4 months ago
ሦስት የቤተክርስቲያን የዕውቀት መዛግብት በአንድ ላይ ተመረቁ
#ethiopia |የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዕውቀት ምሶሶ የሆኑት፣ የ98 ዓመቱ ዕድሜ ባለጸጋ ርእሰ ሊቃውንት ክንፈርግብ ማርቆስ እና መጋቢ ምስጢር አማኑኤል መንግሥተአብ ያዘጋጇቸው ሦስት አዳዲስ መጽሐፍት ዛሬ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አዳራሽ በድምቀት ተመርቀዋል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ፣ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ፣ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ፕሬዝዳንት ደራሲ አበረ አዳሙ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በዕለቱ ለንባብ የበቁት መጽሐፍት በሁለቱ ሊቃውንት የተዘጋጁ ሲሆኑ፣ ይዘታቸውም የሚከተለው ነው፦
✅ ሦስቱ ሐዲሳት (በርእሰ ሊቃውንት ክንፈርግብ ማርቆስ): የቤተክርስቲያንን ጥልቅ ትርጓሜ ለትውልድ የሚያስተላልፍ።
✅ ሃይማኖተ አበው (በርእሰ ሊቃውንት ክንፈርግብ ማርቆስ): የሊቃውንቱን የዘመናት ዕውቀት የሰነቀ መሠረታዊ መጽሐፍ።
✅ የጸሎት መጽሐፍ Prayer Book - The Oriental Orthodox Church (በመጋቢ ምስጢር አማኑኤል መንግሥተአብ): በዓለም አቀፍ ቋንቋ የተዘጋጀ የጸሎት መጽሐፍ።
🔹ርእሰ ሊቃውንት ክንፈርግብ ማርቆስ ከ50 በላይ መጽሐፍትን ለንባብ ያበቁ አንጋፋ ሊቅ ናቸው። በመጀመሪያው የኢትዮጵያ ልማት በሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጅነታቸው የሚታወቁት ሊቁ፤ በቅዳሴ፣ በቅኔና በሐዲሳት መጽሐፍት ትርጓሜ ያላቸውን ጥልቅ ዕውቀት ለትውልድ ለማሻገር በ98 ዓመት ዕድሜያቸውም በትጋት ላይ ይገኛሉ።
🔹መጋቢ ምስጢር አማኑኤል መንግሥተአብ የቅኔና የሐዲሳት መምህር ሲሆኑ፣ እስካሁን 13 መጽሐፍትን ለቤተክርስቲያንና ለሀገር አበርክተዋል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ መጽሐፍቱን የተመለከተ ሒሳዊ ዳሰሳ የቀረበ ሲሆን፤ በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የተክሌ ዝማሜ፣ የበገና መዝሙራት እና በልዩ የቅኔ ድግስ ታጅቦ በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።
#ethiopia #eotc (Ethiopian Orthodox Tewahedo Church) #booklaunch #ethiopianliterature #churchfathers #gheezliterature #religiousbooks
#ethiopia |የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዕውቀት ምሶሶ የሆኑት፣ የ98 ዓመቱ ዕድሜ ባለጸጋ ርእሰ ሊቃውንት ክንፈርግብ ማርቆስ እና መጋቢ ምስጢር አማኑኤል መንግሥተአብ ያዘጋጇቸው ሦስት አዳዲስ መጽሐፍት ዛሬ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አዳራሽ በድምቀት ተመርቀዋል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ፣ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ፣ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ፕሬዝዳንት ደራሲ አበረ አዳሙ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በዕለቱ ለንባብ የበቁት መጽሐፍት በሁለቱ ሊቃውንት የተዘጋጁ ሲሆኑ፣ ይዘታቸውም የሚከተለው ነው፦
✅ ሦስቱ ሐዲሳት (በርእሰ ሊቃውንት ክንፈርግብ ማርቆስ): የቤተክርስቲያንን ጥልቅ ትርጓሜ ለትውልድ የሚያስተላልፍ።
✅ ሃይማኖተ አበው (በርእሰ ሊቃውንት ክንፈርግብ ማርቆስ): የሊቃውንቱን የዘመናት ዕውቀት የሰነቀ መሠረታዊ መጽሐፍ።
✅ የጸሎት መጽሐፍ Prayer Book - The Oriental Orthodox Church (በመጋቢ ምስጢር አማኑኤል መንግሥተአብ): በዓለም አቀፍ ቋንቋ የተዘጋጀ የጸሎት መጽሐፍ።
🔹ርእሰ ሊቃውንት ክንፈርግብ ማርቆስ ከ50 በላይ መጽሐፍትን ለንባብ ያበቁ አንጋፋ ሊቅ ናቸው። በመጀመሪያው የኢትዮጵያ ልማት በሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጅነታቸው የሚታወቁት ሊቁ፤ በቅዳሴ፣ በቅኔና በሐዲሳት መጽሐፍት ትርጓሜ ያላቸውን ጥልቅ ዕውቀት ለትውልድ ለማሻገር በ98 ዓመት ዕድሜያቸውም በትጋት ላይ ይገኛሉ።
🔹መጋቢ ምስጢር አማኑኤል መንግሥተአብ የቅኔና የሐዲሳት መምህር ሲሆኑ፣ እስካሁን 13 መጽሐፍትን ለቤተክርስቲያንና ለሀገር አበርክተዋል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ መጽሐፍቱን የተመለከተ ሒሳዊ ዳሰሳ የቀረበ ሲሆን፤ በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የተክሌ ዝማሜ፣ የበገና መዝሙራት እና በልዩ የቅኔ ድግስ ታጅቦ በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።
#ethiopia #eotc (Ethiopian Orthodox Tewahedo Church) #booklaunch #ethiopianliterature #churchfathers #gheezliterature #religiousbooks
4 months ago
የኦሬንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት የጸሎት ሥርዓት ላይ የሚያተኩር መጽሐፍ ተመረቀ
#fastmereja I ታዋቂው ጸሐፊ መጋቤ ምሥጢር አማኑኤል መንግሥተአብ ያዘጋጁትና "Prayer Book the Oriental Orthodox Churches" በሚል ርዕስ ለንባብ የበቃው አዲስ መጽሐፍ ዛሬ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አዳራሽ በታላቅ ሥነ-ሥርዓት ተመረቀ።
ዛሬ በተከናወነው በዚህ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች፣ ከፍተኛ ምሁራንና የጥበብ ሰዎች ተገኝተዋል። መጽሐፉ በዋናነት የእህት አብያተ ክርስቲያናት የሆኑትን የኢትዮጵያ፣ የግብፅ፣ የሶሪያ፣ የአርመን እና የኤርትራ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት የጸሎት ሥርዓት ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን፣ በግዕዝ እና በእንግሊዘኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።
ደራሲው መጋቤ ምሥጢር አማኑኤል መንግሥተአብ ከዚህ ቀደም 13 መጻሕፍትን ለንባብ ያበቁ ሲሆን፣ ይህ አዲስ መጽሐፋቸው በዓይነቱ ለየት ያለና ለዓለም አቀፍ ምዕመናንም ጭምር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። መጽሐፉን በአማዞን ድረ-ገጽ እንዲሁም በአዲስ አበባ በሚገኙ የመጽሐፍት መሸጫ መደብሮች ማግኘት እንደሚቻል በምረቃው ወቅት ተመልክቷል።
በዚሁ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ በተጨማሪም የ98 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ እና እስካሁን ከ50 በላይ መጻሕፍትን ለንባብ ያበቁት አንጋፋው ደራሲ ርእሰ ሊቃውንት ክንፈርግብ ማርቆስ ተገኝተው "ሰለስቱ ሐዲሳት" እና "ሃይማኖተ አበው" የተሰኙ ሁለት ስራዎቻቸውን በጋራ አስመርቀዋል።
የመጽሐፉ ምረቃ በሊቃነ ጳጳሳት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የተከፈተ ሲሆን፣ በተጨማሪም በምሁራን የቀረበ ጥናታዊ ጽሑፍ፣ በበገና፣ በዝማሜና በቅኔ የታጀቡ መንፈሳዊ መርሐ-ግብሮች ታጅበዋል።
ይህ አዲስ የጸሎት መጽሐፍ የአምስቱን አብያተ ክርስቲያናት መንፈሳዊና ታሪካዊ አንድነት ከመዘከር ባለፈ፣ ለጸሎት ሥርዓታቸው ዓለም አቀፋዊ እውቅናን ለመስጠትና ለትውልድ ለማስተላለፍ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።
#fastmereja I ታዋቂው ጸሐፊ መጋቤ ምሥጢር አማኑኤል መንግሥተአብ ያዘጋጁትና "Prayer Book the Oriental Orthodox Churches" በሚል ርዕስ ለንባብ የበቃው አዲስ መጽሐፍ ዛሬ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አዳራሽ በታላቅ ሥነ-ሥርዓት ተመረቀ።
ዛሬ በተከናወነው በዚህ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች፣ ከፍተኛ ምሁራንና የጥበብ ሰዎች ተገኝተዋል። መጽሐፉ በዋናነት የእህት አብያተ ክርስቲያናት የሆኑትን የኢትዮጵያ፣ የግብፅ፣ የሶሪያ፣ የአርመን እና የኤርትራ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት የጸሎት ሥርዓት ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን፣ በግዕዝ እና በእንግሊዘኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።
ደራሲው መጋቤ ምሥጢር አማኑኤል መንግሥተአብ ከዚህ ቀደም 13 መጻሕፍትን ለንባብ ያበቁ ሲሆን፣ ይህ አዲስ መጽሐፋቸው በዓይነቱ ለየት ያለና ለዓለም አቀፍ ምዕመናንም ጭምር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። መጽሐፉን በአማዞን ድረ-ገጽ እንዲሁም በአዲስ አበባ በሚገኙ የመጽሐፍት መሸጫ መደብሮች ማግኘት እንደሚቻል በምረቃው ወቅት ተመልክቷል።
በዚሁ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ በተጨማሪም የ98 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ እና እስካሁን ከ50 በላይ መጻሕፍትን ለንባብ ያበቁት አንጋፋው ደራሲ ርእሰ ሊቃውንት ክንፈርግብ ማርቆስ ተገኝተው "ሰለስቱ ሐዲሳት" እና "ሃይማኖተ አበው" የተሰኙ ሁለት ስራዎቻቸውን በጋራ አስመርቀዋል።
የመጽሐፉ ምረቃ በሊቃነ ጳጳሳት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የተከፈተ ሲሆን፣ በተጨማሪም በምሁራን የቀረበ ጥናታዊ ጽሑፍ፣ በበገና፣ በዝማሜና በቅኔ የታጀቡ መንፈሳዊ መርሐ-ግብሮች ታጅበዋል።
ይህ አዲስ የጸሎት መጽሐፍ የአምስቱን አብያተ ክርስቲያናት መንፈሳዊና ታሪካዊ አንድነት ከመዘከር ባለፈ፣ ለጸሎት ሥርዓታቸው ዓለም አቀፋዊ እውቅናን ለመስጠትና ለትውልድ ለማስተላለፍ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።
4 months ago
Funeral Program
(የቀብር ፕሮግራም)
Terry will be received on Sunday (እሁድ), ጥር 17 2018 ዓ.ም. / January 26, 2026 at 9:00 p.m. (3:00 ምሽት በአማርኛ ሰዓት) from the Cargo Aviation terminal and taken to her residence.
The Fetat prayer service will be conducted throughout the night. On the following day, Monday (ሰኞ), ጥር 18 2018 ዓ.ም. / January 27, 2026, she will be taken to Salete Mihret Church at 11:00 a.m. (5:00 ጠዋት በአማርኛ ሰዓት).
The Ye-Fithat Zena (funeral service) will begin at 12:00 noon (6:00 ጠዋት በአማርኛ ሰዓት), followed by the procession to the burial place
After the completion of the burial service,family, relatives, and friends will gather at Bet Mariam Hall at Salete Mihret Church to remember and honor her life.
Food and drinks prepared by family and friends will be served
“The Lord is our shepherd; in His care she shall rest in eternal peace. He leads her beside still waters and restores her soul.”
— Psalm 23:1–
(የቀብር ፕሮግራም)
Terry will be received on Sunday (እሁድ), ጥር 17 2018 ዓ.ም. / January 26, 2026 at 9:00 p.m. (3:00 ምሽት በአማርኛ ሰዓት) from the Cargo Aviation terminal and taken to her residence.
The Fetat prayer service will be conducted throughout the night. On the following day, Monday (ሰኞ), ጥር 18 2018 ዓ.ም. / January 27, 2026, she will be taken to Salete Mihret Church at 11:00 a.m. (5:00 ጠዋት በአማርኛ ሰዓት).
The Ye-Fithat Zena (funeral service) will begin at 12:00 noon (6:00 ጠዋት በአማርኛ ሰዓት), followed by the procession to the burial place
After the completion of the burial service,family, relatives, and friends will gather at Bet Mariam Hall at Salete Mihret Church to remember and honor her life.
Food and drinks prepared by family and friends will be served
“The Lord is our shepherd; in His care she shall rest in eternal peace. He leads her beside still waters and restores her soul.”
— Psalm 23:1–
4 months ago
🕯️ "የሞተ ሠውሰ አረፈ፤ ነገር ግን መታሠቢያውን አድርግለት" (ሲራክ 38፥23)
የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ መታሰቢያ በልጅነት ሰፈሩ በቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን
በቅርቡ በሞት የተለየን የጥበብ ሰው ወንድማችን አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ተወልዶ ባደገበት በደብረ ፅጌ ቅዱሥ ዑራኤል ቤተክርስቲያን፤ የአካባቢው ወጣቶች በተባበረ ክንድ የሻማ ማብራት እና የፀሎት መረሃ ግብር አዘጋጅተዋል።
በዚህ ታላቅ መንፈሳዊ መርሐ-ግብር ላይ ብፁሃን አባቶች፣ ሰባክያንን፣ ዘማሪያን፣ የጥበብ ሙያ አጋሮቹ እና ቤተሰቦቹ ይገኛሉ።
እናንተም የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ አድናቂዎች፣ የኪነ-ጥበብ ቤተሰቦች እና ወዳጆች በዚህ የመታሰቢያ ፕሮግራም ላይ በመገኘት አብራችሁን እንድትሆኑ የዑራኤል አካባቢ ወጣቶች ጥሪያቸውን ያቀርባሉ።
📅 ቀን: አርብ ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ ሰዓት: ከቀኑ 10:00 ጀምሮ
📍 ቦታ: ደብረ ፅጌ ቅዱሥ ዑራኤል ቤተክርስቲያን
ነፍስ ይማር!
#netsanetworkneh #memorial #uraelchurch #candlelight #prayer #ethiopianartist #rip
የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ መታሰቢያ በልጅነት ሰፈሩ በቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን
በቅርቡ በሞት የተለየን የጥበብ ሰው ወንድማችን አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ተወልዶ ባደገበት በደብረ ፅጌ ቅዱሥ ዑራኤል ቤተክርስቲያን፤ የአካባቢው ወጣቶች በተባበረ ክንድ የሻማ ማብራት እና የፀሎት መረሃ ግብር አዘጋጅተዋል።
በዚህ ታላቅ መንፈሳዊ መርሐ-ግብር ላይ ብፁሃን አባቶች፣ ሰባክያንን፣ ዘማሪያን፣ የጥበብ ሙያ አጋሮቹ እና ቤተሰቦቹ ይገኛሉ።
እናንተም የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ አድናቂዎች፣ የኪነ-ጥበብ ቤተሰቦች እና ወዳጆች በዚህ የመታሰቢያ ፕሮግራም ላይ በመገኘት አብራችሁን እንድትሆኑ የዑራኤል አካባቢ ወጣቶች ጥሪያቸውን ያቀርባሉ።
📅 ቀን: አርብ ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ ሰዓት: ከቀኑ 10:00 ጀምሮ
📍 ቦታ: ደብረ ፅጌ ቅዱሥ ዑራኤል ቤተክርስቲያን
ነፍስ ይማር!
#netsanetworkneh #memorial #uraelchurch #candlelight #prayer #ethiopianartist #rip
Sponsored by
Surafel
9 months ago
ዶ/ር አብተው ለጂቦ ድልበቶ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ
#ethiopia | ዶክተር አብተው ለጂቦ ድልበቶ ወላይታ ሶዶ ዩንቨርሲቲ ሲመሰረት ከነበሩ ከመጀመሪያዎቹ አንጋፋ ምሁራን መካከል አንዱ ናቸው። ዶ/ር አብተው በዩኒቨርሲቲው ከ1999 ዓ.ም እስከ 2002 ዓ.ም የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆንም በቅንነት እና ታማኝነት አገልግለዋል።
በተቋሙ በነበራቸው ቆይታ በግብርና ኮሌጅ ሆርቲካልቸር ት/ት ክፍል በመማር ማስተማር እና በችግር ፈቺ ሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር መስክ በተለይ በእንሰት ተክል ባካሄዱት ጥልቅ ምርምር እንደ ሀገር የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ሲካሄድ በነበረ ጥረት ጉልህ አሻራ አሳርፈዋል። በሙያቸው የማስተርስና ዶክትሬት ዲግሪ ተማሪዎችን በማማከር እና አቅጣጫ በማሳየትም ከፍተኛ እገዛ አድርገዋል።
ዶ/ር አብተው በሙያቸው መስክ በዋና እንዲሁም ተባባሪ ተመራማሪነት ከ40 የሚበልጡ ሳይንሳዊ የጥናትና ምርምር ስራዎች በዓለም አቀፍ ጆርናል ላይ በማሳተም ለአካዳሚው ዓለም የጥናትና ምርምር እድገት የማይተካ ሚና ነበራቸው።
ዶክተር አብተው በሀገረ ስዊድን ኡፕሳላ ከተማ በሚገኘው ❝የስዊድን ግብርና ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ❞ በመምህርነት እና ተመራማሪነት ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን፤በሚኖሩበት ስውዲን ሀገር ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተሰምቷል።
ዶ/ር አብተው በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ መስራች በመሆን በተቋም ደረጃ በምክትል ኘሬዝዳንትነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ታሪካዊ አሻራቸውን ከማሳረፋቸውም ባሻገር
በቀድሞ የደቡብ/ብ/ብ/ህ/ክ መንግስት በአመራርነት እንዳገለገሉ የግለ ታሪክ ማህደራቸው ያመላክታል።
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር በቀድሞ የዩኒቨርሲቲው ባልደረባ እና አንጋፋ ምሁር በሆኑት ዶ/ር አብተው ለጅቦ ድልበቶ ህልፈት የተሰማውን ልባዊ ሀዘን በመግለጽ ለመላ ቤተሰባቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለአካዳሚው ማህበረሰብ መጽናናትን ይመኛል!!
ነፍስ ይማር
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር!!
Condolence Message for Abitew Lagibo Dalbato (Dr.)
We are deeply saddened by the passing of Dr. Abitew Lagibo Dalbato, a brilliant researcher, dedicated educator, and compassionate soul whose work touched lives far beyond the academic sphere. His pioneering research on Ensete ventricosum and sustainable agriculture has left an enduring legacy that will continue to inspire future generations.
Dr. Dalbato was not only a scholar of great intellect but also a person of humility, kindness, and unwavering commitment to improving food security and environmental resilience. His contributions to science and society will be remembered with profound respect and admiration.
Our thoughts and prayers are with his family, friends, and colleagues during this difficult time. May his memory be a blessing, and may his work continue to flourish in the hands of those he inspired.
Rest in peace, Dr. Abitew. Your work lives on. 🌿
#rip #abitewdalbato #agriculturalscience #ensetresearch #wsu #sustainableagriculture #legacyoflearning #ethiopia #slu #plantpropagation
***
በመማሩ ማይታበየው ትሁቱና ቀናው ሰው !
በሽግግር መንግስቱ ሁሉም አከባቢውን እንዲያለማ ጥሪ ይተላለፋል።ዶ/ር አብተው ለጂቦ ደሞ በጊዜው ልእለ ሀያል ደረጃ ባለችው በሀገረ ጀርመን 2ኛ ዲግሪውን ያጠናቀቀበት ጊዜ ነበር። በትምህርት ዝግጅቱ በተማረበት ሀገርም ሆነ በሀገራችን አሉ በሚባሉ የሙያም ሆነ በስልጣን ደረጃ ማገልገል የሚያስችል አቅሙ ብቻ ሳይሆን እድሉም ነበረው። ቅድሚያ ለምቾቱ ሳይሆን ለህዝቡ በመስጠት ጥሪውን ተቀብሎ የዞኑን የግብርና ዘርፍ በዱራሜ ለመምራት በሰው ሀይልም ፣በግብአትም ሆነ በበጀት ያልተደራጀ ተቋም ለማደራጀት ምቹ እድሉን ሰውቶ ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ቆራጥ ሰው ነበረ።
የቀድሞ የደ/ብ/ብ/ህ/ክ ክልሉን በአመራርነት ፤የወላይታ ዩኒቨርሲቲ መስራችና በምክትል ኘረዝደንትነት ታሪካዊ አሻራውን ያሳረፈ ፤ በሀገረ ሲውዲን ስመጥር ተመራማሪው ዶ/ር አብተው ዛሬ ከዚህ ዓለም መለየቱን ስሰማ ልቤ ተሰበረ።
ሩቅ አላሚው ለሀገሩም ለህዝቡም ብዙ ራእይ እንደነበረው ያጫወተኝ ነገር ትልቅ ሸክም ፈጥሮብኛል።የማይቀርበት ቢሄድም በማይሞተው ራእይውና ሌጋሲው ሁሌም ከትውልዱ ጋር ይኖራል።
ነፍስህን በአጸደ ገነት ያሳርፍልን!
ለቅሶ ሥነ ስርዓቱ የሚከናወነዉ በትዉልድ ስፍራዉ አሽራ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቤቄራ አከባቢ በቀን 21-12-2017 ከ 5:00 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል።
#ethiopia | ዶክተር አብተው ለጂቦ ድልበቶ ወላይታ ሶዶ ዩንቨርሲቲ ሲመሰረት ከነበሩ ከመጀመሪያዎቹ አንጋፋ ምሁራን መካከል አንዱ ናቸው። ዶ/ር አብተው በዩኒቨርሲቲው ከ1999 ዓ.ም እስከ 2002 ዓ.ም የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆንም በቅንነት እና ታማኝነት አገልግለዋል።
በተቋሙ በነበራቸው ቆይታ በግብርና ኮሌጅ ሆርቲካልቸር ት/ት ክፍል በመማር ማስተማር እና በችግር ፈቺ ሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር መስክ በተለይ በእንሰት ተክል ባካሄዱት ጥልቅ ምርምር እንደ ሀገር የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ሲካሄድ በነበረ ጥረት ጉልህ አሻራ አሳርፈዋል። በሙያቸው የማስተርስና ዶክትሬት ዲግሪ ተማሪዎችን በማማከር እና አቅጣጫ በማሳየትም ከፍተኛ እገዛ አድርገዋል።
ዶ/ር አብተው በሙያቸው መስክ በዋና እንዲሁም ተባባሪ ተመራማሪነት ከ40 የሚበልጡ ሳይንሳዊ የጥናትና ምርምር ስራዎች በዓለም አቀፍ ጆርናል ላይ በማሳተም ለአካዳሚው ዓለም የጥናትና ምርምር እድገት የማይተካ ሚና ነበራቸው።
ዶክተር አብተው በሀገረ ስዊድን ኡፕሳላ ከተማ በሚገኘው ❝የስዊድን ግብርና ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ❞ በመምህርነት እና ተመራማሪነት ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን፤በሚኖሩበት ስውዲን ሀገር ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተሰምቷል።
ዶ/ር አብተው በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ መስራች በመሆን በተቋም ደረጃ በምክትል ኘሬዝዳንትነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ታሪካዊ አሻራቸውን ከማሳረፋቸውም ባሻገር
በቀድሞ የደቡብ/ብ/ብ/ህ/ክ መንግስት በአመራርነት እንዳገለገሉ የግለ ታሪክ ማህደራቸው ያመላክታል።
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር በቀድሞ የዩኒቨርሲቲው ባልደረባ እና አንጋፋ ምሁር በሆኑት ዶ/ር አብተው ለጅቦ ድልበቶ ህልፈት የተሰማውን ልባዊ ሀዘን በመግለጽ ለመላ ቤተሰባቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለአካዳሚው ማህበረሰብ መጽናናትን ይመኛል!!
ነፍስ ይማር
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር!!
Condolence Message for Abitew Lagibo Dalbato (Dr.)
We are deeply saddened by the passing of Dr. Abitew Lagibo Dalbato, a brilliant researcher, dedicated educator, and compassionate soul whose work touched lives far beyond the academic sphere. His pioneering research on Ensete ventricosum and sustainable agriculture has left an enduring legacy that will continue to inspire future generations.
Dr. Dalbato was not only a scholar of great intellect but also a person of humility, kindness, and unwavering commitment to improving food security and environmental resilience. His contributions to science and society will be remembered with profound respect and admiration.
Our thoughts and prayers are with his family, friends, and colleagues during this difficult time. May his memory be a blessing, and may his work continue to flourish in the hands of those he inspired.
Rest in peace, Dr. Abitew. Your work lives on. 🌿
#rip #abitewdalbato #agriculturalscience #ensetresearch #wsu #sustainableagriculture #legacyoflearning #ethiopia #slu #plantpropagation
***
በመማሩ ማይታበየው ትሁቱና ቀናው ሰው !
በሽግግር መንግስቱ ሁሉም አከባቢውን እንዲያለማ ጥሪ ይተላለፋል።ዶ/ር አብተው ለጂቦ ደሞ በጊዜው ልእለ ሀያል ደረጃ ባለችው በሀገረ ጀርመን 2ኛ ዲግሪውን ያጠናቀቀበት ጊዜ ነበር። በትምህርት ዝግጅቱ በተማረበት ሀገርም ሆነ በሀገራችን አሉ በሚባሉ የሙያም ሆነ በስልጣን ደረጃ ማገልገል የሚያስችል አቅሙ ብቻ ሳይሆን እድሉም ነበረው። ቅድሚያ ለምቾቱ ሳይሆን ለህዝቡ በመስጠት ጥሪውን ተቀብሎ የዞኑን የግብርና ዘርፍ በዱራሜ ለመምራት በሰው ሀይልም ፣በግብአትም ሆነ በበጀት ያልተደራጀ ተቋም ለማደራጀት ምቹ እድሉን ሰውቶ ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ቆራጥ ሰው ነበረ።
የቀድሞ የደ/ብ/ብ/ህ/ክ ክልሉን በአመራርነት ፤የወላይታ ዩኒቨርሲቲ መስራችና በምክትል ኘረዝደንትነት ታሪካዊ አሻራውን ያሳረፈ ፤ በሀገረ ሲውዲን ስመጥር ተመራማሪው ዶ/ር አብተው ዛሬ ከዚህ ዓለም መለየቱን ስሰማ ልቤ ተሰበረ።
ሩቅ አላሚው ለሀገሩም ለህዝቡም ብዙ ራእይ እንደነበረው ያጫወተኝ ነገር ትልቅ ሸክም ፈጥሮብኛል።የማይቀርበት ቢሄድም በማይሞተው ራእይውና ሌጋሲው ሁሌም ከትውልዱ ጋር ይኖራል።
ነፍስህን በአጸደ ገነት ያሳርፍልን!
ለቅሶ ሥነ ስርዓቱ የሚከናወነዉ በትዉልድ ስፍራዉ አሽራ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቤቄራ አከባቢ በቀን 21-12-2017 ከ 5:00 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል።
10 months ago
የ28 ዓመቱ የአልጀዚራ ጋዜጠኛ አናስ ጀማል አልሸሪፍ ከትናንት በስቲያ እሁድ በጋዛ በተፈጸመ የእስራኤል የቦንብ ጥቃት ተገደለ።
የባያን ባለቤት : የሻምና የሳላህ አባት ላለፉት 22 ወራት ዓለምአቀፍ ጋዜጠኞች እንዳይገቡ በታገዱባት ጋዛ የህዝብ ድምጽ ሆኖ ብዙ ዋጋ ከፍሏል። በተደጋጋሚ ዛቻ እና የግድያ ሙከራ አስተናግዷል ። ከወራት በፊት ለእርሱ ጥቃት አባቱን አሳጥቶታል።
ወርሃ ጥር ብዙ ተስፋ የተደረገበት የተኩስ አቁም ስምምነት ሲደረስ በቀጥታ ስርጭት የአደጋ መከላከያ ሄልሜቱንና ልብሱን አውልቆ ደስታውን ገልጾ ነበር ። ስምምነቱም የአናስም ተስፋ የነበራቸው እድሜ ግን አጭር ነበር። ሁለት ወር ብቻ ።
..
እስራኤል የሃማስ ሰው ነው ብላ ትወነጅለዋለች። እሱና የሚያውቁት ብቻ ሳይሆኑ የተመድ ሰዎችም ከጋዛ ህዝብ ጋር እንጂ በፍጹም ከሃማስ ጋር ንክኪ የለውም ብለው መስክረውለታል ።
ከጋዛ ሰማይ ስር ሰላም ሰፍኖ : የሰው ልጆች ሰቆቃ አብቅቶ ወደትውልድ ቀዬው : ወደ ብላቴና ልጆቹ ወደ አስቃላን የመመለስ ተስፋ ነበረው ።
..
እንደ አላህ ፈቃድ እንጂ እርሱ ተስፋ እንዳደረገው አልሆነም። ከትናንት በስትያ 'ሚዲያ' የሚል ጽሁፍ ከተለጠፈበት የማረፊያ ድንኳኑ ደጃፍ ከሌሎች አራት ባልደረቦቹ ጋር ላይመለስ ሄደ።
ከሳምንት በፊት ስሞት አውጡልኝ ብሎ የኑዛዜ ቃሉን ጽፎ ነበር።
' ጋዛን እንዳትዘነጓት : እኔንም በጸሎታችሁ አስቡኝ' ብሏል ።
አላህ ይዘንለት
...
“I have lived through pain in all its details, tasted suffering and loss many times, yet I never once hesitated to convey the truth as it is, without distortion or falsification… If I die, I die steadfast upon my principles,” he wrote.
“Do not forget Gaza … and do not forget me in your sincere prayers for forgiveness and acceptance.”
..
May Allah forgive him !
የባያን ባለቤት : የሻምና የሳላህ አባት ላለፉት 22 ወራት ዓለምአቀፍ ጋዜጠኞች እንዳይገቡ በታገዱባት ጋዛ የህዝብ ድምጽ ሆኖ ብዙ ዋጋ ከፍሏል። በተደጋጋሚ ዛቻ እና የግድያ ሙከራ አስተናግዷል ። ከወራት በፊት ለእርሱ ጥቃት አባቱን አሳጥቶታል።
ወርሃ ጥር ብዙ ተስፋ የተደረገበት የተኩስ አቁም ስምምነት ሲደረስ በቀጥታ ስርጭት የአደጋ መከላከያ ሄልሜቱንና ልብሱን አውልቆ ደስታውን ገልጾ ነበር ። ስምምነቱም የአናስም ተስፋ የነበራቸው እድሜ ግን አጭር ነበር። ሁለት ወር ብቻ ።
..
እስራኤል የሃማስ ሰው ነው ብላ ትወነጅለዋለች። እሱና የሚያውቁት ብቻ ሳይሆኑ የተመድ ሰዎችም ከጋዛ ህዝብ ጋር እንጂ በፍጹም ከሃማስ ጋር ንክኪ የለውም ብለው መስክረውለታል ።
ከጋዛ ሰማይ ስር ሰላም ሰፍኖ : የሰው ልጆች ሰቆቃ አብቅቶ ወደትውልድ ቀዬው : ወደ ብላቴና ልጆቹ ወደ አስቃላን የመመለስ ተስፋ ነበረው ።
..
እንደ አላህ ፈቃድ እንጂ እርሱ ተስፋ እንዳደረገው አልሆነም። ከትናንት በስትያ 'ሚዲያ' የሚል ጽሁፍ ከተለጠፈበት የማረፊያ ድንኳኑ ደጃፍ ከሌሎች አራት ባልደረቦቹ ጋር ላይመለስ ሄደ።
ከሳምንት በፊት ስሞት አውጡልኝ ብሎ የኑዛዜ ቃሉን ጽፎ ነበር።
' ጋዛን እንዳትዘነጓት : እኔንም በጸሎታችሁ አስቡኝ' ብሏል ።
አላህ ይዘንለት
...
“I have lived through pain in all its details, tasted suffering and loss many times, yet I never once hesitated to convey the truth as it is, without distortion or falsification… If I die, I die steadfast upon my principles,” he wrote.
“Do not forget Gaza … and do not forget me in your sincere prayers for forgiveness and acceptance.”
..
May Allah forgive him !