልቁንም አዲስ የቱሪዝም ታሪክ በተግባር እየጻፈች ትገኛለች። ለምሳሌ ያህል፣ በቅርቡ ተገንብተው ለፍሬ የበቁት የ"ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ታላላቅ ፕሮጀክቶች፣ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ መናፈሻዎች፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና አረንጓዴ ስፍራዎች ኢትዮጵያን ከባህላዊ መዳረሻነት ወደ ዘመናዊ የጉዞ ልምድ እየቀየሯት ይገኛሉ።
በጎርጎራ የጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ የተገነቡት ዘመናዊ የመስተንግዶ ማዕከላት፣ በወንጪ የተራራ ሐይቅን የሚያቅፉት አስደናቂ የእይታ መድረኮች፣ እንዲሁም በሀላላ ኬላ የተፈጥሮንና የታሪክን ውበት የሚያሳዩት መዝናኛዎች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገጽታ በአዲስ መልክ የሳሉት ትልልቅ ስኬቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም የአንድነት ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ፣ የእንጦጦ ተፈጥሮ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የአዲስ አበባ አዳዲስ አረንጓዴ መናፈሻዎች የከተማ ቱሪዝምን ወደ ላቀ የደረጃ ማማ አሸጋግረውታል።
ነገር ግን ሀገራችን የዘመናዊ ቱሪዝም ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ስታስፋፋ የትናንት ታሪኳንና ማንነቷን ከቶም አልዘነጋችም። እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት፣ የአክሱም ሐውልቶች፣ የፋሲል ግቢ፣ የሰሜንና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርኮች፣ እሳተ-ገሞራማው የዳናኪል ምድር እና የአንትሮፖሎጂ መገኛ የሆነው የኦሞ ሸለቆ ያሉ ዓለም አቀፍ ቅርሶች ከአዳዲሶቹ መዳረሻዎች ጋር ተደምረው ለጎብኚዎች ልዩና ድንቅ የጉዞ ተሞክሮ እየፈጠሩ ይገኛሉ።
ዓለም ዛሬ መዝናናትንና መጎብኘትን ብቻ ሳይሆን፣ የማይረሳ ሕያው ተሞክሮን አጥብቆ በሚሻበት በዚህ ዘመን፤ ኢትዮጵያ ያንን ፍላጎት በተፈጥሮ፣ በታሪክ፣ በሕዝቦቿ ሞቅ ያለ ፈገግታና በዘመናዊ ልማቶቿ በአንድ ላይ አሟልታ ታቀርባለች። ዛሬ ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የምትጋብዝበት ምክንያት ትናንቷ ብቻ አይደለም፤ ብሩህ የሆነው ነገዋም ጭምር ነው። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ታሪኳን በአግባቡ ጠብቃ፣ የወደፊቱን የአፍሪካ የቱሪዝም ካርታ በበላይነት እየሳለች ያለች ታላቅ ሀገር መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በልዩ እሸቱ
#ebc #ethiopia #tourism #landoforigins #visitethiopia
20 days ago
የዛሬ ምሽት ዜና መፅሔት ጉዳዮች
👉ከህዳሴ ግድብ እስከ ቀይ ባህር የድል ታሪክ ስኬትን ለመመዝገብ የውስጥ አንድነት ምን አቅም አለው?ለዚህም የምክክሩ እገዛስ?
👉 የሀገራዊ ምክክሩ የቆዩና ያልተፈቱ አስተዳደራዊ ችግሮች የሚፈቱበት ጠቃሚ የሆኑ ጉዳዮች ወደ ተግባር የምንቀይርበት እንደሆነ ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ያነጋገራቸዉ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁራን ነግረዉናል፡፡
👉 ከተማዋን ማኅበራዊ ፍትሕ የሰፈነባት፤ ውብና ጽዱ በማድረግ እንዲሁም በበርካታ ዘርፎች ትልቅ ስኬት ብናስመዘግብም አሁንም ያልተሻገርናቸው የቤት ሥራዎች አሉ ብለዋል የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፡፡
👉 ቻይና እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ ጦርነት ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉ ትንታኔዎች እየወጡ ነው፡፡
👉ስፖርት - አዳዲስ መረጃዎች ተዘጋጅተዋል።
የዕለቱ አብይ ርእሰ ጉዳዮች በዝርዝር እና በትንታኔ ።
የዜና ክፍል ጋዜጠኞች እነዚህን ጨምሮ ሌሎች ዘገባዎችን አካተው በፋና የምሽቱ ዜና መፅሔት ሊያስደምጧችሁ ዝግጁ ናቸው ።
ጌታቸው አለሙ ይጠብቃችኋል ።
በኤፍ ኤም 98 .1 እና በተለያዩ ክልሎች በሚገኙ ኤፍ ኤሞቻችን እንዲሁም በwww.fanamc.com በመላው ሀገሪቱና በዓለም ዙሪያ ስርጭታችንን መከታተል ትችላላችሁ።
ከምሽቱ 1 ሰዓት ይጠብቁን።
👉ከህዳሴ ግድብ እስከ ቀይ ባህር የድል ታሪክ ስኬትን ለመመዝገብ የውስጥ አንድነት ምን አቅም አለው?ለዚህም የምክክሩ እገዛስ?
👉 የሀገራዊ ምክክሩ የቆዩና ያልተፈቱ አስተዳደራዊ ችግሮች የሚፈቱበት ጠቃሚ የሆኑ ጉዳዮች ወደ ተግባር የምንቀይርበት እንደሆነ ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ያነጋገራቸዉ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁራን ነግረዉናል፡፡
👉 ከተማዋን ማኅበራዊ ፍትሕ የሰፈነባት፤ ውብና ጽዱ በማድረግ እንዲሁም በበርካታ ዘርፎች ትልቅ ስኬት ብናስመዘግብም አሁንም ያልተሻገርናቸው የቤት ሥራዎች አሉ ብለዋል የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፡፡
👉 ቻይና እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ ጦርነት ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉ ትንታኔዎች እየወጡ ነው፡፡
👉ስፖርት - አዳዲስ መረጃዎች ተዘጋጅተዋል።
የዕለቱ አብይ ርእሰ ጉዳዮች በዝርዝር እና በትንታኔ ።
የዜና ክፍል ጋዜጠኞች እነዚህን ጨምሮ ሌሎች ዘገባዎችን አካተው በፋና የምሽቱ ዜና መፅሔት ሊያስደምጧችሁ ዝግጁ ናቸው ።
ጌታቸው አለሙ ይጠብቃችኋል ።
በኤፍ ኤም 98 .1 እና በተለያዩ ክልሎች በሚገኙ ኤፍ ኤሞቻችን እንዲሁም በwww.fanamc.com በመላው ሀገሪቱና በዓለም ዙሪያ ስርጭታችንን መከታተል ትችላላችሁ።
ከምሽቱ 1 ሰዓት ይጠብቁን።
20 days ago
የሰውን ስሜት ተረድቶ ምላሽ የሚሰጠው አዲሱ የቴክኖሎጂ እመርታ
የሰውን ልጅ የድምፅ ቃና፣ የፊት ገጽታና የሰውነት ሁኔታ በመገምገም ስሜትን መረዳትና ተገቢውን ምላሽ መስጠት የሚችል አዲስ የሮቦቲክስና የሰው ሰራሽ አስተዋፅዖ (AI) ቴክኖሎጂ ይፋ ተደረገ።
ይህ በቴክኖሎጂው ዓለም ከፍተኛ ትኩረትን የሳበው እመርታ፣ ሮቦቶች ከተራ የቤት ውስጥ ረዳትነት ባለፈ የሰዎችን ስሜታዊ ፍላጎት መለየትና እንደየሁኔታው ማጽናናት፣ ማበረታታት እንዲሁም የቅርብ ክትትል ማድረግ የሚያስችላቸውን አቅም ፈጥሯል።
ይህ ቴክኖሎጂ በተለይ ብቻቸውን የሚኖሩ አረጋውያንን፣ የድብርትና የጭንቀት ሰለባ የሆኑ ሰዎችን እንዲሁም የቅርብ ክትትል የሚያስፈልጋቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ለመደገፍ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል።
በቴክኖሎጂ፣ በሳይንስና በፈጠራ ሥራዎች ላይ ትኩረት አድርገው የሚዘግቡት ተጽዕኖ ፈጣሪ ዓለም አቀፍ የሳይንስ መጽሔቶችና የቴክኖሎጂ ሚዲያዎች የዜና ዘገባየው አካል አድርገውታል።
ዘገባው በዓለም አቀፍ ደረጃ በቴክኖሎጂው ዘርፍ የተሰማሩ ግንባር ቀደም ተቋማት ያበለጸጓቸውን ስሜት ተገንዛቢ (Emotion-AI) የቤት ውስጥ ረዳት ሮቦቶችና የገበያ ተደራሽነታቸውን አስመልክቶ ካቀረበው ትንታኔ የተወሰደ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
የሰውን ልጅ የድምፅ ቃና፣ የፊት ገጽታና የሰውነት ሁኔታ በመገምገም ስሜትን መረዳትና ተገቢውን ምላሽ መስጠት የሚችል አዲስ የሮቦቲክስና የሰው ሰራሽ አስተዋፅዖ (AI) ቴክኖሎጂ ይፋ ተደረገ።
ይህ በቴክኖሎጂው ዓለም ከፍተኛ ትኩረትን የሳበው እመርታ፣ ሮቦቶች ከተራ የቤት ውስጥ ረዳትነት ባለፈ የሰዎችን ስሜታዊ ፍላጎት መለየትና እንደየሁኔታው ማጽናናት፣ ማበረታታት እንዲሁም የቅርብ ክትትል ማድረግ የሚያስችላቸውን አቅም ፈጥሯል።
ይህ ቴክኖሎጂ በተለይ ብቻቸውን የሚኖሩ አረጋውያንን፣ የድብርትና የጭንቀት ሰለባ የሆኑ ሰዎችን እንዲሁም የቅርብ ክትትል የሚያስፈልጋቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ለመደገፍ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል።
በቴክኖሎጂ፣ በሳይንስና በፈጠራ ሥራዎች ላይ ትኩረት አድርገው የሚዘግቡት ተጽዕኖ ፈጣሪ ዓለም አቀፍ የሳይንስ መጽሔቶችና የቴክኖሎጂ ሚዲያዎች የዜና ዘገባየው አካል አድርገውታል።
ዘገባው በዓለም አቀፍ ደረጃ በቴክኖሎጂው ዘርፍ የተሰማሩ ግንባር ቀደም ተቋማት ያበለጸጓቸውን ስሜት ተገንዛቢ (Emotion-AI) የቤት ውስጥ ረዳት ሮቦቶችና የገበያ ተደራሽነታቸውን አስመልክቶ ካቀረበው ትንታኔ የተወሰደ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
20 days ago
የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ መታሰቢያ ሐውልት በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ተመረቀ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ፣ በዲፕሎማሲ፣ በሥነ ጽሑፍና በሕዝብ አገልግሎት ዘርፍ የማይረሳ አሻራ ያሳረፉትን ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴን ለመዘከር የተገነባው የመታሰቢያ ሐውልት ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ በይፋ ተመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የቤተሰብ አባላት፣ የአካዳሚው አመራሮች፣ ምሁራንና የተለያዩ የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር በላይ ካሳ እንደገለጹት፣ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ ከ24 በላይ መጻሕፍትን በመጻፍ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነ ጽሑፍ መሠረት ከጣሉ ሊቃውንት አንዱ ሲሆኑ፣ በዲፕሎማሲ፣ በባንክ ሥርዓት፣ በቴአትር፣ በቀይ መስቀል ማኅበር እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዘርፎችም የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ አባልነት እንድትቀላቀል በተደረገው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ጉልህ ሚና የተጫወቱ ሲሆን፣ ከአምባሳደርነት እስከ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሀገራቸውን በታማኝነት ማገልገላቸው ተጠቅሷል።
አካዳሚው ታሪካዊ መኖሪያ ቤታቸውን በቅርስነት በመጠበቅ ዋና መሥሪያ ቤት አድርጎ እየተጠቀመበት ሲሆን፣ የግል ሰነዶቻቸውን፣ ፎቶግራፎችን፣ መጻሕፍቶችንና ሌሎች ቅርሶችን የያዘ ቋሚ ሙዚየምም ለጎብኚዎች ክፍት አድርጓል።
ሐውልቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእይታ ጥበብ ባለሙያ ሠዓሊ ኢዮብ ኪታባ እና በቡድናቸው የተቀረጸ ሲሆን፣ ለሥራው መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የልጅ ልጅ ልጅ ወይዘሮ ገነት ኅሩይ የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።
ይህ የመታሰቢያ ሐውልት የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴን ታሪካዊ አስተዋጽኦ ለቀጣዩ ትውልድ በማስተላለፍ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ተገልጿል።
#ethiopia #scienceacademy #blatengetahruy #history #heritage #getutemesgen #ጌጡተመስገን
#ethiopia | በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ፣ በዲፕሎማሲ፣ በሥነ ጽሑፍና በሕዝብ አገልግሎት ዘርፍ የማይረሳ አሻራ ያሳረፉትን ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴን ለመዘከር የተገነባው የመታሰቢያ ሐውልት ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ በይፋ ተመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የቤተሰብ አባላት፣ የአካዳሚው አመራሮች፣ ምሁራንና የተለያዩ የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር በላይ ካሳ እንደገለጹት፣ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ ከ24 በላይ መጻሕፍትን በመጻፍ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነ ጽሑፍ መሠረት ከጣሉ ሊቃውንት አንዱ ሲሆኑ፣ በዲፕሎማሲ፣ በባንክ ሥርዓት፣ በቴአትር፣ በቀይ መስቀል ማኅበር እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዘርፎችም የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ አባልነት እንድትቀላቀል በተደረገው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ጉልህ ሚና የተጫወቱ ሲሆን፣ ከአምባሳደርነት እስከ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሀገራቸውን በታማኝነት ማገልገላቸው ተጠቅሷል።
አካዳሚው ታሪካዊ መኖሪያ ቤታቸውን በቅርስነት በመጠበቅ ዋና መሥሪያ ቤት አድርጎ እየተጠቀመበት ሲሆን፣ የግል ሰነዶቻቸውን፣ ፎቶግራፎችን፣ መጻሕፍቶችንና ሌሎች ቅርሶችን የያዘ ቋሚ ሙዚየምም ለጎብኚዎች ክፍት አድርጓል።
ሐውልቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእይታ ጥበብ ባለሙያ ሠዓሊ ኢዮብ ኪታባ እና በቡድናቸው የተቀረጸ ሲሆን፣ ለሥራው መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የልጅ ልጅ ልጅ ወይዘሮ ገነት ኅሩይ የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።
ይህ የመታሰቢያ ሐውልት የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴን ታሪካዊ አስተዋጽኦ ለቀጣዩ ትውልድ በማስተላለፍ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ተገልጿል።
#ethiopia #scienceacademy #blatengetahruy #history #heritage #getutemesgen #ጌጡተመስገን
Sponsored by
Surafel
20 days ago
የትራምፕ አስተዳደር የውጭ አገራት ተማሪዎች የቪዛ ደንቦችን አጠበቀ
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለውጭ አገራት ተማሪዎች ጥብቅ የቪዛ ደንቦችን ለመተግበር የመጨረሻ ውሳኔ ላይ መድረሱ ተገለጸ።
ውሳኔው ተማሪዎች ያለ ፌደራል መንግሥት ፈቃድ ከአራት ዓመት በላይ በአሜሪካ እንዳይቆዩ ማገድ እና ሌሎችም ጥብቅ እርምጃዎችን ያካተተ ነው።
ዩኒቨርሲቲ መለወጥ ወይም የትምህርት ክፍል መቀየር ላይም ገደብ ይጣላል ተብሏል። እስካሁን ድረስ ባለው አሠራር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቪዛ እንዲራዘም የማድረግ ሥልጣን ነበራቸው።
ፖሊሲው የሚተገበረው ከቀጣዩ መስከረም አንስቶ ሲሆን፤ የአሜሪካ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ "የቪዛ ብዝበዛን የሚገዳደር እና የጀርባ ታሪክ ምርመራ በማድረግ ብሔራዊ ደኅንነትን የሚያጠናክር አሠራር ነው" ብሏል።
የዓለም አቀፍ መምህራን ማኅበር ግን ውሳኔውን "የተዛባ እና አላስፈላጊ" ሲል ኮንኖታል።
እስካሁን ድረስ ይተገበር በነበረው አሠራር ኤፍ-1 እና ጄ-1 የውጭ አገራት ተማሪዎች ቪዛ ያላቸው ትምህርት እስከሚያጠናቅቁ ድረስ በአሜሪካ መቆየት ይፈቀድላቸዋል።
ከዚህ በኋላ ግን የተማሪዎች የቆይታ ጊዜ ላይ ገደብ የሚጣል ይሆናል።
የአገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ ማርክዌይን ሙሊን "ለአሥርታት የውጭ አገራት ተማሪዎች ያለ ጊዜ ገደብ ወደ አሜሪካ ሲመጡ ነበር። በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ትምህርቶች እየጀመሩ አሜሪካ በመቆየት የስደተኞች ሥርዓቱን በዝብዘዋል" ብለዋል
በአሜሪካ በአብዛኞቹ የትምህርት ክፍሎች የመጀመሪያ ዲግሪ ለማጠናቀቅ አራት ዓመት ይወስዳል። ሦስተኛ ዲግሪ ግን ዘለግ ያለ ጊዜ ያስፈልገዋል።
የውጭ አገራት ተማሪዎች የመጀመሪያ ዲግሪ በብዛት የሚሠሩት በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ነው።
ትምህርቶቹን እንዲሁም የመመረቂያ ጽሑፍ ለመጨረስም ጊዜ ያስፈልጋል።
ጥናት እና ምርምር ለማከናወን የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት የሚደረገው ጥረትም ተጨማሪ ጊዜ ይወስዳል።
የትራምፕ አስተዳደር ባወጣው አዲስ ፖሊሲ መሠረት ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ በ30 ቀናት ውስጥ ከአሜሪካ መውጣት አለባቸው። ሌላው አማራጭ የቪዛ ዓይነት መቀየር ሲሆን፤ ይህም 60 ተጨማሪ ቀናት ለማግኘት ይረዳል።
የዓለም አቀፍ መምህራን ማኅበር ዋና ኃላፊ ፋንታ አው ፖሊሲ "ጥርጣሬ የሚያጭር፣ በቢሮክራሲ የተሞላ፣ በአግባቡ የሚሠራ ሥርዓት ላይ ፍርሃት የሚያሳድር፣ ችግር በሌለበት መፍትሔ የሚፈልግ ነው" ሲሉ ተችተዋል።
የትራምፕ አስተዳደር የውጭ አገራት ተማሪዎች እና የስደተኞን ቁጥር ለመቀነስ የተለያዩ እርምጃዎች መውሰዱን ቀጥሏል።
አንዳንድ ዕውቅ ዩኒቨርስቲዎች የሚቀበሏቸውን የውጭ አገራት ተማሪዎች ቁጥር እንዲቀንሱ ለማድረግ ተሞክሯል። የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የተቃወሙ ተማሪዎች ቪዛ እንዲሰረዝም ተወስኗል።
BBC
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለውጭ አገራት ተማሪዎች ጥብቅ የቪዛ ደንቦችን ለመተግበር የመጨረሻ ውሳኔ ላይ መድረሱ ተገለጸ።
ውሳኔው ተማሪዎች ያለ ፌደራል መንግሥት ፈቃድ ከአራት ዓመት በላይ በአሜሪካ እንዳይቆዩ ማገድ እና ሌሎችም ጥብቅ እርምጃዎችን ያካተተ ነው።
ዩኒቨርሲቲ መለወጥ ወይም የትምህርት ክፍል መቀየር ላይም ገደብ ይጣላል ተብሏል። እስካሁን ድረስ ባለው አሠራር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቪዛ እንዲራዘም የማድረግ ሥልጣን ነበራቸው።
ፖሊሲው የሚተገበረው ከቀጣዩ መስከረም አንስቶ ሲሆን፤ የአሜሪካ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ "የቪዛ ብዝበዛን የሚገዳደር እና የጀርባ ታሪክ ምርመራ በማድረግ ብሔራዊ ደኅንነትን የሚያጠናክር አሠራር ነው" ብሏል።
የዓለም አቀፍ መምህራን ማኅበር ግን ውሳኔውን "የተዛባ እና አላስፈላጊ" ሲል ኮንኖታል።
እስካሁን ድረስ ይተገበር በነበረው አሠራር ኤፍ-1 እና ጄ-1 የውጭ አገራት ተማሪዎች ቪዛ ያላቸው ትምህርት እስከሚያጠናቅቁ ድረስ በአሜሪካ መቆየት ይፈቀድላቸዋል።
ከዚህ በኋላ ግን የተማሪዎች የቆይታ ጊዜ ላይ ገደብ የሚጣል ይሆናል።
የአገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ ማርክዌይን ሙሊን "ለአሥርታት የውጭ አገራት ተማሪዎች ያለ ጊዜ ገደብ ወደ አሜሪካ ሲመጡ ነበር። በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ትምህርቶች እየጀመሩ አሜሪካ በመቆየት የስደተኞች ሥርዓቱን በዝብዘዋል" ብለዋል
በአሜሪካ በአብዛኞቹ የትምህርት ክፍሎች የመጀመሪያ ዲግሪ ለማጠናቀቅ አራት ዓመት ይወስዳል። ሦስተኛ ዲግሪ ግን ዘለግ ያለ ጊዜ ያስፈልገዋል።
የውጭ አገራት ተማሪዎች የመጀመሪያ ዲግሪ በብዛት የሚሠሩት በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ነው።
ትምህርቶቹን እንዲሁም የመመረቂያ ጽሑፍ ለመጨረስም ጊዜ ያስፈልጋል።
ጥናት እና ምርምር ለማከናወን የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት የሚደረገው ጥረትም ተጨማሪ ጊዜ ይወስዳል።
የትራምፕ አስተዳደር ባወጣው አዲስ ፖሊሲ መሠረት ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ በ30 ቀናት ውስጥ ከአሜሪካ መውጣት አለባቸው። ሌላው አማራጭ የቪዛ ዓይነት መቀየር ሲሆን፤ ይህም 60 ተጨማሪ ቀናት ለማግኘት ይረዳል።
የዓለም አቀፍ መምህራን ማኅበር ዋና ኃላፊ ፋንታ አው ፖሊሲ "ጥርጣሬ የሚያጭር፣ በቢሮክራሲ የተሞላ፣ በአግባቡ የሚሠራ ሥርዓት ላይ ፍርሃት የሚያሳድር፣ ችግር በሌለበት መፍትሔ የሚፈልግ ነው" ሲሉ ተችተዋል።
የትራምፕ አስተዳደር የውጭ አገራት ተማሪዎች እና የስደተኞን ቁጥር ለመቀነስ የተለያዩ እርምጃዎች መውሰዱን ቀጥሏል።
አንዳንድ ዕውቅ ዩኒቨርስቲዎች የሚቀበሏቸውን የውጭ አገራት ተማሪዎች ቁጥር እንዲቀንሱ ለማድረግ ተሞክሯል። የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የተቃወሙ ተማሪዎች ቪዛ እንዲሰረዝም ተወስኗል።
BBC
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በደቡባዊ ኢራን ባንዳር ካሚር በተሰኘችው የወደብ ከተማ ውስጥ አሜሪካ በድልድዮች ላይ በፈጸመችው የሌሊት የአየር ጥቃት የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የሀገሪቱ መንግሥታዊ የዜና ወኪል ኢርና )ዘገበ።
የዜና ወኪሉ የሆርሞዝጋን የሕክምና ሳይንስ ዩኒቨርሲቲን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ በጥቃቱ ሳቢያ የሰባት ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ አልፏል።
የኢራን መንግሥታዊ መገናኛ ብዙኃን ትናንት ምሽት ባወጡት መረጃ፣ የአሜሪካ የአየር ጥቃቶች በደቡባዊ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ አየር ማረፊያ እና ሁለት ድልድዮችን መምታታቸውን አስታውቀዋል። በተጨማሪም በባንዳር ካሚር ዞን በኮሁሬስታን መንደር እና በሾር ወንዝ አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት ድልድዮች በዚሁ ጥቃት መመታታቸውን ዘገባው አመልክቷል።
ይህ ጥቃት አሜሪካ በኢራን ወታደራዊ አቅም ላይ እየሰነዘረችው ያለችው ተከታታይ ጥቃት አካል መሆኑ ይታወቃል።
የዜና ወኪሉ የሆርሞዝጋን የሕክምና ሳይንስ ዩኒቨርሲቲን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ በጥቃቱ ሳቢያ የሰባት ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ አልፏል።
የኢራን መንግሥታዊ መገናኛ ብዙኃን ትናንት ምሽት ባወጡት መረጃ፣ የአሜሪካ የአየር ጥቃቶች በደቡባዊ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ አየር ማረፊያ እና ሁለት ድልድዮችን መምታታቸውን አስታውቀዋል። በተጨማሪም በባንዳር ካሚር ዞን በኮሁሬስታን መንደር እና በሾር ወንዝ አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት ድልድዮች በዚሁ ጥቃት መመታታቸውን ዘገባው አመልክቷል።
ይህ ጥቃት አሜሪካ በኢራን ወታደራዊ አቅም ላይ እየሰነዘረችው ያለችው ተከታታይ ጥቃት አካል መሆኑ ይታወቃል።
21 days ago
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 100ኛ ዓመቱን አከበረ
#ethiopia | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) "የአንድ ክፍለ ዘመን ጥረት ለተሻለ የሕብረተሰብ ጤና" በሚል መሪ ቃል ታሪካዊ የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ዛሬ በከፍተኛ ድምቀት አክብሯል።
ይህ መቶ ዓመታትን የተሻገረው ክብረ በዓል ተቋሙ ላለፉት አሥርት ዓመታት የሀገሪቱን የጤና ደህንነት ለመጠበቅ ያደረገውን ዘርፈ ብዙ ጉዞ የዘከረ ሲሆን፣ በቀጣይም የጤና ሥርዓቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር አዲስ ቃል ኪዳን የተገባበት መድረክ ሆኗል።
በበዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ክቡር ታዬ አፅቀስላሴ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት የሀገር ደህንነትና ልማት መሠረቶች መሆናቸውን በመግለጽ፣ መንግሥት ተቋሙን ይበልጥ ለማጠናከር ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
ፕሬዚዳንቱ አክለውም ተቋሙ ከጊዜው ጋር እንዲራመድ የዲጂታል ቴክኖሎጂንና የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አጠቃቀምን ማሳደግ እንደሚገባው አሳስበዋል።
በተመሳሳይ መልኩ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ ተቋሙ ላለፉት 100 ዓመታት በበሽታ ቅኝት፣ በላቦራቶሪ አገልግሎትና በምርምር ዘርፍ ያበረከተውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያወሱ ሲሆን፣ አዳዲስ ወረርሽኞችንና የአየር ንብረት ለውጥ ያመጣቸውን የጤና ተግዳሮቶች ለመመከት ጠንካራ ተቋማዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት ገልጸዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በኢትዮጵያ ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካስሎ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ በአፍሪካ እጅግ ጠንካራ ከሆኑ የልህቀት ማዕከላት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ ተቋሙን የዓለም ጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ይፋ አድርገዋል።
የአፍሪካ የበሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጄን ካሴያም በበኩላቸው የወደፊቱ የሕብረተሰብ ጤና ያለ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የማይታሰብ መሆኑን ጠቁመው፣ ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ እያደረገች ያለችው ጥረት ለጤናው ዘርፍ ስኬት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ተቋሙ ያለፉትን ስኬቶች መሠረት በማድረግ በቀጣዩ መቶ ዓመታት የሀገሪቱን የሳይንስና የጤና ሉዓላዊነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ቃል ገብተዋል።
በበዓሉ ማጠቃለያ ላይም ላለፉት ዓመታት ተቋሙን በምርምርና በአመራርነት ያገለገሉ ባለውለታዎች ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀስላሴ እጅ የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthsovereignty #publichealthethiopia
#aiinhealthcare #ethiopia
#ephi #ministryofhealthethiopia
#ethiopia | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) "የአንድ ክፍለ ዘመን ጥረት ለተሻለ የሕብረተሰብ ጤና" በሚል መሪ ቃል ታሪካዊ የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ዛሬ በከፍተኛ ድምቀት አክብሯል።
ይህ መቶ ዓመታትን የተሻገረው ክብረ በዓል ተቋሙ ላለፉት አሥርት ዓመታት የሀገሪቱን የጤና ደህንነት ለመጠበቅ ያደረገውን ዘርፈ ብዙ ጉዞ የዘከረ ሲሆን፣ በቀጣይም የጤና ሥርዓቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር አዲስ ቃል ኪዳን የተገባበት መድረክ ሆኗል።
በበዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ክቡር ታዬ አፅቀስላሴ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት የሀገር ደህንነትና ልማት መሠረቶች መሆናቸውን በመግለጽ፣ መንግሥት ተቋሙን ይበልጥ ለማጠናከር ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
ፕሬዚዳንቱ አክለውም ተቋሙ ከጊዜው ጋር እንዲራመድ የዲጂታል ቴክኖሎጂንና የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አጠቃቀምን ማሳደግ እንደሚገባው አሳስበዋል።
በተመሳሳይ መልኩ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ ተቋሙ ላለፉት 100 ዓመታት በበሽታ ቅኝት፣ በላቦራቶሪ አገልግሎትና በምርምር ዘርፍ ያበረከተውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያወሱ ሲሆን፣ አዳዲስ ወረርሽኞችንና የአየር ንብረት ለውጥ ያመጣቸውን የጤና ተግዳሮቶች ለመመከት ጠንካራ ተቋማዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት ገልጸዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በኢትዮጵያ ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካስሎ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ በአፍሪካ እጅግ ጠንካራ ከሆኑ የልህቀት ማዕከላት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ ተቋሙን የዓለም ጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ይፋ አድርገዋል።
የአፍሪካ የበሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጄን ካሴያም በበኩላቸው የወደፊቱ የሕብረተሰብ ጤና ያለ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የማይታሰብ መሆኑን ጠቁመው፣ ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ እያደረገች ያለችው ጥረት ለጤናው ዘርፍ ስኬት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ተቋሙ ያለፉትን ስኬቶች መሠረት በማድረግ በቀጣዩ መቶ ዓመታት የሀገሪቱን የሳይንስና የጤና ሉዓላዊነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ቃል ገብተዋል።
በበዓሉ ማጠቃለያ ላይም ላለፉት ዓመታት ተቋሙን በምርምርና በአመራርነት ያገለገሉ ባለውለታዎች ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀስላሴ እጅ የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthsovereignty #publichealthethiopia
#aiinhealthcare #ethiopia
#ephi #ministryofhealthethiopia
21 days ago
በሊንክድኢን ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና የይዘት ፈጣሪዎች ሊሸለሙ ነው
#fastmereja :-በኢትዮጵያ በሊንክድኢን (LinkedIn) መድረክ ላይ ንቁ ተሳትፎ ላላቸው የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና ባለሙያዎች እውቅና ለመስጠት የተቋቋመው "የሊንክድኢን ቼንጅሜከርስ አዋርድስ ኢትዮጵያ (LCAE)" የመጀመሪያውን የሽልማት ስነ-ስርዓት ሊያካሂድ መሆኑን በዛሬዉ እለት በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ይህ መርሃ ግብር የፊታችን ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (August 1, 2026) በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ቲያትር አዳራሽ በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል።
በጉሩጂ ኤአር ኢትዮጵያ ከዥማ ሚዲያና ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚህ የክብር ምሸት ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎችና የልማት አጋሮች የሚታደሙ ሲሆን፤ በህዝብ ጥቆማ፣ በድምፅ አሰጣጥ እና በባለሙያዎች ጥብቅ ግምገማ ያለፉ ድንቅ እጩዎች ሽልማት ይበረከትላቸዋል።
የጉሩጂ ኤአር ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ያብስራ መካሻ እንደገለጹት፤ ሽልማቱ በሀገሪቱ የሙያ ስነ-ምህዳር ውስጥ የነበረውን ክፍተት ለመሙላትና ይዘታቸው ሌሎችን የሚያነቃቃና ትርጉም ያለው ሙያዊ ውይይት የሚፈጥሩ ሰዎችን ለማበረታታት ያለመ ነው፡፡
ይህ አገር አቀፍ ሽልማት በሳይንስና ቴክኖሎጂ (STEM)፣ በጤና፣ በስራ ፈጠራ፣ በአየር ንብረት እና በማርኬቲንግ ጨምሮ በ6 ዋና ዋና ምድቦች የተከፋፈለ ሲሆን፤ ከዲጂታል መድረክ ባሻገር በተጨባጭ ማህበረሰባዊ ተፅዕኖ የፈጠሩ ባለሙያዎችን ይሸልማል።
የሊንክድኢን ተፅእኖ ፈጣሪዎች ሽልማት ኢትዮጵያ (LCAE) በሀገሪቱ ሙያዊ እና ማህበራዊ መልክዓ-ምድር ላይ በተጨባጭ የሚለካ ተፅዕኖ እያሳደሩ ያሉ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን እውቅና የሚሰጥ የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ብሔራዊ፣ ሁለገብ ዘርፍ መድረክ ነው።
#ኹነት
#fastmereja :-በኢትዮጵያ በሊንክድኢን (LinkedIn) መድረክ ላይ ንቁ ተሳትፎ ላላቸው የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና ባለሙያዎች እውቅና ለመስጠት የተቋቋመው "የሊንክድኢን ቼንጅሜከርስ አዋርድስ ኢትዮጵያ (LCAE)" የመጀመሪያውን የሽልማት ስነ-ስርዓት ሊያካሂድ መሆኑን በዛሬዉ እለት በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ይህ መርሃ ግብር የፊታችን ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (August 1, 2026) በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ቲያትር አዳራሽ በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል።
በጉሩጂ ኤአር ኢትዮጵያ ከዥማ ሚዲያና ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚህ የክብር ምሸት ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎችና የልማት አጋሮች የሚታደሙ ሲሆን፤ በህዝብ ጥቆማ፣ በድምፅ አሰጣጥ እና በባለሙያዎች ጥብቅ ግምገማ ያለፉ ድንቅ እጩዎች ሽልማት ይበረከትላቸዋል።
የጉሩጂ ኤአር ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ያብስራ መካሻ እንደገለጹት፤ ሽልማቱ በሀገሪቱ የሙያ ስነ-ምህዳር ውስጥ የነበረውን ክፍተት ለመሙላትና ይዘታቸው ሌሎችን የሚያነቃቃና ትርጉም ያለው ሙያዊ ውይይት የሚፈጥሩ ሰዎችን ለማበረታታት ያለመ ነው፡፡
ይህ አገር አቀፍ ሽልማት በሳይንስና ቴክኖሎጂ (STEM)፣ በጤና፣ በስራ ፈጠራ፣ በአየር ንብረት እና በማርኬቲንግ ጨምሮ በ6 ዋና ዋና ምድቦች የተከፋፈለ ሲሆን፤ ከዲጂታል መድረክ ባሻገር በተጨባጭ ማህበረሰባዊ ተፅዕኖ የፈጠሩ ባለሙያዎችን ይሸልማል።
የሊንክድኢን ተፅእኖ ፈጣሪዎች ሽልማት ኢትዮጵያ (LCAE) በሀገሪቱ ሙያዊ እና ማህበራዊ መልክዓ-ምድር ላይ በተጨባጭ የሚለካ ተፅዕኖ እያሳደሩ ያሉ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን እውቅና የሚሰጥ የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ብሔራዊ፣ ሁለገብ ዘርፍ መድረክ ነው።
#ኹነት
Sponsored by
Surafel
22 days ago
"በጭንቀት ልንፈነዳ ደርሰናል" – በፌደራል እና በትግራይ የ12ተኛ ክፍል ፈተና ውዝግብ ግራ የተጋቡት ተማሪዎች
የትግራይ ክልል የ12ተኛ ክፍል የወረቀት ተፈታኞችን የጊዜ ሰሌዳ በተመለከተ በክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲሁም በፌደራሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መካከል የተፈጠረው ውዝግብ ግራ መጋባት ውስጥ እንደከተታቸው የክልሉ ተማሪዎች ተናገሩ።
ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም. ጀምሮ በስድስት ዙሮች በበይነ መረብ እና በወረቀት መሰጠት በጀመረው በዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከ563 ሺህ በላይ ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ተገልጿል።
በመጨረሻዎቹ ዙሮች የሚካሄደው የወረቀት ፈተና ከሐምሌ 1 እስከ 17 እንደሚካሄድ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቆ ነበር።
ይሁን እንጂ በትግራይ ክልል የሚካሄደው የወረቀት ምዘና ቀኑ ተራዝሞ ከሐምሌ 22 ጀምሮ ለሦስት ቀናት እንዲካሄድ መወሰኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በሚመራው የክልሉ አስተዳደር ሥር የሚገኘው የትምህርት ቢሮ የጊዜ ሰሌዳ ለውጡን አልተቀበለውም። ትምህርት ቢሮው የቀን ለውጡን "ፖለቲካዊ ውሳኔ" እና "በትግራይ ሕዝብ ላይ በተለያየ መንገድ እየተፈጸመ የመጣው እና እየቀጠለ ያለው ጥቃት አካል" ሲል ገልጾታል።
ትምህርት ሚኒስቴር አገር አቀፉን ፈተና በተመለከተ "እርስ በራሳቸው የሚጣረሱ፣ ግልፅነት የጎደላቸው፣ በየጊዜው የሚቀያየሩ" ውሳኔዎች አሳልፏል በማለትም ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን ለፌደራል ትምህርት ተቋማት በጻፈው ደብዳቤ ወቅሷል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ በክልሉ ለሚገኙ ተማሪዎች የራሱን ፈተና አውጥቶ እንደሚሰጥም አስታውቋል።
አገር አቀፍ ፈተናዎችን የማስተደዳር ሥልጣን ያለውን መሥሪያ ቤት የሚመሩት ዶ/ር እሸቱ በበኩላቸው ከትግራይ ውጪ "በሌሎች ክልሎችም ላይ በተለያየ ምክንያት" በእነዚህ ቀናት ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎች እንዳሉ ይናገራሉ።
ፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ እና የትግራይ ትምህርት ቢሮ ውሳኔ አጣብቂኝ ውስጥ የገቡት የክልሉ ተማሪዎች ጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በፌስቡክ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ፤ "በተወሰኑ የመሠረተ ልማት ጉድለት ባለባቸው አካባቢዎች በወረቀት በተለያዩ አራት ዙሮች ማለትም ለተፈጥሮ ሳይንስ፣ ለማኅበራዊ ሳይንስ እንዲሁም በቀድሞ ሥርዓተ ትምህርት ለተማሩ እና የትግራይ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች በስድስቱ ዙር ላልተፈተኑ ተፈታኞች ከበይነ መረቡ ፈተና ጎን ለጎን በወረቀት ፈተና እየሰጠ ይገኛል" ብሏል።
ከሐምሌ 22 እስከ 24/ 2018 ዓ. ም. የሚሰጠው ፈተና በመቀለ ዩኒቨርሲቲ እና በአክሱም ዩኒቨርሲቲ እንደሚካሄድም ይጠቅሳል።
በሰሜናዊ ምዕራብ ትግራይ አዲ ዳእሮ የፈተናና ምዘና ሒደት አስተባባሪ እና መምህር የሆኑት አቶ ተስፋይ ገብረእግዚአብሔር እንደሚናገሩት የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና ሐምሌ 1 እና የማኅበራዊ ሳይንስ ሐምሌ 6 እንደሚሰጥ ከአንድ ወር በፊት ተገልጾ ነበር።
"ነገር ግን በ28 ፈተናው ተራዝሟል ሲባል ወላጆች እና ተማሪዎች በጣም ነው የተጨነቁት" ብለዋል።
"ፕሮግራም ወጥቶ የደከሙበት እና ውጤት የሚያይዩበትን [ፈተና] እየጠበቁ ስለነበር ተራዝሟል ሲባል በጣም ነው የተደናገጡት።"
ለምን የትግራይ ብቻ እንደዚህ ሆነ? የሚለው ጥያቄ ወላጆች እና ልጆችን "መጨነቅ እና ተስፋ መቁረጥ" እንደከተታቸውን ገልጸዋል።
የትግራይ የትምህርት ቢሮ እና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አንድ ላይ ሆነው የተራዘመበትን ምክንያት አለመግለጻቸው ተማሪዎቹን "እንደረበሻቸው" አቶ ተስፋይ አክለዋል።
"ተማሪዎች እንኳን ተረጋግቶ ፈተና መግባት ጭንቅ ላይ ነው ያሉት። እኛም መልስ የለንም" ብለዋል።
ለትግራይ ክልል "የተለየ ፈተና የሚዘጋጅ ከሆነ ተቀባይነት የለውም" ያሉት አቶ ተስፋይ "ተማሪዎች ለ12 ዓመት የለፉበትን ሥራ ውጤት ለማየት ተቸግረዋል. . . የፖለቲካ ችግር ካለም ተማሪዎቹ የኢትዮጵያ፣ የትግራይ ተረካቢ ዜጎች ናቸውና ችግራ ይፈታ" በማለትም አሳስበዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማክሰኞ ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም. ባወጣው ማስታወቂያ በትግራይ ክልል እና በሌሎችም አካባቢዎች ፈተናው የሚሰጥበትን ጊዜ ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሠረት በትግራይ ክልል ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 22 አስከ 24 ድረስ በክልሉ ውስጥ በሚገኙ ሁለት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
BBC
የትግራይ ክልል የ12ተኛ ክፍል የወረቀት ተፈታኞችን የጊዜ ሰሌዳ በተመለከተ በክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲሁም በፌደራሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መካከል የተፈጠረው ውዝግብ ግራ መጋባት ውስጥ እንደከተታቸው የክልሉ ተማሪዎች ተናገሩ።
ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም. ጀምሮ በስድስት ዙሮች በበይነ መረብ እና በወረቀት መሰጠት በጀመረው በዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከ563 ሺህ በላይ ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ተገልጿል።
በመጨረሻዎቹ ዙሮች የሚካሄደው የወረቀት ፈተና ከሐምሌ 1 እስከ 17 እንደሚካሄድ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቆ ነበር።
ይሁን እንጂ በትግራይ ክልል የሚካሄደው የወረቀት ምዘና ቀኑ ተራዝሞ ከሐምሌ 22 ጀምሮ ለሦስት ቀናት እንዲካሄድ መወሰኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በሚመራው የክልሉ አስተዳደር ሥር የሚገኘው የትምህርት ቢሮ የጊዜ ሰሌዳ ለውጡን አልተቀበለውም። ትምህርት ቢሮው የቀን ለውጡን "ፖለቲካዊ ውሳኔ" እና "በትግራይ ሕዝብ ላይ በተለያየ መንገድ እየተፈጸመ የመጣው እና እየቀጠለ ያለው ጥቃት አካል" ሲል ገልጾታል።
ትምህርት ሚኒስቴር አገር አቀፉን ፈተና በተመለከተ "እርስ በራሳቸው የሚጣረሱ፣ ግልፅነት የጎደላቸው፣ በየጊዜው የሚቀያየሩ" ውሳኔዎች አሳልፏል በማለትም ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን ለፌደራል ትምህርት ተቋማት በጻፈው ደብዳቤ ወቅሷል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ በክልሉ ለሚገኙ ተማሪዎች የራሱን ፈተና አውጥቶ እንደሚሰጥም አስታውቋል።
አገር አቀፍ ፈተናዎችን የማስተደዳር ሥልጣን ያለውን መሥሪያ ቤት የሚመሩት ዶ/ር እሸቱ በበኩላቸው ከትግራይ ውጪ "በሌሎች ክልሎችም ላይ በተለያየ ምክንያት" በእነዚህ ቀናት ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎች እንዳሉ ይናገራሉ።
ፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ እና የትግራይ ትምህርት ቢሮ ውሳኔ አጣብቂኝ ውስጥ የገቡት የክልሉ ተማሪዎች ጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በፌስቡክ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ፤ "በተወሰኑ የመሠረተ ልማት ጉድለት ባለባቸው አካባቢዎች በወረቀት በተለያዩ አራት ዙሮች ማለትም ለተፈጥሮ ሳይንስ፣ ለማኅበራዊ ሳይንስ እንዲሁም በቀድሞ ሥርዓተ ትምህርት ለተማሩ እና የትግራይ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች በስድስቱ ዙር ላልተፈተኑ ተፈታኞች ከበይነ መረቡ ፈተና ጎን ለጎን በወረቀት ፈተና እየሰጠ ይገኛል" ብሏል።
ከሐምሌ 22 እስከ 24/ 2018 ዓ. ም. የሚሰጠው ፈተና በመቀለ ዩኒቨርሲቲ እና በአክሱም ዩኒቨርሲቲ እንደሚካሄድም ይጠቅሳል።
በሰሜናዊ ምዕራብ ትግራይ አዲ ዳእሮ የፈተናና ምዘና ሒደት አስተባባሪ እና መምህር የሆኑት አቶ ተስፋይ ገብረእግዚአብሔር እንደሚናገሩት የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና ሐምሌ 1 እና የማኅበራዊ ሳይንስ ሐምሌ 6 እንደሚሰጥ ከአንድ ወር በፊት ተገልጾ ነበር።
"ነገር ግን በ28 ፈተናው ተራዝሟል ሲባል ወላጆች እና ተማሪዎች በጣም ነው የተጨነቁት" ብለዋል።
"ፕሮግራም ወጥቶ የደከሙበት እና ውጤት የሚያይዩበትን [ፈተና] እየጠበቁ ስለነበር ተራዝሟል ሲባል በጣም ነው የተደናገጡት።"
ለምን የትግራይ ብቻ እንደዚህ ሆነ? የሚለው ጥያቄ ወላጆች እና ልጆችን "መጨነቅ እና ተስፋ መቁረጥ" እንደከተታቸውን ገልጸዋል።
የትግራይ የትምህርት ቢሮ እና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አንድ ላይ ሆነው የተራዘመበትን ምክንያት አለመግለጻቸው ተማሪዎቹን "እንደረበሻቸው" አቶ ተስፋይ አክለዋል።
"ተማሪዎች እንኳን ተረጋግቶ ፈተና መግባት ጭንቅ ላይ ነው ያሉት። እኛም መልስ የለንም" ብለዋል።
ለትግራይ ክልል "የተለየ ፈተና የሚዘጋጅ ከሆነ ተቀባይነት የለውም" ያሉት አቶ ተስፋይ "ተማሪዎች ለ12 ዓመት የለፉበትን ሥራ ውጤት ለማየት ተቸግረዋል. . . የፖለቲካ ችግር ካለም ተማሪዎቹ የኢትዮጵያ፣ የትግራይ ተረካቢ ዜጎች ናቸውና ችግራ ይፈታ" በማለትም አሳስበዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማክሰኞ ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም. ባወጣው ማስታወቂያ በትግራይ ክልል እና በሌሎችም አካባቢዎች ፈተናው የሚሰጥበትን ጊዜ ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሠረት በትግራይ ክልል ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 22 አስከ 24 ድረስ በክልሉ ውስጥ በሚገኙ ሁለት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
BBC
26 days ago
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ለቀጣናዊ ሰላም
የአፍሪካ ቀንድ በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ላይ ባለው ስልታዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ሳቢያ ሁልጊዜም የጂኦፖለቲካ ፍላጎቶች መናኸሪያ ነው።
በዚህ ቀጣና ውስጥ ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ የባህር በር አልባ መሆኗ የራሷን የኢኮኖሚ እድገት ከመገደቡ ባለፈ በቀጣናው መረጋጋት ላይ የራሱ ተጽእኖ አለው።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የሀገሪቱን የልማት ጥያቄ ከመመለስ ባለፈ ለአጠቃላይ ቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ትስስር ሚናው ወሳኝ ነው።
የፖለቲካ ሳይንስ ሳይንሳዊ እውነታዎች እንደሚያሳዩት፣ ሀገራት በኢኮኖሚ እርስ በርስ የሚኖራቸው ትስስር በጠነከረ ቁጥር በመካከላቸው የመተማመንና የመተባበር መንፈስ በርትቶ የግጭት ዕድል በእጅጉ ይቀንሳል።
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ ቀጥተኛ የባህር በር ካላት የምርት ወጪዋ ይቀንሳል፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በሙሉ አቅማቸው ያመርታሉ፣ ሰፊ የሥራ ዕድልም ይፈጠራል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል እና የወደብ መዋቅር ሲኖራት፣ በቀጣናው የሚስተዋሉትን የባህር ላይ ወንብድና እና የሽብርተኝነት ስጋቶች ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመከላከል ሰፊ አቅም ይፈጥራል።
ይህ ደግሞ በኤደን ባህረ-ሰላጤ እና በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ህገ-ወጥ ስደት እና የወንጀል ተጋላጭነት ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዲፕሎማሲ እና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ካገኘ፣ በሀገሪቱ ላይ የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ መታፈን ያስወግዳል። ይህ ደግሞ ስጋት-ወለድ ለሆኑ ግጭቶች በር ይዘጋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋን የምታነሳው የዓለም አቀፍ የባህር ህግን እና የጋራ ልማት መርሆዎችን መሠረት አድርጋ ነው።
ይህ አካሄድ ከሃይል ይልቅ በድርድር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የዲፕሎማሲ ባህል በአፍሪካ ቀንድ እንዲዳብር መንገድ ከፍቷል።
በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ቀንድ የሰላም ዋስትና ነው።
በመሆኑም የባህር በር ጥያቄው መመለስ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያፋጥን እና ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍን ታሪካዊ እርምጃ ነው።
የአፍሪካ ቀንድ በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ላይ ባለው ስልታዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ሳቢያ ሁልጊዜም የጂኦፖለቲካ ፍላጎቶች መናኸሪያ ነው።
በዚህ ቀጣና ውስጥ ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ የባህር በር አልባ መሆኗ የራሷን የኢኮኖሚ እድገት ከመገደቡ ባለፈ በቀጣናው መረጋጋት ላይ የራሱ ተጽእኖ አለው።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የሀገሪቱን የልማት ጥያቄ ከመመለስ ባለፈ ለአጠቃላይ ቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ትስስር ሚናው ወሳኝ ነው።
የፖለቲካ ሳይንስ ሳይንሳዊ እውነታዎች እንደሚያሳዩት፣ ሀገራት በኢኮኖሚ እርስ በርስ የሚኖራቸው ትስስር በጠነከረ ቁጥር በመካከላቸው የመተማመንና የመተባበር መንፈስ በርትቶ የግጭት ዕድል በእጅጉ ይቀንሳል።
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ ቀጥተኛ የባህር በር ካላት የምርት ወጪዋ ይቀንሳል፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በሙሉ አቅማቸው ያመርታሉ፣ ሰፊ የሥራ ዕድልም ይፈጠራል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል እና የወደብ መዋቅር ሲኖራት፣ በቀጣናው የሚስተዋሉትን የባህር ላይ ወንብድና እና የሽብርተኝነት ስጋቶች ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመከላከል ሰፊ አቅም ይፈጥራል።
ይህ ደግሞ በኤደን ባህረ-ሰላጤ እና በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ህገ-ወጥ ስደት እና የወንጀል ተጋላጭነት ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዲፕሎማሲ እና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ካገኘ፣ በሀገሪቱ ላይ የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ መታፈን ያስወግዳል። ይህ ደግሞ ስጋት-ወለድ ለሆኑ ግጭቶች በር ይዘጋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋን የምታነሳው የዓለም አቀፍ የባህር ህግን እና የጋራ ልማት መርሆዎችን መሠረት አድርጋ ነው።
ይህ አካሄድ ከሃይል ይልቅ በድርድር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የዲፕሎማሲ ባህል በአፍሪካ ቀንድ እንዲዳብር መንገድ ከፍቷል።
በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ቀንድ የሰላም ዋስትና ነው።
በመሆኑም የባህር በር ጥያቄው መመለስ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያፋጥን እና ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍን ታሪካዊ እርምጃ ነው።
26 days ago
በዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ የተጻፉ ሁለት አዳዲስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መጽሐፍት ተመረቁ
#ethiopia | የቀድሞው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ አዴ፣ የወደፊቱን ዓለም በሳይንስና በቴክኖሎጂ የሚመለከቱ ሁለት አዳዲስ መጽሐፍትን ለንባብ አበቁ።
«Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization» እና «Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide» በሚል ርዕስ የቀረቡት መጽሐፍት፣ የወደፊቱን የሰው ልጅ ሥልጣኔ፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ሚና፣ እንዲሁም የጠፈር ሳይንስ እድሎችን በሰፊው የሚዳስሱ መሆናቸው ተገልጿል።
በመጽሐፍቱ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ዶ/ር ይሹሩን እንዳስታወቁት፣ «Architecting the Future» የሰው ልጅ ሕይወትን በፍጥነት እየቀየሩ ባሉ ቴክኖሎጂዎች መካከል የወደፊቱን ዓለም በሰብዓዊ እሴቶች፣ በዘላቂነትና በራዕይ መገንባት ላይ ያተኩራል።
ሁለተኛው መጽሐፍ «Introduction to Astronautics» ደግሞ የጠፈር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለዕለት ተዕለት ኑሮ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለብሔራዊ ደህንነት ያለውን ፋይዳ በቀላል አቀራረብ በማስረዳት፣ በተለይም አፍሪካውያን ወጣቶች በጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያበረታታል።
ደራሲው እንደገለጹት፣ ሁለቱ መጽሐፍት አንዱ የወደፊት ራዕይን ሲያስቀምጥ፣ ሌላው ደግሞ ያንን ራዕይ ለማሳካት የሚያስፈልጉ ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ መሠረቶችን ያቀርባል።
መጽሐፍቱ ወጣቶችን ወደ STEM (ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና ሂሳብ) ዘርፎች ለመሳብ፣ በኢትዮጵያ የምርምርና የፈጠራ ባህልን ለማጠናከር እንዲሁም ፖሊሲ አውጪዎች የረጅም ጊዜ ስትራቴጂያዊ እይታ እንዲኖራቸው በማገዝ ረገድ አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopia #science #technology #innovation #spacescience #stem #booklaunch #getutemesgen #ጌጡተመስገን
#ethiopia | የቀድሞው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ አዴ፣ የወደፊቱን ዓለም በሳይንስና በቴክኖሎጂ የሚመለከቱ ሁለት አዳዲስ መጽሐፍትን ለንባብ አበቁ።
«Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization» እና «Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide» በሚል ርዕስ የቀረቡት መጽሐፍት፣ የወደፊቱን የሰው ልጅ ሥልጣኔ፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ሚና፣ እንዲሁም የጠፈር ሳይንስ እድሎችን በሰፊው የሚዳስሱ መሆናቸው ተገልጿል።
በመጽሐፍቱ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ዶ/ር ይሹሩን እንዳስታወቁት፣ «Architecting the Future» የሰው ልጅ ሕይወትን በፍጥነት እየቀየሩ ባሉ ቴክኖሎጂዎች መካከል የወደፊቱን ዓለም በሰብዓዊ እሴቶች፣ በዘላቂነትና በራዕይ መገንባት ላይ ያተኩራል።
ሁለተኛው መጽሐፍ «Introduction to Astronautics» ደግሞ የጠፈር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለዕለት ተዕለት ኑሮ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለብሔራዊ ደህንነት ያለውን ፋይዳ በቀላል አቀራረብ በማስረዳት፣ በተለይም አፍሪካውያን ወጣቶች በጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያበረታታል።
ደራሲው እንደገለጹት፣ ሁለቱ መጽሐፍት አንዱ የወደፊት ራዕይን ሲያስቀምጥ፣ ሌላው ደግሞ ያንን ራዕይ ለማሳካት የሚያስፈልጉ ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ መሠረቶችን ያቀርባል።
መጽሐፍቱ ወጣቶችን ወደ STEM (ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና ሂሳብ) ዘርፎች ለመሳብ፣ በኢትዮጵያ የምርምርና የፈጠራ ባህልን ለማጠናከር እንዲሁም ፖሊሲ አውጪዎች የረጅም ጊዜ ስትራቴጂያዊ እይታ እንዲኖራቸው በማገዝ ረገድ አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopia #science #technology #innovation #spacescience #stem #booklaunch #getutemesgen #ጌጡተመስገን
26 days ago
በዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ የተሰናዱ ሁለት የሳይንስና የወደፊት ራዕይ መጻሕፍት ተመረቁ!
#fastmereja :- በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ እና በሰው ልጅ ቀጣይ ስልጣኔ ላይ የሚያተኩሩ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍት በዛሬዉ እለት በልዩ ስነ-ስርዓት ተመረቁ።
የቴክኖሎጂ ባለሙያውና ተመራማሪው ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ ያዘጋጇቸዉ «Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization>> እና «Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide» የተሰኙት መጻሕፍት፤ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአካዳሚክ ማህበረሰብ፣ ዲፕሎማቶችና የቴክኖሎጂ ዘርፍ አጋሮች በተገኙበት ነው ለንባብ የበቁት።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት ደራሲው ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ፣ መጻሕፍቱ የተዘጋጁት መረጃ ለመስጠት ብቻ ሳይሆን አገር በቀል እውቀትን በማሳደግ የወደፊቱን ትውልድ ለታላቅ ስኬት ለማነሳሳት መሆኑን ገልጸዋል።
"ሀገራት የሚለወጡትና ከፍ የሚሉት በእውቀት፣ በፈጠራ፣ በሳይንስና በቴክኖሎጂ ራዕይ ብቻ ነው" ያሉት ደራሲው፣ ሁለቱ መጽሐፍት በይዘታቸው የተለያዩ ቢመስሉም የሚያስተላልፉት መልዕክት ግን በአንድ ማዕቀፍ ውስጥ የሚቀመር መሆኑን አስገንዝበዋል።
የመጀመሪያው መጽሐፍ-«Architecting the Future» -አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)፣ ሮቦቲክስ፣ ኳንተም ኮምፒውቲንግ፣ ባዮቴክኖሎጂ እና የዲጂታል ኢኮኖሚ የሰው ልጅን ህይወት በከፍተኛ ፍጥነት እየቀየሩት ባሉበት በዚህ ወቅት፣ የወደፊቱን ዓለም በሥነ-ምግባር፣ በሰብዓዊ እሴቶችና በፍትሐዊነት እንዴት መምራት እንደሚቻል ስልታዊ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል። መጽሐፉ ለመንግሥታት የፖሊሲ አቅጣጫን፣ ለዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ የምርምር ራዕይን ለመስጠት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል «Introduction to Astronautics>> የተሰኘው ሁለተኛው መጽሐፍ የጠፈር ቴክኖሎጂን በቀላል ቋንቋ የሚያስተምር ሲሆን፤ የሮኬት ሳይንስ፣ ሳተላይቶች፣ የጠፈር ህግና ዲፕሎማሲ እንዲሁም የጠፈር ኢኮኖሚ በተግባራዊ መልኩ የቀረቡበት ነው። በተለይም ኢትዮጵያና አጠቃላይ አፍሪካ በአዲሱ የጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ተገብሮ ተመልካች ሳይሆኑ፣ ንቁ ተሳታፊ መሆን እንዳለባቸው መጽሐፉ በግልጽ እኖደሚያሳይ ተገልጿል።
ዶ/ር ይሹሩን የሁለቱን መጻሕፍት ትስስር ሲያስረዱም፦
#fastmereja :- በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ እና በሰው ልጅ ቀጣይ ስልጣኔ ላይ የሚያተኩሩ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍት በዛሬዉ እለት በልዩ ስነ-ስርዓት ተመረቁ።
የቴክኖሎጂ ባለሙያውና ተመራማሪው ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ ያዘጋጇቸዉ «Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization>> እና «Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide» የተሰኙት መጻሕፍት፤ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአካዳሚክ ማህበረሰብ፣ ዲፕሎማቶችና የቴክኖሎጂ ዘርፍ አጋሮች በተገኙበት ነው ለንባብ የበቁት።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት ደራሲው ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ፣ መጻሕፍቱ የተዘጋጁት መረጃ ለመስጠት ብቻ ሳይሆን አገር በቀል እውቀትን በማሳደግ የወደፊቱን ትውልድ ለታላቅ ስኬት ለማነሳሳት መሆኑን ገልጸዋል።
"ሀገራት የሚለወጡትና ከፍ የሚሉት በእውቀት፣ በፈጠራ፣ በሳይንስና በቴክኖሎጂ ራዕይ ብቻ ነው" ያሉት ደራሲው፣ ሁለቱ መጽሐፍት በይዘታቸው የተለያዩ ቢመስሉም የሚያስተላልፉት መልዕክት ግን በአንድ ማዕቀፍ ውስጥ የሚቀመር መሆኑን አስገንዝበዋል።
የመጀመሪያው መጽሐፍ-«Architecting the Future» -አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)፣ ሮቦቲክስ፣ ኳንተም ኮምፒውቲንግ፣ ባዮቴክኖሎጂ እና የዲጂታል ኢኮኖሚ የሰው ልጅን ህይወት በከፍተኛ ፍጥነት እየቀየሩት ባሉበት በዚህ ወቅት፣ የወደፊቱን ዓለም በሥነ-ምግባር፣ በሰብዓዊ እሴቶችና በፍትሐዊነት እንዴት መምራት እንደሚቻል ስልታዊ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል። መጽሐፉ ለመንግሥታት የፖሊሲ አቅጣጫን፣ ለዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ የምርምር ራዕይን ለመስጠት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል «Introduction to Astronautics>> የተሰኘው ሁለተኛው መጽሐፍ የጠፈር ቴክኖሎጂን በቀላል ቋንቋ የሚያስተምር ሲሆን፤ የሮኬት ሳይንስ፣ ሳተላይቶች፣ የጠፈር ህግና ዲፕሎማሲ እንዲሁም የጠፈር ኢኮኖሚ በተግባራዊ መልኩ የቀረቡበት ነው። በተለይም ኢትዮጵያና አጠቃላይ አፍሪካ በአዲሱ የጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ተገብሮ ተመልካች ሳይሆኑ፣ ንቁ ተሳታፊ መሆን እንዳለባቸው መጽሐፉ በግልጽ እኖደሚያሳይ ተገልጿል።
ዶ/ር ይሹሩን የሁለቱን መጻሕፍት ትስስር ሲያስረዱም፦
Sponsored by
Surafel
Comments