19 hours ago
ሊዮኔል ሜሲ በስፔን በሰደድ እሳት ለወደሙ አካባቢዎች 80 ሺህ ዩሮ ለገሰ
#ethiopia | የእግር ኳስ ኮከቡ ሊዮኔል ሜሲ በስፔን ማድሪድ ሴራ ኦኤስቴ ክልል በሰደድ እሳት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት የሚያግዝ 80 ሺህ ዩሮ መለገሱን የማድሪድ ማህበር ፕሬዝዳንት ዩሮፕ ፕሬስን ጠቅሰው አስታውቀዋል።
አደጋው ወደ 30 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ የደን መሬት ያወደመ ሲሆን የሜሲ ድጋፍም የወደሙትን አካባቢዎች መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
ሜሲ ከዚህ ቀደም በስፔን ለተከሰቱ የሰደድ እሳት አደጋዎች ለቀይ መስቀል ድጋፍ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በቫሌንሲያ ለተከሰተው የጎርፍ አደጋ እና በቬኔዙዌላ የመሬት መንቀጥቀጥ ተጎጂዎችም ከባለቤቱ አንቶኔላ ጋር በመሆን እርዳታ አበርክቷል።
በተጨማሪም በጋራሃን ፋውንዴሽን በኩል 500 ሺህ ዩሮ በመለገስ በካንሰር ለተጠቁ ህጻናትና ለአርጀንቲና ሆስፒታሎች ያደረገው ድጋፍ የሚጠቀስ ሲሆን ሜሲ በሜዳ ውስጥ ባለው ድንቅ የእግር ኳስ ብቃቱ ብቻ ሳይሆን ከሜዳ ውጭ በሚያሳየው ታላቅ የሰብአዊነት ተግባር ይታወቃል ።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የእግር ኳስ ኮከቡ ሊዮኔል ሜሲ በስፔን ማድሪድ ሴራ ኦኤስቴ ክልል በሰደድ እሳት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት የሚያግዝ 80 ሺህ ዩሮ መለገሱን የማድሪድ ማህበር ፕሬዝዳንት ዩሮፕ ፕሬስን ጠቅሰው አስታውቀዋል።
አደጋው ወደ 30 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ የደን መሬት ያወደመ ሲሆን የሜሲ ድጋፍም የወደሙትን አካባቢዎች መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
ሜሲ ከዚህ ቀደም በስፔን ለተከሰቱ የሰደድ እሳት አደጋዎች ለቀይ መስቀል ድጋፍ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በቫሌንሲያ ለተከሰተው የጎርፍ አደጋ እና በቬኔዙዌላ የመሬት መንቀጥቀጥ ተጎጂዎችም ከባለቤቱ አንቶኔላ ጋር በመሆን እርዳታ አበርክቷል።
በተጨማሪም በጋራሃን ፋውንዴሽን በኩል 500 ሺህ ዩሮ በመለገስ በካንሰር ለተጠቁ ህጻናትና ለአርጀንቲና ሆስፒታሎች ያደረገው ድጋፍ የሚጠቀስ ሲሆን ሜሲ በሜዳ ውስጥ ባለው ድንቅ የእግር ኳስ ብቃቱ ብቻ ሳይሆን ከሜዳ ውጭ በሚያሳየው ታላቅ የሰብአዊነት ተግባር ይታወቃል ።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
22 hours ago
በትግራይ ክልል ግጭት በማገርሸቱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ያለው ስጋት ዳግም አሳሳቢ መሆኑን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ‼️
በሀገር የመከላከያ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል አዲስ ግጭት መቀስቀሱን ተከትሎ የክልሉ ነዋሪዎች ዳግም ለከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የመጋለጥ ስጋት እንደደገነባቸው አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ።
የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ቲገሬ ቻጉታህ እንደገለጹት ማህበረሰቡ ቀደም ሲል ከደረሱበት አሰቃቂ ጥቃቶች ሳያገግምና ተጠያቂነት ሳይረጋገጥ አዲስ ግጭት ውስጥ መግባቱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ስጋቱን ይበልጥ ከፍ እንዲል አድርጎታል ብለዋል።
በትግራይ ክልል ያገረሸው ግጭት ከአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ውጊያዎች ጋር ተደማምሮ በሀገሪቱ ከፍተኛ የመብት ጥሰቶች እየደረሰ መሆኑን የገለጸው አምነስቲ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብቶች መርማሪ አካላትን ሥራ በአስቸኳይ መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከዚህ ቀደም በነበረው ጦርነት፤ የጦር ወንጀል እና በሰብአዊነት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችን ጨምሮ በርካታ ጥሰቶች መመዝገባቸውን ያስታወሰው ተቋሙ በጥፋተኞች ላይ ምርመራ እና ክስ ያለማቅረብ አካሄድ ልማዳዊ ሊሆን አይገባም ብሏል።
የፌደራል መንግሥት እና የትግራይ ባለስልጣናት ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችን እንዲያከብሩ፣ ሰላማዊ ሰዎችን እንዲጠብቁ፣ እንዲሁም ለነጻ የሰብአዊ መብት ተከታታዮች፣ ለሰብአዊ እርዳታ አቅራቢዎች እና ለገለልተኛ መገናኛ ብዙሃን ያልተገደበ እንቅስቃሴ ፈቃድ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርቧል።
Seledadotio
Seledadotio
በሀገር የመከላከያ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል አዲስ ግጭት መቀስቀሱን ተከትሎ የክልሉ ነዋሪዎች ዳግም ለከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የመጋለጥ ስጋት እንደደገነባቸው አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ።
የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ቲገሬ ቻጉታህ እንደገለጹት ማህበረሰቡ ቀደም ሲል ከደረሱበት አሰቃቂ ጥቃቶች ሳያገግምና ተጠያቂነት ሳይረጋገጥ አዲስ ግጭት ውስጥ መግባቱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ስጋቱን ይበልጥ ከፍ እንዲል አድርጎታል ብለዋል።
በትግራይ ክልል ያገረሸው ግጭት ከአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ውጊያዎች ጋር ተደማምሮ በሀገሪቱ ከፍተኛ የመብት ጥሰቶች እየደረሰ መሆኑን የገለጸው አምነስቲ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብቶች መርማሪ አካላትን ሥራ በአስቸኳይ መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከዚህ ቀደም በነበረው ጦርነት፤ የጦር ወንጀል እና በሰብአዊነት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችን ጨምሮ በርካታ ጥሰቶች መመዝገባቸውን ያስታወሰው ተቋሙ በጥፋተኞች ላይ ምርመራ እና ክስ ያለማቅረብ አካሄድ ልማዳዊ ሊሆን አይገባም ብሏል።
የፌደራል መንግሥት እና የትግራይ ባለስልጣናት ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችን እንዲያከብሩ፣ ሰላማዊ ሰዎችን እንዲጠብቁ፣ እንዲሁም ለነጻ የሰብአዊ መብት ተከታታዮች፣ ለሰብአዊ እርዳታ አቅራቢዎች እና ለገለልተኛ መገናኛ ብዙሃን ያልተገደበ እንቅስቃሴ ፈቃድ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርቧል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
ካንተ ጋር በመስራቴ ኩራት ይሰማኛል
አንጀሊና ጆሊ
#ethiopia | አንጄሊና ጆሊ የቲፐረሪ ዓለም አቀፍ የሰላም ሽልማት ላሸነፈው የሙያ አጋሯ አድናቆቷን አቅርባለች።
የ2025 የቲፐረሪ ዓለም አቀፍ የሰላም ሽልማት ተሸላሚ ለሆነው የረጅም ጊዜ ወዳጇ እና የሙያ አጋሯ የሆነው ፎቶግራፈሯ አድናቆቷን ገልጻለች።
ጆሊ በሰጠችው አስተያየት የሙያ አጋሯ በፎቶግራፍ ሙያው በኩል ለሰላምና ለሰብአዊነት ላበረከተው አስተዋጽኦ ይህንን ታላቅ የሰላም ሽልማት በማሸነፉ መደሰቷን ገልጻ የደስታው ተካፋይ መሆኗን ገልጻለች።
አንጀሊና ጆሊ ለበርካታ ዓመታት ከሙያ አጋሯ ጋር አብራ ለመስራት በመታደሏ ኩራት እንደሚሰማትም ገልፃለች።
ሽልማቱ በስራዎቹ አማካኝነት ለዓለም አቀፍ ሰላምና ሰብአዊነት ላበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ ውጤት ነው ስትል የተናገረችው።
የቲፐረሪ ዓለም አቀፍ የሰላም ሽልማት በየዓመቱ በዓለም ዙሪያ ለሰላም ለሰብአዊ መብት እና ለግጭቶች እልባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለሚያደርጉ አካላት የሚሰጥ ዓለም አቀፍ ሽልማት ነው።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #peace #award #angelinajolly
አንጀሊና ጆሊ
#ethiopia | አንጄሊና ጆሊ የቲፐረሪ ዓለም አቀፍ የሰላም ሽልማት ላሸነፈው የሙያ አጋሯ አድናቆቷን አቅርባለች።
የ2025 የቲፐረሪ ዓለም አቀፍ የሰላም ሽልማት ተሸላሚ ለሆነው የረጅም ጊዜ ወዳጇ እና የሙያ አጋሯ የሆነው ፎቶግራፈሯ አድናቆቷን ገልጻለች።
ጆሊ በሰጠችው አስተያየት የሙያ አጋሯ በፎቶግራፍ ሙያው በኩል ለሰላምና ለሰብአዊነት ላበረከተው አስተዋጽኦ ይህንን ታላቅ የሰላም ሽልማት በማሸነፉ መደሰቷን ገልጻ የደስታው ተካፋይ መሆኗን ገልጻለች።
አንጀሊና ጆሊ ለበርካታ ዓመታት ከሙያ አጋሯ ጋር አብራ ለመስራት በመታደሏ ኩራት እንደሚሰማትም ገልፃለች።
ሽልማቱ በስራዎቹ አማካኝነት ለዓለም አቀፍ ሰላምና ሰብአዊነት ላበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ ውጤት ነው ስትል የተናገረችው።
የቲፐረሪ ዓለም አቀፍ የሰላም ሽልማት በየዓመቱ በዓለም ዙሪያ ለሰላም ለሰብአዊ መብት እና ለግጭቶች እልባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለሚያደርጉ አካላት የሚሰጥ ዓለም አቀፍ ሽልማት ነው።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #peace #award #angelinajolly
3 days ago
ኢትዮጵያ ሆይ ! - ስደተኛው ልጅሽ ከ27 ዓመታት በኋላ መጥቷል! - ደስ ይበልሽ!"
· አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ፦ የሰዎች ህመም የሚሰማቸው፣ ተስፋን በተግባር የሚተረጉሙት ስራ ፈጣሪ
“Life’s most persistent and urgent question is, 'What are you doing for others?'”
(የህይወት ዘወተር እና አጣዳፊው ጥያቄ፦ ‘ለሌሎች ሰዎች ምን እያደረግክ ነው?’ የሚለው ነው።)
— ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር
በማህበረሰብ ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶችን አይቶ ከመቆጨት ይልቅ የመፍትሔ አካል ለመሆን መነሳት የትልልቅ ሰዎች መለያ ባህሪይ ነው። በትውልደ ኢትዮጵያዊው ስራ ፈጣሪ አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ዘንድም የሚታየው ይህ ህያው እውነት ነው፤ ጥበብን፣ የበጎ አድራጎት መንፈስን እና ዘመናዊ የህክምና አገልግሎትን በማስተሳሰር በሀገራችን ልዩ የለውጥ አሻራ በማስቀመጥ ላይ ይገኛሉ።
የተድላ አምቡላንስ መወለድ፦
የህይወት አድን አገልግሎት ራዕይ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በሀገራችን በህክምና ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትልቅ ክፍተት በጥናት በመረዳት ነው "ተድላ አምቡላንስን" ወደ ስራ ያስገቡት። በተለይም አካል ጉዳተኞች፣ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት (ኦቲዝም) ያለባቸው፣ የዳያሊሲስ ህመምተኞች እና አረጋውያን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ የሚያጋጥማቸውን የእንቅስቃሴ እና የትራንስፖርት እንግልት በመመልከት፣ ደረጃውን የጠበቀና ዘመናዊ የድንገተኛ እና ድንገተኛ ያልሆነ የህክምና መጓጓዣ አገልግሎት እንዲመሰረት አድርገዋል።
ድርጅቱ ከንግድ ስራ በላይ የማህበረሰብ አለኝታነትን መርሁ በማድረግ፦
· ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ያቀረበ፣
· በገንዘብም ሆነ በአገልግሎት ደረጃ አቅም የሌላቸውን ለመደገፍ የተጋ፣
· ለሁሉ አቀፍ ተደራሽነትና ለዜጎች ክብር የቆመ ተቋም ሆኖ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።
“The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others.”
(ራስህን ለማግኘት የሚቻለው የተሻለው መንገድ በሌሎች አገልግሎት ውስጥ ራስህን ስትሰጥ ነው።)
— ማሃትማ ጋንዲ
“ማንም የላት”፦
ጥበብ ለሰብአዊነት እና ለማህበራዊ ንቅናቄ
አቶ ሳሚ ከስራ ፈጣሪነታቸው ባሻገር፣ ጥበብ ለማህበራዊ ለውጥ ያላትን ትልቅ ሀይል በመረዳት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ “ማንም የላት” የተሰኘውን ታሪካዊ የኅብረት ዜማ ፕሮዲዩስ አድርገዋል።
ይህ ስራ በግጥም ናትናኤል ግርማቸው፣ በዜማ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ በቅንብር ታምሩ አማረ (ቶሚ) እንዲሁም በዳይሬክቲንግ ነፃዓለም አብዲ የተቃኘ ሲሆን፤ ድምፃውያን ማስተዋል እያዩ፣ ሄዋን ገብረወልድ፣ ሀና ግርማ እና አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) ድምፃቸውን ሰጥተውበታል። ከ50 በላይ የሙያ አጋሮች የተሳተፉበት ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ ህብረተሰቡን ስሜታዊ ጉዳት ውስጥ ሳይከት በደማቅ ቅንብር የችግሩን አሳሳቢነትና የለውጥ አስፈላጊነት ያሳያል።
አካል ጉዳተኝነት የችግር ምንጭ ሳይሆን፣ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እና የትራንስፖርት እጥረት ዋናው ክፍተት መሆኑን ማሳወቅ ነው። “ማንም የላት” የሚለውን ስሜት “እኛ አለንላት!”በሚል አዎንታዊ ምላሽ ለመተካት ያለመ ማህበራዊ ንቅናቄ ነው።
አቶ ሳሚ ካህሳይ እና ድርጅታቸው ተድላ አምቡላንስ ቃላቸውን በተግባር በማስመስከር፤ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ በተደረገ ስነ-ስርዓት፦የሙዚቃ ቪዲዮውን ገቢ፦ በሰይፉ ኦን ኢቢኤስ (Seifu on EBS) የዩቲዩብ ቻናል ተለቆ የሚሰበሰበው ሙሉ ገቢ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማዕከል እንዲሆን አስረክበው ነበር።
በርካታ ዊልቸሮች፣ ዘይት፣ ላርጎ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለመቄዶንያ መስራች ለዶ/ር ቢንያም በለጠ በአካል አስረክበዋል።
ተድላ አምቡላንስ ለማንኛውም ሰዓት ለመቄዶንያ ማዕከል ነፃ የአምቡላንስ አገልግሎት ለመስጠት በይፋ ቃል ገብተዋል።
የአቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ህልም በዋና ከተማው አዲስ አበባ ብቻ የተገደበ አይደለም። በክልሎች፣ በገጠራማ አካባቢዎች እና ክፍለ ሀገራት የሚኖሩ፣ አማራጭ ያጡ ዜጎች ዘንድ ይሄው ዘመናዊና የተከበረ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲደርስ ከመንግስት እና ከተለያዩ አካላት ጋር በትስስር ለመስራት አቅደዋል።
“No one has ever become poor by giving.”
(መስጠት ማንም ሰው ደሃ አያደርግም።)
— አን ፍራንክ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ በስራ ፈጠራቸው ሀገራዊ ክፍተትን የደፈኑ፣ በጥበብ ስራቸው የማህበረሰብ ህሊናን ያነቁ፣ በበጎ አድራጎታቸው ደግሞ የብዙዎችን እምባ ያበሱ የዘመናችን አርአያ ናቸው።
ተድላ አምቡላንስ “ሕይወትን ለማስቀጠል እየመጣን ነው!” በሚለው መሪ ቃሉ፣ የብዙዎችን ህይወት የመታደግ እና ተስፋ የመንዛት ታላቅ ሀገራዊ አገልግሎቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።
መደምደሚያ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ከ 27 ዓመታት ሰድት በኋላ አገር ቤት መጥተዋል። የእናት ሀገር ኢትዮጵያ ጥሪ ተቀብለው "እናቴ፤ ኢትዮጵያ ሆይ ! - ስደተኛው ልጅሽ ከ27 ዓመታት በኋላ መጥቷል! - ደስ ይበልሽ!"
የሀገር ጥሪን የመለሰ የዲያስፖራ ተሳትፎ፦ ህልምን በሀገር ላይ መተርጎም እንደነሳሚ ነው።
“Ask not what your country can do for you — ask what you can do for your country.”*
(ሀገሬ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን፣ እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ ብለህ ጠይቅ።)
— ጆን ኤፍ. ኬኔዲ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በምዕራቡ ዓለም (በአሜሪካ) ያካበቱትን የሙያ ልምድ፣ እውቀትና ሀብት ይዘው ወደ ሀገራቸው በመመለስ በህክምናና በትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩት በምክንያት ነው። መንግስትና የሀገር ጥሪ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያቀረቡትን ጥሪ መሰረት በማድረግ፣ በውጭ ሀገር ያዩትን ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥና ህልማቸውን በሀገራቸው ምድር ላይ ተግባራዊ አድርገዋል።
ይህ እርምጃቸው ክፍተቶችን በመሙላት ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተ ሲሆን፤ ሌሎች በውጭ ሀገር የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንም በየተሰማሩበት የሙያ ዘርፍ መጥተው ሀገራቸውንና ህዝባቸውን እንዲያገለግሉ ትልቅ ማነቃቂያና መንገድ ጠራጊ አርአያ የሚሆን ነው።
እናንት ያገሬ ልጆች
ግልጽነት ለዘላለም ይኑር!
መሥራት ጀግንነት ነው፤ ማድነቅ ደግሞ ጀግንነት ነው!
ለሥራቸው፤ ለሰበአዊነታቸው እጅ እንነሳለን!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
"ሕይወትን ማዳን፤ የመጀመሪያ ቅድሚያችን!"
– ተድላ አንቡላንስ
📞 ለአስቸኳይ ጥሪዎች 24 ሰዓት፣ 7 ቀናት ዝግጁ
☎️ +251 985 585 888
📞 8558
የማኅበራዊ ሚዲያ ሊንኮች ናቸው - ይከተሉን፦
Facebook: fb.com/Tedlaambulance
Instagram: instagram.com/tedlaambulance
Telegram: t.me/tedlaambulanceservice
TikTok: tiktok.com/tedlaambulance
· አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ፦ የሰዎች ህመም የሚሰማቸው፣ ተስፋን በተግባር የሚተረጉሙት ስራ ፈጣሪ
“Life’s most persistent and urgent question is, 'What are you doing for others?'”
(የህይወት ዘወተር እና አጣዳፊው ጥያቄ፦ ‘ለሌሎች ሰዎች ምን እያደረግክ ነው?’ የሚለው ነው።)
— ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር
በማህበረሰብ ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶችን አይቶ ከመቆጨት ይልቅ የመፍትሔ አካል ለመሆን መነሳት የትልልቅ ሰዎች መለያ ባህሪይ ነው። በትውልደ ኢትዮጵያዊው ስራ ፈጣሪ አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ዘንድም የሚታየው ይህ ህያው እውነት ነው፤ ጥበብን፣ የበጎ አድራጎት መንፈስን እና ዘመናዊ የህክምና አገልግሎትን በማስተሳሰር በሀገራችን ልዩ የለውጥ አሻራ በማስቀመጥ ላይ ይገኛሉ።
የተድላ አምቡላንስ መወለድ፦
የህይወት አድን አገልግሎት ራዕይ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በሀገራችን በህክምና ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትልቅ ክፍተት በጥናት በመረዳት ነው "ተድላ አምቡላንስን" ወደ ስራ ያስገቡት። በተለይም አካል ጉዳተኞች፣ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት (ኦቲዝም) ያለባቸው፣ የዳያሊሲስ ህመምተኞች እና አረጋውያን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ የሚያጋጥማቸውን የእንቅስቃሴ እና የትራንስፖርት እንግልት በመመልከት፣ ደረጃውን የጠበቀና ዘመናዊ የድንገተኛ እና ድንገተኛ ያልሆነ የህክምና መጓጓዣ አገልግሎት እንዲመሰረት አድርገዋል።
ድርጅቱ ከንግድ ስራ በላይ የማህበረሰብ አለኝታነትን መርሁ በማድረግ፦
· ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ያቀረበ፣
· በገንዘብም ሆነ በአገልግሎት ደረጃ አቅም የሌላቸውን ለመደገፍ የተጋ፣
· ለሁሉ አቀፍ ተደራሽነትና ለዜጎች ክብር የቆመ ተቋም ሆኖ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።
“The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others.”
(ራስህን ለማግኘት የሚቻለው የተሻለው መንገድ በሌሎች አገልግሎት ውስጥ ራስህን ስትሰጥ ነው።)
— ማሃትማ ጋንዲ
“ማንም የላት”፦
ጥበብ ለሰብአዊነት እና ለማህበራዊ ንቅናቄ
አቶ ሳሚ ከስራ ፈጣሪነታቸው ባሻገር፣ ጥበብ ለማህበራዊ ለውጥ ያላትን ትልቅ ሀይል በመረዳት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ “ማንም የላት” የተሰኘውን ታሪካዊ የኅብረት ዜማ ፕሮዲዩስ አድርገዋል።
ይህ ስራ በግጥም ናትናኤል ግርማቸው፣ በዜማ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ በቅንብር ታምሩ አማረ (ቶሚ) እንዲሁም በዳይሬክቲንግ ነፃዓለም አብዲ የተቃኘ ሲሆን፤ ድምፃውያን ማስተዋል እያዩ፣ ሄዋን ገብረወልድ፣ ሀና ግርማ እና አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) ድምፃቸውን ሰጥተውበታል። ከ50 በላይ የሙያ አጋሮች የተሳተፉበት ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ ህብረተሰቡን ስሜታዊ ጉዳት ውስጥ ሳይከት በደማቅ ቅንብር የችግሩን አሳሳቢነትና የለውጥ አስፈላጊነት ያሳያል።
አካል ጉዳተኝነት የችግር ምንጭ ሳይሆን፣ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እና የትራንስፖርት እጥረት ዋናው ክፍተት መሆኑን ማሳወቅ ነው። “ማንም የላት” የሚለውን ስሜት “እኛ አለንላት!”በሚል አዎንታዊ ምላሽ ለመተካት ያለመ ማህበራዊ ንቅናቄ ነው።
አቶ ሳሚ ካህሳይ እና ድርጅታቸው ተድላ አምቡላንስ ቃላቸውን በተግባር በማስመስከር፤ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ በተደረገ ስነ-ስርዓት፦የሙዚቃ ቪዲዮውን ገቢ፦ በሰይፉ ኦን ኢቢኤስ (Seifu on EBS) የዩቲዩብ ቻናል ተለቆ የሚሰበሰበው ሙሉ ገቢ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማዕከል እንዲሆን አስረክበው ነበር።
በርካታ ዊልቸሮች፣ ዘይት፣ ላርጎ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለመቄዶንያ መስራች ለዶ/ር ቢንያም በለጠ በአካል አስረክበዋል።
ተድላ አምቡላንስ ለማንኛውም ሰዓት ለመቄዶንያ ማዕከል ነፃ የአምቡላንስ አገልግሎት ለመስጠት በይፋ ቃል ገብተዋል።
የአቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ህልም በዋና ከተማው አዲስ አበባ ብቻ የተገደበ አይደለም። በክልሎች፣ በገጠራማ አካባቢዎች እና ክፍለ ሀገራት የሚኖሩ፣ አማራጭ ያጡ ዜጎች ዘንድ ይሄው ዘመናዊና የተከበረ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲደርስ ከመንግስት እና ከተለያዩ አካላት ጋር በትስስር ለመስራት አቅደዋል።
“No one has ever become poor by giving.”
(መስጠት ማንም ሰው ደሃ አያደርግም።)
— አን ፍራንክ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ በስራ ፈጠራቸው ሀገራዊ ክፍተትን የደፈኑ፣ በጥበብ ስራቸው የማህበረሰብ ህሊናን ያነቁ፣ በበጎ አድራጎታቸው ደግሞ የብዙዎችን እምባ ያበሱ የዘመናችን አርአያ ናቸው።
ተድላ አምቡላንስ “ሕይወትን ለማስቀጠል እየመጣን ነው!” በሚለው መሪ ቃሉ፣ የብዙዎችን ህይወት የመታደግ እና ተስፋ የመንዛት ታላቅ ሀገራዊ አገልግሎቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።
መደምደሚያ
አቶ ሳሚ ካህሳይ ተድላ ከ 27 ዓመታት ሰድት በኋላ አገር ቤት መጥተዋል። የእናት ሀገር ኢትዮጵያ ጥሪ ተቀብለው "እናቴ፤ ኢትዮጵያ ሆይ ! - ስደተኛው ልጅሽ ከ27 ዓመታት በኋላ መጥቷል! - ደስ ይበልሽ!"
የሀገር ጥሪን የመለሰ የዲያስፖራ ተሳትፎ፦ ህልምን በሀገር ላይ መተርጎም እንደነሳሚ ነው።
“Ask not what your country can do for you — ask what you can do for your country.”*
(ሀገሬ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን፣ እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ ብለህ ጠይቅ።)
— ጆን ኤፍ. ኬኔዲ
አቶ ሳሚ ካህሳይ በምዕራቡ ዓለም (በአሜሪካ) ያካበቱትን የሙያ ልምድ፣ እውቀትና ሀብት ይዘው ወደ ሀገራቸው በመመለስ በህክምናና በትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩት በምክንያት ነው። መንግስትና የሀገር ጥሪ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያቀረቡትን ጥሪ መሰረት በማድረግ፣ በውጭ ሀገር ያዩትን ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥና ህልማቸውን በሀገራቸው ምድር ላይ ተግባራዊ አድርገዋል።
ይህ እርምጃቸው ክፍተቶችን በመሙላት ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተ ሲሆን፤ ሌሎች በውጭ ሀገር የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንም በየተሰማሩበት የሙያ ዘርፍ መጥተው ሀገራቸውንና ህዝባቸውን እንዲያገለግሉ ትልቅ ማነቃቂያና መንገድ ጠራጊ አርአያ የሚሆን ነው።
እናንት ያገሬ ልጆች
ግልጽነት ለዘላለም ይኑር!
መሥራት ጀግንነት ነው፤ ማድነቅ ደግሞ ጀግንነት ነው!
ለሥራቸው፤ ለሰበአዊነታቸው እጅ እንነሳለን!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
"ሕይወትን ማዳን፤ የመጀመሪያ ቅድሚያችን!"
– ተድላ አንቡላንስ
📞 ለአስቸኳይ ጥሪዎች 24 ሰዓት፣ 7 ቀናት ዝግጁ
☎️ +251 985 585 888
📞 8558
የማኅበራዊ ሚዲያ ሊንኮች ናቸው - ይከተሉን፦
Facebook: fb.com/Tedlaambulance
Instagram: instagram.com/tedlaambulance
Telegram: t.me/tedlaambulanceservice
TikTok: tiktok.com/tedlaambulance
Sponsored by
Surafel
6 days ago
ይድረስ ለአራቱ ድምፃውያን
– “ማንም የላት” ከተሰኘው የኅብረት ዜማ ጋር በተያያዘ
ከተመስገን ኡካሬ (የሐጌ ልጅ)
#ethiopia | "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ሙዚቃ ብቻ አይደለም፤ የህሊና ጥሪ፣ የማህበራዊ ኃላፊነት ማንቂያ እና የሰብአዊነት መልዕክት ነው። ይህ ስራ የአካል ጉዳተኞችንና የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያላቸውን ወገኖች በርኅራኄ ከመመልከት ይልቅ፣ እንደ ሙሉ መብት ባለቤቶች እንድናያቸው ያስጠይቃል።
ሙዚቃው የሚያነሳው ዋና ጥያቄ አካል ጉዳተኝነት ሳይሆን፣ እኛ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እጥረት ነው። ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ስራ፣ የህዝብ አገልግሎቶች እና ማህበራዊ ተሳትፎ ለሁሉም እኩል ተደራሽ ናቸው ወይ? የሚለውን ጥያቄ በጥልቅ ያቀርባል።
የኅብረት ዜማዎች ሁልጊዜም የዘመናቸውን ማህበራዊ ጉዳይ ያንጸባርቃሉ። "ማለባበስ ይቅር"፣ "ስደት"፣ "ሰላም ለሀገራችን" እና ሌሎችም እንደ ነበሩት ሁሉ፣ "ማንም የላት" ደግሞ የዚህ ዘመን የህሊና ጥሪ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ ስራ በስሜት ብቻ የተሞላ አይደለም፤ መፍትሄ የሚፈልግ ጥያቄ ያቀርባል። "ማንም የላት" የሚለውን አባባል "እኛም አለን" በሚል ተግባራዊ መልስ እንድንተካው ይጋብዘናል።
በዚህ ዜማ ላይ የተሳተፉት ድምፃዊ ማስተዋል እያዩ፣ ድምፃዊት ሀና ግርማ፣ ድምፃዊ አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) እና ድምፃዊት ሄዋን ገብረወልድ እያንዳንዳቸው መልዕክቱን በሚመጥን ስሜት አቅርበዋል።
ግጥሙን ናትናኤል ግርማቸው፣ ዜማውን አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ ቅንብሩን ደግሞ ታምሩ አማረ (ቶሚ) በሙያዊ ብቃት አስውበውታል። የግጥሙ፣ የዜማው፣ የድምፅ አቀራረቡና የቅንብሩ መዋሃድ ሙዚቃውን ከመዝናኛነት በላይ ወደ ማህበራዊ ንቅናቄ አሳድጎታል።
ይህ ዜማ የሚያስታውሰን አንድ እውነት አለ፤ ሰብአዊነት በቃላት ሳይሆን በተግባር ይለካል። አካል ጉዳተኞች ርኅራኄ አይፈልጉም፤ እኩል ዕድል፣ ተደራሽነትና ክብር ይፈልጋሉ።
ይድረስ ለአራቱ ድምፃውያን፤ ለህዝብ የሚያስብ፣ ህሊናን የሚያነቃ እና ማህበረሰብን ወደ በጎ ለውጥ የሚጋብዝ ስራ ስላቀረባችሁ ምስጋና ይገባችኋል። ይህ ዜማ በሙዚቃ ታሪክ ውስጥ እንደ ዜማ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ማህበራዊ ጥሪ የሚታወስ ስራ ይሆናል።
አቶ ሳሚ ተድላ ( የተድላ አምቡላንስ መሥራችና ባለቤት ) "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ፕሮውዲሰር ምስጋና ይገባቸዋል።
በተለይም ጥበብንና በጎ አድራጎትን አጣምሮ በመያዝ፣ አቅም የሌላቸውንና ረዳት ያጡ ወገኖችን ድምፅ ለማሰማት ያደረጉት ጥረትና ያወጡት ወጪ የሚወደስ ነው።
በተጨማሪም በተድላ አምቡላንስ በኩል የሚያደርጉት ድገስ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴ፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ ትልቅ አክብሮትና ምስጋና የሚያሰጣቸው ያደርጋቸዋል። እንደዚህ ያሉ በጎ አድራጊ ባለሃብቶችና ድርጅቶች ለሌላውም አርአያ የሚሆኑ ናቸው።
– “ማንም የላት” ከተሰኘው የኅብረት ዜማ ጋር በተያያዘ
ከተመስገን ኡካሬ (የሐጌ ልጅ)
#ethiopia | "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ሙዚቃ ብቻ አይደለም፤ የህሊና ጥሪ፣ የማህበራዊ ኃላፊነት ማንቂያ እና የሰብአዊነት መልዕክት ነው። ይህ ስራ የአካል ጉዳተኞችንና የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያላቸውን ወገኖች በርኅራኄ ከመመልከት ይልቅ፣ እንደ ሙሉ መብት ባለቤቶች እንድናያቸው ያስጠይቃል።
ሙዚቃው የሚያነሳው ዋና ጥያቄ አካል ጉዳተኝነት ሳይሆን፣ እኛ እንደ ማህበረሰብ የፈጠርነው የመዳረሻ እጥረት ነው። ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ስራ፣ የህዝብ አገልግሎቶች እና ማህበራዊ ተሳትፎ ለሁሉም እኩል ተደራሽ ናቸው ወይ? የሚለውን ጥያቄ በጥልቅ ያቀርባል።
የኅብረት ዜማዎች ሁልጊዜም የዘመናቸውን ማህበራዊ ጉዳይ ያንጸባርቃሉ። "ማለባበስ ይቅር"፣ "ስደት"፣ "ሰላም ለሀገራችን" እና ሌሎችም እንደ ነበሩት ሁሉ፣ "ማንም የላት" ደግሞ የዚህ ዘመን የህሊና ጥሪ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ ስራ በስሜት ብቻ የተሞላ አይደለም፤ መፍትሄ የሚፈልግ ጥያቄ ያቀርባል። "ማንም የላት" የሚለውን አባባል "እኛም አለን" በሚል ተግባራዊ መልስ እንድንተካው ይጋብዘናል።
በዚህ ዜማ ላይ የተሳተፉት ድምፃዊ ማስተዋል እያዩ፣ ድምፃዊት ሀና ግርማ፣ ድምፃዊ አብርሃም በላይነህ (ሻላዬ) እና ድምፃዊት ሄዋን ገብረወልድ እያንዳንዳቸው መልዕክቱን በሚመጥን ስሜት አቅርበዋል።
ግጥሙን ናትናኤል ግርማቸው፣ ዜማውን አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፣ ቅንብሩን ደግሞ ታምሩ አማረ (ቶሚ) በሙያዊ ብቃት አስውበውታል። የግጥሙ፣ የዜማው፣ የድምፅ አቀራረቡና የቅንብሩ መዋሃድ ሙዚቃውን ከመዝናኛነት በላይ ወደ ማህበራዊ ንቅናቄ አሳድጎታል።
ይህ ዜማ የሚያስታውሰን አንድ እውነት አለ፤ ሰብአዊነት በቃላት ሳይሆን በተግባር ይለካል። አካል ጉዳተኞች ርኅራኄ አይፈልጉም፤ እኩል ዕድል፣ ተደራሽነትና ክብር ይፈልጋሉ።
ይድረስ ለአራቱ ድምፃውያን፤ ለህዝብ የሚያስብ፣ ህሊናን የሚያነቃ እና ማህበረሰብን ወደ በጎ ለውጥ የሚጋብዝ ስራ ስላቀረባችሁ ምስጋና ይገባችኋል። ይህ ዜማ በሙዚቃ ታሪክ ውስጥ እንደ ዜማ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ማህበራዊ ጥሪ የሚታወስ ስራ ይሆናል።
አቶ ሳሚ ተድላ ( የተድላ አምቡላንስ መሥራችና ባለቤት ) "ማንም የላት" የተሰኘው የኅብረት ዜማ ፕሮውዲሰር ምስጋና ይገባቸዋል።
በተለይም ጥበብንና በጎ አድራጎትን አጣምሮ በመያዝ፣ አቅም የሌላቸውንና ረዳት ያጡ ወገኖችን ድምፅ ለማሰማት ያደረጉት ጥረትና ያወጡት ወጪ የሚወደስ ነው።
በተጨማሪም በተድላ አምቡላንስ በኩል የሚያደርጉት ድገስ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴ፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ ትልቅ አክብሮትና ምስጋና የሚያሰጣቸው ያደርጋቸዋል። እንደዚህ ያሉ በጎ አድራጊ ባለሃብቶችና ድርጅቶች ለሌላውም አርአያ የሚሆኑ ናቸው።
7 days ago
ሳዳም በስቅላት!
በኢራቅ ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች አልተገኙም!
#ethiopia | እ.ኤ.አ. መጋቢት 20 ቀን 2003 አሜሪካ ከብሪታንያ እና ከሌሎች አጋሮቿ ጋር በመሆን በኢራቅ ላይ ድንገተኛ ወረራ ፈጸመች።
የወረራው ዋነኛ ምክንያት ሳዳም ሁሴን የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች ባለቤት ናቸው ለዓለምም ስጋት ደቅነዋል የሚል ነበረ።
ይህንን ተከትሎ በባግዳድ ሰማይ ስር የተካሄደው ከባድ የቦምብ ድብደባ የብዙ ንጹሃንን ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን መኖሪያ ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ ትምህርት ቤቶች እና መሠረተ ልማቶች እንዲወድሙ ምክንያት ሆኗል።
በርካታ ቤተሰቦች ሲፈናቀሉ፣ ሕፃናት ተቀብረዋል አገሪቱም እስከዛሬ ድረስ ወደማያበቃ መከራና ውዥንብር ውስጥ ገብታለች።
ከወራት መሸሸግ በኋላ በታህሳስ 13 ቀን 2003 ሳዳም ሁሴን በተክሪት አቅራቢያ በአሜሪካ ጦር ከተያዙ በኋላ በጥቅምት 19 ቀን 2005 በባግዳድ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር በሚገኘው የኢራቅ ከፍተኛ ችሎት ፍርድ ቤት ቀረቡ።
በሕዳር 5 ቀን 2006 በ1982 በዱጃይል ከተፈጸመው የሰዎች ግድያ ጋር ተያይዞ በሰብአዊነት ላይ በተፈጸመ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በሞት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው ሲሆን፣ በታህሳስ 30 ቀን 2006 ቅጣታቸው ስቅላት ሆኗል።
ሆኖም ለወረራውና ለተከተለው የሃያ ዓመታት መከራ መነሻ የተደረጉት የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች በኢራቅ ምድር በጭራሽ ሳይገኙ ቀርተዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
በኢራቅ ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች አልተገኙም!
#ethiopia | እ.ኤ.አ. መጋቢት 20 ቀን 2003 አሜሪካ ከብሪታንያ እና ከሌሎች አጋሮቿ ጋር በመሆን በኢራቅ ላይ ድንገተኛ ወረራ ፈጸመች።
የወረራው ዋነኛ ምክንያት ሳዳም ሁሴን የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች ባለቤት ናቸው ለዓለምም ስጋት ደቅነዋል የሚል ነበረ።
ይህንን ተከትሎ በባግዳድ ሰማይ ስር የተካሄደው ከባድ የቦምብ ድብደባ የብዙ ንጹሃንን ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን መኖሪያ ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ ትምህርት ቤቶች እና መሠረተ ልማቶች እንዲወድሙ ምክንያት ሆኗል።
በርካታ ቤተሰቦች ሲፈናቀሉ፣ ሕፃናት ተቀብረዋል አገሪቱም እስከዛሬ ድረስ ወደማያበቃ መከራና ውዥንብር ውስጥ ገብታለች።
ከወራት መሸሸግ በኋላ በታህሳስ 13 ቀን 2003 ሳዳም ሁሴን በተክሪት አቅራቢያ በአሜሪካ ጦር ከተያዙ በኋላ በጥቅምት 19 ቀን 2005 በባግዳድ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር በሚገኘው የኢራቅ ከፍተኛ ችሎት ፍርድ ቤት ቀረቡ።
በሕዳር 5 ቀን 2006 በ1982 በዱጃይል ከተፈጸመው የሰዎች ግድያ ጋር ተያይዞ በሰብአዊነት ላይ በተፈጸመ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በሞት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው ሲሆን፣ በታህሳስ 30 ቀን 2006 ቅጣታቸው ስቅላት ሆኗል።
ሆኖም ለወረራውና ለተከተለው የሃያ ዓመታት መከራ መነሻ የተደረጉት የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች በኢራቅ ምድር በጭራሽ ሳይገኙ ቀርተዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
8 days ago
ሳዑዲ አረቢያ አምስት ተጨማሪ ኢትዮጵያውያንን በሞት ቀጣች
የሳዑዲ አረቢያ አገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አምስት ተጨማሪ ኢትዮጵያውያንን በሞት መቅጣቱን አስታወቀ።
ወደ ሳዑዲ አረቢያ አደንዛዥ ዕጽ በድብቅ ሲያስገቡ ተይዘዋል የተባሉት ኢትዮጵያውያን በሞት የተቀጡት ሰኞ ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም. በአሲር ግዛት መሆኑን የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስቴር ገልጿል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሳዑዲ መንግሥት የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር 17 ደርሷል።
ከዚህ ቀደም ሰኔ 16 አምስት፣ ሰኔ 1 አራት፣ ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም. ደግሞ ሦስት ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ተፈጽሞባቸዋል።
የሳዑዲ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው "የፀጥታ አካላት ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር አውለው ባደረጉት ምርመራ ጥፋቱን መፈጸማቸው በመረጋገጡ ክስ እንዲመሠረትባቸው ተደርጓል" ብሏል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ ይግባኝ ተጠይቆ የነበረ ቢሆንም የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ብይኑን በማጽናቱ እና በሸሪዓ ሕግ መሠረት የንጉሣዊ ትዕዛዙ ተፈጻሚ አንዲሆን መደረጉ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ የሞት ቅጣቱ ዓላማ "የዜጎችን ደኅንነት ለመከላከል እና ነዋሪዎችን ከአደንዛዥ ዕፅ አደጋ ለመጠበቅ እንዲሁም አደንዛዥ ዕፅን ለሚያዘዋውሩ እና ለሚያስፋፉ አካላት በሕግ የተደነገጉትን እጅግ ከባድ ቅጣቶች ተፈጸሚ ማድረግ" መሆኑን በመግለጫው ላይ ጠቅሷል።
ከዚህ ቀደም ሂዩማን ራይትስ ዎች ሐሚስ ሙሻይት በተባለው እስር ቤት ቢያንስ 63 ኢትዮጵያውያን ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት እንደተጋረጠባቸው በማስጠንቀቅ መግለጫ አውጥቶ ነበር።
የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ይህንን መግለጫ ካወጣ በኋላ የ14 ኢትዮጵያውያን በሞት ተቀጥተዋል።
የመገናኛ ብዙኃን ከ200 በላይ ኢትዮጵያውያን በሐሚስ ሙሻይት እስር ቤት የሞት ቅጣታቸውን እየተጠባበቁ መሆኑን ዘግበዋል።
ነገር ግን ይህ ቁጥር በሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በገለልተኝነት አልተረጋገጠም።
እንደ ሳዑዲ ባለሥልጣናት ገለጻ ከሆነ ኢትዮጵያውያኑ ሞት የተፈረደባቸው ሃሺሽ ይዘው በመገኘታቸው ነው።
በሂዩማን ራይትስ ዎች ከፍተኛ የስደተኞችና የስደተኞች መብቶች ተመራማሪ የሆኑት ናዲያ ሃርድማን "ሳዑዲ አረቢያ አመጽ ያልተቀላቀለባቸው ወንጀሎችን ፈጽመው የተገኙ የውጭ ዜጎችን ከፍርድ በኋላ መሠረታዊ የፍትህ ሂደትን በመከልከል በሞት ለመቅጣት የላት ቁርጠኝነት ለመብቶቻቸውና ለሕይወታቸው ከፍተኛ አክብሮት አለማሳየቷን ያስረዳል" በማለት ዓለም አቀፍ አጋሮች ጣልቃ እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ዓለም አቀፍ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድኖች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶች እና መንግሥት የሳዑዲ መንግሥት ለስደተኞቹ ምህረት አድርጎ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ እንዲፈቅድ ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ ባወጣው መግለጫ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸውን ስደተኞች በሚመለከት ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ሐምሌ 6 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ አረቢያ የሚመለከታቸው አካላት ጋር "የሕግ ሂደት ላይ ያሉ እና የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው" ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ "ከሚመለከታቸው" የአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር "በቅርበት እየተነጋገረ" መሆኑን አስታውቋል።
በተጨማሪም ሪያድ ውስጥ በሚገኘው ኤምባሲ እና በጅዳ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት አማካኝነት "አስቸጋሪ ሁኔታዎች ለገጠሟቸው የኢትዮጵያውያን ዜጎች ሰብአዊነትን ከግምት ያስገባ" እርምጃ እንዲወሰድ የሚደረገው ጥረት መቀጠሉን ገልጿል።
በዲፕሎማሲያዊ ቢሮዎቹ አማካኝነት ኢትዮጵያውያኑ "የቆንስላ ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ እና ተገቢውን መፍትሔ ለማስገኘት ከሚመለከታቸው የሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር መደበኛ ግንኙነት እና ገንቢ ውይይት" እየተካሄደ መሆኑንም ጠቅሷል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደሚገልጸው፤ ጥረቶች ሳዑዲ ውስጥ ፍርድ የተላለፈባቸው በአጠቃላይ 1,971 ኢትዮጵያውያን ንጉሳዊ ምሕረት እንዲያገኙ አስችለዋል። እነዚህን ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው የመመለስ ተግባር መጀመሩንም በመግለጫው አንስቷል።
BBC
የሳዑዲ አረቢያ አገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አምስት ተጨማሪ ኢትዮጵያውያንን በሞት መቅጣቱን አስታወቀ።
ወደ ሳዑዲ አረቢያ አደንዛዥ ዕጽ በድብቅ ሲያስገቡ ተይዘዋል የተባሉት ኢትዮጵያውያን በሞት የተቀጡት ሰኞ ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም. በአሲር ግዛት መሆኑን የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስቴር ገልጿል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሳዑዲ መንግሥት የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር 17 ደርሷል።
ከዚህ ቀደም ሰኔ 16 አምስት፣ ሰኔ 1 አራት፣ ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም. ደግሞ ሦስት ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ተፈጽሞባቸዋል።
የሳዑዲ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው "የፀጥታ አካላት ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር አውለው ባደረጉት ምርመራ ጥፋቱን መፈጸማቸው በመረጋገጡ ክስ እንዲመሠረትባቸው ተደርጓል" ብሏል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ ይግባኝ ተጠይቆ የነበረ ቢሆንም የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ብይኑን በማጽናቱ እና በሸሪዓ ሕግ መሠረት የንጉሣዊ ትዕዛዙ ተፈጻሚ አንዲሆን መደረጉ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ የሞት ቅጣቱ ዓላማ "የዜጎችን ደኅንነት ለመከላከል እና ነዋሪዎችን ከአደንዛዥ ዕፅ አደጋ ለመጠበቅ እንዲሁም አደንዛዥ ዕፅን ለሚያዘዋውሩ እና ለሚያስፋፉ አካላት በሕግ የተደነገጉትን እጅግ ከባድ ቅጣቶች ተፈጸሚ ማድረግ" መሆኑን በመግለጫው ላይ ጠቅሷል።
ከዚህ ቀደም ሂዩማን ራይትስ ዎች ሐሚስ ሙሻይት በተባለው እስር ቤት ቢያንስ 63 ኢትዮጵያውያን ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት እንደተጋረጠባቸው በማስጠንቀቅ መግለጫ አውጥቶ ነበር።
የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ይህንን መግለጫ ካወጣ በኋላ የ14 ኢትዮጵያውያን በሞት ተቀጥተዋል።
የመገናኛ ብዙኃን ከ200 በላይ ኢትዮጵያውያን በሐሚስ ሙሻይት እስር ቤት የሞት ቅጣታቸውን እየተጠባበቁ መሆኑን ዘግበዋል።
ነገር ግን ይህ ቁጥር በሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በገለልተኝነት አልተረጋገጠም።
እንደ ሳዑዲ ባለሥልጣናት ገለጻ ከሆነ ኢትዮጵያውያኑ ሞት የተፈረደባቸው ሃሺሽ ይዘው በመገኘታቸው ነው።
በሂዩማን ራይትስ ዎች ከፍተኛ የስደተኞችና የስደተኞች መብቶች ተመራማሪ የሆኑት ናዲያ ሃርድማን "ሳዑዲ አረቢያ አመጽ ያልተቀላቀለባቸው ወንጀሎችን ፈጽመው የተገኙ የውጭ ዜጎችን ከፍርድ በኋላ መሠረታዊ የፍትህ ሂደትን በመከልከል በሞት ለመቅጣት የላት ቁርጠኝነት ለመብቶቻቸውና ለሕይወታቸው ከፍተኛ አክብሮት አለማሳየቷን ያስረዳል" በማለት ዓለም አቀፍ አጋሮች ጣልቃ እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ዓለም አቀፍ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድኖች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶች እና መንግሥት የሳዑዲ መንግሥት ለስደተኞቹ ምህረት አድርጎ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ እንዲፈቅድ ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ ባወጣው መግለጫ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸውን ስደተኞች በሚመለከት ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ሐምሌ 6 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ አረቢያ የሚመለከታቸው አካላት ጋር "የሕግ ሂደት ላይ ያሉ እና የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው" ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ "ከሚመለከታቸው" የአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር "በቅርበት እየተነጋገረ" መሆኑን አስታውቋል።
በተጨማሪም ሪያድ ውስጥ በሚገኘው ኤምባሲ እና በጅዳ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት አማካኝነት "አስቸጋሪ ሁኔታዎች ለገጠሟቸው የኢትዮጵያውያን ዜጎች ሰብአዊነትን ከግምት ያስገባ" እርምጃ እንዲወሰድ የሚደረገው ጥረት መቀጠሉን ገልጿል።
በዲፕሎማሲያዊ ቢሮዎቹ አማካኝነት ኢትዮጵያውያኑ "የቆንስላ ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ እና ተገቢውን መፍትሔ ለማስገኘት ከሚመለከታቸው የሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር መደበኛ ግንኙነት እና ገንቢ ውይይት" እየተካሄደ መሆኑንም ጠቅሷል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደሚገልጸው፤ ጥረቶች ሳዑዲ ውስጥ ፍርድ የተላለፈባቸው በአጠቃላይ 1,971 ኢትዮጵያውያን ንጉሳዊ ምሕረት እንዲያገኙ አስችለዋል። እነዚህን ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው የመመለስ ተግባር መጀመሩንም በመግለጫው አንስቷል።
BBC
9 days ago
''I Love You''
የነጻ ምሳ የሚበላበት ሬስቶራንት
#ethiopia |የሆሊውዱ ኮከከብ የዊል ስሚዝ ሁለተኛ ልጅ ድምጻዊና ተዋናይ ጄደን ስሚዝ የራሱን ገቢ ማሳደጊያ የሚሆን ውድ የከበርቴዎች ምግብ ቤት ከመክፈት ይልቅ ቤት አልባዎች በነፃ የሚመገቡበት የበጎ አድራጎት ድርጅት በመስረት ለጎዳና ተዳዳሪዎች አርአያነት ያለው ደግነት እያሳየ ይገኛል።
እ.ኤ.አ. በ2019 "አይ ላቭ ዩ" (I Love You) በሚል ስያሜ በተንቀሳቃሽ የምግብ መኪና የተጀመረው ይህ ጥረት በሎስ አንጀለስ በሚገኘው 'ስኪድ ሮው' ለሚኖሩ ቤት አልባዎች ነፃ የእፅዋት ተወፅኦ ምግቦችን በማቅረብ ስራውን ጀምሯል።
ይህ በጎ አድራጎት በአሁኑ ወቅት አቅሙን በማሳደግ ትኩስ ምግቦችን፣ የታሸጉ ውሃዎችንና የተለገሱ አልባሳትን ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚያቀርብ ተቋም ሆኗል።
በአንዳንድ አጋጣሚዎች በአንድ መርሃ-ግብር ብቻ እስከ 500 የሚደርሱ ነፃ ምግቦችን የሚያከፋፍለው ይህ ድርጅት በቀጣይም በዚሁ አካባቢ ቋሚ ህንፃ በመገንባት በየቀኑ ቁርስ፣ ምሳ እና እራት በነፃ ለማቅረብ እንዲሁም የስራ እድልና አዎንታዊ የማህበረሰብ መኖሪያ ቦታ ለመፍጠር አልሞ እየሰራ ይገኛል።
የዚህ ወደፊት የሚገነባው ምግብ ቤት አሰራር አቅም የሌላቸው ወገኖች በነፃ እንዲመገቡ የሚያደርግ ሲሆን የገንዘብ አቅም ያላቸው ደንበኞች ደግሞ የሌሎችን ምግብ የሚሸፍን ክፍያ እንዲከፍሉ በሚያስችል የመረዳዳት መርህ ላይ የተመሰረተ እንቅስቃሴ ያደርጋል።
ጄደን ስሚዝ ይህንን ተቋም "አይ ላቭ ዩ" ብሎ የሰየመበት ዋና ምክንያት ''ፍቅር በቃል የሚነገር መፈክር ብቻ ሳይሆን በተግባር የሌላውን ሰው ረሃብ በማስወገድ የሚገለጽ እውነተኛ ሰብአዊነት በመሆኑ ነው'' ብሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
የነጻ ምሳ የሚበላበት ሬስቶራንት
#ethiopia |የሆሊውዱ ኮከከብ የዊል ስሚዝ ሁለተኛ ልጅ ድምጻዊና ተዋናይ ጄደን ስሚዝ የራሱን ገቢ ማሳደጊያ የሚሆን ውድ የከበርቴዎች ምግብ ቤት ከመክፈት ይልቅ ቤት አልባዎች በነፃ የሚመገቡበት የበጎ አድራጎት ድርጅት በመስረት ለጎዳና ተዳዳሪዎች አርአያነት ያለው ደግነት እያሳየ ይገኛል።
እ.ኤ.አ. በ2019 "አይ ላቭ ዩ" (I Love You) በሚል ስያሜ በተንቀሳቃሽ የምግብ መኪና የተጀመረው ይህ ጥረት በሎስ አንጀለስ በሚገኘው 'ስኪድ ሮው' ለሚኖሩ ቤት አልባዎች ነፃ የእፅዋት ተወፅኦ ምግቦችን በማቅረብ ስራውን ጀምሯል።
ይህ በጎ አድራጎት በአሁኑ ወቅት አቅሙን በማሳደግ ትኩስ ምግቦችን፣ የታሸጉ ውሃዎችንና የተለገሱ አልባሳትን ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚያቀርብ ተቋም ሆኗል።
በአንዳንድ አጋጣሚዎች በአንድ መርሃ-ግብር ብቻ እስከ 500 የሚደርሱ ነፃ ምግቦችን የሚያከፋፍለው ይህ ድርጅት በቀጣይም በዚሁ አካባቢ ቋሚ ህንፃ በመገንባት በየቀኑ ቁርስ፣ ምሳ እና እራት በነፃ ለማቅረብ እንዲሁም የስራ እድልና አዎንታዊ የማህበረሰብ መኖሪያ ቦታ ለመፍጠር አልሞ እየሰራ ይገኛል።
የዚህ ወደፊት የሚገነባው ምግብ ቤት አሰራር አቅም የሌላቸው ወገኖች በነፃ እንዲመገቡ የሚያደርግ ሲሆን የገንዘብ አቅም ያላቸው ደንበኞች ደግሞ የሌሎችን ምግብ የሚሸፍን ክፍያ እንዲከፍሉ በሚያስችል የመረዳዳት መርህ ላይ የተመሰረተ እንቅስቃሴ ያደርጋል።
ጄደን ስሚዝ ይህንን ተቋም "አይ ላቭ ዩ" ብሎ የሰየመበት ዋና ምክንያት ''ፍቅር በቃል የሚነገር መፈክር ብቻ ሳይሆን በተግባር የሌላውን ሰው ረሃብ በማስወገድ የሚገለጽ እውነተኛ ሰብአዊነት በመሆኑ ነው'' ብሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
13 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የስፔንና የባርሴሎናው ኮከብ ላሚን ያማል የፍቅር ጓደኛ የሆነችው ኢኔስ ጋርሲያ፣ ስፔን የዓለም ዋንጫን ካሸነፈች በኋላ በማኅበራዊ ሚዲያ በኩል የደረሰባትን ሰፊ የስድብና የጥላቻ መልዕክቶች በጽኑ ኮነነች። ጋርሲያ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጿ ባሰፈረችው መልዕክት፣ ሰዎች ከስክሪኑ በስተጀርባ የሚጽፉትን የጥላቻ ቃል ከማሰራጨታቸው በፊት መሠረታዊ የሰው ልጅ አዘኔታና ሰብአዊነት እንዲኖራቸው ጥሪ አቅርባለች።
ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ የዓለም ዋንጫን ካነሳች በኋላ፣ ኢኔስ ጋርሲያ በኒው ዮርክ ኒው ጄርሲ ስታዲየም ከያማል ጋር በደስታ የተነሱትን ፎቶ በማጋራት "አደረግኸው፤ እንኳን ደስ አለህ የኔ ፍቅር፣ የዓለም ሻምፒዮን ነህ" በማለት ደስታዋን ገልጻ ነበር። ሆኖም ይህንን ተከትሎ ከፍተኛ የኦንላይን ትንኮሳና የቃላት ጥቃቶች ደርሰውባታል። ጋርሲያ በሰጠችው ስሜታዊ ምላሽ፣ ከማኅበራዊ ሚዲያ መለያዋ በስተጀርባ የሚሰማት፣ የሚያልቃት፣ ስህተት የሚሰራና ስሜት ያለው የሰው ልጅ መኖሩን ሰዎች ሊረዱ እንደሚገባ አስረድታለች።
አክላም ሰው ሁሉ እሷን እንዲወዳት እንደማትጠብቅና አክብሮት የተሞላበትን ትችት እንደምትቀበል የገለጸችው ኢኔስ፣ ነገር ግን ሰዎችን ዝቅ ለማድረግ፣ ለመሳደብና ክፉ ለመመኘት የሚደረገው ጥረት ፍጹም የጨካኝነት ተግባር መሆኑን ገልጻለች። ምንም አጥፊ ድርጊት ሳትፈጽም እንዲህ ያለ የጥላቻ ማበበሪያ መሆኗ አሳዛኝ መሆኑንና ማኅበራዊ ሚዲያ ይበልጥ ሰብአዊነት የሚንጸባረቅበት ቦታ እንዲሆን ተመኝታለች።
ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ የዓለም ዋንጫን ካነሳች በኋላ፣ ኢኔስ ጋርሲያ በኒው ዮርክ ኒው ጄርሲ ስታዲየም ከያማል ጋር በደስታ የተነሱትን ፎቶ በማጋራት "አደረግኸው፤ እንኳን ደስ አለህ የኔ ፍቅር፣ የዓለም ሻምፒዮን ነህ" በማለት ደስታዋን ገልጻ ነበር። ሆኖም ይህንን ተከትሎ ከፍተኛ የኦንላይን ትንኮሳና የቃላት ጥቃቶች ደርሰውባታል። ጋርሲያ በሰጠችው ስሜታዊ ምላሽ፣ ከማኅበራዊ ሚዲያ መለያዋ በስተጀርባ የሚሰማት፣ የሚያልቃት፣ ስህተት የሚሰራና ስሜት ያለው የሰው ልጅ መኖሩን ሰዎች ሊረዱ እንደሚገባ አስረድታለች።
አክላም ሰው ሁሉ እሷን እንዲወዳት እንደማትጠብቅና አክብሮት የተሞላበትን ትችት እንደምትቀበል የገለጸችው ኢኔስ፣ ነገር ግን ሰዎችን ዝቅ ለማድረግ፣ ለመሳደብና ክፉ ለመመኘት የሚደረገው ጥረት ፍጹም የጨካኝነት ተግባር መሆኑን ገልጻለች። ምንም አጥፊ ድርጊት ሳትፈጽም እንዲህ ያለ የጥላቻ ማበበሪያ መሆኗ አሳዛኝ መሆኑንና ማኅበራዊ ሚዲያ ይበልጥ ሰብአዊነት የሚንጸባረቅበት ቦታ እንዲሆን ተመኝታለች።
22 days ago
አከራዮች ላይ ከተማ አስተዳደሩ የማያዳግም እርምጃ እወስዳለሁ አለ‼️
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያን 11.5 በመቶ ማድረጉን ተከትሎ፣ ሕግን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ አከራዮች ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
በተለይም ተከራዮችን “ቤቱን ለራሴ ወይም ለዘመዴ እፈልገዋለሁ” በሚል ሐሰተኛ ምክንያት በማስለቀቅ፣ በምትኩ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ በመጫን፣ የ11.5 በመቶውን ጭማሪም ሕጋዊ አስመስለው የመጫን ተግባራት በስፋት እየተስተዋሉ ነው።
በተጨማሪም፣ አከራዮች በውል ሰነድ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ11.5 በመቶ ጣሪያ በመጥቀስ በሕጋዊ መንገድ እየተስማሙ፣ በተግባር ግን በአፍ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ በመደራደር ተከራዩን ለከፍተኛ የገንዘብ ጫና የሚዳርጉበት የ”ድርብ ውል” አሰራር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን የተሰጡ ጥቆማዎች ያመለክታሉ። ይህ ድርጊት በግልጽ ሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ ሕገ-ወጥ ተግባር መሆኑን ቢሮው አስገንዝቧል።
በዚህ ረገድ ተከራዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል። በተለይም በአፍ የተጠየቀው ከፍተኛ የክፍያ ዋጋ በውል ሰነድ ላይ ካልተቀመጠ፣ ተከራዮች ክፍያቸውን ሁልጊዜ በባንክ በኩል ብቻ እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕገ-ወጥነቱን በማስረጃነት እንዲይዙ መክሯል።
ቢሮው አክሎም፣ አከራዮች መተሳሰብና ሰብአዊነትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ በማቅረብ፣ ሕግ ተላልፈው በሚገኙት ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቋል። ማህበረሰቡም ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር በጋራ ለመከላከል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
Seledadotio
Seledadotio
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያን 11.5 በመቶ ማድረጉን ተከትሎ፣ ሕግን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ አከራዮች ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
በተለይም ተከራዮችን “ቤቱን ለራሴ ወይም ለዘመዴ እፈልገዋለሁ” በሚል ሐሰተኛ ምክንያት በማስለቀቅ፣ በምትኩ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ በመጫን፣ የ11.5 በመቶውን ጭማሪም ሕጋዊ አስመስለው የመጫን ተግባራት በስፋት እየተስተዋሉ ነው።
በተጨማሪም፣ አከራዮች በውል ሰነድ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ11.5 በመቶ ጣሪያ በመጥቀስ በሕጋዊ መንገድ እየተስማሙ፣ በተግባር ግን በአፍ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ በመደራደር ተከራዩን ለከፍተኛ የገንዘብ ጫና የሚዳርጉበት የ”ድርብ ውል” አሰራር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን የተሰጡ ጥቆማዎች ያመለክታሉ። ይህ ድርጊት በግልጽ ሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ ሕገ-ወጥ ተግባር መሆኑን ቢሮው አስገንዝቧል።
በዚህ ረገድ ተከራዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል። በተለይም በአፍ የተጠየቀው ከፍተኛ የክፍያ ዋጋ በውል ሰነድ ላይ ካልተቀመጠ፣ ተከራዮች ክፍያቸውን ሁልጊዜ በባንክ በኩል ብቻ እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕገ-ወጥነቱን በማስረጃነት እንዲይዙ መክሯል።
ቢሮው አክሎም፣ አከራዮች መተሳሰብና ሰብአዊነትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ በማቅረብ፣ ሕግ ተላልፈው በሚገኙት ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቋል። ማህበረሰቡም ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር በጋራ ለመከላከል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
Seledadotio
Seledadotio
23 days ago
አከራዮች ከተማ አስተዳደሩ የማያዳግም እርምጃ እወስዳለሁ አለ
#fastmereja | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያን 11.5 በመቶ ማድረጉን ተከትሎ፣ ሕግን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ አከራዮች ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ እንደገለጸው፣ አንዳንድ አከራዮች በተቀመጠው የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ከመስራት ይልቅ፣ ሕገ-ወጥ አሰራሮችን እየተገበሩ ይገኛሉ። በተለይም ተከራዮችን "ቤቱን ለራሴ ወይም ለዘመዴ እፈልገዋለሁ" በሚል ሐሰተኛ ምክንያት በማስለቀቅ፣ በምትኩ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ በመጫን፣ የ11.5 በመቶውን ጭማሪም ሕጋዊ አስመስለው የመጫን ተግባራት በስፋት እየተስተዋሉ ነው።
በተጨማሪም፣ አከራዮች በውል ሰነድ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ11.5 በመቶ ጣሪያ በመጥቀስ በሕጋዊ መንገድ እየተስማሙ፣ በተግባር ግን በአፍ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ በመደራደር ተከራዩን ለከፍተኛ የገንዘብ ጫና የሚዳርጉበት የ"ድርብ ውል" አሰራር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን የተሰጡ ጥቆማዎች ያመለክታሉ። ይህ ድርጊት በግልጽ ሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ ሕገ-ወጥ ተግባር መሆኑን ቢሮው አስገንዝቧል።
በዚህ ረገድ ተከራዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል። በተለይም በአፍ የተጠየቀው ከፍተኛ የክፍያ ዋጋ በውል ሰነድ ላይ ካልተቀመጠ፣ ተከራዮች ክፍያቸውን ሁልጊዜ በባንክ በኩል ብቻ እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕገ-ወጥነቱን በማስረጃነት እንዲይዙ መክሯል።
ቢሮው አክሎም፣ አከራዮች መተሳሰብና ሰብአዊነትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ በማቅረብ፣ ሕግ ተላልፈው በሚገኙት ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቋል። ማህበረሰቡም ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር በጋራ ለመከላከል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
#fastmereja | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያን 11.5 በመቶ ማድረጉን ተከትሎ፣ ሕግን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ አከራዮች ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ እንደገለጸው፣ አንዳንድ አከራዮች በተቀመጠው የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ከመስራት ይልቅ፣ ሕገ-ወጥ አሰራሮችን እየተገበሩ ይገኛሉ። በተለይም ተከራዮችን "ቤቱን ለራሴ ወይም ለዘመዴ እፈልገዋለሁ" በሚል ሐሰተኛ ምክንያት በማስለቀቅ፣ በምትኩ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ በመጫን፣ የ11.5 በመቶውን ጭማሪም ሕጋዊ አስመስለው የመጫን ተግባራት በስፋት እየተስተዋሉ ነው።
በተጨማሪም፣ አከራዮች በውል ሰነድ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ11.5 በመቶ ጣሪያ በመጥቀስ በሕጋዊ መንገድ እየተስማሙ፣ በተግባር ግን በአፍ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ በመደራደር ተከራዩን ለከፍተኛ የገንዘብ ጫና የሚዳርጉበት የ"ድርብ ውል" አሰራር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን የተሰጡ ጥቆማዎች ያመለክታሉ። ይህ ድርጊት በግልጽ ሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ ሕገ-ወጥ ተግባር መሆኑን ቢሮው አስገንዝቧል።
በዚህ ረገድ ተከራዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል። በተለይም በአፍ የተጠየቀው ከፍተኛ የክፍያ ዋጋ በውል ሰነድ ላይ ካልተቀመጠ፣ ተከራዮች ክፍያቸውን ሁልጊዜ በባንክ በኩል ብቻ እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕገ-ወጥነቱን በማስረጃነት እንዲይዙ መክሯል።
ቢሮው አክሎም፣ አከራዮች መተሳሰብና ሰብአዊነትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ በማቅረብ፣ ሕግ ተላልፈው በሚገኙት ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቋል። ማህበረሰቡም ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር በጋራ ለመከላከል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
Sponsored by
Surafel
25 days ago
ከፖለቲካ ሽኩቻ የላቀው የጋራ ተቋማችንን እናክብር
****************
የአንድ ሀገር ጥንካሬ ከሚገለጽባቸው መሠረታዊ ጉዳዮች መካከል አንዱ ዜጎች በጋራ የሚግባቡባቸው እና በኩራት የሚጠሯቸው ጠንካራ ብሔራዊ ተቋማት መኖራቸው ነው።
ከእነዚህ ተቋማት መካከል ደግሞ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀዳሚውን እና የክብር ማማውን ስፍራ ይይዛል።
የዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ስንመለከት፣ በሠለጠኑ ዴሞክራሲያዊ ሀገራት የሠራዊት አባላትን ማክበር ከፖለቲካዊ ሽኩቻዎች የላቀ ብሔራዊ መግባባት የተገነባበት ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን።
በአሜሪካ የፖለቲካ ምኅዳር ውስጥ በፓርቲዎች መካከል የጎላ ርዕዮተ ዓለማዊ ልዩነት ቢኖርም፣ ሠራዊቱን ከፖለቲካ ፉክክር ውጪ የማድረግ ብሔራዊ ስምምነት አለ።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የመንግሥትን ፖሊሲ በሚተቹበት ወቅት እንኳ በጦር ግንባር የተሰማሩትን ወታደሮች እንደ ጀግና በመቁጠር ውዳሴ እና ክብር ያቀርባሉ።
በዩናይትድ ኪንግደም "የጦር ኃይሎች ቃል ኪዳን" (Armed Forces Covenant) የተሰኘው ብሔራዊ ሰነድ የሠራዊት አባላት ልዩ ክብር እንዲያገኙ ያደርጋል።
ካናዳ ለአርበኞች ልዩ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ስታቋቁም፣ ፈረንሳይ ደግሞ ሠራዊቷን የሀገሯ የክብር እና የአጋርነት ብሔራዊ ተምሳሌት በማድረግ በትልቅ ማዕረግ ትዘክራለች።
ወደ ሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ስንመጣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በባሕርይው እጅግ ሕዝባዊ የሆነ፣ ከሀገር አልፎ ለዓለም የሰላም ዘብ በመሆን ደሙን የገበረ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።
የኢትዮጵያ ወታደር በኮሪያ ልሳነ ምድር በቃኘው ሻለቃ አማካኝነት "አንድም ወታደር አልተማረከም፤ የሞተ ጓዱንም ጥሎ አልመጣም" የሚል የዓለምን አስደናቂ ሪከርድ ያስመዘገበ ጀግና ነው።
በኮንጎ፣ በሩዋንዳ፣ በቡሩንዲ፣ በላይቤሪያ፣ በአብዬ፣ በዳርፉር እና በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ላይ በመሰማራት አፍሪካውያን ወንድሞቹን ከእልቂት የታደገ፣ የራሱን ሬሽን እያካፈለ የውጭ ሀገር ዜጎችን ያኖረ የሰብአዊነት ተምሳሌት ነው።
ይህ ሠራዊት በሀገር ውስጥም ቢሆን ጦር መሣሪያውን አስቀምጦ በክረምት የገበሬውን ማሳ ሲያርስ እና በመኸር ሲያጭድ፣ የተፈጥሮ አደጋ ሲያጋጥም ከነፍስ አድን ሥራ እስከ አንበጣ መንጋ ማባረር ድረስ ከሕዝቡ ጎን የቆመ ታላቅ አለኝታ ነው።
ነገር ግን አለመታደል ሆኖ፣ የሀገራችን መከላከያ ሠራዊት በፖለቲካ ኃይሎች መካከል በሚደረጉ ፍልሚያዎች ውስጥ የከፉ ምኞቶች ሰለባ ሲሆን ይስተዋላል።
አንዳንዴም የፖለቲካ ልዩነትን እና የሀገርን የፀጥታ ምሰሶ መለየት ያቃታቸው አካላት ሠራዊቱን የማንቋሸሽ አዝማሚያ ያሳያሉ።
የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ማክበር እና ለሀገር ሕልውና የሚከፍለውን ዋጋ ማወቅ የአንድ ማኅበረሰብ የሥልጣኔ መገለጫ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተደጋጋሚ አስገንዝበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ በፓርላማ ባደረጉት ንግግር፣ ሀገርን ጠብቆ የሚያኖርን ኃይል እንደ "ገዳይ" መፈረጅ እና ተቋማዊ ክብሩን አለማወቅ የሲቪል-ወታደራዊ ግንኙነትን አለመረዳት እና ያለመሠልጠን ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
መንግሥት እና ፖሊሲ አውጪዎችን በጥብቅ መተቸት የዴሞክራሲ አካል ነው። ነገር ግን ለሀገር ሕልውና አጥንቱን የሚከሰክሰውን ሠራዊት ከተቋማዊ ትችት ነፃ አድርጎ በጀግንነት መዘከር ይገባል።
በመሠረቱ ሠራዊቱ ሕዝብን የመጠበቅ ግዴታ ሲኖርበት፣ መንግሥት እና ሕዝብ ደግሞ የሠራዊቱን መሥዋዕትነት የመካስ የሞራል ግዴታ አለባቸው።
ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ትኩረት አድርጋ ከሠራችባቸው የሪፎርም ሥራዎች መካከል የፀጥታ ተቋማት ግንባታ ዋነኛው የሆነውም ለዚሁ ነው።
ሠራዊታችን ከፖለቲካ ልዩነቶቻችን በላይ የሆነ የጋራ የብረት አጥራችን እና የሕልውናችን ምሰሶ በመሆኑ ዘወትር ክብር እና ሞገስ ይገባዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #endf #nationalpride #standwithourtroops
****************
የአንድ ሀገር ጥንካሬ ከሚገለጽባቸው መሠረታዊ ጉዳዮች መካከል አንዱ ዜጎች በጋራ የሚግባቡባቸው እና በኩራት የሚጠሯቸው ጠንካራ ብሔራዊ ተቋማት መኖራቸው ነው።
ከእነዚህ ተቋማት መካከል ደግሞ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀዳሚውን እና የክብር ማማውን ስፍራ ይይዛል።
የዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ስንመለከት፣ በሠለጠኑ ዴሞክራሲያዊ ሀገራት የሠራዊት አባላትን ማክበር ከፖለቲካዊ ሽኩቻዎች የላቀ ብሔራዊ መግባባት የተገነባበት ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን።
በአሜሪካ የፖለቲካ ምኅዳር ውስጥ በፓርቲዎች መካከል የጎላ ርዕዮተ ዓለማዊ ልዩነት ቢኖርም፣ ሠራዊቱን ከፖለቲካ ፉክክር ውጪ የማድረግ ብሔራዊ ስምምነት አለ።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የመንግሥትን ፖሊሲ በሚተቹበት ወቅት እንኳ በጦር ግንባር የተሰማሩትን ወታደሮች እንደ ጀግና በመቁጠር ውዳሴ እና ክብር ያቀርባሉ።
በዩናይትድ ኪንግደም "የጦር ኃይሎች ቃል ኪዳን" (Armed Forces Covenant) የተሰኘው ብሔራዊ ሰነድ የሠራዊት አባላት ልዩ ክብር እንዲያገኙ ያደርጋል።
ካናዳ ለአርበኞች ልዩ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ስታቋቁም፣ ፈረንሳይ ደግሞ ሠራዊቷን የሀገሯ የክብር እና የአጋርነት ብሔራዊ ተምሳሌት በማድረግ በትልቅ ማዕረግ ትዘክራለች።
ወደ ሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ስንመጣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በባሕርይው እጅግ ሕዝባዊ የሆነ፣ ከሀገር አልፎ ለዓለም የሰላም ዘብ በመሆን ደሙን የገበረ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።
የኢትዮጵያ ወታደር በኮሪያ ልሳነ ምድር በቃኘው ሻለቃ አማካኝነት "አንድም ወታደር አልተማረከም፤ የሞተ ጓዱንም ጥሎ አልመጣም" የሚል የዓለምን አስደናቂ ሪከርድ ያስመዘገበ ጀግና ነው።
በኮንጎ፣ በሩዋንዳ፣ በቡሩንዲ፣ በላይቤሪያ፣ በአብዬ፣ በዳርፉር እና በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ላይ በመሰማራት አፍሪካውያን ወንድሞቹን ከእልቂት የታደገ፣ የራሱን ሬሽን እያካፈለ የውጭ ሀገር ዜጎችን ያኖረ የሰብአዊነት ተምሳሌት ነው።
ይህ ሠራዊት በሀገር ውስጥም ቢሆን ጦር መሣሪያውን አስቀምጦ በክረምት የገበሬውን ማሳ ሲያርስ እና በመኸር ሲያጭድ፣ የተፈጥሮ አደጋ ሲያጋጥም ከነፍስ አድን ሥራ እስከ አንበጣ መንጋ ማባረር ድረስ ከሕዝቡ ጎን የቆመ ታላቅ አለኝታ ነው።
ነገር ግን አለመታደል ሆኖ፣ የሀገራችን መከላከያ ሠራዊት በፖለቲካ ኃይሎች መካከል በሚደረጉ ፍልሚያዎች ውስጥ የከፉ ምኞቶች ሰለባ ሲሆን ይስተዋላል።
አንዳንዴም የፖለቲካ ልዩነትን እና የሀገርን የፀጥታ ምሰሶ መለየት ያቃታቸው አካላት ሠራዊቱን የማንቋሸሽ አዝማሚያ ያሳያሉ።
የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ማክበር እና ለሀገር ሕልውና የሚከፍለውን ዋጋ ማወቅ የአንድ ማኅበረሰብ የሥልጣኔ መገለጫ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተደጋጋሚ አስገንዝበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ በፓርላማ ባደረጉት ንግግር፣ ሀገርን ጠብቆ የሚያኖርን ኃይል እንደ "ገዳይ" መፈረጅ እና ተቋማዊ ክብሩን አለማወቅ የሲቪል-ወታደራዊ ግንኙነትን አለመረዳት እና ያለመሠልጠን ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
መንግሥት እና ፖሊሲ አውጪዎችን በጥብቅ መተቸት የዴሞክራሲ አካል ነው። ነገር ግን ለሀገር ሕልውና አጥንቱን የሚከሰክሰውን ሠራዊት ከተቋማዊ ትችት ነፃ አድርጎ በጀግንነት መዘከር ይገባል።
በመሠረቱ ሠራዊቱ ሕዝብን የመጠበቅ ግዴታ ሲኖርበት፣ መንግሥት እና ሕዝብ ደግሞ የሠራዊቱን መሥዋዕትነት የመካስ የሞራል ግዴታ አለባቸው።
ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ትኩረት አድርጋ ከሠራችባቸው የሪፎርም ሥራዎች መካከል የፀጥታ ተቋማት ግንባታ ዋነኛው የሆነውም ለዚሁ ነው።
ሠራዊታችን ከፖለቲካ ልዩነቶቻችን በላይ የሆነ የጋራ የብረት አጥራችን እና የሕልውናችን ምሰሶ በመሆኑ ዘወትር ክብር እና ሞገስ ይገባዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #endf #nationalpride #standwithourtroops
26 days ago
የቤት ኪራይና ድራማዎቹ🤔
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያው 11.5% መሆኑን ትላንት ይፋ አድርጓል። ነገር ግን ወዲያውኑ አንዳንድ አከራዮች ወደተከራዮቻቸው ስልክ ማስጮህና አዳዲስ ሴራዎችን መሸረብ ጀምረዋል። ቃሉ ምናልባት ለሚፈጥረው የሚጎረብጥ ስሜት ይቅርታ እጠይቃለሁ! ግን ደግሞ አሁን ላይ በርከት የሚለውን ተከራይ ማህበረሰብ ምርር ካደረጉ ጉዳዮች አንዱ የኪራይ ዋጋ ነው።
የነዚህ አንዳንድ አከራዮች ድራማ ሁለት ነው፦
ድራማ 1፦“ቤቱን ፈልጌዋለሁ!” - የስልኩ መነሻ “እናቴ፣ አክስቴ ወይም እህቴ ልትመጣ ስለሆነ ቤቱን ፈልጌዋለሁ፤ ቤት ፈልጉ ወዘተ...” ነው። ዓላማው ግን ግልጽ ነው፦ ተከራዩን አስለቅቆ አዲስና ሰማይ የነካ የቤት ኪራይ ዋጋ Set አድርጎ ሌላ ተከራይ መጠበቅ! ከዚያም በዚያው በተጋነነ አዲስ ዋጋ ላይ የ11.5% ጭማሪዋን ጣል አድርጎ ህጋዊ አስመስሎ ትልቅ ገንዘብ እየተቀበሉ መቀጠል።
ድራማ 2፦ ሌላ ውል ማስፈረም!
ይህ ደግሞ አዲሱ አካሄድ ነው። አከራዮች ተከራዮቻቸውን ከበፊቱ እጅግ በከፍተኛ ዋጋ በአፍ ያስማማሉ። ሰነድ ላይ ግን መንግስት (ክፍለ ከተማው) ባወጣው የክራይ ዋጋና በተፈቀደው የ11.5% ጭማሪ ጣሪያ እንዲፈርሙላቸው ያደርጋሉ። ይህ በህግ ፊት ንፁህ በመምሰል ከጀርባ የተከራይን ላብ የሚመዘብሩበት ሌላኛው ዘመናዊ ውንብድና ነው ማለት ይቻላል።
ህገ-ወጥ ድራማው በአዲስ አበባ ዛሬም በየደቂቃው እየተከሰተ መሆኑን ለማወቅ ለቡና አብሮ የተቀመጠን ወይም ታክሲ የተጋራን መንገደኛ ለአፍታ መጠየቅ በቂ ነው። አዲሱ አካሄድ «ህጋዊ አሰራርን በሴራ መሸወድና ማላገጥ» ሆኗል።
ሊደረጉ የሚገቡ አስቸኳይ መፍትሔዎች፦
1. ለከተማ አስተዳደሩ፦ ህግ ማውጣት ብቻውን በቂ አይደለም! የወረቀት ውልን ብቻ አይቶ ማፅደቅም ልክ አይሆንም። ከጀርባ ያለውን እውነተኛ የገንዘብ ልውውጥና በአቋራጭ ተከራይን ለማፈናቀል የሚሞክሩ አከራዮችን የሚቀጣ ጠንካራ የቁጥጥር ስራ ያስፈልጋል።
2. ለተከራዮች፦ አከራዮች በአፍ ከፍ ያለ ዋጋ ጠይቀው ውል ላይ ግን ዝቅተኛ ዋጋ ካስፈረሟችሁ ክፍያውን ሁልጊዜ በባንክ ብቻ በማስተላለፍ ህገ-ወጥነቱ በማስረጃ እንዲረጋገጥ አድርጉ። ይህንን ማስረጃ ይዛችሁ መብታችሁን ማስከበር ትችላላችሁ።
3. ለአከራዮች፦ ጊዜው ገንዘብ ብቻ ሳይሆን የመተዛዘን ሰብአዊነትን ማጎልበትንም ይፈለጋል። ጊዜው ለሁሉም እኩል ተለዋዋጭ ነው። እንደዚህ የምታደርጉ አከራዮች ግን ዛሬ የምትዘሩትን ነገ እንደምታጭዱ አስታውሱ።
👉 እናንተስ [አንባቢያን] ምን ትላላችሁ? ከአከራያችሁ ስልክ የተደወለላችሁ ስንቶቻችሁ ናችሁ? የ“ፎርማሊቲ ውል” ድራማውስ ደርሶባችኋል? ያጋጠማችሁን በኮሜንት አካፍሉን።
ጋዜጠኛ ሶዶ ለማ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያው 11.5% መሆኑን ትላንት ይፋ አድርጓል። ነገር ግን ወዲያውኑ አንዳንድ አከራዮች ወደተከራዮቻቸው ስልክ ማስጮህና አዳዲስ ሴራዎችን መሸረብ ጀምረዋል። ቃሉ ምናልባት ለሚፈጥረው የሚጎረብጥ ስሜት ይቅርታ እጠይቃለሁ! ግን ደግሞ አሁን ላይ በርከት የሚለውን ተከራይ ማህበረሰብ ምርር ካደረጉ ጉዳዮች አንዱ የኪራይ ዋጋ ነው።
የነዚህ አንዳንድ አከራዮች ድራማ ሁለት ነው፦
ድራማ 1፦“ቤቱን ፈልጌዋለሁ!” - የስልኩ መነሻ “እናቴ፣ አክስቴ ወይም እህቴ ልትመጣ ስለሆነ ቤቱን ፈልጌዋለሁ፤ ቤት ፈልጉ ወዘተ...” ነው። ዓላማው ግን ግልጽ ነው፦ ተከራዩን አስለቅቆ አዲስና ሰማይ የነካ የቤት ኪራይ ዋጋ Set አድርጎ ሌላ ተከራይ መጠበቅ! ከዚያም በዚያው በተጋነነ አዲስ ዋጋ ላይ የ11.5% ጭማሪዋን ጣል አድርጎ ህጋዊ አስመስሎ ትልቅ ገንዘብ እየተቀበሉ መቀጠል።
ድራማ 2፦ ሌላ ውል ማስፈረም!
ይህ ደግሞ አዲሱ አካሄድ ነው። አከራዮች ተከራዮቻቸውን ከበፊቱ እጅግ በከፍተኛ ዋጋ በአፍ ያስማማሉ። ሰነድ ላይ ግን መንግስት (ክፍለ ከተማው) ባወጣው የክራይ ዋጋና በተፈቀደው የ11.5% ጭማሪ ጣሪያ እንዲፈርሙላቸው ያደርጋሉ። ይህ በህግ ፊት ንፁህ በመምሰል ከጀርባ የተከራይን ላብ የሚመዘብሩበት ሌላኛው ዘመናዊ ውንብድና ነው ማለት ይቻላል።
ህገ-ወጥ ድራማው በአዲስ አበባ ዛሬም በየደቂቃው እየተከሰተ መሆኑን ለማወቅ ለቡና አብሮ የተቀመጠን ወይም ታክሲ የተጋራን መንገደኛ ለአፍታ መጠየቅ በቂ ነው። አዲሱ አካሄድ «ህጋዊ አሰራርን በሴራ መሸወድና ማላገጥ» ሆኗል።
ሊደረጉ የሚገቡ አስቸኳይ መፍትሔዎች፦
1. ለከተማ አስተዳደሩ፦ ህግ ማውጣት ብቻውን በቂ አይደለም! የወረቀት ውልን ብቻ አይቶ ማፅደቅም ልክ አይሆንም። ከጀርባ ያለውን እውነተኛ የገንዘብ ልውውጥና በአቋራጭ ተከራይን ለማፈናቀል የሚሞክሩ አከራዮችን የሚቀጣ ጠንካራ የቁጥጥር ስራ ያስፈልጋል።
2. ለተከራዮች፦ አከራዮች በአፍ ከፍ ያለ ዋጋ ጠይቀው ውል ላይ ግን ዝቅተኛ ዋጋ ካስፈረሟችሁ ክፍያውን ሁልጊዜ በባንክ ብቻ በማስተላለፍ ህገ-ወጥነቱ በማስረጃ እንዲረጋገጥ አድርጉ። ይህንን ማስረጃ ይዛችሁ መብታችሁን ማስከበር ትችላላችሁ።
3. ለአከራዮች፦ ጊዜው ገንዘብ ብቻ ሳይሆን የመተዛዘን ሰብአዊነትን ማጎልበትንም ይፈለጋል። ጊዜው ለሁሉም እኩል ተለዋዋጭ ነው። እንደዚህ የምታደርጉ አከራዮች ግን ዛሬ የምትዘሩትን ነገ እንደምታጭዱ አስታውሱ።
👉 እናንተስ [አንባቢያን] ምን ትላላችሁ? ከአከራያችሁ ስልክ የተደወለላችሁ ስንቶቻችሁ ናችሁ? የ“ፎርማሊቲ ውል” ድራማውስ ደርሶባችኋል? ያጋጠማችሁን በኮሜንት አካፍሉን።
ጋዜጠኛ ሶዶ ለማ
1 month ago
እዚያም ሆኖ ግጥም መጻፉ አይቀርም!
#ethiopia | ነቢይ ግጥም ሲጽፍ ነው የኖረው፤ ግጥም ብቻ ግን አይደለም፣ ምርጥ ቲያትሮችንም ጽፏል፡፡ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈለት “ባለጉዳይ” የቴሌቪዥን ድራማውም አይረሳም፡፡ የትርጉም ሥራዎቹም ድንቅና ልዩ ናቸው፡፡
ነቢይ የብዕር ሰው ብቻ አልነበረም፤ ጨዋታው አፍ የሚያስከፍት አንደበተ ርቱዕም ነበረ እንጂ፡፡ ሰብአዊነት የተላበሰ፣ ደግና የፍቅር ሰው፣ የእውነትም ሰው ነበር።
ከነበረን ቅርበት የተነሳ ከለገሰኝ ወንድማዊ ምክሮቹ መካከል “ጭብጨባ ወዳለበት ሥፍራ አታዘወትር” የሚለው ሁሌም ከሕሊናዬ አይጠፋም፤ እጅጉን ጠቅሞኛልም። ጊዜ ተወስዶ በጥሞና የሚጻፉ ሌሎች ብዙ አይረሴ ቁምነገሮችንም ነግሮኛል፡፡
ግን ግን አሁንም ነፍሱ ከግጥም የምትለይ አይመስለኝም፡፡ ነፍሱና ግጥም የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው፡፡ እናም ሰማይ ቤት ሆኖም ግጥም እየጻፈ ያለ ይመስለኛል፤ ክፋቱ ግን እኛ አናነበውም፡፡ በሞት መለየቱ፣ ሌላው ቢቀር ብዙ ግጥሞችን አሳጥቶናል፡፡ ይሁንና የፈጣሪ ፈቃድ ነውና ነፍሱ በሰላም ትረፍ፡፡
ሁሌም አንረሳህም!
የሥራ ባልደረባህ
#ethiopia | ነቢይ ግጥም ሲጽፍ ነው የኖረው፤ ግጥም ብቻ ግን አይደለም፣ ምርጥ ቲያትሮችንም ጽፏል፡፡ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈለት “ባለጉዳይ” የቴሌቪዥን ድራማውም አይረሳም፡፡ የትርጉም ሥራዎቹም ድንቅና ልዩ ናቸው፡፡
ነቢይ የብዕር ሰው ብቻ አልነበረም፤ ጨዋታው አፍ የሚያስከፍት አንደበተ ርቱዕም ነበረ እንጂ፡፡ ሰብአዊነት የተላበሰ፣ ደግና የፍቅር ሰው፣ የእውነትም ሰው ነበር።
ከነበረን ቅርበት የተነሳ ከለገሰኝ ወንድማዊ ምክሮቹ መካከል “ጭብጨባ ወዳለበት ሥፍራ አታዘወትር” የሚለው ሁሌም ከሕሊናዬ አይጠፋም፤ እጅጉን ጠቅሞኛልም። ጊዜ ተወስዶ በጥሞና የሚጻፉ ሌሎች ብዙ አይረሴ ቁምነገሮችንም ነግሮኛል፡፡
ግን ግን አሁንም ነፍሱ ከግጥም የምትለይ አይመስለኝም፡፡ ነፍሱና ግጥም የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው፡፡ እናም ሰማይ ቤት ሆኖም ግጥም እየጻፈ ያለ ይመስለኛል፤ ክፋቱ ግን እኛ አናነበውም፡፡ በሞት መለየቱ፣ ሌላው ቢቀር ብዙ ግጥሞችን አሳጥቶናል፡፡ ይሁንና የፈጣሪ ፈቃድ ነውና ነፍሱ በሰላም ትረፍ፡፡
ሁሌም አንረሳህም!
የሥራ ባልደረባህ
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሱዳን ጦር ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘውን ኩምሩክ ከተማ ‹‹በጥቂት ሰአታት ውስጥ›› እንደሚቆጣጠር አስታወቀ፡፡ አልሻረቅ አልአውሳት የተሰኘው ጋዜጣ እንደዘገበው በሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን የሚመራው የሱዳን ጦር ሀይል በብሉ ናይል ግዛት ውስጥ በሚገኘው ኩምሩክ ከተማ አካባቢ ከፍተኛ ሀይል እያስገባ ይገኛል፡፡ ወታደራዊ ምንጮቹን ዋቢ ያደረገው ዘገባው እንዳለው ሀይል ማጠናከር ያስፈለገው በተፋላሚው ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ታጣቂዎች ምሽግ ላይ እያደረሰ ያለውን የመድፍ ድብደባ ተከትሎ ነው፡፡ በተጨማሪም ድሮኖችን በመጠቀም በተፋላሚው ታጣቂዎች ላይ ጥቃቱን መቀጠሉን ያስታወቀው ዘገባው ይህም የጦር ሀይሉ ወደፊት እንዲገፋ እንዳስቻለው አስታውቋል፡፡
ይህንን ተከትሎም አሁን በከተማው ዙሪያ በሚገኙ መንደሮች ውስጥ የምድር ጦር ፍልሚያ መጀመሩን ጠቅሷል፡፡ ለዚህ ፍልሚያ እንዲረዳው ሀይሉን በማጠናከር ላይ የሚገኘው የሱዳን ጦር ወታደራዊ ምንጮች ጨምረው እንደገለፁት ጦርነቱ በሚቀጥሉት ሰአታት ውስጥ ኩምሩክ ከተማ ውስጥ ዘልቆ እንደሚገባ እምነት አሳድረዋል፡፡ ስለጉዳዩ ከዜና አውታሩ የተጠየቁት የኩምሩክ ከተማ ገዥው አብዱል አቲ አል ፋቂ ሲናገሩ ‹‹ወታደራዊ ድሉ እየተቃረበ ነው›› ካሉ በኋላ ይህ ፍልሚያ በብሉ ናይል ግዛት ውስጥ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉን ጠራርጎ ለማስወጣት ‹‹የመጨረሻው አውደ ግንባር ነው›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም የሱዳን ጦርና አጋሮቹ የመንግስትን ክብር ለመመለስና የተነጠቁ አካባቢዎችን ለማስመለስ ቁርጠኛ ሆነው እየተፋለሙ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡ እንደዘገባው ካለፈው መጋቢት ወር አንስቶ በብሉ ናይል ግዛት ውስጥ የሱዳን ጦር በአንድ በኩል እንዲሁም ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉና አጋሮቹ በሌላ በኩል ሆነው ከባድ ጦርነት እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡
ይህንን ተከትሎም ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ከኢትዮጵያና ከደቡብ ሱዳን ጋር የሚዋሰነውን ኩምሩክ ከተማ ለመቆጣጠር ችሎ ነበር፡፡ የከተማው ገዢ የሆኑት አል ፋቂ ለአልሻረቅ አልአውሳት በሰጡት መግለጫ በአካባቢው ያለው የሰብአዊነት ሁኔታ ልዩ ትኩረት የሚያስፈልገው ነው፡፡ በአካባቢው ለወራት በዘለቀው በዚህ ጦርነት ወደ100 ሺህ ያህል ሰዎች መፈናቀላቸውን ጠቅሰው ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የመብራትና የውሀ መሰረተ ልማቶችንና የጤና አገልግሎት መስጫዎችን በማውደሙ ችግሩን የከፋ እንዳደረገው አስረድተዋል፡፡ እንደዘገባው ኩምሩክ ከተማ በደቡብ ምስራቃዊ ሱዳን በብሉናይል ግዛት ውስጥ የሚገኝና ከኢትዮጵያ ጋር ድንበር የሚዋሰን ነው፡፡
ይህ ከተማ የግዛቱ ዋና ከተማ ከሆነው ዳዝሚን በ200 ኪሎ ሜትር ርቀት ይገኛል፡፡ ከተማው በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የአቅርቦት ሰንሰለት ያለበት በመሆኑ ትልቅ ወታደራዊ ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ እንዳለውም አስረድቷል፡፡
ይህንን ተከትሎም አሁን በከተማው ዙሪያ በሚገኙ መንደሮች ውስጥ የምድር ጦር ፍልሚያ መጀመሩን ጠቅሷል፡፡ ለዚህ ፍልሚያ እንዲረዳው ሀይሉን በማጠናከር ላይ የሚገኘው የሱዳን ጦር ወታደራዊ ምንጮች ጨምረው እንደገለፁት ጦርነቱ በሚቀጥሉት ሰአታት ውስጥ ኩምሩክ ከተማ ውስጥ ዘልቆ እንደሚገባ እምነት አሳድረዋል፡፡ ስለጉዳዩ ከዜና አውታሩ የተጠየቁት የኩምሩክ ከተማ ገዥው አብዱል አቲ አል ፋቂ ሲናገሩ ‹‹ወታደራዊ ድሉ እየተቃረበ ነው›› ካሉ በኋላ ይህ ፍልሚያ በብሉ ናይል ግዛት ውስጥ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉን ጠራርጎ ለማስወጣት ‹‹የመጨረሻው አውደ ግንባር ነው›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም የሱዳን ጦርና አጋሮቹ የመንግስትን ክብር ለመመለስና የተነጠቁ አካባቢዎችን ለማስመለስ ቁርጠኛ ሆነው እየተፋለሙ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡ እንደዘገባው ካለፈው መጋቢት ወር አንስቶ በብሉ ናይል ግዛት ውስጥ የሱዳን ጦር በአንድ በኩል እንዲሁም ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉና አጋሮቹ በሌላ በኩል ሆነው ከባድ ጦርነት እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡
ይህንን ተከትሎም ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ከኢትዮጵያና ከደቡብ ሱዳን ጋር የሚዋሰነውን ኩምሩክ ከተማ ለመቆጣጠር ችሎ ነበር፡፡ የከተማው ገዢ የሆኑት አል ፋቂ ለአልሻረቅ አልአውሳት በሰጡት መግለጫ በአካባቢው ያለው የሰብአዊነት ሁኔታ ልዩ ትኩረት የሚያስፈልገው ነው፡፡ በአካባቢው ለወራት በዘለቀው በዚህ ጦርነት ወደ100 ሺህ ያህል ሰዎች መፈናቀላቸውን ጠቅሰው ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የመብራትና የውሀ መሰረተ ልማቶችንና የጤና አገልግሎት መስጫዎችን በማውደሙ ችግሩን የከፋ እንዳደረገው አስረድተዋል፡፡ እንደዘገባው ኩምሩክ ከተማ በደቡብ ምስራቃዊ ሱዳን በብሉናይል ግዛት ውስጥ የሚገኝና ከኢትዮጵያ ጋር ድንበር የሚዋሰን ነው፡፡
ይህ ከተማ የግዛቱ ዋና ከተማ ከሆነው ዳዝሚን በ200 ኪሎ ሜትር ርቀት ይገኛል፡፡ ከተማው በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የአቅርቦት ሰንሰለት ያለበት በመሆኑ ትልቅ ወታደራዊ ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ እንዳለውም አስረድቷል፡፡
Sponsored by
Surafel
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዘለንስኪ ‹‹በእርግጠኝነት ሩሲያን እንበቀላታለን›› አሉ፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ በትላንትናው እለት በዋና ከተማቸው በተፈፀመው ጥቃት ጉዳት የደረሰባቸውን ቦታዎች ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝታቸው ወቅት ባደረጉት ንግግርም በሩሲያ ላይ ‹‹በእርግጠኝነት›› የበቀል እርምጃ እንደሚወስዱ አስታውቀዋል፡፡
ከጉብኝቱ በኋላ በቴሌግራም ገፃቸው ላይ ባስተላለፉት መልእክት ‹‹ትላንት በሩሲያ ጥቃት በተፈፀመባቸው 3 ቦታዎች ላይ አሁንም ህይወት የማዳን ፍለጋው ቀጥሏል፡፡ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ፍርስራሾችን እየጠረጉ ቢሆንም እስካሁን 10 ሰዎች የት እንዳሉ አልታወቀም፡፡ በዚህ ጥቃት 30 ሰዎች መገደላቸው የተረጋገጠ ሲሆን ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን እመኛለሁ፡፡›› ያሉት ዘለንስኪ ህፃናትን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ መቁሰላቸውንም አስረድተዋል፡፡ ትላንት በኬይቭ ብቻም ሳይሆን በሌሎች ግዛቶች ውስጥም ድብደባ መከናወኑን ያስረዱት ፕሬዝደንቱ በክሪቪ ሪህ አንድ ጋራዥ፣ ሁለት ትምህርት ቤቶችና የመኖሪያ ህንፃዎች ጉዳት እንደደረሰባቸውና 7 ሰዎች እንቆሰሉ ጠቅሰዋል፡፡
እንዲሁም በኬርሰን ግዛት ደግሞ አንድ ሆስፒታል በሚሳኤል መመታቱን ገልፀዋል፡፡ ሲያስረዱም ‹‹ሩሲያዊያን ምን ኢላማ እንዳደረጉ ያውቁ ነበር፡፡ በኬርሰን የመቱት ምንም ወታደራዊ ጠቀሜታ የሌለው ሆስፒታል ነው፡፡ በዚህም በሚያሳዝን ሁኔታ አንድ ዶክተር ሲገደል ሌላ ነርስ ቆስላለች፡፡ በሱሚ ግዛት ደግሞ በአንድ አፓርታማ ላይ ባደረሱት ጥቃት አንዲት እናትና ሴት ልጇን ጨምሮ 4 ሰዎች ተገድለዋል፡፡›› በማለት አስታውቀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ የትላንቱን የሩሲያ ጥቃት አውግዘው ተኩስ አቁም እንዲደረግ በድጋሚ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ዋና ፀሀፊው ጨምረውም ‹‹በየትኛውም ቦታ በሲቪሎችና ሲቪል መሰረተ ልማት ላይ የሚደረግ ጥቃት አለም አቀፍ የሰብአዊነት ህግን የሚጥስ በመሆኑ በአስቸኳይ መቆም ይኖርበታል›› ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ዲፕሎማት የሆኑት ካጃ ካላስ በዚህ ጥቃት የተነሳ በሩሲያ ላይ አዲስ ማእቀብ እንደሚጣል አስታውቀዋል፡፡ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ በዛሬ መልእክታቸው ሩሲያ ቀንና ለሊት በዩክሬይን ላይ ጥቃት ልትፈፅም እንደምትችል ገልፀው አጋሮቻቸው አስተማማኝ የአየር መቃወሚያ እንዲሰጧቸውም ጠይቀዋል፡፡
ከጉብኝቱ በኋላ በቴሌግራም ገፃቸው ላይ ባስተላለፉት መልእክት ‹‹ትላንት በሩሲያ ጥቃት በተፈፀመባቸው 3 ቦታዎች ላይ አሁንም ህይወት የማዳን ፍለጋው ቀጥሏል፡፡ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ፍርስራሾችን እየጠረጉ ቢሆንም እስካሁን 10 ሰዎች የት እንዳሉ አልታወቀም፡፡ በዚህ ጥቃት 30 ሰዎች መገደላቸው የተረጋገጠ ሲሆን ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን እመኛለሁ፡፡›› ያሉት ዘለንስኪ ህፃናትን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ መቁሰላቸውንም አስረድተዋል፡፡ ትላንት በኬይቭ ብቻም ሳይሆን በሌሎች ግዛቶች ውስጥም ድብደባ መከናወኑን ያስረዱት ፕሬዝደንቱ በክሪቪ ሪህ አንድ ጋራዥ፣ ሁለት ትምህርት ቤቶችና የመኖሪያ ህንፃዎች ጉዳት እንደደረሰባቸውና 7 ሰዎች እንቆሰሉ ጠቅሰዋል፡፡
እንዲሁም በኬርሰን ግዛት ደግሞ አንድ ሆስፒታል በሚሳኤል መመታቱን ገልፀዋል፡፡ ሲያስረዱም ‹‹ሩሲያዊያን ምን ኢላማ እንዳደረጉ ያውቁ ነበር፡፡ በኬርሰን የመቱት ምንም ወታደራዊ ጠቀሜታ የሌለው ሆስፒታል ነው፡፡ በዚህም በሚያሳዝን ሁኔታ አንድ ዶክተር ሲገደል ሌላ ነርስ ቆስላለች፡፡ በሱሚ ግዛት ደግሞ በአንድ አፓርታማ ላይ ባደረሱት ጥቃት አንዲት እናትና ሴት ልጇን ጨምሮ 4 ሰዎች ተገድለዋል፡፡›› በማለት አስታውቀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ የትላንቱን የሩሲያ ጥቃት አውግዘው ተኩስ አቁም እንዲደረግ በድጋሚ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ዋና ፀሀፊው ጨምረውም ‹‹በየትኛውም ቦታ በሲቪሎችና ሲቪል መሰረተ ልማት ላይ የሚደረግ ጥቃት አለም አቀፍ የሰብአዊነት ህግን የሚጥስ በመሆኑ በአስቸኳይ መቆም ይኖርበታል›› ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ዲፕሎማት የሆኑት ካጃ ካላስ በዚህ ጥቃት የተነሳ በሩሲያ ላይ አዲስ ማእቀብ እንደሚጣል አስታውቀዋል፡፡ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ በዛሬ መልእክታቸው ሩሲያ ቀንና ለሊት በዩክሬይን ላይ ጥቃት ልትፈፅም እንደምትችል ገልፀው አጋሮቻቸው አስተማማኝ የአየር መቃወሚያ እንዲሰጧቸውም ጠይቀዋል፡፡
1 month ago
የማዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ የሻሸመኔ ካምፓስ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ
#ethiopia | በ ሻሸመኔ ካምፓስ 405 ተማሪዎች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ ዘርፎች በተለያዩ ሙያዎች የተማሩ ተማሪዎች በዛሬው ቀን በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመርቀዋል።
የምረቃው ሥነ-ሥርዓት በ ካምፓስ ተካሂዶ የተማሪዎች ቤተሰቦች፣ እንግዶች እና የክልል ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የፕሬዚዳንቱ መልዕክት
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በምረቃው ላይ ባሰሙት መልዕክት፣ የተማሪዎች የትምህርት ጉዞ መጨረሻ ብቻ ሳይሆን አዲስ ተልዕኮ መጀመሪያ መሆኑን አስገንዝበዋል። የተማሪዎች ድካም፣ የቤተሰቦች መስዋዕትነት እና የመምህራን ትጋት በታላቅ ክብር መታወስ እንዳለበት ገልጸዋል።
“አንድ ጉዞ መጨረሻ ሌላ ጉዞ መጀመሪያ ነው” በሚል አባባል በመጠቀም፣ ተመራቂዎች እውቀታቸውን በሙሉ ታማኝነት፣ ብቃት እና ርህራሄ ለሕዝብ አገልግሎት እንዲያውሉ አሳስበዋል።
ሙያዊ አቅጣጫ እና ምክር
ፕሬዚዳንቱ ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በተለይ ለጤና ባለሙያዎች እውቀታቸው አካልን እንዲፈውስ ሲያግዝ፣ ርህራሄ እና ሰብአዊነት ግን ልብን እንደሚፈውስ ገልጸዋል። ለመምህራን ደግሞ ትምህርት የወደፊት ትውልድ መሠረት መሆኑን አስታውቀዋል።
የተገኙ ኃላፊዎች መልዕክት
የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ ዶ/ር ቦኮና ጉታ በበኩላቸው፣ መንግሥት የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት ጥራት ያለው ትምህርት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የ ከንቲባ አቶ አዳነ ተክለጊዮርጊስ እና ሌሎች የክልል፣ ዞን እና ከተማ ኃላፊዎችም በሥነ-ሥርዓቱ ተገኝተዋል።
የተመራቂዎች ቃል
ተመራቂዎች በበኩላቸው ያገኙትን እውቀት በመጠቀም ለሕብረተሰብ አገልግሎት ለመቆም ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የምረቃው ሥነ-ሥርዓት 405 ተማሪዎች ወደ አዲስ የሙያ ጉዞ በተስፋ፣ በኃላፊነት እና በአገልግሎት መንፈስ እንዲገቡ የሚያሳይ ታላቅ የትምህርት በዓል ሆኖ ተጠናቋል።
#ethiopia | በ ሻሸመኔ ካምፓስ 405 ተማሪዎች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ ዘርፎች በተለያዩ ሙያዎች የተማሩ ተማሪዎች በዛሬው ቀን በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመርቀዋል።
የምረቃው ሥነ-ሥርዓት በ ካምፓስ ተካሂዶ የተማሪዎች ቤተሰቦች፣ እንግዶች እና የክልል ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የፕሬዚዳንቱ መልዕክት
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በምረቃው ላይ ባሰሙት መልዕክት፣ የተማሪዎች የትምህርት ጉዞ መጨረሻ ብቻ ሳይሆን አዲስ ተልዕኮ መጀመሪያ መሆኑን አስገንዝበዋል። የተማሪዎች ድካም፣ የቤተሰቦች መስዋዕትነት እና የመምህራን ትጋት በታላቅ ክብር መታወስ እንዳለበት ገልጸዋል።
“አንድ ጉዞ መጨረሻ ሌላ ጉዞ መጀመሪያ ነው” በሚል አባባል በመጠቀም፣ ተመራቂዎች እውቀታቸውን በሙሉ ታማኝነት፣ ብቃት እና ርህራሄ ለሕዝብ አገልግሎት እንዲያውሉ አሳስበዋል።
ሙያዊ አቅጣጫ እና ምክር
ፕሬዚዳንቱ ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በተለይ ለጤና ባለሙያዎች እውቀታቸው አካልን እንዲፈውስ ሲያግዝ፣ ርህራሄ እና ሰብአዊነት ግን ልብን እንደሚፈውስ ገልጸዋል። ለመምህራን ደግሞ ትምህርት የወደፊት ትውልድ መሠረት መሆኑን አስታውቀዋል።
የተገኙ ኃላፊዎች መልዕክት
የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ ዶ/ር ቦኮና ጉታ በበኩላቸው፣ መንግሥት የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት ጥራት ያለው ትምህርት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የ ከንቲባ አቶ አዳነ ተክለጊዮርጊስ እና ሌሎች የክልል፣ ዞን እና ከተማ ኃላፊዎችም በሥነ-ሥርዓቱ ተገኝተዋል።
የተመራቂዎች ቃል
ተመራቂዎች በበኩላቸው ያገኙትን እውቀት በመጠቀም ለሕብረተሰብ አገልግሎት ለመቆም ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የምረቃው ሥነ-ሥርዓት 405 ተማሪዎች ወደ አዲስ የሙያ ጉዞ በተስፋ፣ በኃላፊነት እና በአገልግሎት መንፈስ እንዲገቡ የሚያሳይ ታላቅ የትምህርት በዓል ሆኖ ተጠናቋል።
1 month ago
የአንድ ጀግና አባት ህልፈት የትናንት ጉልበት የዛሬው የቤተሰብ ጣጣ
👉ሼር በማድረግ ተባበሩ
ባሳለፍነው ሳምንት ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. የተሰማው መራር ዜና፣ የብዙዎችን ልብ ሰብሮ አልፏል።
የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሚዲያ ኃላፊ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (አዲስ ቴሌቪዥን) ጋዜጠኛ የነበረው ሳህለገብርኤል፤ ለሀገሩ፣ ለሙያው እና ለቤተሰቡ የነበረው ቁርጠኝነት አርአያ የሚባል ነበር።
ለ20 ዓመታት በፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ውስጥ ፍትህን ለማስፈንና የህግ ታራሚዎችን ለመቅረጽ የነበረው ጉልበትና እውቀት፤ ከሙያው ባለፈ ለሀገር የነበረው ፍቅር መገለጫ ነበር።
በተለይም ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ያሳየው ትጋት፣ በጋዜጠኝነት ሙያው ውስጥ ለተተኪዎች ትልቅ ትምህርት ነው።
ከሞቱ ሁለት ቀናት በፊት እንኳ ለተቋሙ ማሻሻያ ትልቅ እቅድ አውጥቶ የነበረው ሳህለገብርኤል፣ ዛሬ በሞት ተነጥቆ የሶስት የዋህ ልጆች አባትና ባለቤቱን በከፍተኛ ሁኔታ ጥሎ አልፏል።
የዛሬው አሳዛኝ እውነታ ግን የሞቱ ዜና ብቻ ሳይሆን፣ ከኋላው የቀሩት ቤተሰቦቹ በከፍተኛ የኑሮ ችግር ውስጥ መውደቃቸው ነው።
ጋዜጠኛ ሳህለገብርኤል በህይወት በነበረበት ወቅት ለሌሎች የነበረው ደግነት፣ ዛሬ ለቤተሰቡ መመለስ አለበት። በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የአባሎች መኖሪያ ካምፕ የሚኖሩት ቤተሰቦቹ፣ የወደፊታቸው እጅግ አሳሳቢ ሆኗል።
ለልጆቹ መኖሪያ፡ መጠለያ ማግኘት አቅማቸው በላይ ሆኗል።
የልጆቹ የወደፊት ተስፋ የሆነው ትምህርት እንዲቀጥል ድጋፍ ይፈልጋሉ።
በበዓላት እና በዕለት ተዕለት ኑሮአቸው ከጎናቸው የሚቆም ሰው ይሻሉ።
ይህ ጥሪ ለክቡርት ከንቲባ አዳነች አበቤ፣ ለፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ፣ ለበጎ አድራጊ ድርጅቶች እና ለሰብአዊነት ለሚቆሙ ወገኖች ሁሉ የሚቀርብ የአደራ ጥሪ ነው።
አጋርነታችሁን ግለጹ
የሳህለገብርኤልን አሻራ ለማስታወስ እና ቤተሰቡን ከመከራ ለመታደግ፣ ያላችሁን ትንሽ ድጋፍ እንድትለግሱ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ባንክ: ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የሂሳብ ቁጥር: 1000081155457
ሙሉ ስም: ጎጃም ይበልጣል ከበደ
ለቤተሰቦቹ የምናደርገው እያንዳንዱ እርዳታ፣ የጀግናውን ጋዜጠኛ ነፍስ የሚያሳርፍ፣ ለልጆቹ ደግሞ ተስፋን የሚሰጥ ነው።
#ሼርርርርርር
👉ሼር በማድረግ ተባበሩ
ባሳለፍነው ሳምንት ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. የተሰማው መራር ዜና፣ የብዙዎችን ልብ ሰብሮ አልፏል።
የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሚዲያ ኃላፊ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (አዲስ ቴሌቪዥን) ጋዜጠኛ የነበረው ሳህለገብርኤል፤ ለሀገሩ፣ ለሙያው እና ለቤተሰቡ የነበረው ቁርጠኝነት አርአያ የሚባል ነበር።
ለ20 ዓመታት በፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ውስጥ ፍትህን ለማስፈንና የህግ ታራሚዎችን ለመቅረጽ የነበረው ጉልበትና እውቀት፤ ከሙያው ባለፈ ለሀገር የነበረው ፍቅር መገለጫ ነበር።
በተለይም ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ያሳየው ትጋት፣ በጋዜጠኝነት ሙያው ውስጥ ለተተኪዎች ትልቅ ትምህርት ነው።
ከሞቱ ሁለት ቀናት በፊት እንኳ ለተቋሙ ማሻሻያ ትልቅ እቅድ አውጥቶ የነበረው ሳህለገብርኤል፣ ዛሬ በሞት ተነጥቆ የሶስት የዋህ ልጆች አባትና ባለቤቱን በከፍተኛ ሁኔታ ጥሎ አልፏል።
የዛሬው አሳዛኝ እውነታ ግን የሞቱ ዜና ብቻ ሳይሆን፣ ከኋላው የቀሩት ቤተሰቦቹ በከፍተኛ የኑሮ ችግር ውስጥ መውደቃቸው ነው።
ጋዜጠኛ ሳህለገብርኤል በህይወት በነበረበት ወቅት ለሌሎች የነበረው ደግነት፣ ዛሬ ለቤተሰቡ መመለስ አለበት። በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የአባሎች መኖሪያ ካምፕ የሚኖሩት ቤተሰቦቹ፣ የወደፊታቸው እጅግ አሳሳቢ ሆኗል።
ለልጆቹ መኖሪያ፡ መጠለያ ማግኘት አቅማቸው በላይ ሆኗል።
የልጆቹ የወደፊት ተስፋ የሆነው ትምህርት እንዲቀጥል ድጋፍ ይፈልጋሉ።
በበዓላት እና በዕለት ተዕለት ኑሮአቸው ከጎናቸው የሚቆም ሰው ይሻሉ።
ይህ ጥሪ ለክቡርት ከንቲባ አዳነች አበቤ፣ ለፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ፣ ለበጎ አድራጊ ድርጅቶች እና ለሰብአዊነት ለሚቆሙ ወገኖች ሁሉ የሚቀርብ የአደራ ጥሪ ነው።
አጋርነታችሁን ግለጹ
የሳህለገብርኤልን አሻራ ለማስታወስ እና ቤተሰቡን ከመከራ ለመታደግ፣ ያላችሁን ትንሽ ድጋፍ እንድትለግሱ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ባንክ: ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የሂሳብ ቁጥር: 1000081155457
ሙሉ ስም: ጎጃም ይበልጣል ከበደ
ለቤተሰቦቹ የምናደርገው እያንዳንዱ እርዳታ፣ የጀግናውን ጋዜጠኛ ነፍስ የሚያሳርፍ፣ ለልጆቹ ደግሞ ተስፋን የሚሰጥ ነው።
#ሼርርርርርር
1 month ago
የመደመር መንግሥት ስንል?
********
ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንቃኝ፣ ኢትዮጵያ የነፃነት ተምሳሌት፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣ እና የብዙ ፀጋዎች ማህደር ሆና እናገኛታለን።
አባቶቻችን በደማቸው አቅንተውና ጠብቀው ያቆዩልንን ይህች ምድር፣ ሀብቷ ሳይደመርና አ ቅሟ ሳይቀናጅ ለዘመናት በመቆየቱ ምክንያት፣ በእጦት አዙሪትና በድህነት ማጥ ውስጥ ስትዳክር ኖራለች።
“የኢትዮጵያውያንን ህይወት እንለውጣለን” የሚለው መፈክር በተፈራረቁ መንግስታትና ትውልዶች ዘንድ በተደጋግሚ ቢነገርም፣ በተግባር ግን እንደ ጉም ርቆን፣ እንደ ህልም ተንሳፎ ቆይቷል።
ዘመናት ነጎዱ፣ ትውልዶች ተፈራረቁ፤ እኛ ግን በተረገጥንበት ቦታ መቆማችንን አልተውንም። በዚህ የታሪክ መስቀለኛ መንገድ እና በተከማቸ የቤት ስራ አጣብቂኝ ውስጥ ነው እንግዲህ "የመደመር መንግስት" ብቅ ያለው።
ለመሆኑ የመደመር መንግስት ምንነት ምንድን ነው?
የመደመር መንግስት ማለት መከፋፈልን፣ መነጠልን፣ እና የአንዱን መቃብር የሌላው ዙፋን የሚያደርገውን የዜሮ ድምር ጨዋታ በመፀየፍ፣ ሀገራዊ ፀጋዎችንና አቅሞችን ወደ አንድ የብልፅግና ወንዝ የሚያፈስ ስርዓት ነው። በመደመር ፍልስፍና መነፅር፣ የመንግስት ሚና እንደ ባለፈው ዘመን ሁሉን አድራጊ ፈጣሪ ወይም ጨቋኝ መሆን ሳይሆን፣ የትብብር ሞተር መሆን ነው።
ይህ መንግስት ዜጎችን፣ የግሉን ዘርፍ፣ እና ሀገራዊ አቅሞችን በማስተባበር፤ ትላንት ያመለጠንን የባከነ ጊዜ "በፈጠራ እና በፍጥነት" የሚያካክስ፣ ገቢር ነበብ (Pragmatic) የሆነ የዘመነ መንግስታዊ መዋቅር ነው።
መሰረታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ዲፓርቸሩም ይሄው ነው፡ ትናንትን ከስህተቱ ተምሮ ማረም፣ ዛሬን በትጋት መስራት፣ እና ነገን በምናብ ተልሞ ማለም።
የመደመር መንግሥት ስንል፣ በፍልስፍና መሠረቱ ከታሕታይ መዋቅር (እንደ ኢኮኖሚ እና መሠረተ ልማት) ለውጥ ይልቅ ለላዕላይ መዋቅር (አስተሳሰብ እና ባህል) ለውጥ ቅድሚያ የሚሰጥ ሥርዓት ማለታችን ነው። ይህ መንግሥት የማኅበረሰብን ልዩ ልዩ ጸጋዎች፣ ዕሴቶች፣ እና አቅሞች ማሰባሰብ ለብልጽግና ወሳኝ መሆኑን በፅኑ ያምናል።
የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ኃይሎች በሚፈጥሩት ፍትጊያ ውስጥ ሚዛን (ወርቃማውን አማካይ) በመጠበቅ ሁሉንም አቅፎ የሚጓዝ ነው።
ይህንን እውነት ይበልጥ ለመረዳት የመደመርን መንግሥት መሠረታዊ መለያዎች ካለፉት መንግሥታት ታሪክ ጋር ማነፃፀር ግድ ይላል።
የሀገራችን የፖለቲካ ጉዞ ከውጭ ሀገር (ከምዕራብም ሆነ ከምሥራቅ) የልማት ሞዴሎችን እንዳለ ገልብጦ በማምጣት የኢትዮጵያን ነባራዊ እውነታ ለማሳጣት ሲጥር የኖረ ፤የንጉሡ ሥርዓት "ሰማይ አይታረስ፣ ንጉሥ አይከሰስ" በሚል መርህ አይነኬነትን ያነገሠ፣ ለውጥን የሚጠላና ቆሞ-ቀርነትን ያተረፈ ፊውዳላዊ ሥርዓት ሆና የተካው የደርግ መንግሥት ደግሞ የሶቪየትን ሞዴል በጭፍን በመከተል "ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ" እንዲሉ፣ በኅብረተሰብአዊነት ስም የግሉን ዘርፍ አቀጭጮ፣ ሀብት ፈጣሪነትን አውግዞ ሀገርን ለከፋ የኢኮኖሚ ቀውስና አዙሪት ዳርጓል።
የኢሕአዴግ መንግሥት በበኩሉ ብሔርን ከአስተዳደራዊ ወሰን ጋር በማስተሳሰሩ ጽንፈኝነትን ያቀጣጠለ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሸረሸረ እና በመጨረሻም የሀገር ሀብት በጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን እጅ እንዲወድቅ ያደረገ ፣እነዚህ ሁሉ መንግሥታት ከዜሮ ድምር ፖለቲካ፣ ተቀናቃኝን አሳዶ ከማጥፋት፣ እና የሕዝብን እያደገ የሚመጣ ፍላጎት በጊዜው ካለመመለስ አባዜ አልወጡም ነበር።
ከዚህ በተቃራኒ፣ የመደመር መንግሥት የገበያ መር እና የመንግሥት መር ፅንፎችን በማስወገድ "የትብብር ሞዴልን" ገንዘቡ ያደርጋል። የግሉ ዘርፍ ሀብት እንዲፈጥር ሲያበረታታ፣ መንግሥትም ራሱ በኢንተርፕረነርሺፕ (ስራ ፈጣሪነት)ዕሳቤ አዳዲስ ዘርፎችን በመፍጠርና ሀገራዊ ሀብትን በማከማቸት ይተጋል።
የመደመር መንግሥት ሌላው ግዙፍ መለያው "የዔሊ ጉዞን" ሰብሮ በ"ፍጥነት፣ ፈጠራ እና ዝላይ" መገስገሱ ነው። አዳጊ ሀገራት የበለፀጉት ሀገራት የሄዱበትን የክፍለ ዘመናት አዝጋሚ (ደረጃ በደረጃ) ጉዞ መከተል የለባቸውም በማለት፣ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በቀጥታ በመቀላቀል "የዝላይ መንገድን" (Leapfrogging) በመጠቀም ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሠራል።
ከዚህም ባሻገር፣ የመደመር መንግሥት "ምናባዊ ከፍታን" ተላብሷል። የይድረስ ይድረስ ጊዜያዊ ማስታገሻዎችን ትቶ፣ እንደ አዲስ አበባ ወንዞች ልማት (ገበታ ለሸገር) እና የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሮችን በመሰሉ ሩቅ አላሚ ፕሮጀክቶች ሀሳብን ወደ መሬት በማውረድ "የማድረግ ዐቅሙን" በተግባር አረጋግጧል።
በአጠቃላይ የመደመር መንግሥት የትናንትናውን የተከማቸ ዕዳ በፈጠራ የሚያቃልል፣ ያመለጠንን የኢንዱስትሪ አብዮት ጊዜ የሚያካክስ፣ እና ኢትዮጵያን በጠንካራ ሥርዓታዊ መዋቅርና ትብብር ወደ ብልጽግና ማማ የሚያሸጋግር መሪ ብርሃን ነው።
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopianbroadcastingcorporation #medemer #philosophyofmedemer #nationalunity
********
ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንቃኝ፣ ኢትዮጵያ የነፃነት ተምሳሌት፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣ እና የብዙ ፀጋዎች ማህደር ሆና እናገኛታለን።
አባቶቻችን በደማቸው አቅንተውና ጠብቀው ያቆዩልንን ይህች ምድር፣ ሀብቷ ሳይደመርና አ ቅሟ ሳይቀናጅ ለዘመናት በመቆየቱ ምክንያት፣ በእጦት አዙሪትና በድህነት ማጥ ውስጥ ስትዳክር ኖራለች።
“የኢትዮጵያውያንን ህይወት እንለውጣለን” የሚለው መፈክር በተፈራረቁ መንግስታትና ትውልዶች ዘንድ በተደጋግሚ ቢነገርም፣ በተግባር ግን እንደ ጉም ርቆን፣ እንደ ህልም ተንሳፎ ቆይቷል።
ዘመናት ነጎዱ፣ ትውልዶች ተፈራረቁ፤ እኛ ግን በተረገጥንበት ቦታ መቆማችንን አልተውንም። በዚህ የታሪክ መስቀለኛ መንገድ እና በተከማቸ የቤት ስራ አጣብቂኝ ውስጥ ነው እንግዲህ "የመደመር መንግስት" ብቅ ያለው።
ለመሆኑ የመደመር መንግስት ምንነት ምንድን ነው?
የመደመር መንግስት ማለት መከፋፈልን፣ መነጠልን፣ እና የአንዱን መቃብር የሌላው ዙፋን የሚያደርገውን የዜሮ ድምር ጨዋታ በመፀየፍ፣ ሀገራዊ ፀጋዎችንና አቅሞችን ወደ አንድ የብልፅግና ወንዝ የሚያፈስ ስርዓት ነው። በመደመር ፍልስፍና መነፅር፣ የመንግስት ሚና እንደ ባለፈው ዘመን ሁሉን አድራጊ ፈጣሪ ወይም ጨቋኝ መሆን ሳይሆን፣ የትብብር ሞተር መሆን ነው።
ይህ መንግስት ዜጎችን፣ የግሉን ዘርፍ፣ እና ሀገራዊ አቅሞችን በማስተባበር፤ ትላንት ያመለጠንን የባከነ ጊዜ "በፈጠራ እና በፍጥነት" የሚያካክስ፣ ገቢር ነበብ (Pragmatic) የሆነ የዘመነ መንግስታዊ መዋቅር ነው።
መሰረታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ዲፓርቸሩም ይሄው ነው፡ ትናንትን ከስህተቱ ተምሮ ማረም፣ ዛሬን በትጋት መስራት፣ እና ነገን በምናብ ተልሞ ማለም።
የመደመር መንግሥት ስንል፣ በፍልስፍና መሠረቱ ከታሕታይ መዋቅር (እንደ ኢኮኖሚ እና መሠረተ ልማት) ለውጥ ይልቅ ለላዕላይ መዋቅር (አስተሳሰብ እና ባህል) ለውጥ ቅድሚያ የሚሰጥ ሥርዓት ማለታችን ነው። ይህ መንግሥት የማኅበረሰብን ልዩ ልዩ ጸጋዎች፣ ዕሴቶች፣ እና አቅሞች ማሰባሰብ ለብልጽግና ወሳኝ መሆኑን በፅኑ ያምናል።
የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ኃይሎች በሚፈጥሩት ፍትጊያ ውስጥ ሚዛን (ወርቃማውን አማካይ) በመጠበቅ ሁሉንም አቅፎ የሚጓዝ ነው።
ይህንን እውነት ይበልጥ ለመረዳት የመደመርን መንግሥት መሠረታዊ መለያዎች ካለፉት መንግሥታት ታሪክ ጋር ማነፃፀር ግድ ይላል።
የሀገራችን የፖለቲካ ጉዞ ከውጭ ሀገር (ከምዕራብም ሆነ ከምሥራቅ) የልማት ሞዴሎችን እንዳለ ገልብጦ በማምጣት የኢትዮጵያን ነባራዊ እውነታ ለማሳጣት ሲጥር የኖረ ፤የንጉሡ ሥርዓት "ሰማይ አይታረስ፣ ንጉሥ አይከሰስ" በሚል መርህ አይነኬነትን ያነገሠ፣ ለውጥን የሚጠላና ቆሞ-ቀርነትን ያተረፈ ፊውዳላዊ ሥርዓት ሆና የተካው የደርግ መንግሥት ደግሞ የሶቪየትን ሞዴል በጭፍን በመከተል "ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ" እንዲሉ፣ በኅብረተሰብአዊነት ስም የግሉን ዘርፍ አቀጭጮ፣ ሀብት ፈጣሪነትን አውግዞ ሀገርን ለከፋ የኢኮኖሚ ቀውስና አዙሪት ዳርጓል።
የኢሕአዴግ መንግሥት በበኩሉ ብሔርን ከአስተዳደራዊ ወሰን ጋር በማስተሳሰሩ ጽንፈኝነትን ያቀጣጠለ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሸረሸረ እና በመጨረሻም የሀገር ሀብት በጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን እጅ እንዲወድቅ ያደረገ ፣እነዚህ ሁሉ መንግሥታት ከዜሮ ድምር ፖለቲካ፣ ተቀናቃኝን አሳዶ ከማጥፋት፣ እና የሕዝብን እያደገ የሚመጣ ፍላጎት በጊዜው ካለመመለስ አባዜ አልወጡም ነበር።
ከዚህ በተቃራኒ፣ የመደመር መንግሥት የገበያ መር እና የመንግሥት መር ፅንፎችን በማስወገድ "የትብብር ሞዴልን" ገንዘቡ ያደርጋል። የግሉ ዘርፍ ሀብት እንዲፈጥር ሲያበረታታ፣ መንግሥትም ራሱ በኢንተርፕረነርሺፕ (ስራ ፈጣሪነት)ዕሳቤ አዳዲስ ዘርፎችን በመፍጠርና ሀገራዊ ሀብትን በማከማቸት ይተጋል።
የመደመር መንግሥት ሌላው ግዙፍ መለያው "የዔሊ ጉዞን" ሰብሮ በ"ፍጥነት፣ ፈጠራ እና ዝላይ" መገስገሱ ነው። አዳጊ ሀገራት የበለፀጉት ሀገራት የሄዱበትን የክፍለ ዘመናት አዝጋሚ (ደረጃ በደረጃ) ጉዞ መከተል የለባቸውም በማለት፣ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በቀጥታ በመቀላቀል "የዝላይ መንገድን" (Leapfrogging) በመጠቀም ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሠራል።
ከዚህም ባሻገር፣ የመደመር መንግሥት "ምናባዊ ከፍታን" ተላብሷል። የይድረስ ይድረስ ጊዜያዊ ማስታገሻዎችን ትቶ፣ እንደ አዲስ አበባ ወንዞች ልማት (ገበታ ለሸገር) እና የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሮችን በመሰሉ ሩቅ አላሚ ፕሮጀክቶች ሀሳብን ወደ መሬት በማውረድ "የማድረግ ዐቅሙን" በተግባር አረጋግጧል።
በአጠቃላይ የመደመር መንግሥት የትናንትናውን የተከማቸ ዕዳ በፈጠራ የሚያቃልል፣ ያመለጠንን የኢንዱስትሪ አብዮት ጊዜ የሚያካክስ፣ እና ኢትዮጵያን በጠንካራ ሥርዓታዊ መዋቅርና ትብብር ወደ ብልጽግና ማማ የሚያሸጋግር መሪ ብርሃን ነው።
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopianbroadcastingcorporation #medemer #philosophyofmedemer #nationalunity
Sponsored by
Surafel
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አሜሪካ ‹‹የሱዳንን ጦርነት እያቀጣጠሉ ነው›› ባለቻቸው 8 ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ማእቀብ ጣለች፡፡ የአሜሪካ ግምጃ ቤት የውጭ ሀብት ቁጥጥር ቢሮ ባወጣው መግለጫ በሱዳን መንግስትና በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት የማቀጣጠል ሚና እየተጫወቱ ባሉ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ማእቀብ መጣሉን አስታውቋል፡፡ እነዚህ ማእቀቡ የተጣለቸው 8 ግለሰቦችና ተቋማት ከጦር መሳሪያ ግዢ አንስቶ ወታደሮችን እስከመመልመል ድረስ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ መሆናቸውንም አስረድቷል፡፡
በሱዳን ያለው ጦርነት በአለማችን ላይ እጅግ አስከፊ የሆነ ሰብአዊ ቀውስ መፍጠሩን የጠቀሰው መግለጫው እንዲሁም በቀጠናው አለመረጋጋት እንዲከሰት ከማድረጉም በላይ አሸባሪ ቡድኖች እንዲስፋፉ በማድረግ የአሜሪካ ደህንነትና ጥቅም ላይ ስጋት ማሳደሩን ገልጿል፡፡ የአሜሪካ ግምጃ ቤት ሴክሪተሪ ስኮት ቤኔሴት ሲናገሩ ‹‹የትራምፕ አስተዳደር በሱዳን ውስጥ ግጭቱን በማስቆም ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ ቁርጠኛ ነው›› ያሉ ሲሆን ሁለቱም ተፋላሚ አካላት በአስቸኳይና ያለቅድመ ሁኔታ የሰብአዊነት ተኩስ አቁም እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ግምጃ ቤቱ የሱዳንን ግጭት በማቀጣጠል በሚል ይህንን ማእቀብ የጣለው በልዩ ፕሬዝደንታዊ ትእዛዝ ቁጥር 14098 መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
በማእቀቡ ውስጥ በመጀመሪያ የሰፈረው በጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን ለሚመራው ጦር ሀይል የጦር መሳሪያ የሚገዙና የሚያቀርቡ አካላት ላይ ነው፡፡ የሱዳን ትልቁ የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሲስተም(ዲአይኤስ) ጦር መሳሪያዎችን፣ ጥይቶችን፣ ተሸከርካሪዎችንና የተለያዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ለጦር ሀይሉ እንደሚያቀርብ ያወሳው መግለጫው ይህ ተቋም አብዛኛውን ጊዜ ከኢራንና ሌሎችም የውጭ አገር ደጋፊ አገራት እነዚህን መሳሪያዎች እንደሚገዛ አስረድቷል፡፡ እንዲሁም ዲአይኤስ በስሩ ባሉት ጂያድ ኢንዱስትሪያል ግሩፕና ጋይድ ኢንዱስትሪያል ግሩፕ የተሰኙ ድርጅቶች አማካኝነት ግልፅ ባልሆነና ውስብስብ በሆነ መንገድ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደሚያንቀሳቅስ ጠቅሷል፡፡
የአሜሪካ ግምጃ ቤት በእነዚህ 3 ተቋማት ማለትም ዲአይኤስ፣ ጂያድና ጋይድ ላይ እ.ኤ.አ በ2023 ማእቀብ መጣሉንም አውስቷል፡፡ አሁን ማእቀብ ከተጣለባቸው ውስጥ የመጀመሪያው ታርጌት መልቲ አክቲቭ ካምፓኒ ሊሚትድ የሚባል ሲሆን እንደመግለጫው ይህ ድርጅት በጋይድ አማካኝነት ዲአይኤስን የሚቆጣጠር ነው፡፡ በሁለተኝነት ማእቀቡ ያረፈባቸው ደግሞ የዚህ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ታሪክ ሁሴን መሀመድ ማዳኒ የተባሉ ግለሰብ ናቸው፡፡ በ3ተኛነት ማእቀብ የተጣለበት ደግሞ መቀመጫውን በህንድ ያደረገውና ኤስቢኤል ኢንጂነሪንግ የተሰኘው ፈንጂ አምራች ድርጅት ነው፡፡
የዚህ ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ህንዳዊው አሎክ ቾዳህሪም በተመሳሳይ ማእቀቡ ተጥሎባቸዋል፡፡ መግለጫው ጨምሮም በ5ተኛነት ማእቀብ የተጣለበት በሆንግ ኮንግ የሚገኘው ፕሮቴክስ ትሬድ ሊሚትድ የተሰኘው ድርጅት መሆኑን ጠቅሶ ይህ ድርጅት ከኢራን ድሮኖችን በመግዛት ለሱዳን ጦር ሀይል መልሶ የመሸጥ ተግባር ላይ መሰማራቱን አስረድቷል፡፡
በ6ተኛነት የዚህ ድርጅት ስራ አስኪያጁ አህመድ አብደላም የማእቀቡ ሰለባ ሆነዋል፡፡ እነዚህ 6 ማእቀቦች የጄኔራል አልብሩሀን ጦር ሀይልን በመደገፍ ስራ ላይ በተሰማሩ አካላትና ድርጅቶች ላይ የተጣሉ ሲሆኑ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉን በመደገፍ ደግሞ ታለንት ብሪጅ የተሰኘው የፓናማ ድርጅት ማእቀብ ተጥሎበታል፡፡ ይህ ድርጅት የቀድሞ የኮሎምቢያ ጦር ሀይል አባላትን በመመልመል ለፈጥኖደራሽ ሀይሉ በተዋጊነት በማስቀጠር ክስ ቀርቦበታል፡፡ እንዲሁም ፍሮንት ካምፓኒ የተሰኘው ድርጅት አመራሮች የሆኑት የፓናማ ዜጎችም ከዚህ ጋር በተያያዘ ማእቀቡ እንደተጣለባቸው መግለጫው አስታውቋል፡፡
በሱዳን ያለው ጦርነት በአለማችን ላይ እጅግ አስከፊ የሆነ ሰብአዊ ቀውስ መፍጠሩን የጠቀሰው መግለጫው እንዲሁም በቀጠናው አለመረጋጋት እንዲከሰት ከማድረጉም በላይ አሸባሪ ቡድኖች እንዲስፋፉ በማድረግ የአሜሪካ ደህንነትና ጥቅም ላይ ስጋት ማሳደሩን ገልጿል፡፡ የአሜሪካ ግምጃ ቤት ሴክሪተሪ ስኮት ቤኔሴት ሲናገሩ ‹‹የትራምፕ አስተዳደር በሱዳን ውስጥ ግጭቱን በማስቆም ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ ቁርጠኛ ነው›› ያሉ ሲሆን ሁለቱም ተፋላሚ አካላት በአስቸኳይና ያለቅድመ ሁኔታ የሰብአዊነት ተኩስ አቁም እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ግምጃ ቤቱ የሱዳንን ግጭት በማቀጣጠል በሚል ይህንን ማእቀብ የጣለው በልዩ ፕሬዝደንታዊ ትእዛዝ ቁጥር 14098 መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
በማእቀቡ ውስጥ በመጀመሪያ የሰፈረው በጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን ለሚመራው ጦር ሀይል የጦር መሳሪያ የሚገዙና የሚያቀርቡ አካላት ላይ ነው፡፡ የሱዳን ትልቁ የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሲስተም(ዲአይኤስ) ጦር መሳሪያዎችን፣ ጥይቶችን፣ ተሸከርካሪዎችንና የተለያዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ለጦር ሀይሉ እንደሚያቀርብ ያወሳው መግለጫው ይህ ተቋም አብዛኛውን ጊዜ ከኢራንና ሌሎችም የውጭ አገር ደጋፊ አገራት እነዚህን መሳሪያዎች እንደሚገዛ አስረድቷል፡፡ እንዲሁም ዲአይኤስ በስሩ ባሉት ጂያድ ኢንዱስትሪያል ግሩፕና ጋይድ ኢንዱስትሪያል ግሩፕ የተሰኙ ድርጅቶች አማካኝነት ግልፅ ባልሆነና ውስብስብ በሆነ መንገድ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደሚያንቀሳቅስ ጠቅሷል፡፡
የአሜሪካ ግምጃ ቤት በእነዚህ 3 ተቋማት ማለትም ዲአይኤስ፣ ጂያድና ጋይድ ላይ እ.ኤ.አ በ2023 ማእቀብ መጣሉንም አውስቷል፡፡ አሁን ማእቀብ ከተጣለባቸው ውስጥ የመጀመሪያው ታርጌት መልቲ አክቲቭ ካምፓኒ ሊሚትድ የሚባል ሲሆን እንደመግለጫው ይህ ድርጅት በጋይድ አማካኝነት ዲአይኤስን የሚቆጣጠር ነው፡፡ በሁለተኝነት ማእቀቡ ያረፈባቸው ደግሞ የዚህ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ታሪክ ሁሴን መሀመድ ማዳኒ የተባሉ ግለሰብ ናቸው፡፡ በ3ተኛነት ማእቀብ የተጣለበት ደግሞ መቀመጫውን በህንድ ያደረገውና ኤስቢኤል ኢንጂነሪንግ የተሰኘው ፈንጂ አምራች ድርጅት ነው፡፡
የዚህ ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ህንዳዊው አሎክ ቾዳህሪም በተመሳሳይ ማእቀቡ ተጥሎባቸዋል፡፡ መግለጫው ጨምሮም በ5ተኛነት ማእቀብ የተጣለበት በሆንግ ኮንግ የሚገኘው ፕሮቴክስ ትሬድ ሊሚትድ የተሰኘው ድርጅት መሆኑን ጠቅሶ ይህ ድርጅት ከኢራን ድሮኖችን በመግዛት ለሱዳን ጦር ሀይል መልሶ የመሸጥ ተግባር ላይ መሰማራቱን አስረድቷል፡፡
በ6ተኛነት የዚህ ድርጅት ስራ አስኪያጁ አህመድ አብደላም የማእቀቡ ሰለባ ሆነዋል፡፡ እነዚህ 6 ማእቀቦች የጄኔራል አልብሩሀን ጦር ሀይልን በመደገፍ ስራ ላይ በተሰማሩ አካላትና ድርጅቶች ላይ የተጣሉ ሲሆኑ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉን በመደገፍ ደግሞ ታለንት ብሪጅ የተሰኘው የፓናማ ድርጅት ማእቀብ ተጥሎበታል፡፡ ይህ ድርጅት የቀድሞ የኮሎምቢያ ጦር ሀይል አባላትን በመመልመል ለፈጥኖደራሽ ሀይሉ በተዋጊነት በማስቀጠር ክስ ቀርቦበታል፡፡ እንዲሁም ፍሮንት ካምፓኒ የተሰኘው ድርጅት አመራሮች የሆኑት የፓናማ ዜጎችም ከዚህ ጋር በተያያዘ ማእቀቡ እንደተጣለባቸው መግለጫው አስታውቋል፡፡
1 month ago
"የምረቃዋ ቀን ያገኘችው ያልጠበቀችው ስጦታ"
#ethiopia | የምረቃ ቀን... ለብዙዎች ከዓመታት ጥረት በኋላ የሚደርስ የደስታ ጊዜ ነው። ቤተሰብ፣ ጓደኞች እና ወዳጆች ተሰባስበው "እንኳን ደስ አለህ!" የሚሉበት ልዩ ዕለት።
ነገር ግን ለአንዲት የህግ ተመራቂ፣ ይህ ቀን በደስታ ሳይሆን በሀዘን ተጀመረ።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ሁሉም ከቤተሰቦቻቸው ጋር ሲተቃቀፉ፣ ፎቶ ሲነሱ እና ሲደሰቱ፣ እሷ ግን ብቻዋን ነበረች። ቤተሰቦቿ ሊመጡ አልቻሉም፤ ምክንያቱ ምናልባት የአቅም ጉዳይ ሊሆን ይችላል።
ልቧ በሀዘን ተሞልቶ፣ ወደ ዶርሟ ተመልሳ እንባዋን አፈሰሰች። ከተረጋጋች በኋላም አየር ለመቀየር ወደ ከተማ ወጣች። አንድ ካፌ ውስጥ ገብታ ምግቧን በልታ፣ መጠጧን ጠጥታ በሐሳብ ተውጣ ተቀምጣ ሳለች...
በድንገት የካፌው ሙዚቃ ተቀየረ። የ"እንኳን ደስ አለሽ!" ድምፅ ተሰማ።
ግራ ተጋብታ ዞር ስትል፣ አራት የባህር ዳር ወጣቶች የ"እንኳን ደስ አለሽ" ጽሑፍ የተጻፈበትን ኬክ ከተበራ ሻማ ጋር ይዘው ወደ እሷ እየመጡ ነበር።
ያልጠበቀችው ይህ የፍቅርና የሰብአዊነት ስጦታ ልቧን በእጅጉ አነካው። እንባዋን መቆጣጠር አልቻለችም። የደስታ እንባ በጉንጮቿ ላይ ፈሰሰ።
"እስከ ዛሬ ብቻዬን ነበርኩ። የቅርብ ጓደኛ እንኳን የለኝም። የሚከፋኝ አይመስለኝም ነበር፤ ግን በዚህ ቀን በጣም ከፋኝ። አለቀስኩ። ከዚያም ይህ ሆነ..." ስትል በእንባ ደስታዋን ገለጸች።
በመጨረሻም ለእነዚያ ደግ የባህር ዳር ልጆች ከልብ ምስጋናዋን አቀረበች።
አንዳንድ ጊዜ የሰውን ልብ የሚያክም ትልቅ ስጦታ ገንዘብ ሳይሆን፣ "አንቺን አስበናል" የሚል ትንሽ የደግነት ተግባር ብቻ ነው።
#ሞገደኛው አበባው
#ethiopia | የምረቃ ቀን... ለብዙዎች ከዓመታት ጥረት በኋላ የሚደርስ የደስታ ጊዜ ነው። ቤተሰብ፣ ጓደኞች እና ወዳጆች ተሰባስበው "እንኳን ደስ አለህ!" የሚሉበት ልዩ ዕለት።
ነገር ግን ለአንዲት የህግ ተመራቂ፣ ይህ ቀን በደስታ ሳይሆን በሀዘን ተጀመረ።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ሁሉም ከቤተሰቦቻቸው ጋር ሲተቃቀፉ፣ ፎቶ ሲነሱ እና ሲደሰቱ፣ እሷ ግን ብቻዋን ነበረች። ቤተሰቦቿ ሊመጡ አልቻሉም፤ ምክንያቱ ምናልባት የአቅም ጉዳይ ሊሆን ይችላል።
ልቧ በሀዘን ተሞልቶ፣ ወደ ዶርሟ ተመልሳ እንባዋን አፈሰሰች። ከተረጋጋች በኋላም አየር ለመቀየር ወደ ከተማ ወጣች። አንድ ካፌ ውስጥ ገብታ ምግቧን በልታ፣ መጠጧን ጠጥታ በሐሳብ ተውጣ ተቀምጣ ሳለች...
በድንገት የካፌው ሙዚቃ ተቀየረ። የ"እንኳን ደስ አለሽ!" ድምፅ ተሰማ።
ግራ ተጋብታ ዞር ስትል፣ አራት የባህር ዳር ወጣቶች የ"እንኳን ደስ አለሽ" ጽሑፍ የተጻፈበትን ኬክ ከተበራ ሻማ ጋር ይዘው ወደ እሷ እየመጡ ነበር።
ያልጠበቀችው ይህ የፍቅርና የሰብአዊነት ስጦታ ልቧን በእጅጉ አነካው። እንባዋን መቆጣጠር አልቻለችም። የደስታ እንባ በጉንጮቿ ላይ ፈሰሰ።
"እስከ ዛሬ ብቻዬን ነበርኩ። የቅርብ ጓደኛ እንኳን የለኝም። የሚከፋኝ አይመስለኝም ነበር፤ ግን በዚህ ቀን በጣም ከፋኝ። አለቀስኩ። ከዚያም ይህ ሆነ..." ስትል በእንባ ደስታዋን ገለጸች።
በመጨረሻም ለእነዚያ ደግ የባህር ዳር ልጆች ከልብ ምስጋናዋን አቀረበች።
አንዳንድ ጊዜ የሰውን ልብ የሚያክም ትልቅ ስጦታ ገንዘብ ሳይሆን፣ "አንቺን አስበናል" የሚል ትንሽ የደግነት ተግባር ብቻ ነው።
#ሞገደኛው አበባው
1 month ago
ባለውለታዋን እናት
ከ12 ዓመታት በኋላ የተገለጠ የደግነት ታሪክ
ብሩክታይት ሽመልስ ባለውለታዋን እናት አገኘች፤ የእንባና የምስጋና አፍታ
#ethiopia | አንዳንድ የሰው መልካምነት ከጊዜ ጋር አይረሳም፤ ዓመታት ቢያልፉም በሰው ልብ ውስጥ እንደ ብርሃን ይኖራል። በ"ሰይፉ በኢቢኤስ" ፕሮግራም ላይ የታየው የብሩክታይት ሽመልስ (ብርክቲ) እና የወይዘሮ አዜብ ገብረ መስቀል መገናኘት የዚህ እውነት ሕያው ማሳያ ነው።
ያልተረሳ ውለታ
ከ12 ዓመታት በፊት፣ የ15 ዓመት ታዳጊ የነበረችው ብሩክታይት ከሐዋሳ ወጥታ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ላይ ሳለች ጭንቀትና ፍርሃት ውስጥ ገብታ ነበር። በዚያ አስቸጋሪ ወቅት ሕይወቷን የቀየረች አንዲት ሴት አገኘቻት፤ ዛሬ የምትጠራት "ባለውለታዬ" ብላ ነው።
"ማን እንደላካት አላውቅም፤ እኔ ግን እግዚአብሔር የላከልኝ ሰው ነበረች ብዬ አምናለሁ" ስትል ብሩክታይት የዚያን ቀን ትዝታ በእንባ አስታወሰች።
አንዲት እናት... አንድ የሰብአዊነት ውሳኔ
ወይዘሮ አዜብ ገብረ መስቀል በዚያ ዕለት ብሩክታይትን በአውቶቡስ ላይ አገኘቻት። የታዳጊዋ ጭንቀትና ፍርሃት በፊቷ ይነበብ ነበር።
ምሳ እንድትበላ ብትጋብዛትም እንባዋን ማቆም አልቻለችም። ወይዘሮ አዜብም ጉዳዩን በእርጋታ ለማወቅ ሞከረች፤ ከዚያም ወደ ቤቷ ወስዳ አሳረፈቻት፣ አረጋጋቻት፣ ከቤተሰቦቿም ጋር እንድትገናኝ አደረገች።
"እናትሽና አባትሽ በጣም ይጨነቃሉ፤ የምትፈልጊው ቦታ በሰላም ትደርሻለሽ" ብላ በፍቅር ያረጋጋቻትን ቀን ዛሬም በግልጽ ታስታውሳለች።
"ይህ የኢትዮጵያዊነት ባህል ነው"
ወይዘሮ አዜብ ያደረገችውን እንደ ልዩ ጀግንነት አትቆጥረውም። ይልቁንም እውነተኛ ኢትዮጵያዊነት መሆኑን ትገልጻለች።
"እኔ ልጅ ያለችኝ እናት ነኝ። ያንን ልጅ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ቢያገኛት እንደዚያው ያደርግላት ነበር። ይህ የባህላችንና የማንነታችን መገለጫ ነው" ብላለች።
የደግነት ዋጋ
በፕሮግራሙ ላይ የተፈጠረው መገናኘት የተመልካቾችን ልብ ነክቷል። ብሩክታይት ባለውለታዋን እናት አቅፋ ስታለቅስ፣ ወይዘሮ አዜብም በደስታ እንባ ታጠበች።
ይህ ታሪክ የሚያስተምረን አንድ ትልቅ እውነት አለ፤ የሰው መልካምነት አይጠፋም፣ አይረሳም። በአንድ አስቸጋሪ ወቅት የተዘራ የደግነት ዘር፣ ከዓመታት በኋላም በምስጋና፣ በክብርና በፍቅር ፍሬውን ያፈራል።
ወይዘሮ አዜብ የተናገረችው አንድ ሐረግ ደግሞ የዚህን ታሪክ ሙሉ ትርጉም ይገልጻል፦
"ለሰው ብትኖር ምንም አትጎዳም፤ በምድርም በሰማይም ዋጋውን ታገኛለህ።"
ከ12 ዓመታት በኋላ የተገለጠ የደግነት ታሪክ
ብሩክታይት ሽመልስ ባለውለታዋን እናት አገኘች፤ የእንባና የምስጋና አፍታ
#ethiopia | አንዳንድ የሰው መልካምነት ከጊዜ ጋር አይረሳም፤ ዓመታት ቢያልፉም በሰው ልብ ውስጥ እንደ ብርሃን ይኖራል። በ"ሰይፉ በኢቢኤስ" ፕሮግራም ላይ የታየው የብሩክታይት ሽመልስ (ብርክቲ) እና የወይዘሮ አዜብ ገብረ መስቀል መገናኘት የዚህ እውነት ሕያው ማሳያ ነው።
ያልተረሳ ውለታ
ከ12 ዓመታት በፊት፣ የ15 ዓመት ታዳጊ የነበረችው ብሩክታይት ከሐዋሳ ወጥታ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ላይ ሳለች ጭንቀትና ፍርሃት ውስጥ ገብታ ነበር። በዚያ አስቸጋሪ ወቅት ሕይወቷን የቀየረች አንዲት ሴት አገኘቻት፤ ዛሬ የምትጠራት "ባለውለታዬ" ብላ ነው።
"ማን እንደላካት አላውቅም፤ እኔ ግን እግዚአብሔር የላከልኝ ሰው ነበረች ብዬ አምናለሁ" ስትል ብሩክታይት የዚያን ቀን ትዝታ በእንባ አስታወሰች።
አንዲት እናት... አንድ የሰብአዊነት ውሳኔ
ወይዘሮ አዜብ ገብረ መስቀል በዚያ ዕለት ብሩክታይትን በአውቶቡስ ላይ አገኘቻት። የታዳጊዋ ጭንቀትና ፍርሃት በፊቷ ይነበብ ነበር።
ምሳ እንድትበላ ብትጋብዛትም እንባዋን ማቆም አልቻለችም። ወይዘሮ አዜብም ጉዳዩን በእርጋታ ለማወቅ ሞከረች፤ ከዚያም ወደ ቤቷ ወስዳ አሳረፈቻት፣ አረጋጋቻት፣ ከቤተሰቦቿም ጋር እንድትገናኝ አደረገች።
"እናትሽና አባትሽ በጣም ይጨነቃሉ፤ የምትፈልጊው ቦታ በሰላም ትደርሻለሽ" ብላ በፍቅር ያረጋጋቻትን ቀን ዛሬም በግልጽ ታስታውሳለች።
"ይህ የኢትዮጵያዊነት ባህል ነው"
ወይዘሮ አዜብ ያደረገችውን እንደ ልዩ ጀግንነት አትቆጥረውም። ይልቁንም እውነተኛ ኢትዮጵያዊነት መሆኑን ትገልጻለች።
"እኔ ልጅ ያለችኝ እናት ነኝ። ያንን ልጅ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ቢያገኛት እንደዚያው ያደርግላት ነበር። ይህ የባህላችንና የማንነታችን መገለጫ ነው" ብላለች።
የደግነት ዋጋ
በፕሮግራሙ ላይ የተፈጠረው መገናኘት የተመልካቾችን ልብ ነክቷል። ብሩክታይት ባለውለታዋን እናት አቅፋ ስታለቅስ፣ ወይዘሮ አዜብም በደስታ እንባ ታጠበች።
ይህ ታሪክ የሚያስተምረን አንድ ትልቅ እውነት አለ፤ የሰው መልካምነት አይጠፋም፣ አይረሳም። በአንድ አስቸጋሪ ወቅት የተዘራ የደግነት ዘር፣ ከዓመታት በኋላም በምስጋና፣ በክብርና በፍቅር ፍሬውን ያፈራል።
ወይዘሮ አዜብ የተናገረችው አንድ ሐረግ ደግሞ የዚህን ታሪክ ሙሉ ትርጉም ይገልጻል፦
"ለሰው ብትኖር ምንም አትጎዳም፤ በምድርም በሰማይም ዋጋውን ታገኛለህ።"
1 month ago
"የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሰብአዊነትና የበጎ አገልግሎት ተምሳሌት ነው"
- ዶክተር መቅደስ ዳባ
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮው ዓመት ከሀገሪቱ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሁለተኛ፣ ከአፍሪካ ቀንድ ደግሞ አራተኛ ደረጃን በመያዝ የልህቀት ጉዞውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገለጸ።
በዛሬው እለት የጎንደር ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች የምረቃ በዓል መርሐግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር አስራት አጸደወይን እንደገለጹት፣ ተቋሙ ከቅድመ አንደኛ እስከ ከፍተኛ የዶክተራልና ሰብ-ስፔሻሊቲ ደረጃ ድረስ የትምህርት አድማሱን ያሰፋ ግዙፍ ማዕከል ለመሆን በቅቷል።
በአሁኑ ወቅት ሰፊ ተቋማዊ ሪፎርም እያካሄደ እንደሚገኝ የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፈር ቀዳጅነት የተጀመረውና ተቋሙን ሁለንተናዊ ራስን የመቻል አቅም የሚያጎናጽፈው ወደ ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲነት የመሸጋገር ሂደት የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ መድረሱን አብስረዋል።
ዩኒቨርሲቲው በዘንድሮው ዓመት ከሀገሪቱ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሁለተኛ፣ ከአፍሪካ ቀንድ ደግሞ አራተኛ ደረጃን በመያዝ የልህቀት ጉዞውን አጠናክሮ መቀጠሉን በትምህርት ጥራትና በሁሉም ተደራሽ በሆነ አካታች ስራ የተመዘገበ ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ሚኒስትር ሚኒስቴር ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ የጎንደር ህዝብ እንግዶችን አቅፎና መርቆ የመሸኘት ታላቅ ባህል ያለውን እሴት በማንሳት ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ተቋም ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ዘመናዊ የጤና ትምህርትና የባለሙያ ልማት መፍለቂያ፣ እንዲሁም በሪፈራል ሆስፒታሉ አማካኝነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን በተለያዩ ልዩ የህክምና ዘርፎች የሚታደግ የሰብአዊነትና የበጎ አገልግሎት ተምሳሌት መሆኑን ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
አዲስ ተመራቂዎችም በትምህርት ቆይታቸው ያካበቱትን እውቀት ብቻ ሳይሆን የተቋሙን መለያ የሆነውን ሰብአዊነት፣ ታማኝነትና ደግነት በተግባር በማሳየት ማህበረሰባቸውንና ሀገራቸውን በቅንነት እንዲያገለግሉ አደራ ብለዋል።
በመጨረሻም፣ ዘመኑ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስና በቴክኖሎጂ ፍጥነት እየተቀየረ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ፣ ተመራቂዎች የዓለምን የእድገት ደረጃ በመከተል ራሳቸውን ዘወትር በዕውቀት እንዲያጎለብቱና የጣለባቸውን ተስፋ በተግባር እንዲያለመልሙ መልዕክት ተላልፏል።
ጌትነት ተመስገን
ከጎንደር
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#uoggraduation #universityofgondar #ethiopianeducation #autonomy #graduation2018
- ዶክተር መቅደስ ዳባ
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮው ዓመት ከሀገሪቱ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሁለተኛ፣ ከአፍሪካ ቀንድ ደግሞ አራተኛ ደረጃን በመያዝ የልህቀት ጉዞውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገለጸ።
በዛሬው እለት የጎንደር ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች የምረቃ በዓል መርሐግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር አስራት አጸደወይን እንደገለጹት፣ ተቋሙ ከቅድመ አንደኛ እስከ ከፍተኛ የዶክተራልና ሰብ-ስፔሻሊቲ ደረጃ ድረስ የትምህርት አድማሱን ያሰፋ ግዙፍ ማዕከል ለመሆን በቅቷል።
በአሁኑ ወቅት ሰፊ ተቋማዊ ሪፎርም እያካሄደ እንደሚገኝ የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፈር ቀዳጅነት የተጀመረውና ተቋሙን ሁለንተናዊ ራስን የመቻል አቅም የሚያጎናጽፈው ወደ ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲነት የመሸጋገር ሂደት የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ መድረሱን አብስረዋል።
ዩኒቨርሲቲው በዘንድሮው ዓመት ከሀገሪቱ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሁለተኛ፣ ከአፍሪካ ቀንድ ደግሞ አራተኛ ደረጃን በመያዝ የልህቀት ጉዞውን አጠናክሮ መቀጠሉን በትምህርት ጥራትና በሁሉም ተደራሽ በሆነ አካታች ስራ የተመዘገበ ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ሚኒስትር ሚኒስቴር ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ የጎንደር ህዝብ እንግዶችን አቅፎና መርቆ የመሸኘት ታላቅ ባህል ያለውን እሴት በማንሳት ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ተቋም ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ዘመናዊ የጤና ትምህርትና የባለሙያ ልማት መፍለቂያ፣ እንዲሁም በሪፈራል ሆስፒታሉ አማካኝነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን በተለያዩ ልዩ የህክምና ዘርፎች የሚታደግ የሰብአዊነትና የበጎ አገልግሎት ተምሳሌት መሆኑን ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
አዲስ ተመራቂዎችም በትምህርት ቆይታቸው ያካበቱትን እውቀት ብቻ ሳይሆን የተቋሙን መለያ የሆነውን ሰብአዊነት፣ ታማኝነትና ደግነት በተግባር በማሳየት ማህበረሰባቸውንና ሀገራቸውን በቅንነት እንዲያገለግሉ አደራ ብለዋል።
በመጨረሻም፣ ዘመኑ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስና በቴክኖሎጂ ፍጥነት እየተቀየረ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ፣ ተመራቂዎች የዓለምን የእድገት ደረጃ በመከተል ራሳቸውን ዘወትር በዕውቀት እንዲያጎለብቱና የጣለባቸውን ተስፋ በተግባር እንዲያለመልሙ መልዕክት ተላልፏል።
ጌትነት ተመስገን
ከጎንደር
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#uoggraduation #universityofgondar #ethiopianeducation #autonomy #graduation2018
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የሊቢያ መንግሥት ባለሥልጣናት የአራት አጎራባች የአፍሪቃ ሃገራት ዜጎች ወደ ሀገሪቱ እንዳይገቡ አገዱ
የምሥራቅ ሊቢያ መንግሥት ባለሥልጣናት የአራት አጎራባች የአፍሪቃ ሃገራት ዜጎች ወደ ሀገሪቱ እንዳይገቡ አገዱ። የባለሥልጣናቱ እርምጃ በምዕራባዊ የሊቢያ የባሕር ወደብ በኩል ወደ አውሮጳ ለመሻገር የሚያልሙ ተሰዳጆችን ቁጥር ለመቀነስ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በሊቢያ ባለሥልጣናት እገዳ የተጣለባቸው የሱዳን፤ የኤርትራ፣ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ዜጎች መሆናቸው ተገልጿል። የሊቢያ የባሕር ወደብ የተሻለ ሕይወትን አልመው ወደ አውሮጳ ለመሰደድ የሚሞክሩ በርካታ የአፍሪቃ ተሰዳጆች የሚያዘወትሩት መሸጋገሪያ መስመር ነው።
ተሰዳጆቹ በሕገወጥ ሰው አሸጋጋሪዎች አማካኝነት ለጉዞ አስተማማኝ ባልሆኑ ትናንሽ ጀልባዎች ከመጠን በላይ ተጠቅጥቀው የሚሳፈሩ ሲሆን ባሕር ላይ በሚያጋጥመው አደጋ በሺህዎች የሚቆጠሩት ካሰቡበት ሳይደርሱ ሕይወታቸው እንደሚቀጠፍ በየጊዜው ይዘገባል። ትናንት ይፋ የተደረገው እገዳ የሱዳን፤ የኤርትራ፤ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ተሰዳጆች በየብስም ሆነ በባሕር እና በአየር ወደ ሊቢያ ግዛት እንዳይገቡ ከልክሏል። መግለጫው አክሎም ክልከላው ዲፕሎማቶች፤ የጤና እና የትምህርት ዘርፍ ሠራተኞችን እንደማይመለከት አስታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ከሌላ ሃገር ወደ ሊቢያ የሚላኩ ስደተኞችን ጉዳይ በተመለከተ በምሥራቅ እና ምዕራብ የሊቢያ መንግሥታት መካከል ላለፉት ወራት ውጥረት አስነስቷል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል እንደሚለው ስደተኞች ላይ በተደረገው ክትትል በሺህዎች የሚቆጠሩ በዚሁ ምክንያት ታስረዋል። የተመድ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ ሊቢያ ውስጥ ከ900 ሺህ በላይ ስደተኞች ይገኛሉ። ከእነዚህ መካከል ከፍተኛውን ቁጥር የያዙት የሱዳን ዜጎች ናቸው። አብዛኞቹ ስደተኞች ወደ አውሮጳ ለመሻገር የሚፈልጉ ቢሆንም ስደተኞችን የጫኑ ጀልባዎች በባሕር ላይ ቃኚዎች እየተያዙ ወደ ሊቢያ እንዲመለሱ እየተደረገ ነው። ስደተኞቹ በሊቢያ መንግሥታት እስር ቤቶች የሚያዙ ሲሆን እንግልት፤ የግዳጅ የጉልበት ሥራ፤ ድብደባ፣ አስገድዶ መድፈር እና ማሰቃየት እንደሚፈጸምባቸው ተገልጿል። የተመድ መርማሪ ኮሚሽንም ስደተኞቹ ላይ የሚደርሰውን እንግልት በሰብአዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል ነው ብሎታል።
DW Amharic
የምሥራቅ ሊቢያ መንግሥት ባለሥልጣናት የአራት አጎራባች የአፍሪቃ ሃገራት ዜጎች ወደ ሀገሪቱ እንዳይገቡ አገዱ። የባለሥልጣናቱ እርምጃ በምዕራባዊ የሊቢያ የባሕር ወደብ በኩል ወደ አውሮጳ ለመሻገር የሚያልሙ ተሰዳጆችን ቁጥር ለመቀነስ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በሊቢያ ባለሥልጣናት እገዳ የተጣለባቸው የሱዳን፤ የኤርትራ፣ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ዜጎች መሆናቸው ተገልጿል። የሊቢያ የባሕር ወደብ የተሻለ ሕይወትን አልመው ወደ አውሮጳ ለመሰደድ የሚሞክሩ በርካታ የአፍሪቃ ተሰዳጆች የሚያዘወትሩት መሸጋገሪያ መስመር ነው።
ተሰዳጆቹ በሕገወጥ ሰው አሸጋጋሪዎች አማካኝነት ለጉዞ አስተማማኝ ባልሆኑ ትናንሽ ጀልባዎች ከመጠን በላይ ተጠቅጥቀው የሚሳፈሩ ሲሆን ባሕር ላይ በሚያጋጥመው አደጋ በሺህዎች የሚቆጠሩት ካሰቡበት ሳይደርሱ ሕይወታቸው እንደሚቀጠፍ በየጊዜው ይዘገባል። ትናንት ይፋ የተደረገው እገዳ የሱዳን፤ የኤርትራ፤ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ተሰዳጆች በየብስም ሆነ በባሕር እና በአየር ወደ ሊቢያ ግዛት እንዳይገቡ ከልክሏል። መግለጫው አክሎም ክልከላው ዲፕሎማቶች፤ የጤና እና የትምህርት ዘርፍ ሠራተኞችን እንደማይመለከት አስታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ከሌላ ሃገር ወደ ሊቢያ የሚላኩ ስደተኞችን ጉዳይ በተመለከተ በምሥራቅ እና ምዕራብ የሊቢያ መንግሥታት መካከል ላለፉት ወራት ውጥረት አስነስቷል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል እንደሚለው ስደተኞች ላይ በተደረገው ክትትል በሺህዎች የሚቆጠሩ በዚሁ ምክንያት ታስረዋል። የተመድ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ ሊቢያ ውስጥ ከ900 ሺህ በላይ ስደተኞች ይገኛሉ። ከእነዚህ መካከል ከፍተኛውን ቁጥር የያዙት የሱዳን ዜጎች ናቸው። አብዛኞቹ ስደተኞች ወደ አውሮጳ ለመሻገር የሚፈልጉ ቢሆንም ስደተኞችን የጫኑ ጀልባዎች በባሕር ላይ ቃኚዎች እየተያዙ ወደ ሊቢያ እንዲመለሱ እየተደረገ ነው። ስደተኞቹ በሊቢያ መንግሥታት እስር ቤቶች የሚያዙ ሲሆን እንግልት፤ የግዳጅ የጉልበት ሥራ፤ ድብደባ፣ አስገድዶ መድፈር እና ማሰቃየት እንደሚፈጸምባቸው ተገልጿል። የተመድ መርማሪ ኮሚሽንም ስደተኞቹ ላይ የሚደርሰውን እንግልት በሰብአዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል ነው ብሎታል።
DW Amharic
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የፀጥታው ምክር ቤት RSF የሚያደርገውን ጥቃት እንዲያቆም አሳሰበ፡፡ የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ወይንም RSF በአል ኦቤድ አካባቢ ወታደራዊ ሀይሉን እያጠናከረ መሆኑን መስማቱን ገልፆ ይህም በከተማው ውስጥ ጥቃት ለመፈፀም መዘጋጀቱን እንደሚያመለክት አስረድቷል፡፡
ጨምሮም ሁኔታው የጅምላ ግድያን ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ስላደረበት ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ጥቃቱን በአስቸኳይ እንዲያቆም አሳስቧል፡፡ መግለጫው በመቀጠልም ‹‹‹የምክር ቤቱ አባላት በኮርዶፋን ግዛት እየተባባሰ የመጣውን ግጭት ጨምሮ በሱዳን የቀጠለው ጦርነት አስከፊ የሆነውን የሰብአዊነት ሁኔታ የባሰ ያደርገዋል በሚል በጥልቅ አሳስቧቸዋል፡፡ በመሆኑም በአስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጥሪ ያቀርባሉ›› ብሏል፡፡ አስከትሎም ሁሉም ተፋላሚ አካላት ሲቪሎችን የመጠበቅና አለም አቀፍ ህጎችን የማክበር ግዴታ እንዳለባቸው ገልጿል፡፡
በአል ኦቢድ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉና ሁለቱም ተፋላሚዎች ደግሞ በመላው አገሪቱ የሚያከናውኑት የድሮን ጥቃት እንዳሳሰበው የጠቀሰው ምክር ቤቱ በተፈፀሙ ሁሉም የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ላይ ምርመራ ተደርጎ አጥፊዎች ተጠያቂ እንዲሆኑም አሳስቧል፡፡
ሁለቱም ተፋላሚዎች ያልተገደበ የሰብአዊ እርዳታ እንቅስቃሴ የመፍቀድ ግዴታ እንዳለባቸውም ገልፆ ይህ ጦርነት እንዲቀጥልና ሰላም እንዳይፈጠር ድጋፍ የሚያደርጉ የውጭ አካላትም ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ መልእክት አስተላልፏል፡፡ የፀጥታው ምክር ቤት ጨምሮም ለሱዳን ሉአላዊነት፣ ነፃነትና የግዛት አንድነት እውቅና እንደሚሰጥ ያረጋገጠ ሲሆን ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች የመሰረተው ትይዩ መንግስት ተቀባይነት እንደሌለው አስታውቋል፡፡
ጨምሮም ሁኔታው የጅምላ ግድያን ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ስላደረበት ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ጥቃቱን በአስቸኳይ እንዲያቆም አሳስቧል፡፡ መግለጫው በመቀጠልም ‹‹‹የምክር ቤቱ አባላት በኮርዶፋን ግዛት እየተባባሰ የመጣውን ግጭት ጨምሮ በሱዳን የቀጠለው ጦርነት አስከፊ የሆነውን የሰብአዊነት ሁኔታ የባሰ ያደርገዋል በሚል በጥልቅ አሳስቧቸዋል፡፡ በመሆኑም በአስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጥሪ ያቀርባሉ›› ብሏል፡፡ አስከትሎም ሁሉም ተፋላሚ አካላት ሲቪሎችን የመጠበቅና አለም አቀፍ ህጎችን የማክበር ግዴታ እንዳለባቸው ገልጿል፡፡
በአል ኦቢድ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉና ሁለቱም ተፋላሚዎች ደግሞ በመላው አገሪቱ የሚያከናውኑት የድሮን ጥቃት እንዳሳሰበው የጠቀሰው ምክር ቤቱ በተፈፀሙ ሁሉም የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ላይ ምርመራ ተደርጎ አጥፊዎች ተጠያቂ እንዲሆኑም አሳስቧል፡፡
ሁለቱም ተፋላሚዎች ያልተገደበ የሰብአዊ እርዳታ እንቅስቃሴ የመፍቀድ ግዴታ እንዳለባቸውም ገልፆ ይህ ጦርነት እንዲቀጥልና ሰላም እንዳይፈጠር ድጋፍ የሚያደርጉ የውጭ አካላትም ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ መልእክት አስተላልፏል፡፡ የፀጥታው ምክር ቤት ጨምሮም ለሱዳን ሉአላዊነት፣ ነፃነትና የግዛት አንድነት እውቅና እንደሚሰጥ ያረጋገጠ ሲሆን ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች የመሰረተው ትይዩ መንግስት ተቀባይነት እንደሌለው አስታውቋል፡፡
2 months ago
ታላቅ የምስራች! በካንሰር ህመም ሲሰቃይ የነበረው ሶላን ከህክምና መልስ በጤንነት ወደ ቤተሰቡ ተመለሰ
#fastmereja I በደም ካንሰር ህመም ምክንያት ለረጅም ጊዜ ሲሰቃይ የነበረው ሶላን፣ በለጋሾች እና በበጎ አድራጊዎች ድጋፍ ወደ ህንድ ሀገር ተጉዞ ህክምናውን አጠናቆ በጤንነት ወደ ሀገሩ መመለሱን አቲስ ነማ ፋውንዴሽን አስታወቀ።
ሶላን በህመም ውስጥ በነበረበት ወቅት የገንዘብ እና የሞራል ድጋፍ ያደረጉለት ወገኖች ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በተለይም የጊምቢ ከተማ እና የምዕራብ ወለጋ ህዝብ ላደረጉት የላቀ የሰብአዊነት ድጋፍ የሶላን ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም አቲስ ነማ ፋውንዴሽን ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል።
#fastmereja I በደም ካንሰር ህመም ምክንያት ለረጅም ጊዜ ሲሰቃይ የነበረው ሶላን፣ በለጋሾች እና በበጎ አድራጊዎች ድጋፍ ወደ ህንድ ሀገር ተጉዞ ህክምናውን አጠናቆ በጤንነት ወደ ሀገሩ መመለሱን አቲስ ነማ ፋውንዴሽን አስታወቀ።
ሶላን በህመም ውስጥ በነበረበት ወቅት የገንዘብ እና የሞራል ድጋፍ ያደረጉለት ወገኖች ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በተለይም የጊምቢ ከተማ እና የምዕራብ ወለጋ ህዝብ ላደረጉት የላቀ የሰብአዊነት ድጋፍ የሶላን ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም አቲስ ነማ ፋውንዴሽን ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል።
2 months ago
“ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ በሰብአዊነት፣ ብሔራዊ አንድነት እና ሁለንተናዊ ሪፎርም ላይ አዲስ የአመራር ምዕራፍ እያስመዘገቡ ነው” - የዱባይ ዶት ኒውስ ጋዜጠኛ ጄራርድ ኡርባኖዞ
************************
የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ዜና ኔትወርክ በሆነው የዱባይ ዶት ኒውስ ጋዜጠኛ ጄራርድ ኡርባኖዞ በጻፈው ሐተታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰብአዊነትን እና ሁለንተናዊ ሪፎርምን ማዕከል ያደረገ የአመራር ጉዞ እያስመዘገቡ መሆናቸውን ገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰብአዊነትን፣ ማኅበራዊ አገልግሎትን እና ብሔራዊ አንድነትን ያቀናጀ አዲስ የአመራር ምዕራፍ በኢትዮጵያ እያሰፈኑ መሆናቸውንም አመልክቷል።
ከመጀመሪያው የአመራር ቀናቸው ጀምሮ መቻቻልን እና አንድነትን የፖለቲካ ማዕቀፍ ማድረጋቸውን የሚገልጸው ጽሑፉ፣ በወቅቱ የነበረውን ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ መከፋፈል ለመፍታት ለብሔራዊ አንድነት እና አብሮ መኖር ቅድሚያ መስጠታቸውን አስረድቷል።
ይህንን ሕዝባዊ ወገንተኝነታቸውን በተግባር ለማሳየትም ከጎዳና ተዳዳሪዎች ጋር ማዕድ ከመጋራት ጀምሮ የደካሞችን ቤት እስከማደስ እና ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የሀገር መሪዎችን በራሳቸው መኪና እየነዱ ማስተናገዳቸውን አብራርቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወደ መሪነት ከመምጣታቸው በፊት በተለያዩ ቦታዎች በኃላፊነት ማገልገላቸውን የሚገልጸው ጽሑፉ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ትላልቅ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ለውጦችን ማከናወናቸውን አስታውሷል።
በዚህም በሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞች መፈታታቸውን፣ ‘አሸባሪ’ ተብለው ከተፈረጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይቶች መደረጉን፣ የሕግ እና የፍትሕ ማሻሻያዎች መጀመሩን እንዲሁም ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች መከናወናቸውን አስረድቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን የብዝኃነት ማኅበራዊ መሠረት ወደ የወል፣የተስማማ እና የበለጸገ ስብስብ ለመቀየር በማለም ሀገር በቀል የ‘መደመር’ ፍልስፍናን በዋናነት እንደተጠቀሙም አብራርቷል።
ጋዜጠኛ ጄራርድ ኡርባኖዞ በጽሑፉ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሩን በስፋት ያተተ ሲሆን በዘንድሮ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋ ማስጀመራቸውን አመልክቷል።
በዚህም ኢትዮጵያ 65 ቢሊዮን ዛፎችን ለመትከል በያዘችው ብሔራዊ ግብ መሠረት የዘንድሮውን ሳይጨምር 48 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን አብራርቷል።
መርሐ ግብሩ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና አረንጓዴ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ትኩረት የሳበ ንቅናቄ መሆኑንም ጠቅሷል።
#ethiopia #ebc #pmabiyahmed #dubaidotnews
************************
የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ዜና ኔትወርክ በሆነው የዱባይ ዶት ኒውስ ጋዜጠኛ ጄራርድ ኡርባኖዞ በጻፈው ሐተታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰብአዊነትን እና ሁለንተናዊ ሪፎርምን ማዕከል ያደረገ የአመራር ጉዞ እያስመዘገቡ መሆናቸውን ገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰብአዊነትን፣ ማኅበራዊ አገልግሎትን እና ብሔራዊ አንድነትን ያቀናጀ አዲስ የአመራር ምዕራፍ በኢትዮጵያ እያሰፈኑ መሆናቸውንም አመልክቷል።
ከመጀመሪያው የአመራር ቀናቸው ጀምሮ መቻቻልን እና አንድነትን የፖለቲካ ማዕቀፍ ማድረጋቸውን የሚገልጸው ጽሑፉ፣ በወቅቱ የነበረውን ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ መከፋፈል ለመፍታት ለብሔራዊ አንድነት እና አብሮ መኖር ቅድሚያ መስጠታቸውን አስረድቷል።
ይህንን ሕዝባዊ ወገንተኝነታቸውን በተግባር ለማሳየትም ከጎዳና ተዳዳሪዎች ጋር ማዕድ ከመጋራት ጀምሮ የደካሞችን ቤት እስከማደስ እና ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የሀገር መሪዎችን በራሳቸው መኪና እየነዱ ማስተናገዳቸውን አብራርቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወደ መሪነት ከመምጣታቸው በፊት በተለያዩ ቦታዎች በኃላፊነት ማገልገላቸውን የሚገልጸው ጽሑፉ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ትላልቅ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ለውጦችን ማከናወናቸውን አስታውሷል።
በዚህም በሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞች መፈታታቸውን፣ ‘አሸባሪ’ ተብለው ከተፈረጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይቶች መደረጉን፣ የሕግ እና የፍትሕ ማሻሻያዎች መጀመሩን እንዲሁም ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች መከናወናቸውን አስረድቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን የብዝኃነት ማኅበራዊ መሠረት ወደ የወል፣የተስማማ እና የበለጸገ ስብስብ ለመቀየር በማለም ሀገር በቀል የ‘መደመር’ ፍልስፍናን በዋናነት እንደተጠቀሙም አብራርቷል።
ጋዜጠኛ ጄራርድ ኡርባኖዞ በጽሑፉ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሩን በስፋት ያተተ ሲሆን በዘንድሮ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋ ማስጀመራቸውን አመልክቷል።
በዚህም ኢትዮጵያ 65 ቢሊዮን ዛፎችን ለመትከል በያዘችው ብሔራዊ ግብ መሠረት የዘንድሮውን ሳይጨምር 48 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን አብራርቷል።
መርሐ ግብሩ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና አረንጓዴ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ትኩረት የሳበ ንቅናቄ መሆኑንም ጠቅሷል።
#ethiopia #ebc #pmabiyahmed #dubaidotnews
2 months ago
በወዙና በደሙ ኢትዮጵያን ያፀና:- የጀግንነት አምባ
*****************
"የኩሩ ህዝቦች መኖሪያ የህብረ ብሄር ቡቃያ፣ የሰላም ተምሳሌት ዓርማ የቀለሞች ህብር ኢትዮጵያ!"
ይህ የክብርና የሉዓላዊነት ብሔራዊ መዝሙር ስንኝ፣ ተራ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የታሪክ፣ የፅናትና የማንነት መልክ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የህሊና ብሩህ መስታወት ነው።
የመከላከያ ሰራዊቱ የማይበገር ጥንካሬ የሚመነጨው በልቡ ውስጥ ከነደደው የማያልቅ የሀገር ፍቅር እሳትና በውስጡ ከሰረጸው ጠንካራ ወታደራዊ ዲሲፕሊን ነው።
ሰራዊቱ ሀገርን በመጠበቅና ዳር ድንበርን በማስከበር ረገድ በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ የሌለው፣ የታሪክን ታላላቅ ፈተናዎች በትከሻው የተሸከመ የሰላም ጽኑ ዐለት ነው።
የጦር ሜዳ ውሎው ስልታዊና አስፈሪ፣ የሰላም ጊዜው ደግሞ ለህዝብ አጋዥና መከታ ነው።
ይህ ሰራዊት የሀገር ውስጥ ጋሻ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም በአህጉሪቱና በዓለም አቀፍ ደረጃ በተሰማራባቸው የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ሁሉ ሰብአዊነትንና የህግ የበላይነትን ያስቀደመ፣ የሌሎችን ህዝቦች ነፃነትና ክብር እንደ ራሱ አድርጎ የጠበቀ እጅግ ተወዳጅና የተከበረ ኃይል ነው። በሊቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በዳርፉርና በሶማሊያ በረሃዎች ውስጥ የፈሰሰው ላቡና ደሙ፣ የኢትዮጵያን ስም በዓለም የክብር መዝገብ ላይ በደመቀ ቀለም አስፍሮታል።
የሰራዊቱ አባላት ሌሎችን ማክበርና ለተቸገሩት መድረስ ከአባቶቻቸው የወረሱት የደም እሴት በመሆኑ, በተሰማራበት አህጉርና ቀጠና ሁሉ በህዝቦች ልብ ውስጥ የማይጠፋ የፍቅርና የታማኝነት አሻራ ጥሏል። በዚህም የተነሳ በአፍሪካ ምድር ህዝቦች ዘንድ እጅግ ተወዳጅ ነው።
ከዚህም በላይ፣ ይህ የጀግኖች ስብስብ ጠመንጃ ብቻ ሳይሆን አካፋና ዶማም መያዝ የሚችል የልማት ግንባር ቀደም ኃይል ነው። በኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ውስጥ፣ በታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶች፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በታላቁ ህዳሴ ግድብና በህዝባዊ አገልግሎቶች ላይ ቀዳሚ በመሆን ድህነትን የሚዋጋ፣ ህዝቡን ከረሃብና ከችግር የሚታደግ የላብ አርበኛ ነው።
ሰላምን በደሙ፣ ልማትንና ብልጽግናን ደግሞ በላቡ እያረጋገጠ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እውን ያደርጋል። ይህ ሰራዊት በጦር ግንባር ጀግና፣ በልማት ግንባር ደግሞ መሀንዲስ ሆኖ ሀገርን ወደ ታላቅ ከፍታ ይመራታል።
ባጠቃላይ፣ የኩሩ ህዝቦች መኖሪያ የሆነችውን ኢትዮጵያን እንደ አክሊል ደፍቶ፣ ቀለማቷን ጠብቆ፣ ታሪኳን አድሶ፣ ፈተናዎችን በብቃት ተሻግሮና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ አግዞ የሚጓዘው የመከላከያ ሰራዊታችን፣ የኢትዮጵያ ህያው ህልውና፣ የነፃነቷ ዐለት፣ የብዝሃነቷ ውበት እና የነገው ታላቅነቷ እውነተኛ ዋስትና ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
Ethiopian Broadcasting Corporation #ጀግንነት #ኢትዮጵያ #ሰላም
*****************
"የኩሩ ህዝቦች መኖሪያ የህብረ ብሄር ቡቃያ፣ የሰላም ተምሳሌት ዓርማ የቀለሞች ህብር ኢትዮጵያ!"
ይህ የክብርና የሉዓላዊነት ብሔራዊ መዝሙር ስንኝ፣ ተራ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የታሪክ፣ የፅናትና የማንነት መልክ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የህሊና ብሩህ መስታወት ነው።
የመከላከያ ሰራዊቱ የማይበገር ጥንካሬ የሚመነጨው በልቡ ውስጥ ከነደደው የማያልቅ የሀገር ፍቅር እሳትና በውስጡ ከሰረጸው ጠንካራ ወታደራዊ ዲሲፕሊን ነው።
ሰራዊቱ ሀገርን በመጠበቅና ዳር ድንበርን በማስከበር ረገድ በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ የሌለው፣ የታሪክን ታላላቅ ፈተናዎች በትከሻው የተሸከመ የሰላም ጽኑ ዐለት ነው።
የጦር ሜዳ ውሎው ስልታዊና አስፈሪ፣ የሰላም ጊዜው ደግሞ ለህዝብ አጋዥና መከታ ነው።
ይህ ሰራዊት የሀገር ውስጥ ጋሻ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም በአህጉሪቱና በዓለም አቀፍ ደረጃ በተሰማራባቸው የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ሁሉ ሰብአዊነትንና የህግ የበላይነትን ያስቀደመ፣ የሌሎችን ህዝቦች ነፃነትና ክብር እንደ ራሱ አድርጎ የጠበቀ እጅግ ተወዳጅና የተከበረ ኃይል ነው። በሊቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በዳርፉርና በሶማሊያ በረሃዎች ውስጥ የፈሰሰው ላቡና ደሙ፣ የኢትዮጵያን ስም በዓለም የክብር መዝገብ ላይ በደመቀ ቀለም አስፍሮታል።
የሰራዊቱ አባላት ሌሎችን ማክበርና ለተቸገሩት መድረስ ከአባቶቻቸው የወረሱት የደም እሴት በመሆኑ, በተሰማራበት አህጉርና ቀጠና ሁሉ በህዝቦች ልብ ውስጥ የማይጠፋ የፍቅርና የታማኝነት አሻራ ጥሏል። በዚህም የተነሳ በአፍሪካ ምድር ህዝቦች ዘንድ እጅግ ተወዳጅ ነው።
ከዚህም በላይ፣ ይህ የጀግኖች ስብስብ ጠመንጃ ብቻ ሳይሆን አካፋና ዶማም መያዝ የሚችል የልማት ግንባር ቀደም ኃይል ነው። በኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ውስጥ፣ በታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶች፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በታላቁ ህዳሴ ግድብና በህዝባዊ አገልግሎቶች ላይ ቀዳሚ በመሆን ድህነትን የሚዋጋ፣ ህዝቡን ከረሃብና ከችግር የሚታደግ የላብ አርበኛ ነው።
ሰላምን በደሙ፣ ልማትንና ብልጽግናን ደግሞ በላቡ እያረጋገጠ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እውን ያደርጋል። ይህ ሰራዊት በጦር ግንባር ጀግና፣ በልማት ግንባር ደግሞ መሀንዲስ ሆኖ ሀገርን ወደ ታላቅ ከፍታ ይመራታል።
ባጠቃላይ፣ የኩሩ ህዝቦች መኖሪያ የሆነችውን ኢትዮጵያን እንደ አክሊል ደፍቶ፣ ቀለማቷን ጠብቆ፣ ታሪኳን አድሶ፣ ፈተናዎችን በብቃት ተሻግሮና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ አግዞ የሚጓዘው የመከላከያ ሰራዊታችን፣ የኢትዮጵያ ህያው ህልውና፣ የነፃነቷ ዐለት፣ የብዝሃነቷ ውበት እና የነገው ታላቅነቷ እውነተኛ ዋስትና ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
Ethiopian Broadcasting Corporation #ጀግንነት #ኢትዮጵያ #ሰላም
Sponsored by
Surafel
2 months ago
እባካችሁ በኦቲዝም ስም አትነግዱ!
"ከወላጆች አይን እንባ በዝታለች፣ እግዚአብሄርም ያያል !"
( መላኩ ብርሃኑ)
ኢትዮጵያ ውስጥ ኦቲዝም "እጅግ በጣም ውድ" ችግር ነው፡፡ ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ የወላጅን ሸክም ለማቅለል የተዘረጋ ምንም አይነት ስርዓት ስለሌለ ኦቲዝም ወደአንድ ቤት ሲመጣ የዚያ ቤት ህይወት ከመሰረቱ ይናጋል።
ልጆቹ የሙሉ ጊዜ ጥበቃ ስለሚያስፈልጋቸው ወላጅ እየሰራ ከሆነ ስራውን፣ እየተማረ ከሆነም ትምህርቱን ለመተው ይገደዳል። ይህ ደግሞ ለኦኮኖሚ ጫና፣ ለስነልቡና ቀውስ፣ ለማህበራዊ ግንኙነት መዳከምና አልፎ ተርፎም ለከባድ የጤና ቀውስ ይዳርጋል።
እስኪ አስቡት !
ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ልጅ ኦቲዝም እንዳለበት ለመመርመር (Diagnose) ለማድረግ የላብሯቶሪ ወጪውን ሳይጨምር ለህክምና ባለሙያው ብቻ የሚከፈል እስከ 20 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ይደርሳል።
እስከ 25 ሺህ ብር የሚደርስ የሃገር ውስጥ ምርመራን እንተወውና እንደ yeast overgrowth, heavy metal test, OAT test, FRAT test ውጪ ልኮ ለማሰራት ከ100 -200 ሺህ ብር በላይ ይጠየቃል።
ኦቲዝም ያላቸው ልጆች ብዙውን ጊዜ ከአንጀታቸው ጋር የተያያዘ የጤና ችግር አለባቸው ተብሎ ስለሚታመን 'ግሉቲን እና ኬዚን' የሚባሉ ንጥረነገሮች ካሏቸው ምግቦች ነጻ መሆን አለባቸው። እኛ ሃገር ደግሞ “ግሉቲን ፍሪ፣ ኬዚን ፍሪ” የሚባሉት የምግብ አይነቶች በአቅርቦት ደረጃ ውስንና በጣም ውድ ናቸው።ከሰንዴ ዘርና ከወተት መራቅ አለባቸው።
ለነሱ የሚሆን ወተት ለመስራት የሚጠቅም አንድ ኪሎ 'አልመንድ' የሚባል ፍሬ በትንሹ እስከ 5 ሺህ ብር ያስወጣል። ምግባቸው ውድ በሆነው የንጹህ የወይራ ዘይት ካልሆነ በቀር በሌላ መሰራት አይችልም። ስኳርና ሰውሰራሽ ማጣፈጫ ስለማይጠቀሙ በምትኩ ቴምር ለመግዛት በኪሎ ከ1500-3500 ብር ድረስ ይጠይቃል።
በዚህ ሳቢያ ልጆቹ የሚወስዱት ምግብ አይነት ስለሚያንስ እንዳይጎዱ ሲባል 'ሰፕሊመንት' ያስፈልጋቸዋል። ለምሳሌ ለነሱ የሚሆን የአሳ ዘይት ዋጋው ከ 12 ሺህ እስከ 35ሺህ ብር ይሸጣል። ለጥቂት ቀን ብቻ የሚሆን ቫይታሚን ዲ ደግሞ እስከ 5 ሺህ ብር ይሸጣል። አቅም ላለው ወላጅ እንኳን ሌሎች ሌሎች ተጨምረው የሰፕሊመንት ዋጋ ብቻ በወር ከ50 ሺህ ብር በላይ ያስወጣዋል።
በአጠቃላይ ለአንድ ኦቲዝም ላለበት ልጅ የሚወጣው የአንድ ወር የምግብ ወጪ አንድ ቤት ውስጥ ለሙሉ ቤተሰብ ከሚወጣው የቀለብ ወጪ ይበልጣል።
ኦቲዝም በሽታ ስላልሆነ መድሃኒት የለውም፡፡ ለኦቲዝም የሚደረገው ድጋፍ በአብዛኛው የንግግር፣ የባህሪና የአካልና ሰውነት ቅንጅት ቴራፒ ነው፡፡ እዚህ ጋር ደግሞ ነጋዴዎቹ ተሰብስበዋል።
የሚችሉትም የማይችሉትም የሆነች ዛኒጋባ ተከራይተው እንሰጣለን ለሚሉት ተራፒ የሚያስከፍሉት ዋጋ በጣም ውድ ነው። ለአንድ ልጅ በወር 30 ሰዓት ቴራፒ ለመስጠት የሚከፈለው ገንዘብ የአንድ ልጅን የ6 ወር የግል ትምህርት ቤት ክፍያ ይበልጣል።
በቁጥር ጥቂት የሆኑት 'የልዩ ፍላጎት አካቶ' ያላቸው ትምህርት ቤቶች ክፍያ ዋጋ ደግሞ አይወራ። ታዋቂ ነን የሚሉት አንዳንዶቹ ትምህርት ቤቶች በወር እስከ 100 ሺህ ብር ያስከፍላሉ። በጨበጣ ያለምንም እውቀት ኦቲዝምን ቢዝነስ ያደረጉ አንዳንድ ነጋዴ ግለሰቦች የከፈቱት ትምህርት ቤት ደሞ አለ። አዳሪ ብለው እስከ 300ሺህ ብር በወር ያስከፍላሉ።
ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤቶች እንኳን የማያስከፍሉትን አይነት ገንዘብ የሚያስከፍሉ አካቶ ት/ቤቶችና በኦቲዝም ስም የተቋቋሙ ተቋማት በጣም ብዙ ናቸው፡፡
በዚህ ላይ ልጁ ትምህርት ቤት ሲሄድም ሆነ ሲመለስ ሰርቪስ የሚጠቀም ከሆነ ወላጆች ለመጓጓዣው ከመደበኞቹ ህጻናት በእጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ፡፡
ይህን ይህን ሳይ በሃገሬ ተስፋ እቆርጣለሁ። ስርዓት ያልተዘረጋለት፣ ደንብና ህግ ያልወጣለት፣ በሙስና ሰንሰለት የተጨማለቀ ፣ ከኤንጂኦ እስከ ግለሰቦች ድረስ በኦቲዝም ስም የጦፈ ንግድ ሲካሄድ ሃይ ባይ የታጣበት ሃገር ላይ ነን ያለነው።
እንደኔ ጠለቅ ብሎ ለሚያየው እዚህ ዘርፍ ላይ ያለው መጨመላለቅና ብዝበዛ በጣም ይሰቀጥጣል፡፡
መቼም በጥቂቱ ካነሳሁት እውነት አንጻር በዚህ ዘመን የኑሮ ውድነት አንድ ወላጅ ቤት ኦቲዝም ሲደረብበት በስነልቡናም፣ በገንዘብም ምን ያህል ከባድ የህይወት መርግ እንደሚፈጥር ካሰባችሁት ይበቃል፡፡
እናንት 'ሞራል አልባ' ነጋዴዎች! እንዲህ ባለ 'ውድ' ችግር ላይ አይናችሁን አጥባችሁ ገንዘብ ለማጋበስና መሄጃ አጥቶ የተቸገረውን ወላጅ ለመበዝበዝ እንዴት ህሊናችሁ እሺ አላችሁ ግን? (በርግጥ ህሊና የላችሁም!)
በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡ይህ'ኮ ኢሰብአዊነት ነው። ወንጀል ነው። የሞራል ዝቅጠት ነው። ዛሬ ከኔ ባልተሻለ ጥቂት ንባብ ብቻ ተነስታችሁ ቤት ተከራይታችሁና ማዕከል ከፍታችሁ ‘ባለሙያ ነን’ እያላችሁ 'ቢዝነስ' የምትሰሩ ፣ ቲክቶኩንና ሶሻል ሚዲያውን ያጣበባችሁ ሰዎች ... ምናችሁን ነው የሚያማችሁ? ነገ'ኮ ይህ በህጋዊነት ሽፋን ያለቁጥጥር በተለቀቀ ሜዳ ላይ ስትፋንኑ የበደላችሁት ወላጅ እንባ ቤታችሁ ድረስ ይመጣል።
ኦቲዝም ላይ እንሰራለን ብላችሁ የምትደሰኩሩ ሃኪሞችምም፣ ሳይኮሎጂስቶችም፣ ቴራፒስቶችም፣ አካቶ ትምህርት ቤቶችም፣ማዕከላትም ቆም ብላችሁ ብታስቡ ይበጃችኋል!
ይህ ምርጫ ያጣ… ተመልካች ያጣ፣ ልጄ ቢሻሻልልኝ ብሎ እዚህም እዚያም መፍትሄ ፍለጋ የሚኳትን ወላጅ በኦቲዝም ምክንያት ጥሪቱን አሟጦ ሌሎች ልጆቹን የሚያሳድግበትና ቤቱን የሚመራበት ገንዘብ እስኪያጣ ድረስ ሲቸገር እናንተ አላግባብ በዘረፋችሁት ገንዘብ ሰላም፣ ጤናና የሰላም እንጀራ አይኖራችሁም ።
አያሳዝናችሁም ግን ? በናንተ የዋጋ ውድነትና ሳቢያ አቅም አጥቶ ዕድሜውን ሙሉ ‘ለልጄ ይህንን ሳላደርግለት’ ብሎ በጸጸት እንባ የሚታጠብ ወላጅ ግን አያሳዝናችሁም?
በዚህ ወላጅ ላይ ህይወት ላይ እየተጫወታችሁ እስከመቼ ራሳችሁን ታበለጽጋላችሁ ?
አንድ ቀን ግን ይመጣል! አላግባብ ለምትሰበስቡት ትርፍ አንድ ቀን እግዚአብሄር ይፈርድባችኋል ! የወላጅ እንባ በቤታችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይመጣል። ያኔ እናንተም ቁጭ ብላችሁ ታለቅሳላችሁ !
(ማሳሰቢያ ፤ ይህ ጽሁፍ በሃቅ የሚሰሩ፣ ልጆቹንና ወላጆችን ለመርዳት የሚለፉትን ባለሙያዎች አይመለከትም)
ሜርድ!!
"ከወላጆች አይን እንባ በዝታለች፣ እግዚአብሄርም ያያል !"
( መላኩ ብርሃኑ)
ኢትዮጵያ ውስጥ ኦቲዝም "እጅግ በጣም ውድ" ችግር ነው፡፡ ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ የወላጅን ሸክም ለማቅለል የተዘረጋ ምንም አይነት ስርዓት ስለሌለ ኦቲዝም ወደአንድ ቤት ሲመጣ የዚያ ቤት ህይወት ከመሰረቱ ይናጋል።
ልጆቹ የሙሉ ጊዜ ጥበቃ ስለሚያስፈልጋቸው ወላጅ እየሰራ ከሆነ ስራውን፣ እየተማረ ከሆነም ትምህርቱን ለመተው ይገደዳል። ይህ ደግሞ ለኦኮኖሚ ጫና፣ ለስነልቡና ቀውስ፣ ለማህበራዊ ግንኙነት መዳከምና አልፎ ተርፎም ለከባድ የጤና ቀውስ ይዳርጋል።
እስኪ አስቡት !
ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ልጅ ኦቲዝም እንዳለበት ለመመርመር (Diagnose) ለማድረግ የላብሯቶሪ ወጪውን ሳይጨምር ለህክምና ባለሙያው ብቻ የሚከፈል እስከ 20 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ይደርሳል።
እስከ 25 ሺህ ብር የሚደርስ የሃገር ውስጥ ምርመራን እንተወውና እንደ yeast overgrowth, heavy metal test, OAT test, FRAT test ውጪ ልኮ ለማሰራት ከ100 -200 ሺህ ብር በላይ ይጠየቃል።
ኦቲዝም ያላቸው ልጆች ብዙውን ጊዜ ከአንጀታቸው ጋር የተያያዘ የጤና ችግር አለባቸው ተብሎ ስለሚታመን 'ግሉቲን እና ኬዚን' የሚባሉ ንጥረነገሮች ካሏቸው ምግቦች ነጻ መሆን አለባቸው። እኛ ሃገር ደግሞ “ግሉቲን ፍሪ፣ ኬዚን ፍሪ” የሚባሉት የምግብ አይነቶች በአቅርቦት ደረጃ ውስንና በጣም ውድ ናቸው።ከሰንዴ ዘርና ከወተት መራቅ አለባቸው።
ለነሱ የሚሆን ወተት ለመስራት የሚጠቅም አንድ ኪሎ 'አልመንድ' የሚባል ፍሬ በትንሹ እስከ 5 ሺህ ብር ያስወጣል። ምግባቸው ውድ በሆነው የንጹህ የወይራ ዘይት ካልሆነ በቀር በሌላ መሰራት አይችልም። ስኳርና ሰውሰራሽ ማጣፈጫ ስለማይጠቀሙ በምትኩ ቴምር ለመግዛት በኪሎ ከ1500-3500 ብር ድረስ ይጠይቃል።
በዚህ ሳቢያ ልጆቹ የሚወስዱት ምግብ አይነት ስለሚያንስ እንዳይጎዱ ሲባል 'ሰፕሊመንት' ያስፈልጋቸዋል። ለምሳሌ ለነሱ የሚሆን የአሳ ዘይት ዋጋው ከ 12 ሺህ እስከ 35ሺህ ብር ይሸጣል። ለጥቂት ቀን ብቻ የሚሆን ቫይታሚን ዲ ደግሞ እስከ 5 ሺህ ብር ይሸጣል። አቅም ላለው ወላጅ እንኳን ሌሎች ሌሎች ተጨምረው የሰፕሊመንት ዋጋ ብቻ በወር ከ50 ሺህ ብር በላይ ያስወጣዋል።
በአጠቃላይ ለአንድ ኦቲዝም ላለበት ልጅ የሚወጣው የአንድ ወር የምግብ ወጪ አንድ ቤት ውስጥ ለሙሉ ቤተሰብ ከሚወጣው የቀለብ ወጪ ይበልጣል።
ኦቲዝም በሽታ ስላልሆነ መድሃኒት የለውም፡፡ ለኦቲዝም የሚደረገው ድጋፍ በአብዛኛው የንግግር፣ የባህሪና የአካልና ሰውነት ቅንጅት ቴራፒ ነው፡፡ እዚህ ጋር ደግሞ ነጋዴዎቹ ተሰብስበዋል።
የሚችሉትም የማይችሉትም የሆነች ዛኒጋባ ተከራይተው እንሰጣለን ለሚሉት ተራፒ የሚያስከፍሉት ዋጋ በጣም ውድ ነው። ለአንድ ልጅ በወር 30 ሰዓት ቴራፒ ለመስጠት የሚከፈለው ገንዘብ የአንድ ልጅን የ6 ወር የግል ትምህርት ቤት ክፍያ ይበልጣል።
በቁጥር ጥቂት የሆኑት 'የልዩ ፍላጎት አካቶ' ያላቸው ትምህርት ቤቶች ክፍያ ዋጋ ደግሞ አይወራ። ታዋቂ ነን የሚሉት አንዳንዶቹ ትምህርት ቤቶች በወር እስከ 100 ሺህ ብር ያስከፍላሉ። በጨበጣ ያለምንም እውቀት ኦቲዝምን ቢዝነስ ያደረጉ አንዳንድ ነጋዴ ግለሰቦች የከፈቱት ትምህርት ቤት ደሞ አለ። አዳሪ ብለው እስከ 300ሺህ ብር በወር ያስከፍላሉ።
ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤቶች እንኳን የማያስከፍሉትን አይነት ገንዘብ የሚያስከፍሉ አካቶ ት/ቤቶችና በኦቲዝም ስም የተቋቋሙ ተቋማት በጣም ብዙ ናቸው፡፡
በዚህ ላይ ልጁ ትምህርት ቤት ሲሄድም ሆነ ሲመለስ ሰርቪስ የሚጠቀም ከሆነ ወላጆች ለመጓጓዣው ከመደበኞቹ ህጻናት በእጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ፡፡
ይህን ይህን ሳይ በሃገሬ ተስፋ እቆርጣለሁ። ስርዓት ያልተዘረጋለት፣ ደንብና ህግ ያልወጣለት፣ በሙስና ሰንሰለት የተጨማለቀ ፣ ከኤንጂኦ እስከ ግለሰቦች ድረስ በኦቲዝም ስም የጦፈ ንግድ ሲካሄድ ሃይ ባይ የታጣበት ሃገር ላይ ነን ያለነው።
እንደኔ ጠለቅ ብሎ ለሚያየው እዚህ ዘርፍ ላይ ያለው መጨመላለቅና ብዝበዛ በጣም ይሰቀጥጣል፡፡
መቼም በጥቂቱ ካነሳሁት እውነት አንጻር በዚህ ዘመን የኑሮ ውድነት አንድ ወላጅ ቤት ኦቲዝም ሲደረብበት በስነልቡናም፣ በገንዘብም ምን ያህል ከባድ የህይወት መርግ እንደሚፈጥር ካሰባችሁት ይበቃል፡፡
እናንት 'ሞራል አልባ' ነጋዴዎች! እንዲህ ባለ 'ውድ' ችግር ላይ አይናችሁን አጥባችሁ ገንዘብ ለማጋበስና መሄጃ አጥቶ የተቸገረውን ወላጅ ለመበዝበዝ እንዴት ህሊናችሁ እሺ አላችሁ ግን? (በርግጥ ህሊና የላችሁም!)
በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡ይህ'ኮ ኢሰብአዊነት ነው። ወንጀል ነው። የሞራል ዝቅጠት ነው። ዛሬ ከኔ ባልተሻለ ጥቂት ንባብ ብቻ ተነስታችሁ ቤት ተከራይታችሁና ማዕከል ከፍታችሁ ‘ባለሙያ ነን’ እያላችሁ 'ቢዝነስ' የምትሰሩ ፣ ቲክቶኩንና ሶሻል ሚዲያውን ያጣበባችሁ ሰዎች ... ምናችሁን ነው የሚያማችሁ? ነገ'ኮ ይህ በህጋዊነት ሽፋን ያለቁጥጥር በተለቀቀ ሜዳ ላይ ስትፋንኑ የበደላችሁት ወላጅ እንባ ቤታችሁ ድረስ ይመጣል።
ኦቲዝም ላይ እንሰራለን ብላችሁ የምትደሰኩሩ ሃኪሞችምም፣ ሳይኮሎጂስቶችም፣ ቴራፒስቶችም፣ አካቶ ትምህርት ቤቶችም፣ማዕከላትም ቆም ብላችሁ ብታስቡ ይበጃችኋል!
ይህ ምርጫ ያጣ… ተመልካች ያጣ፣ ልጄ ቢሻሻልልኝ ብሎ እዚህም እዚያም መፍትሄ ፍለጋ የሚኳትን ወላጅ በኦቲዝም ምክንያት ጥሪቱን አሟጦ ሌሎች ልጆቹን የሚያሳድግበትና ቤቱን የሚመራበት ገንዘብ እስኪያጣ ድረስ ሲቸገር እናንተ አላግባብ በዘረፋችሁት ገንዘብ ሰላም፣ ጤናና የሰላም እንጀራ አይኖራችሁም ።
አያሳዝናችሁም ግን ? በናንተ የዋጋ ውድነትና ሳቢያ አቅም አጥቶ ዕድሜውን ሙሉ ‘ለልጄ ይህንን ሳላደርግለት’ ብሎ በጸጸት እንባ የሚታጠብ ወላጅ ግን አያሳዝናችሁም?
በዚህ ወላጅ ላይ ህይወት ላይ እየተጫወታችሁ እስከመቼ ራሳችሁን ታበለጽጋላችሁ ?
አንድ ቀን ግን ይመጣል! አላግባብ ለምትሰበስቡት ትርፍ አንድ ቀን እግዚአብሄር ይፈርድባችኋል ! የወላጅ እንባ በቤታችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይመጣል። ያኔ እናንተም ቁጭ ብላችሁ ታለቅሳላችሁ !
(ማሳሰቢያ ፤ ይህ ጽሁፍ በሃቅ የሚሰሩ፣ ልጆቹንና ወላጆችን ለመርዳት የሚለፉትን ባለሙያዎች አይመለከትም)
ሜርድ!!
2 months ago
የኢትዮጵያ ታላቅ ወዳጅ:
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ መታሰቢያ
* ጣሊያናዊ ምሁር፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ናቸው
* ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ሌጋሲያቸውን ( Legacy ) ለማስቀጠል እየታተሩ ናቸው
#ethiopia | በአፍሪካና በኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት በሕክምና ሙያቸው፣ በደራሲነታቸውና በሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎቻቸው ደካማና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች ሲረዱ የቆዩት ታዋቂው ጣሊያናዊ ምሁር ፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ (ዶክተር) በተወለዱ በ81 ዓመታቸው ሰኔ 10 ቀን 2024 ዓ.ም. ተለይተውናል።
ፕሮፌሰሩ ለአርባ አምስት ዓመታት በዘለቀው ሙያዊ ሕይወታቸው በአርባ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት እየተዘዋወሩ በበጎ ፈቃደኝነት የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኦርቶፔዲክስ (የአጥንት) እና በዴርማቶሎጂ (የቆዳ) ሕክምና ስፔሻሊስት ነበሩ።
በሱዳን የሚገኘውን ትልቅ ሆስፒታል ጣሊያኖች በሚገነቡበት ወቅት ከፍተኛ የገንዘብ ፈንድ በማምጣት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በሀገራችን ኢትዮጵያም ለሀያ ዓመታት ያህል ያገለገሉ ሲሆን፣ የአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታልን በማቋቋም የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በተጨማሪም በዳኑ ሆስፒታል፣ በአቤት ሆስፒታል ድንገተኛ አደጋ ክፍል በአጥንት ስፔሻሊስትነት የሰሩ ሲሆን፣ በየዓመቱ ከጣሊያን ወደ ወሊሶ ሆስፒታል እየመጡ ሰፊ የኦፕራሲዮን ሕክምና አገልግሎት በነፃ ይሰጡ ነበር።
ፕሮፌሰር ኤንሪኮ የሰውን ልጅ በዘር፣ በቋንቋ፣ በቆዳ ቀለምና በሃይማኖት የማይለዩ ፍፁም የሰብአዊነት ተምሳሌት ነበሩ። በአውሮፓ የኮሶቮ ጦርነት ወቅት የአንድ ዓመት ደሞዛቸውን በመተው በጦርነቱ መሃል በነፃ የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅትም በመጀመሪያዎቹ አምስት ጣሊያናውያን የሕክምና ባለሙያዎች ቡድን ውስጥ በመሆን በሄሊኮፕተር ወደ ስፍራው ያቀኑ ታላቅ ባለውለታ ናቸው።
በጣሊያን ሚላኖ "ናጋ" የተሰኘ የሕክምና ማዕከል በማቋቋምም አፍሪካውያንና የሌሎች ሀገራት ስደተኞችን፣ በተለይም የሕጋዊ ሰነድና የገንዘብ አቅም የሌላቸውን ወገኖች በነፃ ሲያክሙ ቆይተዋል።
ብዙዎች ስለ ሀገር ሲያነሱ "የአባት ሀገር" ወይም "የእናት ሀገር" ቢሉም፣ ፕሮፌሰሩ ግን ለኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅር ጥልቅ በመሆኑ ሁልጊዜም "የልጄ የካሌብ ሀገር" በማለት በኩራት ይገልጿት ነበር።
ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ወታደራዊ ታሪክ በርካታ ምርምሮችን ያደረጉት ፕሮፌሰሩ፣ በአጠቃላይ ከ46 በላይ መጻሕፍትን በኢንግሊዘኛና በጣሊያንኛ ቋንቋዎች አሳትመዋል።
ከእነዚህም መካከል "The History of Imperial Ethiopian Army" የተሰኘውና ለኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርምር ማዕከል ያበረከቱት መጽሐፍ፣ "ደስታስ ይርስ ኤንድ ላይፍ 1892-1937" እና "Aethiopia la moneta Africana" የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። የቡና አመጣጥ ከኢትዮጵያ መሆኑን ለአለም ካስተዋወቁበት ስራቸው ባሻገር የዘመነ መሳፍንትን ፍፃሜ የሚያሳይ ታሪካዊ መጽሐፍ ይጠቀሳሉ።
እኝህ ታላቅ ምሁር ስኮላር፣ ዶክተር፣ የሚሊተሪ ኦፊሰር እና ደራሲ ብቻ ሳይሆኑ፣ በሚላኖ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ "ትንሹ ልዑል" የተሰኘውን የሕጻናት መጽሐፍ በ55 ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተሙ ተርጓሚና ድንቅ የቅብ ሥራዎችን ያበረከቱ ሰዓሊም ነበሩ።
ምንም እንኳን ሞት በድንገት ከሚወዷቸው ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ቢለያቸውም፣ ያኖሩት ታላቅ አሻራ ግን ከመቃብር በላይ ሁሌም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ባለቤታቸውና ልጃቸው የፕሮፌሰሩን ውርስና ሌጋሲ ለማስቀጠል፣ እሳቸው ሳይታተሙ የተዉትንና ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ በአምስት መቶ አምስት መቶ ገጾች የተቀነበቡ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍትን ለሕትመት ለማብቃት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያን የመወደዳቸው ምዕራፍ የተገለጠው፤ የተጀመረው በባለቤታቸውና በልጃቸው እንደሆነ ይናገሩ ነበር። በዚህ መሠረት ቤተሰቦቻቸው በኢትዮጵያ ምድር በስማቸው ሙዚየም ለመክፈት አልያም በእርሳቸው የተሰሩ ሥራዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ለማበርከት ሰፊ እንቅስቃሴ ላይ ናቸው።
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲን ሕይወትና ሥራዎች ፤ ለአገርና ለሕዝብ ያበረከቱትን አስተዋጸኦ በክብር የሚዘክር ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይጠበቃል።
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Ethiopia’s Great Friend:
In Memory of Professor Colonel Enrico Piero Bossi
Italian scholar and human rights advocate
His wife, Mrs. Sara Yemane, and their son, Caleb Giorgi, are working to preserve and continue his legacy.
#ethiopia | The renowned Italian scholar, Professor Colonel Enrico Piero Bossi (M.D.), who dedicated many years of his life in Africa and Ethiopia through his medical profession, authorship, and humanitarian activities, helping vulnerable and disadvantaged communities, passed away at the age of 81 on June 17, 2024.
During his distinguished 45-year professional career, Professor Bossi volunteered medical services across 42 African countries. He was a specialist in Orthopedics (bone and musculoskeletal medicine) and Dermatology (skin medicine).
He made a significant contribution to securing major funding for the construction of a large hospital in Sudan built by Italian organizations.
In Ethiopia, where he served for nearly twenty years, he played a key role in establishing Adama General Hospital and served as its first director.
Additionally, he worked as an orthopedic specialist at Danu Hospital and in the Emergency Department of Abet Hospital. Every year, he traveled from Italy to Woliso Hospital, where he provided extensive surgical services free of charge.
Professor Enrico was a true symbol of humanity, treating all people equally regardless of race, language, skin color, or religion. During the Kosovo War in Europe, he gave up an entire year’s salary to provide free medical services in the war zone. Likewise, during the Ethio-Eritrean War, he was among the first five Italian medical professionals who flew by helicopter to the conflict area to provide humanitarian assistance.
In Milan, Italy, he founded the medical center known as “NAGA,” where he provided free healthcare services to African immigrants and migrants from other countries, particularly those lacking legal documentation or financial means.
While many people refer to their homeland as their “fatherland” or “motherland,” Professor Bossi’s love for Ethiopia was so profound that he proudly referred to it as “the country of my son, Caleb.”
A dedicated researcher of Ethiopian history, culture, and military history, Professor Bossi authored and published more than 46 books in English and Italian.
Among his notable works are:
The History of Imperial Ethiopian Army
Destas Yirs and Life 1892–1937
Aethiopia la Moneta Africana
His work helped introduce Ethiopia’s role as the birthplace of coffee to the wider world. He also authored historical works documenting the end of the Era of the Princes (Zemene Mesafint).
Professor Bossi was not only a scholar, physician, military officer, and author, but also a translator and artist. At the Catholic University of Milan, he translated and published The Little Prince in 55 international languages and contributed remarkable artistic and illustrative works.
Although death unexpectedly separated him from his beloved wife, Mrs. Sara Yemane, and his son, Caleb Giorgi, the remarkable legacy he left behind will remain alive far beyond his grave.
To preserve Professor Bossi’s legacy, his wife and son are working to complete and publish two previously unpublished manuscripts. These extensive works, each consisting of approximately 500 pages, focus on Ethiopian subjects and were left unfinished by the professor.
The professor used to say that the chapter of his love for Ethiopia was revealed—and indeed began—with his wife and his child. Based on this, his family is actively working either to open a museum in Ethiopia bearing his name or to donate his works, along with various personal artifacts and items, to the Ethiopian National Museum.
It is hoped that the Ethiopian Heritage Authority will undertake initiatives to honor and commemorate Professor Colonel Enrico Piero Bossi’s life, work, and invaluable contributions to the nation and its people.
May his memory and contributions continue to inspire future generations.
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ መታሰቢያ
* ጣሊያናዊ ምሁር፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ናቸው
* ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ሌጋሲያቸውን ( Legacy ) ለማስቀጠል እየታተሩ ናቸው
#ethiopia | በአፍሪካና በኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት በሕክምና ሙያቸው፣ በደራሲነታቸውና በሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎቻቸው ደካማና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች ሲረዱ የቆዩት ታዋቂው ጣሊያናዊ ምሁር ፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ (ዶክተር) በተወለዱ በ81 ዓመታቸው ሰኔ 10 ቀን 2024 ዓ.ም. ተለይተውናል።
ፕሮፌሰሩ ለአርባ አምስት ዓመታት በዘለቀው ሙያዊ ሕይወታቸው በአርባ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት እየተዘዋወሩ በበጎ ፈቃደኝነት የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኦርቶፔዲክስ (የአጥንት) እና በዴርማቶሎጂ (የቆዳ) ሕክምና ስፔሻሊስት ነበሩ።
በሱዳን የሚገኘውን ትልቅ ሆስፒታል ጣሊያኖች በሚገነቡበት ወቅት ከፍተኛ የገንዘብ ፈንድ በማምጣት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በሀገራችን ኢትዮጵያም ለሀያ ዓመታት ያህል ያገለገሉ ሲሆን፣ የአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታልን በማቋቋም የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በተጨማሪም በዳኑ ሆስፒታል፣ በአቤት ሆስፒታል ድንገተኛ አደጋ ክፍል በአጥንት ስፔሻሊስትነት የሰሩ ሲሆን፣ በየዓመቱ ከጣሊያን ወደ ወሊሶ ሆስፒታል እየመጡ ሰፊ የኦፕራሲዮን ሕክምና አገልግሎት በነፃ ይሰጡ ነበር።
ፕሮፌሰር ኤንሪኮ የሰውን ልጅ በዘር፣ በቋንቋ፣ በቆዳ ቀለምና በሃይማኖት የማይለዩ ፍፁም የሰብአዊነት ተምሳሌት ነበሩ። በአውሮፓ የኮሶቮ ጦርነት ወቅት የአንድ ዓመት ደሞዛቸውን በመተው በጦርነቱ መሃል በነፃ የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅትም በመጀመሪያዎቹ አምስት ጣሊያናውያን የሕክምና ባለሙያዎች ቡድን ውስጥ በመሆን በሄሊኮፕተር ወደ ስፍራው ያቀኑ ታላቅ ባለውለታ ናቸው።
በጣሊያን ሚላኖ "ናጋ" የተሰኘ የሕክምና ማዕከል በማቋቋምም አፍሪካውያንና የሌሎች ሀገራት ስደተኞችን፣ በተለይም የሕጋዊ ሰነድና የገንዘብ አቅም የሌላቸውን ወገኖች በነፃ ሲያክሙ ቆይተዋል።
ብዙዎች ስለ ሀገር ሲያነሱ "የአባት ሀገር" ወይም "የእናት ሀገር" ቢሉም፣ ፕሮፌሰሩ ግን ለኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅር ጥልቅ በመሆኑ ሁልጊዜም "የልጄ የካሌብ ሀገር" በማለት በኩራት ይገልጿት ነበር።
ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ወታደራዊ ታሪክ በርካታ ምርምሮችን ያደረጉት ፕሮፌሰሩ፣ በአጠቃላይ ከ46 በላይ መጻሕፍትን በኢንግሊዘኛና በጣሊያንኛ ቋንቋዎች አሳትመዋል።
ከእነዚህም መካከል "The History of Imperial Ethiopian Army" የተሰኘውና ለኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርምር ማዕከል ያበረከቱት መጽሐፍ፣ "ደስታስ ይርስ ኤንድ ላይፍ 1892-1937" እና "Aethiopia la moneta Africana" የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። የቡና አመጣጥ ከኢትዮጵያ መሆኑን ለአለም ካስተዋወቁበት ስራቸው ባሻገር የዘመነ መሳፍንትን ፍፃሜ የሚያሳይ ታሪካዊ መጽሐፍ ይጠቀሳሉ።
እኝህ ታላቅ ምሁር ስኮላር፣ ዶክተር፣ የሚሊተሪ ኦፊሰር እና ደራሲ ብቻ ሳይሆኑ፣ በሚላኖ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ "ትንሹ ልዑል" የተሰኘውን የሕጻናት መጽሐፍ በ55 ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተሙ ተርጓሚና ድንቅ የቅብ ሥራዎችን ያበረከቱ ሰዓሊም ነበሩ።
ምንም እንኳን ሞት በድንገት ከሚወዷቸው ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ቢለያቸውም፣ ያኖሩት ታላቅ አሻራ ግን ከመቃብር በላይ ሁሌም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ባለቤታቸውና ልጃቸው የፕሮፌሰሩን ውርስና ሌጋሲ ለማስቀጠል፣ እሳቸው ሳይታተሙ የተዉትንና ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ በአምስት መቶ አምስት መቶ ገጾች የተቀነበቡ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍትን ለሕትመት ለማብቃት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያን የመወደዳቸው ምዕራፍ የተገለጠው፤ የተጀመረው በባለቤታቸውና በልጃቸው እንደሆነ ይናገሩ ነበር። በዚህ መሠረት ቤተሰቦቻቸው በኢትዮጵያ ምድር በስማቸው ሙዚየም ለመክፈት አልያም በእርሳቸው የተሰሩ ሥራዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ለማበርከት ሰፊ እንቅስቃሴ ላይ ናቸው።
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲን ሕይወትና ሥራዎች ፤ ለአገርና ለሕዝብ ያበረከቱትን አስተዋጸኦ በክብር የሚዘክር ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይጠበቃል።
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Ethiopia’s Great Friend:
In Memory of Professor Colonel Enrico Piero Bossi
Italian scholar and human rights advocate
His wife, Mrs. Sara Yemane, and their son, Caleb Giorgi, are working to preserve and continue his legacy.
#ethiopia | The renowned Italian scholar, Professor Colonel Enrico Piero Bossi (M.D.), who dedicated many years of his life in Africa and Ethiopia through his medical profession, authorship, and humanitarian activities, helping vulnerable and disadvantaged communities, passed away at the age of 81 on June 17, 2024.
During his distinguished 45-year professional career, Professor Bossi volunteered medical services across 42 African countries. He was a specialist in Orthopedics (bone and musculoskeletal medicine) and Dermatology (skin medicine).
He made a significant contribution to securing major funding for the construction of a large hospital in Sudan built by Italian organizations.
In Ethiopia, where he served for nearly twenty years, he played a key role in establishing Adama General Hospital and served as its first director.
Additionally, he worked as an orthopedic specialist at Danu Hospital and in the Emergency Department of Abet Hospital. Every year, he traveled from Italy to Woliso Hospital, where he provided extensive surgical services free of charge.
Professor Enrico was a true symbol of humanity, treating all people equally regardless of race, language, skin color, or religion. During the Kosovo War in Europe, he gave up an entire year’s salary to provide free medical services in the war zone. Likewise, during the Ethio-Eritrean War, he was among the first five Italian medical professionals who flew by helicopter to the conflict area to provide humanitarian assistance.
In Milan, Italy, he founded the medical center known as “NAGA,” where he provided free healthcare services to African immigrants and migrants from other countries, particularly those lacking legal documentation or financial means.
While many people refer to their homeland as their “fatherland” or “motherland,” Professor Bossi’s love for Ethiopia was so profound that he proudly referred to it as “the country of my son, Caleb.”
A dedicated researcher of Ethiopian history, culture, and military history, Professor Bossi authored and published more than 46 books in English and Italian.
Among his notable works are:
The History of Imperial Ethiopian Army
Destas Yirs and Life 1892–1937
Aethiopia la Moneta Africana
His work helped introduce Ethiopia’s role as the birthplace of coffee to the wider world. He also authored historical works documenting the end of the Era of the Princes (Zemene Mesafint).
Professor Bossi was not only a scholar, physician, military officer, and author, but also a translator and artist. At the Catholic University of Milan, he translated and published The Little Prince in 55 international languages and contributed remarkable artistic and illustrative works.
Although death unexpectedly separated him from his beloved wife, Mrs. Sara Yemane, and his son, Caleb Giorgi, the remarkable legacy he left behind will remain alive far beyond his grave.
To preserve Professor Bossi’s legacy, his wife and son are working to complete and publish two previously unpublished manuscripts. These extensive works, each consisting of approximately 500 pages, focus on Ethiopian subjects and were left unfinished by the professor.
The professor used to say that the chapter of his love for Ethiopia was revealed—and indeed began—with his wife and his child. Based on this, his family is actively working either to open a museum in Ethiopia bearing his name or to donate his works, along with various personal artifacts and items, to the Ethiopian National Museum.
It is hoped that the Ethiopian Heritage Authority will undertake initiatives to honor and commemorate Professor Colonel Enrico Piero Bossi’s life, work, and invaluable contributions to the nation and its people.
May his memory and contributions continue to inspire future generations.
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi
Comments