15 hours ago
የዘመናችን ሉዓላዊነት፡ ከድንበር ጥበቃ እስከ ኢኮኖሚያዊና ዲጂታል ልዕልና
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
18 hours ago
ከዛፎች ጥላ ስር
ትናንት የተከልናቸው ችግኞች አድገው ጥላ ሆነውን፣ ከስሮቻቸው ተሰብስበን ጉዳዮቻችንን ተወያይተንባቸዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ፍሬ አፍርቶ፣ የህይወት እስትንፋስ የሆነውን ተፈጥሮን ዳግም አስነስቶልናል።
በእነዚህ የዛፍ ጥላዎች ስር ሆነን፣ ከባቢ አየራችን እንዴት እንደተቀየረ መመስከር ጀምረናል። የተራቆቱ ተራሮቻችን አረንጓዴ ለብሰው የአፈር መሸርሸር ቆሟል፤ የጠፉ ምንጮቻችን ፈልቀው የተፈጥሮ የውሃ ዑደታችንን በሚገርም ሁኔታ መልሰነዋል።
ውይይታችን ወደ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋቶቻችን ሄዶ፣ የተከልናቸው የፍራፍሬ እና የጥምር ደን ግብርና ችግኞች የምግብ ዋስትናችንን እያረጋገጡልን መሆኑን አንስተናል። ለወጣቶቻችን የስራ እድል ከመፍጠር ባለፈ፣ የቤተሰብ ገቢያችንን በከፍተኛ ደረጃ አሳድገንበታል።
ይህ አረንጓዴ ጉዞ ማህበራዊ ትስስራችንንም እጅግ አጠናክሮታል።
በክረምት ዝናብና ጭቃው ሳይበግረን አብረን የተከልነው እያንዳንዱ ችግኝ፣ የብሔራዊ አንድነታችንና የጋራ ራዕያችን ህያው ሀውልት ሆኖ ዛሬም በመካከላችን የፍቅር ጥላ ዘርግቷል።
እያደረግን ያለነው የአየር ንብረት ለውጥን የመከላከል ትግል ለዓለም ትልቅ ትምህርት ሆኗል። ከድርቅ ስጋት ተላቀን፣ ለምድራችን ጤንነት ግንባር ቀደም ጠበቆች በመሆናችን ልባዊ ኩራት ይሰማናል።
ከዛፎቹ ጥላ ስር የምንነሳው ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች እና የበለጸገች ሀገር ለማስረከብ ቃል በመግባት ነው። አረንጓዴ ዐሻራችን የህልውናችን መሰረት ሆኗል፡፡
ትናንት የተከልናቸው ችግኞች አድገው ጥላ ሆነውን፣ ከስሮቻቸው ተሰብስበን ጉዳዮቻችንን ተወያይተንባቸዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ፍሬ አፍርቶ፣ የህይወት እስትንፋስ የሆነውን ተፈጥሮን ዳግም አስነስቶልናል።
በእነዚህ የዛፍ ጥላዎች ስር ሆነን፣ ከባቢ አየራችን እንዴት እንደተቀየረ መመስከር ጀምረናል። የተራቆቱ ተራሮቻችን አረንጓዴ ለብሰው የአፈር መሸርሸር ቆሟል፤ የጠፉ ምንጮቻችን ፈልቀው የተፈጥሮ የውሃ ዑደታችንን በሚገርም ሁኔታ መልሰነዋል።
ውይይታችን ወደ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋቶቻችን ሄዶ፣ የተከልናቸው የፍራፍሬ እና የጥምር ደን ግብርና ችግኞች የምግብ ዋስትናችንን እያረጋገጡልን መሆኑን አንስተናል። ለወጣቶቻችን የስራ እድል ከመፍጠር ባለፈ፣ የቤተሰብ ገቢያችንን በከፍተኛ ደረጃ አሳድገንበታል።
ይህ አረንጓዴ ጉዞ ማህበራዊ ትስስራችንንም እጅግ አጠናክሮታል።
በክረምት ዝናብና ጭቃው ሳይበግረን አብረን የተከልነው እያንዳንዱ ችግኝ፣ የብሔራዊ አንድነታችንና የጋራ ራዕያችን ህያው ሀውልት ሆኖ ዛሬም በመካከላችን የፍቅር ጥላ ዘርግቷል።
እያደረግን ያለነው የአየር ንብረት ለውጥን የመከላከል ትግል ለዓለም ትልቅ ትምህርት ሆኗል። ከድርቅ ስጋት ተላቀን፣ ለምድራችን ጤንነት ግንባር ቀደም ጠበቆች በመሆናችን ልባዊ ኩራት ይሰማናል።
ከዛፎቹ ጥላ ስር የምንነሳው ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች እና የበለጸገች ሀገር ለማስረከብ ቃል በመግባት ነው። አረንጓዴ ዐሻራችን የህልውናችን መሰረት ሆኗል፡፡
19 hours ago
በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ዓለም አቀፍ እውቅና የተሻገረችው ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀልበስ ያለመው ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ፤ ዛሬ በአንድ ጀንበር ከ800 ሚሊየን በላይ ችግኞችን የመትከል ታሪካዊ መርሃ ግብሩን በስኬት እያከናወነ ይገኛል።
የዘንድሮውን ሀገራዊ የችግኝ ተከላ እና የደረሰበትን ምዕራፍ አስመልክቶ የብሔራዊ አረንጓዴ አሻራ ቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ አረንጓዴ አሻራ በሀገር ውስጥ ካመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ባሻገር ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል እያስገኘ ነው ብለዋል፡፡
ከስምንት ዓመታት በፊት በከፍተኛ ሁኔታ የሙቀት መጨመር፣ የደን ሽፋን መመናመን፣ የዱር እንስሳት ስደት እና የግብርና ምርታማነት መቀነስ የመሳሰሉ ችግሮች እየጨመሩ መጥተው ነበር፡፡ ይህን አሳሳቢ ሁኔታ ለመቀልበስ የተጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን መትከል መቻሉን ዶ/ር አደፍርስ ገልጸዋል።
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም ዜጋ እና ተቋማት በአንድነት በተሳተፉበት በዚህ ንቅናቄ፤ አሳሳቢ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን 23.6 መድረስ ችሏል።
ኢትዮጵያ ባከናወነችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከዚህ ቀደም በየዓመቱ እስከ 92 ሺህ ሄክታር ይደርስ የነበረው የደን ጭፍጨፋ አሁን ላይ ወደ 27 ሺህ ሄክታር ዝቅ እንዲል ማድረግ ተችሏል።
በመርሃ ግብሩም የደን፣ የፍራፍሬ፣ የእንስሳት መኖ እና ልዩ ልዩ ችግኞችን በማፍላት እና በመንከባከብ ሂደት ከ2 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል።
ይህም ለዜጎች የገቢ ምንጭ ከመሆኑም በላይ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ምርት እና ምርታማነትን ለመጨመር አስችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ የመጣው ድምር ሥነ-ምህዳራዊ ውጤት፤ እንደ ሐረማያ እና አቢጃታ-ሻላ ያሉ የደረቁ እና መጠናቸው በከፍኛ ሁኔታ የቀነሱ ሐይቆች ዳግም እንዲያንሰራሩ ጭምር ትልቅ ሚና መጫወቱን ዶክተር አደፍርስ ወርቁ አብራርተዋል።
እንደ ዶ/ር አደፍርስ ማብራሪያ፣ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ሲጀመር በተለይም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ጥርጣሬ ነበረ።
ነገር ግን ኢትዮጵያ ከእቅዷ በላይ በመትከል እና አጽድቃ በማሳየት ይህንን ትርክት መቀየር ችላለች ብለዋል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስለ አየር ንብረት ለውጥ በንድፈ ሀሳብ ከመወያየት ባለፈ፤ የኢትዮጵያን ተግባራዊ ስራዎች እና ውጤቶች በማየት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት ጀምሯል።
ይሄም ሀገሪቱ በዲፕሎማሲው መስክ ትልቅ ትሩፋት እንድታገኝ እና ስሟ በበጎ እንዲነሳ ማድረጉ አስተባባሪው ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) እንድታዘጋጅ መመረጧ የዚሁ ጥረት ውጤት መሆኑንና፤ ጉባኤውም ትክክለኛው የአፍሪካ ኮፕ እንደሚሆን ዶክተር አደፍርስ አብራርተዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ አርሶ አደሩን እና አርብቶ አደሩን ከሚያጋጥመው የድርቅ ፈተና ከመታደግ ባለፈ፣ ኢትዮጵያ የዓለምን የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳትን በመቀልበስ ረገድ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው።
በዓለምሰገድ አሳዬ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀልበስ ያለመው ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ፤ ዛሬ በአንድ ጀንበር ከ800 ሚሊየን በላይ ችግኞችን የመትከል ታሪካዊ መርሃ ግብሩን በስኬት እያከናወነ ይገኛል።
የዘንድሮውን ሀገራዊ የችግኝ ተከላ እና የደረሰበትን ምዕራፍ አስመልክቶ የብሔራዊ አረንጓዴ አሻራ ቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ አረንጓዴ አሻራ በሀገር ውስጥ ካመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ባሻገር ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል እያስገኘ ነው ብለዋል፡፡
ከስምንት ዓመታት በፊት በከፍተኛ ሁኔታ የሙቀት መጨመር፣ የደን ሽፋን መመናመን፣ የዱር እንስሳት ስደት እና የግብርና ምርታማነት መቀነስ የመሳሰሉ ችግሮች እየጨመሩ መጥተው ነበር፡፡ ይህን አሳሳቢ ሁኔታ ለመቀልበስ የተጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን መትከል መቻሉን ዶ/ር አደፍርስ ገልጸዋል።
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም ዜጋ እና ተቋማት በአንድነት በተሳተፉበት በዚህ ንቅናቄ፤ አሳሳቢ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን 23.6 መድረስ ችሏል።
ኢትዮጵያ ባከናወነችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከዚህ ቀደም በየዓመቱ እስከ 92 ሺህ ሄክታር ይደርስ የነበረው የደን ጭፍጨፋ አሁን ላይ ወደ 27 ሺህ ሄክታር ዝቅ እንዲል ማድረግ ተችሏል።
በመርሃ ግብሩም የደን፣ የፍራፍሬ፣ የእንስሳት መኖ እና ልዩ ልዩ ችግኞችን በማፍላት እና በመንከባከብ ሂደት ከ2 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል።
ይህም ለዜጎች የገቢ ምንጭ ከመሆኑም በላይ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ምርት እና ምርታማነትን ለመጨመር አስችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ የመጣው ድምር ሥነ-ምህዳራዊ ውጤት፤ እንደ ሐረማያ እና አቢጃታ-ሻላ ያሉ የደረቁ እና መጠናቸው በከፍኛ ሁኔታ የቀነሱ ሐይቆች ዳግም እንዲያንሰራሩ ጭምር ትልቅ ሚና መጫወቱን ዶክተር አደፍርስ ወርቁ አብራርተዋል።
እንደ ዶ/ር አደፍርስ ማብራሪያ፣ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ሲጀመር በተለይም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ጥርጣሬ ነበረ።
ነገር ግን ኢትዮጵያ ከእቅዷ በላይ በመትከል እና አጽድቃ በማሳየት ይህንን ትርክት መቀየር ችላለች ብለዋል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስለ አየር ንብረት ለውጥ በንድፈ ሀሳብ ከመወያየት ባለፈ፤ የኢትዮጵያን ተግባራዊ ስራዎች እና ውጤቶች በማየት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት ጀምሯል።
ይሄም ሀገሪቱ በዲፕሎማሲው መስክ ትልቅ ትሩፋት እንድታገኝ እና ስሟ በበጎ እንዲነሳ ማድረጉ አስተባባሪው ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) እንድታዘጋጅ መመረጧ የዚሁ ጥረት ውጤት መሆኑንና፤ ጉባኤውም ትክክለኛው የአፍሪካ ኮፕ እንደሚሆን ዶክተር አደፍርስ አብራርተዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ አርሶ አደሩን እና አርብቶ አደሩን ከሚያጋጥመው የድርቅ ፈተና ከመታደግ ባለፈ፣ ኢትዮጵያ የዓለምን የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳትን በመቀልበስ ረገድ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው።
በዓለምሰገድ አሳዬ
22 hours ago
"ደቦ" የጥንቱ የኢትዮጵያውያን ትብብር ለዘመናዊው የአካባቢ ጥበቃ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያውያን በዚህ ክረምት የደቦ (ጅጌ) ሥራ አለባቸው፡፡ ሀገራቸው ደግሳ ልጆቿን ለብርቱ ሥራ ጋብዛለች - ለአረንጓዴ ዐሻራ፡፡
በተለያዩ የኢትዮጵያ ማሕበረሰቦች ባህል፣ የአንድነት፣ የደግነት፣ የትብብር እና የጋራ ጥንካሬ ትልቁ መገለጫ «ደቦ» ወይም በአንዳንድ አካባቢዎች «ጅጌ» ተብሎ የሚጠራው ሥርዓት ነው።
ይህ ከትውልድ ወደ ትውልድ የተሻገረ የጋራ የሥራ ባህል፣ ግለሰቦች ብቻቸውን ሊወጡት የማይችሉትን ከባድ የግብርና፣ የቤት ግንባታ እና የማኅበራዊ ሕይወት ፈተናዎች በአንድነት ለማሸነፍ የሚያስችል ጥንታዊ መፍትሔ ነው።
ዛሬ ላይ ይህ ታላቅ ማኅበራዊ እሴት አዲስ መልክና ብሔራዊ ግብ አንግቦ በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይ በደመቀ ሁኔታ እየተተገበረ ይገኛል።
ይህን ጥንታዊ የማሕበረሰብ ዕውቀት ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል በወሳኝ ብሔራዊ ጉዳይ ላይ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
ደቦ በባህሪው ለአንድ አምራች ወይም ባለሥራ ሳምንታት ሊፈጅ የሚችልን የአዝመራ ስብሰባ ወይም የአፈር ጥበቃ ሥራ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ በማጠናቀቅ ጊዜንና ጉልበትን ለመቆጠብ ያስችላል፡፡
ኢትዮጵያም በዚህ የክረምቱ ወቅት ልትተክል ያሰበችውን 8 ቢሊየን ችግኝ እቅድ ማሳካት የሚያስችላትን ከፍ ያለ ሥራ ከውናለች፡፡
ክረምቱ ከገባበት ጊዜ እንስቶ እስካሁን ድረስ 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ ዛሬ በሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ብቻ ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ከእቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡
በሰዎች መካከል መተባበርን፣ መከባበርንና ማኅበራዊ ትስስርን የሚያጠናክረው የደቦ ሥርዓት አሁን በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይም ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ለሀገራቸው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአንድ እንዲቆሙ አድርጓል፣ አስተባብሯልም፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በየዓመቱ በተሳካ ሁኔታ እንዲቀጥል ያደረገው ዋናው ሞተርም ይህ የቆየው የደቦ (ጂጌ) ባህል ነው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ የተለያዩ የችግኝ ዝርያዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመትከል የመንግሥት መዋቅር ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የጂጌ መንፈስ እንደ ዋና መፍትሔ ሆኖ አገልግሏል።
ልክ ለአዝመራ መሰብሰብ እንደምንሰባሰበው ሁሉ፣ ዛሬም የመንግሥት ሠራተኛው፣ አርሶ አደሩ፣ ተማሪዎቸ፣ የኃይማኖት መሪዎች፣ ሴቶች ፣ወንዶች ፣ህጻናቱ ሳይቀሩ በአንድነት ብርዱ እና ክረምቱ ቅዝቃዜ ሳይበግራቸው ወደ ችግኝ መትከያ ቦታዎች በመትመም ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡
ደቦ «የወንድሜ ሥራ የኔም ሥራ ነው» የሚል እሳቤ አለው። የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄም «የሀገር ስራ የሁሉም ትውልድ ሥራ ነው፣ ሀገር የሁሉም በመሆኗ አካባቢን የመጠበቅ ኃላፊነትም የጋራ ነው» የሚል ተመሳሳይ መርህን ይከተላል።
በችግኝ ተከላው ወቅት በአባቶች እናቶችና ወጣቶች ዘንድ የሚታየው የትብብር ትዕይንት ዕድሜ ጠገቡ የሀገር ቤት የደቦ ሥርዓት በትልልቅ ብሔራዊ መድረኮች ለትውልድ ግንባታ እየዋለ ለመሆኑ ጠቋሚ ነው፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአንድ በኩል የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከልና የሀገሪቱን የደን ሽፋን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ሲያግዝ በሌላ በኩል ደግሞ በቴክኖሎጂና በዘመናዊነት ምክንያት እየጠፋ የመጣውን የትብብር ባህል አዲሱ ትውልድ በተግባር እንዲማረውና እንዲረከበው በር ከፍቷል።
ባጭሩ የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬት የኢትዮጵያውያን ጥንታዊ የደቦ ባህል ዛሬም ሕያው መሆኑን እና ለዘመናዊ ዓለም አቀፋዊ ችግሮች እንደ አካባቢ መራቆት ያሉ ፈተናዎች ሀገር በቀል መፍትሔ መሆን እንደሚችል ያሳየበት ታላቅ ማረጋገጫ ነው።
ኢትዮጵያም ባለፉት 7 ዓመታት ልጆቿን አሰባስባ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ተክላለች፡፡ በዛሬው ዕለት ደግሞ በአንድ ጀምበር ልጆቿን ደቦ ጠርታ ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን መትከል ችላለች፡፡
በእመቤት ሲሳይ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያውያን በዚህ ክረምት የደቦ (ጅጌ) ሥራ አለባቸው፡፡ ሀገራቸው ደግሳ ልጆቿን ለብርቱ ሥራ ጋብዛለች - ለአረንጓዴ ዐሻራ፡፡
በተለያዩ የኢትዮጵያ ማሕበረሰቦች ባህል፣ የአንድነት፣ የደግነት፣ የትብብር እና የጋራ ጥንካሬ ትልቁ መገለጫ «ደቦ» ወይም በአንዳንድ አካባቢዎች «ጅጌ» ተብሎ የሚጠራው ሥርዓት ነው።
ይህ ከትውልድ ወደ ትውልድ የተሻገረ የጋራ የሥራ ባህል፣ ግለሰቦች ብቻቸውን ሊወጡት የማይችሉትን ከባድ የግብርና፣ የቤት ግንባታ እና የማኅበራዊ ሕይወት ፈተናዎች በአንድነት ለማሸነፍ የሚያስችል ጥንታዊ መፍትሔ ነው።
ዛሬ ላይ ይህ ታላቅ ማኅበራዊ እሴት አዲስ መልክና ብሔራዊ ግብ አንግቦ በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይ በደመቀ ሁኔታ እየተተገበረ ይገኛል።
ይህን ጥንታዊ የማሕበረሰብ ዕውቀት ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል በወሳኝ ብሔራዊ ጉዳይ ላይ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
ደቦ በባህሪው ለአንድ አምራች ወይም ባለሥራ ሳምንታት ሊፈጅ የሚችልን የአዝመራ ስብሰባ ወይም የአፈር ጥበቃ ሥራ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ በማጠናቀቅ ጊዜንና ጉልበትን ለመቆጠብ ያስችላል፡፡
ኢትዮጵያም በዚህ የክረምቱ ወቅት ልትተክል ያሰበችውን 8 ቢሊየን ችግኝ እቅድ ማሳካት የሚያስችላትን ከፍ ያለ ሥራ ከውናለች፡፡
ክረምቱ ከገባበት ጊዜ እንስቶ እስካሁን ድረስ 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ ዛሬ በሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ብቻ ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ከእቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡
በሰዎች መካከል መተባበርን፣ መከባበርንና ማኅበራዊ ትስስርን የሚያጠናክረው የደቦ ሥርዓት አሁን በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይም ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ለሀገራቸው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአንድ እንዲቆሙ አድርጓል፣ አስተባብሯልም፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በየዓመቱ በተሳካ ሁኔታ እንዲቀጥል ያደረገው ዋናው ሞተርም ይህ የቆየው የደቦ (ጂጌ) ባህል ነው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ የተለያዩ የችግኝ ዝርያዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመትከል የመንግሥት መዋቅር ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የጂጌ መንፈስ እንደ ዋና መፍትሔ ሆኖ አገልግሏል።
ልክ ለአዝመራ መሰብሰብ እንደምንሰባሰበው ሁሉ፣ ዛሬም የመንግሥት ሠራተኛው፣ አርሶ አደሩ፣ ተማሪዎቸ፣ የኃይማኖት መሪዎች፣ ሴቶች ፣ወንዶች ፣ህጻናቱ ሳይቀሩ በአንድነት ብርዱ እና ክረምቱ ቅዝቃዜ ሳይበግራቸው ወደ ችግኝ መትከያ ቦታዎች በመትመም ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡
ደቦ «የወንድሜ ሥራ የኔም ሥራ ነው» የሚል እሳቤ አለው። የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄም «የሀገር ስራ የሁሉም ትውልድ ሥራ ነው፣ ሀገር የሁሉም በመሆኗ አካባቢን የመጠበቅ ኃላፊነትም የጋራ ነው» የሚል ተመሳሳይ መርህን ይከተላል።
በችግኝ ተከላው ወቅት በአባቶች እናቶችና ወጣቶች ዘንድ የሚታየው የትብብር ትዕይንት ዕድሜ ጠገቡ የሀገር ቤት የደቦ ሥርዓት በትልልቅ ብሔራዊ መድረኮች ለትውልድ ግንባታ እየዋለ ለመሆኑ ጠቋሚ ነው፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአንድ በኩል የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከልና የሀገሪቱን የደን ሽፋን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ሲያግዝ በሌላ በኩል ደግሞ በቴክኖሎጂና በዘመናዊነት ምክንያት እየጠፋ የመጣውን የትብብር ባህል አዲሱ ትውልድ በተግባር እንዲማረውና እንዲረከበው በር ከፍቷል።
ባጭሩ የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬት የኢትዮጵያውያን ጥንታዊ የደቦ ባህል ዛሬም ሕያው መሆኑን እና ለዘመናዊ ዓለም አቀፋዊ ችግሮች እንደ አካባቢ መራቆት ያሉ ፈተናዎች ሀገር በቀል መፍትሔ መሆን እንደሚችል ያሳየበት ታላቅ ማረጋገጫ ነው።
ኢትዮጵያም ባለፉት 7 ዓመታት ልጆቿን አሰባስባ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ተክላለች፡፡ በዛሬው ዕለት ደግሞ በአንድ ጀምበር ልጆቿን ደቦ ጠርታ ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን መትከል ችላለች፡፡
በእመቤት ሲሳይ
1 day ago
ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናዎን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 2፡00-11፡00
👉ጎጃም በረንዳ ጫፍ፣ ጳውሎስ ሆስፒታል፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ሰን ሆቴል፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ እና አካባቢው፣
👉 ዳውን ታውን ሆቴል፣ አውራሪስ ሆቴል፣ አዲሱ ስታዲየም፣ ካልዲስ ቡና፣ መድሓኒዓለም ቤ/ክ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 10፡00
👉 ጉርድ ሾላ፣ ትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻ ድርጅት፣ ግብርና ምርምር፣ ጃክሮስ አደባባይ በስተጀርባ እና አካባቢው፣
👉 ላምበረት መናኸሪያ ፣ ላመበረት፣ እስራኤል ኤምባሲ፣ አቢሲኒያ ሆቴል፣ ሱሉልታ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 4፡00 - 8፡00
👉 ከደንበሯ ሆስፒታል ፣ በግ ተራ፣ ምስራቅ አጠቃላይ፣ ሾላ ገበያ፣ የካ መንፈሻ፣ ዘፍመሽ ሞል፣ እና አካባቢው፣
👉 አትላስ ሆቴል፣ ሻላ መናፈሻ፣ ኤስኦኤስ፣ ደሳለኝ ሆተል ጀርባ፣ ደሳለኝ ሆቴል፣ ፕሬዚደንሺያል ሆቴል፣ሩዋንዳ ኦቨርፓስ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 11፡00
👉በጭሮ ሪጅን ደደር፣ ሜታ ፣ መልካ በሎ ፣ ጎሮ ጉቱ ወረዳዎች እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 11፡00
በበህርዳር ሪጅን ቀበሌ 16 ነጋድራስ በቄ ሰፈር፣ ዶንጎስ መኪና ማሰልጠኛ፣ቤዛ ብዙሃን ት/ቤት እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
ነገ ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናዎን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 2፡00-11፡00
👉ጎጃም በረንዳ ጫፍ፣ ጳውሎስ ሆስፒታል፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ሰን ሆቴል፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ እና አካባቢው፣
👉 ዳውን ታውን ሆቴል፣ አውራሪስ ሆቴል፣ አዲሱ ስታዲየም፣ ካልዲስ ቡና፣ መድሓኒዓለም ቤ/ክ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 10፡00
👉 ጉርድ ሾላ፣ ትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻ ድርጅት፣ ግብርና ምርምር፣ ጃክሮስ አደባባይ በስተጀርባ እና አካባቢው፣
👉 ላምበረት መናኸሪያ ፣ ላመበረት፣ እስራኤል ኤምባሲ፣ አቢሲኒያ ሆቴል፣ ሱሉልታ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 4፡00 - 8፡00
👉 ከደንበሯ ሆስፒታል ፣ በግ ተራ፣ ምስራቅ አጠቃላይ፣ ሾላ ገበያ፣ የካ መንፈሻ፣ ዘፍመሽ ሞል፣ እና አካባቢው፣
👉 አትላስ ሆቴል፣ ሻላ መናፈሻ፣ ኤስኦኤስ፣ ደሳለኝ ሆተል ጀርባ፣ ደሳለኝ ሆቴል፣ ፕሬዚደንሺያል ሆቴል፣ሩዋንዳ ኦቨርፓስ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 11፡00
👉በጭሮ ሪጅን ደደር፣ ሜታ ፣ መልካ በሎ ፣ ጎሮ ጉቱ ወረዳዎች እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 11፡00
በበህርዳር ሪጅን ቀበሌ 16 ነጋድራስ በቄ ሰፈር፣ ዶንጎስ መኪና ማሰልጠኛ፣ቤዛ ብዙሃን ት/ቤት እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
“ታሪክ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም-የነፍስ መገለጥ እንጂ”
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
1 day ago
በጅማ ዞን «ተስፋን እንትከል» በሚል መርህ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሄደ
#fastmereja I በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን፣ ሰቃ ወረዳ ቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም «ተስፋን እንትከል» በሚል መርህ የመላው ኢትዮጵያውያንን ጥሪ ያቀናጀ ታላቅ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል። ይህ በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው አገራዊ ግብ መሠረት የተከናወነ ሲሆን፣ የአረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ አገራዊ ጥረት አካል እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ለዝግጅቱ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በዕለቱ በተካሄደው የችግኝ ተከላ ስነ-ስርዓት ላይ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ከታደሙት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች መካከል የግብርና ሚኒስቴር ደኤታ ዶክተር ኢፋ ሙለታ፣ የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር፣ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ደኤታ ነፊሳ አልመሃዲ፣ የግሪን ዌቭ አሊያንስ መስራች አምባሳደር ሚካኤል ነጋሳ እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ መልካሙ ዴሲሳ ይገኙበታል።
በተጨማሪም የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች እና የቲክቶክ ይዘት ፈጣሪዎች በስፍራው በመገኘት አረንጓዴ አሻራቸውን በማሳረፍ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።
መርሃ ግብሩ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤን ለማጠናከር እና የወደፊት ትውልድን የወደፊት እጣ ፈንታ በተግባር ለመገንባት ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
#fastmereja I በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን፣ ሰቃ ወረዳ ቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም «ተስፋን እንትከል» በሚል መርህ የመላው ኢትዮጵያውያንን ጥሪ ያቀናጀ ታላቅ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል። ይህ በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው አገራዊ ግብ መሠረት የተከናወነ ሲሆን፣ የአረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ አገራዊ ጥረት አካል እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ለዝግጅቱ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በዕለቱ በተካሄደው የችግኝ ተከላ ስነ-ስርዓት ላይ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ከታደሙት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች መካከል የግብርና ሚኒስቴር ደኤታ ዶክተር ኢፋ ሙለታ፣ የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር፣ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ደኤታ ነፊሳ አልመሃዲ፣ የግሪን ዌቭ አሊያንስ መስራች አምባሳደር ሚካኤል ነጋሳ እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ መልካሙ ዴሲሳ ይገኙበታል።
በተጨማሪም የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች እና የቲክቶክ ይዘት ፈጣሪዎች በስፍራው በመገኘት አረንጓዴ አሻራቸውን በማሳረፍ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።
መርሃ ግብሩ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤን ለማጠናከር እና የወደፊት ትውልድን የወደፊት እጣ ፈንታ በተግባር ለመገንባት ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ለትውልድ የሚሻገር አኩሪ ታሪክ የሚጻፍበት የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት የደን ሀብቷን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን የመቋቋም ጉዞ ዛሬ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚጠቀስ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል።
ይህ በየዓመቱ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚታወቀው መርሐ ግብር የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የወደፊት ትውልድ ተስፋን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በየዓመቱ የሚካሄደው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሚሊየኖች ከዳር እስከ ዳር በዝናብና በብርድ ሳይበገሩ በመዝመት ምድርን የሚያለመልሙበት መድረክ ሆኗል።
ነገ ማለዳ በይፋ ለሚጀመረው የዘንድሮው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እንደ ሀገር አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፥ የነገው መርሐ ግብር የኢትዮጵያውያን ክንድ ተባብሮ፣ በአንድ ጀንበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል ሌላ ታሪክ የምንሰራበት ነው ብለዋል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የደን ሽፋንን በእጥፍ ከማሳደግ ባሻገር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የውሃ አካላትን ለማበልጸግና የግብርና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሚተከሉት ችግኞች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ተክሎች እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥቅም የሚሰጡ የዛፍ ዝርያዎችን ያካተቱ በመሆናቸው ለሀገራችን የኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች ሕዝቡ ባደረገው ከፍተኛ ተሳትፎ መርሐ ግብሩ ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገራዊ አንድነት መገለጫ መሆን ችሏል።
800 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀንበር የመትከል ዘመቻው ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት፣ የአየር ንብረት ተጽዕኖን ለመቋቋም፣ ለምግብ ዋስትናና ለትውልድ ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብት ግንባታ የሚያበረክተውን ድርሻ የበለጠ የሚያጎላ ነው።
እያንዳንዱ ዜጋ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት የድርሻውን እንዲወጣ የሚጠይቀው ይህ ሀገራዊ ጥሪ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በማለዳው በመውጣት የራሳቸውን ታሪካዊ ዐሻራ እንዲያኖሩ በር የከፈተ ሆኗል።
ይህ እቅድ የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጽናት፣ የህብረትና የልማት ታላቅ መገለጫ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሀብታቸው ላይ አዲስ ሕይወት የሚዘሩበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለም እና አረንጓዴ ሀገር የሚያስረክቡበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብና የመጠበቅ ባሕልን ማሳደግ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ የተተከለ ችግኝ ጸድቆ ለፍሬ እንዲበቃ ሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረትና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት የደን ሀብቷን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን የመቋቋም ጉዞ ዛሬ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚጠቀስ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል።
ይህ በየዓመቱ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚታወቀው መርሐ ግብር የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የወደፊት ትውልድ ተስፋን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በየዓመቱ የሚካሄደው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሚሊየኖች ከዳር እስከ ዳር በዝናብና በብርድ ሳይበገሩ በመዝመት ምድርን የሚያለመልሙበት መድረክ ሆኗል።
ነገ ማለዳ በይፋ ለሚጀመረው የዘንድሮው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እንደ ሀገር አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፥ የነገው መርሐ ግብር የኢትዮጵያውያን ክንድ ተባብሮ፣ በአንድ ጀንበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል ሌላ ታሪክ የምንሰራበት ነው ብለዋል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የደን ሽፋንን በእጥፍ ከማሳደግ ባሻገር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የውሃ አካላትን ለማበልጸግና የግብርና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሚተከሉት ችግኞች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ተክሎች እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥቅም የሚሰጡ የዛፍ ዝርያዎችን ያካተቱ በመሆናቸው ለሀገራችን የኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች ሕዝቡ ባደረገው ከፍተኛ ተሳትፎ መርሐ ግብሩ ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገራዊ አንድነት መገለጫ መሆን ችሏል።
800 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀንበር የመትከል ዘመቻው ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት፣ የአየር ንብረት ተጽዕኖን ለመቋቋም፣ ለምግብ ዋስትናና ለትውልድ ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብት ግንባታ የሚያበረክተውን ድርሻ የበለጠ የሚያጎላ ነው።
እያንዳንዱ ዜጋ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት የድርሻውን እንዲወጣ የሚጠይቀው ይህ ሀገራዊ ጥሪ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በማለዳው በመውጣት የራሳቸውን ታሪካዊ ዐሻራ እንዲያኖሩ በር የከፈተ ሆኗል።
ይህ እቅድ የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጽናት፣ የህብረትና የልማት ታላቅ መገለጫ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሀብታቸው ላይ አዲስ ሕይወት የሚዘሩበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለም እና አረንጓዴ ሀገር የሚያስረክቡበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብና የመጠበቅ ባሕልን ማሳደግ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ የተተከለ ችግኝ ጸድቆ ለፍሬ እንዲበቃ ሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረትና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
2 days ago
የሐረማያ ሐይቅ ማንሰራራት፦ የአረንጓዴ ዐሻራ ትሩፋት ማሳያ
********************
በተፈጥሯዊ እና በሰው ሰራሽ ምክንያት ሙሉ በሙሉ ደርቆ ወደ አቧራማ ሜዳነት ተቀይሮ የነበረው ታሪካዊው ሐረማያ ሐይቅ አሁን ላይ በዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት ወደ ቀድሞ ይዘቱ ተመልሷል።
የሐረማያ ሐይቅ በዚህ መልኩ ማገገሙ በዕቅድ እና በጋራ ጥረት የተራቆቱ ሌሎች ተፋሰሶችንም ወደነበሩበት ሁኔታ መመለስ እንደሚቻል የሚያሳይ ሕያው ማረጋገጫ ሆኗል።
ሐረማያ ሐይቅ ለሐረማያ እና ለሐረር ከተሞች፣ ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ለአካባቢው ነዋሪዎች ዋነኛ የንጹህ መጠጥ ውኃና የግብርና መሠረት የነበረ ቢሆንም፣ በከፍተኛ የደን መጨፍጨፍ እና በደለል መሞላት ምክንያት ውኃ የመያዝ አቅሙን አጥቶ ተስፋ ተቆርጦበት የነበረ ነው።
ሆኖም ባለፉት ዓመታት በሐይቁ የላይኛው ተፋሰስ አካባቢዎች በተከናወነ የችግኝ ተከላ እና የእርከን ሥራ ወደ ሐይቁ ይገባ የነበረውን ከፍተኛ ደለል ከምንጩ መግታት ተችሏል።
በሌላ በኩል በሐይቁ ዙሪያ በተሠሩ የውኃ ማሳረፊያዎች አማካኝነት የዝናብ ውኃ ወደ መሬት እንዲሰርግ በማድረግ የሐይቁን ከርሰ ምድር ውኃ ክምችት እንዲጨምር ሆኗል።
በዚህም ሐይቁ ዳግም ውኃ መያዝ በመጀመሩ ቀደም ሲል አካባቢውን ለቀው የተሰደዱ በርካታ አእዋፍ፣ የጠፉ ዓሳዎች እና ሌሎች የውኃ ሕይወቶች እየተመለሱ ይገኛሉ።
የሐረማያ ሐይቅ ተሞክሮ ነገ የሚካሄደው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ተራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሳይሆን የታመመ ተፈጥሮን አክሞ የማዳን ሀገራዊ ጥረት መሆኑን የሚያስረግጥ ነው።
ይህ ተሞክሮ እያንዳንዱ ችግኝ የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ የማቋቋም፣ የውኃ አካላትን የመታደግ እና የተጎዳ ተፈጥሮን የማከም ወሳኝ ድርሻ ይጫወታል።
ነገ በአንድ ጀምበር በጋራ የምናኖረው አረንጓዴ ዐሻራ የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ በውኃ ሀብት እና በልምላሜ ሙሉ የሚያደርግ ታሪካዊ ተግባር ነው።
በሐና ምንዳሁን
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #800milliontrees #lakeharamaya #ebc #ebcdotstream
********************
በተፈጥሯዊ እና በሰው ሰራሽ ምክንያት ሙሉ በሙሉ ደርቆ ወደ አቧራማ ሜዳነት ተቀይሮ የነበረው ታሪካዊው ሐረማያ ሐይቅ አሁን ላይ በዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት ወደ ቀድሞ ይዘቱ ተመልሷል።
የሐረማያ ሐይቅ በዚህ መልኩ ማገገሙ በዕቅድ እና በጋራ ጥረት የተራቆቱ ሌሎች ተፋሰሶችንም ወደነበሩበት ሁኔታ መመለስ እንደሚቻል የሚያሳይ ሕያው ማረጋገጫ ሆኗል።
ሐረማያ ሐይቅ ለሐረማያ እና ለሐረር ከተሞች፣ ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ለአካባቢው ነዋሪዎች ዋነኛ የንጹህ መጠጥ ውኃና የግብርና መሠረት የነበረ ቢሆንም፣ በከፍተኛ የደን መጨፍጨፍ እና በደለል መሞላት ምክንያት ውኃ የመያዝ አቅሙን አጥቶ ተስፋ ተቆርጦበት የነበረ ነው።
ሆኖም ባለፉት ዓመታት በሐይቁ የላይኛው ተፋሰስ አካባቢዎች በተከናወነ የችግኝ ተከላ እና የእርከን ሥራ ወደ ሐይቁ ይገባ የነበረውን ከፍተኛ ደለል ከምንጩ መግታት ተችሏል።
በሌላ በኩል በሐይቁ ዙሪያ በተሠሩ የውኃ ማሳረፊያዎች አማካኝነት የዝናብ ውኃ ወደ መሬት እንዲሰርግ በማድረግ የሐይቁን ከርሰ ምድር ውኃ ክምችት እንዲጨምር ሆኗል።
በዚህም ሐይቁ ዳግም ውኃ መያዝ በመጀመሩ ቀደም ሲል አካባቢውን ለቀው የተሰደዱ በርካታ አእዋፍ፣ የጠፉ ዓሳዎች እና ሌሎች የውኃ ሕይወቶች እየተመለሱ ይገኛሉ።
የሐረማያ ሐይቅ ተሞክሮ ነገ የሚካሄደው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ተራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሳይሆን የታመመ ተፈጥሮን አክሞ የማዳን ሀገራዊ ጥረት መሆኑን የሚያስረግጥ ነው።
ይህ ተሞክሮ እያንዳንዱ ችግኝ የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ የማቋቋም፣ የውኃ አካላትን የመታደግ እና የተጎዳ ተፈጥሮን የማከም ወሳኝ ድርሻ ይጫወታል።
ነገ በአንድ ጀምበር በጋራ የምናኖረው አረንጓዴ ዐሻራ የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ በውኃ ሀብት እና በልምላሜ ሙሉ የሚያደርግ ታሪካዊ ተግባር ነው።
በሐና ምንዳሁን
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #800milliontrees #lakeharamaya #ebc #ebcdotstream
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹የሱዳንና የኤርትራ አጋርነት ለአፍሪካ ቀንድና ቀይ ባህር መረጋጋት ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡›› ሲሉ በኤርትራ የሱዳን አምባሳደር ገለፁ፡፡ በኤርትራ የሱዳን አምባሳደር የሆኑት ኦሳማ አህመድ አደል ባሪ ዛሬ ባሰራጩት ዘለግ ያለ ፅሁፍ የሁለቱን አገራት ግንኙነት ጠቀሜታ አጉልተው ለማሳየት ጥረዋል፡፡ በሱዳን ሆራይዘን ጋዜጣ ላይ በሰፈረው በዚህ ፅሁፋቸው ‹‹ቀይ ባህርና የአፍሪካ ቀንድ በአሁኑ ጊዜ በፍጥነት በሚለዋወጥ ጂኦፖለቲካዊ ባህርይና በመርከቦች ጉዞ፣ በአቅርቦት ሰንሰለት፣ በነዳጅ ሀብትና በተፈጥሮ ሀብት ላይ በሚደረግ ፉክክር ወሳኝ ምእራፍ ውስጥ ይገኛሉ›› በማለት ጀምረዋል፡፡
አስከትለውም ከዚህ በመነሳት ከክልላዊ አጋርነት በተሻለ ሰፋ ያሉ የደህንነት፣ የልማትና ዘላቂ መረጋጋትን አላማው ያደረገ ስትራቴጂያዊ ጥምረት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ አምባሳደሩ ሲቀጥሉም ‹‹ከዚህ አንፃር የሱዳንና ኤርትራ ስትራቴጂያዊ አጋርነት የተረጋጋ ቀጣናዊ የሀይል ሚዛን እንዲኖር የሚያስችል ትልቅ መሰረት ነው›› ያሉ ሲሆን ሁለቱ አገራት በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ የጋራ ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሱዳን በቀይ ባህር ዳርቻዋ በኩል ሰሜን አፍሪካን ከምስራቅና ከመካከለኛው አፍሪካ ጋር የምታገናኝ ድልድይ ናት፡፡
እንዲሁም ባላት የግብርና፣ የውሀና የማእድን ሀብቶች በቀጠናው ውስጥ ትልቅ የልማት ሞተር ሆና ማገልገል ትችላለች፡፡ በሌላ በኩል ኤርትራ ደግሞ በቀይ ባህር ላይ ልዩ የሆነ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ያላት ከመሆኑም በላይ ሰፊ የባህር ዳርቻና ተስፋ ሰጪ ወደቦችን የያዘች ናት፡፡ ስለዚህም እነዚህ ጉዳዮች ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለመፍጠርና በቀጠናው ውስጥ የተረጋጋ ፖለቲካ ለመፍጠር ምሰሶ ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ›› በማለት ገልፀው ሁለቱ አገራት ዘላቂነት ያለውና ረጅም ራእይ የሰነቀ ስትራቴጂያዊ አጋርነት መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡
አስከትለውም ከዚህ በመነሳት ከክልላዊ አጋርነት በተሻለ ሰፋ ያሉ የደህንነት፣ የልማትና ዘላቂ መረጋጋትን አላማው ያደረገ ስትራቴጂያዊ ጥምረት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ አምባሳደሩ ሲቀጥሉም ‹‹ከዚህ አንፃር የሱዳንና ኤርትራ ስትራቴጂያዊ አጋርነት የተረጋጋ ቀጣናዊ የሀይል ሚዛን እንዲኖር የሚያስችል ትልቅ መሰረት ነው›› ያሉ ሲሆን ሁለቱ አገራት በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ የጋራ ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሱዳን በቀይ ባህር ዳርቻዋ በኩል ሰሜን አፍሪካን ከምስራቅና ከመካከለኛው አፍሪካ ጋር የምታገናኝ ድልድይ ናት፡፡
እንዲሁም ባላት የግብርና፣ የውሀና የማእድን ሀብቶች በቀጠናው ውስጥ ትልቅ የልማት ሞተር ሆና ማገልገል ትችላለች፡፡ በሌላ በኩል ኤርትራ ደግሞ በቀይ ባህር ላይ ልዩ የሆነ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ያላት ከመሆኑም በላይ ሰፊ የባህር ዳርቻና ተስፋ ሰጪ ወደቦችን የያዘች ናት፡፡ ስለዚህም እነዚህ ጉዳዮች ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለመፍጠርና በቀጠናው ውስጥ የተረጋጋ ፖለቲካ ለመፍጠር ምሰሶ ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ›› በማለት ገልፀው ሁለቱ አገራት ዘላቂነት ያለውና ረጅም ራእይ የሰነቀ ስትራቴጂያዊ አጋርነት መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡
2 days ago
የአረንጓዴ ዐሻራ የሰባት ዓመታት ሰባት አንኳር ስኬቶች
*************
አረንጓዴ ዐሻራ በኢትዮጵያ ምድር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ ሀገራችንን ከአፈር መሸርሸር እና ከበረሃማነት የመታደግ ሀገራዊ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የምድርን ሕይወት የሚያድስ፣ የዜጎችን ሥነ-ልቦናዊ አስተሳሰብ የሚቀርጽ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚገነባ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ሀገራዊ የሕልውና ጥረት ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂዎች ጋር ተናብቦ ባለፉት ሰባት ዓመታት ያስመዘገባቸው ሰባት ዋና ዋና ተጨባጭ ስኬቶች እንደሚከተለው ተተንትነዋል።
1. የችግኝ ብዛትን ከጽድቀት ምጣኔ ጋር ያጣመረ አዲስ ታሪካዊ ሽግግር
ባለፉት ሰባት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው ብቻ ሳይሆን፣ የተከላው ዋና ትኩረት ወደ ጥራት እና ድኅረ-ተከላ እንክብካቤ በማደጉ የችግኞች ጽድቀት ምጣኔ ከ80 በመቶ በላይ ማደግ ችሏል።
ይህም ቀደም ሲል የነበረውን "መተከል እንጂ አለመጽደቅ" የሚል የብክነት ታሪክን በመቀየር በቆላ እና በደጋ አካባቢዎች የተጎዱ መሬቶች በፍጥነት አረንጓዴ እንዲለብሱ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ሚዛን እንዲጠበቅ አድርጓል።
2. ከአካባቢ ጥበቃ ወደ የምግብ ዋስትና የተደረገ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር
አረንጓዴ ዐሻራ ከተፈጥሮ የደን ዛፎች ባሻገር እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ቡና ያሉ ፍሬያማ ተክሎችን በስፋት አካትቷል።
ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ፕሮጀክቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ እና አባወራዎችን የገበያ ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ብሎም የሀገራችን የግብርና ምርት የወጪ ንግድ የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር አድርጎታል።
ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ማሻሻል ግብ ጋር በማስተሳሰር ዘላቂነቱ የተረጋገጠ የልማት ምሰሶ እንዲሆን አስችሎታል።
3. የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ
በመላ ሀገራችን የተቋቋሙት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ለብዙ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለሴቶች አዲስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።
ችግኝ ማፍላት፣ መንከባከብ እና ለገበያ ማቅረብ በራሱ አዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጅማሮ በጠንካራ መሠረት ላይ አኑሮታል።
ችግኞች ከተተከሉ በኋላ የሚደረገው ጥበቃ እና ክብካቤም በርካታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ቋሚ የሥራ ዘርፍ መሆን ችሏል።
4. የውኃ ሀብት እና የታላላቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ዋስትና
በስፋት የተከናወነው የደን ልማት እና የአፈር ጥበቃ ሥራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች በደለል እንዳይሞሉ የመከላከል ታሪካዊ ሚና ተጫውቷል።
በተጨማሪም የከርሰ ምድር ውኃ መጠን እንዲያገግም እና የደረቁ የምንጭ ውኃዎች መልሰው እንዲፈልቁ በማድረግ አስተማማኝ የውኃ ዋስትናን እያረጋገጠ ይገኛል።
ይህ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ አቅም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን የውኃ ምንጭ ለሆነችላቸው የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ትልቅ ትሩፋት ነው።
5. አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እና የቀጣናዊ ትሥሥር ማጠናከሪያ
ኢትዮጵያ ያዘጋጀቻቸውን ችግኞች እንደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ላሉት ጎረቤት ሀገራት በማጋራት፣ የምሥራቅ አፍሪካን እና የአፍሪካ ቀንድን የቀጣና አየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት በጋራ የመከላከል መሪነት ሚናዋን በተግባር አሳይታለች።
ይህም አረንጓዴ ዐሻራን የድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲ፣ የቀጠናው ሰላም እና የጋራ ልማት መሣሪያ አድርጎታል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም የኢትዮጵያን ፈለግ በመከተል የአረንጓዴ ልማትን በሀገሮቻቸው እያስፋፉ ይገኛሉ።
ከዚህ ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ባመጣቻቸው ተጨባጭ ስኬቶች “ዘላቂ የደን ልማት አያያዝ እና አጠቃቀም” በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ከፍተኛ እውቅናን አግኝታለች።
6. የከተሞች ሥነ-ምኅዳር መታደስ እና የኮሪደር ልማት ውበት
አረንጓዴ ዐሻራ በገጠር ተራራዎች ብቻ ተወስኖ ሳይቀር ወደ ከተሞች በመግባት የዘመናዊ ፓርኮች ግንባታ፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና አሁን ላይ በስፋት እየተተገበረ ላለው የኮሪደር ልማት ዋነኛ አካል ሆኗል።
ይህም የከተሞችን የአየር ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩም በላይ፣ የሥነ-ሕይወት ስብጥርን ወደ ነበረበት በመመለስ እና ለዜጎች ምቹ የመዝናኛ እና የኑሮ አካባቢን በመፍጠር የከተሞቻችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመለወጥ ላይ ይገኛል።
7. ሕዝባዊ ንቅናቄ እና የዜግነት አገልግሎት ባህል ግንባታ
በአንድ ጀምበር በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ችግኝ የመተከል ልምዳቸው፣ የአካባቢ ጥበቃን ከዘመቻነት አውጥቶ የባህል እና የዜግነት ግዴታ አካል አድርጎታል።
ይህም የሕዝባዊ ወንድማማችነትን ያጠናከረ እና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤን በማሳደግ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር እጅግ ግዙፍ ማኅበራዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ስኬት ነው።
በአጠቃላይ አረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተፈጥሮ ሀብታችንን ከመመለስ አልፎ ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ አቅማችንን የገነባ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ አቅራቢ ሀገር ያደረገ አንጸባራቂ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #climateaction #greendiplomacy #greeneconomy
*************
አረንጓዴ ዐሻራ በኢትዮጵያ ምድር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ ሀገራችንን ከአፈር መሸርሸር እና ከበረሃማነት የመታደግ ሀገራዊ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የምድርን ሕይወት የሚያድስ፣ የዜጎችን ሥነ-ልቦናዊ አስተሳሰብ የሚቀርጽ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚገነባ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ሀገራዊ የሕልውና ጥረት ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂዎች ጋር ተናብቦ ባለፉት ሰባት ዓመታት ያስመዘገባቸው ሰባት ዋና ዋና ተጨባጭ ስኬቶች እንደሚከተለው ተተንትነዋል።
1. የችግኝ ብዛትን ከጽድቀት ምጣኔ ጋር ያጣመረ አዲስ ታሪካዊ ሽግግር
ባለፉት ሰባት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው ብቻ ሳይሆን፣ የተከላው ዋና ትኩረት ወደ ጥራት እና ድኅረ-ተከላ እንክብካቤ በማደጉ የችግኞች ጽድቀት ምጣኔ ከ80 በመቶ በላይ ማደግ ችሏል።
ይህም ቀደም ሲል የነበረውን "መተከል እንጂ አለመጽደቅ" የሚል የብክነት ታሪክን በመቀየር በቆላ እና በደጋ አካባቢዎች የተጎዱ መሬቶች በፍጥነት አረንጓዴ እንዲለብሱ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ሚዛን እንዲጠበቅ አድርጓል።
2. ከአካባቢ ጥበቃ ወደ የምግብ ዋስትና የተደረገ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር
አረንጓዴ ዐሻራ ከተፈጥሮ የደን ዛፎች ባሻገር እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ቡና ያሉ ፍሬያማ ተክሎችን በስፋት አካትቷል።
ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ፕሮጀክቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ እና አባወራዎችን የገበያ ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ብሎም የሀገራችን የግብርና ምርት የወጪ ንግድ የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር አድርጎታል።
ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ማሻሻል ግብ ጋር በማስተሳሰር ዘላቂነቱ የተረጋገጠ የልማት ምሰሶ እንዲሆን አስችሎታል።
3. የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ
በመላ ሀገራችን የተቋቋሙት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ለብዙ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለሴቶች አዲስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።
ችግኝ ማፍላት፣ መንከባከብ እና ለገበያ ማቅረብ በራሱ አዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጅማሮ በጠንካራ መሠረት ላይ አኑሮታል።
ችግኞች ከተተከሉ በኋላ የሚደረገው ጥበቃ እና ክብካቤም በርካታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ቋሚ የሥራ ዘርፍ መሆን ችሏል።
4. የውኃ ሀብት እና የታላላቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ዋስትና
በስፋት የተከናወነው የደን ልማት እና የአፈር ጥበቃ ሥራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች በደለል እንዳይሞሉ የመከላከል ታሪካዊ ሚና ተጫውቷል።
በተጨማሪም የከርሰ ምድር ውኃ መጠን እንዲያገግም እና የደረቁ የምንጭ ውኃዎች መልሰው እንዲፈልቁ በማድረግ አስተማማኝ የውኃ ዋስትናን እያረጋገጠ ይገኛል።
ይህ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ አቅም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን የውኃ ምንጭ ለሆነችላቸው የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ትልቅ ትሩፋት ነው።
5. አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እና የቀጣናዊ ትሥሥር ማጠናከሪያ
ኢትዮጵያ ያዘጋጀቻቸውን ችግኞች እንደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ላሉት ጎረቤት ሀገራት በማጋራት፣ የምሥራቅ አፍሪካን እና የአፍሪካ ቀንድን የቀጣና አየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት በጋራ የመከላከል መሪነት ሚናዋን በተግባር አሳይታለች።
ይህም አረንጓዴ ዐሻራን የድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲ፣ የቀጠናው ሰላም እና የጋራ ልማት መሣሪያ አድርጎታል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም የኢትዮጵያን ፈለግ በመከተል የአረንጓዴ ልማትን በሀገሮቻቸው እያስፋፉ ይገኛሉ።
ከዚህ ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ባመጣቻቸው ተጨባጭ ስኬቶች “ዘላቂ የደን ልማት አያያዝ እና አጠቃቀም” በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ከፍተኛ እውቅናን አግኝታለች።
6. የከተሞች ሥነ-ምኅዳር መታደስ እና የኮሪደር ልማት ውበት
አረንጓዴ ዐሻራ በገጠር ተራራዎች ብቻ ተወስኖ ሳይቀር ወደ ከተሞች በመግባት የዘመናዊ ፓርኮች ግንባታ፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና አሁን ላይ በስፋት እየተተገበረ ላለው የኮሪደር ልማት ዋነኛ አካል ሆኗል።
ይህም የከተሞችን የአየር ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩም በላይ፣ የሥነ-ሕይወት ስብጥርን ወደ ነበረበት በመመለስ እና ለዜጎች ምቹ የመዝናኛ እና የኑሮ አካባቢን በመፍጠር የከተሞቻችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመለወጥ ላይ ይገኛል።
7. ሕዝባዊ ንቅናቄ እና የዜግነት አገልግሎት ባህል ግንባታ
በአንድ ጀምበር በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ችግኝ የመተከል ልምዳቸው፣ የአካባቢ ጥበቃን ከዘመቻነት አውጥቶ የባህል እና የዜግነት ግዴታ አካል አድርጎታል።
ይህም የሕዝባዊ ወንድማማችነትን ያጠናከረ እና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤን በማሳደግ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር እጅግ ግዙፍ ማኅበራዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ስኬት ነው።
በአጠቃላይ አረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተፈጥሮ ሀብታችንን ከመመለስ አልፎ ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ አቅማችንን የገነባ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ አቅራቢ ሀገር ያደረገ አንጸባራቂ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #climateaction #greendiplomacy #greeneconomy
Sponsored by
Surafel
2 days ago
በጅማ ዞን ለሚካሄደው የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ የተለያዩ እንግዶች ጅማ ገቡ!
በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሰቃ ወረዳ በቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚካሄደውና ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ የቀረበበት የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ዝግጅት መጠጠናቀቁ ተገለጸ። በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ግብ መሠረት የሚከናወነው ይህ መርሃ-ግብር፤ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ-ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዘጋጅነት የቀረበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን ቴክኒካል ድጋፍ በማድረግ ተሳትፏል።።
ለዝግጅቱ ስኬት በጅማ ከተማ የደረሱ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ቲክቶክሮች እና የጥሪው ተጋባዦች በዞኑ እና በከተማ አስተዳደሩ፣ በአባ ገዳዎች፣ በሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ነገ በሚካሄደው በዚህ ታሪካዊ ኹነት ህብረተሰቡ በነቃ ሁኔታ እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።
በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሰቃ ወረዳ በቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚካሄደውና ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ የቀረበበት የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ዝግጅት መጠጠናቀቁ ተገለጸ። በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ግብ መሠረት የሚከናወነው ይህ መርሃ-ግብር፤ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ-ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዘጋጅነት የቀረበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን ቴክኒካል ድጋፍ በማድረግ ተሳትፏል።።
ለዝግጅቱ ስኬት በጅማ ከተማ የደረሱ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ቲክቶክሮች እና የጥሪው ተጋባዦች በዞኑ እና በከተማ አስተዳደሩ፣ በአባ ገዳዎች፣ በሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ነገ በሚካሄደው በዚህ ታሪካዊ ኹነት ህብረተሰቡ በነቃ ሁኔታ እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።
2 days ago
የውኃ ሉዓላዊነታችን በተግባር፡ ከ18 ዓመታት የእንቅልፍ ዘመን የነቃው የመገጭ ግድብ
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በአማራ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ከእነዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን የረዥም ዘመን የመጠጥ ውኃ ጥያቄ የሚመልሰው እና ሰፊ የመስኖ ልማት አቅም ያለው የመገጭ ግድብ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡
ግንባታው በ2001 ዓ.ም. የተጀመረው ይህ ግድብ፣ ላለፉት 18 ዓመታት የመልካም አስተዳደር እና የፕሮጀክት አመራር ድክመት ተጓትቶ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ በ2017 በጀት ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥተኛ አመራር፣ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ የነበረው ተቋራጭ ከፕሮጀክቱ እንዲወጣ ተደርጎ ሥራው ለሀገር በቀል ተቋራጭ ተሰጥቷል፡፡
የውጭ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተጋብዘው የመሬት መንሸራተት ችግሩ በጥናት እንዲፈታ መደረጉ፣ እንዲሁም ሥራው በቀን እና በሌሊት ፈረቃ እንዲከናወን መወሰኑ ፕሮጀክቱን ከእንቅልፉ ቀስቅሶ ወደ ጤናማ እና ፈጣን የአፈጻጸም ምዕራፍ አሸጋግሮታል፡፡
በዚህም የግንባታው ወሳኝ ምዕራፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በቅርቡ ለፍሬ እንደሚበቃ ይጠበቃል፡፡
የመገጭ ግድብ ከግንባታ ባለፈ የኢትዮጵያውያን የልማት ፅናት ማሳያ ነው፡፡ አጠቃላይ የውኃ መያዝ አቅሙ 185 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 116 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የሚሆነው ለመስኖ ልማት የሚውል ነው፡፡
ይህም 17 ሺህ ሔክታር መሬትን በመስኖ በማልማት የጎንደር ከተማን እንዲሁም የምሥራቅ እና የምዕራብ ደምቢያ አካባቢ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ክልሉ ያለውን ሰፊ የውኃ እና የመሬት ሀብት አቀናጅቶ ለመጠቀም እየተገነቡ ካሉ ሰፋፊ የመስኖ አውታሮች አንዱ የሆነው ይህ ፕሮጀክት፣ የሀገራችን የግብርና ትራንስፎርሜሽን እና የምግብ ዋስትና ራዕይ በጉልህ የሚያሳካ የዘመን ትሩፋት ነው፡፡
ይህ የኢትዮጵያ የማይቆም የልማት እርምጃ እንደተለመደው የግብፅ ሚዲያዎችን ሰላም ነስቷል፡፡
የመገጭ ግድብ በጣና ሐይቅ ገባር ወንዝ ላይ የሚገነባ መካከለኛ ፕሮጀክት ቢሆንም፣ የግብፅ ሚዲያዎች ፕሮጀክቱን በተመለከተ ሰሞኑን እያስተጋቡት ያለው ጩኸት ሀገሪቱ ከያዘችው የቆየ እና ራስ ወዳድ የውኃ ፖሊሲ የሚመነጭ ነው፡፡
ግብፅ ኢትዮጵያ የውኃ ሀብቷን እንዳትጠቀም የማስፈራራት ፖሊሲን ብትከተልም፣ ኢትዮጵያ ግን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ አጠናቅቃ ልማቷን የሚያፋጥኑ እንደ መገጭ ያሉ ግድቦችን መቀጠ "ኢትዮጵያ አትጨበጥም" የሚል ድንጋጤ ፈጥሮባቸዋል፡፡
ግብፅ አሁንም ጊዜ ያለፈባቸውን የቅኝ ግዛት ውሎች እያነሳች የትኛውም የኢትዮጵያ ልማት ግብርናዋን እንደሚጎዳ በማስመሰል ከእውነት የራቀ ኢ-ፍትሐዊ ትርክት ታራምዳለች፡፡
ኢትዮጵያ ግን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውኃ አጠቃቀም መርህን (CFA) በመከተል ሕዝቧን ለመመገብ የገዛ ሀብቷን የማልማት ተፈጥሯዊና ሕጋዊ መብቷን እያስከበረች ትገኛለች፡፡
ከዚህም ባሻገር እንደ መገጭ ባሉ የኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ግድብ መሥራት የውኃ ትነትን እጅግ የሚቀንስ መሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ማንንም የማይጎዳ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ማረጋገጫ ነው፡፡
እውነታው ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ምዕራፍ ከትላንቱ በእጅጉ የተለየ መሆኑ ነው፡፡ ሀገራችን የዜጎቿን ሕይወት ለመለወጥ እና ከድህነት ለመውጣት የምታደርገውን የልማት ጉዞ በማንኛውም የውጭ ኃይል እጅ ጥምዘዛ የማታቆምበት ታሪካዊ ከፍታ ላይ ትገኛለች፡፡
የመገጭ ግድብም ሆነ ሌሎች በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የዚሁ ሉዓላዊ መብት አካል ናቸው፡፡
ማንም ይጩህ ማን፣ ኢትዮጵያ በራሷ ሀብት፣ በራሷ አቅም እና በራሷ ጊዜ የጀመረቻቸውን የልማት ሥራዎች ከዳር በማድረስ ታሪኳን በአዲስ መልክ መጻፏን አጠናክራ ትቀጥላለች፡፡
መንግሥትም በቀጣይ የመገጭ ግድብ ቀሪ ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎችን በማጠናከር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የዲፕሎማሲ ሥራውን በማስፋት የኢትዮጵያን ብልጽግና ያረጋግጣል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #megechdam #nile #development #amhararegion
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በአማራ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ከእነዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን የረዥም ዘመን የመጠጥ ውኃ ጥያቄ የሚመልሰው እና ሰፊ የመስኖ ልማት አቅም ያለው የመገጭ ግድብ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡
ግንባታው በ2001 ዓ.ም. የተጀመረው ይህ ግድብ፣ ላለፉት 18 ዓመታት የመልካም አስተዳደር እና የፕሮጀክት አመራር ድክመት ተጓትቶ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ በ2017 በጀት ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥተኛ አመራር፣ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ የነበረው ተቋራጭ ከፕሮጀክቱ እንዲወጣ ተደርጎ ሥራው ለሀገር በቀል ተቋራጭ ተሰጥቷል፡፡
የውጭ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተጋብዘው የመሬት መንሸራተት ችግሩ በጥናት እንዲፈታ መደረጉ፣ እንዲሁም ሥራው በቀን እና በሌሊት ፈረቃ እንዲከናወን መወሰኑ ፕሮጀክቱን ከእንቅልፉ ቀስቅሶ ወደ ጤናማ እና ፈጣን የአፈጻጸም ምዕራፍ አሸጋግሮታል፡፡
በዚህም የግንባታው ወሳኝ ምዕራፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በቅርቡ ለፍሬ እንደሚበቃ ይጠበቃል፡፡
የመገጭ ግድብ ከግንባታ ባለፈ የኢትዮጵያውያን የልማት ፅናት ማሳያ ነው፡፡ አጠቃላይ የውኃ መያዝ አቅሙ 185 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 116 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የሚሆነው ለመስኖ ልማት የሚውል ነው፡፡
ይህም 17 ሺህ ሔክታር መሬትን በመስኖ በማልማት የጎንደር ከተማን እንዲሁም የምሥራቅ እና የምዕራብ ደምቢያ አካባቢ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ክልሉ ያለውን ሰፊ የውኃ እና የመሬት ሀብት አቀናጅቶ ለመጠቀም እየተገነቡ ካሉ ሰፋፊ የመስኖ አውታሮች አንዱ የሆነው ይህ ፕሮጀክት፣ የሀገራችን የግብርና ትራንስፎርሜሽን እና የምግብ ዋስትና ራዕይ በጉልህ የሚያሳካ የዘመን ትሩፋት ነው፡፡
ይህ የኢትዮጵያ የማይቆም የልማት እርምጃ እንደተለመደው የግብፅ ሚዲያዎችን ሰላም ነስቷል፡፡
የመገጭ ግድብ በጣና ሐይቅ ገባር ወንዝ ላይ የሚገነባ መካከለኛ ፕሮጀክት ቢሆንም፣ የግብፅ ሚዲያዎች ፕሮጀክቱን በተመለከተ ሰሞኑን እያስተጋቡት ያለው ጩኸት ሀገሪቱ ከያዘችው የቆየ እና ራስ ወዳድ የውኃ ፖሊሲ የሚመነጭ ነው፡፡
ግብፅ ኢትዮጵያ የውኃ ሀብቷን እንዳትጠቀም የማስፈራራት ፖሊሲን ብትከተልም፣ ኢትዮጵያ ግን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ አጠናቅቃ ልማቷን የሚያፋጥኑ እንደ መገጭ ያሉ ግድቦችን መቀጠ "ኢትዮጵያ አትጨበጥም" የሚል ድንጋጤ ፈጥሮባቸዋል፡፡
ግብፅ አሁንም ጊዜ ያለፈባቸውን የቅኝ ግዛት ውሎች እያነሳች የትኛውም የኢትዮጵያ ልማት ግብርናዋን እንደሚጎዳ በማስመሰል ከእውነት የራቀ ኢ-ፍትሐዊ ትርክት ታራምዳለች፡፡
ኢትዮጵያ ግን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውኃ አጠቃቀም መርህን (CFA) በመከተል ሕዝቧን ለመመገብ የገዛ ሀብቷን የማልማት ተፈጥሯዊና ሕጋዊ መብቷን እያስከበረች ትገኛለች፡፡
ከዚህም ባሻገር እንደ መገጭ ባሉ የኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ግድብ መሥራት የውኃ ትነትን እጅግ የሚቀንስ መሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ማንንም የማይጎዳ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ማረጋገጫ ነው፡፡
እውነታው ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ምዕራፍ ከትላንቱ በእጅጉ የተለየ መሆኑ ነው፡፡ ሀገራችን የዜጎቿን ሕይወት ለመለወጥ እና ከድህነት ለመውጣት የምታደርገውን የልማት ጉዞ በማንኛውም የውጭ ኃይል እጅ ጥምዘዛ የማታቆምበት ታሪካዊ ከፍታ ላይ ትገኛለች፡፡
የመገጭ ግድብም ሆነ ሌሎች በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የዚሁ ሉዓላዊ መብት አካል ናቸው፡፡
ማንም ይጩህ ማን፣ ኢትዮጵያ በራሷ ሀብት፣ በራሷ አቅም እና በራሷ ጊዜ የጀመረቻቸውን የልማት ሥራዎች ከዳር በማድረስ ታሪኳን በአዲስ መልክ መጻፏን አጠናክራ ትቀጥላለች፡፡
መንግሥትም በቀጣይ የመገጭ ግድብ ቀሪ ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎችን በማጠናከር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የዲፕሎማሲ ሥራውን በማስፋት የኢትዮጵያን ብልጽግና ያረጋግጣል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #megechdam #nile #development #amhararegion
3 days ago
የአርሶ አደሩን ድካም የሚያቃልል አዲስ ማሽን በደብረ ታቦር ተፈጠረ
#ethiopia | የደብረ ታቦር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች በረከት ፀጋው እና ቤዛዊት ሲሳይ ሰብልን በአንድ ጊዜ የሚወቃና የሚያበጥር አዲስ የግብርና ማሽን በመፍጠር ትኩረት ስበዋል።
አዲሱ ማሽን አርሶ አደሮች እህል ለመውቃት ይጠቀሙበት የነበረውን ብዙ የሰው ኃይልና የእንስሳት ጉልበት የሚተካ ሲሆን፣ ሥራውን በሁለት ሰዎች ብቻ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ያስችላል። ይህም የምርት ሂደቱን በማፋጠን የሥራ ወጪን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
ወጣቶቹ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ይህን ፈጠራ ማበልጸጋቸው ለሌሎች ወጣቶች በፈጠራና በራስ አቅም ሥራ ፈጠራ ረገድ አርአያ ሆኗል።
የደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደርም ለፈጠራው ቀጣይ እድገት የቦታ፣ የሼድ እና የብድር ድጋፍ በማድረግ ከፈጣሪዎቹ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።
አሚኮ (AMICO)
#ethiopia #debretabor #innovation #agritech #tvet #ethiopianyouth #agriculture #ግብርና #ፈጠራ
#ethiopia | የደብረ ታቦር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች በረከት ፀጋው እና ቤዛዊት ሲሳይ ሰብልን በአንድ ጊዜ የሚወቃና የሚያበጥር አዲስ የግብርና ማሽን በመፍጠር ትኩረት ስበዋል።
አዲሱ ማሽን አርሶ አደሮች እህል ለመውቃት ይጠቀሙበት የነበረውን ብዙ የሰው ኃይልና የእንስሳት ጉልበት የሚተካ ሲሆን፣ ሥራውን በሁለት ሰዎች ብቻ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ያስችላል። ይህም የምርት ሂደቱን በማፋጠን የሥራ ወጪን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
ወጣቶቹ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ይህን ፈጠራ ማበልጸጋቸው ለሌሎች ወጣቶች በፈጠራና በራስ አቅም ሥራ ፈጠራ ረገድ አርአያ ሆኗል።
የደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደርም ለፈጠራው ቀጣይ እድገት የቦታ፣ የሼድ እና የብድር ድጋፍ በማድረግ ከፈጣሪዎቹ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።
አሚኮ (AMICO)
#ethiopia #debretabor #innovation #agritech #tvet #ethiopianyouth #agriculture #ግብርና #ፈጠራ
3 days ago
የአርሰናል ደጋፊዎችን የሚያገናኝ "ገነርስ" የተሰኘ ማህበር ተመሠረተ
#ethiopia | የእግር ኳስ ፍቅርን ከአባላት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ጋር የሚያስተሳስረው አዲሱ ዓለም አቀፍ ተቋም "ገነርስ"የሚል ስያሜ የተሰጠው ማህበር በኢትዮጵያ፣ በጀርመን እና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መሠረቱን ጥሎ በይፋ ሥራ መጀመሩን አሳወቀ።
ተቋሙ በአለም ዙሪያ የሚገኙ የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎችን በአንድ ጠንካራ ማህበረሰብ ስር በማሰባሰብ፣ አባላቱ በህይወታቸው እርስ በርስ እንዲደጋገፉ እና አዲስ የዕድል በሮች እንዲከፈቱላቸው የሚያስችል ዘላቂ ስርዓት ዘርግቷል።
ከደጋፊነት ማዕቀፍ ባለፈም ከመንግስታዊ እና ከግል ተቋማት ጋር ስትራቴጂካዊ አጋርነት በመመስረት ለአባላቱ ተጨባጭ ጥቅሞችን፣ የሥራ ዕድሎችን እና የንግድ አማራጮችን ለማስፋፋት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
አባላቱ በዕለት ተዕለት ኑሯቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሰፊ አገልግሎቶችን የሚዘረጋው ገርነስ ማህበር ፤ ከግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች ግብይት ጀምሮ እስከ ጤና፣ ሆቴል፣ ቱሪዝም እና የጉዞ አገልግሎቶች ድረስ በተመረጡ አጋር ተቋማት ልዩ ቅናሾችንና መስተንግዶዎችን እያቀረበ ይገኛል።
ከዚህም በተጨማሪ አባላትን የሚያዝናኑ፣ ጠቃሚ መረጃዎችን የሚያጋሩ ሳቢ የዲጂታል ሚዲያ ይዘቶችን በማዘጋጀት የማህበረሰብ ትስስሩን ይበልጥ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመድረኩ ላይ ተገልጿል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#gunners #arsenal #arsenalethiopia #gunners #ethiopiangunners
#ethiopia | የእግር ኳስ ፍቅርን ከአባላት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ጋር የሚያስተሳስረው አዲሱ ዓለም አቀፍ ተቋም "ገነርስ"የሚል ስያሜ የተሰጠው ማህበር በኢትዮጵያ፣ በጀርመን እና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መሠረቱን ጥሎ በይፋ ሥራ መጀመሩን አሳወቀ።
ተቋሙ በአለም ዙሪያ የሚገኙ የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎችን በአንድ ጠንካራ ማህበረሰብ ስር በማሰባሰብ፣ አባላቱ በህይወታቸው እርስ በርስ እንዲደጋገፉ እና አዲስ የዕድል በሮች እንዲከፈቱላቸው የሚያስችል ዘላቂ ስርዓት ዘርግቷል።
ከደጋፊነት ማዕቀፍ ባለፈም ከመንግስታዊ እና ከግል ተቋማት ጋር ስትራቴጂካዊ አጋርነት በመመስረት ለአባላቱ ተጨባጭ ጥቅሞችን፣ የሥራ ዕድሎችን እና የንግድ አማራጮችን ለማስፋፋት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
አባላቱ በዕለት ተዕለት ኑሯቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሰፊ አገልግሎቶችን የሚዘረጋው ገርነስ ማህበር ፤ ከግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች ግብይት ጀምሮ እስከ ጤና፣ ሆቴል፣ ቱሪዝም እና የጉዞ አገልግሎቶች ድረስ በተመረጡ አጋር ተቋማት ልዩ ቅናሾችንና መስተንግዶዎችን እያቀረበ ይገኛል።
ከዚህም በተጨማሪ አባላትን የሚያዝናኑ፣ ጠቃሚ መረጃዎችን የሚያጋሩ ሳቢ የዲጂታል ሚዲያ ይዘቶችን በማዘጋጀት የማህበረሰብ ትስስሩን ይበልጥ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመድረኩ ላይ ተገልጿል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#gunners #arsenal #arsenalethiopia #gunners #ethiopiangunners
Sponsored by
Surafel
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በትግራይ ክልል ከ 3.7 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በኤልኒኞ ምክንያት ለተከሰተ ከባድ ድርቅ መጋለጣቸውን ተከትሎ፣ የሰብአዊ ዕርዳታ ኤጀንሲዎች የ623 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ እጥረት (ክፍተት) እንደገጠማቸው አሳወቁ። የትግራይ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን (TDRMC) እና አለም አቀፍ አጋሮች ባወጡት የጋራ ሪፖርት መሰረት፣ አደጋውን ለመቀልበስ ከሚያስፈልገው 626.8 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ እስካሁን የተገኘው 3.38 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ሲሆን፣ ይህም ከሚያስፈልገው አጠቃላይ በጀት 99 በመቶው ያልተሸፈነ መሆኑን በማሳየት ሁኔታውን እጅግ አሳሳቢ አድርጎታል።
በድርቁ አደጋ የዕርዳታ ፈላጊ ከሆኑት ወገኖች መካከል ከ900 ሺህ በላይ የውስጥ ተፈናቃዮች እና አንድ ሚሊዮን የሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚዎች ይገኙበታል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የጋራ ትንበያ በመጪው የ2026 የክረምት ወቅት ዝናብ ሊዘገይ፣ ቀድሞ ሊያቆም፣ የተራዘመ ደረቃማ ጊዜ እና ከፍተኛ የሙቀት መጠን ሊኖር እንደሚችል ያረጋገጠ ሲሆን፣ በክልሉ ከሚገኙ 50 የገጠር ወረዳዎች ውስጥ 21ዱ እጅግ "በከፍተኛ ደረጃ አደገኛ" በተባለው ምድብ (Risk Level 5) ውስጥ ተመድበዋል።
አደጋው ሙሉ በሙሉ ጉዳት ከማድረሱ በፊት የቅድመ መከላከል ጣልቃ ገብነት ለማድረግ የ6 ሳምንታት ጠባብ ጊዜ ብቻ የቀረ ሲሆን፣ አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታው ብቻ 366.78 ሚሊዮን ዶላር ይፈልጋል። ከዚህ በተጨማሪ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ንፅህና (50.95 ሚሊዮን ዶላር)፣ የስነ-ምግብ፣ የግብርና እና የጤና ዘርፎች የየራሳቸው የሆነ ከፍተኛ በጀት ጠይቀዋል። ይህ የገንዘብ እጥረት በፍጥነት ተቀርፎ የዕርዳታ አቅርቦት ካልተጀመረ፣ በቀጠናው የከፋ የሰብአዊ ቀውስ ሊከሰት እንደሚችል ኮሚሽኑ አጥብቆ አስጠንቅቋል።
በድርቁ አደጋ የዕርዳታ ፈላጊ ከሆኑት ወገኖች መካከል ከ900 ሺህ በላይ የውስጥ ተፈናቃዮች እና አንድ ሚሊዮን የሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚዎች ይገኙበታል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የጋራ ትንበያ በመጪው የ2026 የክረምት ወቅት ዝናብ ሊዘገይ፣ ቀድሞ ሊያቆም፣ የተራዘመ ደረቃማ ጊዜ እና ከፍተኛ የሙቀት መጠን ሊኖር እንደሚችል ያረጋገጠ ሲሆን፣ በክልሉ ከሚገኙ 50 የገጠር ወረዳዎች ውስጥ 21ዱ እጅግ "በከፍተኛ ደረጃ አደገኛ" በተባለው ምድብ (Risk Level 5) ውስጥ ተመድበዋል።
አደጋው ሙሉ በሙሉ ጉዳት ከማድረሱ በፊት የቅድመ መከላከል ጣልቃ ገብነት ለማድረግ የ6 ሳምንታት ጠባብ ጊዜ ብቻ የቀረ ሲሆን፣ አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታው ብቻ 366.78 ሚሊዮን ዶላር ይፈልጋል። ከዚህ በተጨማሪ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ንፅህና (50.95 ሚሊዮን ዶላር)፣ የስነ-ምግብ፣ የግብርና እና የጤና ዘርፎች የየራሳቸው የሆነ ከፍተኛ በጀት ጠይቀዋል። ይህ የገንዘብ እጥረት በፍጥነት ተቀርፎ የዕርዳታ አቅርቦት ካልተጀመረ፣ በቀጠናው የከፋ የሰብአዊ ቀውስ ሊከሰት እንደሚችል ኮሚሽኑ አጥብቆ አስጠንቅቋል።
3 days ago
800 ሚሊዮን ችግኞች በአንድ ጀምበር ኢትዮጵያ ለዓለም የምታሳየው ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ
************************
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ዘመነ-ተሻጋሪ ተጽዕኖ ለመቋቋም፣ የተጎዱ መሬቶችን ለማደስ እና የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህይወት ለማሻሻል ያለመ ሀገራዊ ራዕይ ሰንቃ በመንቀሳቀስ ላይ ትገኛለች።
የዚሁ ዘላቂ ጥረት አካል የሆነውና በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ግብ፣ ሀገራችን ለአረንጓዴ ልማትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዳግም በተግባር የሚያስመሰክር ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ይህ ዘመቻ ተራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ብቻ ሳይሆን፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በአንድ ልብና በአንድ ዓላማ በመነሳት የሚያደርጉት የተቀናጀ አቅምና አንድነት ማሳያ እንዲሁም የተፈጥሮ ሚዛንን ለመመለስ የተደረገ ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
በዚህ ታሪካዊ ቀን ከሚተከሉት ችግኞች መካከል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ እና ዘይቱን ያሉ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ተክሎች ይገኙበታል።
እነዚህ የፍራፍሬ ዛፎች የምግብ አቅርቦትን ከማሳደግ ባሻገር ለገበሬዎች የገቢ ምንጭ በመሆን የገጠር ኢኮኖሚን ለማጠናከር በከፍተኛ ሁኔታ ያግዛሉ።
በተጨማሪም የደን ሽፋን መጨመር የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጎለብት ያደርጋል፤ ታላላቅ የኃይል ማመንጫ ግድቦች እና የመስኖ መሠረተ ልማቶች በደለል እንዳይሞሉ በመከላከል የአገልግሎት ዘመናቸውን ያራዝማል።
የአካባቢ ሙቀትን በመቀነስና የዝናብ ዘይቤን በማስተካከልም ለግብርናው ዘርፍ የተሻለ እና አስተማማኝ ሁኔታ ይፈጥራል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የነገዋን አረንጓዴ፣ በምግብ ራሷን የቻለች እና የተፈጥሮ ሀብቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለመገንባት የተጣለ ጠንካራ መሠረት ነው።
ዛሬ በትጋት መሬት የሚይዘው እያንዳንዱ ችግኝ የነገው የኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ፣ አረንጓዴ ተፈጥሮ እና ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ ታሪካዊ አሻራ ደማቅ መገለጫ ነው።
በኢንቲሃድ አብራር
#greenlegacy #ethiopia #climateaction #treeplanting #sustainability
************************
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ዘመነ-ተሻጋሪ ተጽዕኖ ለመቋቋም፣ የተጎዱ መሬቶችን ለማደስ እና የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህይወት ለማሻሻል ያለመ ሀገራዊ ራዕይ ሰንቃ በመንቀሳቀስ ላይ ትገኛለች።
የዚሁ ዘላቂ ጥረት አካል የሆነውና በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ግብ፣ ሀገራችን ለአረንጓዴ ልማትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዳግም በተግባር የሚያስመሰክር ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ይህ ዘመቻ ተራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ብቻ ሳይሆን፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በአንድ ልብና በአንድ ዓላማ በመነሳት የሚያደርጉት የተቀናጀ አቅምና አንድነት ማሳያ እንዲሁም የተፈጥሮ ሚዛንን ለመመለስ የተደረገ ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
በዚህ ታሪካዊ ቀን ከሚተከሉት ችግኞች መካከል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ እና ዘይቱን ያሉ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ተክሎች ይገኙበታል።
እነዚህ የፍራፍሬ ዛፎች የምግብ አቅርቦትን ከማሳደግ ባሻገር ለገበሬዎች የገቢ ምንጭ በመሆን የገጠር ኢኮኖሚን ለማጠናከር በከፍተኛ ሁኔታ ያግዛሉ።
በተጨማሪም የደን ሽፋን መጨመር የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጎለብት ያደርጋል፤ ታላላቅ የኃይል ማመንጫ ግድቦች እና የመስኖ መሠረተ ልማቶች በደለል እንዳይሞሉ በመከላከል የአገልግሎት ዘመናቸውን ያራዝማል።
የአካባቢ ሙቀትን በመቀነስና የዝናብ ዘይቤን በማስተካከልም ለግብርናው ዘርፍ የተሻለ እና አስተማማኝ ሁኔታ ይፈጥራል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የነገዋን አረንጓዴ፣ በምግብ ራሷን የቻለች እና የተፈጥሮ ሀብቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለመገንባት የተጣለ ጠንካራ መሠረት ነው።
ዛሬ በትጋት መሬት የሚይዘው እያንዳንዱ ችግኝ የነገው የኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ፣ አረንጓዴ ተፈጥሮ እና ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ ታሪካዊ አሻራ ደማቅ መገለጫ ነው።
በኢንቲሃድ አብራር
#greenlegacy #ethiopia #climateaction #treeplanting #sustainability
4 days ago
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የCGIAR የመጀመሪያው የቦርድ ሊቀመንበር ሆነው ተሾሙ
#ethiopia | የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ቦሼ በዓለም አቀፍ የግብርና ምርምር ትብብር ተቋም CGIAR አዲስ የተዋቀረው የቦርድ የመጀመሪያ ሊቀመንበር ሆነው መሾማቸውን ተቋሙ በይፋ አስታውቋል። ሹመታቸው ከነሐሴ 1 ቀን 2026 ጀምሮ በይፋ ተግባራዊ ይሆናል።
እንደ CGIAR መግለጫ፣ አዲሱ ቦርድ የተቋሙን የዓለም አቀፍ የግብርና ምርምር ሥራዎች በማስተባበር በምግብ ዋስትና፣ በግብርና ምርታማነት፣ በአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅም እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ዙሪያ የሚከናወኑ ስትራቴጂያዊ ውሳኔዎችን ይመራል።
ሹመቱ የተካሄደው ለወራት የዘለቀ የምልመላና የእጩ ምርጫ ሂደት ተጠናቆ ሲሆን፣ ኃይለማርያም ደሳለኝ በግብርና ፖሊሲ፣ በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ትብብር፣ እንዲሁም በሳይንስን መሠረት ባደረገ የልማት አመራር ያላቸው ልምድ ለሹመታቸው ዋና ምክንያት መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።
የCGIAR ጊዜያዊ የቦርድ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ሮኤል መርክስ በሰጡት መግለጫ፣ ኃይለማርያም በሳይንስ ላይ የተመሰረተ የግብርና ልማትን ለማራመድ ያላቸው ልምድና አመራር ለተቋሙ ትልቅ እሴት እንደሚያመጣ ገልጸዋል።
ኃይለማርያም ደሳለኝ ከ2019 ጀምሮ የAGRA (Alliance for a Green Revolution in Africa) ቦርድ ሊቀመንበር በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን፣ በተጨማሪም የTradeMark Africa ቦርድን ጨምሮ በበርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት የአመራር ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ቦሼ በዓለም አቀፍ የግብርና ምርምር ትብብር ተቋም CGIAR አዲስ የተዋቀረው የቦርድ የመጀመሪያ ሊቀመንበር ሆነው መሾማቸውን ተቋሙ በይፋ አስታውቋል። ሹመታቸው ከነሐሴ 1 ቀን 2026 ጀምሮ በይፋ ተግባራዊ ይሆናል።
እንደ CGIAR መግለጫ፣ አዲሱ ቦርድ የተቋሙን የዓለም አቀፍ የግብርና ምርምር ሥራዎች በማስተባበር በምግብ ዋስትና፣ በግብርና ምርታማነት፣ በአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅም እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ዙሪያ የሚከናወኑ ስትራቴጂያዊ ውሳኔዎችን ይመራል።
ሹመቱ የተካሄደው ለወራት የዘለቀ የምልመላና የእጩ ምርጫ ሂደት ተጠናቆ ሲሆን፣ ኃይለማርያም ደሳለኝ በግብርና ፖሊሲ፣ በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ትብብር፣ እንዲሁም በሳይንስን መሠረት ባደረገ የልማት አመራር ያላቸው ልምድ ለሹመታቸው ዋና ምክንያት መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።
የCGIAR ጊዜያዊ የቦርድ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ሮኤል መርክስ በሰጡት መግለጫ፣ ኃይለማርያም በሳይንስ ላይ የተመሰረተ የግብርና ልማትን ለማራመድ ያላቸው ልምድና አመራር ለተቋሙ ትልቅ እሴት እንደሚያመጣ ገልጸዋል።
ኃይለማርያም ደሳለኝ ከ2019 ጀምሮ የAGRA (Alliance for a Green Revolution in Africa) ቦርድ ሊቀመንበር በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን፣ በተጨማሪም የTradeMark Africa ቦርድን ጨምሮ በበርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት የአመራር ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
5 days ago
የአየር ንብረት ለውጥ አውሮፓን እያመሰ ነው
* በከፍተኛ ሙቀት እና በሰደድ እሳት ሺዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል
#ethiopia | የአየር ንብረት ለውጥ በአውሮፓ ከፍተኛ ሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ሥነ-ምህዳራዊ ቀውስ እያስከተለ መሆኑን የቅርብ ጊዜ ዓለም አቀፍ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በሰኔ መጨረሻ እና በሐምሌ ወር የተከሰቱ ከባድ የሙቀት ማዕበሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሕልፈት ዳርገዋል፤ በበርካታ አገራት ደግሞ ሰደድ እሳቶች መኖሪያ ቤቶችን፣ ደኖችንና የግብርና መሬቶችን አውድመዋል።
የአውሮፓ በሽታ መከላከያ ማዕከል (ECDC) እና የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በሚደግፉት የEuroMOMO የሞት ክትትል መረጃ መሠረት፣ በሰኔ 22 እስከ 28 ቀን 2026 ብቻ ከ10 ሺህ በላይ ተጨማሪ ሞቶች ተመዝግበዋል።
ከእነዚህ ውስጥ ከ9 ሺህ በላይ የሚሆኑት ዕድሜያቸው 65 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች ናቸው። ባለሙያዎች ይህን ያልተለመደ የሞት ጭማሪ በዋነኝነት ከከፍተኛ ሙቀት ጋር ያያይዙታል።
በጀርመን ብቻ በ2026 እስከ ሐምሌ መጨረሻ ድረስ 9,800 የሚጠጉ ከሙቀት ጋር የተያያዙ ሞቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።
በእንግሊዝ ደግሞ 2,800 በላይ ሰዎች በሙቀት ምክንያት መሞታቸው ተነግሯል፤ ይህም የ2022 ሪከርድን ሊበልጥ እንደሚችል ባለሥልጣናት አስጠንቅቀዋል።
በፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ግሪክ፣ ጣሊያን እና ፖርቱጋል የተቀሰቀሱ ሰደድ እሳቶች በመቶ ሺዎች ሄክታር የሚቆጠር ደን እንዲቃጠል አድርገዋል።
በፈረንሳይ ብቻ ከ220 ሺህ በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል፤ በግሪክ ደግሞ ሶስት የአደጋ አደራሽ ሠራተኞች በእሳት ማጥፋት ስራ ላይ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
ሳይንቲስቶች እንደሚገልጹት፣ በሰኔ መጨረሻ የተመዘገበው የሙቀት ማዕበል የሰው ልጅ የፈጠረው የአየር ንብረት ለውጥ ባይኖር ሊከሰት ፈጽሞ የማይችል ነበር።
አውሮፓ በዓለም ላይ ከሌሎች አህጉራት በበለጠ ፍጥነት እየሞቀች ያለች አህጉር መሆኗም ችግሩን እያባባሰው ነው።
በዚህ ሁኔታ የአውሮፓ መንግሥታት የሙቀት አደጋ ማስጠንቀቂያ ሥርዓቶችን ማጠናከር፣ ለአረጋውያንና ለተጋላጭ ማኅበረሰቦች የጤና ጥበቃን ማሳደግ፣ እንዲሁም የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ የበለጠ ቁርጠኛ እርምጃ እንዲወስዱ ተጠይቀዋል።
በሌላ በኩል፣ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በ"አረንጓዴ ዐሻራ" መርሃ ግብር ባለፉት ሰባት ዓመታት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋኗን ለማሳደግና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ጥረት እያደረገች ትገኛለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
* በከፍተኛ ሙቀት እና በሰደድ እሳት ሺዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል
#ethiopia | የአየር ንብረት ለውጥ በአውሮፓ ከፍተኛ ሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ሥነ-ምህዳራዊ ቀውስ እያስከተለ መሆኑን የቅርብ ጊዜ ዓለም አቀፍ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በሰኔ መጨረሻ እና በሐምሌ ወር የተከሰቱ ከባድ የሙቀት ማዕበሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሕልፈት ዳርገዋል፤ በበርካታ አገራት ደግሞ ሰደድ እሳቶች መኖሪያ ቤቶችን፣ ደኖችንና የግብርና መሬቶችን አውድመዋል።
የአውሮፓ በሽታ መከላከያ ማዕከል (ECDC) እና የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በሚደግፉት የEuroMOMO የሞት ክትትል መረጃ መሠረት፣ በሰኔ 22 እስከ 28 ቀን 2026 ብቻ ከ10 ሺህ በላይ ተጨማሪ ሞቶች ተመዝግበዋል።
ከእነዚህ ውስጥ ከ9 ሺህ በላይ የሚሆኑት ዕድሜያቸው 65 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች ናቸው። ባለሙያዎች ይህን ያልተለመደ የሞት ጭማሪ በዋነኝነት ከከፍተኛ ሙቀት ጋር ያያይዙታል።
በጀርመን ብቻ በ2026 እስከ ሐምሌ መጨረሻ ድረስ 9,800 የሚጠጉ ከሙቀት ጋር የተያያዙ ሞቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።
በእንግሊዝ ደግሞ 2,800 በላይ ሰዎች በሙቀት ምክንያት መሞታቸው ተነግሯል፤ ይህም የ2022 ሪከርድን ሊበልጥ እንደሚችል ባለሥልጣናት አስጠንቅቀዋል።
በፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ግሪክ፣ ጣሊያን እና ፖርቱጋል የተቀሰቀሱ ሰደድ እሳቶች በመቶ ሺዎች ሄክታር የሚቆጠር ደን እንዲቃጠል አድርገዋል።
በፈረንሳይ ብቻ ከ220 ሺህ በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል፤ በግሪክ ደግሞ ሶስት የአደጋ አደራሽ ሠራተኞች በእሳት ማጥፋት ስራ ላይ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
ሳይንቲስቶች እንደሚገልጹት፣ በሰኔ መጨረሻ የተመዘገበው የሙቀት ማዕበል የሰው ልጅ የፈጠረው የአየር ንብረት ለውጥ ባይኖር ሊከሰት ፈጽሞ የማይችል ነበር።
አውሮፓ በዓለም ላይ ከሌሎች አህጉራት በበለጠ ፍጥነት እየሞቀች ያለች አህጉር መሆኗም ችግሩን እያባባሰው ነው።
በዚህ ሁኔታ የአውሮፓ መንግሥታት የሙቀት አደጋ ማስጠንቀቂያ ሥርዓቶችን ማጠናከር፣ ለአረጋውያንና ለተጋላጭ ማኅበረሰቦች የጤና ጥበቃን ማሳደግ፣ እንዲሁም የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ የበለጠ ቁርጠኛ እርምጃ እንዲወስዱ ተጠይቀዋል።
በሌላ በኩል፣ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በ"አረንጓዴ ዐሻራ" መርሃ ግብር ባለፉት ሰባት ዓመታት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋኗን ለማሳደግና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ጥረት እያደረገች ትገኛለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
5 days ago
ቱርክ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ዘመናዊ የችግኝ ማዕከል ገነባች
#ethiopia | የቱርክ ትብብርና ቅንጅት ኤጀንሲ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቡና እና የፍራፍሬ ችግኞችን የሚያፈራ ዘመናዊ የችግኝ ማዕከል በኢትዮጵያ ገነባ።
ይህ የችግኝ ማዕከል የተገነባው የኢትዮጵያ የፍራፍሬ ልማት ድጋፍ ፕሮጀክት አካል ሲሆን ዓላማውም የአካባቢውን የግብርና አቅም በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን መቋቋም የሚያስችሉ የልማት አሰራሮችን ማስፋፋት ነው።
ይህ ሞዴል የግሪን ሃውስ ማዕከል በየዓመቱ ዘመናዊ የማባዛትና የመቀላቀል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ወደ 20 ሺህ የሚጠጉ የተሻሻሉ የቡና፣ የአቮካዶ እና የሌሎች ፍራፍሬዎች ችግኞችን ያመርታል።
ማዕከሉ ከችግኝ ማፍላት ባለፈ የተግባር ስልጠና የሚሰጥበት፣ የግብርና ምርምሮች የሚካሄዱበት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚደረግበት ዋነኛ ማዕከል ሆኖ የሚያገለግል ይሆናል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የቱርክ ትብብርና ቅንጅት ኤጀንሲ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቡና እና የፍራፍሬ ችግኞችን የሚያፈራ ዘመናዊ የችግኝ ማዕከል በኢትዮጵያ ገነባ።
ይህ የችግኝ ማዕከል የተገነባው የኢትዮጵያ የፍራፍሬ ልማት ድጋፍ ፕሮጀክት አካል ሲሆን ዓላማውም የአካባቢውን የግብርና አቅም በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን መቋቋም የሚያስችሉ የልማት አሰራሮችን ማስፋፋት ነው።
ይህ ሞዴል የግሪን ሃውስ ማዕከል በየዓመቱ ዘመናዊ የማባዛትና የመቀላቀል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ወደ 20 ሺህ የሚጠጉ የተሻሻሉ የቡና፣ የአቮካዶ እና የሌሎች ፍራፍሬዎች ችግኞችን ያመርታል።
ማዕከሉ ከችግኝ ማፍላት ባለፈ የተግባር ስልጠና የሚሰጥበት፣ የግብርና ምርምሮች የሚካሄዱበት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚደረግበት ዋነኛ ማዕከል ሆኖ የሚያገለግል ይሆናል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
5 days ago
በጅማ ዞን ከ1,800 በላይ የልማት ፕሮጀክቶች በ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ተገነቡ
#ethiopia | በጅማ ዞን በ2018 በጀት ዓመት ከ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ 1,876 የልማት ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር ገልጸዋል።
አስተዳዳሪው ይህን ያስታወቁት በጅማ ዞን ሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ የተገነቡ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች በይፋ በተመረቁበት ሥነ ሥርዓት ላይ ነው።
ለአገልግሎት ከተከፈቱት ፕሮጀክቶች መካከል መንገዶች፣ ድልድዮች፣ የሁለተኛ ትውልድ ጤና ኬላ፣ የገበያ ማዕከል፣ የግብርና ግብዓት ማከማቻ መጋዘን፣ የወረዳ አስተዳደር ሕንፃ እና ሌሎች ማህበራዊ መሠረተ ልማቶች ይገኙበታል።
አቶ ቲጃኒ ናስር እንደገለጹት፣ የህብረተሰቡን የመሠረተ ልማት ፍላጎት ለማሟላት ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት እንዲገነቡ ትኩረት ተሰጥቶ ተሠርቷል።
በመንግሥትና በህዝብ ትብብር የተገነቡት እነዚህ ፕሮጀክቶች የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክቱም ገልጸዋል።
የሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አብዱልከሪም አባራያ በበኩላቸው፣ በወረዳው ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ግንባታቸው ከተጀመሩ 33 ፕሮጀክቶች ውስጥ 23ቱ ተጠናቀው ለአገልግሎት መከፈታቸውን ገልጸው፣ ቀሪዎቹም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለህብረተሰቡ ጥቅም እንደሚውሉ አስታውቀዋል።
የአካባቢው ነዋሪ አቶ መሀመድ ዘይን ተማም በበኩላቸው፣ በወረዳው የተከናወኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ በመመለስ የኑሮ ሁኔታን እያሻሻሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተመሳሳይ የዶዩ ቃጨማ ቀበሌ ነዋሪ አቶ አብዱላሂ አባ ጀበል፣ በአካባቢው የተገነባው የግብርና ግብዓት ማከማቻ መጋዘን ከዚህ ቀደም ግብዓቶችን ለማግኘት ወደ አጎራባች ወረዳዎች በመጓዝ የሚባክነውን ጊዜና ወጪ እንዳስቀረላቸው ገልጸዋል።
የፕሮጀክቶቹ መጠናቀቅ በዞኑ የትራንስፖርት፣ የጤና፣ የንግድና የግብርና አገልግሎቶችን ተደራሽነት በማሳደግ የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ የበለጠ እንደሚያነቃቃ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | በጅማ ዞን በ2018 በጀት ዓመት ከ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ 1,876 የልማት ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር ገልጸዋል።
አስተዳዳሪው ይህን ያስታወቁት በጅማ ዞን ሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ የተገነቡ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች በይፋ በተመረቁበት ሥነ ሥርዓት ላይ ነው።
ለአገልግሎት ከተከፈቱት ፕሮጀክቶች መካከል መንገዶች፣ ድልድዮች፣ የሁለተኛ ትውልድ ጤና ኬላ፣ የገበያ ማዕከል፣ የግብርና ግብዓት ማከማቻ መጋዘን፣ የወረዳ አስተዳደር ሕንፃ እና ሌሎች ማህበራዊ መሠረተ ልማቶች ይገኙበታል።
አቶ ቲጃኒ ናስር እንደገለጹት፣ የህብረተሰቡን የመሠረተ ልማት ፍላጎት ለማሟላት ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት እንዲገነቡ ትኩረት ተሰጥቶ ተሠርቷል።
በመንግሥትና በህዝብ ትብብር የተገነቡት እነዚህ ፕሮጀክቶች የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክቱም ገልጸዋል።
የሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አብዱልከሪም አባራያ በበኩላቸው፣ በወረዳው ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ግንባታቸው ከተጀመሩ 33 ፕሮጀክቶች ውስጥ 23ቱ ተጠናቀው ለአገልግሎት መከፈታቸውን ገልጸው፣ ቀሪዎቹም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለህብረተሰቡ ጥቅም እንደሚውሉ አስታውቀዋል።
የአካባቢው ነዋሪ አቶ መሀመድ ዘይን ተማም በበኩላቸው፣ በወረዳው የተከናወኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ በመመለስ የኑሮ ሁኔታን እያሻሻሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተመሳሳይ የዶዩ ቃጨማ ቀበሌ ነዋሪ አቶ አብዱላሂ አባ ጀበል፣ በአካባቢው የተገነባው የግብርና ግብዓት ማከማቻ መጋዘን ከዚህ ቀደም ግብዓቶችን ለማግኘት ወደ አጎራባች ወረዳዎች በመጓዝ የሚባክነውን ጊዜና ወጪ እንዳስቀረላቸው ገልጸዋል።
የፕሮጀክቶቹ መጠናቀቅ በዞኑ የትራንስፖርት፣ የጤና፣ የንግድና የግብርና አገልግሎቶችን ተደራሽነት በማሳደግ የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ የበለጠ እንደሚያነቃቃ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
6 days ago
በ800 ሚሊየን ችግኞች የሚጻፈው አሻራ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት የደን ሀብቷን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን የመቋቋም ጉዞ ዛሬ ላይ የሀገሪቱን ገጽታ ከመቀየር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚጠቀስ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል።
ይህ በየዓመቱ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚታወቀው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የወደፊት ትውልድ ተስፋን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በየዓመቱ የሚካሄደው ይህ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሚሊየኖች ከዳር እስከ ዳር በዝናብና በብርድ ሳይበገሩ በመዝመት ምድርን የሚያለመልሙበት ህያው መድረክ ሆኗል።
በዚህ ዓመትም በይፋ በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ በመላው ኢትዮጵያ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተከናወነ ሲሆን፤ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላን ለማከናወንም ዝግጅት ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት ባስተላለፉት ጥሪ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም ታሪክ ለመጻፍ አስፈላጊው ዝግጅት ሁሉ እንዲደረግ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያውያን የተቀናጀ ክንድና ህብረት በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን ተክሎ ሌላ ተአምር ለማስመዝገብ የቀሩት አምስት ቀናት ብቻ መቅረቱንም ነው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት የገለጹት።
ይህ ታላቅ ጥረት የደን ሽፋንን በእጥፍ ከማሳደግ ባሻገር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የውሃ አካላትን ለማበልጸግና የግብርና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን፣ የሚተከሉት ችግኞች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ተክሎች እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥቅም የሚሰጡ የዛፍ ዝርያዎችን ያካተቱ በመሆናቸው ለሀገራችን የኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች ተማሪዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የጸጥታ አካላት፣ የመንግሥት ተቋማት፣ ባለሀብቶች፣ ሃይማኖታዊ ተቋማትና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጭምር በመሳተፍ መርሐ ግብሩ ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገራዊ አንድነት መገለጫ እንዲሆን አድርገውታል።
በመሆኑም በቀጣዮቹ ቀናት የሚካሄደው 800 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀምበር የመትከል ዘመቻ ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት፣ ለአየር ንብረት መቋቋም፣ ለምግብ ዋስትናና ለትውልድ ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብት ግንባታ የሚያበረክተውን ድርሻ የበለጠ በማጉላት ትልቅ አስተዋጽዖ ያበረክታል።
እያንዳንዱ ዜጋ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት የድርሻውን እንዲወጣ የሚጠይቀው ይህ ሀገራዊ ጥሪ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ ወጣቶች፣ አባቶች፣ እናቶችና ህፃናት እጅ ለእጅ ተያይዘው ወደ መስክ በመውጣት የራሳቸውን ታሪካዊ ዐሻራ እንዲያኖሩ በር የከፈተ ሆኗል።
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን የመትከል እቅድ የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጽናት፣ የህብረትና የልማት ታላቅ መግለጫ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሃብታቸው ላይ አዲስ ሕይወት የሚዘሩበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለም፣ አረንጓዴና የተባረከች ሀገር የሚያስረክቡበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ እና የመጠበቅ ባሕልን ማሳደግ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ የተተከለ ችግኝ ጸድቆ ለፍሬ እንዲበቃ ሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረትና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት የደን ሀብቷን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን የመቋቋም ጉዞ ዛሬ ላይ የሀገሪቱን ገጽታ ከመቀየር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚጠቀስ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል።
ይህ በየዓመቱ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚታወቀው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የወደፊት ትውልድ ተስፋን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በየዓመቱ የሚካሄደው ይህ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሚሊየኖች ከዳር እስከ ዳር በዝናብና በብርድ ሳይበገሩ በመዝመት ምድርን የሚያለመልሙበት ህያው መድረክ ሆኗል።
በዚህ ዓመትም በይፋ በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ በመላው ኢትዮጵያ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተከናወነ ሲሆን፤ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላን ለማከናወንም ዝግጅት ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት ባስተላለፉት ጥሪ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም ታሪክ ለመጻፍ አስፈላጊው ዝግጅት ሁሉ እንዲደረግ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያውያን የተቀናጀ ክንድና ህብረት በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን ተክሎ ሌላ ተአምር ለማስመዝገብ የቀሩት አምስት ቀናት ብቻ መቅረቱንም ነው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት የገለጹት።
ይህ ታላቅ ጥረት የደን ሽፋንን በእጥፍ ከማሳደግ ባሻገር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የውሃ አካላትን ለማበልጸግና የግብርና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን፣ የሚተከሉት ችግኞች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ተክሎች እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥቅም የሚሰጡ የዛፍ ዝርያዎችን ያካተቱ በመሆናቸው ለሀገራችን የኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች ተማሪዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የጸጥታ አካላት፣ የመንግሥት ተቋማት፣ ባለሀብቶች፣ ሃይማኖታዊ ተቋማትና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጭምር በመሳተፍ መርሐ ግብሩ ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገራዊ አንድነት መገለጫ እንዲሆን አድርገውታል።
በመሆኑም በቀጣዮቹ ቀናት የሚካሄደው 800 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀምበር የመትከል ዘመቻ ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት፣ ለአየር ንብረት መቋቋም፣ ለምግብ ዋስትናና ለትውልድ ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብት ግንባታ የሚያበረክተውን ድርሻ የበለጠ በማጉላት ትልቅ አስተዋጽዖ ያበረክታል።
እያንዳንዱ ዜጋ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት የድርሻውን እንዲወጣ የሚጠይቀው ይህ ሀገራዊ ጥሪ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ ወጣቶች፣ አባቶች፣ እናቶችና ህፃናት እጅ ለእጅ ተያይዘው ወደ መስክ በመውጣት የራሳቸውን ታሪካዊ ዐሻራ እንዲያኖሩ በር የከፈተ ሆኗል።
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን የመትከል እቅድ የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጽናት፣ የህብረትና የልማት ታላቅ መግለጫ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሃብታቸው ላይ አዲስ ሕይወት የሚዘሩበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለም፣ አረንጓዴና የተባረከች ሀገር የሚያስረክቡበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ እና የመጠበቅ ባሕልን ማሳደግ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ የተተከለ ችግኝ ጸድቆ ለፍሬ እንዲበቃ ሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረትና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
በዮናስ ጌትነት
7 days ago
የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ተጨባጭ ጉዞ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ላይ እያጋጠመ ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና ለመሻገር እየተወሰዱ ካሉ ርምጃዎች መካከል አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት አንደኛውና ዋነኛው ነው።
ኢትዮጵያ ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ መሰረቶች ውስጥ ቀዳሚው የሆነውን የታዳሽ ኃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራች ትገኛለች።
የመደመር መንግሥት ሀገሪቱ በታዳሽ የሀይል ምንጮች ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግርን እውን ለማድረግ በሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት አስመዝግቧል።
በውሃ፣ በፀሐይ፣ በንፋስ እና በጂኦተርማል ሀብቶች የታደለችው ኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦቷን በማዘመን የዜጎችን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ለቀጣናዊ ትስስር ቁልፍ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።
ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት የምስራቅ አፍሪካ የሀይል ማዕከል ለመሆን በምታደርገው ጥረት የኤሌክትሪክ ሀይል መሰረተ ልማት ዝርጋታ የሀገሪቱን የሁለገብ ዕድገት ለማፋጠን ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የሀይል አቅርቦትን አስተማማኝና ተደራሽ ማድረግ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ፓርኮችና የግብርና ተቋማት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚደረገው ጥረት አንኳር ጉዳይ ነው።
የሀገሪቱ የሀይል ምንጭ በዋናነት በውሃ ላይ የተመሰረተ ቢሆንም፤ በፀሐይና በንፋስ ሀይል እንዲታገዝ የሚደረገው ጥረት የላቀ ውጤት እያመጣ ይገኛል።
ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ የሀይል ዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ሲሆን፥ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ትኩረት ተሰጥቷል።
የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃት የዘርፉን ተስፋ የሚጨበጥ አድርገውታል።
በግንባታ ላይ የሚገኘው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በሀይል ልማት ቀጣናዊ ትስስርን ለመፍጠር የጀመረችውን ጉዞ ከዳር የማድረስ ቁመና ላይ መገኘቷን ያሳያል።
የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት መደገፍና የዜጎችን የኤሌክትሪክ ሀይል ፍላጎት የተሟላ ለማድረግ የሚሰራው የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት አቅም ተሻሽሏል።
ከንፋስ ኃይል፣ ከፀሐይ እና ከጂኦተርማል የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ይገኛል።
የኤሌክትሪክ ሀይል ከማመንጨት ስራው ጎን ለጎንም የሀይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዝግጁነትን የማሳደግ ተግባር መከናወኑ አስተማማኝ የሀይል አቅርቦት አቅም እየተገነባ እንደሆነ ያመላክታል።
በአጠቃላይ የኤሌክትሪክ ሀይል በማመንጨት ዜጎችን ተጠቃሚ የማድረግና ቀጣናዊ ትስስርን የማጎልበት እንቅስቃሴ ባለፉት ዓመታት ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል።
የዘርፉን አቅም በማጎልበት የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ፣ የከተማና ገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን እንዲሁም በኢነርጂ የቀጣናውን ሀገራት ይበልጥ ለማስተሳሰር የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ላይ እያጋጠመ ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና ለመሻገር እየተወሰዱ ካሉ ርምጃዎች መካከል አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት አንደኛውና ዋነኛው ነው።
ኢትዮጵያ ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ መሰረቶች ውስጥ ቀዳሚው የሆነውን የታዳሽ ኃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራች ትገኛለች።
የመደመር መንግሥት ሀገሪቱ በታዳሽ የሀይል ምንጮች ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግርን እውን ለማድረግ በሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት አስመዝግቧል።
በውሃ፣ በፀሐይ፣ በንፋስ እና በጂኦተርማል ሀብቶች የታደለችው ኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦቷን በማዘመን የዜጎችን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ለቀጣናዊ ትስስር ቁልፍ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።
ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት የምስራቅ አፍሪካ የሀይል ማዕከል ለመሆን በምታደርገው ጥረት የኤሌክትሪክ ሀይል መሰረተ ልማት ዝርጋታ የሀገሪቱን የሁለገብ ዕድገት ለማፋጠን ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የሀይል አቅርቦትን አስተማማኝና ተደራሽ ማድረግ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ፓርኮችና የግብርና ተቋማት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚደረገው ጥረት አንኳር ጉዳይ ነው።
የሀገሪቱ የሀይል ምንጭ በዋናነት በውሃ ላይ የተመሰረተ ቢሆንም፤ በፀሐይና በንፋስ ሀይል እንዲታገዝ የሚደረገው ጥረት የላቀ ውጤት እያመጣ ይገኛል።
ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ የሀይል ዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ሲሆን፥ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ትኩረት ተሰጥቷል።
የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃት የዘርፉን ተስፋ የሚጨበጥ አድርገውታል።
በግንባታ ላይ የሚገኘው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በሀይል ልማት ቀጣናዊ ትስስርን ለመፍጠር የጀመረችውን ጉዞ ከዳር የማድረስ ቁመና ላይ መገኘቷን ያሳያል።
የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት መደገፍና የዜጎችን የኤሌክትሪክ ሀይል ፍላጎት የተሟላ ለማድረግ የሚሰራው የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት አቅም ተሻሽሏል።
ከንፋስ ኃይል፣ ከፀሐይ እና ከጂኦተርማል የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ይገኛል።
የኤሌክትሪክ ሀይል ከማመንጨት ስራው ጎን ለጎንም የሀይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዝግጁነትን የማሳደግ ተግባር መከናወኑ አስተማማኝ የሀይል አቅርቦት አቅም እየተገነባ እንደሆነ ያመላክታል።
በአጠቃላይ የኤሌክትሪክ ሀይል በማመንጨት ዜጎችን ተጠቃሚ የማድረግና ቀጣናዊ ትስስርን የማጎልበት እንቅስቃሴ ባለፉት ዓመታት ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል።
የዘርፉን አቅም በማጎልበት የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ፣ የከተማና ገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን እንዲሁም በኢነርጂ የቀጣናውን ሀገራት ይበልጥ ለማስተሳሰር የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
7 days ago
ከውኃ ኃይል ባሻገር፤ የኢትዮጵያ አዲሱ የኒዩክሌር ኃይል ጉዞ እና የብልጽግና ተስፋ
****************
ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት የኃይል አቅርቦትና ፍላጎቷን ለማመጣጠን ከውኃ እስከ ንፋስ፣ ከጂኦተርማል እስከ ፀሐይ ኃይል ማመንጫዎችን በመገንባት በአፍሪካ አህጉር ተምሳሌታዊ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች።
ከጊቤ I እስከ ኮይሻ ያሉ ግዙፍ የውኃ ኃይል ማመንጫዎች እንዲሁም ከአባ ሳሙኤል እስከ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዘረጉት መሠረተ ልማቶች ማኅበረሰቡንና የአምራች ኢንዱስትሪዎችን በማንቀሳቀስ ለሀገራችን ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም ሆነዋል።
ሆኖም ዘላቂ የኃይል ፍላጎትን በተወሰኑ አማራጮች ብቻ ማሟላት አዋጭ አለመሆኑን የተረዳው መንግሥት፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ የኒዩክሌር ኃይል አስፈላጊነትን በመገንዘብ ስትራቴጂካዊ የኃይል አቅርቦት ፍኖተ ካርታ በማዘጋጀት ወደ ተግባር ገብቷል።
የኒዩክሌር ቴክኖሎጂ እንደ ፀሐይና ንፋስ ከአየር ንብረት ጋር የማይቀያየርና በቀን 24 ሰዓት በሳምንት 7 ቀን ያለማቋረጥ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው በመሆኑ ለትላልቅ ኢንዱስትሪዎች፣ ለአምራች ሴክተሮችና ለቴክኖሎጂ ማዕከላት የማይንቀሳቀስ መሠረት ይጥላል።
ይህ ቴክኖሎጂ ኤሌክትሪክ በሚያመነጭበት ወቅት ምንም ዓይነት የካርቦን ልቀት የሌለው በመሆኑ ለአየር ንብረት ለውጥ ትግልና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው።
በተጨማሪም ከቅሪተ አካል ነዳጆች የዋጋ መዋዥቅና ጥገኝነት ነፃ የሚያደርግ ሲሆን፣ ከኃይል ማመንጨት ባለፈ በሕክምና፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና ውኃ ማጣራት እንዲሁም ለብዙ ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ አለው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ፈረንሳይ 70 በመቶ የኤሌክትሪክ ፍላጎቷን በኒዩክሌር በመሸፈን አነስተኛ የካርቦን ልቀት ማረጋገጥ ስትችል፤ አሜሪካ፣ ቻይና፣ ደቡብ ኮሪያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶችም በዘርፉ ትልቅ ስኬት አስመዝግበዋል።
ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ በመቅሰም ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል የኒዩክሌር ኃይል ፍኖተ ካርታ ቀርጻለች።
ሀገራችን በዘርፉ የተሻለ ልምድና ተሞክሮ ካለው የሩሲያው ሮሳቶም (Rosatom) ስቴት ኮርፖሬሽን ጋር ስትራቴጂካዊ ስምምነት ያደረገች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም ጠንካራ የደህንነት መሠረተ ልማትና የፋይናንስ ዝግጅት በማጠናከር ቴክኖሎጂውን ለኢንዱስትሪ፣ ለሕክምናና ለሳይንስ ዕድገት ለማዋል የጀመረችውን ጉዞ አጠናክራ ቀጥላለች።
በመሐመድ ፊጣሞ
#ethiopia #nuclearenergy #greeneconomy #sustainabledevelopment #energytransition
****************
ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት የኃይል አቅርቦትና ፍላጎቷን ለማመጣጠን ከውኃ እስከ ንፋስ፣ ከጂኦተርማል እስከ ፀሐይ ኃይል ማመንጫዎችን በመገንባት በአፍሪካ አህጉር ተምሳሌታዊ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች።
ከጊቤ I እስከ ኮይሻ ያሉ ግዙፍ የውኃ ኃይል ማመንጫዎች እንዲሁም ከአባ ሳሙኤል እስከ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዘረጉት መሠረተ ልማቶች ማኅበረሰቡንና የአምራች ኢንዱስትሪዎችን በማንቀሳቀስ ለሀገራችን ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም ሆነዋል።
ሆኖም ዘላቂ የኃይል ፍላጎትን በተወሰኑ አማራጮች ብቻ ማሟላት አዋጭ አለመሆኑን የተረዳው መንግሥት፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ የኒዩክሌር ኃይል አስፈላጊነትን በመገንዘብ ስትራቴጂካዊ የኃይል አቅርቦት ፍኖተ ካርታ በማዘጋጀት ወደ ተግባር ገብቷል።
የኒዩክሌር ቴክኖሎጂ እንደ ፀሐይና ንፋስ ከአየር ንብረት ጋር የማይቀያየርና በቀን 24 ሰዓት በሳምንት 7 ቀን ያለማቋረጥ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው በመሆኑ ለትላልቅ ኢንዱስትሪዎች፣ ለአምራች ሴክተሮችና ለቴክኖሎጂ ማዕከላት የማይንቀሳቀስ መሠረት ይጥላል።
ይህ ቴክኖሎጂ ኤሌክትሪክ በሚያመነጭበት ወቅት ምንም ዓይነት የካርቦን ልቀት የሌለው በመሆኑ ለአየር ንብረት ለውጥ ትግልና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው።
በተጨማሪም ከቅሪተ አካል ነዳጆች የዋጋ መዋዥቅና ጥገኝነት ነፃ የሚያደርግ ሲሆን፣ ከኃይል ማመንጨት ባለፈ በሕክምና፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና ውኃ ማጣራት እንዲሁም ለብዙ ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ አለው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ፈረንሳይ 70 በመቶ የኤሌክትሪክ ፍላጎቷን በኒዩክሌር በመሸፈን አነስተኛ የካርቦን ልቀት ማረጋገጥ ስትችል፤ አሜሪካ፣ ቻይና፣ ደቡብ ኮሪያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶችም በዘርፉ ትልቅ ስኬት አስመዝግበዋል።
ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ በመቅሰም ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል የኒዩክሌር ኃይል ፍኖተ ካርታ ቀርጻለች።
ሀገራችን በዘርፉ የተሻለ ልምድና ተሞክሮ ካለው የሩሲያው ሮሳቶም (Rosatom) ስቴት ኮርፖሬሽን ጋር ስትራቴጂካዊ ስምምነት ያደረገች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም ጠንካራ የደህንነት መሠረተ ልማትና የፋይናንስ ዝግጅት በማጠናከር ቴክኖሎጂውን ለኢንዱስትሪ፣ ለሕክምናና ለሳይንስ ዕድገት ለማዋል የጀመረችውን ጉዞ አጠናክራ ቀጥላለች።
በመሐመድ ፊጣሞ
#ethiopia #nuclearenergy #greeneconomy #sustainabledevelopment #energytransition
8 days ago
ለመጪው ትውልድ የተተከለ ተስፋ፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ጉዞ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለብዙ ዓመታት ከፍተኛ የመሬት መሸርሸር ተደጋጋሚ ድርቅ እና የደን ሽፋን መሳሳት ለኢትዮጵያ ሥነ ምህዳራዊ ሚዛን እና የግብርና ምርታማነት ትልቅ አደጋ ደቅነው ቆይተዋል።
አሁን ግን የአረንጓዴ ልማትና የደን ሽፋን ንቅናቄ መልክዓ ምድርን እየለወጠ፤ በመላ ሀገሪቱ በተደረገ ስልታዊ አመራር ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ታሪኳን በአዲስ መልክ እየጻፈች ትገኛለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እየተመራች ሀገሪቱ በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ እጅግ ግዙፍ ከሆኑት ተፈጥሮ ተኮር መፍትሔዎች አንዱን እየተገበረች ትገኛለች::
ይህም በሚሊየን የሚቆጠር ሄክታር መሬት በማንሰራራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሲሆን ÷ ወደ አረንጓዴ መሪነት የሚያሸጋግረው የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የአካባቢ ጥበቃ ግብ ግልጽ እና ለውጥ አምጪ ነው፡፡
እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ማሳደግ እና ከ54 ሚሊየን ሄክታር በላይ የተበላሸ መሬት እንዲያገግም በማድረግና የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤን ለሀገራዊ ብልጽግና፣ ለአየር ንብረት ደህንነት እና ለግብርና መነቃቃት መሠረታዊ ለውጥ ተደርጎ ይወሰዳል።
ከደን ልማት አጀንዳው ስልታዊ ማዕቀፎች አንዱ በሆነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም በየዓመቱ በክረምት ወቅት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማንቀሳቀስ በመላ ሀገሪቱ በቢሊየን የሚቆጠሩ ችግኞችን በስኬት መተከል ተችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለሀገር በቀል ዛፎች ቅድሚያ መስጠት በችግኝ ጣቢያዎች ምርት ላይ ትልቅ ትኩረት አግኝቷል፡፡
ለተስማሚ ሥነ ምህዳር በየዓመቱ ከሚተከሉት ችግኞች የሀገር በቀል ዛፎች የአካባቢውን አየር ንብረት ለማሻሻል፣ የመሬት መሸርሸርን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ውኃ ተፋሰሶችን ለመጠበቅ ታስበው የተመረጡ ናቸው።
መንግሥት የፍራፍሬ ችግኞች እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ እና የእንስሳት መኖ እፅዋትን በስፋት እንዲተከሉ በማበረታታት እና አርሶ አደሮችን ከንግድ ሰንሰለቶች ጋር በማገናኘት ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ እንዲሁም የቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ወጪ ንግድን እንዲፋጠን በማድረግ ላይ ነው።
በደን መልሶ ማልማት በበጎ ፈቃድ የተከናወኑ በገንዘብ የማይለኩ አካባቢያዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡
በከፍተኛ ቦታዎች ላይ የተካሄደው ደን ልማት የከርሰ-ምድር ውኃ ክምችትን ያሻሻለ ሲሆን÷ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ላይ የሚያርፈውን የደለል ክምችት ቀንሶታል።
በቁልቁለታማና ኮረብታ ቦታዎች ላይ የተሰሩ እርከኖች እና የተተከሉ ዛፎች ለም አፈር እንዳይሸረሸር በመከላከል ለምግብ ምርት የሚሆን ለም መሬት እንዲጠበቅ ማድረግ አስችሏል።
በደን ልማት መነሻነት የማህበር እና የግል ችግኝ ጣቢያዎች መስፋፋት በተለይም ለወጣቶች ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን የፈጠረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ የደን ልማት ጥረቶች የተባበሩት መንግሥታት የሥነ ምህዳር ማገገሚያ አስር ዓመት፣ የቦን ፈተና እና ሀገራዊ የካርቦን ቅነሳ ቃልኪዳኖችን ጨምሮ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በቀጥታ የሚጣጣሙ ናቸው።
በሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ የበረሃማነትን ሒደት መመለስ እንደሚቻል በማስመስከር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ለዓለም አርአያ ሆና እያገለገለች ነው።
ይህ ዓለም አቀፍ መሪነት ያለው የደን ልማት እና የቀጣይ መንገድ የመደመር መንግሥት ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ሀገር ለማስረከብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በምሕረት ደምሴ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለብዙ ዓመታት ከፍተኛ የመሬት መሸርሸር ተደጋጋሚ ድርቅ እና የደን ሽፋን መሳሳት ለኢትዮጵያ ሥነ ምህዳራዊ ሚዛን እና የግብርና ምርታማነት ትልቅ አደጋ ደቅነው ቆይተዋል።
አሁን ግን የአረንጓዴ ልማትና የደን ሽፋን ንቅናቄ መልክዓ ምድርን እየለወጠ፤ በመላ ሀገሪቱ በተደረገ ስልታዊ አመራር ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ታሪኳን በአዲስ መልክ እየጻፈች ትገኛለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እየተመራች ሀገሪቱ በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ እጅግ ግዙፍ ከሆኑት ተፈጥሮ ተኮር መፍትሔዎች አንዱን እየተገበረች ትገኛለች::
ይህም በሚሊየን የሚቆጠር ሄክታር መሬት በማንሰራራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሲሆን ÷ ወደ አረንጓዴ መሪነት የሚያሸጋግረው የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የአካባቢ ጥበቃ ግብ ግልጽ እና ለውጥ አምጪ ነው፡፡
እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ማሳደግ እና ከ54 ሚሊየን ሄክታር በላይ የተበላሸ መሬት እንዲያገግም በማድረግና የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤን ለሀገራዊ ብልጽግና፣ ለአየር ንብረት ደህንነት እና ለግብርና መነቃቃት መሠረታዊ ለውጥ ተደርጎ ይወሰዳል።
ከደን ልማት አጀንዳው ስልታዊ ማዕቀፎች አንዱ በሆነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም በየዓመቱ በክረምት ወቅት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማንቀሳቀስ በመላ ሀገሪቱ በቢሊየን የሚቆጠሩ ችግኞችን በስኬት መተከል ተችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለሀገር በቀል ዛፎች ቅድሚያ መስጠት በችግኝ ጣቢያዎች ምርት ላይ ትልቅ ትኩረት አግኝቷል፡፡
ለተስማሚ ሥነ ምህዳር በየዓመቱ ከሚተከሉት ችግኞች የሀገር በቀል ዛፎች የአካባቢውን አየር ንብረት ለማሻሻል፣ የመሬት መሸርሸርን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ውኃ ተፋሰሶችን ለመጠበቅ ታስበው የተመረጡ ናቸው።
መንግሥት የፍራፍሬ ችግኞች እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ እና የእንስሳት መኖ እፅዋትን በስፋት እንዲተከሉ በማበረታታት እና አርሶ አደሮችን ከንግድ ሰንሰለቶች ጋር በማገናኘት ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ እንዲሁም የቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ወጪ ንግድን እንዲፋጠን በማድረግ ላይ ነው።
በደን መልሶ ማልማት በበጎ ፈቃድ የተከናወኑ በገንዘብ የማይለኩ አካባቢያዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡
በከፍተኛ ቦታዎች ላይ የተካሄደው ደን ልማት የከርሰ-ምድር ውኃ ክምችትን ያሻሻለ ሲሆን÷ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ላይ የሚያርፈውን የደለል ክምችት ቀንሶታል።
በቁልቁለታማና ኮረብታ ቦታዎች ላይ የተሰሩ እርከኖች እና የተተከሉ ዛፎች ለም አፈር እንዳይሸረሸር በመከላከል ለምግብ ምርት የሚሆን ለም መሬት እንዲጠበቅ ማድረግ አስችሏል።
በደን ልማት መነሻነት የማህበር እና የግል ችግኝ ጣቢያዎች መስፋፋት በተለይም ለወጣቶች ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን የፈጠረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ የደን ልማት ጥረቶች የተባበሩት መንግሥታት የሥነ ምህዳር ማገገሚያ አስር ዓመት፣ የቦን ፈተና እና ሀገራዊ የካርቦን ቅነሳ ቃልኪዳኖችን ጨምሮ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በቀጥታ የሚጣጣሙ ናቸው።
በሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ የበረሃማነትን ሒደት መመለስ እንደሚቻል በማስመስከር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ለዓለም አርአያ ሆና እያገለገለች ነው።
ይህ ዓለም አቀፍ መሪነት ያለው የደን ልማት እና የቀጣይ መንገድ የመደመር መንግሥት ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ሀገር ለማስረከብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በምሕረት ደምሴ
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢትዮጵያ እያሻቀበ የመጣው የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት፣ 92 ሚሊዮን የሚጠጋ የሀገሪቱን ሕዝብ "ጤናማ የምግብ ሥርዓት" መከተል እንዳይችል ማድረጉን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የቅርብ ጊዜ የምግብ ዋስትና ሪፖርት ይፋ አደረገ።
ሪፖርቱ እንዳመለከተው፣ በኢትዮጵያ ጤናማ የምግብ ሥርዓትን ለማስጠበቅ በነፍስ ወከፍ የሚወጣው ወጪ በቀጠናው (ምሥራቅ አፍሪካ) ከፍተኛው ሆኗል። ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት (2025) በኢትዮጵያ አንድ ሰው ጤናማ ምግብ ለማግኘት በቀን 4 ነጥብ 7 ዶላር ማውጣት የነበረበት ሲሆን፣ ይህ አኃዝ ከጎረቤት ሀገራቱ ኬንያ፣ ኡጋንዳ እና ታንዛኒያ በእጅጉ የላቀ ነው።
ከፈረንጆቹ 2023 እስከ 2025 ባለው ጊዜ ውስጥም 60 በመቶ የሚሆነው ኢትዮጵያዊ "መካከለኛ" እና "ከፍተኛ" የምግብ ዋስትና እጦት ገጥሞት እንደነበር ሪፖርቱ አብራርቷል። ይሁን እንጂ ይህ የተመድ ሪፖርት ባለፉት ዓመታት በጦርነት ክፉኛ የተጎዳውን የትግራይ ክልል መረጃ ያላካተተ በመሆኑ፣ ሀገራዊ የምግብ ቀውሱ አኃዝ ሪፖርቱ ካቀረበው እጅግ የከፋ ሊሆን እንደሚችል የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይገምታሉ።
ይህ የተመድ ሪፖርት የሚያሳየው የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ቀውስ በዜጎች የእለት ተእለት ህይወት እና ጤና ላይ እያደረሰ ያለውን አውዳሚ ተጽእኖ ነው። አንድ ኢትዮጵያዊ ጤናማ ምግብ ለመመገብ በቀን 4.7 ዶላር (በወቅቱ የባንክ ምንዛሪ ወደ 500 ብር ገደማ) ማውጣት አለበት ማለት፣ አብዛኛው የሀገሪቱ ህዝብ በቀን ከሚያገኘው አጠቃላይ ገቢ በእጅጉ የላቀ ነው።
ይህ የዋጋ ንረት ሀገሪቱ በግብርናው ዘርፍ እያመጣች ነው ከምትለው የምርት እድገት ትርክት ጋር በእጅጉ ይቃረናል። በተጨማሪም 92 ሚሊዮን ህዝብ (ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው ዜጋ) ጤናማ ምግብ የማግኘት አቅም የለውም ማለት፤ ሀገሪቱ ወደፊት ለከፍተኛ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት፣ በሽታ እና ተያያዥ ማህበራዊ ቀውሶች እየተጋለጠች መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ አደገኛ አመልካች ነው። መንግስት የፖለቲካ እና የጸጥታ ቀውሶችን ፈትቶ ምርታማነትን ካላሳደገ እና የዋጋ ግሽበቱን መቆጣጠር ካልቻለ፣ ይህ የምግብ ዋስትና እጦት ወደ ሀገራዊ የህልውና አደጋ ማምራቱ የማይቀር መሆኑን ይህ ክስተት በግልጽ ያሳስባል።
ሪፖርቱ እንዳመለከተው፣ በኢትዮጵያ ጤናማ የምግብ ሥርዓትን ለማስጠበቅ በነፍስ ወከፍ የሚወጣው ወጪ በቀጠናው (ምሥራቅ አፍሪካ) ከፍተኛው ሆኗል። ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት (2025) በኢትዮጵያ አንድ ሰው ጤናማ ምግብ ለማግኘት በቀን 4 ነጥብ 7 ዶላር ማውጣት የነበረበት ሲሆን፣ ይህ አኃዝ ከጎረቤት ሀገራቱ ኬንያ፣ ኡጋንዳ እና ታንዛኒያ በእጅጉ የላቀ ነው።
ከፈረንጆቹ 2023 እስከ 2025 ባለው ጊዜ ውስጥም 60 በመቶ የሚሆነው ኢትዮጵያዊ "መካከለኛ" እና "ከፍተኛ" የምግብ ዋስትና እጦት ገጥሞት እንደነበር ሪፖርቱ አብራርቷል። ይሁን እንጂ ይህ የተመድ ሪፖርት ባለፉት ዓመታት በጦርነት ክፉኛ የተጎዳውን የትግራይ ክልል መረጃ ያላካተተ በመሆኑ፣ ሀገራዊ የምግብ ቀውሱ አኃዝ ሪፖርቱ ካቀረበው እጅግ የከፋ ሊሆን እንደሚችል የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይገምታሉ።
ይህ የተመድ ሪፖርት የሚያሳየው የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ቀውስ በዜጎች የእለት ተእለት ህይወት እና ጤና ላይ እያደረሰ ያለውን አውዳሚ ተጽእኖ ነው። አንድ ኢትዮጵያዊ ጤናማ ምግብ ለመመገብ በቀን 4.7 ዶላር (በወቅቱ የባንክ ምንዛሪ ወደ 500 ብር ገደማ) ማውጣት አለበት ማለት፣ አብዛኛው የሀገሪቱ ህዝብ በቀን ከሚያገኘው አጠቃላይ ገቢ በእጅጉ የላቀ ነው።
ይህ የዋጋ ንረት ሀገሪቱ በግብርናው ዘርፍ እያመጣች ነው ከምትለው የምርት እድገት ትርክት ጋር በእጅጉ ይቃረናል። በተጨማሪም 92 ሚሊዮን ህዝብ (ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው ዜጋ) ጤናማ ምግብ የማግኘት አቅም የለውም ማለት፤ ሀገሪቱ ወደፊት ለከፍተኛ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት፣ በሽታ እና ተያያዥ ማህበራዊ ቀውሶች እየተጋለጠች መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ አደገኛ አመልካች ነው። መንግስት የፖለቲካ እና የጸጥታ ቀውሶችን ፈትቶ ምርታማነትን ካላሳደገ እና የዋጋ ግሽበቱን መቆጣጠር ካልቻለ፣ ይህ የምግብ ዋስትና እጦት ወደ ሀገራዊ የህልውና አደጋ ማምራቱ የማይቀር መሆኑን ይህ ክስተት በግልጽ ያሳስባል።
Sponsored by
Surafel
8 days ago
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ23 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰበሰበ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ23 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)።
ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት በግብርና ዘርፍ የላቀ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በእርሻ ዘርፍ በሁሉም የምርት ወቅቶች ከ801 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑንና የምርት ዕድገቱም ከ2014 መነሻ ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ60 ነጥብ 3 በመቶ ማደጉን አስረድተዋል።
በተጨማሪም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ5 ሺህ 700 ሄክታር በላይ ማሳ በማልማት ከ192 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር 390 ሚሊየን ሊትር የወተት፣ 362 ሚሊየን እንቁላል፣ 79 ሺህ ቶን በላይ የማርና 81 ሺህ ቶን በላይ የስጋ ምርት ለገበያ ማቅረብ መቻሉንም አመልክተዋል።
ከ61 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ በመላክ ከመነሻ ዓመቱ የ74 በመቶ እድገት መመዝገቡንና በሕገ ወጥ ቡና ዝውውር ቁጥጥርም 33 ሚሊየን ብር ወደ መንግሥት ካዝና ገቢ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል።
የኅብረት ሥራ ማህበራት ከወጪ ንግድ 2 ነጥብ 89 ሚሊየን ዶላር ያስገኙ ሲሆን፤ በአደጋ ስጋት ሥራ አመራርም 86 በመቶ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ማሸጋገር ተችሏል ነው ያሉት።
በሰብል ምርምር 19 የገብስ ዘረ መሎች የተሰበሰቡ ሲሆን በአጃ፣ ሩዝ እና በተሻሻሉ የጤፍ ዝርያዎች ምርታማነት ላይ የሙከራ ጥናቶች መካሄዱን ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የገንዲ በሽታ ስጋት ጠቋሚ ካርታ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በማህበረሰብ አቀፍ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ፕሮጀክት 1 ሺህ 22 የዘር በጎች ተመርጠው 831 የተሻሻሉ በጎች ለአርሶ አደሩ መሰራጨታቸውን አንስተዋል።
በመጥፋት ላይ ያሉ ሀገር በቀል ዛፎችንና የሸኮ ዳልጋ ከብት ዝርያን የመጠበቅ ሥራ ተከናውኗል ነው ያሉት።
ከ88 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት የደን ሽፋኑን ከ43 ነጥብ 85 በመቶ ወደ 44 ነጥብ 65 በመቶ ማሳደግ የተቻለ ሲሆን፤ ከደን ውጤቶችም ከ11 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በላይ የሮያሊቲ ክፍያ መሰብሰቡን አመልክተዋል።
የከተሞችን የቆሻሻ ችግር ለመቅረፍ በርካታ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው ለ509 አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ይሁንታ ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል የላከው መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ23 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)።
ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት በግብርና ዘርፍ የላቀ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በእርሻ ዘርፍ በሁሉም የምርት ወቅቶች ከ801 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑንና የምርት ዕድገቱም ከ2014 መነሻ ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ60 ነጥብ 3 በመቶ ማደጉን አስረድተዋል።
በተጨማሪም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ5 ሺህ 700 ሄክታር በላይ ማሳ በማልማት ከ192 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር 390 ሚሊየን ሊትር የወተት፣ 362 ሚሊየን እንቁላል፣ 79 ሺህ ቶን በላይ የማርና 81 ሺህ ቶን በላይ የስጋ ምርት ለገበያ ማቅረብ መቻሉንም አመልክተዋል።
ከ61 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ በመላክ ከመነሻ ዓመቱ የ74 በመቶ እድገት መመዝገቡንና በሕገ ወጥ ቡና ዝውውር ቁጥጥርም 33 ሚሊየን ብር ወደ መንግሥት ካዝና ገቢ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል።
የኅብረት ሥራ ማህበራት ከወጪ ንግድ 2 ነጥብ 89 ሚሊየን ዶላር ያስገኙ ሲሆን፤ በአደጋ ስጋት ሥራ አመራርም 86 በመቶ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ማሸጋገር ተችሏል ነው ያሉት።
በሰብል ምርምር 19 የገብስ ዘረ መሎች የተሰበሰቡ ሲሆን በአጃ፣ ሩዝ እና በተሻሻሉ የጤፍ ዝርያዎች ምርታማነት ላይ የሙከራ ጥናቶች መካሄዱን ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የገንዲ በሽታ ስጋት ጠቋሚ ካርታ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በማህበረሰብ አቀፍ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ፕሮጀክት 1 ሺህ 22 የዘር በጎች ተመርጠው 831 የተሻሻሉ በጎች ለአርሶ አደሩ መሰራጨታቸውን አንስተዋል።
በመጥፋት ላይ ያሉ ሀገር በቀል ዛፎችንና የሸኮ ዳልጋ ከብት ዝርያን የመጠበቅ ሥራ ተከናውኗል ነው ያሉት።
ከ88 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት የደን ሽፋኑን ከ43 ነጥብ 85 በመቶ ወደ 44 ነጥብ 65 በመቶ ማሳደግ የተቻለ ሲሆን፤ ከደን ውጤቶችም ከ11 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በላይ የሮያሊቲ ክፍያ መሰብሰቡን አመልክተዋል።
የከተሞችን የቆሻሻ ችግር ለመቅረፍ በርካታ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው ለ509 አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ይሁንታ ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል የላከው መረጃ ያመላክታል።
9 days ago
እንደምን አደራችሁ
የሌማት ትሩፋት - ከጓሮ የተበሰረ ሀገራዊ ህዳሴ
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ምግብን በራስ አቅም ለመሸፈንና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዘመናዊና ፈጣን ለውጥ የሚያመጡ በርካታ ሀገራዊ ንቅናቄዎችን ተግባራዊ እያደረገች ነው።
ከእነዚህም መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ይፋ የተደረገው "የሌማት ትሩፋት" ንቅናቄ የብዙ ኢትዮጵያውያንን እና የሀገሪቱን የምግብ ስርዓት መልክ እየቀየረ ይገኛል።
የንቅናቄው ዓላማ በዋናነት የወተት፣ የዶሮ፣ የማር፣ የሥጋና የዓሣ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን ማረጋገጥና የኢኮኖሚ አቅምን መገንባት ነው።
የሌማት ትሩፋት ከጓሮ እስከ ገበያ በተጨባጭ ያመጣቸው ለውጦች በርካታ ናቸው፡፡
ከእነዚህም ውስጥ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በወተትና ሥጋ ምርት፣ በዶሮና እንቁላል ልማት፣ በንብ እርባታና የዓሣ ልማት የመጡት ለውጦችና መነሳሳቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው፡፡
በሌላ በኩል የሌማት ትሩፋት የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በማሳደግ በተለይም ህፃናትና ነፍሰ ጡር እናቶች የወተት፣ እንቁላልና ሥጋ ተጠቃሚነታቸው እንዲጨመር በማድረግ የመቀንጨርና የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።
በተጨማሪም ለወጣቶችና ሴቶች በርካታ የስራ እድሎች የፈጠረ ሲሆን የዶሮ እርባታ፣ የወተት ማሰባሰብና ማዘጋጀት፣ እንዲሁም የመኖ ዝግጅት አዳዲስ የንግድ መስኮች እየሆኑ መጥተዋል።
የሌማት ትሩፋት አርሶ አደሮችና የከተማ ነዋሪዎች ከራሳቸው ፍጆታ የተረፈውን ምርት ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ ማግኘት እንዲችሉም እድል ፈጥሯል፡፡
በዚህም የቤተሰብን የኢኮኖሚ አቅም በማጠናከር ድህነትን ለመቀነስ ጉልህ ሚና እተጫወተ ይገኛል።
ንቅናቄው የከተማ ግብርናን ባህል በማሳደግ በከተሞች አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች የጓሮ ቦታቸውን፣ በረንዳቸውንና ክፍት ቦታዎችን በመጠቀም አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የዶሮና ወተት ልማት ላይ በስፋት እንዲሰማሩ እያደረገ ነው።
የሌማት ትሩፋት - ከጓሮ የተበሰረ ሀገራዊ ህዳሴ
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ምግብን በራስ አቅም ለመሸፈንና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዘመናዊና ፈጣን ለውጥ የሚያመጡ በርካታ ሀገራዊ ንቅናቄዎችን ተግባራዊ እያደረገች ነው።
ከእነዚህም መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ይፋ የተደረገው "የሌማት ትሩፋት" ንቅናቄ የብዙ ኢትዮጵያውያንን እና የሀገሪቱን የምግብ ስርዓት መልክ እየቀየረ ይገኛል።
የንቅናቄው ዓላማ በዋናነት የወተት፣ የዶሮ፣ የማር፣ የሥጋና የዓሣ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን ማረጋገጥና የኢኮኖሚ አቅምን መገንባት ነው።
የሌማት ትሩፋት ከጓሮ እስከ ገበያ በተጨባጭ ያመጣቸው ለውጦች በርካታ ናቸው፡፡
ከእነዚህም ውስጥ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በወተትና ሥጋ ምርት፣ በዶሮና እንቁላል ልማት፣ በንብ እርባታና የዓሣ ልማት የመጡት ለውጦችና መነሳሳቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው፡፡
በሌላ በኩል የሌማት ትሩፋት የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በማሳደግ በተለይም ህፃናትና ነፍሰ ጡር እናቶች የወተት፣ እንቁላልና ሥጋ ተጠቃሚነታቸው እንዲጨመር በማድረግ የመቀንጨርና የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።
በተጨማሪም ለወጣቶችና ሴቶች በርካታ የስራ እድሎች የፈጠረ ሲሆን የዶሮ እርባታ፣ የወተት ማሰባሰብና ማዘጋጀት፣ እንዲሁም የመኖ ዝግጅት አዳዲስ የንግድ መስኮች እየሆኑ መጥተዋል።
የሌማት ትሩፋት አርሶ አደሮችና የከተማ ነዋሪዎች ከራሳቸው ፍጆታ የተረፈውን ምርት ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ ማግኘት እንዲችሉም እድል ፈጥሯል፡፡
በዚህም የቤተሰብን የኢኮኖሚ አቅም በማጠናከር ድህነትን ለመቀነስ ጉልህ ሚና እተጫወተ ይገኛል።
ንቅናቄው የከተማ ግብርናን ባህል በማሳደግ በከተሞች አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች የጓሮ ቦታቸውን፣ በረንዳቸውንና ክፍት ቦታዎችን በመጠቀም አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የዶሮና ወተት ልማት ላይ በስፋት እንዲሰማሩ እያደረገ ነው።
10 days ago
የኢትዮጵያ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ እመርታ
****************
ኢትዮጵያ ግብርና መር ኢኮኖሚዋን ወደ ማኑፋክቸሪንግ እና ኢንዱስትሪ ለማሸጋገር በምታደርገው ጥረት፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ማሳደጓ ጠንካራ መዋቅራዊ መደላድል እየፈጠረ ይገኛል።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ማዕቀፍ የተተገበሩት ፖሊሲዎች የፓርኮቹን አስተዳደር ወደ ግል ዘርፉ በማሸጋገር የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መዋቅር ሙሉ በሙሉ እየቀየሩት ነው።
ይህ ታሪካዊ ሽግግር በተለይም አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ ረገድ አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል።
በማሳያነትም በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ብቻ ከ750 ሚሊዮን ዶላር በላይ የመነሻ ካፒታል ያስመዘገቡ 166 አዳዲስ ባለሀብቶች ወደ ዘርፉ ተቀላቅለዋል።
ይበልጥ ተስፋ የሚሰጠው ደግሞ ከእነዚህ ውስጥ 84 በመቶ የሚሆኑት የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች መሆናቸው ነው። ይህ አዲሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም የፈጠረውን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት እና አቅም በግልጽ የሚያሳይ ነው።
ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖቹ በሥራ ዕድል ፈጠራ በኩል የዜጎችን በተለይም የወጣት ሴቶችን ሕይወት በተጨባጭ እየቀየሩ ነው። በመላው ሀገራችን በሚገኙ ፓርኮች ውስጥ ከ100 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀጥተኛና ቋሚ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።
በኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ትክክለኛ የኢንዱስትሪ ግብዓት ትስስር በመፍጠር የአርሶ አደሩን ምርት ከፋብሪካዎች ጋር በቀጥታ ማስተሳሰር ተችሏል። እስካሁን ባለው ሂደት ከ100 ሺህ በላይ አምራቾች እና አርሶ አደሮች ከትላልቅ ገዢዎች ጋር በቀጥታ ተገናኝተዋል።
በዚህም በአርሶ አደሮች እና በፋብሪካዎች መካከል ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የንግድ ግብይት መፈጸሙ፣ የኢንዱስትሪው ትስስር ምን ያህል ወደ ታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል እንደወረደ ያመላክታል።
የውጭ ምንዛሬን በማመንጨት እና የገቢ ምርቶችን በመተካት በኩል የተመዘገቡት ስኬቶች የኢትዮጵያን የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ።
በ2018 በጀት ዓመት ፓርኮቹ ከወጪ ንግድ 266.9 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት በታሪካቸው ከፍተኛ የተባለ ውጤት አስመዝግበዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ከ26.7 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን የገቢ ምርቶች በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ታድገዋል።
ይህ በፓርኮች የታየው ስኬት በሀገር አቀፍ ደረጃ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስተባባሪነት እየተተገበረ ካለው "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ጋር ተጣምሮ ታላቅ ሀገራዊ ውጤት አምጥቷል።
ንቅናቄው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 13 በመቶ ያሳደገው ሲሆን፣ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ የገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት አስችሏል።
ለእነዚህ ተጨባጭ ለውጦች እና ስኬቶች በዋናነት በምክንያትነት የሚጠቀሰው በቅርቡ የፀደቀው የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጅ እና መንግሥት ያቀረባቸው ሰፊ ማበረታቻዎች ናቸው።
አዲሱ የሕግ ማዕቀፍ ፓርኮቹን በጨርቃጨርቅ ምርት ላይ ብቻ ከነበረ ጥገኝነት አውጥቶ ግብርናን፣ ሳይንስን እና የሎጂስቲክስ አገልግሎትን እንዲያካትቱ አድርጓል።
ከዚህም በተጨማሪ የጉምሩክ ቀረጥ ነፃ መብቶች፣ የዜሮ ምጣኔ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ለኤክስፖርት አምራቾች የተሰጡ የአምስት ዓመት የግብር እፎይታዎች፣ እንዲሁም የውጭ ሀገር ባንኮች በዞኖቹ ውስጥ በነፃነት እንዲሠሩ መፈቀዱ ዘርፉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ አድርጎታል።
የጥራት፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የሠራተኞች ደህንነት (ISO) ደረጃዎችን ያካተተ የተቀናጀ የአመራር ሥርዓት መዘርጋቱም የኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዕድገት ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ጽኑ መሠረት ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #industrialparks #specialeconomiczones #investinethiopia #ethiopiatamirt
****************
ኢትዮጵያ ግብርና መር ኢኮኖሚዋን ወደ ማኑፋክቸሪንግ እና ኢንዱስትሪ ለማሸጋገር በምታደርገው ጥረት፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ማሳደጓ ጠንካራ መዋቅራዊ መደላድል እየፈጠረ ይገኛል።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ማዕቀፍ የተተገበሩት ፖሊሲዎች የፓርኮቹን አስተዳደር ወደ ግል ዘርፉ በማሸጋገር የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መዋቅር ሙሉ በሙሉ እየቀየሩት ነው።
ይህ ታሪካዊ ሽግግር በተለይም አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ ረገድ አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል።
በማሳያነትም በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ብቻ ከ750 ሚሊዮን ዶላር በላይ የመነሻ ካፒታል ያስመዘገቡ 166 አዳዲስ ባለሀብቶች ወደ ዘርፉ ተቀላቅለዋል።
ይበልጥ ተስፋ የሚሰጠው ደግሞ ከእነዚህ ውስጥ 84 በመቶ የሚሆኑት የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች መሆናቸው ነው። ይህ አዲሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም የፈጠረውን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት እና አቅም በግልጽ የሚያሳይ ነው።
ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖቹ በሥራ ዕድል ፈጠራ በኩል የዜጎችን በተለይም የወጣት ሴቶችን ሕይወት በተጨባጭ እየቀየሩ ነው። በመላው ሀገራችን በሚገኙ ፓርኮች ውስጥ ከ100 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀጥተኛና ቋሚ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።
በኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ትክክለኛ የኢንዱስትሪ ግብዓት ትስስር በመፍጠር የአርሶ አደሩን ምርት ከፋብሪካዎች ጋር በቀጥታ ማስተሳሰር ተችሏል። እስካሁን ባለው ሂደት ከ100 ሺህ በላይ አምራቾች እና አርሶ አደሮች ከትላልቅ ገዢዎች ጋር በቀጥታ ተገናኝተዋል።
በዚህም በአርሶ አደሮች እና በፋብሪካዎች መካከል ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የንግድ ግብይት መፈጸሙ፣ የኢንዱስትሪው ትስስር ምን ያህል ወደ ታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል እንደወረደ ያመላክታል።
የውጭ ምንዛሬን በማመንጨት እና የገቢ ምርቶችን በመተካት በኩል የተመዘገቡት ስኬቶች የኢትዮጵያን የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ።
በ2018 በጀት ዓመት ፓርኮቹ ከወጪ ንግድ 266.9 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት በታሪካቸው ከፍተኛ የተባለ ውጤት አስመዝግበዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ከ26.7 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን የገቢ ምርቶች በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ታድገዋል።
ይህ በፓርኮች የታየው ስኬት በሀገር አቀፍ ደረጃ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስተባባሪነት እየተተገበረ ካለው "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ጋር ተጣምሮ ታላቅ ሀገራዊ ውጤት አምጥቷል።
ንቅናቄው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 13 በመቶ ያሳደገው ሲሆን፣ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ የገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት አስችሏል።
ለእነዚህ ተጨባጭ ለውጦች እና ስኬቶች በዋናነት በምክንያትነት የሚጠቀሰው በቅርቡ የፀደቀው የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጅ እና መንግሥት ያቀረባቸው ሰፊ ማበረታቻዎች ናቸው።
አዲሱ የሕግ ማዕቀፍ ፓርኮቹን በጨርቃጨርቅ ምርት ላይ ብቻ ከነበረ ጥገኝነት አውጥቶ ግብርናን፣ ሳይንስን እና የሎጂስቲክስ አገልግሎትን እንዲያካትቱ አድርጓል።
ከዚህም በተጨማሪ የጉምሩክ ቀረጥ ነፃ መብቶች፣ የዜሮ ምጣኔ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ለኤክስፖርት አምራቾች የተሰጡ የአምስት ዓመት የግብር እፎይታዎች፣ እንዲሁም የውጭ ሀገር ባንኮች በዞኖቹ ውስጥ በነፃነት እንዲሠሩ መፈቀዱ ዘርፉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ አድርጎታል።
የጥራት፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የሠራተኞች ደህንነት (ISO) ደረጃዎችን ያካተተ የተቀናጀ የአመራር ሥርዓት መዘርጋቱም የኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዕድገት ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ጽኑ መሠረት ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #industrialparks #specialeconomiczones #investinethiopia #ethiopiatamirt
10 days ago
ከችርቻሮ የሱቅ ስራ የተነሳው ጊፍት ትሬዲንግ 35ኛ አመቱን አከበረ
#ethiopia | በኢትዮጵያ በገቢና ወጪ ንግድ ዘርፍ አንጋፋ ከሆኑ ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ጊፍት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ የተመሰረተበትን 35ኛ ዓመት የምስረታ ኢዮቤልዩ በዓል በዛሬዉ እለት አክብሯል።
በንግድ ማህበረሰቡ፣ በመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና በድርጅቱ አመራሮች በተገኙበት በዚህ መርሃ-ግብር ላይ ኩባንያው ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ከግማሽ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ያቀረበ ሲሆን፣ በቀጣይም ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሸጋገር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል።
ድርጅቱ ይፋ ባደረገው እቅድ መሠረት በአዳማ እና ሞጆ ከተሞች መካከል በሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ፍሪ ዞን ውስጥ 7,527.54 ካሬ ሜትር ቦታ መረከቡን ገልፀዉ ቦታው ከጅቡቲ ኮሪደር እና ከሞጆ ደረቅ ወደብ አቅራቢያ የሚገኝ በመሆኑ፣ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴውን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳልጠው የተገለጸ ሲሆን፤ የአካባቢው የዲዛይን ስራ ተጠናቆ ወደ ግንባታ ምዕራፍ መሸጋገሩ ተመልክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ኩባንያው እሴት በተጨመረባቸው የግብርና ምርቶች ዘርፍ መሰማራት የጀመረ ሲሆን፣ በተለይም በድፍድፍ የአቮካዶ ዘይት ማምረት እና በከባድ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች አስመጪነት ዘርፍ ለመግባት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።
የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን ለማሳደግ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በቤንች ሸኮ ዞን የጥቁር አዝሙድ እርሻ መጀመሩን የጠቆመው ጊፍት ትሬዲንግ፤ በቀጣይ ስድስት ወራት ውስጥ 300 ሄክታርየቡና እርሻ መሬት ተረክቦ ወደ ምርት እንደሚገባ አስታውቋል።
ከ50 ዓመታት በፊት በመርካቶ በታዋቂው የቢዝነስ ሰው በአቶ ገብረኢየሱስ ኢጋታ ሲማ በትንሽ የችርቻሮ ሱቅ የተጀመረው ይህ የንግድ እንቅስቃሴ፣ በ1980ዎቹ መጀመሪያ ወደ ገቢና ወጪ ንግድ በማደግ ለዛሬው ግዙፉ ጊፍት ቢዝነስ ግሩፕ (ጊፍት ሪል እስቴት፣ ጊፍት ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ብረታ ብረት፣ ጊፍት ፕሮፐርቲ እና ጊፍት ቱር ኤንድ ትራቭል) መፈጠር መሰረት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም B-29 የልብስ ሳሙና፣ የሮድ ስቶን የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ የጂንዳል ቆርቆሮዎች፣ የብረትና የኬሚካል ምርቶችን ጨምሮ በርካታ ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ በማስተዋወቅ ረገድ ኩባንያው የነበረው ሚና ከፍተኛ እንደነበር ተገልጿል።
ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2030 በኢትዮጵያ በቡና፣ ቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ እና ቅመማ ቅመም ላኪነት ከግንባርቀደም 5 ኩባንያዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #gifttradingrealstate #construction #technology
#ethiopia | በኢትዮጵያ በገቢና ወጪ ንግድ ዘርፍ አንጋፋ ከሆኑ ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ጊፍት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ የተመሰረተበትን 35ኛ ዓመት የምስረታ ኢዮቤልዩ በዓል በዛሬዉ እለት አክብሯል።
በንግድ ማህበረሰቡ፣ በመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና በድርጅቱ አመራሮች በተገኙበት በዚህ መርሃ-ግብር ላይ ኩባንያው ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ከግማሽ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ያቀረበ ሲሆን፣ በቀጣይም ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሸጋገር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል።
ድርጅቱ ይፋ ባደረገው እቅድ መሠረት በአዳማ እና ሞጆ ከተሞች መካከል በሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ፍሪ ዞን ውስጥ 7,527.54 ካሬ ሜትር ቦታ መረከቡን ገልፀዉ ቦታው ከጅቡቲ ኮሪደር እና ከሞጆ ደረቅ ወደብ አቅራቢያ የሚገኝ በመሆኑ፣ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴውን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳልጠው የተገለጸ ሲሆን፤ የአካባቢው የዲዛይን ስራ ተጠናቆ ወደ ግንባታ ምዕራፍ መሸጋገሩ ተመልክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ኩባንያው እሴት በተጨመረባቸው የግብርና ምርቶች ዘርፍ መሰማራት የጀመረ ሲሆን፣ በተለይም በድፍድፍ የአቮካዶ ዘይት ማምረት እና በከባድ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች አስመጪነት ዘርፍ ለመግባት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።
የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን ለማሳደግ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በቤንች ሸኮ ዞን የጥቁር አዝሙድ እርሻ መጀመሩን የጠቆመው ጊፍት ትሬዲንግ፤ በቀጣይ ስድስት ወራት ውስጥ 300 ሄክታርየቡና እርሻ መሬት ተረክቦ ወደ ምርት እንደሚገባ አስታውቋል።
ከ50 ዓመታት በፊት በመርካቶ በታዋቂው የቢዝነስ ሰው በአቶ ገብረኢየሱስ ኢጋታ ሲማ በትንሽ የችርቻሮ ሱቅ የተጀመረው ይህ የንግድ እንቅስቃሴ፣ በ1980ዎቹ መጀመሪያ ወደ ገቢና ወጪ ንግድ በማደግ ለዛሬው ግዙፉ ጊፍት ቢዝነስ ግሩፕ (ጊፍት ሪል እስቴት፣ ጊፍት ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ብረታ ብረት፣ ጊፍት ፕሮፐርቲ እና ጊፍት ቱር ኤንድ ትራቭል) መፈጠር መሰረት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም B-29 የልብስ ሳሙና፣ የሮድ ስቶን የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ የጂንዳል ቆርቆሮዎች፣ የብረትና የኬሚካል ምርቶችን ጨምሮ በርካታ ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ በማስተዋወቅ ረገድ ኩባንያው የነበረው ሚና ከፍተኛ እንደነበር ተገልጿል።
ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2030 በኢትዮጵያ በቡና፣ ቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ እና ቅመማ ቅመም ላኪነት ከግንባርቀደም 5 ኩባንያዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #gifttradingrealstate #construction #technology
Sponsored by
Surafel
Comments